1 የዳዊት ልጅ፣ የአብርሃም ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ መጽሐፍ፡፡ 2 አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፤ ይስሐቅም ያዕቆብን ወለደ፤ ያዕቆብም ይሁዳንና የይሁዳን ወንድሞች ወለደ፤ 3 ይሁዳም ከትዕማር ፋሬስንና ዛራን ወለደ፤ ፋሬስም ኤስሮምን ወለደ፤ ኤስሮምም አራምን ወለደ፤ 4 አራምም አሚናዳብን ወለደ፤ አሚናዳብም ነአሶንን ወለደ፤ ነአሶንም ሰልሞንን ወለደ፤ 5 ሰልሞንም ከረዐብ ቦዔዝን ወለደ፤ ቦዔዝም ከሩት ኢዮቤድን ወለደ፤ ኢዮቤድም እሴይን ወለደ፤ እሴይም ንጉሥ ዳዊትን ወለደ፡፡ 6 ንጉሥ ዳዊትም ከኦርዮ ሚስት ሰሎሞንን ወለደ፤ 7 ሰሎሞንም ሮበዓምን ወለደ፤ ሮብዓምም አብያን ወለደ፤ አብያም አሳፍን ወለደ፤ 8 አሳፍም ኢዮሣፍጥን ወለደ፤ ኢዮሣፍጥም ኢዮራምን ወለደ፤ ኢዮራምም ዖዝያንን ወለደ፤ 9 ዖዝያንም ኢዮአታምን ወለደ፤ ኢዮአታምም አካዝን ወለደ፤ አካዝም ሕዝቅያስን ወለደ፤ 10 ሕዝቅያስም ምናሴን ወለደ፤ ምናሴም አሞጽን ወለደ፤ አሞጽም ኢዮስያስን ወለደ፤ 11 ኢዮስያስም በባቢሎን ምርኮ ጊዜ ኢኮንያንንና ወንድሞቹን ወለደ፡፡ 12 ከባቢሎን ምርኮ በኋላም፣ ኢኮንያን ሰላትያልን ወለደ፤ ሰላትያልም ዘሩባቤልን ወለደ፤ 13 ዘሩባቤልም አብዩድን ወለደ፤ አብዩድም ኤልያቄምን ወለደ፤ ኤልያቄምም አዛርን ወለደ፤ 14 አዛርም ሳዶቅን ወለደ፤ ሳዶቅም አኪምን ወለደ፤ አኪምም ኤልዩድን ወለደ፤ 15 ኤልዩድም አልዓዛርን ወለደ፤ አልዓዛርም ማታንን ወለደ፤ ማታንም ያዕቆብን ወለደ፤ 16 ያዕቆብም ክርስቶስ ተብሎ የሚጠራውን ኢየሱስን የወለደችውን፣ የማርያምን ባል ዮሴፍን ወለደ፡፡ 17 ከአብርሃም እስከ ዳዊት፣ የነበሩት ትውልዶች ሁሉ ዐሥራ አራት፤ ከዳዊት እስከ ባቢሎን ምርኮ ድረስም እንደዚሁ ዐሥራ አራት፤ ከባቢሎን ምርኮ እስከ ክርስቶስ ድረስ የነበሩትም ዐሥራ አራት ትውልዶች ናቸው፡፡ 18 የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በሚከተለው መንገድ ተፈጸመ፡- እናቱ ማርያም ዮሴፍን ልታገባው ታጭታ ነበር፤ ነገር ግን ሳይጋቡ በመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች፡፡ 19 ዮሴፍ ጻድቅ ነበረ፤ በመሆኑም እርሷን በሕዝብ ፊት ሊያዋርዳት አልፈለገም፡፡ ስለዚህ ከእርሷ ጋር የነበረውን የዕጮኛነቱን ግንኙነት በምስጢር ለማቋረጥ ወሰነ፡፡ 20 ዮሴፍ ስለ እነዚህ ነገሮች እያሰበ ሳለ፣ የጌታ መልአክ፣ "የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ፣ ማርያምን ለመውሰድ አትፍራ፤ ምክንያቱም እርሷ የፀነሰችው በመንፈስ ቅዱስ ነው። 21 እርሷ ወንድ ልጅ ትወልዳለች፣ ሕዝቡንም ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ብለህ ትጠራዋለህ" በማለት ተገለጠለት። 22-23 ይህ ሁሉ የሆነው፣ "እነሆ ድንግል ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፤ ስሙንም ዐማኑኤል ብለው ይጠሩታል፤ ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው ማለት ነው" ብሎ ጌታ በነቢይ የተናገረው እንዲፈጸም ነው። 24 ዮሴፍ ከእንቅልፉ ነቃ፣ የጌታ መልአክ አዝዞት እንደ ነበረውም አደረገ፡- ማርያምን እን ደሚስቱ ወሰዳት፡፡ 25 (ይሁን እንጂ፣ ልጅ እስከምትወልድ ድረስ ከእርሷ ጋር ግንኙነት አላደረገም፡፡) የሕፃኑንም ስም ኢየሱስ አለው፡፡
አጠቃላይ መረጃ ጸሐፊው ኢየሱስ ከዳዊት እና ከአብርሃም ዘር እንደመጣ ለማሳየት ጽሑፉን የጀመረው ከኢየሱስ የዘር ሀረግ ነው። ይህ የዘር ሀረግ ዝርዝር እስክ ዲረስ ይቀጥላል MAT 1:17 የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ መጽሐፍ ይህ የኢየሱስ ትውልድ ዝርዝር ነው። የዳዊት ልጅ፥ የአብርሃም ልጅ በኢየሱስ፥ በዳዊት እና በአብረሃም መካከል ብዙ ትውልዶች አሉ። በዚህ ሥፍራ "ልጅ" ማለት "ዘር' ማለት ነው። "የዳዊት ልጅ የሆነው እርሱ የአብርሃምም ልጅ ነው።" የዳዊት ልጅ አንዳንድ ጊዜ "የዳዊት ልጅ" የሚልው ሀረግ እንደ ስያሜ ሆኖ ያገልግላል ነገር ግን በዚህ ሥፍራ ላይ የኢየሱስን ቅድመ አያቶች ለማሳየት የገባ ቃል ነው። አብርሃም የይሳቅ አባት ነው። ይህንን በተለያዩ መንገዶች መተርጎም ይቻላል። በዬትኛውም መንገድ ተርጉሙት በዘር ሀርግ ዝርዝር ውስጥ ተመሳሳ በሆነ መልኩ መተርጎሙ ጥሩ ነው። ትርጉም፡ "አብርሃም የይሳቅ አባት ሆነ" ወይም "አብርሃም ይሳቅ የሚባል ልጅ ነበረው፨" ፋሬስንና ዛራን . . . ኤስሮምን . . . አራም እነዚህ የሰዎች ስም ። ፋሬስን . . . አባት ነው ኤስሮም . . . ነው።
ሰልሞንም የቦኤዝ አባት ነው "ሰልሞን የቦኤዝ አባት ነው፤ የቦኤዝ እናት ደግሞ ረአብ ናት" ወይም "ሰልሞን እና ረአብ የቦኤዝ ወላጆች ናቸው።" ቦኤዝ የኢዮቤድ አባት ነው፤ የኢዮቤድም እናት ሩት ናቴ" ወይም "ቦኤዝ እና ሩት የኢዮቤድ ወላጆች ናቸው። ዳዊትን የኦርዮ ሚስት ከነበረችው ምስቱ ሰሎሞንን ወልዶ አባቱ ሆን ወይም "ዳዊት እና የኦርዮ ሚስት የነበረችው ምስቱ የሰለሞን ወላጆች ናቸው። የኦርዮ ሚስት የነበረችው ሰለሞን የተወለደው ኦርዩ ከሞተ በኃላ ነው።
አሳ አንዳንድ ጊዜ "አሳፍ" ተብሎ ይተረጎማል። የዖዝያን ትክክለኛ ስሙ ሮብዓም፥ ስለዚህም "አባት" የሚለው ቃል "የዘር ሀረግ" ተብሎ መተርጎም ይችላል። ሰሎሞንም ሮብዓምን ወለደ፤ ሮብዓምም አቢያን ወለደ፤ (UDB).
አሞን አሞን አንዳንድ ጊዜ "አሞፅ" ተብሎ ይተረጎማል። ኢዮስያስ የኢኮንያንን አባት ነው እውነታው ኢዮስያስ የኢኮንያንን አያት ነው። በባቢሎንም ምርኮ ጊዜ "ወደ ባቢሎን በምርኮ ተገደው እንዲሄዱ ሲድረግ" ወይም "ባቢሎናዊያን ቁጥጥር በሆኑ ጊዜና ወደ ባቢሎን እንዲሄዱ ስያስገድዷቸው።" በቋንቋችሁ ማን ወደ ባቢሎን እንደሄደ መግለጽ አስፈላጊ ከሆነ እንዲህ ማለት ትችላላችሁ "እስራኤላዊያን" ወይም "በይሁዳ ይኖሩ የነበሩ እስራኤላዊያን" ባቢሎን በዚህ ሥፍራ ላይ ባቢሎን የሚለው ቃል የሚያመለክተው ባቢሎን የተሰኘችውን ሀገር እንጂ የባቢሎን ከተማን ብቻ አይደለም።
ከባቢሎንም ምርኮ በኋላ MAT 1:11. ላይ ከተጠቀምከው ቃል ጋር ተመሳሳይ ቃልን ተጠቀም። ሰላትያል የዘሩባቤል አባት ነው እውነታው ሰላትያል የዘሩባቤል አያት ነው፨
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጸሐፊው በ MAT 1:1. ላይ የጀመረውን የኢየሱስን የትውልድ ሀርግ ያጠናቅቃል። ኢየሱስን የወለደችው ማሪያም ኤቲ፡ "ኢየሱስን የወለደችው ማሪያም" ( ይመልከቱ) ክርስቶስ የተባለው ይህ እንዲህ ልተረጎም ይችላል፡ ኤቲ፡ "ሰዎች ክርስቶስ ብለው የሚጠሩት።" ( ተመልከቱ) ዐሥራት አራት "14" ( ተመልከቱ) የባቢሎን ምርኮ MAT 1:11. ላይ ከተጠቀምከው ቃል ጋር ተመሳሳይ ቃልን ተጠቀም።
አጠቃላይ መረጃ ይህ ክፍል ጸሐፊው ለኢየሱስ መወለድ ምክንያት የሆኑ ሁኔታዎችን የገለጸበት የታርኩ አዲሱ ጅማሬ ነው። እናቱ ማርያም ለዮሴፍ ታጭታ ነበር "እናቱ ማርያም ዮሴፍን ልታገባ ነበር።" ብዘመኑ ወላጆች ለልጆቻቸው ትዳር አጋር ያዘጋጁ ነበር። ኤቲ፡ "የኢየሱስ እናት የሆነችው ሪያም ወላጆቿ ለዮሴፍ እርሷን ለመዳር ተስማምተዋል።" ( ተመልከት) እናቱ ማርያም ታጭታ ነበር ማርያም ለዮሴፍ ታጭታ በነበረበት ወቅት ኢየሱስ አለመወለዱን በሚያሳይ መንገድ ተርጉሙት። ኤቲ፡ "ኋላ ላይ ኢየሱስን የወለደችው ማሪያም ታጭታ ነበር" ሳይገናኙ "ከመጋባታቸው በፊት።" ይህ ዮሴፍ እና ማሪያም አብረው ከመተኛታቸው በፊት" የሚለውን የሚያመልክት ይሆናል። ኤቲ፡ "አብረው ከመተኛታቸው በፊት"። ( ተመልከት) አርግዛ ተገኘች ይህ እንዲህ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ልጅ ልትወልድ እንደሆነ አወቁ” ወይም “አረገዘች፡፡” ( ተመልከት) በመንፈስ ቅዱስ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ማሪያም ከሰው ጋር ሳትተኛ ማርገዝ እንድትችል አደረጋት፡፡ ባሏ ዮሴፍ ዮሴፍ ማሪያምን ገና አላገባትም ነበር ይሁን እንጂ አንድ ወንድ እና አንድ ሴት ትዳር ለመጋባት ቃል ከተገባቡ ምንም እንኳ አብረው መኖር ባይጀምሩም አይሁዶች ባል እና ምስት አድርገው ይቆጥሯቸው ነበር፡፡ ከእርሷ ጋር የተነበረውን እጮኝነት ለማቆም “ለመጋባት የነበራቸውን እቅድ ለመሰረዝ”
እንዳሰበው “ዳዊት እንዳሰበው” በሕልም ተገለጠለት “ለዮሴፍ በሕልም ተገልጦለት” የዳዊት ልጅ በዚህ ሥፍራ “ልጅ” ማለት “የልጅ ልጅ” ማለት ነው፡፡ በማሕጸኗ ውስጥ የተሸከመችው ልጅ የተጸነሰው በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ነው ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “መንፈስ ቅዱስ ማሪያም እንዲትጸንስ አደረገ፡፡” ( ተመልከት) ወንድ ልጅ ትወልዳለች እግዚአብሔር መልአክን ስላዘዘ መልአኩ የተወለደው ወንድ ልጅ እንደሆነ ያውቅ ነበር፡፡ እንዲህ ብለሽ ትጠሪዋለሽ ይህ ትዕዛዝ ነው፡፡ ኤቲ፡ “እንዲህ ብለሽ ጥሪው” ወይም “እንዲህ የሚል ስም ልትሰጪው ይገባል፡፡ ያድናልና በዚህ ሥፍራ ላይ ተርጓሚዎች እንዲህ የሚል የግሪጌ ማስታወሻ መጨመር ይችላሉ፡ “ኢየሱስ የሚለው ስም ጌታ ያድናል ማለት ነው፡፡ ሕዝቡን ይህ የሚያመለክተው አይሁዳዊያንን ነው
አጠቃላይ መረጃ ጸሐፊው የኢየሱስ አወላለድ በቅዱሳት መጽሐፍት አስቀድሞ በተነገረው መሠረት መሆኑን ለማሳየት ከነብይ ኢሳያስ መጽሐፍ ጠቅሶዋል፡፡ ( ተመልከት) ይህ ሁሉ ሆነ መልአኩ መናገር አቁሟል፡፡ አሁን ማቴዎስ መልአኩ የተናገረው ነገር ምን ያኽል አስፈላጊ እንደሆነ እያብራራ ነው፡፡ ጌታ በመላዕክቱ አማካኝነት የተናገረው ነገር ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡ ኤቲ፡ “ጌታ ለነብይ ኢሳያስ ከብዙ ዘመናት በፊት የተናገረው እንዲጽፍ የነገረው ነገር፡፡” ( ተመልከት) እነሆ . . . አማኑኤል በዚህ ሥፍራ ላይ ማቴዎስ ከነብዩ ኢሳያስ መጽሐፍ ጠቅሷል፡፡ እነሆ ይህ ቃል ሰዎች ከዚህ በኋላ ለሚነገረው ነገር አጽኖት እንዲሰጡ የሚጨመር ቃል ነው፡ ኤቲ፡ “ተመልከቱ” ወይም “አድምጡ” ወይም “አሁን ለምነግራችሁ ነገር ትኩረት ስጡ”:: አማኑኤል ይህ የወንድ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው” ማለት ነው ይህ በኢሳያስ መጽሐፍ ውስጥ የለም፡፡ ማቴዎስ የስሙን ትርጉም እያብራራ ነው፡፡ ይህን ለብቻው በአንድ ዐረፍተ ነገር መተርጎም ትችላላችሁ፡፡ ኤቲ፡ “የዚህ ስም ትርጉም “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው” ማለት ነው፡፡
አያያዥ ዐረፍተ ነገር ጸሐፊው የኢየሱስ አወላለድን ምን ይመስል እንደነበር የሰጠውን ገለጻ አጠናቀቀ፡፡ የጌታ መልአክ ባዘዘው መሠረት መልአኩ ዮሴፍን ማሪያምን ምስቱ አድርጎ እንዲወስዳት እና የልጁንም ስም ኢየሱስ እንዲለው አዘዘው፡፡ እርሱም እርሷን ምስቱ አድርጎ ወሰዳት “አገባት” ለልጁ ዮሴፍ እውነተኛ አባቱ አለመሆኑን ግልጽ መሆኑን እርግጠኞች ሁኑ፡፡ ኤቲ፡ “ወንድ ልጅ” ወይም “ለልጇ” እና ኢየሱስ ብሎ ስም ጠራው “ዮሴፍ ሕጻኑን ኢየሱስ የሚል ስም አወጣለት”
1 በንጉሥ ሄሮድስ ዘመን ኢየሱስ በቤተ ልሔም ይሁዳ ከተወለደ በኋላ፣ ጠቢባን ሰዎች ከምሥራቅ ወደ ኢየሩሳሌም መጡ፡፡ እንደዚህም በማለት ጠየቁ፤ 2 ‹‹የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ የት ነው? የእርሱን ኮከብ በምሥራቅ አየን፣ ልንሰግድለትም መጥተናል፡፡›› 3 ንጉሡ ሄሮድስ ይህን ሲሰማ ተረበሸ፤ መላው ኢየሩሳሌምም ከእርሱ ጋር ታወከ፡፡ 4 ሄሮድስ የካህናቱን አለቆችና የሕዝቡን የሕግ መምህራን ሰብስቦ፣ ‹‹ክርስቶስ የሚወለደው የት ነው?›› በማለት ጠየቀ፡፡ 5 ‹‹በቤተ ልሔም ይሁዳ›› አሉት፤ በነቢዩ የተጻፈው ይህ ነውና፡ 6 በይሁዳ ምድር የምትገኚ አንቺ ቤተ ልሔም፣ ከይሁዳ ገዦች በምንም አታንሺም፣ ሕዝቡን እስራኤልን የሚጠብቅ ገዥ፣ ከአንቺ ይወጣልና፡፡ 7 ከዚያም በኋላ ሄሮድስ ኮከቡ በትክክል በምን ሰዓት ታይቶ እንደ ነበር ሊጠይቃቸው ጠቢባኑን በምስጢር ጠራቸው፡፡ 8 ወደ ቤተ ልሔምም ላካቸው፤ ‹‹ሂዱና ሕፃኑን በጥንቃቄ ፈልጉ፡፡ ስታገኙት እኔም ደግሞ እንድመጣና እንድሰግድለት ንገሩኝ›› አላቸው፡፡ 9 ንጉሡ የተናገረውን ከሰሙ በኋላ ሄዱ፤ በምሥራቅ አይተውት የነበረውም ኮከብ ሕፃኑ በነበረበት ላይ እስኪደርስና እስኪቆም ድረስ በፊታቸው ይሄድ ነበር፡፡ 10 ጠቢባኑ ኮከቡን ባዩት ጊዜ፣ እጅግ በጣም ተደሰቱ፡፡ 11 ወደ ቤት ገብተው ሕፃኑንም ከእናቱ ከማርያም ጋር አዩት፤ ተንበርክከውም ሰገዱለት፡፡ ሣጥኖቻቸውንም ከፍተው የወርቅ፣ የዕጣንና የከርቤ ስጦታ አቀረቡለት፡፡ 12 እግዚአብሔር ጠቢባኑን ወደ ሄሮድስ ተመልሰው እንዳይሄዱ በሕልም አስጠነቀቃቸው፤ ስለዚህም በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ፡፡ 13 ጠበባኑ ከሄዱ በኋላ፣ የጌታ መልአክ ለዮሴፍ በሕልም ተገለጠለትና፣ "ተነሥ፣ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ፡፡ እኔ እስክነግርም ድረስ እዚያ ቈይ፤ ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ይፈልጋልና" አለው፡፡ 14 በዚያ ሌሊት ዮሴፍ ተነሣ፣ ሕፃኑንና እናቱንም ይዞ ወደ ግብፅ ሄደ፡፡ 15 ሄሮድስ እስኪሞት ድረስ እዚያው ቈየ፡፡ በዚህም ጌታ፣ ‹‹ልጄን ከግብፅ ጠራሁት›› ብሎ በነቢዩ የተናገረው ቃል ተፈጸመ፡፡ 16 ከዚያም ሄሮድስ ጠቢባኑ እንደ ተሣለቁበት ሲገነዘብ በጣም ተናደደ፡፡ በቤተ ልሔምና በዚያ አውራጃ የነበሩ ወንድ ሕፃናትን፣ እንደዚሁም ሁለት ዓመትና ከዚያም በታች የሆኑትን ሁሉ ከጠቢባኑ በትክክል በተረዳው ጊዜ መሠረት ልኮ አስፈጀ፡፡ 17 በዚያም በነቢዩ ኤርምያስ ተነግሮ የነበረው፡- 18 ‹‹ድምፅ በራማ ተሰማ፣ ልቅሶና መሪር ዋይታ፣ ራሔል ስለ ልጆቿ በማልቀስ፣ ለመጽናናትም እምቢ አለች፣ በሕይወት የተረፈ የለምና›› የሚለው ተፈጸመ፡፡ 19 ሄሮድስ ሲሞት፣ እነሆ፣ የጌታ መልአክ በግብፅ ለዮሴፍ በሕልም ተገለጠለትና፣ 20 ‹‹ሕፃኑን ሊገድሉት የፈለጉት ስለ ሞቱ፣ ተነሣ፤ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ እስራኤል አገር ሂድ›› አለው፡፡ 21 ዮሴፍ ተነሣ፣ ሕፃኑንና እናቱን ይዞ ወደ እስራኤል አገር ሄደ፡፡ 22 አርኬላዎስ በአባቱ በሄሮድስ ስፍራ ተተክቶ ይሁዳን ይገዛ እንደ ነበረ ሲሰማ ግን ወደዚያ ለመሄድ ፈራ፡፡ እግዚአብሔር በሕልም ካስጠነቀቀው በኋላ፣ ወደ ገሊላ አውራጃ ሄደ፤ 23 ናዝሬት በምትባል ከተማ ውስጥም ኖረ፡፡ ይህ በነቢዩ ተነግሮ የነበረውን፣ ናዝራዊ ተብሎ ይጠራል የሚለውን እንዲፈጸም አደረገ፡፡
አጠቃላይ መረጃ የታሪኩ አዲስ ክፍል የሚጀምረው በዚህ ሥፍራ ላይ ነው፡፡ ከዚያም እስከ ምዕራፉ መጨረሻ ድረስ ይሄዳል፡፡ ጸሐፊው ሄሮዶስ አዲሱን የአይሁድ ንጉሥ ለመግደል ስላደረገው ሙከራ ይነግረናል፡፡ ቤተልሔም ይሁዳ “በይሁዳ ግዛት ውስጥ የሚትገኝ የቤተልሔም ከተማ” ሄሮዶስ ንጉሥ በነበረበት ዘመን “በዚያ ሄሮዶስ ንጉሥ ሆኖ ሳለ” ሄሮዶስ ሄሮዶስ የሚለው ቃል የሚያመለክተው ታላቁን ሄሮዶስን ነው፡፡ የተማሩ ሰዎች “ክዋክብትን ያጠኑ ሰዎች” (UDB) ከምስራቅ የመጡ “ከይሁዳ በስተምስራቅ በኩል ከሚገኝ ሀገር የመጡ” የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ዬት አለ? ሰዎቹ ከክዋክብት ጥናታቸው የአይሁድ ንጉሥ ለመሆን የተወለደ ልጅ እንዳለ አውቀዋል፡፡ በዬት ሥፍራ እንዳለ ለማወቅ ፈልገዋል፡፡ ኤቲ፡ “የአይሁድ ንጉሥ ለመሆን አንድ ልጅ ተወልዷል፡፡ ዬት ነው ያለው?” የእርሱ ኮከብ ኮከቧ ትክክለኛ ባለቤት ልጁ ነው እያሉ አይደለም፡፡ ኤቲ፡ “ስለ እርሱ የሚትናገረው ኮከብ” ወይም “ከእርሱ መወለድ ጋር የተያያዘችው ኮከብ” በምስራቅ “በምስራቅ በወጣች ጊዜ” ወይም “በሀገራችን ሳለን” ማምለክ አማራጭ ትርጉሞች 1) ልጁ መለኮት እንደሆነ ተገንዝበወ ለማምለክ ፈልገዋል ወይምመ 2) እንደ አንድ ንጉሥ ልያከብሩት ፈልገዋል፡፡ ቋንቀዋችሁ ሁለቱንም ትርጉሞች መያዝ የሚችል ቃል ካለው በዚህ ሥፍራ ላይ ይህንን ቃል መጠቀምንን ከግንዛቤ ውስጥ አስገቡ፡፡ ተጨነቀ “ፈራ”፡፡ ይህ ልጅ ንግሥናዬን ይቀማኛል ብሎ በመፍራት ተጨነቀ፡፡ ኢየሩሳሌም በሙሉ በዚህ ሥፍራ ላይ “ኢየሩሳሌም” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሰዎችን ነው፡፡ እንዲሁም “ሁሉም” ማለት “ብዙ” ማለት ነው፡፡ ማቴዎስ በዚህ ሥፍራ ላይ ብዙ ሰዎች በዚህ ጉዳይ መጨነቃቸውን ለማመልከት ግነት ተጠቅሟል፡፡ ኤቲ፡ “በኢየሩሳሌም ያሉ ብዙ ሰዎች፡፡” (UDB) ( and ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ በቁጥር 6 ላይ ካህናት አለቆች እና ጸሐፊት ክርስቶስ በቤተልሔም ከተማ እንደሚወል ከሚልክያስ መጽሐፍ በመጥቀስ አሳይተዋል፡፡ በቤተልሔም ይሁዳ “በይሁዳ ግዛት የሚትገኘው ቤተልሔም ውስጥ” ይህ በነብያት የተነገረው ነገር ነው ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡ ኤቲ፡ “ይህ ነቢያት ከብዙ ዘመናት በፊት የጻፉት ነገር ነው፡፡” (፡ ተመልከት) እና አንች፣ ቤተልሔም . . . ኢስራኤል ከሚልክያስ መጽሐፍ ላይ እየጠቀሱ ነው፡፡ አንች፣ ቤተልሔም . . . ከይሁዳ መሪዎች መካከል መጨረሻ አይደለሽም ሚልክያስ በቤተልሔም ይኖሩ ለነበሩ ሰዎች ከእርሱ ጋር እንደሆኑ አድርጎ ይነግራቸው ነበር ነገር ግን እነርሱ ጋር ከእርሱ ጋር አልነበሩም፡፡ በተጨማሪም “የመጨረሻ አልነበሩም” ይህ አዎንታዊ በሆነ ሀረግ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እናንተ የቤተልሔም ሰዎች . . . ከተማችሁ በይሁዳ ግዛት ውስጥ ከሚገኙ ከተሞች መካል ትልቁ ነው፡፡” ( እና ተመልከቱ) ሕዝቤን ኢስራኤል የሚጠብቅ ማን ነው ሚልክያስ እነዚህን ገዥዎችን እንደ እርኛ አድርጎ ይናገራቸዋል፡፡ ይህ ማለት ሕዝቡን የሚመሩ እና የሚንከባከቡ፡፡ ኤቲ፡ “እረኛ በጎቹን እንደሚመራ ሁሉ ሕዝቤን የሚመራ ማን ነው” ( ተመልከት)
ሄሮዶስ በሚስጥር የተማሩ ሰዎችን ጠራቸው ይህ ማለት ሄሮዶስ የተማሩ ሰዎችን ሌሎች ሰዎች ሳያውቁ በድብቅ አስጠርቶ አናገራቸው ማለት ነው፡፡ ኮከቡ የታየው በትክክል መቼ እንደሆነ ጠያቃቸው ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ከዚያም እንዲህ ሲል ጠየቃቸው፣ “ኮከቡ በትክክል የታየው መቼ ነበር?” ( ተመልከት) ኮከቡ የታየው መቼ ነበር ይህ የተማሩት ሰዎች ከኮቡን መቼ እንደተመለከቱት በተዘዋዋር መንገድ እንደነገሩት ያሳያል፡፡ የተማሩትም ሰዎች ለሄሮዶስ ኮከቡን መቼ እንደተመለከቱ ነገሩት፡፡ ( ተመልከት) ጨቅላው ሕጻን ይህ ኢየሱስ የሚያመለክት ነው፡፡ ቃል አምጡልኝ ኤቲ፡ “አሳውቁኝ” ወይም “ንገሩኝ”( ተመልከት) እንዳመልከው ይህንን በ MAT 2:2 ላይ በተረጎምከው መሠረት ተርጉመው፡፡
ከእነርሱ በኋላ “ከተማሩተ ሰዎች በኋላ” በምስራቅ ተመለከቱ “በምስራቅ በኩል ስወጣ አዩት” ወይም “በሀገራቸው አዩት” ከፊት ፊታቸው ይሄድ ነበር “ይመራቸው ነበር” ወይም “መንገድ ያሳያቸው ነበር” ቀጥ ብሎ ቆመ “ቆመ” ጨቅላው ሕጻን ያለበት “ጨቅላው ሕጻን ያለበት ሥፍራ ስደረስ”
አያያዥ ዐረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ላይ የታሪኩ ፍሰት ወደ ማሪያም፣ ዮሴፍ እና ትንሹ ኢየሱስ ወደ ሚኖሩበት ቦታ ተለውጧል፡፡ ሄዱ “የተማሩት ሰዎች ሄዱ” አምልኮ ይህንን በ MAT 1:2 ላይ በተረጎምከው መሠረት ተርጉመው፡፡ ንብረታቸው በዚህ ሥፍራ ላይ “ንብረታቸው” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ንብረታቸውን ብዙ ጊዜ የሚይዙበት ሳጥን ወይም ሻንጣን ነው፡፡ ኤቲ፡ “ንብረታቸውን የሚይዙበት ሻንጣ፡፡” ." ( ተመልከት) እግዚአብሔር አስጠነቀቃቸው “ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር አስጠነቀቃቸው፡፡ ሄሮዶስ ልጁን ሊገድለው እንደሚፈልግ እግዚአብሔር ያውቃል፡፡ ወደ ሄሮዶስ እንዳይመለሱ ይህ በትምህረተ ጥቅስ ውስጥ ተደርጎ መተርጎም ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እንዲህ በማለት “ወደ ንጉሥ ሄሮዶስ ተመልሳችሁ እንዳትሄዱ፡፡” ( ተመልከቱ)
አጠቃላይ መረጃ በቁጥር 15 ላይ ጸሐፊው ክርስቶስ በግብጽ ምድር እንደሚቆይ ከነብዩ ሆሴን ይጠቅሳል፡፡ ሄዱ “የተማሩት ሰዎች ሄዱ” ለዮሴፍ በሕልም ተገለጠለት “ዮሴፍ ሕልም እያለመ ሳለ ወደ እርሱ መጣ” ተነስ፣ ያዝ . . . ሽሽ . . . ቆይ . . . አንተ እግዚአብሔር ለዮሴፍ ተናገረው፡፡ ስለዚህ ሁሉም በነጠላ ቁጥር ሊሆኑ ይገባቸዋል፡፡ . ( ተመልከት) እስክነግርህ ድረስ የዚህ ዓረፍተ ነገር ሙሉ ትርጉም በግልጽ መቀመጥ ይኖርበታል፡፡ ኤቲ፡ “መመለስህ ሰላም እንደሆነ እኔ እስክነገር ድረስ” ( ተመልከት) ቆየ ይህ ዮሴፍ፣ ማሪያም እና ኢየሱስ በግብጽ ምድር ውስጥ መቆየታቸውን ያሳያል፡፡፡፡ ኤቲ፡ “በዚያ ቆዩ” ( ተመልከት) ሄሮዶስ እስኪሞት ድረስ ሄሮዶስ MAT 2:19. ድረስ አልመተም፡፡ ይህ ዓረፍተ ነገር በግብጽ ምድር ውስጥ ለምን ያኽል ጊዜ እንደቆዩ ያሳያል እንዲሁም በእነዚህ ጊዜያት ሄሮዶስ እንደሞተ አይናገረም፡፡ ልጄን ከግብጽ ምድር ጠራሁት “ልሄን ከግብጽ ጠራት” ልጄ በሆሴ ውስጥ ይህ እስራኤላዊያንን የሚያመለክት ቃል ነው፡፡ ማቴዎስ ይህ እውነተኛ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ለመናገር ይህንን ክፍል ጠቅሶታል፡፡ ይህንን ብቸኛ ልጅ ወይም የመጀመሪያ ልጅን በሚያሳይ ቃል ተርጉሙት፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ላይ የታርኩ ፍሰት ወደ ሄሮዶስ ይመለሳልና የተማሩት ሰዎች እንዳታለሉት ሄሮዶስ ባወቀ ጊዜ ያደረገውን ይነግረናል፡፡ አጠቃላይ መረጃ ይህ ሁኔታ የተከሰተው ጸሐፊው MAT 2:15. ላይ የጠቀሰው እና ሄሮዶስ ከመሞቱ በፊት ነው፡፡ ( ተመልከት) የተማሩት ሰዎች ቀለዱበት ይህ እንዲህ ባለ መልኩ ሊገለጽ ይችላል፡ ኤቲ፡ “የተማሩት ሰዎች ሸውደውት ሄደው አዋረዱት”፡፡ ( ተመልከት) ሰዎችን ልኮ ሁሉንም ልጆች አስገደላቸው ሄሮዶስ ልጆቹን እርሱ ራሱ አልገደላቸውም፡፡ ኤቲ፡ “ሁሉንም ወንድ ልጆችን ይገድሉ ዘንድ ግን ትዕዛዝ ሰጣቸው” ወይም “ሁሉንም ወንድ ሕጻናትን ይገድሉ ዘንድ ወታደሮቹን ላካቸወ፡፡” ( ተመልከት) ሁለት እና ከሁለት ዓመት በታች የሆኑትን “2 ዓመት እና ከዚያ በታች ያሉትን” (UDB) ( ተመልከት) እንደግዜው “በጊዜው መሠረት”
አጠቃላይ መረጃ በይሁዳ ግዛት ውስጥ የነበሩት ወንድ ልጆች ሁሉ መገደላቸው በቅዱሳት መጽሐፍት በተነገረው መሠረት መሆኑን ጸሐፊው ነብዩ ኤርሚያስን በመጥቀስ ጽፏል፡፡ ይህም ተፈጸመ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ይህ ተፈጸመ” ወይም “የሄሮዶስ ተግባር ተፈጸመ፡፡” ( ተመልከት) የተፈጸመው ነገር በነብይ ኤርሚያስ አስቀድሞ ተነግሮ ነበር ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ገታ በነብይ ኤርሚያስ አማካኝነት ከብዙ ዘመናት በፊት እንደተናገረው፡፡” ( ተመልከት) ድምፅ ተሰማ . . . ከእንግዲህ የሉም ማቴዎስ ነብዩን ኤርሚያስን እየጠቀሰ ነው ድምፅ ተሰማ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡ ኤቲ፡ “ሰዎች ድምፅ ሰሙ” ወይም “ከፍተኛ ድምፅ ነበር፡፡ ( ተመልከት) ራሔል ስለልጆቿ አለቀሰች ራሔል ይህ ነገር ከመሆኑ ብዙ ዓመታት በፊት ነው የኖረችው፡፡ ይህ ትንቢት የሚያሳያው ከብዙ ዓመታት በፊት የሞተችው ራሔል ስለ ልጆቿ ማልቀሷን ነው፡፡ መጽናናትንም እንቢ አለች ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ማንም ሊያጽናናት አልቻለም፡፡” ( ተመልከት) የሉምና “ልጆቿ ጠፍተዋል እንዲሁም እንደገና ፈጽመው አይመለሱም፡፡ በዚህ ሥፍራ “የሉም” የሚለው ቃል ለዘብ ባለ ቃል መሞታቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ ኤቲ፡ “ስለሞቱ”፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ የታርኩ ፍሰት ዮሴፍ፣ ማሪያም እና ጨቅላው ኢየሱስ ወደሚኖሩበት ወደ ግብጽ ተቀይሯል፡፡ እነሆ ይህ በትልቁ ታርክ ውስጥ አንድ ሌላ ሁኔታ የመጀመሩ ምልክት ነው፡፡ ከዚህ ቀደም ካሉት ሁኔታዎች ውስጥ ከነበሩት ሰዎች ተጨማሪ ሰዎችን ሊጨምር ይችላል፡፡ በቋንቋችሁ ይህንን የሚትገልጹበት መንገድ ሊኖራችሁ ይችላል፡፡ የሕጻኑን ሕይወት የሚፈልጉት ሰዎች ኤቲ፡ “ሕጻኑን ለመግደል የሚፈልጉት ሰዎች”፡፡ ( ተመልከት) የሚፈልጉት ሰዎች ይህ ንጉሥ ሄሮዶስን እና አማካሪዎቹን የሚያመለክት ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ በ MAT 2:1 የተጀመረው ታርክ ሄሮዶስ የአይሁድ አዲሱን ንጉሥ ለመግደል ያደረገው ሙከራ የመጨረሻው ክፍል ነው፡፡ ይህንን በሰማ ጊዜ “ዮሴፍ ይህንን ስሰማ ግን” አርኬላዎስ ይህ የሄሮዶስ ልጅ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) ፈራ “ዮሴፍ ፈራ” በነቢያቱ የተነገረው ነገር ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ከብዙ ዘመናት በፊት ጊዜ በነቢያቱ አማካኝት እንደተናገረው፡፡” ( ተመልከት) ናዝራዊ ተብሎ ይጠራል በዚህ ሥፍራ “እርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው፡፡ ከእርሱ በፊት ይኖሩ የነሩ ነቢያት ስለ እርሱ ስባገሩ መስሑ ወይም ክርስቶስ ብለው ይጠሩታል፡፡ ኤቲ፡ “ሰዎች ክርስቶስ ናዝራዊ ነው ይላሉ፡፡” ( ተመልከት)
1 በእነዚያ ቀኖች መጥምቁ ዮሐንስ በይሁዳ ምድረ በዳ ፤ 2 "መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ" እያለ እየሰበከ መጣ። 3 በነቢዩ ኢሳይያስ፦ "ምድረ በዳ ውስጥ የሚጮኽ ሰው ድምፅ፣ የጌታን መንገድ አዘጋጁ፣ ጎዳናዎቹንም አስተካክሉ" ተብሎ የተነገረለት ይህ ነውና። 4 ዮሐንስ ይለብስ የነበረው የግመል ጠጕር፣ በወገቡ የሚታጠቀውም የቆዳ ጠፍር ነው፤ ምግቡም አንበጣና የዱር ማር ነበረ። 5 በዚያ ጊዜ ኢየሩሳሌም፣ መላው ይሁዳና በዮርዳኖስ ወንዝ ዙሪያ ያለ አገር ሁሉ ወደ እርሱ ይመጡ ነበር። 6 ሕዝቡ ኀጢአታቸውን እየተናዘዙ በዮርዳኖስ ወንዝ በእርሱ እጅ ተጠመቁ። 7 ነገር ግን ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን ብዙዎች ለመጠመቅ ወደ እርሱ ሲመጡ ባየ ጊዜ፣ "እናንተ የመርዛማ እባቦች ልጆች ከሚመጣው ቊጣ ለማምለጥ ማን አስጠነቀቃችሁ? 8 ለንስሐ የሚጠቅም ፍሬ ይኑራችሁ። 9 ለራሳችሁም አብርሃም አባታችን አለን" ብላችሁ አታስቡ። እግዚአብሔር ከእነዚህ ድንጋዮች እንኳ ለአብርሃም ልጆችን ማስነሣት እንደሚችል እነግራችኋለሁና። 10 አሁን መጥረቢያው በዛፎቹ ሥር ተቀምጦአል። ስለዚህ መልካም ፍሬ የማያፈራ ዛፍ ሁሉ ይቆረጣል በእሳት ውስጥም ይጣላል። 11 እኔ ለንስሐ የማጠምቃችሁ በውሃ ነው፤ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቃል፤ ጫማውን መሸከምም እንኳ አይገባኝም። እርሱ በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ያጠምቃችኋል። 12 ዐውድማውን ፈጽሞ ለማጥራትና ስንዴውን በጎተራ ውስጥ ለመክተት መንሹ በእጁ ነው። ገለባውን ግን ፈጽሞ በማይጠፋ እሳት ያቃጥለዋል። 13 ከዚያም ኢየሱስ በዮሐንስ እጅ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ መጣ። 14 ነገር ግን "እኔ አንተ እንድታጠምቀኝ ሲገባ፣ አንተ እንዴት ወደ እኔ ትመጣለህ?" በማለት ሊያስቆመው ሞከረ። 15 ኢየሱስም መልሶ፣ "አሁን ይህን ፍቀድ፤ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ለእኛ ተገቢ ነውና" አለው። ከዚያም በኋላ ዮሐንስ ፈቀደለት። 16 ኢየሱስ ከተጠመቀ በኋላ፣ ወዲያውኑ ከውሃ ውስጥ ወጣ፤ እነሆም ሰማያት ተከፈቱ። የእግዚአብሔር መንፈስ በርግብ መልክ ሲወርድና በእርሱ ላይ ሲቀመጥ አየ። 17 እነሆ፣ የምወደው ልጄ ይህ ነው። "በእርሱ እጅግ ደስ ይለኛል" የሚል ድምፅ ከሰማያት መጣ።
አጠቃላይ መረጃ፡ ይህ ጸሐፊው የመጥመቁ ዮሐንስን ታሪክ የተነናገረበት አዲስ የታሪኩ አካል መጀመሪያ ነው፡፡ በቁ. 3 ላይ ጸሐፊው የኢየሱስ አገልግሎት መንገድን ያዘጋጅ ዘንድ መጥመቁ ዮሐንስ በእግዚብሔር የተመረጠ መሆኑን ከነብዩ ኢሳያስ መጽሐፍ ጠቅሶ ጽፏል፡፡ በእነዚህ ቀናት ይህ ዮሴፍ እና የእርሱ ቤተሰብ ከግብጽ ምድር ወደ ናዝሬት ከተመሰሉ ብዙ ዓመታት በኋላ የሆነ ነው፡፡ ይህ ምናልባትም ኢየሱስ አገልግሎቱን ለመጀመር በተቃረበበት ጊዜ የተፈጸመ ነገር ይሆናል፡፡ ኤቲ፡ “ከዚያ በኋላ” ወይም “ከጥቂት ዓመታት በኋላ” ንሰሓ ግቡ ይህ በቅርጹ ብዙ ቁጥር ነው፡፡ ዮሐንስ ይህንን ለሕዝቡ እየተናገረ ነው፡፡ ( ተመልከት) የእግዚአብሔር መንግስት ቀርባለች “የእግዚአብሔር መንግስት ቀርባለች” የሚለው ሀረግ እግዚአብሔር ንጉሥ ሆነ መግዛቱን ያሳያል፡፡ ይህ ሀረግ በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ ብቻ ይገኛል፡፡ ከተቻለ በትርጉምህ ውስጥ “ሰማይ” የሚል ቃልን ተጠቀም፡፡ ኤቲ፡ “በሰማይ የሚኖር አባታችን ራሱን እንደ ንጉሥ አድርጎ በቅርቡ ያሳያል፡፡” ( ተመልከት) በነብዩ ኢሳያስ አስቀድሞ ስለ እርሱ እንዲህ ተብሎ የተነገረው ይህ ስለሆነ ነው ይህ እንዲህ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡፡ “ነብዩ ኢሳያስ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡” ( ተመልከት) የአንድ ሰው ድምፅ በዚህ ሥፍራ ላይ “ድምፅ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሙሉ ሰውን ነው፡፡ ኤቲ፡ “አንድ ሰው አለ፡፡” ( ተመልከት) የጌታን መንገድ አዘጋጁ፣ መንገዱንም አቅኑ “የጌታን መንገድ አዘጋጁ፣ መንገዱንም አቅኑ”፡፡ ይህ በዮሐንስ ሰዎችን ለኢየሱስ መምጣት ሰዎችን በንሰሓ የሚያዘጋጅ ምሳሌያዊ መልዕክት ነው፡፡ ( ተመልከት)
አሁን . . . የበረሃ ማር “አሁን” የሚለው ቃል በታሪኩ ፍሰት ውስጥ በዚህ ሥፍራ ለአንባቢው ምልክት እንዲሰጥ ተብሎ ጥቅም ላይ የዋለ ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ማቴዎስ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ የኋላ ታሪክ መረጃን ይሰጣል፡፡ ( ተመልከት) የግመል ጠጉር ይለብስ ነበር እንዲሁም ጠፍርንም ይታጠቅ ነበር ይህ የዮሐንስ አለባበስ ከእርሱ በፊት ይኖሩ እንደነበሩ ነብያት በተለይም እንደ ለነብዩ ኤልሳ ትንብታዊ መልዕክት ነበረው፡፡ ( እና ተመልከት) ኢየሩሳሌም፣ ይሁዳ ሁሉ እና በአከባቢው ያሉ ሁሉ ይህ በዚህ አከባቢ ይኖሩ የነበሩ ሰዎችን የሚያመለክት ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ “ሁሉም” የሚለው ቃ “ብዙ” ማለት ነው፡፡ ማቴወዎስ ወደ መጥመቁ ዮሐንስ የመጡት ብዙ ሰዎች መሆናቸውን አጽኖት ይሰጠቃል፡፡ ( እና ተመልከት) በእርሱ ተጠመቁ ይህ እንዲህ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ዮሐንስ አጠመቃቸው፡፡” ( ተመልከቱ) እነርሱ ይህ ማለት ከኢየሩሳሌም፣ ከይዳ እና ከዮርዳኖስ ዙሪያ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች መምጣታቸውን ያመለክታል፡፡
አጠቃላይ መረጃ መጥመቁ ዮሐንስ ፈርሳዊያንን እና ሳዱቃዊያንን ይገስጻቸው ጀመረ፡፡ እናንተ የመርዛማ እባብ ልጆች ይህ ምሳሌያዊ አነጋገር ነው፡፡ መርዛማ እባቦች አደገኛ ናቸው እንደሁም ክፋትን ይወክላሉ፡፡ ኤቲ፡ “እናንተ መርዛማ እባቦች!” ወይም “ልክ እንደ መርዝማ እባቦች ክፉዎች ናችሁ፡፡” ( ተመልከት ከሚመጣው ቁጣ እንድታመልጡ ማን አስጠነቀቃችሁ ዮሐንስ ፈርሳዊያንን እና ሳዱቃዊያንን ለማስጠንቀቅ ምክንያቱም እግዚአብሔር እንዳይቀጣቸው ዮሐንስ ያጠምቃቸው ዘንድ ይጠይቁት ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ኃጢአት ማድረጋቸውን ማቆም አይፈልጉም ነበር፡፡ ኤቲ፡ “በዚህ ዓይነት መንገድ ከእግዚአብሔር ፍርድ ማምለጥ አይቻልም፡፡” ወይም “እኔ ስላጠመኳችሁ ከእግዚአብሔር ፍርድ የሚታመልጡ አይመስላችሁ፡፡” ( ተመልከት) ከሚመጣው ቁጣ እንድታመልጡ “ቁጣ” የሚለው ቃል በዚህ ሥፍራ ጥቅም ላይ የዋለው የእግዚአብሔርን ቁጣ ለማመለከት ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ ይህ ከእግዚአብሔር ቅጣት ቀድሞ የሚመጣ ስለሆነ ነው፡፡ ኤቲ፡ “ከሚመጣው ቅጣት ለማምለጥ” ወይም “ከእግዚአብሔር ቅጣት ለማምለጥ፡፡” ( ተመልከት) የንሰሓን ፍሬ አፍሩ “አፍሩ” የሚለው ቃል ምሳሌያዊ አነጋገር ሲሆን የሰውዬውን ተግበባራት ያሳያል፡፡ ኤቲ፡ “ተግባራችሁ በእውነት ንሰሓ እንደገባችሁ ያሳይ፡፡” ( ተመልከት) አባታችን አብረሃም አለልን “አብረሃም አባታችን ነው” ወይም “እኛ የአብረሃም ዘሮች ነን፡፡” የአይሁድ መሪዎች የአብረሃም ዘሮች በመሆናቸው ምክንያት እግዚአብሔር እንደማይቀጣቸው ያስቡ ነበር፡፡” ( ተመልከት) እኔ ግን እንዲህ እላችኋለሁ ይህ ዮሐንስ ቀጥሎ ስለሚናር ነገር አጽኖት እንድሰጠ ያሳያል፡፡ ከእነዚህ ድንጋዮች እግዚአብሔር ልጆችን ማስነሳት ይችላል “ከእነዚህ ድንጋዮች ሳይቅር እግዚአብሔር ለአብረሃም ለልጆችን አበጅቶ ለአብረሃም መስጠጥ ይችላል፡፡”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር መጥመቁ ዮሐንስ ፈርሳዊያንን እና ሳዱቃዊያንን መገሰጹን ቀጥሏል፡፡ በዛፉ ሥር ላይ መሳሩ ተቀምጦዋል፡፡ መልካምን ፍሬ የማያፈራ ዘፍ ሁሉ ተቆርጦ ወደ እሳት ይጣላል፡፡ ይህ ምሳሌ እግዚአብሔር ኃጢአተኞችን ለመቅጣት ተዘጋጅቷል፡፡ ይህ በዚህ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚብሔር ምሳሩን አንስቷል፡፡ መጥፎ ፍሬ የሚያፈሩ ዛፎችን ለመቁረጥ እና ለማቃጠል ተዘጋጅቷል” ወይም “አንድ ሰው መጥፎ ፍሬ የሚያፈራን ዘፍ ለመቁረጥ እና ለማቃጠል ምሳሩን እንደሚያዘጋጅ ሁሉ እግዚአብሔርም ስለኃጢአታችሁ ሊቀጣችሁ ተዘጋጅቷል፡፡ ( እና ተመልከት) ለንሰሓ “ንሰሓ እንደገባችሁ የሚያሳይ ነገር” ነገር ግን ከእኔ በኋላ የሚመጣው ኢየሱስ ከዮሐንስ በኋላ የሚመጣው ነው፡፡ ከእኔ ይልቅ ኃይለኛ ነው “ከእኔ ይልቅ በጣም ጠቃሚ ነው፡፡” በመንፈስ ቅዱስ እና በእሳት ያጠምቃችኋል ይህ ምሳሌ የዮሐንስን ጥምቀት ለወደፊት ከሚሆነው በእሳት መጠመቅ ጋር ያነጻጽራል፡፡ ይህ ማለት የዮሐንስ ጥምቀት ሰዎች ከኃጢአታቸው መንጻታቸው ውጫዊ ምሳሌ ሆኖ የሚያገለግል ብቻ ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ እና በእሳት መጠመቅ ግን ሰዎችን በእውነት ከኃጢአታቸው ያነጻል፡፡ ከዮሐንስ ጥምቀት ጋር ለማነጻጸር ይረዳ ዘንድ በትርጉማችሁ ውስጥ ከተቻለ “መጠመቅ” የሚለውን ቃል ጥቅም ላይ አውሉት፡፡ ( ተመልከት) ስንዴውን ከገለባው መለየት እንዲችል መንሹ በእጁ ላይ ነው ይህ ምሳሌ ስንዴ ከገለባ እንደሚለይ ሁሉ ክርስቶስ ጻድቅ የሆኑ ሰዎችን ኃጢአተኞች ከሆኑን ይለያል፡፡ ኤቲ፡ “ክርስቶስ በእጁ መንሽን እንደያዘ ሰው ነው፡፡” ( ተመልከት) መንሽ በእጁ ላይ ነው በዚህ ሥፍራ “በእጁ ላይ ነው” የሚለው ሀረግ ሰውየው ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ያሳያል፡፡ ኤቲ፡ “ክርስቶስም መንሹን በእጁ ይዟል ምክንያቱም ዝግጁ ነው፡፡” መንሽ ይህ የስንዴ ነዶን ወደ ሰማይ በመወርወር በንፋስ አማካኝነት ገለባውን ከፍሬው ለመለየት የሚረዳ መሣሪያ ነው፡፡ ክብደት ያለው ፍሬው መደመሬት ስወድቅ የማይፈለገው ገለባው ግን በንፋስ ይወሰዳል፡፡ ከሹካ ጋር ተመሳሳይ ቅርጽ ያለው ሲሆን መንሽ ግን የሚሠራው ከእንጨት ነው፡፡ ( ተመልከት) አውድማ “እህል የሚወቃበት ሜዳ” ወይም “ፍሬው እና ገለባው የሚለይበት ሥፍራ” ምርቱንም ወደ ጎተራው ይከተዋል . . . ገለባውን ግን ወደ ማይጠፋ እሳት ውስጥ ይጨምረዋል፡፡
ይህ እግዚአብሔር እንዴት ጻድቃንን ከኃጢአትን እንደሚለይ የሚያሳይ ምሳሌ ነው፡፡ ገበሬ ስንዴውን ወደ ጎተራው እንደሚያስገባ ሁሉ ጻድቃንም ወደ ሰማይ ይሄዳሉ እንዲሁም እንደ ገለባው ያሉትን ሰዎች እግገዚአብሔር ወደ ማይጠፋ እሳት ውስጥ ይጨምራቸዋል፡፡ ( ተመልከት) ወደማይጠፋ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላለል፡፡ ኤቲ፡ “ነዶ ወደማያልቅ፡፡” ( ማይጠፋ እሳት ውስጥ ይጨምራቸዋል፡፡ ( ተመልከት))
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ጸሐፊው ታርኩ በኋላ ላይ ዮሐንስን ኢየሱስን ወደ አጠመቀበት ይቀይረዋል፡፡ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ
ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ዮሐንስ ያጠምቀው ዘንድ፡፡” ( ተመልከት) አንተ ወደ እኔ ትመጣለህ? እኔ በአንተ እጅ መጠመቅ ያስፈልገኛል፡፡
ኢየሱስ ለጠየቀው ጥያቄ ዮሐንስ በአግራሞት በጥያቄ መልክ ስመልስ እናያለን፡፡ ኤቲ፡ “አንተ ከእኔ ይልቅ አስፈላጊ ነህ፡፡ እኔ አንተን ማጥመቅ የለብኝም፡፡ አንተ እኔ ማጥመቅ አለብህ፡፡” ( ተመልከት) ለእኛ በዚህ ሥፍራ “እኛ” የሚለው ቃል ኢየሱስን እና ዮሐንስን የሚታመለክት ናት፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ የተነገረው ታርክ መጨረሻ እና ኢየሱስን ካጠመቀ በኋላ ምን እንደሆነ የተገለጸበት ክፍል ነው፡፡ ከተጠመቀ በኋላ ይህ በቀጥታ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ዮሐንስ ኢየሱስን ካጠመቀ በኋላ፡፡” ( ተመልከት) እነሆ “እነሆ” የሚለው ከዚህ ቀጥሎ ያለው ማስረጃ አስገራሚ ስለሆነ አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ ሰማያት ለእርሱ ተከፈቱ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ኢየሱስ ሰማያት ተከፍቶ ተመለከተ” ወይም “እግዚአብሔር ሰማያትን ለኢየሱስ ከፈተ”፡፡ ( ተመልከት) በእርግም አምሳሌ ወረደ አማራጭ ትርጉሞች እነዚህ ናቸው 1) መንፈስ በእርግም አምሳሌ መውረዱን የሚያመለክት ቀጥተኛ ትርጉም ወይም 2) እርግም በቀስታ እንደሚትወርድ ሁሉ ልክ እንደዚሁ መንፈስ ቅዱስ በቀስታ በኢየሱስ ላይ መውረዱን የሚያመለክት ምሳሌ ነው፡፡ ( ተመልከት) እንዲህ የሚል ድምፅ ከሰማይ መጣ “ኢየሱስ ድምፅ ከሰማይ ሰማ፡፡” (UDB) ( ተመልከት) ልጅ ይህ የኢየሱስ በጣም አስፈላጉ የማዕረግ ስም ነው፣ የእግዚአብሔር ልጅ፡፡ ( ተመልከት)
1 ከዚያም በኋላ በዲያብሎስ ሊፈተን መንፈስ ኢየሱስን ወደ ምድረ በዳ መራው፡፡ 2 ኢየሱስ ዐርባ ቀንና ዐርባ ሌሊት ከጾመ በኋላ ተራበ፡፡ 3 ፈታኙ ወደ እርሱ መጣና፣ ‹‹የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፣ እንጀራ እንዲሆኑ እነዚህን ድንጋዮች እዘዛቸው›› አለው፡፡ 4 ኢየሱስ ግን መለሰና፣ ‹‹ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣው ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል" አለው፡፡ 5 ከዚያም ዲያብሎስ ወደ ቅድስቲቱ ከተማ ወሰደው፤ በቤተ መቅደስ ሕንጻ ዐናት ላይም አቁሞ፣ 6 የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፣ ራስህን ወደ ታች ወርውር፤ ‹እንዲጠብቁህ መላእክቱን ይልካል፣› እና ‹‹እግርህ ድንጋይ እንዳይመታው፣ በእጆቻቸው ያነሡሃል›› ተብሎ ተጽፎአል አለው፡፡ 7 ኢየሱስም፣ ‹‹‹ጌታ አምላክህን አትፈታተን› ተብሎም ተጽፎአል›› አለው፡፡ 8 እንደ ገናም ዲያብሎስ ወደ አንድ ተራራ ወሰደውና የዓለምን መንግሥታት ሁሉ ከሙሉ ክብራቸው ጋር አሳየው፡፡ 9 ‹‹ብትወድቅና ብትሰግድልኝ፣ እነዚህን ሁሉ እሰጥሃለሁ›› አለው፡፡ 10 ከዚያም ኢየሱስ፣ አንተ ሰይጣን ከዚህ ሂድ! ‹ለጌታ ለአምላክህ ስገድ፣ እርሱንም ብቻ አምልክ››› ተብሎ ተጽፎአልና አለው፡፡ 11 ከዚያ በኋላ ዲያብሎስ ተወው፤ እነሆም፣ መላእክት መጡና ኢየሱስን አገለገሉት፡፡ 12 ኢየሱስ የዮሐንስን መያዝ ሲሰማ፣ ወደ ገሊላ ሄደ፡፡ 13 ናዝሬትን ትቶ በመሄድ በዛብሎንና በንፍታሌም አገር በገሊላ ባሕር አጠገብ ባለው በቅፍርናሆም ኖረ፡፡ 14 ይህ የሆነው፣ በነቢዩ ኢሳይያስ ተነግሮ የነበረው እንዲፈጸም ነው፤ ይኸውም፡- 15 ‹‹የዛብሎን ምድርና የንፍታሌም ምድር፣ በባሕሩ አቅጣጫ፣ ከዮርዳኖስ ማዶ፣ የአሕዛብ ገሊላ! 16 በጨለማ ውስጥ የኖረ ሕዝብ ታላቅ ብርሃን አየ፣ በሞት ጥላና ምድር ውስጥ ለሚኖሩትም፣ ብርሃን ወጣላቸው›› የሚለው ነው፡፡ 17 ኢየሱስ ከዚያ ጊዜ አንሥቶ፣ ‹‹መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ›› እያለ መስበክ ጀመረ፡፡ 18 ኢየሱስ በገሊላ ባሕር አጠገብ እየሄደ ሳለ፣ ሁለት ወንድማማቾችን አየ፤ ጴጥሮስ ተብሎ የሚጠራው ስምዖንና ወንድሙ እንድርያስ ዓሣ አጥማጆች ስለ ነበሩ፣ ወደ ባሕሩ መረብ እየጣሉ ነበር፡፡ 19 ኢየሱስ፣ ‹‹ኑ፣ ተከተሉኝ፤ ሰዎችን የምታጠምዱ አደርጋችኋለሁ›› አላቸው፡፡ 20 እነርሱም ወዲያውኑ መረባቸውን ትተው ተከተሉት፡፡ 21 ኢየሱስ ከዚያ ዐለፍ እንዳለም ሁለት ሌሎች ወንድማማቾችን፣ የዘብዴዎስን ልጅ ያዕቆብንና ወንድሙን ዮሐንስን አየ፤ ከአባታቸው ከዘብዴዎስ ጋር በጀልባ ውስጥ መረቦቻቸውን ያበጃጁ ነበር፡፡ ኢየሱስም ጠራቸው፡፡ 22 ወዲያውኑ ጀልባዋንና አባታቸውን ትተው ተከተሉት፡፡ 23 ኢየሱስ በምኵራቦቻቸው ውስጥ እያስተማረ፣ የመንግሥትን ወንጌልም እየሰበከና በሕዝቡ መካከል ያሉ በሁሉም የደዌና የበሽታ ዐይነት የሚሠቃዩትን እየፈወሰ በመላው ገሊላ ተዘዋወረ፡፡ 24 ስለ እርሱ በሶርያ ምድር ሁሉ ተወራ፤ ሕዝቡም የታመሙትን ሁሉ፣ በልዩ ልዩ ደዌና ሕመም የሚሠቃዩትን፣ በአጋንንት የተያዙትንና የሚጥል በሽታ ያለባቸውን፣ ሽባዎችንም ወደ እርሱ አመጡ፤ እርሱም ፈወሳቸው፡፡ 25 ከገሊላ፣ ከዐሥሩ ከተሞች፣ ከኢየሩሳሌም፣ ከይሁዳና ከዮርዳኖስ ወንዝ ማዶ እጅግ ብዙ ሕዝብ ተከተሉት፡፡
አጠቃላይ መረጃ በዚህ ሥፍራ ላይ ጸሐፊው ኢየሱስ በምድረ በዳ 40 ቀናትን ያሳለፈበትን፣ በሴጣን የተፈተነበትን የታሪኩን አዲስ ክፍል ይጀምራል፡፡ በቁጥር 4 ላይ ኢየሱስ ከዘዳግም መጽሐፍ በተወሰዱ ጥቅሶች አማካኝነት ሴጣንን ስገስጸው እንመለከታለን፡፡ ኢየሱስ በመንፈስ ተመርቶ
ይህ በቀጥታ በዚህ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “መንፈስ ኢየሱስን መራው፡፡” ( ተመልከት) በዳብሎስ ይፈተን ዘንድ ይህ በቀጥታ በዚህ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ዳብሎስ እርሱን መፈተን ይችል ዘንድ፡፡” ( ተመልከት) ዳቢሎስ . . . ፈታኙ እነዚህ ሁለት ቃላት የሚያመለክቱት አንድ ነው፡፡ እነዚህ ሁለቱን ለመተርጎም አንድ ቃል መጠቀም ትችላላችሁ፡፡ ጾመ . . . ተራበ ይህ ስለኢየሱስ የተባለ ነው፡፡ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ እዘዝ የዚህ ሀረግ አማራጭ ትርጓሜዎች 1) ይህ ፈተና ኢየሱስ ለራሱ ጥቅም ተዓምራትን ይሠራ ዘንድ የቀረበ ፈተና ነው፡፡ ኤቲ፡ “አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ስለዚህ ማዘዝ ትችላለህ፡፡” 2) ይህ የሚያመለክተው በኢየሱስ ላይ የቀረበውን ክስ ነው፡፡ ኤቲ፡ “የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህ ትዕዛዝ በመስጠት አረጋግጥ፡፡” ሴጣን ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ እንደሚያውቅ ማሰቡ ይበልጥ ተመራጭ ነው፡፡
የእግዚአብሔር ልጅ ይህ በኢየሱስ እና በእግዚአብሔር መካከሎ ያለውን ግንኙነት የሚገልጽ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) ድንጋዩ ዳቦ እዲሆን እዘዝ ይህንን በቀጥጣ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ለእነዚህ ድንጋዮች እንዲህ ብለህ ተናገር፣ ዳቦ ሁኑ!” ( ተመልከት)
ዳቦ ኤቲ፡ “ምግብ” ( ተመልከት)
እንዲህ ተብሎ ተጽፏል ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ሙሴ ከብዙ ዘመናት በፊት እንዲህ በማለት ጽፏል፡፡” ( ተመልከት)
የሰው ልጅ በዳቦ ብቻ አይኖርም ይህ በቀላሉ በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ ከምግብ በላይ ሌላ በጣም አስፈላጊ ነገር አለ ማለት ነው፡፡
ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ማንኛውም ቃ እንጂ በዚህ ሥፍራ “ቃል” እና “አፍ” የሚሉ ቃላት እግዚአብሔር የተናገራቸውን ነገሮችን ያመለክታሉ፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር የተናገራቸውን ነገሮች በማድመጥ እንጂ፡፡” ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጥር 6 ላይ ሴጣን ከመዝሙረ ዳዊት መጽሐፍ ውስጥ ኢየሱስን ለመፈተን ሲል የሆነ ሀሳብ ስወስድ እናያለን፡፡
አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ራስህን ወደታች ወርውር የዚህ ሀረግ አማራጭ ትርጉሞች 1) 1) ይህ ፈተና ኢየሱስ ለራሱ ጥቅም ተዓምራትን ይሠራ ዘንድ የቀረበ ፈተና ነው፡፡ ኤቲ፡ “አንተ የእግዚአብሔር ልጅ በመሆንህ ራስህን ወደታች መወርወር ትችላለህ፡፡” ወይም 2) ይህ የሚያመለክተው በኢየሱስ ላይ የቀረበውን ክስ ነው፡፡ ኤቲ፡ “አንተ በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ስለመሆንህ ራስህን ወደታች በመወርወር አረጋግጥ፡፡” (UDB) ሴጣን ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ እንደሚያውቅ ማሰቡ ይበልጥ ተመራጭ ነው፡፡
የእግዚአብሔር ልጅ ይህ በኢየሱስ እና በእግዚአብሔር መካከሎ ያለውን ግንኙነት የሚገልጽ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
ራስህን ወደታች ወርውር “ወደታች ራስህን ወርውረህ ውደቅ” ወይም “ወደታች ዝለል”
እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና ይህ በዚህ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “መዝሙረኛው በመመጽሐፉ ውስጥ አንዲህ ብሎ ጽፏልና” ወይም “በቅዱሳት መጽሐፍ ውስጥ እንዲህ ተብሏልና፡፡” ( ተመልከት)
ይጠብቁህ ዘንድ መልአክቱን ስለአንተ ያዛልና “አንተን እንዲጠብቁህ እግዚአብሔር መልአክቱን ስለአንተ ያዛል፡፡” ይህ እንዲህ ተብሎ በትምህረተ ጥቅስ ውስጥ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ለመልአክቱ እንዲህ ይላቸዋል፣ “ጠብቁት፡፡” ( ተመልከት)
ያነሱሃል “መልአክቱ ይይዙሃል”
አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጥር 7 ላይ ኢየሱስ ሴጣንን የገሰጸው ከዘዳግም መጽሐፍ ውስጥ በተወሰደ ጥቅ አማካኝነት ነው፡፡
እንደገና እንዲህ ተብሎ ተጽፏል ኢየሱስ እንዲህ ማለቱ እንደገና ከመጽሐፍ ቅዱስ መጥቀሱን የሚያመለክት ነው፡፡ ኤቲ፡ “እንደገና ሙሴ በቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ የጻፈውን ነገር እነግርሃለሁ፡፡” ( እና ተመልከት)
አትፈታተኑት በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ማንኛውንም ሰው ነው፡፡ ኤቲ፡ “ማንም እርሱን መፈታተን የለበትም” ወይም “ማንኛውም ሰው እርሱን መፈታተን የለበትም፡፡”
እንደገና ዳቢሎስ “በመቀጠልም ዳቢሎስ”
እንዲህ አለው “ዳቢሎስ ኢየሱስን እንዲህ አለው፡፡”
እነዚህን ነገሮች ሁሉ እሰጥሃለሁ፡፡ “እነዚህ ነገሮች ሁሉ እሰጥሃለሁ፡፡” ፈታኙ አንዳንዶቹን ሳይሆን “ሁሉንም ነገሮች” እንደሚሰጠው አጽኖት ሰጥቶዋል፡፡”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ይህ ሴጣን ኢየሱስን እንዴት እንደፈተነው የሚያወሳው ታሪክ የመጨረሻው ክፍል ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጥር 10 ላይ ኢየሱስ ከዘዳግም መጽሐፍ ውስጥ በመውሰድ ሴጣንን ገስጾታል፡፡
እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና ይህ በዚህ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “መዝሙረኛው በመመጽሐፉ ውስጥ አንዲህ ብሎ ጽፏልና” ወይም “በቅዱሳት መጽሐፍ ውስጥ እንዲህ ተብሏልና፡፡” ( ተመልከት)
አንተ አለብህ በዚህ ሥፍራ “አንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ማንኛውንም ሰው ነው፡፡ ( ተመልከት)
እነሆ “እነሆ” የሚለው ቃል ከዚህ በመቀጠል የሚሰጠው መረጃ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን የሚያመለክት ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃዎች፡ ይህ ኢየሱስ በገሊላ አገልግሎቱን የጀመረበትን መንገድ ጸሐፊው የገለጸበት አዲሱ የታሪኩክፍል ጅማሬ ነው፡፡ እነዚህ ጥቅሶች ኢየሱስ እንዴት ወደ ገሊላ እንደመጣ ያብራራሉ፡፡ ( ተመልከት)
አሁን ይህ ቃል በታሪኩ ፍሰት ውስጥ ያለውን ክፍተት ለማሳየት ጥቅም ላይ የዋሉ ናቸው፡፡ ማቴዎስ በዚህ ሥፍራ ላይ የታሪኩን አንዲስ ጅማሬ ክፍል ይናገራል፡፡ ዮሐንስ ተሠረ ይህ በቀጥታ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ንጉሡ ዮሐንስን አሠረው፡፡” ( ተመልከት)
በዛብሎን እና ንፍታሌን አገር እነዚህ ከብዙ ዓመታት በፊት ከሌላ ሀገር የመጡ ሰዎች ቦታወን ከመቆጣጠራቸው በፊት በእነዚህ ሥፍራዎች ይኖሩ የነበሩ ጎሣዎች ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጥር 15 እና 16 ላይ ኢየሱስ በገሊላ የነበረው አገልግሎት ከዚህ በፊት ተነግሮ የነበረ ትንቢት ፍጻሜ መሆኑን ለማሳየት ጸሐፊው ከነብዩ ኢሳያስ መጽሐፍ ይጠቅሳል፡፡
እንዲህም ሆነ ይህ ኢየሱስ ቅፍርናሆም ወደ ተሰኘው መንደር ለመኖር መምጣቱን ያመለክታል፡፡
ከዚህ በፊት እንደተነገረው ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር እንደተናገረው፡፡” ( ተመልከት)
የዛብሎን እና የንፍታሌን አገር . . . የአሕዛብ ገሊላ እነዚህ ሁሉ ስሞች አንድን አከባቢ የሚያመለክቱ ናቸው፡፡ ይህ በአንድ ዓረፍተ ነገር ሊተረጎም ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “በዛብሎን እና ንፍታሌን አገር . . . ብዙ አሕዛብ የሚኖሩበት የገሊላ መንድ፡፡”
በባሕር መንገድ ይህ የገሊላን ባሕርን ያመለክታል፡፡
በጨለማ የተቀመጠ ሕዝብ ታላቅ ብርሃንን አየ በዚህ ሥፍራ “ብርሃን” የሚለው ቃል ግብረገባዊ ጨለማን ወይም ሰዎችን ከእግዚአብሔር የለየውን ኃጢአትን የሚያመለክት ነው፡፡ ይህ አሁን ከእግዚአብሔር ዘንድ ተስፋን ያገኙ ነገር ግን አስቀድሞ ምንም ተስፋ ያልነበራቸውን ሕዝቦች ያሳያል፡፡ ( ተመልከት)
በዚያ አከባቢ የሚኖሩ እና በሞት ጥላ ሥር ላሉ ሕዝቦች ብርሃን ወጣላቸው ይህ ከመጀመሪያው የዓረፍተ ነገሩ ክፍል ጋር ተመሳሳይ ትርጉም አለው፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ “አከባቢ እና በሞት ጥላ ሥር” የሚለው ሀረግ የሚያመለክተው መንፈሳዊ ሞት ወይም ከእግዚአብሔር መለየት ነው፡፡ ( እና ተመልከት)
መንግስተ ሰማያት ቀርባለችና ንሰሓ ግቡ ይህን በ MAT 3:2 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
አጠቃላይ መረጃ ይህ በታሪኩ ውስጥ ኢየሱስ በገሊላ ስለነበረው አገልግሎት አስመልክቶ አዲስ ታሪክ የተጀመረበት ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ሰዎች የእርሱ ደቀ መዛሙርት ይሆኑ ዘንድ መሰብሰብ ጀመረ፡፡
መረባቸውን ወደ ባሕሩ ይጥሉ ነበር ኤቲ፡ “ዓሳ ለማጥመድ መረባቸውን ወደ ውሃው ውሰጥ ይጨምሩ” ( ተመልከት)
ተከተሉኝ ኢየሱስ ጴጥሮስ እና እንድርያስን ይከተሉት፣ ከእርሱ ጋር ይኖሩ እና የእርሱ ደቀ መዛሙርት ይሆኑ ዘንድ ጠራቸው፡፡ ኤቲ፡ “ደቀ መዛሙርቴ ሁኑ፡፡” ሰዎችን የሚታጠምዱ አደርጋችኋለሁ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ጴጥሮስ እና እንድርያስ እውነተኛውን መልዕክት ለእግዚአብሔርን ሕዝብ በማስተማሪ ሌሎችም ደግሞ ኢየሱስን እንዲከተሉ ያደርጋሉ፡፡ ኤቲ፡ “ዓሳ ታጠምዱ በነበረበት መንገድ እናንተም ሰዎችን እንዴት መሰብሰብ እንደሚትችል አስተምራችኋለሁ፡፡” ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ ይሆኑ ዘንድ ተጨማሪ ሰዎችን ጠራ፡፡
ጠራቸው “ኢየሱስ ዮሐንስ እና ያዕቆብን ጠራቸው፡፡” ይህ ሀረግም ኢየሱስ ይከተሉት፣ ከእርሱ ጋር ይኖሩ እና የእርሱ ደቀ መዛሙርት ይሆኑ ዘነድ ጠራቸው ማለት ነው፡፡
ወዲያውኑ “በዚያኑ ጊዜ”
ታንኳቸውን ትተው . . እና ተከተሉት ይህ የሕይወት ዘይቤ ለውጥ መሆኑን መግለጽ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ወደ ዓሳ አጥማጅነታቸው እና የቤተሰባቸውን ሥራ ከዚያን ጊዜ ጀምረው በሕይወታቸው ዘመን ሁሉ ኢየሱስን ለመከተል ትተዋለል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ይህ ኢየሱስ በገሊላ የጀመረው አገክግሎት ታሪክ የመጨረሻው ክፍል ነው፡፡ እነዚህ ቁጥሮች ምን እንዳደረገ እና ሰዎች የሰጡት ምላሽ ምን እንደሆነ ጠቅለል አድርጎ ያሳየናል፡፡ ([[End of Story]] ተመልከት)
በምኩራቦቻቸው እያስተማረ “በገሊላ ውስጥ በሚገኙ ምኩራቦች ውስጥ እያስተማረ” ወይም “በእነዚህ ሰዎች ምኩራብ ውስጥ እያስተማረ፡፡”
የመንግስቱን ወንጌል እየሰበከ በዚህ ሥፍራ ላይ “መንግስት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚብሔር ንጉሥ ሆኖ መንገሡን ነው፡፡ ኤቲ፡ “ወንጌልን ማለትም እግዚአብሔር እንዴት ራሱን ንጉሥ አድርጎ እንደገለጠ እየሰበከ” (UDB) ( ተመልከት)
ሁሉንም ዓይነት በሽታዎች እና ደዌዎች “ማንኛውንም በሽታ እና ደዌ፡፡” “በሽታ” እና “ደዌ” የሚሉት ቃላት በጣም የተቀራረቡ ናቸው ነገር ግን ከተቻለ በሁለት የተያዩ ቃላት አማካኝነት ቢተረጎሙ መልካም ነው፡፡ “በሽታ” አንድ ሰው አንዲታመም የሚያደርገው ነገር ነው፡፡ “ደዌ” አካላዊ ድክመት ወይም በሽተኛ በመሆን በአካል ላይ የሚሆን ህመም ነው፡፡
በዳቢሎስ የተያዙ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “በዳቢሎስ የተያዘ” ወይም “ዳቢሎስ የተቆጣጠራቸው፡፡” ( ተመልከት) የሚጥል በሽታ “የሚጥል በሽታ ያለባቸው” ወይም “ካለባቸው በሽታ የተነሳ የሚወድቁትን”
ሽባዎችን “መራመድ የማይችሉትን” ከዐሥሩም ከተሞች ይህ “ዐሥር ከተማዎች” ስም ነው፡፡ ." (UDB) ይህ ከገሊላ ባሕር በደቡብ ምስራቅ በኩሉ የሚገኘውን አከባቢ መጠሪያ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
1 ኢየሱስ ሕዝቡን ሲያይ፣ ወደ ተራራ ወጣ፤ እዚያም ሲቀመጥ ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ መጡ። 2 እንደዚህ እያለም አስተማራቸው፤ 3 በመንፈስ የደኸዩ የተባረኩ ናቸው፤ መንግሥተ ሰማይ የእነርሱ ናትና። 4 የሚያዝኑ የተባረኩ ናቸው፤ ይጽናናሉና። 5 የዋሆች የተባረኩ ናቸው፤ ምድርን ይወርሳሉና። 6 ለጽድቅ የሚራቡና የሚጠሙ የተባረኩ ናቸው፤ ይጠግባሉና። 7 የሚምሩ የተባረኩ ናቸው፤ ይማራሉና። 8 ልበ ንጹሖች የተባረኩ ናቸው እግዚአብሔርን ያዩታልና። 9 የሚያስታርቁ የተባረኩ ናቸው፤ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና። 10 ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ የተባረኩ ናቸው፤ መንግሥተ ሰማይ የእነርሱ ናትና። 11 ሰዎች ሲሰድቧችሁና ሲያሳድዷችሁ፣ ወይም በእኔ የተነሣ ክፉውን ሁሉ በእናንተ ላይ በሐሰት ሲናገሩ ብፁዓን ናችሁ። 12 በሰማይ ዋጋችሁ ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ፣ ሐሤትም አድርጉ። ሰዎች ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያት በዚህ መንገድ አሳድደዋቸዋልና። 13 እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው ጣዕሙን ካጣ፣ እንደ ገና ጨው እንዴት መሆን ይችላል? ወደ ውጭ ተጥሎ በእግር ከመረገጥ በቀር ፈጽሞ ለምንም አይጠቅምም። 14 እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ የተመሠረተች ከተማ ልትሰወር አትችልም። 15 ሰዎች መብራት አብርተው ቤት ውስጥ ላሉት ሁሉ እንዲበራ በመቅረዝ ላይ ያስቀምጡታል እንጂ በቅርጫት ሥር አያስቀምጡትም። 16 መልካሙን ሥራችሁን እንዲያዩና በሰማይ ያለ አባታችሁን እንዲያከብሩት መብራታችሁ እንዲሁ በሰዎች ፊት ይብራ። 17 ሕግንና ነቢያትን ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ የመጣሁት ልሽራቸው ሳይሆን ልፈጽማቸው ነው። 18 ምክንያቱም፣ ሰማይና ምድር እስኪያልፍ፣ ሁሉ እስኪፈጸምም ድረስ፣ ከሕግ እንዷ ፊደል ወይም ቅንጣት ከቶ አታልፍም ብዬ በእውነት እነግራችኋለሁ። 19 እንግዲህ ከእነዚህ ትእዛዞች ትንሿን የሚሽርና ለሌሎችም እንዲሁ እንዲያደርጉ የሚያስተምር፣ በመንግሥተ ሰማይ ታናሽ ይባላል። የሚጠብቃቸውና የሚያስተምራቸው ግን በመንግሥተ ሰማይ ታላቅ ይባላል። 20 ምክንያቱም፣ ጽድቃችሁ ከሕግ መምህራንና ከፈሪሳውያን ጽድቅ ልቆ ካልተገኘ መንግሥተ ሰማይ ከቶ አትገቡም እላችኋለሁ። 21 ለቀደሙት፣ 'አትግደል፣ የገደለ ይፈረድበታል' እንደ ተባለ ሰምታችኋል። 22 እኔ ግን፣ 'ወንድሙን የሚቆጣ ሁሉ ይፈረድበታል፣ ወንድሙን፣ 'አንተ የማትረባ!' የሚለው የሸንጎ ፍርድ፣ 'ቂል' የሚለውም የገሃነመ እሳት ፍርድ ይፈረድበታል። 23 እንግዲህ መባህን በመሠዊያው ላይ ልታቀርብ ከሆነና ወንድምህ አንዳች ነገር በአንተ ላይ እንዳለው ካስታወስህ፣ 24 መባህን በመሠዊያው ፊት ትተህ ሂድ፣ በቅድሚያ ከወንድምህ ጋር ታረቅ፣ ከዚያም ተመልሰህ መጥተህ መባህን አቅርብ። 25 ባላጋራህ ለዳኛው፣ ዳኛውም ለአሳሪው አሳልፎ እንዳይሰጥህና በወህኒ ውስጥ እንዳትጣል፣ ወደ ፍርድ ቤት ዐብረኸው እየሄድህ ሳለ ከሚከስስህ ባላጋራህ ጋር በፍጥነት ተስማማ። 26 እውነት እነግርሃለሁ፣ የመጨረሻዋን ሳንቲም እስክትከፍል ድረስ ከዚያ ፈጽሞ አትወጣም። 27 "አታመንዝር" እንደ ተባለ ሰምታችኋል፤ 28 እኔ ግን፣ ሴትን ተመኝቷት የሚመለከት ሁሉ በልቡ አመንዝሯል እላችኋለሁ። 29 የቀኝ ዐይንህ ቢያሰናክህል አውጥተህ ጣለው፤ መላ ሰውነትህ በገሃነም ከሚቃጠል፣ ከሰውነትህ ክፍሎች አንዱ ቢጠፋ ይሻልሃልና። 30 የቀኝ እጅህም ቢያሰናክልህ ቆርጠህ ጣለው፤ መላ ሰውነትህ ገሃነም ውስጥ ከሚገባ ከሰውነትህ ክፍሎች አንዱ ቢጠፋ ይሻልሃል። 31 'ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ የፍቺ ማረጋገጫ ይስጣት' ተብሎአል። 32 እኔ ግን፣ 'በዝሙት ምክንያት ካልሆነ በቀር ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ፣ እንድታመንዝር ያደርጋታል፤ ከተፈታች በኋላ የሚያገባትም ምንዝርና ይፈጽማል። 33 ደግሞም ለቀደሙት፣ በሐሰት አትማል፣ መሐላዎችህንም ለጌታ ስጥ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። 34 እኔ ግን ከቶ አትማሉ፤ በሰማይም፣ የእግዚአብሔር ዙፋን ነውና፤ 35 በምድርም፣ እግሩ የሚያርፍባት ናትና፤ በኢየሩሳሌምም፣ የታላቁ ንጉሥ ከተማ ናትና። 36 በራሳችሁም አትማሉ፤ አንዷን ጠጕር ነጭ ወይም ጥቍር ማድረግ አትችሉምና። 37 ነገር ግን ንግግራችሁ 'አዎ፣ አዎ'፣ ወይም 'አይደለም፣ አይደለም' ይሁን። ከዚህ የወጣ ሁሉ ከክፉው ነው። 38 ዐይን ስለ ዐይን፣ ጥርስ ስለ ጥርስ እንደ ተባለ ሰምታችኋል፣ 39 እኔ ግን እላችኋለሁ፣ 'ክፉውን ሰው አትቃወሙት፣ ይልቁን የቀኝ ጕንጭህን ለሚመታህ ሌላውንም አዙርለት። 40 ማንም ሰው ሊከስስህና ኮትህን ሊወስድ ቢመኝ፣ ካባህንም ይውሰድ። 41 አንድ ምዕራፍ እንድትሄድ ማንም ሰው ቢያስገድድህ፣ ዐብረኸው ሁለት ምዕራፍ ሂድ። 42 ለሚለምንህ ሁሉ ስጥ፣ ከአንተ መበደር ከሚፈልገውም ፊትህን አታዙር። 43 ባልንጀራህን ውደድ፣ ጠላትህንም ጥላ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። 44 እኔ ግን ጠላቶችህን ውደድ ለሚያሳድዷችሁም ጸልዩ ብዬ እነግራችኋለሁ። 45 ይኸውም በሰማያት ያለ አባታችሁ ልጆች እንድትሆኑ ነው። እርሱ ፀሐይን በክፉዎችና በደጎች ላይ ያወጣል፤ ዝናብም በጻድቃንና በኅጥኣን ላይ ያዘንባል። 46 የሚወድዷችሁን ብትወዱ፣ ምን ዋጋ ታገኛላችሁ? ቀራጮች እንኳ እንደዚህ ያደርጉ የለምን? 47 ለወንድሞቻችሁ ብቻ ሰላምታ ብታቀርቡ፣ ከሌሎች የበለጠ የምታደርጉት ምንድን ነው? አሕዛብስ እንኳ ይህንኑ ያደርጉ የለምን? 48 እንግዲህ የሰማይ አባታችሁ ፍጹም እንደ ሆነ እናንተም ፍጹማን ሁኑ።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ይህ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ማስመተማር የጀመረበት አዲስ ታሪክ ጅማሬ ክፍል ነው፡፡ ይህ ክፍል እስከ ምዕራፍ 7 ድረስ ይቀጥላል እንዲሁም ብዙ ጊዜም የተራራው ስብከት ተብሎ ይጠራል፡፡
አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጥር 3 ላይ ኢየሱስ የተባረኩ ሰዎች ባሕርያት ምን ምን እንደሆኑ መግለጽ ይጀምራል፡፡
አፉን ከፍቶ ኤቲ፡ “ኢየሱስ መናገር ጀመረ” ( ተመልከት)
አስተማራቸው “እነርሱን” የሚለው ቃል ደቀ መዛሙርቱን የሚያመለክት ነው፡፡
በመንፈሰስ ድሆች ይህ ማለት ትሁት የሆነ ማለት ነው፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር እንደሚያስፈልጋቸው ያወቁ፡፡” ( ተመልከት)
መንግስተ ሰማያት የእነርሱ ናትና በዚህ ሥፍራ ላይ “መንግስተ ሰማየት” የሚያመለክተው እግዚአብሔር እንደ ንጉሥ መግዛቱን፡፡ ይህ ሀረግ በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ ብቻ ነው የሚገኘው፡፡ ከተቻለ በትርጉማችሁ ውስጥ “ሰማይ” የሚለው ቃል እንዲኖር አድርጉ፡፡ ኤቲ፡ “በሰማይ ያለው እግዚአብሔር ንጉሣቸው ይሆናልና፡፡” ( ተመልከት)
የሚያለቅሱ ያዘኑበት ምክንያት ሊሆን የሚችለው 1) በዚህ ዓለም ኃጢአት ወይም 2) በራሳቸው ኃጢአት ወይም 3) በሌላ ሰው ሞት ምክንያት፡፡ ቋንቋችሁ ካላስገደዳችሁ በስቀተር ምክንያቱን አትግለጹ፡፡
ይጽናናሉና ይህ እንዲህ በቀጥታ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ያጽናናቸዋል፡፡” ( ተመልከት)
የዋሆች “ትሁታን” ወይም “በራሳቸው ኃይል የማይታመኑት”
ምድርን ይወርሳሉ “እግዚአብሔር ምድርን ሁሉ ይሰጣቸዋል”
ጽድቅን የሚራቡ እና የሚጠሙ ይህ ምሳሌያዊ አነጋገር ትክክለኛውን ነገር ለማድረግ ከልቡ የሚሻ ሰው ማለት ነው፡፡ ኤቲ፡ “ውሃ እና ምግብን ሰው እንደሚሻ ሁሉ በጽድቅ ለመኖር የሚሹ” ( ተመልከት)
ይሞላሉ ይህ እንዲህ ተብሎ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ይሞላቸዋ” ወይም “እግዚብሔር ያረካቸዋል፡፡” : ( ተመልከት)
ልበ ንጹሖች
“ልባቸው ንጹሕ የሆኑ ሰዎች፡፡” በዚህ ሥፍራ “ልብ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የአንድ ሰውን ፍላጎት ነው፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔርን ለማገልገል የሚፈልጉ ሰዎች፡፡” ( ተመልከት)
እግዚአብሔርን ያዩታል በዚህ ሥፍራ ላይ “ማየት” የሚለው ቃል በእግዚአብሔር መገኘት ውስጥ መኖር መቻልን የሚያመለክት ነው፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር መኖር እንዲችሉ ይፈቅድላቸዋል፡፡”
አስታራቂዎች እነዚህ ሌሎች ሰዎች እርስ በእርሳቸው ሰላም እንዲሆኑየሚያግዙ ሰዎችን ናቸው፡፡ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና ይህ በእንዲህ ዓይነት መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ልጆቼ ብሎ ይጠራቸዋልና” ወይም “የእግዚአብሔር ልጆች ይሆናሉና፡፡” (: ተመልከት)
የእግዚአብሔር ልጅ “ልጆች” የሚለውን ቃል በእናንተ ቋንቋ ለሰው ልጅ ወይም ሕጻናት በተለምዶ የሚትጠቀምበትን ተመሳሳይ ቃላት መጠቀሙ ጥሩ ነው፡፡
የሚሰደዱ ይህ በቀጥታ በዚህ ዓይነት መልኩ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ሌሎእ ሰዎች በተገቢው መንገድ ያልያዟቸው ሰዎች፡፡” ( ተመልከት)
ስለጽድቅ “እግዚአብሔር እንዲያደርጉ የሚፈልገውን ነገር በማድረጋቸው ምክንያት”
መንግስተ ሰማያት የእነርሱ ናትና ይህንን በ MAT 5:3 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ኢየሱስ የተባረኩ ሰዎች ባሕርያትን ማብራሩትን ጨርሷል፡፡
የተባረካቹ ናቸሁ “እናንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥር ነው፡፡ ( ተመልከት)
ስለ አንተ በውሸት ክፉ ነገሮችን ሁሉ ይናገራሉ፡፡ “ስለ አንተ ሁሉንም ዓይነት ክፉ ውሸትን ይናገራሉ” ወይም “እውነት ያልሆነ መጥፎ መጥፎ ነገሮችን ይናገራሉ”
ስለ እኔ ሲባል “እኔን በመከተልህ ምክንያት” ወይም “በእኔ በማመንህ ምክንያት”
ደስ ይበላችሁ እንዲሁም ሐሴትም አድርጉ “ደስ ይበላችሁ” እና “ሐሴት አድርጉ” የሚሉት ሁለቱ ቃላት ተመሳሳይ መልዕክቶችን የሚያስተልፉ ናቸው፡፡ ኢየሱስ አድማጮቹ ደስ ይበላችሁ ብቻ አላላቸው ነገር ግን ከተቻለ ከመደሰት በላይ እንዲያደርጉ ነግሮዋቸዋል፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እንደ ጨው እና ብርሃን ይሆኑ ዘንድ ማስተማር ጀመረ፡፡
እናንተ የምድር ጨው ናቸው አማራጭ ትርጓሜዎች 1) ጨው ለምግብት ጣእም እንደሚሰጥ ሁሉ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት በዓለም ውስጥ ያሉ ሰዎች መልካም ይሆኑ ዘንድ ተጽእኖ ፈጣሪዎች መሆን ይኖርባቸዋል ወይም 2) ልክ ጨው ምግብ ለረጅም ጊዜ ሳይበላሽ እንዲቆይ እንደሚያደረግ ሁሉ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ሰዎች ሙሉ ለሙሉ እንዳይበላሹ የሚያደርጉ ሊሆኑ ይባል፡፡ ኤቲ፡ “ለዓለም ሕዝቦች እናንተ ልክ እንደ ጨው ናችሁ” ወይም “ጨው ለምግብ እንደሆነ ሁሉ እናንተም ለዓለም እንደዚሁ ናችሁ፡፡” ( ተመልከት)
ጨው ጣእሙን ካጣ አማራጭ ትርጉሞች 1) “ጨው ጨው የሚሠራውን ነገር መሠርት የሚያስችለውን ኃይሉን ካጣ” ((UDB) ወይም 2) “ጨው ጣዕሙን ካጣ፡፡” ( ተመልከት)
እንዴት ጨው የሚሰጠውን ጥቅም ሊሰጥ ይችላል? “እንደገና እንዴት ጠቃሚ ሊሆን ይችላል?” ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለማስተማር ጥያቄን ይጠቀማል፡፡ ኤቲ፡ “አንደገና ጠቃሚ መሆን የሚችልበት ምንም ዓይነት መንገድ የለም፡፡” ( እና ተመልከት)
ወደ ውጪ ከመጣል እና በሰዎች ከመረገጥ በስቀር ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡ ኤቲ፡ “በመንገድ ዳር ይጥሉታል፤ ሰዎችም ይረጋግጡታል፡፡” (See: ተመልከት)
እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ ይህም ማለት የኢየሱስ ተከታዮች የእግዚአበብሔር እውነት ያለበትን መልዕክት እግዚብሔርን ወደ ማያውቁት ሰዎች ሁሉ ድረስ የሚያደርሱ ናቸው፡፡ ኤቲ፡ “እናንተ በዓለም ውስጥ ላሉ ሰዎች ልክ እንደ ብርሃን ናችሁ፡፡” (See: ተመልከት)
በተራራ ላይ ያለች ከተማ ፈጽሞ ልትደበቅ አትችልም ይህ ሰዎች የከተማዋን ብርሃን በምሽት መመልከት ይችላሉ ማለት ነው፡፡ ይህ በቀጥታ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “በምሽት በተራራ ላይ ያለች ከተማን ብርሃን ማንም ሰው ሊከልል አይችልም፡፡ ( እና ተመልከት)
መብራት የሚያበራ ሰውም እንዲሁ “ሰዎች መብራትን እንዲሁ አብርቶ
ከእንቅብ በታች አያኖረውም “መብራቱን ከቅርጫት በታች አያኖረውምለለ”፡፡ ይህ ማለት መብራን አብርቶ ሰዎች እንዳያዩት መደበቅ ሞኝነት ነው የሚል ነግግር ነው፡፡
ብርሃናችሁ በሰዎች ሁሉ ፊት ያብራ ይህ ማለት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ሌሎች ሰዎች የእግዚአብሔር እውነት ከእነርሱ መማር በሚችሉበት መንገድ መኖር አለባቸው ማለት ነው፡፡ ኤቲ፡ “ሕይወታችሁ ልክ እንደ መብራት በሰዎች ፊት ይብራ፡፡” ( ተመልከት)
በሰማይ የሚኖረው አባታችሁ “አባት” የሚለውን ቃል በጥሩ ሁኔታ ለመተርጎም በቋንቋችሁ ውስጥ አንድን አባት ለመጥራት የሚትጠቀሙትን ቃል ተጠቀሙ፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ኢየሱስ በብሉይ ኪዳን መጽሕፍት ውስጥ የተጻፉትን ሕግጋት ለመፈጸም እንደመጣ ማስተማሪ ጀመረ፡፡ ነቢያት ይህ ነቢያት በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የጻፏቸውን መጽሐፍትን ያመለክታል፡፡ ( ተመልከት) እውነት እላችኋለሁ “እውነት እላችኋለሁ፡፡” ይህ ሀረግ ኢየሱስ ቀጥሎሊናገረው ያለው ሀሳብ አጽኖት ልሰጥበት የሚገባ መሆኑን ያመለክታል፡፡ ሰማይና ምድር ያልፋሉ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር የፈጠራቸው ነገሮች ሁሉ ያልፋሉ፡፡” ( ተመልከት) አንድት ነጥብ “ከፊደል ትንሸዋ እንኳ ሳትቀር፡፡ ይህ ከቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ በሰዎች ይህንን ያኸለ አስፈላጊ አይደሉም ተብሎ የሚቆጠሩት እንኳ ሳይቀሩ የሚለውን ለማሳየት የቀረበበ ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ ኤቲ፡ “አስፈላጊ የማይመስሉ ሕግጋት እንኳ ሳይቀሩ”፡፡ ( ተመልከት) ሁሉ ነገር ይፈጸማል ይህ በግልጽ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር በሕግ ውስጥ የተጻፉትን ነገሮች ሁሉ ፈጽሟል፡፡ ( ተመልከት)
የተላለፈ ማንኛውም ሰው “የማይታዘዝ ማንኛውም ሰው” ወይም “ሳይታዘዝ የቀረ ማንኛውም ሰው” ከእነዚህ ትዕዛዛት መካከል ትንሹን “ከእነዝህ ትዕዛዛት መካከል፣ ጥቅሟ በጣም ትንሽ የሆነችውን ትዕዛዛ እንኳ ሳይቀር” ተብሎ ይጠራል ይህ እንዲህ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ያንን ሰው አግዚአብሔር እንዲህ ብሎ ይጠራዋል፡፡” ( ተመልከት) በመንግስተ ሰማይ ውስጥ ትንሽ “መንግስተ ሰማይ” ሚለው ሀረግ የእግዚአብሔር አገዛዝ ያመለክታል፡፡ ይህ ሀረግ የሚገኘው በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ ብቻ ነው፡፡ የሚቻል ከሆነ “በትርጉማችሁ ውሰጥ “ሰማይ” የሚለው ቃል ተጠቀሙ፡፡ ኤቲ፡ “በመንግስተ ሰማይ ውስጥ አስፈላጊነቱ ትንሽ ይሆናል” ወይም “በሰማይ የእግዚአብሔ አገዛዝ ውስጥ ያለው ጠቀሜታ በጣም ትንሽ ይሆናል፡፡” ( ተመልከት) ጠብቋቸው እንዲሁም አስተምሯቸው “እነዚህ ትዕዛዛት ሁሉ ታዘዙ እንዲሁም ሌሎችም ይህንኑ ያደርጉ ዘንድ አስተምሯቸው፡፡” ታላቅ “በጣም አስፈላጊ” እንዲህ ብዬአችኋለሁ ይህ ኢየሱስ ከዚህ በመቀጠል ስለሚናገረው ነገር አጽኖት ይሰጣል፡፡ አንተ . . . እናንተ . . . አንተ ይህ ብዙ ቁጥርን ያመለክታል፡፡ ( ጽድቃችሁ ካልበለጥ . . . ልትገቡ አትችሉም ይህ በአዎንታዊ መንገድ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ጽድቃችሁ መብለጥ አለበት . . . ለመግባት፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍ ነገር ኢሰየሱስ የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን ለመፈጸም መምጣቱን ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ በዚህ ሥፍራ ስለ ነፍስ ማጥፋት እና ንዴት ተናግሯል፡፡ አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ ለተሰበሰቡት ሰዎች እንደ ግለሰብ እያንዳንዳቸው ምን ሊያጋጥማቸው እንደሚችል እየተናገረ ነው፡፡ “ሰምታችኋል” የሚለው ሀረግ ውስጥ ያለው “እናንተ” የሚለው ቃል እና “እላችኋለሁ” ሀረግ ብዙ ቁጥር ነው፡፡ “አትግደል” የሚለው ሀረግነጠላ ቁጥር ነው ይሁን እንጂ በብዙ ቁጥር ሊተረጎም ይችላል፡፡ በጥት ዘመን እንዲህ ተብሎ ተነግሯቸዋል ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ከብዙ ዘመናት በፊት እግዚአብሔር ተናግሮ ነበር፡፡ ( ተመልከት) ነፈስ ያጠፋ ማንኛውም ሰው ፍርድ አለበት በዚህ ሥፍራ “ፍርድ” የሚለው ቃል ይህ ሰው እንዲገደል የሚያዘውን ሕግ የሚያሳይ ነው፡፡ ኤቲ፡ “ሌላ ሰው የገደለ ማንኛው ሰው ላይ ዳጃው ይፈርዳል፡፡” ( ተመልከት) ግዲያ. . . ግድያዎች ይህ የሚያመለክተው ቃል ሆኖ ነፍስ ማጥፋት እንጂ ሁሉንም ዓይነት የግዲያ አይነቶችን አይደለም፡፡ ነገር ግን እኔ እንዲህ እላችኋለሁ “እኔ” የሚትለው ቃ አጽኖታዊ ናት፡፡ ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስ የተናገረው ነገር እግዚአብሐየር በመጀመሪያ ከሰጠው ትዕዛዝ ጋር የሚስተካከል ነው፡፡ ስትተረጉም ይህንን አጽኖት በሚያሳይ ሀረግ ለመተርጎም ሞከር፡፡ ወንድም ይህ አማኝን እንጂ በሥጋ ወንድምን ወይም ጎረበትን የሚያመለክት አይደለም፡፡ ፍርድ ይገባዋል በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ እየተናገረ ያለው ስለ ሰው ፍርድ ሳይሆን በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሰውን እግዚአብሔር የሚያመጣውን ፍርድ ነው፡፡ ( ተመልከት) እርባና የሌለው . . . ሞኝ ይህ በትክክል ማሰብ የማይችሉ ሰዎች የሚሰደቡትን ስድብ የሚያመለክት ነው፡፡ “እርባና ያሌለው” የሚለው ቃል “አእምሮ የሌለው” ከሚለው ቃል ጋር ተቀራራቢ ሲሆን “ሞኝ የሚለው ደግሞ እግዚአብሔርን አለመታዘዝ ጋር ተያያዥነት ያለው ሀሳብ ነው፡፡ ሸንጎ ይህ በኢየሩሳሌም የሚገኘው የሸንጎ ሳይሆን በአከባቢው ያለው ሸንጎ ነው፡፡
እንተ ኢየሱስ በቡድን ላሉ ሰዎች እያንዳንዳቸው ምን እንደሚያጋጥማቸው እየተናገረ ነው፡፡ “አንተ” የሚለው ቃል ነጠላ ቁጥር ነው፡፡ እናንተ ግን በቋንቋች በብዙ ቁጥር ሊትተረጉሙት ትችላላችሁ፡፡ ( ተመልከት) መባህን “ስጦታ ስትሰጥ” ወይም “ስጦታህ ስታቀርብ” በመሠዊያው ላይ ይህ በኢየሩሳሌሚ ቤተ መቅደስ ውስጥ የሚገኘውን የእግዚአብሄርን መሠዊያ የሚያመለክት ነው፡፡ ኤቲ፡ “በቤተ መቅዲስ ውስጥ በሚገኘው የእግዚአብሔር መሠዊያ ላይ፡፡” ( ተመልከት) በዚያ ሳለህ ቢታስታውስ “በመሠዊያው ፊት ቆመህ ሳለ ቢታስታውስ” ወንድምህ አንዳች ነገር ከአንተ ጋር እንዳለው “አንተ ባደረከው አንድ ነገር የተነሳ ወንድም በአንተ የተቆጣ መሆኑን ካስታወስክ” በመጀመሪያ ሂድና ከወንድምህ ጋር ታረቅ ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ከሰውዬው ጋር ሰላምን ፍጠር፡፡” ( ተመልከት)
ከአንተ . . . ጋር ተስማማ ኢየሱስ በቡድን ላሉ ሰዎች እያንዳንዳቸው ምን እንደሚያጋጥማቸው እየተናገረ ነው፡፡ “አንተ” የሚለው ቃል ነጠላ ቁጥር ነው፡፡ እናንተ ግን በቋንቋች በብዙ ቁጥር ሊትተረጉሙት ትችላላችሁ፡፡ ( ተመልከት) ከከሳሽ ጋር ይህ ሰው ሌላኛውን ሰው በደል እየነቀሰ የሚወቅስ ሰው ነው፡፡ በዳኛ ፊት ሆኖ ሌላኛው ሰው የበደለውን በደል በመናገር ይከሳል፡፡ ለዳኛ አሳልፎ ይሰጥሃል በዚህ ሥፍራ ላይ “አሳልፎ ይሰጥሃል” የሚለው ሀረግ ትርጉሙ አንድን ሰው በሌላ ሰው ቁጥጥር ሥር እንዲሆን መስጠትን ያመለክታል፡፡ ኤቲ፡ “ዳኛው በሕጉ መሠረት እንዲፈርድብህ ያደርጋል፡፡” ( ተመልከት) ዳኛውም ለወህኒ ጠባቂዎች አሳልፎ ይሰጥሃል በዚህ ሥፍራ ላይ “አሳልፎ ይሰጥሃል” የሚለው ሀረግ ትርጉሙ አንድን ሰው በሌላ ሰው ቁጥጥር ሥር እንዲሆን መስጠትን ያመለክታል፡፡ ኤቲ፡ “ዳኛውም ለወህኒ ጠበቂ አሳልፎ ይሰጥሃል፡፡” ( ተመልከት) የወህኒ ጠባቂ ይህ ሰው ሰው በዳኛው የተሰጠውን ውሳኔ የሚያስፈጽም ግለሰብ ነው፡፡ ወደ ወህኒ ትጣላለህ ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “የወህኒ ጠባቂው በወህኒ ቤት ውስጥ እንዲትታሠር ያደርጋል፡፡” ( ተመልከት) እውነት እውነት እላችኋለሁ “እውነት እውነት እላችኋለሁ”፡፡ ይህ ሀረግ ኢየሱስ ቀጥሎ ለሚናገረው ነገር አጽኖት እንዲንሰጥ ያደርገናል፡፡ ከዚያ ሥፍራም “ከወህኒ ቤት”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን ለመፈጸም መምጣቱን ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ በዚህ ሥፍራ ስለዝሙት እና ምኞች ማስተማር ጀምሯል፡፡ አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “ሰምታችኋል” በሚለው ሀረግ ውስጥ የሚገኘው “እናንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥር ነው፡፡ “አታመንዝር” የሚለው ትዕዛዝ “አንተ” የሚለውን ቃ በውስጡ ይዞዋል ይሁን እንጂ “አንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር መተርጎም ትችላለህ፡፡ ( ተመልከት) እንዲህ እንደተባለ ሰምታችኋል ይህ በቀጥታ እንዲህ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር እንዲህ ብሏል፡፡” ( ተመልከት) መፈጸም ይህ ቃል አንድን ነገር ማድረግን ያመለክታል፡፡ እኔ ግን እንዲህ እላችኋለሁ ይህንን በ MAT 5:22 እንደ ተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡ ሴትን ተመልክቶ በልቡ የተመኛት ማንኛውም ሰው አመንዝሯል ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ሴትን ተመልክቶ በልቡ የተመኛት ማንኛውም ሰው ካመነዘረ ሰው እኩሉ ጥፋተኛ መሆኑን ያሳያል፡፡ ( ተመልከት) የተመኛት “እንዲሁም የተመኛት” ወይም “ከእርሷ ጋር ለመተኛት የተመኘ ሰው” በልቡ በዚህ ሥፍራ “ልብ” የሚያመለክተው የአንድን ሰው ሀሳብ ነው፡፡ ኤቲ፡ “በአእምሮው” ወይም “በሀሳቡ”፡፡ ( ተመልከት)
የአንተ . . . ከ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “አንተ” የሚለው ቃል ነጠላ ቁጥር ነው ይሁን እንጂ በብዙ ቁጥር መተርጎም የግድ ሊሆንብህ ይችላል፡፡ ( ተመልከት) የቀኝ ዐይንህ ካሰናከለችህ በዚህ ሥፍራ “ዐይን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አንድ ሰው የሚያየውን ነው፡፡ እንዲሁም “መሰናከል” ምሳሌያዊ ንግግር ሲሆን “ኃጢአት” ማለት ነው፡፡ ኤቲ፡ “የሚትመለከተው ነገር እንድትሰናከል የሚያደርግ ከሆነ” ወይም “ከሚታየው ነገር የተነሳ ኃጢአት ማድረግ የሚትሻ ከሆነ፡፡” ( እና ተመልከት) ቀኝ ዐይን . . . ቀኝ እጅ ከግራ ዐይን ወይም እጅ በተቃራኒው በጣም ጠቃሚው ዐይን ወይም እጅ፡፡ “ቀኝ” የሚለው ቃል “አስፈላጊ የሆነ” ወይም “ብቸኛ” በሚሉ ቃላት ለትተረጉማቸው ትችላለህ፡፡ ( ተመልከት) አውጥተህ “በኃይል ማስወገድ” ወይም “ማጥፋት”፡፡ ቀኝ ዐይን የሚለው በቀጥታ ካልተጠቀሰ “ዐይንህ አጥፋ” ብለህ ልትተረጉም ትችላል፡፡ ዐይን የተጠቀሰ ከሆነ “አጥፋቸው” ብለህ ልትተረጉም ትችላለህ፡፡ አውጣው . . . ቁረጠው ኢየሱስ የኃጢአትን አደገኝነት ላይ አጽኖት በመስጠት ለዚህ ሰዎች መስጠት ስላለባቸው ምላሽ ግነት የተሞላት መልኩ ተናገግሯል፡፡ ( ተመልከት) አውጥተህ ጣለው “አስወግደው” ከሰውነት ክፍለህ አንዱ ይጥፋ “ከሰውነት ክፍልህ አንዱን ማጣት ይሻላል፡፡” መላ አካልህ ወደ ሲኦል ከሚጣል ይልቅ ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላለል፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር መላ አካልህን ወደ ሲኦል ከሚጨምረው ይልቅ፡፡” ( ተመልከት) ቀኝ እጂህ ካሰናከለችህ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር የአንድ ሰው ሁለተናዊ ተግባርን ከእጁ ጋር ታያይዛለች፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን እንዴት ለመፈጸም እንደመጣ ማስተማሩ ቀጥሏል፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ስለፍች ማስተማር ጀምሯል፡፡ እንዲህም ተብሏል “የተናገረው” እግዚአብሔር ነው፡፡ ኢየሱስ የእርሱ ተቃርኖ ከእግዚብሔር ወይም ከእግዚብሔር ቃል ጋር አለመሆኑን ለመግለጽ ነው ይህን ዓይነት ንግግር የተናገረው፡፡ ይልቁንም ፍች የተፈቀደው ለትክክለኛ ምክንያት ብቻ ነው፡፡ ወንዱ ምንም እንኳ በትዕዛዛቱ መሠረት የፍች ወረቀቷን ለሚስቱ ቢሰጣትም እንኳ ፍትሓዊ አይደለም፡፡ ( ተመልከት) ሚስቱን የሚሰዳት ይህ ፍችን የሚያመለክት ምሳሌያዊ አነጋገር ነው፡፡ ( ተመልከት) ይስጣት “ልሰጣት ይገባል” እኔ ግን እንዲህ እላለሁ ይህንን በ MAT 5:22 በምን ዓይነት መንገድ እንደተረጎማችሁ ተመልከቱ፡፡ አመንዝራ ያደርጋታል ትክክለኛ ባልሆነ መንገድ ሚስቱን የፈታት ሰው “እንድታመነዝር ያደርጋል”፡፡ በብዙ ባሕሎች ውስጥ እንደገና ማግባት ትችላለች ነገር ግን የተፋታችው ትክክለኛ ባልሆነ መንገድ ከሆነ ግን እንዲህ አይነቱ ትዳር ዝሙት ነው፡፡ ከተፋታች በኋላ ይህ በቀጥታ እንዲህ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ባሏ ከፈታት በኋላ” ወይም “ፍች የፈጸመችው ሴት”፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን እንዴት ለመፈጸም እንደመጣ ማስተማሩ ቀጥሏል፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ስለመሃላ ማስተማር ጀምሯል፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “ሰምታችኋል በሚለው ሀረግ ውስጥ ያለው “እናንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ ይሁን እንጂ “አትማል” እና “ፈጽማቸው” በሚለው ውስጥ ያለው “አንተ” የሚለው ቃል በነጠላ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ እንደገና አንተ “አንተም ደግሞ” ወይም “ሌላ ምሳሌ ይኼው፡፡ አንተ” እንዲህ ሲባል ሰምታችኋል . . . በውሸት አትማሉ በዚህ ሥፍራ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር እና ከቃሉ ጋር በግልጽ የሚስማማ ነገር ስናገር ትመለከታላችሁ፡፡ ይሁን እንጂ ሰዎችን ለማሳመን የእነርሱ ያልሆነ ነገር እንዳይናገሩ ያሳስባቸዋል፡፡ ኤቲ፡ “የሃይማኖት መሪዎቻችሁ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ብለው ነግረዋችኋል . . . አትማሉ፡፡” ( ተመልከት) በውሸት አትማሉ መኃላችሁን ፈጽሙ እንጂ አማራጭ ትርጉሞች 1) የማትፈጽሙትን ነገር አደርጋለሁ ብላችሁ በእግዚአብሔር ፊት አትማሉ ወይም 2) አንድ ነገር ውሸት መሆኑን እያወቃችሁ በእግዚአብሔር ፊት እውነት ነው ብላችሁ አትማሉ፡፡ እኔ ግን እንዲህ እላችኋለሁ በ MAT 5:22 የሚገኘውን በምን መንገድ እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡ ፈጽሞ አትማሉ . . . የታላቁ ንጉሥ ከተማ በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ የተናገረው ማንም ሰው ፈጽሞ መማል እንዳሌለበት ነው፡፡ አንዳንዶች አንድ ሰው የማለው ከእግዚአብሔር ውጪ በሆነ ነገር ማለትም በሰማይ፣ በምድር ዌም በኢየሩሳም የማለ ከሆነ መሃላውን ሳይፈጽም ቢቀር ይህን ያኽል ጉዳት የለውም ብለው ሳያስተምሩ አልቀሩም፡፡ ኢየሱስ ይህም ቢሆን እንደ ማንኛውም መሃላ መጥፎ ነው ምክንያቱም ሁሉ ነገር የእግዚአብሔር ስለሆነ ነው፡፡ ፈጽሞ አትማሉ ለዚህ ትዕዛዝ የሚሆን ቃል በቋንቋችሁ በብዙ ቁጥር የሚገኝ ከሆነ በዚህ ሥፍራ ይህንን ቃል ተጠቀሙ፡፡ “በውሸት አትማሉ” የሚለው ሀረግ አድማጮች መማል እንደሚቻል ነገር ግን በውሸት መማል የማይቻል እንደሆነ ያሳያል፡፡ “ፈጽሞ አትማሉ” የሚለው ሀረግ ግን ሁሉንም ዓይነት መሃላዎችን ይከለክላል፡፡ የእግዚአብሔር ዚፋን ነው በዚህ ሥፍራ ላይ “ዙፋን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔር እንደ ንጉሥ መግዛቱን ነው፡፡ ኤቲ፡ “የእግዚአብሔር አገዛዝ”፡፡ ( ተመልከት) የእግሩ መረገጫ ናት ይህ ምሳሌያዊ አነጋገር ምድርም ቢትሆን የእግዚአብሔር መሆኗን ያሳያል፡፡ ኤቲ፡ “ንጉሥ እግሩን የሚያሳርፍበት የእግሩ መርገጫ ሥፍራ ዓይነት ናት፡፡ ( ተመልከት) የታላቁ ንጉሥ ከተማ ናትና “ይህች ከተማ የታላቁ ንጉሥ የእግዚአብሔር ከተማ ናትና፡፡”
አጠቃላይ መረጃ፡ ከዚህ በፊት በነበረው ክፍል ውስጥ ኢየሱስ ስለ እግዚአብሔር ዙፋን፣ የእግሩ መረገጫ እና ምድራዊ ቤተ ጭምር ሊምሉበት የሚገባ የእርሱ ንብረት አለመሆኑን ገልጾዋል፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ደግሞ በራሳቸው ላይ ባለው ጸጉር እንኳ መማል እንደማይገባቸው ይናገራል፡፡ እናንተ . . . አንተ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “አትማል” እና “አትችልም” በሚሉ ሀረጋት ውስጥ ያለው “አንተ” የሚለው ቃል በነጠላ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ ይሁን እንጁ በምትተረጉሙበት ጊዜ በብዙ ቁጥር ልትተረጉሙ ትችላላችሁ፡፡ ( ተመልከት) መሃላ በ MAT 5:34እንዴት እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡ ንግግርህ “አዎ፣ አዎ ወይም አይ ፣ አይ” ይሁን” “አዎ ማለት ከፈለግህ “አዎ” በል እንዲሁም “አይ” ማለት ከፈለግህ “አይ” በል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን እንዴት ለመፈጸም እንደመጣ ማስተማሩ ቀጥሏል፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ጠላትን ስለመበቀል ማስተማር ጀምሯል፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “ሰምታችኋል” እና “እኔ እንዲህ እላችኋለሁ” በሚለው ሀረግ ውስጥ የሚገኘው “እናንተ” የሚለው ቃል የተገለጸው በብዙ ቁጥር ነው፡፡ “ማንም ቢመታህ” የሚለው ሀረግ ውስጥ የሚገኘው “አንተ” የሚለው ቃል ግን በብዙ ቁጥር መተርጎም ትችላላችሁ፡፡ ( ተመልከት) እንዲህ መባሉን ሰምታችኋል ይህንን በ MAT 5:33 እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከት፡፡ ዐይን ለዐይን ጥርስ ለጥርስ የሙሴ ሕግ የጎዳንን ሰው በተመሳሳይ መንገድ እንዲጎዳ ያዛል ይሁን እንጂ ከዚያ በላይ እንዲጎዳ አያደርግም፡፡ እኔ ግን እንዲህ እላለሁ ይህንን በ MAT 5:22.እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከት፡፡ ክፉውን “ክፉ የሆነ ሰው” ወይም “የጎዳችሁ ሰው” (UDB) ቀኝ ጉንጫችሁን የመታችሁ ኢየሱስ በኖረበት ባሕል ውስጥ የአንድን ሰው ቀኝ ጉንጭ በጥፊ መምታት ስድብ ነው፡፡ ልክ እንደ ዐይን እና እጅ ሁሉ ቀኝ ጉንጭም በጣም ጠቃሚ ነገር ነው፡፡ ጉንጭን በጥፊ መምታት ትልቅ ስድብ ነው፡፡ መምታት “በጥፊ መምታት”፡፡ ይህ ማለት በቃሪያ ጥፉ አንድን ሰው መምታት ማለት ነው፡፡ ሌላኛውንም ፊት አዙሩለት “ሌላኛውን ፊታችሁን የሚታችሁ ዘንድ አዙሩለት”
አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “ፍቀድ”፣ “ሂድ”፣ “ስጥ” እና “አትመለስ” በሚሉ ቃላት ውስጥ ያለው “አንተ” የሚለው ቃል በነጠላ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ ( ተመልከት) ኮትህ . . . መጎናጸፊያ “ኮት” በሰዉነት ላይ እንደ ቲሸረት የሚጠለቅ ነው፡፡ “መጎናጸፊያ” ከእነዚህ ይልቅ ውድ የሆነ “ከኮት” ላይ ለሙቀት የሚደረብ እንዲሁም በሽት ለሙቀት የሚለበስ ነገር ነው፡፡ ይወስድ ዘንድ ፍቀድለት “ለዚያ ሰው ስጠው” ማንምን ሰው “እንዲሁም ይህ ሰው”፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ በተዘዋዋር መንገድ የተጠቀሰው የሮማዊያን ወታደር ነው፡፡ ( ተመልከት) አንድ ምዕራፍ አንድ የሮም ወታደር በዚያ ዘመን አንድን ሰው አንድ ዕቃ ተሸክሞ እንዲሄድ በሕግ ማስገደድ የሚችለው አንድ ሺህ እርምጃዎች ያኽል ነው፡፡ “ማይል” የሚለው ቃል የሚያምታታ ከሆነ “አንድ ኪሎ ሜትር” ወይም “ረጅም ርቀት” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ከእርሱ ጋር አብረኸው እንዲትሄድ ያስገደደ ሰውን ያመለክታል፡፡ ከእርሱ ጋር እጥፍ መንገድ ሂደት “አስገድዶህ እንዲትሄድ ያደረግህን ምዕራፍ ያኸል ሂደት ከዚያም ሌላ አንድ ማዕራፍ ጨምርለት፡፡” “ማይል” የሚለው ቃል የሚያምታታ ከሆነ “ሁለት ኪሎ ሜትር” ወይም “እጥፍ ርቀት” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ አትከልክል “እንዲሁም ሊበደርህ የሚፈልግ ሰውን አትከልክል፡፡” ይህ በአውንታዊ መንገድ ሊገለጽ ይገባል፡፡ ኤቲ፡ “አበድር”፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ኢየሱስ የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን እንዴት ለመፈጸም እንደመጣ ማስተማሩ ቀጥሏል፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ጠላትን ስለመውደድ ማስተማር ጀምሯል፡፡ አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “የሚወድሁን ውደድ . . . የሚጠሉህ ጥላ” የሚለው ብቻ በነጠላ ቁጥ የተጻፈ ሲሆን እነዚህም ቢሆን በብዙ ቁጥር መተርጎም ትችላህ፡፡ ለሌሎች “እናንተ” የሚል ቃል ባለባቸው ሥፍራዎች ሁሉ እና “ፍቅር”እና “ጸሎት” ቦታዎች በብዙ ቁጥር የተገለጹ ናቸው፡፡ ( ተመልከት) እንዲህ እንደተባለ ሰምታችኋል ይህንን በ MAT 5:33. እንደተረጎማችሁት ተመልከት፡፡ ባለንጀራህን “ባለንጀራ” የሚለው ቃል አንድ ሰው በመልካም መንገድ ማስተናገድ የሚሻውን የተመሳሳይ ማህበረሰብ ወይም ቡድን አባላትን የሚያመለክት እንጂ በአከባቢያችን የሚኖሩ ሰዎችን ሁሉ አያመለክትም፡፡ ይህንን የብዙ ቁጥርን በሚያመለክት ቃል ልትተረጉሙት ትችላላችሁ፡፡ እኔ ግን እንዲህ እላችኋለሁ ይህንን በ MAT 5:22. እንደተረጎማችሁት ተመልከት፡፡ የአባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ “ልጆች” የሚለው ቃል በጥሩ ሁኔታ ለመተርጎም በቋንቋችሁ ለሰው ልጆችን ወይም ሕጻናት የሚትጠቀሙትን ቃል ተጠቀሙ፡፡ አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን እንዴት ለመፈጸም እንደመጣ ያስተማረውን ትምህርት በዚህ ከፍል ውስጥ ያጠናቅቃል፡፡ ይህ ክፍል የሚጀምረው በ MAT 5:17 ላይ ነው፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ ያኽል “እናንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥር አመልካች ነው፡፡ በእነዚህ ቁጥሮች ውስጥ የሚገኘው ጥያቄ መጠይቃዊ ነው፡፡ ( እና ተመልከት) ታላቅ ይህ አድማጮቹ መልካምነት ያለውን መሻት የሚያሳይ አጠቃላይ ቃል ነው፡፡አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
1 ሰዎች እንዲያዩአችሁ የጽድቅ ተግባሮቻችሁን በፊታቸው ከማከናወን ተጠንቀቁ፤ አለበለዚያ ከሰማይ አባታችሁ ዋጋ አታገኙም፡፡ 2 ስለዚህ አንተ ምጽዋት ስትሰጥ ግብዞች የሰዎችን ከበሬታ ለማግኘት በምኵራቦችና በጐዳና ላይ እንደሚያደርጉት፣ በፊትህ ጥሩንባ አታስነፋ፡፡ በእውነት እነግራችኋለሁ፣ ዋጋቸውን ተቀብለዋል፡፡ 3 አንተ ግን ምጽዋት ስትሰጥ፣ የቀኝ እጅህ የሚያደርገውን የግራ እጅህ እንዲያውቅ አታድርግ፤ 4 ይኸውም ምጽዋትህ በስውር የሚሰጥ እንዲሆንና ከዚያም በስውር የሚያይ አባትህ ዋጋህን እንዲከፍልህ ነው፡፡ 5 ስትጸልዩም እንደ ግብዞች አትሁኑ፤ ግብዞች ሕዝብ እንዲያያቸው በምኵራቦችና በጐዳና ማእዘኖች ላይ ቆመው መጸለይ ይወዳሉና፡፡ በእውነት እነግራችኋለሁ፤ ዋጋቸውን ተቀብለዋል፡፡ 6 አንተ ግን ስትጸልይ ወደ ጓዳህ ገብተህ በር ዝጋና በስውር ወዳለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር የሚያይ አባትህም ዋጋህን ይከፍልሃል፡፡ 7 ስትጸልይም አሕዛብ እንደሚያደርጉት ረብ የለሽ ድግግሞሽ አታድርግ፤ አሕዛብ በንግግራቸው ብዛት ምክንያት የሚሰሙ ይመስላቸዋልና፡፡ 8 ስለዚህ እንደ እነርሱ አትሁኑ፤ እናንተ ከመለመናችሁ በፊት ምን እንደሚያስፈልጋችሁ አባታችሁ ያውቃልና፡፡ 9 እንግዲህ እንደዚህ ጸልዩ፡- ‹በሰማይ የምትኖር አባታችን ሆይ፣ ስምህ ይቀደስ፡ 10 መንግሥትህ ትምጣ፡፡ ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነች፣ እንዲሁ በምድር ትሁን፡፡ 11 የዕለት እንጀራችንን ዛሬ ስጠን፡፡ 12 በደላችንን ይቅር በለን፣ እኛም የበደሉንን ይቅር እንደምንል፡፡ 13 ወደ ፈተና አታግባን፣ ከክፉው አድነን እንጂ፡፡› [መንግሥት፣ ኀይል፣ ክብርም የአንተ ነውና፣ ለዘላለም፣ አሜን፡፡] 14 የሰዎችን ኀጢአት ይቅር ብትሉ፣ የሰማይ አባታችሁ እናንተንም ይቅር ይላችኋል፡፡ 15 የሰዎችን ኀጢአት ይቅር ካላላችሁ ግን፣ የሰማይ አባታችሁ የእናንተን ኀጢአት ይቅር አይልም፡፡ 16 ስትጾሙም ግብዞች እንደሚያደርጉት ፊታችሁን አታጠውልጉ፤ እንደ ጾመኛ ለመታየት ግብዞች ፊታቸውን ያጠወልጋሉና፡፡ በእውነት እነግራችኋለሁ፣ዋጋቸውን ተቀብለዋል፡፡ 17 አንተ ግን ስትጾም ራስህን ተቀባ፣ ፊትሀንም ታጠብ፣ 18 ይኸውም፣ በስውር ላለው የሰማይ አባትህ ብቻ እንጂ ለሰዎች ጾመኛ መስለህ እንዳትታይ ነው፡፡ በስውር የሚያይ የሰማይ አባትህም ዋጋህን ይከፍልሃል፡፡ 19 ብልና ዝገት በሚበላውና ሌቦችም ሰብረው በሚሰርቁበት በምድር ላይ ሀብትን ለራሳችሁ አታከማቹ፡፡ 20 ይልቁን ብልም ሆነ ዝገት በማያጠፋበት፣ ሌቦችም ሰብረው በማይሰርቁበት በሰማይ ሀብትን ለራሳችሁ አከማቹ፡፡ 21 ሀብታችሁ ባለበት ልባችሁም ይገኛልና፡፡ 22 ዐይን የሰውነት መብራት ነው፡፡ ስለሆነም ዐይንህ ጤናማ ከሆነ፣ መላ ሰውነትህ በብርሃን ይሞላል፡፡ 23 ዐይንህ ጤናማ ካልሆነ ግን፣ መላ ሰውነትህ ጨለማ ይሆናል፡፡ እንግዲህ በውስጥህ ያለው መብራት በእውነት ጨለማ ከሆነ፣ ጨለማው እንዴት ከባድ ይሆን 24 ! ሁለት ጌቶችን ማገልገል የሚችል ማንም የለም፤ አንዱን ይጠላል ሌላውንም ይወዳል፣ ወይም ለአንዱ ይታዘዛል ሌላውን ደግሞ ይንቃል፡፡ እግዚአብሔርንና ሀብትን ማገልገል አትችሉም፡፡ 25 ስለዚህ ስለ ሕይወታችሁ ምን እንደምትበሉ ወይም ምን እንደምትጠጡ፡- ወይም ስለ ሰውነታችሁ ምን እንደምትለብሱ አትጨነቁ፤ ሕይወት ከምግብ፣ ሰውነትስ ከልብስ አይበልጥምን? 26 አየር ላይ የሚበርሩ ወፎችን ተመልከቱ! እነርሱ እህል አይዘሩም ወይም አያጭዱም፣ በጐተራም አያከማቹም፤ ይሁን እንጂ፣ የሰማይ አባታችሁ ይመግባቸዋል፡፡ ከወፎች ይልቅ እናንተ እጅግ የሚበልጥ ዋጋ ያላችሁ አይደላችሁምን? 27 ከእናንተ መካከል ተጨንቆ በዕድሜው ላይ አንድ ቀን መጨመር የሚችል ይገኛልን? 28 ስለ ልብስስ የምትጨነቁት ለምንድን ነው? 29 ነገር ግን እነግራችኋለሁ፤ ሰሎሞን እንኳ በዚያ ክብሩ ሁሉ ከእነዚህ አበቦች እንደ አንዱ አልለበሰም፡፡ 30 እግዚአብሔር ዛሬ የሚታየውንና ነገ እሳት ውስጥ የሚጣለውን የሜዳ ሣር እንደዚህ ካለበሰ፣ እናንት እምነት የጐደላችሁ! እናንተንማ እንዴት እጅግ የበለጠ አያለብሳችሁም? 31 እንግዲህ ‹ምን እንበላለን?› ወይም ‹ምን እንጠጣለን?› ወይም ‹ምን እንለብሳለን?› ብላችሁ አትጨነቁ፡፡ 32 አሕዛብ እነዚህን ሁሉ ይፈልጋሉና፤ የሰማይ አባታችሁ እነዚህ ሁሉ እንደሚያስፈልጓችሁ ያውቃል፡፡ 33 ነገር ግን በመጀመሪያ መንግሥቱንና ጽድቁን ፈልጉ፤ ከዚያም እነዚህ ሁሉ ይጨመሩላችኋል፡፡ 34 ስለዚህ ለነገ አትጨነቁ፤ ነገ ለራሱ ይጨነቃልና፡፡ ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ በ MAT 5:3ላይ የተጀመረውን የተራራው ስብከቱን ማስተማር ቀጥሏል፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “የጽድቅን ተግባራት” የሆኑትን አስራት ማውጣት፣ ጸሎት እና ጾምን አስመልክቶ አስምሯል፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “እናንተ” የሚለው ቃል ሁሉም በብዙ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ በሰዎች ለመታየት ለሰዎች ብለው የሚያደርጉ ሰዎች እርሱን እያከበሩት እንዳልሆነ በተዘዋዋር መልኩ ያመለክታል፡፡ ይህ እንዲህ ባለ መልኩ በቀጥታ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ስላደጋችሁት ነገር ሰዎች ያመሰግናችሁ ዘንድ በሰዎች ፊት የሚታደርጉት ከሆነ፡፡” ( እና ተመልከት) አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) ለራስህ መለከት አታስነፋ ይህ ምሳሌ የሚያሳየው የሰዎችን ትኩረት ሆን ብለህ ለመሳብ የተለያዩ ነገሮችን ማድረግ ነው፡፡ ኤቲ፡ “በብዙ ሰዎች መካከል መለከት በታላቅ ድምፅ እንደሚነፋ ሰው ወደ ራሰህ የሰዎችን ትኩረት ለመሳብ ጥረት አታድረግ፡፡” ( ተመልከት) እውነት እልሃለሁ “እውነቱን እነግርሃለሁ”፡፡ ይህ ሀረግ ኢየሱስ በመቀጠል ስለሚናገረው ነገር አጽኖት የሚሰጥ ሀረግ ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ኢየሱስ ስመ ስጦታ መስተማሩን ቀጥሏል፡፡ አጠቃላያ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “እናንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥር አመልከች ነው፡፡ ግራ እጅህ ቀኝ እጅህ የሚሰጠውን አይወቅ ይህ የሚታደርገው ነገር ሁሉ ሙሉ ለሙሉ ምስጥር መሆን እንዳለበት የሚያሳይ ምሳሌ ነው፡፡ ምንም እንኳ ሁለቱም እጆች ብዙ ጊዜ ነገሮችን በጋራ የሚያከናውኑ ቢሆንም እንኳ፣ አንዱ የሚያደርገውን ሌላኛው “የሚያውቅ” ቢሆንም እንኳ ለድሆች በሚትሰጥበት ጊዜ እነዚህ በጣም የሚቀራረቡ እጆች እንኳ አንደኛው የሌላኛውን ማወቅ የለበትም፡፡ ( ተመልከት) ስጦታችሁ በድብቅ ይሁን ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ሌሎች ሰዎች መስጠትህ ሳያውቁ ለድሆች ልትሰጥ ትችላለህ፡፡” ( ተመልከት) ይሸልምሃል “ሽልማት ይሰጥሃል፡፡” (UDB)
አያያዥ ዓረፍተ ነገሮች ኢየሱስ ስለ ጸሎት እንዲህ በማለት ማስተማር ጀመረ፡፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በቁጥር 5 እና 7 ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የብዙ ቁጥር አመልካች ቃል ሲሆን በቁጥር 6 ላይ ግን በነጠላ ቁጥር ተገልጾዋል፡፡ ይሁን እንጂ ይህንን በብዙ ቁጥር ልትተረጉመው ትችላለህ፡፡ ( ተመልከት) ሌሎች ሰዎች የሚያደርጉትን ያዩላቸው ዘንድ በዚህ ሀረግ ውስጥ ተመልካቾቹ ድርጊቱን ተመልክተው ክብር እንደሚሰጧቸው በተዘዋዋር መንገድ ያሳያል፡፡ ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ሰዎች ያዮዋቸው እና ክብር ይሰጧቸው ዘንድ፡፡” ( እና ተመልከት) እውነት እውነት እላችኋለሁ “እውነቱን እነግራቿለሁ”፡፡ ይህ ሀረግ ኢየሱስ በመቀጠል ለመናገረው ነገረ ትኩርት እንዲንሰጥ ያደርገናል፡፡ ወደ እልፍኝህ ግባ፡፡ በርህንም ዝጋ “ለብቻ ወደምትሆንበት ሥፍራ ግባ” ወይም “ለብቻ መሆን ወደምትችልበት ሥፍራ ሂድ” በውስር ያለው አባት ለዚህ አማራጭ ትርጉሞች 1) እግዚአብሔርን ማንም ሰው ማየት አይችልም ወይም 2) እግዚአብሔር በዚያ ለብቻው ከሚጸልየው ሰው ጋር አለ፡፡ አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) በስውር የሚታደርገውን የሚያይ አባት “አባትህ በስውር የሚታደርገውን ያያል” በከንቱ አትድገም “ትርጉም የሌሽ ቃላትን አትደጋግም” ይሰማል ይህ እንዲህ በቀላሉ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “የሐሰት አማልክቶች ይሰሟቸዋል፡፡” ( ተመልከት) ብዙ በመናገራቸው “በረጃጅም ጸሎቶቻቸው” ወይም “ በብዙ ቃሎቶቻቸው፡፡”
አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “እንዲህ ጸልዩ” እስከሚለው ድረስ ለቡድን ተናግሯል፡፡ “እናንተ” ከሚለው ቀጥሎ ያለው “ሰማያዊ አባታችሁ” የሚለው ቃል በነጠላ ቁጥር ነው የተቀመጠው፡፡ (See: ተመልከት) አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) ስምህን ይቀደስ በዚህ ሥፍራ ላይ “ስም” የሚለው ቃል እግዚአብሔርን የሚያመለክት ነው፡፡ ኤቲ፡ “ቅዱስ እንደሆንክ ሁሉም ሰው ይወቅት፡፡” ( ተመልከት) መንግስትህ ትምጣ በዚህ ሥፍራ “መንግስት” የሚለው ቃል እግዚአብሔር እንደ ንጉሥ ሆኖ የሚገዛበትን የሚያመለክት ቃል ነው፡፡ ኤቲ፡ “በሁሉም ላይ ገዥ ሁን እና ሙሉ ለሙሉ ሁሉን ግዛ፡፡” ( ተመልከት) ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እዲሁም በምድር ላይ ትሁን ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “በሰማይ ያሉት ሁሉም እንደሚታዘዙህ ሁሉ በምድር ላይ ያሉት ሁሉ ይታዘዙህ፡፡” ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ “እኛ” እና “የእኛ” የሚሉት ቃላት ኢየሱስ እየተናገራቸው ያለውን የተሰበሰበውን ሕዝብ ያመለክታል፡፡ ( ተመልከት) የእለት እንጀራችንን በዚህ ሥፍራ ይ “እንጀራ” የሚለው ቃል በአጠቃላይ ምግብን ያመለክታል፡፡ ( ተመልከት) ብድር ብድር አንድ ሰው ያለበት ዕዳ ነው፡፡ ይህ ኃጢአትን በምሳሌ ለመግለጽ ጥቅም ላይ የዋለ ቃል ነው፡፡ ( ተመልከት) ባለዕዳ ባለዕዳለ ከሌላ ሰው የተበደረ ሰው ነው፡፡ ይህ ኃጢአትን በምሳሌ ለመግለጽ ጥቅም ላይ የዋለ ቃል ነው፡፡ ( ተመልከት) ወደ ፈተና አታግባን “ፈተና” የሚለው ቃል በግሥ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ምንም ነገር እንድፈትነን አትፍቀድለት” ወይም “ኃጢአትን እንድንመኝ የሚያደረግ ማንኛውንም ነገር ሕይወታችን ውስጥ አትፍቀድ፡፡” ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚገኝበት ሥፍራ ሁሉ በብዙ ቁጥር ነው፡፡ ይሁን እንጂ ኢየሱስ ሌሎች ሰዎችን ይቅር ካላሉ በግል ምን እንደሚደርስባቸው እየነገራቸው ነው፡፡ ተመልከት) መተላለፍ “ስህተት” ወይም “ኃጢአት” አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ስለ ጾም ማስተማር ጀመረ፡፡ አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በቁጥር 17 አና 18 ላይ “አንተ” የሚለው ቃል በነጠላ ቁጥር የተገለጸ ሲሆን በቁጥር 16 ላይ ካለው ጋር ተመሳሳይ እንዲሆን በብዙ ቁጥር ልትተረጉመው ትፈልግ ይሆናል፡፡ ( ተመልከት) በተጨማሪ “እንዲሁም” ፊታቸውን ያጎሳቁላሉ ግብዞች ፍታቸውን አይታጠቡም ወይም ጸጉራቸውን አያበጥሩም፡፡ ይህንን የሚያደርጉት ሆን ብለው እየጾሙ መሆናቸውን ለማሳየት የሰዎችን ትኩረት ለመሳብ እና ከእነርሱ ክብር ለማግኘት ሲሉ ይህንን ያደርጋሉ፡፡ እውነት እውነት እላችኋለሁ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፡፡” ይህ ሀረግ ኢየሱስ በመቀጠል ለሚናገረው ነገር ትኩረት መስጠቱን ያመለክታል፡፡ ራስህን ዘይት ተቀባ “ዘይት ተቀባ” ወይም “ጸጉርህን አበጥር”፡፡ ራስህን “ተቀባ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ለጸጉር የተለመደውን እንክብካቤ ማድረግ ነው፡፡ “ከክርስቶስ” “የተቀባው” መሆኑ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም፡፡ ኢየሱስ ማለት የፈለገው ሰዎች ጾም እየጾሙም ሆነ ሳይጾሙ ተመሳሳይ መሆን አለባቸው ነው፡፡ በስውር ያለው አባት . . . በስውር የሚያይ ይህንን እንዴት በ MAT 6:6. እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ስለ ገንዘብ እና ንብረት ማስማር ጀመረ፡፡ አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “አንተ” የሚል ቃል ጥቅም ላይ በዋለባቸው ሥፍራዎች ከቁር 21 በስተቀር ብዙ ቁጥርን ያመለክታል፡፡ ይሁን እንጂ በቁትር 21 ላይ ነጠላ ቁጥር ነው፡፡ ( ተመልከት) ንብረት “ሀብት” ብል እና ዝገት የሚበሉት “ብል እና ዝገት የሚያበላሹት ሀብት” ብል ብል ልብስን የሚያበላሹ በራሪ ነፍሳት ናቸው፡፡ ዝገት ብረት ውሃ ሲነካው የሚፈጠር ቡናማ ቀለም ያለው ነገር ነው፡፡ store up for yourselves treasures in heaven This is a metaphor that means do good things on earth so God will bless you in heaven. በሰማይ ሀብትን አከማቹ ይህ ምሳሌ የሚያሳየው እግዚአብሔር በሰማይ ይበባርካችሁ ዘንድ በምድር ላይ ሳላቹ መልካምን ነገር አድርጉ፡፡ ( ተመልከት) ልብህም ደግሞ በዚያ ይሆናል በዚህ ሥፍራ ላይ “ልብ1 ማለት አሳብ እና ፍላጎት ማለት ነው፡፡ ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “አንተ” የሚል ቃል ጥቅም ላይ በዋለባቸው ሥፍራዎች ውስጥ በነጠላ ቁጥር የተጠቀሰ ሲሆን አንተ ግን በብዙ ቁጥር ለመተርጎም ታስብ ይሆናል፡፡ ( ተመልከት) ዐይን የሰውነት ብርሃን ነች . . . ጨለማው ምን ያኽል ታላቅ ይሆን ይህ ማየት የሚችል ጤናማ ዐይንን አንድን ሰው ዐይነ ሥውር ከሚያደረግ በሽታ ጋር ያነነጻጽራል፡፡ ይህ ምሳሌ የሚያመለክተው መንፈሳዊ ጤንነትን ነው፡፡ ብዙ ጊዜ አይሁዳዊያን “መጥፎ ዐይንን” ከስስት ጋር ያይዙታል፡፡ ትርጉሙም አንድ ሰው ሁለተናውን ለእግዚአብሔር ከሰጠ እንዲሁም ሁሉንም ነገር ከእግዚአብሔር አንጻር መመልከት ከቻለ ትክክለኛውን ነገር ያደርጋል፡፡ ይሁን እንጂ አንድ ሰው ስስታም ከሆነ ክፋትን ያደርጋል፡፡ ( ተመልከት) ዐይን የሰውነት ብርሃን ነው የዚህ ምሳሌያዊ ንግግር ትርጉም ልክ መብራት በጨለማ ውስጥ ሰው አጥርቶ እንዲያይ እንደሚያደርግ ሁሉ ዐይንም አንድ ሰው በደንብ ማየት እንዲችል ያደርገዋ፡፡ ኤቲ፡ “እንደ መብራት ዐይን ነገሮችን በግልጽ ማየት እንድትችል ያደርጋል፡፡” ( ተመልከት) ዐይን ይህንን በብዙ ቁጥር ልትተረጉመው ትችላለህ፤ “ዐይኖች”፡፡ ዐይንህ መጥፎ ቢሆን ይህ ምትሃትን አያመለክትም፡፡ አይሁዶች ብዙ ጊዜ ስስታምነትን በዚህ ምሳሌያዊ አነጋገር ይገልጹታል፡፡ ( ተመልከት) አንዱን ይወዳል ሌላኛውን ይጠላል ወይም ለአንዱ ይገዛል ሌላኛውን ደግሞ ይንቃል ሁለቱም በመሠረታዊ ሀሳባቸው አንድ ናቸው፡፡ አጽኖት የሚሰጡት አንድ ሰው እግዚአብሔር መውደድ እና መገዛት እንዲሁም ገንዘብንም መውደድና ለእርሱ መገዛት በአንድ ጊዜ አይችልመም፡፡ ( ተመልከት) ለሀብት እና ለእግዚአብሔር መገዛት አትችሉም፡፡ “በአንድ ጊዜ እግዚአብሔርን እና ገንዘብን መውደድ አትችሉም፡፡”
እላችኋለሁ ይህ ኢየሱስ ከዚህ በመቀጠል የሚናገረው ነገር አጽኖት ሊሰጠው የሚገባ መሆኑን ያሳያል፡፡ ለእናንተ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “እናንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ ( ተመልከት) ሕይወት ከመብል እንዲሁም ሰውነት ከልብስ አይበልጥምን? በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ ሰዎችን ለማሰተማር ጥያቄን ተጠቅሟል፡፡ ኤቲ፡ “በእርግጥ ሕይወት ከምግብ እንዲሁም አካል ከምንለብሰው ልብስ ይበልጣል፡፡” ( ተመልከት) ጎተራ እህል ማጠራቀሚያ ሥፍራ፡፡ አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) Are not you of much more value than they? Jesus uses a question to teach the people. AT: "Obviously you are more valuable than birds." አንተ ከእነርሱ ይልቅ በጣም ኩቡር አይደለህምን? ኢየሱስ ሰዎችን ለማስተማር ጥያቄን ይጠቀማል፡፡ ኤቲ፡ “ከሰማይ ወፎች ይልቅ አንተ ክቡር ነህ፡፡” ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “እናንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ ( ተመልከት) ከእናንተ መካከል በመጨነቅ በእድሜው ላይ ስንዝር ታኽል የጨመረ ማን ነው? ኢየሱስ ሰዎችን ለማስተማር ጥያቄን ይጠቀማል፡፡ ይህ ማለት ማንም በጭንቀት ረጅም እድሜ መኖር የሚችል የለም፡፡ ( ተመልከት) አንድ ክንድ “አንድ ክንድ” ከከግማሽ ሜትር ትንሽ የሚያንስ ነው፡፡በዚህ ሥፍራ ላይ ጥቅም ላይ የዋለው አንድ ሰው በእድሜው ላይ ምንም መጨመር እንደማይችል በምሳሌ ለመግለጽ ነው፡፡ ( እና ተመልከት) ስለምትለብሱት ነገር ስለምንት ትጨነቃላችሁ? ኢየሱስ ሰዎችን ለማስተማር ጥያቄን ይጠቀም ነበረወ፡፡ ኤቲ፡ “ምን እለብሳለሁ ብላችሁ አትጨነቁ፡፡” ( ተመልከት) ስለአንድ ነገር ማሰብ “መጨነቅ” አበቦች የሜዳ አበቦች ( ተመልከቱ) እላችኋለሁ ይህ ኢየሱስ ከዚህ በመቀጠል የሚናገረው ነገር አጽኖት ሊሰጠው የሚገባ መሆኑን ያሳያል፡፡ ማንም እንደነዚህ አግጦ አያውቅም ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እንደነዚህ የሜዳ አበቦች ያጌጠ ልብስ ማንም ለብሶ አያውቅም፡፡”
አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ “እናንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡ እነዚህ ሣሮች እንደዚህ ካለበሳቸው ይህ ምሳሌ እግዚአብሔር አበቦችን እንዲህ ውብ ካደረጋቸው ማለት ነው፡፡ ( ተመልከት) ሣር በቋንቋችሁ ሣር የሚለው ቃል የሚያካትት እና ከከዚህ በፊት የሜዳ አበባዎች ተብሎ የተተረጎመውን የሚያካትት ከተገኘ ያንን ቃል ተጠቀም፡፡ ወደ ማቃጠያ እቶን የሚጣለውን አይሁዳዊያን ምግባቸውን ለማብሰል ሣርን ይጠቀማሉ፡፡ ይህ በቀጥታ እንዲህ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ወደ ማቃጠያ ይጥለዋል” ወይም “አንድ ሰው እንዲቀጣል ያደርገዋል፡፡” ( ተመልከት) እናንተ ምን አያለብሳችሁም . . . እምነት? ኢየሱስ ሰዎችን ለማስተማር ጥያቄን ይጠቀም ነበር፡፡ ኤቲ፡ “በእርግጠኝነት ያለብሳችኋል . . . እምነት፡፡” ( ተመልከት) እናንተ እምነት የጎደላችሁ “እናንተ ትንሽ እምነት ያላችሁ፡፡” በእግዚአብሔር ላይ ያላቸው እምነት በጣም ትንሽ ከመሆኑ የተነሳ ኢየሱስ ሰዎችን ይገስጻቸዋል፡፡ ስለዚህ “እነዚህ ሁሉ ምክንቶች”
አሕዛብም እነዚህ ነገሮች ሁሉ ይፈልጋሉ “አሕዛብም ነገ ምን እንደሚበሉ፣ እንደሚጠጡ እና እንደሚለብሱ ይጨነቃሉ፡፡” በሰማይ ያለው አባታችሁ የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ ያውቃል ኢየሱስ በዚህ ንግግሩ ውስጥ በተዘዋዋር መልኩ የሚያስረግጠው ነገር መሠረታዊ ፍላጎቶቻችሁ በእግዚአብሔር በእርግጠኝነት ይሟላሉ፡፡ አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) በመጀመሪያ መግስቱን እና ጽድቁን ፈልጉ በዚህ ሥፍራ ላይ “መንግስቱ” የሚለው ቃል እግዚብሔር እንደ ንጉሥ መግዛቱን የሚያመለክት ነው፡፡ ኤቲ፡ “ንጉሥ የሆነውን እግዚአብሔርን አገልግል እንዲሁም መልካም የሆነውን ነገር አድርግ፡፡” ( ተመልከት) እነዚህ ሁሉ ነገሮች ይጨመሩልሃል ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር እነዚህ ነገሮች ያዘጋጅልሃል፡፡” ( ተመልከት) ስለዚህ “በእነዚህ ሁሉ ምክንቶች” tomorrow will be anxious for itself Jesus is describing "tomorrow" as if it is a person that can worry. Jesus means that a person will have enough to worry about when the next day comes. ነገ ስለራሱ ይጨነቅ በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ “ነገን” ልክ እንደ ሰው የሚጨነቅ አድርጎ ያቀርበዋል፡፡ ኢየሱስ አንድ ሰው ነገ ስመጣ በዚያ ቀን በቂ የሚጨነቅበት ነገር አለው ማለቱ ነው፡፡ ( ተመልከት) ለዛሬ የራሱ ክፋት ይበቃዋል “እያንዳንዱ ቀን በውስጡ በቂ የሆነ ክፋትን ይዟል” ወይም “ሁሉም ቀናት በቂ ችግሮች አሏቸው”
1 አትፍረዱ፥ እናንተም አይፈረድባችሁም። 2 በምትፈርዱበት ፍርድ፥ ይፈረድባችኋል፤በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ፥ ለእናንተም ይሰፈርላችኋል። 3 በራስህ ዐይን ውስጥ ያለውን ግንድ ሳታስተውል፥ በወንድምህ ዐይን ውስጥ ያለውን ጉድፍ የምታየው ለምንድን ነው? 4 በአንተ ዐይንህ ውስጥ ግንድ እያለ፣ በወንድምህ ዐይን ውስጥ ያለውን ጉድፍ ላውጣልህ ማለት እንዴት ትችላለህ? 5 አንተ ግብዝ! በወንድምህ ዐይን ውስጥ ያለውን ጉድፍ በደንብ አይተህ ለማውጣት፣ በመጀመሪያ በራስህ ዐይን ውስጥ ያለውን ግንድ አስወግድ። 6 በእግራቸው እንዳይረግጡትና እናንተንም እንዳይቦጫጭቁዋችሁ፤ ቅዱስ የሆነውን ለውሾች አትስጡ፥ እንቁዎቻችሁንም ለዐሳማዎች አትጣሉ። 7 ለምኑ፣ ይሰጣችኋል፤ ፈልጉ፥ ታገኛላችሁ፤ አንኳኩ፣ ይከፈትላችኋል። 8 የሚለምን ሰው ሁሉ ይቀበላልና፣ የሚፈልግ ሰውም ያገኛል፥ ለሚያንኳኳም ሰው ይከፈትለታል። 9 ከእናንተ መካከል ልጁ እንጀራ ሲለምነው፣ ድንጋይ የሚሰጠው፣ 10 ዐሣ ሲለምነው፣ እባብ የሚሰጠው? ምን ዐይነት ሰው ነው? 11 እንግዲህ፥ እናንተ ክፉዎች የሆናችሁ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠት ካወቃችሁ፥ በሰማይ የሚኖር አባታችሁ ለሚለምኑት አብዝቶ መልካም ስጦታን እንዴት አይስጣቸውም? 12 ስለዚህ፣ ማንኛውንም ሰዎች ሊያደርጉላችሁ የምትፈልጉትን ሁሉ፣ እናንተም ልታደርጉላቸው ይገባል፤ ምክንያቱም ሕጉም ነቢያቱም የሚያስተምሩት ይህንኑ ነው፡፡ 13 በጠባቡ በር ግቡ፣ ምክንያቱም ወደ ጥፋት የሚወስደው መንገድ ሰፊ፣ የሚሄዱበትም ብዙዎች ናቸው፡፡ 14 በሩ ጠባብ፣ ወደ ሕይወት የሚወስደውም መንገድ ቀጭን ስለ ሆነ፣ የሚያገኙት ጥቂቶች ናቸው፡፡ 15 የበግ ቆዳ ለብሰው ከሚመጡባችሁ፣ በትክክል ግን ነጣቂ ተኩላዎች ከሆኑ፣ ከሃሰተኛ ነቢያት ተጠንቀቁ። 16 በሚያፈሩት ፍሬ ታውቋቸዋላችሁ፡፡ሰው ከእሾኽ የወይን ፍሬ፣ ወይም ከኩርንችት በለስ ሊሰበስብ ይችላልን? 17 እንደዚያው፥ መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ ያፈራል፣ መጥፎ ዛፍ መጥፎ ፍሬ ያፈራል። 18 መልካም ዛፍ ሆኖ መጥፎ ፍሬ የሚያፈራ፣ ወይም መጥፎ ዛፍ ሆኖ መልካም ፍሬ የሚያፈራ ዛፍ የለም። 19 ማንኛውም መልካም ፍሬ የማያፈራ ዛፍ ሁሉ ይቆረጣል፣ ወደ እሳትም ይጣላል። 20 እንግዲህ በሚያፈሩት ፍሬ ታውቋቸዋላችሁ። 21 በሰማይ ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ እንጂ፣" ጌታ ሆይ፣ ጌታ ሆይ፣" እያለ የሚጠራኝ ሁሉ፣ ወደ መንግሥተ ሰማይ የሚገባ አይደለም፡፡ 22 በዚያ ቀን ብዙዎች፣ "ጌታ ሆይ፣ ጌታ ሆይ፣ በስምህ ትንቢት ተናግረን አልነበረም እንዴ፣ በስምህ አጋንንት አስወጥተን አልነበረም እንዴ፣ በስምህስ ብዙ ታላላቅ ነገሮችን አድርገን አልነበረም እንዴ?" ይሉኛል፡፡ 23 እኔም፣ “እናንት ክፉ አድራጊዎች፣ የት ዐውቃችሁና ነው? ከእኔ ራቁ ብዬ በግልጽ እነግራቸዋለሁ” 24 ስለዚህ፣ ቃሎቼን የሚሰማና የሚታዘዛቸው ልክ ቤቱን በድንጋይ ላይ የመሠረተ አስተዋይ ሰውን ይመስላል፡፡ 25 ዝናብ ዘነበ፣ ጎርፍም ጎረፈ፣ ነፋስም ነፈሰ ያንን ቤት መታው፤ ይሁን እንጂ ቤቱ በዐለት ላይ ስለ ተመሠረተ፣ አልወደቀም፡፡ 26 ሆኖም ቃሌን ሰምቶ የማይታዘዝ፣ ቤቱን በአሸዋ ላይ የመሠረተ ሞኝ ሰውን ይመስላል፡፡ 27 ዝናብ ዘነበ፣ ጎርፍ ጎረፈ፣ ነፋስም ነፈሰ፣ ያንንም ቤት መታው፤ ቤቱም ወደቀ፤ አወዳደቁም ከባድ ሆነ ። 28 ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች ተናግሮ ሲጨርስ፣ ሕዝቡ በትምህርቱ ተገረሙ፡፡ 29 ያስተማረውም እንደ ባለስሥልጣን እንጂ ፣እንደ ጽሐፍት አልነበረም።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ በ in MAT 5:3 በተጀመረው የተራራው ስብከት ውስጥ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “እናንተ” የሚለው ቃል እና የተሰጡት ትዕዛዛት በብዙ ቁጥር ተገልጸዋል፡፡ ( ተመልትከት) አትፍረድ በዚህ ሥፍራ ላይ “አትፍረድ” የሚለው ቃል ጠንከር ያለ “ጠንከር ያለ ማውገዝን” ወይም “ጥፋተኛ አድርጎ መወሰንን” የሚያመለክት ቃል ነው፡፡ ኤቲ፡ “በሰዎችን ላይ አትፍረድ”፡፡ ( ተመልከት) አይፈረድብህም ይህ በግልጽ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “መጥፎ ፍርድ አይፈረድብህም፡፡” ( ተመልከት) Be sure the reader understands the statement in 7:2 is based on what Jesus said in 7:1. ምክንያቱም ኢየሱስ በ7፡2 ላይ የተናገረው ንግግር መሠረቱ በ7፡1ላይ የተናገረው መሆኑን እርግጠኞች ሁኑ፡፡ በፈረዳችሁት ፍርድ እናንተም ላይ እንዲሁ ይፈረዳል ይህ በዚህ መልኩ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “በሌሎች ሰዎች ላይ በፈረዳችሁበት መጥን ልክ እናንተም ላይ እግዚአብሔር ይፈርዳል፡፡” ( ተመልከት) በዚያው ልክ ይፈረዳል ይህ እንዲህ በቀጥታ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር በዚያው ልክ ይፈርዳል፡፡” ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “እንተ” የሚለው ቃል በነጠላ ቁጥር ተገልጸዋል ይን እንጂ በብዙ ቁጥር ልትተረጎማቸው ትችላለህ፡፡ ስለምን ታያለህ . . . እንዴትስ ትለዋለህ ኢየሱስ እነዚህን ሁሉት ጥያቄዎች የተጠቀመው ሰዎችን ለማስተማር እና አመለካከታቸውን እንደገና ይመለከቱት ዘንድ ነው፡፡ የሌሎች ሰዎች ኃጢአት ላይ ጣታቸውን ከመቀሰራቸው በፊት ለራሳቸውን ኃጢአት ትኩረት መስጠት ስለፈለገ ነው፡፡ ( ተመልከት) በጣም ትንሽ ብናኛ “ቆሻሻ”(UDB) ወይም “ብናኝ” ወይም “አፈር”፡፡ ወደ ሰዎች ዐይን ውስጥ ብዙ ጊዜ የሚገባን ነገር ለመግለጽ የሚትጠቀሙትን ቃል ተጠቀም፡፡ ይህ በሰዎች ውስጥ የሚያጋጥምም በጣም ትንሹን ስህተትን ለማመልከት ጥቅም ላይ የዋ ምሳሌ ነው፡፡ ( ተመልከት) ወንድም ይህ የሥጋ ወንድምን ወይም ጎረቤትን ሳይሆን አማኝን የሚያመለክት ነው፡፡ ምሰሶ አንድ ሰው በቆረጠው ዛፍ ውስጥ የሚገኘው ትልቁ ክፍል ምሰሶ ነው፡፡ ይህ ወደ ሰዎች ዐይን ለመግባት በጣም ትልቅ የሆነ ግንድ ነው፡፡ ይህ በሰው ሕይወት ውስጥ ያለ በጣም ትልቅ ስህተትን ያሳያል፡፡ እና ተመልከት)፡፡
አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “እናንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር ተገልጸዋል፡፡ ውሾች . . . እሪያዎች አይሁዶች እነዚህ እንስሳት ቆሻሾች አድርገው ይቆጥሯቨዋል እንዲሁም እግዚአብሔርም እነዚህን እንስሳት እንዳይበሉ አዞዋቸዋል፡፡ ይህ ቅዱስ ለሆነው ነገር ዋጋ የማይሰጡ ኃጢአተኛ ሰዎችን ለማመልከት የቀረበ ምሳሌያዊ አነጋገር ነው፡፡ ይህንን ቃል በቁሙ መተርጎሙ ባጣም ጥሩ ነው፡፡ ( ተመልከት)፡፡ እንቁዎች እነዚህ በጣም ትንንሽ፣ ውድ የሆኑ ድንጋዮች ናቸው፡፡ ይህ ስለእግዚአብሔር ወይም ስለውድ ነገሮች በአጠቃላይ ማወቅ ጋር ተያያዥነት ያለው ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ ( ተመልከት) በእግሮቻቸው ልረጋግጡት ይችላሉ “እሪያዎቹ ይረጋግጡታል” እናም ወደ ትፋታቸው ይመለሳሉ “እናም ውሾች ወደ ትፋታቸው ይመለሳሉ”
አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “እንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር ተገልጸዋል፡፡ ( ተመልከት)፡፡ ጠይቁ . . . ፈልጉ . . . አንኳኩ ይህ ወደ እግዚአብሔር መጸለይን ለማመልከት ጥቅም ላይ የዋለ ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ጥቅም ላይ የዋለው ግሥ እግዚአብሔር ምላሽ እስኪሰጠን ድረስ እንዲንጸለይ የሚያደርግ ነው፡፡ በቋንቋችሁ አንድን ነገር መልሳችሁ መልሳችሁ ማድረግ እንዳለባችሁ የሚገልጽ ቃል ካለ ይህንን ቃል ተጠቀሙ፡፡ ( ተመልከት) ጠይቁ ይህ ከእግዚአብሔር የሆነ ነገርን ጠይቁ ማለት ነው፡፡ (UDB) ይሰጣችኋል ይህ እንዲህ ባለ መልኩ በቀጥታ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “የሚያስፈልጋችሁን ነገር እግዚአብሔር ይሰጣችኋል፡፡ ( ተመልከት) ፈልጉ “ስለምትፈልጉትን ነገር የእግዚአብሔርን ፊት ፈልጉ” አንኳኩ በር ማንኳኳት በቤት ውስጥ ያለ ሰው በሩን እንዲከፍትላችሁ በትህትና መጠየቅ ነው፡፡ በእናንት ባሕል ውስጥ በር ማንኳኳት ትህትና ካልሆነ ሰዎች በእናንተ ባሕል ውስጥ በር እነንዲከፈትላቸው በትህትና የሚጠይቁ በምን ዓይነት መንገድ ነው፣ ይህንንም ቃል ተጠቀሙ፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር በሩን እንዲከፍትላችሁ እንደሚትልጉ ንገሩት፡፡” ወይም ከእናንተ መካከል ማን ነው . . . ድንጋይ? ኢየሱስ ሰዎችን ለማስተማር ጥያቄን ይጠቀማል፡፡ ኤቲ፡ “ከእናንተ መካከል ማንም የለም . . . ድንጋይ፡፡” ( ተመልከት) ቁራጭ ዳቦ ይህ በአጠቃላይ ምግብን ያመለክታል፡፡ ኤቲ፡ “የሆነ ምግብ፡፡” ( ተመልከት) ድንጋይ. . . ዓሳ . . . እባብ እነዚህ ስሞች በቁማቸው መተርጎም አለባቸው፡፡ ወይም ኣሳ ጠይቋችሁ እባብ የምትሰጡት? ኢየሱስ ለማስተማር ሌላ ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡ በዚህ ሥፍራም ኢየሱስ ስለ ሰውዬው እና ልጁ እየተናገረ መሆኑን መረዳት አስፈላጊ ነው፡፡ ኤቲ፡ “ከእናንተ መካከል ልጁ ዓሳ ጠይቆት እባብ የሚሰጠው ማንንም የለም፡፡” ( እና ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ ኢየሱስ በቡድን ለሚያደምጡ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ ምን እንደሚያጋጥማቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “እንተ” የሚለው ቃል በብዙ ቁጥር ተገልጸዋል፡፡ ( ተመልከት)፡፡ በሰማይ ያለው አባታችሁ አስበልጦ ምን ያኽል አይሰጣችሁ . . . አርሱ? በዚህ ሥፍራ ኢየሱስ ሕዝቡን ለማስተማር ጥየቄን ተጠቀሟል፡፡ ኤቲ፡ “በሰማይ ያለው አባታችሁ በእርግጠኝነት ይሰጠዋል . . . እርሱ፡፡” ( ተመልከት) አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) ሰዎችን እንዲያደርጉላችሁ የሚትፈልጉትን ነገር ሁሉ “ሰዎች እንዲያደርጉላችሁ የሚትልጉትን ነገር ሁሉ” (UDB) ሕግ እና ነቢያት እነዚህ ናቸው በዚህ ሥፍራ ላይ “ሕግ” እና “ነቢያት” የሚለው ቃል ሙሴ እና ነቢያት የጻፏቸወ መጽሐፍትን ያመለክታል፡፡ ኤቲ፡ “ይህ ሙሴ እና ነቢያት የጻፉጽ ስለዚህ ጉዳይ ነው፡፡ ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ፡ ስለ ሁለቱ በሮች እና መንገዶች አጽኖት መስጠት ያስችለ ዘንድ ስትተረጉም “ሰፍ” የሚለው ቃል “ጠባብ” ከሚለው በተቻለ መጠን የሚለይ መሆኑን አሳይ፡፡ በጠባቢ በር ግቡ . . የሚገኙት ጥቂቶች ናቸው ይህ በመንገድ ላይ የሚሄድ እና ወደ መንግስቱ በበር የሚገባ ሰው ምስል ነው፡፡ ወደ አንደኛው መንግስት መግባት ቀላል ሲሆን ወደሌላኛው መንግስት መግባት ግን ከባድ ነው፡፡ ይህ ሰዎች የዘላለም ሕይወትን ለማግኘት ሰዎች ከባድ የሆነውን በሕይወታቸው እግዚአብሔርን መታዘዝ መቀበል እንደሚኖርባቸው ለማሳየት የቀረበ ምሳሌ ነው፡፡ እግዚአብሔር የተመታዘዝ ቀላሉን መንገድ ከመረጡ ወደ ስኦል ይገባሉ፡፡ ( ተመልከት) በጠባቢ በር ግቡ ይህንን ወደ ቁጥር 14 መጨረሻ ልትወስዱት ትችላላችሁ፡ “ስለዚህ በጠባቡ በር ግቡ”፡፡ በር . . . መንገድ አማራጭ ትርጉሞች 1) ይህ ወደ መንግስቱ መግቢያ በር እና ወደ በሩ የሚወስድ መንገድን ያመለክታል፡፡ ይህ ከሆነ በUDB ላይ ያለውን ቅደም ተከተል ልታለዋውጠው ትችላለህ፡፡ ወይም 2) “በር” እና “መንገድ” ሁለቱም የመንግስቱ መግቢያነ ናቸው፡፡ ይህ ከሆነ ቅደም ተከተሉን ማለዋወጥ አይኖርብህም፡፡ ( ተመልከት) ወደ ጥፋት . . . ወደ ሕይወት እነዚህ በግስ ልተረጎሙ ይችላሉ፡፡ ኤቲ፡ “ወደምትሞቱበት ሥፍራ . . . በሕይወት ወደሚትኖርቡት ሥፍራ” ( ተመልከት)
ተጠንቀቁ “ራሳችሁን ጠብቁ” የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡ ነገር ግን ተኩላዎች ከሆኑ ይህ ምሳሌያዊ አነጋገር መልካም እና መርዳት የሚፈልጉ መስለው የሚመጡ ነገር ግን ክፉ የሆኑ እና ከሚጎዷችሁ ሐሰተኛ ነቢያት ራሳችሁን ጠብቁ፡፡ ( ተመልከት) በፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ ይህ ምሳሌዊ ንግግር የሰውን ተግባር የሚያመለክት ነው፡፡ ኤቲ፡ “ዘፍ በፍሬው እንደሚታወቅ ሁሉ ሐሰተኛ ነቢያት በሥራቸው ይታወቃሉ፡፡” ( ተመልከት) ሰዎች ከኩርንችት. . . ይለቅማሉን ኢየሱስ ጥየቄን ሰዎችን ለማስተማር ተጠቅሟል፡፡ ሰዎች ለዚህ ጥያቄ ምላሱ አይ መሆኑን ማወቅ አለባቸው፡፡ ኤቲ፡ “ሰዎች ከኩርንችት . . . አይለቅሙም፡፡” ( ተመልከት) መልካም ዛፉ ሁሉ መልካ ፍሬን ያፈራል ኢየሱስ የፍሬን ምሳሌ በመጠቀም ጥሩ ሥራ ወይም ቃል ስለሚያመጡ ስለጥሩ ነቢያት መናገሩን ቀጥሏል፡፡ ( ተመልከት) የተበላሸ ዘፍ መጥፎ ፍሬ ያፈራል ኢየሱስ የፍሬን ምሳሌ በመጠቀም መጥፎ ሥራ ስለሚሠሩ መጥፎ ነቢያት መናገሩን ቀጥሏል፡፡ ( ተመልከት)
መልካምን ፍሬ የማያፈራውን ዘፍ ይቆረጣል እንዲሁም ወደ እሳት ይጣላል ኢየሱስ የፍሬውን ምሳሌ ሐሰተኛ ነቢያትን ለማመልከት ተጠቅሞዋል፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ በመጥፎ ዛፍ ላይ ምን እንደሚሆን ብቻ ተናግሯል፡፡ ይህ በተዘዋዋር መንገድ የሚያሳየው በሐሰተኛ ነቢያት ላይ ተመሳሳይ ነገር ነው፡፡ ( እና ተመልከት) ይቆረጣል፣ ወደ እሳትም ይጣላል ይህ በዚህ መንገድ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ይቆርጡትና ያቃጥሉታል፡፡ “ ( ተመልከት) በፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ “እነርሱን” የሚለው ቃል ነብያቱን ወይም ዛፎቹን ሊያመለክት ይችላል፡፡ የዛፉ ፍሬ እና የነቢያቱ ድርጊት የሁለቱም መልካ ወይም መጥፎ ሊሆን ይችላል፡፡ ከተቻለ ከሁለቱ አንዱን በሚያመለክት መልኩ ተርጉሙት፡፡ ( ተመልከት)
ወደ መንግስተ ሰማያት ይገባል በዚህ ሥፍራ ላይ “መንግስት” የሚለው ቃ እግዚአብሑር እንደ ንጉሥ መግዛቱን ያመለክታል፡፡ “መንግስተ ሰማያት” በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ ብቻ ጥቅም ላይ የዋለ ቃል ነው፡፡ ከተቻለ “ሰማይ” የሚለውን ቃል በትርጉማችሁ ውስጥ ለማኖር ጥረት አድርጉ፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ራሱን እንደ ንጉሥ በሚገልጥበት ጊዜ በሰማይ ከእግዚአብሔር ጋር ይኖራል፡፡” ( ተመልከት) የአባቴን ፈቃድ የሚያደረግ ማንኛውም ሰው “የአባቴን ፍላጎት የሚፈጽም ማንም ሰው” አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) በዚያ ቀን ኢየሱስ “በዚያ ቀን” በማለት የተናገረው አድማጮቹ በዚያ ቀን የሚለው ሀረግ የሚያመለክተው የፍርድ ቀንን እንደሆነ እንደሚገባቸው ታሳቢ በማድረግ ነው፡፡ አንባቢዎቻችሁ በግልጽ በዚያ ቀን የሚለው ሀረግ ትንቢት አልተናገርንምን . . . ሴጣንን አላወጣንምን . . . ብዙ ተዓምራትን አላደረግንምን? ሰዎች እነዚህ ነገሮች ማድረጋቸው ላይ ትኩረት ያደርጋሉ፡፡ ኤቲ፡ “ትንቡትን ተናግረናል . . . ሴጣንን አስወጥተናል . . . ታላላቅ ተዓምራን አድርገናል፡፡” ( ተመልከት) እኛ ይህ “እኛ” የሚለው ቃ ኢየሱስን አያካትትም፡፡ ( ተመልከት) በስምህ በዚህ ሥፍራ ላይ “በስምህ” የሚለው ቃል በኢየሱስ ስልጣን እና ስም” ማት ነው፡፡ ( ተመልከት) ታላላቅ ነገሮችን “ተዓምራትን” አላውቃችሁም ይህ ማለት ይህ ሰው የኢየሱስ አይደለም ማለት ነው፡፡ ኤቲ፡ “አንተ የእኔ ተከታይ አይደለህም” ወይም “ከአንተ ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የለኝም፡፡” ( ተመልከት)
ስለዚህ “በዚህ ምክንያት” ቃሎቼ በዚህ ሥፍራ ላይ “ቃሎቼ” የሚለው ቃል ኢየሱስ የተናገራውን ቃላት ያመለክታል፡፡ ( ተመልከት) በዓለት ላይ ቤትን የሠራን ጠቢብ ሰው ይመስላሉ ኢየሱስ የእርሱን ቃል የሚጠብቁ ሰዎችን ምንም ነገር ልጎዳው በማይችል መሠረት ላይ ቤታውን ከሠሩ ሰዎች ጋር ያነጻጽራል፡፡ ( ተመልከት) ዓለት ይህ በመሬት የላይኛው ክፍል ላይ ከመገኘው አፈር እ አሸዋ ቀጥሎ የሚገኝ ነው፡፡ በዚህ ላይ ቤቱን የገነባ ይህ በቀጥታ እንዲህ ልገለጽ ይገባል፡፡ ኤቲ፡ “የገነባው” ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ በ MAT 5:3. የተጀመረው የኢየሱስ የተራራው ስብከት መጨረሻ ነው፡፡ ሞኝ ሰው ቤቱን በአሸዋ ላይ ይሠራል ኢየሱስ ከዚህ በፊት ያቀረበውን ንጽጽር ቀጥሏል፡፡ ትዕዛዛቱን ያልታዘዙ ሰዎችን ቤታቸውን በአሸዋ ላይ ከሠሩ ሞኝ ሰዎች ጋር አነጻጽሯል፡፡ ቤቱን ዝናብ፣ ጎርፍ እና አውሎ ንፋስ ልያጠፋው በሚችል አሸዋማ መሬት ላይ የሚሠራ ሞኝ ሰው ብቻ ነው፡፡ ( ተመልከት) ወደቀ በቋንቋችሁ አንድ ቤት መውደቁን ለመግለጽ የሚትጠቀሙትን የተለመደ ቃል በዚህ ሥፍራ ላይ ተጠቀሙ፡፡ ጥፋቱ እጅግ በጣም የከፋ ይሆናል ዝናቡ፣ ጎር እና አውሎ ንፋሱ ቤቱን ፈጽሞ ያጠፋዋል፡፡
አጠቃላይ መረጃ እነዚህ ቁጥሮች ኢየሱስ በተራራው ስብከት ውስጥ ስላስተማራቸው ትመህርቶች የሰጠውን ምላሽ ምን ይህንን ከፈጸመ በኋላ ይህ ሀረግ የተራራው ስብከት መጨረሻ ለመሆኑ ምልክት ነው፡፡ ኤቲ፡ በመጨረሻውም” በትምህርቱ እጅግ በጣም ተገረሙ በ7፡29 ላይ ኢየሱስ ባስተማረው ትምህርት ብቻ ሳይሆን ባስተማረበት መንገድም እንደተገረሙ በግልጽ ማየት ይቻላል፡፡ ኤቲ፡ “በማስተማር ዘዴውም እጅግ በጣም ተገረሙ፡፡”
1 ኢየሱስ ከተራራው በወረደ ጊዜ፣ ብዙ ሕዝብ ተከተሉት። 2 እነሆ፣ አንድ ለምጻም ወደ እርሱ መጣ፣ “ጌታ ሆይ፣ ፈቃደኛ ከሆንህ፣ ልታነጻኝ ትችላለህ” በማለት በፊቱ ሰገደለት። 3 ኢየሱስም፣ “ፈቃደኛ ነኝ ንጻ” በማለት እፉን ዘርግቶ ዳሰሰው። ወዲያውኑ ከለምጹ ነጻ። 4 ኢየሱስ፣ “ተጠንቀቅ! ለማንም አትናገር። ዝም ብለህ ሂድና ራስህን ለካህን አሳይ፣ምስክር እንዲሆናቸውም ሙሴ ያዘዘውን ስጦታ አቅርብ”አለው። 5 ኢየሱስ ወደቅፍርናሆም በገባ ጊዜ፣ አንድ የመቶ አለቃ ወደ እርሱ መጥቶ፣ 6 ጌታ ሆይ፣ "አገልጋዬ በከባድ ሕመም ሽባ ሆኖ ቤቴ ተኝቷል" በማለት ለመነው። 7 ኢየሱስ፣ "መጥቼ እፈውሰዋለሁ” አለው። 8 የመቶ አለቃውም መልሶ፣“ጌታ ሆይ፣ አንተ ወደ ቤቴ ጣራ በታች ልትገባ አይገባኝም፣ ነገር ግን ቃል ብቻ ተናገር አገልጋዬም ይፈወሳል” አለው፡፡ 9 እኔ ደግሞ ከሌላው ሥልጣን ሥር ያለሁና በእኔም ሥልጣን ሥር ወታደሮች ያሉኝ ሰው ነኝ። አንዱን “ሂድ” ብለው ይሄዳል፤ ሌላውንም “ና” ብለው ይመጣል፣ አገልጋዬንም 'ይህን አድርግ' ብለው ያደርጋል"፡፡ 10 ኢየሱስም ይህን በሰማ ጊዜ በጣም ተደነቀ፣ ይከተሉት ለነበሩት ሰዎችም “እውነት ነው የምነግራችሁ፣ በእስራኤል እንኳ እንደዚህ ያለ ትልቅ እምነት አላገኘሁም” አላቸው፡፡ 11 እነግራችኋለሁ ብዙዎች ከምሥራቅና ከምዕራብ ይመጣሉ፣ በእግዚአብሔር መንግሥትም ከአብርሃም፣ ከይስሐቅና ከያዕቆብ ጋር በማዕድ ይቀመጣሉ። 12 የመንግሥት ልጆች ግን ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ወደ ውጪው ጨለማ ይጣላሉ፡፡ 13 ኢየሱስም የመቶ አለቃውን፣ “ሂድ! እንደ እምነትህ ይሁንልህ" አለው። አገልጋዩም በዚያው ሰዓት ተፈወሰ ፡፡ 14 ኢየሱስ ወደ ጴጥሮስ ቤት በገባ ጊዜ የጴጥሮስን አማት በትኩሳት ታማ ተኝታ አገኛት። 15 ኢየሱስ እጅዋን ነካት፣ ትኩሳቱም ለቀቃት፣ ተነሥታም ታገለግለው ጀመር። 16 በመሸ ጊዜ፣ ሕዝቡ አጋንንት የያዙአቸውን ብዙዎችን ወደ ኢየሱስ አመጡ፣ እርሱም በቃሉ፣ መናፍስቱን አስወጣቸው፤ ታመው የነበሩትንም ሁሉ ፈወሳቸው። 17 በዚህ ዐይነት፣ በነቢዩ ኢሳይያስ፣ “እርሱ ሕመማችንን ተቀበለ ደዌዎቻችንን ተሸከመ” ተብሎ የተነገረው ተፈጸመ። 18 ኢየሱስም በዙሪያው ያሉትን ሕዝብ ባየ ጊዜ፣ ወደ ገሊላ ባሕር ማዶ እንዲሻገሩ አዘዘ። 19 ከዚያም አንድ ጸሐፊ ወደ እርሱ ቀርቦ፣ “መምህር ሆይ፣ ወደምትሄድበት ሁሉ እከተልሃለሁ” አለው። 20 ኢየሱስም "ቀበሮዎች ጉድጓድ የሰማይ ወፎችም ጎጆዎች አሏቸው። የሰው ልጅ ግን ራሱን የሚያሳርፍበት ምንም ስፍራ የለውም"አለው። 21 ከደቀመዛሙርቱም ሌላው፣ "ጌታ ሆይ፣ በመጀመሪያ እንድሄድና አባቴን እንድቀብር ፍቀድልኝ አለው።" 22 ኢየሱስ ግን፣ “ተከተለኝ፣ ሙታናቸውን እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው” አለው። 23 ኢየሱስ ወደ ጀልባ በገባ ጊዜ፣ ደቀ መዛሙርቱም ተከትለውት ገቡ። 24 እነሆም፣ በባሕሩ ላይ ታላቅ ማዕበል ተነሥቶ ጀልባዋ በማዕበል ተሸፈነች። ኢየሱስ ግን ተኝቶ ነበር። 25 ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ መጥተው፣ "ጌታ ሆ፣ እድነን ልንጠፋ ነው" በማለት ቀሰቀሱት። 26 ኢየሱስ፣ "እናንተ እምነት የጐደላችሁ ስለምን ፈራችሁ?”አላቸው። ከዚያም ተነሥቶ ነፋሱንና ባሕሩን ገሠፀ፣ ከዚያ በኋላ ታላቅ ጸጥታ ሆነ። 27 ሰዎቹም ተገርመው፣ "ይህ ምን ዓይነት ሰው ነው? ነፋሳትና ባሕሩም እንኳ ይታዘዙለታል" አሉ። 28 ኢየሱስም ወደ ማዶ ወደ ጌርጌሴኖን አገር በመጣ ጊዜ፣ አጋንንት የተቆጣጠራቸው ሁለት ሰዎች ተገናኙት። የመጡትም ከመቃብር ነበርና በዚያ ማንም ማለፍ እስከማይችል ድረስ በጣም ኅይለኞች ነበሩ። 29 እነሆም፣ እየጮኹ፣ "አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ሆይ፣ እኛ ከአንተ ምን ጉዳይ አለን? ጊዜው ሳይደርስ ልታሠቃየን ወደዚህ መጣህን?" አሉ። 30 ከዚያ አካባቢ ብዙ ሳይርቅ በግጦሽ ላይ ያሉ ብዙ ዐሳማዎች ነበሩ። 31 አጋንንቱም ኢየሱስን፣ "የምታወጣን ከሆነ ወደዚያ የዐሳማዎች መንጋ ስደደን" ብለው መለመናቸውን ቀጠሉ። 32 ኢየሱስም፣ "ሂዱ!"አላቸው። አጋንንቱም ወጥተው ዐሳማዎቹ ውስጥ ገቡ፤ እነሆም፣ የዐሳማዎቹ መንጋ ሁሉ ወደ ታች ቁልቁለቱን እየተጣደፉ ወደ ባሕሩ ወርደው ውሃው ውስጥ ገብተው ጠፉ፡፡ 33 እነዚያም ዐሳማዎቹን ይጠብቁ የነበሩት ሰዎች ሸሽተው ወደ ከተማ ሄደው የሆነውን ሁሉ ፣ በአጋንንት ተይዘው ስለ ነበሩት ሰለ ሁሉቱ ሰዎችም አወሩ። 34 የከተማውም ሕዝብ ሁሉ ኢየሱስን ለማየት መጡ። ባዩትም ጊዜ አካባቢያቸውን ለቆ አንዲሄድ ለመኑት።
