አጠቃላይ መረጃ ጸሐፊው ኢየሱስ ከዳዊት እና ከአብርሃም ዘር እንደመጣ ለማሳየት ጽሑፉን የጀመረው ከኢየሱስ የዘር ሀረግ ነው። ይህ የዘር ሀረግ ዝርዝር እስክ ዲረስ ይቀጥላል MAT 1:17 የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ መጽሐፍ ይህ የኢየሱስ ትውልድ ዝርዝር ነው። የዳዊት ልጅ፥ የአብርሃም ልጅ በኢየሱስ፥ በዳዊት እና በአብረሃም መካከል ብዙ ትውልዶች አሉ። በዚህ ሥፍራ "ልጅ" ማለት "ዘር' ማለት ነው። "የዳዊት ልጅ የሆነው እርሱ የአብርሃምም ልጅ ነው።" የዳዊት ልጅ አንዳንድ ጊዜ "የዳዊት ልጅ" የሚልው ሀረግ እንደ ስያሜ ሆኖ ያገልግላል ነገር ግን በዚህ ሥፍራ ላይ የኢየሱስን ቅድመ አያቶች ለማሳየት የገባ ቃል ነው። አብርሃም የይሳቅ አባት ነው። ይህንን በተለያዩ መንገዶች መተርጎም ይቻላል። በዬትኛውም መንገድ ተርጉሙት በዘር ሀርግ ዝርዝር ውስጥ ተመሳሳ በሆነ መልኩ መተርጎሙ ጥሩ ነው። ትርጉም፡ "አብርሃም የይሳቅ አባት ሆነ" ወይም "አብርሃም ይሳቅ የሚባል ልጅ ነበረው፨" ፋሬስንና ዛራን . . . ኤስሮምን . . . አራም እነዚህ የሰዎች ስም ። ፋሬስን . . . አባት ነው ኤስሮም . . . ነው።
ሰልሞንም የቦኤዝ አባት ነው "ሰልሞን የቦኤዝ አባት ነው፤ የቦኤዝ እናት ደግሞ ረአብ ናት" ወይም "ሰልሞን እና ረአብ የቦኤዝ ወላጆች ናቸው።" ቦኤዝ የኢዮቤድ አባት ነው፤ የኢዮቤድም እናት ሩት ናቴ" ወይም "ቦኤዝ እና ሩት የኢዮቤድ ወላጆች ናቸው። ዳዊትን የኦርዮ ሚስት ከነበረችው ምስቱ ሰሎሞንን ወልዶ አባቱ ሆን ወይም "ዳዊት እና የኦርዮ ሚስት የነበረችው ምስቱ የሰለሞን ወላጆች ናቸው። የኦርዮ ሚስት የነበረችው ሰለሞን የተወለደው ኦርዩ ከሞተ በኃላ ነው።
አሳ አንዳንድ ጊዜ "አሳፍ" ተብሎ ይተረጎማል። የዖዝያን ትክክለኛ ስሙ ሮብዓም፥ ስለዚህም "አባት" የሚለው ቃል "የዘር ሀረግ" ተብሎ መተርጎም ይችላል። ሰሎሞንም ሮብዓምን ወለደ፤ ሮብዓምም አቢያን ወለደ፤ (UDB).
አሞን አሞን አንዳንድ ጊዜ "አሞፅ" ተብሎ ይተረጎማል። ኢዮስያስ የኢኮንያንን አባት ነው እውነታው ኢዮስያስ የኢኮንያንን አያት ነው። በባቢሎንም ምርኮ ጊዜ "ወደ ባቢሎን በምርኮ ተገደው እንዲሄዱ ሲድረግ" ወይም "ባቢሎናዊያን ቁጥጥር በሆኑ ጊዜና ወደ ባቢሎን እንዲሄዱ ስያስገድዷቸው።" በቋንቋችሁ ማን ወደ ባቢሎን እንደሄደ መግለጽ አስፈላጊ ከሆነ እንዲህ ማለት ትችላላችሁ "እስራኤላዊያን" ወይም "በይሁዳ ይኖሩ የነበሩ እስራኤላዊያን" ባቢሎን በዚህ ሥፍራ ላይ ባቢሎን የሚለው ቃል የሚያመለክተው ባቢሎን የተሰኘችውን ሀገር እንጂ የባቢሎን ከተማን ብቻ አይደለም።
ከባቢሎንም ምርኮ በኋላ MAT 1:11. ላይ ከተጠቀምከው ቃል ጋር ተመሳሳይ ቃልን ተጠቀም። ሰላትያል የዘሩባቤል አባት ነው እውነታው ሰላትያል የዘሩባቤል አያት ነው፨
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጸሐፊው በ MAT 1:1. ላይ የጀመረውን የኢየሱስን የትውልድ ሀርግ ያጠናቅቃል። ኢየሱስን የወለደችው ማሪያም ኤቲ፡ "ኢየሱስን የወለደችው ማሪያም" ( ይመልከቱ) ክርስቶስ የተባለው ይህ እንዲህ ልተረጎም ይችላል፡ ኤቲ፡ "ሰዎች ክርስቶስ ብለው የሚጠሩት።" ( ተመልከቱ) ዐሥራት አራት "14" ( ተመልከቱ) የባቢሎን ምርኮ MAT 1:11. ላይ ከተጠቀምከው ቃል ጋር ተመሳሳይ ቃልን ተጠቀም።
አጠቃላይ መረጃ ይህ ክፍል ጸሐፊው ለኢየሱስ መወለድ ምክንያት የሆኑ ሁኔታዎችን የገለጸበት የታርኩ አዲሱ ጅማሬ ነው። እናቱ ማርያም ለዮሴፍ ታጭታ ነበር "እናቱ ማርያም ዮሴፍን ልታገባ ነበር።" ብዘመኑ ወላጆች ለልጆቻቸው ትዳር አጋር ያዘጋጁ ነበር። ኤቲ፡ "የኢየሱስ እናት የሆነችው ሪያም ወላጆቿ ለዮሴፍ እርሷን ለመዳር ተስማምተዋል።" ( ተመልከት) እናቱ ማርያም ታጭታ ነበር ማርያም ለዮሴፍ ታጭታ በነበረበት ወቅት ኢየሱስ አለመወለዱን በሚያሳይ መንገድ ተርጉሙት። ኤቲ፡ "ኋላ ላይ ኢየሱስን የወለደችው ማሪያም ታጭታ ነበር" ሳይገናኙ "ከመጋባታቸው በፊት።" ይህ ዮሴፍ እና ማሪያም አብረው ከመተኛታቸው በፊት" የሚለውን የሚያመልክት ይሆናል። ኤቲ፡ "አብረው ከመተኛታቸው በፊት"። ( ተመልከት) አርግዛ ተገኘች ይህ እንዲህ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ልጅ ልትወልድ እንደሆነ አወቁ” ወይም “አረገዘች፡፡” ( ተመልከት) በመንፈስ ቅዱስ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ማሪያም ከሰው ጋር ሳትተኛ ማርገዝ እንድትችል አደረጋት፡፡ ባሏ ዮሴፍ ዮሴፍ ማሪያምን ገና አላገባትም ነበር ይሁን እንጂ አንድ ወንድ እና አንድ ሴት ትዳር ለመጋባት ቃል ከተገባቡ ምንም እንኳ አብረው መኖር ባይጀምሩም አይሁዶች ባል እና ምስት አድርገው ይቆጥሯቸው ነበር፡፡ ከእርሷ ጋር የተነበረውን እጮኝነት ለማቆም “ለመጋባት የነበራቸውን እቅድ ለመሰረዝ”
እንዳሰበው “ዳዊት እንዳሰበው” በሕልም ተገለጠለት “ለዮሴፍ በሕልም ተገልጦለት” የዳዊት ልጅ በዚህ ሥፍራ “ልጅ” ማለት “የልጅ ልጅ” ማለት ነው፡፡ በማሕጸኗ ውስጥ የተሸከመችው ልጅ የተጸነሰው በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ነው ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “መንፈስ ቅዱስ ማሪያም እንዲትጸንስ አደረገ፡፡” ( ተመልከት) ወንድ ልጅ ትወልዳለች እግዚአብሔር መልአክን ስላዘዘ መልአኩ የተወለደው ወንድ ልጅ እንደሆነ ያውቅ ነበር፡፡ እንዲህ ብለሽ ትጠሪዋለሽ ይህ ትዕዛዝ ነው፡፡ ኤቲ፡ “እንዲህ ብለሽ ጥሪው” ወይም “እንዲህ የሚል ስም ልትሰጪው ይገባል፡፡ ያድናልና በዚህ ሥፍራ ላይ ተርጓሚዎች እንዲህ የሚል የግሪጌ ማስታወሻ መጨመር ይችላሉ፡ “ኢየሱስ የሚለው ስም ጌታ ያድናል ማለት ነው፡፡ ሕዝቡን ይህ የሚያመለክተው አይሁዳዊያንን ነው
አጠቃላይ መረጃ ጸሐፊው የኢየሱስ አወላለድ በቅዱሳት መጽሐፍት አስቀድሞ በተነገረው መሠረት መሆኑን ለማሳየት ከነብይ ኢሳያስ መጽሐፍ ጠቅሶዋል፡፡ ( ተመልከት) ይህ ሁሉ ሆነ መልአኩ መናገር አቁሟል፡፡ አሁን ማቴዎስ መልአኩ የተናገረው ነገር ምን ያኽል አስፈላጊ እንደሆነ እያብራራ ነው፡፡ ጌታ በመላዕክቱ አማካኝነት የተናገረው ነገር ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡ ኤቲ፡ “ጌታ ለነብይ ኢሳያስ ከብዙ ዘመናት በፊት የተናገረው እንዲጽፍ የነገረው ነገር፡፡” ( ተመልከት) እነሆ . . . አማኑኤል በዚህ ሥፍራ ላይ ማቴዎስ ከነብዩ ኢሳያስ መጽሐፍ ጠቅሷል፡፡ እነሆ ይህ ቃል ሰዎች ከዚህ በኋላ ለሚነገረው ነገር አጽኖት እንዲሰጡ የሚጨመር ቃል ነው፡ ኤቲ፡ “ተመልከቱ” ወይም “አድምጡ” ወይም “አሁን ለምነግራችሁ ነገር ትኩረት ስጡ”:: አማኑኤል ይህ የወንድ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው” ማለት ነው ይህ በኢሳያስ መጽሐፍ ውስጥ የለም፡፡ ማቴዎስ የስሙን ትርጉም እያብራራ ነው፡፡ ይህን ለብቻው በአንድ ዐረፍተ ነገር መተርጎም ትችላላችሁ፡፡ ኤቲ፡ “የዚህ ስም ትርጉም “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው” ማለት ነው፡፡
አያያዥ ዐረፍተ ነገር ጸሐፊው የኢየሱስ አወላለድን ምን ይመስል እንደነበር የሰጠውን ገለጻ አጠናቀቀ፡፡ የጌታ መልአክ ባዘዘው መሠረት መልአኩ ዮሴፍን ማሪያምን ምስቱ አድርጎ እንዲወስዳት እና የልጁንም ስም ኢየሱስ እንዲለው አዘዘው፡፡ እርሱም እርሷን ምስቱ አድርጎ ወሰዳት “አገባት” ለልጁ ዮሴፍ እውነተኛ አባቱ አለመሆኑን ግልጽ መሆኑን እርግጠኞች ሁኑ፡፡ ኤቲ፡ “ወንድ ልጅ” ወይም “ለልጇ” እና ኢየሱስ ብሎ ስም ጠራው “ዮሴፍ ሕጻኑን ኢየሱስ የሚል ስም አወጣለት”
መጀመሪያ ላይ የተዘረዘሩት ሁለቱ አባቶች ዳዊት እና አብርሃም ናቸው። [1:1]
ማርያም የተባለችው የዮሴፍ ሚስት ተጽፏል፣ ምክንያቱም ኢየሱስ በእርሷ በኩል ተወልዷል። [1:16]
ማርያም ከዮሴፍ ጋር ከመጋባቷ በፊት በመንፈስ ቅዱስ ፀነሰች። [1:18]
ዮሴፍ ጻድቅ ሰው ነበር። [1:19]
ዮሴፍ ከማርያም ጋር ያለውን እጮኝነት በድብቅ ለማቆም ወሰነ። [1:19]
አንድ መልአክ በህልሙ ተገልጦ ሕጻኑ በመንፈስ ቅዱስ ስለተፀነሰ ማርያምን ሚስቱ አድርጎ እንዲወስድ ነገረው [1:20]
ዮሴፍ ህፃኑን ኢየሱስን እንዲለው የተነገረው ህዝቡን ከኃጢአታቸው ስለሚያድናቸው ነው። [1:21]
የብሉይ ኪዳን ትንቢት “ድንግል ወንድ ልጅ እንደምትወልድ እና ስሙንም አማኑኤል እንደሚሉት፣ የስሙም ትርጉም “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው” ማለት እንደሆነ ነው። [1:23]
ኢየሱስን እስክትወልድ ድረስ ከማርያም ጋር እንዳይተኛ መጠንቀቅ ነበረበት። [1:25]
አጠቃላይ መረጃ የታሪኩ አዲስ ክፍል የሚጀምረው በዚህ ሥፍራ ላይ ነው፡፡ ከዚያም እስከ ምዕራፉ መጨረሻ ድረስ ይሄዳል፡፡ ጸሐፊው ሄሮዶስ አዲሱን የአይሁድ ንጉሥ ለመግደል ስላደረገው ሙከራ ይነግረናል፡፡ ቤተልሔም ይሁዳ “በይሁዳ ግዛት ውስጥ የሚትገኝ የቤተልሔም ከተማ” ሄሮዶስ ንጉሥ በነበረበት ዘመን “በዚያ ሄሮዶስ ንጉሥ ሆኖ ሳለ” ሄሮዶስ ሄሮዶስ የሚለው ቃል የሚያመለክተው ታላቁን ሄሮዶስን ነው፡፡ የተማሩ ሰዎች “ክዋክብትን ያጠኑ ሰዎች” (UDB) ከምስራቅ የመጡ “ከይሁዳ በስተምስራቅ በኩል ከሚገኝ ሀገር የመጡ” የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ዬት አለ? ሰዎቹ ከክዋክብት ጥናታቸው የአይሁድ ንጉሥ ለመሆን የተወለደ ልጅ እንዳለ አውቀዋል፡፡ በዬት ሥፍራ እንዳለ ለማወቅ ፈልገዋል፡፡ ኤቲ፡ “የአይሁድ ንጉሥ ለመሆን አንድ ልጅ ተወልዷል፡፡ ዬት ነው ያለው?” የእርሱ ኮከብ ኮከቧ ትክክለኛ ባለቤት ልጁ ነው እያሉ አይደለም፡፡ ኤቲ፡ “ስለ እርሱ የሚትናገረው ኮከብ” ወይም “ከእርሱ መወለድ ጋር የተያያዘችው ኮከብ” በምስራቅ “በምስራቅ በወጣች ጊዜ” ወይም “በሀገራችን ሳለን” ማምለክ አማራጭ ትርጉሞች 1) ልጁ መለኮት እንደሆነ ተገንዝበወ ለማምለክ ፈልገዋል ወይምመ 2) እንደ አንድ ንጉሥ ልያከብሩት ፈልገዋል፡፡ ቋንቀዋችሁ ሁለቱንም ትርጉሞች መያዝ የሚችል ቃል ካለው በዚህ ሥፍራ ላይ ይህንን ቃል መጠቀምንን ከግንዛቤ ውስጥ አስገቡ፡፡ ተጨነቀ “ፈራ”፡፡ ይህ ልጅ ንግሥናዬን ይቀማኛል ብሎ በመፍራት ተጨነቀ፡፡ ኢየሩሳሌም በሙሉ በዚህ ሥፍራ ላይ “ኢየሩሳሌም” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሰዎችን ነው፡፡ እንዲሁም “ሁሉም” ማለት “ብዙ” ማለት ነው፡፡ ማቴዎስ በዚህ ሥፍራ ላይ ብዙ ሰዎች በዚህ ጉዳይ መጨነቃቸውን ለማመልከት ግነት ተጠቅሟል፡፡ ኤቲ፡ “በኢየሩሳሌም ያሉ ብዙ ሰዎች፡፡” (UDB) ( and ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ በቁጥር 6 ላይ ካህናት አለቆች እና ጸሐፊት ክርስቶስ በቤተልሔም ከተማ እንደሚወል ከሚልክያስ መጽሐፍ በመጥቀስ አሳይተዋል፡፡ በቤተልሔም ይሁዳ “በይሁዳ ግዛት የሚትገኘው ቤተልሔም ውስጥ” ይህ በነብያት የተነገረው ነገር ነው ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡ ኤቲ፡ “ይህ ነቢያት ከብዙ ዘመናት በፊት የጻፉት ነገር ነው፡፡” (፡ ተመልከት) እና አንች፣ ቤተልሔም . . . ኢስራኤል ከሚልክያስ መጽሐፍ ላይ እየጠቀሱ ነው፡፡ አንች፣ ቤተልሔም . . . ከይሁዳ መሪዎች መካከል መጨረሻ አይደለሽም ሚልክያስ በቤተልሔም ይኖሩ ለነበሩ ሰዎች ከእርሱ ጋር እንደሆኑ አድርጎ ይነግራቸው ነበር ነገር ግን እነርሱ ጋር ከእርሱ ጋር አልነበሩም፡፡ በተጨማሪም “የመጨረሻ አልነበሩም” ይህ አዎንታዊ በሆነ ሀረግ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እናንተ የቤተልሔም ሰዎች . . . ከተማችሁ በይሁዳ ግዛት ውስጥ ከሚገኙ ከተሞች መካል ትልቁ ነው፡፡” ( እና ተመልከቱ) ሕዝቤን ኢስራኤል የሚጠብቅ ማን ነው ሚልክያስ እነዚህን ገዥዎችን እንደ እርኛ አድርጎ ይናገራቸዋል፡፡ ይህ ማለት ሕዝቡን የሚመሩ እና የሚንከባከቡ፡፡ ኤቲ፡ “እረኛ በጎቹን እንደሚመራ ሁሉ ሕዝቤን የሚመራ ማን ነው” ( ተመልከት)
ሄሮዶስ በሚስጥር የተማሩ ሰዎችን ጠራቸው ይህ ማለት ሄሮዶስ የተማሩ ሰዎችን ሌሎች ሰዎች ሳያውቁ በድብቅ አስጠርቶ አናገራቸው ማለት ነው፡፡ ኮከቡ የታየው በትክክል መቼ እንደሆነ ጠያቃቸው ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ከዚያም እንዲህ ሲል ጠየቃቸው፣ “ኮከቡ በትክክል የታየው መቼ ነበር?” ( ተመልከት) ኮከቡ የታየው መቼ ነበር ይህ የተማሩት ሰዎች ከኮቡን መቼ እንደተመለከቱት በተዘዋዋር መንገድ እንደነገሩት ያሳያል፡፡ የተማሩትም ሰዎች ለሄሮዶስ ኮከቡን መቼ እንደተመለከቱ ነገሩት፡፡ ( ተመልከት) ጨቅላው ሕጻን ይህ ኢየሱስ የሚያመለክት ነው፡፡ ቃል አምጡልኝ ኤቲ፡ “አሳውቁኝ” ወይም “ንገሩኝ”( ተመልከት) እንዳመልከው ይህንን በ MAT 2:2 ላይ በተረጎምከው መሠረት ተርጉመው፡፡
ከእነርሱ በኋላ “ከተማሩተ ሰዎች በኋላ” በምስራቅ ተመለከቱ “በምስራቅ በኩል ስወጣ አዩት” ወይም “በሀገራቸው አዩት” ከፊት ፊታቸው ይሄድ ነበር “ይመራቸው ነበር” ወይም “መንገድ ያሳያቸው ነበር” ቀጥ ብሎ ቆመ “ቆመ” ጨቅላው ሕጻን ያለበት “ጨቅላው ሕጻን ያለበት ሥፍራ ስደረስ”
አያያዥ ዐረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ላይ የታሪኩ ፍሰት ወደ ማሪያም፣ ዮሴፍ እና ትንሹ ኢየሱስ ወደ ሚኖሩበት ቦታ ተለውጧል፡፡ ሄዱ “የተማሩት ሰዎች ሄዱ” አምልኮ ይህንን በ MAT 1:2 ላይ በተረጎምከው መሠረት ተርጉመው፡፡ ንብረታቸው በዚህ ሥፍራ ላይ “ንብረታቸው” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ንብረታቸውን ብዙ ጊዜ የሚይዙበት ሳጥን ወይም ሻንጣን ነው፡፡ ኤቲ፡ “ንብረታቸውን የሚይዙበት ሻንጣ፡፡” ." ( ተመልከት) እግዚአብሔር አስጠነቀቃቸው “ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር አስጠነቀቃቸው፡፡ ሄሮዶስ ልጁን ሊገድለው እንደሚፈልግ እግዚአብሔር ያውቃል፡፡ ወደ ሄሮዶስ እንዳይመለሱ ይህ በትምህረተ ጥቅስ ውስጥ ተደርጎ መተርጎም ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እንዲህ በማለት “ወደ ንጉሥ ሄሮዶስ ተመልሳችሁ እንዳትሄዱ፡፡” ( ተመልከቱ)
አጠቃላይ መረጃ በቁጥር 15 ላይ ጸሐፊው ክርስቶስ በግብጽ ምድር እንደሚቆይ ከነብዩ ሆሴን ይጠቅሳል፡፡ ሄዱ “የተማሩት ሰዎች ሄዱ” ለዮሴፍ በሕልም ተገለጠለት “ዮሴፍ ሕልም እያለመ ሳለ ወደ እርሱ መጣ” ተነስ፣ ያዝ . . . ሽሽ . . . ቆይ . . . አንተ እግዚአብሔር ለዮሴፍ ተናገረው፡፡ ስለዚህ ሁሉም በነጠላ ቁጥር ሊሆኑ ይገባቸዋል፡፡ . ( ተመልከት) እስክነግርህ ድረስ የዚህ ዓረፍተ ነገር ሙሉ ትርጉም በግልጽ መቀመጥ ይኖርበታል፡፡ ኤቲ፡ “መመለስህ ሰላም እንደሆነ እኔ እስክነገር ድረስ” ( ተመልከት) ቆየ ይህ ዮሴፍ፣ ማሪያም እና ኢየሱስ በግብጽ ምድር ውስጥ መቆየታቸውን ያሳያል፡፡፡፡ ኤቲ፡ “በዚያ ቆዩ” ( ተመልከት) ሄሮዶስ እስኪሞት ድረስ ሄሮዶስ MAT 2:19. ድረስ አልመተም፡፡ ይህ ዓረፍተ ነገር በግብጽ ምድር ውስጥ ለምን ያኽል ጊዜ እንደቆዩ ያሳያል እንዲሁም በእነዚህ ጊዜያት ሄሮዶስ እንደሞተ አይናገረም፡፡ ልጄን ከግብጽ ምድር ጠራሁት “ልሄን ከግብጽ ጠራት” ልጄ በሆሴ ውስጥ ይህ እስራኤላዊያንን የሚያመለክት ቃል ነው፡፡ ማቴዎስ ይህ እውነተኛ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ለመናገር ይህንን ክፍል ጠቅሶታል፡፡ ይህንን ብቸኛ ልጅ ወይም የመጀመሪያ ልጅን በሚያሳይ ቃል ተርጉሙት፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ላይ የታርኩ ፍሰት ወደ ሄሮዶስ ይመለሳልና የተማሩት ሰዎች እንዳታለሉት ሄሮዶስ ባወቀ ጊዜ ያደረገውን ይነግረናል፡፡ አጠቃላይ መረጃ ይህ ሁኔታ የተከሰተው ጸሐፊው MAT 2:15. ላይ የጠቀሰው እና ሄሮዶስ ከመሞቱ በፊት ነው፡፡ ( ተመልከት) የተማሩት ሰዎች ቀለዱበት ይህ እንዲህ ባለ መልኩ ሊገለጽ ይችላል፡ ኤቲ፡ “የተማሩት ሰዎች ሸውደውት ሄደው አዋረዱት”፡፡ ( ተመልከት) ሰዎችን ልኮ ሁሉንም ልጆች አስገደላቸው ሄሮዶስ ልጆቹን እርሱ ራሱ አልገደላቸውም፡፡ ኤቲ፡ “ሁሉንም ወንድ ልጆችን ይገድሉ ዘንድ ግን ትዕዛዝ ሰጣቸው” ወይም “ሁሉንም ወንድ ሕጻናትን ይገድሉ ዘንድ ወታደሮቹን ላካቸወ፡፡” ( ተመልከት) ሁለት እና ከሁለት ዓመት በታች የሆኑትን “2 ዓመት እና ከዚያ በታች ያሉትን” (UDB) ( ተመልከት) እንደግዜው “በጊዜው መሠረት”
አጠቃላይ መረጃ በይሁዳ ግዛት ውስጥ የነበሩት ወንድ ልጆች ሁሉ መገደላቸው በቅዱሳት መጽሐፍት በተነገረው መሠረት መሆኑን ጸሐፊው ነብዩ ኤርሚያስን በመጥቀስ ጽፏል፡፡ ይህም ተፈጸመ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ይህ ተፈጸመ” ወይም “የሄሮዶስ ተግባር ተፈጸመ፡፡” ( ተመልከት) የተፈጸመው ነገር በነብይ ኤርሚያስ አስቀድሞ ተነግሮ ነበር ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ገታ በነብይ ኤርሚያስ አማካኝነት ከብዙ ዘመናት በፊት እንደተናገረው፡፡” ( ተመልከት) ድምፅ ተሰማ . . . ከእንግዲህ የሉም ማቴዎስ ነብዩን ኤርሚያስን እየጠቀሰ ነው ድምፅ ተሰማ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡ ኤቲ፡ “ሰዎች ድምፅ ሰሙ” ወይም “ከፍተኛ ድምፅ ነበር፡፡ ( ተመልከት) ራሔል ስለልጆቿ አለቀሰች ራሔል ይህ ነገር ከመሆኑ ብዙ ዓመታት በፊት ነው የኖረችው፡፡ ይህ ትንቢት የሚያሳያው ከብዙ ዓመታት በፊት የሞተችው ራሔል ስለ ልጆቿ ማልቀሷን ነው፡፡ መጽናናትንም እንቢ አለች ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ማንም ሊያጽናናት አልቻለም፡፡” ( ተመልከት) የሉምና “ልጆቿ ጠፍተዋል እንዲሁም እንደገና ፈጽመው አይመለሱም፡፡ በዚህ ሥፍራ “የሉም” የሚለው ቃል ለዘብ ባለ ቃል መሞታቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ ኤቲ፡ “ስለሞቱ”፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ የታርኩ ፍሰት ዮሴፍ፣ ማሪያም እና ጨቅላው ኢየሱስ ወደሚኖሩበት ወደ ግብጽ ተቀይሯል፡፡ እነሆ ይህ በትልቁ ታርክ ውስጥ አንድ ሌላ ሁኔታ የመጀመሩ ምልክት ነው፡፡ ከዚህ ቀደም ካሉት ሁኔታዎች ውስጥ ከነበሩት ሰዎች ተጨማሪ ሰዎችን ሊጨምር ይችላል፡፡ በቋንቋችሁ ይህንን የሚትገልጹበት መንገድ ሊኖራችሁ ይችላል፡፡ የሕጻኑን ሕይወት የሚፈልጉት ሰዎች ኤቲ፡ “ሕጻኑን ለመግደል የሚፈልጉት ሰዎች”፡፡ ( ተመልከት) የሚፈልጉት ሰዎች ይህ ንጉሥ ሄሮዶስን እና አማካሪዎቹን የሚያመለክት ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ በ MAT 2:1 የተጀመረው ታርክ ሄሮዶስ የአይሁድ አዲሱን ንጉሥ ለመግደል ያደረገው ሙከራ የመጨረሻው ክፍል ነው፡፡ ይህንን በሰማ ጊዜ “ዮሴፍ ይህንን ስሰማ ግን” አርኬላዎስ ይህ የሄሮዶስ ልጅ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) ፈራ “ዮሴፍ ፈራ” በነቢያቱ የተነገረው ነገር ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ከብዙ ዘመናት በፊት ጊዜ በነቢያቱ አማካኝት እንደተናገረው፡፡” ( ተመልከት) ናዝራዊ ተብሎ ይጠራል በዚህ ሥፍራ “እርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው፡፡ ከእርሱ በፊት ይኖሩ የነሩ ነቢያት ስለ እርሱ ስባገሩ መስሑ ወይም ክርስቶስ ብለው ይጠሩታል፡፡ ኤቲ፡ “ሰዎች ክርስቶስ ናዝራዊ ነው ይላሉ፡፡” ( ተመልከት)
ኢየሱስ የተወለደው በይሁዳ ቤተልሔም ነው። [2:1]
ከምሥራቅ የመጡት ጠቢባን ለኢየሱስ “የአይሁድ ንጉሥ” የሚል መጠሪያ ሰጡ። [2:2]
ጠቢባኑ በምሥራቅ የአይሁድን ንጉሥ ኮከብ አይተው ነበር። [2:2]
ንጉሡ ሄሮድስ ወሬውን ከጠቢባኑ ሲሰማ ተጨነቀ። [2:3]
ክርስቶስ በቤተ ልሔም እንደሚወለድ የተነገረውን ትንቢት ያውቁ ነበር። [2:5]
ክርስቶስ በቤተ ልሔም እንደሚወለድ የተነገረውን ትንቢት ያውቁ ነበር። [2:6]
በምሥራቅ የነበረው ኮከብ ኢየሱስ ወደ ነበረበት ቦታ እስከሚቆም ድረስ ከፊታቸው ይሄድ ነበር። [2:9]
ጠቢባን ሲመጡ ኢየሱስ ትንሽ ልጅ ነበር። [2:11]
ጠቢባን ለኢየሱስ ወርቅ፣ ዕጣንና ከርቤ ሰጡ። [2:11]
ተመልሰው ወደ ሄሮድስ እንዳይሄዱ እግዚአብሔር በሕልም ስላስጠነቀቃቸው ጠቢባኑ በሌላ መንገድ ተመለሱ። [2:12]
ሔሮድስ ኢየሱስን ለመግደል እየሞከረ ስለነበር፣ ዮሴፍ ኢየሱስን እና ማርያምን ይዞ ወደ ግብጽ እንዲሸሽ ተነገረው። [2:13]
ኢየሱስ ኋላ ላይ ከግብጽ ሲመለስ "ልጄን ከግብጽ ጠራሁት" የሚለው ትንቢት ፍጻሜውን አገኘ። [2:15]
ሄሮድስ ሁለት ዓመት ወይም ከዚያ በታች የነበሩ በቤተልሔም የሚገኙ ወንድ ልጆችን በሙሉ አስገደላቸው። [2:16]
ዮሴፍ ወደ እስራኤል ምድር እንዲመለስ በሕልም ታዝዞ ነበር። [2:19]
ዮሴፍ ወደ እስራኤል ምድር እንዲመለስ በሕልም ታዝዞ ነበር። [2:20]
ዮሴፍ በገሊላ ናዝሬት ከማርያምና ከኢየሱስ ጋር ለመኖር ሠፈረ። [2:22]
ዮሴፍ በገሊላ ናዝሬት ከማርያምና ከኢየሱስ ጋር ለመኖር ሠፈረ። [2:23]
ክርስቶስ ናዝራዊ ይባላል ተብሎ የተነገረው ትንቢት ተፈጸመ። [2:23]
አጠቃላይ መረጃ፡ ይህ ጸሐፊው የመጥመቁ ዮሐንስን ታሪክ የተነናገረበት አዲስ የታሪኩ አካል መጀመሪያ ነው፡፡ በቁ. 3 ላይ ጸሐፊው የኢየሱስ አገልግሎት መንገድን ያዘጋጅ ዘንድ መጥመቁ ዮሐንስ በእግዚብሔር የተመረጠ መሆኑን ከነብዩ ኢሳያስ መጽሐፍ ጠቅሶ ጽፏል፡፡ በእነዚህ ቀናት ይህ ዮሴፍ እና የእርሱ ቤተሰብ ከግብጽ ምድር ወደ ናዝሬት ከተመሰሉ ብዙ ዓመታት በኋላ የሆነ ነው፡፡ ይህ ምናልባትም ኢየሱስ አገልግሎቱን ለመጀመር በተቃረበበት ጊዜ የተፈጸመ ነገር ይሆናል፡፡ ኤቲ፡ “ከዚያ በኋላ” ወይም “ከጥቂት ዓመታት በኋላ” ንሰሓ ግቡ ይህ በቅርጹ ብዙ ቁጥር ነው፡፡ ዮሐንስ ይህንን ለሕዝቡ እየተናገረ ነው፡፡ ( ተመልከት) የእግዚአብሔር መንግስት ቀርባለች “የእግዚአብሔር መንግስት ቀርባለች” የሚለው ሀረግ እግዚአብሔር ንጉሥ ሆነ መግዛቱን ያሳያል፡፡ ይህ ሀረግ በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ ብቻ ይገኛል፡፡ ከተቻለ በትርጉምህ ውስጥ “ሰማይ” የሚል ቃልን ተጠቀም፡፡ ኤቲ፡ “በሰማይ የሚኖር አባታችን ራሱን እንደ ንጉሥ አድርጎ በቅርቡ ያሳያል፡፡” ( ተመልከት) በነብዩ ኢሳያስ አስቀድሞ ስለ እርሱ እንዲህ ተብሎ የተነገረው ይህ ስለሆነ ነው ይህ እንዲህ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡፡ “ነብዩ ኢሳያስ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡” ( ተመልከት) የአንድ ሰው ድምፅ በዚህ ሥፍራ ላይ “ድምፅ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሙሉ ሰውን ነው፡፡ ኤቲ፡ “አንድ ሰው አለ፡፡” ( ተመልከት) የጌታን መንገድ አዘጋጁ፣ መንገዱንም አቅኑ “የጌታን መንገድ አዘጋጁ፣ መንገዱንም አቅኑ”፡፡ ይህ በዮሐንስ ሰዎችን ለኢየሱስ መምጣት ሰዎችን በንሰሓ የሚያዘጋጅ ምሳሌያዊ መልዕክት ነው፡፡ ( ተመልከት)
አሁን . . . የበረሃ ማር “አሁን” የሚለው ቃል በታሪኩ ፍሰት ውስጥ በዚህ ሥፍራ ለአንባቢው ምልክት እንዲሰጥ ተብሎ ጥቅም ላይ የዋለ ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ማቴዎስ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ የኋላ ታሪክ መረጃን ይሰጣል፡፡ ( ተመልከት) የግመል ጠጉር ይለብስ ነበር እንዲሁም ጠፍርንም ይታጠቅ ነበር ይህ የዮሐንስ አለባበስ ከእርሱ በፊት ይኖሩ እንደነበሩ ነብያት በተለይም እንደ ለነብዩ ኤልሳ ትንብታዊ መልዕክት ነበረው፡፡ ( እና ተመልከት) ኢየሩሳሌም፣ ይሁዳ ሁሉ እና በአከባቢው ያሉ ሁሉ ይህ በዚህ አከባቢ ይኖሩ የነበሩ ሰዎችን የሚያመለክት ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ “ሁሉም” የሚለው ቃ “ብዙ” ማለት ነው፡፡ ማቴወዎስ ወደ መጥመቁ ዮሐንስ የመጡት ብዙ ሰዎች መሆናቸውን አጽኖት ይሰጠቃል፡፡ ( እና ተመልከት) በእርሱ ተጠመቁ ይህ እንዲህ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ዮሐንስ አጠመቃቸው፡፡” ( ተመልከቱ) እነርሱ ይህ ማለት ከኢየሩሳሌም፣ ከይዳ እና ከዮርዳኖስ ዙሪያ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች መምጣታቸውን ያመለክታል፡፡
አጠቃላይ መረጃ መጥመቁ ዮሐንስ ፈርሳዊያንን እና ሳዱቃዊያንን ይገስጻቸው ጀመረ፡፡ እናንተ የመርዛማ እባብ ልጆች ይህ ምሳሌያዊ አነጋገር ነው፡፡ መርዛማ እባቦች አደገኛ ናቸው እንደሁም ክፋትን ይወክላሉ፡፡ ኤቲ፡ “እናንተ መርዛማ እባቦች!” ወይም “ልክ እንደ መርዝማ እባቦች ክፉዎች ናችሁ፡፡” ( ተመልከት ከሚመጣው ቁጣ እንድታመልጡ ማን አስጠነቀቃችሁ ዮሐንስ ፈርሳዊያንን እና ሳዱቃዊያንን ለማስጠንቀቅ ምክንያቱም እግዚአብሔር እንዳይቀጣቸው ዮሐንስ ያጠምቃቸው ዘንድ ይጠይቁት ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ኃጢአት ማድረጋቸውን ማቆም አይፈልጉም ነበር፡፡ ኤቲ፡ “በዚህ ዓይነት መንገድ ከእግዚአብሔር ፍርድ ማምለጥ አይቻልም፡፡” ወይም “እኔ ስላጠመኳችሁ ከእግዚአብሔር ፍርድ የሚታመልጡ አይመስላችሁ፡፡” ( ተመልከት) ከሚመጣው ቁጣ እንድታመልጡ “ቁጣ” የሚለው ቃል በዚህ ሥፍራ ጥቅም ላይ የዋለው የእግዚአብሔርን ቁጣ ለማመለከት ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ ይህ ከእግዚአብሔር ቅጣት ቀድሞ የሚመጣ ስለሆነ ነው፡፡ ኤቲ፡ “ከሚመጣው ቅጣት ለማምለጥ” ወይም “ከእግዚአብሔር ቅጣት ለማምለጥ፡፡” ( ተመልከት) የንሰሓን ፍሬ አፍሩ “አፍሩ” የሚለው ቃል ምሳሌያዊ አነጋገር ሲሆን የሰውዬውን ተግበባራት ያሳያል፡፡ ኤቲ፡ “ተግባራችሁ በእውነት ንሰሓ እንደገባችሁ ያሳይ፡፡” ( ተመልከት) አባታችን አብረሃም አለልን “አብረሃም አባታችን ነው” ወይም “እኛ የአብረሃም ዘሮች ነን፡፡” የአይሁድ መሪዎች የአብረሃም ዘሮች በመሆናቸው ምክንያት እግዚአብሔር እንደማይቀጣቸው ያስቡ ነበር፡፡” ( ተመልከት) እኔ ግን እንዲህ እላችኋለሁ ይህ ዮሐንስ ቀጥሎ ስለሚናር ነገር አጽኖት እንድሰጠ ያሳያል፡፡ ከእነዚህ ድንጋዮች እግዚአብሔር ልጆችን ማስነሳት ይችላል “ከእነዚህ ድንጋዮች ሳይቅር እግዚአብሔር ለአብረሃም ለልጆችን አበጅቶ ለአብረሃም መስጠጥ ይችላል፡፡”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር መጥመቁ ዮሐንስ ፈርሳዊያንን እና ሳዱቃዊያንን መገሰጹን ቀጥሏል፡፡ በዛፉ ሥር ላይ መሳሩ ተቀምጦዋል፡፡ መልካምን ፍሬ የማያፈራ ዘፍ ሁሉ ተቆርጦ ወደ እሳት ይጣላል፡፡ ይህ ምሳሌ እግዚአብሔር ኃጢአተኞችን ለመቅጣት ተዘጋጅቷል፡፡ ይህ በዚህ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚብሔር ምሳሩን አንስቷል፡፡ መጥፎ ፍሬ የሚያፈሩ ዛፎችን ለመቁረጥ እና ለማቃጠል ተዘጋጅቷል” ወይም “አንድ ሰው መጥፎ ፍሬ የሚያፈራን ዘፍ ለመቁረጥ እና ለማቃጠል ምሳሩን እንደሚያዘጋጅ ሁሉ እግዚአብሔርም ስለኃጢአታችሁ ሊቀጣችሁ ተዘጋጅቷል፡፡ ( እና ተመልከት) ለንሰሓ “ንሰሓ እንደገባችሁ የሚያሳይ ነገር” ነገር ግን ከእኔ በኋላ የሚመጣው ኢየሱስ ከዮሐንስ በኋላ የሚመጣው ነው፡፡ ከእኔ ይልቅ ኃይለኛ ነው “ከእኔ ይልቅ በጣም ጠቃሚ ነው፡፡” በመንፈስ ቅዱስ እና በእሳት ያጠምቃችኋል ይህ ምሳሌ የዮሐንስን ጥምቀት ለወደፊት ከሚሆነው በእሳት መጠመቅ ጋር ያነጻጽራል፡፡ ይህ ማለት የዮሐንስ ጥምቀት ሰዎች ከኃጢአታቸው መንጻታቸው ውጫዊ ምሳሌ ሆኖ የሚያገለግል ብቻ ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ እና በእሳት መጠመቅ ግን ሰዎችን በእውነት ከኃጢአታቸው ያነጻል፡፡ ከዮሐንስ ጥምቀት ጋር ለማነጻጸር ይረዳ ዘንድ በትርጉማችሁ ውስጥ ከተቻለ “መጠመቅ” የሚለውን ቃል ጥቅም ላይ አውሉት፡፡ ( ተመልከት) ስንዴውን ከገለባው መለየት እንዲችል መንሹ በእጁ ላይ ነው ይህ ምሳሌ ስንዴ ከገለባ እንደሚለይ ሁሉ ክርስቶስ ጻድቅ የሆኑ ሰዎችን ኃጢአተኞች ከሆኑን ይለያል፡፡ ኤቲ፡ “ክርስቶስ በእጁ መንሽን እንደያዘ ሰው ነው፡፡” ( ተመልከት) መንሽ በእጁ ላይ ነው በዚህ ሥፍራ “በእጁ ላይ ነው” የሚለው ሀረግ ሰውየው ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ያሳያል፡፡ ኤቲ፡ “ክርስቶስም መንሹን በእጁ ይዟል ምክንያቱም ዝግጁ ነው፡፡” መንሽ ይህ የስንዴ ነዶን ወደ ሰማይ በመወርወር በንፋስ አማካኝነት ገለባውን ከፍሬው ለመለየት የሚረዳ መሣሪያ ነው፡፡ ክብደት ያለው ፍሬው መደመሬት ስወድቅ የማይፈለገው ገለባው ግን በንፋስ ይወሰዳል፡፡ ከሹካ ጋር ተመሳሳይ ቅርጽ ያለው ሲሆን መንሽ ግን የሚሠራው ከእንጨት ነው፡፡ ( ተመልከት) አውድማ “እህል የሚወቃበት ሜዳ” ወይም “ፍሬው እና ገለባው የሚለይበት ሥፍራ” ምርቱንም ወደ ጎተራው ይከተዋል . . . ገለባውን ግን ወደ ማይጠፋ እሳት ውስጥ ይጨምረዋል፡፡
ይህ እግዚአብሔር እንዴት ጻድቃንን ከኃጢአትን እንደሚለይ የሚያሳይ ምሳሌ ነው፡፡ ገበሬ ስንዴውን ወደ ጎተራው እንደሚያስገባ ሁሉ ጻድቃንም ወደ ሰማይ ይሄዳሉ እንዲሁም እንደ ገለባው ያሉትን ሰዎች እግገዚአብሔር ወደ ማይጠፋ እሳት ውስጥ ይጨምራቸዋል፡፡ ( ተመልከት) ወደማይጠፋ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላለል፡፡ ኤቲ፡ “ነዶ ወደማያልቅ፡፡” ( ማይጠፋ እሳት ውስጥ ይጨምራቸዋል፡፡ ( ተመልከት))
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ጸሐፊው ታርኩ በኋላ ላይ ዮሐንስን ኢየሱስን ወደ አጠመቀበት ይቀይረዋል፡፡ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ
ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ዮሐንስ ያጠምቀው ዘንድ፡፡” ( ተመልከት) አንተ ወደ እኔ ትመጣለህ? እኔ በአንተ እጅ መጠመቅ ያስፈልገኛል፡፡
ኢየሱስ ለጠየቀው ጥያቄ ዮሐንስ በአግራሞት በጥያቄ መልክ ስመልስ እናያለን፡፡ ኤቲ፡ “አንተ ከእኔ ይልቅ አስፈላጊ ነህ፡፡ እኔ አንተን ማጥመቅ የለብኝም፡፡ አንተ እኔ ማጥመቅ አለብህ፡፡” ( ተመልከት) ለእኛ በዚህ ሥፍራ “እኛ” የሚለው ቃል ኢየሱስን እና ዮሐንስን የሚታመለክት ናት፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ የተነገረው ታርክ መጨረሻ እና ኢየሱስን ካጠመቀ በኋላ ምን እንደሆነ የተገለጸበት ክፍል ነው፡፡ ከተጠመቀ በኋላ ይህ በቀጥታ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ዮሐንስ ኢየሱስን ካጠመቀ በኋላ፡፡” ( ተመልከት) እነሆ “እነሆ” የሚለው ከዚህ ቀጥሎ ያለው ማስረጃ አስገራሚ ስለሆነ አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ ሰማያት ለእርሱ ተከፈቱ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ኢየሱስ ሰማያት ተከፍቶ ተመለከተ” ወይም “እግዚአብሔር ሰማያትን ለኢየሱስ ከፈተ”፡፡ ( ተመልከት) በእርግም አምሳሌ ወረደ አማራጭ ትርጉሞች እነዚህ ናቸው 1) መንፈስ በእርግም አምሳሌ መውረዱን የሚያመለክት ቀጥተኛ ትርጉም ወይም 2) እርግም በቀስታ እንደሚትወርድ ሁሉ ልክ እንደዚሁ መንፈስ ቅዱስ በቀስታ በኢየሱስ ላይ መውረዱን የሚያመለክት ምሳሌ ነው፡፡ ( ተመልከት) እንዲህ የሚል ድምፅ ከሰማይ መጣ “ኢየሱስ ድምፅ ከሰማይ ሰማ፡፡” (UDB) ( ተመልከት) ልጅ ይህ የኢየሱስ በጣም አስፈላጉ የማዕረግ ስም ነው፣ የእግዚአብሔር ልጅ፡፡ ( ተመልከት)
ዮሐንስ "መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ" በማለት ሰበከ። [3:2]
ትንቢቱ የሚናገረው መጥምቁ ዮሐንስ የጌታን መንገድ እንደሚያዘጋጅ ይናገራል። [3:3]
ሲጠመቁ፣ ኃጢአታቸውን ተናዘዙ። [3:6]
ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያን ለንስሐ የሚገባውን ፍሬ እንዲያፈሩ መጥምቁ ዮሐንስ ነገራቸው። [3:8]
ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያን አብርሃም አባት እንዳላቸው እንዳያስቡ አስጠንቅቋል። [3:9]
መልካም ፍሬ የማያፈራው ዛፍ ሁሉ ተቆርጦ ወደ እሳት እንደሚጣል ዮሐንስ ተናገረ። [3:10]
ከዮሐንስ በኋላ የሚመጣው በመንፈስ ቅዱስ እና በእሳት ያጠምቃል። [3:11]
ጽድቅን ሁሉ ለመፈጸም ሲባል ዮሐንስ ኢየሱስን ማጥመቊ ትክክል እንደሚሆን ኢየሱስ ተናገረ። [3:15]
ከውኃው ሲወጣ ኢየሱስ የእግዚአብሔር መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድበት አየ። [3:16]
ከሰማይ የተሰማው ድምፅ "በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው" የሚል ነበር። [3:17]
አጠቃላይ መረጃ በዚህ ሥፍራ ላይ ጸሐፊው ኢየሱስ በምድረ በዳ 40 ቀናትን ያሳለፈበትን፣ በሴጣን የተፈተነበትን የታሪኩን አዲስ ክፍል ይጀምራል፡፡ በቁጥር 4 ላይ ኢየሱስ ከዘዳግም መጽሐፍ በተወሰዱ ጥቅሶች አማካኝነት ሴጣንን ስገስጸው እንመለከታለን፡፡ ኢየሱስ በመንፈስ ተመርቶ
ይህ በቀጥታ በዚህ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “መንፈስ ኢየሱስን መራው፡፡” ( ተመልከት) በዳብሎስ ይፈተን ዘንድ ይህ በቀጥታ በዚህ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ዳብሎስ እርሱን መፈተን ይችል ዘንድ፡፡” ( ተመልከት) ዳቢሎስ . . . ፈታኙ እነዚህ ሁለት ቃላት የሚያመለክቱት አንድ ነው፡፡ እነዚህ ሁለቱን ለመተርጎም አንድ ቃል መጠቀም ትችላላችሁ፡፡ ጾመ . . . ተራበ ይህ ስለኢየሱስ የተባለ ነው፡፡ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ እዘዝ የዚህ ሀረግ አማራጭ ትርጓሜዎች 1) ይህ ፈተና ኢየሱስ ለራሱ ጥቅም ተዓምራትን ይሠራ ዘንድ የቀረበ ፈተና ነው፡፡ ኤቲ፡ “አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ስለዚህ ማዘዝ ትችላለህ፡፡” 2) ይህ የሚያመለክተው በኢየሱስ ላይ የቀረበውን ክስ ነው፡፡ ኤቲ፡ “የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህ ትዕዛዝ በመስጠት አረጋግጥ፡፡” ሴጣን ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ እንደሚያውቅ ማሰቡ ይበልጥ ተመራጭ ነው፡፡
የእግዚአብሔር ልጅ ይህ በኢየሱስ እና በእግዚአብሔር መካከሎ ያለውን ግንኙነት የሚገልጽ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) ድንጋዩ ዳቦ እዲሆን እዘዝ ይህንን በቀጥጣ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ለእነዚህ ድንጋዮች እንዲህ ብለህ ተናገር፣ ዳቦ ሁኑ!” ( ተመልከት)
ዳቦ ኤቲ፡ “ምግብ” ( ተመልከት)
እንዲህ ተብሎ ተጽፏል ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ሙሴ ከብዙ ዘመናት በፊት እንዲህ በማለት ጽፏል፡፡” ( ተመልከት)
የሰው ልጅ በዳቦ ብቻ አይኖርም ይህ በቀላሉ በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ ከምግብ በላይ ሌላ በጣም አስፈላጊ ነገር አለ ማለት ነው፡፡
ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ማንኛውም ቃ እንጂ በዚህ ሥፍራ “ቃል” እና “አፍ” የሚሉ ቃላት እግዚአብሔር የተናገራቸውን ነገሮችን ያመለክታሉ፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር የተናገራቸውን ነገሮች በማድመጥ እንጂ፡፡” ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጥር 6 ላይ ሴጣን ከመዝሙረ ዳዊት መጽሐፍ ውስጥ ኢየሱስን ለመፈተን ሲል የሆነ ሀሳብ ስወስድ እናያለን፡፡
አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ራስህን ወደታች ወርውር የዚህ ሀረግ አማራጭ ትርጉሞች 1) 1) ይህ ፈተና ኢየሱስ ለራሱ ጥቅም ተዓምራትን ይሠራ ዘንድ የቀረበ ፈተና ነው፡፡ ኤቲ፡ “አንተ የእግዚአብሔር ልጅ በመሆንህ ራስህን ወደታች መወርወር ትችላለህ፡፡” ወይም 2) ይህ የሚያመለክተው በኢየሱስ ላይ የቀረበውን ክስ ነው፡፡ ኤቲ፡ “አንተ በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ስለመሆንህ ራስህን ወደታች በመወርወር አረጋግጥ፡፡” (UDB) ሴጣን ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ እንደሚያውቅ ማሰቡ ይበልጥ ተመራጭ ነው፡፡
የእግዚአብሔር ልጅ ይህ በኢየሱስ እና በእግዚአብሔር መካከሎ ያለውን ግንኙነት የሚገልጽ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
ራስህን ወደታች ወርውር “ወደታች ራስህን ወርውረህ ውደቅ” ወይም “ወደታች ዝለል”
እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና ይህ በዚህ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “መዝሙረኛው በመመጽሐፉ ውስጥ አንዲህ ብሎ ጽፏልና” ወይም “በቅዱሳት መጽሐፍ ውስጥ እንዲህ ተብሏልና፡፡” ( ተመልከት)
ይጠብቁህ ዘንድ መልአክቱን ስለአንተ ያዛልና “አንተን እንዲጠብቁህ እግዚአብሔር መልአክቱን ስለአንተ ያዛል፡፡” ይህ እንዲህ ተብሎ በትምህረተ ጥቅስ ውስጥ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ለመልአክቱ እንዲህ ይላቸዋል፣ “ጠብቁት፡፡” ( ተመልከት)
ያነሱሃል “መልአክቱ ይይዙሃል”
አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጥር 7 ላይ ኢየሱስ ሴጣንን የገሰጸው ከዘዳግም መጽሐፍ ውስጥ በተወሰደ ጥቅ አማካኝነት ነው፡፡
እንደገና እንዲህ ተብሎ ተጽፏል ኢየሱስ እንዲህ ማለቱ እንደገና ከመጽሐፍ ቅዱስ መጥቀሱን የሚያመለክት ነው፡፡ ኤቲ፡ “እንደገና ሙሴ በቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ የጻፈውን ነገር እነግርሃለሁ፡፡” ( እና ተመልከት)
አትፈታተኑት በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ማንኛውንም ሰው ነው፡፡ ኤቲ፡ “ማንም እርሱን መፈታተን የለበትም” ወይም “ማንኛውም ሰው እርሱን መፈታተን የለበትም፡፡”
እንደገና ዳቢሎስ “በመቀጠልም ዳቢሎስ”
እንዲህ አለው “ዳቢሎስ ኢየሱስን እንዲህ አለው፡፡”
እነዚህን ነገሮች ሁሉ እሰጥሃለሁ፡፡ “እነዚህ ነገሮች ሁሉ እሰጥሃለሁ፡፡” ፈታኙ አንዳንዶቹን ሳይሆን “ሁሉንም ነገሮች” እንደሚሰጠው አጽኖት ሰጥቶዋል፡፡”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ይህ ሴጣን ኢየሱስን እንዴት እንደፈተነው የሚያወሳው ታሪክ የመጨረሻው ክፍል ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጥር 10 ላይ ኢየሱስ ከዘዳግም መጽሐፍ ውስጥ በመውሰድ ሴጣንን ገስጾታል፡፡
እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና ይህ በዚህ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “መዝሙረኛው በመመጽሐፉ ውስጥ አንዲህ ብሎ ጽፏልና” ወይም “በቅዱሳት መጽሐፍ ውስጥ እንዲህ ተብሏልና፡፡” ( ተመልከት)
አንተ አለብህ በዚህ ሥፍራ “አንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ማንኛውንም ሰው ነው፡፡ ( ተመልከት)
እነሆ “እነሆ” የሚለው ቃል ከዚህ በመቀጠል የሚሰጠው መረጃ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን የሚያመለክት ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃዎች፡ ይህ ኢየሱስ በገሊላ አገልግሎቱን የጀመረበትን መንገድ ጸሐፊው የገለጸበት አዲሱ የታሪኩክፍል ጅማሬ ነው፡፡ እነዚህ ጥቅሶች ኢየሱስ እንዴት ወደ ገሊላ እንደመጣ ያብራራሉ፡፡ ( ተመልከት)
አሁን ይህ ቃል በታሪኩ ፍሰት ውስጥ ያለውን ክፍተት ለማሳየት ጥቅም ላይ የዋሉ ናቸው፡፡ ማቴዎስ በዚህ ሥፍራ ላይ የታሪኩን አንዲስ ጅማሬ ክፍል ይናገራል፡፡ ዮሐንስ ተሠረ ይህ በቀጥታ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ንጉሡ ዮሐንስን አሠረው፡፡” ( ተመልከት)
በዛብሎን እና ንፍታሌን አገር እነዚህ ከብዙ ዓመታት በፊት ከሌላ ሀገር የመጡ ሰዎች ቦታወን ከመቆጣጠራቸው በፊት በእነዚህ ሥፍራዎች ይኖሩ የነበሩ ጎሣዎች ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጥር 15 እና 16 ላይ ኢየሱስ በገሊላ የነበረው አገልግሎት ከዚህ በፊት ተነግሮ የነበረ ትንቢት ፍጻሜ መሆኑን ለማሳየት ጸሐፊው ከነብዩ ኢሳያስ መጽሐፍ ይጠቅሳል፡፡
እንዲህም ሆነ ይህ ኢየሱስ ቅፍርናሆም ወደ ተሰኘው መንደር ለመኖር መምጣቱን ያመለክታል፡፡
ከዚህ በፊት እንደተነገረው ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር እንደተናገረው፡፡” ( ተመልከት)
የዛብሎን እና የንፍታሌን አገር . . . የአሕዛብ ገሊላ እነዚህ ሁሉ ስሞች አንድን አከባቢ የሚያመለክቱ ናቸው፡፡ ይህ በአንድ ዓረፍተ ነገር ሊተረጎም ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “በዛብሎን እና ንፍታሌን አገር . . . ብዙ አሕዛብ የሚኖሩበት የገሊላ መንድ፡፡”
በባሕር መንገድ ይህ የገሊላን ባሕርን ያመለክታል፡፡
በጨለማ የተቀመጠ ሕዝብ ታላቅ ብርሃንን አየ በዚህ ሥፍራ “ብርሃን” የሚለው ቃል ግብረገባዊ ጨለማን ወይም ሰዎችን ከእግዚአብሔር የለየውን ኃጢአትን የሚያመለክት ነው፡፡ ይህ አሁን ከእግዚአብሔር ዘንድ ተስፋን ያገኙ ነገር ግን አስቀድሞ ምንም ተስፋ ያልነበራቸውን ሕዝቦች ያሳያል፡፡ ( ተመልከት)
በዚያ አከባቢ የሚኖሩ እና በሞት ጥላ ሥር ላሉ ሕዝቦች ብርሃን ወጣላቸው ይህ ከመጀመሪያው የዓረፍተ ነገሩ ክፍል ጋር ተመሳሳይ ትርጉም አለው፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ “አከባቢ እና በሞት ጥላ ሥር” የሚለው ሀረግ የሚያመለክተው መንፈሳዊ ሞት ወይም ከእግዚአብሔር መለየት ነው፡፡ ( እና ተመልከት)
መንግስተ ሰማያት ቀርባለችና ንሰሓ ግቡ ይህን በ MAT 3:2 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
አጠቃላይ መረጃ ይህ በታሪኩ ውስጥ ኢየሱስ በገሊላ ስለነበረው አገልግሎት አስመልክቶ አዲስ ታሪክ የተጀመረበት ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ሰዎች የእርሱ ደቀ መዛሙርት ይሆኑ ዘንድ መሰብሰብ ጀመረ፡፡
መረባቸውን ወደ ባሕሩ ይጥሉ ነበር ኤቲ፡ “ዓሳ ለማጥመድ መረባቸውን ወደ ውሃው ውሰጥ ይጨምሩ” ( ተመልከት)
ተከተሉኝ ኢየሱስ ጴጥሮስ እና እንድርያስን ይከተሉት፣ ከእርሱ ጋር ይኖሩ እና የእርሱ ደቀ መዛሙርት ይሆኑ ዘንድ ጠራቸው፡፡ ኤቲ፡ “ደቀ መዛሙርቴ ሁኑ፡፡” ሰዎችን የሚታጠምዱ አደርጋችኋለሁ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ጴጥሮስ እና እንድርያስ እውነተኛውን መልዕክት ለእግዚአብሔርን ሕዝብ በማስተማሪ ሌሎችም ደግሞ ኢየሱስን እንዲከተሉ ያደርጋሉ፡፡ ኤቲ፡ “ዓሳ ታጠምዱ በነበረበት መንገድ እናንተም ሰዎችን እንዴት መሰብሰብ እንደሚትችል አስተምራችኋለሁ፡፡” ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ ይሆኑ ዘንድ ተጨማሪ ሰዎችን ጠራ፡፡
ጠራቸው “ኢየሱስ ዮሐንስ እና ያዕቆብን ጠራቸው፡፡” ይህ ሀረግም ኢየሱስ ይከተሉት፣ ከእርሱ ጋር ይኖሩ እና የእርሱ ደቀ መዛሙርት ይሆኑ ዘነድ ጠራቸው ማለት ነው፡፡
ወዲያውኑ “በዚያኑ ጊዜ”
ታንኳቸውን ትተው . . እና ተከተሉት ይህ የሕይወት ዘይቤ ለውጥ መሆኑን መግለጽ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ወደ ዓሳ አጥማጅነታቸው እና የቤተሰባቸውን ሥራ ከዚያን ጊዜ ጀምረው በሕይወታቸው ዘመን ሁሉ ኢየሱስን ለመከተል ትተዋለል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ይህ ኢየሱስ በገሊላ የጀመረው አገክግሎት ታሪክ የመጨረሻው ክፍል ነው፡፡ እነዚህ ቁጥሮች ምን እንዳደረገ እና ሰዎች የሰጡት ምላሽ ምን እንደሆነ ጠቅለል አድርጎ ያሳየናል፡፡ ([[End of Story]] ተመልከት)
በምኩራቦቻቸው እያስተማረ “በገሊላ ውስጥ በሚገኙ ምኩራቦች ውስጥ እያስተማረ” ወይም “በእነዚህ ሰዎች ምኩራብ ውስጥ እያስተማረ፡፡”
የመንግስቱን ወንጌል እየሰበከ በዚህ ሥፍራ ላይ “መንግስት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚብሔር ንጉሥ ሆኖ መንገሡን ነው፡፡ ኤቲ፡ “ወንጌልን ማለትም እግዚአብሔር እንዴት ራሱን ንጉሥ አድርጎ እንደገለጠ እየሰበከ” (UDB) ( ተመልከት)
ሁሉንም ዓይነት በሽታዎች እና ደዌዎች “ማንኛውንም በሽታ እና ደዌ፡፡” “በሽታ” እና “ደዌ” የሚሉት ቃላት በጣም የተቀራረቡ ናቸው ነገር ግን ከተቻለ በሁለት የተያዩ ቃላት አማካኝነት ቢተረጎሙ መልካም ነው፡፡ “በሽታ” አንድ ሰው አንዲታመም የሚያደርገው ነገር ነው፡፡ “ደዌ” አካላዊ ድክመት ወይም በሽተኛ በመሆን በአካል ላይ የሚሆን ህመም ነው፡፡
በዳቢሎስ የተያዙ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “በዳቢሎስ የተያዘ” ወይም “ዳቢሎስ የተቆጣጠራቸው፡፡” ( ተመልከት) የሚጥል በሽታ “የሚጥል በሽታ ያለባቸው” ወይም “ካለባቸው በሽታ የተነሳ የሚወድቁትን”
ሽባዎችን “መራመድ የማይችሉትን” ከዐሥሩም ከተሞች ይህ “ዐሥር ከተማዎች” ስም ነው፡፡ ." (UDB) ይህ ከገሊላ ባሕር በደቡብ ምስራቅ በኩሉ የሚገኘውን አከባቢ መጠሪያ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
በዲያቢሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን ወደ ምድረበዳ መራው። [4:1]
ኢየሱስ በምድረ በዳ ለአርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ። [4:2]
ዲያቢሎስ ኢየሱስ ድንጋዩን ወደ ዳቦ እንዲቀይር ፈተነው። [4:3]
ኢየሱስ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም አለ። [4:4]
ኢየሱስ ከቤተ መቅደሱ ራሱን ወደ ታች እንዲጥል ዲያቢሎስ ፈተነው። [4:5]
ኢየሱስ ከቤተ መቅደሱ ራሱን ወደ ታች እንዲጥል ዲያቢሎስ ፈተነው። [4:6]
ኢየሱስ ጌታ አምላክህን አትፈታተነው ሲል መለሰለት። [4:7]
ኢየሱስ የዓለም መንግሥታት ሁሉ እንዲሰጡት ወድቆ ያመልከው ዘንድ ዲያቢሎስ ፈተነው። [4:8]
ኢየሱስ የዓለም መንግሥታት ሁሉ እንዲሰጡት ወድቆ ያመልከው ዘንድ ዲያቢሎስ ፈተነው። [4:9]
ኢየሱስ ጌታ አምላክህን አምልክ፣ እርሱንም ብቻ አገልግል ሲል ኢየሱስ ተናገረ። [4:10]
በገሊላ ያሉ ሰዎች ታላቅ ብርሃን እንደሚያዩ የተነገረው የኢሳይያስ ትንቢት ተፈጸመ። [4:15]
በገሊላ ያሉ ሰዎች ታላቅ ብርሃን እንደሚያዩ የተነገረው የኢሳይያስ ትንቢት ተፈጸመ። [4:16]
"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ" እያለ ኢየሱስ ሰበከ። [4:17]
ጴጥሮስና እንድርያስ አሣ አጥማጆች ነበሩ። [4:18]
ጴጥሮስንና እንድርያስን ሰዎችን አጥማጆች እንደሚያደርጋቸው ኢየሱስ ተናገረ። [4:19]
ያዕቆብና ዮሐንስ አሣ አጥማጆች ነበሩ። [4:21]
ኢየሱስ በገሊላ ምኩራብ አስተማረ። [4:23]
ታመው እና በአጋንንት የተያዙ ሁሉ ወደ ኢየሱስ መጥተው ነበር፣ ኢየሱስም ፈወሳቸው። [4:24]
በዚህ ጊዜ ብዙ ሕዝብ ኢየሱስን እየተከተሉት ነበር። [4:25]
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ይህ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ማስመተማር የጀመረበት አዲስ ታሪክ ጅማሬ ክፍል ነው፡፡ ይህ ክፍል እስከ ምዕራፍ 7 ድረስ ይቀጥላል እንዲሁም ብዙ ጊዜም የተራራው ስብከት ተብሎ ይጠራል፡፡
አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጥር 3 ላይ ኢየሱስ የተባረኩ ሰዎች ባሕርያት ምን ምን እንደሆኑ መግለጽ ይጀምራል፡፡
አፉን ከፍቶ ኤቲ፡ “ኢየሱስ መናገር ጀመረ” ( ተመልከት)
አስተማራቸው “እነርሱን” የሚለው ቃል ደቀ መዛሙርቱን የሚያመለክት ነው፡፡
በመንፈሰስ ድሆች ይህ ማለት ትሁት የሆነ ማለት ነው፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር እንደሚያስፈልጋቸው ያወቁ፡፡” ( ተመልከት)
መንግስተ ሰማያት የእነርሱ ናትና በዚህ ሥፍራ ላይ “መንግስተ ሰማየት” የሚያመለክተው እግዚአብሔር እንደ ንጉሥ መግዛቱን፡፡ ይህ ሀረግ በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ ብቻ ነው የሚገኘው፡፡ ከተቻለ በትርጉማችሁ ውስጥ “ሰማይ” የሚለው ቃል እንዲኖር አድርጉ፡፡ ኤቲ፡ “በሰማይ ያለው እግዚአብሔር ንጉሣቸው ይሆናልና፡፡” ( ተመልከት)
የሚያለቅሱ ያዘኑበት ምክንያት ሊሆን የሚችለው 1) በዚህ ዓለም ኃጢአት ወይም 2) በራሳቸው ኃጢአት ወይም 3) በሌላ ሰው ሞት ምክንያት፡፡ ቋንቋችሁ ካላስገደዳችሁ በስቀተር ምክንያቱን አትግለጹ፡፡
ይጽናናሉና ይህ እንዲህ በቀጥታ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ያጽናናቸዋል፡፡” ( ተመልከት)
የዋሆች “ትሁታን” ወይም “በራሳቸው ኃይል የማይታመኑት”
ምድርን ይወርሳሉ “እግዚአብሔር ምድርን ሁሉ ይሰጣቸዋል”
ጽድቅን የሚራቡ እና የሚጠሙ ይህ ምሳሌያዊ አነጋገር ትክክለኛውን ነገር ለማድረግ ከልቡ የሚሻ ሰው ማለት ነው፡፡ ኤቲ፡ “ውሃ እና ምግብን ሰው እንደሚሻ ሁሉ በጽድቅ ለመኖር የሚሹ” ( ተመልከት)
ይሞላሉ ይህ እንዲህ ተብሎ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ይሞላቸዋ” ወይም “እግዚብሔር ያረካቸዋል፡፡” : ( ተመልከት)
ልበ ንጹሖች
“ልባቸው ንጹሕ የሆኑ ሰዎች፡፡” በዚህ ሥፍራ “ልብ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የአንድ ሰውን ፍላጎት ነው፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔርን ለማገልገል የሚፈልጉ ሰዎች፡፡” ( ተመልከት)
እግዚአብሔርን ያዩታል በዚህ ሥፍራ ላይ “ማየት” የሚለው ቃል በእግዚአብሔር መገኘት ውስጥ መኖር መቻልን የሚያመለክት ነው፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር መኖር እንዲችሉ ይፈቅድላቸዋል፡፡”
አስታራቂዎች እነዚህ ሌሎች ሰዎች እርስ በእርሳቸው ሰላም እንዲሆኑየሚያግዙ ሰዎችን ናቸው፡፡ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና ይህ በእንዲህ ዓይነት መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ልጆቼ ብሎ ይጠራቸዋልና” ወይም “የእግዚአብሔር ልጆች ይሆናሉና፡፡” (: ተመልከት)
የእግዚአብሔር ልጅ “ልጆች” የሚለውን ቃል በእናንተ ቋንቋ ለሰው ልጅ ወይም ሕጻናት በተለምዶ የሚትጠቀምበትን ተመሳሳይ ቃላት መጠቀሙ ጥሩ ነው፡፡
የሚሰደዱ ይህ በቀጥታ በዚህ ዓይነት መልኩ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ሌሎእ ሰዎች በተገቢው መንገድ ያልያዟቸው ሰዎች፡፡” ( ተመልከት)
ስለጽድቅ “እግዚአብሔር እንዲያደርጉ የሚፈልገውን ነገር በማድረጋቸው ምክንያት”
መንግስተ ሰማያት የእነርሱ ናትና ይህንን በ MAT 5:3 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ኢየሱስ የተባረኩ ሰዎች ባሕርያትን ማብራሩትን ጨርሷል፡፡
የተባረካቹ ናቸሁ “እናንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥር ነው፡፡ ( ተመልከት)
ስለ አንተ በውሸት ክፉ ነገሮችን ሁሉ ይናገራሉ፡፡ “ስለ አንተ ሁሉንም ዓይነት ክፉ ውሸትን ይናገራሉ” ወይም “እውነት ያልሆነ መጥፎ መጥፎ ነገሮችን ይናገራሉ”
ስለ እኔ ሲባል “እኔን በመከተልህ ምክንያት” ወይም “በእኔ በማመንህ ምክንያት”
ደስ ይበላችሁ እንዲሁም ሐሴትም አድርጉ “ደስ ይበላችሁ” እና “ሐሴት አድርጉ” የሚሉት ሁለቱ ቃላት ተመሳሳይ መልዕክቶችን የሚያስተልፉ ናቸው፡፡ ኢየሱስ አድማጮቹ ደስ ይበላችሁ ብቻ አላላቸው ነገር ግን ከተቻለ ከመደሰት በላይ እንዲያደርጉ ነግሮዋቸዋል፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እንደ ጨው እና ብርሃን ይሆኑ ዘንድ ማስተማር ጀመረ፡፡
እናንተ የምድር ጨው ናቸው አማራጭ ትርጓሜዎች 1) ጨው ለምግብት ጣእም እንደሚሰጥ ሁሉ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት በዓለም ውስጥ ያሉ ሰዎች መልካም ይሆኑ ዘንድ ተጽእኖ ፈጣሪዎች መሆን ይኖርባቸዋል ወይም 2) ልክ ጨው ምግብ ለረጅም ጊዜ ሳይበላሽ እንዲቆይ እንደሚያደረግ ሁሉ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ሰዎች ሙሉ ለሙሉ እንዳይበላሹ የሚያደርጉ ሊሆኑ ይባል፡፡ ኤቲ፡ “ለዓለም ሕዝቦች እናንተ ልክ እንደ ጨው ናችሁ” ወይም “ጨው ለምግብ እንደሆነ ሁሉ እናንተም ለዓለም እንደዚሁ ናችሁ፡፡” ( ተመልከት)
ጨው ጣእሙን ካጣ አማራጭ ትርጉሞች 1) “ጨው ጨው የሚሠራውን ነገር መሠርት የሚያስችለውን ኃይሉን ካጣ” ((UDB) ወይም 2) “ጨው ጣዕሙን ካጣ፡፡” ( ተመልከት)
እንዴት ጨው የሚሰጠውን ጥቅም ሊሰጥ ይችላል? “እንደገና እንዴት ጠቃሚ ሊሆን ይችላል?” ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለማስተማር ጥያቄን ይጠቀማል፡፡ ኤቲ፡ “አንደገና ጠቃሚ መሆን የሚችልበት ምንም ዓይነት መንገድ የለም፡፡” ( እና ተመልከት)
ወደ ውጪ ከመጣል እና በሰዎች ከመረገጥ በስቀር ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡ ኤቲ፡ “በመንገድ ዳር ይጥሉታል፤ ሰዎችም ይረጋግጡታል፡፡” (See: ተመልከት)
እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ ይህም ማለት የኢየሱስ ተከታዮች የእግዚአበብሔር እውነት ያለበትን መልዕክት እግዚብሔርን ወደ ማያውቁት ሰዎች ሁሉ ድረስ የሚያደርሱ ናቸው፡፡ ኤቲ፡ “እናንተ በዓለም ውስጥ ላሉ ሰዎች ልክ እንደ ብርሃን ናችሁ፡፡” (See: ተመልከት)
በተራራ ላይ ያለች ከተማ ፈጽሞ ልትደበቅ አትችልም ይህ ሰዎች የከተማዋን ብርሃን በምሽት መመልከት ይችላሉ ማለት ነው፡፡ ይህ በቀጥታ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “በምሽት በተራራ ላይ ያለች ከተማን ብርሃን ማንም ሰው ሊከልል አይችልም፡፡ ( እና ተመልከት)
መብራት የሚያበራ ሰውም እንዲሁ “ሰዎች መብራትን እንዲሁ አብርቶ
ከእንቅብ በታች አያኖረውም “መብራቱን ከቅርጫት በታች አያኖረውምለለ”፡፡ ይህ ማለት መብራን አብርቶ ሰዎች እንዳያዩት መደበቅ ሞኝነት ነው የሚል ነግግር ነው፡፡
ብርሃናችሁ በሰዎች ሁሉ ፊት ያብራ ይህ ማለት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ሌሎች ሰዎች የእግዚአብሔር እውነት ከእነርሱ መማር በሚችሉበት መንገድ መኖር አለባቸው ማለት ነው፡፡ ኤቲ፡ “ሕይወታችሁ ልክ እንደ መብራት በሰዎች ፊት ይብራ፡፡” ( ተመልከት)
በሰማይ የሚኖረው አባታችሁ “አባት” የሚለውን ቃል በጥሩ ሁኔታ ለመተርጎም በቋንቋችሁ ውስጥ አንድን አባት ለመጥራት የሚትጠቀሙትን ቃል ተጠቀሙ፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ኢየሱስ በብሉይ ኪዳን መጽሕፍት ውስጥ የተጻፉትን ሕግጋት ለመፈጸም እንደመጣ ማስተማሪ ጀመረ፡፡ ነቢያት ይህ ነቢያት በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የጻፏቸውን መጽሐፍትን ያመለክታል፡፡ ( ተመልከት) እውነት እላችኋለሁ “እውነት እላችኋለሁ፡፡” ይህ ሀረግ ኢየሱስ ቀጥሎሊናገረው ያለው ሀሳብ አጽኖት ልሰጥበት የሚገባ መሆኑን ያመለክታል፡፡ ሰማይና ምድር ያልፋሉ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር የፈጠራቸው ነገሮች ሁሉ ያልፋሉ፡፡” ( ተመልከት) አንድት ነጥብ “ከፊደል ትንሸዋ እንኳ ሳትቀር፡፡ ይህ ከቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ በሰዎች ይህንን ያኸለ አስፈላጊ አይደሉም ተብሎ የሚቆጠሩት እንኳ ሳይቀሩ የሚለውን ለማሳየት የቀረበበ ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ ኤቲ፡ “አስፈላጊ የማይመስሉ ሕግጋት እንኳ ሳይቀሩ”፡፡ ( ተመልከት) ሁሉ ነገር ይፈጸማል ይህ በግልጽ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር በሕግ ውስጥ የተጻፉትን ነገሮች ሁሉ ፈጽሟል፡፡ ( ተመልከት)
የተላለፈ ማንኛውም ሰው “የማይታዘዝ ማንኛውም ሰው” ወይም “ሳይታዘዝ የቀረ ማንኛውም ሰው” ከእነዚህ ትዕዛዛት መካከል ትንሹን “ከእነዝህ ትዕዛዛት መካከል፣ ጥቅሟ በጣም ትንሽ የሆነችውን ትዕዛዛ እንኳ ሳይቀር” ተብሎ ይጠራል ይህ እንዲህ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ያንን ሰው አግዚአብሔር እንዲህ ብሎ ይጠራዋል፡፡” ( ተመልከት) በመንግስተ ሰማይ ውስጥ ትንሽ “መንግስተ ሰማይ” ሚለው ሀረግ የእግዚአብሔር አገዛዝ ያመለክታል፡፡ ይህ ሀረግ የሚገኘው በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ ብቻ ነው፡፡ የሚቻል ከሆነ “በትርጉማችሁ ውሰጥ “ሰማይ” የሚለው ቃል ተጠቀሙ፡፡ ኤቲ፡ “በመንግስተ ሰማይ ውስጥ አስፈላጊነቱ ትንሽ ይሆናል” ወይም “በሰማይ የእግዚአብሔ አገዛዝ ውስጥ ያለው ጠቀሜታ በጣም ትንሽ ይሆናል፡፡” ( ተመልከት) ጠብቋቸው እንዲሁም አስተምሯቸው “እነዚህ ትዕዛዛት ሁሉ ታዘዙ እንዲሁም ሌሎችም ይህንኑ ያደርጉ ዘንድ አስተምሯቸው፡፡” ታላቅ “በጣም አስፈላጊ” እንዲህ ብዬአችኋለሁ ይህ ኢየሱስ ከዚህ በመቀጠል ስለሚናገረው ነገር አጽኖት ይሰጣል፡፡ አንተ . . . እናንተ . . . አንተ ይህ ብዙ ቁጥርን ያመለክታል፡፡ ( ጽድቃችሁ ካልበለጥ . . . ልትገቡ አትችሉም ይህ በአዎንታዊ መንገድ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ጽድቃችሁ መብለጥ አለበት . . . ለመግባት፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍ ነገር ኢሰየሱስ የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን ለመፈጸም መምጣቱን ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ በዚህ ሥፍራ ስለ ነፍስ ማጥፋት እና ንዴት ተናግሯል፡፡ አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ ለተሰበሰቡት ሰዎች እንደ ግለሰብ እያንዳንዳቸው ምን ሊያጋጥማቸው እንደሚችል እየተናገረ ነው፡፡ “ሰምታችኋል” የሚለው ሀረግ ውስጥ ያለው “እናንተ” የሚለው ቃል እና “እላችኋለሁ” ሀረግ ብዙ ቁጥር ነው፡፡ “አትግደል” የሚለው ሀረግነጠላ ቁጥር ነው ይሁን እንጂ በብዙ ቁጥር ሊተረጎም ይችላል፡፡ በጥት ዘመን እንዲህ ተብሎ ተነግሯቸዋል ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ከብዙ ዘመናት በፊት እግዚአብሔር ተናግሮ ነበር፡፡ ( ተመልከት) ነፈስ ያጠፋ ማንኛውም ሰው ፍርድ አለበት በዚህ ሥፍራ “ፍርድ” የሚለው ቃል ይህ ሰው እንዲገደል የሚያዘውን ሕግ የሚያሳይ ነው፡፡ ኤቲ፡ “ሌላ ሰው የገደለ ማንኛው ሰው ላይ ዳጃው ይፈርዳል፡፡” ( ተመልከት) ግዲያ. . . ግድያዎች ይህ የሚያመለክተው ቃል ሆኖ ነፍስ ማጥፋት እንጂ ሁሉንም ዓይነት የግዲያ አይነቶችን አይደለም፡፡ ነገር ግን እኔ እንዲህ እላችኋለሁ “እኔ” የሚትለው ቃ አጽኖታዊ ናት፡፡ ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስ የተናገረው ነገር እግዚአብሐየር በመጀመሪያ ከሰጠው ትዕዛዝ ጋር የሚስተካከል ነው፡፡ ስትተረጉም ይህንን አጽኖት በሚያሳይ ሀረግ ለመተርጎም ሞከር፡፡ ወንድም ይህ አማኝን እንጂ በሥጋ ወንድምን ወይም ጎረበትን የሚያመለክት አይደለም፡፡ ፍርድ ይገባዋል በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ እየተናገረ ያለው ስለ ሰው ፍርድ ሳይሆን በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሰውን እግዚአብሔር የሚያመጣውን ፍርድ ነው፡፡ ( ተመልከት) እርባና የሌለው . . . ሞኝ ይህ በትክክል ማሰብ የማይችሉ ሰዎች የሚሰደቡትን ስድብ የሚያመለክት ነው፡፡ “እርባና ያሌለው” የሚለው ቃል “አእምሮ የሌለው” ከሚለው ቃል ጋር ተቀራራቢ ሲሆን “ሞኝ የሚለው ደግሞ እግዚአብሔርን አለመታዘዝ ጋር ተያያዥነት ያለው ሀሳብ ነው፡፡ ሸንጎ ይህ በኢየሩሳሌም የሚገኘው የሸንጎ ሳይሆን በአከባቢው ያለው ሸንጎ ነው፡፡
እንተ ኢየሱስ በቡድን ላሉ ሰዎች እያንዳንዳቸው ምን እንደሚያጋጥማቸው እየተናገረ ነው፡፡ “አንተ” የሚለው ቃል ነጠላ ቁጥር ነው፡፡ እናንተ ግን በቋንቋች በብዙ ቁጥር ሊትተረጉሙት ትችላላችሁ፡፡ ( ተመልከት) መባህን “ስጦታ ስትሰጥ” ወይም “ስጦታህ ስታቀርብ” በመሠዊያው ላይ ይህ በኢየሩሳሌሚ ቤተ መቅደስ ውስጥ የሚገኘውን የእግዚአብሄርን መሠዊያ የሚያመለክት ነው፡፡ ኤቲ፡ “በቤተ መቅዲስ ውስጥ በሚገኘው የእግዚአብሔር መሠዊያ ላይ፡፡” ( ተመልከት) በዚያ ሳለህ ቢታስታውስ “በመሠዊያው ፊት ቆመህ ሳለ ቢታስታውስ” ወንድምህ አንዳች ነገር ከአንተ ጋር እንዳለው “አንተ ባደረከው አንድ ነገር የተነሳ ወንድም በአንተ የተቆጣ መሆኑን ካስታወስክ” በመጀመሪያ ሂድና ከወንድምህ ጋር ታረቅ ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ከሰውዬው ጋር ሰላምን ፍጠር፡፡” ( ተመልከት)
ከአንተ . . . ጋር ተስማማ ኢየሱስ በቡድን ላሉ ሰዎች እያንዳንዳቸው ምን እንደሚያጋጥማቸው እየተናገረ ነው፡፡ “አንተ” የሚለው ቃል ነጠላ ቁጥር ነው፡፡ እናንተ ግን በቋንቋች በብዙ ቁጥር ሊትተረጉሙት ትችላላችሁ፡፡ ( ተመልከት) ከከሳሽ ጋር ይህ ሰው ሌላኛውን ሰው በደል እየነቀሰ የሚወቅስ ሰው ነው፡፡ በዳኛ ፊት ሆኖ ሌላኛው ሰው የበደለውን በደል በመናገር ይከሳል፡፡ ለዳኛ አሳልፎ ይሰጥሃል በዚህ ሥፍራ ላይ “አሳልፎ ይሰጥሃል” የሚለው ሀረግ ትርጉሙ አንድን ሰው በሌላ ሰው ቁጥጥር ሥር እንዲሆን መስጠትን ያመለክታል፡፡ ኤቲ፡ “ዳኛው በሕጉ መሠረት እንዲፈርድብህ ያደርጋል፡፡” ( ተመልከት) ዳኛውም ለወህኒ ጠባቂዎች አሳልፎ ይሰጥሃል በዚህ ሥፍራ ላይ “አሳልፎ ይሰጥሃል” የሚለው ሀረግ ትርጉሙ አንድን ሰው በሌላ ሰው ቁጥጥር ሥር እንዲሆን መስጠትን ያመለክታል፡፡ ኤቲ፡ “ዳኛውም ለወህኒ ጠበቂ አሳልፎ ይሰጥሃል፡፡” ( ተመልከት) የወህኒ ጠባቂ ይህ ሰው ሰው በዳኛው የተሰጠውን ውሳኔ የሚያስፈጽም ግለሰብ ነው፡፡ ወደ ወህኒ ትጣላለህ ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “የወህኒ ጠባቂው በወህኒ ቤት ውስጥ እንዲትታሠር ያደርጋል፡፡” ( ተመልከት) እውነት እውነት እላችኋለሁ “እውነት እውነት እላችኋለሁ”፡፡ ይህ ሀረግ ኢየሱስ ቀጥሎ ለሚናገረው ነገር አጽኖት እንዲንሰጥ ያደርገናል፡፡ ከዚያ ሥፍራም “ከወህኒ ቤት”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን ለመፈጸም መምጣቱን ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ በዚህ ሥፍራ ስለዝሙት እና ምኞች ማስተማር ጀምሯል፡፡ አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “ሰምታችኋል” በሚለው ሀረግ ውስጥ የሚገኘው “እናንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥር ነው፡፡ “አታመንዝር” የሚለው ትዕዛዝ “አንተ” የሚለውን ቃ በውስጡ ይዞዋል ይሁን እንጂ “አንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር መተርጎም ትችላለህ፡፡ ( ተመልከት) እንዲህ እንደተባለ ሰምታችኋል ይህ በቀጥታ እንዲህ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር እንዲህ ብሏል፡፡” ( ተመልከት) መፈጸም ይህ ቃል አንድን ነገር ማድረግን ያመለክታል፡፡ እኔ ግን እንዲህ እላችኋለሁ ይህንን በ MAT 5:22 እንደ ተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡ ሴትን ተመልክቶ በልቡ የተመኛት ማንኛውም ሰው አመንዝሯል ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ሴትን ተመልክቶ በልቡ የተመኛት ማንኛውም ሰው ካመነዘረ ሰው እኩሉ ጥፋተኛ መሆኑን ያሳያል፡፡ ( ተመልከት) የተመኛት “እንዲሁም የተመኛት” ወይም “ከእርሷ ጋር ለመተኛት የተመኘ ሰው” በልቡ በዚህ ሥፍራ “ልብ” የሚያመለክተው የአንድን ሰው ሀሳብ ነው፡፡ ኤቲ፡ “በአእምሮው” ወይም “በሀሳቡ”፡፡ ( ተመልከት)
የአንተ . . . ከ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “አንተ” የሚለው ቃል ነጠላ ቁጥር ነው ይሁን እንጂ በብዙ ቁጥር መተርጎም የግድ ሊሆንብህ ይችላል፡፡ ( ተመልከት) የቀኝ ዐይንህ ካሰናከለችህ በዚህ ሥፍራ “ዐይን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አንድ ሰው የሚያየውን ነው፡፡ እንዲሁም “መሰናከል” ምሳሌያዊ ንግግር ሲሆን “ኃጢአት” ማለት ነው፡፡ ኤቲ፡ “የሚትመለከተው ነገር እንድትሰናከል የሚያደርግ ከሆነ” ወይም “ከሚታየው ነገር የተነሳ ኃጢአት ማድረግ የሚትሻ ከሆነ፡፡” ( እና ተመልከት) ቀኝ ዐይን . . . ቀኝ እጅ ከግራ ዐይን ወይም እጅ በተቃራኒው በጣም ጠቃሚው ዐይን ወይም እጅ፡፡ “ቀኝ” የሚለው ቃል “አስፈላጊ የሆነ” ወይም “ብቸኛ” በሚሉ ቃላት ለትተረጉማቸው ትችላለህ፡፡ ( ተመልከት) አውጥተህ “በኃይል ማስወገድ” ወይም “ማጥፋት”፡፡ ቀኝ ዐይን የሚለው በቀጥታ ካልተጠቀሰ “ዐይንህ አጥፋ” ብለህ ልትተረጉም ትችላል፡፡ ዐይን የተጠቀሰ ከሆነ “አጥፋቸው” ብለህ ልትተረጉም ትችላለህ፡፡ አውጣው . . . ቁረጠው ኢየሱስ የኃጢአትን አደገኝነት ላይ አጽኖት በመስጠት ለዚህ ሰዎች መስጠት ስላለባቸው ምላሽ ግነት የተሞላት መልኩ ተናገግሯል፡፡ ( ተመልከት) አውጥተህ ጣለው “አስወግደው” ከሰውነት ክፍለህ አንዱ ይጥፋ “ከሰውነት ክፍልህ አንዱን ማጣት ይሻላል፡፡” መላ አካልህ ወደ ሲኦል ከሚጣል ይልቅ ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላለል፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር መላ አካልህን ወደ ሲኦል ከሚጨምረው ይልቅ፡፡” ( ተመልከት) ቀኝ እጂህ ካሰናከለችህ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር የአንድ ሰው ሁለተናዊ ተግባርን ከእጁ ጋር ታያይዛለች፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን እንዴት ለመፈጸም እንደመጣ ማስተማሩ ቀጥሏል፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ስለፍች ማስተማር ጀምሯል፡፡ እንዲህም ተብሏል “የተናገረው” እግዚአብሔር ነው፡፡ ኢየሱስ የእርሱ ተቃርኖ ከእግዚብሔር ወይም ከእግዚብሔር ቃል ጋር አለመሆኑን ለመግለጽ ነው ይህን ዓይነት ንግግር የተናገረው፡፡ ይልቁንም ፍች የተፈቀደው ለትክክለኛ ምክንያት ብቻ ነው፡፡ ወንዱ ምንም እንኳ በትዕዛዛቱ መሠረት የፍች ወረቀቷን ለሚስቱ ቢሰጣትም እንኳ ፍትሓዊ አይደለም፡፡ ( ተመልከት) ሚስቱን የሚሰዳት ይህ ፍችን የሚያመለክት ምሳሌያዊ አነጋገር ነው፡፡ ( ተመልከት) ይስጣት “ልሰጣት ይገባል” እኔ ግን እንዲህ እላለሁ ይህንን በ MAT 5:22 በምን ዓይነት መንገድ እንደተረጎማችሁ ተመልከቱ፡፡ አመንዝራ ያደርጋታል ትክክለኛ ባልሆነ መንገድ ሚስቱን የፈታት ሰው “እንድታመነዝር ያደርጋል”፡፡ በብዙ ባሕሎች ውስጥ እንደገና ማግባት ትችላለች ነገር ግን የተፋታችው ትክክለኛ ባልሆነ መንገድ ከሆነ ግን እንዲህ አይነቱ ትዳር ዝሙት ነው፡፡ ከተፋታች በኋላ ይህ በቀጥታ እንዲህ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ባሏ ከፈታት በኋላ” ወይም “ፍች የፈጸመችው ሴት”፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን እንዴት ለመፈጸም እንደመጣ ማስተማሩ ቀጥሏል፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ስለመሃላ ማስተማር ጀምሯል፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “ሰምታችኋል በሚለው ሀረግ ውስጥ ያለው “እናንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ ይሁን እንጂ “አትማል” እና “ፈጽማቸው” በሚለው ውስጥ ያለው “አንተ” የሚለው ቃል በነጠላ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ እንደገና አንተ “አንተም ደግሞ” ወይም “ሌላ ምሳሌ ይኼው፡፡ አንተ” እንዲህ ሲባል ሰምታችኋል . . . በውሸት አትማሉ በዚህ ሥፍራ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር እና ከቃሉ ጋር በግልጽ የሚስማማ ነገር ስናገር ትመለከታላችሁ፡፡ ይሁን እንጂ ሰዎችን ለማሳመን የእነርሱ ያልሆነ ነገር እንዳይናገሩ ያሳስባቸዋል፡፡ ኤቲ፡ “የሃይማኖት መሪዎቻችሁ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ብለው ነግረዋችኋል . . . አትማሉ፡፡” ( ተመልከት) በውሸት አትማሉ መኃላችሁን ፈጽሙ እንጂ አማራጭ ትርጉሞች 1) የማትፈጽሙትን ነገር አደርጋለሁ ብላችሁ በእግዚአብሔር ፊት አትማሉ ወይም 2) አንድ ነገር ውሸት መሆኑን እያወቃችሁ በእግዚአብሔር ፊት እውነት ነው ብላችሁ አትማሉ፡፡ እኔ ግን እንዲህ እላችኋለሁ በ MAT 5:22 የሚገኘውን በምን መንገድ እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡ ፈጽሞ አትማሉ . . . የታላቁ ንጉሥ ከተማ በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ የተናገረው ማንም ሰው ፈጽሞ መማል እንዳሌለበት ነው፡፡ አንዳንዶች አንድ ሰው የማለው ከእግዚአብሔር ውጪ በሆነ ነገር ማለትም በሰማይ፣ በምድር ዌም በኢየሩሳም የማለ ከሆነ መሃላውን ሳይፈጽም ቢቀር ይህን ያኽል ጉዳት የለውም ብለው ሳያስተምሩ አልቀሩም፡፡ ኢየሱስ ይህም ቢሆን እንደ ማንኛውም መሃላ መጥፎ ነው ምክንያቱም ሁሉ ነገር የእግዚአብሔር ስለሆነ ነው፡፡ ፈጽሞ አትማሉ ለዚህ ትዕዛዝ የሚሆን ቃል በቋንቋችሁ በብዙ ቁጥር የሚገኝ ከሆነ በዚህ ሥፍራ ይህንን ቃል ተጠቀሙ፡፡ “በውሸት አትማሉ” የሚለው ሀረግ አድማጮች መማል እንደሚቻል ነገር ግን በውሸት መማል የማይቻል እንደሆነ ያሳያል፡፡ “ፈጽሞ አትማሉ” የሚለው ሀረግ ግን ሁሉንም ዓይነት መሃላዎችን ይከለክላል፡፡ የእግዚአብሔር ዚፋን ነው በዚህ ሥፍራ ላይ “ዙፋን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔር እንደ ንጉሥ መግዛቱን ነው፡፡ ኤቲ፡ “የእግዚአብሔር አገዛዝ”፡፡ ( ተመልከት) የእግሩ መረገጫ ናት ይህ ምሳሌያዊ አነጋገር ምድርም ቢትሆን የእግዚአብሔር መሆኗን ያሳያል፡፡ ኤቲ፡ “ንጉሥ እግሩን የሚያሳርፍበት የእግሩ መርገጫ ሥፍራ ዓይነት ናት፡፡ ( ተመልከት) የታላቁ ንጉሥ ከተማ ናትና “ይህች ከተማ የታላቁ ንጉሥ የእግዚአብሔር ከተማ ናትና፡፡”
አጠቃላይ መረጃ፡ ከዚህ በፊት በነበረው ክፍል ውስጥ ኢየሱስ ስለ እግዚአብሔር ዙፋን፣ የእግሩ መረገጫ እና ምድራዊ ቤተ ጭምር ሊምሉበት የሚገባ የእርሱ ንብረት አለመሆኑን ገልጾዋል፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ደግሞ በራሳቸው ላይ ባለው ጸጉር እንኳ መማል እንደማይገባቸው ይናገራል፡፡ እናንተ . . . አንተ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “አትማል” እና “አትችልም” በሚሉ ሀረጋት ውስጥ ያለው “አንተ” የሚለው ቃል በነጠላ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ ይሁን እንጁ በምትተረጉሙበት ጊዜ በብዙ ቁጥር ልትተረጉሙ ትችላላችሁ፡፡ ( ተመልከት) መሃላ በ MAT 5:34እንዴት እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡ ንግግርህ “አዎ፣ አዎ ወይም አይ ፣ አይ” ይሁን” “አዎ ማለት ከፈለግህ “አዎ” በል እንዲሁም “አይ” ማለት ከፈለግህ “አይ” በል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን እንዴት ለመፈጸም እንደመጣ ማስተማሩ ቀጥሏል፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ጠላትን ስለመበቀል ማስተማር ጀምሯል፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “ሰምታችኋል” እና “እኔ እንዲህ እላችኋለሁ” በሚለው ሀረግ ውስጥ የሚገኘው “እናንተ” የሚለው ቃል የተገለጸው በብዙ ቁጥር ነው፡፡ “ማንም ቢመታህ” የሚለው ሀረግ ውስጥ የሚገኘው “አንተ” የሚለው ቃል ግን በብዙ ቁጥር መተርጎም ትችላላችሁ፡፡ ( ተመልከት) እንዲህ መባሉን ሰምታችኋል ይህንን በ MAT 5:33 እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከት፡፡ ዐይን ለዐይን ጥርስ ለጥርስ የሙሴ ሕግ የጎዳንን ሰው በተመሳሳይ መንገድ እንዲጎዳ ያዛል ይሁን እንጂ ከዚያ በላይ እንዲጎዳ አያደርግም፡፡ እኔ ግን እንዲህ እላለሁ ይህንን በ MAT 5:22.እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከት፡፡ ክፉውን “ክፉ የሆነ ሰው” ወይም “የጎዳችሁ ሰው” (UDB) ቀኝ ጉንጫችሁን የመታችሁ ኢየሱስ በኖረበት ባሕል ውስጥ የአንድን ሰው ቀኝ ጉንጭ በጥፊ መምታት ስድብ ነው፡፡ ልክ እንደ ዐይን እና እጅ ሁሉ ቀኝ ጉንጭም በጣም ጠቃሚ ነገር ነው፡፡ ጉንጭን በጥፊ መምታት ትልቅ ስድብ ነው፡፡ መምታት “በጥፊ መምታት”፡፡ ይህ ማለት በቃሪያ ጥፉ አንድን ሰው መምታት ማለት ነው፡፡ ሌላኛውንም ፊት አዙሩለት “ሌላኛውን ፊታችሁን የሚታችሁ ዘንድ አዙሩለት”
አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “ፍቀድ”፣ “ሂድ”፣ “ስጥ” እና “አትመለስ” በሚሉ ቃላት ውስጥ ያለው “አንተ” የሚለው ቃል በነጠላ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ ( ተመልከት) ኮትህ . . . መጎናጸፊያ “ኮት” በሰዉነት ላይ እንደ ቲሸረት የሚጠለቅ ነው፡፡ “መጎናጸፊያ” ከእነዚህ ይልቅ ውድ የሆነ “ከኮት” ላይ ለሙቀት የሚደረብ እንዲሁም በሽት ለሙቀት የሚለበስ ነገር ነው፡፡ ይወስድ ዘንድ ፍቀድለት “ለዚያ ሰው ስጠው” ማንምን ሰው “እንዲሁም ይህ ሰው”፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ በተዘዋዋር መንገድ የተጠቀሰው የሮማዊያን ወታደር ነው፡፡ ( ተመልከት) አንድ ምዕራፍ አንድ የሮም ወታደር በዚያ ዘመን አንድን ሰው አንድ ዕቃ ተሸክሞ እንዲሄድ በሕግ ማስገደድ የሚችለው አንድ ሺህ እርምጃዎች ያኽል ነው፡፡ “ማይል” የሚለው ቃል የሚያምታታ ከሆነ “አንድ ኪሎ ሜትር” ወይም “ረጅም ርቀት” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ከእርሱ ጋር አብረኸው እንዲትሄድ ያስገደደ ሰውን ያመለክታል፡፡ ከእርሱ ጋር እጥፍ መንገድ ሂደት “አስገድዶህ እንዲትሄድ ያደረግህን ምዕራፍ ያኸል ሂደት ከዚያም ሌላ አንድ ማዕራፍ ጨምርለት፡፡” “ማይል” የሚለው ቃል የሚያምታታ ከሆነ “ሁለት ኪሎ ሜትር” ወይም “እጥፍ ርቀት” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ አትከልክል “እንዲሁም ሊበደርህ የሚፈልግ ሰውን አትከልክል፡፡” ይህ በአውንታዊ መንገድ ሊገለጽ ይገባል፡፡ ኤቲ፡ “አበድር”፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ኢየሱስ የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን እንዴት ለመፈጸም እንደመጣ ማስተማሩ ቀጥሏል፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ጠላትን ስለመውደድ ማስተማር ጀምሯል፡፡ አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “የሚወድሁን ውደድ . . . የሚጠሉህ ጥላ” የሚለው ብቻ በነጠላ ቁጥ የተጻፈ ሲሆን እነዚህም ቢሆን በብዙ ቁጥር መተርጎም ትችላህ፡፡ ለሌሎች “እናንተ” የሚል ቃል ባለባቸው ሥፍራዎች ሁሉ እና “ፍቅር”እና “ጸሎት” ቦታዎች በብዙ ቁጥር የተገለጹ ናቸው፡፡ ( ተመልከት) እንዲህ እንደተባለ ሰምታችኋል ይህንን በ MAT 5:33. እንደተረጎማችሁት ተመልከት፡፡ ባለንጀራህን “ባለንጀራ” የሚለው ቃል አንድ ሰው በመልካም መንገድ ማስተናገድ የሚሻውን የተመሳሳይ ማህበረሰብ ወይም ቡድን አባላትን የሚያመለክት እንጂ በአከባቢያችን የሚኖሩ ሰዎችን ሁሉ አያመለክትም፡፡ ይህንን የብዙ ቁጥርን በሚያመለክት ቃል ልትተረጉሙት ትችላላችሁ፡፡ እኔ ግን እንዲህ እላችኋለሁ ይህንን በ MAT 5:22. እንደተረጎማችሁት ተመልከት፡፡ የአባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ “ልጆች” የሚለው ቃል በጥሩ ሁኔታ ለመተርጎም በቋንቋችሁ ለሰው ልጆችን ወይም ሕጻናት የሚትጠቀሙትን ቃል ተጠቀሙ፡፡ አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን እንዴት ለመፈጸም እንደመጣ ያስተማረውን ትምህርት በዚህ ከፍል ውስጥ ያጠናቅቃል፡፡ ይህ ክፍል የሚጀምረው በ MAT 5:17 ላይ ነው፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ ያኽል “እናንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥር አመልካች ነው፡፡ በእነዚህ ቁጥሮች ውስጥ የሚገኘው ጥያቄ መጠይቃዊ ነው፡፡ ( እና ተመልከት) ታላቅ ይህ አድማጮቹ መልካምነት ያለውን መሻት የሚያሳይ አጠቃላይ ቃል ነው፡፡አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
በመንፈስ ድሃ የሆኑት ብፁዓን የሆኑት መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ስለሆነች ነው። [5:3]
የሚያለቅሱ ብፁዓን የሆኑት ስለሚጽናኑ ነው። [5:4]
የዋሆች ብፁዓን የሆኑት ምድርን ስለሚወርሱ ነው። [5:5]
ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙት ብፁዓን የሆኑት ስለሚጠግቡ ነው። [5:6]
ስለ ኢየሱስ የሚሰደቡና የሚሰደዱ ብፁዓን የሚሆኑት ዋጋቸው በሰማይ ታላቅ ስለሆነ ነው። [5:11]
ስለ ኢየሱስ የሚሰደቡና የሚሰደዱ ብፁዓን የሚሆኑት ዋጋቸው በሰማይ ታላቅ ስለሆነ ነው። [5:12]
መልካምን ሥራ በማድረግ አማኞች ብርሃናቸው በሰው ፊት እንዲበራ ያደርጋሉ። [5:15]
መልካምን ሥራ በማድረግ አማኞች ብርሃናቸው በሰው ፊት እንዲበራ ያደርጋሉ። [5:16]
ኢየሱስ የመጣው የብሉይ ኪዳን ህግ እና ነብያትን ለመፈጸም ነው። [5:17]
ትእዛዛቱን የሚጠብቁና ለሌሎች የሚያስተምሩ በመንግሥተ ሰማያት ታላቅ ይባላሉ። [5:19]
የሚገድሉ ብቻ ሳይሆን፣ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ በፍርድ አደጋ ውስጥ እንደሆነ ኢየሱስ አስተማረ ። [5:21]
የሚገድሉ ብቻ ሳይሆን፣ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ በፍርድ አደጋ ውስጥ እንደሆነ ኢየሱስ አስተማረ ። [5:22]
ሄደን ከወንድማችን ጋር እንድንታረቅ ኢየሱስ አስተማረ። [5:23]
ሄደን ከወንድማችን ጋር እንድንታረቅ ኢየሱስ አስተማረ። [5:24]
ወደ ፍርድ ቤት ከመድረሱ በፊት ከከሳሻችን ጋር እንድንስማማ ኢየሱስ አስተማረ። [5:25]
ዝሙትን መፈጸም ብቻ ሳይሆን፣ ነገር ግን ሴትን አይቶ መመኘትም ስህተት እንደሆነ ኢየሱስ አስተማረ። [5:27]
ዝሙትን መፈጸም ብቻ ሳይሆን፣ ነገር ግን ሴትን አይቶ መመኘትም ስህተት እንደሆነ ኢየሱስ አስተማረ። [5:28]
ኃጢአት እንድናደርግ የሚያደርገን የትኛውንም ነገር ልናስወግድ እንደሚገባ ኢየሱስ ተናገረ። [5:29]
ኃጢአት እንድናደርግ የሚያደርገን የትኛውንም ነገር ልናስወግድ እንደሚገባ ኢየሱስ ተናገረ። [5:30]
ኢየሱስ ፍቺን የፈቀደው በዝሙት ጉዳይ ሲሆን ነው። [5:32]
ያላግባብ ከፈታትና እርሷም መልሳ ካገባች ባል ሚስቱን አመንዝራ ያደርጋታል። [5:32]
በእነዚህ ሁሉ ነገሮች ከመማል ይልቅ ንግግራችን “አዎን፣ አዎን፣” ወይም “አይደለም፣ አይደለም” ሊሆን እንደሚገባ ኢየሱስ ተናገረ። [5:37]
ክፉ የሚያደርግብንን እንዳንቃወም ኢየሱስ አስተማረ። [5:38]
ክፉ የሚያደርግብንን እንዳንቃወም ኢየሱስ አስተማረ። [5:39]
ጠላቶቻችን እና የሚያሳድዱንን እንድንወድድ እና እንድንጸልይላቸው ኢየሱስ አስተማረ። [5:43]
ጠላቶቻችን እና የሚያሳድዱንን እንድንወድድ እና እንድንጸልይላቸው ኢየሱስ አስተማረ። [5:44]
የሚወድዱንን ብቻ ብንወድድ፣ አሕዛብ የሚያደርጉትን ብቻ ማድረጋችን ስለሆነ ዋጋ እንደማናገኝ ኢየሱስ ተናገረ። [5:46]
የሚወድዱንን ብቻ ብንወድድ፣ አሕዛብ የሚያደርጉትን ብቻ ማድረጋችን ስለሆነ ዋጋ እንደማናገኝ ኢየሱስ ተናገረ። [5:47]
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ በ MAT 5:3ላይ የተጀመረውን የተራራው ስብከቱን ማስተማር ቀጥሏል፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “የጽድቅን ተግባራት” የሆኑትን አስራት ማውጣት፣ ጸሎት እና ጾምን አስመልክቶ አስምሯል፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “እናንተ” የሚለው ቃል ሁሉም በብዙ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ በሰዎች ለመታየት ለሰዎች ብለው የሚያደርጉ ሰዎች እርሱን እያከበሩት እንዳልሆነ በተዘዋዋር መልኩ ያመለክታል፡፡ ይህ እንዲህ ባለ መልኩ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ስላደጋችሁት ነገር ሰዎች ያመሰግናችሁ ዘንድ በሰዎች ፊት የሚታደርጉት ከሆነ፡፡” ( እና ተመልከት) አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) ለራስህ መለከት አታስነፋ ይህ ምሳሌ የሚያሳየው የሰዎችን ትኩረት ሆን ብለህ ለመሳብ የተለያዩ ነገሮችን ማድረግ ነው፡፡ ኤቲ፡ “በብዙ ሰዎች መካከል መለከት በታላቅ ድምፅ እንደሚነፋ ሰው ወደ ራሰህ የሰዎችን ትኩረት ለመሳብ ጥረት አታድረግ፡፡” ( ተመልከት) እውነት እልሃለሁ “እውነቱን እነግርሃለሁ”፡፡ ይህ ሀረግ ኢየሱስ በመቀጠል ስለሚናገረው ነገር አጽኖት የሚሰጥ ሀረግ ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ኢየሱስ ስመ ስጦታ መስተማሩን ቀጥሏል፡፡ አጠቃላያ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “እናንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥር አመልከች ነው፡፡ ግራ እጅህ ቀኝ እጅህ የሚሰጠውን አይወቅ ይህ የሚታደርገው ነገር ሁሉ ሙሉ ለሙሉ ምስጥር መሆን እንዳለበት የሚያሳይ ምሳሌ ነው፡፡ ምንም እንኳ ሁለቱም እጆች ብዙ ጊዜ ነገሮችን በጋራ የሚያከናውኑ ቢሆንም እንኳ፣ አንዱ የሚያደርገውን ሌላኛው “የሚያውቅ” ቢሆንም እንኳ ለድሆች በሚትሰጥበት ጊዜ እነዚህ በጣም የሚቀራረቡ እጆች እንኳ አንደኛው የሌላኛውን ማወቅ የለበትም፡፡ ( ተመልከት) ስጦታችሁ በድብቅ ይሁን ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ሌሎች ሰዎች መስጠትህ ሳያውቁ ለድሆች ልትሰጥ ትችላለህ፡፡” ( ተመልከት) ይሸልምሃል “ሽልማት ይሰጥሃል፡፡” (UDB)
አያያዥ ዓረፍተ ነገሮች ኢየሱስ ስለ ጸሎት እንዲህ በማለት ማስተማር ጀመረ፡፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በቁጥር 5 እና 7 ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የብዙ ቁጥር አመልካች ቃል ሲሆን በቁጥር 6 ላይ ግን በነጠላ ቁጥር ተገልጾዋል፡፡ ይሁን እንጂ ይህንን በብዙ ቁጥር ልትተረጉመው ትችላለህ፡፡ ( ተመልከት) ሌሎች ሰዎች የሚያደርጉትን ያዩላቸው ዘንድ በዚህ ሀረግ ውስጥ ተመልካቾቹ ድርጊቱን ተመልክተው ክብር እንደሚሰጧቸው በተዘዋዋር መንገድ ያሳያል፡፡ ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ሰዎች ያዮዋቸው እና ክብር ይሰጧቸው ዘንድ፡፡” ( እና ተመልከት) እውነት እውነት እላችኋለሁ “እውነቱን እነግራቿለሁ”፡፡ ይህ ሀረግ ኢየሱስ በመቀጠል ለመናገረው ነገረ ትኩርት እንዲንሰጥ ያደርገናል፡፡ ወደ እልፍኝህ ግባ፡፡ በርህንም ዝጋ “ለብቻ ወደምትሆንበት ሥፍራ ግባ” ወይም “ለብቻ መሆን ወደምትችልበት ሥፍራ ሂድ” በውስር ያለው አባት ለዚህ አማራጭ ትርጉሞች 1) እግዚአብሔርን ማንም ሰው ማየት አይችልም ወይም 2) እግዚአብሔር በዚያ ለብቻው ከሚጸልየው ሰው ጋር አለ፡፡ አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) በስውር የሚታደርገውን የሚያይ አባት “አባትህ በስውር የሚታደርገውን ያያል” በከንቱ አትድገም “ትርጉም የሌሽ ቃላትን አትደጋግም” ይሰማል ይህ እንዲህ በቀላሉ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “የሐሰት አማልክቶች ይሰሟቸዋል፡፡” ( ተመልከት) ብዙ በመናገራቸው “በረጃጅም ጸሎቶቻቸው” ወይም “ በብዙ ቃሎቶቻቸው፡፡”
አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “እንዲህ ጸልዩ” እስከሚለው ድረስ ለቡድን ተናግሯል፡፡ “እናንተ” ከሚለው ቀጥሎ ያለው “ሰማያዊ አባታችሁ” የሚለው ቃል በነጠላ ቁጥር ነው የተቀመጠው፡፡ (See: ተመልከት) አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) ስምህን ይቀደስ በዚህ ሥፍራ ላይ “ስም” የሚለው ቃል እግዚአብሔርን የሚያመለክት ነው፡፡ ኤቲ፡ “ቅዱስ እንደሆንክ ሁሉም ሰው ይወቅት፡፡” ( ተመልከት) መንግስትህ ትምጣ በዚህ ሥፍራ “መንግስት” የሚለው ቃል እግዚአብሔር እንደ ንጉሥ ሆኖ የሚገዛበትን የሚያመለክት ቃል ነው፡፡ ኤቲ፡ “በሁሉም ላይ ገዥ ሁን እና ሙሉ ለሙሉ ሁሉን ግዛ፡፡” ( ተመልከት) ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እዲሁም በምድር ላይ ትሁን ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “በሰማይ ያሉት ሁሉም እንደሚታዘዙህ ሁሉ በምድር ላይ ያሉት ሁሉ ይታዘዙህ፡፡” ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ “እኛ” እና “የእኛ” የሚሉት ቃላት ኢየሱስ እየተናገራቸው ያለውን የተሰበሰበውን ሕዝብ ያመለክታል፡፡ ( ተመልከት) የእለት እንጀራችንን በዚህ ሥፍራ ይ “እንጀራ” የሚለው ቃል በአጠቃላይ ምግብን ያመለክታል፡፡ ( ተመልከት) ብድር ብድር አንድ ሰው ያለበት ዕዳ ነው፡፡ ይህ ኃጢአትን በምሳሌ ለመግለጽ ጥቅም ላይ የዋለ ቃል ነው፡፡ ( ተመልከት) ባለዕዳ ባለዕዳለ ከሌላ ሰው የተበደረ ሰው ነው፡፡ ይህ ኃጢአትን በምሳሌ ለመግለጽ ጥቅም ላይ የዋለ ቃል ነው፡፡ ( ተመልከት) ወደ ፈተና አታግባን “ፈተና” የሚለው ቃል በግሥ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ምንም ነገር እንድፈትነን አትፍቀድለት” ወይም “ኃጢአትን እንድንመኝ የሚያደረግ ማንኛውንም ነገር ሕይወታችን ውስጥ አትፍቀድ፡፡” ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚገኝበት ሥፍራ ሁሉ በብዙ ቁጥር ነው፡፡ ይሁን እንጂ ኢየሱስ ሌሎች ሰዎችን ይቅር ካላሉ በግል ምን እንደሚደርስባቸው እየነገራቸው ነው፡፡ ተመልከት) መተላለፍ “ስህተት” ወይም “ኃጢአት” አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ስለ ጾም ማስተማር ጀመረ፡፡ አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በቁጥር 17 አና 18 ላይ “አንተ” የሚለው ቃል በነጠላ ቁጥር የተገለጸ ሲሆን በቁጥር 16 ላይ ካለው ጋር ተመሳሳይ እንዲሆን በብዙ ቁጥር ልትተረጉመው ትፈልግ ይሆናል፡፡ ( ተመልከት) በተጨማሪ “እንዲሁም” ፊታቸውን ያጎሳቁላሉ ግብዞች ፍታቸውን አይታጠቡም ወይም ጸጉራቸውን አያበጥሩም፡፡ ይህንን የሚያደርጉት ሆን ብለው እየጾሙ መሆናቸውን ለማሳየት የሰዎችን ትኩረት ለመሳብ እና ከእነርሱ ክብር ለማግኘት ሲሉ ይህንን ያደርጋሉ፡፡ እውነት እውነት እላችኋለሁ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፡፡” ይህ ሀረግ ኢየሱስ በመቀጠል ለሚናገረው ነገር ትኩረት መስጠቱን ያመለክታል፡፡ ራስህን ዘይት ተቀባ “ዘይት ተቀባ” ወይም “ጸጉርህን አበጥር”፡፡ ራስህን “ተቀባ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ለጸጉር የተለመደውን እንክብካቤ ማድረግ ነው፡፡ “ከክርስቶስ” “የተቀባው” መሆኑ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም፡፡ ኢየሱስ ማለት የፈለገው ሰዎች ጾም እየጾሙም ሆነ ሳይጾሙ ተመሳሳይ መሆን አለባቸው ነው፡፡ በስውር ያለው አባት . . . በስውር የሚያይ ይህንን እንዴት በ MAT 6:6. እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ስለ ገንዘብ እና ንብረት ማስማር ጀመረ፡፡ አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “አንተ” የሚል ቃል ጥቅም ላይ በዋለባቸው ሥፍራዎች ከቁር 21 በስተቀር ብዙ ቁጥርን ያመለክታል፡፡ ይሁን እንጂ በቁትር 21 ላይ ነጠላ ቁጥር ነው፡፡ ( ተመልከት) ንብረት “ሀብት” ብል እና ዝገት የሚበሉት “ብል እና ዝገት የሚያበላሹት ሀብት” ብል ብል ልብስን የሚያበላሹ በራሪ ነፍሳት ናቸው፡፡ ዝገት ብረት ውሃ ሲነካው የሚፈጠር ቡናማ ቀለም ያለው ነገር ነው፡፡ store up for yourselves treasures in heaven This is a metaphor that means do good things on earth so God will bless you in heaven. በሰማይ ሀብትን አከማቹ ይህ ምሳሌ የሚያሳየው እግዚአብሔር በሰማይ ይበባርካችሁ ዘንድ በምድር ላይ ሳላቹ መልካምን ነገር አድርጉ፡፡ ( ተመልከት) ልብህም ደግሞ በዚያ ይሆናል በዚህ ሥፍራ ላይ “ልብ1 ማለት አሳብ እና ፍላጎት ማለት ነው፡፡ ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “አንተ” የሚል ቃል ጥቅም ላይ በዋለባቸው ሥፍራዎች ውስጥ በነጠላ ቁጥር የተጠቀሰ ሲሆን አንተ ግን በብዙ ቁጥር ለመተርጎም ታስብ ይሆናል፡፡ ( ተመልከት) ዐይን የሰውነት ብርሃን ነች . . . ጨለማው ምን ያኽል ታላቅ ይሆን ይህ ማየት የሚችል ጤናማ ዐይንን አንድን ሰው ዐይነ ሥውር ከሚያደረግ በሽታ ጋር ያነነጻጽራል፡፡ ይህ ምሳሌ የሚያመለክተው መንፈሳዊ ጤንነትን ነው፡፡ ብዙ ጊዜ አይሁዳዊያን “መጥፎ ዐይንን” ከስስት ጋር ያይዙታል፡፡ ትርጉሙም አንድ ሰው ሁለተናውን ለእግዚአብሔር ከሰጠ እንዲሁም ሁሉንም ነገር ከእግዚአብሔር አንጻር መመልከት ከቻለ ትክክለኛውን ነገር ያደርጋል፡፡ ይሁን እንጂ አንድ ሰው ስስታም ከሆነ ክፋትን ያደርጋል፡፡ ( ተመልከት) ዐይን የሰውነት ብርሃን ነው የዚህ ምሳሌያዊ ንግግር ትርጉም ልክ መብራት በጨለማ ውስጥ ሰው አጥርቶ እንዲያይ እንደሚያደርግ ሁሉ ዐይንም አንድ ሰው በደንብ ማየት እንዲችል ያደርገዋ፡፡ ኤቲ፡ “እንደ መብራት ዐይን ነገሮችን በግልጽ ማየት እንድትችል ያደርጋል፡፡” ( ተመልከት) ዐይን ይህንን በብዙ ቁጥር ልትተረጉመው ትችላለህ፤ “ዐይኖች”፡፡ ዐይንህ መጥፎ ቢሆን ይህ ምትሃትን አያመለክትም፡፡ አይሁዶች ብዙ ጊዜ ስስታምነትን በዚህ ምሳሌያዊ አነጋገር ይገልጹታል፡፡ ( ተመልከት) አንዱን ይወዳል ሌላኛውን ይጠላል ወይም ለአንዱ ይገዛል ሌላኛውን ደግሞ ይንቃል ሁለቱም በመሠረታዊ ሀሳባቸው አንድ ናቸው፡፡ አጽኖት የሚሰጡት አንድ ሰው እግዚአብሔር መውደድ እና መገዛት እንዲሁም ገንዘብንም መውደድና ለእርሱ መገዛት በአንድ ጊዜ አይችልመም፡፡ ( ተመልከት) ለሀብት እና ለእግዚአብሔር መገዛት አትችሉም፡፡ “በአንድ ጊዜ እግዚአብሔርን እና ገንዘብን መውደድ አትችሉም፡፡”
እላችኋለሁ ይህ ኢየሱስ ከዚህ በመቀጠል የሚናገረው ነገር አጽኖት ሊሰጠው የሚገባ መሆኑን ያሳያል፡፡ ለእናንተ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “እናንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ ( ተመልከት) ሕይወት ከመብል እንዲሁም ሰውነት ከልብስ አይበልጥምን? በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ ሰዎችን ለማሰተማር ጥያቄን ተጠቅሟል፡፡ ኤቲ፡ “በእርግጥ ሕይወት ከምግብ እንዲሁም አካል ከምንለብሰው ልብስ ይበልጣል፡፡” ( ተመልከት) ጎተራ እህል ማጠራቀሚያ ሥፍራ፡፡ አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) Are not you of much more value than they? Jesus uses a question to teach the people. AT: "Obviously you are more valuable than birds." አንተ ከእነርሱ ይልቅ በጣም ኩቡር አይደለህምን? ኢየሱስ ሰዎችን ለማስተማር ጥያቄን ይጠቀማል፡፡ ኤቲ፡ “ከሰማይ ወፎች ይልቅ አንተ ክቡር ነህ፡፡” ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “እናንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ ( ተመልከት) ከእናንተ መካከል በመጨነቅ በእድሜው ላይ ስንዝር ታኽል የጨመረ ማን ነው? ኢየሱስ ሰዎችን ለማስተማር ጥያቄን ይጠቀማል፡፡ ይህ ማለት ማንም በጭንቀት ረጅም እድሜ መኖር የሚችል የለም፡፡ ( ተመልከት) አንድ ክንድ “አንድ ክንድ” ከከግማሽ ሜትር ትንሽ የሚያንስ ነው፡፡በዚህ ሥፍራ ላይ ጥቅም ላይ የዋለው አንድ ሰው በእድሜው ላይ ምንም መጨመር እንደማይችል በምሳሌ ለመግለጽ ነው፡፡ ( እና ተመልከት) ስለምትለብሱት ነገር ስለምንት ትጨነቃላችሁ? ኢየሱስ ሰዎችን ለማስተማር ጥያቄን ይጠቀም ነበረወ፡፡ ኤቲ፡ “ምን እለብሳለሁ ብላችሁ አትጨነቁ፡፡” ( ተመልከት) ስለአንድ ነገር ማሰብ “መጨነቅ” አበቦች የሜዳ አበቦች ( ተመልከቱ) እላችኋለሁ ይህ ኢየሱስ ከዚህ በመቀጠል የሚናገረው ነገር አጽኖት ሊሰጠው የሚገባ መሆኑን ያሳያል፡፡ ማንም እንደነዚህ አግጦ አያውቅም ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እንደነዚህ የሜዳ አበቦች ያጌጠ ልብስ ማንም ለብሶ አያውቅም፡፡”
አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “እናንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ እነዚህ ሣሮች እንደዚህ ካለበሳቸው ይህ ምሳሌ እግዚአብሔር አበቦችን እንዲህ ውብ ካደረጋቸው ማለት ነው፡፡ ( ተመልከት) ሣር በቋንቋችሁ ሣር የሚለው ቃል የሚያካትት እና ከከዚህ በፊት የሜዳ አበባዎች ተብሎ የተተረጎመውን የሚያካትት ከተገኘ ያንን ቃል ተጠቀም፡፡ ወደ ማቃጠያ እቶን የሚጣለውን አይሁዳዊያን ምግባቸውን ለማብሰል ሣርን ይጠቀማሉ፡፡ ይህ በቀጥታ እንዲህ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ወደ ማቃጠያ ይጥለዋል” ወይም “አንድ ሰው እንዲቀጣል ያደርገዋል፡፡” ( ተመልከት) እናንተ ምን አያለብሳችሁም . . . እምነት? ኢየሱስ ሰዎችን ለማስተማር ጥያቄን ይጠቀም ነበር፡፡ ኤቲ፡ “በእርግጠኝነት ያለብሳችኋል . . . እምነት፡፡” ( ተመልከት) እናንተ እምነት የጎደላችሁ “እናንተ ትንሽ እምነት ያላችሁ፡፡” በእግዚአብሔር ላይ ያላቸው እምነት በጣም ትንሽ ከመሆኑ የተነሳ ኢየሱስ ሰዎችን ይገስጻቸዋል፡፡ ስለዚህ “እነዚህ ሁሉ ምክንቶች”
አሕዛብም እነዚህ ነገሮች ሁሉ ይፈልጋሉ “አሕዛብም ነገ ምን እንደሚበሉ፣ እንደሚጠጡ እና እንደሚለብሱ ይጨነቃሉ፡፡” በሰማይ ያለው አባታችሁ የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ ያውቃል ኢየሱስ በዚህ ንግግሩ ውስጥ በተዘዋዋር መልኩ የሚያስረግጠው ነገር መሠረታዊ ፍላጎቶቻችሁ በእግዚአብሔር በእርግጠኝነት ይሟላሉ፡፡ አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) በመጀመሪያ መግስቱን እና ጽድቁን ፈልጉ በዚህ ሥፍራ ላይ “መንግስቱ” የሚለው ቃል እግዚብሔር እንደ ንጉሥ መግዛቱን የሚያመለክት ነው፡፡ ኤቲ፡ “ንጉሥ የሆነውን እግዚአብሔርን አገልግል እንዲሁም መልካም የሆነውን ነገር አድርግ፡፡” ( ተመልከት) እነዚህ ሁሉ ነገሮች ይጨመሩልሃል ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር እነዚህ ነገሮች ያዘጋጅልሃል፡፡” ( ተመልከት) ስለዚህ “በእነዚህ ሁሉ ምክንቶች” tomorrow will be anxious for itself Jesus is describing "tomorrow" as if it is a person that can worry. Jesus means that a person will have enough to worry about when the next day comes. ነገ ስለራሱ ይጨነቅ በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ “ነገን” ልክ እንደ ሰው የሚጨነቅ አድርጎ ያቀርበዋል፡፡ ኢየሱስ አንድ ሰው ነገ ስመጣ በዚያ ቀን በቂ የሚጨነቅበት ነገር አለው ማለቱ ነው፡፡ ( ተመልከት) ለዛሬ የራሱ ክፋት ይበቃዋል “እያንዳንዱ ቀን በውስጡ በቂ የሆነ ክፋትን ይዟል” ወይም “ሁሉም ቀናት በቂ ችግሮች አሏቸው”
ጽድቃቸው በሰው ፊት እንዲታይላቸው የሚያደርጉ ሰዎች የሰዎችን ምስጋና መቀበል ዋጋቸው ይሆናል። [6:2]
ጽድቃችንን በስውር ማድረግ ይኖርብናል። [6:3]
ጽድቃችንን በስውር ማድረግ ይኖርብናል። [6:4]
በሰዎች ለመታየት ሲሉ በግብዝነት የሚጸልዩ ዋጋቸውን ከሰዎች ይቀበላሉ። [6:5]
በስውር የሚጸልዩ ዋጋቸውን የሚቀበሉት ከአብ ነው። [6:6]
ከንቱ ድግግሞሽን በማድረግ ልንጸልይ እንደማይገባን ኢየሱስ የተናገረው አብ የሚያስፈልገንን ሳንጠይቀው ስለሚያውቀው ነው። [6:7]
ፈቃዱ በሰማይ እንደሆነች፣ እንዲሁም በምድር እንድትሆን አብን ልንጠይቅ ይገባናል። [6:10]
የሌሎችን እዳ የማንተው ከሆነ፣ እግዚአብሔርም የእኛን አይተውልንም። [6:15]
እንደምንጾም ለሰዎች ሳንታይ ልንጾም ይገባናል፣ ከዚያም አብ ዋጋ ይከፍለናል። [6:16]
እንደምንጾም ለሰዎች ሳንታይ ልንጾም ይገባናል፣ ከዚያም አብ ዋጋ ይከፍለናል። [6:17]