አጠቃላይ መረጃ፡ ይህ በታሪክ ውስጥ ኢየሱስ ብዙ ሰዎችን የፈወሰበት የአዲሱ ክፍል ጅማሬ ነው፡፡ ይህ ጭብጥ በእነዚህ ውስጥ ይቀጥላል MAT 9:35. ( ተመልከት) ኢየሱስ ከተራራ በወረደ ጊዜ ብዙ ሕዝብ ተከተለው “ኢየሱስ ከተራራ ከወረደ በኋላ ብዙ ሕዝብ ከተለው፡፡” ይህ ሕዝብ በተራራው ከእርሱ ጋር የነበሩትን እንዲሁም ያልነበሩትንም ሊያካትት ይችላል፡፡ እነሆ “እነሆ” የሚለው ቃል በታሪክ ውስጥ አዲስ ሰውን ያስተዋውቀናል፡፡ በቋንቋችሁ ይህንን የሚታደርጉበት ቃል ሊኖራችሁ ይችላል፡፡ ለምጻም “ለምጽ ያለበት ሰው” ወይም “የቆዳ በሽታ ያለበት ሰው፡፡” (UDB) በፊቱ ሰገደ ይህ በኢየሱስ ፊት ያሳየው ትህትና የሞላበት አቀራረብ ምልክት ነው፡፡ ( ተመልከት) ፈቃደኛ ከሆንክ “ከፈለግህ” ወይም “ፍላጎት ካለህ”፡፡ ለምጻሙ ሰው ኢየሱስ እርሱን የመፈወስ ኃይል እንዳለው አውቋል ይሁን እንጂ ኢየሱስ እርሱን ለመንካት ፈቃደኛ ይሁን አይሁን ግን አላወቀም፡፡ ልታነጻኝ ትችላለህ በዚህ ሥፍራ ላይ “ልታነጻኝ” የሚለው ቃል መፈወስን እና በማሀህበረሰቡ ውስጥ እንደገና ተቀላቅሎ መኖርን የሚያመለክት ቃል ነው፡፡ ኤቲ፡ “ልትፈውሰኝ ትችላለህ” ወይም 1እባክህ ፈውሰኝ”፡፡ (UDB) ( ተመልከት) ወዲያው “በዚያን ጊዜ” ከለምጹ ነጻ “ንጻ” የሚለው የኢየሱስ ንግግር ውጤቱ የሰውዬው መፈወስ ነው፡፡ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ጤነኛ ሆነ” ወይም “ለምጹ ለቀቀው” ወይም “ከለምጹ ነጻ”፡፡ ( ተመልከት)
ለእርሱ ይህ ኢየሱስ የፈወሰውን ሰው ያመለክታል፡፡ ለማንም አትናገር “ለማንም ምንም አትናገር” ወይም “እኔ እንደፈወስኩህ ለማንም አትናገር” ለካህናት ራስህን አሳይ የአይሁዳዊያን ሕግ የተፈወሰ ሰው ቆዳውን ለካህናት ማሳየት እንዳለበት ይጠይቃል፡፡ እነርሱም ቆዳውን ከተመለከቱ በኋላ ከሕዝቡ ጋር እንዲቀላቀል ይፈቅዱለታል፡፡ ( ተመልከት) ለእርሱ ምስክር ይሆንህ ዘንድ በሙሴ ትዕዛዝ መሠረት መስዋዕትን አቅርብ በሙሴ ሕግ መሠረት ከለምጽ የተፈወሰ ሰው የምስጋና መስዋዕትን ለከካህናት ማቅረብ ይኖርበታል፡፡ ካህናቱ ስጦታውን ከተቀበሉ ሕዝቡ ይህ ሰው መፈወሱን ያውቃሉ፡፡ ( ተመልከት) ለእነርሱ ይህ የሚያመለክተው 1) ካህናትን ወይም 2) ሌሎች ሰዎችን ወይም 3) ኢየሱስን የሚተቹ ሰዎችን ሊሆን ይችላል፡፡ ከተቻለ ከእነዚህ ቡድኖች መካከል ዬትኛውንም የሚያመለክትን ስም ተጠቀሙ፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ የታሪኩ ክፍል ውስጥ ጸሐፊው ወደሌላ ጊዜ እና ቦታ በመሄድ ኢየሱስ ሌላ ሰው የፈወሰበትን ሁኔታ ያሳያል፡፡ ወደ እርሱ መጥቶ ጠየቀው “በዚህ ሥፍራ “እርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው፡፡ ሽባ “ከበሽታው የተነሳ ከቦታ ቦታ መዘዋወር የማይችል” ኢየሱስም እንዲህ አለው፡፡ “ኢየሱስ ለመቶ አለቃው እንዲህ አለው” መጥቼ እፈውሰዋለሁ “ወደ ቤትህ መጥቼ ባርያህን አድነዋለሁ፡፡”
ወደ ቤቴ ጣሪያ ሥር ግባ “”የቤቴ ጣሪያ ሥር” የሚለው ሀረግ “ቤቴ” ማለት ነው፡፡ ( ተመልከት) ቃል ተናገር በዚህ ሥፍራ “ቃል” የሚለው ቃል ትዕዛዝ ስጥ ማለት ነው፡፡ ኤቲ፡ “ትዕዛዝ ስጥ”፡፡ ( ተመልከት) ይፈወሳል ይህ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ይድናል፡፡” ( ተመልከት) በስልጣን ሥር ያለ ይህ በዚህ መልኩ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “በሌላ ሰው ሥልጣን ሥር ያለ ማንኛውም ሰው፡፡” ( ተመልከት) በሥልጣን ሥር . . . በእኔ ሥር በአንድ ሰው “ሥር” መሆን ማለት የሌላ ሰው ትዕዛዝ እንደሚበልጥ በማወቅ ትዕዛዙን መቀበል፡፡ ( ተመልከት) ወታደሮች “የሰለጠኑ ተደባዳቢዎች” እውነት እልሃለሁ “እውነት እልሃለሁ፡፡” ይህ ሀረግ ኢየሱስ በቀጣይነት የሚናገረው ነገር ላይ ትኩረት እንዲደረግ ይጋብዛል፡፡ እንዲህ ዓይነት እምነት በእስራኤል እንኳ አላገኘሁም የኢየሱስ አድማጮች የእግዚአብሔር ልጆች እንደሆኑ የሚያስቡት በእስራኤል ያሉ አይሁዳዊያን ከማንም ይልቅ ታላቅ የሆነ እምነት እንደሚኖራቸው ያስቡ ነበር፡፡ ኢየሱስ ግን ተሳስተዋል በማለት ተናግሯል፡፡ የመቶ አለቃው እምነት ከሁሉ ታላቅ ነበር፡፡ ( ተመልከት)
አንተ በዚህ ሥፍራ ላይ “አንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥርን የሚያመለክት ሲሆን “እርሱን የሚከተሉትን ሰዎችን” ነው፡፡ MAT 8:10. (: ተመልከት) ከምስራቅ እና ከምዕራብ ተቃራኒ የሆኑትን “ምቅራቅ” እና “ምዕራብ”ን በመጠቀም “በሁሉም አከባቢ” የሚል መልዕክት አስተላልፏል፡፡ ኤቲ፡ “በሁሉም አከባቢ” ወይም “በሁሉም አቅጣጫ ከሩቅ ሥፍራ” ( ተመልከት) በማዕድ ይቀመጣሉ በዚያ ባሕል ውስጥ ያሉ ሰዎች ምግብ በሚመገቡበት ወቅት በጠረጴዛ ዙሪያ ይቀመጣሉ፡፡ ይህ ሀረግ የሚያመለክተው በጠረጴዛው ዙሪያ የሚቀመጡት ቤተሰብ እና የቅርብ ጓደኞች ናቸው፡፡ ኤቲ፡ “እንደ ቤተሰብ ከዳኞች ጋር መኖር”፡፡ ( ተመልከት) በመንግስተ ሰማያት በዚህ ሥፍራ “መንግስት” የሚለው ቃል እግዚአብሔር እንደ ንጉሥ የሚገዛበትን የሚያመለክት ነው፡፡ “መንግስ ሰማያት” የሚለው ሀረግ ጥቅም ላይ የዋለው በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ ብቻ ነው፡፡ ከተቻለ “ሰማይ” የሚለውን ቃል በትርጉማችሁ ውስጥ ላማስቀመት ሞክሩ፡፡ ኤቲ፡ “በሰማይ ያለው አምላካችን ንጉሥ መሆኑን በሚሳይበት ጊዜ፡፡” ( ተመልከት) የመንግስቱ ለልጆች ይጣላሉ ይህ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር የመንግስቱን ልጆች አውጥቶ ይጥላቸዋል፡፡” ( ተመልከት) የመንግስ ልጆች “የ. . . ልጆች” የሚለው ሀረግ የሚያመለክተው የእርሱ የሆኑት ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ የእግዚአብሔር መንግስት የሆኑት ማለት ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በዚህ ሥፍረ ምጸታዊ ንግግር አለ ምክንያቱም እንግዶች ወደ መንግስቱ እንዲገቡ ሲደረግ “ልጆች” ወደ ውጪ ይጣላሉ፡፡ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ይገዛቸው ዘንድ የፈቀዱለት”፡፡ ( እና ተመልከት) ወደ ውጭ ጨለማ ይህ እግዚአብሔርን ያልተቀበሉት ዘላለማዊ መዳረሻቸው ምን እንደሆነ የሚያሳይ ነው፡፡ ኤቲ፡ “ከእግዚአብሔር የራቀ ጨለማ ሥፍራ” ወይም “ስኦል”፡፡ ( ተመልከት) ለእናንተ ይሆን ዘንድ ይህ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ለእናንተ አደርገዋለሁ፡፡” ( ተመልከት) ባሪያው ተፈወሰ ይህ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ኢየሱስ ባሪያወን ፈወሰ፡፡” ( ተመልከት) በዚያው ሰዓት “ኢየሱስ ባሪያውን እፈውሰዋለሁ ብሎ በተናገረበት ቅጽበት”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ጸሐፊው ታሪኩን ወደ ሌላ ጊዜ እና ቦታ በመቀየር ኢየሱስ ሌላ ሰው የፈወሰበትን ሁኔታ ያሳየናል፡፡ ኢየሱስ መጥቶ ደቀ መዛሙርቱ ምናባት ከእርሱ ጋር ልሆኑ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን የታሪኩ ዋና ትኩረት ኢየሱስ ስላደረገው እና ሰስለተናገረው ነገር ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ደቀ መዛሙርቱን የጠቀሰበት ምክንት የተሳሳተ ትርጉም እንዳይኖር በማለት ነው፡፡ የጴጥሮስ አማች “የጴጥሮስ ምስት እናት” ንዳዱ ትቷት ሄደ በቋንቋችሄ እንዲህ ያለ ሰውኛ የአጻጻፍ ስልት ማለትም ንዳድ በራሱ አስቦ አንድን ነገር እንደሚፈጽ የሚሳይ ሰውኛ የአነጋገር ስልት ካለ “ተሸለት” ወይም “ኢየሱስ ፈወሳት” ተብሎ ልተረጎም ይችላል፡፡ ( ተመልከት) ተነስታ “ከተኛችበት አልጋ ተነስታ”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር› በዚህ ሥፍራ የታሪኩ ፍሰት በዚያው ቀን ምሽት ላይ ኢየሱስ ብዙ ሰዎችን ወደ ፈወሰበት እና ሴጣንን ከብዙ ሰዎች ወደአወጣበት ታርክ ይዞራል፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጥር 17 ላይ ጸሐፊው የኢየሱስ የፈውስ አገልግሎቱን በነብያት የተነገው ትንቢት ፍጻሜ መሆኑን ከነብዩ ኢሳያስ መጽሐፍ ውስጥ በመጥቀስ ጽፏል፡፡ በመሸም ጊዜ ይህ ከሰንበት በኋላ መሆኑን ያሳያል ምክንያቱም አይሁዳዊየን በሰንበት ቀን ሥራ አይሠሩም ወይም መንገድ አይሄዱም፡፡ እስኪመሽ ድረስ ጠብቀው ሰዎችን ወደ ኢየሱስ አመጡ፡፡ የተሳሳተ ትርጉምን ከማስወገድ አንጻር ካልሆነ በስተቀር ሰንበት የሚለው ቃል መጥቀሱ አስፈላጊ አይደለም፡፡ ( ተመልከት) በዳብሎ የተያዙ ብዙ ሰዎችን ወደ እርሱ አመጡ ይህ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ብዙ በዳብሎስ የተያዙ” (UDB) ወይም “በዳብሎስ ቁጥር ሥር የሆኑ ብዙ ሰዎች” ( ተመልከት) በቃሉ መናፍስቱን አስወጣ በዚህ ሥፍራ “ቃል” የሚለው ቃል ትርጉሙ ትዕዛዝ ነው፡፡ ኤቲ፡ “መንፈሱ እንዲወጣ አዘዘ፡፡” ( ተመልከት) በነብይ ኢሳያስ የተነገረው ትንቢትን ይፈጽም ነበር ይህ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ነብዩ ኢሳያስ ለእስራኤል ሕዝብ የተናገረው የትንቢት ቃልን ኢየሱስ ፈጸመው፡፡ () ተመልከት) ድካማችን ተቀበለ ደዊያችንንም ተሸከመ ማቴዎስ ከነብዩ ኢሳያስ መጽሐፍ በዚህ ሥፍራ ላይ ጠቅሷል፡፡ እነዚህ ሁለቱ ሀረጋት በመሠረታዊ መልዕክታቸው ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ሁለቱም አጽኖት የሚሰጡት እርሱ ሁሉንም በሽታችንን ፈውሷል፡፡ ኤቲ፡ “የታመሙትን ፈውሷል እንዲሁም ደና አድርጓቸዋል፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ላይ ታሪኩ ኢየሱስ ልከተሉት ለሚፈልጉ ሰዎች የሰጠው ምላሽ ምን እንደሆነ ወደማሳየት ይሄዳል፡፡ አሁን በዚህ ሥፍራ ይህ ቃል ጥቅም ላይ የዋለው በዋናው ታርክ ውስጥ አዲስ ታሪክ መጀመሩን ለማሳየት ነው፡፡ ማቴዎስ በዚህ ሥፍራ ላይ የታሪኩን አዲስ ክፍል ይነግረናል፡፡ መመሪያዎች ሰጠ “ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አላቸው” ከዚያ ማለትም ኢየሰስ “መመሪያዎችን ከሰጠ በኋላ ነገር ግን ወደ ታንኳይቱ ከመግባቱ በፊት በዬትም ሥፍራ “በዬትኛውም ቦታ” ቀበሮዎች ጉድጓድ አላቸው እንዲሁም የሰማይ ወፎች ጎቾ አላቸው ቀበሮዎች ቀበሮዎች እንደ ውሻ ያሉ እንስሳት ናቸው፡፡ በጎጆዋቸው ውስጥ ያሉትን አእዋፋት እና ሌሎች ትንንሽ እንስሳትን ይበላሉ፡፡ ቀበሮዎች በእናንተ ዙሪያ የማይታወቁ ከሆነ እንደ ውሻ ያለ በማለት አጠቃላይ ቃልን ተጠቀሙ፡፡ ( ተመልከቱ) ጉድጋዶች ቀበሮዎች ለመኖሪያቸው የሚሆን ጉድጓድን ይቆፍራሉ፡፡ ቀበሮወችን ለማመልከት የተጠቀማችኋቸው እንስሳት የሚኖሩበትን ሥፍራ ግለጹ፡፡ የሰው ልጅ ኢየሱስ ስለ ራሱ እየተናገረ ነው፡፡ ( ተመልከት) ራሱን የሚያሳርፍበት ሥፍራ ይህ የመተኛ ሥፍራን ያመለክታል፡፡ ኤቲ፡ “የሚተኛበት የራሱ ሥፍራ የለውም፡፡” ( ተመልከት)
በመጀመሪያ አባቴን እንድቀብረው ፍቀድልኝ የሰውዬው አባት መሞቱን እና ወዲያው መቅበር እንዳለበት በእርግጠኝነት ማወቅ አይቻልም ወይም አባቱ እስኪሞት እና እስኪቀበር ድረስ ለረጅም ጊዜ መቀየት ይኖርበት አይኖርበት የሚታወቅ ነገር የለም፡፡ ዋናውን ነጥብ ይህ ሰው ኢየሱስን ከመከተሉ በፊት ሌላ አዲስ ነገር ማድረግ ይፈለጋል ማለት ነው፡፡ ሙታን ሙታናቸውን ይቀብሩ ዘንድ ተዋቸው በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ በቀጥታ የሞቲ ሰዎች ሌሎች የሞቱትን ይቅበሩ ማለቱ አይደለም፡፡ “ሙታን” የሚለው ቃል አማራጭ ትርጉሞች 1) በቅርብ ጊዜ ስለሚሞቱ ሰዎች የሚነገር ምሳሌያዊ አነጋገር ወይም 2) ኢየሱስን የማይከተሉ እና መንፈሳዊ ሞት የሞቱ ሰዎችን ለማመልከት የሚውል ሚሳሌያዊ አነጋገር፡፡ ዋናው ነጥብ ማንኛውም ኢየሱስን መከተል ለሚወድ ሰው ምንም ነገር ሊያዘገየው አይገባም፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ላይ የታሪኩ ፍሰት ኢየሱስ እና ደቀ መዛሙር የገሊላን ባሕር ሽሻገሩ የተነሳውን ማዕበል ኢየሱስ እንዴት ጸጥ እንዳደረገው ወደሚያሳይ ታሪክ ይለወጣል፡፡ ወደ ታንኳይቱ ገቡ “ወደ ተንኳ ገቡ” ደቀ መዛሙርቱ ተከተሉት ለ”ደቀ መዛሙር” እና “ተከተል” ለሚለው ቃል በ(MAT 8:21-22). ላይ የተጠቀምከውን ተመሳሳይ ቃላትን ተጠቀም፡፡ እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይራል፡፡ ኤቲ፡ “በድንገት”(UDB) ወይም “ያለምንም ማስጠንቀቂያ” ባሕሩም በታላቅ ማዕበል ተናወጠ ኤቲ፡ “ታላቅ ማዕበል ባሕሩን አናወጠው” በዚህም ምክንያት ታንኳይቱን ውሃ ሞላት ይህ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “ስለዚህም ምክንያት ታንኳይቱን ውሃ ሞላት”፡፡ ( ተመልከት) ተነስ አድነን አሉት የዚህ ሀረግ አማራጭ ትርጓሜዎች 1) በመጀመሪያ ኢየሱስን ከተኛት ቀስቅሰው “አድነን” አሉት ወይም 2)ኢየሱስን እየቀሰቀሱት “አድነን” አሉት፡፡ እኛ . . . እኛ ይህ ቃል ሁሉን የሚያጠቃልል ወይም የማያጠቃልል አድርገን የሚንተረጉመው ከሆነ ሁሉን የሚያጠቃልል ቃልን ብንጠቀም መልካም ይሆናል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ምናልባት ኢየሱስ እነርሱን እና ራሱን ከትንኳይቱ መስጠም እንዲታደግ ያቀረቡት ጥያቄ ሊሆን ይችላል፡፡ ( ተመልከት) መሞታችን ነው “ልንሞት ነው”
ለእነርሱ “ለደቀ መዛሙርቱ” ለምን ፈራችሁ . . . እምነት? ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ጥያቄ በመጠየቅ ይገስጻቸዋል፡፡ ኤቲ፡ “ልትፈሩ አይገባም . . እምነት” ወይም “የምትፈሩበት አንዳች ምክንያት የለም . . . እምነት፡፡” ( ተመልከት) እናንተ ትንሽ እምነት ያላችሁ ይህንን በ MAT 6:30 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡ ንፋስን እና ባሕር የሚታዘዙለት ይህ ምን ዓይነት ሰው ነው? “ንፋስና ባሕር ይታዘዙታል! ምን ዓይነስ ሰው ነው? ይህ የደቀ መዛሙርቱን አግራሞት የሚያሳይ ጥያቄ ነው፡፡ ኤቲ፡ “ይህ ከሌሎች ሰዎች ሁሉ የተለየ ነው! ንፋስ እና ማዕበል ሳይቀር ይታዘዙታል!” ( ተመልከት) ንፋስ እና ባሕር ሳይቀር ይታዘዙታል ሰዎች ወይም እንስሳት ቢታዘዙት ወይም ባይታዘዙት ብዙም አያስደንቅም ነገር ግን ንፋስ እና ውሃ እርሱን መታዘዛቸው በጣም አስደናቂ ነገር ነው፡፡ ይህ በሰውኛ የቀረበው ሀሳብ ተፈጥሮአዊ ነገሮች ልክ እንደ ሰው ሰምተው ምላሽ መስጠጥ ይችላሉ፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ላይ ጸሐፊው ከዚህ በፊት ወደ ጀመረው ኢየሱስ በሽተኞችን ወደሚፈውስበት አገልግሎት ታሪኩ ተመልሶ እናገኘዋለን፡፡ በዚህ ታሪክ ውስጥ መጀመሪያ ላይ ኢየሱስ ሁለት በዳብሎስ እስራት ተይዘው የነበሩትን ሰዎች ነጻ ሲያወጣ እንመለከታለን፡፡ በዚያኛው በኩል “ከገሊላ ባሕር ማዶ” የጌርጋሴኖን ሀገር ጌርጋሴኖን የጌርጋ ከተማ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) እነርሱም ሰው በዚያ መንገድ ማለፍ እስኪሳነው ድረስ በጣም አስቸጋሪዎች ነበሩ እነዚህን ሁለት ሰዎችን የያዙት ዳብሎሶች በጣም አደገኞች ከመሆናቸው የተነሳ ማንም ሰው በዚያ በኩል ማለፍ አይችልም ነበር፡፡ እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይራል፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ ከአንተ ጋር ምን አለን? ይህንን ጥያቄ የጠየቁት በቁጣ ነበር፡፡ ( ተመልከት) የእግዚአብሔር ልጅ ይህ ኢየሱስ ከእግዚብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያሳይ የኢየሱስ ወሳኝ የሆነ መጠሪያ ስሙ ነው፡፡ ( ተመልከት) ጊዜው ሳይደርስ ልትሣቅየን ወደዚህ መጣህን? ሁለተኛው ጥያቄም ሰላማዊ የሆነ ጥያቄ አልነበረም፡፡ ትረጉሙም “እግዚአብሔር እኛን ለመቅጣት የወሰነው ጊዜ ሳይደርስ መጥተህ እኛን በመቅጣት እግዚአብሔርን መታዘዝ መተው የለብህም፡፡” ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ላይ ጸሐፊው ከዚህ በፊት ወደ ጀመረው ኢየሱስ በሽተኞችን ወደሚፈውስበት አገልግሎት ታሪኩ ተመልሶ እናገኘዋለን፡፡ በዚህ ታሪክ ውስጥ መጀመሪያ ላይ ኢየሱስ ሁለት በዳብሎስ እስራት ተይዘው የነበሩትን ሰዎች ነጻ ሲያወጣ እንመለከታለን፡፡ በዚያኛው በኩል “ከገሊላ ባሕር ማዶ” የጌርጋሴኖን ሀገር ጌርጋሴኖን የጌርጋ ከተማ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) እነርሱም ሰው በዚያ መንገድ ማለፍ እስኪሳነው ድረስ በጣም አስቸጋሪዎች ነበሩ እነዚህን ሁለት ሰዎችን የያዙት ዳብሎሶች በጣም አደገኞች ከመሆናቸው የተነሳ ማንም ሰው በዚያ በኩል ማለፍ አይችልም ነበር፡፡ እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይራል፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ ከአንተ ጋር ምን አለን? ይህንን ጥያቄ የጠየቁት በቁጣ ነበር፡፡ ( ተመልከት) የእግዚአብሔር ልጅ ይህ ኢየሱስ ከእግዚብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያሳይ የኢየሱስ ወሳኝ የሆነ መጠሪያ ስሙ ነው፡፡ ( ተመልከት) ጊዜው ሳይደርስ ልትሣቅየን ወደዚህ መጣህን? ሁለተኛው ጥያቄም ሰላማዊ የሆነ ጥያቄ አልነበረም፡፡ ትረጉሙም “እግዚአብሔር እኛን ለመቅጣት የወሰነው ጊዜ ሳይደርስ መጥተህ እኛን በመቅጣት እግዚአብሔርን መታዘዝ መተው የለብህም፡፡” ( ተመልከት)
አሁን ይህ ቃል ጸሐፊው የታሪኩን ቀጣይ ክፍል ከመተረኩ በፊት አንባቢዎቹ ማወቅ ያለባቸውን አንድ መረጃ እንደሚሰጣቸው ያሳያል፡፡ ኢየሱስ ወደዚያ ሥፍራ ከመምጣቱ በፊት አሳማዎች በዚያ ሥፍራ ነበሩ፡፡ ( ተመልከት) ካስወጣኸን ኤቲ፡ “ልታስወጣን ስለሆነ” እኛ ይህ ሁሉን አቀፍ ነው፤ ትርጉሙም ለአሳማዎች ብቻ ነው፡፡ ( ተመልከት) እነርሱ በሰውዬው ውስጥ ያለው እርኩስ መንፈስ እርኩስ መንፈሱም ከሰውዬው ውስጥ ወጥቶ ወደ አሳማዎቹ ገባ ኤቲ፡ “እርኩስ መንፈሱም ከሰውዬው ውስጥ ወጥቶ ወደ አሳማዎቹ ገባ” እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይራል፡፡ ከተራራወ አፋፍ ወደታች ሮጡ ኤቲ፡ “በፍጥነት ከተራራው አናት ወደታች ሮጡ” በውሃ ውስጥ ሞቱ ኤቲ፡ “በውሃ ውስጥ ወድቀው ሰመጡ”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ኢየሱስ በእርኩስ መንፈስ የተያዙ ሁለት ሰዎችን ኢየሱስ የፈወሰበት ታሪክ ማጠቃለያ ነው፡፡ አሳማዎች የሚያሰማሩ “አሳማዎችን የሚጠብቁ” በእርኩስ መንፈስ የተያዙት ሰዎች ምን እንደሆኑ ኤቲ፡ “በእርኩስ መንፈስ የተያዙትን እነነዚህ ሰዎች ለማገዝ ኢየሱስ ያደረገው ነገር” እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይራል፡፡ በሁሉም ከተሞች ይህ ማለት ብዙ ወይም አብዛኞቹ ሰዎች ማለት እንጁ ሁሉም ሰዎች ማለት የግድ አይደለም፡፡ ( ተመልከት) አከባቢ ኤቲ፡ “ከተማዋ እና በአካቢው ያሉት”
1 ኢየሱስ ወደ ጀልባ ገባ፤ ባሕሩንም አቋርጦ ወደ ገዛ ከተማው መጣ። 2 እነሆ፣ በምንጣፍ የተኛ አንድ ሽባ ሰው ወደ እርሱ አመጡ። ኢየሱስም እምነታቸውን በማየት ሽባውን፣ “አንተ ልጅ፣ አይዞህ፤ ኅጢአትህ ይቅር ተብሎልሃል” አለው፡፡ 3 አንዳንድ ጸሐፍት ግን እርስ በርሳቸው፣ "ይህ ሰው እኮ እየተሳደበ ነው" ተባባሉ ። 4 ኢየሱስም ዐሳባቸውን ዐውቆ፣ “ስለ ምን በልባችሁ ክፉ ታስባላችሁ?” 5 ለመሆኑ የሚቀለው፣'ኃጢአትህ ይቅር ተብሎልሃል' ነው፣ ወይስ 'ተነሣና ሂድ ማለት ነው?' 6 ነገር ግን የሰው ልጅ በምድር ላይ ኃጢአትን ይቅር የማለት ሥልጣን እንዳለው ዕወቁ" አለ፡፡ ሽባውንም፣ "ተነሣና፣ምንጣፍህን ይዘህ ወደ ቤት ሂድ" አለው፡፡ 7 ከዚያም ሰውየው ተነሥቶ ወደ ቤቱ ሄደ። 8 ሕዝቡም ይህን ባዩ ጊዜ ተገርመው፣ ለሰው እንዲህ ያለ ሥልጣን የሰጠውን እግዚአብሔርን አመሰገኑ። 9 ኢየሱስም ከዚያ አለፍ እንዳለ፣ ማቴዎስ የሚባለውን ሰው በቀረጥ መሰብሰቢያ ቦታ ላይ ተቀምጦ አየውና "ተከተለኝ" አለው።እርሱም ተነሥቶ ተከተለው፡፡ 10 ኢየሱስም በቤቱ ውስጥ ለመመገብ በተቀመጠ ጊዜ፣ ቀረጥ የሚሰበስቡ ብዙ ሰዎችና ኃጢአተኞች መጥተው፣ ከኢየሱስና ከደቀ መዛሙርት ጋር አብረው ተመገቡ። 11 ፈሪሳውያንም ይህን ሲያዩ፣ደቀ መዛሙርቱን "ለምንድን ነው መምህራችሁ፣ ከግብር ሰብሳቢዎችና ከኃጢአተኞች ጋር የሚበላው?" አሏቸው፡፡ 12 ኢየሱስም ይህንን ሲሰማ ፣"ሕመምተኞች እንጂ ጤነኞች ሐኪም አያስፈልጋቸውም፡፡ 13 'ሂዱና' ምሕረት እንጂ መሥዋዕትን አልፈልግም' የሚለውን ተማሩ፣ እኔ የመጣሁት ጻድቃንን ሳይሆን ኅጥአንን ወደ ንስሓ ለመጥራት" ነው አለ። 14 ከዚያም የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት መጥተው፣" እኛና ፈሪሳውያን ብዙ ጊዜ እንጾማለን ፣የአንተ ደቀ መዛሙርት ግን የማይጾሙት ለምንድን ነው?" አሉት። 15 ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፣ “ሰርገኞች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር እያለ እንዴት ሊያዝኑ ይችላሉ? ሆኖም ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ጊዜ ይመጣል፣በእነዚያ ቀናት ይጾማሉ። 16 ማንም ሰው በአሮጌ ልብስ ላይ ዐዲስ ቊራጭ ጨርቅ አይለጥፍም፤ ምክንያቱም አሮጌውን ልብስ ይቦጭቀዋል፣ ልብሱም የባሰ ይጐዳል። 17 ሰዎች ዐዲስ የወይን ጠጅ በአሮጌ አቁማዳ ውስጥ አያስቀምጡም፤ እንደዚያ ካደረጉ አቁማዳው ይፈነዳል፣ የወይን ጠጁ ይፈሳል፣ አቁማዳውም ይቀደዳል። ይልቁንም ዐዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ውስጥ ያስቀምጡታል፣ ሁለቱም ይጠበቃሉ፡፡" 18 ኢየሱስ ይህን እየተናገራቸው እያለ፣ አንድ ሹም እየሰገደ ወደ እርሱ መጣ። “ልጄ አሁን ገና ሞተች፣ ነገር ግን ና ና እጅህን ጫንባት በሕይወትም ትኖራለች አለው”። 19 ኢየሱስም ተነሥቶ ተከትሎት ሄደ፤ ደቀ ዛሙርቱም ደግሞ አብረውት ሄዱ። 20 አንዲት ለዐሥራ ሁለት ዓመት ከባድ የደም መፍሰስ የነበረባት ሴት፣ ከኢየሱስ ኋላ መጥታ የልብሱን ጠርዝ ነካች፤ 21 "የልብሱን ጫፍ ብቻ ብነካ ደኅና እሆናለሁ" ብላ ነበርና። 22 ኢየሱስም ዞር ብሎ አያትና፣ “ልጄ ሆይ፣ አይዞሽ እምነትሽ አድኖሻል” አላት። ሴቲቱም ወዲያውኑ ደኅና ሆነች። 23 ኢየሱስም ወደ ሹሙ ቤት በገባ ጊዜ፣ዋሽንት የሚነፉትንና የሚንጫጩትን አይቶ፣ 24 "ወደዚያ ዞር በሉ፣ ልጅቷ ተኝታለች እንጂ አልሞተችም"አላቸው። እነርሱ ግን በማፌዝ ሳቁበት። 25 ሕዝቡን ወደ ውጭ ባስወጡ ጊዜ፥ ኢየሱስ ወደ ክፍሉ ገብቶ እጅዋን ያዘ፤ልጅቱም ተነሣች። 26 ወሬውም በዚያ አካባቢ ሁሉ ተዳረሰ። 27 ኢየሱስም በዚያ ሲያልፍ፣ ሁለት ዐይነ ስውሮች ተከተሉት፣ ያለ ማቋረጥም፣ "የዳዊት ልጅ ማረን!" እያሉ ይጮኹ ነበር። 28 ኢየሱስም ወደ ቤቱ በገባ ጊዜ፣ ዐይነ ስውሮቹ ወደ እርሱ መጡ። ኢየሱስም፣ "ይህን ለማድረግ እንደምችል ታምናላችሁ?" አላቸው። እነርሱም "አዎን፣ ጌታ ሆይ" አሉት፡፡ 29 ከዚያም ኢየሱስ ዐይኖቻቸውን ዳስሶ፣ "እንደ እምነታችሁ ይሁንላችሁ" አላቸው። 30 ዐይኖቻቸውም ተከፈቱ። ከዚያም ኢየሱስ፣"ይህንን ማንም እንዳያውቅ" ብሎ በጥብቅ አዘዛቸው። 31 ሁለቱ ሰዎች ግን ሄደው ወሬውን በየቦታው አዳረሱት። 32 ሁለቱ ሰዎች እየሄዱ እያሉ እነሆ፣ በጋኔን የተያዘ ዲዳ ወደ ኢየሱስ አመጡ። 33 ጋኔኑም ከወጣ በኋላ ዲዳው ተናገረ። ሕዝቡም ተገርመው፣ "እንዲህ ያለ ከዚህ በፊት በእስራኤል አልታየም" አሉ። 34 ፈሪሳውያን ግን "አጋንንትን የሚያወጣው በአጋንንት አለቃ ነው" ይሉ ነበር። 35 ኢየሱስ ወደ ከተሞችና መንደሮች ሁሉ ሄደ፣ በየምኩኲራቦቻቸውም ማስተማሩን፣ የመንግሥትን ወንጌል መስበኩንና፣ ማንኛውንም ዐይነት በሽታና ደዌ መፈወሱን ቀጠለ። 36 ሕዝቡንም ሲያይ፣ ጠባቂ እንደሌላቸው በጎች ተጨንቀውና ግራ ተጋብተው ነበርና ራራላቸው። 37 ለደቀ መዛሙርቱም፣ "መከሩ ብዙ ነው ሠራተኞች ግን ጥቂት ናቸው። 38 ስለዚህ፣ ሠራተኞችን ወደ መከሩ እንዲልክ፣ ወደ መከሩ ጌታ አጥብቃችሁ ጸልዩ" አላቸው።
ማቴዎስ 9፡1-2 አያያዥ ዓረፍተ ነገር ጸሐፊው በ MAT 8:1 የጀመረው ኢየሱስ ሰዎችን ከበሽታ የፈወሰበትን ታሪክ እንደገና ወደ መተረክ ተመልሷል፡፡ በዚህ ታሪክ ውስጥ ኢየሱስ ሽባውን ሰው እንዴት እንደፈወሰው ይተርካል፡፡ ኢየሱስ ወደ ታንኳይቱ ገባ ደቀ መዛሙርቱም ከእርሱ ጋር ሄደው ሊሆን ይችላል፡፡ ታንኳ ይህ ምናልባት በ MAT 8:23 ላይ የተገለጸው ታንኳ ሊሆን ይችላል፡፡ ግራ መጋባትን ለማስወገድ ከፈለግህ ብቻ ይህንን መግለጽ ትችላለህ፡፡ ወደ ገዛ ከተማው መጣ ኤቲ፡ “ወደመከኖርበት ከተማ” (UDB) እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይኖራል፡፡ እነርሱ . . . እነርሱ ይህ ሽባውን ሰው ወደኢየሱስ ያመጡትን ሰዎች ያመለክታል፡፡ ሽባውንም ሰው ሊያመለክት ይችላል፡፡ ልጅ ይህ ሰው በእርግጥ የኢየሱስ ልጅ አይደለም፡፡ ኢየሱስ በዚህ ሥፍራ ላይ በትህትና እያናገረው ነው፡፡ ይህ ሰዎችን ግራ የሚያጋባ ከሆነ እንዲህ በማለት ሊትተረጉመው ተትችላለህ “ወዳጄ ሆይ” ወይም “አንተ ጎበዝ” ወይም ከተውኑ ልትተው ትችላለህ፡፡ ኃጢአትህ ተሰሪያልሃለች ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ኃጢአትህን ሠሪዮልሃል” ወይም “ኃጢአትን ሠሪዬልሃለሁ” ( ተመልከት)
እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይኖራል፡፡ ከእነርሱ መካከል ይህ “ለእነርሱ ለራሳቸው” “በመካከላቸው” ወይም “እርስ በእርሳቸው”፣ “በራሳቸው አፍ” እግዚአብሔርን ይሳደባል እግዚአብሔር ብቻ ሊያደርጋቸው የሚችላቸው ነገሮች ኢየሱስ ማድረግ እችላለው እያለ ነው፡፡ የልባቸውን ሀሳብ አውቆ ኢየሱስ ሀሳባቸውን ያወቀው በልዕለ ተፈጥሮ ኃይል አማካኝነት ነው ወይም እርሱ በእርሳቸው ስነጋገሩ ተመልክቶ ነው፡፡ በልባችሁ ስለምን ክፋትን ታስባላችሁ? ኢየሱስ ይህንን የተናገረው ጸሐፊትን ለመገሰጽ ነው፡፡ ( ተመልከት) አንናተ . . . እናንተ እነዚህ ቃላት ብዙ ቁጥር አመልካች ናቸው፡፡ ( ተመልከት) ክፋት ይህ ግብረገባዊ ክፋት እንጂ ዝም ብሎ ስህተት አይደለም፡፡ ዬቱ ይቀላል . . . ተራመድ ኢየሱስ ጸሐፊዎችን ይህንን ጥያቄ በመጠየቅ ማስታወስ የፈለገው ነገር ሰውዬው ሽባ የሆነው በኃጢአቱ ምክንያት ነው፡፡ ስለዚህም ኃጢአቱ ይቅር ከተባለለት ሽባው ሰው መራመድ ይችላል ማለት ነው፡፡ ስለዚህም ኢየሱስ ኃጢአትን ይቅር ማለት እንደሚችል ጸሐፊት ያውቁ ዘንድ ይህን ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡ ለመናገር ቀላሉ ዬቱ ነው፤ “ኃጢአትህ ተሠረየችልህ” ወይስ “ተነሳና ተራመድ?” ብሎ መናገር ነው ኤቲ፡ ለመናገር ቀላሉ ዬቱ ነው፤ “ኃጢአትህ ተሠረየችልህ” ወይስ “ተነሳና ተራመድ” ብሎ መናገር ነው? Your sins are forgiven This can mean 1) "I forgive your sins" ኃጢአትህ ተሠረየችልህ ይህ ማለት 1) “ኃጢአትን ይቅር ብዬሃለሁ” (UDB) ወይም 2) “እግዚአብሔር ኃጢአትህን ይቅር ብሎልሃል”፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “አንተ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው በነጠላ ቁጥር ነው፡፡ ( ተመልከት) ታውቁ ዘንድ ነው ኤቲ፡ “አረጋግጥላችኋለሁ”፡፡ በዚህ ሥፍራ ለእናንተ የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው የብዙ ቁጥርን በሚያመለክት መልኩ ነው፡፡ ( ተመልከት) your...your These are singular. አንተ . . . አንተ ይህ ነጠላ ቁጥር ነው፡፡ ( ተመልከት) ወደ ቤትህ ሂድ ኢየሱስ ሰውዬውን ወደ ሌላ ቦታ እንዳይሄድ አልከለከለውም፡፡ ለሰውዬው ወደ ቤቱ የሜድ ዕድል ሰጠው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ኢየሱስ ሽባውን ሰው የፈወሰበት ታሪክ ማጠቃለያ ነው፡፡ ከዚያም ኢየሱስ ከቀረጥ ሰብሳቢዎች መካከል አንድ ሰውን የእርሱ ደቀ መዝሙር ይሆን ዘንድ ጠራው፡፡ ምሳጋና በ MAT 5:16 ላይ የተጠቀምከውን ተመሳሳይ ቃል በዚህ ሥፍራም ተጠቀም፡፡ እንዲህ ያለ ስልጣን ኃጢአትን የማስተሰረይ ስልጣን ማቴዎስ . . . እርሱ . . እርሱ የቤተ ክርስቲያን አባቶች በዚህ ሥፍራ ላይ የተጠቀሰው የማቴዎስ ወንጌል ጸሐፊ ማቴዎስ እራሱ ነው ይላሉ፡፡ ይሁን እንጂ በክፍሉ ውስጥ ያለው “እርሱ” የሚለው ቃል “እኔ” ወደሚለው እንዲንለውጥ የሚያደርገን ምንም ምክንያት የለም፡፡ እርሱም እንዲህ አለው “ኢየሱስ ለማቴዎስ እንዲህ አለው” ኢየሱስም በዚያ ስያልፍ ሳለ ይህ ሀረግ እነሆ በሚል ቃል በ MAT 9:8 የተጀመረው ታሪክ መግቢያን የሚያሳይ ነው፡፡ በቋንቋችሁ እንዲህ ማሳየት ከቻላችሁ ተጠቀሙበት፡፡ በዚያ ስያልፍ “መሄድ” የሚለውን ቃል ተጠቀሙ፡፡ ኢየሱስ ወደ ተራራ መውጣቱን ወይም ወደ ሸለቆ መውረዱን ወይም ወደ ቅፍረናሆም መሄዱን ወይም ከዚያ ሪቆ ለመሄድ መነሳቱን የሚገለጽ ምንም ነገር የለም፡፡ ተነሥቶም ተከተለው “ማቴዎስ ተነሣና ኢየሱስን ተከተለው”፡፡ የተከተለው ኢየሱስን እስከሚቀጥለው ሥፍራ ድረስ እንደተከተሉት ሰዎች ሳይሆን እንደ ደቀ መዝሙር ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ ይህ ታሪክ የተፈጸመው በቀራጩ ማቴዎስ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ቤት ይህ ምናልባትም የማቴዎስ ቤት ይሆናል፤ ነገር ግን የኢየሱስም ቤት ሊሆን ይችላል (“ከኢየሱስ እና ከደቀ መዛሙርቱ ጋር አብረው በሉ”፡፡ ግራ መጋባትን የሚፈጥር ከሆነ ብቻ ምንነቱን በመግለጽ አስቀምጡት፡፡ ፈሪሳዊያን ይህንን በተመለከቱ ጊዜ “ፈሪሳዊያን ኢየሱስ ከቀረጥ ሰብሳቢዎች እና ከኃጢአተኛ ሰዎች ጋር እየበላ እንደሆነ በተመለከቱ ጊዜ”
አጠቃላይ መረጃ፡ ይህ ታሪክ የተፈጸመው በቀራጩ ማቴዎስ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ኢየሱስም ይህንን በሰማ ጊዜ “ይህንን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ፈሪሳዊያን ኢየሱስ ስለምን ከቀራጮች እና ከኃጢአተኞች ጋር ይበላል ብለው የጠየቁትን ጥያቄን ያመለክታል፡፡ ጤነኞች ኤቲ፡ “ጤናማ የሆኑ ሰዎች” ( ተመልከት) ሐኪም “ዶክተር”(UDB) ታማሚዎች “ዶክተር የሚያስፈልጋቸው ታማሚዎች ናቸው” ይህ ምን ማለት እንደሆነ ሄዳችሁ አጥኑ ኤቲ፡ “የዚህን ትርጉም ምንነት ሄዳችሁ አጥኑ፡” ሂዱ “እናንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥርን ያመለክታል፡፡
አያያዥ ዓረፈተ ነገር የመጥቁ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ስለምን እንደማይጾሙ ጥያቄ አቀረቡ፡፡ አይጾሙም ጾም ማለት ምንም ነገር አለመብላት ማለት ነው፡፡ ምንም ዓይነት ጾም ባሌለባቸው አንዳንድ ባሕሎች ውስጥ “በቀጣይነት መብላት መቆም” ተብሎ ልገለጽ ይችላል፡፡ ( ተመልከት) የሠረግ ታዳሚዎች ኃዘንተኞች መሆን ይችላሉ . . . እነርሱ? የሠረግ ታዳሚዎች ሠርገኞቹ ከእነርሱ ጋር እያሉ እንድጾሙ የሚጠብቅባቸው ማንም የለም፡፡ ( ተመልከት) የሠርግ ታዳሚዎች ይህ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት የሚያመለክት ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ ( ተመልከት) ሠርገኛወ ገና ከእርሱ ጋር ነውና . . . ሠርገኛው ከእነርሱ ከተለየ በኋላ “ሠርገኛው” ኢየሱስ ነው፣ እርሱ ደግሙ አሁን ከእነርሱ ጋር ነው፡፡ ( ተመልከት) ሠርገኛው ከእነርሱ የሚወሰደብት ጊዜ ይመጣል ኤቲ፡ “የሆነ ሰው ሠርገኛውን ይወስደዋል፡፡” ይህ እንደሚገደል በምሰሌያዊ አነጋገር ስገለጽ ነው፡፡ ( ተመልከት) ያዝናሉ “ያለቅሳሉ” ወይም “ያዝናሉ”(UDB)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ላነሱት ጥያቄ መልስ መስጠቱን ቀጥሏል፡፡ ማንም በአረጀ ልብስ ላይ አዲስ እራፊ የሚሰፋ የለም የዚህ ምሳሌያዊ ንግግር ትርጉሙ አሮጌውን ባሕል የሚያው ሰዎች አዲሱን ለመቀበል አይጓጉም፡፡ ( ተመልከት) ልብስ “ልብስ” እራፊ የተቀደደ ልብስን ለመስፋት የሚሆን “አዲስ ቁራጭ ጨርቅ”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ለተየቁት ጥያቄ መልስ መስጠቱት ቀጥሏል፡፡ በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር ማንም የለም ኢየሱስ ይህንን ምሳሌያዊ አነጋገር የተጠቀመው ለዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ጥያቄ መልስ ለመስጠት ነው፡፡ ጥያቄያቸውም “እኛ እና ፈሪሳዊን እንጾማለን ነገር ነገር የአንተ ደቀ መዛሙርት ግን ስለምን አይጾሙም?” ( ተመልከት) የሚያኖር ማንም የለም ኤቲ፡ “የሚያኖር ማንም የለም” (UDB) ወይም “ሰዎች በጭራሽ አያስቀምጡም” አዲስ ወይን ኤቲ፡ “የወይን ጁስ”፡፡ ይህ ያልፈላ ወይንን ያመለክታል፡፡ ወይን በእናንተ አከባቢ የማይታወቅ ከሆነ ለፍራፍሬ አጠቃላይ ስም የሚውል ቃል ተጠቀሙ፡፡ ( ተመልከት) የአረጀ አቁማዳ ይህ ብዙ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለን አቁማዳ ያመለክታል፡፡ (ተመልከት) አቁማዳ ከእንስሳት ቆዳ የሚሠራ ከረጥት ነው፡፡ “የወይን መያዣ” ወይም “የቆዳ ከረጥት” ተብሎም ይጠራል፡፡ (UDB). ( ተመልከት) አቁማዳው ይፈነዳል አዲሱ ወይን ስፈላ አቁማዳው ይፈነዳል ምክንያቱም ከዚህ በላይ መለጠጥ ስለማይችል ነው፡፡ ( ተመልከት) ይጠፋል “ይበላሻል”(UDB) አዲስ አቁማዳ “አዲስ አቁማዳ” ወይም “አዲስ የወይን ከረጥት”፡፡ ይህ ከዚህ በፊት ጥቅም ላይ ውሎ የማያቅን አቆማዳ ያመለክታል፡፡ ( ተመልከቱ)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ታሪክ የሚጀምረው ኢየሱስ የአይሁድ አለቃነ ሴት ልጅ ከሞት ካስነሳ በበኋላ ነው፡፡ እነዚህ ነገሮች ይህ ኢየሱስ ለዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ስለ ጾም የሰጠውን መልስ የሚያመለክት ነው፡፡ እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይኖራል፡፡ ወድቀው ሰገዱለት ይህ በአይሁድ ባሕል መሠረት ለሰዎች አክበሮትን ማሳያ መንገድ ነው፡፡ ና እና እጅህን በእርሷ ላይ ጫን፤ ከዚያም በሕይወት ትኖራለች ይህ የአይሁድ አለቃ ኢየሱስ ሴት ልጁን ከሞት ለማስነሳት የሚያስችለው ኃይል እንዳለው ያምናል ማለት ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ኢየሱስ ወደ አይሁድ አለቃው ቤት በመሄድ ላይ ሳለ እንዴት አንዲትን ሴት እንደፈወሳት የሚገልጽ ታሪክ ነው፡፡ እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይኖራል፡፡ ከፍተኛ የደም መፍሰስ ኤቲ፡ “በከፍተኛ ሁኔታ ደም ይፈሳታል፡፡” የወር አበባዋ መምጫው ጊዜ እንኳ ሳይሆን ከማሕጸኗ ውስጥ ድም ይፈሳት ነበር፡፡ ይህንን ሁኔታ ለመግለጽ የሚያስችል ቃል በአንዳንድ ባሕሎች ውስጥ አለ፡፡ ( ተመልከት) ልብሶቹን መንካት ብችል እንኳ ደህና እሆናለሁ ኢየሱስ ብዙ ሰዎችን ፈውሷል፤ ከዚህች ሴት ይበልጥ ከፈተኛ በሽታ ውስጥ የሆኑትን ሰዎች እንኳ ፈውሷል፡፡ ( ተመልከት) ጨርቅ “መቀነት” ነገር ግን “ይልቁንም” ሴትቱ ይሆናል ብላ የጠበቀችው ነገር አልሆነም፡፡ ሴት ልጅ ይህች ልጅ የኢየሱስ ልጅ አይደለችም፡፡ ኢየሱስ በትህትና አናገራት፡፡ ይህ በሰዎች አእምሮ ውስጥ ግራ መገጋባትን የሚፈጥር ከሆነ “አንድ ወጣት” ወይም ሳይተረጎም ሊታለፍ ይችላል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ኢየሱስ የአይሁድ አለቃውን ሴት ልጅ ወደ ሕይወት ወደመለሰበት ታሪክ ይመራናል፡፡ የአለቃው ቤት ይህ የአይሁድ አለቃው ቤት ነው፡፡ እምቢልታ ይህ ረጅም የሆነ በአንድ በኩል እስትፋንስ እየተሰጠው ጥቅም ላይ የሚውል የሙዚቃ መሣሪያ ነው፡፡ የእምቢልታ ጠቻዋቾች “እምቢልታ የሚጫወቱ ሰዎች” ሂዱ በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ ለብዙ ሰዎች እየተናገረ ነው፡፡ ስለዚህ በቋንቋችሁ የብዙ ቁጥር አመልካች ቃልን ተጠቀም፡፡ ልጅቱ አልሞተችም አንቀላፍታለች እንጂ በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ የያዘው የቃላት ጫወታ ነው፡፡ ኢየሱስ በኖረበት ዘመን የሞተ ሰው ተኝቷል ብሎ መጥራት የተለመደ ነው፡፡ ይሁን ዘንጂ በዚህ ሥፍራ ሞታ የነበረችው ልጅ ልክ ተኝቶ እንደነበር ሰው ከሞት ተነሳች፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ኢየሱስ የአይሁድ አለቃውን ሴት ልጅ ወደ ሕይወት የመለሰት ታሪክ ማብቂያ ነው፡፡ አጠቃላይ መረጃ ቁጥር 26 ኢየሱስ ልጅቷን ከሞት የማስነሳቱ ውጤት ምን እንደሆነ ማጠቃለያ ሀሳብ ነው፡፡ ሕዝቡ ውጪ እንዲወጣ ካደረገ በኋላ “ኢየሱስ ሕዝቡን ወደ ውጪ ካስወጣ በኋላ” ወይም “የልጅቱ ቤተሰቦች ሕዝቡን ወደ ወጪ ካስወጣ በኋላ” ተነሽ “ከአልጋሽ ተነሽ”፡፡ በ MAT 8:15 ያለው ትርጉም ተመሳሳይ ነው፡፡ የዚህ ነገር ዜና በሀገሩ ሁሉ ተሰማ ይህ ሰውኛ አገላለጽ የዚህ ነገር ዜና መሰራጨቱን ያሳያል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንተያት አንዱ ለሌላኛው ሰው በመንገሩ ነው፡፡ ኤቲ፡ “በአከባቢው የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ ሰለተፈጠረው ነገር ሰሙ” (UDB) ወይም “የልጅቱን በሕይወት መኖር የተመለከቱ ሰዎች በዚያ አለባቢ ላሉ ሰዎች ሁሉ ማናገር ጀመሩ፡፡” ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ስለ ሁለት ዐይነ ስውራን ታሪክ የሚጀመርበት ነው፡፡ ኢየሱስ በዚያ ስያልፍ ሳለ ኢየሱስ አከባቢውን ለቆ ሲሄድ ስያልፍ ኢየሱስ ወደ ተራራ እየወጣ ወይም እየወረደ እንደሆነ ምንም ፍንጭ የለም፡፡ ስለዚህ “ሄደ” የሚል ጠቅለል ያለ ቃል መጠቀሙ ጥሩ ነው፡፡ የዳዊት ልጅ ኢየሱስ በቀጥታ የዳዊት ልጅ አይደለም፡፡ ስለዚህም እንዲህ ልተረጎም ይችላል “ከዳዊት ዘር የሆነው” (UDB)፡፡ ይሁን እንጂ “የዳዊት ልጅ” የሚለው የመስሑ የማዕረግ ስም ነው፡፡ see MAT 21:9 ተመልከት) እና እነዚህ ሰዎችም ምናበት ኢየሱስን ይህንኑ የማዕረግ ስሙን ታሳቢ በማድረግ ጠርተውታል፡፡ ወደ ቤትም በገባ ጊዜ ይህ ኢየሱስ ወደ ገዛ ቤቱ መግባቱን (UDB) ወይም በ MAT 9:10 ላይ የተጠቀሰውን ቤት ልያመለክት ይችላል፡፡ አዎን፥ ጌታ ሆይ ኤቲ፡ “አዎን ጌታዬ አንተ መፈወስ እንደሚትችል እናምናለን፡፡”
ዓይኖቻቸውን ዳሰሰ። ኢየሱስ የሁለቱንም ሰዎች ዐይኖች እንዴት በአንድ ጊዜ መዳሰስ እንደቻለ ግልጽ አይደለም ወይም በቀኝ እጁ የአንዱን ዐይን በሌላኛው እጁ ደግሞ የሌላኛውን ዐይን ዳስሶ ይሆናል፡፡ የግራ እጅ ብዙ ጊዜ ንጹሕ ላልሆነ ነገር እንደመዋሉ መጠን ኢየሱስ እነዚህን ሰዎች የፈወሳቸው ቀኝ እጂን ተጠቅሞ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ እየዳሰሳቸው ሳለ ቃል መናገር አለመናገሩ ወይም በመጀመሪያ መዳሰሱን ከዚያመ ቃል መናገሩን የሚታወቅ ነገር የለም፡፡ ዐይኖቻቸው ተከፈቱ ኤቲ፡ “እግዚአብሔር ዐይኖቻቸውን ፈወሰ” ወይም “ሁለቱ ዐይነ ስውራን መመልከት ቻሉ” ( ተመልከት) But "Instead." The men did not do what Jesus told them to do. ነገረ ግን “ይሁን እንጂ” እነዚህ ሰሰዎች ኢየሱስ እንዲያደርጉ የነገራውን ነገር አላደረጉም፡፡ ዜናውን አሰራጩት ኤቲ፡ “ምን እንደተደረገላቸው ለብዙ ሰዎች ተናገሩ”
አያያዥ ዐረፍተ ነገር ይህ ኢየሱስ በእርኩስ መንፈስ በመያዙ ምክያት መናገር የማይችለውን ሰው የፈወሰበት ታሪክ እና ለዚህ ፈውስ ሰዎች የሰጡት ምላሽ ታሪክ ነው፡፡ እነሆ ይህ በትልቁ ታሪክ ውስጥ የአንድ አዲስ ነገር ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ ይህንን ማሳየት የሚቻልበት መንገድ ይኖራል፡፡ ዲዳ መናገር የማይችል ዲዳ ሰው ተናገረ ኤቲ፡ “ዲዳው ሰው ማናገር ጀመረ” ወይም “መናገር የማይችለው ሰውዬ መናገር ቻለ” ወይም “ዲዳ የነበረው ሰው መናገር ቻለ” ሕዝቡም ተገረሙ ኤቲ፡ “ሕዝቡም ተደነቀ” እንዲህ ያለ ነገር ታይቶም አይታወቅም “እንዲህ ዓይነት ሀገር ተደርጎ አይታወቅም” ወይም “ይህን ዓይነት ነገር ከዚህ በፊት ማንም ሰው አድርጎ አያውቅም” ማለት ሊሆን ይችላል፡፡ እርኩሳን መናስፍስት አስወጣ በዚህ ሥፍራ ላጥ “እርሱ” የሚለው የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ቁጥር 35 በ MAT 8:1 የተጀመረው ኢየሱስ በገሊላ የነረው የፈውስ አገልግሎት ታሪክ ማብቂያ ነው፡፡ (የታሪኩ ማብቂያ) አጠቃላይ መረጃ፡ ከቁጥር 36 ጀምሮ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን በማስተማር እርሱ እንዳደረገው ይስብኩና ይፈውሱ ዘንድ የላካቸው ታሪክ አዲስ የታሪኩ ክፍል ጅማሬ ነው፡፡ በሁሉም ከተሞች ኤቲ፡ “በብዙ ከተሞች” ( ተመልከት) ከተሞች . . . መንደሮች ኤቲ፡ “ትልልቅ መንደሮች . . . ትንንሽ መንደሮች” ወይም “ትልልቅ ከተሞች . . . ትንንሽ ከተሞች” ሁሉንም ዓይነት በሽታዎች እና ሕመሞች ኤቲ፡ “ሁሉንም በሽታዎች እና ሕመሞች”፡፡ “በሽታ” እና “ሕመም” ተቀራራቢ የሆኑ ነገሮች ይሁን እንዲ ከተቻለ በሁለት የተለያዩ ቃላት ቢተረጎሙ የተሸለ ነው፡፡ “በሽታ” አንድ ሰው እንዲታመም የሚያደርጉት ነገሮች ሲሆኑ፡፡ “በሽታ” ደግሞ በዚህ በሽታ ከመያዛችን የተነሳ የሚሰማን አካላዊ ድካም ወይም ሕመም ነው፡፡ እረኞች እንደሌላቸው በጎች ተቅበዝብዘዋል ኤቲ፡ “ሰዎቹ መሪ አልበራቸውም” ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ፡ ኢየሱስ የመከርን ምሳሌ በመጠቀም ከዚህ በፊት ለነበረው የሕዝቡ ፍላጎት ደቀ መዛሙርቱ በምን ዓይነት መንገድ ምላሽ መስጠት እንዳለባቸው ነገራቸው፡፡ መከሩ ብዙ ነው ሠራተኞቹ ግን ጥቂቶች ናቸው ይህ ምሰሌያዊ ንግግር በእግዚአብሔር የሚያምኑ እና ወደ መንግስቱ የሚጨመሩ ሰዎች ቁጥር በእርሻ ማሳ ውስጥ በለ ሰብል በመመሰል ስ እግዚአብሔር ለሰዎች የሚናገሩ ሰዎችን በሠራተኞች በመመሰል ያነጻጽራል፡፡ የዚህ ምሳሌያዊ ንግግር ዋናው ነጥብ ስለ እግዚአብሔር የሚናገሩ በጣም ጥቂት ሰዎች ናቸው ነው፡፡ መከር ኤቲ፡ “የደረሰ ሰብል” ሠራተኞች “ሠራተኞች” ለመከሩ ጌታ ጸልዩ ኤቲ፡ “የመከሩ ባለቤት ወደሆነው ጌታ ጸልዩ”
1 ሁለቱን ደቀ መዛሙርት በአንድ ላይ ጠርቶ፣ ርኩሳን መናፍስትን እንዲያወጡ፣ ሁሉንም ዐይነት በሽታና ደዌ እንዲፈውሱ ሥልጣንን ሰጣቸው፡፡ 2 የዐስራ ሁለቱም ሐዋርያት ስም ይህ ነው፤ የመጀመሪያው ጴጥሮስ የተባለው ስምዖንና ወንድሙ እንድርያስ፣ የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብና ወንድሙ ዮሐንስ፣ 3 ፊልጶስና በርተሎሜዎስ፣ ቶማስና ቀረጥ ሰብሳቢው ማቴዎስ፣ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብና ታዴዎስ፣ 4 ቀነናዊው ስምዖን፣አሳልፎ የሚሰጠው የአስቆሮቱ ይሁዳ። 5 ኢየሱስ እነዚህን ዐሥራ ሁለቱን "አሕዛብ ወደሚኖሩበት የትኛውም ቦታ አትሂዱ፤ ወደ የትኛውም የሳምራውያን ከተማ አትግቡ። 6 ከዚያ ይልቅ ወደ ጠፉት የእስራኤል ቤት በጐች ሂዱ። 7 መንግሥተ ሰማይ ቀርባለች፣ ብላችሁ ስበኩ" ብሎ አስተምሮ ላካቸው። 8 ሕሙማንን ፈውሱ፣ ሙታንን አስነሡ፣ ለምጻሞችን አንጹ፣ አጋንንትንም አስወጡ፣ በነጻ ተቀብላችኋል በነጻ ስጡ። 9 በቦርሳችሁ ወርቅ ብር ወይም ናስ አትያዙ፤ 10 ለሠራተኛ ቀለቡ የሚገባው ስለ ሆነ፣ ለመንገዳችሁ ሻንጣ ወይም ትርፍ ልብስ፣ ወይም ጫማ፣ ወይም በትር አትያዙ። 11 ወደ የትኛውም ከተማ ወይም መንደር ስትገቡ፣ በዚያ ተገቢ የሆነው ሰው ማን እንደሆን እወቁ፤ ለቃችሁ እስከምትሄዱ ድረስ በዚያው ቆዩ። 12 ወደ ቤት ስትገቡ፣ ሰላምታ ስጡ። 13 ቤቱ የሚገባው ከሆነ ሰላማችሁ ይደርሰዋል፤ የማይገባው ከሆነ ግን ሰላማችሁ ይመለስላችኋል። 14 እናንተን የማይቀበላችሁን፣ ወይም ቃላችሁን የማይሰማውን በተመለከተ ግን፣ ከዚያ ቤት ወይም ከተማ ስትወጡ የእግራችሁን አቧራ አራግፉ። 15 እውነት እላችኋለሁ፣ በፍርድ ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶምና ለገሞራ ይቀልላቸዋል። 16 ተመልከቱ፣ እንደ በጎች በተኲላዎች መካከል እልካችኋለሁ። ስለዚህ፣ እንደ እባብ ብልኆች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ። 17 ከሰዎች ተጠበቁ፣ ወደ ፍርድ ሸንጎ ያቅርቧችኋል፣ በምኲራባቸውም ይገርፏችኋል። 18 ለእነርሱና ለአሕዛብ ምስክር እንዲሆን፣ በእኔም ምክንያት ወደ ገዥዎችና ነገሥታት ፊት ትቀርባላችሁ። 19 ለፍርድም ሲያቀርቧችሁ፣ በዚያች ሰዓት የምትናገሩት ስለሚሰጣችሁ፣ ምን ወይም እንዴት እንደምትናገሩ አትጨነቁ። 20 በእናንተ ውስጥ የሚናገረው የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ የምትናገሩት እናንተ አይደላችሁም። 21 ወንድም ወንድሙን፣ አባትም ልጁን፣ ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፤ ልጆችም በወላጆቻቸው ላይ ተነሥተው ያስገድሏቸዋል። 22 ከስሜ የተነሣ በሰው ሁሉ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ ነገር ግን ማንም እስከ መጨረሻ የሚጸና እርሱ ይድናል። 23 በዚህች ከተማ በሚያሳድዷችሁ ጊዜ ወደሚቀጥለው ከተማ ሽሹ። እውነት እላችኋለሁ፣ የሰው ልጅ ከመምጣቱ በፊት፣ የእስራኤልን ከተሞች አታዳርሱም። 24 ደቀ መዝሙር ከመምህሩ አይበልጥም፤ ወይም አገልጋይ ከጌታው በላይ አይደለም። 25 ለደቀ መዝሙር ልክ እንደ መምህሩ፣ ለአገልጋይም ልክ እንደ ጌታው መሆን ይበቃዋል። 26 እንግዲህ አትፍሯቸው፤ የማይገለጥ የተሰወረ፣ የማይታወቅ የተደበቀ ምንም የለም። 27 በጨለማ የምነግራችሁን በብርሃን፣ በሹክሹክታ የምትሰሙትንም በአደባባይ ተናገሩት፡፡ 28 ሥጋን እንጂ ነፍስን መግደል የማይችሉትን አትፍሩ፤ ከዚያ ይልቅ ነፍስንም፣ ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚችለውን ፍሩ፡፡ 29 ሁለት ድንቢጦች በትንሽ ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ሆኖም አንዷም ብትሆን አባታችሁ ሳያውቅ በመሬት ላይ አትወድቅም፡፡ 30 የእናንተ ግን የራሳችሁ ጠጉር እንኳን ሳይቀር የተቈጠረ ነው፡፡ 31 አትፍሩ፤ ከብዙ ድንቢጦች የበለጠ ዋጋ አላችሁ፡፡ 32 ስለዚህ በሰዎች ፊት ለሚመሰክርልኝ፣ እኔም በሰማይ ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ፡፡ 33 በሰው ፊት የሚክደኝን ግን፣ እኔም ደግሞ በሰማይ ባለው በአባቴ ፊት እክደዋለሁ፡፡ 34 በምድር ላይ ሰላምን ለማምጣት የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ሰይፍን እንጂ፣ ሰላምን ለማምጣት አልመጣሁም፡፡ 35 ሰውን በአባቱ ላይ፣ ሴት ልጅን በእናቷ ላይ፣ ምራትን በአማቷ ላይ ለማነሣሣት መጥቻለሁ፡፡ 36 የሰውም ጠላቶቹ የገዛ ቤተ ሰቦቹ ይሆናሉ፡፡ 37 አባትን ወይም እናትን ከእኔ የበለጠ የሚወድ ለእኔ የተገባ አይደለም፤ እንዲሁም ወንድ ልጅን፣ ወይም ሴት ልጅን ከእኔ የበለጠ የሚወድ ለእኔ የተገባ አይደለም። 38 መስቀሉን ተሸክሞ፣ ከኋላዬ የማይከተለኝ የእኔ ሊሆን አይገባውም፡፡ 39 ሕይወቱን የሚያገኛት ያጣታል፤ ስለ እኔ ብሎ ሕይወቱን የሚያጣት ግን ያገኛታል፡፡ 40 እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፤ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል፡፡ 41 ነቢይ ስለ ሆነ ነቢይን የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ያገኛል፤ ጻድቅ ስለ ሆነ ጻድቅን የሚቀበል የጻድቅን ዋጋ ያገኛል፡፡ 42 እውነት እላችኋለሁ፣ ከእነዚህ ታናናሾች ለአንዱ፣ ደቀ መዝሙሬ ስለ ሆነ፣ አንድ ብርጭቆ ቀዝቃዛ ውሃ እንኳ የሚሰጥ ማንም፣ በምንም ዐይነት ዋጋውን አያጣም፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ይህ ኢየሱስ ዐሥራ ሁለት ደቀ መዛሙርቱን የእርሱን ሥራ ይሠሩ ዘንድ የለከበት ታሪክ መጀመሪያ ነው፡፡ የእርሱ የሆኑትን ዐሥራ ሁለቱን በአንድነት ጠርቶ ኤቲ፡ “የእረሱን ዐሥራ ሁለት ደቀ መዛሙርት ጠርቶ” ሥልጣንን ሰጣቸው በዚህ ክፍል ውስጥ የተሰጣቸው ስልጣን 1) እርሰኩስ መንፈስን ማስወጣት እንዲችሉ 2) በሽታን እና ደዌን ይፈውሱ ዘንድ እንደሆነ ክፍሉ በግልጽ እንደሚናገር እርግጠኞች ሁኑ፡፡ ማስወጣት ኤቲ፡ “እርኩስ መንፈስ እንዲወጣ ማድረግ” ሁሉንም ዓይነት በሽታዎች እና ሕመሞች ኤቲ፡ “ሁሉንም በሽታዎች እና ሕመሞች”፡፡ “በሽታ” እና “ሕመም” ተቀራራቢ የሆኑ ነገሮች ይሁን እንዲ ከተቻለ በሁለት የተለያዩ ቃላት ቢተረጎሙ የተሸለ ነው፡፡ “በሽታ” አንድ ሰው እንዲታመም የሚያደርጉት ነገሮች ሲሆኑ፡፡ “በሽታ” ደግሞ በዚህ በሽታ ከመያዛችን የተነሳ የሚሰማን አካላዊ ድካም ወይም ሕመም ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃዎች በዚህ ሥፍራ ላይ ጸሐፊው የዐሥራ ሁሉትን ሐዋሪያት ስም በመዘርዝር የኋላ ታሪክ መረጃ ይሰጣል፡፡ ( ተመልከት) መጀመሪያ በቅደም ተከተል እንጂ በደረጃ አይደለም ቀናተኛው የዚህ ቃል አንዱ ትርጉም ሊሆን የሚችለው 1) “ቀናተኛ”፡፡ አይሁዳዊያንን ከሮማዊያን አገዛዝ ነጻ ለማውጣት የሚፈልጉ ቡድች ውስጥ ያለን ሰው ያመለክታል፡፡ ኤቲ፡ “ታጋይ” ወይም “የሀገር ፍቅር ያለው” ወይም “የነጻነት ታጋይ”፡፡ ሌላኛው የቃሉ ትርጉም ሊሆን የሚችለው 2 “ቀናተኛ የሆነው”፡፡ ይህ እግዚአብሔር ይከብር ዘንድ ይቀና የነበረው እንደ ማለት ነው፡፡ ማቴዎስ ቀረጥ ሰብሳቢው “ቀረጥ ይሰበስብ የነበረው ማቴዎስ” እርሱን የካደው “ኢየሱስን የካደው”
ዓያያዥ ዓረፍተ ነገር በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ለመስበክ ስሄድ ምን ማድረግ እንዳለባቸው እና ምን እንደሚያጋጥማቸው መመሪያ መስጠት መጀመሩን እንመለከታለን፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ ምንም እንኳ ቁጥር 5 የሚጀምረው ኢየሱስ ዐሥራ ሁለቱን ላካቸው በማለት ቢሆንም ኢየሱስ ይህንን መመሪያ የሰጣቸው እነርሱን ከመላኩ በፊት ነው፡፡ ( ተመልከት) እነዚህን ዐሥራ ሁለቱን ላካቸው ኤቲ፡ “ኢየሱስ እነዚህ ዐሥራ ሁለት ሰዎች ላካቸው” ወይም “ኢየሱስ የላካቸው እነዚህን ዐሥራ ሁለት ሰዎችን ነው” የተላከ ኢየሱስ የላካቸው ለተወሰነ ዓላማ ነው፡፡ “የተላከ” የሚለው ቃል በ MAT 10:2 ውስጥ ጥቅም ላይ የዋለው “አፖስትል” የሚለው ቃል የግሥ ቅርጹ ነው፡፡ አዘዛዘቸው ኤቲ፡ “ምን ማድረግ እንዳለባቸው ነገራው” ወይም “አዘዛቸው” የጠፉት የእስራኤል በጎች ይህ ምሳሌያዊ አነጋገር አጠቀላይ የእስራኤልን ሕዝብ ከእረኛቸው ከጠፉት በጎች ጋር የሚያነጻጽር ነው፡፡ (UDB) ( ተመልከት) የእስራኤል ቤት ይህ ገለጻ የእስራኤልን ሕዝብ የሚገልጽ ነው፡፡ ኤቲ፡ “የእስራኤል ሕዝብ” ወይም “የእስራኤል ዘር” ( ተመልከት) እንዲሁም ስትሄዱ “እናንተ” የሚለው ተውላጠ ስም ዐሥራ ሁለቱን ሐዋርያትን የሚያመለክት ነው፡፡ (: ተመልከት) የእግዚአብሔር መንግስ ቀርባለች ይህንን በ MAT 3:2 ውስጥ ያለውን ተመሳሳይ ሀሳብ በተረጎምክበት መንገድ መተርጎም ይኖርብሃል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ለመስበክ በሚወጡበት ወቅት ምን ማድረግ እንዳለባቸው እና ምን እንደሚጠብቃቸው ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ትዕዛዝ መስጠቱን ቀጥሏል፡፡ እናንተ ይህ ቃል የሚያመለክተው ዐሥራ ሁለቱን ሐዋርያት ነው፡፡ ወርቅ፣ ብር ወይም ናስ እነዚህ ሳንትሞች የሚሠሩባቸው ብረታ ብረቶች ናቸው፡፡ እነዚህ የገንዘብ ተለዋጭ ዝርዝሮች ናቸው፡፡ ብረታ ብረቶች በአካቢያችሁ የማዬታወቁ ከሆነ እነዚህ”ገንዝብ” ብለህ መተርጎም ትችላለህ፡፡ ( ተመልከት) ቦርሳ ይህ “ቀበቶ” ወይም “የገንዘብ ቀበቶ” ማለት ነው ነገር ግን ማንኛውንም ገንዘብ ለመያዝ የሚያገለግል ነገርን ሊያመለክት ይችላል፡፡ ቀበቶ ረጅም የጨርቅ መቀነት ወይም በወገብ ዙሪያ ሰዎች የሚታጠቁት ከቆዳ የሚሠራ ነገር ነወ፡፡ ብዙ ጊዜ ታጥፎ በውስጡ ሳንቲሞችን እና ገንዘብን ለመያዝ የሚያስችለው ስፋት አለው፡፡ የጉዞ ቦርሳ ይህ በጉዞ ወቅት አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን ለመያዝ የሚያገለግል ቦርሳ ወይም በሰዎች ምግብ ወይም ገንዘብ ለመሰበብሰብ የሚሆን ቦርሳን ያመለክታል፡፡ ተጨማሪ ነገሮችን በ MAT 5:40 ውስጥ ተጨማሪ ነገሮችን ብላችሁ የተረጎማችሁትን ቃል በዚህ ሥፍራ ተጠቀሙ፡፡ ሠራተኛ “ሠራተኛ” ምግቡ ኤቲ፡ “የሚያስፈልገው ነገር”
አያያዥ ዓረፈተ ነገር ለመስበክ በሚወጡበት ወቅት ምን ማድረግ እንዳለባቸው እና ምን እንደሚጠብቃቸው ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ትዕዛዝ መስጠቱን ቀጥሏል፡፡ እናንተ እነዚህ ተውላጠ ስሞች ዐሥራ ሁለቱን ሐዋርያትን ያመለክታሉ፡፡ ወደዬትኛው ከተማ ወይም መንደር ስትገቡ ኤቲ፡ “ወደ አንድ ከተማ ወይም መንድር ስትገቡ” ወይም “ወደዬትኛውም መንደር ወይም ከተማ ስትገቡ” ከተማ ወይም መንደር “ትልቅ መንደር . . . ትንንሽ መንደር” ወይም “ታላላቅ ከተማ . . . ትንንሽ ከተማ፡፡” በ MAT 9:35 ውስጥ የተጠቀምከውን ተመሳሳይ ቃል በዚህም ሥፍራ ተጠቀም፡፡ ከዚያ ከተማ ለቃችሁ እስክትወጡ ድረስ በዚያ ቆዩ ኤቲ፡ “ከተማውን ወይም መንደሩን ለቃችሁ እስኪትወጡ ድረስ በዚያ ሰው ቤት ውስጥ ቆዩ” As you enter into the house, greet it AT: "As you enter into the house, greet the people who live in it." A common greeting in those days was "Peace be to this house!" ወደቤትም ስትገቡ ሰላምታ ስጡ ኤቲ፡ “ወደቤት ስትገቡ በዚያ የሚኖሩ ሰዎችን ሰላም በሏቸው፡፡” በዚያ ዘመን የተለመደው የሠላምታ ዓይነት “ሰላም ለዚህ ቤት ይሁን” የሚል ነበር›› ( ተመልከቱ) ቤቱም የሚገባው ቢሆን ኤቲ፡ “በዚያ ቤት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ከተቀበሏችሁ” (UDB) ወይም “በዚያ ቤት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች በሚገባ ከተንከባከቧችሁ” ( ተመልከት) ሰላማችሁ ይሁንለት ኤቲ፡ “ሠላም ይሁንለት” ወይም “በዚያ ቤት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች በሠላም ይኑሩ” ሰላማችሁ ይህ ሐዋርያቱ በዚያ ቤት ውስጥ በሚኖሩ ሰዎች ዘንድ ይመጣ ዘንድ እግዚአብሔርን የሚጠይቁት ሰላም ነው፡፡ ባይገባው ግን ኤቲ፡ “በደንብ ካልተቀበሏችሁ” (UDB) ወይም “በደንብ ያላስተናገዷችሁ ከሆነ” ሰላማችሁ ይመለስ ይህ ሁለት አማራጭ ትርጓሜዎች ይሩታል፡ 1) ይህ ቤት ያልተገባው ከሆነ እግዚአብሔር ሰላሙን ወይም በረከቱን ከዚያ ቤት ላይ ይይዘዋል ወይም 2) ቤቱ ያልተገባው ከሆነ ሐዋርያቱ አንድ ነገር ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ይኸውም እግዚአብሔርን ያቀረቡላቸውን ሰላምታ እንዲያከብር መጠየቅ፡፡ ሰላምታችሁን መልሳችሁ መውሰድ ወይም የዚህ ውጤት አስመልክቶ በቋንቋችሁ ውስጥ ያሉት ቃላት ተመሳሳይ ከሆኑ በዚህ ሥፍራ መጠቀም ያለባችሁም እነዚህኑ ቃላት ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ለመስበክ በሚወጡበት ወቅት ምን ማድረግ እንዳለባቸው እና ምን እንደሚጠብቃቸው ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ትዕዛዝ መስጠቱን ቀጥሏል፡፡ ከማይቀበላችሁም ቃላችሁንም ከማይሰሙ ሁሉ ኤቲ፡ “በከተማው ውስጥ ከሚኖሩ ሰዎች መካከል ማንም ሳይበቀላች ቢቀር ወይም ያደመጣችሁ ሰው ባይኖር” እናንተ ይህ ዐሥራ ሁለት ደቀ መዛሙርት ያመለክታል፡፡ ቃላችሁን የማይሰሙ ቢሆን ኤቲ፡ “መልዕክታችሁን ማድመጥ” " (UDB) ወይም “ማለት የፈለጋችሁትን የሚያደምጥ” ከተማ ይህንን በ MAT 10:11 ከተጠቀምከው ቃል ጋር ተመሳሳይ የሆነ ቃልን በመጠቀም ሊትተረጉመው ትችላለህ፡፡ የእግራችሁን ትቢያ አራግፉ ኤቲ፡ “ከእግራችሁ ላይ የዚያን ቤት ወይም ከተማ አቧራ አራግፉ፡፡” ይህ እግዚአብሔር በዚያ ቤት ወይም ከተማ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን መተውን የሚያመለክት ምልክት ነው፡፡ ይበልጥ ይቀልላቸዋል ኤቲ፡ “መከራቸው ትንሽ ይሆናል፡፡” የሶዶም እና ገሞራ ምድር ኤቲ፡ እግዚአብሔር ከሰማይ በመጣ እሳት ያጠፋቸው በ“ሰዶም እና ገሞራ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች፡፡ ይችህ ከተማ ይህ ሐዋርያትን ወይም መልዕክቶቻቸውን ያልተቀበሉ በከተማይቱ የሚኖሩ ሰዎችን ያመለክታል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርን ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ በዚህም ሥፍራ ላይ ለመስበክ በሚሄዱበት ወቅት ስለሚያጋጥማቸው ስደት ይነግራቸው ጀምሯል፡፡ ተመልከቱ “ተመልከቱ” የሚለው ቃል በዚህ ሥፍራ ላይ ያለው ጠቀሜታ ከዚህ በታች የተጠቀሰው ሀሳብ ትኩረት እንዲሰጠው ማድረግ ነው፡፡ ኤቲ፡ “ተመልከቱ” ወይም “አዲምጡ” ወይም “ ከዚህ በመቀጠል ለሚናረው ነገር ትኩረት ስጡ”፡፡ እልካችኋለሁ ለተወሰነ ዓላማ ኦየሱስ ልኳቸዋል፡፡ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ራሳቸውን መከላከል በማይችሉ እንስሳት በመመሰል ሊያጠቋቸው በሚችሉ የዱር እንስሳት መካከል እንደሚልካቸው ይናገራል፡፡ ( ተመልከት) እንደ በጎች በጎች ራሳቸውን መከላከል አይችሉም፡፡ ( ተመልከት) በተኩላዎች መካከል ኤቲ፡ “እንደ ተኩላ አደገኛ በሆኑ ሰዎች መካከል” ወይም “አደገኛ እንስሳት ከሚያደርጓቸው ነገሮች ጋር የሚመሳሰል ተግባር በሚያደርጉ ሰዎች መካከል” ወይም “ሊያጠቋችሁ በሚችሉ ሰዎች መካከል” ( ተመልከት) እንደ እባብ ብልጦች እና እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ ንጽጽሩን አለመግለጡ የተሻለ ነው፡፡ ኤቲ፡ “በመረዳት እና በጥንቃቄ እንዲሁም በንጹሕ ልብ እና ሥነ-ምግባርን በጠበቀ መልኩ ነገሮችን ፈጽሙ” ( ተመልከቱ) ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጧችኋል ኤቲ፡ “ምክንያቱም ወደ ፍርድ ቤታቸው አሳልፈው ይሰጧኋል” ሸንጎዎች እነዚህ የማህረሰቡን ሰላም የሚጠብቁ የአከባቢው የሃይማኖት መሪዎችን ወይም ሽማግሌዎች ናቸው፡፡ ኤቲ፡ “ፍርድ ቤቶች” ይገርፏችኋል ኤቲ፡ “በመግረፊያ ይገርፏቸኋል” አሳልፈው ይሰጧኋል “ይወስዷችኋል” ወይም “ይጎትቷችኋል” ( ተመልከት) ስለ እኔ ኤቲ፡ “የእኔ ስለሆናችሁ” (UDB) ወይም “እኔን በመከተላችሁ ምክንያት” ለእነርሱና ለአሕዛብም “ለእነርሱ” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው “ገዥዎች እና ነገሥታት” ነው ወይም አይሁዳዊያን ከሳሾችን ነው (10፡17)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለመስበክ ስወጡ ስለሚጋጥማቸው ስደት ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ “ሰዎች ወደ ሸንጎ ስወሰዷችሁ”፡፡ በዚህ ሥፍራ “ሰዎች” ተብሎ የተጠቀሱት በ MAT 10:17 ላይ ሰዎች ተብለው ከተጠቀሱት ጋር ተመሳሳይ ናቸው፡፡ እናንተ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ዐሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርት ነው፡፡ አትፍሩ ኤቲ፡ “አትጨነቁ” እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ “እንዴት መናገር እንዳለባችሁ ወይም ምን መናገር እንዳለባችሁ”፡፡ እነዚህ ሁለት ሀሳቦች በአንድነት ሊጣመሩ ይችላሉ፡፡ “ምን ማለት እንዳለባችሁ” ( ተመልከት) በዚያች ሰዓት ኤቲ፡ “በዚያን ጊዜ” (: ተመልከት) የአባታችሁ መንፈስ አስፈላጊ ከሆነ ይህ “የሰማያዊ አበባተታችሁ የእግዚአብሔር መንፈስ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል ወይም ይህ የእግዚአብሔርብ መንፈስ የሚያመለክት እንጂ ምድራዊ አባትን የማያመለከት እንደሆነ ለማሳየት የግርጌ ማስታወሻ መጨመረም ይቻላል፡፡ አባት ይህ የእግዚአብሔር ዋና መጠሪያ ነው ( ተመልከት) በእናንተ ውስጥ ኤቲ፡ “በእናንተ በኩል”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለመስበክ ስወጡ ስለሚጋጥማቸው ስደት ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ ወንድምም ወንድሙን፥ አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፥ ኤቲ፡ “ወንድም ወንድሙን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል እንዲሁም አባቶች ልጆቻቸውን ለሞት አሳልፈው ይሰጣሉ፡፡” አሳልፎ መስጠት በ MAT 10:17 በተረጎምከው መሠረት ይህንን መተርጎም፡፡ ይነሣሉ ኤቲ፡ “ማመጽ”(UDB) ወይም “መቃወም” ይገድሉአቸውማል ኤቲ፡ “ያስገድሏቿል” ወይም “ ባለስልታናቱ እንዲገድሏቸው ደርጋሉ በሁሉም የተጠላችሁ ትሆናላችሁ ኤቲ፡ “በሁሉም የተጠላች ትሆናላችሁ” ወይም “ሁሉም ሰዎች ይጠሏችኋል”ተመልከቱ) እናንተ … እናንተ . . . እናንተ ይህ ዐሥራ ሁለቱን ሐዋርያትን የሚያመለክት ነው፡፡ ስለስሜ ኤቲ፡ “በስሜ ምክንያት” ወይም “በእኔ በማመናችሁ ምክንያት” (UDB) እስከ መጨረሻ የሚጸና ኤቲ፡ “እስከ መጨረሻ በታማኝነት የሚቆይ” እርሱ ይድናል ኤቲ፡ “ያን ሰው እግዚአብሔር ያድነዋል” ( ተመልከት) ወደ ቀጣዩ ሽሹ “ወደ ቀጣዩ ከተማ ሽሹ” እስኪመጣ ኤቲ፡ እስኪመጣ
አያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለመስበክ ስወጡ ስለሚጋጥማቸው ስደት ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ ደቀ መዝሙር ከመምህሩ አይበልጥም ይህ በአጠቃላይ እውነት የሆነ ነገር ነው፡፡ ይን አንጂ ይህንን ዓረፍተ ነገር ለሁሉም ደቀ መዝሙር እና መምህር ማዋል አንችል፡፡ ደቀ መዝሙር ከመምህሩ “በላይ ጠቃሚ” አይደለም፡፡ ይህ ምልባትም ከመመምህሩ “በላይ ስለማያውቅ” ወይም “ከፍተኛ ደረጃ ስለሌለው” ወይም “የተሸለ ስላልሆነ” ሊሆን ይችላል፡፡ ኤቲ፡ “የደቀ መዝሙሩ አስፈላጊነት ሁል ጊዜ ከመምህሩ ያነሰ ነው” ወይም “መምህሩ አስፈላጊነቱ ከደቀ መዝሙር ሁሉ ጊዜ የተሻለ ነው፡፡ ባሪያም ከጌታው አይበልጥም “ጌታው ከመምህሩ አይበልጥም”፡፡ ይህ አጠቃላይ መርህ እንጂ ማንኛውንም ባሪያን እና ጌታን አይወክልም፡፡ ባሪያው ከጌታው “አይበልጥም” ወይም “የተሻለ ጠቃሚ” አይደለም፡፡ ኤቲ፡ “ባሪያ ያለው ጠቄታ ሁል ጊዜ ከጌታው ያነሰ ነው፡፡” ወይም “ጌታው ያለው ጠቀሜታ ከባሪያው ሁልጊዜ የበለጠ ነው፡፡” አገልጋይ “ባሪያ” ጌታ “ባለቤት” ደቀ መዝሙር እንደ መምህሩ መሆኑ ይበቃዋል ኤቲ፡ “ደቀ መዝሙር እንደ መምህሩ መሆኑ በቂው ነው” እንደ መምህሩ ኤቲ፡ “መምህሩ የሚያውቀውን ያኽል ቢያውቅ” ወይም “እንደ መምህሩ ቢሆን” እንዲሁም ባሪያውም እንደ ጌታው ኤቲ፡ “ባሪያው እንደ መምህሩ ጠቃሚ መሆኑ ይበቃዋል” ባለቤቱን ብዔል ዜቡል ካሉት፥ ቤተሰዎቹንማ እንዴት አብዝተው አይሉአቸው ኢየሱስን አንገላተውታል ስለዚህም ደቀ መዛሙርቱም ተመሳሳይ ነገር እንደሚጠብቃቸው ማወቅ አለባቸው፡፡ ካሉት ኤቲ፡ “ሰዎች አንዲህ ብለው ከጠሩት” የቤቱን ባለቤት ኢየሱስ ይህንን ምሳሌያዊ ንግግር የተናገረው ስለራሱ ነው፡፡ ( ተመልከት) ብዔል ዜቡል ይህ ስም 1) እንዳለ “ብዔል ዘቡል” ወይም 2) ጸሐፊው ማስተላለፍ የፈለገው ትርጉም “ሴጣን” በሚለው ሊተረጎም ይችላል፡፡ ቤተሰቦቹ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር የሚያመለክተው የኢየሱስን ደቀ መዛሙርት ነው፡፡ ( ተመልከት)
አያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለመስበክ ስወጡ ስለሚጋጥማቸው ስደት ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ አትፍሩአቸው በዚህ ሥፍራ ላይ “እነርሱን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የኢየሱ ደቀ መዛሙርትን የሚያንገላቱትን ሰዎች ነው፡፡ የማይገለጥ የተከደነ፥ የማይታወቅም የተሰወረ ምንም የለምና። ኤቲ፡ ሰዎች የደበቋቸውን ነገሮች እግዚአብሔር ይገልጣቸዋል፡፡ ( ተመልከት) በጨለማ የምነግራችሁን በብርሃን ተናገሩ፤ በጆሮም የምትሰሙትን በሰገነት ላይ ስበኩ። ኤቲ፡ “በጨለማ የነገርኳችሁ ነገር በቀን ለሰዎች ተናገሩ እንዲሁም በጆሮዋችሁ የነገርኳችሁን ነገር ለሰዎች ንገሩ፡፡” ( ተመልከት) በጨለማ የምነግራችሁን ኤቲ፡ “በሚስጥር የሚነግራችሁን” ወይም “በግላችሁ የሚነግራችሁን ነገር” ( ተመልከት) በብርሃን ተናገሩ፤ ኤቲ፡ “በግልጽ ተናገሩ” ወይም “በአደባባይ ተናገሩ” ( ተመልከት) በጆሮም የምትሰሙትን ኤቲ፡ “በጆሮዋችሁ የነገርኳችሁን ነገር” በሰገነት ላይ ስበኩ። ኤቲ፡ “በሚሰማ ድምጽ ሁሉም እንዲሰማ አድርጋችሁ ተናገሩ”፡፡ ሰገነት ኢየሱስ በኖረበት ሥፍራ በከፍታ ላይ ያለ ሥፍራ ሲሆን በከፍተኛ ድምፅ ከዚህ ሥፍራ ሆኖ የሚደረግን ንግግር በሩቅ ሥፍራ ያሉ ሰዎች እንኳ ይሰሙታል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለመስበክ ስወጡ ስለሚጋጥማቸው ስደት ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ አጠቃላይ መረጃ በተጨማሪም በዚህ ክፍል ውስጥ ኢየሱ ደቀ መዛሙርቱ የሚያጋጥማቸውን ስደት መፍራት ያሌለባቸው ለምን እንደሆነ መናገር የጀመረበት ክፍል ነው፡፡ ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ “ሰዎችን አትፍሩ፡፡ ሥጋን መግደል ይችላሉ ነገር ግ ነፍስን ግን መግደል አይችሉም፡፡” ሥጋን መግደል አካላዊ ሞት ማስከተል፡፡ እነዚህ ቃላት ግራ የሚጋቡ ከሆኑ “ልገድሉአችሁ” ወይም “ሌሎች ሰዎችን መግደል” የሚለችሉ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ሥጋ በእጅ ልዳሰስ የሚችል የሰው ክፍል ነፍስ መግደል ሰዎች ከሞቱ በኋላ መጉደት ነፍስ በእጅ ልዳሰስ የማይችል የሰው ክፍል እና ከአካላዊ ሞት በኋላ የሚኖር ሁለት ድንቢጦች በአምስት ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ይህ ጥያቄ እንነዲህ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል “ስለ ድንቢጦች አስቡ፡፡ ያላቸው ዋጋ በጣም ትንሽ ከመሆኑ የተነሳ በአምስት ሳንቲም ሁለቱን ልትገዟቸው ትችለላላችሁ” (UDB). ( ተመልከት) ድንቢጦች እነዚህ በጣም ትንንሽ የሆኑ ጥራጥሬ የሚበሉ ወፎች ሲሆን በዚህ ምሌያዊ ንግግር ውስጥም ሰዎች ምንም ጥቅም የላቸው ብለው ከሚያስባቸው ነገሮች ጋር ተነጻጽሮ ቀርቧል፡፡ አምስት ሳንቲም ይህ ብዙ ጊዜ በሚተረጎምበት ቋንቋ ውስጥ ጥቅም ላይ በዋለው ገንዘብ ውስጥ በሚገኘው ሳንቲም ይተረጎማል፡፡ ይህ የመዳብ ሳንቲም ሲሆን አንድ ሰው በቀን ከሚገኘው ገቢ ውስጥ አንድ ዐሥራ ስድስተኛው ያኸል ነው፡፡ “በጣም ትንሽ ገንዘብ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ከእነርሱም አንዲቱ ያለ አባታችሁ ፈቃድ በምድር ላይ አትወድቅም። ይህ ንግግር እንዲህ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል “ከእነዚህ መካከል አንዱ እንኳ ወደ ምድር የሚወድቀው አባታችሁ ካወቀው ብቻ ነው” ወይም “አባታችሁ ካወቀው ብቻ ነው ከእነዚህ መካከል አንዱ ወደ ምድር ሊወድቅ የሚችለው”፡፡ (: ተመልከት) አንዱም እንኳ “አንድ ድንቢጥ እንኳ” ወደ ምድረ አይወድቅም “አይሞትም” የእናንተስ የራሳችሁ ጠጉር ሁሉ እንኳ ተቈጥሮአል “በራሳችሁ ላይ እንኳ ስንት ጸጉር እንዳለ እግዚአብሔር ያውቃል” ( ተመልከት) ተቆጥሮአል “ተቆጥሮአል” በዋጋችሁ ከብዙ ድንቢጦች ትበልጣላችሁ “ከብዙ ድንቢጦች ይልቅ እግዚአብሔር ለእናንተ ዋጋ ይሰጣል”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለመስበክ ስወጡ ስለሚጋጥማቸው ስደት ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ “ለሌሎች የእኔ ደቀ መዝሙር መሆኑን የሚናገር ማንኛውም ሰው” ወይም “ለእኔ ታማኝ መሆኑን ለማንም ሰው የሚናገር ማንም ሰው” መመስከር “መናገር” በሰዎች ፊት “በሰዎች ፊት” ወይም “በሌሎች ሰዎች ፊት” አባት ይህ የእግዚአብሔር ዋና መጠሪያ ነው ( ተመልከት) በሰዎች ፊት የሚክደኝ ሁሉ “በሰዎች ፊት የሚክደኝ ሁሉ” ወይም “በሰዎች ፊት የማይቀበለኝ ሁሉ” ወይም “በሌሎች ሰዎች ፊት የእኔ ደቀ መዝሙር መሆኑን የማይናር ሁሉ” ወይም “ለእኔ ታማኝ መሆኑን የማይናገር ሁሉ”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ሊያጋጥማቸው የሚችለውን ስደት መፍራት የሌለባቸው በምን ምክንያት እንደሆነ ማስተማሩን ቀጥሏል አይምሰላችሁ “እንደዚህ አታስቡ” ወይም “እንዲህ አይምሰላችሁ” ሰይፍ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር 1)የአመጽ ሞት ("መስቀል" በ MAT 10:38(ተመልከት) ወይም 2) መከፋፈልን የሚያመጣ መከራ ( ተመልከት) ለማምጣት “መመለስ” ወይም "መከፋፈል" ወይም "መለያየት" ሰውን ከአባቱ “ልጅን በአባቱ ላይ” ለሰውም ጠላቶች “የሰው ጠላቶሱ” ወይም “የሰው መጥፎ ጠላቶቹ” ቤተ ሰዎቹ ናቸው “የራሱ ቤተሰብ አባላት ናቸው”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ሊያጋጥማቸው የሚችለውን ስደት መፍራት የሌለባቸው በምን ምክንያት እንደሆነ ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ የሚወድ . . . ሊሆን አይገባውም፤ ኤቲ፡ “የሚወድ . . . ሊሆን አይገባውም፤” ወይም “የሚትወዱ ከሆነ . . . አትገቡም” የ ይህ “ማንም” ወይም “ይህንን የሚያደረግ” ወይም “ይህንን የሚያደረግ ማንን ሰው” ወይም “ይህንን የሚያደርጉ ሰዎች” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ መውደድ በዚህ ሥፍራ ላይ መውደድ የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው “ወንድማዊ መዋደድን” ወይም “ከጓደኛ የሚገኝ ፍቅርን” የሚያመለክት ነው፡፡ በተጨማሪም “መንከባከብ” ወይም “መሰጠት” ወይም “የሚገኝ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ይህ እንዲህ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል “የእኔ ሊሆን ፈጽሞ አይገባውም” ወይም “የእኔ ደቀ መዝሙር ሊሆን አይገባውም” ወይም “የእኔ መሆን አይገባውም” የማይዝ . . . አይሆንም አማራጭ ትርጉሞች፡ “የማይዙ . . አይደሉም” ወይም “የማትይዝ ከሆነ . . . አይደለህም” ወይም “የማትይዙ ከሆነ . . . አይደላችሁም፡፡” አንሣ . . . መስቀሉን እና ተከተለኝ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ለመሞት ፈቃደኛ መሆን ማለት ነው፡፡ ማንሣትን እና ከሌላ ሰው ኋላ መከተልን የሚያመለክቱ የተለመዱ ቃላትን ተጠቀም፡፡ ( ተመልከት) አንሣ “አንሣ” ወይም “አንሣና ተሸከም” የሚያገኝ . . . ያጠፋታል . . የሚያጠፋ . . . ያገኛታል፡፡ እነዚህ ቃላት በተቻለ መጠን በጣም ትንሽ ቃላት አማካኝነት ሊተረጎሙ ይገባል፡፡ አማራጨ ትርጓሜዎች፡ “የሚያገኗት. . . ያጠፏታል . . . የሚያጠፏት . . . ያገኟታል” ወይም “ካገኘሃት . . . ታጠፋታለህ . . . ካጠፋሃት . . . ታገኛታለህ” ማግኘት ይህ “መጠበቅ” ወይም “ደንነቱን መጠበቅ” ከሚለው ቃል ጋር ተቀራራቢ ትርጉም ያለው ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜዎቹ፡ “ለመጠበቅ የሚሞክር” ወይም “ለማዳን የሚሞክር” ( ተመልከት) ያጠፋታል ይህ ሰውዬው ይሞታል ማለት አይደለም፡፡ “እውነተኛ ሕይወት አይኖረውም” ለሚለው ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ ( ተመልከት) ነፍሱን የሚያጠፋ ይህ ማለት መሞት ማለት አይደለም፡፡ ይህ ማለት ከራሱ ሕይወት ይልቅ ኢየሱስን መታዘዝ አስፈላጊ መሆኑን መገንዘብ ማለት ነው፡፡ ኤቲ፡ “የራሱን ሕይወት የካደ፡፡” ለእኔ ሲል “በእኔ በማመኑ ምክንያት” ወይም “ለእኔ ሲል” ወይም “በእኔ ምክንያት”፡፡ ይህ በ MAT 10:18. ላይ ካለው “ለእኔ ሲል” ከሚለው ሀረግ ጋር ተመሳሳይ ሀሳብ ያለው ነው፡፡ ያገኛታል ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ትርጉሙ “እውነተኛ ሕይወትን ያገኛል” ማለት ነው፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ሊያጋጥማቸው የሚችለውን ስደት መፍራት የሌለባቸው በምን ምክንያት እንደሆነ ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡ የሚ ይህ እንዲህ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል “ማንም” ወይም “ማንም ሰው” ወይም “ይህን ያደረገ ሰው” የሚቀበል ይህ በ MAT 10:14 ውስጥ “መቀበል” ከሚለው ቃል ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ ትርጉሙም “እንደ እንግዳ መቀበል ማለት ነው፡፡” እናንተ በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስ እያስረማራቸው ያሉትን ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ነው፡፡ የላከኝን ይቀበላል። “የላከኝን እግዚአብሔር አብን ይቀበላል”
አያያዥ ዓርፈተ ነገር ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለመስበክ ሲወጡ ምን ማድረግ እንዳለባቸው እና ምን ምን ነገር እንደሚያጋጥማቸው ማስተማሩን አጠናቀቀ፡፡ የሚሰጥ ሁሉ “የሚሰጥ ማንኛውም ሰው” ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ ይህ እንዲህ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል “የእኔ ደቀ መዝሙር ስለሆነ ከእነዚህ ከታነናናሺቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ውሃ የሚሰጥ ማንም ሰው” ወይም “ከእነዚህ ደቀ መዛሙርቶቼ መካከል ለአንዱ ቀዝቃዛ ውሃ እንዲጠጣ የሚሰጥ ማንኛውም ሰው” ዋጋው አይጠፋበትም። “ይህ ሰው በእርግጥ ሽልማቱን ይቀበላል” ( ተመልከት) አያጣም “አይከለከልም”፡፡ ይህ በምንም ዓይነት መንገድ ንብረቱን ከመውሰድ ጋር አይገናኝም፡፡
1 እንዲህም ሆነ፣ ኢየሱስ አሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርት አዝዞ ከጨረሰ በኋላ፣ በከተሞቻቸው ሊያስተምርና ሊሰብክ ከዚያ ሄደ፡፡ 2 ዮሐንስ በወህኒ ቤት ሆኖ የክርስቶስን ሥራዎች በሰማ ጊዜ፣ በደቀ መዛሙርቱ መልእክት ላከበት፡፡ 3 እንዲህም አለው፣ "የሚመጣው አንተ ነህ፣ ወይስ መጠበቅ ያለብን ሌላ ሰው አለ?" 4 ኢየሱስም መለሰ እንዲህም አላቸው፤ “ሂዱና፣ ለዮሐንስ የምታዩትንና የምትሰሙትን እንዲህ ብላችሁ ንገሩት፤ 5 ዕውሮች ብርሃናቸውን እያገኙ፣ አንካሶች እየተራመዱ፣ ለምጻሞች እየነጹ፣ መስማት የተሳናቸው እየሰሙ፣ ሙታን እየተነሡ፣ ድኾችም የምሥራች እየሰሙ ነው፡፡ 6 በማንኛውም ሁኔታ በእኔ የማይሰናከል ሁሉ የተባረከ ነው" ። 7 እነዚህ ሰዎች እንደ ሄዱ፣ ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ ዮሐንስ መናገር ጀመረ፣ እንዲህም አለ፣ "ምን ልታዩ ወደ በረሓ ወጣችሁ? ነፋስ የሚያወዛውዘውን ሸምበቆን? 8 ግን ምን ልታዩ ወጣችሁ? የሚያምር ልብስ የለበሰውን? በርግጥ፣ ጥሩ ልብስ የሚለብሱ የሚኖሩት በቤተ መንግሥት ነው፡፡ 9 ግን ምን ልታዩ ወጣችሁ? ነቢይን ነውን? አዎ፣ እላችኋለሁ፣ ከነቢይም የሚበልጠውን ነው፡፡ 10 እንዲህ ተብሎ የተጻፈው ስለ እርሱ ነው፦ 'መንገድህን የሚያዘጋጅ መልእከተኛዬን በፊትህ እልካለሁ፡፡' 11 እውነት እላችኋለሁ፣ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከዮሐንስ የሚበልጥ ማንም የለም። በመንግሥተ ሰማይ ግን፣ ታናሹ ሰው ከእርሱ ይበልጣል፡፡ 12 ከመጥምቁ ዮሐንስ ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ፣ የእግዚአብሔር መንግሥት በዐመፅ ትቸገራለች፣ ዐመጸፀኞች ግን በኅይል ይወስዷታል፡፡ 13 እስከ ዮሐንስ ዘመን ድረስ ሕጉም፣ ነቢያቱም ሁሉ ትንቢት ሲናገሩ ነበርና፡፡ 14 እንግዲህ ልትቀበሉት ፈቃደኞች ከሆናችሁ፣ የሚመጣው ኤልያስ እርሱ ነው፡፡ 15 የሚሰማ ጆሮ ያለው፣ ይስማ። 16 ይህን ትውልድ ከምን ጋር ላነጻጽረው? በገበያ ተቀምጠው፣ እየተቀባበሉ እንደሚዘፍኑ ልጆች ነው፡፡ 17 'ዋሽንት ነፋንላችሁ፣ አልጨፈራችሁም፤ ሙሾ አወጣንላችሁ እናንተም አላለቀሳችሁም' ይላሉ። 18 ዮሐንስ እንጀራ ሳይበላና የወይን ጠጅ ሳይጠጣ በመምጣቱ፣'ጋኔን አለበት' አሉት። 19 የሰው ልጅ እየበላና እየጠጣ በመምጣቱ፣ 'ተመልከቱ ይህ ሰው በላተኛና ጠጪ፣ የቀረጥ ሰብሳቢዎችና፣ የኃጢአተኞች ወዳጅ ነው!' አሉት ነገር ግን ጥበብ በሥራዋ ትክክል ሆነች፡፡ 20 ኢየሱስም ብዙ ታላላቅ ሥራዎች ያደረገባቸውን ከተማዎች፣ ንስሓ ባለመግባታቸው ይገሥጻቸው ጀመር፡፡ 21 ወዮልሽ ኮራዚን! ወዮልሽ ቤተሳይዳ! በእናንተ የተደረጉት ታላላቅ ሥራዎች በጢሮስና በሲዶና ተደርገው ቢሆን ኖሮ፣ ማቅ ለብሰውና፥ ዐመድ ነስንሰው ድሮ ንስሓ በገቡ ነበር፡፡ 22 ነገር ግን በፍርድ ቀን ከእናንተ ይልቅ፣ ለጢሮስና ለሲዶና ይቀልላቸዋል፡፡ 23 አንቺ ቅፍርናሆም፣ እስከ ሰማይ የወጣሽ ይመስልሻልን? በፍጹም፤ ወደ ሲኦል ትወርጂያለሽ፡፡ ለአንቺ እንደተደረጉት ትልልቅ ነገሮች በሰዶም ተደርገው ቢሆን ፣ እስከ አሁን በኖረች ነበር፡፡ 24 ነገር ግን እላችኋለሁ፣ በፍርድ ቀን፣ ከእናንተ ይልቅ ለሰዶም ይቀልላታል፡፡ 25 በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም አለ፤ “የሰማይና የምድር ጌታ አባት ሆይ፣ ይህን ከዐዋቂዎችና ከአስተዋዮች ሰውረህ እንደ ሕፃናት ላልተማሩት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግንሃለሁ።” 26 አዎ፣ አባት ሆይ፣ በፊትህ እጅግ ደስ የሚያሰኝህ ይህ ሆኖአልና፡፡ 27 ከአባቴ ሁሉ ተሰጥቶኛል፣ ከአባት በቀር ማንም ልጅን የሚያውቀው የለም፤ ከልጅም በቀር፣ ልጁም ሊገልጥለት ከሚፈልገው በቀር፣ አባትን የሚያውቅ ማንም የለም፡፡ 28 እናንተ ደካሞች፣ ሸክም የከበዳችሁ ሁሉ ወደ እኔ ኑ፣ እኔም ዕረፍት እሰጣችኋላሁ፡፡ 29 ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ፣ ከእኔም ተማሩ፣ እኔ የዋህና በልቤ ትሁት ነኝ፣ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፡፡ 30 ቀንበሬ ቀላል፣ ሸክሜም የማይከብድ ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ ይህ በታሪከው ውስጥ ጸሐፊው ኢየሱስ ለመጥመቁ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ጥያቄ ምን ዓይነት ምላሽ እንደሰጠ የሚተርከው ታሪክ ጅማሬ ነው፡፡ ( ተመልከት) ከዚያ አለፈ ይህ ሀረግ የአዲስ ታሪክ ጅማሬ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ የአንድ ታሪክ ጅማሬን ማሳያ መንገድ በቋንቋችሁ ውስጥ ካለ ያንን መጠቀም ትችላላችሁ፡፡ “ከዚያ” ወየም “ከዚያ በኋላ” በሚሉ ቃላት ሊተረጎም ይችላል፡፡ ማዘዙን ይህ ቃል “ማስተማር” ወይም “ትዕዛዝ መስጠት” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ዐሥራ ሁለቱ የእርሱ ደቀ መዛሙርት ይህ በኢየሱስን የተመረጡን ዐሥራ ሁለቱን ያመለክታል፡፡ አሁን “በዚያን ጊዜ”፡፡ ይህንን ሳትተረጉሙት ማለፍ ትችላላችሁ፡፡ ዮሐንስ በእስር ቤት ሆኖ በሰማ ጊዜ አማራጭ ትርጓሜዎች፡ “በእርስ ቤት ያለው ዮሐንስ በሰማ ጊዜ” ወይም “ሌሎች ሰዎች በእርስ ላይ ላለው ለዮሐንስ በነገሩት ጊዜ” በደቀ መዛሙርቱ በኩል መልዕክትን ላከ መጥመቁ ዮሐንስ በራሱ ደቀ መዛሙርት በኩል ወደ ኢየሱስ መልዕክትን ላከ እንዲህም አለው “እርሱን” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው ኢየሱስ ነው፡፡ የሚትመጣው አንተ ነህን “የሚትመጣው” ወይም “ትመጣለህ ተብለህ የሚትጠበቀው” ተብሎ ይተርጎም ይህ የሚያመለክተው መስሑን ወይም ክርስቶስን ነው፡፡ ( ተመልከት) ሌላ እንፈለግ “ሌላ እንጠብቅ”፡፡ “እኛ” የሚለው ተውላጠ ስም ሁሉንም አይሁዳዊንን የሚያመለክታል እንጂ የዮሐንስን ደቀ መዛሙርት ብቻ አይደለም፡፡
ለዮሐንስ መልሱ ነገሩት “ለዮሐንስ ነገሩት”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለመጥመቁ ዮሐንስ መናገር ጀመረ፡፡ ምን ልታዩ ወጣችሁ . . . ንፋስ? ኢየሱስ ሕዝቡ ስለመጥመቁ ዮሐንስ እንዲያስቡ ለማድረግ እነዚህ ሦስት ደረጃዎች ያሉት ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡ እንዲህ ሊተረጎም ይችላል “ንፋስ . . . ለማየት ነው የወጣችሁትን? በእርግጥ አይደለም!” ወይም “በእርግጠኝነት ንፋስን ለማየት አልወጣችሁም!” ( ተመልከት) በንፋስ የሚወዛወዝ ሸንበቆ ይህ እንዲህ ሊሆን ይችላል 1) በዮርዳኖስ ወንዝ አጠገብ የሚበቅሉ ተክሎች ወይም 2) አንድን ሰው ለማመልከት የቀረበ ምሳሌያዊ ንግግር፡ “በንፋስ እንደሚዠዋዠው ሸንበቆ ያለ ሰው፡፡” ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ሁለት አማራጭ ትርጓሜዎች ይኖሩታል፡ እንዲህ ዓይነቱ ሰው 1) በቀላሉ በንፋስ አማካኝነት የሚንቀሳቀስ፣ ይህ ሀሳቡን በቀላሉ የሚለውጥ ሰውን ለማመልከት ጥቅም ላይ የዋለ ምሳሌያዊ አነጋገር ነው፡፡ ወይም 2) ንፋሱ ስነፍስ ድምፅ የሚያሰማ፡፡ ይህ ምሳሌያዊ ገለጻ ብዙ ነገር ይናገራል ይሁን እንጂ ይህን ያኸል ጠቃሚ ነገር አይናገርም፡፡ ( and ተመልከት) ሸንበቆ “ረጅም፣ ሳር መሰል ተክል” ለስላሳ ልብስ የለበሰ “ውድ ልብስ የለበሰ”፡፡ ሀብታሞች ይህንን ዓይነት ልብስ ይለብሱ ነበር፡፡ የምር ይህ ቃል ብዙ ጊዜ “እነሆ” በሚል ቀጥሎ ለሚመጣው ሀሳብ ትኩረት መስጠት እንደሚያስፈልግ በሚያሳስብ ቃል ተተርጉሟል፡፡ ተለዋጭ ትርጉሙለ “በእርግጥ”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ መናገሩን ቀጥሏል፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጥር 10 ላይ ኢየሱስ ከነቢይ ሚልክያስ መጽሐፍ በመጥቀስ የመጥመቁ ዮሐንስ ሕይወት እና አገልግሎት በተነገረው ትንቢት መሠረት መሆኑን አሳይቷል፡፡ ነገር ግን ምን ልታዩ ወጣችሁ - ነብይ ይህ ስለመጥመቁ ዮሐንስ የተጠየቁ ተከታታይ ጥያቄዎች ቀጣዩ ክፍል ነው፡፡ ( ተመልከት) ነገር ግን ምን ልታዩ ወጣችሁ - ነብይ? አዎን እላችኋለሁ “እናንተ” የሚለው በብዙ ቁጥር የተገለጸው ተውላጠ ስም በሁለቱም ሁኔታዎች ውስጥ ሕዝቡን የሚያመለክት ነው፡፡ ከነቢይም የሚበልጥ “ተራ ነቢይ ያለሆነ” ወይም “ከተራ ነቢይ በጣም የሚበልጥ” ይህ እርሱ ነው “ይህ” መጥመቁ ዮሐንስ የሚያመለክት ነው፡፡ ስለ እርሱ የተጻፈው እርሱ ነው “እርሱ” የሚው ቃል “በቀጣዩ ሀረግ ውስጥ “መልዕክተኛዬ” የተባለው የሚያመለክት ነው፡፡ መልዕክተኛዬን እልካለሁ “እኔ” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው እግዚአብሔር ነው፡፡ የዚህ የብሉይ ኪዳን ትንቢት ጸሐፊ እግዚአብሔር የተናገረውን በቀጥታ ጽፏል፡፡ በፊትህ “ከፊትህ” ወይም “ከአንተ በፊት ይሄድ ዘንድ፡፡” “አንተ” የሚለው ተውላጠ ስም የነጠላ ቁጥር ነው፡፡ ምክንያቱም በትምህርተ ጥቅስ ውስጥ እግዚአብሔር ስለ መስሑ የተነገረ ነው፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ መናገሩን ቀጥሏል፡፡ ከሴቶች ከተወለዱ ሁሉ “ሴቶች ከወለዷቸው ሰዎች መካከል” ወይም “በምድር ላይ ከኖሩ ሰዎች መካከል” ከመጥመቁ ዮሐንስ የሚበልጥ ማንም የለም ኤቲ፡ “መጥመቁ ዮሐንስ ትልቁ ነው” በመንግስተ ሰማያት እግዚብሔር በሚመሰርተው አገዛዝ ውስጥ፡፡ ኤቲ፡ “ወደ መንግስተ ሰማየት ከሚገቡ ሰዎች መካከል” ከእርሱ የሚበልጥ የለም “ከመጥመቁ ዮሐንስ በላይ ጠቃሚ የለም” ከመጥመቁ ዮሐንስ ዘመን ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ “”ከመጥምቁም ከዮሐንስ ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ” መንግሥተ ሰማያት ትገፋለች፥ ግፈኞችም ይናጠቋታል። አማራጭ ትርጓሜዎቹ 1) ግፈኞች በግፍ ይናጠቁታል ወይም 2) “ሰዎች የመንግስተ ሰማይን ዋና ሀሳብ ያሳድዳሉ እንዲሁም ግፈኞች ልቆጣጠሩት ይሞክራሉ” ወይም 3) “መንግስተ ሰማያት በኃይል ወደፊት ትሄዳለች እንዲሁም ኃይለኛ የሆኑ ሰዎች የዚህ አካል ለመሆን ይፈልጋሉ፡፡”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ መናገሩን ቀጥሏል፡፡ ሕግ “የሙሴ ሕግ” ዮሐንስ “መጥመቁ ዮሐንስ” እና አናንተ ከሆነክ “አናንተ” የሚለው ተውላጠ ስም በሕዝቡ መካከል ያሉ ሰዎችን ነው፡፡ ይህ ኤልያስ ነው “ይህ” መጥመቁ ዮሐንስ የሚያመለክት ነው፡፡ ይህ ሀረግ መጥመቁ ዮሐንስ በብሉይ ኪዳን የተገለጸው የነብዩ ኤልያስ ጋር ተዛምዶ ያለው ነው ይሁን እንጂ መጥመቁ ዮሐንስ ኤልያስ ግን ማለት አይደለም፡፡ ( ተመልከት) የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ ኤቲ፡ “የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ” የሚሰማ ጆሮ ያለው “መስማት የሚችል ጆሮ ያለው” ወይም “የሚሰማኝ ሁሉ” ይስማ በደንብ ይስማ” ወይም “ለተናገርኩት ነገር ትኩረት ይስጥ”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ መናገሩን ቀጥሏል፡፡ ይህን በምን እመስለዋለሁ? ይህ የጥያቄ መጀመሪያ ነው፡፡ይህንን ጥያቄ ኢየሱስ የተጠቀመው በዚያ ዘመን ይኖር የነበረውን ሕዝብ እና ሕጻናት በገቢያ ሥፍራ ከሚያደርት ነገር ጋር በማነጻጸር ነው፡፡ በጥያቄ ጀምሯል፡፡ “ ( ተመልከት) በገበያ የሚቀመጡትን ልጆች ይመስላሉ፥ እነርሱም በዚያ ተቀምጠው እርስ በእርሳቸው ይጠራራሉ፡፡ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ትርጉም እንደዚህ ሊሆን ይችላል 1) ኢየሱስ “ዋሽንት ነፋላቸው” እንዲሁም ዮሐንስ “አለቀሰላቸው” ነገር ግን “ይህ ትውልድ” ለመደነስም ሆነ ለማልቀስ አሻፈረኝ አለ፡፡ ይህ የመታዘዝ ምሳሌ ነው፡፡ ወይም 2) ፈሪሳዊያን እና ሌለች ሃይማኖታዊ መሪዎች እነርሱ በሙሴ ሕግ ላይ የጨመሯቸውን ሕጎች አልታዘዝ አለ በማለት ሕዝቡን ይወቅሱታል፡፡ ( ተመልከት) ይህ ተውልድ “በዚህ ዘመን የሚኖሩ ሰዎች” ወይም “እነዚህ ሰዎች” ወይም “እናንተ የዚህ ዘመን ሰዎች” የገቢያ ሥፍራ ይህ ትልቅ የሆነ ሰዎች የተለያዩ ነገሮችን የሚገዙበትን እና የሚሸጡበት ክፍት ሥፍራ ነው፡፡ ዋሽንት ተጫወትንላችሁ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በገቢያ ሥፍራ የተቀመጡትን ልጆች ነው፡፡ “እናንተ” የሚለው ቃ የሚያመለክተው “ይህንን ተውልድ” ነው ወይም ሙዝቃ ሰምቶ ምንም ምላሽ ያልሰጠውን ሕዝብ ነው፡፡ ዋሽንት የመሰለ የሙዚቃ መሣሪያ ይህ ረጅም የሆነ የትንፋሽ የሙዚቃ መሣሪያ ነው፡፡ እንዲሁም አልደነሳችሁም “ይሁን እንጂ በሙዚቃው አልተጫወታችሁም” ወይም አላለቀሳችሁም "ከእኛ ጋርም አላለቀሳችሁም"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ መጥመቁ ዮሐንስ መናገሩን አጠናቀቀ፡፡ ምግብ ሳይበላና ሳይጠጣ "ምግብ ሳይበላ" ይህ ዮሐንስ ምንም ዓይነት ምግብ በልቶ አያውቅም ማለት አይደለም፡፡ ኤቲ፡ “ብዙ ጊዜ ይጾም ነበር” ወይም “ጥሩ ምግብ አይበላም ነበር” (UDB) እንዲህ አሉት፡፡ “እርኩስ መንፈስ አለበት” ኢየሱስ ሰዎች ስለ ዮሐንስ የተናገሩትን በቀጥታ ጠቅሷል፡፡ ይህ በቀጥታ እንዲህ ሊጠቀስ ይችላል ፡ “እነርሱም እርኩስ መንፈስ አለበት አሉት” ወይም “ዳብሎስ አለበት አሉት” ወይም “እርኩስ መንፈስ አለበት ብለው ከሰሱት”( ተመልከት) እነርሱ “እነርሱ” የሚለው ተውላጠ ስም በዚያ ዘመን ይኖሩ የነበረው ሰዎችን ያመለክታል፡፡ የሰው ልጅ በዚያ ዘመን ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ኢየሱስ የሰው ልጅ እንደሆነ መረዳት ይኖርባቸው ብሎ ይጠብቅ ስነበር እንዲህ ተብሎ መተርጎም ይችላል “እኔ የሰው ልጅ እነርሱ ግን እንዲህ አሉት፣ “እነሆ፥ በላተኛው ኢየሱስ እንደ የሰው ልጅነቱ ሰዎች ስለ እርሱ የተናገረውን ጠቅሷል፡፡ ይህንን በትምህርት ጥቅስ ውስጥ ሳናስቀምጥ እንዲህ ሊተረጎም ይችላል፡ “በታለተኛ ነው አሉት” ወይም “ብዙ ይበላል ብለው ከሰሱት”፡፡ የሰው ልጅ የሚለው ሀረግ 1እኔ የሰው ልጅ” ብለህ ከተጎምህ ይህንን ደግሞ “እኔን በታለተኛ ነው አሉኝ” ብለህ መተርም ትችላለህ፡፡ በታለተኛና ነው "እርሱ በላተኛ ነው” ወይም “ሁል ጊዜ ብዙ ምግብ ይበላል” ጠጭ "ጠጭ" ወይም "ብዙ አልኮል ሁል ጊዜ ይጠጠቃል" ይሁን እንጂ ጥበብም በሥራዋ ጸደቀች። ይህ ምናልባትም ኢየሱስ ከሁኔታው ጋር ተስማሚ የሆነ ምሳሌን የተናገረበት ነው፡፡ ምክንያቱም ሕዘቡም እርሱ እና ዮሐንስን ስለ ጥበባቸው አልተቀበሏቸውም፡፡ በ UDB ውስጥ ባለው መሠረት በቀጥታ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ( ተመልከት) ጥበብ ጸደቀች በዚህ ገለጻ መሠረት ኢየሱስ ጥበብን በሴት ይመስላታል፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ጠበብ ከእግዚአብሔር ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንደሚያደረገን የሚናገር ሳይሆን ጥበብ ራሱ ትክክለኛ እንደሆነች የተገለጸበት ነው ( ተመልከት) በሥራዎቿ “እርሷ” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው “”ኢየሱስ በሴት የመሰላትን ጥበብን ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ: ኢየሱስ ከዚህ በፊት የተለያዩ ተዓምራትን ባደረገባቸው ሥፍራዎች ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን መገሰጽ ጀመረ፡፡ ከተማዎቹን ገሰጸ ኢየሱስ በዚህ ሥፍራ ላይ ምሌን በመጠቀም በከተማዎቹ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን ትክክለኛ ስላልሆነው ሥራቸው ገሰጸቻ ( ተመልከት) ከተማዎች "ከተማዎች" ታላላቅ ተዓምራት የተደረጉባቸው ይህ እንዲህ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡ “ብዙዎቹን ታላላቅ ተዓራትን ያደረገባቸው ሥፍራዎች” ( ተመልከት) ታላላቅ ተዓምራት ኤቲ፡ “ታላላቅ ሥራዎች” ወይም “ታላላቅ ኃይል” ወይም “ተዓምራት” ንሰሓ ስላልገቡ “እነርሱ” የሚለው ተውላጠ ስም በከተማዎቹ ውስጥ የሚኖሩ ንሰሓ ያልገቡትን ሰዎች ያመለክታል፡፡ ወዮልሽ ኮራዚ፤ ወዮልሽ ቤተ ሳይዳ! ኢየሱስ ኮራዚ እና ቤተ ሳይዳ የተባሉ ከተማዎች የሚደምጡ አድርጎ ነው የተናገረው፡፡ ይሁን እንጂ እነርሱ አይሰሙን፡፡ ( ተመልከት) ኮራዚ . . . ቤተ ሳይዳ . . . ጢሮስ . . . ሲዶና በእነዚያ ከተሞች ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን ለማመልከት የዋለ ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ ( ተመልከት) እናንተ የተደረገው ተአምራት በጢሮስና በሲዶና ተደርጎ ቢሆን፥ ይህ እንዲህ ሊተረጎም ይችላል: "በእናንተ መካከል ያደረኩትን ተዓምራት በጢሮስና በሲሶና ባደረግ ኖሮ” ( ተመልከት) ወዮልሽ . . . በእናንተ መካከል የተደረገው “አንተ” የሚለው ተውላጠ ስም የተገለጸወ በነጣ ቁጥር ነው፡፡ ከብዙ ጊዜ በፊት ንስሐ በገቡ ነበርና። በዚህ ሥፍራ “እነርሱ” ተብሎ የተገለጸው የጢሮስና ሲዶና ሰዎች ነው፡፡ ንሰሓ "ስለ ኃጢአታቸው ይቅርታን በጠየቁ ነበር" በፍርድ ቀን ከእናንተ ይልቅ ለጢሮስና ለሲዶና ይቀልላቸዋል። "በፍርድ ቀን ከእናንተ ይልቅ እግዚብሔር ለጢሮስ እና ለሲዶና የተሻለ መምህረት ያደርግላቸዋል" ወይም "እግዚብሔር ከጢሮስ እና ከሶዶና ሐህዝቦች ይልቅ እግዚአብሔር እናንተን ይቀጣል፡፡” በተዘዋዋር የተገለጸው መረጃ “ምንም እንኳ ያደረኳቸውን ተዓምራትን ቢትመለከቱም ንሰሓ ስላልገባቹ እና በእኔ ስላላመናችሁ፡፡” ( ተመልከት) ከአንተ ይልቅ በዚህ ሥፍራ “አንተ” የሚለው ተውላጠ ስም በነጠላ ቁጥር ሲሆን ኮራዚ ወይም ቤተ ሳይዳን ያመለክታል፡፡ ( ተመልከት)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ኢየሱስ ከዚህ በፊት ተዓምራት ያደረገባቸው ከተማዎች ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን መገሰጹን ቀጥሏል፡፡ . እንች ቅፍርናሆም በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ በቅርፍናሆን የሚኖሩ ሰዎች ልክ እንደሚያደምጡ አድርጎ ይናገራል ይሁን እንጂ እነርሱ እየሰዳመጡት አይደለም፡፤ “አንተ” የሚለው ተውላጠ ስም በነጠላ ቁጥር የተገለጸ ሲሆን በእነዚህ ሁለት ጥቅሶች ውስጥ ቅፍርናሆምን የሚያመለክት ነው፡፡ ( and ተመልከት) ቅፍርናሆም . . . ሶዶም የእነዚህ ከተሞች ስም በቅፍርናሆም እና ሶዶም ውስጥ ለሞኖሩ ሰዎች ምሳሌ ሆኖ ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ ( ተመልከት) እስከ ሰማይ ከፍ አልኩ ብለስ ታስቢያለሽ? የቅፍርናሆም ሕዝቦች ስላላቸው ትምክት ለመገሰጽ ኢየሱስ የተጠቀመው ጥያቄ ነው፡፡ በዚህ ዓይነት መንገድ ሊተረጎም ይችላል “እስከ ሰማይ እሄዳለሁ?" ወይም “እግዚአብሔር ያከብረኛል ብለሽ ታስቢያለሽ?" ( እና ተመልከት) ከፍ ከፍ እላለሁ "እከብራለሁ" ( ተመልከት) ወደ ሲኦል ትወርጂያለሽ "እግዚአብሔር ወደ ሲኦል ያወርድሻ" ( ተመልከት) በአንቺ የተደረገው ተአምራት በሰዶም ተደርጎ ቢሆን፥ "በእናንተ ያደረኳቸውን ተዓምራት በሶዶም አድርጌ ቢሆን ኖሮ" ( ተመልከት) ታላላቅ ነገሮች "ታላላቅ ሥራዎች" ወይም "የኃይል ሥራ" ወይን "ተዓምራት" እስከ ዛሬ በኖረች ነበርና። “እርሷ” የሚለው ተውላጠ ስም የሶዶምን ከተማ ያመለክታል፡፡ በፍርድ ቀን ከአንቺ ይልቅ ለሰዶም አገር ይቀልላታል። ይህ እንዲህ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል “በፍርድ ቀን እግዚብሔር ከእናንተ ይልቅ ለሶዶም ምድር ይበልይ ምህረት ያደርግላታል” ወይም “በፍርድ ቀን እግገዚአብሔር እናንተ ከሶዶም ይልቅ ይቀጣችኋል”፡፡ ይህ በተዘወዘዋር መልኩ የሚሰጠው መረጃ “ምንም እንኳ እኔ የሠራኋቸውን ተዓምራትን ቢትመለከቱም ንሰሓ ስላልገባቹ እና በእኔ ስላለመናችሁ” ( ተመልከት)
አጠቃላይ መረጃ: በቁጥር 25 እና 26 ላይ በሕዝቡ መካከል ሆኖ በሰማይ ወደሚኖረው አባቱ ጸለየ፡፡ በቁጥር 27 እንደገና ለሕዝቡ መናገር ጀመረ፡፡ ኢየሱስ እንዲህ የሚል ምላሽ ሰጠ ከዚያም እንዲህ አለ ይህ እንዲህ ማለት ሊሆን ይችላል 1) በ MAT 10:5 የተላኩት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ከሄዱበት ተመልሰዋል (MAT 12:1 ተመልከት) እንዲሁም አንድ ሰው ስላለው አንድ ነገር ኢየሱስ ምላሽ እየሰጠ ነው ወይም 2) ኢየሱስ ንሰሓ ስላልገቡት ከተሞች የተናገረውን የፍረድ ንግግር አጠቃሏል፡ “ከዚህ በተጨማሪ ኢየሱስ እንዲህ አለ፡፡” አባት . . . ልጅ በእግዚአብሔር እና ኢየሱስ መካከል ያለውን የአባት እና ልጅ ግንኙነት የሚያሳይ የማዕረግ ስም ነው ( የሰማይ እና የምድር ጌታ ይህንን እንደ ምሳሌ መረደት ይቻላል “በሰማይ እና በምደር ባሉት ነገሮቸ ሁሉ ላይ ጌታ የሆነ” ወይም “የዓለማት ሁሉ ጌታ” ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው “እነዚህን ነገሮች” የሚለው ሀረግ ምንን እንደሚያመለክት ግልጽ ነው፡፡ ይህ ምን ማለት እንደሆነ በግልጽ ቋንቋ ለመናገር አማራጭ ትርጉም ተመራጭ ይሆናል፡ “ጠብባን እና የተማሩ ሰዎች ለማወቅ ያልተፈቀደላቸውን እውነት ምንም ለማያውቁ ሰዎች ገለጥክላቸው፡፡” ይህንን ነገር ከ . . . ሰወርክ “ይህንን ከ. . . ሰወርክ” ወይም “ይህንን ነገር ለ . . . አልገለጥክም”፡፡ አልገለጥም የሚለው ግሥ “የመገለጥ” ተቃራኒ ነው፡፡ ጠቢባን እና አዋቂዎች "ጠቢባን እናነአዋቂዎች የሆኑ ሰዎች” ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ጠቢባን እና አዋቂዎች እንደሆኑ የሚያስቡ ሰዎች” ( ተመልከት) ገለጥክላቸው “አስታወካቸው”፡፡ “ለእርሱ” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው በዚህ ቁጥር መጀመሪያ አከባቢ የተጠቀሰውን “እነዚህ ነገሮች” የሚለውን ነው፡፡ ላልተማሩ፣ እንደ ትንንሽ ሕጻናት ላሉት ይህ አጠቃላይ ሀረግ “ትንንሽ ልጆች1 እና “ያልተማሩ” ወይም “የማያውቁ” የሚለውን በውስጡ አጠቃሎ በመያዝ የተተረጎመ ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ምንም የማያውቁ ትንንሽ ልጆች” ይህ በአንተ ፊት መልካም ፈቃድህ ሆነ በፊትህ መልካም ፈቃድ ሆነ - "ምክንያቱም ይህንን ማድረግ መልካም እንደሆነ ተመለከትህ"
እንደ ትንንሽ ሕጻናት ያሉ ጠብባን ያልሆኑ ወይም በጣም ያልተማሩ ሰዎችን ወይም ጠብባን እና በሚገባ የተማሩ እንዳልሆኑ ለሚያውቁ ሰዎች ለማመልከት ጥቅም ላይ የዋለ ምሳሌ ነው፡፡ ( ተመለልከት) ይህ በአንተ ፊት መልካም ፈቃድህ ሆነ በፊትህ መልካም ፈቃድ ሆነ - "ምክንያቱም ይህንን ማድረግ መልካም እንደሆነ ተመለከትህ"
ሁሉ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቶኛል፤ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊተረጎም ይችላል፡ “አባቴ ሁሉን ነገር ሰጥቶኛል” ወይም “አባቴ ሁሉን ነገር ለእኔ ሰጥቶኛል”፡፡ እግዚአብሔር አብ ከእግዚአብሔር ወልድ፣ ከኢየሱስ ጋር ዘላለማዊ ግንኙነት ያለው ሲሆን ይም በእግዚአብሐየር አብ እና ወልድ መካከል ባለ የአባት እና ልጅ ግንኙነት ተገልጧል፡፡ “አባት” እና “ልጅ” የሚሉ ቃላት በመጀመሪያዎቹ ቅዱሳት መጽሐፍ ውስጥ ጥቅም ላይ የዋሉት ይህንን ግንኙነት ለመግሌ ነው ( እና ተመልከት ከአብ በቀር ልጅን የሚያውቅ የለም "ልጅን የሚያውቅ አብ ብቻ ነው፡፡" አባት እና ልጅ በእርግጠኝነት እርስ በእርስ የእውነት የሚተዋወቁ ናቸው (ከእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጋር)፡፡ ልጅን የሚያውቅ ካላቸው ግንኙነተ የተነሳ ልጅን ማወቅ ልጅ በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ ራሱን በሦስተኛ መደብ ይጠራል፡፡ ( ተመልከት) ከልጅ በስተቀር አባትን የሚያውቅ ማንም የለም “ከወልድም በቀር አብን የሚያውቅ የለም።” አብን የሚያውቅ ከግል ግንኙነታች የተነሳ ወልድም ሊገለጥለት ከሚፈቅድ በቀር ለተርጓሚዎች ምክር፡ "ሰዎች አብ ማን እንደሆነ ማወቅ የሚችሉት ልህ አብን ልገልጥላቸው ከወደደ ብቻ ነው፡፡”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ኢየሱስ ለለሕዝቡ ማናገሩን ጨረሰ፡፡ ደካች እና ሸክም የከበደባችሁ ይህ ምሳሌ የአይሁድ ሕግ “ቀንበር” የሚያመለክት ነው፡፡ ( ተመልከት) እኔም አሳርፋችኋለሁ "ከድካማችሁ እና ሸክማችሁ አሳርፋችኋለሁ" ( ተመልከት) ቀንበሬን ተሸከሙ “እናንተ” የሚለው ተውላጠ ስም “ደካሞች እና ሸክም የከበደበባችሁ ሁሉ” የሚለውን የሚያመለክት ነው፡፡ የዚህ ምሳሌ ትርጉሙ “የሰጠኋችሁን ሥራ ተቀበሉ” ወይም “ከእኔ ጋር ተባብራችሁ ሥሩ” ( ተመልከት) ሸክሜ ቀሊል ነው “ቀላል” የሚለው ቃል የከባድ ተቃራኒ እንጂ የጨለማ ተቃራኒ አይደለም
1 በዚያን ጊዜ ኢየሱስ በሰንበት በእርሻ መካከል ሄደ። ደቀ መዛሙርቱም ተርበው ስለ ነበር፣ እሸቱን እየቀጠፉ ይበሉ ጀመር፡፡ 2 ፈሪሳውያንም ያንን ባዩ ጊዜ፣ “ኢየሱስን፣ ደቀ መዛሙርትህ በሰንበት የሚያደርጉትን የማይገባ ነገር ተመልከት” አሉት፡፡ 3 ኢየሱስ ግን፣ "ዳዊትና ከእርሱ ጋር የነበሩት ሰዎች በተራቡ ጊዜ ያደረገውን ከቶ አላነበባችሁምን? 4 ወደ እግዚአብሔር ቤት ገብቶ፣ ለካህናት ብቻ እንጂ ለእርሱና ከእርሱ ጋር ለነበሩት ያልተፈቀደውን የተቀደሰ እንጀራ እንዴት እንደበላ?" አላቸው። 5 በሰንበት ካህናት በቤተ በመቀደስ ሥራ እንድሚሠሩና፣ ሰንበትን እንደሚያረክሱ፣ በደልም እንደማይሆንባቸው ከሕጉ አላነበባችሁምን? 6 እኔ ግን እላችኋለሁ፣ ከቤተ መቅደስ የሚበልጠው እዚህ አለ፡፡ 7 “መሥዋዕትን ሳይሆን ምሕረትን እፈልጋለሁ” የሚለውን ብታውቁ ኖሮ፣ በደል የሌለባቸውን አትፈርዱባቸውም ነበር፡፡ 8 የሰው ልጅ የሰንበት ጌታ ነውና።" 9 ከዚያም ኢየሱስ ከዚያ ተነስቶ፣ ወደ ምኲራባቸው ገባ። 10 እነሆ፣ እጁ ሽባ የሆነ አንድ ሰው ነበረ፡፡ ፈሪሳውያንም ኢየሱስን በኅጢአት ለመክሰስ፣ "ሕጉ በሰንበት መፈወስን ይፈቅዳልን?" ብለው ጠየቁት፡፡ 11 ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፤ “ከእናንተ መካከል አንድ በግ ብቻ ብትኖረውና፣ ያቺም በግ ጉድጓድ ውስጥ ብትገባበት፣ በሰንበት የማያወጣት ማን ነው? 12 ታዲያ ሰውማ ፣ ከበግ ይልቅ ምን ያህል ዋጋ ይኖረዋል! ስለዚህ በሰንበት መልካም መሥራት ተፈቅዷል ፡፡" 13 ከዚያም ኢየሱስ፣ ሰውየውን፣ “እጅህን ዘርጋ” አለው፡፡ እጁንም ዘረጋ፣ እንደ ሌላውም እጅ ጤነኛ ሆነ፡፡ 14 ነገር ግን ፈሪሳውያን ሄደው አሤሩበት፣ እርሱን የሚገድሉበትን መንገድ ይፈልጉ ነበር፡፡ 15 ኢየሱስ ይህን እንዳወቀ፣ ከዚያ ፈቀቅ አለ። ብዙ ሰዎች ተከተሉት፤ እርሱም ሁሉንም ፈወሳቸው፡፡ 16 ሰዎቹን ስለ እርሱ ለሌሎች እንዳይገልጹ አዘዛቸው፣ 17 ይህም የሆነው በነቢዩ በኢሳይያስ እንዲህ ተብሎ የተነገረው እንዲፈጸም ነው፤ 18 እነሆ፣ እኔ የመረጥኩት አገልጋዬ፤ የምወደው ነፍሴም ደስ የተሰኘችበት። መንፈሴን በእርሱ ላይ አኖራለሁ፤ እርሱም ፍትሕን ለአሕዛብ ያውጃል። 19 አይጨቃጨቅም ወይም አይጮህም፤ ወይም ማንም ድምፁን በጐዳናዎች ላይ አይሰማም። 20 ፍርድን ለድል እስኪያበቃ ድረስ፤ የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም፣ የሚጤሰውንም የጧፍ ክር አያጠፋም፣ 21 አሕዛብም በስሙ ይታመናሉ።" 22 ከዚያም በአጋንንት የተያዘን ዐይነ ስውርና ዲዳ ሰው ወደ ኢየሱስ አመጡ፤ እርሱም ፈወሰው፤ ዲዳውም ተናገረ፣ አየም። 23 ሕዝቡም በመገረም፣ "ይህ ሰው የዳዊት ልጅ ይሆን እንዴ?" አሉ፡፡ 24 ነገር ግን ፈሪሳውያን ይህን ተአምር በሰሙ ጊዜ “ይህ ሰው በአጋንንት አለቃ በብዔልዜቡል ካልሆነ በቀር አጋንንቱን አያወጣም ነበር" አሉ፡፡ 25 ኢየሱስም ዐሳባቸውን ዐውቆ ፣“እርስ በርሱ የሚከፋፈል መንግሥት ይወድቃል፤ እርስ በርሱ የሚለያይ ከተማ ወይም ቤት ሁሉ አይጸናም፡፡ 26 ሰይጣን ሰይጣንን የሚያወጣ ከሆነ፣ እርስ በርሱ ተከፋፍሏል፣ መንግሥቱስ እንዴት ይቆማል? 27 እኔ አጋንንትን የማወጣው በብዔልዜቡል ከሆነ፣ ተከታዮቻችሁ በማን ሊያወጡ ነው? ከዚህ የተነሣ እነርሱው ይፈርዱባችኋል፡፡ 28 ነገር ግን በእግዚአብሔር መንፈስ አጋንንትን የማወጣ ከሆነ፣ እንግዲህ የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ መጥታለች፡፡ 29 ማንም ኃይለኛውን ሳያስር ወደ ቤቱ ገብቶ ንብረቱን እንዴት መዝረፍ ይችላል?፡፡ ካሰረው በኋላ ግን፣ ንብረቱን ይዘርፋል። 30 ከእኔ ጋር ያልሆነ ተቃዋሚዬ ነው፣ ከእኔም ጋር የማይሰበስብ ይበትናል፡፡ 31 ስለዚህ እላችኋለሁ፣ ማንኛውም ኅጢአትና ስድብ ለሰዎች ይቅር ይባልላቸዋል ፤መንፈስ ቅዱስን የሚሳደብ ግን ይቅር አይባልም፡፡ 32 በሰው ልጅ ላይ ማንኛውንም ቃል የሚናገር ይቅር ይባልለታል፤ በመንፈስ ቅዱስ ላይ የሚናገር ግን፣ በዚህ ዓለምም ሆነ በሚመጣው ይቅር አይባልም። 33 እንግዲህ ዛፍ የሚታወቀው በፍሬው ስለ ሆነ ዛፉን መልካም አድርጉ፤ ፍሬውም መልካም ይሆናል፣ ወይም ዛፉን መጥፎ አድርጉ ፍሬውም መጥፎ ይሆናል፡፡ 34 እናንተ የእባብ ልጆች ክፉዎች ስለ ሆናችሁ፣ እንዴት መልካም ልትናገሩ ትችላላችሁ? ምክንያቱም በልብ ውስጥ የሞላውን አፍ ይናገረዋል፡፡ 35 . መልካም ሰው በልቡ ውስጥ ካለው መልካም መዝገብ፣ መልካሙን ያወጣል፤ ክፉ ሰውም ልቡ ውስጥ ካለው ክፉ መዝገብ ክፉውን ይወጣል። 36 ለእናንተም እላችኋለሁ፣ በፍርድ ቀን ሰዎች ስለ ተናገሯቸው ከንቱ ንግግሮች መልስ ይሰጣሉ፡፡ 37 ምትናገሩት ትጸድቃላችሁ፣ በምትናገሩትም ይፈረድባችኋልና፡፡ 38 አንዳንድ የሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን መልሰው ኢየሱስን፣ “መምህር ሆይ፣ ምልክት እንድታሳየን እንፈልጋለን" አሉት። 39 ኢየሱስ ግን መልሶ እንዲህ አላቸው፣ ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይፈልጋል፤ ነገር ግን ከነቢዩ ከዮናስ ምልክት በቀር ምንም አይሰጠውም፡፡ 40 ዮናስ በትልቅ ዐሣ ሆድ ውስጥ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ፣ የሰው ልጅም ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት በምድር ልብ ውስጥ ይሆናል፡፡ 41 የነነዌ ሰዎች በዮናስ ስብከት ንስሓ በመግባታቸው፣ በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ሰዎች ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፡፡ ደግሞም ከዮናስ የሚበልጥ እዚህ አለ፡፡ 42 የደቡብ ንግሥት፣ የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳርቻዎች መጥታለችና፣ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድበታለች፡፡ደግሞም ከሰሎሞን የሚበልጥ እዚህ አለ፡፡ 43 ርኩስ መንፈስ ከሰው በወጣ ጊዜ፣ ዕረፍት ፍለጋ ውሃ በሌለባቸው ቦታዎች ያልፋል፣ ነገር ግን አያገኝም። 44 ከዚያም፣ 'ወደ ወጣሁበት ቤቴ እመለሳለሁ' ይላል። ሲመለስም ቤቱ ጸድቶ ተዘጋጅቶ ያገኘዋል፡፡ 45 ከዚያም ይሄድና ከእርሱ ይልቅ የከፉትን ሰባት ሌሎች መናፍስትን ይዞ ይመጣል፣ ሁሉም በዚያ ለመኖር ይመጣሉ፡፡ የዚያም ሰው የመጨረሻው ሁኔታ ከመጀመሪያው የከፋ ይሆናል፡፡ በዚህ ክፉ ትውልድ ላይ የሚሆነውም እንደዚሁ ነው፡፡ 46 ኢየሱስም ለሕዝቡ እየተናገረ እያለ፣ እናቱና ወንድሞቹ ሊያናግሩት ፈልገው፣ በውጭ ቆመው ነበር። 47 አንድ ሰውም፣ "እነሆ፣ እናትህና ወንድሞችህ ሊያነጋግሩህ በውጭ ቆመዋል" አለው። 48 ኢየሱስም መልሶ ለነገረው ሰው፣ "እናቴ ማን ናት? ወንድሞቼስ እነማን ናቸው?" አለው። 49 ከዚያም እጁን ወደ ደቀ መዛሙርቱ ዘርግቶ፣ "እናቴና ወንድሞቼ እነዚህ ናቸው! 50 በሰማይ ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ፣ ወንድሜ፣ እኅቴ እናቴም ነውና" አለ።
አጠቃላይ መረጃ: ይህ አዲስ የታሪኩ አዲስ ክፍል ሲሆን ጸሐፊው በዚህ ክፍል ውስጥ በኢየሱስ አገልግሎት ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ስለመጣው ተቃውሞ ይተርካል፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥም ፈርሳዊያን የእርሱን ደቀ መዛሙርት በሰንበት አሸት መቅጠፋቸውን አስመልክቶ ያቀረቡትን ተቃውሞ እንመለከታለን፡፡ የእርሻ ማሳ ሰብል የተዘራበት መሬት፡፡ ስንዴ በአከባቢያችሁ የማይታወቅ ከሆነ “ሰብል”፣ “ዳቦ ለመጋገር የሚሆን እህል ማብቀያ ሥፍራ” በሚል አጠቃላይ መጠሪያን ተጠቀሙ፡፡ እሸት ይቀጥፉ ይበሉም ጀመር . . . በሰንበት ማድረግ ያልተፈቀደውን ያደርጋሉ በሰዎች ማሳ ውስጥ የሚገኝን እሸት ቀጥፈው መብላት ሌብነት አይደለም፡፡ ጥያቄው በበሰንበት ማድረግ ያልተፈቀደን ነገር ማድረግ ይቻላል ወይ የሚል ነው፡፡ ይህንን የእሼቱን ጫፍ ቀንጠበው እሸቱን ጫፍ ይህ ረጅም ሳሪ ከሚመስለው የስንዴ ተክል ጫፍ ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ይህ ጫፍ የተክሉን ፍሬ በውስጡ ይይዛል፡፡ ተመልከት አማራጭ ትርጉሞች፡ “ተመልከት”ወይም “አድምጥ” ወይም “አሁን ለምናገረው ነገር ትኩረት ስጥ”
አጠቃላይ መረጃ: ይህ አዲስ የታሪኩ አዲስ ክፍል ሲሆን ጸሐፊው በዚህ ክፍል ውስጥ በኢየሱስ አገልግሎት ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ስለመጣው ተቃውሞ ይተርካል፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥም ፈርሳዊያን የእርሱን ደቀ መዛሙርት በሰንበት አሸት መቅጠፋቸውን አስመልክቶ ያቀረቡትን ተቃውሞ እንመለከታለን፡፡ የእርሻ ማሳ ሰብል የተዘራበት መሬት፡፡ ስንዴ በአከባቢያችሁ የማይታወቅ ከሆነ “ሰብል”፣ “ዳቦ ለመጋገር የሚሆን እህል ማብቀያ ሥፍራ” በሚል አጠቃላይ መጠሪያን ተጠቀሙ፡፡ እሸት ይቀጥፉ ይበሉም ጀመር . . . በሰንበት ማድረግ ያልተፈቀደውን ያደርጋሉ በሰዎች ማሳ ውስጥ የሚገኝን እሸት ቀጥፈው መብላት ሌብነት አይደለም፡፡ ጥያቄው በበሰንበት ማድረግ ያልተፈቀደን ነገር ማድረግ ይቻላል ወይ የሚል ነው፡፡ ይህንን የእሼቱን ጫፍ ቀንጠበው እሸቱን ጫፍ ይህ ረጅም ሳሪ ከሚመስለው የስንዴ ተክል ጫፍ ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ይህ ጫፍ የተክሉን ፍሬ በውስጡ ይይዛል፡፡ ተመልከት አማራጭ ትርጉሞች፡ “ተመልከት”ወይም “አድምጥ” ወይም “አሁን ለምናገረው ነገር ትኩረት ስጥ”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ኢየሱስ ለፈርሳዊያን ትችት ምላሽ መስጠቱን ቀጥሏል፡፡ አናንተ . . . አናንተ ፈርሳዊያን በ . . . ውስጥ እንዲህ የሚል ቃል አላነበባችሁምን “ሕግ ምን እንደሚል ታውቁ ዘንድ የሕግ መጽሐፍትን አላነበባችሁምን" ( ተመልከት) ሰንበትን አያከብሩም "በሌሎች ቀናት የሚያደርጉትን ነገር በሰንበትም ያደርጋሉ" ጥፋት የለባቸውም "እግዚብሔር አይቀጣቸውም" ከመቅደስ የሚበልጥ በዚህ አለ "ከመቅደሱ ይበልጥ ጠቃሙ የሆነ”፡፡ ኢየሱስ የሚበልጠው ብሎ የተናገረው ስለ ራሱ ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ኢየሱስ ለፈሪሳዊያን ምላሽ መስጠቱን ቀጥሏል፡፡ አጠቃላይ መረጃ፡ በቁጠር 7 ላይ ኢየሱስ ፈሪሳዊያንን ለመገሰጽ ከነብዩ ሆሴ መጽሐፍ ጠቅሷል፡፡ ብታውቁ ኖሮ "አታውቁም" እናንተ . . . እናንተ ፈሪሳዊያን ምሕረትን እወዳለሁ መሥዋዕትንም አይደለም መሥዋዕት ጥሩ ነገር ነው ነገር ግን ምህረት ግን ይሻላል፡፡ ( ተመልከት) ይህ ማለት ምን ማለት ነው "እግዚአብሔር በቅዱሳት መጽሐፍቱ አማካኝነት ምን አለ" እወዳለሁ “እኔ” የሚለው ተውላጠ ስም እግዚአብሔርን የሚያመለክት ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ፡ በዚህ ሥፍራ ፈሪሳዊያን ኢየሱስ በሰንበት አንድ ሰውን መፈወሱን ወደተቃወሙበት የታሪኩ አቅጣጫ ይለወጣል፡፡ ኢየሱስ ከዚያ አልፎ ሄደ "ኢየሱስ የእርሻ ማሳውን ለቆ ወጣ" የእነርሱ ኢየሱስ እየተናገራቸው ያሉት ፈሪሳዊያን ምኩራብ እነሆ “እነሆ” የሚለው ቃል በታሪክ ውስጥ አዲስ ሰውን ያስተዋውቀናል፡፡ በቋንቋችሁ እንዲህ ዓይነት ነገር ማድረግ ይቻል ይሆናል፡፡ እጁ የሰለለች ሰው ነበረ "የሰለለች" ወይም "ያጠረች"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ኢየሱስ ለፈሪሳዊያን ትችት ምላሽ ሰጠ፡፡ ከእናንተ . . . ይዞ የማያወጣው ሰው ማን ነው? አማራጭ ትርጉም፡ “ሁላችሁም . . . ጎትታችሁ ታወጣላችሁ ( ተመልከት) እናንተ . . . እናንተ ፈሪሳዊያን ያለው "ያለው ሰው" በዚያ የሚተወው "በጉን በጉድጓድ ውስጥ የሚተወው" መልካም ማድረግ በሕግ ተፈቅዷል "መልካም የሚያደርጉ ሰዎች ሕጉን እየተላለፉ አይደለም” ወይም “መልካም የሚያደርጉ ሰዎች ሕጉን እየታዘዙ ነው"
ሰው የሰለለች እጅ ያለው ሰው እጅህን ዘርጋ "እጅህን አንሳ" ወይም እጅህን ዘርጋ" እርሱ ሰውዬው እጁ የሰውዬው እጅ ጤናው ተመለሰች "ሙሉ ለሙሉ ተፈወሰ" ወይም "ሙሉ ጤነኛ ሆነ" በእርሱ ላይ ተማከሩበት "እንዲያጠፉት ተማከሩ" እንዴት አድርገው "ዘዴ ፈለጉ" እርሱን ለመግደል ኢየሱስን ለመግደል h
አጠቃላይ መረጃ፡ ይህ ታሪክ እንዴት የኢየሱስ ተግባር የነብዩ ኢሳያስን ፍጻሜ እንደሆነ ያሳያል፡፡ ይህ "ፈሪሳዊያን እርሱን ለመግደል አቀዱ" ትቷቸው ሄደ "ተዋቸው" እንዳይገልጡትም ነገራቸው "ስለ እርሱ ለሌላ ለማንም ሰው እንዳይናገሩ" በነቢዩ በኢሳይያስ የተባለው ይፈጸም ዘንድ እንዲህ ሲል፦ "እግዚአብሔር በነብዩ ኢሳያስ አማካኝነት የተናገረው እና የተጻፈው"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: በዚህ ክፍል ውስጥ ጸሐፊው የኢየሱስ አገልግሎት በነብዬ ኢሳያስ የተጻፈው የትንቢት ቃል ፍጻሜ መሆኑን ለማሳየት ጠቅሶታ፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጸሐፊው ነብዩ ኢሳያስን መጥቀሱን ቀጥሏል፡፡ የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም "ደካማ ሰዎችን አያጠቃም” ( ተመልከት) የተቀጠቀጠ "በግማሽ የተሰበረ ወይም ጉዳት የደረሰበት” የሚጤስን የጥዋፍ ክርም የጥዋፍ ክር አንድ ጊዜ መብራት ከጀመረ በኋላ ጠንካራ አይደለም፤ ይህ ደግሞ ረዳት ያሌላቸው ሰዎችን ያመለክታል ( ተመልከት) እስኪ. . . ይህ ከአዲስ ዓረፍተ ነገር ጋር እንዲህ ሊተረጎም ይችላል፡ “ይህን እስኪያመጣ ድረስ ይህንን ያደርጋል” ወደ ድል የሚያደርስ ፍርድን ያመጣል "እኔ ትክክል እንደሆንኩ ሰዎችን ያሳምናል" በእርሱ ስም ለተርጓሚዎች ምክር: "በእርሱ" ( ተመልከት)
አንድ ዕውር ዲዳም የሆነ ሰው "ማየት እና መናገር የማይችል አንድ ሰው" ሕብዙም ሁሉ ተገረሙ "ኢየሱስ ሰወዬውን እንደፈወሰው የተመለከቱ ሰዎች ሁሉ በጣም ተገረሙ"
ይት ተዓምር የዐይነ ስውሩ፣ ደንቆሮው እና በእርኩስ መንፈስ የተያዘው ሰው የመፈወሱ ተዓምር ይህ ሰው በብዔል ዜቡል በአጋንንት አለቃ ካልሆነ በቀር አጋንንትን አያወጣም "ይህ ሰው አጋንትን ማውጣት የቻለበት ብቸኛው ምክንያት የብዔል ዜቡል አገልጋይ በመሆኑ ነው" ይህ ሰው ፈሪሳዊያን ኢየሱስን ያለመቀበላቸውን ለማሳየጥ የእርሱን ስም አይጠሩም ነበር፡፡ እናንተ . . . እናንተ ፈሪሳዊያን
ሰይጣንም ሰይጣንን የሚያወጣ ከሆነ "ሴጣን የራሱን መንግስት ተቃውሞ የሚሠራ ከሆነ" ( ተመልከት) መንግስቱ እንዴት ጸንታ ትቆማለች? "የሴጣን መንግስት ጸንቶ ሊቆም አይችልም" ወይም "የሴጣን መንግስት ይፈራርሳል" ( ተመልከት) ማስወጣት "አስገድዶ ማስወጣት" ወይም "ማበባረር" ወይም "አውጥቶ መወርወር" ወይም "ነቅሎ ማውጣት" ተከታዮቻችሁ በማን ያወጧቸዋል ለተርጓሚዎች ምክር፡ "የእናንተ ተከታዮች አጋንትን የሚያስወጡት በብዔል ዘቡል ኃይል አማካኝነት ነው" (ወይም UDB ተመልከት) ( ተመልከት) እነርሱ ፈራጆች ይሆኑባችኋል ለተርጓሚዎች ምክር፡ "አጋንትን በእግዚአብሔር ኃይል የሚያስወጡት የእናንተ ተከታዮች እኔን በብዔል ዘቡል ኃይል አጋንት ያስወጣል በማለታችሁ በእናንተ ላይ ይፈርዳሉ"
ወደ እናንተ ደርሳለች በፈሪሳዊያን ላይ መጣለች በመጀመሪያ ኃይለኛውን ሳያስሩ "ኃይለኛውን በመጀመሪያ በቁጥጥር ሥር ሳያደርጉ" ከእኔ ጋር ያልሆነ "እኔን የማይደግፈኝ” ወይም “ከእኔ ጋር የማይሠራ" የእኔ ተቃዋሚ ነው "እኔን ተቃውሞ ይሠራል" ወይም "ሥራዬን ያፈርሳል" መሰብሰብ ይህ ሰብል መሰብሰብ የሚያመለክት የተለመደ ቃል ነው፡፡ ( ተመልከት)
ማንኛው ኃጢአት እና በእግዚአብሔር ላይ የሚደረግ ስድብ ለሰዎች ይሰረይላቸዋል "ሰዎች የፈጸሟቸው ኃጢአቶች እና ስድቦችን እግዚአብሔር ይቅር ይላቸዋል” ወይም “ኃጢአት የፈጸሙ ሰዎችን ሁሉ እግዚአብሔር ይቅር ይላቸዋል፡፡ ወይም “እግዚብሔር ኃጢአት ያደረጉ ወይም የተሳደቡ ሰዎችን ሁሉ ይቅር ይላቸዋል” ( ተመልከት) በመንፈስ ቅዱስ ላይ ግን የሚናገር ሁሉ አይሰረይለትም። "መንፈስ ቅዱስን የሚሳደብን ግን እገግዚአብሔር ይቅር አይለውም" ( ተመልከት) እንነዲሁም በሰው ልጅ ላይ የሚናገር ኃጢአቱ ይሰረይለታል "የሰው ልጅን በመቃወም የሚነገርን ንግግር እግዚአብሔር ይቅር ይለዋል" በዚህ ዓለም ቢሆን ወይም በሚመጣው ለተርጓሚዎች ምክር፡ "በዚህ ጊዜ . . . በመጪው ጊዜ"
ዛፍዋን መልካም፥ ፍሬዋንም መልካም አድርጉ፥ ወይም ዛፍዋን ክፉ ፍሬዋንም ክፉ አድርጉ። "ፍሬዋ መልካም ከሆነ ዛፏ መልካም እንደሆነች እንዲሁም ፍሬዋ ክፉ ከሆነ ዛፏም ክፉ እንደሆነች ይታወቃል" መልካም . . . ክፉ ይህ ማለት 1) “ጤናማ . . . ጤናማ ያልሆነ” ወይም 2) "የሚበላ . . . የማይበላ" ዘፍ በፍሬው ይታወቃል ይህ እንዲህ ሊሆን ይችላል 1) "ሰዎች አንድ ዘፍ ጤናማ መሆን አለመሆኑን ፍሬውን ተመልክተው ያውቃሉ" ወይም 2) "ሰዎች የዛፉን ፍሬ በመመልከት የዛፉን ዝሪያ ያውቃሉ" ( ተመልከት) እናንተ . . . እናንተ ፈሪሳዊያን በልብ ሞልቶ ከተረፈው አፍ ይናገራልና። "አንድ ሰው በአንደበቱ የሚናገረው በልቡ ውስጥ ካለው ብቻ ነው” ( ተመልከት) መልካም መዝገብ . . . ክፉ መዝገብ "ትክክለኛ ሀሳቦች. . . ክፉ ሀሳቦች" ( ተመልከት)
እናንተ . . . እናንተ ፈሪሳዊያን ሰዎች ስለሚናገሩት ነገር . . .መልስ ይሰጡበታል፤ "እግዚአብሔር ይጠይቀቸዋል" ወይም "እግዚአብሔር ቃላቸውን ይመዝናል" እርባና የሌለው "ጥቅም የሌለው" ለተርጓሚዎች ምክር: "የሚጎዳ" እነርሱ "ሕዝቡ" ትጸድቃለህ . . . ትኰነናለህ "እግዚአብሔር ያጸድቅሃል . . . እግዚአብሔር ይፈርድብሃል" ( ተመልከት)
መሻት "ፍላጎት" ክፉና አመንዝራ ትውልድ በዚህ ዘመን የሚኖሩ ሰዎች ክፉ ማድረግ ይወዳሉ እንዲሁም ከእግዚአብሔር ታማኞች አይደሉም፡፡ ምንም ዓይነት ምልክት አይሰጣቸውም "ለዚህ ክፉ እና አመንዝራ ትውልድ እግዚአብሔር ምንም ዓይነት ምልክት አይሰጥም" ( ተመልከት) የዮናስ ምልክት ለትርጓሚዎች ምክር፡ "ለዮናስ ምን ሆነ" ወይም "ለዮናስ እግዚአብሔር ያደረገው ተዓምር ምን ነበር” ( ተመልከት) በመሬት ልብ ውስጥ በመቃብር ውስጥ ( ተመልከት)
የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "የነነዌ ሰዎች ይህንን ትውልድ ይከሳሉ . . . እንዲሁም እግዚአብሔር ክዳቸውን ይሰማል እና በእናንተ ላይም ይፈርዳል” "እግዚአብሔር የነነዌ ሰዎችን እና ይህንን ትውልድ በኃጢአተኛነታቸው ይፈርድባቸዋል ይሁን እንጂ እነርሱ ንሰሓ ገብተዋል፤ እናንተ ግን አልገባችሁም ስለዚህም በእናንተ ላይ ብቻ ይፈርዳል” ( ተመልከት) ይህ ትውልድ ኢየሱስ በኖረበት እና ባገለገለበት ዘመን ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ( ተመልከት) የሚበልጥ "ይበልጥ አስፈላጊ የሆነ"
የደቡድ ንግሥተ ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድበታለች፤ ለተርጓሚዎች ምክር: "የደቡድ ንግሥት በዚህ ትውልድ ላይ ትፈርዳለች . . . እግዚአብሔርም ፍርዷን ይሰማል በእናንተም ላይ ይፈርዳል” ወይም እግዚአብሔር በደቡቧ ንግሥት እና በዚህ ትውልድ ላይ በኃጢአታቸው ይፈርዳል ይሁን እንጂ እርሷ ንጉሥ ሰለሞንን ስለመጣች እናንተ ግን እኔን ስላልሰማችሁ የሚፈረደው በእናንተ ላይ ብቻ ይሆናል፡፡ ( ተመልከት) የደቡቧ ንግሥት ይህ የአሕዛብ መንግስ ንግሥት ሳባን ያመለክታል ( ተመልከት) ከምድር ዳርቻ መጥታለች "በጣም ሩቅ ከሆነ ሥፍራ መጥታለች” ( ተመልከት) ይህ ትውልድ ኢየሱስ ባገለገለበት ዘመን ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ( ተመልከት) የሚበልጥ "ይበልጥ አስፈላጊ የሆነ"
ውሃ የሌለበት ሥፍራ "ደረቅ ቦታ" ወይም "ሰዎች የማይኖሩበት ቦታ" አያገኝም "የሚያርፍበት ቦታ አያገኝም" እንዲህም ይላል "እርኩስ መንፈሱም እንዲህ ይላል" ቢመጣም ባዶ ሆኖ ተጠርጎና አጊጦ ያገኘዋል። ለተርጓሚዎች ምክር፡ "እርኩስ መንፈሱም ቤቱ ጸድቶ እና ሁሉ ነገር ተስተካክሎ ያገኘዋል" ( ተመልከት)
እናቱ የኢየሱስ እናት ወንድሞቹ ይህ እንዲህ ሊሆን ይችላል 1) የእናቱ እና የአባቱ ልጆች ወይም 2) የቅርብ ጓደኞቹ ወይም በእስራኤል ውስጥ ከእርሱ ጋር የሚቀራረቡ
ፍለጋውን "ፈለጉት"
እርሱ ለነገረው "ለኢየሱስ እናቱ እና ወንድሞቹ ልያናግሩት እንደሚፈለጉ ለነገረወ ሰው" እናቴ ማን ናት? ወንድሞቼስ እነማን ናቸው? ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እናቴ እና ወንድሞቼ እነማን እንደሆኑ በእርግጥ እነግራችኋለሁ" ( ተመልከት) ማንም "ማንም" አባት ይህ ለእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
1 በዚያ ቀን ኢየሱስ ከቤት ወጥቶ በባሕር ዳርቻ ተቀመጠ። 2 በጣም ብዙ ሕዝብ በዙሪያው ተሰበሰቡ፣ ስለዚህ ጀልባ ውስጥ ገብቶ ተቀመጠ፤ ሕዝቡም ሁሉ በባሕሩ ዳርቻ ቆመው ነበር። 3 ከዚያም ኢየሱስ በምሳሌ ብዙ ነገር ነገራቸው። እንዲህም አለ፤ "ዘሪ ለመዘራት ወጣ። 4 ሲዘራም፣ አንዳንዱ ዘር በመንገድ አጠገብ ወድቆ፣ ወፎች መጥተው በሉት። 5 ሌላውም ዘር በቂ አፈር በሌለበት በዐለታማ መሬት ላይ ወደቀ። አፈሩም ጥልቀት ስላልነበረው ወዲያው በቀለ። 6 ፀሐይ ሲወጣ ግን፣ሥር ስላልነበረው ጠውልጎ ደረቀ። 7 ሌላው ዘር ደግሞ በእሾኽማ ቊጥቋጦ መካከል ወደቀ፣ እሾኹም አድጎ አነቀው። 8 ሌላው ዘር በመልካም መሬት ላይ ወድቆ ፍሬ አፈራ፤ አንዳንዱ መቶ፣ አንዳንዱ ሥልሳ፣ አንዳንዱም ሠላሳ ፍሬ አፈራ። 9 ጆሮ ያለው ይሰማ።" 10 ደቀ መዛሙርቱም መጡና ኢየሱስን፣ “ለምንድን ነው ለሕዝቡ በምሳሌ የምትናገረው?" አሉት። 11 ኢየሱስም መልሶ፣ "ለእናንተ የመንግሥተ ሰማይን ምስጢር ማወቅ ተሰጥቷችኋል፣ ለእነርሱ ግን አልተሰጣቸውም" አላቸው። 12 ምክንያቱም ላለው ሁሉ የበለጠ ይሰጠዋል፤ ይበዛለትማል። የሌለው ግን ያለው እንኳ ይወሰድበታል። 13 ስለዚህ ለእነርሱ በምሳሌ እነግራቸዋለሁ፤ ምክንያቱም ቢያዩ እንኳ እያዩ አይደለም፣ ቢሰሙም እየሰሙ አይደለም፣ ወይም አያስተውሉም። 14 በእነርሱ ላይ እንዲህ የሚለው የኢሳይያስ ትንቢት ተፈጸመ ፦ መስማትን ትሰማላችሁ፣ ነገር ግን በምንም መንገድ አታስተውሉም፣ ማየትን ታያላችሁ፣ ግን ምንም አትገነዘቡትም። 15 በዐይናቸውም እንዳይመለከቱ፣ በጆሮአቸውም እንዳይሰሙ፣ በልባቸውም እንዳያስተውሉ ጆሯቸው ለመስማት ተደፍኗል፣ ዐይናቸውም ተጨፍኗል። እንዳይመለሱና እኔም እንዳልፈውሳቸው የዚህ ሕዝብ ልብ ደንድኗል። 16 የእናንተ ዐይኖች ግን ስለሚያዩ፣ ጆሮቻችሁም ስለሚሰሙ የተባረኩ ናቸው። 17 እውነት እላችኋለሁ፣ ብዙ ነቢያትና ጻድቃን የምታዩትን ለማየት ተመኝተው አላዩም፤ የምትሰሙትን ለመስማት ተመኝተው አልሰሙም። 18 እንግዲህ የዘሪውን ምሳሌ ስሙ። 19 ማንም የመንግሥትን ቃል ሰምቶ ባያስተውል፣ ክፉው ይመጣል በልቡም የተዘራውን ይነጥቃል። ይህም በመንገድ ዳር የተዘራውን ይመስላል። 20 በዐለት ላይ የተዘራው ፣ቃሉን የሚሰማና ወዲያውኑ በደሰታ የሚቀበለው ነው፤ 21 ሆኖም በራሱ ሥር ስለሌለው፣ የሚቆየው ለአጭር ጊዜ ነው። በቃሉ ምክንያት መከራ ወይም ስደት በሚነሣበት ጊዜ፣ ወዲያውኑ ይሰናከላል። 22 በእሾኽ ተክሎች መካከል የተዘራው፣ ቃሉን የሚሰማ ሆኖ የዓለም ዐሳብ፣ የብልጥግናም አሳሳችነት ቃሉን ያንቁታል፣ ፍሬ ቢስም ይሆናል። 23 በመልካም መሬት ላይ የተዘራው፣ ቃሉን የሚሰማና የሚረዳ ነው፤ በርግጥ የሚያድገውና ፍሬ የሚሰጠውም ይህኛው ነው፤ አንዱ መቶ፣ አንዱም ሥልሳ፣ አንዱም ሠላሣ እጥፍ ያፈራል። 24 ኢየሱስ ሌላ ምሳሌ ነገራቸው፤ እንዲህ አለ፤ “መንግሥተ ሰማይ በዕርሻው ላይ መልካም ዘር የዘራ ሰው ትመስላለች። 25 ሰዎቹ በተኙ ጊዜ ግን፣ ጠላቱ መጥቶ በስንዴው መካከል እንክርዳድ ዘርቶ ሄደ። 26 ቅጠሉም በለመለመና ፍሬ ማፍራት በጀመረ ጊዜ፣ እንክርዳዱ ደግሞ አለ። 27 የዕርሻው ባለቤት አገልጋዮች መጥተው፣ "ጌታ ሆይ፣ በዕርሻው ላይ መልካም ዘር ዘርተህ አልነበረምን? ታዲያ እንክርዳድ የበቀለው እንዴት ነው?"አሉት። 28 እርሱም፣ “ጠላት ይህን አደረገ" አላቸው። አገልጋዮቹም መልሰው፣"ስለዚህ ሄደን እንድንነቅለው ትፈልጋለህን?" አሉት። 29 የዕርሻውም ባለቤት፣ 'አይሆንም፣ እንክርዳዱን በምትነቅሉበት ጊዜ ስንዴውንም አብራችሁ ልትነቅሉት ትችላላችሁ 'አላቸው። 30 እስከ መከር ድረስ አብረው ይደጉ። በመከሩ ጊዜ ለኣጫጆቹ፣ "መጀመሪያ እንክርዳዱን ነቅላችሁ እንዲቃጠል አንድ ላይ ሰብስቡ። ስንዴውን ግን ሰብስባችሁ ወደ ጎተራዬ አስገቡት እላቸዋለሁ" አላቸው። 31 ኢየሱስም ሌላ ምሳሌ ነገራቸው። እንዲህም አለ፤ “መንግሥተ ሰማይ ሰው ወስዶ በዕርሻው ላይ የዘራትን የሰናፍጭ ዘር ትመስላለች። 32 በርግጥ ይህች ዘር ከሌሎች ዘሮች ሁሉ ታንሳለች። በምታድግበት ጊዜ ግን የሰማይ ወፎች በቅርንጫፎቿ እስኪሰፍሩባት ድረስ፣ ከሌሎች ዛፎች ትበልጣለች፡፡ 33 ከዚያም ኢየሱስ ሌላ ምሳሌ ነገራቸው፤ “መንግሥተ ሰማይ ሴት ወስዳ ኩፍ እስኪል ድረስ ከሦስት እጅ ዱቄት ጋር የደባለቀችውን እርሾ ትመስላለች።” 34 ኢየሱስም ለሕዝቡ እነዚህን ነገሮች ሁሉ በምሳሌ ተናገረ፣ ያለ ምሳሌም ምንም አልነገራቸውም። 35 ይህም ፦ "አፌን በምሳሌ እከፍታለሁ፣ ከዓለም መጀመሪያ ጀምሮ የተሰወረውን እገልጣለሁ" ተብሎ በነቢዩ የተነገረው እንዲፈጸም ነው። 36 ኢየሱስ ሕዝቡን ትቶ ወደ ቤት ገባ። ደቀ መዛሙርቱም ወደ እርሱ መጥተው "በዕርሻው የነበረውን የእንክርዳዱን ምሳሌ አስረዳን" አሉት። 37 ኢየሱስ መለሰ እንዲህም አለ፤ “መልካሙን ዘር የዘራው የሰው ልጅ ነው። 38 ዕርሻው ይህ ዓለም ነው፣ መልካሙ ዘር የመንግሥቱ ልጆች ናቸው። እንክርዳዱ የክፉው ልጆች ናቸው፤ 39 ዘሩን የዘራው ጠላት ዲያብሎስ ነው። መከሩ የዓለም መጨረሻ ሲሆን፣ አጫጆቹም መላእክት ናቸው። 40 ስለዚህ እንክርዳዱ ተሰብስቦ በእሳት እንደሚቃጠል፣ በዓለም መጨረሻም እንዲሁ ይሆናል። 41 የሰው ልጅ መላእክቱን ይልካል፣ ከመንግሥቱ ለኅጢአት ምክንያት የሆኑ ነገሮችን ሁሉና፣ ክፉ አድራጊዎችን ይሰበስቧቸዋል፣ 42 ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት፣ ወደ እቶን እሳትም ይጥሏቸዋል። 43 ከዚያም ፃድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ያበራሉ። ጆሮ ያለው ይስማ። 44 መንግሥተ ሰማይ በዕርሻ ውስጥ የተደበቀ ሀብት ትመስላለች፣ አንድ ሰውም አግኝቶ ደበቃት፤ ከደስታውም የተነሳ ያለውን ንብረት ሁሉ ሸጦ ያንን ዕርሻ ገዛው። 45 ደግሞም፣ መንግሥተ ሰማይ የከበሩ ዕንቈች የሚፈልግ ነጋዴን ትመስላለች። 46 በጣም ትልቅ ዋጋ ያለው ዕንቊ ባገኘ ጊዜ፣ ሄዶ ያለውን ንበረት ሁሉ ሸጠና ገዛው። 47 እንዲሁም፣መንግሥተ ሰማይ ወደ ባሕር የተጣለችና ሁሉም ዓይነት ፍጥረታት የሰበሰበች መረብን ትመስላለች። 48 መረቡዋ ስትሞላ፣ ዓሣ አጥማጆቹ ወደ ዳር አወጡት። ተቀምጠውም መልካም መልካሙን ሰብስበው በዕቃ አደረጉ፣ የማይጠቅመውን ግን አውጥተው ጣሉት። 49 በዓለም መጨረሻ እንዲሁ ይሆናል፣ መላእክት መጥተው ከጻድቃን መካከል ክፉዎችን ይለያሉ። 50 ከዚያም ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት፣ ወደሚነደው እቶን እሳት ይጥሏቸዋል። 51 ይህን ሁሉ ተረድታችኋል?" አላቸው። ደቀ መዛሙርቱም፣ “አዎን” አሉት። 52 ከዚያም ኢየሱስ፣ “ ስለዚህ የመንግሥተ ሰማይ ደቀ መዝሙር የሆነ ጸሐፊ ሁሉ፣ ከሀብቱ መካከል አሮጌውንና ዐዲሱን ያወጣ የቤት ጌታን ይመስላል አላቸው"። 53 ከዚያም ኢየሱስ እነዚህን ምሳሌዎች በጨረሰ ጊዜ፣ ከዚያ ስፍራ ሄደ። 54 ኢየሱስ ወደ ራሱ አገር መጥቶ፣ በምኲራቦቻቸው ሕዝቡን አስተማረ፣ ከዚህም የተነሣ ተገርመው፣ "ይህ ሰው ይህን ጥበቡንና እነዚህን ተአምራት ከየት አገኘ? 55 ይህ ሰው የአናጢው ልጅ አይደለምን? እናቱስ ማርያም አይደለችም ወይ? ያዕቆብ፣ ዮሴፍ፣ ስምዖንና ይሁዳስ ወንድሞቹ አይደሉም ወይ? 56 እኅቶቹስ ከእኛው ጋር አይደሉም ወይ? ታዲያ ይህ ሰው እነዚህን ነገሮች ሁሉ ከየት አገኛቸው?" አሉ። 57 በእርሱም ተሰናከሉበት። ኢየሱስ ግን፣ "ነቢይ ከገዛ አገሩና ከገዛ ቤተ ሰቡ በቀር መከበሩ አይቀርም" አላቸው። 58 በአለማናቸውም ምክንያት ፣በዚያ ብዙ ተአምራት አላደረገም።
በዚያ ቀን ይህ ነገር የፈጸመው ከዚህ በፊት ባለው ምዕራፍ ውስጥ የተገለጸው ታሪክ በተፈመበት ዕለት ነው፡፡ ከቤት ውጪ ኢየሱስ በማን ቤት ውስጥ በእንግድነት እንደተቀመጠ አልተገለጸም፡፡ ወደ ተንኳይቱ ገብቶ ይህ ምናልባትም ከእንጨት የተሠራ የዓሳ ማጥመጃ ጀልባ ሊሆን ይችላል፡፡
ኢየሱስ በምሳሌም ብዙ ነገራቸው "ኢየሱስ በምሳሌም ብዙ ነገራቸው " ለእነርሱ ለሕዝቡ to the people in the crowd እነሆ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "ተመልከቱ” ወይም “አድምጡ” ወይም “አሁን ለምነግራችሁ ነገር ትኩረት ስጡ” ዘሪ ሊዘራ ወጣ "አንድ ገበሬ በማሳው ላይ ዘርን ለመዝራት ወጣ" እርሱም ሲዘራ "ገበሬው ስዘራ ሳለ" መንገድ ዳር ከማሳው አጠገብ ባለ “መንገድ” ላይ፡፡ ብዙ ሰዎች በዚያ መንገድ ላይ ከመራመዳቸው የተነሳ መንገዱ ጠንክሯል፡፡ ለቀሟቸው "የተዘሩትን ዘሮች ለቀሟቸው" ዓለታማ መሬት በድንጋይ ላይ ብዙ አፈር ያሌለበት ወዲያው በቀለ "የተዘረዘው ዘር ወዲያው በቀለ” ጠወለገ "ፀሐይ በወጣ ጊዜ ግን ጠወለገ፤ በጣም ይሞቅ ነበር" ( ተመልከት) ደረቀ "ተክሉ ደረቀና ሞተ"
በእሾህ መካከል ወደቀ "የእሾህ ተክል ባለበት ሥፍራ ወደቀ" አነቀው "አዲሱን ተክል አነቀው፡፡" የተለመዱ አረሞች ሌሎች ተክሎች እንዳያድጉ የሚገልጽን ቃል ተጠቀሙ፡፡ ፍሬ ሰጠ "ፍሬ አፈራ" ወይም "ብዙ ፍሬ አፈራ” የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ። ለተርጓሚዎች ምክር፡ "ለመስማት ጆሮ ያላችሁ ስሙ" ጆሮ ያለው "ማስማት የሚችሉ ሁሉ” ወይም “የሚሰማኝ ሁሉ" ያድምጠኝ “በሚገባ ያድምጠኝ" ወይም "አሁን ለሚናገረው ነገር ትኩረት ይስጥ"
ለእነርሱ ለደቀ መዛሙርቱ ለእናንተ የመንግሥተ ሰማያትን ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቶአችኋል፥ ለእነርሱ ግን አልተሰጣቸውም። ይህ በቀጥታ በተዘዋዋሪ መንገድ የተሰጡ መረጃዎችን በማካተት እንዲህ ሊገለጽ ይችላል ፡ እግዚአብሔር የመንግስተ ሰማያትን ምስጢር መረዳት የሚትችሉበትን ዕድል ሰጥቶዋችኋ ይሁን እንጂ ይህ እድል ለሌሎች ሰዎች አልተሰጠም፡፡” ወይም እግዚአብሔር የመንግስተ ሰማያትን ምስጢር መረዳት እንዲትችሉ አድርጓል ይሁን እንጂ ለሌሎች ግን ይህ ችሎታ አልተሰጣቸውም፡፡” (en:ta:vol2:translate: and ተመልከት) አናንተ ደቀ መዛሙርት ምስጢር ለብዙ ጊዜ ተደብቆ የነበረው እውነት አሁን በኢየሱስ ተገጦዋል፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ምስጢር” ወይም “የተደበቀ እውነት”፡፡ ይህ የተሰጠው "ይህንን መረዳት የተሰጠው" ወይም "የማስተምረው ነገርን የተቀበለ ማንም ነው" ለእርሱ ተጨማሪ ይሰጠዋል ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊተረጎም ይችላል፡ “እግዚአብሐየር ተጨማሪ መረዳትን ይሰጠዋ፡፡” ( ተመልከት) ይህንን መረዳት ላለው "በግልጽ መረዳት ይችላል" ይህንን መረዳት ላሌለው "ይህንን መረዳት ላሌለው ሁሉ” ወይም "የማስተምረውን ነገር ያልተቀበለ ሰው ሁሉ" ያለው እንኳ ይወሰድበታል ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊተረጎም ይችላል፡ "ያለውን እንኳ እግዚአብሔር ይወስድበታል፡፡” ( ተመልከት)
እነግራቸዋለሁ በእነዚህ ሁለት ቁጥሮች ውስጥ “እነርሱ” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው ሕዝቡን ነው፡፡ ስለዚህ እያዩ ስለማያዩ እየሰሙም ስለማይሰሙ ስለማያስተውሉም በምሳሌ እነግራቸዋለሁ። ኢየሱስ ይህንን ትይዩዋዊ ንጽትር የጠጠቀመው ሕዝቡ ለመስማት አሻፈረኝ ማለቱን ለደቀ መዛሙርቱ ለመናገር ነው፡፡ ( ተመልከት) ማየትም ታያላችሁና አትመለከቱም። "ምንም እንኳ በዐይናቸው ቢመለከቱም አይረዱትም”፡፡ “መምለከት “ የሚለው ሁለተኛው ቃል ትርጉም መረዳት ነው፡፡ መስማት ትሰማላችሁና አታስተውሉም፥ የተሰማው ነገር ምን እንደሆነ በግልጽ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ምንም እንኳ ትምህርቱን ቢሰሙም እውነቱን ግን አይረዱተም፡፡” ( ተመልከት) መስማትን ትሰማላችሁ ነገር ግን አትረዱትም፤ ማየትን ታያላችሁ ነገር ግን አታስተውሉም ይህ ከነብዩ ኢሳያስ የተወሰደው በኢሳያስ ዘመን ይኖሩ ስለነበሩ የማያምኑ ሰዎች የተነገረው ክፍል የሚጀምርበት ነው፡፡ ኢየሱስ ይህንን ክፍል በመውሰድ እያዳመጡ ያሉት ሰዎችን ለመግለጽ ተጠቅሞበታል፡፡ ይህ ሌላኛው ትይዩዋዊ ንጽጽር ነው ( ተመልከት) መስማትን ትሰማላችሁ ነገር ግን በጭራሽ አታስተውሉም "ነገሮችን ተሰማላችሁ ነገር ግን አትረዷቸውም"፡፡ የተሰማው ነገር ምን እንደሆነ በግልጽ እንዲህ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ትምህርቱን ትሰማላችሁ ነገር ግን እውነቱን ግን አትረዱም” ( ተመልቱ) ማየትን ታያላችሁ ነገር ግን በጭራሽ አታስተውሉም "ነገሮችን ትመለከታላችሁ ነገር ግን አትረዷቸውም"
የዚህ ሕዝብ ልብ ደንድኖአልና "ይህ ሕዝብ ከእንግዲህ በኋላ አይማርም" ለመስማት አስቸጋሪዎች ሆነዋል "ለመስማት ምንም ፍላጎት የላቸውም" ዐይኖቻቸውን ጨፍነዋል "ለመስማት አሻፈረኝ ብለዋል" በዓይናቸው እንዳያዩ፥ ወይም በጆሮአቸውም እንዳይሰሙ፥ ወይም በልባቸውም እንዳያስተውሉ፥ እንዳይመሰሉ "በዐይኖቻው እንዳያዩ፣ በጆሮአቸውም እንዳይሰሙ፣ በልባቸውም እንዳያስተውሉ እና በዚህም ምክንያት እንዳይመለሱ" እንዳይመለሱ “ወደኋላ እንዳይመሰሉ” ወይም "ንሰሓ እንዳይገቡ” እንድፈውሳቸው "እኔ እንዳድናቸው" ለተርጓሚዎች ምክር፤ "እንደገና እንድቀበላቸው" ( ተመልከት)
እናንተ . . . እናንተ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርት እየተናገር ነው፡፡ እናንተ ስለሚታዩ "ማየት ስለሚችሉ” ወይም “እናንተ ማየት ስለሚችሉ" እናንተ ስለሙትሰሙ "እናንተ መስማት ስለሚትችሉ” ወይም “እናንተ መስማት ስለሚትችሉ” ያያችሁትን ነገር "ሳደረግ ያያችሁኝን ነገሮች" የሰማችሁኝ ነገሮች "ስናገር የሰማችሁኝን ነገሮች