ከዚያ ሊጠፋ ወይም ሊሰረቅ ስለማይችል መዝገባችንን በሰማይ ልናኖር ይገባናል። [6:19]
ከዚያ ሊጠፋ ወይም ሊሰረቅ ስለማይችል መዝገባችንን በሰማይ ልናኖር ይገባናል። [6:20]
መዝገባችን ባለበት ልባችን ይኖራል። [6:21]
ጌታችን ልናደርግ ከሁለት አንዳቸውን የምንመርጣቸው እግዚአብሔር ወይም ብልጥግና ናቸው። [6:24]
ስለ ምግብ፣ መጠጥ እና ልብስ መጨነቅ የሌለብን ለወፎች ግድ የሚለው አብ ከእነርሱ አብልጦ ለእኛ ግድ ስለሚለው ነው። [6:25]
ስለ ምግብ፣ መጠጥ እና ልብስ መጨነቅ የሌለብን ለወፎች ግድ የሚለው አብ ከእነርሱ አብልጦ ለእኛ ግድ ስለሚለው ነው። [6:26]
በእድሜያችን ላይ ተጨንቀን አንዲት ሰዓት ልንጨምር እንደማንችል ኢየሱስ አስታውሶናል። [6:27]
አስቀድመን የእግዚአብሔርን መንግሥት እና ጽድቅ ስንሻ፣ ከዚያም ምድራዊው ነገር ሁሉ ይጨመርልናል። [6:33]
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ በ in MAT 5:3 በተጀመረው የተራራው ስብከት ውስጥ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “እናንተ” የሚለው ቃል እና የተሰጡት ትዕዛዛት በብዙ ቁጥር ተገልጸዋል፡፡ ( ተመልትከት) አትፍረድ በዚህ ሥፍራ ላይ “አትፍረድ” የሚለው ቃል ጠንከር ያለ “ጠንከር ያለ ማውገዝን” ወይም “ጥፋተኛ አድርጎ መወሰንን” የሚያመለክት ቃል ነው፡፡ ኤቲ፡ “በሰዎችን ላይ አትፍረድ”፡፡ ( ተመልከት) አይፈረድብህም ይህ በግልጽ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “መጥፎ ፍርድ አይፈረድብህም፡፡” ( ተመልከት) Be sure the reader understands the statement in 7:2 is based on what Jesus said in 7:1. ምክንያቱም ኢየሱስ በ7፡2 ላይ የተናገረው ንግግር መሠረቱ በ7፡1ላይ የተናገረው መሆኑን እርግጠኞች ሁኑ፡፡ በፈረዳችሁት ፍርድ እናንተም ላይ እንዲሁ ይፈረዳል ይህ በዚህ መልኩ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “በሌሎች ሰዎች ላይ በፈረዳችሁበት መጥን ልክ እናንተም ላይ እግዚአብሔር ይፈርዳል፡፡” ( ተመልከት) በዚያው ልክ ይፈረዳል ይህ እንዲህ በቀጥታ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር በዚያው ልክ ይፈርዳል፡፡” ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “እንተ” የሚለው ቃል በነጠላ ቁጥር ተገልጸዋል ይን እንጂ በብዙ ቁጥር ልትተረጎማቸው ትችላለህ፡፡ ስለምን ታያለህ . . . እንዴትስ ትለዋለህ ኢየሱስ እነዚህን ሁሉት ጥያቄዎች የተጠቀመው ሰዎችን ለማስተማር እና አመለካከታቸውን እንደገና ይመለከቱት ዘንድ ነው፡፡ የሌሎች ሰዎች ኃጢአት ላይ ጣታቸውን ከመቀሰራቸው በፊት ለራሳቸውን ኃጢአት ትኩረት መስጠት ስለፈለገ ነው፡፡ ( ተመልከት) በጣም ትንሽ ብናኛ “ቆሻሻ”(UDB) ወይም “ብናኝ” ወይም “አፈር”፡፡ ወደ ሰዎች ዐይን ውስጥ ብዙ ጊዜ የሚገባን ነገር ለመግለጽ የሚትጠቀሙትን ቃል ተጠቀም፡፡ ይህ በሰዎች ውስጥ የሚያጋጥምም በጣም ትንሹን ስህተትን ለማመልከት ጥቅም ላይ የዋ ምሳሌ ነው፡፡ ( ተመልከት) ወንድም ይህ የሥጋ ወንድምን ወይም ጎረቤትን ሳይሆን አማኝን የሚያመለክት ነው፡፡ ምሰሶ አንድ ሰው በቆረጠው ዛፍ ውስጥ የሚገኘው ትልቁ ክፍል ምሰሶ ነው፡፡ ይህ ወደ ሰዎች ዐይን ለመግባት በጣም ትልቅ የሆነ ግንድ ነው፡፡ ይህ በሰው ሕይወት ውስጥ ያለ በጣም ትልቅ ስህተትን ያሳያል፡፡ እና ተመልከት)፡፡
አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “እናንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር ተገልጸዋል፡፡ ውሾች . . . እሪያዎች አይሁዶች እነዚህ እንስሳት ቆሻሾች አድርገው ይቆጥሯቨዋል እንዲሁም እግዚአብሔርም እነዚህን እንስሳት እንዳይበሉ አዞዋቸዋል፡፡ ይህ ቅዱስ ለሆነው ነገር ዋጋ የማይሰጡ ኃጢአተኛ ሰዎችን ለማመልከት የቀረበ ምሳሌያዊ አነጋገር ነው፡፡ ይህንን ቃል በቁሙ መተርጎሙ ባጣም ጥሩ ነው፡፡ ( ተመልከት)፡፡ እንቁዎች እነዚህ በጣም ትንንሽ፣ ውድ የሆኑ ድንጋዮች ናቸው፡፡ ይህ ስለእግዚአብሔር ወይም ስለውድ ነገሮች በአጠቃላይ ማወቅ ጋር ተያያዥነት ያለው ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ ( ተመልከት) በእግሮቻቸው ልረጋግጡት ይችላሉ “እሪያዎቹ ይረጋግጡታል” እናም ወደ ትፋታቸው ይመለሳሉ “እናም ውሾች ወደ ትፋታቸው ይመለሳሉ”
አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “እንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር ተገልጸዋል፡፡ ( ተመልከት)፡፡ ጠይቁ . . . ፈልጉ . . . አንኳኩ ይህ ወደ እግዚአብሔር መጸለይን ለማመልከት ጥቅም ላይ የዋለ ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ጥቅም ላይ የዋለው ግሥ እግዚአብሔር ምላሽ እስኪሰጠን ድረስ እንዲንጸለይ የሚያደርግ ነው፡፡ በቋንቋችሁ አንድን ነገር መልሳችሁ መልሳችሁ ማድረግ እንዳለባችሁ የሚገልጽ ቃል ካለ ይህንን ቃል ተጠቀሙ፡፡ ( ተመልከት) ጠይቁ ይህ ከእግዚአብሔር የሆነ ነገርን ጠይቁ ማለት ነው፡፡ (UDB) ይሰጣችኋል ይህ እንዲህ ባለ መልኩ በቀጥታ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “የሚያስፈልጋችሁን ነገር እግዚአብሔር ይሰጣችኋል፡፡ ( ተመልከት) ፈልጉ “ስለምትፈልጉትን ነገር የእግዚአብሔርን ፊት ፈልጉ” አንኳኩ በር ማንኳኳት በቤት ውስጥ ያለ ሰው በሩን እንዲከፍትላችሁ በትህትና መጠየቅ ነው፡፡ በእናንት ባሕል ውስጥ በር ማንኳኳት ትህትና ካልሆነ ሰዎች በእናንተ ባሕል ውስጥ በር እነንዲከፈትላቸው በትህትና የሚጠይቁ በምን ዓይነት መንገድ ነው፣ ይህንንም ቃል ተጠቀሙ፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር በሩን እንዲከፍትላችሁ እንደሚትልጉ ንገሩት፡፡” ወይም ከእናንተ መካከል ማን ነው . . . ድንጋይ? ኢየሱስ ሰዎችን ለማስተማር ጥያቄን ይጠቀማል፡፡ ኤቲ፡ “ከእናንተ መካከል ማንም የለም . . . ድንጋይ፡፡” ( ተመልከት) ቁራጭ ዳቦ ይህ በአጠቃላይ ምግብን ያመለክታል፡፡ ኤቲ፡ “የሆነ ምግብ፡፡” ( ተመልከት) ድንጋይ. . . ዓሳ . . . እባብ እነዚህ ስሞች በቁማቸው መተርጎም አለባቸው፡፡ ወይም ኣሳ ጠይቋችሁ እባብ የምትሰጡት? ኢየሱስ ለማስተማር ሌላ ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡ በዚህ ሥፍራም ኢየሱስ ስለ ሰውዬው እና ልጁ እየተናገረ መሆኑን መረዳት አስፈላጊ ነው፡፡ ኤቲ፡ “ከእናንተ መካከል ልጁ ዓሳ ጠይቆት እባብ የሚሰጠው ማንንም የለም፡፡” ( እና ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “እንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር ተገልጸዋል፡፡ ( ተመልከት)፡፡ በሰማይ ያለው አባታችሁ አስበልጦ ምን ያኽል አይሰጣችሁ . . . አርሱ? በዚህ ሥፍራ ኢየሱስ ሕዝቡን ለማስተማር ጥየቄን ተጠቀሟል፡፡ ኤቲ፡ “በሰማይ ያለው አባታችሁ በእርግጠኝነት ይሰጠዋል . . . እርሱ፡፡” ( ተመልከት) አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) ሰዎችን እንዲያደርጉላችሁ የሚትፈልጉትን ነገር ሁሉ “ሰዎች እንዲያደርጉላችሁ የሚትልጉትን ነገር ሁሉ” (UDB) ሕግ እና ነቢያት እነዚህ ናቸው በዚህ ሥፍራ ላይ “ሕግ” እና “ነቢያት” የሚለው ቃል ሙሴ እና ነቢያት የጻፏቸወ መጽሐፍትን ያመለክታል፡፡ ኤቲ፡ “ይህ ሙሴ እና ነቢያት የጻፉጽ ስለዚህ ጉዳይ ነው፡፡ ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ፡ ስለ ሁለቱ በሮች እና መንገዶች አጽኖት መስጠት ያስችለ ዘንድ ስትተረጉም “ሰፍ” የሚለው ቃል “ጠባብ” ከሚለው በተቻለ መጠን የሚለይ መሆኑን አሳይ፡፡ በጠባቢ በር ግቡ . . የሚገኙት ጥቂቶች ናቸው ይህ በመንገድ ላይ የሚሄድ እና ወደ መንግስቱ በበር የሚገባ ሰው ምስል ነው፡፡ ወደ አንደኛው መንግስት መግባት ቀላል ሲሆን ወደሌላኛው መንግስት መግባት ግን ከባድ ነው፡፡ ይህ ሰዎች የዘላለም ሕይወትን ለማግኘት ሰዎች ከባድ የሆነውን በሕይወታቸው እግዚአብሔርን መታዘዝ መቀበል እንደሚኖርባቸው ለማሳየት የቀረበ ምሳሌ ነው፡፡ እግዚአብሔር የተመታዘዝ ቀላሉን መንገድ ከመረጡ ወደ ስኦል ይገባሉ፡፡ ( ተመልከት) በጠባቢ በር ግቡ ይህንን ወደ ቁጥር 14 መጨረሻ ልትወስዱት ትችላላችሁ፡ “ስለዚህ በጠባቡ በር ግቡ”፡፡ በር . . . መንገድ አማራጭ ትርጉሞች 1) ይህ ወደ መንግስቱ መግቢያ በር እና ወደ በሩ የሚወስድ መንገድን ያመለክታል፡፡ ይህ ከሆነ በUDB ላይ ያለውን ቅደም ተከተል ልታለዋውጠው ትችላለህ፡፡ ወይም 2) “በር” እና “መንገድ” ሁለቱም የመንግስቱ መግቢያነ ናቸው፡፡ ይህ ከሆነ ቅደም ተከተሉን ማለዋወጥ አይኖርብህም፡፡ ( ተመልከት) ወደ ጥፋት . . . ወደ ሕይወት እነዚህ በግስ ልተረጎሙ ይችላሉ፡፡ ኤቲ፡ “ወደምትሞቱበት ሥፍራ . . . በሕይወት ወደሚትኖርቡት ሥፍራ” ( ተመልከት)
ተጠንቀቁ “ራሳችሁን ጠብቁ” የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡ ነገር ግን ተኩላዎች ከሆኑ ይህ ምሳሌያዊ አነጋገር መልካም እና መርዳት የሚፈልጉ መስለው የሚመጡ ነገር ግን ክፉ የሆኑ እና ከሚጎዷችሁ ሐሰተኛ ነቢያት ራሳችሁን ጠብቁ፡፡ ( ተመልከት) በፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ ይህ ምሳሌዊ ንግግር የሰውን ተግባር የሚያመለክት ነው፡፡ ኤቲ፡ “ዘፍ በፍሬው እንደሚታወቅ ሁሉ ሐሰተኛ ነቢያት በሥራቸው ይታወቃሉ፡፡” ( ተመልከት) ሰዎች ከኩርንችት. . . ይለቅማሉን ኢየሱስ ጥየቄን ሰዎችን ለማስተማር ተጠቅሟል፡፡ ሰዎች ለዚህ ጥያቄ ምላሱ አይ መሆኑን ማወቅ አለባቸው፡፡ ኤቲ፡ “ሰዎች ከኩርንችት . . . አይለቅሙም፡፡” ( ተመልከት) መልካም ዛፉ ሁሉ መልካ ፍሬን ያፈራል ኢየሱስ የፍሬን ምሳሌ በመጠቀም ጥሩ ሥራ ወይም ቃል ስለሚያመጡ ስለጥሩ ነቢያት መናገሩን ቀጥሏል፡፡ ( ተመልከት) የተበላሸ ዘፍ መጥፎ ፍሬ ያፈራል ኢየሱስ የፍሬን ምሳሌ በመጠቀም መጥፎ ሥራ ስለሚሠሩ መጥፎ ነቢያት መናገሩን ቀጥሏል፡፡ ( ተመልከት)
መልካምን ፍሬ የማያፈራውን ዘፍ ይቆረጣል እንዲሁም ወደ እሳት ይጣላል ኢየሱስ የፍሬውን ምሳሌ ሐሰተኛ ነቢያትን ለማመልከት ተጠቅሞዋል፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ በመጥፎ ዛፍ ላይ ምን እንደሚሆን ብቻ ተናግሯል፡፡ ይህ በተዘዋዋር መንገድ የሚያሳየው በሐሰተኛ ነቢያት ላይ ተመሳሳይ ነገር ነው፡፡ ( እና ተመልከት) ይቆረጣል፣ ወደ እሳትም ይጣላል ይህ በዚህ መንገድ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ይቆርጡትና ያቃጥሉታል፡፡ “ ( ተመልከት) በፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ “እነርሱን” የሚለው ቃል ነብያቱን ወይም ዛፎቹን ሊያመለክት ይችላል፡፡ የዛፉ ፍሬ እና የነቢያቱ ድርጊት የሁለቱም መልካ ወይም መጥፎ ሊሆን ይችላል፡፡ ከተቻለ ከሁለቱ አንዱን በሚያመለክት መልኩ ተርጉሙት፡፡ ( ተመልከት)
ወደ መንግስተ ሰማያት ይገባል በዚህ ሥፍራ ላይ “መንግስት” የሚለው ቃ እግዚአብሑር እንደ ንጉሥ መግዛቱን ያመለክታል፡፡ “መንግስተ ሰማያት” በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ ብቻ ጥቅም ላይ የዋለ ቃል ነው፡፡ ከተቻለ “ሰማይ” የሚለውን ቃል በትርጉማችሁ ውስጥ ለማኖር ጥረት አድርጉ፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ራሱን እንደ ንጉሥ በሚገልጥበት ጊዜ በሰማይ ከእግዚአብሔር ጋር ይኖራል፡፡” ( ተመልከት) የአባቴን ፈቃድ የሚያደረግ ማንኛውም ሰው “የአባቴን ፍላጎት የሚፈጽም ማንም ሰው” አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) በዚያ ቀን ኢየሱስ “በዚያ ቀን” በማለት የተናገረው አድማጮቹ በዚያ ቀን የሚለው ሀረግ የሚያመለክተው የፍርድ ቀንን እንደሆነ እንደሚገባቸው ታሳቢ በማድረግ ነው፡፡ አንባቢዎቻችሁ በግልጽ በዚያ ቀን የሚለው ሀረግ ትንቢት አልተናገርንምን . . . ሴጣንን አላወጣንምን . . . ብዙ ተዓምራትን አላደረግንምን? ሰዎች እነዚህ ነገሮች ማድረጋቸው ላይ ትኩረት ያደርጋሉ፡፡ ኤቲ፡ “ትንቡትን ተናግረናል . . . ሴጣንን አስወጥተናል . . . ታላላቅ ተዓምራን አድርገናል፡፡” ( ተመልከት) እኛ ይህ “እኛ” የሚለው ቃ ኢየሱስን አያካትትም፡፡ ( ተመልከት) በስምህ በዚህ ሥፍራ ላይ “በስምህ” የሚለው ቃል በኢየሱስ ስልጣን እና ስም” ማት ነው፡፡ ( ተመልከት) ታላላቅ ነገሮችን “ተዓምራትን” አላውቃችሁም ይህ ማለት ይህ ሰው የኢየሱስ አይደለም ማለት ነው፡፡ ኤቲ፡ “አንተ የእኔ ተከታይ አይደለህም” ወይም “ከአንተ ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የለኝም፡፡” ( ተመልከት)
ስለዚህ “በዚህ ምክንያት” ቃሎቼ በዚህ ሥፍራ ላይ “ቃሎቼ” የሚለው ቃል ኢየሱስ የተናገራውን ቃላት ያመለክታል፡፡ ( ተመልከት) በዓለት ላይ ቤትን የሠራን ጠቢብ ሰው ይመስላሉ ኢየሱስ የእርሱን ቃል የሚጠብቁ ሰዎችን ምንም ነገር ልጎዳው በማይችል መሠረት ላይ ቤታውን ከሠሩ ሰዎች ጋር ያነጻጽራል፡፡ ( ተመልከት) ዓለት ይህ በመሬት የላይኛው ክፍል ላይ ከመገኘው አፈር እ አሸዋ ቀጥሎ የሚገኝ ነው፡፡ በዚህ ላይ ቤቱን የገነባ ይህ በቀጥታ እንዲህ ልገለጽ ይገባል፡፡ ኤቲ፡ “የገነባው” ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ በ MAT 5:3. የተጀመረው የኢየሱስ የተራራው ስብከት መጨረሻ ነው፡፡ ሞኝ ሰው ቤቱን በአሸዋ ላይ ይሠራል ኢየሱስ ከዚህ በፊት ያቀረበውን ንጽጽር ቀጥሏል፡፡ ትዕዛዛቱን ያልታዘዙ ሰዎችን ቤታቸውን በአሸዋ ላይ ከሠሩ ሞኝ ሰዎች ጋር አነጻጽሯል፡፡ ቤቱን ዝናብ፣ ጎርፍ እና አውሎ ንፋስ ልያጠፋው በሚችል አሸዋማ መሬት ላይ የሚሠራ ሞኝ ሰው ብቻ ነው፡፡ ( ተመልከት) ወደቀ በቋንቋችሁ አንድ ቤት መውደቁን ለመግለጽ የሚትጠቀሙትን የተለመደ ቃል በዚህ ሥፍራ ላይ ተጠቀሙ፡፡ ጥፋቱ እጅግ በጣም የከፋ ይሆናል ዝናቡ፣ ጎር እና አውሎ ንፋሱ ቤቱን ፈጽሞ ያጠፋዋል፡፡
አጠቃላይ መረጃ እነዚህ ቁጥሮች ኢየሱስ በተራራው ስብከት ውስጥ ስላስተማራቸው ትመህርቶች የሰጠውን ምላሽ ምን ይህንን ከፈጸመ በኋላ ይህ ሀረግ የተራራው ስብከት መጨረሻ ለመሆኑ ምልክት ነው፡፡ ኤቲ፡ በመጨረሻውም” በትምህርቱ እጅግ በጣም ተገረሙ በ7፡29 ላይ ኢየሱስ ባስተማረው ትምህርት ብቻ ሳይሆን ባስተማረበት መንገድም እንደተገረሙ በግልጽ ማየት ይቻላል፡፡ ኤቲ፡ “በማስተማር ዘዴውም እጅግ በጣም ተገረሙ፡፡”
ራሳችንን መፈተሽ እና ወንድማችንን ከመርዳታችን በፊት በዐይናችን ውስጥ ያለውን ግንድ ልናስወግድ ይገባናል። [7:3]
ራሳችንን መፈተሽ እና ወንድማችንን ከመርዳታችን በፊት በዐይናችን ውስጥ ያለውን ግንድ ልናስወግድ ይገባናል። [7:4]
ራሳችንን መፈተሽ እና ወንድማችንን ከመርዳታችን በፊት በዐይናችን ውስጥ ያለውን ግንድ ልናስወግድ ይገባናል። [7:5]
ቅዱስ የሆነውን ለውሾች ከሰጣችሁ፣ ሊረግጡት እና ነክሰው ሊቦጫጭቋችሁ ይችላሉ። [7:6]
ከአብ ለመቀበል ልንጠይቅ፣ ልንፈልግ እና ልናንኳኳ ይገባናል። [7:8]
እግዚአብሔር ለሚጠይቊት መልካም ነገሮችን ይሰጣቸዋል። [7:11]
ሰዎች እንዲያደርጉልን እንደምንፈልግ እኛም እንድናደርግላቸው ህግ እና ነብያት ያስተምራሉ። [7:12]
ሰፊው መንገድ ወደ ጥፋት ያመራል። [7:13]
ሰፊው መንገድ ወደ ጥፋት ያመራል። [7:14]
ጠባቡ መንገድ ወደ ሕይወት ያመራል። [7:14]
ሐሰተኛ አስተማሪዎችን የምንለያቸው በሕይወታቸው ፍሬ ነው። [7:15]
ሐሰተኛ አስተማሪዎችን የምንለያቸው በሕይወታቸው ፍሬ ነው። [7:16]
የአብን ፈቃድ የሚያደርጉት ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባሉ። [7:21]
“ከቶ አላወቅኋችሁም! ከፊቴ ዘወር በሉ እናንተ ክፉዎች!” ይላቸዋል። [7:22]
“ከቶ አላወቅኋችሁም! ከፊቴ ዘወር በሉ እናንተ ክፉዎች!” ይላቸዋል። [7:23]
የኢየሱስን ቃሎች ሰምቶ የሚታዘዛቸው ልክ እንደ ብልኅ ሰው ነው። [7:24]
የኢየሱስን ቃሎች ሰምቶ የማይታዘዛቸው ልክ እንደ ሰነፍ ሰው ነው። [7:26]
ጸሐፍት እንደሚያስተምሩት ሳይሆን፣ ኢየሱስ ያስተማራቸው እንደ ባለሥልጣን ነበር። [7:29]
አጠቃላይ መረጃ፡ ይህ በታሪክ ውስጥ ኢየሱስ ብዙ ሰዎችን የፈወሰበት የአዲሱ ክፍል ጅማሬ ነው፡፡ ይህ ጭብጥ በእነዚህ ውስጥ ይቀጥላል MAT 9:35. ( ተመልከት) ኢየሱስ ከተራራ በወረደ ጊዜ ብዙ ሕዝብ ተከተለው “ኢየሱስ ከተራራ ከወረደ በኋላ ብዙ ሕዝብ ከተለው፡፡” ይህ ሕዝብ በተራራው ከእርሱ ጋር የነበሩትን እንዲሁም ያልነበሩትንም ሊያካትት ይችላል፡፡ እነሆ “እነሆ” የሚለው ቃል በታሪክ ውስጥ አዲስ ሰውን ያስተዋውቀናል፡፡ በቋንቋችሁ ይህንን የሚታደርጉበት ቃል ሊኖራችሁ ይችላል፡፡ ለምጻም “ለምጽ ያለበት ሰው” ወይም “የቆዳ በሽታ ያለበት ሰው፡፡” (UDB) በፊቱ ሰገደ ይህ በኢየሱስ ፊት ያሳየው ትህትና የሞላበት አቀራረብ ምልክት ነው፡፡ ( ተመልከት) ፈቃደኛ ከሆንክ “ከፈለግህ” ወይም “ፍላጎት ካለህ”፡፡ ለምጻሙ ሰው ኢየሱስ እርሱን የመፈወስ ኃይል እንዳለው አውቋል ይሁን እንጂ ኢየሱስ እርሱን ለመንካት ፈቃደኛ ይሁን አይሁን ግን አላወቀም፡፡ ልታነጻኝ ትችላለህ በዚህ ሥፍራ ላይ “ልታነጻኝ” የሚለው ቃል መፈወስን እና በማሀህበረሰቡ ውስጥ እንደገና ተቀላቅሎ መኖርን የሚያመለክት ቃል ነው፡፡ ኤቲ፡ “ልትፈውሰኝ ትችላለህ” ወይም 1እባክህ ፈውሰኝ”፡፡ (UDB) ( ተመልከት) ወዲያው “በዚያን ጊዜ” ከለምጹ ነጻ “ንጻ” የሚለው የኢየሱስ ንግግር ውጤቱ የሰውዬው መፈወስ ነው፡፡ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ጤነኛ ሆነ” ወይም “ለምጹ ለቀቀው” ወይም “ከለምጹ ነጻ”፡፡ ( ተመልከት)
ለእርሱ ይህ ኢየሱስ የፈወሰውን ሰው ያመለክታል፡፡ ለማንም አትናገር “ለማንም ምንም አትናገር” ወይም “እኔ እንደፈወስኩህ ለማንም አትናገር” ለካህናት ራስህን አሳይ የአይሁዳዊያን ሕግ የተፈወሰ ሰው ቆዳውን ለካህናት ማሳየት እንዳለበት ይጠይቃል፡፡ እነርሱም ቆዳውን ከተመለከቱ በኋላ ከሕዝቡ ጋር እንዲቀላቀል ይፈቅዱለታል፡፡ ( ተመልከት) ለእርሱ ምስክር ይሆንህ ዘንድ በሙሴ ትዕዛዝ መሠረት መስዋዕትን አቅርብ በሙሴ ሕግ መሠረት ከለምጽ የተፈወሰ ሰው የምስጋና መስዋዕትን ለከካህናት ማቅረብ ይኖርበታል፡፡ ካህናቱ ስጦታውን ከተቀበሉ ሕዝቡ ይህ ሰው መፈወሱን ያውቃሉ፡፡ ( ተመልከት) ለእነርሱ ይህ የሚያመለክተው 1) ካህናትን ወይም 2) ሌሎች ሰዎችን ወይም 3) ኢየሱስን የሚተቹ ሰዎችን ሊሆን ይችላል፡፡ ከተቻለ ከእነዚህ ቡድኖች መካከል ዬትኛውንም የሚያመለክትን ስም ተጠቀሙ፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ የታሪኩ ክፍል ውስጥ ጸሐፊው ወደሌላ ጊዜ እና ቦታ በመሄድ ኢየሱስ ሌላ ሰው የፈወሰበትን ሁኔታ ያሳያል፡፡ ወደ እርሱ መጥቶ ጠየቀው “በዚህ ሥፍራ “እርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው፡፡ ሽባ “ከበሽታው የተነሳ ከቦታ ቦታ መዘዋወር የማይችል” ኢየሱስም እንዲህ አለው፡፡ “ኢየሱስ ለመቶ አለቃው እንዲህ አለው” መጥቼ እፈውሰዋለሁ “ወደ ቤትህ መጥቼ ባርያህን አድነዋለሁ፡፡”
ወደ ቤቴ ጣሪያ ሥር ግባ “”የቤቴ ጣሪያ ሥር” የሚለው ሀረግ “ቤቴ” ማለት ነው፡፡ ( ተመልከት) ቃል ተናገር በዚህ ሥፍራ “ቃል” የሚለው ቃል ትዕዛዝ ስጥ ማለት ነው፡፡ ኤቲ፡ “ትዕዛዝ ስጥ”፡፡ ( ተመልከት) ይፈወሳል ይህ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ይድናል፡፡” ( ተመልከት) በስልጣን ሥር ያለ ይህ በዚህ መልኩ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “በሌላ ሰው ሥልጣን ሥር ያለ ማንኛውም ሰው፡፡” ( ተመልከት) በሥልጣን ሥር . . . በእኔ ሥር በአንድ ሰው “ሥር” መሆን ማለት የሌላ ሰው ትዕዛዝ እንደሚበልጥ በማወቅ ትዕዛዙን መቀበል፡፡ ( ተመልከት) ወታደሮች “የሰለጠኑ ተደባዳቢዎች” እውነት እልሃለሁ “እውነት እልሃለሁ፡፡” ይህ ሀረግ ኢየሱስ በቀጣይነት የሚናገረው ነገር ላይ ትኩረት እንዲደረግ ይጋብዛል፡፡ እንዲህ ዓይነት እምነት በእስራኤል እንኳ አላገኘሁም የኢየሱስ አድማጮች የእግዚአብሔር ልጆች እንደሆኑ የሚያስቡት በእስራኤል ያሉ አይሁዳዊያን ከማንም ይልቅ ታላቅ የሆነ እምነት እንደሚኖራቸው ያስቡ ነበር፡፡ ኢየሱስ ግን ተሳስተዋል በማለት ተናግሯል፡፡ የመቶ አለቃው እምነት ከሁሉ ታላቅ ነበር፡፡ ( ተመልከት)
አንተ በዚህ ሥፍራ ላይ “አንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥርን የሚያመለክት ሲሆን “እርሱን የሚከተሉትን ሰዎችን” ነው፡፡ MAT 8:10. (: ተመልከት) ከምስራቅ እና ከምዕራብ ተቃራኒ የሆኑትን “ምቅራቅ” እና “ምዕራብ”ን በመጠቀም “በሁሉም አከባቢ” የሚል መልዕክት አስተላልፏል፡፡ ኤቲ፡ “በሁሉም አከባቢ” ወይም “በሁሉም አቅጣጫ ከሩቅ ሥፍራ” ( ተመልከት) በማዕድ ይቀመጣሉ በዚያ ባሕል ውስጥ ያሉ ሰዎች ምግብ በሚመገቡበት ወቅት በጠረጴዛ ዙሪያ ይቀመጣሉ፡፡ ይህ ሀረግ የሚያመለክተው በጠረጴዛው ዙሪያ የሚቀመጡት ቤተሰብ እና የቅርብ ጓደኞች ናቸው፡፡ ኤቲ፡ “እንደ ቤተሰብ ከዳኞች ጋር መኖር”፡፡ ( ተመልከት) በመንግስተ ሰማያት በዚህ ሥፍራ “መንግስት” የሚለው ቃል እግዚአብሔር እንደ ንጉሥ የሚገዛበትን የሚያመለክት ነው፡፡ “መንግስ ሰማያት” የሚለው ሀረግ ጥቅም ላይ የዋለው በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ ብቻ ነው፡፡ ከተቻለ “ሰማይ” የሚለውን ቃል በትርጉማችሁ ውስጥ ላማስቀመት ሞክሩ፡፡ ኤቲ፡ “በሰማይ ያለው አምላካችን ንጉሥ መሆኑን በሚሳይበት ጊዜ፡፡” ( ተመልከት) የመንግስቱ ለልጆች ይጣላሉ ይህ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር የመንግስቱን ልጆች አውጥቶ ይጥላቸዋል፡፡” ( ተመልከት) የመንግስ ልጆች “የ. . . ልጆች” የሚለው ሀረግ የሚያመለክተው የእርሱ የሆኑት ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ የእግዚአብሔር መንግስት የሆኑት ማለት ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በዚህ ሥፍረ ምጸታዊ ንግግር አለ ምክንያቱም እንግዶች ወደ መንግስቱ እንዲገቡ ሲደረግ “ልጆች” ወደ ውጪ ይጣላሉ፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ይገዛቸው ዘንድ የፈቀዱለት”፡፡ ( እና ተመልከት) ወደ ውጭ ጨለማ ይህ እግዚአብሔርን ያልተቀበሉት ዘላለማዊ መዳረሻቸው ምን እንደሆነ የሚያሳይ ነው፡፡ ኤቲ፡ “ከእግዚአብሔር የራቀ ጨለማ ሥፍራ” ወይም “ስኦል”፡፡ ( ተመልከት) ለእናንተ ይሆን ዘንድ ይህ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ለእናንተ አደርገዋለሁ፡፡” ( ተመልከት) ባሪያው ተፈወሰ ይህ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ኢየሱስ ባሪያወን ፈወሰ፡፡” ( ተመልከት) በዚያው ሰዓት “ኢየሱስ ባሪያውን እፈውሰዋለሁ ብሎ በተናገረበት ቅጽበት”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ጸሐፊው ታሪኩን ወደ ሌላ ጊዜ እና ቦታ በመቀየር ኢየሱስ ሌላ ሰው የፈወሰበትን ሁኔታ ያሳየናል፡፡ ኢየሱስ መጥቶ ደቀ መዛሙርቱ ምናባት ከእርሱ ጋር ልሆኑ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን የታሪኩ ዋና ትኩረት ኢየሱስ ስላደረገው እና ሰስለተናገረው ነገር ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ደቀ መዛሙርቱን የጠቀሰበት ምክንት የተሳሳተ ትርጉም እንዳይኖር በማለት ነው፡፡ የጴጥሮስ አማች “የጴጥሮስ ምስት እናት” ንዳዱ ትቷት ሄደ በቋንቋችሄ እንዲህ ያለ ሰውኛ የአጻጻፍ ስልት ማለትም ንዳድ በራሱ አስቦ አንድን ነገር እንደሚፈጽ የሚሳይ ሰውኛ የአነጋገር ስልት ካለ “ተሸለት” ወይም “ኢየሱስ ፈወሳት” ተብሎ ልተረጎም ይችላል፡፡ ( ተመልከት) ተነስታ “ከተኛችበት አልጋ ተነስታ”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር› በዚህ ሥፍራ የታሪኩ ፍሰት በዚያው ቀን ምሽት ላይ ኢየሱስ ብዙ ሰዎችን ወደ ፈወሰበት እና ሴጣንን ከብዙ ሰዎች ወደአወጣበት ታርክ ይዞራል፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጥር 17 ላይ ጸሐፊው የኢየሱስ የፈውስ አገልግሎቱን በነብያት የተነገው ትንቢት ፍጻሜ መሆኑን ከነብዩ ኢሳያስ መጽሐፍ ውስጥ በመጥቀስ ጽፏል፡፡ በመሸም ጊዜ ይህ ከሰንበት በኋላ መሆኑን ያሳያል ምክንያቱም አይሁዳዊየን በሰንበት ቀን ሥራ አይሠሩም ወይም መንገድ አይሄዱም፡፡ እስኪመሽ ድረስ ጠብቀው ሰዎችን ወደ ኢየሱስ አመጡ፡፡ የተሳሳተ ትርጉምን ከማስወገድ አንጻር ካልሆነ በስተቀር ሰንበት የሚለው ቃል መጥቀሱ አስፈላጊ አይደለም፡፡ ( ተመልከት) በዳብሎ የተያዙ ብዙ ሰዎችን ወደ እርሱ አመጡ ይህ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ብዙ በዳብሎስ የተያዙ” (UDB) ወይም “በዳብሎስ ቁጥር ሥር የሆኑ ብዙ ሰዎች” ( ተመልከት) በቃሉ መናፍስቱን አስወጣ በዚህ ሥፍራ “ቃል” የሚለው ቃል ትርጉሙ ትዕዛዝ ነው፡፡ ኤቲ፡ “መንፈሱ እንዲወጣ አዘዘ፡፡” ( ተመልከት) በነብይ ኢሳያስ የተነገረው ትንቢትን ይፈጽም ነበር ይህ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ነብዩ ኢሳያስ ለእስራኤል ሕዝብ የተናገረው የትንቢት ቃልን ኢየሱስ ፈጸመው፡፡ () ተመልከት) ድካማችን ተቀበለ ደዊያችንንም ተሸከመ ማቴዎስ ከነብዩ ኢሳያስ መጽሐፍ በዚህ ሥፍራ ላይ ጠቅሷል፡፡ እነዚህ ሁለቱ ሀረጋት በመሠረታዊ መልዕክታቸው ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ሁለቱም አጽኖት የሚሰጡት እርሱ ሁሉንም በሽታችንን ፈውሷል፡፡ ኤቲ፡ “የታመሙትን ፈውሷል እንዲሁም ደና አድርጓቸዋል፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ላይ ታሪኩ ኢየሱስ ልከተሉት ለሚፈልጉ ሰዎች የሰጠው ምላሽ ምን እንደሆነ ወደማሳየት ይሄዳል፡፡ አሁን በዚህ ሥፍራ ይህ ቃል ጥቅም ላይ የዋለው በዋናው ታርክ ውስጥ አዲስ ታሪክ መጀመሩን ለማሳየት ነው፡፡ ማቴዎስ በዚህ ሥፍራ ላይ የታሪኩን አዲስ ክፍል ይነግረናል፡፡ መመሪያዎች ሰጠ “ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አላቸው” ከዚያ ማለትም ኢየሰስ “መመሪያዎችን ከሰጠ በኋላ ነገር ግን ወደ ታንኳይቱ ከመግባቱ በፊት በዬትም ሥፍራ “በዬትኛውም ቦታ” ቀበሮዎች ጉድጓድ አላቸው እንዲሁም የሰማይ ወፎች ጎቾ አላቸው ቀበሮዎች ቀበሮዎች እንደ ውሻ ያሉ እንስሳት ናቸው፡፡ በጎጆዋቸው ውስጥ ያሉትን አእዋፋት እና ሌሎች ትንንሽ እንስሳትን ይበላሉ፡፡ ቀበሮዎች በእናንተ ዙሪያ የማይታወቁ ከሆነ እንደ ውሻ ያለ በማለት አጠቃላይ ቃልን ተጠቀሙ፡፡ ( ተመልከቱ) ጉድጋዶች ቀበሮዎች ለመኖሪያቸው የሚሆን ጉድጓድን ይቆፍራሉ፡፡ ቀበሮወችን ለማመልከት የተጠቀማችኋቸው እንስሳት የሚኖሩበትን ሥፍራ ግለጹ፡፡ የሰው ልጅ ኢየሱስ ስለ ራሱ እየተናገረ ነው፡፡ ( ተመልከት) ራሱን የሚያሳርፍበት ሥፍራ ይህ የመተኛ ሥፍራን ያመለክታል፡፡ ኤቲ፡ “የሚተኛበት የራሱ ሥፍራ የለውም፡፡” ( ተመልከት)
በመጀመሪያ አባቴን እንድቀብረው ፍቀድልኝ የሰውዬው አባት መሞቱን እና ወዲያው መቅበር እንዳለበት በእርግጠኝነት ማወቅ አይቻልም ወይም አባቱ እስኪሞት እና እስኪቀበር ድረስ ለረጅም ጊዜ መቀየት ይኖርበት አይኖርበት የሚታወቅ ነገር የለም፡፡ ዋናውን ነጥብ ይህ ሰው ኢየሱስን ከመከተሉ በፊት ሌላ አዲስ ነገር ማድረግ ይፈለጋል ማለት ነው፡፡ ሙታን ሙታናቸውን ይቀብሩ ዘንድ ተዋቸው በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ በቀጥታ የሞቲ ሰዎች ሌሎች የሞቱትን ይቅበሩ ማለቱ አይደለም፡፡ “ሙታን” የሚለው ቃል አማራጭ ትርጉሞች 1) በቅርብ ጊዜ ስለሚሞቱ ሰዎች የሚነገር ምሳሌያዊ አነጋገር ወይም 2) ኢየሱስን የማይከተሉ እና መንፈሳዊ ሞት የሞቱ ሰዎችን ለማመልከት የሚውል ሚሳሌያዊ አነጋገር፡፡ ዋናው ነጥብ ማንኛውም ኢየሱስን መከተል ለሚወድ ሰው ምንም ነገር ሊያዘገየው አይገባም፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ላይ የታሪኩ ፍሰት ኢየሱስ እና ደቀ መዛሙር የገሊላን ባሕር ሽሻገሩ የተነሳውን ማዕበል ኢየሱስ እንዴት ጸጥ እንዳደረገው ወደሚያሳይ ታሪክ ይለወጣል፡፡ ወደ ታንኳይቱ ገቡ “ወደ ተንኳ ገቡ” ደቀ መዛሙርቱ ተከተሉት ለ”ደቀ መዛሙር” እና “ተከተል” ለሚለው ቃል በ(MAT 8:21-22). ላይ የተጠቀምከውን ተመሳሳይ ቃላትን ተጠቀም፡፡ እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይራል፡፡ ኤቲ፡ “በድንገት”(UDB) ወይም “ያለምንም ማስጠንቀቂያ” ባሕሩም በታላቅ ማዕበል ተናወጠ ኤቲ፡ “ታላቅ ማዕበል ባሕሩን አናወጠው” በዚህም ምክንያት ታንኳይቱን ውሃ ሞላት ይህ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ስለዚህም ምክንያት ታንኳይቱን ውሃ ሞላት”፡፡ ( ተመልከት) ተነስ አድነን አሉት የዚህ ሀረግ አማራጭ ትርጓሜዎች 1) በመጀመሪያ ኢየሱስን ከተኛት ቀስቅሰው “አድነን” አሉት ወይም 2)ኢየሱስን እየቀሰቀሱት “አድነን” አሉት፡፡ እኛ . . . እኛ ይህ ቃል ሁሉን የሚያጠቃልል ወይም የማያጠቃልል አድርገን የሚንተረጉመው ከሆነ ሁሉን የሚያጠቃልል ቃልን ብንጠቀም መልካም ይሆናል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ምናልባት ኢየሱስ እነርሱን እና ራሱን ከትንኳይቱ መስጠም እንዲታደግ ያቀረቡት ጥያቄ ሊሆን ይችላል፡፡ ( ተመልከት) መሞታችን ነው “ልንሞት ነው”
ለእነርሱ “ለደቀ መዛሙርቱ” ለምን ፈራችሁ . . . እምነት? ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ጥያቄ በመጠየቅ ይገስጻቸዋል፡፡ ኤቲ፡ “ልትፈሩ አይገባም . . እምነት” ወይም “የምትፈሩበት አንዳች ምክንያት የለም . . . እምነት፡፡” ( ተመልከት) እናንተ ትንሽ እምነት ያላችሁ ይህንን በ MAT 6:30 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡ ንፋስን እና ባሕር የሚታዘዙለት ይህ ምን ዓይነት ሰው ነው? “ንፋስና ባሕር ይታዘዙታል! ምን ዓይነስ ሰው ነው? ይህ የደቀ መዛሙርቱን አግራሞት የሚያሳይ ጥያቄ ነው፡፡ ኤቲ፡ “ይህ ከሌሎች ሰዎች ሁሉ የተለየ ነው! ንፋስ እና ማዕበል ሳይቀር ይታዘዙታል!” ( ተመልከት) ንፋስ እና ባሕር ሳይቀር ይታዘዙታል ሰዎች ወይም እንስሳት ቢታዘዙት ወይም ባይታዘዙት ብዙም አያስደንቅም ነገር ግን ንፋስ እና ውሃ እርሱን መታዘዛቸው በጣም አስደናቂ ነገር ነው፡፡ ይህ በሰውኛ የቀረበው ሀሳብ ተፈጥሮአዊ ነገሮች ልክ እንደ ሰው ሰምተው ምላሽ መስጠጥ ይችላሉ፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ላይ ጸሐፊው ከዚህ በፊት ወደ ጀመረው ኢየሱስ በሽተኞችን ወደሚፈውስበት አገልግሎት ታሪኩ ተመልሶ እናገኘዋለን፡፡ በዚህ ታሪክ ውስጥ መጀመሪያ ላይ ኢየሱስ ሁለት በዳብሎስ እስራት ተይዘው የነበሩትን ሰዎች ነጻ ሲያወጣ እንመለከታለን፡፡ በዚያኛው በኩል “ከገሊላ ባሕር ማዶ” የጌርጋሴኖን ሀገር ጌርጋሴኖን የጌርጋ ከተማ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) እነርሱም ሰው በዚያ መንገድ ማለፍ እስኪሳነው ድረስ በጣም አስቸጋሪዎች ነበሩ እነዚህን ሁለት ሰዎችን የያዙት ዳብሎሶች በጣም አደገኞች ከመሆናቸው የተነሳ ማንም ሰው በዚያ በኩል ማለፍ አይችልም ነበር፡፡ እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይራል፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ ከአንተ ጋር ምን አለን? ይህንን ጥያቄ የጠየቁት በቁጣ ነበር፡፡ ( ተመልከት) የእግዚአብሔር ልጅ ይህ ኢየሱስ ከእግዚብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያሳይ የኢየሱስ ወሳኝ የሆነ መጠሪያ ስሙ ነው፡፡ ( ተመልከት) ጊዜው ሳይደርስ ልትሣቅየን ወደዚህ መጣህን? ሁለተኛው ጥያቄም ሰላማዊ የሆነ ጥያቄ አልነበረም፡፡ ትረጉሙም “እግዚአብሔር እኛን ለመቅጣት የወሰነው ጊዜ ሳይደርስ መጥተህ እኛን በመቅጣት እግዚአብሔርን መታዘዝ መተው የለብህም፡፡” ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ላይ ጸሐፊው ከዚህ በፊት ወደ ጀመረው ኢየሱስ በሽተኞችን ወደሚፈውስበት አገልግሎት ታሪኩ ተመልሶ እናገኘዋለን፡፡ በዚህ ታሪክ ውስጥ መጀመሪያ ላይ ኢየሱስ ሁለት በዳብሎስ እስራት ተይዘው የነበሩትን ሰዎች ነጻ ሲያወጣ እንመለከታለን፡፡ በዚያኛው በኩል “ከገሊላ ባሕር ማዶ” የጌርጋሴኖን ሀገር ጌርጋሴኖን የጌርጋ ከተማ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) እነርሱም ሰው በዚያ መንገድ ማለፍ እስኪሳነው ድረስ በጣም አስቸጋሪዎች ነበሩ እነዚህን ሁለት ሰዎችን የያዙት ዳብሎሶች በጣም አደገኞች ከመሆናቸው የተነሳ ማንም ሰው በዚያ በኩል ማለፍ አይችልም ነበር፡፡ እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይራል፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ ከአንተ ጋር ምን አለን? ይህንን ጥያቄ የጠየቁት በቁጣ ነበር፡፡ ( ተመልከት) የእግዚአብሔር ልጅ ይህ ኢየሱስ ከእግዚብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያሳይ የኢየሱስ ወሳኝ የሆነ መጠሪያ ስሙ ነው፡፡ ( ተመልከት) ጊዜው ሳይደርስ ልትሣቅየን ወደዚህ መጣህን? ሁለተኛው ጥያቄም ሰላማዊ የሆነ ጥያቄ አልነበረም፡፡ ትረጉሙም “እግዚአብሔር እኛን ለመቅጣት የወሰነው ጊዜ ሳይደርስ መጥተህ እኛን በመቅጣት እግዚአብሔርን መታዘዝ መተው የለብህም፡፡” ( ተመልከት)
አሁን ይህ ቃል ጸሐፊው የታሪኩን ቀጣይ ክፍል ከመተረኩ በፊት አንባቢዎቹ ማወቅ ያለባቸውን አንድ መረጃ እንደሚሰጣቸው ያሳያል፡፡ ኢየሱስ ወደዚያ ሥፍራ ከመምጣቱ በፊት አሳማዎች በዚያ ሥፍራ ነበሩ፡፡ ( ተመልከት) ካስወጣኸን ኤቲ፡ “ልታስወጣን ስለሆነ” እኛ ይህ ሁሉን አቀፍ ነው፤ ትርጉሙም ለአሳማዎች ብቻ ነው፡፡ ( ተመልከት) እነርሱ በሰውዬው ውስጥ ያለው እርኩስ መንፈስ እርኩስ መንፈሱም ከሰውዬው ውስጥ ወጥቶ ወደ አሳማዎቹ ገባ ኤቲ፡ “እርኩስ መንፈሱም ከሰውዬው ውስጥ ወጥቶ ወደ አሳማዎቹ ገባ” እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይራል፡፡ ከተራራወ አፋፍ ወደታች ሮጡ ኤቲ፡ “በፍጥነት ከተራራው አናት ወደታች ሮጡ” በውሃ ውስጥ ሞቱ ኤቲ፡ “በውሃ ውስጥ ወድቀው ሰመጡ”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ኢየሱስ በእርኩስ መንፈስ የተያዙ ሁለት ሰዎችን ኢየሱስ የፈወሰበት ታሪክ ማጠቃለያ ነው፡፡ አሳማዎች የሚያሰማሩ “አሳማዎችን የሚጠብቁ” በእርኩስ መንፈስ የተያዙት ሰዎች ምን እንደሆኑ ኤቲ፡ “በእርኩስ መንፈስ የተያዙትን እነነዚህ ሰዎች ለማገዝ ኢየሱስ ያደረገው ነገር” እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይራል፡፡ በሁሉም ከተሞች ይህ ማለት ብዙ ወይም አብዛኞቹ ሰዎች ማለት እንጁ ሁሉም ሰዎች ማለት የግድ አይደለም፡፡ ( ተመልከት) አከባቢ ኤቲ፡ “ከተማዋ እና በአካቢው ያሉት”
የተፈወሰው ለምጻም ወደ ካህን እንዲሄድ ኢየሱስ የነገረው ለእነርሱ ምስክርነት እንዲሆን ነበር። [8:4]
ወደ መቶ አለቃው ቤት ሄዶ አገልጋዩን እንደሚፈውስ ኢየሱስ ተናገረ። [8:7]
ኢየሱስ ወደ ቤቱ ይገባ ዘንድ እንደማይገባው፣ ቃል ብቻ መናገር እንደሚችልና አገልጋዩን እንደሚፈውስ ተናገረ። [8:8]
የመቶ አለቃውን ያክል እምነት ያለውን ሰው በእስራኤል እንኳን ከአንድም ሰው እንዳላገኘ ኢየሱስ ተናገረ። [8:10]
ብዙዎች ከምሥራቅና ከምእራብ መጥተው በመንግሥተ ሰማያት ገበታ ላይ እንደሚቀመጡ ኢየሱስ ተናገረ። [8:11]
የመንግሥተ ሰማያት ልጆች ወደ ውጫዊው ጨለማ እንደሚጣሉ ኢየሱስ ተናገረ። [8:12]
ኢየሱስ ወደ ጴጥሮስ ቤት በገባ ጊዜ የጴጥሮስን ዐማት ፈወሳት። [8:14]
ኢየሱስ ወደ ጴጥሮስ ቤት በገባ ጊዜ የጴጥሮስን ዐማት ፈወሳት። [8:15]
“እርሱ ደዌያችንን ተሸከመ፣ ሕመማችንንም ተቀበለ” የሚለው የኢሳይያስ ትንቢት ተፈጸመ። [8:17]
ቋሚ የሆነ ቤት እንደሌለው ኢየሱስ ተናገረ። [8:20]
ለደቀመዝሙሩ እንዲከተለው፣ ሙታን ሙታናቸውን እንዲቀብሩ እንዲተዋቸው ኢየሱስ ነገረው። [8:21]
ለደቀመዝሙሩ እንዲከተለው፣ ሙታን ሙታናቸውን እንዲቀብሩ እንዲተዋቸው ኢየሱስ ነገረው። [8:22]
ታላቅ ማእበል በባህር ላይ በተነሣ ጊዜ ኢየሱስ ተኝቶ ነበር። [8:24]
ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ “እናንት እምነት የጎደላችሁ ስለምን ትፈራችሁ?” አላቸው [8:26]
ደቀመዛሙርቱ በኢየሱስ የተደነቁት ነፋሳት እና ባህር ስለታዘዙት ነበር። [8:27]
እጅግ ኃይለኞች የነበሩትን ሁለት በአጋንንት የተያዙ ሰዎችን ኢየሱስ አገኛቸው። [8:28]
ጊዜው ሳይደርስ ኢየሱስ ሊያሰቃያቸው እንደመጣ አጋንንቱ አሳስቧቸው ተናገሩ። [8:29]
ኢየሱስ አጋንንቱን ባስወጣ ጊዜ፣ ወደ እርያ መንጋ ሄደው ገቡ፤ እርያዎቹም ወደ ባሕር ተጣድፈው ገቡ። [8:32]
ሰዎቹ አካባቢያቸውን ለቅቆ እንዲወጣ ኢየሱስን ለመኑት። [8:34]
ማቴዎስ 9፡1-2 አያያዥ ዓረፍተ ነገር ጸሐፊው በ MAT 8:1 የጀመረው ኢየሱስ ሰዎችን ከበሽታ የፈወሰበትን ታሪክ እንደገና ወደ መተረክ ተመልሷል፡፡ በዚህ ታሪክ ውስጥ ኢየሱስ ሽባውን ሰው እንዴት እንደፈወሰው ይተርካል፡፡ ኢየሱስ ወደ ታንኳይቱ ገባ ደቀ መዛሙርቱም ከእርሱ ጋር ሄደው ሊሆን ይችላል፡፡ ታንኳ ይህ ምናልባት በ MAT 8:23 ላይ የተገለጸው ታንኳ ሊሆን ይችላል፡፡ ግራ መጋባትን ለማስወገድ ከፈለግህ ብቻ ይህንን መግለጽ ትችላለህ፡፡ ወደ ገዛ ከተማው መጣ ኤቲ፡ “ወደመከኖርበት ከተማ” (UDB) እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይኖራል፡፡ እነርሱ . . . እነርሱ ይህ ሽባውን ሰው ወደኢየሱስ ያመጡትን ሰዎች ያመለክታል፡፡ ሽባውንም ሰው ሊያመለክት ይችላል፡፡ ልጅ ይህ ሰው በእርግጥ የኢየሱስ ልጅ አይደለም፡፡ ኢየሱስ በዚህ ሥፍራ ላይ በትህትና እያናገረው ነው፡፡ ይህ ሰዎችን ግራ የሚያጋባ ከሆነ እንዲህ በማለት ሊትተረጉመው ተትችላለህ “ወዳጄ ሆይ” ወይም “አንተ ጎበዝ” ወይም ከተውኑ ልትተው ትችላለህ፡፡ ኃጢአትህ ተሰሪያልሃለች ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ኃጢአትህን ሠሪዮልሃል” ወይም “ኃጢአትን ሠሪዬልሃለሁ” ( ተመልከት)
እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይኖራል፡፡ ከእነርሱ መካከል ይህ “ለእነርሱ ለራሳቸው” “በመካከላቸው” ወይም “እርስ በእርሳቸው”፣ “በራሳቸው አፍ” እግዚአብሔርን ይሳደባል እግዚአብሔር ብቻ ሊያደርጋቸው የሚችላቸው ነገሮች ኢየሱስ ማድረግ እችላለው እያለ ነው፡፡ የልባቸውን ሀሳብ አውቆ ኢየሱስ ሀሳባቸውን ያወቀው በልዕለ ተፈጥሮ ኃይል አማካኝነት ነው ወይም እርሱ በእርሳቸው ስነጋገሩ ተመልክቶ ነው፡፡ በልባችሁ ስለምን ክፋትን ታስባላችሁ? ኢየሱስ ይህንን የተናገረው ጸሐፊትን ለመገሰጽ ነው፡፡ ( ተመልከት) አንናተ . . . እናንተ እነዚህ ቃላት ብዙ ቁጥር አመልካች ናቸው፡፡ ( ተመልከት) ክፋት ይህ ግብረገባዊ ክፋት እንጂ ዝም ብሎ ስህተት አይደለም፡፡ ዬቱ ይቀላል . . . ተራመድ ኢየሱስ ጸሐፊዎችን ይህንን ጥያቄ በመጠየቅ ማስታወስ የፈለገው ነገር ሰውዬው ሽባ የሆነው በኃጢአቱ ምክንያት ነው፡፡ ስለዚህም ኃጢአቱ ይቅር ከተባለለት ሽባው ሰው መራመድ ይችላል ማለት ነው፡፡ ስለዚህም ኢየሱስ ኃጢአትን ይቅር ማለት እንደሚችል ጸሐፊት ያውቁ ዘንድ ይህን ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡ ለመናገር ቀላሉ ዬቱ ነው፤ “ኃጢአትህ ተሠረየችልህ” ወይስ “ተነሳና ተራመድ?” ብሎ መናገር ነው ኤቲ፡ ለመናገር ቀላሉ ዬቱ ነው፤ “ኃጢአትህ ተሠረየችልህ” ወይስ “ተነሳና ተራመድ” ብሎ መናገር ነው? Your sins are forgiven This can mean 1) "I forgive your sins" ኃጢአትህ ተሠረየችልህ ይህ ማለት 1) “ኃጢአትን ይቅር ብዬሃለሁ” (UDB) ወይም 2) “እግዚአብሔር ኃጢአትህን ይቅር ብሎልሃል”፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “አንተ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው በነጠላ ቁጥር ነው፡፡ ( ተመልከት) ታውቁ ዘንድ ነው ኤቲ፡ “አረጋግጥላችኋለሁ”፡፡ በዚህ ሥፍራ ለእናንተ የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው የብዙ ቁጥርን በሚያመለክት መልኩ ነው፡፡ ( ተመልከት) your...your These are singular. አንተ . . . አንተ ይህ ነጠላ ቁጥር ነው፡፡ ( ተመልከት) ወደ ቤትህ ሂድ ኢየሱስ ሰውዬውን ወደ ሌላ ቦታ እንዳይሄድ አልከለከለውም፡፡ ለሰውዬው ወደ ቤቱ የሜድ ዕድል ሰጠው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ኢየሱስ ሽባውን ሰው የፈወሰበት ታሪክ ማጠቃለያ ነው፡፡ ከዚያም ኢየሱስ ከቀረጥ ሰብሳቢዎች መካከል አንድ ሰውን የእርሱ ደቀ መዝሙር ይሆን ዘንድ ጠራው፡፡ ምሳጋና በ MAT 5:16 ላይ የተጠቀምከውን ተመሳሳይ ቃል በዚህ ሥፍራም ተጠቀም፡፡ እንዲህ ያለ ስልጣን ኃጢአትን የማስተሰረይ ስልጣን ማቴዎስ . . . እርሱ . . እርሱ የቤተ ክርስቲያን አባቶች በዚህ ሥፍራ ላይ የተጠቀሰው የማቴዎስ ወንጌል ጸሐፊ ማቴዎስ እራሱ ነው ይላሉ፡፡ ይሁን እንጂ በክፍሉ ውስጥ ያለው “እርሱ” የሚለው ቃል “እኔ” ወደሚለው እንዲንለውጥ የሚያደርገን ምንም ምክንያት የለም፡፡ እርሱም እንዲህ አለው “ኢየሱስ ለማቴዎስ እንዲህ አለው” ኢየሱስም በዚያ ስያልፍ ሳለ ይህ ሀረግ እነሆ በሚል ቃል በ MAT 9:8 የተጀመረው ታሪክ መግቢያን የሚያሳይ ነው፡፡ በቋንቋችሁ እንዲህ ማሳየት ከቻላችሁ ተጠቀሙበት፡፡ በዚያ ስያልፍ “መሄድ” የሚለውን ቃል ተጠቀሙ፡፡ ኢየሱስ ወደ ተራራ መውጣቱን ወይም ወደ ሸለቆ መውረዱን ወይም ወደ ቅፍረናሆም መሄዱን ወይም ከዚያ ሪቆ ለመሄድ መነሳቱን የሚገለጽ ምንም ነገር የለም፡፡ ተነሥቶም ተከተለው “ማቴዎስ ተነሣና ኢየሱስን ተከተለው”፡፡ የተከተለው ኢየሱስን እስከሚቀጥለው ሥፍራ ድረስ እንደተከተሉት ሰዎች ሳይሆን እንደ ደቀ መዝሙር ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ ይህ ታሪክ የተፈጸመው በቀራጩ ማቴዎስ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ቤት ይህ ምናልባትም የማቴዎስ ቤት ይሆናል፤ ነገር ግን የኢየሱስም ቤት ሊሆን ይችላል (“ከኢየሱስ እና ከደቀ መዛሙርቱ ጋር አብረው በሉ”፡፡ ግራ መጋባትን የሚፈጥር ከሆነ ብቻ ምንነቱን በመግለጽ አስቀምጡት፡፡ ፈሪሳዊያን ይህንን በተመለከቱ ጊዜ “ፈሪሳዊያን ኢየሱስ ከቀረጥ ሰብሳቢዎች እና ከኃጢአተኛ ሰዎች ጋር እየበላ እንደሆነ በተመለከቱ ጊዜ”
አጠቃላይ መረጃ፡ ይህ ታሪክ የተፈጸመው በቀራጩ ማቴዎስ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ኢየሱስም ይህንን በሰማ ጊዜ “ይህንን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ፈሪሳዊያን ኢየሱስ ስለምን ከቀራጮች እና ከኃጢአተኞች ጋር ይበላል ብለው የጠየቁትን ጥያቄን ያመለክታል፡፡ ጤነኞች ኤቲ፡ “ጤናማ የሆኑ ሰዎች” ( ተመልከት) ሐኪም “ዶክተር”(UDB) ታማሚዎች “ዶክተር የሚያስፈልጋቸው ታማሚዎች ናቸው” ይህ ምን ማለት እንደሆነ ሄዳችሁ አጥኑ ኤቲ፡ “የዚህን ትርጉም ምንነት ሄዳችሁ አጥኑ፡” ሂዱ “እናንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥርን ያመለክታል፡፡
አያያዥ ዓረፈተ ነገር የመጥቁ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ስለምን እንደማይጾሙ ጥያቄ አቀረቡ፡፡ አይጾሙም ጾም ማለት ምንም ነገር አለመብላት ማለት ነው፡፡ ምንም ዓይነት ጾም ባሌለባቸው አንዳንድ ባሕሎች ውስጥ “በቀጣይነት መብላት መቆም” ተብሎ ልገለጽ ይችላል፡፡ ( ተመልከት) የሠረግ ታዳሚዎች ኃዘንተኞች መሆን ይችላሉ . . . እነርሱ? የሠረግ ታዳሚዎች ሠርገኞቹ ከእነርሱ ጋር እያሉ እንድጾሙ የሚጠብቅባቸው ማንም የለም፡፡ ( ተመልከት) የሠርግ ታዳሚዎች ይህ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት የሚያመለክት ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ ( ተመልከት) ሠርገኛወ ገና ከእርሱ ጋር ነውና . . . ሠርገኛው ከእነርሱ ከተለየ በኋላ “ሠርገኛው” ኢየሱስ ነው፣ እርሱ ደግሙ አሁን ከእነርሱ ጋር ነው፡፡ ( ተመልከት) ሠርገኛው ከእነርሱ የሚወሰደብት ጊዜ ይመጣል ኤቲ፡ “የሆነ ሰው ሠርገኛውን ይወስደዋል፡፡” ይህ እንደሚገደል በምሰሌያዊ አነጋገር ስገለጽ ነው፡፡ ( ተመልከት) ያዝናሉ “ያለቅሳሉ” ወይም “ያዝናሉ”(UDB)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ላነሱት ጥያቄ መልስ መስጠቱን ቀጥሏል፡፡ ማንም በአረጀ ልብስ ላይ አዲስ እራፊ የሚሰፋ የለም የዚህ ምሳሌያዊ ንግግር ትርጉሙ አሮጌውን ባሕል የሚያው ሰዎች አዲሱን ለመቀበል አይጓጉም፡፡ ( ተመልከት) ልብስ “ልብስ” እራፊ የተቀደደ ልብስን ለመስፋት የሚሆን “አዲስ ቁራጭ ጨርቅ”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ለተየቁት ጥያቄ መልስ መስጠቱት ቀጥሏል፡፡ በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር ማንም የለም ኢየሱስ ይህንን ምሳሌያዊ አነጋገር የተጠቀመው ለዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ጥያቄ መልስ ለመስጠት ነው፡፡ ጥያቄያቸውም “እኛ እና ፈሪሳዊን እንጾማለን ነገር ነገር የአንተ ደቀ መዛሙርት ግን ስለምን አይጾሙም?” ( ተመልከት) የሚያኖር ማንም የለም ኤቲ፡ “የሚያኖር ማንም የለም” (UDB) ወይም “ሰዎች በጭራሽ አያስቀምጡም” አዲስ ወይን ኤቲ፡ “የወይን ጁስ”፡፡ ይህ ያልፈላ ወይንን ያመለክታል፡፡ ወይን በእናንተ አከባቢ የማይታወቅ ከሆነ ለፍራፍሬ አጠቃላይ ስም የሚውል ቃል ተጠቀሙ፡፡ ( ተመልከት) የአረጀ አቁማዳ ይህ ብዙ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለን አቁማዳ ያመለክታል፡፡ (ተመልከት) አቁማዳ ከእንስሳት ቆዳ የሚሠራ ከረጥት ነው፡፡ “የወይን መያዣ” ወይም “የቆዳ ከረጥት” ተብሎም ይጠራል፡፡ (UDB). ( ተመልከት) አቁማዳው ይፈነዳል አዲሱ ወይን ስፈላ አቁማዳው ይፈነዳል ምክንያቱም ከዚህ በላይ መለጠጥ ስለማይችል ነው፡፡ ( ተመልከት) ይጠፋል “ይበላሻል”(UDB) አዲስ አቁማዳ “አዲስ አቁማዳ” ወይም “አዲስ የወይን ከረጥት”፡፡ ይህ ከዚህ በፊት ጥቅም ላይ ውሎ የማያቅን አቆማዳ ያመለክታል፡፡ ( ተመልከቱ)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ታሪክ የሚጀምረው ኢየሱስ የአይሁድ አለቃነ ሴት ልጅ ከሞት ካስነሳ በበኋላ ነው፡፡ እነዚህ ነገሮች ይህ ኢየሱስ ለዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ስለ ጾም የሰጠውን መልስ የሚያመለክት ነው፡፡ እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይኖራል፡፡ ወድቀው ሰገዱለት ይህ በአይሁድ ባሕል መሠረት ለሰዎች አክበሮትን ማሳያ መንገድ ነው፡፡ ና እና እጅህን በእርሷ ላይ ጫን፤ ከዚያም በሕይወት ትኖራለች ይህ የአይሁድ አለቃ ኢየሱስ ሴት ልጁን ከሞት ለማስነሳት የሚያስችለው ኃይል እንዳለው ያምናል ማለት ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ኢየሱስ ወደ አይሁድ አለቃው ቤት በመሄድ ላይ ሳለ እንዴት አንዲትን ሴት እንደፈወሳት የሚገልጽ ታሪክ ነው፡፡ እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይኖራል፡፡ ከፍተኛ የደም መፍሰስ ኤቲ፡ “በከፍተኛ ሁኔታ ደም ይፈሳታል፡፡” የወር አበባዋ መምጫው ጊዜ እንኳ ሳይሆን ከማሕጸኗ ውስጥ ድም ይፈሳት ነበር፡፡ ይህንን ሁኔታ ለመግለጽ የሚያስችል ቃል በአንዳንድ ባሕሎች ውስጥ አለ፡፡ ( ተመልከት) ልብሶቹን መንካት ብችል እንኳ ደህና እሆናለሁ ኢየሱስ ብዙ ሰዎችን ፈውሷል፤ ከዚህች ሴት ይበልጥ ከፈተኛ በሽታ ውስጥ የሆኑትን ሰዎች እንኳ ፈውሷል፡፡ ( ተመልከት) ጨርቅ “መቀነት” ነገር ግን “ይልቁንም” ሴትቱ ይሆናል ብላ የጠበቀችው ነገር አልሆነም፡፡ ሴት ልጅ ይህች ልጅ የኢየሱስ ልጅ አይደለችም፡፡ ኢየሱስ በትህትና አናገራት፡፡ ይህ በሰዎች አእምሮ ውስጥ ግራ መገጋባትን የሚፈጥር ከሆነ “አንድ ወጣት” ወይም ሳይተረጎም ሊታለፍ ይችላል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ኢየሱስ የአይሁድ አለቃውን ሴት ልጅ ወደ ሕይወት ወደመለሰበት ታሪክ ይመራናል፡፡ የአለቃው ቤት ይህ የአይሁድ አለቃው ቤት ነው፡፡ እምቢልታ ይህ ረጅም የሆነ በአንድ በኩል እስትፋንስ እየተሰጠው ጥቅም ላይ የሚውል የሙዚቃ መሣሪያ ነው፡፡ የእምቢልታ ጠቻዋቾች “እምቢልታ የሚጫወቱ ሰዎች” ሂዱ በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ ለብዙ ሰዎች እየተናገረ ነው፡፡ ስለዚህ በቋንቋችሁ የብዙ ቁጥር አመልካች ቃልን ተጠቀም፡፡ ልጅቱ አልሞተችም አንቀላፍታለች እንጂ በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ የያዘው የቃላት ጫወታ ነው፡፡ ኢየሱስ በኖረበት ዘመን የሞተ ሰው ተኝቷል ብሎ መጥራት የተለመደ ነው፡፡ ይሁን ዘንጂ በዚህ ሥፍራ ሞታ የነበረችው ልጅ ልክ ተኝቶ እንደነበር ሰው ከሞት ተነሳች፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ኢየሱስ የአይሁድ አለቃውን ሴት ልጅ ወደ ሕይወት የመለሰት ታሪክ ማብቂያ ነው፡፡ አጠቃላይ መረጃ ቁጥር 26 ኢየሱስ ልጅቷን ከሞት የማስነሳቱ ውጤት ምን እንደሆነ ማጠቃለያ ሀሳብ ነው፡፡ ሕዝቡ ውጪ እንዲወጣ ካደረገ በኋላ “ኢየሱስ ሕዝቡን ወደ ውጪ ካስወጣ በኋላ” ወይም “የልጅቱ ቤተሰቦች ሕዝቡን ወደ ወጪ ካስወጣ በኋላ” ተነሽ “ከአልጋሽ ተነሽ”፡፡ በ MAT 8:15 ያለው ትርጉም ተመሳሳይ ነው፡፡ የዚህ ነገር ዜና በሀገሩ ሁሉ ተሰማ ይህ ሰውኛ አገላለጽ የዚህ ነገር ዜና መሰራጨቱን ያሳያል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንተያት አንዱ ለሌላኛው ሰው በመንገሩ ነው፡፡ ኤቲ፡ “በአከባቢው የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ ሰለተፈጠረው ነገር ሰሙ” (UDB) ወይም “የልጅቱን በሕይወት መኖር የተመለከቱ ሰዎች በዚያ አለባቢ ላሉ ሰዎች ሁሉ ማናገር ጀመሩ፡፡” ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ስለ ሁለት ዐይነ ስውራን ታሪክ የሚጀመርበት ነው፡፡ ኢየሱስ በዚያ ስያልፍ ሳለ ኢየሱስ አከባቢውን ለቆ ሲሄድ ስያልፍ ኢየሱስ ወደ ተራራ እየወጣ ወይም እየወረደ እንደሆነ ምንም ፍንጭ የለም፡፡ ስለዚህ “ሄደ” የሚል ጠቅለል ያለ ቃል መጠቀሙ ጥሩ ነው፡፡ የዳዊት ልጅ ኢየሱስ በቀጥታ የዳዊት ልጅ አይደለም፡፡ ስለዚህም እንዲህ ልተረጎም ይችላል “ከዳዊት ዘር የሆነው” (UDB)፡፡ ይሁን እንጂ “የዳዊት ልጅ” የሚለው የመስሑ የማዕረግ ስም ነው፡፡ see MAT 21:9 ተመልከት) እና እነዚህ ሰዎችም ምናበት ኢየሱስን ይህንኑ የማዕረግ ስሙን ታሳቢ በማድረግ ጠርተውታል፡፡ ወደ ቤትም በገባ ጊዜ ይህ ኢየሱስ ወደ ገዛ ቤቱ መግባቱን (UDB) ወይም በ MAT 9:10 ላይ የተጠቀሰውን ቤት ልያመለክት ይችላል፡፡ አዎን፥ ጌታ ሆይ ኤቲ፡ “አዎን ጌታዬ አንተ መፈወስ እንደሚትችል እናምናለን፡፡”
ዓይኖቻቸውን ዳሰሰ። ኢየሱስ የሁለቱንም ሰዎች ዐይኖች እንዴት በአንድ ጊዜ መዳሰስ እንደቻለ ግልጽ አይደለም ወይም በቀኝ እጁ የአንዱን ዐይን በሌላኛው እጁ ደግሞ የሌላኛውን ዐይን ዳስሶ ይሆናል፡፡ የግራ እጅ ብዙ ጊዜ ንጹሕ ላልሆነ ነገር እንደመዋሉ መጠን ኢየሱስ እነዚህን ሰዎች የፈወሳቸው ቀኝ እጂን ተጠቅሞ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ እየዳሰሳቸው ሳለ ቃል መናገር አለመናገሩ ወይም በመጀመሪያ መዳሰሱን ከዚያመ ቃል መናገሩን የሚታወቅ ነገር የለም፡፡ ዐይኖቻቸው ተከፈቱ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ዐይኖቻቸውን ፈወሰ” ወይም “ሁለቱ ዐይነ ስውራን መመልከት ቻሉ” ( ተመልከት) But "Instead." The men did not do what Jesus told them to do. ነገረ ግን “ይሁን እንጂ” እነዚህ ሰሰዎች ኢየሱስ እንዲያደርጉ የነገራውን ነገር አላደረጉም፡፡ ዜናውን አሰራጩት ኤቲ፡ “ምን እንደተደረገላቸው ለብዙ ሰዎች ተናገሩ”
አያያዥ ዐረፍተ ነገር ይህ ኢየሱስ በእርኩስ መንፈስ በመያዙ ምክያት መናገር የማይችለውን ሰው የፈወሰበት ታሪክ እና ለዚህ ፈውስ ሰዎች የሰጡት ምላሽ ታሪክ ነው፡፡ እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይኖራል፡፡ ዲዳ መናገር የማይችል ዲዳ ሰው ተናገረ ኤቲ፡ “ዲዳው ሰው ማናገር ጀመረ” ወይም “መናገር የማይችለው ሰውዬ መናገር ቻለ” ወይም “ዲዳ የነበረው ሰው መናገር ቻለ” ሕዝቡም ተገረሙ ኤቲ፡ “ሕዝቡም ተደነቀ” እንዲህ ያለ ነገር ታይቶም አይታወቅም “እንዲህ ዓይነት ሀገር ተደርጎ አይታወቅም” ወይም “ይህን ዓይነት ነገር ከዚህ በፊት ማንም ሰው አድርጎ አያውቅም” ማለት ሊሆን ይችላል፡፡ እርኩሳን መናስፍስት አስወጣ በዚህ ሥፍራ ላጥ “እርሱ” የሚለው የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ቁጥር 35 በ MAT 8:1 የተጀመረው ኢየሱስ በገሊላ የነረው የፈውስ አገልግሎት ታሪክ ማብቂያ ነው፡፡ (የታሪኩ ማብቂያ) አጠቃላይ መረጃ፡ ከቁጥር 36 ጀምሮ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን በማስተማር እርሱ እንዳደረገው ይስብኩና ይፈውሱ ዘንድ የላካቸው ታሪክ አዲስ የታሪኩ ክፍል ጅማሬ ነው፡፡ በሁሉም ከተሞች ኤቲ፡ “በብዙ ከተሞች” ( ተመልከት) ከተሞች . . . መንደሮች ኤቲ፡ “ትልልቅ መንደሮች . . . ትንንሽ መንደሮች” ወይም “ትልልቅ ከተሞች . . . ትንንሽ ከተሞች” ሁሉንም ዓይነት በሽታዎች እና ሕመሞች ኤቲ፡ “ሁሉንም በሽታዎች እና ሕመሞች”፡፡ “በሽታ” እና “ሕመም” ተቀራራቢ የሆኑ ነገሮች ይሁን እንዲ ከተቻለ በሁለት የተለያዩ ቃላት ቢተረጎሙ የተሸለ ነው፡፡ “በሽታ” አንድ ሰው እንዲታመም የሚያደርጉት ነገሮች ሲሆኑ፡፡ “በሽታ” ደግሞ በዚህ በሽታ ከመያዛችን የተነሳ የሚሰማን አካላዊ ድካም ወይም ሕመም ነው፡፡ እረኞች እንደሌላቸው በጎች ተቅበዝብዘዋል ኤቲ፡ “ሰዎቹ መሪ አልበራቸውም” ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ የመከርን ምሳሌ በመጠቀም ከዚህ በፊት ለነበረው የሕዝቡ ፍላጎት ደቀ መዛሙርቱ በምን ዓይነት መንገድ ምላሽ መስጠት እንዳለባቸው ነገራቸው፡፡ መከሩ ብዙ ነው ሠራተኞቹ ግን ጥቂቶች ናቸው ይህ ምሰሌያዊ ንግግር በእግዚአብሔር የሚያምኑ እና ወደ መንግስቱ የሚጨመሩ ሰዎች ቁጥር በእርሻ ማሳ ውስጥ በለ ሰብል በመመሰል ስ እግዚአብሔር ለሰዎች የሚናገሩ ሰዎችን በሠራተኞች በመመሰል ያነጻጽራል፡፡ የዚህ ምሳሌያዊ ንግግር ዋናው ነጥብ ስለ እግዚአብሔር የሚናገሩ በጣም ጥቂት ሰዎች ናቸው ነው፡፡ መከር ኤቲ፡ “የደረሰ ሰብል” ሠራተኞች “ሠራተኞች” ለመከሩ ጌታ ጸልዩ ኤቲ፡ “የመከሩ ባለቤት ወደሆነው ጌታ ጸልዩ”
አንዳንዶቹ ጸሐፍት ኢየሱስ እግዚአብሔርን እየሰደበ የመሰላቸው ለሽባው ሰው ኃጢአቱ እንደተሰረየለችለት ኢየሱስ ስለነገረው ነው። [9:3]
አንዳንዶቹ ጸሐፍት ኢየሱስ እግዚአብሔርን እየሰደበ የመሰላቸው ለሽባው ሰው ኃጢአቱ እንደተሰረየለችለት ኢየሱስ ስለነገረው ነው። [9:4]
አንዳንዶቹ ጸሐፍት ኢየሱስ እግዚአብሔርን እየሰደበ የመሰላቸው ለሽባው ሰው ኃጢአቱ እንደተሰረየለችለት ኢየሱስ ስለነገረው ነው። [9:5]
ለሽባው ሰው ኃጢአቱ እንደተሰረየችለት ኢየሱስ መናገሩ በምድር ላይ ኃጢአትን ለማስተሰረይ ሥልጣን እንዳለው ያሳያል። [9:5]
ለሽባው ሰው ኃጢአቱ እንደተሰረየችለት ኢየሱስ መናገሩ በምድር ላይ ኃጢአትን ለማስተሰረይ ሥልጣን እንዳለው ያሳያል። [9:6]
እንዲህ ያለውን ሥልጣን ለሰዎች በመስጠቱ ተደንቀው እግዚአብሔርን አመሰገኑ። [9:8]
ማቴዎስ ኢየሱስን ከመከተሉ በፊት ቀረጥ ሰብሳቢ ነበር። [9:9]
ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱ የበሉት ከቀረጥ ሰብሳቢዎች እና ኃጢአተኛ ሰዎች ጋር ነበር። [9:10]
ኃጢአተኞችን ወደ ንስሃ ለመጥራት እንደመጣ ኢየሱስ ተናገረ። [9:13]
ደቀመዛሙርቱ እንደማይጾሙ ኢየሱስ የተናገረው እርሱ ከእነርሱ ጋር ስላለ ነበር። [9:15]
ከእነርሱ በሚወሰድባቸው ጊዜ ደቀመዛሙርቱ እንደሚጾሙ ኢየሱስ ተናገረ። [9:15]
ብዙ ደም የሚፈስሳት ሴት ልብሱን ብቻ ብነካ እድናለሁ ብላ በማሰብ የኢየሱስን ልብስ ጫፍ ነካች። [9:20]
ብዙ ደም የሚፈስሳት ሴት ልብሱን ብቻ ብነካ እድናለሁ ብላ በማሰብ የኢየሱስን ልብስ ጫፍ ነካች። [9:21]
ብዙ ደም የሚፈስሳት ሴት የዳነችው በእምነቷ እንደሆነ ኢየሱስ ተናገረ። [9:22]
ልጅቷ እንዳልሞተች፣ ነገር ግን እንደተኛች ኢየሱስ በመናገሩ ሰዎቹ በኢየሱስ ላይ ሳቁበት። [9:24]
ልጅቷን ከሙታን የማስነሣቱ ዜና በክልሉ ሁሉ ናኘ። [9:26]
“የዳዊት ልጅ ሆይ ማረን!” እያሉ መጮኻቸውን ቀጠሉ። [9:27]
ሁለቱን ማየት የተሣናቸው ሰዎች ኢየሱስ የፈወሳቸው እምነታቸውን መሠረት አድርጎ ነው። [9:29]
ፈሪሳውያን አጋንንትን በአጋንንት አለቃ ያወጣል ሲሉ ከሰሱት። [9:34]
ኢየሱስ ለሕዝቡ ያዘነላቸው ተጨንቀው እና ግራ ተጋብተው ስለነበረ፣ ደግሞም እረኛ እንደሌላቸው በጎች ስለነበሩ ነበር። [9:36]
የመከሩ ጌታ ሠራተኞችን ወደ መከሩ እንዲልክ እንዲጸልዩ ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ ነገራቸው። [9:38]
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ኢየሱስ ዐሥራ ሁለት ደቀ መዛሙርቱን የእርሱን ሥራ ይሠሩ ዘንድ የለከበት ታሪክ መጀመሪያ ነው፡፡ የእርሱ የሆኑትን ዐሥራ ሁለቱን በአንድነት ጠርቶ ኤቲ፡ “የእረሱን ዐሥራ ሁለት ደቀ መዛሙርት ጠርቶ” ሥልጣንን ሰጣቸው በዚህ ክፍል ውስጥ የተሰጣቸው ስልጣን 1) እርሰኩስ መንፈስን ማስወጣት እንዲችሉ 2) በሽታን እና ደዌን ይፈውሱ ዘንድ እንደሆነ ክፍሉ በግልጽ እንደሚናገር እርግጠኞች ሁኑ፡፡ ማስወጣት ኤቲ፡ “እርኩስ መንፈስ እንዲወጣ ማድረግ” ሁሉንም ዓይነት በሽታዎች እና ሕመሞች ኤቲ፡ “ሁሉንም በሽታዎች እና ሕመሞች”፡፡ “በሽታ” እና “ሕመም” ተቀራራቢ የሆኑ ነገሮች ይሁን እንዲ ከተቻለ በሁለት የተለያዩ ቃላት ቢተረጎሙ የተሸለ ነው፡፡ “በሽታ” አንድ ሰው እንዲታመም የሚያደርጉት ነገሮች ሲሆኑ፡፡ “በሽታ” ደግሞ በዚህ በሽታ ከመያዛችን የተነሳ የሚሰማን አካላዊ ድካም ወይም ሕመም ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃዎች በዚህ ሥፍራ ላይ ጸሐፊው የዐሥራ ሁሉትን ሐዋሪያት ስም በመዘርዝር የኋላ ታሪክ መረጃ ይሰጣል፡፡ ( ተመልከት) መጀመሪያ በቅደም ተከተል እንጂ በደረጃ አይደለም ቀናተኛው የዚህ ቃል አንዱ ትርጉም ሊሆን የሚችለው 1) “ቀናተኛ”፡፡ አይሁዳዊያንን ከሮማዊያን አገዛዝ ነጻ ለማውጣት የሚፈልጉ ቡድች ውስጥ ያለን ሰው ያመለክታል፡፡ ኤቲ፡ “ታጋይ” ወይም “የሀገር ፍቅር ያለው” ወይም “የነጻነት ታጋይ”፡፡ ሌላኛው የቃሉ ትርጉም ሊሆን የሚችለው 2 “ቀናተኛ የሆነው”፡፡ ይህ እግዚአብሔር ይከብር ዘንድ ይቀና የነበረው እንደ ማለት ነው፡፡ ማቴዎስ ቀረጥ ሰብሳቢው “ቀረጥ ይሰበስብ የነበረው ማቴዎስ” እርሱን የካደው “ኢየሱስን የካደው”
ዓያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ለመስበክ ስሄድ ምን ማድረግ እንዳለባቸው እና ምን እንደሚያጋጥማቸው መመሪያ መስጠት መጀመሩን እንመለከታለን፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ ምንም እንኳ ቁጥር 5 የሚጀምረው ኢየሱስ ዐሥራ ሁለቱን ላካቸው በማለት ቢሆንም ኢየሱስ ይህንን መመሪያ የሰጣቸው እነርሱን ከመላኩ በፊት ነው፡፡ ( ተመልከት) እነዚህን ዐሥራ ሁለቱን ላካቸው ኤቲ፡ “ኢየሱስ እነዚህ ዐሥራ ሁለት ሰዎች ላካቸው” ወይም “ኢየሱስ የላካቸው እነዚህን ዐሥራ ሁለት ሰዎችን ነው” የተላከ ኢየሱስ የላካቸው ለተወሰነ ዓላማ ነው፡፡ “የተላከ” የሚለው ቃል በ MAT 10:2 ውስጥ ጥቅም ላይ የዋለው “አፖስትል” የሚለው ቃል የግሥ ቅርጹ ነው፡፡ አዘዛዘቸው ኤቲ፡ “ምን ማድረግ እንዳለባቸው ነገራው” ወይም “አዘዛቸው” የጠፉት የእስራኤል በጎች ይህ ምሳሌያዊ አነጋገር አጠቀላይ የእስራኤልን ሕዝብ ከእረኛቸው ከጠፉት በጎች ጋር የሚያነጻጽር ነው፡፡ (UDB) ( ተመልከት) የእስራኤል ቤት ይህ ገለጻ የእስራኤልን ሕዝብ የሚገልጽ ነው፡፡ ኤቲ፡ “የእስራኤል ሕዝብ” ወይም “የእስራኤል ዘር” ( ተመልከት) እንዲሁም ስትሄዱ “እናንተ” የሚለው ተውላጠ ስም ዐሥራ ሁለቱን ሐዋርያትን የሚያመለክት ነው፡፡ (: ተመልከት) የእግዚአብሔር መንግስ ቀርባለች ይህንን በ MAT 3:2 ውስጥ ያለውን ተመሳሳይ ሀሳብ በተረጎምክበት መንገድ መተርጎም ይኖርብሃል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ለመስበክ በሚወጡበት ወቅት ምን ማድረግ እንዳለባቸው እና ምን እንደሚጠብቃቸው ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ትዕዛዝ መስጠቱን ቀጥሏል፡፡ እናንተ ይህ ቃል የሚያመለክተው ዐሥራ ሁለቱን ሐዋርያት ነው፡፡ ወርቅ፣ ብር ወይም ናስ እነዚህ ሳንትሞች የሚሠሩባቸው ብረታ ብረቶች ናቸው፡፡ እነዚህ የገንዘብ ተለዋጭ ዝርዝሮች ናቸው፡፡ ብረታ ብረቶች በአካቢያችሁ የማዬታወቁ ከሆነ እነዚህ”ገንዝብ” ብለህ መተርጎም ትችላለህ፡፡ ( ተመልከት) ቦርሳ ይህ “ቀበቶ” ወይም “የገንዘብ ቀበቶ” ማለት ነው ነገር ግን ማንኛውንም ገንዘብ ለመያዝ የሚያገለግል ነገርን ሊያመለክት ይችላል፡፡ ቀበቶ ረጅም የጨርቅ መቀነት ወይም በወገብ ዙሪያ ሰዎች የሚታጠቁት ከቆዳ የሚሠራ ነገር ነወ፡፡ ብዙ ጊዜ ታጥፎ በውስጡ ሳንቲሞችን እና ገንዘብን ለመያዝ የሚያስችለው ስፋት አለው፡፡ የጉዞ ቦርሳ ይህ በጉዞ ወቅት አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን ለመያዝ የሚያገለግል ቦርሳ ወይም በሰዎች ምግብ ወይም ገንዘብ ለመሰበብሰብ የሚሆን ቦርሳን ያመለክታል፡፡ ተጨማሪ ነገሮችን በ MAT 5:40 ውስጥ ተጨማሪ ነገሮችን ብላችሁ የተረጎማችሁትን ቃል በዚህ ሥፍራ ተጠቀሙ፡፡ ሠራተኛ “ሠራተኛ” ምግቡ ኤቲ፡ “የሚያስፈልገው ነገር”
አያያዥ ዓረፈተ ነገር ለመስበክ በሚወጡበት ወቅት ምን ማድረግ እንዳለባቸው እና ምን እንደሚጠብቃቸው ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ትዕዛዝ መስጠቱን ቀጥሏል፡፡ እናንተ እነዚህ ተውላጠ ስሞች ዐሥራ ሁለቱን ሐዋርያትን ያመለክታሉ፡፡ ወደዬትኛው ከተማ ወይም መንደር ስትገቡ ኤቲ፡ “ወደ አንድ ከተማ ወይም መንድር ስትገቡ” ወይም “ወደዬትኛውም መንደር ወይም ከተማ ስትገቡ” ከተማ ወይም መንደር “ትልቅ መንደር . . . ትንንሽ መንደር” ወይም “ታላላቅ ከተማ . . . ትንንሽ ከተማ፡፡” በ MAT 9:35 ውስጥ የተጠቀምከውን ተመሳሳይ ቃል በዚህም ሥፍራ ተጠቀም፡፡ ከዚያ ከተማ ለቃችሁ እስክትወጡ ድረስ በዚያ ቆዩ ኤቲ፡ “ከተማውን ወይም መንደሩን ለቃችሁ እስኪትወጡ ድረስ በዚያ ሰው ቤት ውስጥ ቆዩ” As you enter into the house, greet it AT: "As you enter into the house, greet the people who live in it." A common greeting in those days was "Peace be to this house!" ወደቤትም ስትገቡ ሰላምታ ስጡ ኤቲ፡ “ወደቤት ስትገቡ በዚያ የሚኖሩ ሰዎችን ሰላም በሏቸው፡፡” በዚያ ዘመን የተለመደው የሠላምታ ዓይነት “ሰላም ለዚህ ቤት ይሁን” የሚል ነበር›› ( ተመልከቱ) ቤቱም የሚገባው ቢሆን ኤቲ፡ “በዚያ ቤት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ከተቀበሏችሁ” (UDB) ወይም “በዚያ ቤት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች በሚገባ ከተንከባከቧችሁ” ( ተመልከት) ሰላማችሁ ይሁንለት ኤቲ፡ “ሠላም ይሁንለት” ወይም “በዚያ ቤት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች በሠላም ይኑሩ” ሰላማችሁ ይህ ሐዋርያቱ በዚያ ቤት ውስጥ በሚኖሩ ሰዎች ዘንድ ይመጣ ዘንድ እግዚአብሔርን የሚጠይቁት ሰላም ነው፡፡ ባይገባው ግን ኤቲ፡ “በደንብ ካልተቀበሏችሁ” (UDB) ወይም “በደንብ ያላስተናገዷችሁ ከሆነ” ሰላማችሁ ይመለስ ይህ ሁለት አማራጭ ትርጓሜዎች ይሩታል፡ 1) ይህ ቤት ያልተገባው ከሆነ እግዚአብሔር ሰላሙን ወይም በረከቱን ከዚያ ቤት ላይ ይይዘዋል ወይም 2) ቤቱ ያልተገባው ከሆነ ሐዋርያቱ አንድ ነገር ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ይኸውም እግዚአብሔርን ያቀረቡላቸውን ሰላምታ እንዲያከብር መጠየቅ፡፡ ሰላምታችሁን መልሳችሁ መውሰድ ወይም የዚህ ውጤት አስመልክቶ በቋንቋችሁ ውስጥ ያሉት ቃላት ተመሳሳይ ከሆኑ በዚህ ሥፍራ መጠቀም ያለባችሁም እነዚህኑ ቃላት ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ለመስበክ በሚወጡበት ወቅት ምን ማድረግ እንዳለባቸው እና ምን እንደሚጠብቃቸው ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ትዕዛዝ መስጠቱን ቀጥሏል፡፡ ከማይቀበላችሁም ቃላችሁንም ከማይሰሙ ሁሉ ኤቲ፡ “በከተማው ውስጥ ከሚኖሩ ሰዎች መካከል ማንም ሳይበቀላች ቢቀር ወይም ያደመጣችሁ ሰው ባይኖር” እናንተ ይህ ዐሥራ ሁለት ደቀ መዛሙርት ያመለክታል፡፡ ቃላችሁን የማይሰሙ ቢሆን ኤቲ፡ “መልዕክታችሁን ማድመጥ” " (UDB) ወይም “ማለት የፈለጋችሁትን የሚያደምጥ” ከተማ ይህንን በ MAT 10:11 ከተጠቀምከው ቃል ጋር ተመሳሳይ የሆነ ቃልን በመጠቀም ሊትተረጉመው ትችላለህ፡፡ የእግራችሁን ትቢያ አራግፉ ኤቲ፡ “ከእግራችሁ ላይ የዚያን ቤት ወይም ከተማ አቧራ አራግፉ፡፡” ይህ እግዚአብሔር በዚያ ቤት ወይም ከተማ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን መተውን የሚያመለክት ምልክት ነው፡፡ ይበልጥ ይቀልላቸዋል ኤቲ፡ “መከራቸው ትንሽ ይሆናል፡፡” የሶዶም እና ገሞራ ምድር ኤቲ፡ እግዚአብሔር ከሰማይ በመጣ እሳት ያጠፋቸው በ“ሰዶም እና ገሞራ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች፡፡ ይችህ ከተማ ይህ ሐዋርያትን ወይም መልዕክቶቻቸውን ያልተቀበሉ በከተማይቱ የሚኖሩ ሰዎችን ያመለክታል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርን ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ በዚህም ሥፍራ ላይ ለመስበክ በሚሄዱበት ወቅት ስለሚያጋጥማቸው ስደት ይነግራቸው ጀምሯል፡፡ ተመልከቱ “ተመልከቱ” የሚለው ቃል በዚህ ሥፍራ ላይ ያለው ጠቀሜታ ከዚህ በታች የተጠቀሰው ሀሳብ ትኩረት እንዲሰጠው ማድረግ ነው፡፡ ኤቲ፡ “ተመልከቱ” ወይም “አዲምጡ” ወይም “ ከዚህ በመቀጠል ለሚናረው ነገር ትኩረት ስጡ”፡፡ እልካችኋለሁ ለተወሰነ ዓላማ ኦየሱስ ልኳቸዋል፡፡ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ራሳቸውን መከላከል በማይችሉ እንስሳት በመመሰል ሊያጠቋቸው በሚችሉ የዱር እንስሳት መካከል እንደሚልካቸው ይናገራል፡፡ ( ተመልከት) እንደ በጎች በጎች ራሳቸውን መከላከል አይችሉም፡፡ ( ተመልከት) በተኩላዎች መካከል ኤቲ፡ “እንደ ተኩላ አደገኛ በሆኑ ሰዎች መካከል” ወይም “አደገኛ እንስሳት ከሚያደርጓቸው ነገሮች ጋር የሚመሳሰል ተግባር በሚያደርጉ ሰዎች መካከል” ወይም “ሊያጠቋችሁ በሚችሉ ሰዎች መካከል” ( ተመልከት) እንደ እባብ ብልጦች እና እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ ንጽጽሩን አለመግለጡ የተሻለ ነው፡፡ ኤቲ፡ “በመረዳት እና በጥንቃቄ እንዲሁም በንጹሕ ልብ እና ሥነ-ምግባርን በጠበቀ መልኩ ነገሮችን ፈጽሙ” ( ተመልከቱ) ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጧችኋል ኤቲ፡ “ምክንያቱም ወደ ፍርድ ቤታቸው አሳልፈው ይሰጧኋል” ሸንጎዎች እነዚህ የማህረሰቡን ሰላም የሚጠብቁ የአከባቢው የሃይማኖት መሪዎችን ወይም ሽማግሌዎች ናቸው፡፡ ኤቲ፡ “ፍርድ ቤቶች” ይገርፏችኋል ኤቲ፡ “በመግረፊያ ይገርፏቸኋል” አሳልፈው ይሰጧኋል “ይወስዷችኋል” ወይም “ይጎትቷችኋል” ( ተመልከት) ስለ እኔ ኤቲ፡ “የእኔ ስለሆናችሁ” (UDB) ወይም “እኔን በመከተላችሁ ምክንያት” ለእነርሱና ለአሕዛብም “ለእነርሱ” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው “ገዥዎች እና ነገሥታት” ነው ወይም አይሁዳዊያን ከሳሾችን ነው (10፡17)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለመስበክ ስወጡ ስለሚጋጥማቸው ስደት ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ “ሰዎች ወደ ሸንጎ ስወሰዷችሁ”፡፡ በዚህ ሥፍራ “ሰዎች” ተብሎ የተጠቀሱት በ MAT 10:17 ላይ ሰዎች ተብለው ከተጠቀሱት ጋር ተመሳሳይ ናቸው፡፡ እናንተ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ዐሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርት ነው፡፡ አትፍሩ ኤቲ፡ “አትጨነቁ” እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ “እንዴት መናገር እንዳለባችሁ ወይም ምን መናገር እንዳለባችሁ”፡፡ እነዚህ ሁለት ሀሳቦች በአንድነት ሊጣመሩ ይችላሉ፡፡ “ምን ማለት እንዳለባችሁ” ( ተመልከት) በዚያች ሰዓት ኤቲ፡ “በዚያን ጊዜ” (: ተመልከት) የአባታችሁ መንፈስ አስፈላጊ ከሆነ ይህ “የሰማያዊ አበባተታችሁ የእግዚአብሔር መንፈስ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል ወይም ይህ የእግዚአብሔርብ መንፈስ የሚያመለክት እንጂ ምድራዊ አባትን የማያመለከት እንደሆነ ለማሳየት የግርጌ ማስታወሻ መጨመረም ይቻላል፡፡ አባት ይህ የእግዚአብሔር ዋና መጠሪያ ነው ( ተመልከት) በእናንተ ውስጥ ኤቲ፡ “በእናንተ በኩል”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለመስበክ ስወጡ ስለሚጋጥማቸው ስደት ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ ወንድምም ወንድሙን፥ አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፥ ኤቲ፡ “ወንድም ወንድሙን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል እንዲሁም አባቶች ልጆቻቸውን ለሞት አሳልፈው ይሰጣሉ፡፡” አሳልፎ መስጠት በ MAT 10:17 በተረጎምከው መሠረት ይህንን መተርጎም፡፡ ይነሣሉ ኤቲ፡ “ማመጽ”(UDB) ወይም “መቃወም” ይገድሉአቸውማል ኤቲ፡ “ያስገድሏቿል” ወይም “ ባለስልታናቱ እንዲገድሏቸው ደርጋሉ በሁሉም የተጠላችሁ ትሆናላችሁ ኤቲ፡ “በሁሉም የተጠላች ትሆናላችሁ” ወይም “ሁሉም ሰዎች ይጠሏችኋል”ተመልከቱ) እናንተ … እናንተ . . . እናንተ ይህ ዐሥራ ሁለቱን ሐዋርያትን የሚያመለክት ነው፡፡ ስለስሜ ኤቲ፡ “በስሜ ምክንያት” ወይም “በእኔ በማመናችሁ ምክንያት” (UDB) እስከ መጨረሻ የሚጸና ኤቲ፡ “እስከ መጨረሻ በታማኝነት የሚቆይ” እርሱ ይድናል ኤቲ፡ “ያን ሰው እግዚአብሔር ያድነዋል” ( ተመልከት) ወደ ቀጣዩ ሽሹ “ወደ ቀጣዩ ከተማ ሽሹ” እስኪመጣ ኤቲ፡ እስኪመጣ
አያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለመስበክ ስወጡ ስለሚጋጥማቸው ስደት ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ ደቀ መዝሙር ከመምህሩ አይበልጥም ይህ በአጠቃላይ እውነት የሆነ ነገር ነው፡፡ ይን አንጂ ይህንን ዓረፍተ ነገር ለሁሉም ደቀ መዝሙር እና መምህር ማዋል አንችል፡፡ ደቀ መዝሙር ከመምህሩ “በላይ ጠቃሚ” አይደለም፡፡ ይህ ምልባትም ከመመምህሩ “በላይ ስለማያውቅ” ወይም “ከፍተኛ ደረጃ ስለሌለው” ወይም “የተሸለ ስላልሆነ” ሊሆን ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “የደቀ መዝሙሩ አስፈላጊነት ሁል ጊዜ ከመምህሩ ያነሰ ነው” ወይም “መምህሩ አስፈላጊነቱ ከደቀ መዝሙር ሁሉ ጊዜ የተሻለ ነው፡፡ ባሪያም ከጌታው አይበልጥም “ጌታው ከመምህሩ አይበልጥም”፡፡ ይህ አጠቃላይ መርህ እንጂ ማንኛውንም ባሪያን እና ጌታን አይወክልም፡፡ ባሪያው ከጌታው “አይበልጥም” ወይም “የተሻለ ጠቃሚ” አይደለም፡፡ ኤቲ፡ “ባሪያ ያለው ጠቄታ ሁል ጊዜ ከጌታው ያነሰ ነው፡፡” ወይም “ጌታው ያለው ጠቀሜታ ከባሪያው ሁልጊዜ የበለጠ ነው፡፡” አገልጋይ “ባሪያ” ጌታ “ባለቤት” ደቀ መዝሙር እንደ መምህሩ መሆኑ ይበቃዋል ኤቲ፡ “ደቀ መዝሙር እንደ መምህሩ መሆኑ በቂው ነው” እንደ መምህሩ ኤቲ፡ “መምህሩ የሚያውቀውን ያኽል ቢያውቅ” ወይም “እንደ መምህሩ ቢሆን” እንዲሁም ባሪያውም እንደ ጌታው ኤቲ፡ “ባሪያው እንደ መምህሩ ጠቃሚ መሆኑ ይበቃዋል” ባለቤቱን ብዔል ዜቡል ካሉት፥ ቤተሰዎቹንማ እንዴት አብዝተው አይሉአቸው ኢየሱስን አንገላተውታል ስለዚህም ደቀ መዛሙርቱም ተመሳሳይ ነገር እንደሚጠብቃቸው ማወቅ አለባቸው፡፡ ካሉት ኤቲ፡ “ሰዎች አንዲህ ብለው ከጠሩት” የቤቱን ባለቤት ኢየሱስ ይህንን ምሳሌያዊ ንግግር የተናገረው ስለራሱ ነው፡፡ ( ተመልከት) ብዔል ዜቡል ይህ ስም 1) እንዳለ “ብዔል ዘቡል” ወይም 2) ጸሐፊው ማስተላለፍ የፈለገው ትርጉም “ሴጣን” በሚለው ሊተረጎም ይችላል፡፡ ቤተሰቦቹ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር የሚያመለክተው የኢየሱስን ደቀ መዛሙርት ነው፡፡ ( ተመልከት)
አያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለመስበክ ስወጡ ስለሚጋጥማቸው ስደት ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ አትፍሩአቸው በዚህ ሥፍራ ላይ “እነርሱን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የኢየሱ ደቀ መዛሙርትን የሚያንገላቱትን ሰዎች ነው፡፡ የማይገለጥ የተከደነ፥ የማይታወቅም የተሰወረ ምንም የለምና። ኤቲ፡ ሰዎች የደበቋቸውን ነገሮች እግዚአብሔር ይገልጣቸዋል፡፡ ( ተመልከት) በጨለማ የምነግራችሁን በብርሃን ተናገሩ፤ በጆሮም የምትሰሙትን በሰገነት ላይ ስበኩ። ኤቲ፡ “በጨለማ የነገርኳችሁ ነገር በቀን ለሰዎች ተናገሩ እንዲሁም በጆሮዋችሁ የነገርኳችሁን ነገር ለሰዎች ንገሩ፡፡” ( ተመልከት) በጨለማ የምነግራችሁን ኤቲ፡ “በሚስጥር የሚነግራችሁን” ወይም “በግላችሁ የሚነግራችሁን ነገር” ( ተመልከት) በብርሃን ተናገሩ፤ ኤቲ፡ “በግልጽ ተናገሩ” ወይም “በአደባባይ ተናገሩ” ( ተመልከት) በጆሮም የምትሰሙትን ኤቲ፡ “በጆሮዋችሁ የነገርኳችሁን ነገር” በሰገነት ላይ ስበኩ። ኤቲ፡ “በሚሰማ ድምጽ ሁሉም እንዲሰማ አድርጋችሁ ተናገሩ”፡፡ ሰገነት ኢየሱስ በኖረበት ሥፍራ በከፍታ ላይ ያለ ሥፍራ ሲሆን በከፍተኛ ድምፅ ከዚህ ሥፍራ ሆኖ የሚደረግን ንግግር በሩቅ ሥፍራ ያሉ ሰዎች እንኳ ይሰሙታል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለመስበክ ስወጡ ስለሚጋጥማቸው ስደት ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ አጠቃላይ መረጃ በተጨማሪም በዚህ ክፍል ውስጥ ኢየሱ ደቀ መዛሙርቱ የሚያጋጥማቸውን ስደት መፍራት ያሌለባቸው ለምን እንደሆነ መናገር የጀመረበት ክፍል ነው፡፡ ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ “ሰዎችን አትፍሩ፡፡ ሥጋን መግደል ይችላሉ ነገር ግ ነፍስን ግን መግደል አይችሉም፡፡” ሥጋን መግደል አካላዊ ሞት ማስከተል፡፡ እነዚህ ቃላት ግራ የሚጋቡ ከሆኑ “ልገድሉአችሁ” ወይም “ሌሎች ሰዎችን መግደል” የሚለችሉ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ሥጋ በእጅ ልዳሰስ የሚችል የሰው ክፍል ነፍስ መግደል ሰዎች ከሞቱ በኋላ መጉደት ነፍስ በእጅ ልዳሰስ የማይችል የሰው ክፍል እና ከአካላዊ ሞት በኋላ የሚኖር ሁለት ድንቢጦች በአምስት ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ይህ ጥያቄ እንነዲህ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል “ስለ ድንቢጦች አስቡ፡፡ ያላቸው ዋጋ በጣም ትንሽ ከመሆኑ የተነሳ በአምስት ሳንቲም ሁለቱን ልትገዟቸው ትችለላላችሁ” (UDB). ( ተመልከት) ድንቢጦች እነዚህ በጣም ትንንሽ የሆኑ ጥራጥሬ የሚበሉ ወፎች ሲሆን በዚህ ምሌያዊ ንግግር ውስጥም ሰዎች ምንም ጥቅም የላቸው ብለው ከሚያስባቸው ነገሮች ጋር ተነጻጽሮ ቀርቧል፡፡ አምስት ሳንቲም ይህ ብዙ ጊዜ በሚተረጎምበት ቋንቋ ውስጥ ጥቅም ላይ በዋለው ገንዘብ ውስጥ በሚገኘው ሳንቲም ይተረጎማል፡፡ ይህ የመዳብ ሳንቲም ሲሆን አንድ ሰው በቀን ከሚገኘው ገቢ ውስጥ አንድ ዐሥራ ስድስተኛው ያኸል ነው፡፡ “በጣም ትንሽ ገንዘብ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ከእነርሱም አንዲቱ ያለ አባታችሁ ፈቃድ በምድር ላይ አትወድቅም። ይህ ንግግር እንዲህ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል “ከእነዚህ መካከል አንዱ እንኳ ወደ ምድር የሚወድቀው አባታችሁ ካወቀው ብቻ ነው” ወይም “አባታችሁ ካወቀው ብቻ ነው ከእነዚህ መካከል አንዱ ወደ ምድር ሊወድቅ የሚችለው”፡፡ (: ተመልከት) አንዱም እንኳ “አንድ ድንቢጥ እንኳ” ወደ ምድረ አይወድቅም “አይሞትም” የእናንተስ የራሳችሁ ጠጉር ሁሉ እንኳ ተቈጥሮአል “በራሳችሁ ላይ እንኳ ስንት ጸጉር እንዳለ እግዚአብሔር ያውቃል” ( ተመልከት) ተቆጥሮአል “ተቆጥሮአል” በዋጋችሁ ከብዙ ድንቢጦች ትበልጣላችሁ “ከብዙ ድንቢጦች ይልቅ እግዚአብሔር ለእናንተ ዋጋ ይሰጣል”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለመስበክ ስወጡ ስለሚጋጥማቸው ስደት ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ “ለሌሎች የእኔ ደቀ መዝሙር መሆኑን የሚናገር ማንኛውም ሰው” ወይም “ለእኔ ታማኝ መሆኑን ለማንም ሰው የሚናገር ማንም ሰው” መመስከር “መናገር” በሰዎች ፊት “በሰዎች ፊት” ወይም “በሌሎች ሰዎች ፊት” አባት ይህ የእግዚአብሔር ዋና መጠሪያ ነው ( ተመልከት) በሰዎች ፊት የሚክደኝ ሁሉ “በሰዎች ፊት የሚክደኝ ሁሉ” ወይም “በሰዎች ፊት የማይቀበለኝ ሁሉ” ወይም “በሌሎች ሰዎች ፊት የእኔ ደቀ መዝሙር መሆኑን የማይናር ሁሉ” ወይም “ለእኔ ታማኝ መሆኑን የማይናገር ሁሉ”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ሊያጋጥማቸው የሚችለውን ስደት መፍራት የሌለባቸው በምን ምክንያት እንደሆነ ማስተማሩን ቀጥሏል አይምሰላችሁ “እንደዚህ አታስቡ” ወይም “እንዲህ አይምሰላችሁ” ሰይፍ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር 1)የአመጽ ሞት ("መስቀል" በ MAT 10:38(ተመልከት) ወይም 2) መከፋፈልን የሚያመጣ መከራ ( ተመልከት) ለማምጣት “መመለስ” ወይም "መከፋፈል" ወይም "መለያየት" ሰውን ከአባቱ “ልጅን በአባቱ ላይ” ለሰውም ጠላቶች “የሰው ጠላቶሱ” ወይም “የሰው መጥፎ ጠላቶቹ” ቤተ ሰዎቹ ናቸው “የራሱ ቤተሰብ አባላት ናቸው”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ሊያጋጥማቸው የሚችለውን ስደት መፍራት የሌለባቸው በምን ምክንያት እንደሆነ ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ የሚወድ . . . ሊሆን አይገባውም፤ ኤቲ፡ “የሚወድ . . . ሊሆን አይገባውም፤” ወይም “የሚትወዱ ከሆነ . . . አትገቡም” የ ይህ “ማንም” ወይም “ይህንን የሚያደረግ” ወይም “ይህንን የሚያደረግ ማንን ሰው” ወይም “ይህንን የሚያደርጉ ሰዎች” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ መውደድ በዚህ ሥፍራ ላይ መውደድ የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው “ወንድማዊ መዋደድን” ወይም “ከጓደኛ የሚገኝ ፍቅርን” የሚያመለክት ነው፡፡ በተጨማሪም “መንከባከብ” ወይም “መሰጠት” ወይም “የሚገኝ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ይህ እንዲህ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል “የእኔ ሊሆን ፈጽሞ አይገባውም” ወይም “የእኔ ደቀ መዝሙር ሊሆን አይገባውም” ወይም “የእኔ መሆን አይገባውም” የማይዝ . . . አይሆንም አማራጭ ትርጉሞች፡ “የማይዙ . . አይደሉም” ወይም “የማትይዝ ከሆነ . . . አይደለህም” ወይም “የማትይዙ ከሆነ . . . አይደላችሁም፡፡” አንሣ . . . መስቀሉን እና ተከተለኝ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ለመሞት ፈቃደኛ መሆን ማለት ነው፡፡ ማንሣትን እና ከሌላ ሰው ኋላ መከተልን የሚያመለክቱ የተለመዱ ቃላትን ተጠቀም፡፡ ( ተመልከት) አንሣ “አንሣ” ወይም “አንሣና ተሸከም” የሚያገኝ . . . ያጠፋታል . . የሚያጠፋ . . . ያገኛታል፡፡ እነዚህ ቃላት በተቻለ መጠን በጣም ትንሽ ቃላት አማካኝነት ሊተረጎሙ ይገባል፡፡ አማራጨ ትርጓሜዎች፡ “የሚያገኗት. . . ያጠፏታል . . . የሚያጠፏት . . . ያገኟታል” ወይም “ካገኘሃት . . . ታጠፋታለህ . . . ካጠፋሃት . . . ታገኛታለህ” ማግኘት ይህ “መጠበቅ” ወይም “ደንነቱን መጠበቅ” ከሚለው ቃል ጋር ተቀራራቢ ትርጉም ያለው ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜዎቹ፡ “ለመጠበቅ የሚሞክር” ወይም “ለማዳን የሚሞክር” ( ተመልከት) ያጠፋታል ይህ ሰውዬው ይሞታል ማለት አይደለም፡፡ “እውነተኛ ሕይወት አይኖረውም” ለሚለው ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ ( ተመልከት) ነፍሱን የሚያጠፋ ይህ ማለት መሞት ማለት አይደለም፡፡ ይህ ማለት ከራሱ ሕይወት ይልቅ ኢየሱስን መታዘዝ አስፈላጊ መሆኑን መገንዘብ ማለት ነው፡፡ ኤቲ፡ “የራሱን ሕይወት የካደ፡፡” ለእኔ ሲል “በእኔ በማመኑ ምክንያት” ወይም “ለእኔ ሲል” ወይም “በእኔ ምክንያት”፡፡ ይህ በ MAT 10:18. ላይ ካለው “ለእኔ ሲል” ከሚለው ሀረግ ጋር ተመሳሳይ ሀሳብ ያለው ነው፡፡ ያገኛታል ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ትርጉሙ “እውነተኛ ሕይወትን ያገኛል” ማለት ነው፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ሊያጋጥማቸው የሚችለውን ስደት መፍራት የሌለባቸው በምን ምክንያት እንደሆነ ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ የሚ ይህ እንዲህ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል “ማንም” ወይም “ማንም ሰው” ወይም “ይህን ያደረገ ሰው” የሚቀበል ይህ በ MAT 10:14 ውስጥ “መቀበል” ከሚለው ቃል ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ ትርጉሙም “እንደ እንግዳ መቀበል ማለት ነው፡፡” እናንተ በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስ እያስረማራቸው ያሉትን ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ነው፡፡ የላከኝን ይቀበላል። “የላከኝን እግዚአብሔር አብን ይቀበላል”
አያያዥ ዓርፈተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለመስበክ ሲወጡ ምን ማድረግ እንዳለባቸው እና ምን ምን ነገር እንደሚያጋጥማቸው ማስተማሩን አጠናቀቀ፡፡ የሚሰጥ ሁሉ “የሚሰጥ ማንኛውም ሰው” ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ ይህ እንዲህ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል “የእኔ ደቀ መዝሙር ስለሆነ ከእነዚህ ከታነናናሺቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ውሃ የሚሰጥ ማንም ሰው” ወይም “ከእነዚህ ደቀ መዛሙርቶቼ መካከል ለአንዱ ቀዝቃዛ ውሃ እንዲጠጣ የሚሰጥ ማንኛውም ሰው” ዋጋው አይጠፋበትም። “ይህ ሰው በእርግጥ ሽልማቱን ይቀበላል” ( ተመልከት) አያጣም “አይከለከልም”፡፡ ይህ በምንም ዓይነት መንገድ ንብረቱን ከመውሰድ ጋር አይገናኝም፡፡
ኢየሱስ ለዐሥራ ሁለቱ ደቀመዛሙርት እርኩሳን መናፍስትን እንዲያስወጡ እና ሁሉንም ዓይነት በሽታዎች እንዲፈውሱ ሥልጣን ሰጣቸው። [10:1]
ኢየሱስን አሳልፎ የሚሰጠው ደቀመዛሙር ስም የአስቆሮቱ ይሁዳ ነበር። [10:4]
ኢየሱስ ደቀመዛሙርቱን የላከው ከእሥራኤል ቤት ወደ ጠፉት በጎች ብቻ ነበር። [10:6]
በፍጹም፣ ደቀመዛሙርቱ የትኛውንም ልብስ ወይም ተጨማሪ ልብስ መያዝ አይይዙም። [10:9]
በፍጹም፣ ደቀመዛሙርቱ የትኛውንም ልብስ ወይም ተጨማሪ ልብስ መያዝ አይይዙም። [10:10]
ደቀመዛሙርት በመንደሩ ውስጥ የተገባው የሆነን ሰው አግኝተው ለቅቀው እስኪሄዱ ድረስ በዚያ ይቆያሉ። [10:11]
ደቀመዛሙርቱን ባልተቀበሉ ወይም ቃሎቻቸውን ባልሰሙት ከተሞች ላይ የሚኖረው ፍርድ ከሶዶም እና ጎሞራ ፍርድ የባሰ ይሆናል። [10:14]
ደቀመዛሙርቱን ባልተቀበሉ ወይም ቃሎቻቸውን ባልሰሙት ከተሞች ላይ የሚኖረው ፍርድ ከሶዶም እና ጎሞራ ፍርድ የባሰ ይሆናል። [10:15]
ሰዎች ደቀመዛሙርትን ወደ ሸንጎዎች አሳልፈው እንደሚሰጡ፣ እንግሚገርፏቸው፣ ወደ መንግሥታትና ገዢዎች እንደሚያመጧቸው ኢየሱስ ተናገረ። [10:17]
ሰዎች ደቀመዛሙርትን ወደ ሸንጎዎች አሳልፈው እንደሚሰጡ፣ እንግሚገርፏቸው፣ ወደ መንግሥታትና ገዢዎች እንደሚያመጧቸው ኢየሱስ ተናገረ። [10:18]
የአብ መንፈስ ደቀመዛሙርቱ በተወሰዱ ጊዜ በእነርሱ አልፎ ይናገራል። [10:20]
እስከ መጨረሻ የሚጸኑት ብቻ እንደሚድኑ ኢየሱስ ተናገረ። [10:22]
ኢየሱስን የሚጠሉት ደቀመዛሙርቱንም ይጠሏቸዋል። [10:24]
ኢየሱስን የሚጠሉት ደቀመዛሙርቱንም ይጠሏቸዋል። [10:25]
ሰውነትን ገድለው ነፍስን ግን መግደል የማይችሉትን መፍራት የለብንም። [10:28]
ሰውነትን ገድለው ነፍስን ግን መግደል የማይችሉትን መፍራት የለብንም። [10:28]
በመንግሥተ ሰማይ በአብ ፊት ኢየሱስ ይመሰክርለታል። [10:32]
በመንግሥተ ሰማይ በአብ ፊት ኢየሱስ ይክደዋል። [10:33]
በቤት ውስጥ መከፋፈልን ለማድረግ እንደ መጣ ኢየሱስ ተናገረ። [10:34]
በቤት ውስጥ መከፋፈልን ለማድረግ እንደ መጣ ኢየሱስ ተናገረ። [10:35]
በቤት ውስጥ መከፋፈልን ለማድረግ እንደ መጣ ኢየሱስ ተናገረ። [10:36]
ስለ ኢየሱስ ሲል ሕይወቱን የሚያጣ ሕይወቱን ያገኛል። [10:39]
ከደቀመዛሙርቱ ለትንሹ ቀዝቃዛ ውሃ የሚሰጥ ሰው ዋጋውን ይቀበላል። [10:42]
አጠቃላይ መረጃ ይህ በታሪከው ውስጥ ጸሐፊው ኢየሱስ ለመጥመቁ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ጥያቄ ምን ዓይነት ምላሽ እንደሰጠ የሚተርከው ታሪክ ጅማሬ ነው፡፡ ( ተመልከት) ከዚያ አለፈ ይህ ሀረግ የአዲስ ታሪክ ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ የአንድ ታሪክ ጅማሬን ማሳያ መንገድ በቋንቋችሁ ውስጥ ካለ ያንን መጠቀም ትችላላችሁ፡፡ “ከዚያ” ወየም “ከዚያ በኋላ” በሚሉ ቃላት ሊተረጎም ይችላል፡፡ ማዘዙን ይህ ቃል “ማስተማር” ወይም “ትዕዛዝ መስጠት” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ዐሥራ ሁለቱ የእርሱ ደቀ መዛሙርት ይህ በኢየሱስን የተመረጡን ዐሥራ ሁለቱን ያመለክታል፡፡ አሁን “በዚያን ጊዜ”፡፡ ይህንን ሳትተረጉሙት ማለፍ ትችላላችሁ፡፡ ዮሐንስ በእስር ቤት ሆኖ በሰማ ጊዜ አማራጭ ትርጓሜዎች፡ “በእርስ ቤት ያለው ዮሐንስ በሰማ ጊዜ” ወይም “ሌሎች ሰዎች በእርስ ላይ ላለው ለዮሐንስ በነገሩት ጊዜ” በደቀ መዛሙርቱ በኩል መልዕክትን ላከ መጥመቁ ዮሐንስ በራሱ ደቀ መዛሙርት በኩል ወደ ኢየሱስ መልዕክትን ላከ እንዲህም አለው “እርሱን” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው ኢየሱስ ነው፡፡ የሚትመጣው አንተ ነህን “የሚትመጣው” ወይም “ትመጣለህ ተብለህ የሚትጠበቀው” ተብሎ ይተርጎም ይህ የሚያመለክተው መስሑን ወይም ክርስቶስን ነው፡፡ ( ተመልከት) ሌላ እንፈለግ “ሌላ እንጠብቅ”፡፡ “እኛ” የሚለው ተውላጠ ስም ሁሉንም አይሁዳዊንን የሚያመለክታል እንጂ የዮሐንስን ደቀ መዛሙርት ብቻ አይደለም፡፡
ለዮሐንስ መልሱ ነገሩት “ለዮሐንስ ነገሩት”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለመጥመቁ ዮሐንስ መናገር ጀመረ፡፡ ምን ልታዩ ወጣችሁ . . . ንፋስ? ኢየሱስ ሕዝቡ ስለመጥመቁ ዮሐንስ እንዲያስቡ ለማድረግ እነዚህ ሦስት ደረጃዎች ያሉት ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡ እንዲህ ሊተረጎም ይችላል “ንፋስ . . . ለማየት ነው የወጣችሁትን? በእርግጥ አይደለም!” ወይም “በእርግጠኝነት ንፋስን ለማየት አልወጣችሁም!” ( ተመልከት) በንፋስ የሚወዛወዝ ሸንበቆ ይህ እንዲህ ሊሆን ይችላል 1) በዮርዳኖስ ወንዝ አጠገብ የሚበቅሉ ተክሎች ወይም 2) አንድን ሰው ለማመልከት የቀረበ ምሳሌያዊ ንግግር፡ “በንፋስ እንደሚዠዋዠው ሸንበቆ ያለ ሰው፡፡” ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ሁለት አማራጭ ትርጓሜዎች ይኖሩታል፡ እንዲህ ዓይነቱ ሰው 1) በቀላሉ በንፋስ አማካኝነት የሚንቀሳቀስ፣ ይህ ሀሳቡን በቀላሉ የሚለውጥ ሰውን ለማመልከት ጥቅም ላይ የዋለ ምሳሌያዊ አነጋገር ነው፡፡ ወይም 2) ንፋሱ ስነፍስ ድምፅ የሚያሰማ፡፡ ይህ ምሳሌያዊ ገለጻ ብዙ ነገር ይናገራል ይሁን እንጂ ይህን ያኸል ጠቃሚ ነገር አይናገርም፡፡ ( and ተመልከት) ሸንበቆ “ረጅም፣ ሳር መሰል ተክል” ለስላሳ ልብስ የለበሰ “ውድ ልብስ የለበሰ”፡፡ ሀብታሞች ይህንን ዓይነት ልብስ ይለብሱ ነበር፡፡ የምር ይህ ቃል ብዙ ጊዜ “እነሆ” በሚል ቀጥሎ ለሚመጣው ሀሳብ ትኩረት መስጠት እንደሚያስፈልግ በሚያሳስብ ቃል ተተርጉሟል፡፡ ተለዋጭ ትርጉሙለ “በእርግጥ”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ መናገሩን ቀጥሏል፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጥር 10 ላይ ኢየሱስ ከነቢይ ሚልክያስ መጽሐፍ በመጥቀስ የመጥመቁ ዮሐንስ ሕይወት እና አገልግሎት በተነገረው ትንቢት መሠረት መሆኑን አሳይቷል፡፡ ነገር ግን ምን ልታዩ ወጣችሁ - ነብይ ይህ ስለመጥመቁ ዮሐንስ የተጠየቁ ተከታታይ ጥያቄዎች ቀጣዩ ክፍል ነው፡፡ ( ተመልከት) ነገር ግን ምን ልታዩ ወጣችሁ - ነብይ? አዎን እላችኋለሁ “እናንተ” የሚለው በብዙ ቁጥር የተገለጸው ተውላጠ ስም በሁለቱም ሁኔታዎች ውስጥ ሕዝቡን የሚያመለክት ነው፡፡ ከነቢይም የሚበልጥ “ተራ ነቢይ ያለሆነ” ወይም “ከተራ ነቢይ በጣም የሚበልጥ” ይህ እርሱ ነው “ይህ” መጥመቁ ዮሐንስ የሚያመለክት ነው፡፡ ስለ እርሱ የተጻፈው እርሱ ነው “እርሱ” የሚው ቃል “በቀጣዩ ሀረግ ውስጥ “መልዕክተኛዬ” የተባለው የሚያመለክት ነው፡፡ መልዕክተኛዬን እልካለሁ “እኔ” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው እግዚአብሔር ነው፡፡ የዚህ የብሉይ ኪዳን ትንቢት ጸሐፊ እግዚአብሔር የተናገረውን በቀጥታ ጽፏል፡፡ በፊትህ “ከፊትህ” ወይም “ከአንተ በፊት ይሄድ ዘንድ፡፡” “አንተ” የሚለው ተውላጠ ስም የነጠላ ቁጥር ነው፡፡ ምክንያቱም በትምህርተ ጥቅስ ውስጥ እግዚአብሔር ስለ መስሑ የተነገረ ነው፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ መናገሩን ቀጥሏል፡፡ ከሴቶች ከተወለዱ ሁሉ “ሴቶች ከወለዷቸው ሰዎች መካከል” ወይም “በምድር ላይ ከኖሩ ሰዎች መካከል” ከመጥመቁ ዮሐንስ የሚበልጥ ማንም የለም ኤቲ፡ “መጥመቁ ዮሐንስ ትልቁ ነው” በመንግስተ ሰማያት እግዚብሔር በሚመሰርተው አገዛዝ ውስጥ፡፡ ኤቲ፡ “ወደ መንግስተ ሰማየት ከሚገቡ ሰዎች መካከል” ከእርሱ የሚበልጥ የለም “ከመጥመቁ ዮሐንስ በላይ ጠቃሚ የለም” ከመጥመቁ ዮሐንስ ዘመን ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ “”ከመጥምቁም ከዮሐንስ ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ” መንግሥተ ሰማያት ትገፋለች፥ ግፈኞችም ይናጠቋታል። አማራጭ ትርጓሜዎቹ 1) ግፈኞች በግፍ ይናጠቁታል ወይም 2) “ሰዎች የመንግስተ ሰማይን ዋና ሀሳብ ያሳድዳሉ እንዲሁም ግፈኞች ልቆጣጠሩት ይሞክራሉ” ወይም 3) “መንግስተ ሰማያት በኃይል ወደፊት ትሄዳለች እንዲሁም ኃይለኛ የሆኑ ሰዎች የዚህ አካል ለመሆን ይፈልጋሉ፡፡”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ መናገሩን ቀጥሏል፡፡ ሕግ “የሙሴ ሕግ” ዮሐንስ “መጥመቁ ዮሐንስ” እና አናንተ ከሆነክ “አናንተ” የሚለው ተውላጠ ስም በሕዝቡ መካከል ያሉ ሰዎችን ነው፡፡ ይህ ኤልያስ ነው “ይህ” መጥመቁ ዮሐንስ የሚያመለክት ነው፡፡ ይህ ሀረግ መጥመቁ ዮሐንስ በብሉይ ኪዳን የተገለጸው የነብዩ ኤልያስ ጋር ተዛምዶ ያለው ነው ይሁን እንጂ መጥመቁ ዮሐንስ ኤልያስ ግን ማለት አይደለም፡፡ ( ተመልከት) የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ ኤቲ፡ “የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ” የሚሰማ ጆሮ ያለው “መስማት የሚችል ጆሮ ያለው” ወይም “የሚሰማኝ ሁሉ” ይስማ በደንብ ይስማ” ወይም “ለተናገርኩት ነገር ትኩረት ይስጥ”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ መናገሩን ቀጥሏል፡፡ ይህን በምን እመስለዋለሁ? ይህ የጥያቄ መጀመሪያ ነው፡፡ይህንን ጥያቄ ኢየሱስ የተጠቀመው በዚያ ዘመን ይኖር የነበረውን ሕዝብ እና ሕጻናት በገቢያ ሥፍራ ከሚያደርት ነገር ጋር በማነጻጸር ነው፡፡ በጥያቄ ጀምሯል፡፡ “ ( ተመልከት) በገበያ የሚቀመጡትን ልጆች ይመስላሉ፥ እነርሱም በዚያ ተቀምጠው እርስ በእርሳቸው ይጠራራሉ፡፡ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ትርጉም እንደዚህ ሊሆን ይችላል 1) ኢየሱስ “ዋሽንት ነፋላቸው” እንዲሁም ዮሐንስ “አለቀሰላቸው” ነገር ግን “ይህ ትውልድ” ለመደነስም ሆነ ለማልቀስ አሻፈረኝ አለ፡፡ ይህ የመታዘዝ ምሳሌ ነው፡፡ ወይም 2) ፈሪሳዊያን እና ሌለች ሃይማኖታዊ መሪዎች እነርሱ በሙሴ ሕግ ላይ የጨመሯቸውን ሕጎች አልታዘዝ አለ በማለት ሕዝቡን ይወቅሱታል፡፡ ( ተመልከት) ይህ ተውልድ “በዚህ ዘመን የሚኖሩ ሰዎች” ወይም “እነዚህ ሰዎች” ወይም “እናንተ የዚህ ዘመን ሰዎች” የገቢያ ሥፍራ ይህ ትልቅ የሆነ ሰዎች የተለያዩ ነገሮችን የሚገዙበትን እና የሚሸጡበት ክፍት ሥፍራ ነው፡፡ ዋሽንት ተጫወትንላችሁ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በገቢያ ሥፍራ የተቀመጡትን ልጆች ነው፡፡ “እናንተ” የሚለው ቃ የሚያመለክተው “ይህንን ተውልድ” ነው ወይም ሙዝቃ ሰምቶ ምንም ምላሽ ያልሰጠውን ሕዝብ ነው፡፡ ዋሽንት የመሰለ የሙዚቃ መሣሪያ ይህ ረጅም የሆነ የትንፋሽ የሙዚቃ መሣሪያ ነው፡፡ እንዲሁም አልደነሳችሁም “ይሁን እንጂ በሙዚቃው አልተጫወታችሁም” ወይም አላለቀሳችሁም "ከእኛ ጋርም አላለቀሳችሁም"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ መናገሩን አጠናቀቀ፡፡ ምግብ ሳይበላና ሳይጠጣ "ምግብ ሳይበላ" ይህ ዮሐንስ ምንም ዓይነት ምግብ በልቶ አያውቅም ማለት አይደለም፡፡ ኤቲ፡ “ብዙ ጊዜ ይጾም ነበር” ወይም “ጥሩ ምግብ አይበላም ነበር” (UDB) እንዲህ አሉት፡፡ “እርኩስ መንፈስ አለበት” ኢየሱስ ሰዎች ስለ ዮሐንስ የተናገሩትን በቀጥታ ጠቅሷል፡፡ ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊጠቀስ ይችላል ፡ “እነርሱም እርኩስ መንፈስ አለበት አሉት” ወይም “ዳብሎስ አለበት አሉት” ወይም “እርኩስ መንፈስ አለበት ብለው ከሰሱት”( ተመልከት) እነርሱ “እነርሱ” የሚለው ተውላጠ ስም በዚያ ዘመን ይኖሩ የነበረው ሰዎችን ያመለክታል፡፡ የሰው ልጅ በዚያ ዘመን ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ኢየሱስ የሰው ልጅ እንደሆነ መረዳት ይኖርባቸው ብሎ ይጠብቅ ስነበር እንዲህ ተብሎ መተርጎም ይችላል “እኔ የሰው ልጅ እነርሱ ግን እንዲህ አሉት፣ “እነሆ፥ በላተኛው ኢየሱስ እንደ የሰው ልጅነቱ ሰዎች ስለ እርሱ የተናገረውን ጠቅሷል፡፡ ይህንን በትምህርት ጥቅስ ውስጥ ሳናስቀምጥ እንዲህ ሊተረጎም ይችላል፡ “በታለተኛ ነው አሉት” ወይም “ብዙ ይበላል ብለው ከሰሱት”፡፡ የሰው ልጅ የሚለው ሀረግ 1እኔ የሰው ልጅ” ብለህ ከተጎምህ ይህንን ደግሞ “እኔን በታለተኛ ነው አሉኝ” ብለህ መተርም ትችላለህ፡፡ በታለተኛና ነው "እርሱ በላተኛ ነው” ወይም “ሁል ጊዜ ብዙ ምግብ ይበላል” ጠጭ "ጠጭ" ወይም "ብዙ አልኮል ሁል ጊዜ ይጠጠቃል" ይሁን እንጂ ጥበብም በሥራዋ ጸደቀች። ይህ ምናልባትም ኢየሱስ ከሁኔታው ጋር ተስማሚ የሆነ ምሳሌን የተናገረበት ነው፡፡ ምክንያቱም ሕዘቡም እርሱ እና ዮሐንስን ስለ ጥበባቸው አልተቀበሏቸውም፡፡ በ UDB ውስጥ ባለው መሠረት በቀጥታ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ( ተመልከት) ጥበብ ጸደቀች በዚህ ገለጻ መሠረት ኢየሱስ ጥበብን በሴት ይመስላታል፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ጠበብ ከእግዚአብሔር ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንደሚያደረገን የሚናገር ሳይሆን ጥበብ ራሱ ትክክለኛ እንደሆነች የተገለጸበት