ክፉው ይመጣል፥ በልቡ የተዘራውንም ይነጥቃል፤ "ሴጣን የሰማውን የእግዚአብሔርን ቃል እንዲረሣ ያደርገዋል” ይነጥቃል የአንድ ሰውን ንብረት በጉልበት መቀማትን ለመግለጥ የሚያገለግል ቃልን ተጠቀሙ፡፡ በልቡ የተዘራውንም ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊተረጎም ይችላል፡ “የእግዚአብሔር ቃል በልብቡ ውስጥ ተዘርቷል” ( ተመልከት) በልቡም ውስጥ በአድማጩ ልብ ውስጥ በመንገድ ዳር የተዘራው ይህ ነው። የቁም ትርጉሙ ምንም ትርጉም የማይሰጥ ከሆነ አንባቢዎቹ ዘሪው ኢየሱስ፣ ዘሩ መልዕክቱ እና በመንገድ ዳር ያለው አፈር ደግሞ አድማጮቹ መሆናቸው መረዳት በሚችሉበት መንገድ ለመተርጎም ጥረት አድርጉ ( and ተመልከት) በመንገድ ዳር "መንገድ” ወይም "መተላለፊያ" ይህንን በ MAT 13:4 ላይ በተረጎማችሁት መንገድ ተርጉሙት፡፡
በጭንጫ ላይ የተዘራውም የቁም ትርጉሙ ምንም ትርጉም የማይሰጥ ከሆነ አንባቢዎቹ ዘሪው ኢየሱስ፣ ዘሩ መልዕክቱ እና በመንገድ ዳር ያለው አፈር ደግሞ አድማጮቹ መሆናቸው መረዳት በሚችሉበት መንገድ ለመተርጎም ጥረት አድርጉ ( and ተመልከት) ሥር የለውም "ረጅም ሥር የለውም” ወይም “አዲሱ ተክል ለሥሩ የሚሆን ሥፍራን አያገኝም”( እና ተመልከት) ከቃሉ የተነሣ "ከመልዕክቱ የተነሣ" ወዲያውኑ ይሰናከላል "ወዲያውኑ ወድቃል" ወይም "ወዲያውኑ እምነቱን ይተዋል" ( ተመልከት)
በእሾህ መካከል የተዘራው . . . በመልካም መሬት የተዘራው የቁም ትርጉሙ ምንም ትርጉም የማይሰጥ ከሆነ አንባቢዎቹ ዘሪው ኢየሱስ፣ ዘሩ መልዕክቱ እና እሾሃማ መሬት ደግሞ አድማጮቹ መሆናቸው መረዳት በሚችሉበት መንገድ ለመተርጎም ጥረት አድርጉ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “በእሾህ መካከል የተዘረው ዘር እንዲህ ሆነ . . . በመልካም መሬት ላይ የተዘራው ዘር እንዲህ ሆነ ( እና ተመልከት) ቃል "መልዕክት" የዚህም ዓለም አሳብና የባለጠግነት መታለል ቃሉን ያንቃል፥ የማያፈራም ይሆናል። ለተርጓሚዎች ምክር፡ "አረሞች መልካም ተክል እንዳያድግ እንደሚያደርጉት ሁሉ የዓለም አሳብና የባለጠግነት መታለልም ይህ ሰው ፍሬያማ እንዳይሆን ያደርጉታል ( ተመልከት) የዓለም አሳብ "በዚህ ዓለም ውስጥ ያሉና ሰዎችን የሚያሳስቡ ነገሮች" ፍሬያማ እንዳይሆኑ ያደርጋል "ውጤታማ እንዳይሆኑ ያደርጋል" ይህ በእውነት ፍሬ የሚያፈራ ነውና ተንከባከቡት "እነዚህ ፈፍሬ የሚያፈሩ እና ውጤታማ የሚሆኑት ናቸው" ወይም "መልካም ፍሬን እንደሚያፈሩት ጤናማ አትክልቶች እነዚህ ሰዎች ውጤታማ ናቸው" ( እና ተመልከት)
ኢየሱስ ሌላ ምሳሌ ነገራቸው ኢየሱስ ለሕዝቡ ሌላ ምሳሌ ነገራው፡፡ ( ተመልከት) መንግስተ ሰማይት . . . ሰው ትመስላለች ትርጉም መነንግስተ ሰማይን ከሰውዬው ጋር እኩል ማድረግ የለበትም ይልቁንም መንግስተ ሰማያት በምሳሌ ውስጥ ከተገለጸው ሁኔታ ጋር ይመሳሰላል፡፡ *ተመልከት: መልካም ዘር "መልካም ዘሮች" ወይም "መልካም የሰብል ዘሮች”፡፡ ኢየሱስን የሚያደምጡት ሰዎች ኢየሱስ ስለ ስንዴት እየተናገረ እንደሆነ ተገንዝበዋል፡፡ ( ተመልከት) ጠላቱ መጥቶ "ጠላቱ ወደ ማሳው መጥቶ" አረሞች እነዚህ አረሞች ገና በለጋነታቸው የምግብ አትክሎቶችን የሚመስል ቢሆንም ፍሬያቸው ግን መርዛማ ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “መጥፎ ዘሮች” ወይም “የአረም ፍሬዎች” (UDB) ስንዴው በበቀለ ጊዜ "የስንዴው ዘር በበቀለ ጊዜ” ወይም “ፍሬው በበቀለ ጊዜ” ፍሬያቸውን ባፈሩ ጊዜ "ፍሬያቸውን ስያፈሩ" ወይም "የስንዴ ፍሬ ባፈራ ጊዜ" አረሞችም አብረው በቀሉ ለተርጓማች ምክር፡ "ከዚያም ሰዎች በማሳው ውስጥ አረሞችም መኖራቸውን ተመለከቱ"
የእርሻው ባለቤት ይህ በእርሻ ማሳው ላይ መልካም ዘርን ከዘራው ሰው ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ መልካምን ዘር በእርሻህ ዘርተህ አልነበርህምን? "መልካም ዘርን በእርሻህ ዘርተህ ነበር”፡፡ የመሬቱ ባለቤት ባሮቹ እንዲዘሩ አድርጋቸው ይሆናል፡፡ ( እና ተመልከት) አንዲህም አላቸው "የመሬቱ ባለቤት ለሎሌዎቹ እንዲህ አላቸው" እኛ . . . ትፈልጋለህን “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሎሌዎቹን ነው፡፡
የመሬቱ ባለቤት እንዲህ አለ "የመሬቱ ባለቤት ለሎሌዎቹ እንዲህ አለ" አጫጆችን፦ “እንክርዳዱን አስቀድማችሁ ልቀሙ በእሳትም ለማቃጠል በየነዶው እሰሩ፥ ስንዴውን ግን በጎተራዬ ክተቱ” እላለሁ አለ። ይህንን በትምህርተ ጥቅስ ውስጥ ሳትከቱ መተርጎም ትችላላችሁ፡ “ለአጫጆቹ እንዲህ እላቸዋለሁ፤ በመጀመሪያ በእሳት እዲቃጠል እንክርዳዱን ሰብሰቡና በአንድ ላይ እሰሩ ከዚያም ስዴውን ሰብስባችሁ ወደ ጎተራዬ አስገቡ ( ተመልከት) ጎተራዬ ጎተራ በእርሻ ቦታ የሚሠራ የሰብል ምርት ማከማቻ ነው፡፡
ኢየሱስ እንዲህ ሲል ሌላ ምሳሌ አቀረበላቸው "ኢየሱስ ለሕዝቡ ሌላ ምሳሌ ነገራቸው" ( ተመልከት) መንግስተ ሰማያት . . . ትመስላለች ይህንን በ MAT 13:24 ላይ እንዴት እንደተረጎምህ ተመልከት፡፡ የሰናፍጭ ፍሬ ትልቅ ዛፍ የሚትሆን በጣም ትን ሽ ዘር ( ተመልከት) ይህ ዘር ከሌሎች ዘሮች ሁሉ ይልቅ በጣም ትንሽ ናት የምሳሌው የመጀመሪያ አድማጮች ከሚያውቋቸው ዘሮ መካከል በጣም ትንሸዋ የሰናፍጭ ፍሬ ናት ( ተመልከት) ይሁን እንጂ ካደገች በኋላ "ይሁን እንጂ ተክሏ ካደገች በኋላ" ዛፍ ይሆናል "በጣም ትልቅ ዛፍ ይሆናል" ( እና እና ተመልከት) የሰማይ ወፎች "ወፎች" ( ተመልከት)
ከዚያም ኢየሱስ ሌላ ምሳሌ ነገራቸው "ከዚያም ኢየሱስ ለሕዝቡ ሌላ ምሳሌ ነገራቸው" ( ተመልከት) መንግስተ ሰማየት . . . ትመስላለች በ MAT 13:24 ላይ እንዴት እንደተረጎምህ ተመልከት፡፡ መንግስቱ እንደ እርሾ አይደለም ይሆኑ እንጂ የመንግስቱ መስፋፋት እንደ እርሾ ነው ተመልከት) ሦስት መሥፈሪያ ዱቄት "ብዙ ዱቄት" ወይም በባሕላችሁ ውስጥ ብዙ መጠን ያለው የዱቄት መሥፈሪያን መጠቀም ትችላላችሁ፡፡ እስኪቦካ ድረስ እስኪቦካ ድረስ፡፡ በዚህ ሥፍራ በተዘዋዋር የተሰጠው መረጃ ዳቦ ለመጋገር በሦስት መሥፈሪያ ዱቄቱ ላይ እርሾ ተጨምሮ መቦካቱ ነው፡፡ ( ተመልከት)
ኢየሱስም ለሕዝቡ ይህን ሁሉ በምሳሌ ተናገረ፤ ያለ ምሳሌ አልተናገራቸውም። ቅደም ተከተሉ “ተናገረ . . . በምሳሌዎች . . . በምሳሌዎች . . . ተናገረ”፡፡ ይህንን ቅደም ተከተል የተከተለው በምሳሌ እንደተናገራቸው አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ ( ተመልከት) እነዚህን ሁሉ ነገሮች ይህ ኢየሱስ በ MAT 13:1 መጀመሪያ ላይ ያስተማረውን ያመለክታል፡፡ ያለ ምሳሌ ምንም አልተናገራቸውም "ከምሳሌ ውጪ ምንም አልነገራቸውም" ለተርጓሚዎች መክር፡ "የነገራውን ሁሉ በምሳሌ ነገራቸው" ( እና ተመልከት) በነቢዩምየተባለው ይፈጸም ዘንድ፣ እኔ ስናገር ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ልገለጽ ይችላል፡ “ከብዙ ዘመናት በፊት እግዚአብሔር ለአንድ ነቢይ እንዲጽፍ ያደረገው ነገር እውን እንዲሆን አደረገ” (UDB). ( ተመልከት) የተሰወረ ነገር ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ልገለጽ ይችላል፡ “ለብዙ ጊዜያት ተሰውሮ የነበረው ነገር" ( ተመልከት) ዓለም ከተፈጠረ ጊዜ ጀምሮ "ከፍጠትረታት ጅማሬ አንስቶ" ወይም "እግዚብሔር ዓለምን ከፈጠረበት ጊዜ አንስቶ"
ወደ ቤት ገባ "ወደ ቤት ውስጥ ገባ" ወይም "ወደሚያርፍበት ቤት ገባ" ዘር የዘራው "ዘሪው" የሰው ልጅ በዚህ ሥፍራ ኢየሱስ ራስን እያመለከተ ነው፡፡ የመንግስቱ ልጆች "የመንግስቱ አካል የሆኑ ሰዎች” የክፉ ልጆች "የክፉ የሆኑት ሰዎች" ጠላት የዘራቸው እንክርዳዱን የዘረው ጠላት የዓለም መጨረሻ "የዘመን መጨረሻ"
ስለዚህ እንክርዳዱ ተሰብስቦ እንዲቃጠል ሲደረግ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ በቀጥታ ሊተረጎም ይችላል፡ “ስለዚህም ሰዎቹ እንክርዳዱን ሰብስበው ስያቃጥሉ" ( ተመልከት) የዓለም መጨረሻ "የዘመን መጨረሻ" የሰው ልጅ መላእክቱን ይልካል በዚህ ሥፍራ ኢየሱስ ስለ ራሱ እየተናገረ ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እኔ፣ የሰው ልጅ መላእክት እልካቸዋለሁ”፡፡ ዓመፃን የሚያደርጉት "ክፋትን የሚያደርጉ" ወይም "ክፉ ሰዎች" እቶን እሳት ለተርጓሚዎች ምክር፡ "እቶን እሳት”፡፡ “ማቃጠያ ሥፍራ” የሚለው ቃል በእናንተ አከባቢ የማይታወቅ ከሆነ “እሳት ማንደጃ ሥፍራ” የሚለውን ቃል መውሰድ ይቻላል፡፡ እንደ ጸሐይ ይበራል "ልክ እንደ ፀሐይ የሚትታዩ ሁኑ” ( ተመልከት) የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ። ለተርጓሚዎች ምክር: "ጆሮ ያለው ይስማ” ወይም “ጆሮዎች ያሉት እንገግዲህ ያድምጥ"፡፡
መንግስተ ሰማያት . . . ትመስላለች በ MAT 13:24 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ (ተመልከት) በእርሻ ውስጥ የተሰወረን መዝገብ ትመስላለች መዝገብ በጣም ጠቃ፣ እና ውድ የሆኑ ነገሮች ስብስብ ነው፡፡ ይህ እንዲህ ባለ መንገድ ሊተረጎም ይችላል፡ “የሆነ ሰው በእርሻ ውስጥ የደበቀው መዝገብ” ( እና ተመልከት) ደበቀው "covered it up" ያለውን ሁሉ ሸጠና ያን እርሻ ገዛ በዚህ ሥፍራ ላይ በተዘዋዋሪ መንገድ የተገለጸው መረጃ የተሰወረ መዝገብ በውስጡ የያዘው የእርሻ ቦት ሰውዬው መግዛቱ ነው፡፡ (ተመልከት ነጋዴ ነጋዴ የተለያዩ ነገሮችን የሚሸጥ፣ ብዙ ጊዜም የሚሸጡ ነገሮችን ከሩቅ ሥፍራ የሚያመጣ ነው፡፡ መልካምን ዕንቁ የሚሻ ነጋዴን ትመስላለች፤ በዚህ ሥፍራ ላይ በተዘዋዋር መንድ የተገለጸው መረጃ መሠረት ይህ ሰው መልካም ዕንቁን ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ውድ ዕንቁ “ዕንቁ” ለስላሳ፣ ጠንካራ፣ የሚያንጸባርቅ፣ ነጭ ወይም ቀለል ያለ ቀለም ያለው ከውሃ ውስጥ የሚገኝ እና ውድ የሆኑ ጌጣ ጌጦችን ለማዘጋጀት የሚውል ውስድ ነገር ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “መልካም ዕንቆዎች” ወይም “የሚያምሩ ዕንቁዎች”፡፡
መንግስተ ሰማያት . . . ትመስላለች በ MAT 13:24 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ የእግዚአብሔር መንግስት እንደ መረብ አይደለችም ይሁን እንጂ መንግስተ ሰማያት ልክ መረብ የተለያዩ ዓሳዎችን እንደሚይዝ እንዲሁ መንግስተ ሰማይም ሁሉንም ዓይነት ሰዎችን ወደራሱ ይሰበስባል፡፡ ( ተመልከት) ወደ ባሕር እንደሚጣል መረብ ይህ በዚህ ዓይነት መንገድ ሊተረጎም ይችላል፡ “አንዳንድ ዓሳ አጥማጆች ዓሳ ለማጥመድ ወደ ባሕር ውስጥ እንደሚጥሉት መረብ፡፡” ( ተመልከት) ወደ ባሕር ውስጥ የሚጣል ባሕር "ወደ ባሕር ውስጥ የሚጣል መረብ" ሁሉንም ዓይነት ፍጥረታትን እንደሚሰበስብ "ሁሉንም ዓይነት ዓሳዎች እንደሚይዝ" ወደ ወደቡ አወጦአት "መረቡን ወደ ባሕሩ ዳርቻ አወጡት” ወይም “መረቡን ወደ ባሕሩ ዳርቻ ጎትተው አወጡት" መልካም የሆኑ ነገሮችን "ጥሩ ጥሩውን ነገር" ጥቅም ያሌለውን "መጥፎዎቹን ዓሳዎች" ወይም "የማይበሉ የዓሳ ዓይነቶችን ግን" አውጥተው ይጥሉአቸዋል "አያስቀምጡትም"
ማቴዎስ 13፡49-50
የዓለም መጨረሻ "የዘመን መጨረሻ" መጣ "ከሌላ ቦታ የመጣ" ወይም "የሚሄድ" ወይም "ከሰማይ የመጣ" ወረወራቸው "ክፉዎቹን ወረወራቸው" ቆሻሻ ማቃጠያ እሳት ይህ የገሃነም እሳት ምሳሌ ነው፡፡ “ቆሻሻ ማቃጠያ” የሚለው የማይታወቅ ከሆነ “ማቃጠያ” የሚል ቃል ልንጠቀም እንችላለን፡፡ ለተርጓማች ምክር፡ "የማቃጠያ ሥፍራ" ( ተመልከት) በዚያ ለቅሶ እና የጥርስ ማፋጨት ይሆናል "ክፉዎች የሚያለቅሱበት እና ጥርሳቸውን የሚያፋጩበት ሥፍራ"
ማቴዎስ 13፡51-53
ይህን ሁሉ አስተዋላችሁን? ደቀ መዛሙርቱ “አዎን” አሉት፡፡ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ይህን በቀጥታ በመጥቀስ ሳይጠቀስ ማስቀመጥ ይቻላል፡፡ “ይህንን ሁሉ በደንብ መረዳታቸውን ኢየሱስ ጠየቃቸው፣ እነርሱን አዎን ተረድተነዋል ( ተመልከት) ደቀ መዝሙር የሆነ "ስለሆነ ነገር ተማረ" መዝገብ መዝገብ በጣም ውድ እና ዋጋ ያላቸው ነገሮች ስብስብ ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ እነዚህ ነገሮች የተከማቹበት ሥፍራን፣ “መጋዝን” ማለት ነው፡:
ወደ ገዛ አገሩ "የእርሱ ሀገር" ወደ ምኩራቦች በዚህ ሥፍራ ላይ “የእነርሱ” የተጠቀሰው ተውላጠ ስም በዚያ አከባቢ ያሉ ሰዎችን ያመለክታል፡፡ በጣም ተገረሙ "ተደነቁ" በእነዚህ ተዓምራቶች "እነዚህን ተዓምራት ያደረገበትን ኃይል ከዬት አገኘ” ( ተመልከት) የአናጥዉ ስም አናጢ ከእንጨት ወይም ከድንጋይ የተለያዩ ነገሮችን የሚያበጅ ሰው ነው፡፡ “አናጢ” የሚለው ቃል በእናንተ ዘንድ የማይታወቅ ከሆነ “ግንበኛ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡
ተሰናከሉበት "ኢየሱስ በሚኖርበት መንደር ውስጥ የሚኖሩት ሰዎች በእርሱ ተሰናከሉበት” ወይም “. . . እርሱን አይቀበሉትም” ነብይ አይከበርም "ነብይ በሁሉም ሥፍራ ይከበራል" “ነብይ ክብርን በሁሉም ሥፍራ ያገኛል” ወይ “በሁሉም ሥፍራ ያሉ ሰዎች ነብያትን ያከብራሉ” ( ተመልከት) በገዛ ሀገሩ "በአከባቢው" ወይም "በመንደሩ" የገዛ ቤተሰቦቹ "በራሱ ቤት" በዚያም ብዙ ተዓምራትን አላደረገም “ኢየሱስ በገዛ ሀገሩ ብዙ ተዓምራትን አላደረገም”፡፡
1 በዚያን ጊዜ፣ የአራተኛው ክፍል ገዢ የነበረው ሄሮድስ ስለ ኢየሱስ ሰማ። 2 አገልጋዮቹንም፣ "ይህ መጥምቁ ዮሐንስ ነው። ስለዚህ ይህ ሁሉ ኅይል በእርሱ የሚሠራው ከሞት ስለ ተነሣ ነው" አላቸው። 3 ሄሮድስ፣ በወንድሙ በፊልጶስ ሚስት በሄሮድያዳ ምክንያት፣ ይዞ አሳስሮት ነበርና፡፡ 4 ምክንያቱም ዮሐንስ፣ "እርሷን ማግባትህ ተገቢ አይደለም" ይለው ነበር። 5 ሄሮድስ ሊያስገድለው ፈልጎ፣ ሕዝቡን ፈራ፣ ምክንያቱም ሕዝቡ ዮሐንስን እንደ ነቢይ ያዩት ነበር። 6 ነገር ግን በሄሮድስ የልደት ቀን፣ የሄሮድያዳ ልጅ በመካከል ስትጨፍር፣ ሄሮድስን ደስ አሰኘችው። 7 በዚህም ምክንያት፣ የምትጠይቀውን ሁሉ እንደሚሰጣት በመሓላ ቃል ገባላት። 8 በእናቷም ተመክራ፣ “የመጥምቁ ዮሐንስን ራስ እዚሁ፣ በሳሕን አድርገህ ስጠኝ” አለችው። 9 ንጉሡ በጥያቄዋ በጣም ዐዘነ፣ ነገር ግን በመሓላውና ከእርሱ ጋር እራት ላይ በነበሩት ምክንያት፣ የተናገረው እንዲፈጸም አዘዘ። 10 ሰው ልኮ፣ በወህኒ ቤት የዮሐንስን ራስ አስቈረጠ። 11 ከዚያም ራሱ በሳሕን ተደርጎ ለልጅቱ ተሰጣት፣ እርሷም ለእናቷ ወስዳ ሰጠች። 12 ከዚያም የእርሱ ደቀ መዛሙርት መጥተው፣ በድኑን ወስደው ቀበሩት። ከዚህ በኋላ ሄደው ለኢየሱስ ነገሩት። 13 ኢየሱስም ይህን በሰማ ጊዜ፣ በጀልባ ገለል ወዳለ ቦታ ሄደ። ሕዝቡም ይህን በሰሙ ጊዜ ፣ ከየከተሞቹ በእግር ተከተሉት። 14 ከዚያም ኢየሱስ ቀድሞአቸው መጥቶ ብዙ ሕዝብ አየና ራራላቸው፣ ሕመምተኞቻቸውንም ፈወሰ። 15 በመሸም ጊዜ፣ ደቀ መዛሙርቱ መጡና፣ “ቀኑ መሽቷል ይህም ስፍራ ምድረ በዳ ነው ። ሕዝቡን ወደ መንደሮች እንዲሄዱና፣ ለራሳቸው ምግብ እንዲገዙ አሰናብት" አሉት። 16 ኢየሱስ ግን፣ "መሄድ አያስፈልጋቸውም፤ እናንተው የሚበሉትን ስጧቸው" አላቸው። 17 እነርሱም፣ “ እኛ ያለን አምስት እንጀራና ሁለት ዐሣ ብቻ ነው" አሉት። 18 ኢየሱስም፣ "እነርሱኑ ወደ እኔ አምጡአቸው" አለ። 19 ከዚያም ኢየሱስ ሣሩ ላይ እንዲቀምጡ ሕዝቡን አዘዘ። ዐምስቱን እንጀራና ሁለቱን ዐሣ ወሰደ፣ ወደ ሰማይ አሻቅቦ እያየ፣ አመሰገነ፤ እንጀራውንም ቈርሶ፣ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው፤ ደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ ሰጡ። 20 ሁሉም በልተው ጠገቡ፡፡ ከዚያም የተረፈውን ዐሥራ ሁለት መሶብ ሙሉ ቊርስራሽ ሰበሰቡ። 21 የበሉትም፣ ከሴቶችና ከልጆች ሌላ፣ ዐምስት ሺ ያህል ወንዶች ነበሩ። 22 እርሱም ሕዝቡን እያሰናበተ እያለ፣ ደቀ መዛሙርቱን ወዲያው ወደ ጀልባ ገብተው፣ ከእርሱ በፊት ወደ ማዶ እንዲሄዱ አዘዛቸው። 23 ሕዝቡን ካሰናበተ በኋላ፣ ብቻውን ለመጸለይ ወደ ተራራ ወጣ። በመሸ ጊዜ፣ በዚያ እርሱ ብቻውን ነበር። 24 ጀልባዋ በባሕሩ መካከል እያለች፤ ከተቃራኒ አቅጣጫ ይነፍስ ስለ ነበር፣ በማዕበሉ ክፉኛ ትንገላታ ነበር። 25 ከምሽቱ በአራተኛው ክፍል፣ ኢየሱስ በባሕሩ ላይ እየተራመደ ወደ እነርሱ እየመጣ ነበር። 26 ደቀ መዛሙርቱም በባሕር ላይ እየተራመደ ሲያዩት፣ እጅግ ደንግጠው፣ “መንፈስ ነው”ብለው በፍርሀት ጮኹ። 27 ኢየሱስ ግን ወዲያውኑ፣ “አይዟችሁ! እኔ ነኝ! አትፍሩ” ብሎ ተናገራቸው። 28 ጴጥሮስም መልሶ፣ “ጌታ ሆይ፣ አንተስ ከሆንህ፣ በውሃው ላይ ወደ አንተ እንድመጣ እዘዘኝ" አለው። 29 ኢየሱስም፣ “ና" አለው። ስለዚህ ጴጥሮስ ከጀልባው ወጥቶ ወደ ኢየሱስ ለመሄድ፣ በውሃው ላይ ተራመደ። 30 ነገር ግን ጴጥሮስ ነፋሱን አይቶ በመፍራት፣ መስጠም በጀመረ ጊዜ ፣ “ጌታ ሆይ፣ አድነኝ” ብሎ ጮኸ። 31 ኢየሱስም ያኔውኑ እጁን ዘርግቶ ጴጥሮስን ያዘውና፣ “አንተ እምነት የጎደለህ፣ ለምን ትጠራጠራለህ?” አለው። 32 ከዚያም ኢየሱስና ጴጥሮስ ወደ ጀልባው በገቡ ጊዜ፣ ነፋሱ መንፈሱን አቆመ። 33 በጀልባው ውስጥ የነበሩት ደቀ መዛሙርትም ኢየሱስን፣ “አንተ በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነህ” ብለው ሰገዱለት። 34 ከተሻገሩም በኋላ፣ ጌንሳሬጥ ወደ ተባለ አገር መጡ። 35 በዚያም ስፍራ የነበሩ ሰዎች ኢየሱስ መሆኑን ባወቁ ጊዜ፣ በአካባቢው ወዳለ ስፍራ ሁሉ መልእክት ላኩና፣ የታመመውን ሁሉ ወደ እርሱ አመጡ። 36 የልብሱን ጫፍ ብቻ ለመንካት ለመኑት፣ የነኩትም ሁሉ ተፈወሱ።
በዚያ ጊዜ "በዚያ ዘመን" ወይም “ኢየሱስ በገሊላ እያገለገለ ሳለ" የአራተኛው ክፍል ገዥ የሆነው ሄሮዶስ ሄሮድ አንቲፓስ የእስራኤልን አንድ አረተኛ ግዛት ይገዛ ነበር ( ተመልከት) ስለኢየሱስ ዝና ሰማ "ሰዎች ስኢየሱስ የሚሉትን ሰማ" ወይም "ስለ ኢየሱስ ዝና ሰማ" እንዲህም አለ "ሄሮዶስ እንዲህ አለ"
ሄሮዶስ ዮሐንስን አስይዞ አሳስሮት በወህኒ አኑሮት ነበር ይህ የሚሆነው ሄሮዶስ ሌሎች ሰዎችን በእርሱ ፈንታ ሄደው ዮሐንስን እንዲይዙት በማዘዝ ነው ( ተመልከት) ሄሮዶስ ዮሐንስን አስያዘው "ሄሮዶስ ዮሐንስ እንድታሠሰር አደረገ" ዮሐንስ፦ እርስዋ ለአንተ ትሆን ዘንድ አልተፈቀደም ይለው ነበርና። “እርሷን ምስትህ አድርገህ መውሰድ ለአንድ አልተፈቀደም ስላለው ነው ( ተመልከት) ዮሐንስ ስላለው ነው "ዮሐንስ ይህንን ደጋግሞ ለሄሮዶስ ይለው ነበር" በሕግ አክተፈቀደም ሄሮዶስ ሄሮዲያስን ስያገባ ፊልፕ በሕይወት ነበር፡፡
በዚህ መካከል የልደት ክብረ በዓል ለማክበር የመጡ እንግዶች መካከል ( ተመልከት)
የእናቷን ምክር ተከትላ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እናትየው ከመከረቻት በኋላ" ( ተመልከት) ተምክራ "መመሪያ መሠረት" እንዲህ አለች “እርሷ” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው የሄሮዲስን ሴት ልጅ ነው፡፡ ሳህን ትልቅ ሳህን ንጉሡ በጥያቄዋ እጅግ በጣም ተበሳጨ "ጥያቄዋ ንጉሡን አበሳጨው" ( ተመልከት) ንጉሥ የአራረተኛ ክፍል ገዥው ሄሮዶስ አንቲፓስ (MAT 14:1).
ጭንቅላቱን በሳህን አድርገው ለልጅቷ ሰጧት "የሆነ ሰው ጭንቅላቱን በሳህን አድርጎ ለልጅቷ ሰጣት" ( ተመልከት) ሳህን ትልቅ ሳህን ሴት ልጅ ያላገባች ልጅን የሚያመለክት ቃልን ተጠቀም፡፡ ደቀ መዛሙርቱ "የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት" ሬሳውን "በድኑን" ወደ ኢየሱስ ሄደው ነገሩት "የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ ኢየሱስ ዘንድ ሄደው መጥመቁ ዮሐንስ ላይ ምን እንዳደረጉበት ለኢየሱስ ነገሩት ( ተመልከት
ይህንን ስሰማ "በዮሐንስ ላይ የሆነውን ነገር ስሰማ" ወይም "ስለ ዮሐንስ የተነገረውን ነገር ስሰማ” ( ተመልከት) ፈቀቅ አለ ከሕዝቡ ተለይቶ ሄደ ከዚያ "ከዚያ ሥፍራ" ሕዝቡን ይህንን ስሰሙ “ሕዝቡን ወዴት እንደሄደ በሰሙ ጊዜ” ወይም “እንደሄደ ሕዝቡ በሰሙ ጊዜ” ሕዝቡ "ሕዝቡ" ወይም “የተሰበሰበው ሕዝብ” ኢየሱስ ወደ እነርሱ መጥቶ የተሰበሰበውን ብዙ ሕዝብ ተመለከተ "ኢየሱስ ወደ ባሕሩ ዳርጃ በመጣ ጊዜ ብዙ ሕዝብ ተሰብስቦ ተመለከተ”
ደቀ መዛሙርቱም ወደ እርሱ መጥተው "የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ መጥተው"
አያስፈልጋቸውም "ሕዝቡ . . . አያስፈልጋቸውም" እናንተ ስጧቸው “አናንተ” የሚለው ቃል የብዙ ቁጥር አመልካች ሲሆን የሚያመለክተውም ደቀ መዛሙርቱን ነው፡፡ (en:ta:vol1:translate: ተመልከት) እነርሱም እንዲህ አሉት "ደቀ መዛርቱ ለኢየሱስ እንዲህ አሉት" አምስት ዳቦ እና ሁለት ዓሣ "5 ዳቦዎች እና 2 ዓሣዎች ( ተመልከት) እነርሱን ወደ እኔ አምጧቸው "ዳቦዎቹን እና ዓሣዎቹን ወደ እኔ አምጧቸው"
ተቀመጡ ወይም “ይረፉ”፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ በእናንተ ባሕል ውስጥ ሰዎች ምግብ ለመመገብ የሚቀመጡበትን መንገድ የሚገልጽ ቃልን ተጠቀሙ፡፡ ወሰደ "በእጆቹ ይዞ፡፡" ሰርቋቸው አይደለም፡፡ (en:ta:vol1:translate: ተመልከት) ዳቦዎች "ዳቦዎች” ወይም “ያላቸውን ሁሉ ዳቦ" ወደ ሰማይ ተመለከተ ይህ ማለት 1) “ወደላይ እየተመለከተ” ወይም 2) “ወደላይ ከተመለከተ በኋላ”፡፡ እነርሱም ወደ ላይ ተመለከቱ "ደቀ መዛሙርቱም ደወ እርሱ ተሰበሰቡ " የበሉትም ሰዎች ዳቦውን እና ዓሣውን የበሉት ሰዎች" ( ተመልከት)
ወዲያውም "ኢየሱስ አምስት ሺህ ሰዎችን ከመገበ በኋላ" በመሸም ጊዜ "ወደ ምሽት ላይ” ወይም “በጨለመ ጊዜ”" ከማዕበሉ የተነሳ ልቆጣጠሯት አልቻሉም "ማዕበሉ ታንኳይቱን ያናውጣት ነበር"
በባሕሩ ላይ እየተራመደ "በውሃው ላይ እየተራመደ" በጣም ፈሩ "ደቀ መዛሙርቱ በጣም ፈሩthe disciples were very afraid" ምትሃት የሞተ ሰውን ትቶ የሄደ መንፈስ መሰላቸው
ጴጥሮስ እንዲህ ሲል መለሰ "ጴጥሮስ ለኢየሱስ እንዲህ ሲል መለሰ"
አንተ እምነት የጎደለህ በ MAT 6:30 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ስለምን ትጠራጠራለህ? "ልትጠራጠር አይገባህም" ( ተመልከት) የእግዚአብሔር ልጅ የይህ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት የሚገልጽ በጣም አስፈላጊ የሆነ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
በተሻገሩም ጊዜ "ኢየሱስ እና ደቀ መዛሙርቱ ባሕሩን ከተሸገሩ በኋላ" ጌንሴሬጥ ከገሊላ ባሕር ማዶ በሰሜን ደቡብ በኩል የሚትገኝ ትንሽ መንደር ናት ( ተመልከት) መልዕከት ላኩ "በዚያ አከባቢ የሚኖሩ ሰዎች መልዕክት ላኩ” ለመኑት "የታመሙት ሰዎች ለመኑት" ልብስ "የለበሰው ልብስ”
1 ከዚያም አንዳንድ ፈሪሳውያንና የአይሁድ የሕግ መምህራን ከኢየሩሳሌም ኢየሱስን ለማነጋገር መጥተው እንዲህ አሉ፤ 2 "ደቀ መዛሙርትህ የሽማግሌዎችን ወግ የሚጥሱት ለምንድነው? ምግብ ከመብላታቸው በፊት እንደ ወጉ እጃቸውን አይታጠቡምና።" 3 ኢየሱስም መለሰና፣ "እናንተስ ስለ ወጋችሁ ስትሉ ለምን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ትተላለፋላችሁ?" አላቸው፡፡ 4 እግዚአብሔር፣ ‹አባትህንና እናትህን አክብር፣› ‹ስለ አባቱ ወይም ስለ እናቱ ክፉ የሚናገር በርግጥ ይሞታል› ብሏልና፡፡ 5 እናንተ ግን፣ "አባቱን ወይም እናቱን፣ 'ከእኔ የተቀበላችሁት ማንኛውም እርዳታ ለእግዚአብሔር የተሰጠ ስጦታ ነው ትላላችሁ፡፡' 6 ያ ሰው አባቱን ማክበር አያስፈልገውም። ስለ ወጋችሁ ስትሉ የእግዚአብሔርን ቃል ትሽራላችሁ፡፡ 7 እናንተ ግብዞች፣ ኢሳይያስ ስለ እናንተ፣ 8 'ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል፤ ልቡ ግን ከእኔ የራቀ ነው፤ 9 የሰዎችን ትእዛዝ እንደ ሕግ በመቊጠር የራሳቸውን ትምህርት ስለሚያስተምሩ፣ እኔን በከንቱ ያመልኩኛል›› ብሎ ትንቢት በመናገሩ መልካም አድርጓል። 10 ከዚያ ሕዝቡን ወደ ራሱ ጠርቶ፣ "አድምጡ አስተውሉም፡- 11 ወደ አፍ የሚገባ ሰውን ምንም አያረክስም፡፡ ይልቁንም ከአፍ የሚወጣው ሰውን የሚያረክስ ነው" አላቸው፡፡ 12 ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ መጥተው ኢየሱስን፣ ‹‹ፈሪሳውያን ይህን ቃል ሲሰሙ እንደ ተሰናከሉ ዐወቀሃል?›› አሉት፡፡ 13 ኢየሱስም መለሰና፣ ‹‹አባቴ ያልተከለው ተክል ሁሉ ይነቀላል፤ 14 እነርሱን ተዉአቸው፤ ዐይነ ስውር መሪዎች ናቸው፡፡ አንድ ዐይነ ስውር ሌላውን ዐይነ ስውር ቢመራው ሁለቱም ተያይዘው ጕድጓድ ውስጥ ይወድቃሉ፡፡›› 15 ጴጥሮስ መልሶ ኢየሱስን፣ ‹‹ይህን ምሳሌ አብራራልን›› አለው፡፡ 16 ኢየሱስ፣ ‹‹እናንተ ደግሞ አሁንም አታስተውሉምን? 17 ወደ አፍ የሚገባው ሁሉ ወደ ሆድ እንደሚሄድና ከዚያም ዐይነ ምድር ሆኖ ወደ ውጭ እንደሚጣል አታስተውሉምን? 18 ዳሩ ግን ከአፍ የሚወጣ ከልብ ይወጣል፡፡ እነዚህ ነገሮች ሰውን ያረክሳሉ፡፡ 19 ከልብ ክፉ ዐሳብ፣ ነፍስ መግደል፣ ምንዝርና፣ ዝሙት፣ ስርቆት፣ የሐሰት ምስክርነትና ስድብ ይወጣሉ፤ 20 ሰውን የሚያረክሱት እነዚህ ናቸው፡፡ ነገር ግን ባልታጠበ እጅ መብላት ሰውን አያረክስም፡፡" 21 ቀጥሎም ኢየሱስ ከዚያ ወደ ጢሮስና ወደ ሲዶና ከተሞች አካባቢ ሄደ፡፡ 22 እነሆም፣ አንዲት ከነዓናዊት ሴት ከዚያ አካባቢ ወጣችና ጮኽ ብላ እንዲህ አለች፣ ‹‹የዳዊት ልጅ፣ ጌታ ሆይ፣ ማረኝ፡፡ ልጄ በጋኔን ተይዛ በጣም እየተሠቃየች ነው፡፡›› 23 ኢየሱስ ግን አንድም ቃል አልመለሰላትም፡፡ ደቀ መዛሙርቱ መጥተው፣ ‹‹ይህች ሴት ትጮኽብናለችና ሸኛት›› ብለው ለመኑት፡፡ 24 ነገር ግን ኢየሱስ መልሶ፣ ‹‹እንደ በግ ወደ ጠፉት የእስራኤል ቤት ሰዎች ካልሆነ በቀር ወደ ማንም አልተላክሁም›› አለ፡፡ 25 ነገር ግን ሴቲቱ "ጌታ ሆይ፣ እርዳኝ" በማለት መጥታ በፊቱ ሰገደች፡፡ 26 ኢየሱስ መልሶ፣ "የልጆችን እንጀራ ወስዶ ለቡችሎች መጣል ትክክል አይደለም" አለ፡፡ 27 ሴቲቱ፣ "አዎን፣ ጌታ ሆይ፣ ቡችሎችም እኮ ከጌቶቻቸው ማዕድ ከሚወድቀው የተወሰነውን ትርፍራፊ ይበላሉ" አለች፡፡ 28 ከዚያም ኢየሱስ መልሶ፣ "አንቺ ሴት እምነትሽ ታላቅ ነው፤ ልክ እንደ ተመኘሽው ይሁንልሽ" አላት፡፡ ልጇም በዚያች ሰዓት ተፈወሰች፡፡ 29 ኢየሱስ ከዚያ ቦታ ወደ ገሊላ ባሕር አቅራቢያ ሄደ፡፡ ከዚያም ወደ አንድ ኮረብታ ወጥቶ በዚያ ተቀመጠ፡፡ 30 ብዙ ሕዝብም ወደ እርሱ መጡ፤ አንካሶችን፣ ዐይነ ስውሮችን፣ ዲዳዎችንና ጕንድሾችን፣ እንዲሁም ሌሎች ታመው የነበሩ ብዙዎችን ይዘው መጡ፡፡ በኢየሱስ እግር አጠገብም አስቀመጧቸው፤ እርሱም ፈወሳቸው፡፡ 31 ስለዚህ ሕዝቡ ዲዳዎች ሲናገሩ፣ ጕንድሾች ሲፈወሱ፣ አንካሶች ሲራመዱ፣ ዐይነ ስውሮችም ሲያዩ አይተው ተደነቁ፡፡ የእስራኤልንም አምላክ አመሰገኑ፡፡ 32 ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ወደ ራሱ ጠርቶ፣ "ለሕዝቡ አዝንላቸዋለሁ፤ ምክንያቱም ከእኔ ጋር ሦስት ቀን ቈይተዋል፣ የሚበሉትም የላቸውም፡፡ በመንገድ ላይ ዝለው እንዳይወድቁ ሳይበሉ ዝም ብዬ አላሰናብታቸውም" አለ፡፡ 33 ደቀ መዛሙርቱ፣ "በዚህ በረሓ ይህን የሚያህል ብዙ ሕዝብ የሚያጠግብ እንጀራ ከየት እናገኛለን?" አሉት፡፡ 34 ኢየሱስ፣ "ስንት እንጀራ አላችሁ?" አላቸው፡፡ "ሰባት እንጀራና ጥቂት ትናንሽ ዐሣ አለ" አሉት፡፡ 35 ከዚያም ኢየሱስ ሕዝቡን መሬት ላይ እንዲቀመጡ አዘዛቸው፡፡ 36 ኢየሱስ ሰባቱን እንጀራና ዐሣዎቹን ይዞ ካመሰገነ በኋላ እንጀራውን ቈርሶ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ ሰጧቸው፡፡ 37 ሕዝቡ ሁሉ በሉና ጠገቡ፡፡ ትርፍራፊውንም ሰበሰቡ፤ ትርፍራፊውም ሰባት ቅርጫት ሙሉ ነበር፡፡ 38 የበሉትም ከሴቶችና ከልጆች በቀር አራት ሺህ ወንዶች ነበሩ፡፡ 39 ከዚያም ኢየሱስ ሕዝቡን አሰናበተና በጀልባም ገብቶ መጌዶን ወደ ተባለ ክፍለ አገር ሄደ፡፡
የሽማግሌዎችን ወግ ይተላለፋሉ "በትልልቅ የሃይማኖት መሪዎች የተሰጡትን ደንቦች አይጠብቁም" እጃቸውን አይጣጠቡም "በሕጉ መሠረት የተሰጠውን የእጅ መታጠብ ስርዓትን በመከተል እጃቸውን አይታጠቡም ( ተመልከት)
ማንም "ዬትኛውም ሰው" ወይም "ማንም ቢሆን" አባቱን ሊያከብር የማይወድ አባቱን በመንከባከብ ለእርሱ ያለውን አክብሮት ለማሳየት የማይፈልግ ሰው ለወጋችሁ ስትሉ የእግዚአብሔርን ቃል አፍርሳችሁታል ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ስለ ወጋችሁም የእግዚአብሔርን ቃል ሻራችሁ።”
ኢሳያስ ስለ እናንተ ምን አለ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "ኢሳያስ በዚህ ትንቢት ላይ የተናገረው እውነት ነው” እንዲህ ሲል ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እግዚአብሔር የተናገረውን ስናገር" ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል ኤቲ፡ “ይህ ሕዝብ ስለእኔ ትክክል የሆኑ ነገሮችን ይናገራል” ልቡ ግን ከእኔ ርቋል ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ይሁን እንጂ በእርግጥ አይወዱኝ” (en:ta:vol1:translate: ተመልከት) እንዲሁ በከንቱ ያመልኩኛል ለተርጓሚዎች ምክር፡ “አምልኮአቸው ለእኔ ምንም አይደለም” ወይም “እኔን ያመለኩ ያስመስላሉ” የሰው ስርዓት "ሰዎች በሰሩት ስርዓት"
ሰሙ አስተዋሉም ኢየሱስ ከዚህ ቀጥሎ ላለው ዓረፍተ ነገር አጽኖት በመስጠት ተናግሯል
ይህን ቃል የሰሙ ፈሪሳዊያን እንደ ተሰናከሉብህ አወቅህን? ለተሯሚዎች ምክር፡ “ይህ ዓረፍተ ነገር ፈሪሳዊያንን አበሳጭቷቸዋል?" ወይም "ይህ ዓረፍተ ነገር ፈሪሳዊያንን አሰናክለሏልን?" ( ተመልከት)
ለእኛ "ለእኛ ለደቀ መዛሙርትህ" ያለፋል "ይወጣል" እዳሪ ሰዎች የሆድ እዳሪያቸውን የሚያስወግዱበት ሥፍራን በጨዋ ቋንቋ ለመግለጽ ነው፡፡
ከአፍ የሚወጣ "አንድ ሰው የሚናገረው ቃል" ከልብ ይወጣል "ከሰውዬው እውነተኛ ስሜት እና ሀሳቦች ውጤት ናቸው” መግደል ንጹሕ ሰውን መግደል ስድብ "ሌላ ሰውን የሚያሰናክል ነገር ማነገር" ያልታጠበ እጅ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ ያልታጠበ እጅ
ከነናዊት ሴት ከዚያ አገር ሴትቱ ሀገሯን ትታ ወደ እስራኤል በመምጣት ኢየሱስን አገኘችው ከነናዊት ሴት ከነዓን የሚባል ሀገር አሁን የለም፡፡ “ከነዓን ተባለ ሀገር ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች መካከል የሆነች አንዲት ሴት" ሴት ልጄን ጋኔን ክፉኛ ይዞአታል "ሴት ልጄን ጋኔን በጣም እያሰቃያት ነው” ( ተመልከት) ምንም ቃል አልመለሰላትም "ዝም አላት"
ወደ እርሱ መጣች "ከነዓናዊቷ ሴት ወደ እርሱ መጣች" የልጆችን እንጀራ ...ለቡችሎች "በትክክለኛው መንገድ ለአይሁዶች የሆነውን ነገር . . . ለአሕዛብ" ( ተመልከት)
ቡችሎች እንኳ ከጌቶቻቸው ማዕድ የተራረፈውን ይበላሉ አሕዛብ ከአይሁዳዊያን የተራረፈው መልካም ነገር ልያገኙ ይገባል፡፡ ( ተመልከት) ሴት ልጇ ተፈወሰች "ኢየሱስ ሴት ልጇን ፈወሰላት” ወይም "ኢየሱስ የሴት ልጇን ጤና መለሰላት” ( ተመልከት) በዚያን ጊዜ "በተመሳሳይ ሰዓት" ወይም "ወዲያው"
ሽባ፣ ዐይነ ስውር፣ ዲዳ እና መሄድ የማይችል "መራመድ የማይችሉ ሰዎች፣ ማየት የማይችሉ አንዳንዶች፣ መናገር የማይችሉ፣ እግራው እና እጃቸው የማይሰራ ሰዎች”፡፡ አንዳንድ ጥንታዊያን ቅጅዎች እነዚህን ቃላት በተለያየ ቅደም ተከተል አስቀምጠውታል፡፡ በኢየሱስ እግሪ ፊት አስቀመጡ "ሕዝቡ የታመመውን ሰው በኢየሱስ ፊት አስቀመጡ"
ዝለው እንዳይወድቁ አማራጭ ትርጉሞች 1) “ራሳቸነውን እንዳይስቱ በመፍራት” ወይም 2) “ሊደክማቸው ይችላል ከሚል ስጋት” ( ተመልከት) ተቀመጡ ጠረጴሳ ባሌለበት ሁኔታ ሰዎች ምግብ ለመመገብ በባሕላችሁ የሚቀመጡበትን መንገድ የሚገልጽ ቃልን ተጠቀም፡፡
ወሰደ "ኢየሱስ ወስዶ” ፡፡ ይህንን በ MAT 14:19 በተረጎምከው መሠረት ተርጉመው፡፡ ስጧቸው "ዳቦዎቹን እና ዓሳዎቹን ስጧቸው" ለቀሟአቸው "ደቀ መዛሙርቱ ለቀሙ" የተመገቡት "የበሉት ሰዎች" አከባቢ "የአንድ ሀገር አንዱ ክፍል" መጌዶል አንዳንድ ጊዜ “ማጌዳላ” ተብሎ ይጠራል ( ተመልከት)
1 ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያንም መጥተው ከሰማይ ምልክት እንዲያሳያቸው በመጠየቅ ኢየሱስን ፈተኑት፡፡ 2 ነገር ግን ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አላቸው፣ "በመሸ ጊዜ ሰማዩ ቀልቷልና ዝናብ አይኖርም ትላላችሁ 3 በነጋ ጊዜም፣ ‹ዛሬ ሰማዩ ስለ ጠቈረ ይዘንባል› ትላላችሁ፤ የዘመኑን ምልክት ግን መለየት አትችሉም፡፡ 4 ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል፤ ነገር ግን ከነቢዩ ከዮናስ ምልክት በቀር ሌላ ምልክት አይሰጠውም፡፡" ከዚያም ኢየሱስ ትቶአቸው ሄደ፡፡ 5 ደቀ መዛሙርቱ ወደ ማዶ ተሻገሩ፤ እንጀራ መያዝን ግን ረሱ፡፡ 6 ኢየሱስ፣ "ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን እርሾ ተጠንቀቁ፣ ተጠበቁም" አላቸው፡፡ 7 ደቀ መዛሙርቱ፣ "እንጀራ ስላልያዝን ነው" ብለው እርስ በርሳቸው ተነጋገሩ፡፡ 8 ኢየሱስ ይህን ዐውቆ፣ "እናንተ እምነተ ጎደሎዎች፣ እንጀራ ስላልያዝን ነው ብላችሁ ስለ ምን እርስ በርሳችሁ ትነጋገራላችሁ?" 9 ዐምስት እንጀራ ለዐምስቱ ሺህ እንደ በቃና ስንት ቅርጫት እንደ ሰበሰባችሁ አሁንም አታስተውሉም ወይም አታስታውሱም? 10 ወይም ደግሞ ሰባቱ እንጀራ ለአራቱ ሺህ እንደ በቃና ስንት ቅርጫት እንዳነሣችሁስ አታስታውሱምን? 11 እኔ የነገርኋችሁ ስለ እንጀራ እንዳልነበረ እንዴት ነው የማታስተውሉት? ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያ እርሾ ተጠንቀቁ፣ ተጠበቁም፡፡" 12 ከዚያም እርሱ ሲነግራቸው የነበረው ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን ትምህርት እንዲጠበቁ እንጂ፣ ስለ እንጀራ እርሾ እንዳልነበረ ተረዱ፡፡ 13 ኢየሱስም ወደ ቂሣርያ ፊልጶስ ክልል በመጣ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፣ "ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ነው ይላሉ?" በማለት ጠየቃቸው፡፡ 14 እነርሱ፣ እንዲህ አሉ፤ "አንዳንዶች መጥምቁ ዮሐንስ፣ ሌሎች ኤልያስ፣ የቀሩትም ኤርምያስ፣ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ፡፡" 15 "እናንተስ እኔን ማን ትሉኛላችሁ?" አላቸው፡፡ 16 ስምዖን ጴጥሮስ፣ "አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ" በማለት መልስ ሰጠ፡፡ 17 ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አለው፣ "የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፣ አንተ የተባረክህ ነህ፤ ይህን የገለጠልህ የሰማዩ አባቴ ነው እንጂ፣ ሥጋና ደም አይደለም፡፡ 18 ደግሞም አንተ ጴጥሮስ ነህም እላለሁ፤ በዚህም አለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፤ የገሃነም ደጆችም አያሸንፏትም፡፡ 19 እኔ የመንግሥተ ሰማያትን መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፡፡ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማይ የታሰረ ይሆናል፤ በምድር የምትፈታውም ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሆናል፡፡›› 20 ከዚያም ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ መሆኑን ለማንም እንዳይናገሩ ደቀ መዛሙርቱን አዘዛቸው፡፡ 21 ከዚያን ጊዜ አንሥቶ ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም መሄድ፣ በሽማግሌዎችና በካህናት አለቆች፣ በፈሪሳውያንና በሕግ መምህራንም እጅ ብዙ መከራ መቀበልና መገደል፣ በሦስተኛውም ቀን መነሣት እንዳለበት ለደቀ መዛሙርቱ ይነግራቸው ጀመር፡፡ 22 ከዚያም ጴጥሮስ ኢየሱስን ለብቻው ገለል አድርጎ፣ "ጌታ ሆይ፣ ይህ ከአንተ ይራቅ፤ ይህም ከቶ አይሁንብህ" በማለት ገሠጸው፡፡ 23 ኢየሱስ ግን ዞር ብሎ ጴጥሮስን፣ "ከፊቴ ዞር በል፣ ሰይጣን! ስለ ሰው እንጂ ስለ እግዚአብሔር ነገር ደንታ የለህምና አንተ ለእኔ እንቅፋት ነህ" አለው፡፡ 24 ከዚያም በኋላ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እንዲህ አላቸው፤ "ሊከተለኝ የሚፈልግ ማንም ቢኖር፣ ራሱን መካድ፣ የራሱን መስቀል መሸከምና እኔን መከተል አለበት፡፡ 25 ሕይወቱን ለማዳን የሚፈልግ ሁሉ ያጣዋል፤ ስለ እኔ ሕይወቱን የሚያጣ ግን ያገኘዋል፡፡ 26 ሰው ሙሉውን ዓለም የራሱ ቢያደርግ ሕይወቱን ግን ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል? ሰው በሕይወቱ ፈንታ ምን መስጠት ይችላል? 27 የሰው ልጅ በአባቱ ክብር ከመላእክቱ ጋር ይመጣልና፡፡ ከዚያም ለእያንዳንዱ ሰው እንደ ሥራው ይከፍለዋል፡፡ 28 እውነት እላችኋለሁ፤ እዚህ ከቆማችሁት መካከል የሰው ልጅ በመንግሥቱ ሲመጣ እስኪያዩ ድረስ ሞትን የማይቀምሱ አንዳንዶች አሉ፡፡"
ሰማይ . . . ሰማይ የአይሁድ መሪዎች ከእግዚአብሔር ዘንድ ምልክትን ይሹ ነበር ይሁን እንጂ ኢየሱስ ማየት ወደሚችሉት ሰማይ ይመለከቱ ዘንድ ነገራቸው፡፡ አንባቢዎቹ የትርጉም ልዩነቱን መረዳት የሚችሉ ከሆነ ብቻ ለእግዚአብሔር ማደሪያም እንዲሁም ለሰማይ ከተቻለ አንድ ቃል ተጠቀም፡፡ ( ተመልከት) በመሸም ጊዜ ፀሐጥ በጠለቀች ጊዜ ጥሩ የአየር ሁኔታ ግልጽ እና ጥርት ያለ ሰማይ ነው ሰማዩ ቀልቷል ሰማዩ ብርሃማ እና ከፀሐይ መትለቅ ጋር ተያይዞ ቀላልቷል
የአየር ጸባዩ ጥሩ አይደለም "ዳመናማ እና ጭጋጋማ ነው" ጨልሟል "ጨለማ እና የሚያስፈራ ነው" ምንም ዓይነት ምልክት አይሰጣችሁም ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ለእናነት ምንም ምልክት እግዚአብሔር አይሰጣችሁም (en:ta:vol2:translate: እና ተመልከት)
እርሾ ክፉ ሀሳቦች እና ስህተት ትምህርት ( ተመልከት) ምክንያት "መከራከር" ወይም “መጣላት"
ለአምስቱ ሺህ አምስቱ እንጀራ፥ ስንት መሶብም እንዳነሣችሁ ትዝ አይላችሁምን? ወይስ ለአራቱ ሺህ ሰባቱ እንጀራ፥ ስንት ቅርጫትም እንዳነሣችሁ ትዝ አይላችሁምን? ኢየሱስ እየገሰጻቸው ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “በአምስት ዳቦ 5000 ሰዎች የተመገቡበት እና ምን ያህል ቅርጫት እንደሰበሰባችሁ መረዳት እና ማስታወስ ነበረባችሁ! ከዚህ በተጨማሪ በ7 ዳቦዎችን 4000 ሰዎች ስትመግቡ ምን ያህል ሰበሰባችሁ! ( and ተመልከት)
ስለ እንጀራ እንዳልተናገርኋችሁ እንዴት አታስተውሉምን? "በእርግጥ ስለ እንጀራ እያወራሁ እንዳልሆነ መረዳት ነበረባችሁ፡፡” (UDB) ( ተመልከት) እርሾ ክፉ ሀሳቦች እና የተሳሳቱ ትምህርቶች ( ተመልከት) እነርሱ . . . እነርሱ “ደቀ መዛሙርቱ”
ነገር ግን እናንተ እኔ ማን እንደሆኑ ትለላላችሁ? "እናንተን ግል ልጠይቃች፡ እኔ ማን እንደሆኑን ትላላችሁ?"
የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ "የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ " (UDB) ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህም "ይህንን ዬትኛው የሰው ልጅ አልገለጠልህም” ( ተመልከት)፡፡ “አንተ ክርስቶስ ፣ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ” የሚለው የጴጥሮስ ንግግር ወደ ጴጥሮስ የመጣው በማንም ሳይሆን በእግዚአብሔር በራሱ ነው፡ አባት ይህ በኢየሱስ እና በእግዚአብሔር መካከል ያለው ግንኙነት በሚገባ የሚገልጽ በጣም ጠቃሚ የሆነ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) የገሃነም ደጆች አይችሏትም አማራጭ ትርጉሞች: 1) "የሞት ኃይል ልቋቋማት አይችልም " ወይም 2) የጦር ሠራዊት አንድን ከተማ ሰብሮ እንደሚገባው ሁሉ የሞትን ኃይል ይሠባብራል፡፡ ( ተመልከት)
የመንግስተ ሰማያት ቁልፍ አገልጋይ ሰዎች ወደቤት ስገቡ ተቀበሎ እንደሚያገልግል ሁሉ ሰዎች የእግዚአብሔር ሕዝብ መሆን የሚችሉበትን መንገድ የመክፈት ክህሎት ( ተመልከት) በምድር ያሠራችሁት . . . በሰማይ የተፈራ ይሆናል በሰማይ እንደሚሆነው ሁሉ ለሰዎች ይቅርታን መስጠት ወይም በእነርሱ ላይ መፍረድ ( ተመልከት)
ከዚያ ቀን ጀምሮ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እርሱ ክርስቶስ መሆኑን ለሌላ ለማንም እንዳይናገሩ ካዘዛቸው በኋላ እግዚአብሔር ለእርሱ ያለው እቅዱን ያካፍላቸው ጀመረ፡፡ anded his disciples not to tell anyone that he was the Christ, he began sharing God's plan for himself. እንደሚሞት ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እንደሚገድሉት” ( ተመልከት) በሦስተኛው ቀን በሕይወት እንደሚነሳ "በሦስተኛው ቀን እግዚአብሔር እንደገና ሕያው እንደሚያደርገው"
ተከተለኝ "ደቀ መዝሙሬ ሁን" ራስህን ካድ "በራስህ ምኞች አትወሰድ" ወይም "የራስህን መሻት ተው" መስቀሉን ተሸከምና ተከተለኝ "መስቀሉን አንሳ፣ ተሸከም እና ከእኔ በኋላ ተከተል”፣ መከራን ለመቀበል እና ለክርስቶስ ለመሞት ፈቃደኛ ሁን ( ተመልከት) የሚወድ ማንም ቢኖር "የሚፈልግ ማንም ቢኖር" ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ "በዓለም ያለውን ሁሉ ቢያተርፍ" ነፍሱን ግን ቢያጎድል "እርሱን ግን ቢጠፋ”
የሰው ልጅ . . . አባቱ ኢየሱስ እንደ “ሰው ልጅነቱ” እና “የእርሱ” ልጅ መሆኑን ስገልጽ በሥላሴ ውስጥ እንዳለ ሦስተኛ አካል ያሳያል ፡፡ ለተሯሚዎች ምክር፡ "እኔ፣ የሰው ልጅ . . . አባቴ” ( ተመልከት) አባቱ ይህ በኢየሱስ እና በእግዚአብሔር መካከል ያለው ግንኙነት በሚገባ የሚገልጽ በጣም ጠቃሚ የሆነ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት) የሰው ልጅ በመንግስቱ እስኪመጣ ድረስ ሞትን አይቀምሱም "ከመሞታቸው በፊት የሰው ልጅ በመንግስቱ ስመጣ ያዩታል” ሞትን አይቀምሱም "ሞትን አያዩም" ወይም “አይሞቱም" የሰው ልጅ በመንግስቱ ሲመጣ ኢየሱስ ራሱን እንደ ሥላሴ ሦተኛ አካል እየጠራ ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “በመንግስቴ ሲመጣ እስኪያዩኝ ድረስ” ( ተመልከት)
1 ከስድስት ቀን በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ ዮሐንስን፣ ያዕቆብንና ወንድሙን ይዞ ብቻቸውን ወደ ረጅም ተራራ አወጣቸው፡፡ 2 በፊታቸውም መልኩ ተለወጠ፤ ፊቱ እንደ ፀሐይ አበራ፤ ልብሱም እንደ ብርሃን አንጸባረቀ፡፡ 3 እነሆ፣ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው፡፡ 4 ጴጥሮስ መልሶ ኢየሱስን፣ "ጌታ ሆይ፣ እዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፡፡ ብትፈልግ እኔ እዚህ ሦስት ዳሶችን፡- አንድ ለአንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ አንድ ለኤልያስ እሠራለሁ" አለው፡፡ 5 እርሱ ገና እየተናገረ እያለ፣ እነሆ፣ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፡፡ ከደመናውም፣ "በእርሱ እጅግ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት" የሚል ድምፅ ነበረ፡፡ 6 ደቀ መዛሙርቱ ድምፁን በሰሙ ጊዜ ፈሩ፣ በግንባራቸውም ወደቁ፡፡ 7 ከዚያም ኢየሱስ መጥቶ ዳሰሳቸውና፣ ‹‹ተነሡ አትፍሩ›› አላቸው፡፡ 8 ከዚያም እነርሱ ቀና ብለው ተመለከቱ፣ ነገር ግን ከኢየሱስ ብቻ በቀር ማንንም አላዩም፡፡ 9 ከተራራ ሲወርዱም ኢየሱስ፣ "የሰው ልጅ ከሙታን እስኪነሣ ድረስ ይህን ያያችሁትን ለማንም አትንገሩ" ብሎ አዘዛቸው፡፡ 10 ደቀ መዛሙርቱ፣ "እንግዲያው የአይሁድ ሕግ መምህራን መጀመሪያ ኤልያስ መምጣት አለበት ለምን ይላሉ?" በማለት ጠየቁት፡፡ 11 ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አለ፤ "ኤልያስ በርግጥ ይመጣል፣ ሁሉንም ነገር ያስተካክላል፡፡ 12 ነገር ግን እላችኋለሁ፤ ኤልያስ አስቀድሞ መጥቷል፤ ነገር ግን አላወቁትም፡፡ በዚህ ፈንታ የፈለጉትን ነገር ሁሉ አደረጉበት፡፡ በተመሳሳይ መንገድ የሰው ልጅ በእነርሱ እጅ መከራ ይቀበላል፡፡›› 13 በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ የተናገራቸው ስለ መጥምቁ ዮሐንስ እንደ ነበረ ተረዱ፡፡ 14 ወደ ሕዝቡ በመጡ ጊዜ አንድ ሰው መጥቶ በፊቱ ተንበረከከ፤ እንዲህም አለው፤ 15 "ጌታ ሆይ፣ ልጄን ማረው፣ የሚጥል በሽታ ይዞት በኀይል ይሠቃያል፤ ብዙ ጊዜ በእሳት ወይም በውሃ ውስጥ ይጥለዋልና፡፡ 16 ወደ ደቀ መዛሙርትህ አመጣሁት፤ ነገር ግን እነርሱ ሊፈውሱት አልቻሉም፡፡› 17 ኢየሱስ መልሶ፣ "የማታምኑና ምግባረ ብልሹ ትውልድ፣ እስከ መቼ ድረስ ከእናንተ ጋር እቆያለሁ? እስከ መቼስ እናንተን መታገሥ አለብኝ? እስቲ ወደ እኔ አምጡት" አለ፡፡ 18 ኢየሱስ ገሠጸው፤ ጋኔኑም ከእርሱ ወጣ፤ ልጁም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ተፈወሰ፡፡ 19 ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ ኢየሱስ መጥተው፣ "እኛ ልናወጣው ያልቻልነው ለምንድን ነው?" አሉ፡፡ 20 ኢየሱስ፣ ‹‹በእምነታችሁ ማነስ ምክንያት፤ እውነት እላችኋለሁና፣ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት እንኳ ቢኖራችሁ ይህን ተራራ ከዚህ ተነሥተህ ወደ ማዶ ሂድ ብትሉት ይሄዳል፡፡ ማድረግ የሚሳናችሁ ምንም ነገር አይኖርም፡፡ 21[1]22 በገሊላ እያሉ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን፣ "የሰው ልጅ በሰዎች እጅ ተላልፎ ይሰጣል፤ 23 እነርሱም ይገድሉታል፤ በሦስተኛውም ቀን ይነሣል" አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱ በጣም ዐዘኑ፡፡ 24 ወደ ቅፍርናሆም በመጡ ጊዜ ግማሽ ሰቅል ቀረጥ የሰበሰቡ ሰዎች ወደ ጴጥሮስ መጥተው፣ "መምህራችሁ ግማሽ ሰቅሉን ቀረጥ አይከፍልምን?" አሉ፡፡ 25 እርሱ፣ "አዎ" አለ፡፡ ጴጥሮስ ወደ ቤት በገባ ጊዜ ግን ኢየሱስ መጀመሪያ እርሱን ተናገረው፤ "ስምዖን ሆይ፣ ምን ይመስልሃል? የምድር ነገሥታት ቀረጥ ወይም ግብር የሚሰበስቡት ከማን ነው? ከዜጎቻቸው ወይስ ከውጭ አገር ሰዎች?" አለው፡፡ 26 ጴጥሮስ፣ "ከውጭ አገር ሰዎች" ባለ ጊዜ፣ ኢየሱስ እንዲህ አለው፤ "እንግዲያስ ዜጎቹ ከክፍያ ነጻ ናቸው፡፡ 27 ነገር ግን ቀረጥ ሰብሳቢዎቹን ኃጢአት እንዲሠሩ እንዳናደርጋቸው ወደ ባሕር ሄደህ መንጠቆ ጣል፤ በመጀመሪያ የምታጠምደውን ዐሣ አፍ ስትከፍት አንድ ሰቅል ታገኛለህ፤ ያንን ወስደህ ስለ እኔና ስለ አንተ ክፈል፡፡››
ማቴዎስ 17፡ 1-2
ጴጥሮስ እና ያዕቆብ እንዲሁም ወንድሙ ዮሐንስ "ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ እና የያዕቆብ ወንድም ዮሐንስ” ተለወጠ "እግዚአብሔር የኢየሱስ መልክ ሙሉ ለሙሉ ለወጠው” ወይም ( ተመልከት) ልብሶች "ልብስ" እንደ ብርሃን ያበሩ ነበር "እንደ ብርሃን ያንጸባርቁ ነበር" ( ተመልከት)
ማቴዎስ 17፡3-4
እነሆ ይህ ቃል ሰዎች ከዚህ በኋላ ለሚነገረው ነገር አጽኖት እንዲሰጡ የሚጨመር ቃል ነው፡፡ ለእነረሱ ከኢየሱስ ጋር ለነበሩት ደቀ መዛሙርት እንዲህ ሲል መለሰላቸው "አላቸው” ጴጥሮስ ለተጠየቀው ጥያቄ መልስ እየሰጠ አይደለም፡፡ በዚህ መሆን ለእኛ ይሻላል አማራጭ ትርጉሞች፡ 1) "እኛ ደቀ መዛሙርት በዚህ ከአንተ፣ ከሙሴ እና ከኤልያስ ጋር መሆናችን መልካም ነው” ወይም “አንተ፣ ሙሴ፣ ኤልያስ እና እኛ ደቀ መዛሙርትህ በአንድነት መሆናችን መልካም ነው፡፡” ( ተመልከት) መጠለያዎች አማራጭ ትርጉሞች 1) ሰዎች ለአምልኮ የሚመጧቸው ሥፍራዎች ወይም 2) ሰዎች በጊዜያዊነት ለመተኛ የሚዘጋጇቸው
እነሆ ይህ ቃል ሰዎች ከዚህ በኋላ ለሚነገረው ነገር አጽኖት እንዲሰጡ የሚጨመር ቃል ነው፡፡ በግንባራቸው መሬት ላይ ተደፍተው "ደቀ መዛሙርተ በግንባራቸው በመሬት ላይ ተደፍተው”
እነርሱ . . . ሳለ "ኢየሱስ እና ደቀ መዛሙርቱ . . . ሰለ"
ሁሉን ነገር ያድሳል "ሁሉን ነገር በሥርዓት ያደርጋል" እነርሱ . . . እነርሱ . . . እነርሱ አማራጭ ትርጉሞች: 1) የአይሁድ መሪች ወይም 2) ሁሉም የአይሁድ ሕዝቦች
የሚጥል በሽታ ያለበት ራሱን ስቶ የሚያደርገው ነገር የማያውቅ ሰው
ከእናንተ ጋር እስከ መቼ እቆያለሁ? እስከ መቼስ እታገሣችኋለሁ? ኢየሱስ በሕዝቡ ደስተኛ አልነበረም፡፡ የተርጓሚዎች ምክር፡ ከእናንተ ጋር መሆን ደከመኝ! አለማመናችሁ እና ክፋታችሁ ሰለቸኝ!” ( ,ተመልከት)
እኛ ተናጋሪው እንጂ ሰሚዎቹ አይደሉም ( ተመልከት) እኛ ማውጣት ያቃተን ለምንድ ነው "ጋኔኑ እንዲወጣ ማድረግ ያቃጠን ለምንድ ነው” ማድረግ የማትችሉት ነገር የለለምNothing will be impossible for you to do "ምንም ነገር ማድረግ ትችላላችሁ” ( ተመልከት)
በዚያም ቆዩ "ደቀ መዛሙር እና ኢየሱስ በዚያ ቆዩ" የሰው ልጅ አሳልፎ ይሰጣል ለተርጓሚዎች ምክር፡ "የሆኑ ሰዎች የሰው ልጅን አሳልፈው ይሰጡታል” ( ተመልከት) ይገድሉታ "ባለስልጣናት የሰወ ልጅን ይገድሉታል” ከሞት ይነሣል "እግዚብሔር ከሞት ያሥነሣዋል” ወይም “እንደገና ወደ ህይወት ይመላሳለር” ( ተመልትከት)
በ . . . ጊዜ እነርሱ ኢየሱስ እና ደቀ መዛሙርቱ በ . . ጊዜ
ሥር ያሉ በአጋዘዙ ውስጥ ወይም በንጉሥ ሥር ያሉ አፉ "የዓሣ አፍ" ውሰዱ "አስታተር ውሰድና"
1 በዚያው ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሱስ መጥተው፣ "በእግዚአብሔር መንግሥት ከሁሉ የሚበልጥ ማን ነው?" አሉ 2 ኢየሱስ አንድ ትንሽ ልጅ ጠርቶ በመካከላቸው አቆመው፤ 3 እንዲህም አለ፡- "እውነት እላችኋለሁ፤ ንስሐ ካልገባችሁና እንደ ልጆች ካልሆናችሁ በምንም መንገድ ወደ መንግሥተ ሰማያት አትገቡም፡፡ 4 ስለዚህ እንደዚህ ልጅ ራሱን ዝቅ የሚያደርግ ሰው ሁሉ፣ እንዲሁ በመንግሥተ ሰማያት ከሁሉ ይበልጣል፡፡ 5 እንደዚህ ያለውን ልጅ በስሜ የሚቀበል ሁሉ እኔን ይቀበላል፡፡ 6 ነገር ግን በእኔ ከሚያምነው ከእነዚህ ልጆች አንዱን ኀጢአት እንዲሠራ የሚያደርግ ማንም፣ ትልቅ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቁ ባሕር ቢሰጥም ይሻለዋል፡፡ 7 የመሰናክል ምክንያት በመሆኗ ለዓለም ወዮላት! መሰናክል መምጣቱ ግድ ነው፤ ነገር ግን መሰናክሉን ለሚያመጣ ሰው ወዮለት! 8 እጅህ ወይም እግርህ ቢያሰናክልህ፣ ቈርጠህ ከአንተ ጣለው፡፡ ሁለት እጆች ወይም እግሮች ኖረውህ ወደ ዘላለም እሳት ከምትጣል የአካል ጉዳተኛ ወይም አንካሳ ሆነህ ወደ ሕይወት ብትገባ ይሻልሃል፡፡ 9 ዐይንህ እንድትሰናከል ቢያደርግህ፣ አውጥተህ ከአንተ ጣለው፡፡ ሁለት ዐይኖች ኖረውህ ወደ ዘላለም እሳት ከምትጣል፣ አንድ ዐይን ኖሮህ ወደ ሕይወት ብትገባ ይሻላል፡፡ 10 ከእነዚህ ከታናናሾች ማንኛውንም እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፡፡ በሰማይ ያሉ መላእክታቸው በሰማይ ያለውን የአባቴን ፊት ሁልጊዜ ያያሉና፡፡ 11 (2) ብዙ ምንጮች፣ አንዳንድ የጥንት የሆኑ ቊ. 11ን ያስገባሉ፡፡ 11[1]12 ምን ይመስላችኋል? አንድ ሰው መቶ በጎች ቢኖሩት፣ ከእነርሱም አንዱ ቢጠፋ፣ ዘጠና ዘጠኙን በኮረብታው ጥግ ትቶ የጠፋውን ሊፈልግ አይሄድምን? 13 በሚያገኘውም ጊዜ፣ እውነት እላችኋለሁ፣ ካልጠፉት ከዘጠና ዘጠኙ ይልቅ በእርሱ ደስ ይለዋል፡፡ 14 በተመሳሳይ መንገድ ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱ እንዲጠፋ የሰማዩ አባታችሁ ፈቃድ አይደለም፡፡ 15 ወንድምህ ቢበድልህ፣ ሂድና አንተና እርሱ ብቻ ሆናችሁም ጥፋቱን አሳየው፡፡ ቢሰማህ፣ ወንድምህን የራስህ ታደርገዋለህ፡፡ 16 ባይሰማህ ግን፣ ቃል ሁሉ በሁለት ወይም በሦስት ምስክሮች ይጸናልና፣ ከአንተ ጋር አንድ ወይም ሁለት ተጨማሪ ወንድሞችን ይዘህ ሂድ፡፡ 17 እነርሱንም አልሰማም ቢል፣ ጉዳዩን ለቤተ ክርስቲያን ንገር፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ደግሞ አልሰማም ቢል፣ እንደ አረመኔና እንደ ቀራጭ ቊጠረው፡፡ 18 እውነት እላችኋለሁ፣ በምድር የምታስሩት ነገር ሁሉ በሰማይ የታሰረ ይሆናል፤ በምድር የምትፈቱትም ነገር ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሆናል፡፡ 19 በተጨማሪም እላችኋለሁ፣ ከእናንተ ሁለቱ በምድር ስለሚለምኑት ስለ ማንኛውም ነገር ቢስማሙ፣ በሰማይ ያለው አባቴ ያደርግላቸዋል፡፡ 20 ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት ቦታ እዚያ በመካከላቸው እገኛለሁና፡፡ 21 ከዚያም ጴጥሮስ መጥቶ ኢየሱስን፣ ‹‹ጌታ ሆይ፣ ወንድሜ ቢበድለኝ ስንት ጊዜ ይቅር ልበለው? እስከ ሰባት ጊዜ ነውን?›› አለው፡፡ 22 ኢየሱስም፣ ‹‹ሰባ ጊዜ ሰባት እንጂ፣ ሰባት ጊዜ አልልህም›› አለው፡፡ 23 ስለዚህ መንግሥተ ሰማያት ከአገልጋዮቹ ጋር ሒሳብ ሊተሳሰብ የፈለገ ንጉሥን ትመስላለች፡፡ 24 መተሳሰቡን እንደ ጀመረ፣ የዐሥር ሺህ መክሊት ዕዳ ያለበትን አገልጋይ ወደ እርሱ አመጡ፡፡ 25 ነገር ግን የሚከፍልበት መንገድ ስላልነበረው፣ ጌታው ከሚስቱና ከልጆቹ ጋር ያለውም ሁሉ ተሸጦ ክፍያው እንዲፈጸም አዘዘው፡፡ 26 ስለዚህ አገልጋዩ ወድቆ በፊቱ ተንበረከከ እንዲህም አለ፤ ‹ጌታዬ ሆይ፣ ታገሠኝ፣ ሁሉንም እከፍልሃለሁ፡፡› 27 ስለዚህ የዚያ አገልጋይ ጌታ ስለ ራራለት፣ ተወው፤ ዕዳውንም ሠረዘለት፡፡ 28 ነገር ግን ያ አገልጋይ ወጥቶ አብረውት ከሚሠሩት አገልጋዮች መቶ ዲናር ያበደረውን አንዱን አገልጋይ አግኝቶ ያዘው፤ ጕሮሮውን አነቀውና፣ ‹‹ያለብህን ዕዳ ክፈለኝ›› አለው፡፡ 29 ነገር ግን የሥራ ባልደረባው፣ ‹‹ታገሠኝ፣ እከፍልሃለሁ›› በማለት ወድቆ ለመነው፡፡ 30 የመጀመሪያው አገልጋይ ግን አሻፈረኝ አለ፤ በዚህ ፈንታ ያለበትን ዕዳ እስኪከፍለው ድረስ በእስር ቤት ጣለው፡፡ 31 የሥራ ጓደኞቹ የሆኑት አገልጋዮች የሆነውን ነገር ባዩ ጊዜ፣ በጣም ተበሳጩ፤ መጥተውም ለጌታቸው የሆነውን ሁሉ ነገሩት፡፡ 32 ከዚያም የዚያ አገልጋይ ጌታ ጠራው፣ እንዲህም አለው፤ 'አንተ ክፉ አገልጋይ፣ ስለ ለመንኸኝ ያን ሁሉ ዕዳ ተውሁልህ፡፡ 33 እኔ አንተን እንደማርሁህ፣ የሥራ ባልደረባህ የሆነውን አገልጋይ ልትምረው አይገባህም ነበርን?' 34 ጌታው ተቈጥቶ ዕዳውን ሁሉ እስኪከፍል ድረስ ለሚያሠቃዩት አሳልፎ ሰጠው፡፡ 35 ስለዚህም ከእናንተ እያንዳንዱ ወንድሙን ከልብ ይቅር ባይል የሰማዩ አባቴ እንዲሁ ያደርግበታል፡፡"
እንደ ሕጻን መሆን "ሕጻናት እነደሚያስቡት ማሰብ፡፡” (MAT 18:4 እና ተመልከት)
እንደዚህ ሕጻን ራሱን የሚያዋርድ "ይህ ሕጻን ራሱን በሚያዋርድበት መንገድ ራሱን የሚያዋርድ ማንኛውም ሰው" ( ተመልከት) የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቅ ባሕር መስጠም ይሻለው ነበር። "የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ አስረው ወደ ጥልቅ ባሕር መስጠም ከተሻለው”( ተመልከት የወፍጮ ድንጋይ ትልቅ፣ ክብ ቅርጽ ያለው ከባድ ድንጋይ ሆኖ እህል ለመፍጨት የሚያገለግል ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "ከባድ ድንጋይ"
እጅህ ኢየሱስ አድማጮቹ እንደ አንድ ሰው አድርጎ በነጠላ ቁጥር እየተናገራቸው ነው፡፡
አውጥተህ ጣለው ይህ ሀረግ የሚያሳየው ተከታታይነት ያለው አለማመንን እና የሚያስከፍለውን ማንኛውንም ዋጋ መሸሽን ነው፡፡ ወደ ሕይወት መግባት "ወደ ዘላለም ሕይወት መግባት"
አትናቁ "አትናቁ" ወይም "ጠቃሚ አይደሉም ብላችሁ አታስቡ" ለተርጓሚዎች ምክር፡ "አክብሩ" ሁል ጊዜ . . . ፊት ያያሉ "ሁል ጊዜ ቅርብ ናቸው "
ምን ይመስላችኋል? “ሰዎች ምን እንደሚያደርጉ አስቡ" ( ተመልከት) ትቶ ሄዶም የባዘነውን አይፈልግምን? "ሁልጊዜ ትቶ ሄዶ የባዘነውን ይፈልጋል፡፡” ዘጠና ዘጠኝ “99” ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱ እንዲጠፋ በሰማያት ያለው አባታችሁ ፈቃድ አይደለም። "በሰማይ ያለው አባታችሁ እነዚህ ትንንሾቹም ሁሉ እንዲኖሩ ፈቃዱ ነው" ( ተመልከት)
ወንድምህን ገንዘብ አደረግኸው "ከወንድምህ ጋር ያለህን ግንኙነት እንደገና መልካም ታደርጋለህ” አፍ ለምስክሮችህ “አፍ” በሚወጣው ቃል ( ተመልከት)
እነርሱ መስማት ምስክሮቹን መስማት (MAT 18:16) ለአንተ ልክ እንደ አሕዛብ እና ቀራጭ ይሁንልህ "አሕዛብን እና ቀራጭን እንደሚትመለከተው እንደዚያው ይሁንልህ"
ያሰራችሁት … የታሰረ . . . -ፈታችሁት . . . የተፈታ ይህህ በ MAT 16:19 ላይ እንዴት እንደተረጎምከተው ተመልከት፡፡ ይታሰራል . . . ይፈታል "እግዚአብሔር ያስረዋል . . . እግዚአብሔር ይፈተዋል" ( ተመልከት) እነርሱ . . . እነርሱ "ሁለት ሆናችሄ" ሁለት ወይም ሦስት "ሁለት ወይም ከዚያ በላይ" ወይም "ቢያንስ ሁለት" ተሰብሰባችሁ "ስበሰባ" አባት ይህ የእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ( ተመልከት)
ሰባት እጥፍ "7 እጥፍ" ( ተመልከት ሰባ ጊዜ ሰባት አማራጭ ትርጉሞች: 1) "70 ጊዜ 7" (ULB) ወይም 2) "77 ጊዜ"፡፡ ቁጥርን መጠቀም ግራ የሚያጋባ ከሆነ እንዲህ ማለት ትችላለህ “መቁጠር ከማትችለው ቁጥር በላይ" ( ተመልከት)
አንድ አገልጋይ አመጡ "አንድ ሰው ከንጉሡ አገልጋዮች መካከል አንድ ሰው አመጣ" ( ተመልከት) ዐስር ሺህ መክልት "10,000 መክልቶች" ወይም "አገልጋዩ መክፍለል ከሚችለው በላይ" ( ተመልከት) አለቃው ተሸጦ ክፍያው እንዲፈጸም አዘዘ "ንጉሡ ይህ ሰው እንዲሸጥና ከሽያጩ ላይ እዳው እንዲከፈል አዘዘ"
በፊቱ ወድቆ በመስገድ "በጉልበቱ ወድቆ አንገቱን ወደ ታች ደፍቶ" በእርሱ ፊት "በንጉሡ ፊት" ለቀቀው "እንዲሄድ ፈቀለትet him"
አንድ መቶ ዲናር "100 ዲናር" ወይም "የመቶ ቀን የሥራ ክፍያ ( ተመልከት) ያዘው "አሰረው" ወይም “ያዘው" (UDB) በፊቱ ወደቀ . . . ታገሰኝ እና እከፍልሃለሁ ይህንን በ MAT 18:26 ላይ “በፊቱ ወደቀ . . . ታገሰኝ እና እከፍልሃለሁ” በተረጎምከው መሠረት ትርጉመው፡፡ ( ተመልከት)
ከዚያም የአገልጋዩ ጌታ ጠራው "ከዚያ ንጉሡ የመጀመሪያውን አገልጋይ ጠርቶት" አይገባህምን "አይገባህምን” ( ተመልከት)
ማቴዎስ 18፡ 34-35
1 እንዲህም ሆነ፤ ኢየሱስ ንግግሩን በጨረሰ ጊዜ ገሊላን ትቶ፣ በዮርዳኖስ ወንዝ ማዶ ወዳለው ወደ ይሁዳ ጠረፍ መጣ፡፡ 2 ብዙ ሕዝብ ተከተሉት፤ እዚያም ፈወሳቸው፡፡ 3 ፈሪሳውያን እንዲህ በማለት ሊፈትኑት ወደ እርሱ መጡ፤ "በማንኛውም ምክንያት ሰው ሚስቱን ቢፈታ ሕጋዊ ነውን?" 4 ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አለ፣ "ከመጀመሪያው የፈጠራቸው እግዚአብሔር ወንድና ሴት አድርጎ እንደ ፈጠራቸውና 5 ደግሞም፣ 'በዚህ ምክንያት ሰው አባቱንና እናቱን ትቶ ከሚስቱ ጋር ይጣመራል፤ አንድ ሥጋም ይሆናሉ' የተባለውን አላነበባችሁምን? 6 ስለዚህ እነርሱ ከእንግዲህ አንድ ሥጋ እንጂ ሁለት አይደሉም፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር አንድ ላይ ያጣመረውን፣ ማንም አይለየው፡፡›› 7 እነርሱ፣ "ታዲያ የፍቺ የምስክር ወረቀት ሰጥተን ከዚያ በኋላ እንድናባርራት ሙሴ ለምን አዘዘን?" አሉት፡፡ 8 ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፣ "ከልባችሁ ድንዳኔ የተነሣ ሚስቶቻችሁን እንድትፈቱ ሙሴ ፈቀደላችሁ፤ ነገር ግን ከመጀመሪያው እንደዚያ አልነበረም፡፡ 9 እኔ እላችኋለሁ፣ ከዝሙት በቀር ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ፣ ሌላይቱንም የሚያገባ ያመነዝራል፤ የተፈታችውንም የሚያገባ ያመነዝራል፡፡" 10 ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስን፣ "የባልና የሚስት ጉዳይ እንዲህ ከሆነ ማግባት ጥሩ አይደለም" አሉት፡፡ 11 ኢየሱስ ግን እንዲህ አላቸው፤ "እንዲቀበሉት የተፈቀደላቸው እንጂ፣ ሁሉም ሰው ይህን ትምህርት አይቀበለውም፡፡ 12 በተፈጥሮ ከእናታቸው ማኅፀን ስልብ ሆነው የተወለዱ አሉና፡፡ ሰዎች የሰለቧቸውም ይገኛሉ፡፡ ስለ መንግሥተ ሰማያት ሲሉም ራሳቸውን ስልብ ያደረጉ አሉ፡፡ ይህን ትምህርት መቀበል የሚችል፣ ይቀበለው፡፡›› 13 በዚያን ጊዜ እጁን ጭኖ እንዲጸልይላቸው ሰዎች ልጆችን ወደ እርሱ አመጡ፤ ደቀ መዛሙርቱ ግን ገሠጿቸው፡፡ 14 ኢየሱስ ግን፣ "ልጆቹን ተዉአቸው፤ ወደ እኔም እንዲመጡ አትከልክሏቸው፤ መንግሥተ ሰማያት እንደነዚህ ላሉት ናትና" አለ፡፡ 15 15 እጁንም በልጆቹ ላይ ጫነባቸው፤ ከዚያም ያን ቦታ ትቶ ሄደ፡፡ 16 እነሆ፣ አንድ ሰው ወደ ኢየሱስ መጥቶ፣ ‹‹መምህር ሆይ፣ የዘላለም ሕይወት እንዳገኝ ምን መልካም ነገር ማድረግ አለብኝ?›› አለ፡፡ 17 ኢየሱስ፣ ‹‹ስለ መልካም ነገር ለምን ትጠይቀኛለህ? መልካም አንድ ብቻ ነው፤ ነገር ግን ወደ ሕይወት ለመግባት ብትፈልግ ትእዛዛትን ጠብቅ›› አለው፡፡ 18 ሰውዬው፣ ‹‹የትኞቹን ትእዛዛት? አለ፡፡ ኢየሱስ እንዲህ አለው፤ "አትግደል፤" "አታመንዝር" "አትስረቅ፤" "በሐሰት አትመስክር፤" 19 "አባትህንና እናትህን አክብር፤" እንዲሁም፣ "ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ፡፡" 20 ወጣቱ፣ "እነዚህን ነገሮች ሁሉ ፈጽሜአለሁ፣ ሌላስ ምን ያስፈልገኛል?" አለው፡፡ 21 ኢየሱስ እንዲህ አለው፤ "ፍጹም ለመሆን ብትፈልግ፣ ሂድና ያለህን ሽጠህ ለድኾችም ስጠው፤ በሰማይም ሀብት ይኖርሃል፡፡ ከዚያም መጥተህ ተከተለኝ፡፡›› 22 ነገር ግን ወጣቱ ኢየሱስ የተናገረውን በሰማ ጊዜ፣ ብዙ ንብረት ነበረውና ዐዝኖ ሄደ፡፡ 23 ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እንዲህ አላቸው፤ "እውነት እላችኋለሁ፤ ለባለ ጠጋ ወደ መንግሥተ ሰማያት መግባት ከባድ ነው፡፡ 24 ደግሜ እላችኋለሁ፤ ለባለ ጠጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከመግባት፣ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢያልፍ ይቀላል፡፡" 25 ደቀ መዛሙርቱ ይህን በሰሙ ጊዜ በጣም ተደነቁና፣ "ታዲያ ማን ሊድን ይችላል?" አሉ፡፡ 26 ኢየሱስ ወደ እነርሱ ተመልክቶ፣ "ይህ ለሰዎች የማይቻል ነው፤ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ሁሉ ይቻላል" አለ፡፡ 27 ከዚያም ጴጥሮስ መልሶ፣ "ተመልከት፣ እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ፤ ታዲያ ምን እናገኛለን?" አለ፡፡ 28 ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፤ "እውነት እላችኋለሁ፣ እናንተ እኔን የተከተላችሁኝ፣ በዐዲሱ ልደት የሰው ልጅ በክብሩ ዙፋን ላይ በሚቀመጥበት ጊዜ፣ እናንተም በዐሥራ ሁለት ዙፋኖች ላይ ትቀመጣላችሁ፤ በዐሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶችም ላይ ትፈርዳላችሁ፡፡ 29 ስለ ስሜ ቤቶችን፣ ወንድሞችን፣ እኅቶችን፣ አባትን፣ እናትን፣ ልጆችን፣ ወይም ርስትን የተወ ሁሉ፣ መቶ እጥፍ ይቀበላል፣ የዘላለምንም ሕይወት ይወርሳል፡፡ 30 ነገር ግን አሁን ፊተኞች የሆኑ ብዙዎች ኋለኞች ይሆናሉ፤ ኋለኞች የሆኑ ብዙዎችም ፊተኞች ይሆናሉ፡፡
ከዚያ በኋላ በቋንቋችሁ የአንድን ታሪክ አዲስ ክፍል ለመጀመር የሚያገለግል ቃል ካለ ይህንን ቃል ተጠቀሙ፡፡ እነዚህ ቃላት የ . . . ቃላት MAT 18:1-35 ተለየ "ከእነርሱ ራቀ” ወይም "ተዋቸው" በዚያው ክልል ውስጥ "በዚያው አከባቢ"
ወደ እርሱ መጣ "ወደ ኢየሱስ መጣ" አላነበባችሁምን . . . ሴት? ኢየሱስ ፈሪሳዊያኑን ሊያሳፍራቸው ፈልጎሏል፡፡ ( ተመልከት)
እንዲሁም እንዲህ አለ .. . ሥጋ? በ MAT 19:3 ላይ የተጀመረው ጥያቄ የቀጠለ ነው፡ "በተጨማሪም እንዲህ የሚል ነገር አላነባችሁምን . . . ሥጋ?" ( እና ተመልከት) ከምስቱ ጋር ይጣበቃል "ከምስቱ ጋር ይቀራረባል" አንድ ሥጋ "አንድ ሰው"
እንዲህ አሉት "ፈሪሳዊያኑ ለኢየሱስ አንዲህ አሉት" አዞናል "አይሁዳዊ እንደመሆናችን እንዲህ ታዘናል" የፊች ወረቀት ጋብቻው ሕጋዊ በሆነ መንገድ መቆሙን የሚሳይ ወረቅት ከመጀመሪያው ግን እንዲህ አልነበረም "እግዚብሔር ወንድን እና ሴትን ሲፈጥር መቼም ቢሆን እንድፋቱ አልነበረም" የተፈታቸችሁንም የሚያገባ ማንኛውም ሰው ያመነዝራል ብዙዎቹ የጥንት ቅጂዎች እነዚህንን ቃላት አይጨምሩትም፡፡
ራሱን ጃንደረባ ያደረገ አማራጭ ትርጉሞች 1) "የግል አካሉን ቆርጦ የጣለ” ወይም 2) "ላለማግባት እና ምንም ዓይነት ግብረስጋ ግንኙነት ላለማድረግ የወሰነ ሰው” ( ተመልከት) ለመንግስተ ሰማያት ሲል "እግዚአብሔርን ይበልጥ ለማገልገል ይችል ዘንድ" ይህንን ትምህርት ተቀበል . . . ተቀበል “ይህንን ትምህርት ተቀበል . . . ተቀበል” የሚለው በ19፡11 ላይ እንዴት እንደተረጎምከተው ተመልከት፡፡
ሕጻናትን ወደ እርሱ አመጡ ለተርጓሚዎች ምክት፡ “አንዳንድ ሰዎች ሕጻናትን ወደ ኢየሱስ አመጡ፡፡” ( ተመልከት) ፈቃድ "ፍቀዱ" ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ አትከልክሏቸው "ወደ እኔ እንዳይመጡ አትከልክሏቸው" የመንግስተ ሰማያት እንደነዚህ ላሉት ናትና "መንግስተ ሰማየት እንደነዚህ ላሉ ሰዎች ናትና” ወይም “ልክ እንደነዚህ ሕጻናት የሆኑ ሰዎች ብቻ ናቸው ወደ መንግስተ ሰማያት መግባት የሚችሉት"
እነሆ ይህ ቃል ሰዎች ከዚህ በኋላ ለሚነገረው ነገር አጽኖት እንዲሰጡ የሚጨመር ቃል ነው፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ተመልከቱ” ወይም “አድምጡ” ወይም “አሁን ለምነግራችሁ ነገር ትኩረት ስጡ”:: መልካም ነገር እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ነገር
ምኞት "ፍላጎት"
ሀብታም ወደ እግዚአብሔር መንግስት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ብትሾልክ ይቀላል ለሀብታም ወደ እግዚአብሔር መንግስር መግባት በጣም ከባድ ነው ( ተመልከት) የመርፌ ቀዳዳ ለክር ማስገቢያ የሚሆን በመርፌ አናት ላይ የሚገኝ ቀዳዳ
በጣም ተገረሙ "ደቀ መዛሙርቱ ተደነቁ" ማን ልድን ይችላል? አማራጭ ትርጉሞች: 1) መልስ እየፈለጉ ነው ወይም 2) ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ማንም ሊድን አይችልም!” ( ተመልከት) እኛ ሁሉን ነገር ተውን "ሀብታችንን ሁሉ ተውን" ወይም "ያለንን ነገር ሁሉ ተውን" ታዲያ ምን እናገኛለን? "እግዚአብሔር ለእኛ ምን መልካም ነገር ይሰጠናል?"