ነው ( ተመልከት) በሥራዎቿ “እርሷ” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው “”ኢየሱስ በሴት የመሰላትን ጥበብን ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ: ኢየሱስ ከዚህ በፊት የተለያዩ ተዓምራትን ባደረገባቸው ሥፍራዎች ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን መገሰጽ ጀመረ፡፡ ከተማዎቹን ገሰጸ ኢየሱስ በዚህ ሥፍራ ላይ ምሌን በመጠቀም በከተማዎቹ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን ትክክለኛ ስላልሆነው ሥራቸው ገሰጸቻ ( ተመልከት) ከተማዎች "ከተማዎች" ታላላቅ ተዓምራት የተደረጉባቸው ይህ እንዲህ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡ “ብዙዎቹን ታላላቅ ተዓራትን ያደረገባቸው ሥፍራዎች” ( ተመልከት) ታላላቅ ተዓምራት ኤቲ፡ “ታላላቅ ሥራዎች” ወይም “ታላላቅ ኃይል” ወይም “ተዓምራት” ንሰሓ ስላልገቡ “እነርሱ” የሚለው ተውላጠ ስም በከተማዎቹ ውስጥ የሚኖሩ ንሰሓ ያልገቡትን ሰዎች ያመለክታል፡፡ ወዮልሽ ኮራዚ፤ ወዮልሽ ቤተ ሳይዳ! ኢየሱስ ኮራዚ እና ቤተ ሳይዳ የተባሉ ከተማዎች የሚደምጡ አድርጎ ነው የተናገረው፡፡ ይሁን እንጂ እነርሱ አይሰሙን፡፡ ( ተመልከት) ኮራዚ . . . ቤተ ሳይዳ . . . ጢሮስ . . . ሲዶና በእነዚያ ከተሞች ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን ለማመልከት የዋለ ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ ( ተመልከት) እናንተ የተደረገው ተአምራት በጢሮስና በሲዶና ተደርጎ ቢሆን፥ ይህ እንዲህ ሊተረጎም ይችላል: "በእናንተ መካከል ያደረኩትን ተዓምራት በጢሮስና በሲሶና ባደረግ ኖሮ” ( ተመልከት) ወዮልሽ . . . በእናንተ መካከል የተደረገው “አንተ” የሚለው ተውላጠ ስም የተገለጸወ በነጣ ቁጥር ነው፡፡ ከብዙ ጊዜ በፊት ንስሐ በገቡ ነበርና። በዚህ ሥፍራ “እነርሱ” ተብሎ የተገለጸው የጢሮስና ሲዶና ሰዎች ነው፡፡ ንሰሓ "ስለ ኃጢአታቸው ይቅርታን በጠየቁ ነበር" በፍርድ ቀን ከእናንተ ይልቅ ለጢሮስና ለሲዶና ይቀልላቸዋል። "በፍርድ ቀን ከእናንተ ይልቅ እግዚብሔር ለጢሮስ እና ለሲዶና የተሻለ መምህረት ያደርግላቸዋል" ወይም "እግዚብሔር ከጢሮስ እና ከሶዶና ሐህዝቦች ይልቅ እግዚአብሔር እናንተን ይቀጣል፡፡” በተዘዋዋር የተገለጸው መረጃ “ምንም እንኳ ያደረኳቸውን ተዓምራትን ቢትመለከቱም ንሰሓ ስላልገባቹ እና በእኔ ስላላመናችሁ፡፡” ( ተመልከት) ከአንተ ይልቅ በዚህ ሥፍራ “አንተ” የሚለው ተውላጠ ስም በነጠላ ቁጥር ሲሆን ኮራዚ ወይም ቤተ ሳይዳን ያመለክታል፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ኢየሱስ ከዚህ በፊት ተዓምራት ያደረገባቸው ከተማዎች ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን መገሰጹን ቀጥሏል፡፡ . እንች ቅፍርናሆም በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ በቅርፍናሆን የሚኖሩ ሰዎች ልክ እንደሚያደምጡ አድርጎ ይናገራል ይሁን እንጂ እነርሱ እየሰዳመጡት አይደለም፡፤ “አንተ” የሚለው ተውላጠ ስም በነጠላ ቁጥር የተገለጸ ሲሆን በእነዚህ ሁለት ጥቅሶች ውስጥ ቅፍርናሆምን የሚያመለክት ነው፡፡ ( and ተመልከት) ቅፍርናሆም . . . ሶዶም የእነዚህ ከተሞች ስም በቅፍርናሆም እና ሶዶም ውስጥ ለሞኖሩ ሰዎች ምሳሌ ሆኖ ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ ( ተመልከት) እስከ ሰማይ ከፍ አልኩ ብለስ ታስቢያለሽ? የቅፍርናሆም ሕዝቦች ስላላቸው ትምክት ለመገሰጽ ኢየሱስ የተጠቀመው ጥያቄ ነው፡፡ በዚህ ዓይነት መንገድ ሊተረጎም ይችላል “እስከ ሰማይ እሄዳለሁ?" ወይም “እግዚአብሔር ያከብረኛል ብለሽ ታስቢያለሽ?" ( እና ተመልከት) ከፍ ከፍ እላለሁ "እከብራለሁ" ( ተመልከት) ወደ ሲኦል ትወርጂያለሽ "እግዚአብሔር ወደ ሲኦል ያወርድሻ" ( ተመልከት) በአንቺ የተደረገው ተአምራት በሰዶም ተደርጎ ቢሆን፥ "በእናንተ ያደረኳቸውን ተዓምራት በሶዶም አድርጌ ቢሆን ኖሮ" ( ተመልከት) ታላላቅ ነገሮች "ታላላቅ ሥራዎች" ወይም "የኃይል ሥራ" ወይን "ተዓምራት" እስከ ዛሬ በኖረች ነበርና። “እርሷ” የሚለው ተውላጠ ስም የሶዶምን ከተማ ያመለክታል፡፡ በፍርድ ቀን ከአንቺ ይልቅ ለሰዶም አገር ይቀልላታል። ይህ እንዲህ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል “በፍርድ ቀን እግዚብሔር ከእናንተ ይልቅ ለሶዶም ምድር ይበልይ ምህረት ያደርግላታል” ወይም “በፍርድ ቀን እግገዚአብሔር እናንተ ከሶዶም ይልቅ ይቀጣችኋል”፡፡ ይህ በተዘወዘዋር መልኩ የሚሰጠው መረጃ “ምንም እንኳ እኔ የሠራኋቸውን ተዓምራትን ቢትመለከቱም ንሰሓ ስላልገባቹ እና በእኔ ስላለመናችሁ” ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ: በቁጥር 25 እና 26 ላይ በሕዝቡ መካከል ሆኖ በሰማይ ወደሚኖረው አባቱ ጸለየ፡፡ በቁጥር 27 እንደገና ለሕዝቡ መናገር ጀመረ፡፡ ኢየሱስ እንዲህ የሚል ምላሽ ሰጠ ከዚያም እንዲህ አለ ይህ እንዲህ ማለት ሊሆን ይችላል 1) በ MAT 10:5 የተላኩት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ከሄዱበት ተመልሰዋል (MAT 12:1 ተመልከት) እንዲሁም አንድ ሰው ስላለው አንድ ነገር ኢየሱስ ምላሽ እየሰጠ ነው ወይም 2) ኢየሱስ ንሰሓ ስላልገቡት ከተሞች የተናገረውን የፍረድ ንግግር አጠቃሏል፡ “ከዚህ በተጨማሪ ኢየሱስ እንዲህ አለ፡፡” አባት . . . ልጅ በእግዚአብሔር እና ኢየሱስ መካከል ያለውን የአባት እና ልጅ ግንኙነት የሚያሳይ የማዕረግ ስም ነው ( የሰማይ እና የምድር ጌታ ይህንን እንደ ምሳሌ መረደት ይቻላል “በሰማይ እና በምደር ባሉት ነገሮቸ ሁሉ ላይ ጌታ የሆነ” ወይም “የዓለማት ሁሉ ጌታ” ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው “እነዚህን ነገሮች” የሚለው ሀረግ ምንን እንደሚያመለክት ግልጽ ነው፡፡ ይህ ምን ማለት እንደሆነ በግልጽ ቋንቋ ለመናገር አማራጭ ትርጉም ተመራጭ ይሆናል፡ “ጠብባን እና የተማሩ ሰዎች ለማወቅ ያልተፈቀደላቸውን እውነት ምንም ለማያውቁ ሰዎች ገለጥክላቸው፡፡” ይህንን ነገር ከ . . . ሰወርክ “ይህንን ከ. . . ሰወርክ” ወይም “ይህንን ነገር ለ . . . አልገለጥክም”፡፡ አልገለጥም የሚለው ግሥ “የመገለጥ” ተቃራኒ ነው፡፡ ጠቢባን እና አዋቂዎች "ጠቢባን እናነአዋቂዎች የሆኑ ሰዎች” ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ጠቢባን እና አዋቂዎች እንደሆኑ የሚያስቡ ሰዎች” ( ተመልከት) ገለጥክላቸው “አስታወካቸው”፡፡ “ለእርሱ” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው በዚህ ቁጥር መጀመሪያ አከባቢ የተጠቀሰውን “እነዚህ ነገሮች” የሚለውን ነው፡፡ ላልተማሩ፣ እንደ ትንንሽ ሕጻናት ላሉት ይህ አጠቃላይ ሀረግ “ትንንሽ ልጆች1 እና “ያልተማሩ” ወይም “የማያውቁ” የሚለውን በውስጡ አጠቃሎ በመያዝ የተተረጎመ ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ምንም የማያውቁ ትንንሽ ልጆች” ይህ በአንተ ፊት መልካም ፈቃድህ ሆነ በፊትህ መልካም ፈቃድ ሆነ - "ምክንያቱም ይህንን ማድረግ መልካም እንደሆነ ተመለከትህ"
እንደ ትንንሽ ሕጻናት ያሉ ጠብባን ያልሆኑ ወይም በጣም ያልተማሩ ሰዎችን ወይም ጠብባን እና በሚገባ የተማሩ እንዳልሆኑ ለሚያውቁ ሰዎች ለማመልከት ጥቅም ላይ የዋለ ምሳሌ ነው፡፡ ( ተመለልከት) ይህ በአንተ ፊት መልካም ፈቃድህ ሆነ በፊትህ መልካም ፈቃድ ሆነ - "ምክንያቱም ይህንን ማድረግ መልካም እንደሆነ ተመለከትህ"
ሁሉ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቶኛል፤ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊተረጎም ይችላል፡ “አባቴ ሁሉን ነገር ሰጥቶኛል” ወይም “አባቴ ሁሉን ነገር ለእኔ ሰጥቶኛል”፡፡ እግዚአብሔር አብ ከእግዚአብሔር ወልድ፣ ከኢየሱስ ጋር ዘላለማዊ ግንኙነት ያለው ሲሆን ይም በእግዚአብሐየር አብ እና ወልድ መካከል ባለ የአባት እና ልጅ ግንኙነት ተገልጧል፡፡ “አባት” እና “ልጅ” የሚሉ ቃላት በመጀመሪያዎቹ ቅዱሳት መጽሐፍ ውስጥ ጥቅም ላይ የዋሉት ይህንን ግንኙነት ለመግሌ ነው ( እና ተመልከት ከአብ በቀር ልጅን የሚያውቅ የለም "ልጅን የሚያውቅ አብ ብቻ ነው፡፡" አባት እና ልጅ በእርግጠኝነት እርስ በእርስ የእውነት የሚተዋወቁ ናቸው (ከእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጋር)፡፡ ልጅን የሚያውቅ ካላቸው ግንኙነተ የተነሳ ልጅን ማወቅ ልጅ በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ ራሱን በሦስተኛ መደብ ይጠራል፡፡ ( ተመልከት) ከልጅ በስተቀር አባትን የሚያውቅ ማንም የለም “ከወልድም በቀር አብን የሚያውቅ የለም።” አብን የሚያውቅ ከግል ግንኙነታች የተነሳ ወልድም ሊገለጥለት ከሚፈቅድ በቀር ለተርጓሚዎች ምክር፡ "ሰዎች አብ ማን እንደሆነ ማወቅ የሚችሉት ልህ አብን ልገልጥላቸው ከወደደ ብቻ ነው፡፡”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ኢየሱስ ለለሕዝቡ ማናገሩን ጨረሰ፡፡ ደካች እና ሸክም የከበደባችሁ ይህ ምሳሌ የአይሁድ ሕግ “ቀንበር” የሚያመለክት ነው፡፡ ( ተመልከት) እኔም አሳርፋችኋለሁ "ከድካማችሁ እና ሸክማችሁ አሳርፋችኋለሁ" ( ተመልከት) ቀንበሬን ተሸከሙ “እናንተ” የሚለው ተውላጠ ስም “ደካሞች እና ሸክም የከበደበባችሁ ሁሉ” የሚለውን የሚያመለክት ነው፡፡ የዚህ ምሳሌ ትርጉሙ “የሰጠኋችሁን ሥራ ተቀበሉ” ወይም “ከእኔ ጋር ተባብራችሁ ሥሩ” ( ተመልከት) ሸክሜ ቀሊል ነው “ቀላል” የሚለው ቃል የከባድ ተቃራኒ እንጂ የጨለማ ተቃራኒ አይደለም
ከመለየቱ በፊት ኢየሱስ ደቀመዛሙርቱን ማዘዝ ጨረሰ። [11:1]
መጥምቊ ዮሐንስ የላከው “የምትመጣው አንተ ነህ፣ ወይስ ሌላውን እንጠብቅ” የሚል ነበር፤ [11:3]
በሽተኞች ይፈወሳሉ፣ ሙታን ይነሣሉ፣ ለድኾችም የምሥራቹ ወንጌል እየተሰበከ ነው። [11:5]
በእርሱ ለማይሰናከሉት እንደሚባረኩ ኢየሱስ ቃል ገባ። [11:6]
መጥምቊ ዮሐንስ ሊመጣ ካለው በፊት ሆኖ መንገድን የሚያዘጋጅ የተተነበየው መልእክተኛ እንደሆነ ኢየሱስ ተናገረ። [11:9]
መጥምቊ ዮሐንስ ሊመጣ ካለው በፊት ሆኖ መንገድን የሚያዘጋጅ የተተነበየው መልእክተኛ እንደሆነ ኢየሱስ ተናገረ። [11:10]
መጥምቊ ዮሐንስ ኤልያስ እንደነበረ ኢየሱስ ተናገረ። [11:14]
መጥምቊ ዮሐንስ አጋንንት እንዳለበት ትውልዱ ተናገረ። [11:18]
ኢየሱስ ስስታምና ጠጪ እንደሆነ፣ የቀረጥ ሰብሳቢዎችና የኃጢአተኞች ወዳጅ እንደሆነ ያ ትውልድ ተናገረ። [11:19]
ኢየሱስ ታላላቅ ተዓምራት የተፈጸመባቸውን፣ ነገር ግን ንስሃ ያልገቡትን ከተሞች ገሠጻቸው። [11:20]
ብልኅ ነን፣ እናውቃለን ለሚሉ የእግዚአብሔርን መንግሥት ስለ ሰወረባቸው ኢየሱስ እግዚአብሔርን አመሰገነ። [11:25]
ብልኅ ነን፣ እናውቃለን ለሚሉ የእግዚአብሔርን መንግሥት ስለ ሰወረባቸው ኢየሱስ እግዚአብሔርን አመሰገነ። [11:25]
እርሱ እና ሊገልጥለት የሚወድደው ሁሉ አብን እንደሚያውቅ ኢየሱስ ተናገረ። [11:27]
ኢየሱስ ለማሳረፍ ቃል የገባው ሸክም ለከበደባቸው ሁሉ ነው። [11:28]
አጠቃላይ መረጃ: ይህ አዲስ የታሪኩ አዲስ ክፍል ሲሆን ጸሐፊው በዚህ ክፍል ውስጥ በኢየሱስ አገልግሎት ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ስለመጣው ተቃውሞ ይተርካል፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥም ፈርሳዊያን የእርሱን ደቀ መዛሙርት በሰንበት አሸት መቅጠፋቸውን አስመልክቶ ያቀረቡትን ተቃውሞ እንመለከታለን፡፡ የእርሻ ማሳ ሰብል የተዘራበት መሬት፡፡ ስንዴ በአከባቢያችሁ የማይታወቅ ከሆነ “ሰብል”፣ “ዳቦ ለመጋገር የሚሆን እህል ማብቀያ ሥፍራ” በሚል አጠቃላይ መጠሪያን ተጠቀሙ፡፡ እሸት ይቀጥፉ ይበሉም ጀመር . . . በሰንበት ማድረግ ያልተፈቀደውን ያደርጋሉ በሰዎች ማሳ ውስጥ የሚገኝን እሸት ቀጥፈው መብላት ሌብነት አይደለም፡፡ ጥያቄው በበሰንበት ማድረግ ያልተፈቀደን ነገር ማድረግ ይቻላል ወይ የሚል ነው፡፡ ይህንን የእሼቱን ጫፍ ቀንጠበው እሸቱን ጫፍ ይህ ረጅም ሳሪ ከሚመስለው የስንዴ ተክል ጫፍ ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ይህ ጫፍ የተክሉን ፍሬ በውስጡ ይይዛል፡፡ ተመልከት አማራጭ ትርጉሞች፡ “ተመልከት”ወይም “አድምጥ” ወይም “አሁን ለምናገረው ነገር ትኩረት ስጥ”
አጠቃላይ መረጃ: ይህ አዲስ የታሪኩ አዲስ ክፍል ሲሆን ጸሐፊው በዚህ ክፍል ውስጥ በኢየሱስ አገልግሎት ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ስለመጣው ተቃውሞ ይተርካል፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥም ፈርሳዊያን የእርሱን ደቀ መዛሙርት በሰንበት አሸት መቅጠፋቸውን አስመልክቶ ያቀረቡትን ተቃውሞ እንመለከታለን፡፡ የእርሻ ማሳ ሰብል የተዘራበት መሬት፡፡ ስንዴ በአከባቢያችሁ የማይታወቅ ከሆነ “ሰብል”፣ “ዳቦ ለመጋገር የሚሆን እህል ማብቀያ ሥፍራ” በሚል አጠቃላይ መጠሪያን ተጠቀሙ፡፡ እሸት ይቀጥፉ ይበሉም ጀመር . . . በሰንበት ማድረግ ያልተፈቀደውን ያደርጋሉ በሰዎች ማሳ ውስጥ የሚገኝን እሸት ቀጥፈው መብላት ሌብነት አይደለም፡፡ ጥያቄው በበሰንበት ማድረግ ያልተፈቀደን ነገር ማድረግ ይቻላል ወይ የሚል ነው፡፡ ይህንን የእሼቱን ጫፍ ቀንጠበው እሸቱን ጫፍ ይህ ረጅም ሳሪ ከሚመስለው የስንዴ ተክል ጫፍ ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ይህ ጫፍ የተክሉን ፍሬ በውስጡ ይይዛል፡፡ ተመልከት አማራጭ ትርጉሞች፡ “ተመልከት”ወይም “አድምጥ” ወይም “አሁን ለምናገረው ነገር ትኩረት ስጥ”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ኢየሱስ ለፈርሳዊያን ትችት ምላሽ መስጠቱን ቀጥሏል፡፡ አናንተ . . . አናንተ ፈርሳዊያን በ . . . ውስጥ እንዲህ የሚል ቃል አላነበባችሁምን “ሕግ ምን እንደሚል ታውቁ ዘንድ የሕግ መጽሐፍትን አላነበባችሁምን" ( ተመልከት) ሰንበትን አያከብሩም "በሌሎች ቀናት የሚያደርጉትን ነገር በሰንበትም ያደርጋሉ" ጥፋት የለባቸውም "እግዚብሔር አይቀጣቸውም" ከመቅደስ የሚበልጥ በዚህ አለ "ከመቅደሱ ይበልጥ ጠቃሙ የሆነ”፡፡ ኢየሱስ የሚበልጠው ብሎ የተናገረው ስለ ራሱ ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ኢየሱስ ለፈሪሳዊያን ምላሽ መስጠቱን ቀጥሏል፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጠር 7 ላይ ኢየሱስ ፈሪሳዊያንን ለመገሰጽ ከነብዩ ሆሴ መጽሐፍ ጠቅሷል፡፡ ብታውቁ ኖሮ "አታውቁም" እናንተ . . . እናንተ ፈሪሳዊያን ምሕረትን እወዳለሁ መሥዋዕትንም አይደለም መሥዋዕት ጥሩ ነገር ነው ነገር ግን ምህረት ግን ይሻላል፡፡ ( ተመልከት) ይህ ማለት ምን ማለት ነው "እግዚአብሔር በቅዱሳት መጽሐፍቱ አማካኝነት ምን አለ" እወዳለሁ “እኔ” የሚለው ተውላጠ ስም እግዚአብሔርን የሚያመለክት ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ፡ በዚህ ሥፍራ ፈሪሳዊያን ኢየሱስ በሰንበት አንድ ሰውን መፈወሱን ወደተቃወሙበት የታሪኩ አቅጣጫ ይለወጣል፡፡ ኢየሱስ ከዚያ አልፎ ሄደ "ኢየሱስ የእርሻ ማሳውን ለቆ ወጣ" የእነርሱ ኢየሱስ እየተናገራቸው ያሉት ፈሪሳዊያን ምኩራብ እነሆ “እነሆ” የሚለው ቃል በታሪክ ውስጥ አዲስ ሰውን ያስተዋውቀናል፡፡ በቋንቋችሁ እንዲህ ዓይነት ነገር ማድረግ ይቻል ይሆናል፡፡ እጁ የሰለለች ሰው ነበረ "የሰለለች" ወይም "ያጠረች"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ኢየሱስ ለፈሪሳዊያን ትችት ምላሽ ሰጠ፡፡ ከእናንተ . . . ይዞ የማያወጣው ሰው ማን ነው? አማራጭ ትርጉም፡ “ሁላችሁም . . . ጎትታችሁ ታወጣላችሁ ( ተመልከት) እናንተ . . . እናንተ ፈሪሳዊያን ያለው "ያለው ሰው" በዚያ የሚተወው "በጉን በጉድጓድ ውስጥ የሚተወው" መልካም ማድረግ በሕግ ተፈቅዷል "መልካም የሚያደርጉ ሰዎች ሕጉን እየተላለፉ አይደለም” ወይም “መልካም የሚያደርጉ ሰዎች ሕጉን እየታዘዙ ነው"
ሰው የሰለለች እጅ ያለው ሰው እጅህን ዘርጋ "እጅህን አንሳ" ወይም እጅህን ዘርጋ" እርሱ ሰውዬው እጁ የሰውዬው እጅ ጤናው ተመለሰች "ሙሉ ለሙሉ ተፈወሰ" ወይም "ሙሉ ጤነኛ ሆነ" በእርሱ ላይ ተማከሩበት "እንዲያጠፉት ተማከሩ" እንዴት አድርገው "ዘዴ ፈለጉ" እርሱን ለመግደል ኢየሱስን ለመግደል h
አጠቃላይ መረጃ፡ ይህ ታሪክ እንዴት የኢየሱስ ተግባር የነብዩ ኢሳያስን ፍጻሜ እንደሆነ ያሳያል፡፡ ይህ "ፈሪሳዊያን እርሱን ለመግደል አቀዱ" ትቷቸው ሄደ "ተዋቸው" እንዳይገልጡትም ነገራቸው "ስለ እርሱ ለሌላ ለማንም ሰው እንዳይናገሩ" በነቢዩ በኢሳይያስ የተባለው ይፈጸም ዘንድ እንዲህ ሲል፦ "እግዚአብሔር በነብዩ ኢሳያስ አማካኝነት የተናገረው እና የተጻፈው"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: በዚህ ክፍል ውስጥ ጸሐፊው የኢየሱስ አገልግሎት በነብዬ ኢሳያስ የተጻፈው የትንቢት ቃል ፍጻሜ መሆኑን ለማሳየት ጠቅሶታ፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጸሐፊው ነብዩ ኢሳያስን መጥቀሱን ቀጥሏል፡፡ የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም "ደካማ ሰዎችን አያጠቃም” ( ተመልከት) የተቀጠቀጠ "በግማሽ የተሰበረ ወይም ጉዳት የደረሰበት” የሚጤስን የጥዋፍ ክርም የጥዋፍ ክር አንድ ጊዜ መብራት ከጀመረ በኋላ ጠንካራ አይደለም፤ ይህ ደግሞ ረዳት ያሌላቸው ሰዎችን ያመለክታል ( ተመልከት) እስኪ. . . ይህ ከአዲስ ዓረፍተ ነገር ጋር እንዲህ ሊተረጎም ይችላል፡ “ይህን እስኪያመጣ ድረስ ይህንን ያደርጋል” ወደ ድል የሚያደርስ ፍርድን ያመጣል "እኔ ትክክል እንደሆንኩ ሰዎችን ያሳምናል" በእርሱ ስም ለተርጓሚዎች ምክር: "በእርሱ" ( ተመልከት)
አንድ ዕውር ዲዳም የሆነ ሰው "ማየት እና መናገር የማይችል አንድ ሰው" ሕብዙም ሁሉ ተገረሙ "ኢየሱስ ሰወዬውን እንደፈወሰው የተመለከቱ ሰዎች ሁሉ በጣም ተገረሙ"
ይት ተዓምር የዐይነ ስውሩ፣ ደንቆሮው እና በእርኩስ መንፈስ የተያዘው ሰው የመፈወሱ ተዓምር ይህ ሰው በብዔል ዜቡል በአጋንንት አለቃ ካልሆነ በቀር አጋንንትን አያወጣም "ይህ ሰው አጋንትን ማውጣት የቻለበት ብቸኛው ምክንያት የብዔል ዜቡል አገልጋይ በመሆኑ ነው" ይህ ሰው ፈሪሳዊያን ኢየሱስን ያለመቀበላቸውን ለማሳየጥ የእርሱን ስም አይጠሩም ነበር፡፡ እናንተ . . . እናንተ ፈሪሳዊያን
ሰይጣንም ሰይጣንን የሚያወጣ ከሆነ "ሴጣን የራሱን መንግስት ተቃውሞ የሚሠራ ከሆነ" ( ተመልከት) መንግስቱ እንዴት ጸንታ ትቆማለች? "የሴጣን መንግስት ጸንቶ ሊቆም አይችልም" ወይም "የሴጣን መንግስት ይፈራርሳል" ( ተመልከት) ማስወጣት "አስገድዶ ማስወጣት" ወይም "ማበባረር" ወይም "አውጥቶ መወርወር" ወይም "ነቅሎ ማውጣት" ተከታዮቻችሁ በማን ያወጧቸዋል ለተርጓሚዎች ምክር፡ "የእናንተ ተከታዮች አጋንትን የሚያስወጡት በብዔል ዘቡል ኃይል አማካኝነት ነው" (ወይም UDB ተመልከት) ( ተመልከት) እነርሱ ፈራጆች ይሆኑባችኋል ለተርጓሚዎች ምክር፡ "አጋንትን በእግዚአብሔር ኃይል የሚያስወጡት የእናንተ ተከታዮች እኔን በብዔል ዘቡል ኃይል አጋንት ያስወጣል በማለታችሁ በእናንተ ላይ ይፈርዳሉ"
ወደ እናንተ ደርሳለች በፈሪሳዊያን ላይ መጣለች በመጀመሪያ ኃይለኛውን ሳያስሩ "ኃይለኛውን በመጀመሪያ በቁጥጥር ሥር ሳያደርጉ" ከእኔ ጋር ያልሆነ "እኔን የማይደግፈኝ” ወይም “ከእኔ ጋር የማይሠራ" የእኔ ተቃዋሚ ነው "እኔን ተቃውሞ ይሠራል" ወይም "ሥራዬን ያፈርሳል" መሰብሰብ ይህ ሰብል መሰብሰብ የሚያመለክት የተለመደ ቃል ነው፡፡ ( ተመልከት)
ማንኛው ኃጢአት እና በእግዚአብሔር ላይ የሚደረግ ስድብ ለሰዎች ይሰረይላቸዋል "ሰዎች የፈጸሟቸው ኃጢአቶች እና ስድቦችን እግዚአብሔር ይቅር ይላቸዋል” ወይም “ኃጢአት የፈጸሙ ሰዎችን ሁሉ እግዚአብሔር ይቅር ይላቸዋል፡፡ ወይም “እግዚብሔር ኃጢአት ያደረጉ ወይም የተሳደቡ ሰዎችን ሁሉ ይቅር ይላቸዋል” ( ተመልከት) በመንፈስ ቅዱስ ላይ ግን የሚናገር ሁሉ አይሰረይለትም። "መንፈስ ቅዱስን የሚሳደብን ግን እገግዚአብሔር ይቅር አይለውም" ( ተመልከት) እንነዲሁም በሰው ልጅ ላይ የሚናገር ኃጢአቱ ይሰረይለታል "የሰው ልጅን በመቃወም የሚነገርን ንግግር እግዚአብሔር ይቅር ይለዋል" በዚህ ዓለም ቢሆን ወይም በሚመጣው ለተርጓሚዎች ምክር፡ "በዚህ ጊዜ . . . በመጪው ጊዜ"
ዛፍዋን መልካም፥ ፍሬዋንም መልካም አድርጉ፥ ወይም ዛፍዋን ክፉ ፍሬዋንም ክፉ አድርጉ። "ፍሬዋ መልካም ከሆነ ዛፏ መልካም እንደሆነች እንዲሁም ፍሬዋ ክፉ ከሆነ ዛፏም ክፉ እንደሆነች ይታወቃል" መልካም . . . ክፉ ይህ ማለት 1) “ጤናማ . . . ጤናማ ያልሆነ” ወይም 2) "የሚበላ . . . የማይበላ" ዘፍ በፍሬው ይታወቃል ይህ እንዲህ ሊሆን ይችላል 1) "ሰዎች አንድ ዘፍ ጤናማ መሆን አለመሆኑን ፍሬውን ተመልክተው ያውቃሉ" ወይም 2) "ሰዎች የዛፉን ፍሬ በመመልከት የዛፉን ዝሪያ ያውቃሉ" ( ተመልከት) እናንተ . . . እናንተ ፈሪሳዊያን በልብ ሞልቶ ከተረፈው አፍ ይናገራልና። "አንድ ሰው በአንደበቱ የሚናገረው በልቡ ውስጥ ካለው ብቻ ነው” ( ተመልከት) መልካም መዝገብ . . . ክፉ መዝገብ "ትክክለኛ ሀሳቦች. . . ክፉ ሀሳቦች" ( ተመልከት)
እናንተ . . . እናንተ ፈሪሳዊያን ሰዎች ስለሚናገሩት ነገር . . .መልስ ይሰጡበታል፤ "እግዚአብሔር ይጠይቀቸዋል" ወይም "እግዚአብሔር ቃላቸውን ይመዝናል" እርባና የሌለው "ጥቅም የሌለው" ለተርጓሚዎች ምክር: "የሚጎዳ" እነርሱ "ሕዝቡ" ትጸድቃለህ . . . ትኰነናለህ "እግዚአብሔር ያጸድቅሃል . . . እግዚአብሔር ይፈርድብሃል" ( ተመልከት)
መሻት "ፍላጎት" ክፉና አመንዝራ ትውልድ በዚህ ዘመን የሚኖሩ ሰዎች ክፉ ማድረግ ይወዳሉ እንዲሁም ከእግዚአብሔር ታማኞች አይደሉም፡፡ ምንም ዓይነት ምልክት አይሰጣቸውም "ለዚህ ክፉ እና አመንዝራ ትውልድ እግዚአብሔር ምንም ዓይነት ምልክት አይሰጥም" ( ተመልከት) የዮናስ ምልክት ለትርጓሚዎች ምክር፡ "ለዮናስ ምን ሆነ" ወይም "ለዮናስ እግዚአብሔር ያደረገው ተዓምር ምን ነበር” ( ተመልከት) በመሬት ልብ ውስጥ በመቃብር ውስጥ ( ተመልከት)
የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "የነነዌ ሰዎች ይህንን ትውልድ ይከሳሉ . . . እንዲሁም እግዚአብሔር ክዳቸውን ይሰማል እና በእናንተ ላይም ይፈርዳል” "እግዚአብሔር የነነዌ ሰዎችን እና ይህንን ትውልድ በኃጢአተኛነታቸው ይፈርድባቸዋል ይሁን እንጂ እነርሱ ንሰሓ ገብተዋል፤ እናንተ ግን አልገባችሁም ስለዚህም በእናንተ ላይ ብቻ ይፈርዳል” ( ተመልከት) ይህ ትውልድ ኢየሱስ በኖረበት እና ባገለገለበት ዘመን ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ( ተመልከት) የሚበልጥ "ይበልጥ አስፈላጊ የሆነ"
የደቡድ ንግሥተ ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድበታለች፤ ለተርጓሚዎች ምክር: "የደቡድ ንግሥት በዚህ ትውልድ ላይ ትፈርዳለች . . . እግዚአብሔርም ፍርዷን ይሰማል በእናንተም ላይ ይፈርዳል” ወይም እግዚአብሔር በደቡቧ ንግሥት እና በዚህ ትውልድ ላይ በኃጢአታቸው ይፈርዳል ይሁን እንጂ እርሷ ንጉሥ ሰለሞንን ስለመጣች እናንተ ግን እኔን ስላልሰማችሁ የሚፈረደው በእናንተ ላይ ብቻ ይሆናል፡፡ ( ተመልከት) የደቡቧ ንግሥት ይህ የአሕዛብ መንግስ ንግሥት ሳባን ያመለክታል ( ተመልከት) ከምድር ዳርቻ መጥታለች "በጣም ሩቅ ከሆነ ሥፍራ መጥታለች” ( ተመልከት) ይህ ትውልድ ኢየሱስ ባገለገለበት ዘመን ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ( ተመልከት) የሚበልጥ "ይበልጥ አስፈላጊ የሆነ"
ውሃ የሌለበት ሥፍራ "ደረቅ ቦታ" ወይም "ሰዎች የማይኖሩበት ቦታ" አያገኝም "የሚያርፍበት ቦታ አያገኝም" እንዲህም ይላል "እርኩስ መንፈሱም እንዲህ ይላል" ቢመጣም ባዶ ሆኖ ተጠርጎና አጊጦ ያገኘዋል። ለተርጓሚዎች ምክር፡ "እርኩስ መንፈሱም ቤቱ ጸድቶ እና ሁሉ ነገር ተስተካክሎ ያገኘዋል" ( ተመልከት)
እናቱ የኢየሱስ እናት ወንድሞቹ ይህ እንዲህ ሊሆን ይችላል 1) የእናቱ እና የአባቱ ልጆች ወይም 2) የቅርብ ጓደኞቹ ወይም በእስራኤል ውስጥ ከእርሱ ጋር የሚቀራረቡ
ፍለጋውን "ፈለጉት"
እርሱ ለነገረው "ለኢየሱስ እናቱ እና ወንድሞቹ ልያናግሩት እንደሚፈለጉ ለነገረወ ሰው" እናቴ ማን ናት? ወንድሞቼስ እነማን ናቸው? ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እናቴ እና ወንድሞቼ እነማን እንደሆኑ በእርግጥ እነግራችኋለሁ" ( ተመልከት) ማንም "ማንም" አባት ይህ ለእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
የኢየሱስ ደቀመዛሙርት በሰንበት ቀን ማድረግ ያልተፈቀደ ተብሎ የሚታመነውን እሸት እየቀጠፉ ይበሉ ስለነበረ ፈሪሳውያን ስሞታ አቀረቡ። [12:2]
ኢየሱስ እርሱ ከመቅደስ እንደሚበልጥ ተናገረ። [12:6]
ኢየሱስ የሰው ልጅ የሰንበት ጌታ ነው። [12:8]
ፈሪሳውያን ኢየሱስን የጠየቁት “በሰንበት መፈወስ ተፈቅዷልን?” በማለት ነው፤ [12:10]
በሰንበት መልካምን ማድረግ እንደተፈቀደ ኢየሱስ ተናግሯል። [12:12]
ፈሪሳውያን ወጥተው እንዴት እንደሚያጠፉት ተማረከሩ። [12:14]
አሕዛብ የእግዚአብሔርን ፍርድ ሰምተው በኢየሱስ መተማመን ይኖራቸዋል። [12:18]
ኢየሱስ አይጨቃጨቅም፣ አይጮኽም፣ ድምፁን በአደባባይ አያሰማም፣ የተቀጠቀጠ ሸንበቆን አይሰብርም፣ የሚጤስንም የጧፍ ክር አያጠፋም። [12:19]
ኢየሱስ አይጨቃጨቅም፣ አይጮኽም፣ ድምፁን በአደባባይ አያሰማም፣ የተቀጠቀጠ ሸንበቆን አይሰብርም፣ የሚጤስንም የጧፍ ክር አያጠፋም። [12፡20]
ሰይጣን ሰይጣንን ቢያስወጣው፣ እንግዲያው የሰይጣን መንግሥት እንዴት ይቆማል? [12:26]
አጋንንትን በእግዚአብሔር መንፈስ ቢያስወጣ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደመጣች ኢየሱስ ተናገረ። [12:28]
መንፈስ ቅዱስን መሳደብ ይቅር እንደማይባል ኢየሱስ ተናገረ። [12:31]
ዛፍ በፍሬው ይታወቃል። [12:33]
ፈሪሳውያን በቃላቸው እንደሚጸድቊ ወይም እንደሚኮነኑ ኢየሱስ ተናገረ። [12:37]
ለትውልዱ የዮናስን ከምድር ልብ በታች ሦስት ቀንና ሦስት ቀናት ያደረበትን ምልክት ነገራቸው። [12:39]
ለትውልዱ የዮናስን ከምድር ልብ በታች ሦስት ቀንና ሦስት ቀናት ያደረበትን ምልክት ነገራቸው። [12:40]
ኢየሱስ እርሱ ከዮናስ እንደሚበልጥ ተናገረ። [12:41]
የነነዌ ሰዎች የኢየሱስን ትውልድ የሚኮንኑት የእግዚአብሔርን ቃል በዮናስ በኩል ስለ ሰሙ፣ ነገር ግን የኢየሱስ ትውልድ ከዮናስ የሚበልጠውን የሰው ልጅ ሰምተው እንኳን ስለማያውቊ ነው። [12:41]
እርሱ ከሰሎሞን እንደሚበልጥ ኢየሱስ ተናገረ። [12:42]
የኢየሱስ ትውልድ እርኩስ መንፈስ ለቅቆት እንደ ሄደበት ሰው ይመስሉ የነበረው እርኩሱ መንፈስ ከሌሎች ሰባት መናፍስት ጋር ስለሚመለሱበት እና የሰውዬው የመጨረሻ ሁኔታ ከመጀመሪያው ይልቅ የከፋ ስለሚሆን ነው። [12:43]
የኢየሱስ ትውልድ እርኩስ መንፈስ ለቅቆት እንደ ሄደበት ሰው ይመስሉ የነበረው እርኩሱ መንፈስ ከሌሎች ሰባት መናፍስት ጋር ስለሚመለሱበት እና የሰውዬው የመጨረሻ ሁኔታ ከመጀመሪያው ይልቅ የከፋ ስለሚሆን ነው። [12:44]
የኢየሱስ ትውልድ እርኩስ መንፈስ ለቅቆት እንደ ሄደበት ሰው ይመስሉ የነበረው እርኩሱ መንፈስ ከሌሎች ሰባት መናፍስት ጋር ስለሚመለሱበት እና የሰውዬው የመጨረሻ ሁኔታ ከመጀመሪያው ይልቅ የከፋ ስለሚሆን ነው። [12:45]
የአብን ፈቃድ የሚያደርጉ ሁሉ ወንድሙ፣ እህቱና እናቱ እንደሆኑ ኢየሱስ ተናገረ። [12:48]
የአብን ፈቃድ የሚያደርጉ ሁሉ ወንድሙ፣ እህቱና እናቱ እንደሆኑ ኢየሱስ ተናገረ። [12:49]
የአብን ፈቃድ የሚያደርጉ ሁሉ ወንድሙ፣ እህቱና እናቱ እንደሆኑ ኢየሱስ ተናገረ። [12:50]
በዚያ ቀን ይህ ነገር የፈጸመው ከዚህ በፊት ባለው ምዕራፍ ውስጥ የተገለጸው ታሪክ በተፈመበት ዕለት ነው፡፡ ከቤት ውጪ ኢየሱስ በማን ቤት ውስጥ በእንግድነት እንደተቀመጠ አልተገለጸም፡፡ ወደ ተንኳይቱ ገብቶ ይህ ምናልባትም ከእንጨት የተሠራ የዓሳ ማጥመጃ ጀልባ ሊሆን ይችላል፡፡
ኢየሱስ በምሳሌም ብዙ ነገራቸው "ኢየሱስ በምሳሌም ብዙ ነገራቸው " ለእነርሱ ለሕዝቡ to the people in the crowd እነሆ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "ተመልከቱ” ወይም “አድምጡ” ወይም “አሁን ለምነግራችሁ ነገር ትኩረት ስጡ” ዘሪ ሊዘራ ወጣ "አንድ ገበሬ በማሳው ላይ ዘርን ለመዝራት ወጣ" እርሱም ሲዘራ "ገበሬው ስዘራ ሳለ" መንገድ ዳር ከማሳው አጠገብ ባለ “መንገድ” ላይ፡፡ ብዙ ሰዎች በዚያ መንገድ ላይ ከመራመዳቸው የተነሳ መንገዱ ጠንክሯል፡፡ ለቀሟቸው "የተዘሩትን ዘሮች ለቀሟቸው" ዓለታማ መሬት በድንጋይ ላይ ብዙ አፈር ያሌለበት ወዲያው በቀለ "የተዘረዘው ዘር ወዲያው በቀለ” ጠወለገ "ፀሐይ በወጣ ጊዜ ግን ጠወለገ፤ በጣም ይሞቅ ነበር" ( ተመልከት) ደረቀ "ተክሉ ደረቀና ሞተ"
በእሾህ መካከል ወደቀ "የእሾህ ተክል ባለበት ሥፍራ ወደቀ" አነቀው "አዲሱን ተክል አነቀው፡፡" የተለመዱ አረሞች ሌሎች ተክሎች እንዳያድጉ የሚገልጽን ቃል ተጠቀሙ፡፡ ፍሬ ሰጠ "ፍሬ አፈራ" ወይም "ብዙ ፍሬ አፈራ” የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ። ለተርጓሚዎች ምክር፡ "ለመስማት ጆሮ ያላችሁ ስሙ" ጆሮ ያለው "ማስማት የሚችሉ ሁሉ” ወይም “የሚሰማኝ ሁሉ" ያድምጠኝ “በሚገባ ያድምጠኝ" ወይም "አሁን ለሚናገረው ነገር ትኩረት ይስጥ"
ለእነርሱ ለደቀ መዛሙርቱ ለእናንተ የመንግሥተ ሰማያትን ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቶአችኋል፥ ለእነርሱ ግን አልተሰጣቸውም። ይህ በቀጥታ በተዘዋዋሪ መንገድ የተሰጡ መረጃዎችን በማካተት እንዲህ ሊገለጽ ይችላል ፡ እግዚአብሔር የመንግስተ ሰማያትን ምስጢር መረዳት የሚትችሉበትን ዕድል ሰጥቶዋችኋ ይሁን እንጂ ይህ እድል ለሌሎች ሰዎች አልተሰጠም፡፡” ወይም እግዚአብሔር የመንግስተ ሰማያትን ምስጢር መረዳት እንዲትችሉ አድርጓል ይሁን እንጂ ለሌሎች ግን ይህ ችሎታ አልተሰጣቸውም፡፡” (en:ta:vol2:translate: and ተመልከት) አናንተ ደቀ መዛሙርት ምስጢር ለብዙ ጊዜ ተደብቆ የነበረው እውነት አሁን በኢየሱስ ተገጦዋል፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ምስጢር” ወይም “የተደበቀ እውነት”፡፡ ይህ የተሰጠው "ይህንን መረዳት የተሰጠው" ወይም "የማስተምረው ነገርን የተቀበለ ማንም ነው" ለእርሱ ተጨማሪ ይሰጠዋል ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊተረጎም ይችላል፡ “እግዚአብሐየር ተጨማሪ መረዳትን ይሰጠዋ፡፡” ( ተመልከት) ይህንን መረዳት ላለው "በግልጽ መረዳት ይችላል" ይህንን መረዳት ላሌለው "ይህንን መረዳት ላሌለው ሁሉ” ወይም "የማስተምረውን ነገር ያልተቀበለ ሰው ሁሉ" ያለው እንኳ ይወሰድበታል ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊተረጎም ይችላል፡ "ያለውን እንኳ እግዚአብሔር ይወስድበታል፡፡” ( ተመልከት)
እነግራቸዋለሁ በእነዚህ ሁለት ቁጥሮች ውስጥ “እነርሱ” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው ሕዝቡን ነው፡፡ ስለዚህ እያዩ ስለማያዩ እየሰሙም ስለማይሰሙ ስለማያስተውሉም በምሳሌ እነግራቸዋለሁ። ኢየሱስ ይህንን ትይዩዋዊ ንጽትር የጠጠቀመው ሕዝቡ ለመስማት አሻፈረኝ ማለቱን ለደቀ መዛሙርቱ ለመናገር ነው፡፡ ( ተመልከት) ማየትም ታያላችሁና አትመለከቱም። "ምንም እንኳ በዐይናቸው ቢመለከቱም አይረዱትም”፡፡ “መምለከት “ የሚለው ሁለተኛው ቃል ትርጉም መረዳት ነው፡፡ መስማት ትሰማላችሁና አታስተውሉም፥ የተሰማው ነገር ምን እንደሆነ በግልጽ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ምንም እንኳ ትምህርቱን ቢሰሙም እውነቱን ግን አይረዱተም፡፡” ( ተመልከት) መስማትን ትሰማላችሁ ነገር ግን አትረዱትም፤ ማየትን ታያላችሁ ነገር ግን አታስተውሉም ይህ ከነብዩ ኢሳያስ የተወሰደው በኢሳያስ ዘመን ይኖሩ ስለነበሩ የማያምኑ ሰዎች የተነገረው ክፍል የሚጀምርበት ነው፡፡ ኢየሱስ ይህንን ክፍል በመውሰድ እያዳመጡ ያሉት ሰዎችን ለመግለጽ ተጠቅሞበታል፡፡ ይህ ሌላኛው ትይዩዋዊ ንጽጽር ነው ( ተመልከት) መስማትን ትሰማላችሁ ነገር ግን በጭራሽ አታስተውሉም "ነገሮችን ተሰማላችሁ ነገር ግን አትረዷቸውም"፡፡ የተሰማው ነገር ምን እንደሆነ በግልጽ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ትምህርቱን ትሰማላችሁ ነገር ግን እውነቱን ግን አትረዱም” ( ተመልቱ) ማየትን ታያላችሁ ነገር ግን በጭራሽ አታስተውሉም "ነገሮችን ትመለከታላችሁ ነገር ግን አትረዷቸውም"
የዚህ ሕዝብ ልብ ደንድኖአልና "ይህ ሕዝብ ከእንግዲህ በኋላ አይማርም" ለመስማት አስቸጋሪዎች ሆነዋል "ለመስማት ምንም ፍላጎት የላቸውም" ዐይኖቻቸውን ጨፍነዋል "ለመስማት አሻፈረኝ ብለዋል" በዓይናቸው እንዳያዩ፥ ወይም በጆሮአቸውም እንዳይሰሙ፥ ወይም በልባቸውም እንዳያስተውሉ፥ እንዳይመሰሉ "በዐይኖቻው እንዳያዩ፣ በጆሮአቸውም እንዳይሰሙ፣ በልባቸውም እንዳያስተውሉ እና በዚህም ምክንያት እንዳይመለሱ" እንዳይመለሱ “ወደኋላ እንዳይመሰሉ” ወይም "ንሰሓ እንዳይገቡ” እንድፈውሳቸው "እኔ እንዳድናቸው" ለተርጓሚዎች ምክር፤ "እንደገና እንድቀበላቸው" ( ተመልከት)
እናንተ . . . እናንተ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርት እየተናገር ነው፡፡ እናንተ ስለሚታዩ "ማየት ስለሚችሉ” ወይም “እናንተ ማየት ስለሚችሉ" እናንተ ስለሙትሰሙ "እናንተ መስማት ስለሚትችሉ” ወይም “እናንተ መስማት ስለሚትችሉ” ያያችሁትን ነገር "ሳደረግ ያያችሁኝን ነገሮች" የሰማችሁኝ ነገሮች "ስናገር የሰማችሁኝን ነገሮች
ክፉው ይመጣል፥ በልቡ የተዘራውንም ይነጥቃል፤ "ሴጣን የሰማውን የእግዚአብሔርን ቃል እንዲረሣ ያደርገዋል” ይነጥቃል የአንድ ሰውን ንብረት በጉልበት መቀማትን ለመግለጥ የሚያገለግል ቃልን ተጠቀሙ፡፡ በልቡ የተዘራውንም ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊተረጎም ይችላል፡ “የእግዚአብሔር ቃል በልብቡ ውስጥ ተዘርቷል” ( ተመልከት) በልቡም ውስጥ በአድማጩ ልብ ውስጥ በመንገድ ዳር የተዘራው ይህ ነው። የቁም ትርጉሙ ምንም ትርጉም የማይሰጥ ከሆነ አንባቢዎቹ ዘሪው ኢየሱስ፣ ዘሩ መልዕክቱ እና በመንገድ ዳር ያለው አፈር ደግሞ አድማጮቹ መሆናቸው መረዳት በሚችሉበት መንገድ ለመተርጎም ጥረት አድርጉ ( and ተመልከት) በመንገድ ዳር "መንገድ” ወይም "መተላለፊያ" ይህንን በ MAT 13:4 ላይ በተረጎማችሁት መንገድ ተርጉሙት፡፡
በጭንጫ ላይ የተዘራውም የቁም ትርጉሙ ምንም ትርጉም የማይሰጥ ከሆነ አንባቢዎቹ ዘሪው ኢየሱስ፣ ዘሩ መልዕክቱ እና በመንገድ ዳር ያለው አፈር ደግሞ አድማጮቹ መሆናቸው መረዳት በሚችሉበት መንገድ ለመተርጎም ጥረት አድርጉ ( and ተመልከት) ሥር የለውም "ረጅም ሥር የለውም” ወይም “አዲሱ ተክል ለሥሩ የሚሆን ሥፍራን አያገኝም”( እና ተመልከት) ከቃሉ የተነሣ "ከመልዕክቱ የተነሣ" ወዲያውኑ ይሰናከላል "ወዲያውኑ ወድቃል" ወይም "ወዲያውኑ እምነቱን ይተዋል" ( ተመልከት)
በእሾህ መካከል የተዘራው . . . በመልካም መሬት የተዘራው የቁም ትርጉሙ ምንም ትርጉም የማይሰጥ ከሆነ አንባቢዎቹ ዘሪው ኢየሱስ፣ ዘሩ መልዕክቱ እና እሾሃማ መሬት ደግሞ አድማጮቹ መሆናቸው መረዳት በሚችሉበት መንገድ ለመተርጎም ጥረት አድርጉ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “በእሾህ መካከል የተዘረው ዘር እንዲህ ሆነ . . . በመልካም መሬት ላይ የተዘራው ዘር እንዲህ ሆነ ( እና ተመልከት) ቃል "መልዕክት" የዚህም ዓለም አሳብና የባለጠግነት መታለል ቃሉን ያንቃል፥ የማያፈራም ይሆናል። ለተርጓሚዎች ምክር፡ "አረሞች መልካም ተክል እንዳያድግ እንደሚያደርጉት ሁሉ የዓለም አሳብና የባለጠግነት መታለልም ይህ ሰው ፍሬያማ እንዳይሆን ያደርጉታል ( ተመልከት) የዓለም አሳብ "በዚህ ዓለም ውስጥ ያሉና ሰዎችን የሚያሳስቡ ነገሮች" ፍሬያማ እንዳይሆኑ ያደርጋል "ውጤታማ እንዳይሆኑ ያደርጋል" ይህ በእውነት ፍሬ የሚያፈራ ነውና ተንከባከቡት "እነዚህ ፈፍሬ የሚያፈሩ እና ውጤታማ የሚሆኑት ናቸው" ወይም "መልካም ፍሬን እንደሚያፈሩት ጤናማ አትክልቶች እነዚህ ሰዎች ውጤታማ ናቸው" ( እና ተመልከት)
ኢየሱስ ሌላ ምሳሌ ነገራቸው ኢየሱስ ለሕዝቡ ሌላ ምሳሌ ነገራው፡፡ ( ተመልከት) መንግስተ ሰማይት . . . ሰው ትመስላለች ትርጉም መነንግስተ ሰማይን ከሰውዬው ጋር እኩል ማድረግ የለበትም ይልቁንም መንግስተ ሰማያት በምሳሌ ውስጥ ከተገለጸው ሁኔታ ጋር ይመሳሰላል፡፡ *ተመልከት: መልካም ዘር "መልካም ዘሮች" ወይም "መልካም የሰብል ዘሮች”፡፡ ኢየሱስን የሚያደምጡት ሰዎች ኢየሱስ ስለ ስንዴት እየተናገረ እንደሆነ ተገንዝበዋል፡፡ ( ተመልከት) ጠላቱ መጥቶ "ጠላቱ ወደ ማሳው መጥቶ" አረሞች እነዚህ አረሞች ገና በለጋነታቸው የምግብ አትክሎቶችን የሚመስል ቢሆንም ፍሬያቸው ግን መርዛማ ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “መጥፎ ዘሮች” ወይም “የአረም ፍሬዎች” (UDB) ስንዴው በበቀለ ጊዜ "የስንዴው ዘር በበቀለ ጊዜ” ወይም “ፍሬው በበቀለ ጊዜ” ፍሬያቸውን ባፈሩ ጊዜ "ፍሬያቸውን ስያፈሩ" ወይም "የስንዴ ፍሬ ባፈራ ጊዜ" አረሞችም አብረው በቀሉ ለተርጓማች ምክር፡ "ከዚያም ሰዎች በማሳው ውስጥ አረሞችም መኖራቸውን ተመለከቱ"
የእርሻው ባለቤት ይህ በእርሻ ማሳው ላይ መልካም ዘርን ከዘራው ሰው ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ መልካምን ዘር በእርሻህ ዘርተህ አልነበርህምን? "መልካም ዘርን በእርሻህ ዘርተህ ነበር”፡፡ የመሬቱ ባለቤት ባሮቹ እንዲዘሩ አድርጋቸው ይሆናል፡፡ ( እና ተመልከት) አንዲህም አላቸው "የመሬቱ ባለቤት ለሎሌዎቹ እንዲህ አላቸው" እኛ . . . ትፈልጋለህን “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሎሌዎቹን ነው፡፡
የመሬቱ ባለቤት እንዲህ አለ "የመሬቱ ባለቤት ለሎሌዎቹ እንዲህ አለ" አጫጆችን፦ “እንክርዳዱን አስቀድማችሁ ልቀሙ በእሳትም ለማቃጠል በየነዶው እሰሩ፥ ስንዴውን ግን በጎተራዬ ክተቱ” እላለሁ አለ። ይህንን በትምህርተ ጥቅስ ውስጥ ሳትከቱ መተርጎም ትችላላችሁ፡ “ለአጫጆቹ እንዲህ እላቸዋለሁ፤ በመጀመሪያ በእሳት እዲቃጠል እንክርዳዱን ሰብሰቡና በአንድ ላይ እሰሩ ከዚያም ስዴውን ሰብስባችሁ ወደ ጎተራዬ አስገቡ ( ተመልከት) ጎተራዬ ጎተራ በእርሻ ቦታ የሚሠራ የሰብል ምርት ማከማቻ ነው፡፡
ኢየሱስ እንዲህ ሲል ሌላ ምሳሌ አቀረበላቸው "ኢየሱስ ለሕዝቡ ሌላ ምሳሌ ነገራቸው" ( ተመልከት) መንግስተ ሰማያት . . . ትመስላለች ይህንን በ MAT 13:24 ላይ እንዴት እንደተረጎምህ ተመልከት፡፡ የሰናፍጭ ፍሬ ትልቅ ዛፍ የሚትሆን በጣም ትን ሽ ዘር ( ተመልከት) ይህ ዘር ከሌሎች ዘሮች ሁሉ ይልቅ በጣም ትንሽ ናት የምሳሌው የመጀመሪያ አድማጮች ከሚያውቋቸው ዘሮ መካከል በጣም ትንሸዋ የሰናፍጭ ፍሬ ናት ( ተመልከት) ይሁን እንጂ ካደገች በኋላ "ይሁን እንጂ ተክሏ ካደገች በኋላ" ዛፍ ይሆናል "በጣም ትልቅ ዛፍ ይሆናል" ( እና እና ተመልከት) የሰማይ ወፎች "ወፎች" ( ተመልከት)
ከዚያም ኢየሱስ ሌላ ምሳሌ ነገራቸው "ከዚያም ኢየሱስ ለሕዝቡ ሌላ ምሳሌ ነገራቸው" ( ተመልከት) መንግስተ ሰማየት . . . ትመስላለች በ MAT 13:24 ላይ እንዴት እንደተረጎምህ ተመልከት፡፡ መንግስቱ እንደ እርሾ አይደለም ይሆኑ እንጂ የመንግስቱ መስፋፋት እንደ እርሾ ነው ተመልከት) ሦስት መሥፈሪያ ዱቄት "ብዙ ዱቄት" ወይም በባሕላችሁ ውስጥ ብዙ መጠን ያለው የዱቄት መሥፈሪያን መጠቀም ትችላላችሁ፡፡ እስኪቦካ ድረስ እስኪቦካ ድረስ፡፡ በዚህ ሥፍራ በተዘዋዋር የተሰጠው መረጃ ዳቦ ለመጋገር በሦስት መሥፈሪያ ዱቄቱ ላይ እርሾ ተጨምሮ መቦካቱ ነው፡፡ ( ተመልከት)
ኢየሱስም ለሕዝቡ ይህን ሁሉ በምሳሌ ተናገረ፤ ያለ ምሳሌ አልተናገራቸውም። ቅደም ተከተሉ “ተናገረ . . . በምሳሌዎች . . . በምሳሌዎች . . . ተናገረ”፡፡ ይህንን ቅደም ተከተል የተከተለው በምሳሌ እንደተናገራቸው አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ ( ተመልከት) እነዚህን ሁሉ ነገሮች ይህ ኢየሱስ በ MAT 13:1 መጀመሪያ ላይ ያስተማረውን ያመለክታል፡፡ ያለ ምሳሌ ምንም አልተናገራቸውም "ከምሳሌ ውጪ ምንም አልነገራቸውም" ለተርጓሚዎች መክር፡ "የነገራውን ሁሉ በምሳሌ ነገራቸው" ( እና ተመልከት) በነቢዩምየተባለው ይፈጸም ዘንድ፣ እኔ ስናገር ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ልገለጽ ይችላል፡ “ከብዙ ዘመናት በፊት እግዚአብሔር ለአንድ ነቢይ እንዲጽፍ ያደረገው ነገር እውን እንዲሆን አደረገ” (UDB). ( ተመልከት) የተሰወረ ነገር ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ልገለጽ ይችላል፡ “ለብዙ ጊዜያት ተሰውሮ የነበረው ነገር" ( ተመልከት) ዓለም ከተፈጠረ ጊዜ ጀምሮ "ከፍጠትረታት ጅማሬ አንስቶ" ወይም "እግዚብሔር ዓለምን ከፈጠረበት ጊዜ አንስቶ"
ወደ ቤት ገባ "ወደ ቤት ውስጥ ገባ" ወይም "ወደሚያርፍበት ቤት ገባ" ዘር የዘራው "ዘሪው" የሰው ልጅ በዚህ ሥፍራ ኢየሱስ ራስን እያመለከተ ነው፡፡ የመንግስቱ ልጆች "የመንግስቱ አካል የሆኑ ሰዎች” የክፉ ልጆች "የክፉ የሆኑት ሰዎች" ጠላት የዘራቸው እንክርዳዱን የዘረው ጠላት የዓለም መጨረሻ "የዘመን መጨረሻ"
ስለዚህ እንክርዳዱ ተሰብስቦ እንዲቃጠል ሲደረግ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊተረጎም ይችላል፡ “ስለዚህም ሰዎቹ እንክርዳዱን ሰብስበው ስያቃጥሉ" ( ተመልከት) የዓለም መጨረሻ "የዘመን መጨረሻ" የሰው ልጅ መላእክቱን ይልካል በዚህ ሥፍራ ኢየሱስ ስለ ራሱ እየተናገረ ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እኔ፣ የሰው ልጅ መላእክት እልካቸዋለሁ”፡፡ ዓመፃን የሚያደርጉት "ክፋትን የሚያደርጉ" ወይም "ክፉ ሰዎች" እቶን እሳት ለተርጓሚዎች ምክር፡ "እቶን እሳት”፡፡ “ማቃጠያ ሥፍራ” የሚለው ቃል በእናንተ አከባቢ የማይታወቅ ከሆነ “እሳት ማንደጃ ሥፍራ” የሚለውን ቃል መውሰድ ይቻላል፡፡ እንደ ጸሐይ ይበራል "ልክ እንደ ፀሐይ የሚትታዩ ሁኑ” ( ተመልከት) የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ። ለተርጓሚዎች ምክር: "ጆሮ ያለው ይስማ” ወይም “ጆሮዎች ያሉት እንገግዲህ ያድምጥ"፡፡
መንግስተ ሰማያት . . . ትመስላለች በ MAT 13:24 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ (ተመልከት) በእርሻ ውስጥ የተሰወረን መዝገብ ትመስላለች መዝገብ በጣም ጠቃ፣ እና ውድ የሆኑ ነገሮች ስብስብ ነው፡፡ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊተረጎም ይችላል፡ “የሆነ ሰው በእርሻ ውስጥ የደበቀው መዝገብ” ( እና ተመልከት) ደበቀው "covered it up" ያለውን ሁሉ ሸጠና ያን እርሻ ገዛ በዚህ ሥፍራ ላይ በተዘዋዋሪ መንገድ የተገለጸው መረጃ የተሰወረ መዝገብ በውስጡ የያዘው የእርሻ ቦት ሰውዬው መግዛቱ ነው፡፡ (ተመልከት ነጋዴ ነጋዴ የተለያዩ ነገሮችን የሚሸጥ፣ ብዙ ጊዜም የሚሸጡ ነገሮችን ከሩቅ ሥፍራ የሚያመጣ ነው፡፡ መልካምን ዕንቁ የሚሻ ነጋዴን ትመስላለች፤ በዚህ ሥፍራ ላይ በተዘዋዋር መንድ የተገለጸው መረጃ መሠረት ይህ ሰው መልካም ዕንቁን ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ውድ ዕንቁ “ዕንቁ” ለስላሳ፣ ጠንካራ፣ የሚያንጸባርቅ፣ ነጭ ወይም ቀለል ያለ ቀለም ያለው ከውሃ ውስጥ የሚገኝ እና ውድ የሆኑ ጌጣ ጌጦችን ለማዘጋጀት የሚውል ውስድ ነገር ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “መልካም ዕንቆዎች” ወይም “የሚያምሩ ዕንቁዎች”፡፡
መንግስተ ሰማያት . . . ትመስላለች በ MAT 13:24 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ የእግዚአብሔር መንግስት እንደ መረብ አይደለችም ይሁን እንጂ መንግስተ ሰማያት ልክ መረብ የተለያዩ ዓሳዎችን እንደሚይዝ እንዲሁ መንግስተ ሰማይም ሁሉንም ዓይነት ሰዎችን ወደራሱ ይሰበስባል፡፡ ( ተመልከት) ወደ ባሕር እንደሚጣል መረብ ይህ በዚህ ዓይነት መንገድ ሊተረጎም ይችላል፡ “አንዳንድ ዓሳ አጥማጆች ዓሳ ለማጥመድ ወደ ባሕር ውስጥ እንደሚጥሉት መረብ፡፡” ( ተመልከት) ወደ ባሕር ውስጥ የሚጣል ባሕር "ወደ ባሕር ውስጥ የሚጣል መረብ" ሁሉንም ዓይነት ፍጥረታትን እንደሚሰበስብ "ሁሉንም ዓይነት ዓሳዎች እንደሚይዝ" ወደ ወደቡ አወጦአት "መረቡን ወደ ባሕሩ ዳርቻ አወጡት” ወይም “መረቡን ወደ ባሕሩ ዳርቻ ጎትተው አወጡት" መልካም የሆኑ ነገሮችን "ጥሩ ጥሩውን ነገር" ጥቅም ያሌለውን "መጥፎዎቹን ዓሳዎች" ወይም "የማይበሉ የዓሳ ዓይነቶችን ግን" አውጥተው ይጥሉአቸዋል "አያስቀምጡትም"
ማቴዎስ 13፡49-50
የዓለም መጨረሻ "የዘመን መጨረሻ" መጣ "ከሌላ ቦታ የመጣ" ወይም "የሚሄድ" ወይም "ከሰማይ የመጣ" ወረወራቸው "ክፉዎቹን ወረወራቸው" ቆሻሻ ማቃጠያ እሳት ይህ የገሃነም እሳት ምሳሌ ነው፡፡ “ቆሻሻ ማቃጠያ” የሚለው የማይታወቅ ከሆነ “ማቃጠያ” የሚል ቃል ልንጠቀም እንችላለን፡፡ ለተርጓማች ምክር፡ "የማቃጠያ ሥፍራ" ( ተመልከት) በዚያ ለቅሶ እና የጥርስ ማፋጨት ይሆናል "ክፉዎች የሚያለቅሱበት እና ጥርሳቸውን የሚያፋጩበት ሥፍራ"
ማቴዎስ 13፡51-53
ይህን ሁሉ አስተዋላችሁን? ደቀ መዛሙርቱ “አዎን” አሉት፡፡ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ይህን በቀጥታ በመጥቀስ ሳይጠቀስ ማስቀመጥ ይቻላል፡፡ “ይህንን ሁሉ በደንብ መረዳታቸውን ኢየሱስ ጠየቃቸው፣ እነርሱን አዎን ተረድተነዋል ( ተመልከት) ደቀ መዝሙር የሆነ "ስለሆነ ነገር ተማረ" መዝገብ መዝገብ በጣም ውድ እና ዋጋ ያላቸው ነገሮች ስብስብ ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ እነዚህ ነገሮች የተከማቹበት ሥፍራን፣ “መጋዝን” ማለት ነው፡:
ወደ ገዛ አገሩ "የእርሱ ሀገር" ወደ ምኩራቦች በዚህ ሥፍራ ላይ “የእነርሱ” የተጠቀሰው ተውላጠ ስም በዚያ አከባቢ ያሉ ሰዎችን ያመለክታል፡፡ በጣም ተገረሙ "ተደነቁ" በእነዚህ ተዓምራቶች "እነዚህን ተዓምራት ያደረገበትን ኃይል ከዬት አገኘ” ( ተመልከት) የአናጥዉ ስም አናጢ ከእንጨት ወይም ከድንጋይ የተለያዩ ነገሮችን የሚያበጅ ሰው ነው፡፡ “አናጢ” የሚለው ቃል በእናንተ ዘንድ የማይታወቅ ከሆነ “ግንበኛ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡
ተሰናከሉበት "ኢየሱስ በሚኖርበት መንደር ውስጥ የሚኖሩት ሰዎች በእርሱ ተሰናከሉበት” ወይም “. . . እርሱን አይቀበሉትም” ነብይ አይከበርም "ነብይ በሁሉም ሥፍራ ይከበራል" “ነብይ ክብርን በሁሉም ሥፍራ ያገኛል” ወይ “በሁሉም ሥፍራ ያሉ ሰዎች ነብያትን ያከብራሉ” ( ተመልከት) በገዛ ሀገሩ "በአከባቢው" ወይም "በመንደሩ" የገዛ ቤተሰቦቹ "በራሱ ቤት" በዚያም ብዙ ተዓምራትን አላደረገም “ኢየሱስ በገዛ ሀገሩ ብዙ ተዓምራትን አላደረገም”፡፡
በመንገድ ዳር የወደቀው ዘር ወፎች ለቀሙት። [13:4]
በዐለታማ መሬት ላይ የወደቀው ዘር ወዲያውኑ በቀለ፣ ነገር ግን ፀሐይ አጠወለገውና ደረቀ። [13:5]
በዐለታማ መሬት ላይ የወደቀው ዘር ወዲያውኑ በቀለ፣ ነገር ግን ፀሐይ አጠወለገውና ደረቀ። [13:6]
በእሾህ መሃል የወደቀው ዘር በእሾኹ ታነቀ። [13:7]
በመልካም መሬት ላይ የወደቀው ዘር አንዳንዱ መቶ እጥፍ፣ ሌላው ስድሳ፣ ሌላው ሠላሳ አፈራ። [13:8]
የኢሳይያስ ትንቢት ሰዎቹ እንደሚሰሙ፣ ነገር ግን እንደማያስተውሉ፣ እንደሚያዩ ግን ልብ እንደማይሉ ይናገራል። [13:14]
ኢየሱስን የሚሰሙ ነገር ግን በሙሉ ልባቸው የማያስተውሉ ሰዎች ልባቸው ደንድኖ መስማት ትተዋል፣ ዐይኖቻቸውም ተጨፍኗል። [13:15]
በመንገድ ዳር እንደተዘራው ዘር የሆነው የመንግሥቱን ቃል ሰምቶ የማያስተውለው ሰው ነው፣ ከዚያም ክፉው መጥቶ በልቡ የተዘራውን ይወስዳል። [13:19]
በዓለታማ መሬት ላይ የተዘራው ዘር ቃሉን ሰምቶ ወዲያውኑ በደስታ የሚቀበለው፣ ነገር ግን ስደት በተነሣ ጊዜ ወዲያውኑ የሚሰናከል ነው። [13:20]
በዓለታማ መሬት ላይ የተዘራው ዘር ቃሉን ሰምቶ ወዲያውኑ በደስታ የሚቀበለው፣ ነገር ግን ስደት በተነሣ ጊዜ ወዲያውኑ የሚሰናከል ነው። [13:21]
በእሾህ መካከል የተዘራው ዘር ቃሉን የሚሰማ፣ ነገር ግን የዚህ ዓለም ጉዳዮች እና የብልጥግና ማታለል ቃሉን አንቆ የሚያስቀርበት ነው። [13:22]
በመልካም መሬት ላይ የተዘራው ዘር ቃሉን ሰምቶ የሚያስተውለው፣ ከዚያም ፍሬ የሚያፈራበት ሰው ነው። [13:23]
በእርሻው ውስጥ ጠላት እንክርዳዱን ዘራ። [13:28]
የእርሻው ባለቤት ስለ እንክርዳዱ እና ስንዴው ለአገልጋዮቹ የሰጠው መመሪያዎች ምንድናቸው?
የስናፍጯ ቅንጣት ከሌሎች አትክልቶች በላይ ትልቅ ዘፍ ሆነችና ከዚያም የተነሣ ወፎች በቅርንጫፎቿ ላይ ተጠለሉ። [13:31]
የስናፍጯ ቅንጣት ከሌሎች አትክልቶች በላይ ትልቅ ዘፍ ሆነችና ከዚያም የተነሣ ወፎች በቅርንጫፎቿ ላይ ተጠለሉ። [13:31]
የእግዚአብሔር መንግሥት ሊጡን ሁሉ እስኪያቦካ ድረስ የተለወሰ ሦስት መስፈሪያ እርሾ ነው በማለት ኢየሱስ ተናገረ። [13:33]
የመልካሙ ዘር ዘሪ የሰው ልጅ ነው፣ እርሻው ዓለም ናት፣ መልካሙ ዘር የመንግሥት ልጆች ናቸው፣ እንክርዳዱ የክፉው ልጆች ናቸው፣ የእንክርዳዱ ዘሪ ዲያቢሎስ ነው። [13:37]
የመልካሙ ዘር ዘሪ የሰው ልጅ ነው፣ እርሻው ዓለም ናት፣ መልካሙ ዘር የመንግሥት ልጆች ናቸው፣ እንክርዳዱ የክፉው ልጆች ናቸው፣ የእንክርዳዱ ዘሪ ዲያቢሎስ ነው። [13:38]
የመልካሙ ዘር ዘሪ የሰው ልጅ ነው፣ እርሻው ዓለም ናት፣ መልካሙ ዘር የመንግሥት ልጆች ናቸው፣ እንክርዳዱ የክፉው ልጆች ናቸው፣ የእንክርዳዱ ዘሪ ዲያቢሎስ ነው። [13:39]
አጫጆቹ መላእክት ሲሆኑ፣ መከሩ ደግሞ የዓለም ፍጻሜ ነው። [13:39]
በዓለም መጨረሻ ላይ ዓመጻን የሚያደርጉት ወደ ሚነድደው እሳት ይጣላሉ። [13:42]
በዓለም መጨረሻ ላይ፣ ጻድቃን እንደ ፀሐይ ያበራሉ። [13:43]
ሃብትን ያገኘው ሰው ያለውን ሁሉ ሸጦ እርሻውን ገዛ። [13:44]
ታላቅ ዋጋ ያላትን ውብ ዕንቊ ያገኘው ሰው ያለውን ሁሉ ነገር ሸጦ ይገዛዋል። [13:45]
ታላቅ ዋጋ ያላትን ውብ ዕንቊ ያገኘው ሰው ያለውን ሁሉ ነገር ሸጦ ይገዛዋል። [13:46]
የማይጠቅሙት ነገሮች ከመልካሞቹ ተለይተው ከመረብ እንደተጣሉ ሁሉ፣ በዓለም መጨረሻ ላይ ክፉዎች ከጻድቃን ተለይተው ወደ እሳት ይጣላሉ። [13:47]
የማይጠቅሙት ነገሮች ከመልካሞቹ ተለይተው ከመረብ እንደተጣሉ ሁሉ፣ በዓለም መጨረሻ ላይ ክፉዎች ከጻድቃን ተለይተው ወደ እሳት ይጣላሉ። [13:48]
ሰዎቹ፣ “ይህ ሰው ይህንን ጥበብ እና ተዓምራት ከየት አገኘው” በማለት ጠየቁ። [13:54]
ነብይ በገዛ አገሩ እንደማይከበር ኢየሱስ ተናገረ። [13:57]
ከሰዎቹ አለማመን የተነሣ፣ ኢየሱስ በገዛ ክልሉ ብዙ ተዓምራት ማድረግ አልቻለም። [13:58]
በዚያ ጊዜ "በዚያ ዘመን" ወይም “ኢየሱስ በገሊላ እያገለገለ ሳለ" የአራተኛው ክፍል ገዥ የሆነው ሄሮዶስ ሄሮድ አንቲፓስ የእስራኤልን አንድ አረተኛ ግዛት ይገዛ ነበር ( ተመልከት) ስለኢየሱስ ዝና ሰማ "ሰዎች ስኢየሱስ የሚሉትን ሰማ" ወይም "ስለ ኢየሱስ ዝና ሰማ" እንዲህም አለ "ሄሮዶስ እንዲህ አለ"
ሄሮዶስ ዮሐንስን አስይዞ አሳስሮት በወህኒ አኑሮት ነበር ይህ የሚሆነው ሄሮዶስ ሌሎች ሰዎችን በእርሱ ፈንታ ሄደው ዮሐንስን እንዲይዙት በማዘዝ ነው ( ተመልከት) ሄሮዶስ ዮሐንስን አስያዘው "ሄሮዶስ ዮሐንስ እንድታሠሰር አደረገ" ዮሐንስ፦ እርስዋ ለአንተ ትሆን ዘንድ አልተፈቀደም ይለው ነበርና። “እርሷን ምስትህ አድርገህ መውሰድ ለአንድ አልተፈቀደም ስላለው ነው ( ተመልከት) ዮሐንስ ስላለው ነው "ዮሐንስ ይህንን ደጋግሞ ለሄሮዶስ ይለው ነበር" በሕግ አክተፈቀደም ሄሮዶስ ሄሮዲያስን ስያገባ ፊልፕ በሕይወት ነበር፡፡
በዚህ መካከል የልደት ክብረ በዓል ለማክበር የመጡ እንግዶች መካከል ( ተመልከት)
የእናቷን ምክር ተከትላ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እናትየው ከመከረቻት በኋላ" ( ተመልከት) ተምክራ "መመሪያ መሠረት" እንዲህ አለች “እርሷ” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው የሄሮዲስን ሴት ልጅ ነው፡፡ ሳህን ትልቅ ሳህን ንጉሡ በጥያቄዋ እጅግ በጣም ተበሳጨ "ጥያቄዋ ንጉሡን አበሳጨው" ( ተመልከት) ንጉሥ የአራረተኛ ክፍል ገዥው ሄሮዶስ አንቲፓስ (MAT 14:1).
ጭንቅላቱን በሳህን አድርገው ለልጅቷ ሰጧት "የሆነ ሰው ጭንቅላቱን በሳህን አድርጎ ለልጅቷ ሰጣት" ( ተመልከት) ሳህን ትልቅ ሳህን ሴት ልጅ ያላገባች ልጅን የሚያመለክት ቃልን ተጠቀም፡፡ ደቀ መዛሙርቱ "የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት" ሬሳውን "በድኑን" ወደ ኢየሱስ ሄደው ነገሩት "የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ ኢየሱስ ዘንድ ሄደው መጥመቁ ዮሐንስ ላይ ምን እንዳደረጉበት ለኢየሱስ ነገሩት ( ተመልከት
ይህንን ስሰማ "በዮሐንስ ላይ የሆነውን ነገር ስሰማ" ወይም "ስለ ዮሐንስ የተነገረውን ነገር ስሰማ” ( ተመልከት) ፈቀቅ አለ ከሕዝቡ ተለይቶ ሄደ ከዚያ "ከዚያ ሥፍራ" ሕዝቡን ይህንን ስሰሙ “ሕዝቡን ወዴት እንደሄደ በሰሙ ጊዜ” ወይም “እንደሄደ ሕዝቡ በሰሙ ጊዜ” ሕዝቡ "ሕዝቡ" ወይም “የተሰበሰበው ሕዝብ” ኢየሱስ ወደ እነርሱ መጥቶ የተሰበሰበውን ብዙ ሕዝብ ተመለከተ "ኢየሱስ ወደ ባሕሩ ዳርጃ በመጣ ጊዜ ብዙ ሕዝብ ተሰብስቦ ተመለከተ”
ደቀ መዛሙርቱም ወደ እርሱ መጥተው "የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ መጥተው"
አያስፈልጋቸውም "ሕዝቡ . . . አያስፈልጋቸውም" እናንተ ስጧቸው “አናንተ” የሚለው ቃል የብዙ ቁጥር አመልካች ሲሆን የሚያመለክተውም ደቀ መዛሙርቱን ነው፡፡ (en:ta:vol1:translate: ተመልከት) እነርሱም እንዲህ አሉት "ደቀ መዛርቱ ለኢየሱስ እንዲህ አሉት" አምስት ዳቦ እና ሁለት ዓሣ "5 ዳቦዎች እና 2 ዓሣዎች ( ተመልከት) እነርሱን ወደ እኔ አምጧቸው "ዳቦዎቹን እና ዓሣዎቹን ወደ እኔ አምጧቸው"
ተቀመጡ ወይም “ይረፉ”፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ በእናንተ ባሕል ውስጥ ሰዎች ምግብ ለመመገብ የሚቀመጡበትን መንገድ የሚገልጽ ቃልን ተጠቀሙ፡፡ ወሰደ "በእጆቹ ይዞ፡፡" ሰርቋቸው አይደለም፡፡ (en:ta:vol1:translate: ተመልከት) ዳቦዎች "ዳቦዎች” ወይም “ያላቸውን ሁሉ ዳቦ" ወደ ሰማይ ተመለከተ ይህ ማለት 1) “ወደላይ እየተመለከተ” ወይም 2) “ወደላይ ከተመለከተ በኋላ”፡፡ እነርሱም ወደ ላይ ተመለከቱ "ደቀ መዛሙርቱም ደወ እርሱ ተሰበሰቡ " የበሉትም ሰዎች ዳቦውን እና ዓሣውን የበሉት ሰዎች" ( ተመልከት)
ወዲያውም "ኢየሱስ አምስት ሺህ ሰዎችን ከመገበ በኋላ" በመሸም ጊዜ "ወደ ምሽት ላይ” ወይም “በጨለመ ጊዜ”" ከማዕበሉ የተነሳ ልቆጣጠሯት አልቻሉም "ማዕበሉ ታንኳይቱን ያናውጣት ነበር"
በባሕሩ ላይ እየተራመደ "በውሃው ላይ እየተራመደ" በጣም ፈሩ "ደቀ መዛሙርቱ በጣም ፈሩthe disciples were very afraid" ምትሃት የሞተ ሰውን ትቶ የሄደ መንፈስ መሰላቸው
ጴጥሮስ እንዲህ ሲል መለሰ "ጴጥሮስ ለኢየሱስ እንዲህ ሲል መለሰ"
አንተ እምነት የጎደለህ በ MAT 6:30 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ስለምን ትጠራጠራለህ? "ልትጠራጠር አይገባህም" ( ተመልከት) የእግዚአብሔር ልጅ የይህ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት የሚገልጽ በጣም አስፈላጊ የሆነ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
በተሻገሩም ጊዜ "ኢየሱስ እና ደቀ መዛሙርቱ ባሕሩን ከተሸገሩ በኋላ" ጌንሴሬጥ ከገሊላ ባሕር ማዶ በሰሜን ደቡብ በኩል የሚትገኝ ትንሽ መንደር ናት ( ተመልከት) መልዕከት ላኩ "በዚያ አከባቢ የሚኖሩ ሰዎች መልዕክት ላኩ” ለመኑት "የታመሙት ሰዎች ለመኑት" ልብስ "የለበሰው ልብስ”
ኢየሱስ ከሞት የተነሣው መጥምቊ ዮሐንስ እንደሆነ ሔሮድስ አሰበ። [14:2]
ሔሮድስ የወንድሙን ሚሰት አግብቶ ነበር። [14:4]
ሔሮድስ መጥምቊ ዮሐንስንስን ወዲያውኑ ያላስገደለው ዮሐንስን እንደ ነበብይ ይቆጥሩ የነበሩትን ሰዎች ስለፈራ ነበር። [14:5]
የምትጠይቀውን ሁሉ ሊሰጣት ሔሮድስ በመሃላ ቃል ገባላት። [14:7]
ሔሮድያዳስ ምን ጠየቀች?
ሔሮድስ ለሔሮድያዳስ የጠየቀችውን የሰጣት ከመሐላው የተነሣ እና እራት ላይ አብረውት ከነበሩት ሰዎች የተነሣ ነው። [14:9]
ብዙ ሕዝብ ሲከተለው ባየ ጊዜ ኢየሱስ ያደረገው ነገር ምን ነበር?
ደቀመዛሙርቱ ለሕዝቡ ምን እንዲያደርጉ ነው ኢየሱስ የጠየቃቸው?
ደቀመዛሙርቱ ለሕዝቡ ምን እንዲያደርጉ ነው ኢየሱስ የጠየቃቸው?
አምስት ሺህ ወንዶች እንዲሁም ሴቶች እና ሕጻናት ተመገቡና ዐሥራ ሁለት ቅርጫት ሙሉ ተረፈ። [14:20]
ምን ያክል ሰዎች ተመገቡ፣ ምን ያክልስ ምግብ ተረፈ?
ኢየሱስ ሕዝቡን ከሸኛቸው በኋላ ምን አደረገ?
የደቀመዛሙርቱ ጀልባ ከንፋሱ እና ከማእበሉ የተነሣ ከሞላ ጎደል ከቊጥጥር ውጪ ሆና ነበር። [14:24]
ኢየሱስ በውሃ ላይ እየተራመደ ወደ ደቀመዛሙርቱ ሄደ። [14:25]
ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ እንዳይደነግጡና እንዳይፈሩ ነገራቸው። [14:27]
ኢየሱስ ለጴጥሮስ የነገረው መጥቶ በውሃ ላይ እንዲራመድ ነበር። [14:29]
ጴጥሮስ ውሃ ውስጥ የሰጠመው በፈራ ጊዜ ነበር። [14:30]
ጴጥሮስ እና ኢየሱስ ወደ ጀልባው በሄዱ ጊዜ፣ ንፋሱ መንፈሱን ተወ። [14:32]
ደቀመዛሙርት ይሄንን ባዩ ጊዜ፣ ኢየሱስን በማምለክ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ተናገረ። [14:33]
ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱ ወደ ባሕሩ ማዶ በደረጉ ጊዜ፣ ሕዝቡ ታምመው የነበሩትን ሁሉ አመጧቸው። [14:35]
የሽማግሌዎችን ወግ ይተላለፋሉ "በትልልቅ የሃይማኖት መሪዎች የተሰጡትን ደንቦች አይጠብቁም" እጃቸውን አይጣጠቡም "በሕጉ መሠረት የተሰጠውን የእጅ መታጠብ ስርዓትን በመከተል እጃቸውን አይታጠቡም ( ተመልከት)
ማንም "ዬትኛውም ሰው" ወይም "ማንም ቢሆን" አባቱን ሊያከብር የማይወድ አባቱን በመንከባከብ ለእርሱ ያለውን አክብሮት ለማሳየት የማይፈልግ ሰው ለወጋችሁ ስትሉ የእግዚአብሔርን ቃል አፍርሳችሁታል ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ስለ ወጋችሁም የእግዚአብሔርን ቃል ሻራችሁ።”
ኢሳያስ ስለ እናንተ ምን አለ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "ኢሳያስ በዚህ ትንቢት ላይ የተናገረው እውነት ነው” እንዲህ ሲል ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እግዚአብሔር የተናገረውን ስናገር" ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል ኤቲ፡ “ይህ ሕዝብ ስለእኔ ትክክል የሆኑ ነገሮችን ይናገራል” ልቡ ግን ከእኔ ርቋል ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ይሁን እንጂ በእርግጥ አይወዱኝ” (en:ta:vol1:translate: ተመልከት) እንዲሁ በከንቱ ያመልኩኛል ለተርጓሚዎች ምክር፡ “አምልኮአቸው ለእኔ ምንም አይደለም” ወይም “እኔን ያመለኩ ያስመስላሉ” የሰው ስርዓት "ሰዎች በሰሩት ስርዓት"
ሰሙ አስተዋሉም ኢየሱስ ከዚህ ቀጥሎ ላለው ዓረፍተ ነገር አጽኖት በመስጠት ተናግሯል
ይህን ቃል የሰሙ ፈሪሳዊያን እንደ ተሰናከሉብህ አወቅህን? ለተሯሚዎች ምክር፡ “ይህ ዓረፍተ ነገር ፈሪሳዊያንን አበሳጭቷቸዋል?" ወይም "ይህ ዓረፍተ ነገር ፈሪሳዊያንን አሰናክለሏልን?" ( ተመልከት)
ለእኛ "ለእኛ ለደቀ መዛሙርትህ" ያለፋል "ይወጣል" እዳሪ ሰዎች የሆድ እዳሪያቸውን የሚያስወግዱበት ሥፍራን በጨዋ ቋንቋ ለመግለጽ ነው፡፡
ከአፍ የሚወጣ "አንድ ሰው የሚናገረው ቃል" ከልብ ይወጣል "ከሰውዬው እውነተኛ ስሜት እና ሀሳቦች ውጤት ናቸው” መግደል ንጹሕ ሰውን መግደል ስድብ "ሌላ ሰውን የሚያሰናክል ነገር ማነገር" ያልታጠበ እጅ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ ያልታጠበ እጅ
ከነናዊት ሴት ከዚያ አገር ሴትቱ ሀገሯን ትታ ወደ እስራኤል በመምጣት ኢየሱስን አገኘችው ከነናዊት ሴት ከነዓን የሚባል ሀገር አሁን የለም፡፡ “ከነዓን ተባለ ሀገር ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች መካከል የሆነች አንዲት ሴት" ሴት ልጄን ጋኔን ክፉኛ ይዞአታል "ሴት ልጄን ጋኔን በጣም እያሰቃያት ነው” ( ተመልከት) ምንም ቃል አልመለሰላትም "ዝም አላት"
ወደ እርሱ መጣች "ከነዓናዊቷ ሴት ወደ እርሱ መጣች" የልጆችን እንጀራ ...ለቡችሎች "በትክክለኛው መንገድ ለአይሁዶች የሆነውን ነገር . . . ለአሕዛብ" ( ተመልከት)
ቡችሎች እንኳ ከጌቶቻቸው ማዕድ የተራረፈውን ይበላሉ አሕዛብ ከአይሁዳዊያን የተራረፈው መልካም ነገር ልያገኙ ይገባል፡፡ ( ተመልከት) ሴት ልጇ ተፈወሰች "ኢየሱስ ሴት ልጇን ፈወሰላት” ወይም "ኢየሱስ የሴት ልጇን ጤና መለሰላት” ( ተመልከት) በዚያን ጊዜ "በተመሳሳይ ሰዓት" ወይም "ወዲያው"
ሽባ፣ ዐይነ ስውር፣ ዲዳ እና መሄድ የማይችል "መራመድ የማይችሉ ሰዎች፣ ማየት የማይችሉ አንዳንዶች፣ መናገር የማይችሉ፣ እግራው እና እጃቸው የማይሰራ ሰዎች”፡፡ አንዳንድ ጥንታዊያን ቅጅዎች እነዚህን ቃላት በተለያየ ቅደም ተከተል አስቀምጠውታል፡፡ በኢየሱስ እግሪ ፊት አስቀመጡ "ሕዝቡ የታመመውን ሰው በኢየሱስ ፊት አስቀመጡ"
ዝለው እንዳይወድቁ አማራጭ ትርጉሞች 1) “ራሳቸነውን እንዳይስቱ በመፍራት” ወይም 2) “ሊደክማቸው ይችላል ከሚል ስጋት” ( ተመልከት) ተቀመጡ ጠረጴሳ ባሌለበት ሁኔታ ሰዎች ምግብ ለመመገብ በባሕላችሁ የሚቀመጡበትን መንገድ የሚገልጽ ቃልን ተጠቀም፡፡
ወሰደ "ኢየሱስ ወስዶ” ፡፡ ይህንን በ MAT 14:19 በተረጎምከው መሠረት ተርጉመው፡፡ ስጧቸው "ዳቦዎቹን እና ዓሳዎቹን ስጧቸው" ለቀሟአቸው "ደቀ መዛሙርቱ ለቀሙ" የተመገቡት "የበሉት ሰዎች" አከባቢ "የአንድ ሀገር አንዱ ክፍል" መጌዶል አንዳንድ ጊዜ “ማጌዳላ” ተብሎ ይጠራል ( ተመልከት)
ፈሪሳውያኑ “ለእግዚአብሔር የሚሰጥ ስጦታ” ነው በማለት ገንዘብ እየወሰዱ ልጆች ወላጆቻቸውን እንዳይረዱ ይከለክሏቸው ነበር። [15:4]
ፈሪሳውያኑ “ለእግዚአብሔር የሚሰጥ ስጦታ” ነው በማለት ገንዘብ እየወሰዱ ልጆች ወላጆቻቸውን እንዳይረዱ ይከለክሏቸው ነበር። [15:4]
ፈሪሳውያኑ “ለእግዚአብሔር የሚሰጥ ስጦታ” ነው በማለት ገንዘብ እየወሰዱ ልጆች ወላጆቻቸውን እንዳይረዱ ይከለክሏቸው ነበር። [15:4]
ፈሪሳውያን እግዚአብሔርን በከንፈራቸው ያከብራሉ፣ ልባቸው ግን ከእግዚአብሔር የራቀ እንደሆነ ኢሳይያስ ተነበየ። [15:7]
ፈሪሳውያን እግዚአብሔርን በከንፈራቸው ያከብራሉ፣ ልባቸው ግን ከእግዚአብሔር የራቀ እንደሆነ ኢሳይያስ ተነበየ። [15:8]
ፈሪሳውያን አስተምህሮ አድርገው ያስተምሩት የነበረው ነገር የሰዎችን ትእዛዛት ነበር። [15:9]
ሰው የሚበላው ነገር እንደማያረክሰው ኢየሱስ ተናገረ። [15:11]
ከሰው አፍ የሚወጣው ሰውን እንደሚያረክስ ኢየሱስ ተናገረ። [15:11]
ኢየሱስ ፈሪሳውያንን እውራን መሪዎች አላቸው፣ ደግሞም ወደ ጉድጓድ እንደሚወድቁ ተናገረ። [15:14]
ከልብ ክፉ አሳብ፣ መግደል፣ ምንዝርና፣ ወሲባዊ ርኩሰት፣ ስርቆሽ፣ በሃሰት መመስከር እና ስድብ ይወጣሉ። [15:19]
ኢየሱስ ቃል እንኳን አልመለሰላትም ነበር። [15:23]
እርሱ የተላከው ከእስራኤል ለጠፉት በጎች ብቻ እንደሆነ ኢየሱስ አስረዳ። [15:24]
ከነዓናዊቷ ሴት ራሷን ስታዋርድ፣ ኢየሱስ ለእርሷ ምን አለ፣ ምንስ አደረገላት?
ኢየሱስ ድዳዎችን፣ ሽባዎችን፣ መራመድ የማይችሉትንና ማየት የማይችሉትን ፈወሳቸው። [15:30]
ኢየሱስ ድዳዎችን፣ ሽባዎችን፣ መራመድ የማይችሉትንና ማየት የማይችሉትን ፈወሳቸው። [15:31]
ደቀመዛሙርት ሰባት እንጀራ እና ጥቂት ትንንሽ አሳዎች ነበሯቸው። [15:34]
እንጀራዎቹን እና አሳዎቹን ኢየሱስ ምን አደረጋቸው?
ሁሉ ከበሉ በኋላ ሰባት ቅርጫት ሙሉ ተረፈ። [15:37]
አራት ሺህ ወንዶች፣ እንዲሁም ሴቶችና ልጆች በልተው ጠገቡ። [15:38]
ሰማይ . . . ሰማይ የአይሁድ መሪዎች ከእግዚአብሔር ዘንድ ምልክትን ይሹ ነበር ይሁን እንጂ ኢየሱስ ማየት ወደሚችሉት ሰማይ ይመለከቱ ዘንድ ነገራቸው፡፡ አንባቢዎቹ የትርጉም ልዩነቱን መረዳት የሚችሉ ከሆነ ብቻ ለእግዚአብሔር ማደሪያም እንዲሁም ለሰማይ ከተቻለ አንድ ቃል ተጠቀም፡፡ ( ተመልከት) በመሸም ጊዜ ፀሐጥ በጠለቀች ጊዜ ጥሩ የአየር ሁኔታ ግልጽ እና ጥርት ያለ ሰማይ ነው ሰማዩ ቀልቷል ሰማዩ ብርሃማ እና ከፀሐይ መትለቅ ጋር ተያይዞ ቀላልቷል
የአየር ጸባዩ ጥሩ አይደለም "ዳመናማ እና ጭጋጋማ ነው" ጨልሟል "ጨለማ እና የሚያስፈራ ነው" ምንም ዓይነት ምልክት አይሰጣችሁም ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ለእናነት ምንም ምልክት እግዚአብሔር አይሰጣችሁም (en:ta:vol2:translate: እና ተመልከት)
እርሾ ክፉ ሀሳቦች እና ስህተት ትምህርት ( ተመልከት) ምክንያት "መከራከር" ወይም “መጣላት"
ለአምስቱ ሺህ አምስቱ እንጀራ፥ ስንት መሶብም እንዳነሣችሁ ትዝ አይላችሁምን? ወይስ ለአራቱ ሺህ ሰባቱ እንጀራ፥ ስንት ቅርጫትም እንዳነሣችሁ ትዝ አይላችሁምን? ኢየሱስ እየገሰጻቸው ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “በአምስት ዳቦ 5000 ሰዎች የተመገቡበት እና ምን ያህል ቅርጫት እንደሰበሰባችሁ መረዳት እና ማስታወስ ነበረባችሁ! ከዚህ በተጨማሪ በ7 ዳቦዎችን 4000 ሰዎች ስትመግቡ ምን ያህል ሰበሰባችሁ! ( and ተመልከት)
ስለ እንጀራ እንዳልተናገርኋችሁ እንዴት አታስተውሉምን? "በእርግጥ ስለ እንጀራ እያወራሁ እንዳልሆነ መረዳት ነበረባችሁ፡፡” (UDB) ( ተመልከት) እርሾ ክፉ ሀሳቦች እና የተሳሳቱ ትምህርቶች ( ተመልከት) እነርሱ . . . እነርሱ “ደቀ መዛሙርቱ”
ነገር ግን እናንተ እኔ ማን እንደሆኑ ትለላላችሁ? "እናንተን ግል ልጠይቃች፡ እኔ ማን እንደሆኑን ትላላችሁ?"
የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ "የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ " (UDB) ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህም "ይህንን ዬትኛው የሰው ልጅ አልገለጠልህም” ( ተመልከት)፡፡ “አንተ ክርስቶስ ፣ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ” የሚለው የጴጥሮስ ንግግር ወደ ጴጥሮስ የመጣው በማንም ሳይሆን በእግዚአብሔር በራሱ ነው፡ አባት ይህ በኢየሱስ እና በእግዚአብሔር መካከል ያለው ግንኙነት በሚገባ የሚገልጽ በጣም ጠቃሚ የሆነ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) የገሃነም ደጆች አይችሏትም አማራጭ ትርጉሞች: 1) "የሞት ኃይል ልቋቋማት አይችልም " ወይም 2) የጦር ሠራዊት አንድን ከተማ ሰብሮ እንደሚገባው ሁሉ የሞትን ኃይል ይሠባብራል፡፡ ( ተመልከት)
የመንግስተ ሰማያት ቁልፍ አገልጋይ ሰዎች ወደቤት ስገቡ ተቀበሎ እንደሚያገልግል ሁሉ ሰዎች የእግዚአብሔር ሕዝብ መሆን የሚችሉበትን መንገድ የመክፈት ክህሎት ( ተመልከት) በምድር ያሠራችሁት . . . በሰማይ የተፈራ ይሆናል በሰማይ እንደሚሆነው ሁሉ ለሰዎች ይቅርታን መስጠት ወይም በእነርሱ ላይ መፍረድ ( ተመልከት)
ከዚያ ቀን ጀምሮ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እርሱ ክርስቶስ መሆኑን ለሌላ ለማንም እንዳይናገሩ ካዘዛቸው በኋላ እግዚአብሔር ለእርሱ ያለው እቅዱን ያካፍላቸው ጀመረ፡፡ anded his disciples not to tell anyone that he was the Christ, he began sharing God's plan for himself. እንደሚሞት ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እንደሚገድሉት” ( ተመልከት) በሦስተኛው ቀን በሕይወት እንደሚነሳ "በሦስተኛው ቀን እግዚአብሔር እንደገና ሕያው እንደሚያደርገው"
ተከተለኝ "ደቀ መዝሙሬ ሁን" ራስህን ካድ "በራስህ ምኞች አትወሰድ" ወይም "የራስህን መሻት ተው" መስቀሉን ተሸከምና ተከተለኝ "መስቀሉን አንሳ፣ ተሸከም እና ከእኔ በኋላ ተከተል”፣ መከራን ለመቀበል እና ለክርስቶስ ለመሞት ፈቃደኛ ሁን ( ተመልከት) የሚወድ ማንም ቢኖር "የሚፈልግ ማንም ቢኖር" ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ "በዓለም ያለውን ሁሉ ቢያተርፍ" ነፍሱን ግን ቢያጎድል "እርሱን ግን ቢጠፋ”
የሰው ልጅ . . . አባቱ ኢየሱስ እንደ “ሰው ልጅነቱ” እና “የእርሱ” ልጅ መሆኑን ስገልጽ በሥላሴ ውስጥ እንዳለ ሦስተኛ አካል ያሳያል ፡፡ ለተሯሚዎች ምክር፡ "እኔ፣ የሰው ልጅ . . . አባቴ” ( ተመልከት) አባቱ ይህ በኢየሱስ እና በእግዚአብሔር መካከል ያለው ግንኙነት በሚገባ የሚገልጽ በጣም ጠቃሚ የሆነ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) የሰው ልጅ በመንግስቱ እስኪመጣ ድረስ ሞትን አይቀምሱም "ከመሞታቸው በፊት የሰው ልጅ በመንግስቱ ስመጣ ያዩታል” ሞትን አይቀምሱም "ሞትን አያዩም" ወይም “አይሞቱም" የሰው ልጅ በመንግስቱ ሲመጣ ኢየሱስ ራሱን እንደ ሥላሴ ሦተኛ አካል እየጠራ ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “በመንግስቴ ሲመጣ እስኪያዩኝ ድረስ” ( ተመልከት)
ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያን ኢየሱስ ከሰማይ የሚያሳያቸውን ምልክት ማየት ፈለጉ። [16:1]
ኢየሱስ ለፈሪሳውያንና ሰዱቃውያን የዮናስን ምልክት እንደሚሰጣቸው ተናገረ። [16:4]
ኢየሱስ ከፈሪሳውያን እና ሰዱቃውያን እርሾ እንዲጠበቁ ነገራቸው። [16:6]
ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ እየነገራቸው የነበረው ከፈሪሳውያን እና ሰዱቃውያን አስተምህሮ እንዲጠበቁ ነበር። [16:12]
ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ፣ “ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል?” ሲል ጠየቃቸው [16:13]
አንዳንድ ሰዎች ኢየሱስ ማለት መጥምቊ ዮሐንስ፣ ወይም ኤልያስ፣ ወይም ኤርምያስ፣ ወይም ከነብያት አንዱ እንደሆነ አስበው ነበር። [16:14]
ጴጥሮስ ሲመልስ “አንተ ክርስቶስ፣ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ” አለ። [16:16]
ጴጥሮስ የኢየሱስን ጥያቄ መልስ ያወቀው አብ ስለገለጠለት ነበር። [16:17]
ኢየሱስ ለጴጥሮስ የሰጠው የመንግሥተ ሰማያትን ቊልፍ ሲሆን፣ ያም በምድር ያሉትን እንዲያስር ወይም እንዲፈታ እና በሰማይ ያሉትን እንዲያስር ወይም እንዲፈታ ነው። [16:19]
ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም መሄድ እንደሚያስፈልገው፣ በብዙ መከራ እንደሚቀበል፣ እንደሚገደል እና በሦስተኛው ቀን እንደሚነሣ ነበር። [16:21]
ኢየሱስ ለጴጥሮስ “ዞር በል፣ አንተ ሰይጣን!” አለው [16:23]
ኢየሱስን መከተል የሚፈልግ ሰው ሁሉ ራሱን መካድና መስቀሉን መሸከም ይኖርበታል። [16:24]
ሰው ዓለሙን ሁሉ አትርፎ፣ ነፍሱን ቢያጣ ምንም እንደማይጠቅመው ኢየሱስ ተናገረ። [16:26]
የሰው ልጅ ከመላእክቱ ጋር በአባቱ ክብር እንደሚመጣ ኢየሱስ ተናገረ። [16:27]
የሰው ልጅ በሚመጣ ጊዜ ለእያንዳንዱ ሰው እንደየ ሥራው ይከፍላል። [16:27]
ከእርሱ ጋር እዚያ ከቆሙት አንዳንዶቹ የሰው ልጅ በመንግሥቱ በሚመጣ ጊዜ እንደሚያዩት ኢየሱስ ተናገረ። [16:28]
ማቴዎስ 17፡ 1-2
ጴጥሮስ እና ያዕቆብ እንዲሁም ወንድሙ ዮሐንስ "ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ እና የያዕቆብ ወንድም ዮሐንስ” ተለወጠ "እግዚአብሔር የኢየሱስ መልክ ሙሉ ለሙሉ ለወጠው” ወይም ( ተመልከት) ልብሶች "ልብስ" እንደ ብርሃን ያበሩ ነበር "እንደ ብርሃን ያንጸባርቁ ነበር" ( ተመልከት)
ማቴዎስ 17፡3-4
እነሆ ይህ ቃል ሰዎች ከዚህ በኋላ ለሚነገረው ነገር አጽኖት እንዲሰጡ የሚጨመር ቃል ነው፡፡ ለእነረሱ ከኢየሱስ ጋር ለነበሩት ደቀ መዛሙርት እንዲህ ሲል መለሰላቸው "አላቸው” ጴጥሮስ ለተጠየቀው ጥያቄ መልስ እየሰጠ አይደለም፡፡ በዚህ መሆን ለእኛ ይሻላል አማራጭ ትርጉሞች፡ 1) "እኛ ደቀ መዛሙርት በዚህ ከአንተ፣ ከሙሴ እና ከኤልያስ ጋር መሆናችን መልካም ነው” ወይም “አንተ፣ ሙሴ፣ ኤልያስ እና እኛ ደቀ መዛሙርትህ በአንድነት መሆናችን መልካም ነው፡፡” ( ተመልከት) መጠለያዎች አማራጭ ትርጉሞች 1) ሰዎች ለአምልኮ የሚመጧቸው ሥፍራዎች ወይም 2) ሰዎች በጊዜያዊነት ለመተኛ የሚዘጋጇቸው
እነሆ ይህ ቃል ሰዎች ከዚህ በኋላ ለሚነገረው ነገር አጽኖት እንዲሰጡ የሚጨመር ቃል ነው፡፡ በግንባራቸው መሬት ላይ ተደፍተው "ደቀ መዛሙርተ በግንባራቸው በመሬት ላይ ተደፍተው”
እነርሱ . . . ሳለ "ኢየሱስ እና ደቀ መዛሙርቱ . . . ሰለ"
ሁሉን ነገር ያድሳል "ሁሉን ነገር በሥርዓት ያደርጋል" እነርሱ . . . እነርሱ . . . እነርሱ አማራጭ ትርጉሞች: 1) የአይሁድ መሪች ወይም 2) ሁሉም የአይሁድ ሕዝቦች
የሚጥል በሽታ ያለበት ራሱን ስቶ የሚያደርገው ነገር የማያውቅ ሰው
ከእናንተ ጋር እስከ መቼ እቆያለሁ? እስከ መቼስ እታገሣችኋለሁ? ኢየሱስ በሕዝቡ ደስተኛ አልነበረም፡፡ የተርጓሚዎች ምክር፡ ከእናንተ ጋር መሆን ደከመኝ! አለማመናችሁ እና ክፋታችሁ ሰለቸኝ!” ( ,ተመልከት)
እኛ ተናጋሪው እንጂ ሰሚዎቹ አይደሉም ( ተመልከት) እኛ ማውጣት ያቃተን ለምንድ ነው "ጋኔኑ እንዲወጣ ማድረግ ያቃጠን ለምንድ ነው” ማድረግ የማትችሉት ነገር የለለምNothing will be impossible for you to do "ምንም ነገር ማድረግ ትችላላችሁ” ( ተመልከት)
በዚያም ቆዩ "ደቀ መዛሙር እና ኢየሱስ በዚያ ቆዩ" የሰው ልጅ አሳልፎ ይሰጣል ለተርጓሚዎች ምክር፡ "የሆኑ ሰዎች የሰው ልጅን አሳልፈው ይሰጡታል” ( ተመልከት) ይገድሉታ "ባለስልጣናት የሰወ ልጅን ይገድሉታል” ከሞት ይነሣል "እግዚብሔር ከሞት ያሥነሣዋል” ወይም “እንደገና ወደ ህይወት ይመላሳለር” ( ተመልትከት)
በ . . . ጊዜ እነርሱ ኢየሱስ እና ደቀ መዛሙርቱ በ . . ጊዜ
ሥር ያሉ በአጋዘዙ ውስጥ ወይም በንጉሥ ሥር ያሉ አፉ "የዓሣ አፍ" ውሰዱ "አስታተር ውሰድና"
ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ እና ዮሐንስ ከፍ ወዳለው ተራራ ወጡ። [17:1]
ፊቱ እንደ ፀሐይ እስኪያበራ፣ ልብሱም እንደ ብርሃን እስኪሆን ድረስ ኢየሱስ ተለወጠ። [17:2]
ሙሴ እና ኤልያስ ተገልጠው ከኢየሱስ ጋር ሲነጋገሩ ነበር። [17:3]
ጴጥሮስ ሦስት ድንኳኖችን ለሦስት ሰዎች ለመሥራት ሃሳብ አቀረበ። [17:4]
ከደመና የወጣው ድምፅ “የምወድደው ልጄ ይህ ነው፣ እርሱን ስሙት” አለ። [17:5]
ያዩትን የሰው ልጅ ከሙታን እስኪነሣ ድረስ ለማንም እንዳይናገሩ ኢየሱስ አዘዛቸው። [17:9]
ኤልያስ በእርግጥም እንደመጣና ሁሉን ነገር እንደ ቀድሞው እንዳደረገ ኢየሱስ ተናገረ። [17:11]
መጥምቊ ዮሐንስ አስቀድሞ የመጣው ኤልያስ እንደሆነ እና፣ በእርሱ ላይ ማድረግ የፈለጉትን ሁሉ እንዳደረጉበት ኢየሱስ ተናገረ። [17:12]
መጥምቊ ዮሐንስ አስቀድሞ የመጣው ኤልያስ እንደሆነ እና፣ በእርሱ ላይ ማድረግ የፈለጉትን ሁሉ እንዳደረጉበት ኢየሱስ ተናገረ። [17:13]
ደቀመዛሙርቱ የሚጥል በሽታ ያለበትን ልጅ ሊፈውሱት አልቻሉም ነበር። [17:14]
ደቀመዛሙርቱ የሚጥል በሽታ ያለበትን ልጅ ሊፈውሱት አልቻሉም ነበር። [17:15]
ደቀመዛሙርቱ የሚጥል በሽታ ያለበትን ልጅ ሊፈውሱት አልቻሉም ነበር። [17:16]
ኢየሱስ አጋንንቱን ገሠጸው፣ ልጁም ከዚያ ሰዓት ጀምሮ ተፈወሰ። [17:18]
ከትንሹ እምነታቸው የተነሣ የሚጥል በሽታ ያለበትን ልጅ መፈወስ እንዳልቻሉ ኢየሱስ ተናገረ። [17:20]
ኢየሱስ በሚገድሉት ሰዎች እጅ ተላልፎ እንደሚሰጥ፣ በሦስተኛውም ቀን እንደሚነሣ ለደቀመዛሙርቱ ነገራቸው። [17:22]
ኢየሱስ በሚገድሉት ሰዎች እጅ ተላልፎ እንደሚሰጥ፣ በሦስተኛውም ቀን እንደሚነሣ ለደቀመዛሙርቱ ነገራቸው። [17:23]
ጴጥሮስ ወደ ባህር እንዲሄድ እና መንጠቆውን በመጣል መጀመሪያ የሚይዘውን አሳ አውጥቶ ለግብር የሚሆነውን ስቅል ከአፉ እንዲያወጣ ነገረው። [17:27]
እንደ ሕጻን መሆን "ሕጻናት እነደሚያስቡት ማሰብ፡፡” (MAT 18:4 እና ተመልከት)
እንደዚህ ሕጻን ራሱን የሚያዋርድ "ይህ ሕጻን ራሱን በሚያዋርድበት መንገድ ራሱን የሚያዋርድ ማንኛውም ሰው" ( ተመልከት) የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቅ ባሕር መስጠም ይሻለው ነበር። "የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ አስረው ወደ ጥልቅ ባሕር መስጠም ከተሻለው”( ተመልከት የወፍጮ ድንጋይ ትልቅ፣ ክብ ቅርጽ ያለው ከባድ ድንጋይ ሆኖ እህል ለመፍጨት የሚያገለግል ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "ከባድ ድንጋይ"
እጅህ ኢየሱስ አድማጮቹ እንደ አንድ ሰው አድርጎ በነጠላ ቁጥር እየተናገራቸው ነው፡፡
አውጥተህ ጣለው ይህ ሀረግ የሚያሳየው ተከታታይነት ያለው አለማመንን እና የሚያስከፍለውን ማንኛውንም ዋጋ መሸሽን ነው፡፡ ወደ ሕይወት መግባት "ወደ ዘላለም ሕይወት መግባት"
አትናቁ "አትናቁ" ወይም "ጠቃሚ አይደሉም ብላችሁ አታስቡ" ለተርጓሚዎች ምክር፡ "አክብሩ" ሁል ጊዜ . . . ፊት ያያሉ "ሁል ጊዜ ቅርብ ናቸው "
ምን ይመስላችኋል? “ሰዎች ምን እንደሚያደርጉ አስቡ" ( ተመልከት) ትቶ ሄዶም የባዘነውን አይፈልግምን? "ሁልጊዜ ትቶ ሄዶ የባዘነውን ይፈልጋል፡፡” ዘጠና ዘጠኝ “99” ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱ እንዲጠፋ በሰማያት ያለው አባታችሁ ፈቃድ አይደለም። "በሰማይ ያለው አባታችሁ እነዚህ ትንንሾቹም ሁሉ እንዲኖሩ ፈቃዱ ነው" ( ተመልከት)
ወንድምህን ገንዘብ አደረግኸው "ከወንድምህ ጋር ያለህን ግንኙነት እንደገና መልካም ታደርጋለህ” አፍ ለምስክሮችህ “አፍ” በሚወጣው ቃል ( ተመልከት)
እነርሱ መስማት ምስክሮቹን መስማት (MAT 18:16) ለአንተ ልክ እንደ አሕዛብ እና ቀራጭ ይሁንልህ "አሕዛብን እና ቀራጭን እንደሚትመለከተው እንደዚያው ይሁንልህ"
ያሰራችሁት … የታሰረ . . . -ፈታችሁት . . . የተፈታ ይህህ በ MAT 16:19 ላይ እንዴት እንደተረጎምከተው ተመልከት፡፡ ይታሰራል . . . ይፈታል "እግዚአብሔር ያስረዋል . . . እግዚአብሔር ይፈተዋል" ( ተመልከት) እነርሱ . . . እነርሱ "ሁለት ሆናችሄ" ሁለት ወይም ሦስት "ሁለት ወይም ከዚያ በላይ" ወይም "ቢያንስ ሁለት" ተሰብሰባችሁ "ስበሰባ" አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
ሰባት እጥፍ "7 እጥፍ" ( ተመልከት ሰባ ጊዜ ሰባት አማራጭ ትርጉሞች: 1) "70 ጊዜ 7" (ULB) ወይም 2) "77 ጊዜ"፡፡ ቁጥርን መጠቀም ግራ የሚያጋባ ከሆነ እንዲህ ማለት ትችላለህ “መቁጠር ከማትችለው ቁጥር በላይ" ( ተመልከት)
አንድ አገልጋይ አመጡ "አንድ ሰው ከንጉሡ አገልጋዮች መካከል አንድ ሰው አመጣ" ( ተመልከት) ዐስር ሺህ መክልት "10,000 መክልቶች" ወይም "አገልጋዩ መክፍለል ከሚችለው በላይ" ( ተመልከት) አለቃው ተሸጦ ክፍያው እንዲፈጸም አዘዘ "ንጉሡ ይህ ሰው እንዲሸጥና ከሽያጩ ላይ እዳው እንዲከፈል አዘዘ"
በፊቱ ወድቆ በመስገድ "በጉልበቱ ወድቆ አንገቱን ወደ ታች ደፍቶ" በእርሱ ፊት "በንጉሡ ፊት" ለቀቀው "እንዲሄድ ፈቀለትet him"
አንድ መቶ ዲናር "100 ዲናር" ወይም "የመቶ ቀን የሥራ ክፍያ ( ተመልከት) ያዘው "አሰረው" ወይም “ያዘው" (UDB) በፊቱ ወደቀ . . . ታገሰኝ እና እከፍልሃለሁ ይህንን በ MAT 18:26 ላይ “በፊቱ ወደቀ . . . ታገሰኝ እና እከፍልሃለሁ” በተረጎምከው መሠረት ትርጉመው፡፡ ( ተመልከት)
ከዚያም የአገልጋዩ ጌታ ጠራው "ከዚያ ንጉሡ የመጀመሪያውን አገልጋይ ጠርቶት" አይገባህምን "አይገባህምን” ( ተመልከት)
ማቴዎስ 18፡ 34-35
ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባት ንስሃ ልንገባ እና ልክ እንደ ልጆች ልንሆን እንደሚያስፈልግ ኢየሱስ ተናገረ። [18:3]
ራሱን ልክ እንደ ትንሽ ልጅ የሚያዋርድ በመንግሥተ ሰማያት ታላቅ እንደሚሆን ኢየሱስ ተናገረ። [18:4]
በኢየሱስ የሚያምነው ታናሽ እንዲስት የሚያደርግ ሁሉ በአንገቱ ላይ የወፍጮ ድንጋይ ታስሮ ወደ ባህር ቢጣል ይሻለዋል። [18:6]
እንድንሰናከል የሚያደርገን ማንኛውም ነገርን ልንጠል እንደሚገባን ኢየሱስ ተናገረ። [18:8]
ታናናሾችን ልንንቅ የማይገባን መላእክቶቻቸው የአብን ፊት ሁልጊዜ ስለሚያዩ ነው። [18:10]
ከታናናሾቹ አንዱ ይጠፋ ዘንድ የፈላጊው ሰው ብቻ ሳይሆን የአብም ፈቃድ አይደለም። [18:12]
ከታናናሾቹ አንዱ ይጠፋ ዘንድ የፈላጊው ሰው ብቻ ሳይሆን የአብም ፈቃድ አይደለም። [18:13]
ከታናናሾቹ አንዱ ይጠፋ ዘንድ የፈላጊው ሰው ብቻ ሳይሆን የአብም ፈቃድ አይደለም። [18:14]
በቅድሚያ፣ ልትሄድ እና ጥፋቱን ብቻችሁን ሆናችሁ ልታሳየው ይገባል። [18:15]
በመቀጠል፣ ከአንተ ጋር አንድ ወይም ሁለት ወንድሞችን ምስክር አድርገህ ልትወስድ ይገባል።
ሦስተኛ፣ ጉዳዩን ለቤተክርስቲያን ልታሳውቅ ይገባል። [18:17]
በስተመጨረሻ፣ ቤተክርስቲያንን የማይሰማ ቢሆን፣ እንደ አረማዊ እና ግብር ሰብሳቢ መቆጠር አለበት። [18:17]
ሁለት ወይም ሦስት በስሙ በሚሰበሰቡ መካከል ለመገኘት ኢየሱስ ቃል ገባ። [18:20]
ወንድማችንን ሰባ ጊዜ ሰባት ይቅር ማለት እንዳለብን ኢየሱስ ተናገረ። [18:21]
ወንድማችንን ሰባ ጊዜ ሰባት ይቅር ማለት እንዳለብን ኢየሱስ ተናገረ። [18:22]
ባርያው ለጌታው ሊከፍለው ያልቻለው ዐሥር ሺህ ታላንት እዳ ነበረበት። [18:24]
ባርያው ለጌታው ሊከፍለው ያልቻለው ዐሥር ሺህ ታላንት እዳ ነበረበት። [18:25]
ጌታው ስለ ራራለት እዳውን ለባርያው ተወለት። [18:27]
ባርያው መታገስ ባለመፈለግ አብሮት የሚያገለግለውን ባርያ ወደ እስር ቤት ጣለው። [18:30]
አብሮት ለሚያገለግለው ባርያ ምሕረት ማድረግ እንደነበረበት ጌታው ለባርያው ነገረው። [18:33]
ጌታው እዳውን ሁሉ እስኪከፍል ድረስ ለሚያሰቃዩት ባርያዎች አሳልፎ ሰጠው። [18:34]
ወንድማችንን ከልባችን ይቅር የማንል ከሆነ ጌታው በባርያው ላይ እንዳደረገ አብ እንደሚያደርግብን ኢየሱስ ተናገረ። [18:35]
ከዚያ በኋላ በቋንቋችሁ የአንድን ታሪክ አዲስ ክፍል ለመጀመር የሚያገለግል ቃል ካለ ይህንን ቃል ተጠቀሙ፡፡ እነዚህ ቃላት የ . . . ቃላት MAT 18:1-35 ተለየ "ከእነርሱ ራቀ” ወይም "ተዋቸው" በዚያው ክልል ውስጥ "በዚያው አከባቢ"
ወደ እርሱ መጣ "ወደ ኢየሱስ መጣ" አላነበባችሁምን . . . ሴት? ኢየሱስ ፈሪሳዊያኑን ሊያሳፍራቸው ፈልጎሏል፡፡ ( ተመልከት)
እንዲሁም እንዲህ አለ .. . ሥጋ? በ MAT 19:3 ላይ የተጀመረው ጥያቄ የቀጠለ ነው፡ "በተጨማሪም እንዲህ የሚል ነገር አላነባችሁምን . . . ሥጋ?" ( እና ተመልከት) ከምስቱ ጋር ይጣበቃል "ከምስቱ ጋር ይቀራረባል" አንድ ሥጋ "አንድ ሰው"
እንዲህ አሉት "ፈሪሳዊያኑ ለኢየሱስ አንዲህ አሉት" አዞናል "አይሁዳዊ እንደመሆናችን እንዲህ ታዘናል" የፊች ወረቀት ጋብቻው ሕጋዊ በሆነ መንገድ መቆሙን የሚሳይ ወረቅት ከመጀመሪያው ግን እንዲህ አልነበረም "እግዚብሔር ወንድን እና ሴትን ሲፈጥር መቼም ቢሆን እንድፋቱ አልነበረም" የተፈታቸችሁንም የሚያገባ ማንኛውም ሰው ያመነዝራል ብዙዎቹ የጥንት ቅጂዎች እነዚህንን ቃላት አይጨምሩትም፡፡
ራሱን ጃንደረባ ያደረገ አማራጭ ትርጉሞች 1) "የግል አካሉን ቆርጦ የጣለ” ወይም 2) "ላለማግባት እና ምንም ዓይነት ግብረስጋ ግንኙነት ላለማድረግ የወሰነ ሰው” ( ተመልከት) ለመንግስተ ሰማያት ሲል "እግዚአብሔርን ይበልጥ ለማገልገል ይችል ዘንድ" ይህንን ትምህርት ተቀበል . . . ተቀበል “ይህንን ትምህርት ተቀበል . . . ተቀበል” የሚለው በ19፡11 ላይ እንዴት እንደተረጎምከተው ተመልከት፡፡
ሕጻናትን ወደ እርሱ አመጡ ለተርጓሚዎች ምክት፡ “አንዳንድ ሰዎች ሕጻናትን ወደ ኢየሱስ አመጡ፡፡” ( ተመልከት) ፈቃድ "ፍቀዱ" ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ አትከልክሏቸው "ወደ እኔ እንዳይመጡ አትከልክሏቸው" የመንግስተ ሰማያት እንደነዚህ ላሉት ናትና "መንግስተ ሰማየት እንደነዚህ ላሉ ሰዎች ናትና” ወይም “ልክ እንደነዚህ ሕጻናት የሆኑ ሰዎች ብቻ ናቸው ወደ መንግስተ ሰማያት መግባት የሚችሉት"
እነሆ ይህ ቃል ሰዎች ከዚህ በኋላ ለሚነገረው ነገር አጽኖት እንዲሰጡ የሚጨመር ቃል ነው፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ተመልከቱ” ወይም “አድምጡ” ወይም “አሁን ለምነግራችሁ ነገር ትኩረት ስጡ”:: መልካም ነገር እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ነገር
ምኞት "ፍላጎት"
ሀብታም ወደ እግዚአብሔር መንግስት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ብትሾልክ ይቀላል ለሀብታም ወደ እግዚአብሔር መንግስር መግባት በጣም ከባድ ነው ( ተመልከት) የመርፌ ቀዳዳ ለክር ማስገቢያ የሚሆን በመርፌ አናት ላይ የሚገኝ ቀዳዳ
በጣም ተገረሙ "ደቀ መዛሙርቱ ተደነቁ" ማን ልድን ይችላል? አማራጭ ትርጉሞች: 1) መልስ እየፈለጉ ነው ወይም 2) ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ማንም ሊድን አይችልም!” ( ተመልከት) እኛ ሁሉን ነገር ተውን "ሀብታችንን ሁሉ ተውን" ወይም "ያለንን ነገር ሁሉ ተውን" ታዲያ ምን እናገኛለን? "እግዚአብሔር ለእኛ ምን መልካም ነገር ይሰጠናል?"