አዲስ ልደት "ሁሉ ነገር አዲስ በሚሆንበት ጊዜ” ወይም "በአዲሱ ዘመን" በዐሥራ ሁለቱ ዙፋናት ላይ ትቀመጣላችሁ፣ ትርዳላችሁ "ነገሥታት እና ፈራጆች ትሆናላችሁ"
መቶ እጥፍ ትቀበላላችሁ "የተዋቿቸውን መልካም ነገሮች ሁሉ በመቶ እጥፍ ትቀበላላችሁ" አሁን መጀመሪያ የነበሩ ብዙዎች መጨረሻ ሆነዋል በሰዎች ዐይን መጀመሪያ የነበሩት ማለትም ሀብታሞች እና ሌሎችን የሚዙ ሰዎች በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ አንድ ቀን መጨረሻ ይናሉ፡፡
1 መንግሥተ ሰማይ ለወይኑ አትክልት ሠራተኞችን ሊቀጥር ማልዶ የወጣ ባለቤትን ትመስላለች። 2 በቀን አንዳንድ ዲናር ሊከፍላቸው ከሠራተኞቹ ጋር ከተስማማ በኋላ፣ ወደ ወይኑ አትክልት ስፍራ ላካቸው። 3 ደግሞም በሦስት ሰዓት ገደማ ወጥቶ በገበያ ቦታ ሥራ ፈትተው የቆሙ ሌሎች ሠራተኞችን አየና፣ 4 'እናንተ ደግሞ ወደ ወይኑ አትክልት ስፍራ ሂዱ፤ የሚገባችሁንም እከፍላችኋለሁ' አላቸው። ስለዚህ እነርሱም ሊሠሩ ሄዱ። 5 ደግሞ በስድስት ሰዓትና በዘጠኝ ሰዓት ገደማ ወጥቶ እንደዚሁ አደረገ። 6 አሁንም በዐሥራ አንደኛው ሰዓት ገደማ ወጥቶ ሥራ ፈትተው የቆሙ ሌሎችን አገኘ። እነርሱንም፣ 'ቀኑን ሙሉ ሥራ ፈትታችሁ እዚህ ለምን ቆማችኋል?' አላቸው። 7 'ማንም ስላልቀጠረን ነው' አሉት። 'እናንተም ደግሞ ወደ ወይኑ አትክልት ስፍራ ሂዱ' አላቸው። 8 ቀኑ በመሸ ጊዜ፣ የወይኑ አትክልት ባለቤት ሥራ አስኪያጁን፣ 'ሠራተኞቹን ጥራ ከኋለኞቹ አንሥተህ እስከ ፊተኞቹ የሠሩበትን ገንዘብ ክፈላቸው' አለው። 9 በዐሥራ አንደኛው ሰዓት የተቀጠሩት ሠራተኞች በመጡ ጊዜ፣ እያንዳንዳቸው አንዳንድ ዲናር ተቀበሉ። 10 ፊተኞቹ ሠራተኞች በመጡ ጊዜ፣ የበለጠ የሚቀበሉ መሰላቸው፤ ነገር ግን እነርሱም ደግም እያንዳንዳቸው አንዳንድ ዲናር ተቀበሉ። 11 ገንዘባቸውን በተቀበሉ ጊዜ፣ በወይኑ አትክልት ባለቤት ላይ አጕረመረሙ። 12 እንዲህም አሉ፤ 'እነዚህ በመጨረሻ የመጡ ሠራተኞች በሥራ ላይ አንድ ሰዓት ብቻ አሳልፈዋል፤ ነገር ግን አንተ የዕለቱን ሸክምና የሚለበልበውን ሙቀት ከተሸከምነው ከእኛ ጋር እኩል አድርገሃቸዋል።' 13 ባለቤቱ ግን መልሶ ከእነርሱ አንዱን እንዲህ አለው፤ "ወዳጄ ሆይ፣ አልበደልኩህም። ከእኔ ጋር በአንድ ዲናር አልተስማማህምን? 14 የሚገባህን ተቀብለህ መንገድህን ሂድ፤ ለእነዚህ በመጨረሻ ለተቀጠሩት ሠራተኞች ልክ እንደ አንተው ልሰጣቸው ደስ ይለኛል። 15 በገዛ ንብረቴ የፈለግሁትን ማድረግ አይገባኝምን? ወይስ እኔ ደግ ስለ ሆንሁ ትመቀኛለህን? 16 ስለዚህ ኋለኞች ፊተኞች፣ ፊተኞችም ኋለኞች ይሆናሉ።" 17 ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም ይወጣ ስለ ነበር፣ ዐሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርት ለብቻቸው ወሰደ፤ በመንገድ ላይም እንዲህ አላቸው፦ 18 እነሆ ወደ ኢየሩሳሌም እንወጣለን፤ የሰው ልጅም ለካህናት አለቆችና ለሕግ መምህራን ተላልፎ ይሰጣል። ሞትም ይፈርዱበታል፤ 19 እንዲዘብቱበት፣ እንዲገርፉት፣ እንዲሰቅሉትም ለአሕዛብ ይሰጡታል። ነገር ግን በሦስተኛው ቀን ይነሣል።" 20 በዚያን ጊዜ የዘብዴዎስ ልጆች እናት ከልጆቿ ጋር ወደ ኢየሱስ መጣች፤ በፊቱ ተንበርክካም ከእርሱ አንድ ነገር ለመነች። 21 ኢየሱስ፣ "ምን ትፈልጊያለሽ?" አላት። እርሷም፣ "በመንግሥትህ እነዚህ ሁለት ልጆቼ አንዱ በቀኝህ፣ አንዱም በግራህ እንዲቀመጡ እዘዝ" አለችው። 22 ኢየሱስ ግን መልሶ፣ "የምትለምኑትን አታውቁም። እኔ የምጠጣውን ጽዋ መጠጣት ትችላላችሁን?" አለ። እነርሱ፣ "እንችላለን" አሉት። 23 ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፤ "በርግጥ ጽዋዬን ትጠጣላችሁ። በቀኜና በግራዬ መቀመጥን የምሰጥ ግን እኔ አይደለሁም፤ ነገር ግን በአባቴ ለተዘጋጀላቸው ለእነርሱ ነው።" 24 ሌሎቹ ዐሥሩ ደቀ መዛሙርት ይህን በሰሙ ጊዜ፣ በሁለቱ ወንድማማች ላይ ተቈጡ። 25 ነገር ግን ኢየሱስ ወደ ራሱ ጠርቶ እንዲህ አላቸው፣ "የአሕዛብ አለቆች ሕዝባቸውን ጨቊነው ይገዛሉ፤ የበላዮቻቸውም ይሠለጥኑባቸዋል። 26 በእናንተ መካከል ግን እንዲህ መደረግ የለበትም። ይልቁንም፣ ከእናንተ መካከል ታላቅ ሊሆን የሚፈልግ ሁሉ አገልጋያችሁ ይሁን፤ 27 ከእናንተም ፊተኛ ሊሆን የሚፈልግ ሁሉ አገልጋያችሁ ይሁን። 28 የሰው ልጅ ሊያገለግል፣ ሕይወቱንም ለብዙዎች ቤዛ አድርጎ ሊሰጥ እንጂ፣ እንዲያገለግሉት አልመጣም።" 29 ከኢያሪኮ እንደ ወጡ፣ ብዙ ሕዝብ ኢየሱስን ተከተሉት። 30 እነሆ፣ ሁለት ዐይነ ስውሮች በመንገድ ዳር ተቀምጠው ነበር፤ ኢየሱስ ሲያልፍ በሰሙ ጊዜ ጮኽ ብለው፣ "ጌታ ሆይ፣ የዳዊት ልጅ፣ ማረን" አሉ። 31 ሕዝቡ ግን ዝም እንዲሉ በመንገር ገሠጿቸው። ይሁን እንጂ፣ እነርሱ አብዝተው በመጮኽ፣ "ጌታ ሆይ፣ የዳዊት ልጅ ማረን" አሉ። 32 በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ቆም ብሎ ጠራቸውና፣ "ምን እንዳደርግላችሁ ትፈልጋላችሁ?" አለ። 33 እነርሱም፣ "ጌታ ሆይ፣ ዐይኖቻችን እንዲከፈቱ ነው" አሉት። 34 ከዚያም ኢየሱስ ራርቶ፣ ዐይኖቻቸውን ዳሰሰ። እነርሱም ወዲያውኑ አይተው ተከተሉት።
መንግስ ሰማያት የመሬት ባለቤትን ትመስላለች እግዚአብሔር በሁሉም ነገር ላይ ያለው አገዛዝ አንድ ባለመሬት መሬቱን የሚያስተዳድርበትን መንገድ ይመስላል ( ተመልከት) መንግስተ ሰማይ ትመስላለች በ MAT 13:24 ላይ በምን መልኩ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ከተስማማ በኋላ "የመሬቱ ባለቤት ከተስማማ በኋላ" በአንድ ዲናር "የአንድ ቀን ገቢ" ( ተመልከት)
እንደ ገና ወጣና "የመሬቱ ባለቤት እንደገና ወጣና" ያለሥራ የቆሙተን "ምንመ የማይሠሩትን” ወይም “ሥራ ያሌላቸውን"
እንደ ገና ወጣና "የመሬቱ ባለቤት እንደገና ወጣና" ያለሥራ የቆሙተን "ምንመ የማይሠሩትን” ወይም “ሥራ ያሌላቸውን"
ለእያንዳንዱ "በዐሥራ አንድ ሰዓት መሥራት ለጀመረውም ለእያንዳንዱ" አንድ ዲናር "የአንድ ቀን ገቢ" ( ተመልከት) እነርሱ እነንዲህ አሰቡ "ረጅም ሰዓት የሠሩት ሠራተኞች እንዲህ አሰቡ"
በተቀበሉ ጊዜ "ረጀም ሰዓት ስሰሩ የነበሩት ሠራተኞች ስቀበሉ" ባለቤቱ "የመሬቱ ባለቤት" ወይም "የወይን እርሻው ባለቤት" የቀኑንም ድካምና ትኩሳት ከተሸከምን "በጠራራ ፀሐይ ቀኑን ሙሉ ሥንሠራ የነበርን"
ከመካከላቸው አንዱ "ረጅሙን ሰዓት ከሠሩት ሠራተኞች መካከል አንዱ" ወዳጆቼ በዚህ ሥፍራ ላይ አንድ ሰው ሌላኛውን ሰው በትህትና ለመገሰጽ የሚጠቀምበትን ቃል ተጠቀም፡፡ በአንድ ዲናር ለመሥራት ከእኔ ጋር አልተስማማችሁምን? ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ለሥራችሁ ዋጋ አንድ ዲናር ለመክፈል ተስማሚቼያለሁ፡፡ (en:ta:vol1:translate: ተመልከት) አንድ ዲናር "የአንድ ቀን ገቢ" ( ተመልከት) መስጠት እወዳለሁ "መስጠት ያስደስተኛል” ወይም “መስጠት እወዳለሁ”
በራሴ ሀብት የፈለኩትን የማድረግ መብት የለኝምን? ለተርጓሚዎች ምክር፡ "በራሴ ሀብት የፈለኩትን ማድረግ እችላለሁ” መብት "ሕጋዊ" ወይም "ፍትሐዊ" ወይም "ትክክል" ወይም እኔ መልካም ስለሆንኩ ቀናችሁን? "ለማይገባቸው ሰዎች መልካም በማድረጌ አልተደሰታችሁምን"
እንሄዳለን ኢየሱስ እና ደቀ መዛሙርቱ የሰው ልጅን አሳልፈው ይሰጡታል "አንድ ሰው የሰው ልጅን አሳልፎ ይሰጠዋል" ይፈርዱበታል. . . እና አሕዛብ ይዘባበቱበት ዘንድ አሳልፎ ይሰጣል የካህናት አለቆች እና ፀሐፍት ይፈርዱበታል እንዲሁም ለአሕዛብ አሳልፈው ይሰጡታል፤ አሕዛብም ይዘባበቱበታል ይነሳል "እግዚብሔር ያስነሳዋል”
በቀኝህ በኩል . . . በግራህ በኩል ሥልጣን ያለው ቦታ
አናንተ እናት እና ልጆች ትችላለህን...ለመጠጣት? "ለመጠጣት . . . ትችላለህን?" ኢየሱስ ይህን የተናረው ለልጆች ብቻ ነው፡፡ አሁን ልጠጣው ያለሂትን ጽዋ ጠጣ "አሁን ልቀበለው ያለሁትን መከራ ውስጥ እለፍ" እነርሱ ልጆች በአባቴ ለተዘጋጀላቸው ነው "ከአጠገቤ በክብር መቀመጥ ይህንን ክብር አባቴ ላዘጋጀላቸው ነው" መዘጋጀት የተዘጋጀላቸው
የአሕዛብ ገዥዎች ይገዟቸዋል "የአሕዛብ ገዥዎች ገዥው የፈለገውን ነገር እንዲያደር ሕዝቡን ያዛሉ" እርሱ በጣም አስፈለጊ ሰው ናቸው በገዥዎች ስልጣን የተሰጣቸው ሰዎች በእነርሱ ላይ ስልጣን አላቸው "ይቆጣጠሯቸዋል" ፍላጎት "ፍላጎት" ወይም "መሻት" ሕይወት መስጠት "ለመሞት መፈለግ"
እንደፈለጉ ለደቀ መዛሙርቱ እና ኢየሱስ ተከተሉት "ኢየሱስን ተከተሉ" እናም ተመለከቱ አንዳንድ ጊዜ “እነሆነ” ተብሎ ተተርጉሟል፡፡ ጸሐፊው ከዚህ በመቀጠል ለሚመጣው ነገር ትኩርት እንዲሰጠው ይፈልጋል፡፡ ይህንን ለማድረግ የሚያስችል ነገር በቋንቋችሁ ውስጥ ይኖራል፡፡ በዚያ ስያልፉ "በዚያ ሥያልፉ" ይበልጥ ድምጻቸው አሰመተው ጮኹ "ዐይነ ሥውራኑ ከበፊቱ ይልቅ አብዝተው ጮኹ” ወይም “ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ጮኹ"
ጠራቸው ዐይነ ሥውራኑን ጠራቸው ፍላጎት "ፍላጎት" እናይ ዘንድ እንወዳለን ለተርጓማች ምክር፡ “ማየት እንችል ዘንድ ታደርግ ዘንድ እንወዳለን" ወይም "ማየት እንችል ዘንድ እንወዳለን ራራላቸው "ራራላቸው” ወይም "ለእነርሱ ራራ"
1 ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሩሳሌም እንደቀረቡ፣ በደብረ ዘይት ወዳለው ወደ ቤተ ፋጌ መጡ፤ 2 ከዚያም ኢየሱስ እንዲህ በማለት ሁለት ደቀ መዛሙርት ላከ፤ “ወደሚቀጥለው መንደር ሂዱ፤ አህያም ከነውርንጫዋ ታስራ ታገኛላችሁ። ፈትታችሁ ወደ እኔ አምጧቸው፤ 3 ማንም ስለዚያ አንዳች ቢናገራችሁ፣ እርሱም ከእናንተ ጋር ፈጥኖ ይሰዳቸዋል።” 4-5 ይህ የሆነው፣ “እነሆ፣ ንጉሥሽ ትሑት ሆኖ በአህያና በውርንጫዋ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል ብላችሁ ለጽዮን ልጅ ንገሯት” ተብሎ በነቢዩ የተተነበየው ይፈጸም ዘንድ ነው። 6 ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ ሄደው ልክ ኢየሱስ እንዳዘዛቸው አደረጉ። 7 አህያይቱንና ውርንጫዋን አመጡ፤ ልብሳቸውንም አደረጉባቸውና ኢየሱስ ተቀመጠባቸው። 8 ከሕዝቡ አብዛኞቹ ልብሳቸውን በመንገድ ላይ አነጠፉ፣ ሌሎችም የዘንባባ ዝንጣፊ እየቈረጡ በመንገድ ላይ አደረጉ። 9 ከኢየሱስ ፊት ይሄዱ የነበሩትና የተከተሉትም ሕዝብ፣ “ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ እርሱ የተባረከ ነው። ሆሣዕና በአርያም ይሁን!” በማለት ጮኹ። 10 ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም በመጣ ጊዜ ከተማይቱ በሞላ ታወከችና፣ “ይህ ማን ነው?” አለች። 11 ሕዝቡ፣ “ይህ ከገሊላ ናዝሬት የሆነው ነቢዩ ኢየሱስ ነው” ብለው መለሱ። 12 ከዚያም ኢየሱስ ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሄደ። በቤተ መቅደስ የሚሸጡትንና የሚገዙትን አስወጣ። የገንዘብ ለዋጮችን ጠረጴዛዎችና ወንበሮች ገለበጠ። 13 እንዲህም አላቸው፤ ‘ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል’ ተብሎ ተጽፏል። እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት።" 14 ከዚያም ዐይነ ስውሮችና ሽባዎች ወደ እርሱ ወደ ቤተ መቅደስ መጡ፤ እርሱም ፈወሳቸው። 15 ነገር ግን የካህናት አለቆችና የሕግ መምህራን እርሱ ያደረጋቸውን ድንቅ ነገሮች ባዩና በቤተ መቅደስ ልጆች፣ “ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ” በማለት ሲጮኹ በሰሙ ጊዜ፣ ተቈጡ። 16 “ሕዝቡ የሚሉትን ትሰማለህን?” አሉት። ኢየሱስ፣ “አዎ! ነገር ግን ‘ከሕፃናትና ከሚጠቡት አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ’ የሚለውን ከቶ አላነበባችሁምን?” አላቸው። 17 ከዚያም ኢየሱስ ትቷቸው ከከተማው ወጣና ወደ ቢታንያ ሄዶ በዚያ ዐደረ። 18 ኢየሱስ ጠዋት ወደ ከተማው እንደተመለሰ፣ ተራበ። 19 በመንገድ ዳር አንዲት የበለስስ ተክል አየና ወደ እርሷ ሄደ፤ ነገር ግን ከቅጠል በቀር ምንም አላገኘባትም። “ሁለተኛ ከቶ ፍሬ አይገኝብሽ” አላት። የበለስ ተክሊቱም ወዲያውኑ ደረቀች። 20 ደቀ መዛሙርቱ ባዩአት ጊዜ ተደንቀው፣ “የበለስ ተክሊቱ እንዴት ወዲያውኑ ደረቀች?” አሉ። 21 ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አላቸው፤ "እውነት እላችኋለሁ፣ እምነት ቢኖራችሁና ባትጠራጠሩ፣ በዚች የበለስ ተክል የሆነባትን ብቻ ሳይሆን፣ ይህን ኮረብታ ከዚህ ተነሥተህ ወደ ባሕር ተወርወር ብትሉት እንኳ ይሆናል። 22 አምናችሁ በጸሎት የምትለምኑትን ሁሉ ትቀበላላችሁ።” 23 ኢየሱስ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ ሲያስተምር የካህናት አለቆችና የሕዝቡ ሽማግሌዎች ወደ እርሱ መጥተው፣ “በምን ሥልጣን እነዚህን ነገሮች ታደርጋለህ? ይህንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ?” አሉ። 24 ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አላቸው፤ “እኔ ደግሞ አንድ ጥያቄ እጠይቃችኋለሁ። ያንን ከነገራችሁኝ እኔ ደግሞ በማን ሥልጣን እነዚህን ነገሮች እንደማደርግ እነግራችኋለሁ። 25 የዮሐንስ ጥምቀት ከየት መጣ ከሰማይ ነውን ወይስ ከሰዎች?” እርስ በርሳቸው እንዲህ በማለት ተነጋገሩ፤ “ከሰማይ ነው ብንለው፣ ‘ለምን አታምኑትም?’ ይለናል። 26 ነገር ግን ‘ከሰው ነው ብንል፣ ዮሐንስን እንደ ነቢይ ስለሚያዩት ሕዝቡን እንፈራለን።” 27 ከዚያም መልሰው ኢየሱስን፣ “አናውቅም” አሉት። እርሱ ደግሞ፣ “እኔም በምን ሥልጣን እነዚህን ነገሮች እንደማደርግ አልነግራችሁም” አላቸው። 28 ነገር ግን ምን ይመስላችኋል? አንድ ሰው ሁለት ልጆች ነበሩት፣ ወደ መጀመሪያው ሄዶ፣ ልጄ ሆይ፣ ዛሬ ወደ ወይኑ አትክልት ስፍራ ሄደህ ሥራ’ አለው። 29 ልጁ መልሶ፣ ‘አልሄድም’ አለ፤ በኋላ ግን ዐሳቡን ለውጦ ሄደ። 30 ሰውዬውም ወደ ሁለተኛው ልጅ ሄዶ ይህንኑ ነገረው። ይህኛው ልጅ መልሶ፣ ‘እሄዳለሁ፣ አባዬ’ አለ። ነገር ግን አልሄደም። 31 ከሁለቱ ልጆች የአባቱን ትእዛዝ የፈጸመው የትኛው ነው? እነርሱ፣ "የመጀመሪያው” አሉ። ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፦ “እውነት እላችኋለሁ፣ ቀረጥ ሰብሳቢዎችና አመንዝራዎች ቀድመዋችሁ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ይገባሉ። 32 ዮሐንስ በጽድቅ መንገድ ወደ እናንተ መጥቶ ነበርና፤ እናንተ ግን አላመናችሁትም፤ ቀረጥ ሰብሳቢዎችና አመንዝራዎች ግን አመኑት። እናንተም ይህ ሲሆን አይታችሁ ታምኑት ዘንድ በኋላ እንኳ ንሰሐ አልገባችሁም። 33 ሌላም ምሳሌ ስሙ። ሰፊ መሬት ያለው አንድ ሰው ነበር። የወይን አትክልት ተከለ፤ ዐጥር አጠረለት፤ የወይን መጥመቂያ ማሰለት፤ መጠበቂያ ማማ ሠራለት፤ ለወይን ገበሬዎችም አከራይቶ ወደ ሌላ አገር ሄደ። 34 የወይን ፍሬ የሚሰበሰብበት ጊዜ እንደ ደረሰ፣ ፍሬውን እንዲቀበሉ ጥቂት አገልጋዮችን ላከ። 35 የወይኑ ገበሬዎች ግን አገልጋዮቹን ያዙ፤ አንዱን ደበደቡት፣ ሌላውን ገደሉት፤ ሌላውንም በድንጋይ ወገሩት። 36 ባለቤቱ እንደ ገና ከፊተኞቹ የበዙ ሌሎች አገልጋዮችን ላከ፤ ነገር ግን የወይን ገበሬዎቹ ያንኑ አደረጉባቸው። 37 ከዚያ በኋላ ባለቤቱ፣ ‘ልጄንስ ያከብሩታል’ በማለት የገዛ ልጁን ላከ። 38 የወይን ገበሬዎቹ ግን ልጁን ባዩ ጊዜ፣ እርስ በርሳቸው፣ 'ይህ ወራሹ ነው፤ ኑ፣ እንግደለውና ርስቱን እንውረስ’ ተባባሉ። 39 ስለዚህ ያዙትና ከወይኑ አትክልት ስፍራ ወደ ውጭ ጣሉት፤ ገደሉትም። 40 እንግዲህ የወይኑ አትክልት ባለቤት በሚመጣበት ጊዜ እነዚያን የወይን ገበሬዎች ምን ያደርጋቸዋል?” 41 ሕዝቡ እንዲህ አሉት፤ “እነዚያን ክፉ ሰዎች እጅግ በጣም አሰቃቂ በሆነ መንገድ ያጠፋቸዋል፤ ከዚያም የወይኑን አትክልት ስፍራ ወይኑ በሚያፈራበት ጊዜ ገንዘቡን ለሚከፍሉ ለሌሎች የወይን ገበሬዎች ያከራየዋል።” 42 ኢየሱስ እነርሱን፣ “ 'ግንበኞች የናቁት ድንጋይ የማዕዘን ራስ ሆነ። ይህ ከጌታ ዘንድ ሆነ፤ ለዐይኖቻችንም ድንቅ ነው ተብሎ የተጻፈውን ፈጽሞ አላነበባችሁም?’ 43 ስለዚህ እላችኋለሁ፣ የእግዚአብሔር መንግሥት ከእናንተ ትወሰድና ፍሬዋን ለሚያፈራ ሕዝብ ትሰጣለች። 44 በዚህ ድንጋይ ላይ የሚወድቅ ሁሉ ይሰባበራል። ድንጋዩ የሚወድቅበትን ሁሉ ግን ይፈጨዋል።” 45 የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን ምሳሌዎቹን በሰሙ ጊዜ፣ የተናገረው ስለ እነርሱ እንደ ሆነ ተረዱ። 46 ነገር ግን ሊይዙት በፈለጉ ጊዜ ሁሉ፣ ሰዎቹ እንደ ነቢይ ይቈጥሩት ስለ ነበር ሕዝቡን ፈሩ።
ቤተ ፋጌ
መንደር
ውርንጭላ
"ትንሽ ወንድ አህያ"
ይህ በነቢያት የተነገረው ይፈጸም ዘንድ ነው "እግዚአብሔር ስለዚህ ጉዳይ ከብዙ ዘመናት በፊት በነቢያ አማካኝነት ምን እንደሚሆን ተናግሮ ነበር” በነቢያት የተነገረው ነገር "ነገሩ ከመፈጸሙ በፊት ነቢያት አስቀድመው የተናገሩት ነገር” የጽዮን ሴት ልጅ እስራኤል አህያ ድሆች የሚጋልቡት እንስሳ ውርንጭላ ትንሽ ወንድ አህያ
ጨርቅ ከውጪ የሚደረብ ወይም ረጅም ኮት ኢየሱስ በዚያ ተቀመጠ "አህያይቱን ጨርቅ አልብሰው ኢየሱስ በዚያ ላይ እንዲቀመጥ አደረጉ"
ሆሣዕና ይህ የዕብራይስጥ ቃል ሲሂን ትርጉሙም “አድነን” ማለት ነው ይሁን እንጂ “እግዚአብሔር ይመስገንም” መሆን ይችላል፡፡ ከተማው ሁሉ ተናወጠ "በከተማይቱ ውስጥ ያሉ ሁሌ እርሱን ለማየት ጓግተው ነበር" ከተማው ሁሉ "በከተማይቱ ውስጥ ያሉ ብዙ ሰዎች"
እንዲህ አላቸው "ገንዘብ ለዋጮቹን እና የተለያዩ ነገሮችን የሚገዙትን እና የሚሸጡትን ሰዎች" የጸሎት ቤት "ሰዎች የሚጸልዩበት ሥፍራ" የወንበዴዎች ዋሻ "እንደ ወንበዴዎች መሸሸጊያ ዋሻ” አንካሳ በጣም ከመጎዳታቸው የተነሳ መራመድ የማይችሉ ሰዎች
ሆሣዕና በ MAT 21:09 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምው ተመልከት፡፡ የዳዊት ልጅ በ MAT 21:09 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ተቆጡ "ኢየሱስን ጠሉት እንዲሁም በጣም ተበሳጩበት" እነዚህ ሰዎች የሚሉትን አትሰማምን? "ሰዎች ስለአንተ እንዲህ ዓይነት ንግግር እንዲያደርጉ ልትፈቅድላቸው አይገባም!" ይሁን እንጂ ፈጽሞ አላነበባችሁምን . . . ምስጋና'? "አዎ አየሰማኋቸው ነው ይሁን እንጂ በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ያነበባችሁት ማስታወስ ይገባችሁ ነበር . . . ምሳጋና" ኢየሱስ ትቷቸው ሄደ "ኢየሱስ የካህናት አለቆችንና ጸሐፊትን ትቶ ሄደ"
ደረቀ "ሞተ" ማቴዎስ 21፡20-21
እምነት ካላችሁና የማትጠራጠሩ ከሆነ እነዚህ ሁለት ሀረጎች የሚስተላልፉት ተመሳሳይ ሀሳብ ነው፡፡ ሁለት ጊዜ የተጻፈው አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ በአንዳንድ ቋንቋዎች ውስጥ አጽኖት መስጫ ሌላ መንገድ አለ፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “በእርግጥ ካመናችሁ” ወዲያው ደረቀ "ደርቆ ሞተ"
እምነት ካላችሁና የማትጠራጠሩ ከሆነ እነዚህ ሁለት ሀረጎች የሚስተላልፉት ተመሳሳይ ሀሳብ ነው፡፡ ሁለት ጊዜ የተጻፈው አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ በአንዳንድ ቋንቋዎች ውስጥ አጽኖት መስጫ ሌላ መንገድ አለ፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “በእርግጥ ካመናችሁ” ወዲያው ደረቀ "ደርቆ ሞተ"
ማቴዎስ 21፡25-27
ከሰማይ "በሰማይ ካለው እግዚአብሔር” እንዲህ ይለናል "ኢየሱስ እንዲህ ይለናል" ሕዝቡን ፈራን "ሕዝቡ ምን እንደሚያስብ ፈራን ወይም ምን እንደሚያደርግብን ፈራን" ዮሐንስን ነብይ አድርገው ይቆጥሩት ነበር "ዮሐንስ ነብይ እንደሆነ ያምኑ ነበር"
እንዲህ አሉ "የካህናት አለቆችና ሽምግሌዎች እንዲህ አሉ" ኢየሱስ አንዲህ አላቸው "ኢየሱስ ለካህናት አለቆችና ለሽማግሌዎች እንዲህ አላቸው" ዮሐንስ ወደ እናንተ መጣ ዮሐንስ ወደ ሃይማኖት መሪዎች እና ሕዘቡ መጥቶ ሰበከ፡፡ በጽድቅን መንገድ ዮሐንስ ሰዎች እንዴት ለእግዚአብሔት ምላሽ መስጠት እንዳለባቸው እና መኖር እንዳለባቸው አሳየ
ትልቅ መሬት ያለው አንድ ሰው "ብዙ ሀብት ያለው አንድ ሰው" ለወይን ተካዮች መሬቱን አከራየ "ወይን የሚያመርቱ ሰዎችን በቦታው ላይ ሾመ” የወይን እርሻው ባለቤት ግን አሁንም ቢሆን የመሬቱ ባለቤት ነው፡፡ የወይን ተክል የሚተክሉ ሰዎች ወይንን እንዴት መትከል እና ማሳደግ እንደሚቻል የሚያውቁ ሰዎች
ሠራተኞችን የመሬቱ ባለቤት ሠራተኞች (MAT 21:33)
ሰዎች እንዲህ አሉት "ሕዝቡ ለኢየሱስ እንዲህ አሉት"
ኢየሱስ እንዲህ አላቸው "ኢየሱስ ለሕዝቡ እንዲህ ብሎ ተናገረ" (MAT 21:41) ግንበኞች የናቁት ድንጋጥ የማዕዘን ራስ ሆነ፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "በአናጽዋች የናቁት ድንጋይ በጣም አስፈላጊው ድንጋይ ሆነ፡፡” ባለስልጣናቱ ኢየሱስን ባይቀበሉትም ነገር ግን እግዚአብሔር የመንግስቱ ራስ ያደርገዋል፡፡ “ ይህ ከጌታ ነው "ይህንን ታላቅ ለውጥ ያመጣው ጌታ ነው"
እላችኋለሁ ኢየሱስ ለካህናት አለቆች እና ሽማግሌዎች እንዲህ አላቸው፡፡ ፍሬውን ተንከባቡ "ትክክለኛውን ነገር አድርጉ ፍሬውን "የእግዚአብሔር መንግስ ፍሬ" በዚህ ድንጋይ ላይ የሚወድቅ ማንም ሰው "በዚህ ድንጋይ የሚሰናከል ማንም ቢኖር የሚወድቅበት ማንም ሰው "ፍርዱ የሚመጣበት ማንም ሰው
የእርሱ ምሳሌዎች "የኢየሱስ ምሳሌዎች" እጃቸውን በእርሱ ላይ አኖሩ "አሰሩት"
1 ኢየሱስም ደግሞ እንዲህ በማለት በምሳሌ መለሰላቸው፤ 2 "መንግሥተ ሰማይ ለልጁ የሰርግ ድግስ የደገሰ ንጉሥን ትመስላለች፡፡ 3 ወደ ሰርጉ እንዲመጡ ወደ ጋበዛቸው ሰዎች አገልጋዮቹን ላከ፤ እነርሱ ግን መምጣት አልፈለጉም፡፡ 4 እንደ ገና ንጉሡ ሌሎች አገልጋዮችን እንዲህ በማለት ላከ፤ "እነሆ፣ እራት አዘጋጅቻለሁ፤ በሬዎቼንና የሰቡ ወይፈኖቼን አርጃለሁ፤ ሁሉም ተዘጋጅቶአልና ወደ ሰርግ ግብዣው ኑ በሏቸው፡፡' " 5 ሰዎቹ ግን ግብዣውን ከልብ አልተቀበሉትም፡፡ አንዳንዶቹ ወደ እርሻዎቻቸው፣ ሌሎች ደግሞ ወደ ሥራ ቦታቸው ሄዱ፡፡ 6 አንዳንዶቹ የንጉሡን አገልጋዮች ደበደቡአቸው፤ አዋረዱአቸው፤ ገደሉአቸው፡፡ 7 ንጉሡ ግን ተቈጣ፤ ወታደሮቹን ላከ፤ እነዚያን ነፍሰ ገዳዮች ገደለ፤ ከተማቸውንም አቃጠለ፡፡ 8 ከዚያም ለአገልጋዮቹ እንዲህ አለ፤ 'ሰርጉ ተዘጋጅቶአል፤ ጥሪ የተደረገላቸው ሰዎች ግን የሚገባቸው ሆነው አልተገኙም፡፡ 9 ስለዚህ ወደ ዐውራ መንገድ ማቋረጫ ሄዳችሁ የምታገኙአቸውን ያህል ሰዎች ወደ ሰርጉ ግብዣ ጥሩ፡፡ 10 ሰዎቹም ወደ ዐውራው መንገድ ሄደው መልካምም ሆኑ መጥፎዎች ያገኙአቸውን ሁሉ አንድ ላይ ሰበሰቡ፡፡ ስለዚህ የግብዣው አዳራሽ በተጋባዦች ተሞላ፡፡ 11 ንጉሡ ተጋባዦቹን ለማየት ሲመጣ ግን፣ የሰርግ ልብስ ያልለበሰ ሰው አየ፡፡ 12 ንጉሡ እንዲህ አለው፤ ‹ወዳጄ፣' የሰርግ ልብስ ሳትለብስ እንዴት ወደዚህ ገባህ?› ሰውየውም ዝም አለ፡፡ 13 ከዚያም ንጉሡ ለአገልጋዮቹ እንዲህ አላቸው፤ እጅና እግሩን አስራችሁ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጥታችሁ ጣሉት፡፡' 14 የተጠሩ ብዙዎች የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸው፡፡" 15 ከዚያም ፈሪሳውያን ሄደው ኢየሱስን እንዴት በንግግሩ ማጥመድ እንደሚችሉ ዕቅድ አወጡ፡፡ 16 ከዚያም ከሄሮድስ ሰዎች ጋር ደቀ መዛሙርታቸውን ወደ እርሱ ላኩ፡፡ ኢየሱስንም እንዲህ አሉት፤ "መምህር ሆይ፣ አንተ በእውነት የእግዚአብሔርን መንገድ የምታስተምር እውነተኛ ሰው መሆንህን እናውቃለን፤ ሰውን በመፍራት ዐሳብህን አትለውጥም፤ በሰዎች መካከል አድልዎ አታደርግም፡፡ 17 እስቲ ንገረን ምን ይመስልሃል? ለቄሳር ግብር መስጠት ተገቢ ነው ወይስ አይደለም?" 18 ኢየሱስ ግን ተንኰላቸውን ዐውቆ እንዲህ አላቸው፤ "እናንት ግብዞች የምትፈትኑኝ ለምንድን ነው? 19 እስቲ የግብሩን ገንዘብ አሳዩኝ" አላቸው፡፡ እነርሱም ዲናሩን አመጡለት፡፡ 20 ኢየሱስም፣ "ይህ የማን መልክና ስም ነው?›› አላቸው፡፡ 21 እነርሱም፣ "የቄሣር፣" አሉት፡፡ ከዚያም ኢየሱስ፣ "እንግዲያስ የቄሣር የሆነውን ለቄሣር ስጡ፤ የእግዚአብሔር የሆነውን ለእግዚአብሔር ስጡ" አላቸው፡፡ 22 ያንን ሲሰሙ ተገረሙ፡፡ ትተውትም ሄዱ፡፡ 23 በዚያው ቀን ትንሣኤ ሙታን የለም የሚሉ ጥቂት ሰዱቃውያን ወደ እርሱ መጡ፡፡ 24 "መምህር ሆይ፣ ‹አንድ ሰው ልጅ ሳይወልድ ከሞተ ሚስቱን ወንድሙ እንዲያገባና ለወንድሙ ልጅ እንዲወልድለት ሙሴ ተናግሮአል› 25 ሰባት ወንድማማች ነበሩ፡፡ የመጀመሪያው አግብቶ ልጅ ሳይወልድ ሞተ፡፡ ሚስቱ የወንድምየው ሆነች፡፡ 26 ሁለተኛውና ሦስተኛውም እስከ ሰባተኛው ድረስ ያንኑ አደረጉ፡፡ 27 ከሁሉም በኋላ ደግሞ ሴትየዋ ሞተች፡፡ 28 እንግዲህ ሰባቱም ወንድማማች አግብተዋት ነበርና በትንሣኤ ቀን የማንኛው ሚስት ልትሆን ነው?" በማለት ጠየቁት፡፡ 29 ኢየሱስ ግን እንዲህ በማለት መለሰላቸው፤ "መጻሕፍትንም ሆነ የእግዚአብሔርን ኀይል ስለማታወቁ ተሳስታችኋል፡፡ 30 ምክንያቱም በትንሣኤ ቀን እንደ ሰማይ መላእክት ይሆናሉ እንጂ፣ አያገቡም፣ ደግሞም አይጋቡም፡፡ 31 ትንሣኤ ሙታንን በተመለከተ፣ እግዚአብሔር 32 "እኔ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅ አምላክ፣ የያዕቆብም አምላክ ነኝ" በማለት ለእናንተ የተናገረውን አላነበባችሁምን? እግዚአብሔር የሕያዋን አምላክ እንጂ፣ የሙታን አምላክ አይደለም፡፡" 33 ሕዝቡ ይህን ሲሰሙ በትምህርቱ ተገረሙ፡፡ 34 ኢየሱስ ሰዱቃውያንን ዝም እንዳሰኛቸው ፈሪሳውያን ሲሰሙ፣ በአንድነት ተሰበሰቡ፡፡ 35 ከእነርሱ መካከል ሕግ ዐዋቂ የሆነ አንዱ እርሱን ለመፈተን፣ 36 "መምህር ሆይ፣ ከሕጉ ሁሉ የሚበልጠው ትእዛዝ የትኛው ነው" ብሎ ጠየቀው፡፡ 37 ኢየሱስም እንዲህ አለው፤ "እግዚአብሔር አምላክህን በሙሉ ልብህ፣ በሙሉ ነፍስህና በሙሉ ዐሳብህ ውደድ፡፡" 38 ከሁሉም የሚበልጠው የመጀመሪያው ትእዛዝ ይህ ነው፡፡ 39 ሁለተኛውም ትእዛዝ ያንኑ ይመስላል፤ 'ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ፡፡' 40 ሕግና ነቢያት ሁሉ የትመሠረቱት በእነዚህ ሁለት ትእዛዛት ላይ ነው፡፡ 41 ፈሪሳውያን በአንድነት ተሰብስበው እያለ ኢየሱስ አንድ ጥያቄ አቀረበላቸው፡፡ 42 "ስለ ክርስቶስ ምን ታስባላችሁ? ለመሆኑ የማን ልጅ ነው?" አላቸው፡፡ "የዳዊት ልጅ ነው" አሉት፡፡ 43 ኢየሱስም፣ "ታዲያ፣ ዳዊት፣ በመንፈስ፣ 44 ጌታ ጌታዬን ‹ጠላቶችህን በእግርህ ሥር እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ' በማለት እንዴት ጌታ ብሎ ይጠራዋል? 45 ዳዊት ክርስቶስን 'ጌታ' በማለት ከጠራው እንዴት የዳዊት ልጅ ሊሆን ይችላል?" 46 ማንም አንዲት ቃል ሊመልስለት አልቻለም፤ ከዚያ ቀን ጀምሮ ጥያቄ ሊያቀርብለት የደፈረ አልነበረም፡፡
መንግሰተ ሰማያት . . . ትመስላለችThe kingdom of heaven is like በ MAT 13:24 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምህ ተመልከት የተጋበዙት ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ንጉሡ የጋበዛቸው ሰዎች
እነዚህ ሰዎች "የተጋበዙት እንግዶች" (MAT 22:4) ግብዣውን ከቁም ነገር አልቆጠሩትም "የእርሱን ግብዣ ቸል አሉት"
የማቋረጫ መንገድ "መንገዶች የሚገናኙበት ቦታ" አደራሽ ትልቅ ክፍል
ኢየሱስ በሚናገርበት ወቅት እንዴት ያቋርጡት ነበር "ኢየሱስ አንድ ነገር ስናገር በየመኃሉ እያቋረጡት ለክስ የሚሆናቸውን ነገር ለማግኘት ጥረት ያደርጉ ነበር፡፡” ከሄሮዶስ ወገን ከሮማዊያን አገዛዝ ጋር ጓድኛ የሆነው የአይሁድ ንጉሥ የሆነው የሄሮዶስ ተወካዮች እና ተከታዮች በሰዎች መካከል ልዩነት አታደረግም "ለሰዎች የተለየ አክብሮት አትሰጥም " ወይም "በጣም ጠቃሚ ለሚባሉ ሰዎች ትኩርት አትሰጥም"
ዲናር የአንድ ቀን ደሞዝ የሆነ የሮማዊን ገንዘብ ነው
የቄሳርን "የቄሳር የሆነው ነገር የእግዚአብሔርን "የእግዚአብሔር የሆነውን ነገር"
መምህር ሙሰተ እንዲህ ብሏል “አንድ ሰው ከሞተ ሙሴ በቅዱሳት መጽሕፍት ውስጥ ስለጻፈው ነገር ጠየቁት፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ በትቅስ ውስጥ ሌላ ትቅስ መጻፍን የማይፈቅድላችሁ ከሆነ በተዘዋዋር መንገድ ሀሳቡን መግለጽ ትችላላችሁለ “ሙሴ አንድ ሰው ከሞት” (ተመልከት ወንድሙ . . . ምስቱ . . ወንድሙ የሞተው ሰው
ሁሉም አንዱ ከሌላኛው በኋላ "የሰውዬው ወንድሞች ሁሉ እርሷን ካገቡ በኋላ ሞቱ” ወይም “ሁሉም ወንድሞቹ ከሞቱ በኋላ”
ማቴዎስ 22፡29-30 የእግዚአብሔርን ኃይል "እግዚአብሔር ምን ማድረግ እንደሚችል"
እንዲህ የሚል ነገር አላነበባችሁምን . . . ያዕቆብ? "እንዳነበባችሁ አውቃለሁ ነገር ግን ያዕቆብ . . . የሚለውን የተረዳችሁት ግን አይመስልም” በ . . . ለእናንተ የተነገረው "እገዚአብሔር ለእናንተ የተናገረው እግዚአብሔር እንዲህ ይላል “እኔ . . . ያዕቆብ”? ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ ነው፡፡ “እግዚአብሔር ለሙሴ እንዲህ አለው፡፡ እኔ እግዚአብሔር የአብረሃም አምላ፣ የይሳቅ አምላክ እና የያዕቆብ አምላክ ነኝ፡፡”
የሕግ ባለሞያዎች የሙሴን ሕግ ጠንቅቀው የሚያውቁት ፈሪሳዊያን
ወደዱት ሕግጋቱን ወደዱት MAT 22:37.
ማቴዎስ 22፡41-42
ጠላቶችህን የእግር መረገጫ እስካደረግ ድረስ "ጠላቶችን እስካጠፋቸው ድረስ”
ዳዊት ክርስቶስን “ጌታዬ” ብሎ ከጠራው እንዴት እርሱ የዳዊት ልጅ ሊሆን ይችላል? ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ዳዊት ጌታዬ ብሎ ጠርቶታል ስለዚህ ክርስቶስ ከዳዊት ዘር በላይ ነው ማለት ነው፡፡” ዳዊት ክርስቶስን እንዲህ ብሎ ከጠራው ዳዊት ክርስቶስን “ጌታዬ” ብሎ ከጠራው፡፡ ይህ ሊሆን የሚችለው ክርስቶስ የዳዊት ዘር የሆነ ብቻ ሳይን ከዚያም በላይ የሆነ ነው፡፡
1 ከዚያም ኢየሱስ ለሕዝቡና ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ ሲል ተናገረ፤ 2 "የአይሁድ የሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን በሙሴ ወንበር ተቀምጠዋል፡፡ 3 ስለዚህ የሚያዝዙአችሁን ሁሉ አድርጉ፤ አክብሩትም፡፡ እነርሱ የሚያደርጉትን ግን አታደርጉ፤ ምክንያቱም እነርሱ ራሳቸው የሚናገሩትን አያደርጉትም፡፡ 4 ለመሸከም የሚያስቸግር ከባድ ሸክም አንሥተው በሰዎች ትከሻ ላይ ይጭናሉ፡፡ እነርሱ ራሳቸው ግን መሸከም ቀርቶ በጣታቸው ሊያነሡት እንኳ አይፈልጉም፡፡ 5 ሥራቸውን ሁሉ የሚያደርጉት በሰዎች ለመታየት ነው፤ አሸንክታባቸውን ያሰፋሉ፤ የልብሳቸውንም ዘርፍ ያስረዝማሉ፡፡ 6 ግብዣ ላይ የከበሬታ ቦታዎችንና በምኵራብ ውስጥ የተለየ መቀመጫ እንዲሰጣቸው ይፈልጋሉ፤ 7 በገበያ ቦታ ሰዎች የተለየ ክብር እንዲሰጧቸውና፣ 'መምህር ሆይ› በማለት እንዲጠሩአቸው ይፈልጋሉ፡፡ 8 እናንተ ግን ያላችሁ አንድ መምህር ብቻ ስለሆነና ሁላችሁም ወንድማማች ስለሆናችሁ ‹መምህር› ተብላችሁ አትጠሩ፡፡ 9 በምድር ላይ ማንንም አባት ብላችሁ አትጥሩ፤ ምክንያቱም በሰማይ የሚኖር አንድ አባት ብቻ አላችሁ፡፡ 10 ‹ሊቅም› ተብላችሁ አትጠሩ፤ ምክንያቱም ያላችሁ አንድ ሊቅ ብቻ ነው፤ እርሱም ክርስቶስ ነው፡፡ 11 ከእናንተ መካከል ታላቅ የሆነው አገልጋያችሁ ይሁን፡፡ 12 ራሱን ከፍ የሚያደርግ ዝቅ ይላል፤ ራሱን ዝቅ የሚያደርግ ከፍ ይላል፡፡ 13 እናንተ፣ ግብዞች የአይሁድ የሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን ግን ወዮላችሁ! በሰዎች ፊት መንግሥተ ሰማይን ትዘጋላችሁ፡፡ እናንተ ራሳችሁ አትገቡበትም፤ የሚገቡትንም እንዳይገቡ ትከለክላላችሁ፡፡ 14[1] እናንተ ግብዞች የአይሁድ የሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን ለታይታ ረጅም ጸሎታችሁን በማድረግ የመበለቶችን ቤት ስለምትበሉ ወዮላችሁ! ስለዚህ የበለጠውን ፍርድ ትቀበላላችሁ፡፡ እናንተ ግብዞች የአይሁድ ሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን ወዮላችሁ! 15 አንድን ሰው ተከታያችሁ ለማድረግ በባሕርና በምድር ትሄዳላችሁ፤ ተከታያችሁ ካደረጋችሁት በኋላ፣ ከእናንተ እጥፍ የሚከፋ የገሃነም ልጅ ታደርጉታላችሁ፡፡ 16 እናንተ ዐይነ ስውራን መሪዎች ወዮላችሁ፤ አንድ ሰው 'በቤተ መቅደሱ ቢምል ምንም ማለት አይደለም፤ ቤተ መቅደሱ ውስጥ ባለው ወርቅ ቢምል ግን፣ በመሐላው ይጠመዳል' ትላላችሁ፡፡ 17 እናንተ የታወራችሁ ሞኞች፣ ለመሆኑ የትኛው ይበልጣል ወርቁ ወይስ ወርቁን የሚቀድሰው ቤተ መቅደሱ? 18 አንድ ሰው በመሠዊያው ቢምል ምንም ማለት አይደለም፤ መሠዊያው ላይ ባለው ስጦታ ቢምል ግን በመሐላው ይጠመዳል ትላላችሁ፡፡ 19 እናንተ ዕውሮች፤ ለመሆኑ የትኛው ይበልጣል ስጦታው ወይስ ስጦታውን የሚቀድሰው መሠዊያ? 20 ስለዚህ በመሠዊያው የሚምል በመሠዊያውና እርሱ ላይ ባሉ ነገሮች ሁሉ ይምላል፡፡ 21 በቤተ መቅደሱ የሚምል በቤተ መቅደስና እርሱ ውስጥ በሚኖረው ይምላል፡፡ 22 በሰማይ የሚምል በእግዚአብሔር ዙፋንና በእርሱ ላይ በተቀመጠው ይምላል፡፡ 23 እናንተ ግብዞች የአይሁድ የሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን ወዮላችሁ፣ ከአዝሙድ፣ ከእንስላልና ከከሙን ዐሥራት ብታወጡም፣ የሕጉን ዋና ዋና ነገሮች ማለትም ፍትሕን፣ ምሕረትንና እምነትን ሥራ ላይ አታውሉም፡፡ ሌላውን ችላ ሳትሉ እነዚህን መፈጸም ነበረባችሁ፡፡ 24 እናንተ ዐይነ ስውራን መሪዎች፣ ትንኝን አውጥታችሁ ትጥላላችሁ፤ ግመልን ግን ትውጣላችሁ! 25 እናንተ ግብዞች የአይሁድ የሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን ወዮላችሁ! የጽዋውንና የሳሕኑን ውጫዊ ክፍል ታጠራላችህ፤ ውስጡ ግን ቅሚያና ስስት ሞልቶበታል፡፡ 26 አንተ ዕውር ፈሪሳዊ፣ ውጫዊ አካሉም ንጹሕ እንዲሆን በመጀመሪያ የጽዋውንና የሳሕኑን ውስጥ አጽዳ፡፡ 27 እናንተ ግብዞች የአይሁድ የሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን ወዮላችሁ! ከውጭ ሲያዩት እንደሚያምር፣ ውስጡ ግን የሞቱ ሰዎች አጥንትና ርኵሰት እንደ ሞላበት መቃብር ናችሁ፡፡ 28 በተመሳሳይ መንገድ እናንተም ከውጭ ለሰዎች ጻድቃን ትመስላላችሁ፤ ውስጣችሁ ግን ግብዝነትና ርኲሰት ሞልቶበታል፡፡ 29 እናንተ ግብዞች የአይሁድ የሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን ወዮላችሁ! የነቢያትን መቃብር ስለምትሠሩ፣ የጻድቃንን መቃብር ስለምታስጌጡ፣ 30 በአባቶቻችን ዘመን ኖረን ቢሆን ኖሮ፣ የነቢያትን ደም በማፍሰስ አንተባበራቸውም ነበር ትላላችሁ፡፡ 31 ስለሆነም የነቢያት ገዳይ ልጆች መሆናችሁን እናንተ ራሳችሁ ትመሰክራላችሁ፡፡ 32 እናንተ ራሳችሁም አባቶቻችሁ የጀመሩትን ኃጢአት ትፈጽማላችሁ፡፡ 33 እናንተ እባቦች፣ እናንተ የእፉኝት ልጆች፣ ከገሃነም ፍርድ እንዴት ታመልጣላችሁ? 34 ስለዚህ ነቢያትን፣ አስተዋይ ሰዎችንና የአይሁድ ሕግ መምህራንን ወደ እናንተ እልካለሁ፡፡ አንዳንዶቹን ትገድላላችሁ፣ ትሰቅላላችሁ፤ ሌሎቹን በምኵራቦቻችሁ ትገርፋላችሁ፣ ከከተማ ወደ ከተማ ታሳድዳላችሁ፡፡ 35 ከጻድቁ ከአቤል አንሥቶ በቤተ መቅደሱና በመሠዊያው መካካል እስከ ገደላችሁት የበራክዩ ልጅ ዘካርያስ ደም ድረስ፣ በምድር ላይ በፈሰሰው ጻድቃን ደም ሁሉ ትጠየቃላችሁ፡፡ 36 እውነት እላችኋለሁ፤ እነዚህ ነገሮች ሁሉ በዚህ ትውልድ ላይ ይሆናሉ፡፡ 37 ኢየሩሳሌም፣ ኢየሩሳሌም ሆይ፣ አንቺ ነቢያትን የምትገድዪ ወደ አንቺ የተላኩትን በድንጋይ የምትወግሪ! ዶሮ ጫጩቶችዋን በክንፎቿ ሥር እንደምትሰበስብ እኔም ልጆችሽን መሰብሰበ ብዙ ጊዜ ፈልጌ ነበር፤ እናንተ ግን አልፈለጋችሁም! 38 ስለሆነም ቤታችሁ ወና ሆኖ ይቀራል፡፡ 39 'በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው' እስክትሉ ድረስ ከአሁን ጀምሮ አታዩኝም እላችኋለሁ፡፡
ከባድና አስቸጋሪ ሸክም ተብትበው በሰው ትከሻ ይጭናሉ፥ "ተግባራዊ ለማድረግ በጣም አስቸጋሪ የሆኑ ደንቦችን በእናንተ ላይ ይጭናሉ" እነርሱ ግን በጣታቸው ስንኳ ሊነኩት አይወዱም። "ምንም ዓይነት እገዛ ለማድረግ ግን ፈቃደኞች አይደሉም" አሸንክታብ ቅዱሳት መጻሕፍት የተጻፉበት ወረቀት መያዥያ ትንሽ የቆዳ ሳጥን
በምድር ላይ ማንንም አባት ብላችሁ አትጥሩ "በምድር ላይ ማንንም አባት ብላችሁ አትጥሩ” ወይም “በምድር ላይ ያለን ማንንም ሰው አባቴ ብላችሁ አትጥሩ" በሰማይ ያለ አንድ አባት አላችሁና እግዚአብሔር አባር የአማኞች ሁሉ “አባት” ነው፡፡ አንድ መምህር አላችሁ እርሱም ክርስቶስ ነው ኢየሱስ “ክርስቶስ” ብሎ ስናገር በሦስተኛ መደብ ስለራሱ መናገሩ ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክርለ “እኔ ክርስቶስ፣ እኔ ብቻ የእናንተ መምህር ነኝ"
ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደረግ "ራሱን በጣም አስፈላጊ የሚያደረግ" ከፍ ከፍ ያለ "ራሱን በጣም አስፈላጊ ያደረገ"
አትገባም "እግዚአብሔር በአንተ ላይ እንዲገዛ አትፈቅድ" የመበልቶችን ቤት መበዝበዝ "የሚጠብቃቸው ወንድ ያሌላቸው ሴቶች ትዘርፋለህ” የገሃነም ልጅ "ለገሃነም የተገባህ ሰው" ወይም "ወደ ገሃነም መግባት ያለበት ሰው
የእውር ምሪት . . . ሞኞች ምንም እንኳ መሪዎቹ ዐይነ ሥውራን ባይሆንም እንደ ተሳቱ ማወቅ አይችሉም ነበር በመኃላ ታሥሯል "ለማድረግ በመኋላ የገባውን ቃል መፈጸም አለበት” ወርቁ ነውን? ወይስ ወርቁን የቀደሰው ቤተ መቅደስ? ኢየሱስ ይህንን ጥቅስ ፈሪሳዊያንን ለመገሰጽ ተጠቅሞበታል፡፡
ዐይነ ሥውራን መንፈሳዊ ዐይነ ሥውርነት ያለባቸው ሰዎች መባው ነውን? ወይስ መባውን የሚቀድሰው መሠዊያው? ኢየሱስ ይህንን ጥቅስ እንሱ እሰቀድመው የሚያውቁትን ነገር ለማስታወስ ተጠቅሞበታል ስጦታ/መባ በመሰዊያው ላይ በእግዚአብሔር ፊት የሚቀርብ የእንስሳት መስዋዕት ወይም እህል መስዋዕት ነው፡፡ አንድ ጊዜ መሰዊያው ላይ ከሆነ ቧላ መስዋእት ይሆናል፡፡
ወዮላችሁ በ MAT 23:13 በምን መንገድ እንተረጎምከው ተመልከት መባው ነውን? ወይስ መባውን የሚቀድሰው መሠዊያው? ለምግብ ጥሩ ጣዕም ለመስጠጥ የሚውሉ ቅጠላ ቅጠሎች እና ፍሬዎች ዐይነ ሥውራነት መሪዎች እነዚህ ሰዎች አካላዊ ዐይናቸው አልጠፋም፡፡ ኢየሱስ አካላዊ ዐይነ ሥውርነትን ከመንፈሳዊ ዐይነ ሥውርነት ጋር ያነጻጽራል፡፡ ትንኝን የምታጠሩ ግመልንም የምትውጡ። በጣም ትንንሽ የሆኑ ንጹሕ እንስሳትን ላለመዋጥ በመጠንቀቅ የትልቁን ንጹሕ ያልሆነ እንስሳ ሥጋ ግን ሆን ብላችሁ ወይም ሳታውቁ ትበላላችሁ ልክ እንደዚሁ በጣም ትንነሽ የሆኑ ሕግጋትን ለመጠበቅ ጥረት ታደርላችሁ ይሂን እንጂ በጣም አስፈላጊ የሆኑ ሕግጋትን ግን ቸል ትላላችሁ፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "ልክ ትንኝ በምጠጣው ነገር ውስጥ የሚያወጣ ነገር ግን ግመል እንደሚውጥ ሰው ሞኞች ናችሁ፡፡” ትንኝን እንዳይገባ ትንንኝ ወደ አፋቸው እንዳይገባ በጨርቅ አጥልለው ይጠጣሉ ትንኝ ትንንሽ በራሪ ነፍሳት
ወዮላችሁ በ MAT 23:13 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ የብርጭቆ እና የሣህኑን ውጪ ታጠራላችሁ “ጸሐፍ” እና “ፈርሳዊያን” ከውጪ በሰዎች ፊት “ንጹሕ መስለው” መታየት ይፈልጋሉ፡፡ በውስጡ ግን የሙታን አጥንት ርኩሰትም ሁሉ የተሞሉ "ከሚያስፈልጋቸው በላይ እንዲኖራው በጉልበት የሌላ ሰውን ነገር ይወስዳሉ “ ዐይነ ሥውራን ፈሪሳዊያን ፈሪሳዊያን እውነቱን አይረዱትም፡፡ አካላዊ ዐይነሥውነት ግን የለባቸውም፡፡ ውጭው ደግሞ ጥሩ እንዲሆን አስቀድመህ የጽዋውንና የወጭቱን ውስጡን አጥራ። ልባቸው ከእግዚአብሔር ጋር ትክክል ከሆነ ሕይወታቸውም ይህንኑ ያሳያል፡፡
የአባቶቻችሁን መስፈሪያ ኃጢአት ሙሉ። "አባቶቻችሁ የጀመሩትን ኃጢአት ፈጽሙ" እናንተ እባቦች፥ የእፉኝት ልጆች "ልክ እንደ አደገኛ እና መርዛማ እባቦች ናችሁ" ከገሃነም ፍርድ እንዴት ታመልጣላችሁ? "የገሃነም ፍርድን የሚታመልጡበት ምንም ዓይነት መንገድ የለም!" (ተመልከት:
ከአቤል . . እስከ ዘካሪያስ አቤል የመጀመሪያው የተገደለ ሰው ነው እንዲሁም ምናልባትም በአይሁዳዊያን ዘንድ በቤተ መቅደስ ውስጥ የተገደለው የመጨረሻው ሰው ነው፡፡ ዘካሪያስ ይህ የመጥመቁ ዮሐንስ አባት አይደለም
እየሩሳሌም፣ እየሩሳሌም ኢየሱስ በእየሩሳሌም የሚኖሩ ሰዎችን ልክ ከተማዋን እንደሚናገር ሰው ይናገራቸዋል፡፡ ልጆቻችሁ የሁሉም እስራኤላዊያን ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላችኋል። ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እግዚአብሔር ቤታችሁን ትቶ ይሄዳል ባዶም ይሆናል” ቤታችሁ አማራጭ ትርጉሞች፡ 1) የኢየሩሳሌም ከተማ ወይም 2) ቤተ መቅደሱ፡፡
1 ኢየሱስ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ እየሄደ ሳለ፤ ደቀ መዛሙርቱ የቤተ መቅደሱን ሕንጻ ሊያሳዩት ወደ እርሱ መጡ፡፡ 2 እርሱ ግን፣ "እነዚህን ሁሉ ነገሮች ታያላችሁ? እውነት እላችኋለሁ፣ ይፈርሳል እንጂ፣ አንድ ድንጋይ እንኳ በሌላ ድንጋይ ላይ እንደ ተነባበረ አይቀርም" በማለት መለሰላቸው፡፡ 3 በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ተቀምጦ እያለ፣ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ መጥተው፣ "እስቲ ንገረን፤ ይህ ሁሉ የሚሆነው መቼ ነው? የአንተ መምጣትና የዓለም መጨረሻስ ምልክቱ ምንድን ነው?" አሉት፡፡ 4 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፣ "ማንም እንዳያሳስታችሁ ተጠንቀቁ፡፡ 5 ምክንያቱም ብዙዎች በስሜ ይመጣሉ፤ 'እኔ ክርስቶስ ነኝ' እያሉ ብዙዎችን ያሳስታሉ 6 ጦርነትንና የጦርነትን ዜና ትሰማላችሁ፤ በፍጹም እንዳትታወኩ፤ ምክንያቱም እነዚህ ነገሮች እንዲሆኑ ግድ ነው፤ ቢሆንም፣ መጨረሻው ገና ነው፡፡ 7 ሕዝብ በሕዝብ ላይ፣ መንግሥት በመንግሥት ላይ ይነሣል፡፡ በተለያየ ቦታ ራብና የምድር መናወጥ ይሆናል፡፡ 8 እነዚሀ ሁሉ ግን የምጥ ጣር መጀመሪያ ብቻ ናቸው፡፡ 9 ከዚያም ለመከራ አሳልፈው ይሰጧችኋል ይገድሏችኋልም፡፡ ስለ ስሜ ሕዝቦች ሁሉ ይጠሏችኋል፡፡ 10 ብዙዎች ይሰናከላሉ፤ እርስ በርስ ይካካዳሉ፤ እርስ በርስ ይጠላላሉ፡፡ 11 ብዙ ሐሰተኛ ነቢያት ተነሥተው፣ ብዙዎችን ያሳስታሉ፡፡ 12 ዐመፅ ስለሚበዛ የብዙዎች ፍቅር ይቀዘቅዛል፡፡ 13 እስከ መጨረሻ የሚታገሥ ግን ይድናል፡፡ 14 ለሕዝቦች ሁሉ ምስክር እንዲሆን የመንግሥቱ ወንጌል ለመላው ዓለም ይሰበካል፤ ከዚያም መጨረሻው ይመጣል፡፡ 15 ስለዚህ በነቢዩ ዳንኤል የተነገረለት የጥፋት ርኲሰት በተቀደሰው ቦታ ቆሞ ስታዩ፣ (ያኔ አንባቢው ያስተውል) 16 በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ፣ 17 ጣራ ላይ ያለ ሰው በቤቱ ያለውን ምንም ነገር ከቤቱ ለመውሰድ አይመለስ፣ 18 በእርሻ ያለ ልብሱን ለመውሰድ አይመለስ፡፡ 19 ልጆች ላሉአቸውና ለሚያጠቡ እናቶች ግን ወዮላቸው! 20 ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ፡፡ 21 ምክንያቱም ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስና ከዚያም በኋላ ፈጽሞ የማይሆን ታላቅ መከራ ይሆናል፡፡ 22 እነዚያ ቀኖች ባያጥሩ ኖሮ፣ ማንም ሥጋ ለባሽ አይድንም ነበር፤ ለተመረጡት ሲባል ግን እነዚያ ቀኖች ያጥራሉ፡፡ 23 ስለዚህ ማንም "እነሆ ክርስቶስ፣ እዚህ ነው" ወይም፣ 'ክርስቶስ እዚያ ነው' ቢላችሁ አትመኑ፡፡ 24 ምክንያቱም ብዙዎችን ለማሳሳት ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት መጥተው ታላላቅ ምልክቶችንና ድንቆችን ያደርጋሉ፤ ከተቻለም የተመረጡትን እንኳ ያሳስታሉ፡፡ 25 ይህ ከመሆኑ በፊት አስቀድሜ ነግሬአችኋለሁ፡፡ 26 ስለዚህ፣ ‹ክርስቶስ በምድረ በዳ ነው› ቢሏችሁ ወደ ምድረ በዳ አትሂዱ ወይም ቤት ውስጥ ነው ቢሏችሁ አትመኑ፡፡ 27 መብረቅ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ በአንዴ እንደሚታይ የሰው ልጅ ሲመጣ እንደዚያው ይሆናል፡፡ 28 የሞተ እንስሳ ባለበት ሁሉ፣ በዚያ አሞሮች ይሰበሰባሉ፡፡ 29 ከእነዚህ የመከራ ቀኖች በኋላ ወዲያውኑ ፀሐይ ትጨልማለች፣ ጨረቃም ብርሃኗን አትሰጥም፤ ከዋክብት ከሰማይ ይወድቃሉ፤ የሰማያት ኅይላት ይናወጣሉ፡፡ 30 ከዚያም የሰው ልጅ ምልክት በሰማይ ይታያል፤ የምድር ነገዶች ሁሉ አምርረው ያለቅሳሉ፡፡ የሰው ልጅንም በኀይልና በታላቅ ክብር ሲመጣ ያዩታል፡፡ 31 መላእክቱንም ከታላቅ መለከት ድምፅ ጋር ይልካቸዋል፤ እነርሱም፣ ከአንድ የሰማይ ጫፍ እስከ ሌላው ጫፍ ድረስ ከአራቱም ነፋሳት ምርጦቹን ይሰበስቧቸዋል፡፡ 32 ከበለስ ዛፍ ተማሩ፡፡ ቅርንጫፎቿ ሲለመልሙና ቅጠሎች ብቅ ብቅ ሲሉ በጋ መቅረቡን ታውቃላችሁ፡፡ 33 እናንተም እነዚህን ሁሉ ስታዩ እርሱ መቅረቡን፣ እንዲያውም በደጅ መሆኑን ዕወቁ፡፡ 34 እውነት እላችኋለሁ፣ እነዚህ ሁሉ እስኪፈጸሙ ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም፡፡ 35 ሰማይና ምድር ያልፋሉ ቃሌ ግን ፈጽሞ አያልፍም፡፡ 36 ስለዚያች ቀንና ሰዓት ግን ማንም አያውቅም፤ የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ አያወቁም፤ አብ ብቻ እንጂ ወልድ እንኳ ቢሆን አያውቅም፡፡ 37 በኖኅ ዘመን እንደ ነበረው፣ የሰው ልጅ መምጣትም እንዲሁ ይሆናል፡፡ 38 ከጥፋት ውሃ በፊት እንደ ነበረው ዘመን፣ ኖኅ ወደ መርከብ እስከ ገባ ድረስ ይበሉና ይጠጡ፣ ያገቡና ይጋቡ ነበር። 39 ጐርፉ መጥቶ እስኪያጠፋቸው ድረስ ምንም አላወቁም፣ የሰው ልጅ ሲመጣም እንዲሁ ይሆናል፡፡ 40 በዚያን ጊዜ ሁለት ሰዎች በዕርሻ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሌላው ይቀራል፡፡ 41 ሁለት ሴቶች በወፍጮ ይፈጫሉ፤ አንዷ ትወሰዳለች ሌላዋ ትቀራለች፡፡ 42 ስለዚህ ጌታችሁ በምን ቀን እንደሚመጣ አታውቁምና ተጠንቀቁ፡፡ 43 ይህን ግን ዕወቁ፤ ሌባው በየትኛው ሰዓት እንደሚመጣ የቤቱ ባለቤት ቢያውቅ ኖሮ ይጠነቀቅ ነበር፤ ቤቱ አይዘረፍም ነበር፡፡ 44 የሰው ልጅ ባልጠበቃችሁት ሰዓት ስለሚመጣ እናንተም ብትሆኑ ተዘጋጅታችሁ መጠበቅ አለባችሁ፡፡ 45 በተገቢው ጊዜ ለቤተ ሰቦቹ ምግባቸውን ለመስጠት ጌታው በቤቱ ላይ ኀላፊነት የሰጠው ታማኝና አስተዋይ አገልጋይ ማን ነው? 46 ጌታው ሲመጣ ያንን እያደረገ የሚያገኘው አገልጋይ የተባረከ ነው፡፡ 47 እውነት እላችኋለሁ የምላችሁ፣ ጌታው ባለው ነገር ሁሉ ላይ ኀላፊ አድርጎ ይሾመዋል፡፡ 48 ይሁን እንጂ፣ አንድ ክፉ አገልጋይ በልቡ፣ ‹‹ጌታዬ ከመምጣት ዘግይቶአል ብሎ ቢያስብ፣ 49 አገልጋይ ጓደኞቹን መደብደብና ከሰካራሞች ጋር መብላት መጠጣት ቢጀምር 50 የዚያ አገልጋይ ጌታ አገልጋዩ ባልጠበቀው ቀንና በማያውቀው ሰዓት ይመጣበታል፡፡ 51 ጌታው ለሁለት ይሰነጥቀዋል፤ ዕጣ ፈንታውን ከግብዞች ጋር ያደርግበታል፣ በዚያም ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል፡፡
ይህን ሁሉ ታያላችሁን? አማራጭ ትርጉሞች: ኢየሱስ እየተናገረ ያው 1) ስለ ቤተ መቅደሱ ግንባታ
ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ "ማንም ስለዚህ ጉዳይ እንዳይዋሻችሁ ተጠንቀቁ"
አትደናገጡ "እነዚህ ነገሮች አያናውጧችሁ"
አሳልፈው ይሰጢ,ጡአችዋል
"የእናንተን መሰደድ የሚወዱ ሰዎች አሳልፈው ይሰጡአችዋል" አሳልፎ መሰጠት በ MAT 10:17 ላይ ምን ብለህ እንዴተረጎምከው ተመልከት፡፡
የብዙዎች ፍቅር እየቀዘቀዘ ይመጣል አማራጭ ትርጉሞች: 1) "ብዙ ሰዎች ሌሎች ሰዎችን መውደድ ይተዋሉ" ወይም 2) "ብዙ ሰዎች እግዚአብሔርን መውደዳቸውን ይተዋሉ" በዓለም ሁሉ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “በሁሉም ሥፍራ ያሉ ሁሉም ሰዎች"
በነብዩ ዳንኤል የተነገረው ትንቢት ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ነብዩ ዳንኤል በጻፈው ትንቢት መሠረት”
ነፍሰ ጡር ያረገዘች ሴት ክረምት "ቀዝቃዛ ወራት" ሥጋ ለባሽ ሰዎች
አትመኑ "የሚነግሯችሁን ውሸት አትመኑ"
መብረቅ ከምሥራቅ ወጥቶ እስከ ምዕራብ እንደሚታይ፥ የሰው ልጅ መምጣት እንዲሁ ይሆናልና፤ አመጣጡ በፍጥነት እና በቀላሉ ለታይ በሚችል መልኩ ነው፡፡ የሞተ እንስሳ ባለበት በዚያ ጥንብ አንሳዎች ይሰበሰባሉ አማራጭ ትርጉሞች 1) የሰው ልጅ በመጣ ጊዜ ሁሉም ሰዎች ያዩታል እንዲሁም የእርሱን መምጣት ያውቃሉ ወይም 2) በመንፈሳዊ ሕይወታቸው የሞቱ ሰዎች ባሉበት ሥፍራ ውሸትን የሚነግሯቸው ሐሰተኛ ነብያት በዚያ አሉ፡፡ ጥንብ አንሳ የሞቱ ወይም ሊሞቱ ያሉ እንስሳትን ሥጋ የሚበሉ አእዋፋት
ወዲያው "በዚያ ቅጽበት" በእነዚያ ቀናት በ MAT 24:23-28 ላይ የተገለጹት ቀናት አራት ንፈሳት ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ከሰሜን፣ ከደቡበድ፣ ከምስራቅ እና ከምዕራብ” ወይም “ከሁሉም አቅጣጫ" የሰማይ ኃይላት ሁሉ ይናወጣሉ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እግዚአብሔር በሰማይ ያሉትን ነገሮች ሁሉ እና ከሰማይ በላይ ያሉትን ነገሮች ያናውጣል
ደረታቸውን ይደቃሉ የሚመጣውን ፍርድ በመፍራት ደረታቸውን ይመታሉ ይሰበሰባሉ "መላዕክቶቹ ይሰበስባሉ" ምርጦቹን የሰው ልጅ የመረጣቸውን ሰዎች ከአራቱም ንፋሳት ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ከሰሜን፣ ከደቡበድ፣ ከምስራቅ እና ከምዕራብ” ወይም “ከሁሉም አቅጣጫ"
በደጅ እንደቀረበ እወቁ ወራሪ ሠራዊት ከተማዋን ሰብሮ ለመግባት ዝግጁ እንደሆነ
ይህ ተውልድ አያልፍም "ዛሬ የሚኖሩ ሰዎች አይሞቱም" ይህ ሁሉ እስኪሆን ድረስ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እነዚህ ነገሮች እግዚብሔር እንዲሆኑ እስኪደረግ ድረስ" ሰማይ እና ምድር ያልፋሉ "ሰማይ እና ምድር ሕልውናቸው ያበቃል"
የሰው ልጅም ቢሆን "የሰው ልጅ እንኳ"
በኖህ ዘመን እንደሆነው የሰው ልጅ መምጣትም እንዲሁ ይሆናል "የሰው ልጅ የሚመጣበት ቀን ልክ በኖህ ዘመን እንደሆነው ነው” ምክንያቱም ማንም መጥፎ ነገር ይሆንብና ብሎ አላሰበም፡፡ በዚያ ዘመን እንደሆነው ከጥፋት ውሃ በፊት ይበሉ እና ይጠጡ . . . ጠራርቆ ወሰዳቸው- የሰው ልጅ መምጣትም እንዲሁ ይሆናል "ከሰው ልጅ መምጣት በፊት ያለው ጊዜ ልክ የጥፋት ውሃ ሊመጣ ሲል ያለውን ይመስላል፣ ሁሉም ስበሉና ስጠጡ ሳለ - - - ጠራትቆ ወሰዳቸው”
ከዚያ የሰው ልጅ ሲመጣ አንዱ ይወሰዳል ሌላኛው ይቀራል አማራጭ ትርጉሞች: 1) እግዚአብሔር ወደ ሰማይ ይወስደዋል ሌሎቹን ደግሞ ለፍርድ በምድር ላይ ይተዋቸዋ፡፡ ወይም 2) መላእክት አንዱ ልፍርድ ይወስዱታል ሌላኛውን ለበረከት ይተውታል ወይም (ተመልከት), MAT 13:40-43). የድንጋይ ወፍጮ እህል ለመከካት የሚሆን እቃ ስለዚህ "ከነገርኳችሁ ነገር የተነሳ" ጸንታችሁ ቁሙ "በንቃት ተከታተሉ"
ሌባ ኢየሱስ ልክ እንደ ሌባ ሰዎች ባላሰቡት ሰዓት እንደሚመጣ ተናግሯል፤ ይሁን እንጂ ሊሰርቅ አይደለም የሚመጣው፡፡ ነቅቶ ይጠብቅ ነበር ቤቱ እንዳይዘረፍ “ነቅቶ በጠበቀ ነበር” ቤቱም ሊቈፈር ባልተወም ነበር። "ማንም ቤቱ ገብቶ ንረቱን አንድሰርቅ ባላደረገ ነበር"
እንኪያስ በጊዜው ይሰጣቸው ዘንድ . . . ታማኝና ልባም ባሪያ ማን ነው? "ታማኝ፣ ልባም ባሪያ ማን ነው? ጌታው በጊዜው . . . እርሱን ነው፡፡” ምግባቸውን ይሰጣቸው ዘንድ "በጌታው ቤት ላሉት ሰዎች ምግባቸውን ይሰጥ ዘንድ"
በለልቡ እንዲህ አለ "በአእምሮው እንዲህ አሰበ" እድል ፈንታወን ለመወሰን "ይቀበሉት ዘንድ"
1 መንግሥተ ሰማይ መብራታቸውን ይዘው ሙሽራውን ለመቀበል የወጡ ዐሥር ድንግሎችን ትመስላለች። 2 ዐምስቱ ሞኞች፣ ዐምስቱ ልባሞች ነበሩ። 3 ሞኞቹ ድንግሎች መብራታቸውን ይዘው ሲሄዱ ምንም ዘይት አልያዙም ነበር። 4 ልባሞቹ ግን ከመብራታቸው ጋር ዘይትም ይዘው ነበር። 5 ሙሽራው በዘገየ ጊዜ እንቅልፍ እንቅልፍ አላቸውና ሁሉም ተኙ። 6 ዕኩለ ሌሊት ላይ ግን፣ “ሙሽራው መጥቶአልና ወጥታችሁ ተቀበሉት!” የሚል ሁካታ ሆነ። 7 ያኔ እነዚያ ድንግሎች ሁሉ ተነሥተው መብራታቸውን አዘጋጁ። 8 ሞኞቹም ልባሞቹን፣ “መብራታችን እየጠፋ ስለ ሆነ፣ ከዘይታችሁ ጥቂት ስጡን” አሏቸው። 9 ልባሞቹ ግን፣ “ለእኛና ለእናንተ የሚበቃ ስለሌለን፣ ወደ ሻጮች ሄዳችሁ ለራሳችሁ ግዙ” በማለት መለሱአቸው። 10 ለመግዛት ሲሄዱ፣ ሙሽራው መጣ፤ ተዘጋጅተው የነበሩት ግብዣው ላይ ለመገኘት ከእርሱ ጋር ሄዱ፤ በሩም ተዘጋ። 11 በኋላ ሌሎቹ ድንግሎች መጥተው፣ “ጌታው፣ በሩን ክፈትልን” አሉ። 12 እርሱ ግን መልሶ፣ “እውነት እላችኋለሁ፣ አላውቃችሁም” አላቸው። 13 ስለዚህ ቀኑን ወይም ሰዓቱን አታውቁምና ነቅታችሁ ጠብቁ። 14 ነገሩ ወደ ሌላ አገር ለመሄድ ያሰበ ሰውን ይመስላልና፤ አገልጋዮቹን ጠርቶ በሀብት በንብረቱ ሁሉ ላይ ኀላፊነት ሰጣቸው። 15 እንደ ዐቅማቸው መጠን ለአንዱ ዐምስት መክሊት፣ ለሌላው ሁለት፣ ለሌላው ደግሞ አንድ መክሊት ሰጣቸውና ሄደ። 16 ዐምስት መክሊት የተቀበለው ወዲያውኑ ሄዶ ነገደበት፤ ሌላ ዐምስት አተረፈ። 17 ሁለት መክሊት የተቀበለውም እንደዚያው ሌላ ሁለት መክሊት አተረፈ። 18 አንድ መክሊት የተቀበለው አገልጋይ ግን ሄዶ ጉድጓድ ቈፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ። 19 ከብዙ ጊዜ በኋላ የእነዚያ አገልጋዮች ጌታ ተመልሶ መጣና ተሳሰባቸው። 20 ዐምስት መክሊት የተቀበለው አገልጋይ ሌላ ዐምስት መክሊት ጨምሮ አመጣና፣ “ጌታ ሆይ፣ ዐምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እኔ ግን ሌላ ዐምስት መክሊት አተረፍሁ” አለ። 21 ጌታውም፣ 'አንተ መልካምና ታማኝ አገልጋይ ደግ አደረግህ! በጥቂት ነገሮች ታምነሃል፤ በብዙ ነገሮች ላይ እሾምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ።' አለው። 22 ሁለት መክሊት ተቀብሎ የነበረው አገልጋይም መጥቶ፣ ‘ጌታ ሆይ፣ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር። ሌላ ሁለት መክሊት አትርፌአለሁ’ አለ። 23 ጌታውም፣ 'አንተ መልካምና ታማኝ አገልጋይ ደግ አደረግህ! በጥቂት ነገሮች ታምነሃል፤ በብዙ ነገሮች ላይ እሾምሃለሁ። ወደ ጌታህ ደስታ ግባ’ አለው። 24 ከዚያም አንድ መክሊት የተቀበለው አገልጋይ መጥቶ፣ 'ጌታ ሆይ፣ ካልዘራህበት የምታጭድ፣ ካልበተንህበት የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ። 25 ስለዚህ ፈራሁ፤ መክሊትህን መሬት ውስጥ ቀበርሁት። መክሊትህ ይኸውልህ' አለው። 26 ጌታው ግን መልሶ፣ 'አንተ ዐመፀኛና ሰነፍ አገልጋይ፤ ካልዘራሁበት የማጭድ፣ ካልበተንሁበት የምሰበስብ መሆኔን ታውቃለህ። 27 ስለዚህ ገንዘቤን በባንክ ማስቀመጥ ይገባህ ነበር፤ እኔ ስመጣ ከነወለዱ እወስደው ነበር' አለው። 28 ስለዚህ መክሊቱን ከእርሱ ወስዳችሁ ዐሥር መክሊት ላለው ስጡት። 29 ላለው የበለጠ እንዲያውም የተትረፈረፈ ይሰጠዋል። ምንም ከሌለው ግን፣ ያው ያለው ነገር እንኳ ይወሰድበታል። 30 ይህን የማይረባ አገልጋይ አውጡና ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት በውጭ ወዳለው ጨለማ ጣሉት” አለ። 31 የሰው ልጅ በክብሩ ከመላእክቱ ሁሉ ጋር ሲመጣ፣ በክብር ዙፋኑ ላይ ይቀመጣል። 32 አሕዛብ ሁሉ በፊቱ ይሰበሰባሉ፤ እረኛ በጎችን ከፍየሎች እንደሚለይ ሕዝቡን ይለያቸዋል። 33 በጎቹን በቀኙ፣ ፍየሎቹን በግራው ያደርጋቸዋል። 34 ከዚያም ንጉሡ በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል፤ 'እናንተ አባቴ የባረካችሁ ኑ፤ ዓለም ከመፈጠሩ በፊት የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ። 35 ተርቤ ነበር ምግብ ሰጣችሁኝ፤ ተጠምቼ ነበር የምጠጣው ሰጣችሁኝ፤ እንግዳ ሆኜ ነበር አስተናገዳችሁኝ፤ 36 ተራቊቼ ነበር አለበሳችሁኝ፤ ታምሜ ነበር ተንከባከባችሁኝ፤ ታስሬ ነበር ጠየቃችሁኝ' ይላቸዋል። 37 ከዚያም ጻድቃን እንዲህ ብለው ይመልሱለታል፣ ‘ጌታ ሆይ፣ ተርበህ ያገኘንህና ያበላንህ ወይስ ተጠምተህ ያጠጣንህ መቼ ነው? 38 38 እንግዳ ሆነህ ያየንህና ያስተናገድንህ መቼ ነው? ወይም ተራቊተህ ያለበስንህ መቼ ነው? 39 ታምመህ የተንከባከብንህ ወይስ ታስረህ የጠየቅንህ መቼ ነው?’ 40 ንጉሡም መልሶ እንዲህ ይላቸዋል፤ ‘እውነት እላችኋለሁ፤ ለእነዚህ ታናናሽ ወንድሞቼ ያደረጋችሁትን ለእኔ አድርጋችሁታል።’ 41 ከዚያም በግራው ያሉትን፣ ‘እናንተ ርጉማን ከእኔ ራቁ፤ ለዲያብሎስና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀው ገሃነም እሳት ሂዱ። 42 ምክንያቱም ‘ተርቤ ነበር አላበላችሁኝም፤ ተጠምቼ ነበር አላጠጣችሁኝም፤ 43 እንግዳ ሆኜ ነበር አልተቀበላችሁኝም፤ ተራቊቼ ነበር አላለበሳችሁኝም፤ ታምሜ፣ ታስሬ ነበር፣ እናንተ ግን አልተንከባከባችሁኝም’ ይላቸዋል። 44 እነርሱም መልሰው እንዲህ ይሉታል፤ ‘ጌታ ሆይ፣ ተርበህ ወይም ተጠምተህ ወይም እንግዳ ሆነህ ወይም ተራቊተህ ወይም ታምመህ ወይም ታስረህ ያላገለገልንህ መቼ ነው?’ 45 እርሱም መልሶ፣ ‘እውነት እላችኋለሁ፣ ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ አለማድረጋችሁ ለእኔ አለማድረጋችሁ ነው’ ይላቸዋል። 46 እነዚህ ወደ ዘላለም ቅጣት፣ ጻድቃን ግን ወደ ዘላለም ሕይወት ይሄዳሉ።"
መብራት ይህ እንዲህ ሊሆን ይችላል 1) መብራት ወይም 2) በእንጨት ጫፍ ላይ ጨርቅ በመጠምጠም ጨርቁን በዘይት በመንከር የሚዘጋጅ ችቦ አምስት ሴቶች "አምስት ልጃገረዶች" ትርፍ ዘይት አልያዙም "በመብራታቸው ውስጥ እንጂ ተጠባባቂ ዘይት አልያዙም"
እንቅልፍ ወሰዳቸው "ዐሥሩም ልጃገረዶች ተኙ"
መብራታቸውን አዘጋጁ "በደንብ እንድበራ መብራቸውን አስተካከሉ " ሞኞቹ ለጠቢባኑ እንዲህ አሏቸው "ሞኞቹ ልጃገረዶች ለጠቢባኑ ልጃገረዶች እንዲህ አሏቸው" ዘይታችን ሊያልቅ ነው "በመብራታችን ውስጥ ያለው ዘይት ደምቆ መብረቱን አቁሟል”
ሄዱ "አምስቱ ሞኝ ልጃገረዶች ሄዱ" ዝግጁዎች የሆኑት ተጠባባቂ ዘይት የነበራቸው ልጃገረዶች በሩ ተዘጋ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ብሩን ተዘጋ" ክፈቱልን "ወደ ውስጥ መግባት እንችል ዘንድ በሩን ክፈቱልን" አላውቃችሁም "ማን እንደሆናችሁ አላውቅም”
ይህንን ይመስላል "መንግስ ሰማያት ይህንን ይመስላል" (ተመልከት MAT 25:1) ለሄድ ስነሳ "ለመሄድ ዝግጁ በሆነ ጊዜ” ወይም “ለመሄድ በተነሳ ጊዜ” ሀብቱን አስረከበ "ሀብቱን ይቆጣጠሩለት ዘንድ ስልጣን ሰጣቸው" ሀብቱ "የእርሱ ሀብት” የእርሱ ሀብት መክሊት “አንድ መክሊት” የሃያ ዓመት ደሞዝ ያክላል፡፡ ይህንን በዘመናዊ የገንዘብ መጠን አትለውጡት፡፡ ምሳሌው በማነጻጸር ላይ ያለው አምስት፣ ሁለት እና አንድ እንዲሁም በጣም ትልቅ ሀብትን ነው፡፡ ለተርጓማች ምክር፡ “አምስት ሻንጣ ሙሉ ወርቅ “ ከዚያም አምስት ጠጨማሪ መክሊቶችን አተረፈ “በመክሊቱ ነግዶ አምስት መክሊቶችን አተረፈ”
ሌላ ሁለት አተረፈ "ሌላ ሁለት መክሊቶችን አተረፈ"
አምስት ተጨማሪ መክሊቶችን አተረፈ "አምስት ተጨማሪ መክሊቶችን አተረፍኩ" መክሊቶች በ MAT 25:15 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፤ ጥሩ አድርገሃል "ጥሩ አድርገሃል” ወይም “መልካም አድርገሃል”፡፡ ባሕላቹ ምናልባት የጌታውን ንግግር ይበልጥ መግለጽ የሚያስችል ቃል ይኖረው ይሆናል፡፡
ተጨማር መክሊቶችን አተረፍኩ በ MAT 25:20 ላይ እንዴት እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡ ጥሩ አድርገሃል . . . የጌታው ሰላም በ MAT 25:21 ላይ እንዴት እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡
ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ r እነዚህ ሁለት ዓረፍተ ነገሮች ተመሳሳይ ሀሳብን የሚያስተላልፉ ናቸው፡፡ አገልጋዩ ጌታውን የእርሱ ያልሆነ ምርትን ይሰበስባል በማለት ይከሰዋል፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ምግብን የአንተ ካልሆነ ማሳ ውሰጥ ትሰበስባለህ” " መዝራት በዚያ ዘመን በመሥመር ከመዝራት ይልቅ በጥቂት በጥቂቱ ይበትኑት ነበር፡፡ ተመልከት የአንተ የሆነውን ይኸው ይዤ መጥቻለሁ "ይኼው፣ የአንተን ይዤ መጥቻለሁ"
አንተ ክፉና ሃኬተኛ ባሪያ "አንተ መስራት የማትፈልግ ክፉ ባሪያ ነህ" ካልዘራሁባት እንዳጭድ ካልበተንሁባትም እንድሰበስብ ይህንን ሀሳብ በ MAT 25:24 ላይ እንዴት እንተረጎምክ ተመልከት፡፡ ጠራሴን እወሰዳለሁ “የራሴን ወርቅ እወስዳለሁ" ትርፍ ከባንክ በብድር የሚወሰድ ብር ላይ የሚደመር ትርፍ
ከዚያም የሚበልጥ "የሚበዛ" በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል። "ሰዎች የሚያለቅሱበት እና ጥርሳቸውን የሚያፋጩበት ቦታ"
ማቴዎስ 25፡31-33
አሕዛብም ሁሉ በፊቱ ይሰበሰባሉ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "በፊቱ ሕዝቦችን ሁሉ ይሰበስባል" በፊቱ "ከእርሱ ፊት" አሕዛብን ሁሉ "ከሁሉም ሀገራት የተውጣጡ ሕዝቦች" ፍየሎች ፍየሎች መካከለኛ መጠን ያላቸው በአራት እግሮቻቸው የሚራመዱ ከበግ ጋር ተመሳሳይ የሆኑ አጥቢ እንስሳት ናቸው፡፡ ያስቀምጣቸዋል "የሰው ልጅ ያስቀምጣቸዋል"
ንጉሥ ይህ ኢየሱስ በ MAT 25:31 ላይ ስለ ሰው ልጅ የተናገረው ሌላኛው ሥፍራ ነው፡፡ ንጉሥ . . . በቀኙ ኢየሱስ ስለ ራሱ በሦስተኛ መደብ እየጠናገረ ነው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እኔ፣ ንጉሡ . . . በቀኜ” ኑ፣ የአባቴ ብሩካን ለተርጓሚዎች ምክር: "ኑ አባቴ የባረካችሁ" አባት ይህ ለእግዚአብሔር የማዕረግ ስም ነው ለእናንተ የተዘጋጀውን መንግስት ውረሱ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እግዚአብሔር ያዘጋጀላችሁን መንግስት ውረሱ"
ንጉሥ "የሰው ልጅ" (MAT 25:31) እንዲህ አላቸው "በቀኙ ላሉት እንዲህ አላቸው" ወንድሞች በቋንቋችሁ ወንዶችን እና ሴቶችን የሚካትት ቃል ቃለ ያንን ቃል ተጠቀሙ፡፡ ለእኔ አድርጋችኋል "ለእኔ እንዳደረጋችሁት እቆጥረዋለሁ"
እናንተ ርጉማን "እናንተ እግዚአብሔር የረገማችሁ" ወደ ተዘጋጀላቸው ዘላለማው እሳት ለተርጓሚዎች ምክር: "እግዚብሔር ያዘጋቸው ዘላለማዊ እሳት" መላእክቱ የእርሱ አጋዦች ታርዤ አላለበሳችሁኝም "ታርዤ አላለበሳችሁኝምን” ታምሜ እና ታስሬ "ታምሜ እነ ታስሬ"
እነርሱም እንዲህ ብለው ይመልሱለታል "በግራው ያሉት" (MAT 25:41) ይመልሱለታል ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ለአንዱ "ከእነዚህ የእኔ ሕዝብ ከሆኑን ለአንዱም” ስላላደረጋችሁ "ለእኔ እንዳላደረጋችሁት አስባለሁ" ወይም "በእርግጥ ያልረዳችሁት እኔን ነው" ዘላለማዊ ቅጣት "ማብቂያ ያሌለው ቅጣት" ጻድቃን ወደ ዘላለም ሕይወት ይገባሉ "ጻድቅ የሆኑ ሰዎች ወደ ዘላለም ሕይወት ይገባሉ"
1 ኢየሱስ እነዚህን ቃሎች ተናግሮ በጨረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን እንዲህ አላቸው፤ 2 "ከሁለት ቀን በኋላ ፋሲካ እንደሚሆን ታውቃላችሁ፣ የሰው ልጅም ተሰቅሎ እንዲገደል ተላልፎ ይሰጣል፡፡" 3 ከዚያ የካህናት አለቆቹና የሕዝቡ ሽማግሌዎች ቀያፋ በሚሉት ሊቀ ካህናት ግቢ ውስጥ ተሰበሰቡ፤ 4 ኢየሱስን በረቀቀ ዘዴ ለማሰርና ለመግደል ተማከሩ፡፡ 5 ምክንያቱም፣ በሕዝቡ መሓል ረብሻ እንዳይነሣ በበዓሉ ሰሞን መሆን የለበትም እያሉ ነበር፡፡ 6 ኢየሱስ በቢታንያ በለምጻሙ ስምዖን ቤት 7 ማዕድ ላይ ተቀምጦ እያለ፣ አንዲት ሴት ዋጋው ውድ የሆነ ሽቱ ያለበት የአልባስጥሮስ ብልቃጥ ይዛ መጣችና ራሱ ላይ አፈሰሰች፡፡ 8 ደቀ መዛሙርቱ ይህን ሲያዩ በጣም ተቈጥተው፣ "ይህ ብክነት ምንድን ነው? 9 ይህ እኮ ከፍ ባለ ዋጋ ተሸጦ ገንዘቡን ለድኾች መስጠት ይቻል ነበር" አሉ፡፡ 10 ኢየሱስም ይህን ዐውቆ እንዲህ አላቸው፣ "ይህችን ሴት ለምን ታስቸግሯታላችሁ? ለእኔ መልካም ነገር አድርጋለች፡፡ 11 ድኾች ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ናቸው፤ እኔ ግን ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር አልሆንም፡፡ 12 ይህን ሽቱ እኔ ላይ ባፈሰሰች ጊዜ ለቀብሬ አድርጋዋለች፡፡ 13 እውነት እላችኋለሁ፣ ይህ ወንጌል በመላው ዓለም ሲሰበክ ለእርሷ መታሰቢያ እንዲሆን ይህች ሴት ያደረገችውም ይነገርላታል።" 14 ከዚያም የአስቆሮቱ ይሁዳ የሚባለው ከዐሥራ ሁለቱ አንዱ ወደ ካህናት አለቆቹ ሄዶ፣ 15 "እርሱን አሳልፌ ብሰጣችሁ ለእኔ ምን ትሰጡኛላችሁ?" አላቸው፡፡ እነርሱም ሠላሣ ጥሬ ብር ተመኑለት፡፡ 16 ከዚያ ጊዜ ወዲህ እርሱን አሳልፎ የሚሰጥበትን ምቹ ጊዜ ይጠባበቅ ጀመር፡፡ 17 በቂጣ በዓል በመጀመሪያው ግን ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሱስ መጥተው፣ "የፋሲካን እራት እንድትበላ የት እንድናዘጋጅልህ ትፈልጋለህ?" አሉት፡፡ 18 እርሱም፣ "ከተማው ውስጥ ወዳለ አንድ ሰው ሂዱና፣ 'መምህሩ "ጊዜዬ ደርሷል፤ ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ፋሲካን በአንተ ቤት ማክበር እፈልጋለሁ' ይልሃል በሉት'" አላቸው፡፡ 19 ደቀ መዛሙርቱም ኢየሱስ እንደ ነገራቸው አደረጉ፤ የፋሲካንም እራት አዘጋጁለት፡ 20 ምሽት ላይ ከዐሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት ጋር ለመብላት ተቀመጠ፡፡ 21 በመብላት ላይ እያሉ፣ "እውነት እላችኋለሁ፣ ከእናንተ አንዱ አሳልፎ ይሰጠኛል" አላቸው፡፡ 22 እነርሱ በጣም ዐዘኑ፤ እያንዳንዱም፣ "እኔ እሆንን?" በማለት ይጠያየቁ ጀመር፡፡ 23 እርሱም፣ "አሳልፎ የሚሰጠኝ ከእኔ ጋር እጁን ወደ ሳሕኑ የሚሰደው ነው፡፡ 24 የሰው ልጅ ስለ እርሱ እንደ ተጻፈው ይሄዳል፤ የሰውን ልጅ አሳልፎ ለሚሰጠው ግን ወዮለት! ያ ሰው ባይወለድ ይሻለው ነበር" በማለት መለሰላቸው፡፡ 25 አሳልፎ የሚሰጠው ይሁዳ፣ "መምህር ሆይ፣ እኔ ነኝ እንዴ?" አለው፤ እርሱም፣ "አንተው ራስህ ብለኸዋል" አለው፡፡ 26 በመብላት ላይ እያሉ፣ ኢየሱስ እንጀራ አንሥቶ ባርኮ ቈረሰ፡፡ "እንካችሁ ውሰዱ፣ ብሉት፤ ይህ ሥጋዬ ነው" ብሎ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው፡፡ 27 ጽዋውንም አንሥቶ አመሰገነና ሰጣቸው፤ እንዲህም አላቸው፤ "ሁላችሁም ጠጡት 28 ይህ ለብዙዎች ኀጢአት ይቅርታ የሚፈስ የኪዳኑ ደሜ ነው፡፡ 29 እንደ ገና በአባቴ መንግሥት ከእናንተ ጋር እስክጠጣው ድረስ ከእንግዲህ ከዚህ ወይን ፍሬ እንደማልጠጣ ግን እነግራችኋለሁ፡፡" 30 መዝሙር ከዘመሩ በኋላ ወደ ደብረ ዘይት ተራራ ወጡ፡፡ 31 ያኔ ኢየሱስ፣ "በዚህ ሌሊት ሁላችሁም በእኔ ምክንያት ትሰናከላላችሁ፤ ምክንያቱም፣ 'እረኛውን እመታለሁ በጎቹም ይበተናሉ' ተብሎ ተጽፎአል፡፡ 32 ከተነሣሁ በኋላ ግን ቀድሜአችሁ ወደ ገሊላ እሄዳለሁ" አላቸው፡፡ 33 ጴጥሮስ ግን፣ "ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እንኳ እኔ አልሰናከልም" አለው፡፡ 34 ኢየሱስም፣ "እውነት እልሃለሁ ፣ በዚህች ሌሊት ዶሮ ከመጮኹ በፊት ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ" አለው፡፡ 35 ጴጥሮስም፣ "ከአንተ ጋር መሞት ቢኖርብኝ እንኳ አልክድህም" አለ፡፡ ሌሎችም ደቀ መዛሙርት ሁሉ እንደዚያው አሉ፡፡ 36 ከዚያም ኢየሱስ ከእነርሱ ጋር ጌቴሴማኒ ወደሚሉት ቦታ ሄደ፤ ደቀ መዛሙርቱንም፣ "ወደዚያ ሄጄ እስክጸልይ ድረስ እዚህ ሁኑ" አላቸው፡፡ 37 ጴጥሮስንና ሁለቱን የዘብዴዎስ ልጆች ይዞ ሄደ፤ ያዝንና ይጨነቅም ጀመር፡፡ ከዚያም፣ 38 "ነፍሴ፣ እስከ ሞት ድረስ በጣም ዐዝናለች፡፡ እዚህ ሆናችሁ ከእኔ ጋር ትጉ" አላቸው፡፡ 39 ጥቂት ራቅ ብሎ በመሄድ በግንባሩ ወድቆ ጸለየ፤ "አባት ሆይ፣ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ፤ ይሁን እንጂ፣ የእኔ ፈቃድ ሳይሆን የአንተ ፈቃድ ይሁን" አለ፡፡ 40 ወደ ደቀ መዛሙርቱ ሲመጣ ተኝተው አገኛቸው፤ ጴጥሮስንም፣ "ከእኔ ጋር አንድ ሰዓት ያህል እንኳ መትጋት አልቻላችሁምን? 41 ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፡፡ መንፈስ በእርግጥ ፈቃደኛ ነው፤ ሥጋ ግን ደካማ ነው" አለው፡፡ 42 ለሁለተኛ ጊዜ ጥቂት ፈቀቅ ብሎ ጸለየ፤ "አባት ሆይ፣ እኔ ካልጠጣሁት በቀር ይህ የማያልፍ ከሆነ፣ ፈቃድህ ይሁን" አለ፡፡ 43 እንደ ገና ሲመጣ ዐይኖቻቸው ከብደው ነበርና ተኝተው አገኛቸው፡፡ 44 እንደ ገና ትቶአቸው ሄዶ ለሦስተኛ ጊዜ ያንኑ ቃል ጸለየ፡፡ 45 ከዚያም ኢየሱስ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጥቶ፣ "አሁንም ዐርፋችሁ ተኝታችኋል? ጊዜው ደርሷል፤ የሰው ልጅ በኀጢአተኞች እጅ ተላልፎ ይሰጣል፡፡ 46 እንግዲህ ተነሡ እንሂድ አሳልፎ የሚሰጠኝ ቀርቧል" አላቸው፡፡ 47 ገና እየተናገረ እያለ፣ ከዐሥራ ሁለቱ አንዱ የሆነው ይሁዳ መጣ፣ ከእርሱም ጋር ከካህናት አለቆችና ከሕዝቡ ሽማግሌዎች የመጡ ሰይፍና ዱላ የያዙ ብዙ ሰዎች ነበሩ፡፡ 48 በዚህ ጊዜ አሳልፎ የሚሰጠው፣ "እኔ የምስመው እርሱ ነው፤ ያዙት" የሚል ምልክት ሰጣቸው፡፡ 49 ወዲያውኑ ወደ ኢየሱስ መጥቶ፣ "መምህር ሆይ፣ ሰላም ለአንተ ይሁን!" ብሎ ሳመው፡፡ 50 ኢየሱስም፣ "ወዳጄ፣ የመጣህበትን ጉዳይ ፈጽም" አለው፡፡ ከዚያም መጡ ኢየሱስ ላይ እጃቸውን ጫኑ፣ ያዙትም። 51 ከኢየሱስ ጋር ከነበሩት አንዱ እጁን ዘርግቶ ሰይፍ አወጣ፤ የሊቀ ካህናቱን አገልጋይ ጆሮ መትቶ ቈረጠ፡፡ 52 ያኔ ኢየሱስ፣ "ሰይፍህን ወደ ቦታው መልስ፤ ሰይፍ የሚያነሡ በሰይፍ ይጠፋሉ፡፡ 53 አባቴን ብጠይቅ በብዙ ሺህ የሚቈጠሩ መላእክት የማይልክልኝ ይመስልሃል? 54 እንደዚያ ከሆነ ይህ እንደሚሆን የሚናገረው መጽሐፉ ቃል እንዴት ይፈጸማል?" አለው፡፡ 55 በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ለሕዝቡ፣ "ወንበዴን እንደምትይዙ ሰይፍና ዱላ ይዛችሁ መጣችሁ? በየቀኑ በቤተ መቅደስ ተቀምጬ እያስተማርሁ ነበርሁ፡፡ እናንተም አልያዛችሁኝም ነበር፡፡ 56 የነቢያት መጽሐፍ እንዲፈጸም ይህ ሆኗል" አላቸው፡፡ ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ትተውት ሸሹ፡፡ 57 ኢየሱስን የያዙ ሰዎች የአይሁድ የሕግ መምህራንና ሽማግሌዎቹ ተሰብስበው ወደ ነበሩበት ወደ ሊቀ ካህናቱ ወደ ቀያፋ ቤት ወሰዱት፡፡ 58 ጴጥሮስ ግን ከሩቅ ሆኖ እስከ ሊቀ ካህናቱ ግቢ ድረስ ተከተለው፤ ወደ ውስጥ ገብቶም የሚሆነውን ለማየት ከጠባቂዎቹ ጋር ተቀመጠ፡፡ 59 እርሱን ለማስገደል የካህናት አለቆቹና ሸንጎው ሁሉ በኢየሱስ ላይ በሐሰት የሚመሰክሩበትን ሰዎች እየፈለጉ ነበር፡፡ 60 ምንም እንኳ ብዙ የሐሰት ምስክሮች ቢመጡም፤ በቂ ማስረጃ አላገኙም፡፡ በኋላ ግን ሁለት ሰዎች ወደ ፊት መጥተው፣ 61 "ይህ ሰው፣ 'የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ አፍርሼ በሦስት ቀን ውስጥ እንደ ገና ልሠራው እችላለሁ' ብሏል" አሉ፡፡ 62 ሊቀ ካህናቱ ተነሥቶ፣ "መልስ የለህም? በአንተ ላይ እየመሰከሩብህ ያለው ምንድን ነው?" አለው፡፡ 63 ኢየሱስ ግን ዝም አለ፡፡ ሊቀ ካህናቱም፣ "በሕያው እግዚአብሔር አዝሃለሁ፤ አንተ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆን አለመሆንህን ንገረን" አለው፡፡ 64 ኢየሱስም፣ "አንተው ራስህ አልህ፤ ግን ልንገርህ፣ ከአሁን ጀምሮ የሰው ልጅ በኀይል ቀኝ በሰማይ ደመና ሲመጣ ታያለህ" በማለት መለሰለት፡፡ 65 ከዚያም ሊቀ ካህናቱ ልብሱን ቀደደና፣ "እግዚአብሔርን ተሳድቧል፤ ታዲያ፣ ምስክር የምንፈልገው ለምንድን ነው? አሁን ስድቡን ሰምታችኋል 66 ለመሆኑ፣ ምን ታስባላችሁ?" አለ፡፡ እነርሱም መልሰው፣ "ሞት ይገባዋል" አሉ፡፡ 67 ከዚያም ፊቱ ላይ ተፉበት፣ በጡጫና በጥፊ መቱት፤ 68 "አንተ ክርስቶስ እስቲ ትንቢት ተናገር፡፡ ለመሆኑ፣ በጥፊ የመታህ ማን ነው?" አሉት፡፡ 69 በዚህ ጊዜ ጴጥሮስ እደጅ ግቢው ውስጥ ተቀምጦ ነበር፤ አንዲት አገልጋይ ልጅ ወደ እርሱ መጥታ፣ "አንተም ደግሞ ከገሊላው ኢየሱስ ጋር ነበርህ" አለችው፡፡ 70 እርሱ ግን፣ "ምን እየተናገርሽ እንደ ሆነ አላውቅም" በማለት በሁሉም ፊት ካደ፡፡ 71 ከግቢው ወደሚያስወጣው በር እየሄደ እያለ፣ ሌላ አገልጋይ ልጅ አየችውና እዚያ ለነበሩት፣ "ይህኛውም ሰውየ ከናዝሬቱ ኢየሱስ ጋር ነበረ" አለች፡፡ 72 እርሱም፣ "ሰውየውን አላውቀወም" በማለት በመሐላ ጭምር በድጋሚ ካደ፡፡ 73 ጥቂት ቆየት ብሎ እዚያ ቆመው የነበሩት መጥተው ጴጥሮስን፣ "በርግጥ አንተም ብትሆን ከእነርሱ አንዱ ነህ፤ አነጋገርህ ራሱ ያጋልጥሃል" አሉት፡፡ 74 ከዚያም፣ "ሰውየውን ጨርሶ አላውቀውም" በማለት ይራገምና ይምል ጀመር፤ ወዲያውኑ ዶሮ ጮኸ፡፡ 75 ጴጥሮስ "ዶሮ ሳይጮኽ ሦስቴ ትክደኛለህ" በማለት ኢየሱስ የተናገረውን አስታወሰ፡፡ ከዚያ ወደ ውጭ ወጥቶ ምርር ብሎ አለቀሰ፡፡
በፈጸመ ጊዜ፥ በቋንቋችሁ አዲስ ታሪክ መጀመሪያን ማሳያ መንገድ ካለ ያንን ተጠቀሙ፡፡ እነዚህ ቃላትን በ MAT 24:4-25:46 ውስጥ ያሉትን ቃላት የሰው ልጅ እንዲሰቀል አሳልፈው ይሰጡታል "አንዳንድ ሰዎች የሰው ልጅን ለሚሰቅሉት አሳልፈው ይሰጡታል"
ተሰበሰቡ "በምስጥር" በበዓል ቀን ግን አይደለም ለተርጓሚዎች ምክር፡ “በበዓል ቀን ኢየሱን መግደል የለብንም” በዓል ዓመታዊ የፈስካ በዓል
ምግብ ለመብላት ተቀምጠው ሳለ በጎናቸው ጋደም ብለው፡፡ ሰዎች ምግብ ለመመገብ የሚቀመጡበትን መንገድ የሚገልጽን ቃል መጠቀም ትችላለህ፡፡ አንድት ሴት ወደ እርሱ መጥታ አንድደት ሴት ወደ ኢየሱስ መጥታ የአልባስጥሮስ ጠርሙስ ከለስላሳ ድንጋይ የሚሰራ በጣም ውድ መያዥያ ነው ሽቶ ጥሩ መዓዛ ያለው ዘይት የዚህ ብክነት ምክንያቱ ምንድ ነው? "ይህች ሴት ይህንን ሽቶ በማባከኗ መጥፎ ነገር አድርጋለች!"