አዲስ ልደት "ሁሉ ነገር አዲስ በሚሆንበት ጊዜ” ወይም "በአዲሱ ዘመን" በዐሥራ ሁለቱ ዙፋናት ላይ ትቀመጣላችሁ፣ ትርዳላችሁ "ነገሥታት እና ፈራጆች ትሆናላችሁ"
መቶ እጥፍ ትቀበላላችሁ "የተዋቿቸውን መልካም ነገሮች ሁሉ በመቶ እጥፍ ትቀበላላችሁ" አሁን መጀመሪያ የነበሩ ብዙዎች መጨረሻ ሆነዋል በሰዎች ዐይን መጀመሪያ የነበሩት ማለትም ሀብታሞች እና ሌሎችን የሚዙ ሰዎች በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ አንድ ቀን መጨረሻ ይናሉ፡፡
ፈሪሳውያን ኢየሱስን “ሰው ሚስቱን በማንኛውም ምክንያት ሊፈታ ተፈቅዷልን?” ብለው ጠየቊት [19:3]
ከፍጥረት መጀመሪያ አንሥቶ እግዚአብሔር ወንድ እና ሴት አድርጎ እንደፈጠራቸው ኢየሱስ ተናገረ። [19:4]
ሰው አባት እና እናቱን መተው እና ከሚስቱም ጋር መጣበቅ እንዳለበት ኢየሱስ ተናገረ። [19:5]
ባል ከሚስቱ ጋር በሚጣበቅበት ጊዜ ሁለቱ አንድ ስጋ እንደሚሆኑ ኢየሱስ ተናገረ። [19:5]
ባል ከሚስቱ ጋር በሚጣበቅበት ጊዜ ሁለቱ አንድ ስጋ እንደሚሆኑ ኢየሱስ ተናገረ። [19:6]
እግዚአብሔር ያጣመረውን ሰው ሊለየው እንደማይገባ ኢየሱስ ተናገረ። [19:6]
የፍቺ ወረቀት እንዲሰጣት ሙሴ ያዘዘው ከአይሁድ ልቦች ደንዳንነት የተነሣ እንደሆነ ኢየሱስ ተናገረ። [19:7]
የፍቺ ወረቀት እንዲሰጣት ሙሴ ያዘዘው ከአይሁድ ልቦች ደንዳንነት የተነሣ እንደሆነ ኢየሱስ ተናገረ። [19:8]
ከዝሙት በስተቀር ሚስቱን ሌላኛዋን የሚያገባ ምንዝርናን ይፈጽማል፣ የተፈታችይቱንም ሴት የሚያገባ ምንዝርና ይፈጽማል። [19:9]
ሊቀበሉት የተፈቀደላቸው ጃንደረባነትን ሊቀበሉ እንደሚችሉ ኢየሱስ ተናገረ። [19:10]
ሊቀበሉት የተፈቀደላቸው ጃንደረባነትን ሊቀበሉ እንደሚችሉ ኢየሱስ ተናገረ። [19:11]
ሊቀበሉት የተፈቀደላቸው ጃንደረባነትን ሊቀበሉ እንደሚችሉ ኢየሱስ ተናገረ። [19:12]
ትንንሽ ልጆች ወደ ኢየሱስ በመጡ ጊዜ፣ ደቀመዛሙርቱ ገሠጿቸው። [19:13]
የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ እነርሱ ላሉት ስለሆነች፣ ትንንሽ ልጆች እንዲመጡ እንዲፈቅዱላቸው ኢየሱስ ተናገረ። [19:14]
ወደ ዘላለም ሕይወት ለመግባት ትእዛዛትን እንዲጠብቅ ኢሱስ ለወጣቱ ነገረው። [19:16]
ወደ ዘላለም ሕይወት ለመግባት ትእዛዛትን እንዲጠብቅ ኢሱስ ለወጣቱ ነገረው። [19:17]
ትእዛዛትን እንደጠበቀ ሰውዬው በተናገረ ጊዜ፣ ያለውን ሁሉ ሸጦ ለድሆች እንዲሰጥ ኢየሱስ ነገረው። [19:20]
ትእዛዛትን እንደጠበቀ ሰውዬው በተናገረ ጊዜ፣ ያለውን ሁሉ ሸጦ ለድሆች እንዲሰጥ ኢየሱስ ነገረው። [19:21]
ወጣቱ ሰው ብዙ ሃብት ስለነበረው እያዘነ ሄደ። [19:22]
ኢየሱስ ሲናገር ለሰው እንደማይቻል፣ ነገር ግን ለእግዚአብሔር ሁሉ ይቻላል። [19:26]
በአዲሱ ልደት በዐሥራ ሁለቱ ዙፋናት ላይ ተቀምጠው በዐሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች ላይ እንደሚፈርዱ ኢየሱስ ተናገረ። [19:28]
አሁን ላይ ፊተኛ የሆኑት ኋለኛ እንደሚሆኑ፣ አሁን ላይ ኋለኛ የሆኑት ፊተኛ እንደሚሆኑ ኢየሱስ ተናገረ። [19:30]
መንግስ ሰማያት የመሬት ባለቤትን ትመስላለች እግዚአብሔር በሁሉም ነገር ላይ ያለው አገዛዝ አንድ ባለመሬት መሬቱን የሚያስተዳድርበትን መንገድ ይመስላል ( ተመልከት) መንግስተ ሰማይ ትመስላለች በ MAT 13:24 ላይ በምን መልኩ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ከተስማማ በኋላ "የመሬቱ ባለቤት ከተስማማ በኋላ" በአንድ ዲናር "የአንድ ቀን ገቢ" ( ተመልከት)
እንደ ገና ወጣና "የመሬቱ ባለቤት እንደገና ወጣና" ያለሥራ የቆሙተን "ምንመ የማይሠሩትን” ወይም “ሥራ ያሌላቸውን"
እንደ ገና ወጣና "የመሬቱ ባለቤት እንደገና ወጣና" ያለሥራ የቆሙተን "ምንመ የማይሠሩትን” ወይም “ሥራ ያሌላቸውን"
ለእያንዳንዱ "በዐሥራ አንድ ሰዓት መሥራት ለጀመረውም ለእያንዳንዱ" አንድ ዲናር "የአንድ ቀን ገቢ" ( ተመልከት) እነርሱ እነንዲህ አሰቡ "ረጅም ሰዓት የሠሩት ሠራተኞች እንዲህ አሰቡ"
በተቀበሉ ጊዜ "ረጀም ሰዓት ስሰሩ የነበሩት ሠራተኞች ስቀበሉ" ባለቤቱ "የመሬቱ ባለቤት" ወይም "የወይን እርሻው ባለቤት" የቀኑንም ድካምና ትኩሳት ከተሸከምን "በጠራራ ፀሐይ ቀኑን ሙሉ ሥንሠራ የነበርን"
ከመካከላቸው አንዱ "ረጅሙን ሰዓት ከሠሩት ሠራተኞች መካከል አንዱ" ወዳጆቼ በዚህ ሥፍራ ላይ አንድ ሰው ሌላኛውን ሰው በትህትና ለመገሰጽ የሚጠቀምበትን ቃል ተጠቀም፡፡ በአንድ ዲናር ለመሥራት ከእኔ ጋር አልተስማማችሁምን? ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ለሥራችሁ ዋጋ አንድ ዲናር ለመክፈል ተስማሚቼያለሁ፡፡ (en:ta:vol1:translate: ተመልከት) አንድ ዲናር "የአንድ ቀን ገቢ" ( ተመልከት) መስጠት እወዳለሁ "መስጠት ያስደስተኛል” ወይም “መስጠት እወዳለሁ”
በራሴ ሀብት የፈለኩትን የማድረግ መብት የለኝምን? ለተርጓሚዎች ምክር፡ "በራሴ ሀብት የፈለኩትን ማድረግ እችላለሁ” መብት "ሕጋዊ" ወይም "ፍትሐዊ" ወይም "ትክክል" ወይም እኔ መልካም ስለሆንኩ ቀናችሁን? "ለማይገባቸው ሰዎች መልካም በማድረጌ አልተደሰታችሁምን"
እንሄዳለን ኢየሱስ እና ደቀ መዛሙርቱ የሰው ልጅን አሳልፈው ይሰጡታል "አንድ ሰው የሰው ልጅን አሳልፎ ይሰጠዋል" ይፈርዱበታል. . . እና አሕዛብ ይዘባበቱበት ዘንድ አሳልፎ ይሰጣል የካህናት አለቆች እና ፀሐፍት ይፈርዱበታል እንዲሁም ለአሕዛብ አሳልፈው ይሰጡታል፤ አሕዛብም ይዘባበቱበታል ይነሳል "እግዚብሔር ያስነሳዋል”
በቀኝህ በኩል . . . በግራህ በኩል ሥልጣን ያለው ቦታ
አናንተ እናት እና ልጆች ትችላለህን...ለመጠጣት? "ለመጠጣት . . . ትችላለህን?" ኢየሱስ ይህን የተናረው ለልጆች ብቻ ነው፡፡ አሁን ልጠጣው ያለሂትን ጽዋ ጠጣ "አሁን ልቀበለው ያለሁትን መከራ ውስጥ እለፍ" እነርሱ ልጆች በአባቴ ለተዘጋጀላቸው ነው "ከአጠገቤ በክብር መቀመጥ ይህንን ክብር አባቴ ላዘጋጀላቸው ነው" መዘጋጀት የተዘጋጀላቸው
የአሕዛብ ገዥዎች ይገዟቸዋል "የአሕዛብ ገዥዎች ገዥው የፈለገውን ነገር እንዲያደር ሕዝቡን ያዛሉ" እርሱ በጣም አስፈለጊ ሰው ናቸው በገዥዎች ስልጣን የተሰጣቸው ሰዎች በእነርሱ ላይ ስልጣን አላቸው "ይቆጣጠሯቸዋል" ፍላጎት "ፍላጎት" ወይም "መሻት" ሕይወት መስጠት "ለመሞት መፈለግ"
እንደፈለጉ ለደቀ መዛሙርቱ እና ኢየሱስ ተከተሉት "ኢየሱስን ተከተሉ" እናም ተመለከቱ አንዳንድ ጊዜ “እነሆነ” ተብሎ ተተርጉሟል፡፡ ጸሐፊው ከዚህ በመቀጠል ለሚመጣው ነገር ትኩርት እንዲሰጠው ይፈልጋል፡፡ ይህንን ለማድረግ የሚያስችል ነገር በቋንቋችሁ ውስጥ ይኖራል፡፡ በዚያ ስያልፉ "በዚያ ሥያልፉ" ይበልጥ ድምጻቸው አሰመተው ጮኹ "ዐይነ ሥውራኑ ከበፊቱ ይልቅ አብዝተው ጮኹ” ወይም “ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ጮኹ"
ጠራቸው ዐይነ ሥውራኑን ጠራቸው ፍላጎት "ፍላጎት" እናይ ዘንድ እንወዳለን ለተርጓማች ምክር፡ “ማየት እንችል ዘንድ ታደርግ ዘንድ እንወዳለን" ወይም "ማየት እንችል ዘንድ እንወዳለን ራራላቸው "ራራላቸው” ወይም "ለእነርሱ ራራ"
የእርሻው ባለቤት በማለዳ ለቀጠራቸው ሠራተኞች በቀን አንድ ዲናገር ለመክፈል ተስማምቶ ነበር። [20:1]
የእርሻው ባለቤት በማለዳ ለቀጠራቸው ሠራተኞች በቀን አንድ ዲናገር ለመክፈል ተስማምቶ ነበር። [20:2]
የእርሻው ባለቤት በሦስተኛው ሰዓት ለቀጠራቸው ሠራተኞች እርሱ የፈለገውን ያክል ለመክፈል ተስማምቶ ነበር። [20:4]
በዐሥራ አንደኛው ሰዓት ላይ የተቀጠሩት አንድ ዲናር ተቀበሉ። [20:9]
ሙሉ ቀን ሠርተው፣ ለአንድ ሰዓት ከሠሩት ጋር ተመሳሳይ ክፍያ እንደተቀበሉ አገሩመረሙ። [20:11]
ሙሉ ቀን ሠርተው፣ ለአንድ ሰዓት ከሠሩት ጋር ተመሳሳይ ክፍያ እንደተቀበሉ አገሩመረሙ። [20:12]
የእርሻው ባለቤት ምንም እንዳልበደላቸው እና ለእነርሱ የተገባቸውን እንደከፈላቸው ተናገረ። [20:13]
የእርሻው ባለቤት ምንም እንዳልበደላቸው እና ለእነርሱ የተገባቸውን እንደከፈላቸው ተናገረ። [20:14]
ለሊቀ ካህናት እና ጸሐፍት ተላልፎ እንደሚሰጥ፣ እስከ ሞት ድረስ እንደሚፈረድበት፣ እንደሚሰቀል፣ እና በሦስተኛው ቀን እንደሚነሣ ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ ነገራቸው። [20:17]
ለሊቀ ካህናት እና ጸሐፍት ተላልፎ እንደሚሰጥ፣ እስከ ሞት ድረስ እንደሚፈረድበት፣ እንደሚሰቀል፣ እና በሦስተኛው ቀን እንደሚነሣ ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ ነገራቸው። [20:18]
ለሊቀ ካህናት እና ጸሐፍት ተላልፎ እንደሚሰጥ፣ እስከ ሞት ድረስ እንደሚፈረድበት፣ እንደሚሰቀል፣ እና በሦስተኛው ቀን እንደሚነሣ ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ ነገራቸው። [20:19]
ሁለቱ ልጆቿ አንደኛው በቀኙ ሌላኛው በግራው እንዲቀመጡ ኢየሱስ እንዲያደርግላት ፈለገች። [20:20]
ሁለቱ ልጆቿ አንደኛው በቀኙ ሌላኛው በግራው እንዲቀመጡ ኢየሱስ እንዲያደርግላት ፈለገች። [20:21]
እነዚያን ቦታዎች ለመረጣቸው አብ እንዳዘጋጀ ኢየሱስ ተናገረ። [20:23]
ታላቅ ሊሆን የሚወድድ ማንም ሰው ቢሆን አገልጋይ መሆን እንዳለበት ኢየሱስ ተናገረ። [20:26]
እርሱ የመጣው ሊያገለግል እና ሕይወቱን ለብዙዎች ቤዛ አድርጎ ሊሰጥ መሆኑን ኢየሱስ ተናገረ። [20:28]
ሁለቱ ማየት የተሳናቸው “ጌታ ሆይ፣ የዳዊት ልጅ ሆይ፣ ማረን” ይሉ ነበር። [20:30]
ኢየሱስ ሁለቱን ማየት የተሳናቸውን ሰዎች የፈወሰው ስላዘነላቸው ነበር። [20:34]
ቤተ ፋጌ
መንደር
ውርንጭላ
"ትንሽ ወንድ አህያ"
ይህ በነቢያት የተነገረው ይፈጸም ዘንድ ነው "እግዚአብሔር ስለዚህ ጉዳይ ከብዙ ዘመናት በፊት በነቢያ አማካኝነት ምን እንደሚሆን ተናግሮ ነበር” በነቢያት የተነገረው ነገር "ነገሩ ከመፈጸሙ በፊት ነቢያት አስቀድመው የተናገሩት ነገር” የጽዮን ሴት ልጅ እስራኤል አህያ ድሆች የሚጋልቡት እንስሳ ውርንጭላ ትንሽ ወንድ አህያ
ጨርቅ ከውጪ የሚደረብ ወይም ረጅም ኮት ኢየሱስ በዚያ ተቀመጠ "አህያይቱን ጨርቅ አልብሰው ኢየሱስ በዚያ ላይ እንዲቀመጥ አደረጉ"
ሆሣዕና ይህ የዕብራይስጥ ቃል ሲሂን ትርጉሙም “አድነን” ማለት ነው ይሁን እንጂ “እግዚአብሔር ይመስገንም” መሆን ይችላል፡፡ ከተማው ሁሉ ተናወጠ "በከተማይቱ ውስጥ ያሉ ሁሌ እርሱን ለማየት ጓግተው ነበር" ከተማው ሁሉ "በከተማይቱ ውስጥ ያሉ ብዙ ሰዎች"
እንዲህ አላቸው "ገንዘብ ለዋጮቹን እና የተለያዩ ነገሮችን የሚገዙትን እና የሚሸጡትን ሰዎች" የጸሎት ቤት "ሰዎች የሚጸልዩበት ሥፍራ" የወንበዴዎች ዋሻ "እንደ ወንበዴዎች መሸሸጊያ ዋሻ” አንካሳ በጣም ከመጎዳታቸው የተነሳ መራመድ የማይችሉ ሰዎች
ሆሣዕና በ MAT 21:09 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምው ተመልከት፡፡ የዳዊት ልጅ በ MAT 21:09 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ተቆጡ "ኢየሱስን ጠሉት እንዲሁም በጣም ተበሳጩበት" እነዚህ ሰዎች የሚሉትን አትሰማምን? "ሰዎች ስለአንተ እንዲህ ዓይነት ንግግር እንዲያደርጉ ልትፈቅድላቸው አይገባም!" ይሁን እንጂ ፈጽሞ አላነበባችሁምን . . . ምስጋና'? "አዎ አየሰማኋቸው ነው ይሁን እንጂ በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ያነበባችሁት ማስታወስ ይገባችሁ ነበር . . . ምሳጋና" ኢየሱስ ትቷቸው ሄደ "ኢየሱስ የካህናት አለቆችንና ጸሐፊትን ትቶ ሄደ"
ደረቀ "ሞተ" ማቴዎስ 21፡20-21
እምነት ካላችሁና የማትጠራጠሩ ከሆነ እነዚህ ሁለት ሀረጎች የሚስተላልፉት ተመሳሳይ ሀሳብ ነው፡፡ ሁለት ጊዜ የተጻፈው አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ በአንዳንድ ቋንቋዎች ውስጥ አጽኖት መስጫ ሌላ መንገድ አለ፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “በእርግጥ ካመናችሁ” ወዲያው ደረቀ "ደርቆ ሞተ"
እምነት ካላችሁና የማትጠራጠሩ ከሆነ እነዚህ ሁለት ሀረጎች የሚስተላልፉት ተመሳሳይ ሀሳብ ነው፡፡ ሁለት ጊዜ የተጻፈው አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ በአንዳንድ ቋንቋዎች ውስጥ አጽኖት መስጫ ሌላ መንገድ አለ፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “በእርግጥ ካመናችሁ” ወዲያው ደረቀ "ደርቆ ሞተ"
ማቴዎስ 21፡25-27
ከሰማይ "በሰማይ ካለው እግዚአብሔር” እንዲህ ይለናል "ኢየሱስ እንዲህ ይለናል" ሕዝቡን ፈራን "ሕዝቡ ምን እንደሚያስብ ፈራን ወይም ምን እንደሚያደርግብን ፈራን" ዮሐንስን ነብይ አድርገው ይቆጥሩት ነበር "ዮሐንስ ነብይ እንደሆነ ያምኑ ነበር"
እንዲህ አሉ "የካህናት አለቆችና ሽምግሌዎች እንዲህ አሉ" ኢየሱስ አንዲህ አላቸው "ኢየሱስ ለካህናት አለቆችና ለሽማግሌዎች እንዲህ አላቸው" ዮሐንስ ወደ እናንተ መጣ ዮሐንስ ወደ ሃይማኖት መሪዎች እና ሕዘቡ መጥቶ ሰበከ፡፡ በጽድቅን መንገድ ዮሐንስ ሰዎች እንዴት ለእግዚአብሔት ምላሽ መስጠት እንዳለባቸው እና መኖር እንዳለባቸው አሳየ
ትልቅ መሬት ያለው አንድ ሰው "ብዙ ሀብት ያለው አንድ ሰው" ለወይን ተካዮች መሬቱን አከራየ "ወይን የሚያመርቱ ሰዎችን በቦታው ላይ ሾመ” የወይን እርሻው ባለቤት ግን አሁንም ቢሆን የመሬቱ ባለቤት ነው፡፡ የወይን ተክል የሚተክሉ ሰዎች ወይንን እንዴት መትከል እና ማሳደግ እንደሚቻል የሚያውቁ ሰዎች
ሠራተኞችን የመሬቱ ባለቤት ሠራተኞች (MAT 21:33)
ሰዎች እንዲህ አሉት "ሕዝቡ ለኢየሱስ እንዲህ አሉት"
ኢየሱስ እንዲህ አላቸው "ኢየሱስ ለሕዝቡ እንዲህ ብሎ ተናገረ" (MAT 21:41) ግንበኞች የናቁት ድንጋጥ የማዕዘን ራስ ሆነ፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "በአናጽዋች የናቁት ድንጋይ በጣም አስፈላጊው ድንጋይ ሆነ፡፡” ባለስልጣናቱ ኢየሱስን ባይቀበሉትም ነገር ግን እግዚአብሔር የመንግስቱ ራስ ያደርገዋል፡፡ “ ይህ ከጌታ ነው "ይህንን ታላቅ ለውጥ ያመጣው ጌታ ነው"
እላችኋለሁ ኢየሱስ ለካህናት አለቆች እና ሽማግሌዎች እንዲህ አላቸው፡፡ ፍሬውን ተንከባቡ "ትክክለኛውን ነገር አድርጉ ፍሬውን "የእግዚአብሔር መንግስ ፍሬ" በዚህ ድንጋይ ላይ የሚወድቅ ማንም ሰው "በዚህ ድንጋይ የሚሰናከል ማንም ቢኖር የሚወድቅበት ማንም ሰው "ፍርዱ የሚመጣበት ማንም ሰው
የእርሱ ምሳሌዎች "የኢየሱስ ምሳሌዎች" እጃቸውን በእርሱ ላይ አኖሩ "አሰሩት"
የታሰረች አህያ ከውርንጫዋ ጋር ሆና እንደሚያገኙ ኢየሱስ ተናገረ። [21:2]
ንጉሥ በአህያ እና በውርንጫዋ ላይ ተቀምጦ እንደሚመጣ ነብዩ ተንብዮ ነበር። [21:4]
ንጉሥ በአህያ እና በውርንጫዋ ላይ ተቀምጦ እንደሚመጣ ነብዩ ተንብዮ ነበር። [21:5]
ሕዝቡ ከላይ የደረቡትን ልብስ ያነጥፉ፣ የዛፍ ቅርንጫፎችንም በመንገዱ ላይ ያኖሩ ነበር። [21:8]
ሕዝቡ፣ “ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፣ ሆሳዕና በአርያም” እያሉ ጮኹ። [21:9]
በመቅደስ ውስጥ ይገዙ እና ይሸጡ የነበሩትን ኢየሱስ አስወጣቸው፣ የገንዘብ ለዋጮችን ጠረጴዛ እና የእርግብ ሻጮችን መቀመጫዎች ገለበጠ። [21:12]
ነጋዴዎቹ የእግዚአብሔርን ቤተመቅደስ የወንበዴዎች ዋሻ እንዳደረጉት ኢየሱስ ተናገረ። [21:13]
እግዚአብሔር ከሕጻናቱ እና ከሚጠቡት አፍ ምስጋናን ለራሱ እንዳዘጋጀ ነብዩ የተናገረውን ኢየሱስ ጠቀሰ። [21:15]
እግዚአብሔር ከሕጻናቱ እና ከሚጠቡት አፍ ምስጋናን ለራሱ እንዳዘጋጀ ነብዩ የተናገረውን ኢየሱስ ጠቀሰ። [21:16]
በላዩዋ ላይ ፍሬ ስላልነበራት ኢየሱስ የበለስ ዛፏ እንድትደርቅ አደረገ። [21:18]
በላዩዋ ላይ ፍሬ ስላልነበራት ኢየሱስ የበለስ ዛፏ እንድትደርቅ አደረገ። [21:19]
አምነው በጸሎት ቢጠይቁ እንደሚቀበሉ ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ አስተማራቸው። [21:20]
አምነው በጸሎት ቢጠይቁ እንደሚቀበሉ ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ አስተማራቸው። [21:21]
አምነው በጸሎት ቢጠይቁ እንደሚቀበሉ ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ አስተማራቸው። [21:22]
ሊቀ ካህናቱ እና ሽማግሌዎቹ ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች የሚያደርገው በምን ሥልጣን እንደሆነ ማወቅ ፈለጉ። [21:23]
መጥምቁ ዮሐንስ ከሰማይ ወይስ ከሰው እንደሆነ የሚያስቡትን ጠየቃቸው። [21:25]
ቀጥሎ ለምን በዮሐንስ እንዳላመኑ ኢየሱስ እንደሚጠይቃቸው ያውቁ ነበር። [21:25]
ዮሐንስ ነብይ ነው ብለው የሚያምኑትን ሕዝብ ፈሩ። [21:26]
የመጀመሪያው ልጅ እንደማይሄድ ተናገረ፣ ነገር ግን አሳቡን ቀይሮ ሄደ። [21:28]
የመጀመሪያው ልጅ እንደማይሄድ ተናገረ፣ ነገር ግን አሳቡን ቀይሮ ሄደ። [21:29]
ሁለተኛው ልጅ እንደሚሄድ ተናገረ፣ ነገር ግን ሳይሄድ ቀረ። [21:30]
የመጀመሪያው። [21:31]
እነርሱ ዮሐንስን አምነውበት ስለነበር፣ ነገር ግን ሊቀ ካህናቱ እና ጸሐፍቱ በዮሐንስ ስላላመኑ እነዚያ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንደሚገቡ ኢየሱስ ተናገረ። [21:31]
እነርሱ ዮሐንስን አምነውበት ስለነበር፣ ነገር ግን ሊቀ ካህናቱ እና ጸሐፍቱ በዮሐንስ ስላላመኑ እነዚያ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንደሚገቡ ኢየሱስ ተናገረ። [21:32]
የወይን እርሻ ሠራተኞቹ አገልጋዮቹን መትተው፣ ገደሏቸው፣ ወገሯቸውም። [21:35]
የወይን እርሻ ሠራተኞቹ አገልጋዮቹን መትተው፣ ገደሏቸው፣ ወገሯቸውም። [21:36]
ባለቤቱ በስተመጨረሻ የገዛ ልጁን ላከ። [21:37]
የወይን እርሻ ሠራተኞቹ የባለቤቱን ልጅ ገደሉት። [21:38]
የወይን እርሻ ሠራተኞቹ የባለቤቱን ልጅ ገደሉት። [21:39]
ባለቤቱ የመጀመሪያዎቹን የወይኑ እርሻ ቅጥረኞች ማጥፋት እና ከዚያም ለሚከፍሉ ሌሎች የወይን እርሻ ሠራተኞች ማከራየት እንዳለበት ተናገሩ። [21:40]
ባለቤቱ የመጀመሪያዎቹን የወይኑ እርሻ ቅጥረኞች ማጥፋት እና ከዚያም ለሚከፍሉ ሌሎች የወይን እርሻ ሠራተኞች ማከራየት እንዳለበት ተናገሩ። [21:41]
ግንበኞች የናቊት ድንጋይ የማእዘን ራስ ሆነ። [21:42]
የእግዚአብሔር መንግሥት ከሊቀ ካህናት እና ፈሪሳውያን እንደሚወሰድ፣ ከዚያም ፍሬ ለሚያፈሩ ሕዝቦች እንደሚሰጥ ኢየሱስ ተናገረ። [21:43]
ሕዝቡ ኢየሱስን እንደ ነብይ ያዩት ስለ ነበረ፣ ሕዝቡን ፈርተው ነበር። [21:46]
መንግሰተ ሰማያት . . . ትመስላለችThe kingdom of heaven is like በ MAT 13:24 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምህ ተመልከት የተጋበዙት ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ንጉሡ የጋበዛቸው ሰዎች
እነዚህ ሰዎች "የተጋበዙት እንግዶች" (MAT 22:4) ግብዣውን ከቁም ነገር አልቆጠሩትም "የእርሱን ግብዣ ቸል አሉት"
የማቋረጫ መንገድ "መንገዶች የሚገናኙበት ቦታ" አደራሽ ትልቅ ክፍል
ኢየሱስ በሚናገርበት ወቅት እንዴት ያቋርጡት ነበር "ኢየሱስ አንድ ነገር ስናገር በየመኃሉ እያቋረጡት ለክስ የሚሆናቸውን ነገር ለማግኘት ጥረት ያደርጉ ነበር፡፡” ከሄሮዶስ ወገን ከሮማዊያን አገዛዝ ጋር ጓድኛ የሆነው የአይሁድ ንጉሥ የሆነው የሄሮዶስ ተወካዮች እና ተከታዮች በሰዎች መካከል ልዩነት አታደረግም "ለሰዎች የተለየ አክብሮት አትሰጥም " ወይም "በጣም ጠቃሚ ለሚባሉ ሰዎች ትኩርት አትሰጥም"
ዲናር የአንድ ቀን ደሞዝ የሆነ የሮማዊን ገንዘብ ነው
የቄሳርን "የቄሳር የሆነው ነገር የእግዚአብሔርን "የእግዚአብሔር የሆነውን ነገር"
መምህር ሙሰተ እንዲህ ብሏል “አንድ ሰው ከሞተ ሙሴ በቅዱሳት መጽሕፍት ውስጥ ስለጻፈው ነገር ጠየቁት፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ በትቅስ ውስጥ ሌላ ትቅስ መጻፍን የማይፈቅድላችሁ ከሆነ በተዘዋዋር መንገድ ሀሳቡን መግለጽ ትችላላችሁለ “ሙሴ አንድ ሰው ከሞት” (ተመልከት ወንድሙ . . . ምስቱ . . ወንድሙ የሞተው ሰው
ሁሉም አንዱ ከሌላኛው በኋላ "የሰውዬው ወንድሞች ሁሉ እርሷን ካገቡ በኋላ ሞቱ” ወይም “ሁሉም ወንድሞቹ ከሞቱ በኋላ”
ማቴዎስ 22፡29-30 የእግዚአብሔርን ኃይል "እግዚአብሔር ምን ማድረግ እንደሚችል"
እንዲህ የሚል ነገር አላነበባችሁምን . . . ያዕቆብ? "እንዳነበባችሁ አውቃለሁ ነገር ግን ያዕቆብ . . . የሚለውን የተረዳችሁት ግን አይመስልም” በ . . . ለእናንተ የተነገረው "እገዚአብሔር ለእናንተ የተናገረው እግዚአብሔር እንዲህ ይላል “እኔ . . . ያዕቆብ”? ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ ነው፡፡ “እግዚአብሔር ለሙሴ እንዲህ አለው፡፡ እኔ እግዚአብሔር የአብረሃም አምላ፣ የይሳቅ አምላክ እና የያዕቆብ አምላክ ነኝ፡፡”
የሕግ ባለሞያዎች የሙሴን ሕግ ጠንቅቀው የሚያውቁት ፈሪሳዊያን
ወደዱት ሕግጋቱን ወደዱት MAT 22:37.
ማቴዎስ 22፡41-42
ጠላቶችህን የእግር መረገጫ እስካደረግ ድረስ "ጠላቶችን እስካጠፋቸው ድረስ”
ዳዊት ክርስቶስን “ጌታዬ” ብሎ ከጠራው እንዴት እርሱ የዳዊት ልጅ ሊሆን ይችላል? ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ዳዊት ጌታዬ ብሎ ጠርቶታል ስለዚህ ክርስቶስ ከዳዊት ዘር በላይ ነው ማለት ነው፡፡” ዳዊት ክርስቶስን እንዲህ ብሎ ከጠራው ዳዊት ክርስቶስን “ጌታዬ” ብሎ ከጠራው፡፡ ይህ ሊሆን የሚችለው ክርስቶስ የዳዊት ዘር የሆነ ብቻ ሳይን ከዚያም በላይ የሆነ ነው፡፡
አንዳንዶች ግብዣውን ከልባቸው አልተቀበሉም ነበርና ወደ ገዛ ሥራቸው ሄዱ፣ ሌሎች በንጉሡ አገልጋዮች ላይ እጆቻቸውን በመጫን ገደሏቸው። [22:5]
አንዳንዶች ግብዣውን ከልባቸው አልተቀበሉም ነበርና ወደ ገዛ ሥራቸው ሄዱ፣ ሌሎች በንጉሡ አገልጋዮች ላይ እጆቻቸውን በመጫን ገደሏቸው። [22:6]
ንጉሡ ሠራዊቱን ልኮ፣ እነዚያን ነፍሰ-ገዳዮች ገደላቸው፣ ከተሞቻቸውንም አቃጠለ። [22:7]
ከዚያ በኋላ ንጉሡ የእርሱ አገልጋዮች ሊያገኟቸው የቻሉትን ያክል መጥፎም ሆነ ጥሩ ሰዎችን ጋበዙ። [22:9]
ከዚያ በኋላ ንጉሡ የእርሱ አገልጋዮች ሊያገኟቸው የቻሉትን ያክል መጥፎም ሆነ ጥሩ ሰዎችን ጋበዙ። [22:10]
ንጉሡ እንዲታሠር እና በውጭ ወዳለው ጨለማ እንዲጣል አስደረገ። [22:13]
ፈሪሳውያኑ ኢየሱስን በገዛ ራሱ ንግግር ለማጥመድ እየሞከሩ ነበር። [22:15]
ለቄሳር ግብር መክፈል ተፈቅዶ እንደሆን ወይም እንዳልሆነ ኢየሱስን ጠየቁት። [22:17]
የቄሳርን ለቄሳር፣ የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር እንዲሰጡ ኢየሱስ ተናገረ። [22:21]
ትንሣኤ የሚባል እንደሌለ ሰዱቃውያኑ ያምኑ ነበር። [22:23]
ሴቲቱ ሰባት ባሎች ነበሯት። [22:26]
ሴቲቱ ሰባት ባሎች ነበሯት። [22:27]
ሰዱቃውያኑ መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል እንደማያውቁ ኢየሱስ ተናገረ። [22:29]
በትንሣኤ ትዳር እንደማይኖር ኢየሱስ ተናገረ። [22:30]
እግዚአብሔር የአብረሃም፣ የይስሃቅ እና የያዕቆብ፣ የሕያዋን አምላክ እንደሆነ የተነጋረበትን ክፍል ኢየሱስ ጠቀሰ። [22:32]
ፈሪሳዊው ህግ ዐዋቂ ኢየሱስን የጠየቀው ከህግ ታላቂቱ ትእዛዝ የትኛዋ እንደሆነች ነበር። [22:36]
እግዚአብሔር አምላክህን በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም ነፍስህ፣ በፍጹም አሳብህ ውደድ የምትለው ታላቅ እና ፊተኛ ትእዛዝ ነች። [22:37]
እግዚአብሔር አምላክህን በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም ነፍስህ፣ በፍጹም አሳብህ ውደድ የምትለው ታላቅ እና ፊተኛ ትእዛዝ ነች። [22:38]
ባልንጀራህን እንደ ራስህ አድርገህ ውደድ የምትለዋ ሁለተኛይቱ ትእዛዝ ነች። [22:39]
ክርስቶስ የማን ልጅ እንደሆነ ኢየሱስ ጠየቃቸው። [22:42]
ክርስቶስ የዳዊት ልጅ እንደሆነ ፈሪሳውያን ተናገሩ። [22:42]
ኢየሱስ ቀጥሎ የጠየቃቸው ዳዊት ልጁን እንዴት ክርስቶስ፣ ጌታዬ ብሎ ሊጠራው እንደቻለ ነበር። [22:45]
ፈሪሳውያን ለኢየሱስ ቃል ምንም መመለስ አልቻሉም ነበር። [22:46]
ከባድና አስቸጋሪ ሸክም ተብትበው በሰው ትከሻ ይጭናሉ፥ "ተግባራዊ ለማድረግ በጣም አስቸጋሪ የሆኑ ደንቦችን በእናንተ ላይ ይጭናሉ" እነርሱ ግን በጣታቸው ስንኳ ሊነኩት አይወዱም። "ምንም ዓይነት እገዛ ለማድረግ ግን ፈቃደኞች አይደሉም" አሸንክታብ ቅዱሳት መጻሕፍት የተጻፉበት ወረቀት መያዥያ ትንሽ የቆዳ ሳጥን
በምድር ላይ ማንንም አባት ብላችሁ አትጥሩ "በምድር ላይ ማንንም አባት ብላችሁ አትጥሩ” ወይም “በምድር ላይ ያለን ማንንም ሰው አባቴ ብላችሁ አትጥሩ" በሰማይ ያለ አንድ አባት አላችሁና እግዚአብሔር አባር የአማኞች ሁሉ “አባት” ነው፡፡ አንድ መምህር አላችሁ እርሱም ክርስቶስ ነው ኢየሱስ “ክርስቶስ” ብሎ ስናገር በሦስተኛ መደብ ስለራሱ መናገሩ ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክርለ “እኔ ክርስቶስ፣ እኔ ብቻ የእናንተ መምህር ነኝ"
ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደረግ "ራሱን በጣም አስፈላጊ የሚያደረግ" ከፍ ከፍ ያለ "ራሱን በጣም አስፈላጊ ያደረገ"
አትገባም "እግዚአብሔር በአንተ ላይ እንዲገዛ አትፈቅድ" የመበልቶችን ቤት መበዝበዝ "የሚጠብቃቸው ወንድ ያሌላቸው ሴቶች ትዘርፋለህ” የገሃነም ልጅ "ለገሃነም የተገባህ ሰው" ወይም "ወደ ገሃነም መግባት ያለበት ሰው
የእውር ምሪት . . . ሞኞች ምንም እንኳ መሪዎቹ ዐይነ ሥውራን ባይሆንም እንደ ተሳቱ ማወቅ አይችሉም ነበር በመኃላ ታሥሯል "ለማድረግ በመኋላ የገባውን ቃል መፈጸም አለበት” ወርቁ ነውን? ወይስ ወርቁን የቀደሰው ቤተ መቅደስ? ኢየሱስ ይህንን ጥቅስ ፈሪሳዊያንን ለመገሰጽ ተጠቅሞበታል፡፡
ዐይነ ሥውራን መንፈሳዊ ዐይነ ሥውርነት ያለባቸው ሰዎች መባው ነውን? ወይስ መባውን የሚቀድሰው መሠዊያው? ኢየሱስ ይህንን ጥቅስ እንሱ እሰቀድመው የሚያውቁትን ነገር ለማስታወስ ተጠቅሞበታል ስጦታ/መባ በመሰዊያው ላይ በእግዚአብሔር ፊት የሚቀርብ የእንስሳት መስዋዕት ወይም እህል መስዋዕት ነው፡፡ አንድ ጊዜ መሰዊያው ላይ ከሆነ ቧላ መስዋእት ይሆናል፡፡
ወዮላችሁ በ MAT 23:13 በምን መንገድ እንተረጎምከው ተመልከት መባው ነውን? ወይስ መባውን የሚቀድሰው መሠዊያው? ለምግብ ጥሩ ጣዕም ለመስጠጥ የሚውሉ ቅጠላ ቅጠሎች እና ፍሬዎች ዐይነ ሥውራነት መሪዎች እነዚህ ሰዎች አካላዊ ዐይናቸው አልጠፋም፡፡ ኢየሱስ አካላዊ ዐይነ ሥውርነትን ከመንፈሳዊ ዐይነ ሥውርነት ጋር ያነጻጽራል፡፡ ትንኝን የምታጠሩ ግመልንም የምትውጡ። በጣም ትንንሽ የሆኑ ንጹሕ እንስሳትን ላለመዋጥ በመጠንቀቅ የትልቁን ንጹሕ ያልሆነ እንስሳ ሥጋ ግን ሆን ብላችሁ ወይም ሳታውቁ ትበላላችሁ ልክ እንደዚሁ በጣም ትንነሽ የሆኑ ሕግጋትን ለመጠበቅ ጥረት ታደርላችሁ ይሂን እንጂ በጣም አስፈላጊ የሆኑ ሕግጋትን ግን ቸል ትላላችሁ፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "ልክ ትንኝ በምጠጣው ነገር ውስጥ የሚያወጣ ነገር ግን ግመል እንደሚውጥ ሰው ሞኞች ናችሁ፡፡” ትንኝን እንዳይገባ ትንንኝ ወደ አፋቸው እንዳይገባ በጨርቅ አጥልለው ይጠጣሉ ትንኝ ትንንሽ በራሪ ነፍሳት
ወዮላችሁ በ MAT 23:13 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ የብርጭቆ እና የሣህኑን ውጪ ታጠራላችሁ “ጸሐፍ” እና “ፈርሳዊያን” ከውጪ በሰዎች ፊት “ንጹሕ መስለው” መታየት ይፈልጋሉ፡፡ በውስጡ ግን የሙታን አጥንት ርኩሰትም ሁሉ የተሞሉ "ከሚያስፈልጋቸው በላይ እንዲኖራው በጉልበት የሌላ ሰውን ነገር ይወስዳሉ “ ዐይነ ሥውራን ፈሪሳዊያን ፈሪሳዊያን እውነቱን አይረዱትም፡፡ አካላዊ ዐይነሥውነት ግን የለባቸውም፡፡ ውጭው ደግሞ ጥሩ እንዲሆን አስቀድመህ የጽዋውንና የወጭቱን ውስጡን አጥራ። ልባቸው ከእግዚአብሔር ጋር ትክክል ከሆነ ሕይወታቸውም ይህንኑ ያሳያል፡፡
የአባቶቻችሁን መስፈሪያ ኃጢአት ሙሉ። "አባቶቻችሁ የጀመሩትን ኃጢአት ፈጽሙ" እናንተ እባቦች፥ የእፉኝት ልጆች "ልክ እንደ አደገኛ እና መርዛማ እባቦች ናችሁ" ከገሃነም ፍርድ እንዴት ታመልጣላችሁ? "የገሃነም ፍርድን የሚታመልጡበት ምንም ዓይነት መንገድ የለም!" (ተመልከት:
ከአቤል . . እስከ ዘካሪያስ አቤል የመጀመሪያው የተገደለ ሰው ነው እንዲሁም ምናልባትም በአይሁዳዊያን ዘንድ በቤተ መቅደስ ውስጥ የተገደለው የመጨረሻው ሰው ነው፡፡ ዘካሪያስ ይህ የመጥመቁ ዮሐንስ አባት አይደለም
እየሩሳሌም፣ እየሩሳሌም ኢየሱስ በእየሩሳሌም የሚኖሩ ሰዎችን ልክ ከተማዋን እንደሚናገር ሰው ይናገራቸዋል፡፡ ልጆቻችሁ የሁሉም እስራኤላዊያን ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላችኋል። ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እግዚአብሔር ቤታችሁን ትቶ ይሄዳል ባዶም ይሆናል” ቤታችሁ አማራጭ ትርጉሞች፡ 1) የኢየሩሳሌም ከተማ ወይም 2) ቤተ መቅደሱ፡፡
ጸሐፍት እና ፈሪሳውያን ከሙሴ ወንበር ሆነው የሚያስተምሯቸውን ነገሮች እንዲያደርጉ እና እንዲፈጽሟቸው ኢየሱስ ለሕዝቡ ተናገረ። [23:2]
ጸሐፍት እና ፈሪሳውያን ከሙሴ ወንበር ሆነው የሚያስተምሯቸውን ነገሮች እንዲያደርጉ እና እንዲፈጽሟቸው ኢየሱስ ለሕዝቡ ተናገረ።። [23:3]
ነገሮችን ስለሚሉ፣ ነገር ግን ስለማያደርጓቸው የእነርሱን ተግባራት መምሰል እንደሌለባቸው ኢየሱስ ተናገረ። [23:3]
ጸሐፍት እና ፈሪሳውያን ተግባራቸውን የሚያደርጉት በሕዝብ ፊት ለመታየት ብለው ነበር። [23:5]
አንዱ አባታችን በሰማይ ያለው፣ እንዲሁም አንዱ መምህራችን ክርስቶስ እንደሆነ ኢየሱስ ተናገረ። [23:8]
አንዱ አባታችን በሰማይ ያለው፣ እንዲሁም አንዱ መምህራችን ክርስቶስ እንደሆነ ኢየሱስ ተናገረ። [23:9]
አንዱ አባታችን በሰማይ ያለው፣ እንዲሁም አንዱ መምህራችን ክርስቶስ እንደሆነ ኢየሱስ ተናገረ [23:10]
ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርገውን እግዚአብሔር ያዋርዳል፣ ራሱን ዝቅ ዝቅ የሚያደርገውን እግዚአብሔር ያከብራል። [23:12]
ኢየሱስ ጸሐፍትንና ፈሪሳውያንን በተደጋጋሚ ግብዞች በማለት ጠርቷቸዋል። [23:13]
ኢየሱስ ጸሐፍትንና ፈሪሳውያንን በተደጋጋሚ ግብዞች በማለት ጠርቷቸዋል። [23:14]
ጸሐፍት እና ፈሪሳዊያን አዲስ አማኝ ሲያገኙ፣ ከእነርሱ እጥፍ ጊዜ የከፋ የሲዖል ልጅ ያደርጉታል። [23:15]
ኢየሱስ ጸሐፍትንና ፈሪሳውያንን በተደጋጋሚ ግብዞች በማለት ጠርቷቸዋል። [23:15]
ጸሐፍት እና ፈሪሳውያን እውራን መሪዎች እና እውራን ሞኞች እንደሆኑ ኢየሱስ ተናገረ። [23:16]
ጸሐፍት እና ፈሪሳውያን እውራን መሪዎች እና እውራን ሞኞች እንደሆኑ ኢየሱስ ተናገረ። [23:17]
ጸሐፍት እና ፈሪሳውያን በሕግ ያሉትን ዋና ነገሮች ማለትም ፍርድን፣ ምህረትን እና ታማኝነትን ማድረግ አቅቷቸው ነበር። [23:23]
ጸሐፍት እና ፈሪሳውያን ማጥራት ያቃታቸው ውጪው ደግሞ ንጹህ እንዲሆን የጽዋቸውን ውስጥ ነበር። [23:25]
ጸሐፍት እና ፈሪሳውያን ማጥራት ያቃታቸው ውጪው ደግሞ ንጹህ እንዲሆን የጽዋቸውን ውስጥ ነበር። [23:26]
ጸሐፍት እና ፈሪሳውያን በውስጣቸው ግብዝነት እና ዐመፀኝነት ተሞልተው ነበር። [23:28]
የጸሐፍት እና ፈሪሳውያን አባቶች የእግዚአብሔርን ነብያት ገድለዋቸው ነበር። [23:29]
የጸሐፍት እና ፈሪሳውያን አባቶች የእግዚአብሔርን ነብያት ገድለዋቸው ነበር። [23:30]
የጸሐፍት እና ፈሪሳውያን አባቶች የእግዚአብሔርን ነብያት ገድለዋቸው ነበር። [23:31]
ጸሐፍትና ፈሪሳውያን የሲዖል ፍርድ ይቀበላሉ። [23:33]
እንደሚገድሏቸው፣ አንዳንዶቹን እንደሚሰቅሏቸው፣ አንዳንዶቹን እንደሚገርፏቸው፣ ሌሎቹን ከከተማ እንደሚያባርሯቸው ኢየሱስ ተናገረ። [23:34]
በምድር ላይ የፈሰሰው የጻድቃን ደም ሁሉ በጸሐፍትና በፈሪሳውያን ላይ ይመጣል። [23:35]
እነዚህ ነገሮች ሁሉ በዚህኛው ትውልድ ላይ እንደሚሆኑ ኢየሱስ ተናገረ። [23:36]
ኢየሱስ የኢየሩሳሌምን ልጆች በአንድ ላይ ለማሰባሰብ ተመኝቶ ነበር፣ ነገር ግን እነርሱ አልተስማሙም። [23:37]
የኢየሩሳሌም ቤት አሁን ላይ የተተወ እንደሆነ ይቀራል። [23:38]
ይህን ሁሉ ታያላችሁን? አማራጭ ትርጉሞች: ኢየሱስ እየተናገረ ያው 1) ስለ ቤተ መቅደሱ ግንባታ
ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ "ማንም ስለዚህ ጉዳይ እንዳይዋሻችሁ ተጠንቀቁ"
አትደናገጡ "እነዚህ ነገሮች አያናውጧችሁ"
አሳልፈው ይሰጢ,ጡአችዋል
"የእናንተን መሰደድ የሚወዱ ሰዎች አሳልፈው ይሰጡአችዋል" አሳልፎ መሰጠት በ MAT 10:17 ላይ ምን ብለህ እንዴተረጎምከው ተመልከት፡፡
የብዙዎች ፍቅር እየቀዘቀዘ ይመጣል አማራጭ ትርጉሞች: 1) "ብዙ ሰዎች ሌሎች ሰዎችን መውደድ ይተዋሉ" ወይም 2) "ብዙ ሰዎች እግዚአብሔርን መውደዳቸውን ይተዋሉ" በዓለም ሁሉ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “በሁሉም ሥፍራ ያሉ ሁሉም ሰዎች"
በነብዩ ዳንኤል የተነገረው ትንቢት ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ነብዩ ዳንኤል በጻፈው ትንቢት መሠረት”
ነፍሰ ጡር ያረገዘች ሴት ክረምት "ቀዝቃዛ ወራት" ሥጋ ለባሽ ሰዎች
አትመኑ "የሚነግሯችሁን ውሸት አትመኑ"
መብረቅ ከምሥራቅ ወጥቶ እስከ ምዕራብ እንደሚታይ፥ የሰው ልጅ መምጣት እንዲሁ ይሆናልና፤ አመጣጡ በፍጥነት እና በቀላሉ ለታይ በሚችል መልኩ ነው፡፡ የሞተ እንስሳ ባለበት በዚያ ጥንብ አንሳዎች ይሰበሰባሉ አማራጭ ትርጉሞች 1) የሰው ልጅ በመጣ ጊዜ ሁሉም ሰዎች ያዩታል እንዲሁም የእርሱን መምጣት ያውቃሉ ወይም 2) በመንፈሳዊ ሕይወታቸው የሞቱ ሰዎች ባሉበት ሥፍራ ውሸትን የሚነግሯቸው ሐሰተኛ ነብያት በዚያ አሉ፡፡ ጥንብ አንሳ የሞቱ ወይም ሊሞቱ ያሉ እንስሳትን ሥጋ የሚበሉ አእዋፋት
ወዲያው "በዚያ ቅጽበት" በእነዚያ ቀናት በ MAT 24:23-28 ላይ የተገለጹት ቀናት አራት ንፈሳት ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ከሰሜን፣ ከደቡበድ፣ ከምስራቅ እና ከምዕራብ” ወይም “ከሁሉም አቅጣጫ" የሰማይ ኃይላት ሁሉ ይናወጣሉ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እግዚአብሔር በሰማይ ያሉትን ነገሮች ሁሉ እና ከሰማይ በላይ ያሉትን ነገሮች ያናውጣል
ደረታቸውን ይደቃሉ የሚመጣውን ፍርድ በመፍራት ደረታቸውን ይመታሉ ይሰበሰባሉ "መላዕክቶቹ ይሰበስባሉ" ምርጦቹን የሰው ልጅ የመረጣቸውን ሰዎች ከአራቱም ንፋሳት ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ከሰሜን፣ ከደቡበድ፣ ከምስራቅ እና ከምዕራብ” ወይም “ከሁሉም አቅጣጫ"
በደጅ እንደቀረበ እወቁ ወራሪ ሠራዊት ከተማዋን ሰብሮ ለመግባት ዝግጁ እንደሆነ
ይህ ተውልድ አያልፍም "ዛሬ የሚኖሩ ሰዎች አይሞቱም" ይህ ሁሉ እስኪሆን ድረስ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እነዚህ ነገሮች እግዚብሔር እንዲሆኑ እስኪደረግ ድረስ" ሰማይ እና ምድር ያልፋሉ "ሰማይ እና ምድር ሕልውናቸው ያበቃል"
የሰው ልጅም ቢሆን "የሰው ልጅ እንኳ"
በኖህ ዘመን እንደሆነው የሰው ልጅ መምጣትም እንዲሁ ይሆናል "የሰው ልጅ የሚመጣበት ቀን ልክ በኖህ ዘመን እንደሆነው ነው” ምክንያቱም ማንም መጥፎ ነገር ይሆንብና ብሎ አላሰበም፡፡ በዚያ ዘመን እንደሆነው ከጥፋት ውሃ በፊት ይበሉ እና ይጠጡ . . . ጠራርቆ ወሰዳቸው- የሰው ልጅ መምጣትም እንዲሁ ይሆናል "ከሰው ልጅ መምጣት በፊት ያለው ጊዜ ልክ የጥፋት ውሃ ሊመጣ ሲል ያለውን ይመስላል፣ ሁሉም ስበሉና ስጠጡ ሳለ - - - ጠራትቆ ወሰዳቸው”
ከዚያ የሰው ልጅ ሲመጣ አንዱ ይወሰዳል ሌላኛው ይቀራል አማራጭ ትርጉሞች: 1) እግዚአብሔር ወደ ሰማይ ይወስደዋል ሌሎቹን ደግሞ ለፍርድ በምድር ላይ ይተዋቸዋ፡፡ ወይም 2) መላእክት አንዱ ልፍርድ ይወስዱታል ሌላኛውን ለበረከት ይተውታል ወይም (ተመልከት), MAT 13:40-43). የድንጋይ ወፍጮ እህል ለመከካት የሚሆን እቃ ስለዚህ "ከነገርኳችሁ ነገር የተነሳ" ጸንታችሁ ቁሙ "በንቃት ተከታተሉ"
ሌባ ኢየሱስ ልክ እንደ ሌባ ሰዎች ባላሰቡት ሰዓት እንደሚመጣ ተናግሯል፤ ይሁን እንጂ ሊሰርቅ አይደለም የሚመጣው፡፡ ነቅቶ ይጠብቅ ነበር ቤቱ እንዳይዘረፍ “ነቅቶ በጠበቀ ነበር” ቤቱም ሊቈፈር ባልተወም ነበር። "ማንም ቤቱ ገብቶ ንረቱን አንድሰርቅ ባላደረገ ነበር"
እንኪያስ በጊዜው ይሰጣቸው ዘንድ . . . ታማኝና ልባም ባሪያ ማን ነው? "ታማኝ፣ ልባም ባሪያ ማን ነው? ጌታው በጊዜው . . . እርሱን ነው፡፡” ምግባቸውን ይሰጣቸው ዘንድ "በጌታው ቤት ላሉት ሰዎች ምግባቸውን ይሰጥ ዘንድ"
በለልቡ እንዲህ አለ "በአእምሮው እንዲህ አሰበ" እድል ፈንታወን ለመወሰን "ይቀበሉት ዘንድ"
አንድም የቤተመቅደሱ ድንጋይ ሳይፈርስ ባለበት እንደማይቀር ኢየሱስ ተነበየ። [24:2]
ደቀመዛሙርቱ እነዚህ ነገሮች ሲከሰቱ፣ የመምጣቱና የዓለም መጨረሻ ምልክት ምን እንደሚሆን ኢየሱስን ጠየቁት። [24:3]
ብዙዎች ክርስቶስ ነን እያሉ እንደሚመጡ እና ብዙዎችንም እንደሚያስቱ ኢየሱስ ተናገረ። [24:5]
ጦርነት፣ ረሃብ፣ የምድር መናወጥ የምጥ ጣር መጀመሪያ እንደሆኑ ኢየሱስ ተናገረ። [24:6]
ጦርነት፣ ረሃብ፣ የምድር መናወጥ የምጥ ጣር መጀመሪያ እንደሆኑ ኢየሱስ ተናገረ። [24:7]
ጦርነት፣ ረሃብ፣ የምድር መናወጥ የምጥ ጣር መጀመሪያ እንደሆኑ ኢየሱስ ተናገረ። [24:8]
አማኞች በመከራ ይሰቃያሉ አንዳንዶቹም ይሰናከላሉ አንዳቸውም ሌላኛቸውን አሳልፈው ይሰጣሉ። [24:9]
አማኞች በመከራ ይሰቃያሉ አንዳንዶቹም ይሰናከላሉ አንዳቸውም ሌላኛቸውን አሳልፈው ይሰጣሉ። [24:10]
እስከ መጨረሻ የሚጸና ይድናል ሲል ኢየሱስ ተናገረ። [24:13]
የመንግሥቱ ወንጌል መጨረሻው ከመምጣቱ በፊት በዓለም ሁሉ ይሰበካል። [24:14]
አማኞች ወደ ተራሮች መሸሽ እንዳለባቸው ኢየሱስ ተናገረ። [24:15]
አማኞች ወደ ተራሮች መሸሽ እንዳለባቸው ኢየሱስ ተናገረ። [24:16]
አማኞች ወደ ተራሮች መሸሽ እንዳለባቸው ኢየሱስ ተናገረ። [24:17]
አማኞች ወደ ተራሮች መሸሽ እንዳለባቸው ኢየሱስ ተናገረ። [24:18]
በእነዚያ ዘመናት፣ መከራው ታላቅ ይሆናል፣ ታላቅነቱም ከዓለም ጅማሬ አንሥቶ ከሆነው ሁሉ በላይ ነው። [24:21]
ሃሰተኛ ክርስቶሶች እና ሃሰተኛ ነብያት ብዙዎችን ለማሳት ታላላቅ ምልክቶች እና ተዓምራትን ያሳያሉ። [24:24]
የሰው ልጅ መምጣት ከምሥራቅ እስከ ምእራብ እንደሚበርቅ መብረቅ ይሆናል። [24:27]
ፀሐይ እና ጨረቃ ይጨልማሉ፣ ክዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ። [24:29]
የምድር ወገኖች ደረታቸውን ይደቃሉ። [24:30]
መላእክት የተመረጡትን በሚሰበስቡበት ጊዜ ታላቅ የመለከት ድምፅ የሚሰማ ይሆናል። [24:31]
እነዚህ ሁሉ ነገሮች እስኪሆኑ ድረስ ይህ ትውልድ እንደማያልፍ ኢየሱስ ተናገረ። [24:34]
ሰማይና ምድር ያልፋሉ፣ ነገር ግን ቃሎቹ ፈጽሞ እንደማያልፉ ኢየሱስ ተናገረ። [24:35]
እነዚህ ክስተቶች መቼ እንደሚሆኑ የሚያውቀው አብ ብቻ ነው። [24:36]
ሰዎች ሊያጠፋቸው ስለሚመጣው ፍርድ ምንም ሳያውቊ ይበላሉ፣ ይጠጣሉ፣ ያገባሉ ይጋባሉ። [24:37]
ሰዎች ሊያጠፋቸው ስለሚመጣው ፍርድ ምንም ሳያውቊ ይበላሉ፣ ይጠጣሉ፣ ያገባሉ ይጋባሉ። [24:38]
ሰዎች ሊያጠፋቸው ስለሚመጣው ፍርድ ምንም ሳያውቊ ይበላሉ፣ ይጠጣሉ፣ ያገባሉ ይጋባሉ። [24:39]
ጌታ የሚመለስበትን ቀን ስለማያውቁ በእርሱ የሚያምኑት ሁልጊዜ ዝግጁ እንዲሆኑ ኢየሱስ ተናገረ። [24:42]
ታማኝ እና ብልኅ የሆነው አገልጋይ ጌታው በሌለበት ጊዜ ላይ የጌታውን ቤተሰብ ይንከባከባል። [24:45]
ታማኝ እና ብልኅ የሆነው አገልጋይ ጌታው በሌለበት ጊዜ ላይ የጌታውን ቤተሰብ ይንከባከባል። [24:46]
በሚመለስበት ጊዜ፣ ጌታው ታማኝ እና ብልኅ የሆነውን አገልጋይ ባለው ሁሉ ላይ ይሾመዋል። [24:47]
ክፉ የሆነው ባርያ ጌታው በሌለበት ጊዜ ላይ አብረውት የሚሠሩትን ባርያዎች ይመታል፣ ይበላል ይጠጣል፣ ይሰክርማል። [24:48]
ክፉ የሆነው ባርያ ጌታው በሌለበት ጊዜ ላይ አብረውት የሚሠሩትን ባርያዎች ይመታል፣ ይበላል ይጠጣል፣ ይሰክርማል። [24:49]
በሚመለስበት ጊዜ፣ ጌታው ክፉውን አገልጋይ ከሁለት ይሰነጥቀዋል፣ ለቅሶ እና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ይልከዋል። [24:51]
መብራት ይህ እንዲህ ሊሆን ይችላል 1) መብራት ወይም 2) በእንጨት ጫፍ ላይ ጨርቅ በመጠምጠም ጨርቁን በዘይት በመንከር የሚዘጋጅ ችቦ አምስት ሴቶች "አምስት ልጃገረዶች" ትርፍ ዘይት አልያዙም "በመብራታቸው ውስጥ እንጂ ተጠባባቂ ዘይት አልያዙም"
እንቅልፍ ወሰዳቸው "ዐሥሩም ልጃገረዶች ተኙ"
መብራታቸውን አዘጋጁ "በደንብ እንድበራ መብራቸውን አስተካከሉ " ሞኞቹ ለጠቢባኑ እንዲህ አሏቸው "ሞኞቹ ልጃገረዶች ለጠቢባኑ ልጃገረዶች እንዲህ አሏቸው" ዘይታችን ሊያልቅ ነው "በመብራታችን ውስጥ ያለው ዘይት ደምቆ መብረቱን አቁሟል”
ሄዱ "አምስቱ ሞኝ ልጃገረዶች ሄዱ" ዝግጁዎች የሆኑት ተጠባባቂ ዘይት የነበራቸው ልጃገረዶች በሩ ተዘጋ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ብሩን ተዘጋ" ክፈቱልን "ወደ ውስጥ መግባት እንችል ዘንድ በሩን ክፈቱልን" አላውቃችሁም "ማን እንደሆናችሁ አላውቅም”
ይህንን ይመስላል "መንግስ ሰማያት ይህንን ይመስላል" (ተመልከት MAT 25:1) ለሄድ ስነሳ "ለመሄድ ዝግጁ በሆነ ጊዜ” ወይም “ለመሄድ በተነሳ ጊዜ” ሀብቱን አስረከበ "ሀብቱን ይቆጣጠሩለት ዘንድ ስልጣን ሰጣቸው" ሀብቱ "የእርሱ ሀብት” የእርሱ ሀብት መክሊት “አንድ መክሊት” የሃያ ዓመት ደሞዝ ያክላል፡፡ ይህንን በዘመናዊ የገንዘብ መጠን አትለውጡት፡፡ ምሳሌው በማነጻጸር ላይ ያለው አምስት፣ ሁለት እና አንድ እንዲሁም በጣም ትልቅ ሀብትን ነው፡፡ ለተርጓማች ምክር፡ “አምስት ሻንጣ ሙሉ ወርቅ “ ከዚያም አምስት ጠጨማሪ መክሊቶችን አተረፈ “በመክሊቱ ነግዶ አምስት መክሊቶችን አተረፈ”
ሌላ ሁለት አተረፈ "ሌላ ሁለት መክሊቶችን አተረፈ"
አምስት ተጨማሪ መክሊቶችን አተረፈ "አምስት ተጨማሪ መክሊቶችን አተረፍኩ" መክሊቶች በ MAT 25:15 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፤ ጥሩ አድርገሃል "ጥሩ አድርገሃል” ወይም “መልካም አድርገሃል”፡፡ ባሕላቹ ምናልባት የጌታውን ንግግር ይበልጥ መግለጽ የሚያስችል ቃል ይኖረው ይሆናል፡፡
ተጨማር መክሊቶችን አተረፍኩ በ MAT 25:20 ላይ እንዴት እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡ ጥሩ አድርገሃል . . . የጌታው ሰላም በ MAT 25:21 ላይ እንዴት እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡
ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ r እነዚህ ሁለት ዓረፍተ ነገሮች ተመሳሳይ ሀሳብን የሚያስተላልፉ ናቸው፡፡ አገልጋዩ ጌታውን የእርሱ ያልሆነ ምርትን ይሰበስባል በማለት ይከሰዋል፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ምግብን የአንተ ካልሆነ ማሳ ውሰጥ ትሰበስባለህ” " መዝራት በዚያ ዘመን በመሥመር ከመዝራት ይልቅ በጥቂት በጥቂቱ ይበትኑት ነበር፡፡ ተመልከት የአንተ የሆነውን ይኸው ይዤ መጥቻለሁ "ይኼው፣ የአንተን ይዤ መጥቻለሁ"
አንተ ክፉና ሃኬተኛ ባሪያ "አንተ መስራት የማትፈልግ ክፉ ባሪያ ነህ" ካልዘራሁባት እንዳጭድ ካልበተንሁባትም እንድሰበስብ ይህንን ሀሳብ በ MAT 25:24 ላይ እንዴት እንተረጎምክ ተመልከት፡፡ ጠራሴን እወሰዳለሁ “የራሴን ወርቅ እወስዳለሁ" ትርፍ ከባንክ በብድር የሚወሰድ ብር ላይ የሚደመር ትርፍ
ከዚያም የሚበልጥ "የሚበዛ" በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል። "ሰዎች የሚያለቅሱበት እና ጥርሳቸውን የሚያፋጩበት ቦታ"
ማቴዎስ 25፡31-33
አሕዛብም ሁሉ በፊቱ ይሰበሰባሉ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "በፊቱ ሕዝቦችን ሁሉ ይሰበስባል" በፊቱ "ከእርሱ ፊት" አሕዛብን ሁሉ "ከሁሉም ሀገራት የተውጣጡ ሕዝቦች" ፍየሎች ፍየሎች መካከለኛ መጠን ያላቸው በአራት እግሮቻቸው የሚራመዱ ከበግ ጋር ተመሳሳይ የሆኑ አጥቢ እንስሳት ናቸው፡፡ ያስቀምጣቸዋል "የሰው ልጅ ያስቀምጣቸዋል"
ንጉሥ ይህ ኢየሱስ በ MAT 25:31 ላይ ስለ ሰው ልጅ የተናገረው ሌላኛው ሥፍራ ነው፡፡ ንጉሥ . . . በቀኙ ኢየሱስ ስለ ራሱ በሦስተኛ መደብ እየጠናገረ ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እኔ፣ ንጉሡ . . . በቀኜ” ኑ፣ የአባቴ ብሩካን ለተርጓሚዎች ምክር: "ኑ አባቴ የባረካችሁ" አባት ይህ ለእግዚአብሔር የማዕረግ ስም ነው ለእናንተ የተዘጋጀውን መንግስት ውረሱ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እግዚአብሔር ያዘጋጀላችሁን መንግስት ውረሱ"
ንጉሥ "የሰው ልጅ" (MAT 25:31) እንዲህ አላቸው "በቀኙ ላሉት እንዲህ አላቸው" ወንድሞች በቋንቋችሁ ወንዶችን እና ሴቶችን የሚካትት ቃል ቃለ ያንን ቃል ተጠቀሙ፡፡ ለእኔ አድርጋችኋል "ለእኔ እንዳደረጋችሁት እቆጥረዋለሁ"
እናንተ ርጉማን "እናንተ እግዚአብሔር የረገማችሁ" ወደ ተዘጋጀላቸው ዘላለማው እሳት ለተርጓሚዎች ምክር: "እግዚብሔር ያዘጋቸው ዘላለማዊ እሳት" መላእክቱ የእርሱ አጋዦች ታርዤ አላለበሳችሁኝም "ታርዤ አላለበሳችሁኝምን” ታምሜ እና ታስሬ "ታምሜ እነ ታስሬ"
እነርሱም እንዲህ ብለው ይመልሱለታል "በግራው ያሉት" (MAT 25:41) ይመልሱለታል ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ለአንዱ "ከእነዚህ የእኔ ሕዝብ ከሆኑን ለአንዱም” ስላላደረጋችሁ "ለእኔ እንዳላደረጋችሁት አስባለሁ" ወይም "በእርግጥ ያልረዳችሁት እኔን ነው" ዘላለማዊ ቅጣት "ማብቂያ ያሌለው ቅጣት" ጻድቃን ወደ ዘላለም ሕይወት ይገባሉ "ጻድቅ የሆኑ ሰዎች ወደ ዘላለም ሕይወት ይገባሉ"
ሰነፎቹ ቆነጃጅት ከመብራታቸው ጋር ምንም ዓይነት ዘይት አልያዙም ነበር። [25:3]
ብልኆቹ ቆነጃጅት ከመብራታቸው ጋር ትርፍ ዘይት ይዘው ነበር። [25:4]
ሙሽራው የመጣው ከሚጠበቅበት ጊዜ ዘግይቶ በእኩለ ሌሊት ላይ ነበር። [25:5]
ሙሽራው የመጣው ከሚጠበቅበት ጊዜ ዘግይቶ በእኩለ ሌሊት ላይ ነበር። [25:6]
ብልኆቹ ቆነጃጅት ከሙሽራው ጋር ወደ ሠርጉ ድግሥ ገቡ። [25:10]
ሰነፎቹ ቆነጃጅት ዘይት ለመግዛት ሄዱ፣ ሲመለሱ ወደ ድግሡ የሚያስገባው በር ተዘጋባቸው። [25:10]
ሰነፎቹ ቆነጃጅት ዘይት ለመግዛት ሄዱ፣ ሲመለሱ ወደ ድግሡ የሚያስገባው በር ተዘጋባቸው። [25:11]
ሰነፎቹ ቆነጃጅት ዘይት ለመግዛት ሄዱ፣ ሲመለሱ ወደ ድግሡ የሚያስገባው በር ተዘጋባቸው። [25:12]
ቀኑንና ሰዓቱን ስለማያውቊ አማኞች መጠንቀቅ እንዳለባቸው ኢየሱስ ተናገረ። [25:13]
አምስት ታላንት ያለው ሌላ አምስት ታላንት አተረፈ፣ ሁለት ታላንት ያለው ሌላ ሁለት ታላንት አተረፈ። [25:16]
አንድ ታላንት ያለው መሬቱን ቆፍሮ የጌታውን ገንዘብ ቀበረ። [25:18]
ጌታው ለረጅም ጊዜ ርቆ ሄዶ ነበር። [25:19]
ጌታቸው “መልካም አንተ በጎና ታማኝ ባርያ!” አለውና በበርካታ ነገሮች ላይ ሾመው። [25:20]
ጌታቸው “መልካም አንተ በጎና ታማኝ ባርያ!” አለውና በበርካታ ነገሮች ላይ ሾመው። [25:21]
ጌታው “አንተ ክፉና ሃኬተኛ ባርያ” አለውና አንዱን ታላንቱን ከወሰደበት በኋላ በውጭ ወዳለው ጨለማ ጣለው። [25:26]
የሰው ልጅ ሕዝቦችን ሁሉ አከማችቶ ሰዎችን አንዳቸው ከሌላኛቸው ይለያቸዋል። [25:31]
የሰው ልጅ ሕዝቦችን ሁሉ አከማችቶ ሰዎችን አንዳቸው ከሌላኛቸው ይለያቸዋል። [25:32]
በንጉሡ ቀኝ እጅ ያሉት ከዓለም መፈጠር በፊት ጀምሮ ለእነርሱ የተዘጋጀላቸውን መንግሥት ይቀበላሉ። [25:34]
በንጉሡ ቀኝ ያሉት ለተራቡት ምግብ ሰጥተዋል፣ የተጠሙትን አጠጥተዋል፣ እንግዶችን ተቀብለዋል፣ የታረዙትን አልብሰዋል፣ ለታመሙት እንክብካቤ አድርገዋል፣ እስረኞችንም ጎብኝተዋል። [25:35]
በንጉሡ ቀኝ ያሉት ለተራቡት ምግብ ሰጥተዋል፣ የተጠሙትን አጠጥተዋል፣ እንግዶችን ተቀብለዋል፣ የታረዙትን አልብሰዋል፣ ለታመሙት እንክብካቤ አድርገዋል፣ እስረኞችንም ጎብኝተዋል። [25:36]
በንጉሡ ግራ ያሉት ለዲያቢሎስ እና ለመላእክቱ ወደተዘጋጀው የዘላለም እሳት ይጣላሉ። [25:41]
በንጉሡ ግራ ያሉት ለተራቡት አላበሉም፣ ለተጠሙት አላጠጡም፣ እንግዶችን አልተቀበሉም፣ የታረዙትን አላለበሱም፣ የታመሙትን አልተንከባከቡም፣ እስረኞችንም አልጎበኙም። [25:42]
በንጉሡ ግራ ያሉት ለተራቡት አላበሉም፣ ለተጠሙት አላጠጡም፣ እንግዶችን አልተቀበሉም፣ የታረዙትን አላለበሱም፣ የታመሙትን አልተንከባከቡም፣ እስረኞችንም አልጎበኙም። [25:43]
በፈጸመ ጊዜ፥ በቋንቋችሁ አዲስ ታሪክ መጀመሪያን ማሳያ መንገድ ካለ ያንን ተጠቀሙ፡፡ እነዚህ ቃላትን በ MAT 24:4-25:46 ውስጥ ያሉትን ቃላት የሰው ልጅ እንዲሰቀል አሳልፈው ይሰጡታል "አንዳንድ ሰዎች የሰው ልጅን ለሚሰቅሉት አሳልፈው ይሰጡታል"
ተሰበሰቡ "በምስጥር" በበዓል ቀን ግን አይደለም ለተርጓሚዎች ምክር፡ “በበዓል ቀን ኢየሱን መግደል የለብንም” በዓል ዓመታዊ የፈስካ በዓል
ምግብ ለመብላት ተቀምጠው ሳለ በጎናቸው ጋደም ብለው፡፡ ሰዎች ምግብ ለመመገብ የሚቀመጡበትን መንገድ የሚገልጽን ቃል መጠቀም ትችላለህ፡፡ አንድት ሴት ወደ እርሱ መጥታ አንድደት ሴት ወደ ኢየሱስ መጥታ የአልባስጥሮስ ጠርሙስ ከለስላሳ ድንጋይ የሚሰራ በጣም ውድ መያዥያ ነው ሽቶ ጥሩ መዓዛ ያለው ዘይት የዚህ ብክነት ምክንያቱ ምንድ ነው? "ይህች ሴት ይህንን ሽቶ በማባከኗ መጥፎ ነገር አድርጋለች!"
ይህችን ሴት ስለምን ታስጨንቋታላችሁ? "ይህችን ሴት ልታስጨንቋት አይገባም!" እናንተ . . . እናንተ . . . አናንተ ደቀ መዛሙርቱ
ለእነርሱ አሳልፎ ይሰጣቸው ዘንድ “አሳልፌ እንድሰጣችሁ” ወይም "ኢየሱስን መያዝ ትችሉ ዘንድ" ሠላሣ ብር ይህ ቃል በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከሚገኘው የትንቢት መልዕክት ጋር ተመሳሳይ ቃል በመሆኑ የገንዘቡን መጠን በዘመናዊ የገንዘብ መጠን ከመጻፍ ይልቅ እንዳለ ማስቀመጡ ተመራጭ ነው፡፡ ለእነርሱ አሳልፎ ለመስጠት "የካህናት አለቆች ኢየሱስን ይዙት ዘንድ ለማገዝ”
እርሱም፦ ወደ ከተማ ከእገሌ ዘንድ ሄዳችሁ፦ መምህር፦ ጊዜዬ ቀርቦአል፤ ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ከአንተ ዘንድ ፋሲካን አደርጋለሁ ይላል በሉት አለ።" ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ለሌላ ሰው ሄደው የኢየሱስን መልክት እንድነገሩት ነገራቸው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ለደቀ መዛሙርቱ ወደ ከተማ እንዲሄዱ፣ ወደ አንድ ሰው ቤትም እንዲሄዱና መምህር እንዲህ ይልሃል ብለው እንድነግሩት ነገራቸው፡፡ “ጊዜዬ ቀርቦአል፡፡ ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ፋስካን በአንተ ቤት ማሳለፍ እፈልጋለሁ” ብሏል ብላችሁ ንገሩት፡፡ ወይም “ ደቀ መዛሙርቱ ወደ አንድ ሰው ዘንድ እንዲሄዱና መምህራቸው ጊዜዬ ቀርቧል፤ ፋስካን በአንተ ቤት ከደቀ መዛሙርተቼ ጋር ማሳለፍ እፈልጋለሁ ብለው ይነግሩት ዘንድ ላካቸው፡፡” ጊዜዬ አማራጭ ትርጉሞች: 1) "የነገርኳችሁ ጊዜ" (UDB) or 2) "እግዚአብሔር ለእኔ አስቀድሞ ያዘጋጀው ጊዜ" ቀርቧል አማራጨ ትርጉሞች: 1) "ቅርብ ነው" ፋስካን ማክበር "የፋስካን መብል መብላት" ወይም "ልዩ የሆነ ምግብ በመብላት ፋስካን ማክበር"
ምግብ ልመገብ ተቀመጠ በባሕላችሁ ሰዎች ምግብ ለመመገብ የሚቀመጡበትን መንግድ የሚገለጽ ቃልን ተጠቀሙ፡፡ ጌታዬ እኔ በእርግጠኝነት አይደለሁም? "በእርግጠኝነት እኔ አይደለሁም፣ ነኝ እንዴ ጌታዬ?"
የሰው ልጅን አሳልፎ የሚሰጥ ሰው "የሰው ልጅን የሚከዳ ሰው" አንተ ራስህ አልክ "አንተ ራስህ እንዳልከው አንተ ነህ" ወይም "አንተ ራስህ አሁን አመንክ"
ወሰደ . . . ባረከው . . . ሰበረው ይህንን በ MAT 14:19 ላይ በተረጎምከው መሠረት ተርጉመው፡፡
ወሰደ ይህንን በ MAT 14:19. ላይ በተረጎምከው መሠረት ተርጉመው፡፡ ሰጣቸው "ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው" ስለቃል ኪዳኑ የሚፈሰው ደሜ ነው "ኪዳኑ የጸና መሆኑን የሚያሳይ ደም ነው”ወይም “ኪዳን እንዲቻል ደረገ ደም ነው" የሚፈሰው "በሞቱ ጊዜ የሚፈሰው” ወይም “በቅርቡ ከአካሌ የሚፈሰው” ወይም ስሞት ከአካሌ የሚፈስ ደም ነው” የወይንን ፍሬ "ወይን" በአባቴ መንግስት ውስጥ አዲሱን ከእናንተ ጋር እስከሚጠጣት ጊዜ ድረስ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው፣ ደሙ በእርሱ ለሚያምኑት ከአባት ዘንድ የዘላለም የኃጢአት ይቅርታን ያስገኘው ኢየሱስ አባቱ በመስቀል ላይ የቀረበውን መስዋእት መርካቱን የሚያከብርበት ነው፡፡ “አባት” እና “ልጅ” የሚለው ቃል በሥላሴ አካላት መካከል መቀራረብ እና ቤተሰባዊ ህብረት ያለ መሆኑን የሚያሳይ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል በመሆኑን እንዳለ በቁሙ መቀመጥ ይኖርበታል፡፡
መዝሙር ለእግዚአብሔር የሚቀርብ የሚስጋና መዝሙር ይወድቃሉ "ትተውኝ ይሄዳሉ" የመንጋውም በጎች ይበተናሉ ለተርጓሚዎች ምክር፡ 1) "ሁሉን የበጎች መንጋዎች ይበተናሉ " (UDB) ወይም 2) "የበጎች መንጋዎቹ በሁሉም አቅጣጫ ይበተናሉ" የበጎች መንጋ ደቀ መዛሙርቱ ከተነሳሁ በኋላ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "እግዚአብሔር ካስነሳኝ በኋላ"
ይበተናሉ ይህንን በ MAT 26:31 ላይ በተረጎምከው መሠረት ትረጉም ዶሮ ሳይጮኽ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "ፀሐይ ከመውጣቱ በፊት" ዶሮ ከመጮኹ rooster ልነጋጋ ሲል ዶሮ የሚያሰማቸው ከፍተኛ ጩኸት የዶሮ ጩኸት ዶሮ የሚያሰማው ጩኸት
ኃዘን በጣም አዘነ
በፊቱ ወድቆ ለመጸለይ ሆን ብሎ ፊቱን በመሬት ላይ መድፋት አባቴ ይህ በእግዚአብሔር እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያሳይ የእግዚአብሔር የማዕረግ ስም ነው ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ ከ “ይህ ጽዋ” የሚለው ቃል ኢየሱስ ሊያልፈበት ያለውን መከራ የሚያመለክት ነው፡፡ ይሁን እንጂ የእኔ ፈቃድ ሳይሆን የአንተ ፈቃድ ይሁን ይህ በሙሉ ዐዓረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እኔ የሚፈልገው አታደርግ ነገር ግን አንተ የሚትፈልገውን አድርግ”"
ማቴዎስ 26፡ 42-44
ሄደ "ኢየሱስ ሄደ" እኔ ካልጠጣሁት "የዚህ የመከራ ጽዋ የማልጠጣ ከሆነ" አባቴ ይህ በእግዚአብሔር እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያሳይ የእግዚአብሔር የማዕረግ ስም ነው ዓይኖቻቸው በእንቅልፍ ከብደው ነበር "እንቅልፍ ይዞዋቸው ነበር"
ሰዓቲቱ ቀርባለች "ጊዜው ቀርቧል" በኃጡአተኞች እጅ "ኃጢአተኞች" ተመልከቱ "አሁን ለምናገረው ነገር ትኩረት ስጡ"
በመናገር ላይ ሳለ "ኢየሱስ እየተናገረ ሳለ" እንዲህ አለ “የሚስመው እርሱ ነውና ያዙት” "እርሱ የሚስመው እርሱ ነውና ያዙት” የሚስመው "አሁን የሚስመው" ወይም "እኔ የሚስመው ሰው" (UDB) መሳም ለአንድ ታላቅ መምህር የሚቀርብ አክብሮት
ወደ ኢየሱስ መጥቶ "ይሁዳ ወደ ኢየሱስ መጥቶ" ሳመው "በመሳም ሰላም አለው" ኢየሱስን ያዙት ኢየሱስን ልጎዱት ያዙት ያዙት እስረኛ አደረጉት
እነሆ ጸሐፊው አዲስ ሰውን በታሪኩ ውስጥ አካቷል፡፡ በቋንቋችሁ ይህንን ለማደረግ የሚያስችል መንገድ ሊኖር ይችላል፡፡ አባቴን እንድለምን እርሱም አሁን ከአሥራ ሁለት ጭፍሮች የሚበዙ መላእክት እንዲሰድልኝ የማይቻል ይመስልሃልን? ለተርጓሚዎች ምክር፡ "አባቴን መጥራት እንደሚችል፣ እርሱ ደግሞ ከዐሥራ ሁለት ጭፍሮች በላይ መላእክትን ልልክልኝ እንደሚችል ማወቅ ነበረባችሁ፡፡” አባቴ ይህ በእግዚአብሔር እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያሳይ የእግዚአብሔር የማዕረግ ስም ነው ከዐሥራ ሁለት ጭፍሮች በላይ መላእክት የመላእክቱ ትክክለኛ ቁጥት ይህን ያኸል አስፈላጊ አይደለም ጭፍሮች የሮማዊያን ሠራዊት አከፋፈል ሆኒ አንዱ ስድት ሺህ ወታደሮችን ይይዛል
ወንበዴን እንደምትይዙ ሰይፍና ጐመድ ይዛችሁ ልትይዙኝ ወጣችሁን? ለተርጓማች ምክር፡ “እኔ ወንበዴ እንዳልሆንኩ ታውቃላችሁ ስለዚህ እኔት ለመያዝ ሰይፍ እና ጎመድ ይዛችሁ መምጣታችሁ ስህተት ነው፡፡” ጎመድ ሰዎችን ለመምታት የሚሆን ጠንካራ ደረቅ ዱላ ተውት በቋንቋችሁ ከእርሱ ጋር መሆን ስገባቸው ትተውት መሄዳቸውን ለማመልከት የሚሆን ቃል ካለ ይህንን ቃል ተጠቀሙ፡፡
ሁለት ሰዎች ወደፊት መጥተው "ሁለት ሰዎች ቀርበው” (UDB) ወይም "ሁለት ምስክሮች ቀርበው" “እነዚህ ሰዎች እንዲህ አሉ፣ እኔ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ አፍርሼ በሦስት ቀን ውስጥ እንደገና እገነባለሁ” ለተርጓሚዎች ምክር: "የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ አፍርሶ በሦስት ቀናት ውስጥ መልሶ እንደሚገነባ ስናገር ሰምተናል ብለው መሰከሩበት” ይህ ሰው እንዲህ አለ "ይህ ሰው ኢየሱስ እንዲህ አለ"
በእርሱ ላይ መሰከሩበት "ምስክሮቹ በኢየሱስ ላይ መሰከሩ" የእግዚብሔር ልጅ ይህ በክርስቶስ እና በእግዚአብሔር መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያሳይ በጣም አስፈላጊ የሆነ ስም ነው፡፡ አንተ ራስህ አልህ ኢየሱስ ራሱ እርሱ “ክርስቶስ፣ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ” አረጋግጧል፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “አንተው ራስህ እንዳልከው ነኝ” ወይም “አንተ ራስህ አሁን አመንክ” ነገር ግን እላችኋለሁ፥ እንግዲህ ወዲህ ኢየሱስ ለሊቀ ካህኑ እና በዚያ ላሉት ሰዎች በመመናር ላይ ነው፡፡ እንግዲህ ወዲህ የሰው ልጅ በኃይል ቀኝ ሲቀመጥ አማራጭ ትርጉሞች ›፡ 1) የሰው ልጅን ወደፊት የሆነ ጊዜ ያዩታል ወይም 2) “አሁን” የሚለው ቃ የሚያመለክተው የሰው ልጅ የሞተበትን፣ ከሞቱ የተነሳበትን እና ወደ ሰማይ ያረገዘበት ጊዜ ነው፡፡ በኃይል ቀኝ "ሁሉን ቻይ በሆነው በእግዚአብሔር ቀኝ” በሰማይም ደመና ሲመጣ "በሰማይ ዳመና ሆኖ ወደ መሬት ሲመጣ"
ሊቀ ካህኑ ልብሱን ቀደደ ልብስ መቅደድ የሚያሳዝን ነገር በመሆኑ የተከሰተ ንዴት ምልክት ማሳያ ነው፡፡ እንዲህ ሲሉ መለሱለት "የአይሁድ መሪዎች እንዲህ ሲሉ መለሱለት"
ከዚያ እነርሱ አማራጭ ትርጉሞች፡ “ከዚያም ከእነርሱ መካከል አንዳንዶቹ” ወይም “ከዚያ ወታደሮቹ” ፊቱ ላይ ተፉበት ይህ ስድብ ነው ትንቢት ንገረን በዚህ ሥፍራ “ትንቢት ንገረን” ማለት “በእግዚአብሔር ኃይል ንገረን” ማለታቸው እንጂ “ወደፊት የሚሆነውን ነገር ንገረን ማለታቸው አይደልም”
እናንተ ስለምትሉት ነገር የማውቀው ነገር የለኝም ጴጥሮስ ይህች ገረድ እያለች ያለው ነገር ገብቶታል፡፡ ከኢየሱስ ጋር የነበረ መሆኑን ለመካድ ይህንን ቃል ተጠቀሟል፡፡
እንዲህ ሲል "ጴጥሮስ እንዲህ ባለ ጊዜ" መግቢያ በግቢው አጥር መግቢያ በር
ከእነርሱ አንዱ "ከኢየሱስ ጋር ከነበሩት አንዱ ነው" የንግግር ቅላጼህ ያስታውቃል "ከገሊላ እንደሆንክ ከንግግርህ ቅላጼ ማወቅ እንችላለን ምክንያቱም የሚትናገረው እንደ ገሊላ ሰዎች ነው፡፡" እምላለሁ “ይህን ሰው ፈጽሞ አላውቀውም” ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ይህን ሰው አላውቀውም”
ፋሲካ በሁለት ቀናት ውስጥ እየመጣ እንደሆነ ኢየሱስ ተናገረ። [26:2]
ኢየሱስን በስውር ለመያዝ አንአ ለመግደል እያሴሩ ነበር። [26:4]
በበዓሉ ሰሞን ኢየሱስን ከገደሉ፣ ሕዝቡ እንዳያምጽ ፈርተው ነበር። [26:5]
ደቀመዛሙርቱ ተቆጡ ሽቱውም ተሽጦ ገንዘቡ ለድሆች ያልተሰጠው ለምን እንደሆነ ማወቅ ፈለጉ። [26:6]
ደቀመዛሙርቱ ተቆጡ ሽቱውም ተሽጦ ገንዘቡ ለድሆች ያልተሰጠው ለምን እንደሆነ ማወቅ ፈለጉ። [26:7]
ደቀመዛሙርቱ ተቆጡ ሽቱውም ተሽጦ ገንዘቡ ለድሆች ያልተሰጠው ለምን እንደሆነ ማወቅ ፈለጉ። [26:8]
ደቀመዛሙርቱ ተቆጡ ሽቱውም ተሽጦ ገንዘቡ ለድሆች ያልተሰጠው ለምን እንደሆነ ማወቅ ፈለጉ። [26:9]
ሴቲቱ ሽቱውን በእርሱ ላይ ያፈሰሰችው ለቀብሩ እንደሆነ ኢየሱስ ተናገረ። [26:12]
ይሁዳ ኢየሱስን በሊቀ ካህናቱ እጅ አሳልፎ ለመስጠት ሠላሳ የብር ሳንቲሞች ተከፍሎት ነበር። [26:14]
ይሁዳ ኢየሱስን በሊቀ ካህናቱ እጅ አሳልፎ ለመስጠት ሠላሳ የብር ሳንቲሞች ተከፍሎት ነበር። [26:15]
ከደቀመዛሙርቱ አንደኛው አሳልፎ እንደሚሰጠው ኢየሱስ ተናገረ። [26:21]
እርሱን አሳልፎ የሰጠው ባይወለድ ይሻለው እንደነበረ ኢየሱስ ተናገረ። [26:24]
ኢየሱስ “አንተው ራስህ ነህ” ሲል መለሰለት። [26:25]
ኢየሱስ “ውሰዱ፣ ብሉ፣ ይህ ስጋዬ ነው” አላቸው። [26:26]
ጸዋው ስለ ኃጢአት ይቅርታ ለብዙዎች የሚፈስሰው የአዲስ ኪዳን ደም እንደሚሆን ኢየሱስ ተናገረ። [26:28]
ሁሉም ከእርሱ የተነሣ በዚያች ሌሊት እንደሚሰናከሉ ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ ነገራቸው። [26:30]
ሁሉም ከእርሱ የተነሣ በዚያች ሌሊት እንደሚሰናከሉ ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ ነገራቸው። [26:31]
ጴጥሮስ ኢየሱስን በዚያች ሌሊት ዶሮ ከመጮኹ በፊት ሦስት ጊዜ እንደሚክደው ኢየሱስ ተናገረ። [26:33]
ጴጥሮስ ኢየሱስን በዚያች ሌሊት ዶሮ ከመጮኹ በፊት ሦስት ጊዜ እንደሚክደው ኢየሱስ ተናገረ። [26:34]
በዚያ እንዲቆዩ እና ከእርሱ ጋር ነቅተው እንዲጠብቁ ኢየሱስ ጠየቃቸው። [26:37]
በዚያ እንዲቆዩ እና ከእርሱ ጋር ነቅተው እንዲጠብቁ ኢየሱስ ጠየቃቸው። [26:38]
ኢየሱስ የጠየቀው የሚቻል ከሆነ፣ ይህ ጽዋ ከእርሱ እንዲያልፍ ነበር። [26:39]
ኢየሱስ ከመጸለይ ሲመለስ ደቀመዛሙርት ተኝተው ነበር። [26:40]
የኢየሱስ የራሱ ፈቃድ ምንም ቢሆን ምን፣ የአብ ፈቃድ እንዲደረግ ኢየሱስ ጸለየ። [26:42]
ለመሄድ እና ለመጸለይ ኢየሱስ ሦስት ጊዜ ደቀመዛሙርቱን ትቷቸው ሄደ። [26:42]
ለመሄድ እና ለመጸለይ ኢየሱስ ሦስት ጊዜ ደቀመዛሙርቱን ትቷቸው ሄደ። [26:43]
ለመሄድ እና ለመጸለይ ኢየሱስ ሦስት ጊዜ ደቀመዛሙርቱን ትቷቸው ሄደ። [26:44]
የሚይዙት ኢየሱስ መሆኑን በምልክት እንዲያውቊ ይሁዳ ኢየሱስን ሳመው። [26:47]
የሚይዙት ኢየሱስ መሆኑን በምልክት እንዲያውቊ ይሁዳ ኢየሱስን ሳመው። [26:48]
ከኢየሱስ ደቀመዛሙርት አንደኛው ሰይፉን መዝዞ የሊቀ ካህናቱን ባርያ ጆሮ ቆረጠ። [26:51]
ዐሥራ ሁለት ጭፍራ ሙሉ መላእክትን ሊልክለት የሚችለውን አብን መጥራት እንደሚችል ኢየሱስ ተናገረ። [26:53]
በእነዚህ ክስተቶች የቅዱሳት መጻሕፍት ትንቢት እየተፈጸመ እንዳለ ኢየሱስ ተናገረ። [26:54]
ደቀመዛሙርቱ ሁሉ ትተውት ሸሹ። [26:56]
ኢየሱስን ለመግደል በኢየሱስ ላይ በሃሰት የሚመሰክሩትን ይፈልጉ ነበር። [26:59]
ሊቀ ካህናቱ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆን አለመሆኑን እንዲነግራቸው ኢየሱስን አዘዘው። [26:63]
ኢየሱስ “አንተ ራስህ ብለሃል” አለ። [26:64]
የሰው ልጅ በልዑል ኃይል ቀኝ ሲቀመጥ፣ እንዲሁም በሰማይ ደመና ሲመጣ ሊቀ ካህናቱ እንደሚያይ ኢየሱስ ተናገረ። [26:64]
ኢየሱስ እንደተሳደበ አድርጎ ሊቀ ካህናቱ ከሰሰው። [26:65]
በኢየሱስ ፊት ላይ ተፉበት፣ መቱት፣ በጥፊ መቱት። [26:67]
ጴጥሮስ ኢየሱስን እንደማያውቅ ሦስት ጊዜ መለሰ። [26:73]
ጴጥሮስ ኢየሱስን እንደማያውቅ ሦስት ጊዜ መለሰ። [26:74]
ጴጥሮስ ለሦስተኛ ጊዜ ምላሽ እንደሰጠ፣ ዶሮ ጮኸ። [26:74]
ኢየሱስን እንደማያውቀው ጴጥሮስ መለሰ። [26:75]
ዶሮ ሳይጮኽ በፊት ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ እንዳለው ጴጥሮስ አስታወሰ። [26:75]
ከዚያም ይሁዳ ይንን ባደረገ ጊዜ በቋንቋችሁ የተጀመረን አንድ ታሪክ አቋርጦ ሌላ ታሪክ መጀመሩን የሚያመለክት ቃል ካለ ይህንን ቃል በዚህ ሥፍራ ላይ ተጠቀም፡፡ ሠላሳ ብር የካህናት አለቆች ይሁዳ ኢየሱስን አሳልፎ ይሰጣቸው ዘንድ ለይዳ የሰጤት ብር ነው (MAT 26:15) ንጹሕ ደም "መሞት የማይገባው ሰው"
ይህንን ማድረግ ሕጋዊ አይደለም "ሕጋችን ይህንን እዲናደረግ አይፈቅድልንም" እንድናስቀመጥ "ይህንን ብር እንድናስቀመጥ" የደም ዋጋ አንድ ሰው እንዲሞት የሚከፈል ገንዘብ የሸክላ መሬት ይህ መሬት በኢየሩሳሌም ከተማ ውስጥ ምጻተኛ የሆነ ሰው ቢሞት የሚቀበርበት ቦታ ነው፡፡ እስከዛሬ ድረስ ጸሐፊው መጽሐፉን እስከ ጻፈበት ጊዜ ድረስ
ነብዩ ኤርሚያስ እንዲህ በማለት የተናገረው የትንቢት ቃል ተፈተመ "ነብዩ ኤርሚያስ ይህንን የትንቢት ቃል ተናገረ፤ እንደተናገውም ሆነ፡፡ ነብዩ ያለው እንዲህ ነው” የእስራኤል ሕዝቦች የእስራኤል የሃይማኖት መሪዎች እንደገመተኝ ነብዩ ኤርሚያስ እንደገመተው
አሁን በቋንቋችሁ ውስጥ የተቋረጠው ታሪክ መቀጠሉን የሚያሳይ ቃል ካለ ይህንን ቃል መጠቀሙ መልካም ይሆናል፡፡ ሀገረ ገዥው ጵላጦስ (MAT 27:1) አንተ አልክ "አንተ ራሰህ ተቀበልከው" ይሁን እንጂ በካህናት ለቆች እና ሽማግሌዎች ክስ በቀረበበት ጊዜ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ነገር ግን የካህናት አለቆች እና ሽምግሌዎች በከሰሰቱት ጊዜ” በእንተ ላይ የሚያቀርቡትን ክስት አትሰማምን? "መጥፎ ነገር አድርጓል ብለው ለሚከሱህ ሰዎች ምንም ምላሽ አለመስጠትህ አስገርሞኛል!” አንዲት ቃል፣ በዚህም ገዥው በጣም ተገረመ፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "አንዲት ቃል፤ ይህ ነገር ገዥውን እጅግ አስገረመው፡፡"
አሁን ይህ ቃል በታሪኩ ፍሰት ውስጥ የእረፈት ጊዜ መኖሩ የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህም ጸሐፊው በ [MAT 27:17] ክብረ በዓል ፋስካ በዓል የሚከበርበት ጊዜ (MAT 26:2) በሕዝቡ የተመረጠው እስረኛ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ሕዝቡ የመረጠው እስረኛ” ነውጠኛ መጥፎ ነገር በማድረግ በጣም የሚታወቅ ሰው
አሳልፈው ሰጡት ጵላጦስ ይፈርድበት ዘንድ "ኢየሱስን ወደ እርሱ አመጡ” በዚያም ተቀምጦ ሳለ "ጵላጦስ በዚያ ተቀምጦ ሳለ" በፍርድ ወንበር ላይ ተቀምጦ ሳለ ፍርድን እንደሚሰጥ ሰው በስራው ላይ ሳለ መልዕክት ላከ "መልዕክት ላከ"
ጠየቃቸው "ሕዝቡን ጠየቀ"
ምን አድርጎ ነው "ኢየሱስ ምን አደረገ" በታላቅ ድምፅ ጮኹ "ሕዝቡም በታላቅ ድምፅ ጮኹ" ደሙ "ሞቱ"
ደሙ በእኛ እና በልጆቻችን ላይ ይሁን፡፡ "አዎ! እኛ እና የእኛ ልጆች በደስታ እርሱን እንዲሞት የማድረግ ኃላፊነቱን እንወስዳን!"
የገዥው ግቢ አማራጭ ትርጉሞች: 1) ወታደሮቹ የሚኖሩበት ሥፍራ ወይም 2) የገዥዎቹ መኖሪያ ልብሱን ገፈፉት "ልብሱን ገፈፉት" (UDB) ቀይ ልብስ ደማቅ ቀይ ልብስ ተዘባበቱበት "እናከብርሃን" ወይም "ረጅም እድሜ ኑር"
እነርሱ . . . እነርሱ . . . እነርሱ የጵላጦስ ወታደሮች እርሱ . . . እርሱ . . . እርሱ . . . እርሱ . . . እርሱ ኢየሱስ
ከዚያ በወጡ ጊዜ "ከእየሩሳሌም እየወጡ ሳለ" የእርሱን መስቀል ይሸከም ዘንድ አስገደዱት "ወታደሮቹ የኢየሱስን መስቀል ይሸከም ዘንድ አስገደዱት" ጎልጎታ ወደ ተባለ ሥፍራ "ሰዎች ጎልጎታ ብለው ወደሚጠሩት ሥፍራ" ሐሞት ሰውነታችን ምግብን ለመፍጨት የሚጠቀምበት ብጫ ፈሳሽ ነገር
ልብስ ኢየሱስ ይለብሰው የነበረውን ልብስ
ማቴዎስ 27፡ 38-40
ከእርሱ ጋር ሁለት ወንበዴዎች ተሰቅለው ነበር ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ወታደሮቹ ሁለት ወንበዴዎችን ከኢየሱስ ጋር ሰቀሉ”፡፡ ራሳቸውን እየነቀነቁ ይህንን ያደረጉት በኢየሱስ ላይ ለመሳለቅ ነው፡፡ አንተ በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ከመስቀል ውረድ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ በመሆኑ ስለማያምኑ ይህን እንዲያረጋግጥላቸው ጠየቁት፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “አንተ በእርግጥ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ከመስቀል በመውረድ ይህንን አረጋግጥልን አሉት” የእግዚብሔር ልጅ ይህ በክርስቶስ እና በእግዚአብሔር ልጅ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያስረዳ በጣም አስፈላጊ የሆነ ስም ነው፡፡
ሌሎቹን አዳነ ነገር ግን ራሱን ማዳን አልቻለም አማራጭ ትርጓሜዎች፡ 1) የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስ ሌሎችን እንዳዳነ አያምኑም ወይም ራሱንም ማዳን እንደሚችል አያምኑም ወይም 2) ሌሎችን እንዳዳነ ያምናሉ ነገር ግን ራሱን ማዳን ስላልቻለ ሳቁበት፡፡ እርሱ የእስራኤል ንጉሥ ነው መሪዎቹ የእስራኤል ንጉሥ እንደሆነ አያምኑም ነበር
የእግዚብሔር ልጅ ይህ በክርስቶስ እና በእግዚአብሔር ልጅ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያስረዳ በጣም አስፈላጊ የሆነ ስም ነው፡፡ ከእርሱ ጋር የተሰቀሉት ወንበዴዎችም "ወታደሮቹ ከኢየሱስ ጋር የሰቀሏቸው ወንበዴዎችም
ጮኸ "ተጣራ" ወይም "በታላቅ ድምፅ ጮኸ" ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ? ተርጓሚዎች ብዙ ጊዜ እነዚህ ቃላት እንዳሉ በዕብራይስጥ ቋንቋዎች ይተዋቸዋል፡፡
ከእነርሱ መካከል አንዱ አማራጭ ትርጉሞች፡ 1) ከወታደሮቹ መካከል አንዱ ወይም 2) ቆመው ከሚመለከቱት መካከል አንዱ እስፖንጅ ከባሕር እንስሳት መካከል የሚሰበሰብ ውሃ ለመያዥያነት የሚገለግል፡፡ ለእርሱ ሰጠው "ለኢየሱስ ሰጠው
እነሆ ይህ ቃል ሰዎች ከዚህ በኋላ ለሚነገረው ነገር አጽኖት እንዲሰጡ የሚጨመር ቃል ነው፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ተመልከቱ” ወይም “አድምጡ” ወይም “አሁን ለምነግራችሁ ነገር ትኩረት ስጡ”:: መቃብሮችም ተከፈቱ፥ ተኝተው ከነበሩትም ከቅዱሳን ብዙ ሥጋዎች ተነሡ፤ "እግዚብሔር መቃብሮችን ከፍቶ ከሞቱት መካል ብዙ ቅዱሳንን ከሞት አስነሣ ተኝተው የነበሩ "የሞቱ" መቃብሮችም ተከፍተው . . . ለብዙዎች ታዩ። ሁኔታዎቹ የተፈጸሙበት የጊዜ ቅደም ተከተል ግልጽ አይደለም፡፡ ሊሆነ የሚችሉት የጊዜ ቅደም ተከተሎች፡ ኢየሱስ ሲሞት በተነሳው ከተነሳው የምድር መንቀጥቀጥ በኋላ መቃብሮች ተከፈቱ 1) ቅዱሳን ተነሱ፣ ኢየሱስ ከሞት ተነሣ እና ቅዱሳን ወደ ከተማው ገቡ እና ለብዙዎች ታዩ ወይም 2) ኢየሱስ ከሞት ተነሣ እና ቅዱሳን ከሞት ተነሡ፣ ወደ ከተማ ገቡ እና ለብዙዎች ታዩ፡፡
የእግዚብሔር ልጅ ይህ በክርስቶስ እና በእግዚአብሔር ልጅ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያስረዳ በጣም አስፈላጊ የሆነ ስም ነው፡፡
ከዚያም ጵላጦስ ይሰጠው ዘንድ አዘዘ "ከዚያም ጵላጦስ ወታደሮቹን የኢየሱስ በድን ለዮሴፍ ይሰጠው ዘንድ አዘዘ፡፡”
ለስላሳ ጨርቅ ብዙ ብር የሚያወጣ ጨርቅ ከመቃብሩ ተቃራኒ "ከመቃብሩ ማዶ"
ዝግጅት ለፋስካ በዓል የሚዘጋጁበት ጊዜ ነበር ይህ አሳች በሕይወት እያለ "አሳቹ ኢየሱስ በሕይወት እያለ"
ጠባቂ 4 እስከ 16 የሮማዊያን ወታደሮች ድንጋዩን በማሕተም አትመው አማራጭ ትርጓሜዎች: 1) በድንጋዩ ዙሪያ ገመድ በማድረግ ወደ መቃብሩ ሌላኛው መግቢያ ጋር በማያያዝ አሠሩት ወይም 2) በድንጋዩ ና በግድግዳው መካከል ማሕተም አኖሩ፡፡ ጠባቂዎች በዚያ አኖሩ "ወታደሮቹ ሰዎች መቃብሩን መንካት የማይችሉበት ቦታ እንዲቆሙ ትዕዛዝ ሰጡ፡፡"
ሲነጋ ወደ ገዢው ወደ ጲላጦስ ወሰዱት። [27:2]
ንፁህ ደም አሳልፎ በመስጠቱ ይሁዳ ተጸጸተ፣ ብሩን መልሶ ወጣና ራሱን ሰቅሎ ሞተ። [27:3]
ንፁህ ደም አሳልፎ በመስጠቱ ይሁዳ ተጸጸተ፣ ብሩን መልሶ ወጣና ራሱን ሰቅሎ ሞተ። [27:4]
ንፁህ ደም አሳልፎ በመስጠቱ ይሁዳ ተጸጸተ፣ ብሩን መልሶ ወጣና ራሱን ሰቅሎ ሞተ። [27:5]
የሸክላ ሠሪውን መሬት ለእንግዶች መቅበሪያ ገዙበት። [27:6]
የሸክላ ሠሪውን መሬት ለእንግዶች መቅበሪያ ገዙበት። [27:7]
እነዚህ ክስተቶች የኤርምያስን ትንቢት ይፈጽማሉ። [27:9]
እነዚህ ክስተቶች የኤርምያስን ትንቢት ይፈጽማሉ። [27:10]
ጲላጦስ ኢየሱስን የጠየቀው እርሱ የአይሁድ ንጉሥ እንደሆነ ሲሆን፣ ኢየሱስ የመለሰው “አንተ እንዳልከው ነው” የሚል ነበር። [27:11]
ኢየሱስ አንዲትም ቃል እንኳን አልመለሰለትም። [27:12]
ኢየሱስ አንዲትም ቃል እንኳን አልመለሰለትም። [27:13]
ኢየሱስ አንዲትም ቃል እንኳን አልመለሰለትም። [27:14]
ጲላጦስ እንደ ፋሲካ በዓል ልማድ ኢየሱስን ለመልቀቅ ፈልጎ ነበር። [27:15]
ጲላጦስ እንደ ፋሲካ በዓል ልማድ ኢየሱስን ለመልቀቅ ፈልጎ ነበር። [27:16]
በዚያ ንጹህ ሰው ላይ ምንም እንዳያደርግበት ለጲላጦስ ነገረችው። [27:19]
ሊቀ ካህናቱ እና ሽማግሌዎቹ ከኢየሱስ ይልቅ በርባን እንዲፈታላቸው ሕዝቡን አሳምነው ነበር። [27:20]
ኢየሱስ እንዲሰቀል እንደሚፈልጉ ሕዝቡ ጮኸ። [27:22]
ጲላጦስ እጆቹን ታጠበ፣ ከዚህ ንፁህ ሰው ደም ንፁህ እንደሆነ ተናገረና ኢየሱስን ለሕዝቡ አሳልፎ ሰጠ። [27:24]
ሕዝቡ “ደሙ በእኛ እና በልጆቻችን ላይ ይሁን” አሉ። [27:25]
ወታደሮቹ ቀይ ልብስ አለበሱትና በራሱም ላይ የእሾህ አክሊል አደረጉበት። [27:27]
ወታደሮቹ ቀይ ልብስ አለበሱትና በራሱም ላይ የእሾህ አክሊል አደረጉበት። [27:28]
ወታደሮቹ ቀይ ልብስ አለበሱትና በራሱም ላይ የእሾህ አክሊል አደረጉበት። [27:29]
ስምዖን የኢየሱስን መስቀል እንዲሸከም ተገደደ። [27:32]
“የራስ ቅል ስፍራ” ማለት ወደ ሆነው ጎልጎታ ሄዱ። [27:33]
ወታደሮቹ የኢየሱስን ልብስ ለመከፋፈል እጣ ተጣጣሉ፣ ከዚያም ተቀምጠው ይጠብቊት ነበር። [27:35]
ወታደሮቹ የኢየሱስን ልብስ ለመከፋፈል እጣ ተጣጣሉ፣ ከዚያም ተቀምጠው ይጠብቊት ነበር። [27:36]
“ይህ የአይሁድ ንጉሥ ነው” የሚል ጻፉ። [27:37]
ሁለት ወንበዴዎች ከኢየሱስ ጋር ተሰቅለው የነበረ ሲሆን፣ አንደኛው በቀኙ፣ ሌላኛው በግራው ነበሩ። [27:38]
ሁሉም ራሱን እንዲያድን እና ከመስቀል እንዲወርድ ሞገቱት። [27:42]
ከስድስት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ ጨለማ በመላው ምድር ላይ መጥቶ ነበር። [27:45]
ኢየሱስ “አምላኬ፣ አምላኬ፣ ስለምን ተውኸኝ?” በማለት ጮኸ [27:46]
ኢየሱስ መንፈሱን ተወ። [27:50]
ኢየሱስ ከሞተ በኋላ የቤተመቅደሱ መጋረጃ ከጫፍ እስከ ታች ድረስ ለሁለት ተቀደደ። [27:51]
ኢየሱስ ከሞተ በኋላ አንቀላፍተው የነበሩት በርካታ ቅዱሳን ተነሥተው ለብዙዎች ታዩ። [27:52]
ኢየሱስ ከሞተ በኋላ አንቀላፍተው የነበሩት በርካታ ቅዱሳን ተነሥተው ለብዙዎች ታዩ። [27:53]
መቶ አለቃው “በእውነት ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ነበር” አለ። [27:54]
ባለጠጋ የነበረው የኢሱስ ደቀ መዝሙር ዮሴፍ፣ ስጋውን ከጲላጦስ ጠይቆ በበፍታ ጠቀለለውና በአዲስ መቃብር ውስጥ አኖረው። [27:57]
ባለጠጋ የነበረው የኢሱስ ደቀ መዝሙር ዮሴፍ፣ ስጋውን ከጲላጦስ ጠይቆ በበፍታ ጠቀለለውና በአዲስ መቃብር ውስጥ አኖረው። [27:58]
የኢየሱስ ስጋ አርፎበት በነበረበት ቦታ በተቃራኒ በበራፉ ትልቅ ድንጋይ ተቀምጦ ነበር። [27:60]
ሊቀ ካህናቱ እና ፈሪሳውያን የኢየሱስ መቃብር በደንብ እየተጠበቀ መሆኑን፣ ከዚያም የተነሣ ማንም ሰውነቱን እንደማይሰርቀው እርግጠኛ መሆን ፈለጉ። [27:62]
ሊቀ ካህናቱ እና ፈሪሳውያን የኢየሱስ መቃብር በደንብ እየተጠበቀ መሆኑን፣ ከዚያም የተነሣ ማንም ሰውነቱን እንደማይሰርቀው እርግጠኛ መሆን ፈለጉ። [27:63]
ሊቀ ካህናቱ እና ፈሪሳውያን የኢየሱስ መቃብር በደንብ እየተጠበቀ መሆኑን፣ ከዚያም የተነሣ ማንም ሰውነቱን እንደማይሰርቀው እርግጠኛ መሆን ፈለጉ። [27:64]
ጲላጦስ ድንጋዩን እንዲያትሙ እና ጠባቂዎችን በመቃብሩ ላይ እንዲያቆሙ ፈቀደላቸው። [27:65]
ጲላጦስ ድንጋዩን እንዲያትሙ እና ጠባቂዎችን በመቃብሩ ላይ እንዲያቆሙ ፈቀደላቸው። [27:66]
በሰንበትም በሳምንቱ መጀመሪያው ቀን መጨረሻ "ሰንበት ካለቀ በኋላ የእሁድ ማለዳ ጸሐይ መውጣት ሲጀምር" ሌላኛዋ ማሪያም "ማሪያም ተብላ የሚትጠራዋ ሌላኛዋ ሴት” የያዕቆብ እና የዮሴፍ እናት የሆነችው ማሪያም (MAT 27:56) እነሆ ይህ ቃል ሰዎች ከዚህ በኋላ ለሚነገረው ነገር አጽኖት እንዲሰጡ የሚጨመር ቃል ነው፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ተመልከቱ” ወይም “አድምጡ” ወይም “አሁን ለምነግራችሁ ነገር ትኩረት ስጡ”:: የጌታ መላእክት በመውረዳቸው . . . እና ድንጋዩን በማንከባለላቸው ምክንያት ታላቅ የመሬት መናወጥ ሆነ አማራጭ ትርጉሞች: 1) የመሬት መናወጡ የተከሰተበት ምክንያት መላእክት በመውረዳቸው እና ድንጋዩን በማንከባለላቸው ነው (ULB) ወይም 2) እነዚህ ሁሉም ነገሮች የሆኑት በተመሳሳይ ጊዜ ነው (UDB). የመሬት መናወጥ (መንቀጥቀጥ) ድንገተኛ እና አስደንጋጭ የመሬት መንቀጥቀጥ
የእርሱ መልክ "የመልአክ መልክ" መብረቅ ይመስል ነበር "እንደ መብረቅ ያበራ ነበር" እንደ በረዶ ነጭ ነበር "በከፍተኛ ሁኔታ ያንጸባርቅ ነበር" እንደ ሞተ ሰው "መንቀሳቀስ ያቃተው"
ሴቶቹ "መግደላዊት ማሪያም እና ማሪያም ተብላ የተጠራው ሌላኛዋ ሴት" የተሰቀለው "ሕዝቡ እና ወታደሮቹ የሰቀሉት" ነገር ግን ተነሣ " ገር ግን እግዚአብሔር አስነሣው"
ሴቶቹ "መግደላዊት ማሪያም እና ማሪያም ተብላ የሚትጠራው ሌላኛይቱ ሴት" እነሆ ጸሐፊው አንድ አስደናቂ ነገር ልሆን እንዳለ ለአንባቢዮቹ ያስታውቃቸዋል፡፡ በቋንቋችሁ ይህን ዓይነቱን ነገር ማድረግ የሚችትችሉበት መንገድ ሊኖር ይችላል፡፡ እግሩን ያዙት "በጉልበታቸው ተንበርክከው እግሩን ያዙት" ወንድሞቼ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት
ሴቶቹ መግደላዊት ማሪያም እና ሌላኛዋ ማሪያም ከእነርሱ ጋር ስለሁኔታው ተወያዩ "ስለ አቀዱት እቅድም በጋራ ወሰኑ፡፡” ካህናቱ እና ሽማግሌዎቹ ለወታደሮቹ ብር ለመስጠት ወሰኑ፡፡ ለሌሎች እንዲህ ብላችሁ ንገሩ “በተኛንበት ሰዓት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት መጥተው . . .” "ለጠየቃችሁ ሁሉ እንዲህ ብላችሁ ንገሩ፣ ተኝተን ሳለ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት መጥተው"
ገዥው ጵላጦስ (MAT 27:2) እንደተነገራቸው እንደዚያው አደረጉ "ካህናቱ እንዲያደርጉ እንደ ነገሯቸው እንደዚያው አደረጉ" ዛሬ ማቴዎስ መጽሐፉን በጻፈበት ወቅት
በስሜ "በእኔ ስልጣን" አብ . . . ወልድ ይህ በእግዚአብሔር አብ እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያብራራ ጠቃሚ ስም ነው፡፡
በሣምንቱ የመጀመሪያ ቀን ሲነጋ ወደ ኢየሱስ መቃብር ሄዱ። [28:1]
የጌታ መልአክ ወረደና ድንጋዩን አንከባለለው። [28:2]
ጠባቂዎቹ በፍርሃት ተንቀጠቀጡና መልአኩን ባዩት ጊዜ እንደ ሞተ ሰው ሆኑ። [28:4]
ኢየሱስ እንደተነሣ እና ወደ ገሊላ ቀድሟቸው እንደሚሄድ መልአኩ ተናገረ። [28:5]
ኢየሱስ እንደተነሣ እና ወደ ገሊላ ቀድሟቸው እንደሚሄድ መልአኩ ተናገረ። [28:6]
ኢየሱስ እንደተነሣ እና ወደ ገሊላ ቀድሟቸው እንደሚሄድ መልአኩ ተናገረ። [28:7]
ሴቶቹ ኢየሱስን አገኙትና እግሩን ይዘው አመለኩት። [28:8]
ሴቶቹ ኢየሱስን አገኙትና እግሩን ይዘው አመለኩት። [28:9]
ሊቀ ካህናቱ ለወታደሮቹ ጠርቀም ያለ ገንዘብ ከፍሏቸው የኢየሱስ ደቀመዛሙርት ሰውነቱን ሰረቀ እንዲሉ ነገሯቸው። [28:11]
ሊቀ ካህናቱ ለወታደሮቹ ጠርቀም ያለ ገንዘብ ከፍሏቸው የኢየሱስ ደቀመዛሙርት ሰውነቱን ሰረቀ እንዲሉ ነገሯቸው። [28:12]
ሊቀ ካህናቱ ለወታደሮቹ ጠርቀም ያለ ገንዘብ ከፍሏቸው የኢየሱስ ደቀመዛሙርት ሰውነቱን ሰረቀ እንዲሉ ነገሯቸው። [28:13]
ደቀመዛሙርቱ ኢየሱስን አመለከቱት፣ አንዳንዶች ግን ተጠራጠሩ። [28:17]
ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር እንደተሰጠው ኢየሱስ ተናገረ። [28:18]
ደቀመዛሙርቱ እንዲሄዱና ደቀመዛሙርትን እንዲያደርጉ፣ እንዲያጠምቋቸውም ኢየሱስ አዘዛቸው። [28:19]
በአብ፣ በወልድ እና በመንፈስ ቅዱስ ስም እንዲያጠምቊ ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ ነገራቸው። [28:19]
ሕዝቦችን ሁሉ እርሱ ያዘዛቸውን ነገሮች መታዘዝን እንዲያስተምሩ ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ አዘዛቸው። [28:20]
ኢየሱስ እስከ ዓለም መጨረሻ ድረስ ከእነርሱ ጋር እንደሚሆን ቃል ገባላቸው። [28:20]