ይህችን ሴት ስለምን ታስጨንቋታላችሁ? "ይህችን ሴት ልታስጨንቋት አይገባም!" እናንተ . . . እናንተ . . . አናንተ ደቀ መዛሙርቱ
ለእነርሱ አሳልፎ ይሰጣቸው ዘንድ “አሳልፌ እንድሰጣችሁ” ወይም "ኢየሱስን መያዝ ትችሉ ዘንድ" ሠላሣ ብር ይህ ቃል በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከሚገኘው የትንቢት መልዕክት ጋር ተመሳሳይ ቃል በመሆኑ የገንዘቡን መጠን በዘመናዊ የገንዘብ መጠን ከመጻፍ ይልቅ እንዳለ ማስቀመጡ ተመራጭ ነው፡፡ ለእነርሱ አሳልፎ ለመስጠት "የካህናት አለቆች ኢየሱስን ይዙት ዘንድ ለማገዝ”
እርሱም፦ ወደ ከተማ ከእገሌ ዘንድ ሄዳችሁ፦ መምህር፦ ጊዜዬ ቀርቦአል፤ ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ከአንተ ዘንድ ፋሲካን አደርጋለሁ ይላል በሉት አለ።" ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ለሌላ ሰው ሄደው የኢየሱስን መልክት እንድነገሩት ነገራቸው፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ለደቀ መዛሙርቱ ወደ ከተማ እንዲሄዱ፣ ወደ አንድ ሰው ቤትም እንዲሄዱና መምህር እንዲህ ይልሃል ብለው እንድነግሩት ነገራቸው፡፡ “ጊዜዬ ቀርቦአል፡፡ ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ፋስካን በአንተ ቤት ማሳለፍ እፈልጋለሁ” ብሏል ብላችሁ ንገሩት፡፡ ወይም “ ደቀ መዛሙርቱ ወደ አንድ ሰው ዘንድ እንዲሄዱና መምህራቸው ጊዜዬ ቀርቧል፤ ፋስካን በአንተ ቤት ከደቀ መዛሙርተቼ ጋር ማሳለፍ እፈልጋለሁ ብለው ይነግሩት ዘንድ ላካቸው፡፡” ጊዜዬ አማራጭ ትርጉሞች: 1) "የነገርኳችሁ ጊዜ" (UDB) or 2) "እግዚአብሔር ለእኔ አስቀድሞ ያዘጋጀው ጊዜ" ቀርቧል አማራጨ ትርጉሞች: 1) "ቅርብ ነው" ፋስካን ማክበር "የፋስካን መብል መብላት" ወይም "ልዩ የሆነ ምግብ በመብላት ፋስካን ማክበር"
ምግብ ልመገብ ተቀመጠ በባሕላችሁ ሰዎች ምግብ ለመመገብ የሚቀመጡበትን መንግድ የሚገለጽ ቃልን ተጠቀሙ፡፡ ጌታዬ እኔ በእርግጠኝነት አይደለሁም? "በእርግጠኝነት እኔ አይደለሁም፣ ነኝ እንዴ ጌታዬ?"
የሰው ልጅን አሳልፎ የሚሰጥ ሰው "የሰው ልጅን የሚከዳ ሰው" አንተ ራስህ አልክ "አንተ ራስህ እንዳልከው አንተ ነህ" ወይም "አንተ ራስህ አሁን አመንክ"
ወሰደ . . . ባረከው . . . ሰበረው ይህንን በ MAT 14:19 ላይ በተረጎምከው መሠረት ተርጉመው፡፡
ወሰደ ይህንን በ MAT 14:19. ላይ በተረጎምከው መሠረት ተርጉመው፡፡ ሰጣቸው "ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው" ስለቃል ኪዳኑ የሚፈሰው ደሜ ነው "ኪዳኑ የጸና መሆኑን የሚያሳይ ደም ነው”ወይም “ኪዳን እንዲቻል ደረገ ደም ነው" የሚፈሰው "በሞቱ ጊዜ የሚፈሰው” ወይም “በቅርቡ ከአካሌ የሚፈሰው” ወይም ስሞት ከአካሌ የሚፈስ ደም ነው” የወይንን ፍሬ "ወይን" በአባቴ መንግስት ውስጥ አዲሱን ከእናንተ ጋር እስከሚጠጣት ጊዜ ድረስ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው፣ ደሙ በእርሱ ለሚያምኑት ከአባት ዘንድ የዘላለም የኃጢአት ይቅርታን ያስገኘው ኢየሱስ አባቱ በመስቀል ላይ የቀረበውን መስዋእት መርካቱን የሚያከብርበት ነው፡፡ “አባት” እና “ልጅ” የሚለው ቃል በሥላሴ አካላት መካከል መቀራረብ እና ቤተሰባዊ ህብረት ያለ መሆኑን የሚያሳይ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል በመሆኑን እንዳለ በቁሙ መቀመጥ ይኖርበታል፡፡
መዝሙር ለእግዚአብሔር የሚቀርብ የሚስጋና መዝሙር ይወድቃሉ "ትተውኝ ይሄዳሉ" የመንጋውም በጎች ይበተናሉ ለተርጓሚዎች ምክር፡ 1) "ሁሉን የበጎች መንጋዎች ይበተናሉ " (UDB) ወይም 2) "የበጎች መንጋዎቹ በሁሉም አቅጣጫ ይበተናሉ" የበጎች መንጋ ደቀ መዛሙርቱ ከተነሳሁ በኋላ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "እግዚአብሔር ካስነሳኝ በኋላ"
ይበተናሉ ይህንን በ MAT 26:31 ላይ በተረጎምከው መሠረት ትረጉም ዶሮ ሳይጮኽ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "ፀሐይ ከመውጣቱ በፊት" ዶሮ ከመጮኹ rooster ልነጋጋ ሲል ዶሮ የሚያሰማቸው ከፍተኛ ጩኸት የዶሮ ጩኸት ዶሮ የሚያሰማው ጩኸት
ኃዘን በጣም አዘነ
በፊቱ ወድቆ ለመጸለይ ሆን ብሎ ፊቱን በመሬት ላይ መድፋት አባቴ ይህ በእግዚአብሔር እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያሳይ የእግዚአብሔር የማዕረግ ስም ነው ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ ከ “ይህ ጽዋ” የሚለው ቃል ኢየሱስ ሊያልፈበት ያለውን መከራ የሚያመለክት ነው፡፡ ይሁን እንጂ የእኔ ፈቃድ ሳይሆን የአንተ ፈቃድ ይሁን ይህ በሙሉ ዐዓረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “እኔ የሚፈልገው አታደርግ ነገር ግን አንተ የሚትፈልገውን አድርግ”"
ማቴዎስ 26፡ 42-44
ሄደ "ኢየሱስ ሄደ" እኔ ካልጠጣሁት "የዚህ የመከራ ጽዋ የማልጠጣ ከሆነ" አባቴ ይህ በእግዚአብሔር እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያሳይ የእግዚአብሔር የማዕረግ ስም ነው ዓይኖቻቸው በእንቅልፍ ከብደው ነበር "እንቅልፍ ይዞዋቸው ነበር"
ሰዓቲቱ ቀርባለች "ጊዜው ቀርቧል" በኃጡአተኞች እጅ "ኃጢአተኞች" ተመልከቱ "አሁን ለምናገረው ነገር ትኩረት ስጡ"
በመናገር ላይ ሳለ "ኢየሱስ እየተናገረ ሳለ" እንዲህ አለ “የሚስመው እርሱ ነውና ያዙት” "እርሱ የሚስመው እርሱ ነውና ያዙት” የሚስመው "አሁን የሚስመው" ወይም "እኔ የሚስመው ሰው" (UDB) መሳም ለአንድ ታላቅ መምህር የሚቀርብ አክብሮት
ወደ ኢየሱስ መጥቶ "ይሁዳ ወደ ኢየሱስ መጥቶ" ሳመው "በመሳም ሰላም አለው" ኢየሱስን ያዙት ኢየሱስን ልጎዱት ያዙት ያዙት እስረኛ አደረጉት
እነሆ ጸሐፊው አዲስ ሰውን በታሪኩ ውስጥ አካቷል፡፡ በቋንቋችሁ ይህንን ለማደረግ የሚያስችል መንገድ ሊኖር ይችላል፡፡ አባቴን እንድለምን እርሱም አሁን ከአሥራ ሁለት ጭፍሮች የሚበዙ መላእክት እንዲሰድልኝ የማይቻል ይመስልሃልን? ለተርጓሚዎች ምክር፡ "አባቴን መጥራት እንደሚችል፣ እርሱ ደግሞ ከዐሥራ ሁለት ጭፍሮች በላይ መላእክትን ልልክልኝ እንደሚችል ማወቅ ነበረባችሁ፡፡” አባቴ ይህ በእግዚአብሔር እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያሳይ የእግዚአብሔር የማዕረግ ስም ነው ከዐሥራ ሁለት ጭፍሮች በላይ መላእክት የመላእክቱ ትክክለኛ ቁጥት ይህን ያኸል አስፈላጊ አይደለም ጭፍሮች የሮማዊያን ሠራዊት አከፋፈል ሆኒ አንዱ ስድት ሺህ ወታደሮችን ይይዛል
ወንበዴን እንደምትይዙ ሰይፍና ጐመድ ይዛችሁ ልትይዙኝ ወጣችሁን? ለተርጓማች ምክር፡ “እኔ ወንበዴ እንዳልሆንኩ ታውቃላችሁ ስለዚህ እኔት ለመያዝ ሰይፍ እና ጎመድ ይዛችሁ መምጣታችሁ ስህተት ነው፡፡” ጎመድ ሰዎችን ለመምታት የሚሆን ጠንካራ ደረቅ ዱላ ተውት በቋንቋችሁ ከእርሱ ጋር መሆን ስገባቸው ትተውት መሄዳቸውን ለማመልከት የሚሆን ቃል ካለ ይህንን ቃል ተጠቀሙ፡፡
ሁለት ሰዎች ወደፊት መጥተው "ሁለት ሰዎች ቀርበው” (UDB) ወይም "ሁለት ምስክሮች ቀርበው" “እነዚህ ሰዎች እንዲህ አሉ፣ እኔ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ አፍርሼ በሦስት ቀን ውስጥ እንደገና እገነባለሁ” ለተርጓሚዎች ምክር: "የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ አፍርሶ በሦስት ቀናት ውስጥ መልሶ እንደሚገነባ ስናገር ሰምተናል ብለው መሰከሩበት” ይህ ሰው እንዲህ አለ "ይህ ሰው ኢየሱስ እንዲህ አለ"
በእርሱ ላይ መሰከሩበት "ምስክሮቹ በኢየሱስ ላይ መሰከሩ" የእግዚብሔር ልጅ ይህ በክርስቶስ እና በእግዚአብሔር መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያሳይ በጣም አስፈላጊ የሆነ ስም ነው፡፡ አንተ ራስህ አልህ ኢየሱስ ራሱ እርሱ “ክርስቶስ፣ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ” አረጋግጧል፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “አንተው ራስህ እንዳልከው ነኝ” ወይም “አንተ ራስህ አሁን አመንክ” ነገር ግን እላችኋለሁ፥ እንግዲህ ወዲህ ኢየሱስ ለሊቀ ካህኑ እና በዚያ ላሉት ሰዎች በመመናር ላይ ነው፡፡ እንግዲህ ወዲህ የሰው ልጅ በኃይል ቀኝ ሲቀመጥ አማራጭ ትርጉሞች ›፡ 1) የሰው ልጅን ወደፊት የሆነ ጊዜ ያዩታል ወይም 2) “አሁን” የሚለው ቃ የሚያመለክተው የሰው ልጅ የሞተበትን፣ ከሞቱ የተነሳበትን እና ወደ ሰማይ ያረገዘበት ጊዜ ነው፡፡ በኃይል ቀኝ "ሁሉን ቻይ በሆነው በእግዚአብሔር ቀኝ” በሰማይም ደመና ሲመጣ "በሰማይ ዳመና ሆኖ ወደ መሬት ሲመጣ"
ሊቀ ካህኑ ልብሱን ቀደደ ልብስ መቅደድ የሚያሳዝን ነገር በመሆኑ የተከሰተ ንዴት ምልክት ማሳያ ነው፡፡ እንዲህ ሲሉ መለሱለት "የአይሁድ መሪዎች እንዲህ ሲሉ መለሱለት"
ከዚያ እነርሱ አማራጭ ትርጉሞች፡ “ከዚያም ከእነርሱ መካከል አንዳንዶቹ” ወይም “ከዚያ ወታደሮቹ” ፊቱ ላይ ተፉበት ይህ ስድብ ነው ትንቢት ንገረን በዚህ ሥፍራ “ትንቢት ንገረን” ማለት “በእግዚአብሔር ኃይል ንገረን” ማለታቸው እንጂ “ወደፊት የሚሆነውን ነገር ንገረን ማለታቸው አይደልም”
እናንተ ስለምትሉት ነገር የማውቀው ነገር የለኝም ጴጥሮስ ይህች ገረድ እያለች ያለው ነገር ገብቶታል፡፡ ከኢየሱስ ጋር የነበረ መሆኑን ለመካድ ይህንን ቃል ተጠቀሟል፡፡
እንዲህ ሲል "ጴጥሮስ እንዲህ ባለ ጊዜ" መግቢያ በግቢው አጥር መግቢያ በር
ከእነርሱ አንዱ "ከኢየሱስ ጋር ከነበሩት አንዱ ነው" የንግግር ቅላጼህ ያስታውቃል "ከገሊላ እንደሆንክ ከንግግርህ ቅላጼ ማወቅ እንችላለን ምክንያቱም የሚትናገረው እንደ ገሊላ ሰዎች ነው፡፡" እምላለሁ “ይህን ሰው ፈጽሞ አላውቀውም” ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ይህን ሰው አላውቀውም”
1 ጠዋት በማለዳ የካህናት አለቆቹና የሕዝቡ ሽማግሌዎች ሁሉ ኢየሱስን ለመግደል ተማከሩ። 2 አስረው ወሰዱትና ለአገሩ ገዢው ለጲላጦስ አስረከቡት። 3 አሳልፎ የሰጠው ይሁዳ ኢየሱስ እንደ ተፈረደበት ባየ ጊዜ ተጸጸተ፣ ሠላሣውን ጥሬ ብር ለካህናት አለቆቹና ለሽማግሌዎቹ መልሶ፣ 4 "ንጹሕ ሰው አሳልፌ በመስጠት በድያለሁ" አለ። እነርሱ ግን፣ “ታዲያ፣ እኛን ምን አገባን? የራስህ ጉዳይ ነው” አሉት። 5 ከዚያም ጥሬ ብሩን በቤተ መቅደሱ ውስጥ ወረወረና ወጥቶ ራሱን ሰቀለ። 6 የካህናት አለቆቹ ጥሬ ብሩን ወስደው፣ “ይህ የደም ዋጋ ስለ ሆነ፣ ከቤተ መቅደሱ ገንዘብ ጋር መቀላቀል ተገቢ አይደለም” አሉ። 7 እርስ በርሳቸው ተነጋግረው የእንግዶች መቀበሪያ እንዲሆን የሸክላ ሠሪውን መሬት ገዙበት። 8 ከዚህ የተነሣ ያ መሬት እስከዚህ ጊዜ ድረስ፣ “የደም መሬት” ተባለ። 9 በነቢዩ ኤርምያስ፣ “የእርሱ ዋጋ እንዲሆን የእስራኤል ልጆች የተመኑለትን ሠላሣ ጥሬ ብር ወሰዱ፣ 10 እግዚአብሔር እንደ አዘዘኝ ለሸክላ ሠሪው መሬት ከፈሉት” ተብሎ የተነገረው ተፈጸመ። 11 ኢየሱስ በአገረ ገዢው ፊት ቆመ፤ አገረ ገዢውም፣ “አንተ የአይሁድ ንጉሥ ነህ እንዴ?” በማለት ጠየቀው። ኢየሱስም፣ “አንተ እንዳልኸው ነው” በማለት መለሰለት። 12 የካህናት አለቆችና፣ ሽማግሌዎቹ፣ ሲከሱት ምንም አልመለሰም። 13 በዚህ ጊዜ ጲላጦስ፣ “በአንተ ላይ የሚያቀርቡትን ክስ ሁሉ አትሰማምን?” አለው። 14 እርሱ ግን አንድ ቃል እንኳ ስላልመለሰለት አገረ ገዡ በጣም ተደነቀ። 15 በዓል ሲመጣ አገረ ገዢው ሕዝቡ የሚፈልጉትን አንድ እስረኛ የመፍታት ልማድ ነበረው። 16 በዚያን ጊዜ በርባን የሚሉት ከባድ ወንጀለኛ በእስር ቤት ውስጥ ነበር። 17 ተሰብስበው እያለ ጲላጦስ፣ “ማንን እንድፈታላችሁ ትፈልጋላችሁ፣ በርባንን ወይስ ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን?” አላቸው። 18 ምክንያቱም አሳልፈው የሰጡት በቅናት መሆኑን ያውቅ ነበር። 19 በፍርድ ወንበር ላይ ተቀምጦ እያለ ሚስቱ፣ “በዚያ ንጹሕ ሰው ላይ ምንም እንዳታደርግ፤ እርሱን በተመለከተ በዚህ ሌሊት በሕልሜ ብዙ መከራ ተቀብያለሁ” የሚል ቃል ላከችበት። 20 የካህናት አለቆቹና ሽማግሌዎቹ በርባን እንዲፈታና ኢየሱስ እንዲገደል እንዲጠይቁ ሕዝቡን ቀሰቀሱ። 21 አገረ ገዢው፣ “ከሁለቱ የትኛውን እንድፈታላችሁ ትፈልጋላችሁ?” በማለት ጠየቃቸው። እነርሱም፣”በርባንን” አሉ። 22 ጲላጦስም፣ “ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስንስ ምን ላድርገው?” አላቸው። ሁሉም፣ “ስቀለው” በማለት መለሱ። 23 እርሱም፣ “ለምን፣ የሠራው ወንጀል ምንድንነው?” አላቸው። እነርሱ ግን፣ “ስቀለው” እያሉ የበለጠ ጮኹ። 24 ስለዚህ ምንም ማድረግ እንዳልቻለና እንዲያውም ዐመፅ እየተነሣ መሆኑን ጲላጦስ ባየ ጊዜ፣ በሕዝቡ ፊት እጁን በውሃ ታጥቦ፣ “እኔ ከዚህ ንጹሕ ሰው ደም ነጻ ነኝ፤ ከእንግዲህ ኀላፊነቱ የእናንተው ነው” አለ። 25 ሕዝቡ ሁሉ፣ “ደሙ በእኛና በልጆቻችን ላይ ይሁን” አሉ። 26 ከዚያም በርባንን ፈታላቸው፤ ኢየሱስን ግን ገርፎ እንዲሰቅሉት ሰጣቸው። 27 የአገረ ገዢው ወታደሮች ኢየሱስን ወደ ገዢው ግቢ ወሰዱትና ወታደሮቹን ሁሉ ሰበሰቡ። 28 ልብሱን ገፍፈው ቀይ ልብስ አለበሱት። 29 ከዚያም የእሾኽ አክሊል ሠርተው በራሱ ላይ ደፉ፣ በቀኝ እጁ በትር አስያዙት፤ በፊቱ ተንበርክከውም፣ “የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፣ ሰላም ለአንተ ይሁን!” እያሉ አሾፉበት። 30 ፊቱ ላይም ተፉበት፤ በትሩን ወስደው ራሱን መቱት። 31 ካፌዙበትም በኋላ ልብሱን አውልቀው የራሱን ልብስ አለበሱትና እንዲሰቀል ወሰዱት። 32 እንደወጡ ስምዖን የሚሉት የቀሬና ሰው አገኙ፤ መስቀሉን እንዲሸከም አስገደዱት። 33 ጎልጎታ ወደሚባል ቦታ መጡ፤ ትርጕሙም “የራስ ቅል” ማለት ነው። 34 ከሐሞት ጋር የተቀላቀለ የወይን ጠጅ ሰጡት፤ እርሱ ግን ቀምሶ ሊጠጣው አልፈለገም። 35 በሰቀሉት ጊዜ ዕጣ በመጣጣል ልብሶቹን ተከፋፈሉ፤ 36 ተቀምጠው ይጠብቁትም ጀመር። 37 ከራሱ በላይ፣ “ይህ የአይሁድ ንጉሥ ኢየሱስ ነው” የሚል የክስ ጽሕፈት አኖሩ። 38 ሁለት ወንበዴዎች አንዱ በቀኙ ሌላው በግራው በኩል ከእርሱ ጋር ተሰቅለው ነበር። 39 የሚያልፉ ሰዎችም ሰደቡት፤ ራሳቸውን እየነቀነቁም 40 “ቤተ መቅደሱን የምታፈርስና በሦስት ቀን የምትሠራ ራስህን አድን። የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ ከመስቀል ውረድ” ይሉት ነበር። 41 በተመሳሳይ መንገድ የካህናት አለቆች፣ ከአይሁድ የሕግ መምህራንና ከሽማግሌዎቹ ጋር አብረው፣ 42 “ሌሎችን አዳነ፤ ራሱን ግን ማዳን አልቻለም። እርሱ የእስራኤል ንጉሥ ነው፣ ከመስቀል ይውረድ፣ ከዚያም እኛ እናምንበታለን። 43 በእግዚአብሔር ተማምኖአል፤ እርሱ ከወደደ ያድነው፤ ምክንያቱም፣ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሏል" እያሉ ያፌዙበት ነበር። 44 ከእርሱ ጋር የተሰቀሉት ወንበዴዎችም እንዲሁ ይሰድቡት ነበር። 45 ከስድስት ሰዓት ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ ምድሩን ሁሉ የሚሸፍን ጨለማ ሆነ። 46 በዘጠኝ ሰዓት ኢየሱስ፣ “ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰባቅታኒ” በማለት በታላቅ ድምፅ ጮኸ፤ ትርጒሙም፣ “አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ” ማለት ነው። 47 እዚያ ቆመው ከነበሩት አንዳንዶቹ ይህን ሲሰሙ፣ “ኤልያስን እየተጣራ ነው” አሉ። 48 ወዲያውኑ ከእነርሱ አንዱ ሮጦ ሄደና ስፖንጁን የኮመጠጠ ወይን ጠጅ ውስጥ ነክሮ በሸንበቆ በትር አድርጎ እንዲጠጣ ሰጠው። 49 የተቀሩትም፣ "እስቲ ተዉት፤ ኤልያስ መጥቶ ሲያድነው እናያለን” አሉ። 50 ከዚያም ኢየሱስ በድጋሚ በታላቅ ድምፅ ጮኾ መንፈሱን ሰጠ። 51 የቤተ መቅደሱ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ለሁለት ተከፈለ፤ ምድር ተናወጠ፤ ዐለቶችም ተሰነጠቁ፤ 52 መቃብሮች ተከፈቱ፤ አንቀላፍተው የነበሩ ብዙ ቅዱሳን ተነሡ። 53 ከትንሣኤው በኋላ ከመቃብር ወጡ፤ ወደ ቅድስት ከተማ ገብተው ለብዙዎች ታዩ። 54 የመቶ አለቃውና ኢየሱስን ይጠብቁ የነበሩ ሰዎች የምድር መናወጡንና የሆኑትን ነገሮች ሲያዩ በጣም ፈርተው፣ "በእውነት ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ነው" አሉ። 55 እርሱን ለመርዳት ከገሊላ ጀምሮ ኢየሱስን ተከትለው የነበሩ ብዙ ሴቶች በሩቅ ሆነው ይመለከቱ ነበር። 56 ማርያም መግደላዊት፣ የያዕቆብና የዮሴፍ እናት ማርያም፣ እንዲሁም የዘብዲዎስ ልጆች እናት ከእነርሱ ጋር ነበሩ። 57 ምሽት ላይ ዮሴፍ የሚሉት አንድ ሀብታም ሰው ከአርማትያስ መጣ፤ እርሱ ራሱ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ነበር። 58 ወደ ጲላጦስ መጥቶ የኢየሱስን አስከሬን እንዲሰጠው ጠየቀ። ጲላጦስም እንዲሰጠው አዘዘ። 59 ዮሴፍ አስከሬኑን ወስዶ፤ በንጹሕ ናይለን ጨርቅ ጠቀለለውና 60 ለራሱ ከዐለት በሠራው መቃብር ውስጥ አኖረው። ከዚያም ትልቅ ድንጋይ አንከባልሎ መቃብሩ ደጃፍ ላይ አድርጎ ሄደ። 61 ማርያም መግደላዊትና ሌላዋ ማርያም መቃብሩ ፊት ለፊት ተቀምጠው በዚያ ነበሩ። 62 በሚቀጥለው ቀን ከዝግጅት በኋላ የካህናት አለቆቹና ፈሪሳውያን በአንድነት ከጲላጦስ ጋር ተሰበሰቡ። 63 እንዲህም አሉ፣ "ጌታ ሆይ፣ ያ አሳሳች በሕይወት በነበረ ጊዜ፣ 'ከሦስት ቀን በኋላ እነሣለሁ' ብሎ እንደ ነበር ትዝ አለን። 64 ስለሆነም፣ እስከ ሦስተኛው ቀን ድረስ መቃብሩ በጥንቃቄ እንዲጠበቅ እዘዝ፤ አለበለዚያ ግን፣ ደቀ መዛሙርቱ መጥተው ሥጋውን ይሰርቁና ለሕዝቡ፣ ‘ከሞት ተነሣ’ ይላሉ፤ የኋላው ስሕተት ከመጀመሪያው የከፋ ይሆናል” አሉት። 65 ጲላጦስም፣ “ጠባቂ ወስዳችሁ፣ የሚቻላችሁን ያህል በጥንቃቄ እንዲጠበቅ አድርጉ” አላቸው። 66 ስለዚህ ሄደው መቃብሩ በጥንቃቄ እንዲጠበቅ አደረጉ፤ ድንጋዩን አተሙ፤ ጠባቂ አኖሩ።
ከዚያም ይሁዳ ይንን ባደረገ ጊዜ በቋንቋችሁ የተጀመረን አንድ ታሪክ አቋርጦ ሌላ ታሪክ መጀመሩን የሚያመለክት ቃል ካለ ይህንን ቃል በዚህ ሥፍራ ላይ ተጠቀም፡፡ ሠላሳ ብር የካህናት አለቆች ይሁዳ ኢየሱስን አሳልፎ ይሰጣቸው ዘንድ ለይዳ የሰጤት ብር ነው (MAT 26:15) ንጹሕ ደም "መሞት የማይገባው ሰው"
ይህንን ማድረግ ሕጋዊ አይደለም "ሕጋችን ይህንን እዲናደረግ አይፈቅድልንም" እንድናስቀመጥ "ይህንን ብር እንድናስቀመጥ" የደም ዋጋ አንድ ሰው እንዲሞት የሚከፈል ገንዘብ የሸክላ መሬት ይህ መሬት በኢየሩሳሌም ከተማ ውስጥ ምጻተኛ የሆነ ሰው ቢሞት የሚቀበርበት ቦታ ነው፡፡ እስከዛሬ ድረስ ጸሐፊው መጽሐፉን እስከ ጻፈበት ጊዜ ድረስ
ነብዩ ኤርሚያስ እንዲህ በማለት የተናገረው የትንቢት ቃል ተፈተመ "ነብዩ ኤርሚያስ ይህንን የትንቢት ቃል ተናገረ፤ እንደተናገውም ሆነ፡፡ ነብዩ ያለው እንዲህ ነው” የእስራኤል ሕዝቦች የእስራኤል የሃይማኖት መሪዎች እንደገመተኝ ነብዩ ኤርሚያስ እንደገመተው
አሁን በቋንቋችሁ ውስጥ የተቋረጠው ታሪክ መቀጠሉን የሚያሳይ ቃል ካለ ይህንን ቃል መጠቀሙ መልካም ይሆናል፡፡ ሀገረ ገዥው ጵላጦስ (MAT 27:1) አንተ አልክ "አንተ ራሰህ ተቀበልከው" ይሁን እንጂ በካህናት ለቆች እና ሽማግሌዎች ክስ በቀረበበት ጊዜ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ነገር ግን የካህናት አለቆች እና ሽምግሌዎች በከሰሰቱት ጊዜ” በእንተ ላይ የሚያቀርቡትን ክስት አትሰማምን? "መጥፎ ነገር አድርጓል ብለው ለሚከሱህ ሰዎች ምንም ምላሽ አለመስጠትህ አስገርሞኛል!” አንዲት ቃል፣ በዚህም ገዥው በጣም ተገረመ፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ "አንዲት ቃል፤ ይህ ነገር ገዥውን እጅግ አስገረመው፡፡"
አሁን ይህ ቃል በታሪኩ ፍሰት ውስጥ የእረፈት ጊዜ መኖሩ የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህም ጸሐፊው በ [MAT 27:17] ክብረ በዓል ፋስካ በዓል የሚከበርበት ጊዜ (MAT 26:2) በሕዝቡ የተመረጠው እስረኛ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ሕዝቡ የመረጠው እስረኛ” ነውጠኛ መጥፎ ነገር በማድረግ በጣም የሚታወቅ ሰው
አሳልፈው ሰጡት ጵላጦስ ይፈርድበት ዘንድ "ኢየሱስን ወደ እርሱ አመጡ” በዚያም ተቀምጦ ሳለ "ጵላጦስ በዚያ ተቀምጦ ሳለ" በፍርድ ወንበር ላይ ተቀምጦ ሳለ ፍርድን እንደሚሰጥ ሰው በስራው ላይ ሳለ መልዕክት ላከ "መልዕክት ላከ"
ጠየቃቸው "ሕዝቡን ጠየቀ"
ምን አድርጎ ነው "ኢየሱስ ምን አደረገ" በታላቅ ድምፅ ጮኹ "ሕዝቡም በታላቅ ድምፅ ጮኹ" ደሙ "ሞቱ"
ደሙ በእኛ እና በልጆቻችን ላይ ይሁን፡፡ "አዎ! እኛ እና የእኛ ልጆች በደስታ እርሱን እንዲሞት የማድረግ ኃላፊነቱን እንወስዳን!"
የገዥው ግቢ አማራጭ ትርጉሞች: 1) ወታደሮቹ የሚኖሩበት ሥፍራ ወይም 2) የገዥዎቹ መኖሪያ ልብሱን ገፈፉት "ልብሱን ገፈፉት" (UDB) ቀይ ልብስ ደማቅ ቀይ ልብስ ተዘባበቱበት "እናከብርሃን" ወይም "ረጅም እድሜ ኑር"
እነርሱ . . . እነርሱ . . . እነርሱ የጵላጦስ ወታደሮች እርሱ . . . እርሱ . . . እርሱ . . . እርሱ . . . እርሱ ኢየሱስ
ከዚያ በወጡ ጊዜ "ከእየሩሳሌም እየወጡ ሳለ" የእርሱን መስቀል ይሸከም ዘንድ አስገደዱት "ወታደሮቹ የኢየሱስን መስቀል ይሸከም ዘንድ አስገደዱት" ጎልጎታ ወደ ተባለ ሥፍራ "ሰዎች ጎልጎታ ብለው ወደሚጠሩት ሥፍራ" ሐሞት ሰውነታችን ምግብን ለመፍጨት የሚጠቀምበት ብጫ ፈሳሽ ነገር
ልብስ ኢየሱስ ይለብሰው የነበረውን ልብስ
ማቴዎስ 27፡ 38-40
ከእርሱ ጋር ሁለት ወንበዴዎች ተሰቅለው ነበር ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ወታደሮቹ ሁለት ወንበዴዎችን ከኢየሱስ ጋር ሰቀሉ”፡፡ ራሳቸውን እየነቀነቁ ይህንን ያደረጉት በኢየሱስ ላይ ለመሳለቅ ነው፡፡ አንተ በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ከመስቀል ውረድ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ በመሆኑ ስለማያምኑ ይህን እንዲያረጋግጥላቸው ጠየቁት፡፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “አንተ በእርግጥ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ከመስቀል በመውረድ ይህንን አረጋግጥልን አሉት” የእግዚብሔር ልጅ ይህ በክርስቶስ እና በእግዚአብሔር ልጅ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያስረዳ በጣም አስፈላጊ የሆነ ስም ነው፡፡
ሌሎቹን አዳነ ነገር ግን ራሱን ማዳን አልቻለም አማራጭ ትርጓሜዎች፡ 1) የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስ ሌሎችን እንዳዳነ አያምኑም ወይም ራሱንም ማዳን እንደሚችል አያምኑም ወይም 2) ሌሎችን እንዳዳነ ያምናሉ ነገር ግን ራሱን ማዳን ስላልቻለ ሳቁበት፡፡ እርሱ የእስራኤል ንጉሥ ነው መሪዎቹ የእስራኤል ንጉሥ እንደሆነ አያምኑም ነበር
የእግዚብሔር ልጅ ይህ በክርስቶስ እና በእግዚአብሔር ልጅ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያስረዳ በጣም አስፈላጊ የሆነ ስም ነው፡፡ ከእርሱ ጋር የተሰቀሉት ወንበዴዎችም "ወታደሮቹ ከኢየሱስ ጋር የሰቀሏቸው ወንበዴዎችም
ጮኸ "ተጣራ" ወይም "በታላቅ ድምፅ ጮኸ" ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ? ተርጓሚዎች ብዙ ጊዜ እነዚህ ቃላት እንዳሉ በዕብራይስጥ ቋንቋዎች ይተዋቸዋል፡፡
ከእነርሱ መካከል አንዱ አማራጭ ትርጉሞች፡ 1) ከወታደሮቹ መካከል አንዱ ወይም 2) ቆመው ከሚመለከቱት መካከል አንዱ እስፖንጅ ከባሕር እንስሳት መካከል የሚሰበሰብ ውሃ ለመያዥያነት የሚገለግል፡፡ ለእርሱ ሰጠው "ለኢየሱስ ሰጠው
እነሆ ይህ ቃል ሰዎች ከዚህ በኋላ ለሚነገረው ነገር አጽኖት እንዲሰጡ የሚጨመር ቃል ነው፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ተመልከቱ” ወይም “አድምጡ” ወይም “አሁን ለምነግራችሁ ነገር ትኩረት ስጡ”:: መቃብሮችም ተከፈቱ፥ ተኝተው ከነበሩትም ከቅዱሳን ብዙ ሥጋዎች ተነሡ፤ "እግዚብሔር መቃብሮችን ከፍቶ ከሞቱት መካል ብዙ ቅዱሳንን ከሞት አስነሣ ተኝተው የነበሩ "የሞቱ" መቃብሮችም ተከፍተው . . . ለብዙዎች ታዩ። ሁኔታዎቹ የተፈጸሙበት የጊዜ ቅደም ተከተል ግልጽ አይደለም፡፡ ሊሆነ የሚችሉት የጊዜ ቅደም ተከተሎች፡ ኢየሱስ ሲሞት በተነሳው ከተነሳው የምድር መንቀጥቀጥ በኋላ መቃብሮች ተከፈቱ 1) ቅዱሳን ተነሱ፣ ኢየሱስ ከሞት ተነሣ እና ቅዱሳን ወደ ከተማው ገቡ እና ለብዙዎች ታዩ ወይም 2) ኢየሱስ ከሞት ተነሣ እና ቅዱሳን ከሞት ተነሡ፣ ወደ ከተማ ገቡ እና ለብዙዎች ታዩ፡፡
የእግዚብሔር ልጅ ይህ በክርስቶስ እና በእግዚአብሔር ልጅ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያስረዳ በጣም አስፈላጊ የሆነ ስም ነው፡፡
ከዚያም ጵላጦስ ይሰጠው ዘንድ አዘዘ "ከዚያም ጵላጦስ ወታደሮቹን የኢየሱስ በድን ለዮሴፍ ይሰጠው ዘንድ አዘዘ፡፡”
ለስላሳ ጨርቅ ብዙ ብር የሚያወጣ ጨርቅ ከመቃብሩ ተቃራኒ "ከመቃብሩ ማዶ"
ዝግጅት ለፋስካ በዓል የሚዘጋጁበት ጊዜ ነበር ይህ አሳች በሕይወት እያለ "አሳቹ ኢየሱስ በሕይወት እያለ"
ጠባቂ 4 እስከ 16 የሮማዊያን ወታደሮች ድንጋዩን በማሕተም አትመው አማራጭ ትርጓሜዎች: 1) በድንጋዩ ዙሪያ ገመድ በማድረግ ወደ መቃብሩ ሌላኛው መግቢያ ጋር በማያያዝ አሠሩት ወይም 2) በድንጋዩ ና በግድግዳው መካከል ማሕተም አኖሩ፡፡ ጠባቂዎች በዚያ አኖሩ "ወታደሮቹ ሰዎች መቃብሩን መንካት የማይችሉበት ቦታ እንዲቆሙ ትዕዛዝ ሰጡ፡፡"
1 ሰንበት እንዳለፈ፣ በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ማለዳ፣ ማርያም መግደላዊትና ሌላዋ ማርያም ወደ መቃብሩ መጡ። 2 የጌታ መልአክ ከሰማይ ወርዶ ነበርና ታላቅ የምድር መንቀጥቀጥ ሆነ፤ መጥቶም ድንጋዩን አንከባልሎ በላዩ ተቀመጠ። 3 መልኩ እንደ መብረቅ፣ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ነበር። 4 ጠባቂዎቹ በፍርሃት ተንቀጠቀጡ፤ እንደ ሞተ ሰውም ሆኑ። 5 መልአኩም እንዲህ በማለት ተናገረ፤ "አትፍሩ፤ ተሰቅሎ የነበረውን ክርስቶስን እንደምትፈልጉ አውቃለሁ። 6 እንደ ተናገረ ተነሥቷል እንጂ፣ እዚህ የለም፤ ኑና የነበረበትን ቦታ እዩ። 7 በፍጥነት ሄዳችሁ፣ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ በማለት ንገሩ፤ 'እርሱ ከሞት ተነሥቷል፤ ቀድሟችሁ ወደ ገሊላ ይሄዳል። እዚያ ታዩታላችሁ።' እንግዲህ ነግሬአችኋለሁ።” 8 ሴቶቹ ፈጥነው በፍርሃትና በታላቅ ደስታ ለደቀ መዛሙርቱ ለመንገር ከመቃብሩ እየሮጡ ሄዱ። 9 እነሆ ኢየሱስ አገኛቸውና፣ “ሰላም ለእናንተ ይሁን” አላቸው። ሴቶቹም እግሮቹን ይዘው ሰገዱለት። 10 ከዚያም ኢየሱስ፣ "አትፍሩ፤ ሄዳችሁ ወደ ገሊላ እንዲሄዱ ለወንድሞቼ ንገሩ፤ እዚያ ያዩኛል" አላቸው። 11 ሴቶቹ እየሄዱ እያሉ፣ ከጠባቂዎች ጥቂቱ ወደ ከተማ ሄደው የሆነውን ሁሉ ለካህናት አለቆቹ ነገሩ። 12 ካህናቱ ከሽማግሌዎቹ ጋር ተገናኝተው የሆነውን ሁሉ ሲናገሩ፣ ለወታደሮቹ ብዙ ገንዘብ በመስጠት፣ 13 “እኛ ተኝተን እያለ ፣ ሌሊት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት መጥተው አስክሬኑን ሰረቁ” ብለው እንዲናገሩ ነገሩዋቸው። 14 ይህ ወሬ ወደ አገረ ገዢው ከደረሰ፤ እኛ እናሳምነዋለን፣ እናንተም ከሥጋት ነጻ ትሆናላችሁ" አሏቸው። 15 ወታደሮቹ ገንዘቡን ተቀብለው ፣ እንደ ተነገራቸው አደረጉ። ይህ ወሬ እስከ ዛሬ ድረስ በአይሁድ መሐል በሰፊው ተሰራጭቷል። 16 ዐሥራ አንዱ ደቀ መዛሙርት ግን ወደ ገሊላ ኢየሱስ ወደ ነገራቸው ተራራ ሄዱ። 17 ባዩት ጊዜ ሰገዱለት፤ አንዳንዶቹ ግን ተጠራጥረው ነበር። 18 ኢየሱስ ወደ እነርሱ መጥቶ፣ “በሰማይና በምድር ሁሉ ላይ ሥልጣን ተሰጠኝ። 19 ስለዚህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ፣ በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስም ስም እያጠመቃችኋቸው፤ 20 እኔ ያዘዝኋችሁን ሁሉ እንዲያደርጉ እያስተማራችኋቸው፤ ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው። እኔም እስከ ዓለም ፍጻሜ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።”
በሰንበትም በሳምንቱ መጀመሪያው ቀን መጨረሻ "ሰንበት ካለቀ በኋላ የእሁድ ማለዳ ጸሐይ መውጣት ሲጀምር" ሌላኛዋ ማሪያም "ማሪያም ተብላ የሚትጠራዋ ሌላኛዋ ሴት” የያዕቆብ እና የዮሴፍ እናት የሆነችው ማሪያም (MAT 27:56) እነሆ ይህ ቃል ሰዎች ከዚህ በኋላ ለሚነገረው ነገር አጽኖት እንዲሰጡ የሚጨመር ቃል ነው፡ ለተርጓሚዎች ምክር፡ “ተመልከቱ” ወይም “አድምጡ” ወይም “አሁን ለምነግራችሁ ነገር ትኩረት ስጡ”:: የጌታ መላእክት በመውረዳቸው . . . እና ድንጋዩን በማንከባለላቸው ምክንያት ታላቅ የመሬት መናወጥ ሆነ አማራጭ ትርጉሞች: 1) የመሬት መናወጡ የተከሰተበት ምክንያት መላእክት በመውረዳቸው እና ድንጋዩን በማንከባለላቸው ነው (ULB) ወይም 2) እነዚህ ሁሉም ነገሮች የሆኑት በተመሳሳይ ጊዜ ነው (UDB). የመሬት መናወጥ (መንቀጥቀጥ) ድንገተኛ እና አስደንጋጭ የመሬት መንቀጥቀጥ
የእርሱ መልክ "የመልአክ መልክ" መብረቅ ይመስል ነበር "እንደ መብረቅ ያበራ ነበር" እንደ በረዶ ነጭ ነበር "በከፍተኛ ሁኔታ ያንጸባርቅ ነበር" እንደ ሞተ ሰው "መንቀሳቀስ ያቃተው"
ሴቶቹ "መግደላዊት ማሪያም እና ማሪያም ተብላ የተጠራው ሌላኛዋ ሴት" የተሰቀለው "ሕዝቡ እና ወታደሮቹ የሰቀሉት" ነገር ግን ተነሣ " ገር ግን እግዚአብሔር አስነሣው"
ሴቶቹ "መግደላዊት ማሪያም እና ማሪያም ተብላ የሚትጠራው ሌላኛይቱ ሴት" እነሆ ጸሐፊው አንድ አስደናቂ ነገር ልሆን እንዳለ ለአንባቢዮቹ ያስታውቃቸዋል፡፡ በቋንቋችሁ ይህን ዓይነቱን ነገር ማድረግ የሚችትችሉበት መንገድ ሊኖር ይችላል፡፡ እግሩን ያዙት "በጉልበታቸው ተንበርክከው እግሩን ያዙት" ወንድሞቼ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት
ሴቶቹ መግደላዊት ማሪያም እና ሌላኛዋ ማሪያም ከእነርሱ ጋር ስለሁኔታው ተወያዩ "ስለ አቀዱት እቅድም በጋራ ወሰኑ፡፡” ካህናቱ እና ሽማግሌዎቹ ለወታደሮቹ ብር ለመስጠት ወሰኑ፡፡ ለሌሎች እንዲህ ብላችሁ ንገሩ “በተኛንበት ሰዓት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት መጥተው . . .” "ለጠየቃችሁ ሁሉ እንዲህ ብላችሁ ንገሩ፣ ተኝተን ሳለ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት መጥተው"
ገዥው ጵላጦስ (MAT 27:2) እንደተነገራቸው እንደዚያው አደረጉ "ካህናቱ እንዲያደርጉ እንደ ነገሯቸው እንደዚያው አደረጉ" ዛሬ ማቴዎስ መጽሐፉን በጻፈበት ወቅት
በስሜ "በእኔ ስልጣን" አብ . . . ወልድ ይህ በእግዚአብሔር አብ እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያብራራ ጠቃሚ ስም ነው፡፡
1 ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መጀመሪያ፡፡ 2 በነብዩ በኢሳይያስ እንደተጻፈው እነሆ! መንገድን የሚያዘጋጅላችሁን መልዕክተኛዬን በፊታችሁ እልካለሁ፤ 3 መንገድን አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ ብሎ በምድረበዳ የሚጮህ ሰው ድምፅ፡፡ 4 በምድረበዳ እያጠመቀና ለኃጢአት ይቅርታ የንሰሐን ጥምቀት እየሰበከ መጣ፡፡ 5 ሁሉና በኢየሩሳሌም ያሉ ሁሉ ወደ እርሱ ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ እየመጡ ኃጢአታቸውን በመናዘዝ ይጠመቁ ነበር፡፡ 6 የግመል ጠጉር ይለብስና ወገቡን በቆዳ መታጠቂያ ይታጠቅ፣ አንበጣና የበረሃ ማርም ይበላ ነበር፡፡ 7 የጫማውን ማሰሪያ ለመፍታት የማልበቃ ከእኔ ይልቅ ታላቅ የሆነ እርሱ ከበስተኋላዬ ይመጣል፡፡ 8 በውሃ አጥምቄአችኋለሁ፤ እርሱ ግን በመንፈስ ቅዱስ ያጠምቃችኋል እያለ ይሰብክ ነበር፡፡ 9 ቀናት ኢየሱስ ከገሊላ ናዝሬት በመምጣት በዮርዳኖስ ውስጥ በዮሐንስ ተጠመቀ፡፡ 10 እንደወጣም ሰማይ ሲከፈት፣ መንፈስ ቅዱስም እንደ እርግብ በእርሱ ላይ ሲወርድ አየ፤ 11 ልጄ አንተ ነህ፤ በአንተ ደስ ይለኛል የሚል ድምጽም ከሰማያት መጣ፡፡ 12 መንፈስ ቅዱስ ወደ ምድረበዳ መራው፡፡ 13 በሰይጣን እየተፈተነም በምድረበዳ ለአርባ ቀን ቆየ፡፡ ከዱር አራዊትም ጋር ነበረ፤ መላዕክትም አገለገሉት፡፡ 14 ታልፎ ከተሰጠ በኋላ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን የምሥራች ቃል እየሰበከ ወደ ገሊላ መጣ፡፡ 15 ተፈጸመ፤የእግዚአብሔር መንግሥት ቀርባለችና ንሰሐ ግቡ፤ በወንጌልም እመኑ ይል ነበር፡፡ 16 ባህር ዳር ሲያልፍ ሳለ ስምዖን ጴጥሮስንና ወንድሙን እንድርያስን መረባቸውን ወደ ባህር ሲጥሉ አያቸው፤ አሳ አጥማጆች ነበሩና፡፡ 17 በኋላዬ ኑና ሰዎችን የምታጠምዱ አደርጋችኋለሁ አላቸው፡፡ 18 መረቦቻቸውን ትተው ተከተሉት፡፡ 19 እልፍ እንዳለም የዘብዴዎስን ልጅ ያዕቆብንና ወንድሙን ዮሐንስን እነርሱም በጀልባቸው ውስጥ መረቦቻቸውን ሲጠግኑ አያቸው፡፡ 20 ጠራቸው፤ እነርሱም ዘብዴዎስ አባታቸውን ከተቀጣሪ ሰራተኞቻቸው ጋር በጀልባው ውስጥ ትተው ተከተሉት፡፡ 21 ቅፍርናሆም ሔዱ፡፡ ወዲያው በሰንበት ቀን ወደ ምኩራብ ገብቶ አስተማራቸው፡፡ 22 ጸሐፍት ሳይሆን ትምህርቱ እንደ ባለሥልጣን ስለነበረ በትምህርቱ ተገረሙ፡፡ 23 ርኩስ መንፈስ ያለበት አንድ ሰው በምኩራባቸው ነበረ፡፡ 24 የናዝሬቱ ኢየሱስ ሆይ! ከአንተ ጋር ምን አለን? ልታጠፋን መጣህን? ማን እንደሆንክ አውቄሃለሁ፤ አንተ የእግዚአብሔር ቅዱስ ብሎ ጮኸ፡፡ 25 ዝም በል! ከእርሱም ውጣ ብሎ ገሰጸው፡፡ 26 መንፈስ መሬት ላይ ጥሎ ካንፈራገጠው በኋላ በታላቅ ድምጽ ጮኾ ወጣ፡፡ 27 ሁሉ በጣም ተገረሙና ይህ አዲስ ትምህርት ምንድነው? ርኩሳን መናፍስትን እንኳን በሥልጣን ያዛቸዋልና እነርሱም ይታዘዙለታል በማለት እርስ በርሳቸው ተጠያየቁ፡፡ 28 እርሱም በገሊላ አውራጃና በዙሪያው ባሉ ሀገራት ሁሉ ዝናው ወጣ፡፡ 29 እንደወጡ ወዲያው ከዮሐንስና ከያዕቆብ ጋር ወደ ስምዖንና እንድርያስ ቤት መጡ፡፡ 30 ጊዜ የስምዖን አማት አተኵሷት ተኝታ ነበርና ወዲያው ስለ እርስዋ ነገሩት፡፡ 31 እጇን ይዞ አስነሳት፤ ወዲያውኑ ትኵሳቱ ለቀቃትና አገለገለቻቸው፡፡ 32 ጠልቃ በመሸ ጊዜም ብዙ በሽተኞችንና በአጋንንት የተያዙትን ወደ እርሱ አመጧቸው፡፡ 33 ሰው ሁሉ በአንድነት በቤቱ ደጃፍ ተከማችቶ ነበር፡፡ 34 በተለያየ በሽታ የታመሙትን ፈወሳቸው፤ ብዙ አጋንንንትንም አወጣ፡፡ አጋንንቱ ማን መሆኑን አውቀውት ነበርና እንዳይገልጡት አዘዛቸው፡፡ 35 እጅግ በማለዳ ተነስቶ ለብቻው ወደ ምድረበዳ ሔደና ጸለየ፡፡ 36 ከእርሱ ጋር የነበሩትም ተከተሉት፡፡ 37 ጊዜ ሕዝቡ ሁሉ ይፈልጉሃል አሉት፡፡ 38 የምሥራቹን ቃል እንድሰብክ ወደ ሌሎቹ ከተሞች ደግሞ እንሂድ፣ ስለዚህ ጉዳይ መጥቻለሁና አላቸው፡፡ 39 ወዳሉ ምኩራቦቻቸው ሁሉ እየገባ ሰበከላቸው፣ አጋንንትንም አወጣ፡፡ 40 ለምጻም ወደ እርሱ መጥቶ ሰገደለትና ብትፈቅድስ ልታነጻኝ ትችላለህ ብሎ ለመነው፡፡ 41 አዘነለት፤ እጁን ዘርግቶ ዳሰሰውና እፈቅዳለሁ፣ ንጻ! አለው፡፡ 42 ለምጹ ለቀቀውና ንጹህ ሆነ፡፡ 43 ለማንም እንዳይናገር አጥብቆ አዘዘውና ወዲያው ሲያሰናብተው ሳለ 44 ግን ራስህን ለካህን አሳይ፤ ስለመንጻትህ ምሥክር እንዲሆንባቸው ሙሴ ያዘዘውን መስዋዕት አቅርብ አለው፡፡ 45 ግን ሄደና ኢየሱስ በግልጽ ወደ ከተማ ለመግባት እስኪሳነው ድረስ ስለዚህ ነገር አብዝቶ ሊያወራና ሊያሰራጭ ጀመረ፡፡ በመሆኑም በምድረበዳ አካባቢዎች እንዲቆይ ሆነ፤ ሰዎችም ከየአቅጣጫው ወደ እርሱ ይመጡ ነበር፡፡
የእግዚአብሔር ልጅ ይህ የኢየሱስ አስፈላጊ የሆነ ስም ነው፡፡ አንተ . . . አንተ ነጠላ ቁጥር መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ “መንገድ” እና “ጥርጊያ” የሚሉት ሁለት ቃላት የኢየሱስን ሕይወት ከመንገድ ጋር የሚያነጻጽሩ ናቸው፡፡ የእነዚህ ሁለት ትዕዛዞች ትርጉም ተመሳሳይ ነው፡፡ በእናንተም ቋንቋ ተመሳሳይ ከሆኑ UDB እንዳደረገው ሁለተኛውን ዐረፍተ ነገር መተው ትችላላችሁ፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: በጣም ወሳኝ የሆነ ሰውን ለመገናኘት ተዘጋጁ
የእግዚአብሔር ልጅ ይህ የኢየሱስ አስፈላጊ የሆነ ስም ነው፡፡ አንተ . . . አንተ ነጠላ ቁጥር መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ “መንገድ” እና “ጥርጊያ” የሚሉት ሁለት ቃላት የኢየሱስን ሕይወት ከመንገድ ጋር የሚያነጻጽሩ ናቸው፡፡ የእነዚህ ሁለት ትዕዛዞች ትርጉም ተመሳሳይ ነው፡፡ በእናንተም ቋንቋ ተመሳሳይ ከሆኑ UDB እንዳደረገው ሁለተኛውን ዐረፍተ ነገር መተው ትችላላችሁ፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: በጣም ወሳኝ የሆነ ሰውን ለመገናኘት ተዘጋጁ
ሰበከ "ዮሐንስ ሰበከ" (ተመልከት (MRK 1:2-3)፡፡ ተጎንብሼ የጫማውን ጠፍር መፍታት የማይገባኝ ዮሐንስ ኢየሱስ ከእርሱ ምን ያኽል እንደሚበልጥ ለማሳየት ራሱን ከአገልጋይ ጋር ያነጻጽራል፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: “እኔ አስደሳች ያልሆነውን የአገልጋይነት ሥራን ለመሥራት እንኳ ብቁ አይደለሁም፡፡” ማጎንበስ "ወደ ታች ገንበስ ማለት" በመንፈስ ቅዱስ ያጠምቃችኋል በዚህ ሥፍራ ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ከውሃ ጥምቀት ጋር ተነጻጽሮ ቅርቧል፡፡ የውሃ ጥምቀት ሰዎች ከውሃ ጋር ግንኙነት እንዲኖራቸው እንደሚያደርጉ ሁሉ የመንፈስ ጥምቀት ሰዎች ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ግንኙነት እንዲያደርጉ ያደርጋል፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: “ከመንፈስ ቅዱስ ወግኖ መገኘት፡፡”
የምወድህ ልጄ እንተ ነህ እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሐየር ወልድ፣ እና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በአንድነት፣ በተመሳሳይ ጊዜ በመገለጥ፡፡ የምወድህ ልጄ ይህ የኢየሱስ ወሳኝ ስም ነው፡፡ እግዚብሔር አባር እርሱን “የምወድህ ልጄ” ብሎ ጠርቶታል፡፡ ይህ የሆነው ደግሞ እርሱ ለእርሱ ካለው ዘላለማዊ ፍቅሩ የተነሳ ነው፡፡
ይሄድ ዘንድ አስገደደው "ኢየሱስን በግድ አስኬደው" በምድረ በዳ ውስጥ ነበር "በምድረ በዳ ውስጥ ቆየ አርባ ቀን እና ሌልት "40 ቀናት" ከ . . . ጋር ነበር "በ . . . መካከል ነበር"
ዮሐንስ አልፎ ከተሰጠ በኋላ "ዮሐንስ ወደ ወህኒ ቤት ከተወሰደ በኋላ." አማራጭ ትርጓሜ: "ዮሐንስን ካሠሩት በኋላ." የእግዚብሔርን ወንጌል ሰበከ "ከእግዚአብሔር ዘንድ የመጣውን መልካሙን ዜና ሰበከ" ዘመኑ ተፈጸመ "ጊዜው አሁን ነው"
ስምኦንና አንድሪውን ተመለከተ "ኢየሱስ ስምኦንና አንድሪውን ተመለከተ" መረብ መጣል "መረብ መወርውር" ዓሣ አጥማጆች ነበሩ "እነርሱ ዓሣ አጥማጆ ስለነበሩ" ተከተሉኝ "እኔን ተከተሉኝ" ሰዎችን የሚታጠምዱ አድርጋችኋለሁ በዚህ ሥፍራ ላይ ኢየሱስ ዓሣ ማጥመድን ከሰው ማጥመድ ጋር እያነጻጸረ ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: "እንዴት ሰውን ማጥመድ እንደሚትችሉ አስትምራችኋለሁ" እነርሱም መረባቸውን ትተው ተከተሉት "የኢየሱስ ተከታዮች ለመሆን የዓሣ ማጥመድ ሥራቸውን ተው"
በታንኳይቱ ውስጥ "በተንኳቸው ውስጥ" መረባቸውን ሲያበጁ "መረባቸውን ስያበጃጁ አየ" ተቀጣሪ ሠራተኞች "ለእነርሱ ተቀጥረው የሚሠሩ ሠራተኞች" ተከተሉት "ያዕቆብ እና ዮሐንስ ከኢየሱስ ጋር ሄዱ"
ምኩራባቸው ይህ ኢየሱስ እና የእርሱ ደቀ መዛሙርት የገቡበት የአምልኮ ሥፍራ ከዚህም በተጨማሪ ኢየሱስ ትምህርት ማስተማር የጀመረበት ሥፍራ ነው፡፡ የመጣኸው እኛል ለማፍታት ነውን? እርኩሳን መናፍሱ ኢየሱስን ይህንን ጥያቄ የጠየቁት ኢየሱስ እንዳይጎዳቸው ለመለመን ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: "እባክህ ፈጽመህ አታጥፋን!"
ከወጡ በኋላ ኢየሱስ፣ ስምኦን እና እንድሪያስ ከዚያ ከወጡ በኋላ ንዳዱ ተዋት "የስምኦን ምስት እናት ከነበረባት ንዳድ በሽታ ተፈወሰች" እርሱንም ታገለግላቸው ጀመረች በዚህ ሥፍራ ላይ በተዘዋዋር መንገድ ታገለግላቸው ጀመረች በሚል ሀረግ የተገለጸው ምግብ ማቅረብ ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: “ምግብ እና የሚጠጣ ነገር ሰጠቻቸው፡፡”
እርሱ . . . እርሱ . . . እርሱ . . . እርሱ እነዚህ ተውላጠ ስሞች የሚመለክቱት ኢየሱስ ነው፡፡ አጠቃላይ ከተማው በበር ላይ ተሰበሰበ በዚህ ሥፍራ ላይ “በአጠቃላይ” የሚለው ቃል ኢየሱስን ፍለጋ የመጠው ሰው ብዙ መሆኑን ለማሳየት የቀረበ በግነታዊ የሥነ-ጽሑፍ ዘይቤ የተገለፀ ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: “ከዚያ ከተማ በጣመ ብዙ ሕዝብ በበሩ አከባቢ ተሰበሰቡ፡፡”
ጸጥ ያለ ሥፍራ "እርሱ ብቻውን መሆን የሚያስችለው ሥፍራ" ሁሉም ሰው እርሱን ይፈልገው ነበር በዚህ ሥፍራ ላይ “ሁሉም” የሚለው ቃል ኢየሱስን ፍለጋ የመጡት ሰዎች ብዙ መሆናቸውን ለማሳየት በግነታዊ የሥነ-ጽሑፍ ዘይቤ በመጠቀም ነው፡፡ ለተሯሚዎች ምክር፡ በጣም ብዙ ሰዎች እየፈለጉህ ነው፡፡”
እርሱ . . . እርሱ . . . እርሱ . . . እርሱ እነዚህ ቃላት የሚያመለክቱት ኢየሱስ ነው፡፡ ወደ ሌላ ሥፍራ እንሂደት "ወደ ሌላ ሥፍራ መሄድ ያስፈልገናል" በገሊላ በኩል አልፎ ሄደ በዚህ ሥፍራ ላይ ጥቅም ላይ የዋለው “አልፎ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስ በአገልግሎቱ ወቅት ወደ ተለያዩ ሥፍራዎች ይሄድ እንደነበረ አጽኖት ለመስጠጥ ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: “በገሊላ ውስጥ ወደ ተለያዩ ሥፍራዎች ሄዷል፡፡”
አንድ ለምጻምም ሰው ወደ እርሱ መጣ፤ በፊቱም በጉልበቱ ተንበርክኮ ለመነው፡፡ እንድህም አለው "አንድ ለምጻምም ሰው ወደ ኢየሱስ መጣ፤ ለምጻሙም ሰው ኢየሱስን በጉልበቶቹ ተንበርክኮ ይለምነው ነበር፡፡ ለምጻሙ ሰው ኢየሱስን እንዲህ አለው” ፈቃድህስ ቢሆን "እኔን ንጹህ ልታደርገኝ ከፈለግህ" ልታነጻኝ ትችላለህ በዚህ ሥፍራ ላይ “ንጹሕ” የሚለው ቃል የሚወክለው ጤናማ መሆንን ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: “እኔን ማዳነት ትችላለህ፡፡” እኔ ፈቃደኛ ነኝ "አንተን ንጹሕ ማድረግ እፈልጋለሁ"
እርሱ . . . እርሱ . . . እርሱ . . . እነዚህ ቃላት የሚያመለክቱት ከለምጹ የተነጻውን ሰው ነው፡፡ ራስህን አሳይ በዚህ ሥፍራ ላይ “ራስህን “ የሚለው ቃል የሚያመለክተው የለምጻሙን ሰው ቆዳ ነው፡፡ ለተርጓሚወች ምክር፡ “ሄደህ ቆዳህን አሳይ፡፡"
ለሁሉም ሰው ተናገር . . . ወሬውም ተዳረሰ እነዚህ ሁለት ሀረጎች ተመሳሳይ ትርጉሞች የሚጋሩ ሲሆን ይህ ሰው ለብዙ ሰዎች መናገሩ ላይ አጽኖት ይሰጣል፡፡ ሁለም ሰዎች በዚህ ሥፍራ ጥቅም ላይ የዋለው “ሁሉም ሰዎች” የሚለው ቃል ግነታዊ የስነ ጽሑፍ ዘይቤን በመጠቀም አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡” ለትርጓሚዎች ምክር፡ “ከብዙ ሰዎች ጋር ተገናኘ”፡፡ ኢየሱስ በነጻነት ወደዬትኛው ከተማ ለመግባት አልቻለም ነበር፡፡ "ኢየሱስ በከተማዎቹ ውስጥ በነጻነት እንዳይንቀሳቀስ ሕዝቡ ከለከሉት፡፡” ከሁሉም ቦታ የመጡ በዚህ ሥፍራ ጥቅም ላይ የዋለው “ከሁሉም ቦታ የመጡ” የሚለው ሀረግ አጽኖት ለመስጠት የገባ ቃል ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: “በአከባቢው የመጡ ሰዎች ሁሉ፡፤”
1 ቀናት በኋላ ኢየሱስ ወደ ቅፍርናሆም ተመልሶ በመጣ ጊዜ፣ በቤት እንዳለ ወሬው ተሰማ፡፡ 2 ሰዎችም ተሰበሰቡ፤ከዚህ የተነሣ በበሩ መግቢያም እንኳ በቂ ቦታ አልነበራቸውም፡፡ ኢየሱስም የእግዚአብሔርን ቃል ነገራቸው፡፡ 3 ሰዎችም አንድ ሽባ ሰው ወደ እርሱ አመጡ፡፡ 4 ብዛት ምክንያት ወደ እርሱ መቅረብ ስላልቻሉ፣ኢየሱስ ባለበት አቅጣጫ ጣሪያውን ነደሉት፡፡ በቀዳዳውም ሽባው ያለበትን ዐልጋ ወደ ታች አወረዱት፡፡ 5 እምነታቸውን አይቶ ሽባውን ሰው፣ "አንተ ልጅ ኀጢአትህ ተሰርዮልሃል" አለው፡፡ 6 ግን አንዳንድ ጸሓፍት በዚያ ተቀምጠው ነበር፡፡ ይህ ሰው እንዲህ ብሎ የሚናገረው ለምንድን ነው? እርሱ እግዚአብሔርን ይሳደባል፤ 7 ከእግዚአብሔር በቀር ኀጢአትን ይቅር ማለት የሚችል ማን ነው? እያሉ በልባቸው ያጉረመርሙ ነበር፡፡ 8 ኢየሱስ በውስጣቸው እያጉረመረሙ እንደሆነ በመንፈሱ ዐውቆ፣ "በልባችሁ የምታጉረመርሙት ለምንድን ነው? አላቸው፡፡ 9 ለሽባው ሰው የትኛውን ማለት ይቀላል? ኀጢኣትህ ተሰርዮልሃል ወይስ ተነሣ ዐልጋህን ተሸክመህ ሂድ ማለት? 10 እንጂ የሰው ልጅ በምድር ላይ ኀጢኣትን የማስተሰረይ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ፣ 11 እልሃለሁ፤ ተነሣ! ዐልጋህን ተሸከምና ወደ ቤትህ ሂድ" አለው፡፡ 12 እርሱም ተነሣ፤ ወዲያውኑም ዐልጋውን ተሸክሞ በሁሉም ፊት ወጥቶ ሄደ፡፡በዚያ የነበሩትም ሁሉም ተገርመው ስለ ነበር እንዲህ ያለ ነገር ፈጽሞ አይተን አናውቅም በማለት እግዚአብሔርን አከበሩ፡፡ 13 ወደ ባሕሩ ዳርቻ ሄደ፡፡ሕዝቡም በሙሉ ወደ እርሱ ተሰበሰቡ፤ አስተማራቸውም፡፡ 14 ሲያልፍም የእልፍዮስን ልጅ ሌዊን ቀረጥ በመሰብሰቢያ ቦታው ተቀምጦ አየውና "ተከተለኝ" አለው፡፡ ተነሥቶም ተከተለው፡፡ 15 በእርሱ(በሌዊ) ቤት ተቀምጦ እየበላ ነበር፡፡ ብዙ ቀራጮችና ኀጢአተኞችም ከኢየሱስና ከደቀመዛሙርቱ ጋር ተቀመጡ፤ ብዙዎቹም ተከትለውት ነበርና፡፡ 16 ጸሓፍትም ከኀጢአተኞችና ከቀራጮች ጋር ሲበላ ሲያዩት ደቀመዛሙርቱን፣ "እርሱ ከቀራጮችና ከኀጢአተኞች ጋር የሚበላውና የሚጠጣው እንዴት ነው" አሏቸው፡፡ 17 ይህን ሲሰማ፣ "ሕሙማን እንጅ ጤናሞች ሐኪም አያስፈልጋቸውም" ፤ እኔ ኀጢአተኞችን እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁም አላቸው፡፡ 18 ደቀመዛሙርትና ፈሪሳውያን ይጾሙ ነበር፡፡ ወደ እርሱም መጥተው የዮሐንስ ደቀመዛሙርትና የፈሪሳውያን ደቀመዛሙርት የሚጾሙት ነገር ግን የአንተ ደቀመዛሙርት የማይጾሙት ለምንድን ነው? አሉት፡፡ 19 እንዲህ አላቸው፡፡ሙሽራው አብሮአቸው ሳለ ሚዜዎቹ ይጾማሉ? ሙሽራው ከእነርሱ ጋር እስካለ ሊጾሙ አይችሉም፡፡ 20 ግን ሙሽራው የሚወሰድበት ቀን ይመጣል፡፡ በዚያን ጊዜ በዚያ ቀን ይጾማሉ፡፡ 21 አዲስ እራፊ ጨርቅ በዐሮጌ ልብስ ላይ አየይጥፍም፤ ያለበለዚያ የተጣፈው እራፊ ይቀደዳል፡፡ ቀዳዳውም የባሰ ይሆናል፡፡ 22 የወይን ጠጅ በዐሮጌ ዐቁማዳ ውስጥ የሚያስቀምጥ ማንም ለም፡፡ አለበለዚያ የወይን ጠጁ ዐቁማዳውን ያፈነዳዋል፤የወይን ጠጁና ዐቁማዳውም ይበላሻሉ፡፡ ነገር ግን አዲስ የወይን ጠጅ በአዲስ ዐቁማዳ ውስጥ ያስቀምጣሉ፡፡ 23 በሰንበት ቀን በእህል ማሳ መካከል ያልፍ ነበር፡፡ ደቀመዛሙርቱም ሲያልፉ እሸት መቅጠፍ ጀመሩ፡፡ 24 ፈሪሳውያንም እነሆ በሕግ ያልተፈቀደውን በሰንበት የሚያደርጉት ለምንድን ነው? አሉት፡፡ 25 እንዲህ አላቸው፡፡ ዳዊት በተራበና በተቸገረ ጊዜ ለራሱና አብረውት ለነበሩት ምን እንዳደረገ፣ አብያታር ሊቀ ካህናት በነበረ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደገባ፤ 26 ብቻ የተፈቀደውን ገጸ ኅብስት እንደ በላ፣ ከእርሱም ጋር ለነበሩት እንደሰጣቸው ፈጽሞ አላነበባችሁምን? እንዲህም አላቸው፡፡ 27 የተፈጠረው ለሰው ነው እንጂ ሰው ለሰንበት አልተፈጠረም፡፡ 28 የሰው ልጅ የሰንበትም እንኳ ጌታ ነው፡፡
በዚያ የነበሩት ሰዎች እርሱ በቤት ውስጥ እንዳሉ ሰምተው "በዚያ የነበሩት ሰዎች በተመሳሳይ ቤት ውስጥ እንዳሉ ሰምተው" በቤት ውስጥ ለእነርሱ የሚሆን በቂ ቦታ አልነበረም "በቤቱ ውስጥ ለእነርሱ የሚሆን በቂ ቦታ አልነበረም”፡፡
አንድ ሽባ ሰው ይዘው ወደ እርሱ መጡ "መራመድ የማይችል ወይም እጁን ማንቀሳቀስ የማይችል አንድ ሰውን ወደ እርሱ አመጡ" አራት ሰዎች "4 ሰዎች" ወደ እርሱ መቅረብ ፈጽመው አልቻሉም "ኢየሱስ ወደአለበት ሥፍራ መቅረብ ፈጽመው አልቻሉም"
እምነታቸውን አይቶ "እነዚህ ሰዎች እምነት እንዳላቸው አውቆ፡፡" ይህ የተለያዩ ትርጉሞች ልኖሩት ይችላል 1) ሽባውን ሰው ተሸክመው የመጡት ሰዎች ብቻ እምነት ነበራቸው ወይም 2) ሽባው ሰው እና ተሸክመውት የመጡ ሰዎች እምነት ነበራቸው፡፡ ሽባወ ሰው "መራመድ የማይችለው ሰው" ልጅ በዚህ ሥፍራ ላይ “ልጅ” የሚለው ቃል የሚያሳየው አባት ልጁን እንደሚንከባከብ ሁሉ ኢየሱስም ለዚህ ሰው ግድ እንደሚለው ለማሳየት ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: “ልጄ” ኃጢአትህ ተሰረየለችልህ አማራጭ ትርጓሚዎች 1) "እግዚብሔር ኃጢአትህን ይቅር ብሎሃል" (ተመልከት 2:7) ወይም 2) "ኃጢአትህን ይቅት ብዬልሃለሁ፡፡" (ተመልከት MRK 2:10) በልባቸው እንዲህ ብለው አሰቡ "ለራሳቸው እንዲህ በማለለት አሰቡ" ይህ ሰው እንዴት እንዲህ ሊናገር ቻለ? ይህ ጥያቄ የተጠየቀው ጸሐፍት ኢየሱስ ኃጢአትን የማስተሰረይ ኃይል እንዳለው ስለተጠራጠሩ ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: "ይህ ሰው እንዲህ ባለ መንገድ እንዴት ይናገራል!" ኃጢአትን ማስተሰይ ኃይል ከእግዚአብሔር ውጪ ያለው ማን ነው? ይህ ጥያቄ የተጠየቀው ጸሐፍት ኢየሱስ አምላክ መሆኑን ለሚጠራጠሩት ለማሳየት ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: “ኃጢአት ማስተሰረይ የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡”
ለራሳቸው እንዲህ ብለው አሰቡ እያንዳንዱ ጸሐፍት ለራሳቸው እንዲህ ብለው አሰቡ፤ ይሁን እንጂ እርስ በእርሳቸው አልተነጋገሩም፡፡ በልባችሁ ስለምን እንዲህ ታስባለህ? ኢየሱስ ይህንን ጥያቄ የጠየቀበት ምክንያት ጸሐፍት የእርሱን ሥልጣን በመጠራጠራው ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: "ሥልጣኔን መጠራጠር የለባችሁም!" ልባቸውም ይህ "ልብ" የሚለው ቃል ብዙ ጊዜ የሰዎችን አመለካከት፣ ስሜት፣ ፍላጎት ወይም ፈቃድ ለማመልከት ነው፡፡ ዬትኛው ይቀላል . . . . ሂድ? ኢየሱስ ይህንን ጥያቄ የጠየቀው ጸሐፍት ሰውዬው ሽባ የሆነው በኃጢአቱ ምክንያት ነው የሚል እምነት ነበራቸው፡፡ ሰውዬው ኃጢአቱ ይቅር ከተባለለት መራመድ ይችላሉ፡፡ ኢየሱስ ሽባውን ሰው ከፈወሰው ጸሐፍት ኢየሱስ ኃጢአትን የማስተሰረይ እንደሚችል ልቀበሉ ይገባቸዋል ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: “ሽባውነን ሰው ኃጠአትህ ተሰረየችልህ ማለት ቀላል ነው!”
ይህንን ታውቁ ዘንድ "ይህንን አረጋግጥላችኋለሁ" የሰው ልጅ በዚህ ሥፍራ ላይ ራሱን “የሰው ልጅ” በማለት ይጠራል፡፡ እናንተ ጸሐፍት እና ሕዝቡ ለሽባው ሰው እንዲህ አለው "መራመድ ለማይችለው ሰው እንዲህ አለው" በሁሉም ሰዎች ፊት "በዚያ ሥፍራ በተሰበሱት ሰዎች ዐይን ፊት”
ሕዝቡም ወደ እርሱ መጥተው "ሕዝቡም እርሱ ወደአለበት ሥፍራ መጥተው"
የሌዊ ቤት "የሌዊ ቤት" በጣም ብዙ ሰዎች የከተሉት ስለነበር ከብዙ ቀራጮች እና ኃጢአተኞች ጋር ኢየሱስ እና የእርሱ ደቀ መዛሙርት ጋር ምግብ ይበሉ ነበር፡፡ "ኢየሱስን ይከተሉት የነበሩት ብዙ ቀራጮች እና ኃጢአተኛ ከእየሱስ እና ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ምግብ ይበሉ ነበር፡፡" ከቀራጮች እና ከኃጢአተኞች ጋር ስለምን ይበላል? ጸሐፍት እና ፈሪሳዊያን ይህንን ጥያቄ የጠየቁት የኢየሱስን ከሁሉም ጋር መሆንን ትክክል አለመሆን ለማሳየት ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: ቀረጥ ከሚሰበስቡ ኃጢአተኛ ሰዎች ጋር መብላት እና መጠጣት የለበትን!"
እንዲህ አላቸው "ለፈሪሳዊያን እንዲህ አላቸው" ጤነኛ የሆኑ ሰዎች ሐኪም አያስፈልጋቸውም፤ ሐኪም የሚያስፈልጋቸው በሽተኞች ብቻ ናቸው ኢየሱስ በዚህ ሥፍራ ላይ ኃጢአተኛ መሆናቸውን የሚያውቁ ሰዎችን መታመማቸውን ከሚያውቁ ሰዎች ጋር ያነጻጽራል፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: "ጻድቃን እንደሆኑ የሚያስቡ ሰዎች እገዛ አይፈልጉም፤ መታመማቸውን የሚያውቁ ሰዎች ብቻ ናቸው ከሌሎች እገዛ የሚፈልጉት! እኔ ጻድቅ የሆኑትን ሰዎች ለመጥራት አልመጣሁም፡፡ ይልቁንም ኃጢአተኛ የሆኑ ሰዎችን ለመጥራት ነው የመጣሁት፡፡ ኢየሱስ የመጣው እገዛን ለሚሹ ሰዎች መሆኑን አድማጮቹ እንዲገነዘቡ ይፈልጋል፡፡ ለትርጓሚዎች ምክር፡ "የመጣሁት ኃጢአተኞች መሆናቸውን ለተገዘነቡ ሰዎች እንጂ ራሳቸውን ጻድቅ አድረገው ለሚቆጥሩ ሰዎች አይደለም፡፡"
ነገር ግን ደቀ መዛሙርቱ አይጾሙም መጾም ማለት ምግብ አለመብላት ማለት ነው፡፡ ጾም በማይጾምበት አከበቢ ባለ ቋንቋ ውስጥ አውንታዊ ዓረፍተ ነገሮችን መጠቀም የተሻለ ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: “ይሁን እንጂ ደቀ መዛሙርትህ ያለማቋረጥ ይበለላሉ፡፡” ሠርገኞች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር እያለ ይጾናሉን? ኢየሱስ ይህንን ጥየቄ እርሱን እና ደቀ መዛሙርቱን ከሙሽራ እና የእርሱ ጓደኛ ጋር ለማነጻጸር ተጠቅሞበታል፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: “እኔ ከእነርሱ ጋር እስካለሁ ድረስ ደቀ መዛሙርቴ በአዚህ ደስ ይላቸዋል፡፡
ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ዘመን ይመጣል ኢየሱስ ስለሞቱ፣ ትንሳዔው እና እርገቱ ስናገር ራሱን ከሙሽራ ጋር ያነጻጽራል፡፡ ቋንቋችሁ ዋነ ገጸባህርው ማን እንደሆነ መግለጽ የሚፈልገው ከሆነ በተቻለ መጠን ጠቅላል ባለ ቋንቋ ግለጸው፡፡ለተርጓሚዎች ምክር: "ሙሽራውን ይወስዱታል” ወይም “ሙሽራው ከእነርሱ ይሄዳል፡፡" እነርሱ . . . እነርሱ በሠርጉ ላይ የታደሙት ሰዎች ማንም አዲስ እራፍ ጨርቅን በአሮጌ ልብስ ላይ የሚጥፍ የለም አዲስ እራፍ ጨርቅን በአሮጌ ልብስ ላይ መጣፍ በአሮጌው ጨርቅ ላይ ያለውን ቀዳዳ ይበልጥ ያሰፋዋል ምክንያቱም አዲሱ ጨርቅ በቀላሉ አይተጣጠፍምና ነው፡፡ አዲሱ ጨርቅ እና አሮጌው ልብስ፣ ሁለቱም ይበላሻሉ፡፡
ማንም አዲስን የወይን ጠጅ በአሮጌ አቆማዳ ውስጥ የሚያስቀምጥ የለም ኢየሱስ በዚህ ሥፍራ ላይ የእርሱ ትምህረት እነና የደቀ መዛሙርቱን ከአዲስ የወይን ጠጅ እና አቆማዳ ጋር አነጻጽረዋል፡፡ይህ ምሳሌያዊ አነጋገር “የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት እና የፈርሳዊያን ደቀ መዛሙረት ለምን እንደሚጾሙ ነገር ግን የአንተ ደቀ መዛሙርት ግን ለምን አይጾሙም” ተብሎ ለተጠየቀው ጥያቄ ምላሽ ይሰጣል፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: “ማንም አዲስ ትምህርት ሌላ ልምምድ ውስጥ ውስጥ ላሉ ሰዎች አደራ ብሎ አይሰጥም፡፡" አዲስ የወይን ጠጅ "የወይን ፍሬ ጁስ"፡፡ ይህ ገና ያልፈለ፣ አልኮል ያሌለው ወይንን ያሳያል፡፡ በአከባያችቹ የወይን ፍሬ የማይታወቅ ከሆነ ለፍራፍሬ መጠሪያ የሚሆን አጠቃላይ ቃልን ተጠቀሙ፡፡ አሮጌ አቆማዳ ይህ ብዙ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለን አቆማዳ ያመለክታል፡፡ አቆማዳ ይህ ከእንስሳት ቆዳ የሚሠራ ከረጥት ነው፡፡ “አቆማዳ” ወይም “የቆዳ ከረጥት” ተብሎ ይጠራል "skin (UDB)፡፡ ወይኑ የቆዳውን ከረጥት ይቀደዋል አዲሱ ወይን ስፈላ እና ስገላበጥ ከዚያ በላይ መለጠጥ ስለማይችል ይቀደዋ፡፡ ይጠፋል "ይበላሻል" (UDB) አዲስ የወይን አቆማዳ "አዲስ የወይን አቆማዳ” ወይም “አዲስ የወይን መያዥያ”፡፡ ይህ ከዚህ በፊት ወይን ተይዞበት የማያውቅን የወይን አቆማዳን ያመለክታል፡፡
እነሆ፥ በሰንበት ያልተፈቀደውን ስለ ምን ያደርጋሉ? አሉት። ፈርሳዊያኑ ይህንን ጥያቄ የጠየቁት ኢየሱን ለመውቀስ ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ: “ተመልከት! የአይሁድ ሕግ ስለ ስንበት የሚናገረውን ሕግ ይሽራሉ፡፡" እሸት እየቀጠፉ ይበላሉ . . . በሰሰንት ያልተፈቀደውን ነገር ያደርጋሉ፡፡ በሌሎች ሰዎች ማሳ ውስጥ ያለን እሸት ቀጥፎ መብላት ስርቆት አይባልም ፡፡ ጥያቄው ይህንን በሰንበት ማድረጋቸው ተገቢ ነው ወይም አይደለም የሚል ነው፡፡ ይህንን ነገር እሼት እሸት ይህ የስንዴ ዘላላ ገና ሳይደርቅ ያለውን ያመለክታል፡፡ በዚህ የስንዴ ተክል አናት ላይ ፍሬዎቹ ይገኛሉ፡፡ ተመልከት "አሁን ለምነገር ነገር ትኩረት ስጥ"
ዳዊት ባስፈለገውና በተራበ ጊዜ፥ እርሱ አብረውት ከነበሩት ጋር ያደረገውን፥ . . . አላነበባችሁምን? አላቸው። ኢየሱስ ጸሐፍት እና ፈርሳዊያን ታሪኩን ከዚህ በፊት ማንበባቸውን ያውቃል፡፡ ይሁን እንጂ ሆን ብለው ታሪኩ ማስተላለፍ የፈለገውን መልዕክት በትክክል አልተረዳችሁትም በማለት ኢየሱስ ይከሳቸዋል፡፡ አማራጭ ትርጉሞች፡ “ዳዊት እና ከእርሱ ጋር የተነበሩት ሰዎች ያደረገጉትን አስታውሱ . . . ይህንን እንዳደረገ ታውቃላችሁ" አብያተር በአይሁድ ታሪክ ውስጥ ዳዊት በኖረበት ዘመን ከነበሩት ሊቀ ካህናት መካከል አንዱ ነው፡፡ እርሱ እንዴት ወደ እግዚብሔር ቤት እንደገባ "ዳዊት ወደ እግዚአብሔር ቤር ገብቶ" (UDB)
ሰንበት ስለ ሰው ተፈጥሮአል አማራጭ ትርጓሜ: "እግዚአብሔር ሰንበትን የፈጠረው ለሰው ልጆች መልካምነት ነው" እንጂ ሰው ስለ ሰንበት አልተፈጠረም፤ አማራጭ ትርጓሜ: "እግዚአብሔር ሰውን ለሰንበት መልካምነት አልፈጠረውም"
1 ምኩራብም ደግሞ ገባ፤ በዚያም እጁ የሰለለችበት ሰው ነበረ፡፡ 2 ሰውየውን በሰንበት ቀን ይፈውሰው እንደሆነ ተመለከቱት፡፡ 3 የሰለለችበትን ሰውየም ተነሥ አለው፡፡ 4 ሕዝቡንም በሰንበት ቀን የተፈቀደው መልካም ማድረግ ነው ወይስ ክፉ ማድረግ? ሕይወትን ማዳን ወይስ ማጥፋት? አላቸው፡፡ ነገር ግን ሕዝቡ ዝም አሉ፡፡ 5 በቁጣ ሲመለከት፣ በልባቸው ድንዳኔ ዐዝኖ፣ ሰውየውን እጅህን ዘርጋ አለው፤ ዘረጋውም፤ ዳነም፡፡ 6 ወጡ፤ ወዲውም እንዴት ሊያጠፉት እንደሚችሉ ከሄሮድስ ወገኖች ጋር በእርሱ ላይ ተማከሩ፡፡ 7 ከደቀ ዛሙርቱ ጋር ወደ ባሕሩ ሄደ፤ ከገሊላም እጅግ ብዙ ሕዝብ ተከትለው፤ ከይሁዳና 8 ከኤዶምያስና ከዮርዳኖስ ማዶ፣ ከጢሮስና ከሲዶና ምን ታላላቅ ነገሮችን እንዳደረገ በመስማት እጅግ ብዙ ሕዝብ ወደ እርሱ መጣ፡፡ 9 የተነሣ እንዳያጨናንቁት ትንሽ ጀልባ እንዲያቆዩለት ለደቀ መዛሙርቱ ተናገረ፤ 10 ፈውሶ ነበርና፡፡ በብዙ ደዌ የሚሠቃዩ ሁሉ ሊዳስሱት ይጋፉት ነበር፡፡ 11 መናፍስትም ባዩት ጊዜ በፊቱ ወደቁ፤ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ እያሉም ጮኹ፡፡ 12 ግን ማንነቱን እንዳይገልጡት አጥብቆ አዘዛቸው፡፡ 13 ወደ ተራራውም ወጣ፤ የሚፈልጋቸውንም ወደ እርሱ ጠራ፤ እነርሱም ወደ እርሱ ሄዱ፡፡ 14 ጋር እንዲሆኑ፣ ለመስበክ እንዲልካቸውና 15 ለማስወጣት ሥልጣን እንዲኖራቸው 16 ሁለት ሾመ፤ ጴጥሮስ ብሎ የሰየመው ስምዖን፣ 17 ልጅ ያዕቆብና የያዕቆብ ወንድም ዮሐንስ፤ እነርሱንም ቦአኔርጌስ ብሎ ጠራቸው፤ የነጎድጓድ ልጆች ማለት ነው፤ 18 እንድርያስና ፊልጶስ፣ በርተሎሜዎስና ማቴያስ፣ ቶማስና የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብ፣ ታዴዎስ፣ ቀናተኛው ስምኦንና 19 የሰጠው የአስቆሮቱ ይሁዳ፡፡ 20 ኢየሱስ ወደ አንድ ቤት ውስጥ ገባ፡፡ መብላት እንኳ እስከማይችሉ ድረስ እንደ ገና ብዙ ሕዝብ መጥቶ ተሰበሰበ፡፡ 21 ዘመዶቹም በሰሙ ጊዜ ይዘውት ሊሄዱ ወደ እርሱ መጡ፤ ዐብዶአል ብለው ነበርና፡፡ 22 የወረዱ ጻፎችም ብዔልዜቡል አለበት፤ አጋንንንትን የሚያስወጣውም በአጋንንት አለቃ ነው አሉ፡፡ 23 እርሱ ጠርቶአቸውም በምሳሌ ነገራቸው፤ ሰይጣን እንዴት ሰይጣንንን ማስወጣት ይችላል? 24 መንግሥትም እርስ በርሱ ቢከፋፈል፣ ያ መንግሥት መቆም አይችልም፤ 25 ቤትም እርስ በርሱ ቢለያይ፣ ያ ቤት ጸንቶ ሊቆም አይችልም፡፡ 26 ሰይጣንም እርስ በርሱ ቢቀዋወምና ቢለያይ፣ ፍጻሜው ይሆናል እንጂ መቆም አይችልም፡፡ በመጀመሪያ ኀይለኛውን ሰው ካላሰረና ከዚያም ንብረቱን ካልዘረፈ በቀር፣ 27 ወደ ኀይለኛው ቤት መግባትና ንብረቱን መዝረፍ የሚችል የለም፡፡ 28 እላችኋለሁ፤ ለሰው ልጆች ኀጢአታቸው ሁሉ፣ የሚሳደቡትም ስድብ ሁሉ ይቅር ይባላል፤ 29 ቅዱስን የሚሳደብ ግን ፈጽሞ ይቅርታ አያገኝም፤ ይልቁንም የየዘለዓለም ኀጢአት ዕዳ አለበት፤ 30 ርኩስ መንፈስ አለበት ብለዋል፡፡ 31 ወንድሞቹም መጡ፤ ውጭ ቆመውም እንዲጠሩት ወደ እርሱ ላኩ፡፡ 32 ብዙ ሰው ተቀምጦ ነበር፤ ሰዎችም እነሆ፣ እናትህና ወንድሞችህ ውጭ ይፈልጉሃል አሉት፡፡ 33 መለሰላቸው፤ አላቸውም፣ እናቴና ወንድሞቼ ማን ናቸው? 34 ዙሪያ የተቀመጡትን ተመልክቶም፣ እነሆ እናቴና ወንድሞቼ! ምክንያቱም 35 ፈቃድ የሚፈጽም ሁሉ ወንድሜ፣ እኅቴና እናቴ ነው፡፡
ኢየሱስ ወደ ምኩራብ ገባ "ኢየሱስ ወደ ምኩራብ ገባ " እጁ የሰለለች ሰው "እጁ ሽባ የሆነችበት ሰው ነበር" ይህንን ሰው ይፈውሰው እንደሆነ ለማየት ይከታተሉት ነበር "ፈርሳዊያን ኢየሱስ ይህንን ሰው ይፈውሰው እንደሆነ ለማየት ይከታተሉት ነበር"
ተነሣና በሁሉም መካከል ቁም "ተነሣና በዚህ ሕዝብ መካከል ቁም፡፡" ለመግደል . . . ተፈቅዷልን? ጸሐፊው “ሁሉም ዝም ማለታቸውን” ስለገለጸልን ኢየሱስ እነርሱን መጠየቁን እና መልስ እንዲሰጡት እየተጠበቀ እንደሆነ እንመለከታለን፡፡ ለተርጓሚዎች: "በሰንበት መልካም ነገርን ማድረግ ወይም መጉዳት ነው የተፈቀደው፤ ነፍስ ማዳን ወይስ መግደል፡፡” በሕግ የተፈቀደው በሙሴ ሕግ መሠረት
እጅህን ዘርጋ "እጅህን ዘርጋ" ኢየሱስ የሰውዬውን እጅ ፈወሰ "ኢየሱስ እጁን አዳነ" ወይም "ኢየሱስ የሰውዬውን እጅ ከዚህ በፊት እንደነበረው ደህና አደረገለት" ከሄሮድስ ወገን ጋር ተማከሩበት። አማራጭ ትርጓሜ: "ከሄሮዶስ ወገን ከሆኑት ጋር ተሰበሰቡ" ወይም "ከሄሮዶስ ወገን ከሆኑት ጋር ተሰብስበው እቅድ አወጡ"
ማደረገውን ነገር ሁሉ ሰማ "ኢየሱስ ስላደረገው ታላላቅ ተአምራት ሁሉ ሰማ" ወደ እርሱም መጥተው "ሕዝቡም ወደ ኢየሱስ ወደአለበት መጥተው"
ለደቀ መዛሙርቱ ጀልባ ያዘጋጁለት ዘንድ ጠየቃቸው "ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አላቸው፡ ጀልባ አዘጋጁልኝ፡፡" የሕዝቡ ተጽእኖ እጅግ በጣም ከባድ ነበር፡፡ "ሕዝቡ እርሱን ለመንካት ወደፊት ይጋፉ ነበር" (UDB) ችግር ያለባቸው ሁሉ እርሱን ለመንካት ይጋፉ ነበር "የታመሙ ሁሉ እርሱን ለመንካት ከፍተኛ ጥረት ያደርጉ ስለነበር እርስ በእርሳቸው ይገፋፋሉ"
እነርሱ . . . እነርሱ . . . እነርሱ በእርኩሳን መናስፍት ቁጥጥር የሆኑት ሰዎች አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ኢየሱስ በእርኩሳን መናስፍት ላይ ያለው ስልጣን ተያያዥነቱ “የእግዚአብሔር ልጅ1,” ከሚለው የእርሱ የማዕረግ ስም ጋር ነው፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ ይህ ወሳኝ የሆነ የኢየሱስ የማዕረግ ስም ነው፡፡
ከእርሱ ጋር ይሆኑ ዘንድ እንዲሁም ወንጌልን እንዲሰብኩ ይልካቸው ዘንድ ነው “ከእርሱ ጋር ይሆኑ ዘንድ እንዲሁም ወንጌልን እንዲሰብኩ ይልካቸው ዘንድ ነው” ወይም ከእርሱ ጋር እንዲሆኑ እና ወንጌልን እንዲሰብኩ እንዲልካቸው" (UDB)
ታዴዎስ "ታዴዎስ" የኢየሱስ 12 ሐዋርያት ይሆኑ ዘንድ ከተመረጡት ሰዎች መካከል አንዱ ነው፡፡
እንደገናም ብዙ በጣም ብዙ ሰዎች ከመሰብሰባቸው የተነሳ ምግብ እንኳ ለመብላት አልቻሉም ነበር፡፡ "በጣም ብዙ ሕዝብ እንደገና ከመሰብሰቡ የተነሳ ምግብ ለመብላት እንኳ ጊዜ አላገኙም ነበር ወይም" ወይም "እርሱ በሚቆይበት ሥፍራ ላይ እንደገና ብዙ ሰዎች ተሰበሰቡ፡፡ በእርሱ ዙሪያም በጣም ብዙ ሰዎች ነበሩ፡፡ እርሱ እና የእርሱ ደቀ መዛሙርት ምግብ ለመብላት በቂ ጊዜ እንኳ ማግኘት አልቻሉም፡፡" (UDB) እርሱን ለመያዝ መጡ የእርሱ ቤተሰብ አባላት ወደ ቤት መጥተው ለመያዝ እና እነርሱ ጋር ወደ ቤት በጉልበት እንዲሄድ መጡ፡፡
ሴጣን እንዴት ሴጣንን ልያስወጣ ይችላል? "ሴጣን ራሱን ማስወጣት አይችልም" ወይም "ሴጣን የራሱ በሆኑት እርኩሳን መናስፍት ተቃራኒ አይሆንም"
መልዕክተኛ ወደእርሱ ዘንድ ሰደዱና አስጠሩት፡፡ "የኢየሱስ እናት እና ታናሽ ወንድሙ አንድ ሰው ወደ ቤቱ ውስጥ ልከው እነርሱ በውጪ እንደሚገኙ ለኢየሱስ ይናገርውና ውጪ ወጥቶ እንዲያናግራቸው ይነግረው ዘንድ መልዕክተኛ ላኩበት፡፡"
በውስጧ ተቀመጠ "ወደ ተንኳይቱ ገብቶ ተቀመጠ"
1 በባህር አጠገብ ማስተማር ጀመረ፡፡ ከህዝቡ መብዛት የተነሳ በባህር ላይ ባለ ጀልባ ገብቶ ተቀመጠ፡፡ ህዝቡም ሁሉ በባህሩ ዳርቻ ላይ ተሰብስበው ነበር፡፡ 2 ነገርም በምሳሌ አስተማራቸው፡፡ በትምህርቱም እንዲህ አላቸው፡፡ 3 ስሙ ዘሪ ሊዘራ ወጣ፡፤ 4 በሚዘራበትም ጊዜ አንዳንዱ በመንገድ ዳር ወደቀ ወፎችም መጥተው ለቀሙት፡፡ 5 ደግሞ ብዙ አፈር በሌለው በድንጋያማ መሬት ላይ ወደቀ፡፡ መሬቱ ጥልቀት ስላልነበረው ወዲያው በቀለ፤ 6 በወጣ ጊዜም ጠወለገ ሥርም ስላልነበረው ደረቀ፡፡ 7 ደግሞም አንዳንዱ በእሾህ መካከል ወደቀ እሾሁም አድጎ አነቀው ፍሬም አላፈራም፡፡ 8 አንዳንዱ በመልካም መሬት ላይ ወደቀ አደገ እየበዛ ሄደ ፍሬም አፈራ ሶስት እጥፍ ስልሳ እጥፍ እና መቶ እጥፍ ፍሬ ሰጠ፡፡ 9 እንዲህም አለ ጆሮ ያለው ይስማ፡፡ 10 በሆነ ጊዜ ከደቀመዛሙርቱ ጋር አብረው የነበሩት ስለ ምሳሌዎቹ ጠየቁት፡፡ 11 አላቸው ለእናንተ የእግዚአብሔር መንግሥት ምስጢር ተሰጥቷችኋል፡፡ በውጭ ላሉት ግን እንዲህ አይደለም 12 እንዳያዩ ሰምተውም እንዳያስተውሉ እንደገና ተመልሰው ይቅር እንዳይባሉ ሁሉም ነገር በምሳሌ ይሆንባቸዋል፡፡ 13 አላቸው እናንተ ይህ ምሳሌ አልገባችሁምን? ሌሎቹን ምሳሌዎች ሁሉ እንዴት ትረዳላችሁ? 14 ዘሪው ቃሉን ዘራ፡፡ 15 በመንገድ ዳር የወደቁት እነዚህ ናቸው ቃሉ በሚዘራበት ጊዜና ቃሉን እንደሰሙ ወዲያውኑ ሰይጣን መጥቶ በውስጣቸው የተዘራውን ቃል ይወስዳል፡፡ 16 በድንጋያማ መሬት ላይ የወደቁት አነዚህ ቃሉን በሰሙ ጊዜ ወዲያውኑ በደስታ ይቀበሉታል 17 ሥር የላቸውምና ለጊዜው ይቀበሉታል ከዚያም በቃሉ ምክንያት መከራ ወይም ስደት በሚነሳበት ጊዜ ወዲያወኑ በቃሉ ይሰናከሉበታል፡፤ 18 ቦታ የወደቁት እነዚህ ቃሉን የሰሙ ናቸው 19 አለም ሀሳብና የባለጠግነት ማታለል የሌሎች ነገሮች ምኞት ይገቡና ዘሩን ያንቁታል ፍሬ የማያፈራም ይሆናል፡፡ 20 መሬት የወደቁት እነዚህ ቃሉን ሰምተው የሚቀበሉት ናቸው ሰላሳ እጥፍ ስልሳ እጥፍ እና መቶ እጥፍ የሚያፈሩ ናቸው፡፡ 21 አላቸው፡- መብራትን ከፍ ባለ ማስመጫ ላይ እንጂ ከእንቅብ በታች ወይም አልጋ ሥር ያስቀምጡታልን? 22 ሳይገለጥ የሚቀር ነገር የለም በሚስጢር የተደረገ ወደ ብርሃንም የማይወጣ የለም፡፡ 23 ያለው ይስማ እንዲህም አላቸው 24-25 አስተውሉ መስፈሪያ ይሰፈርላችኋል ለእናንተም የበለጠ ይሰጣችኋል፡፡ ላለው የበለጠ ይጨመርለታል ከሌለው ግን ያ ያለው እንኳ ይወሰድበታል፡፡ 26 አለ የእግዚአብሔር መንግሥት በመሬት ላይ ዘርን የዘራን ሰው ትመስላለች፡፡ 27 ሲመሽ ይተኛል ሲነጋም ይነቃል፡፡ እንዴት እንደሆነ ባላወቀው መልኩ ዘሩ አቆትቁጦ በቀለ፡፤ 28 ምድር የራሷን ሰብል ፍሬ አፈራች መጀመሪያ ቅጠሉ ቀጥሎም ዛላው በመጨረሻም በዛላው ውስጥ ሙሉ ፍሬ አፈራች፡፡ 29 ግን ፍሬው በደረሰ ጊዜ መከር ነውና ወዲያውኑ ማጭድ አዘጋጀ፡፡ 30 እንዲህ አለ የእግዚአብሔርን መንግሥት በምን እንመስላታለን? ወይም በምን ምሳሌ እንገልጻታለን? 31 ቅንጣት ትመስላለች፡፡ በምድር ላይ በተዘራ ጊዜ ሲዘራ ምንም እንኳ በምድር ካሉ ዘሮች ሁሉ ያነሰ ቢሆንም 32 ጊዜ ያድጋል ቅርንጫፍም ያወጣል የሰማይ ወፎች ከጥላው ሥር እስኪጠለልቡበት ድረስ ከተክሎች ሁሉ ይልቅ ታላቅ ይሆናል፡፡ 33 ሊሰሙ በሚችሉት መጠን ቃሉን በብዙ ምሳሌዎች ተናገራቸው 34 ምሳሌ ምንም አልተናገራቸውም፡፡ ለደቀመዛሙርቱ ግን ለብቻቸው ሁሉንም ነገር ገለጸላቸው፡፡ 35 ቀን በመሸ ጊዜ ወደ ማዶ እንሻገር አላቸው፡፡ 36 ህዝቡንም ትተው በጀልባ ወሰዱት፡፡ ሌሎችም ጀልባዎች ከእርሱ ጋር ነበሩ፡፡ 37 የነፋስ ማዕበልም ተነሳ ጀልባው እስኪጥለቀለቅ ድረስ ማዕበል ጀልባውን መታው፡፡ 38 ከጀልባው በስተኋለኛው ክፍል ትራስ ተንተርሶ ተኝቶ ነበር፡፡ ቀስቅሰውም መምህር ሆይ ስንጠፋ አይገድህምን አሉት፡፡ 39 እርሱም ተነሳ ነፋሱንም ገሰጸው ባህሩንም ዝም በል ጸጥ በል አለው፡፡ ነፋሱም ተወ ታላቅ ጸጥታም ሆነ፡፡ 40 ስለምን ፈራችሁ? እምነት የላችሁምን እምነታችሁስ ወዴት አለ አላቸው፡፡ 41 ፈርተው እርስ በእርሳቸው ነፋሱና ባህሩ እንኳ የሚታዘዙለት እንግዲህ ይህ ማነው? ተባባሉ፡፡
እናም ወደ ባሕሩ ውስጥ ገፏት “እናም ተንኳይቱን ወደ ባሕሩ ውስጥ ገፏት
አደጉ "በፍጥነት ማደግ ጀመሩ"
ጠቀለጉ "ተቃጠሉ"
የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ "በጥሞና የሚሰማ ሰው የዚህን ነገር ትርጉም በሚገባ ይረዳል”፡፡
ለእናንተ ተሰጥቶዋችኋል "እግዚአብሔር ሰጥቶዋችኋል" ወይም "እኔ ሰጥቼአችኋዋለሁ" ያያሉ ግን አያስተውሉም "ይመለከታሉ ነገር ግን ለማስተዋል አይፈልጉም" ወይም "ይመለከታሉ ግን አይረዱም"
ይህንን ምሳሌ ተረድታችሁታልን? እንዲህ ከሆነ እንዴት ሌሎችን ምሳሌው መረዳት ትችላላችሁ? "የዚህን ምሳሌ ትርጉም መረዳት የማትችሉ ከሆነ የተቀሩትን ምሳሌዎችንም መረዳት አትችሉም፡፡"
የዚህ ዓለም ሀሰብ አማራጭ ትርጉም፡ "አሁን ስላለው ሕይወት ግድ የሚላቸው" የባለጠግነት ምኞት አማራጭ ትርጉም፡ "እርካታ የማይሰጡት በሀብት የሚገኘው ደስታ" የሌሎች ነገሮች ምኞች "ከሀብት ውጪ ያሉት ሌሎች መሻቶች"
መብራትን ከእንቅብ ወይም ከአልጋ በታች ለማኖር ወደ ቤት ውስጥ ያመጡታልን? "መብራትክ ከእንቅብ ወይምከአልጋ በታች ለማኖር በእርግጠኝነት ወደ ቤት ውስጥ አታመጡም፡፡" የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ ይህንን በ MRK 4:9 ላይ በተረጎማችሁት መሠረት ትርጉሙት፡፡
በሠፈራችሁት መሥፈሪያ ልክ ትቀበላላችሁ፤ እንዲያው ከዚያ በላይ ታገኛላችሁ "የበለጠ ባደመጣችሁ ቁጥር እግዚብሔር የለልጥ መረዳትን ይሰጣችኋል፡፡" ማንም . . . "ቃሌን የተረዳ ማንም ሰው ቢሆኖር፡፡"
ዘርን እንደሚዘራ ሰው "ዘሩን እንደሚዘራ ገበሬ" ማጭድ የእርሻ ምርት ለማጨድ የሚገለግል መሣሪያ
"የእግዚብሔርን መንግስት ከምን ጋር እናነጻጽራታለን እንዲሁም በምን ምሳሌ እንገልጻታለን? "በዚህ ምሳሌ አማካኝነት የእግዚአብሔር መንግሰት ምን እንደሚትመስል ማስረዳት ይቻላል፡፡
ማድመጥ እስከቻሉ ድረስ "መረዳት እስከቻሉ ድረስ"
ስንጠፋ ግድ አይልህምን? "ለሁኔታው ትኩረት እንድትሰጠው እንፈልጋለን፤ ልንሞት ነው!" - ልንሞት ነው በዚህ ሥፍራ ላይ "እኛ" የሚለው ቃል ደቀ መዛሙርቱን እና ኢየሱስን የሚያካትት ነው፡፡ ገሰጸው "በቁጣ አስተካከለው" ወይም "መገሰጽ" ሠላም፣ ጸጥ በል፡፡ "ሠላም" እና "ጸጥ በል" ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው ቃላት ናቸው፡፡
እንዲህ የምትፈሩ ስለ ምን ነው? "በጣም በመፍራታችሁ በጣም አፍሬባችኋለሁ፡፡" ይህ ማን ሊሆን ይችላል "ይህ ሰው ማን እንደሆነ በጥንቃቄ ልናሰብ ይገባናል!"
1 ባሕሩ ሌላ ዳርቻ፣ ወደ ጌርጌሴኖን አገር መጡ፡፡ 2 ከጀልባዋ ውስጥ ሲወጣም ወዲያውኑ ርኩስ መንፈስ ያለበት አንድ ሰው ከመቃብር ሥፍራ ወጥቶ ተገናኘው፤ 3 በመቃብር ስፍራ አድርጎ ነበር፤ እርሱን በሰንሰለት ሊያስረው የሚችል ሰው አልነበረም፤ 4 ጊዜ በእግር ብረትና በሰንሰለት ይታሰር ስለ ነበር፣ ሰንሰለቶቹን ይበጣጥሳቸው፣ እግር ብረቶቹንም ይሰባብራቸው ነበር፤ እርሱን ለመያዝ የሚያስችል ጥንካሬ ያለው ሰውም አልነበረም፡፡ 5 ቀንና ሌሊት በመቃብሮቹና በተራራዎቹ ዘንድ ሰውነቱን በድንጋይ እየቈረጠ ይጮኽ ነበር፡፡ 6 ከሩቅ ሲያየው፣ ሮጠና ሰገደለት፤ 7 በመጮኽም፣ የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ከአንተ ጋር ምን አለኝ? በእግዚአብሔር አምልሃለሁ፣ አታሠቃየኝ አለ፡፡ 8 ርኩስ መንፈስ ከሰውየው ውጣ ብሎት ነበርና፡፡ 9 ማን ነው ብሎም ጠየቀው፤ ብዙ ነንና ስሜ ሌጌዎን ነው አለው፡፡ 10 እንዳያባርራቸውም አጥብቆ ለመነው፡፡ 11 በተራራው ጥግ ትልቅ የእሪያ መንጋ ይሰማራ ነበር፡፡ 12 በእነርሱ ውስጥ እንድንገባ ወደ እሪያዎቹ ስደደን በማለትም ለመኑት፡፡ 13 እዲሄዱ ፈቀደላቸው፡፡ ርኩሳን መናፍስቱም ወጡ፣ በእሪያዎቹም ውስጥ ገቡ፤ ሁለት ሺ ያህል እሪያ ያለበት መንጋም በቁልቁለቱ ላይ ወደ ባሕሩ እየተንጋጋ ሄደ፤ በባሕሩም ውስጥ ሰመጠ፡፡ 14 የሚጠብቁትም ሸሹ፤ በከተማውና በአገሩ ውስጥም አወሩት፡፡ የሆነውንም እንዴት እንደ ነበረ ለማየትም ሰዎች መጡ፡፡ 15 ኢየሱስም መጥተው አጋንንት ያደሩበትን፣ ሌጌዎንም እንኳ የነበረበትን ሰው ተቀምጦ፣ ልብስ ለብሶና ልቡም ተመልሶለት አይተው ፈሩ፡፡ 16 ሰዎችም አጋንንት ባደሩበት ሰውየ ላይ የታየው እንዴት እንደ ሆነና በእሪያዎቹ የሆነውም እንዴት እንደ ነበረ ነገሯቸው፡፡ 17 ኢየሱስንም ከአገራቸው እንዲወጣ ይለምኑት ጀመር፡፡ 18 ጀልባዋ ውስጥ እየገባ ሳለ፣ በአጋንንት ተይዞ የነበረው ሰው ከአንተ ጋር ልኑር ብሎ ለመነው፡፡ 19 አልፈቀደለትም፤ ይልቁንም ወደ ቤትህ፣ ወደ ዘመዶችህ ሂድ፣ ጌታ ለአንተ እንዴት ታላላቅ ነገሮችን እንዳደረገልህ፣ እንዴትም ምሕረቱን ባንተ ላይ እንዳሳየ ንገራቸው አለው፡፡ 20 ሄደና ኢየሱስ እንዴት ታላላቅ ነገሮችን እንዳደረገለት ዐሥር ከተማ በሚባለው ውስጥ ማሠራጨት ጀመረ፤ ሰዎችም ሁሉ ተደነቁ፡፡ 21 በጀልባዋ ወደ ሌላ አቅጣጫ ይሄድ በነበረ ጊዜም ደግሞ፣ እጅግ ብዙ ሕዝብ ወደ እርሱ ተሰበሰበ፤ እርሱም በባሕሩ አቅራቢያ ነበረ፡፡ 22 ከምኵራብ ኀላፊዎች አንዱ፣ ኢያኢሮስ የሚባል መጣ፣ እርሱንም አይቶ በእግሩ ሥር ወደቀ፤ 23 ልጄ ልትሞት ነው፤ እንድትድንና በሕይወት እንድትኖር መጥተህ እጅህን ትጭንባት ዘንድ እለምንሃለሁ በማለትም አጥብቆ ለመነው፡፡ 24 ዐብሮት ሄደ፤ እጅግ ብዙ ሰዎችም ተከተሉት፤ ይጋፉትም ነበር፡፡ 25 ሁለት ዓመት ደም ይፈስባት የነበረ፣ 26 ብዙ ችግር የደረሰባት ብትሆንና ያላትን ሁሉ ብትከፍልም፣ ምንም ያልተሻላት፣ ይልቁንም የባሰባት 27 ሴት ስለ ኢየሱስ ሰምታ ከሕዝቡ በስተኋላ መጣች፣ የኢየሱስንም ልብስ ነካች፡፡ 28 ላት፣ ይልቁንም የባሰባት 27አንድ ሴት ስለ ኢየሱስ ሰምታ ከሕዝቡ በስተኋላ መጣች፣ የኢየሱስንም ልብስ ነካች፡፡ 28ልብሱን ብቻ ከነካሁ እድናለሁ ብላለችና፡፡ 29 የሚፈስሰው ደሟ ቆመ፤ ከሕማሟ እንደ ተፈወሰችም በሰውነቷ ታወቃት፡፡ 30 ኢየሱስ ኀይል ከእርሱ መውጣቱን በራሱ በመረዳት፣ ዙሪያውን ወደ ሕዝቡ ተመለከተ፤ ልብሴን የነካው ማን ነው? ብሎም ተናገረ፡፡ 31 መዛሙርቱም ሕዝቡ ሲጋፉህ ታያለህ፣ የነካኝ ማን ነውም? ትላለህ፡፡ 32 ይህን ያደረገችውንም ለማየት ዙሪያውን ተመለከተ፡፡ 33 ሴትዮዋ ግን በመፍራትና በመንቀጥቀጥ፣ ለእርሷ የተደረገውንም በማወቅ መጣችና በፊቱ ወደቀች፤ እውነቱንም ሁሉ ነገረችው፡፡ 34 እርሱም፡- ልጄ ሆይ! እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ፣ ከሕማምሽም ተፈወሺ አላት፡፡ 35 ኢየሱስ ገና እየተናገረ ሳለ ከምኵራቡ ኀላፊ ቤት ሰዎች መጡ፤ ልጅህ ሞታለች፤ መምህሩን ለምን ታስቸግረዋለህ ብለውም ተናገሩ፡፡ 36 ኢየሱስ የተናገሩትን ሰምቶ የምኵራቡን ኀላፊ “አትፍራ፤ እመን ብቻ” አለው፡፡ 37 ኢየሱስ ከጴጥሮስ፣ ከያዕቆብና ከያዕቆብ ወንድም ከዮሐንስ በቀር ማንም እንዲከተለው አልፈቀደም፡፡ 38 ወደ ምኵራቡ ኀላፊ ቤት መጡ፤ ኢየሱስ ያዘኑ፣ የሚያለቅሱና የዋይታ ጩኸት የሚያሰሙ ሰዎችን ተመለከተ፡፡ 39 ወደ ውስጥ ገባና “ለምን ታዝናላችሁ? ለምንስ ታለቅሳላችሁ? ልጅቱ ተኝታለች እንጂ አልሞተችም” አላቸው፡፡ 40 ሰዎቹ በኢየሱስ ሣቁበት፤ እርሱ ግን ሁሉንም ወደ ውጭ አስወጣቸው፡፡ የልጅቱን አባትና እናት፣ ከእርሱም ጋር የነበሩትን ይዞ ልጅቱ ወደ ነበረችበት ክፍል ገባ፡፡ 41 ከዚያም ልጅቱን በእጁ ይዞ “ታሊታ ኩም!” ትርጉሙ “ትንሿ ልጅ ተነሺ እልሻለሁ” ማለት ነው፡፡ 42 ወዲያው ልጅቱ ተነሣች፤ መራመድም ጀመረች፡፡ (ዐሥራ ሁለት ዓመቷ ነበርና) በዚህ ሰዎቹ በጣም ተገረሙ፡፡ 43 ከዚያም ኢየሱስ ስለዚህ ጕዳይ ማንም ማወቅ እንደሌለበት ለሰዎቹ ጥብቅ ትእዛዛትን ሰጣቸው፤ የምትበላውንም ስጧት አለ፡፡
እግሮቹ በሰንሰለት የታሠሩ "በሰንሰለት እግሮቹ የታሠሩ" እርሱን መያዝ "እርሱን መቆጣጠር"
ይጮኸ ነበር "እርኩስ መንፈሱ ይጮኸ ነበር" ከአንተ ጋር ምን አለኝ? አማራጭ ትርጉም: "ከአንተ ጋር ምንም ጉዳይ የለኝ" አታሰቃየኝ "አታዘቃየኝ" (UDB) የልዑል የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ? በእግዚአብሔር በራሱ አምልሃለሁ እባክህ አታሰቃየኝ፡፡ “የልዑል የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ” እርኩሳን መናፍስትን የማሰቃየት ኃይል አለው፡፡ የልዑል የእግዚአብሔር ልጅ ይህ የኢየሱስ ወሳኝ የሆነ የማዕረግ ስሙ ነው፡፡
እርሱም እንዲህ አለው፣ "ስሜ ሠሰራዊት ነው፣ ምክንያቱም ብዙዎች ነን፡፡" በሰውዬው ውስጥ ያሉት እርኩሳን መናፍስስት ለኢየሱስ እንዲህ አሉት፤ በዚህ ሰው ውስጥ ያለው አንድ እርኩስ መንፈስ ብቻ ሳይሆን ብዙ እርኩሳን መናፍስት ናቸው፡፡
እርሱም ፈቀደላቸው "ኢየሱስ ለእርኩሳን መናፍስቱ ፈቀደላቸው" ወደ ሁለት ሺህ አከባቢ የሚጠጉ አሳማዎች "ወደ 2000 አከባቢ የሚጠጉ አሳማዎች"
ወደ አእምሮውም ተመለሰ "ወደ አእምሮው ተመለሰ"
በእርኩስ መናፈስት ተይዞ የነበረውም ሰው "በእርኩሳን መናፍስት ቁጥጥር ሥር የነበረው ሰው"
ዐሥር ከተሞች ከገሊላ በባሕር በደቡብ ምሥራቅ አከባቢ
ለዐሥራ ሁለት ዓመታት "ለ 12 ዓመታት"
“አሁን የነካኝ ማን ነው?” ትላለህን አማራጭ ትርጉም፡ “በዚህ ግርግር ውስጥ ሆነህ ማን እንደነካህ መጠየቅህ በጣም አስገርሞናል”
ሴት ልጅ ኢየሱስ ይህንን ቃል የተጠቀመው በምሳሌያዊ የአነጋገር ዘይቤ ሲሆን ማሳየት የፈለገውም ይህች ሴት በእርሱ ማመኗን ነው፡፡
መምህሩን ከዚህ በላይ ለምን ታስቸግሪዋለህ? አማራጭ ትርጉም፡ "መምህሩን ከዚህ በላይ አታስቸግረው፡፡"
ሲንጫጩና ሲያለቅሱ በዚህ ሥፍራ ላይ “ሲንጫጩ” እና “ሲያለቅሱ” የሚሉት ቃላት ተመሳሳይ ትርጓሜዎች አሏቸው፡፡ አማራጨ ትርጉም፡ "ሲያለቅሱ በታላቅ ድምፅ ይጮኹ ነበር"
ስለምን ተቆጣችሁ፣ ሰለምንስ ታለቅሳላችሁ? አማራጭ ትርጉም፡ "መንጫጫትም ሆነ ማልቀስ የለባችሁም፡፡"
የዐሥራ ሁለት ዓመት ዕድሜ ነበራት "ዐሥራ ሁለት ዓመቷ ነበር" በጣም አስጠነቀቃቸው "አጥብቆ ነገራቸው"
1 ከዚያ ወጥቶ ወደ ገዛ ምድሩ መጣ፤ ደቀመዛሙርቱም ተከተሉት፡፡ 2 ሰንበት በሆነ ጊዜም በምኩራብ ውስጥ ሊያስተምር ጀመረ፡፡ የሰሙትም ሁሉ ይህ ሰው እነኚህን ነገሮች ከወዴት አገኛቸው? ለዚህ ሰው የተሰጠችውስ ጥበብ እንደምን ያለች ናት፤ በእጆቹ የሚደረጉት እነዚህ ታላላቅ ነገሮችስ ምን ትርጉም ይኖራቸው ይሆን? 3 ይህ አናጺው የማርያም ልጅ፤ የያዕቆብና የዮሳ፣ የይሁዳና የስምዖን ወንድም አይደለምን? እህቶቹስ ቢሆኑ እዚህ ከእኛ ጋር አይደሉምን? በማለት ተደነቁ፤ ተሰናከሉበትም፡፡ 4 ኢየሱስም ነብይ በሀገሩ፣ በወገኑና በገዛ ቤተሰቡ ካልሆነ በስተቀር ሳይከበር አይቀርም አላቸው፡፡ 5 ላይ እጆቹን ጭኖ ከመፈወስ በስተቀር በዚያ ታላቅ ተአምራት አላደረገም፡፡ 6 ምክንያት ተደነቀ፡፡ በየመንደሮቹም እያስተማረ ዞረ፡፡ 7 አሥራ ሁለቱን ወደ ራሱ ጠራና ሁለት ሁለት አድርጎ ይልካቸው ጀመር፤ በእርኩሳን መናፍስት ላይም ሥልጣንን ሰጣቸው፡፡ 8 ለጉዞአቸውም ከበትራቸው በቀር ምግብ፣ የመንገድ ሻንጣም ሆነ በገንዘብ ቦርሳቸው ውስጥ ገንዘብ እንዳይዙ አዘዛቸው፡፡ 9 በስተቀር ቅያሪ ልብስ አትያዙ አላቸው፡፡ 10 ከዚያ እስክትወጡ ድረስ በምትገቡበት ቤት በዚያ ቆዩ አላቸው፡፡ 11 ቦታ ሁሉ ከማይቀበሏችሁና ከማይሰሟችሁ ሰዎች ምሥክር ይሆንባቸው ዘንድ በጫማችሁ ሥር ያለውን አቧራ አራግፉ፡፡ 12 ደቀ መዛሙርቱም ወጥተው ሰዎች ንሰሐ እንዲገቡ ሰበኩላቸው፡፡ 13 ብዙ አጋንንትን አስወጡ፤ ታመው የነበሩ ብዙዎችንም ዘይት ቀብተው ፈወሱአቸው፡፡ 14 ዝናው ወጥቶ ነበርና ንጉሡ ሔሮድስ በሰማ ጊዜ አጥማቂው ዮሐንስ ከሙታን ተነሥቶአል፤ ስለዚህ እነዚህ ታላላቅ ነገሮች የሚደረጉትም በእርሱ ነው አለ፡፡ 15 ግን ሌሎች ኤልያስ ነው አሉ፡፡ ሌሎቹም ነብይ ወይም ከነብያት አንዱ ነው አሉ፡፡ 16 ነገር ግን ሔሮድስ ይህንን ሁሉ በሰማ ጊዜ እኔ አንገቱን ያስቆረጥኩት ዮሐንስ ተነሥቶአል አለ፡፡ 17 ባገባት በወንድሙ በፊሊጶስ ሚስት በሄሮድያስ ምክንያት ራሱ ልኮ ዮሐንስን በመያዝ በወህኒ አኑሮት ነበርና፡፡ 18 ዮሐንስም ሔሮድስን የወንድምህ ሚስት ለአንተ ልትሆን አይገባም ይለው ነበር፡፡ 19 ሔሮድያዳ ዮሐንስን ትቃወምና ልትገድለው ትፈልግ ነበር፣አልቻለችምም፡፡ 20 ሔሮድስ ዮሐንስን ይፈራው ነበር፡፡ ቅዱስና ጻድቅ እንደሆነ በማወቁም ይጠነቀቅለት ነበር፡፡ በሚሰማው ጊዜ ግራ እየተጋባም ቢሆን በደስታ ይሰማው ነበር፡፡ 21 ምቹ ቀን በመጣ ጊዜም ልደቱን አስመልክቶ ሔሮድስ ለመኳንንቱ፣ ለሹማምንቱና ለገሊላ ታላላቅ ሰዎች የእራት ግብዣ አዘጋጀላቸው፡፡ 22 የሄሮድያዳ ልጅ ራሷ ገብታ በዘፈነች ጊዜም ሔሮድስንና ከእርሱ ጋር በማዕድ የተቀመጡትን አስደሰተቻቸው፡፡ ንጉሱም ልጃገረዲቱን የምትፈልጊውን ሁሉ ጠይቂኝ እሰጥሻለሁ አላት፡፡ 23 ማናቸውንም የምትፈልጊውን ጠይቂኝ፣ የመንግሥቴን ግማሽም ቢሆን እሰጥሻለሁ ብሎ ማለላት፡፡ 24 እርስዋም ወጥታ ወደ እናቷ በመሄድ ምን ልጠይቀው? ብትላት የአጥማቂው የዮሐንስን ራስ አለቻት፡፡ 25 እርስዋም ወደ ንጉሱ ፈጥና በመምጣት የአጥማቂውን የዮሐንስን ራስ በሳህን እንድትሰጠኝ እፈልጋለሁ አለችው፡፡ 26 ንጉሡም እጅግ አዘነ፡፡ ነገር ግን በመሐላዎቹና በማዕድ በተቀመጡት ምክንያት አልተቃወማትም፡፡ 27 ንጉሡም ወዲያውኑ ከጠባቂዎቹ አንደኛውን ወታደር ልኮ ራሱን እንዲያመጣ አዘዘው፡፡ እርሱም ሔደና በወህኒ የዮሐንስን ራስ ቆረጠው፤ 28 በሳህን አምጥቶም ለልጃገረዲቱ ሰጣት፣ ልጃገረዲቱም ለእናቷ ሰጠቻት፡፡ 29 ደቀመዛሙርቱም ይህንን በሰሙ ጊዜ መጡና አስከሬኑን ወስደው በመቃብር አኖሩት፡፡ 30 ሐዋርያቱም ወደ ኢየሱስ ተመልሰው ያደረጉትንና ያስተማሩትን ነገር ሁሉ ነገሩት፡፡ 31 እርሱም እናንተ ራሳችሁ ወደ ምድረበዳ ኑና ጥቂት ጊዜ ዕረፉ አላቸው፡፡ ወደ እነርሱ የሚመጡና የሚሔዱ ብዙዎች ነበሩና ለመብላት እንኳን ጊዜ አጥተው ነበር፡፡ 32 በጀልባ ገብተው ወደ ምድረበዳው ፈቀቅ ብለው ሔዱ፡፡ 33 ሲሔዱም ሕዝቡ አዩአቸውና ብዙዎቹ አወቁአቸው፤ እነርሱም ከየከተሞቹ ሁሉ በአንድነት በሩጫ ቀደሟቸው፡፡ 34 ወደዚያ በመጣም ጊዜ ብዙ ሕዝብ አይቶ እረኛ እንደሌላቸው በጎች ይመስሉ ነበርና አዘነላቸው፡፡ ብዙ ነገሮችንም ያስተምራቸው ጀመር፡፡ 35 ቀኑ በመሸ ጊዜም ደቀመዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀርበው ሥፍራው ምድረበዳ ነው፣ ቀኑም መሽቶአል፤ 36 በአቅራቢያው ወደሚገኙ ከተሞችና መንደሮች ሔደው ለራሳቸው አንዳች የሚበሉትን እንዲገዙ ሕዝቡን አሰናብታቸው አሉት፡፡ 37 እርሱ ግን መልሶ እናንተ የሚበሉትን ስጧቸው አላቸው፡፡ እነርሱም እንሂድና ይበሉ ዘንድ የአንድን ሰው የስድስት ወር ገቢ በሚያህል ገንዘብ እንጀራ ገዝተን እንስጣቸውን? አሉት፡፡ 38 እርሱም ምን ያህል እንጀራ እንዳላችሁ ሂዱና እዩ አላቸው፡፡ ባወቁ ጊዜም ያለው አምስት እንጀራና ሁለት ዓሳ ነው አሉት፡፡ 39 እርሱም ሁሉን በአረንጓዴው ሣር ላይ በቡድን በቡድን እንዲያስቀምጡ አዘዛቸው፡፡ 40 እነርሱም በመቶዎችና በሃምሳዎች እየሆኑ በረድፍ ተቀመጡ፡፡ 41 እርሱም አምስቱን እንጀራና ሁለቱን ዓሳ ተቀብሎ ወደ ሰማይ በመመልከት ባረከውና ቆርሶ ለሕዝቡ እንዲያቀርቡት ለደቀመዛሙርቱ ሰጣቸው፡፡ ሁለቱን ዓሳም ለሁሉም አካፈላቸው፡፡ 42 ሁሉም በልተው ጠገቡ፡፡ 43 አሥራ ሁለት ትላልቅ መሶብ ሙሉ ቁርስራሽ፣ እንዲሁም ከዓሳው ሰበሰቡ፡፡ 44 እንጀራውን የበሉት እነዚያ 5000 ወንዶች ነበሩ፡፡ 45 ወዲያውኑ እርሱ ራሱ ሕዝቡን ሲያሰናብት ሳለ ደቀመዛሙርቱ በጀልባ ገብተው ወደ ማዶ ወደ ቤተሳይዳ ቀድመውት እንዲሻገሩ ግድ አላቸው፡፡ 46 ከተለያቸው በኋላም ሊጸልይ ወደ ተራራ ፈቀቅ አለ፡፡ 47 በመሸም ጊዜ ጀልባዋ በባህር ላይ ነበረች፤ እርሱም ብቻውን በምድር ላይ ነበር፡፡ 48 ነፋሱ ከፊት ለፊታቸው እየተቃወማቸው ሳለ ለመቅዘፍ ሲጨነቁ አያቸውና ከሌሊቱ በአራተኛው ክፍል በባህሩ ላይ እየተራመደ ወደ እነርሱ መጣ፤ ሊያልፋቸውም ይፈልግ ነበር፡፡ 49 ነገር ግን በባህሩ ላይ ሲራመድ ባዩት ጊዜ ምትሃት ነው ብለው ስላሰቡ ጮኹ፡፡ 50 ሁሉም አይተውት ስለነበረ ታወኩ፡፡ እርሱ ግን ወዲያው ተናገራቸውና አይዞአችሁ! እኔ ነኝ አትፍሩ! አላቸው፡፡ 51 ወደ እነርሱ ወጥቶም ወደ ጀልባይቱ ገባ፤ ነፋሱም ተወ፡፡ 52 እነርሱም በራሳቸው ያለመጠን ተገረሙ፤ ልባቸው ደንዝዞ ነበርና ስለ እንጀራው አላስተዋሉም፡፡ 53 በተሻገሩ ጊዜም ወደ ጌንሳሬጥ አገር ወደ ባህሩ ዳርቻ መጡ፡፡ 54 ከጀልባዋ በወጡ ጊዜም ሕዝቡ ወዲያው አወቁትና 55 በዙሪያው ወዳሉ መንደሮች በሞላ በመሮጥ ህሙማንን በአልጋ ተሸክመው እርሱ እንዳለ ወደሰሙበት ወደዚያ አመጧቸው፡፡ 56 በየትኛውም እርሱ በገባባቸው መንደሮች ወይም ከተማዎች ወይም ሀገሮች ህሙማንን በገበያ ሥፍራዎች ያስቀምጧቸው፣ ቢቻላቸው ሊዳስሱት ካልሆነም የልብሱን ጫፍ ለመንካት ይለምኑት ነበር፤ የዳሰሱትም ሁሉ ይድኑ ነበር፡፡
ይህስ ጸራቢው የማርያም ልጅ የያቆብም የዮሳም የይሁዳም የስምዖንም ወንድም አይደለምን? እኅቶቹስ በዚህ በእኛ ዘንድ አይደሉምን? አሉ፤ "እርሱ ተራ ጸራቢ ነው! እርሱ እና የእርሱን ቤተሰቦች እናውቃቸዋለን! እናቱ ማሪያምንም እናውቃታለን! ታናናሽ ወንድሞቹን እና ያዕቆን፣ የዩሳም፣ ይሁዳ እና ስምኦን እናውቃቸዋለን! እንዲሁም ታናሽ እህቱ ከእኛ ጋር በዚህ ትኖራለች!"
ነቢይ ከ . . . ይከበራል "ሰዎች በእርግጠኝነት ሰዎች እኔን እንዲሁም ሌሎች ነቢያትን በሌሎች ሥፍራዎች ያከብራሉ ይሁን እንጂ በገዛ ሀገራችን ግን አይደለም! ዘመዶቻችን እና በገዛ ቤታችን ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች እንኳ ሳይቀሩ እኛን አያከብሩንም!"
ሁለት ሁለት "2 በ 2" ወይም "በጥንድ" ሁለት እጀ ጠባቢ አትልበሱ "ተጨማሪ ከነቴራ አትያዙ፡፡"
ለቃችሁ እስኪትሄዱ ድረስ በዚያ ቆዩ "ከተማውን ለቃችሁ እስኪትሄዱ ድረስ በዚያው ቤት ውስጥ ቆዩ፡፡"
መጥመቁ ዮሐንስ ከሞት ተንስቷል "እግዚአብሔር መጥመቁ ዮሐንስን ከሞት አስነስቶታል"
የወንድሙን የፊልጶስን ሚስት "የወንድሙን የፊልጶስን ሚስት"
ትጠላው ነበር "ትቃወመው"
በሣህን "በትሪ"
ስለማለላት እና ለእንግዶቹ ሲል "ቃል ሲገባላት እንግዶቹ ስለሰሙት፣" በሣህን "በትሪ ላይ"
ሁለት መቶ ዲናር "200 ዲናር፡፡" ዲናር የሮማዊያን ከመዳብ የተሠራ የመገበያያ ገንዘብ ነበር፡፡ አምስት እንጀራ እና ሁለት ዓሣዎች "5 እንጀራ እና 2 ዓሣዎች፡፡" .
በመቶ መቶዎች እና በሃምሳ ሃምሳዎች "100 የሚቆጠሩ እና 50 የሚቆጠሩ፡፡" አምስት እንጀራ እና ሁለት ዓሣዎች "5 እንጀራ እና 2 ዓሣዎች፡፡" .
ዐሥራ ሁለት ቅርጫቶች "12 ቅርጫቶች" አምት ሺህ ወንዶች አማራጭ ትርጉም፡ "5,000 ወንዶች እና የእነርሱ ቤተሰቦች"
ቤተሳይዳ ይህ ከገሊላ ባሕር በስተሰሜን በኩል የሚትገኝ ከተማ ናት፡፡
ከሌሊቱ አራተኛው ክፍል ይህ ከንጋቱ 9 ሰዓት እስከ ፀሐይ መውጫ ያለውን ጊዜ ያመለክታል፡፡ በርቱ!...አትፍሩ እነዚህ ሁለት ዓረፍተ ነገሮች ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው፡፡ ጥቅም ላይ የዋሉትም “እኔን አትፍሩ!” የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ ነው”
ይህንን አልተረዱም ነበር "መረዳት የነበራቸው ያኸል እርሱ ምን ያኸል ኃይለኛ እንደነበር አልተገነዘቡም ነበር፡፡"
ቃሬዛ "ሰዎችን ለመሸከም የሚሆን አልጋ"
ቃሬዛ "ሰዎችን ለመሸከም የሚሆን አልጋ"
1 ፈሪሳውያንና ከኢየሩሳሌም የመጡ አንዳንድ ጸሓፍት በአንድ ላይ ተሰብስበው ወደ ኢየሱስ መጡ፡፡ 2 ከደቀመዛሙርቱ አንዳንዶቹ በረከሰ እጅ ማለትም ባልታጠበ እጅ እንጀራ ሲበሉ አዩ፡፡ 3 (ፈሪሳውያንና ሁሉም አይሁድ የአባቶችን ወግ ስለሚጠብቁ እጆቻቸውን ካልታጠቡ በቀር አይበሉም ነበር) 4 ከገበያ ስፍራ ሲመጡ እጃቸውን ካልታጠቡ በቀር አይበሉም ነበር ፤እንዲሁም ዋንጫዎችን፣ ማሰሮዎችንና የናስ እቃዎችን ማጠብን የመሳሰሉ ሌሎች በርካታ ወጎችን ይጠብቁ ነበር፡፡ 5 ፈሪሳውያንና ጸሓፍት "ደቀመዛሙርትህ በአባቶች ወግ መሰረት የማይጓዙት፣ ነገር ግን ባልታጠበ እጅ የሚበሉት ለምንድን ነው?" ብለው ጠየቁት ፡፡ 6 እርሱም እንዲህ ሲል መለሰላቸው፡፡ ኢሳይያስ ስለ እናንተ ስለ ግብዞች በተናገረው ትንቢት፣ ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ብቻ ያከብረኛል፤ ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፤ 7 ሰው ሠራሽ ሥርዐት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል˝ ተብሎ የተጻፈው ትክክል ነው፡፡ 8 እናንተ የእግዚአብሔርን ሕግ ትታችሁ የሰዎችን ወግ ታጠብቃላችሁ፡፡ 9 እንዲህም አላቸው፡፡ ወጋችሁን ለመጠበቅ ስትሉ የእግዚአብሔርን ሕግ ትሽራላችሁ፡፡ 10 ሙሴ፣ «አባትህንና እናትህን አክብር፤ አባቱን ወይም እናቱን የሚሳደብ ሞትን ይሙት» ብሏልና፡፡ 11 እናንተ ግን አንድ ሰው እናቱን ወይም አባቱን፣ «ከእኔ ልታገኙ የሚገባችሁን እርዳታ ቁርባን አድርጌዋለሁ፤ ማለትም ለእግዚአብሔር ሰጥቼዋለሁ» ቢላቸው፣ 12 ከዚህ በኋላ ለአባቱና ለእናቱ ምንም ነገር እንዲያደርግ አትፈቅዱለትም፡፡ ለሌሎች በምታስተላልፉት ወግ የእግዚአብሔርን ቃል ትሽራላችሁ፡፡ 13 ይህን የመሳሰሉ ብዙ ነገሮችንም ታደርጋላችሁ፡፡ 14 ደግሞም ሕዝቡን ወደ እርሱ ጠርቶ እንዲህ አላቸው፣ ሁላችሁም ስሙኝ ፤ አስተውሉም፡፡ 15 ከውጭ ወደ ውስጡ ገብቶ ሰውን የሚያረክስ ምንም ነገር የለም፡፡ 16 ነገር ግን ከውስጡ የሚወጡ ነገሮች እነርሱ ሰውን ያረክሱታል፡፡ 17 ከሕዝቡ ተለይቶ ወደ ቤት እንደ ገባም ደቀመዛሙርቱ ስለ ምሳሌው ጠየቁት፡፡ 18 እርሱም፣ «እናንተም አልተረዳችሁምን? ከውጭ ወደ ውስጡ ገብቶ ሰውን የሚያረክሰው ምንም ነገር እንደሌለ አታስተውሉምን?» አላቸው፡፡ 19 ምክንያቱም ፣ወደ ውስጡ (ዐፉ) የሚገባው ነገር ወደ ሆዱ እንጂ ወደ ልቡ የሚገባ ስላልሆነ ከሰውነቱ የሚወጣ አይደለምን? ይህን በማለቱ ምግብ ሁሉ ንጹሕ መሆኑን ተናገረ፡፡ 20 20እንዲህም አለ፤ ከሰው የሚወጣ ያ ሰውን ያረክሰዋል፡፡ 21 ከውስጥ ከሰው ልብ ክፉ ሐሳብ፣ ዝሙት፣ መስረቅ፣ መግደል፣ 22 ምንዝር፣ ስግብግብነት፣ ክፋት፣ ማታለል፣ መዳራት፣ ምቀኝነት፣ ስም ማጥፋት፣ ትእቢት፣ ስንፍና ይወጣሉ፡፡ 23 እነዚህ ክፉ ነገሮች ሁሉ ከውስጥ ይወጣሉ፡ ሰውንም ያረክሱታል፡፡ 24 ከዚያም ተነሥቶ ወደ ጢሮስና ሲዶና አካባቢ ሄደ፡፡ ያለበትን ማንም እንዳያውቅም ወደ አንድ ቤት ገባ ፤ሆኖም ሊደበቅ አልቻለም፡፡ 25 ወዲያውኑም ስለ እርሱ የሰማችና ትንሽ ልጅዋ በእርኩስ መንፈስ የተያዘችባት አንዲት ሴት ወደ እርሱ መጥታ በእግሩ ሥር ተደፋች፡፡ 26 ሴቲቱ ዝርያዋ ከሲሮፊኒቃዊት ወገን የሆነ ግሪካዊት ነበረች፡፡ እርስዋም ኢየሱስ በልጅዋ ውስጥ ያለውን ጋኔን እንዲያወጣላት ለመነቸው፡፡ 27 እርሱም «በመጀመሪያ ልጆች ይጥገቡ፤ የልጆችን እንጀራ ወስዶ ለውሾች መስጠት ተገቢ አይደለምና» አላት፡፡ 28 እርስዋ ግን «አዎን ጌታ ሆይ፤ ውሾችም እኮ ከገበታ ሥር የሚወዳድቀውን የልጆችን ፍርፋሪ ይበላሉ፡፡» ብላ መለሰችለት፡፡ 29 ኢየሱስም ፣ እንዲህ በማለትሽ ወደ ቤትሽ ሂጂ ጋኔኑ ከልጅሽ ወጥቷል አላት፡፡ 30 ወደ ቤትዋም ሄደች፤ልጅዋም አጋንንቱ ለቅቋት ዐልጋው ላይ ተኝታ አገኘቻት፡፡ 31 ደግሞም ከጢሮስ አካባቢ ተነሥቶ በሲዶና በኩል አድርጎ በዐሥሩ ከተሞች ዐልፎ ወደ ገሊላ ባሕር መጣ፡፡ 32 እጁን እንዲጭንበትና እንዲፈውሰው አንድ መስማት የተሳነውና ኮልታፋ ሰው ወደ እርሱ አመጡ፡፡ 33 እርሱም ከሕዝቡ ለይቶ ወደ ገለልተኛ ስፍራ ወሰደው፤ጣቶቹን በጆሮዎቹ ውስጥ አስገብቶ እንትፍ አለበት፤ምላሱንም ነካው፡፡ 34 ወደ ሰማይ ቀና ብሎ ተመለከተና በረጅሙ ተንፍሶ «ኤፍታህ» አለው፡፡ ይህም ተከፈት ማለት ነው፡፡ 35 ጆሮዎቹ ተከፈቱ፤ የታሰረውም ምላሱ ተፈታ፡፡ ጥርት አድርጎም ተናገረ፡፡ 36 ኢየሱስም ይህን ለማንም እንዳይናገሩ አዘዛቸው፤ ሆኖም አጥብቆ ባዘዛቸው መጠን አብልጠው አሰራጩት ፡፡ 37 እነርሱም ከልክ በላይ ተደንቀው ፣ ሁሉንም ነገር ደኅና አድርጓል፤እርሱ መስማት የተሣነው እንዲሰማ ኮልታፋውም እንኳ እንዲናገር ያደርጋል አሉ፡፡
የናስ ዕቃዎች፣ እና የመመገቢያ ፍረሽን እንኳ ሳይቀር በዚያ ዘመን ይኖሩ የነበሩ አይሁዳዊያን ምግብ የሚመገቡት በፍራሽ ላይ ተቀምጠው ነበር፡፡ አማራጭ ትርጉሞች፡ “መያዥያዎች እንዲሁም የመመገቢያ መቀመጫዎች”
ደቀ መዛሙርትህ ለምን እንደ ሽማግሌዎች ወግ አይኖሩም፣ ስለምንስ እጃቸውን ሳይታጠቡ ይበላሉ? "የአንተ ደቀ መዛሙርት የሽማግሌዎችን ወግ ይተላለፋሉ! የእኛን ሥርዓት በመጠቀም እጆቻቸውን መታጠብ አለባቸው!" ዳቦ ምግብ
ስለእናንተ ግብዝነት ኢሳያስ በደንብ ትንቢትን ተናግሯል፡ እንዲህ ብሎም ጽፈዋል፡ ከዚህ ቀጥሎ ያሉት ቃላት ኢሳያስ ከተናገራቸው የተወሰዱ ናቸው ISA 29:13-14፡፡
ማጥበቅ ጠንከር አድርጎ ክፋትን የሚናገሩ "የሚረግሙ"
ከእኔ ታገኝ የነበረው እርዳታ ሁሉ ቁርባን ነው ለቤተ መቅዱስ ቃል የተገባ ማንኛውም ገንዝብ ወይም ሌሎች ማንኛውም ነገሮች ለሌላ ዓላማ መዋል እንደሌለባቸው የጸሐፍት ትውፍት ይናገራል፡፡ ቁርባን ጸሐፍው በዚህ ቃል አማካኝነት ማስተላለፍ የፈለገው ነገር የዚህ ቃል ንባብ ከሚሰጠው ድምጽ ጋር ተያያዥነት ስላለው በተቸለ መጠን በቋንቋችሁ ከዚህ ቃል ጋር ተቀራረቢ ድምጽ ያለውን ቃል ተጠቀሙ፡፡
ሁላችሁም አድምጡኝ እንዲሁም የሚናገረውን ነገር ተረዱ በዚህ ክፍል ውስጥ “ማድመጥ” እና “መረዳት” የሚሉት ሁለት ቃላት እርስ በእርሳቸው የተገናኙ ናቸው፡፡ ኢየሱስ እነዚህ ቃላት በአንድነት በንግግሩ ውስጥ የተጠቀመበት ምክንያት አድመወጮቹ እርሱ እየተናገረ ላለው ነገር ትኩረት ይሰጤ ዘንድ ነው፡፡ ከሰው የሚወጣው ያ ነው "የሰው ውስጡ ነው” ወይም “ሰው የሚያስበው ወይም የሚያደርገው ያ ነው"
እናንተ ደግሞ እንደዚህ የማታስተውሉ ናችሁን? አማራጭ ትርጉም: "ይህንን ሁሉ ከተናገርኩ እና ካደረኩ በኋላ በትክክል ትገነዘባላቸሁ ብዬ አስቤ ነበር፡፡"
በፊቱ ወደቀ "ተንበረከከ" ትውልድዋም ሲሮፊኒቃዊት በሦሪያ ሀገር ውስጥ በሚትገኝ ፊኒቃ በተባለች ከተማ ውስጥ ነው የተወለደችው፡፡
ልጆቹ በፊት ይጠግቡ "ልጆች መጀመሪያ መብላት ይኖርባቸዋል" ወይም "በመጀመሪያ ልጆች መመገብ ይገባቸዋል፡፡" ልጆች አይሁዳዊያን፡፡ አማራጭ ትርጉሞች፡ "በመጀመሪያ አይሁዶችን ማገልገል ይገባኛል፡፡" ዳቦ ምግብ ውሾች አሕዛብ፡፡ በጠረጴዛ ሥር ያሉት ውሾች እንኳ ከልጆች እጅ የወዳደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ፡፡ "እኔን ከአሕዛብ ወገን የሆንኩትንም በተመሳሳይ መንገድ ልታገለግለኝ ትችላለህ፡፡" ፍርፋሪዎች የዳቦ ፍርፋሪዎች
አልፎ መጣ "በውስጡ አልፎ ሄደ" ዐሥር ከተሞች "ዐሥሩ ከተሞች፣" ከገሊላ ሀይቅ በደቡብ ምስራቅ በኩል የሚገኝ አከባቢ፡፡ ደንቆሮ "መስማት የማይችል ሰው" መናገር የማይችል፣ አንደበተ ኰልታፋ "ግልጽ በሆነ መንገድ መናገር የማይችል"
ኤፍታህ ጸሐፊው አይህ ቃል ሲነበብ የሚያስማውን ድምጽ አንባቢያኑ እንዲሰሙት ስለሚፈለግ በተቻለ መጠን በቋንቋቹ ፍደላት አማካኝነት ይህንን ቃል ለመጻፍ ጥረት አድርጉ፡፡ ቃተተ ደስተኛ አለመሆኑን ለማሳየት ወደ ውስጥ ሳብ አድርጎ ወደ ውጪ ተነፈሰ ምላሱን ያሠረው ነገር ተፈታ "ምላሱን ያሠረው ነገርን ኢየሱስ አስለቀቀው" ወይም "ግልጽ በሆነ መንገድ እንዳይናገር ካደረገው ነገር ኢየሱስ ፈወሰው"
1 በእነዚያ ቀናት እንደገና ብዙ ህዝብ በተሰበሰበና የሚበሉት ባጡ ጊዜ 2 ኢየሱስም ደቀመዛሙርቱን ወደእርሱ ጠርቶ ህዝቡ ከኔ ጋር ሶስት ቀናት ቆይተዋል የሚበሉትም የላቸውምና እራራላቸዋለሁ 3 ሳይበሉ ብሰዳቸውም በመንገድ ላይ ይደክማሉ አንዳንዶቹም ከሩቅ ሥፍራ ነው የመጡት አላቸው፡፡ 4 ደቀመዛሙርቱም በዚህ ምድረበዳ እነዚህን ሁሉ የሚያጠግብ እንጀራ እንዴት ይገኛል ብለው መለሱለት፡፡ 5 ስንት እንጀራ አላችሁ ብሎ ጠየቃቸው፡፡ ሰባት አሉት ፤ 6 ህዘቡን በምድር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ ሰባቱንም እንጀራ ተቀብሎ እግዚአብሔርን ካመሰገነ በኋላ ቆርሶ እንዲያቀርቡላቸው ለደቀመዛሙርቱ ሰጣቸው እነርሱም ለህዝቡ አቀረቡላቸው፡፤ 7 ጥቂትም ትናንሽ አሦች ነበሯቸው ባርኮም ያንንም አንዲያቀርቡላቸው አዘዘ፡፡ 8 ሕዝቡም በልተውም ጠገቡ፡ ደቀመዛሙርቱም የተረፈውን ቁርስራሽ ሰባት ታላላቅ መሶብ አነሱ፡፡ 9 የህዝቡም ቁጥር ቁጥራቸውም አራት ሺ ያህል ነበር፡፡ ከዚያም ኢየሱስ ህዝቡን አሰናበታቸው ፡፡ 10 ወዲያውም ከደቀመዛሙርቱ ጋር ወደ ጀልባ ገብተው ወደ ዳልማኑታ አውራጃ አካባቢ ሄዱ፡፡ 11 ፈሪሳውያንም ወደ ኢየሱስ እርሱ መጥተው ከእግዚአብሔር ዘንድ የሆነ ምልክትን እንዲያሳያቸው በመፈለግ ሊፈትኑት ይጠይቁት ጀምር፡፡ 12 ኢየሱስም እርሱም በመንፈሱ እጅግ ተበሳጭቶ በዚህ ዘመን ያለ ህዝብ ለምን ምልክት ይፈልጋል እዉነት እላችኋለሁ እናንተ ሰዎች አይሰጣችሁም አላቸው፡፡ 13 ትቶአቸው እንደገና ወደ ጀልባ ገብቶ ወደ ባህሩ ማዶ ተሻገረ፡፡ 14 ደቀመዛሙርቱም እንጀራ መያዝን ረሱ፡፡ 15 በጀልባ ውስጥም ከአንድ እንጀራ በቀር ምንም አልያዙም ነበር። 16 ኢየሱስ ከፈሪሳዊያንና ከንጉሥ ሄሮድስ እርሾ ተጠንቀቁ ብሎ አሳሰባቸው፡፡ እንጀራ ስላልያዝን ነው ብለው እርስ በእርሳቸው ተነጋገሩ ፡፡ 17 ኢየሱስም ይህን አውቆ እንጀራ ስለሌላችሁ ለምን ትነጋገራላችሁ፡፡ እስከአሁን አልገባችሁምን ወይም እስከአሁን አታስተውሉምን ልባችሁ ደንዝዞአልን 18 አይን እያላችሁ አታዩምን ጆሮ እያላችሁ አትሰሙምን አታስታውሱምን 19 አምስቱን እንጀራ ለአምስት ሺ ባካፈልኩ ጊዜ ስንት መሶብ ቁርስራሽ ሰበሰባችሁ ብሎ ጠየቃቸው እነርሱም አሥራ ሁለት ብለው መለሱለት፡፡ 20 ሰባቱን ለአራት ሺ ባካፈልኩ ጊዜስ ስንት ቅርጫት ቁርስራሽ አነሳችሁ አላቸው ሰባት አሉት ፡፡ 21 ገና አታስተውሉምን አላቸው፡፡ 22 ወደ ቤተ ሳይዳም መጡ፡፡ የአካባቢው ሰዎችም አይነ ስውር የሆነን ሰው ወደ እርሱ አምጥተው እንዲዳስሰው ለመኑት፡፡ 23 የአይነስውሩንም ሰው እጅ ይዞ ከመንደሩ ውጭ ወሰደው፡፡ በአይኖቹም ላይ እንትፍ ብሎና እጁን ጭኖ አሁን ይታይሀልን ብሎ ጠየቀው፡፡ 24 ቀና ብሎ ተመለከተና ሰዎች ሲራመዱ እንደዛፍ ሆነው ይታየኛል አለው፡፡ 25 እንደገናም እጁን በአይኑ ላይ በጫነበት ጊዜ በሚገባ ተመለከተ የአይኑም ብርሀን ተመለሰለት ሁሉንም ነገር አጥርቶ አየ፡፡ 26 ኢየሱስም ወደ መንደሩ እንኳ እንዳትገባ ብሎ ወደ ቤቱ አሰናበተው፡፡ 27 ኢየሱስም ከደቀመዛሙርቱ ጋር ወደ ፊሊጶስፕ ቂሳሪያ ዙሪያ ወዳሉ መንደርሮች ሄዱ፡ በመንገድም ላይ ሳሉ ሰዎች እኔን ማነው ይላሉ ብሎ ጠየቃቸው 28 እነርሱም መጥምቁ ዮሐንስ ሌሎች ደግሞ ኤልያስ አንዳንች ግን ከነቢያት አንዱ ብለው መለሱለት፡፡ 29 እንደገናም እናንተስ እኔ ማን እንደሆንኩ ትላለችሁ ብሎ ጠየቃቸው፡፡ ጴጥሮስም አንተ መሲሁ ነህ በማለት መለሰለት፡፡ 30 ስለእርሱ ለማንም እንዳይናገሩ አስጠነቀቃቸው፡፡ 31 የሰው ልጅ ብዙ መከራ እንደሚቀበል በሽማግሌዎች፣ በካህናት አለቆችና በጻፎች እንደሚነቀፍና እንደሚገደል በሦስተኛውም ቀን እንደገና እንደሚነሳ እንዳለው ያስተምራቸው ጀመር፡፡ 32 ይህንንም በግልጽ ተናገረ፡፡ ጴጥሮስም ወስዶ ሊገስጸው ጀመረ፡፡ 33 ኢየሱስም ዞር ብሎ ደቀመዛሙርቱን አየና ወደ ኋላዬ ሂድ አንተ ሰይጣን የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን ነገር አታስብምና ብሎ ጴጥሮስን ገሰጸው፡፡ 34 ህዘቡንና ደቀመዛሙርቱንም ወደ እርሱ ጠርቶ ሊከተለኝ የሚወድ ማንም ቢኖር ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ፡፡ 35 ህይወቱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠጣፋታልና ነፍሱን ግን ስለኔ ወይም ስለወንጌል የሚያጣ ያገኛታልና፡፡ 36 ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ቢያጣ ምን ይጠቅመዋል፡፡ 37 ወይስ ሰው ስለነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል፡፡ 38 በዚህ አመንዝራ ኃጢአተኛ ህዝብ ፊት በእኔና በቃሌ የሚያፍርብኝ ማንም ቢኖር የሰው ልጅም ከቅዱሳን መላዕክቱ ጋር በአባቱ ክብር በሚመጣበት ጊዜ ያፍርበታል፡፡
ሦስት ቀናት "3 ቀናት" ራሳቸውን ሊስቱ ይችላሉ አማራጭ ትርጉሞች፡ 1) "ለአጭር ጊዜ ራሳቸውን ሊስቱ ይችላሉ" ወይም 2) "ደካማ ሊሆኑ ይችላሉ" እነዚህን ሁሉ ሰዎች መመገብ የሚችል በቂ ምግብ ከዬት ማግኘት ይቻላል? ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስ ይህንን ሁሉ ሰው መመገብ የሚያችል ምግብ እንዲፈልጉ መጠየቁ በጣም አስገርሟቸዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ያሉበት ቦት በቂ ለዚህ ሁሉ ሕዝብ የሚሆን ምግብ የማይቻልበት ሥፍራ አይደለም!"
ተቀመጡ ሰዎች ምግብ ለመመገብ ጠረጴዛ በማይኖርበት ሥፍራ ላይ ሰዎች ምግብ የሚመገቡበትን መንገድ የሚትገልጽበትን መንገድ የሚገልጽ ቃልን ተጠቀም፡፡
ዳልማኑታ ከገሊላ ባሕር በሰሜን ምዕራብ በኩሉ የሚገኝ አከባቢ ነው፡፡
ፈለጉት "ለማግኘት ጥረት አደረጉ" በጥብቅ ይህንን በ MRK 7:34 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ይህ ትውልድ ለምን ምልክትን ይሻል በዚህ ሥፍራ ኢየሱስ ኢየገሰጻቸው ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ይህ ትውልድ ምልክትን መሻት አልነበረበተም፡፡” ይህ ትውልድ ይህንን ያደርጋል "ሁላችሁም ይህንን ታደርጋላችሁ"
ተጠንቀቁ እንዲሁ ራሳችሁን ጠብቁ በዚህ ሥፍራ ጥቅም ላይ የዋሉት እነዚህ ሁለት ቃላት የጋራ ፍች ሲኖራው ሁለቱም ጥቅም ላይ የዋሉበት ምክንያት አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ ከፈርሳዊያን እና ከሄሮዶስ ወገን እርሾ አማራጭ ትርጉም፡ "ከፈርሳዊያን የሐሰት ትምህርት እና ከሄሮዶስ ወገን የሐሰት ትምህርት"
እንጀራ ስለሌለ ስለምን በመካከላችሁ ትከራከራላችሁ? ኢየሱስ እርሱ እየነገራቸው እና እያደረገ ያለውን ነገር መረዳት ባለመቻላቸው ተስፋ ቆረጠ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እኔ እየተናገርኩ ያለሁት ስለ ግዑዝ እንጀራ ነው ብላችሁ ማሰብ የለባችሁም፡፡"
ዓይን ሳላችሁ አታዩምን? ጆሮስ ሳላችሁ አትሰሙምን? ትዝስ አይላችሁምን? ኢየሱስ ምንም ልገነዘቡ ባለመቻላቸው ተስፋ ቆርጦዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “የሚያይ ዐይን አላችሁ ይሁን እንጂ የሚትመለከቱትን ነገር አትረዱም! የሚሰማ ጆሮ አላችሁ ይሁን እንጂ የሚትሰሙትን ነገር አትረዱም! እነዚህ ሁሉ ልታስታውሱ ይገባ ነበር!"
ትስዝ አይላችሁምን? አማራጭ ትርጉም፡ "ስለቁሳዊ እንጀራ እያወራሁ እንዳልሆነ በዚህ ጊዜ መገንዘብ ነበረባችሁ፡፡"
ቤተ ሳይዳ ከዮርዳኖስ ወንዝ በስተምስራቅ የሚትገኝ ከተማ
የሰው ልጅ ብዙ መከራ ሊቀበል፥ ከሽማግሌዎችም ከካህናት አለቆችም ከጻፎችም ሊጣል፥ ሊገደልም ወደ ሕይወት ሊነሣ እንዲገባው አማራጭ ትርጉም: "ሽማግሌች እና የካህናት አለቆች እንዲሁም ጻፎችም የሰው ልጅነን አይቀበሉመም እንዲሁም ይገድሉታል፡፡ ይሁን እነንጂ እግዚአብሔር ወደ ሕይወት መልሶ ያመጣዋል፡፡" ሦስት ቀናት "3 ቀናት"
ስለዚህ ኢየሱስ የመሞታቸው ምክንያት ወንጀለኞች ስለሆኑ እንዳልሆነ እና በምንም ምክንያት እንደሆነ ለደቀ መዛሙርቱ ይህንን እንዲያስታውሱ ይነግራቸዋ፡፡(MRK 8:34).
የሰው ልጅ ... በአባቱ ክብር ከቅዱሳን መላእክት ጋር በመጣ ጊዜ የሰው ልጅ እንዲሁም የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ኢየሱስ አባቱ ባለው ክብር እርሱም ተመልሶ ይመጣል፡፡ የሰው ልጅ ይህ የኢየሱስ ወሳኝ የሆነ የማዕረግ ስም ነው፡፡
1 ኢየሱስም እውነት እላችኋለሁ፣ በዚህ ከቆሙት አንዳንዶቹ የእግዚአብሔር መንግሥት በኃይል መምጣቷን ሳያዩ የማይሞቱ አሉ አላቸው፡፡ 2 ከስድስት ቀን በኋላም ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ለብቻቸው ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ላይ አመጣቸው፡፡ 3 በፊታቸውም ተለወጠባቸው፤ ልብሱም አጣቢ በምድር ላይ ሊያነጻው እስከማይችል ድረስ ተብለጭልጮ ነጭ ሆነ፡፡ 4 ሙሴና ኤልያስ ታዩአቸው፤ ከኢየሱስ ጋርም ይነጋገሩ ነበር፡፡ 5 ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን ረቡኒ! በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ አንድ ለአንተ፣ አንድ ለሙሴና አንድ ለኤልያስ ሦስት ዳሶችን እንሥራ አለው፡፡ 6 እጅግ ፈርተው ስለነበረ የሚመልሰውን አያውቅም ነበር፡፡ 7 ከዚያም ደመና መጥቶ ጋረዳቸው፤ ከደመናውም ውስጥ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፣ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ፡፡ 8 ድንገት ዙሪያቸውን ሲመለከቱ ከኢየሱስ በቀር ከእነርሱ ጋር ሌላ ማንንም አላዩም፡፡ 9 ከተራራው ሲወርዱ ሳሉም ይህንን ያዩትን ነገር ሁሉ የሰው ልጅ ከሙታን እስኪነሳ ድረስ ለማንም እንዳይናገሩ አዘዛቸው፡፡ 10 እነርሱም ቃሉን ይዘው ከሙታን መነሳት ማለት ምን ማለት ነው ተባባሉ፡፡ 11 እነርሱም ጸሐፍት አስቀድሞ ኤልያስ መምጣት አለበት የሚሉት ለምንድነው ብለው ጠየቁት፡፡ 12 ኢየሱስም ኤልያስማ በርግጥ አስቀድሞ ይመጣል፤ ሁሉንም ነገር ያስተካክላል፡፡ ስለ ሰው ልጅ ብዙ መከራ እንዲቀበልና እንዲጣል የተጻፈው ታዲያ እንዴት ይሆናል? 13 እኔ ግን እላችኋለሁ! ኤልያስ መጥቷል፤ ስለ እርሱም አንደተጻፈው የወደዱትን አደረጉበት፡፡ 14 ወደ ደቀመዛሙርቱ በመጡ ጊዜ ብዙ ሕዝብ ከበዋቸው ጸሓፍትም ሲጠይቋቸው ተመለከቱ፡፡ 15 ወዲያው ሕዝቡ ሁሉ ኢየሱስን ባዩት ጊዜ እጅግ ተገርመው ወደ እርሱ በመሮጥ ሰላምታ ሰጡት፡፡ 16 እርሱም ስለምንድነው የምትጠይቋቸው? ብሎ ጠየቃቸው፡፡ 17 ከሕዝቡም መሐል አንዱ መምህር ሆይ! ዲዳ መንፈስ ያደረበትን ልጄን ወዳንተ አመጣሁት፡፡ 18 በሚወስደው ቦታ ሁሉ ይጥለውና አረፋ ያስደፍቀዋል፣ ጥርሱን ያንቀጫቅጭና ያደርቀዋል፡፡ እንዲያወጡት ደቀመዛሙርትህን ጠየቅኳቸው፣ እነርሱም አልቻሉም፡፡ 19 ኢየሱስም መልሶ እናንተ የማታምኑ ትውልዶች እስከ መቼ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ? እስከ መቼስ እታገሳችኋለሁ? ወደ እኔ አምጡት አላቸው፡፡ 20 ወደ እርሱም አመጡለት፤ ባየውም ጊዜ ወዲያው መንፈሱ በምድር ላይ በኃይል ጥሎ እያንፈራገጠ አረፋ አስደፈቀው፡፡ 21 ኢየሱስም የልጁን አባት ይህ ከያዘው ምን ያህል ጊዜ ሆነው? ሲል ጠየቀው፡፡ እርሱም ከሕጻንነቱ ጀምሮ ነው፡፡ 22 ብዙ ጊዜ ሊያጠፋው በውሃና በእሳት ላይ ይጥለዋል፤ የሚቻልህ ከሆነ እዘንልንና እርዳን አለው፡፡ 23 ኢየሱስም የሚቻልህ ከሆነ አልክን ለሚያምን ሁሉም ነገር ይቻላል አለው፡፡ 24 ወዲያው የልጁ አባት ጮኸና አምናለሁ፣ እንዳምንም እርዳኝ አለው፡፡ 25 ኢየሱስ ሕዝቡ እየሮጠ ሲመጣ ተመልክቶ እርኩሱን መንፈስ አንተ ዲዳ ደንቆሮም መንፈስ ከእርሱ እንድትወጣ ተመልሰህም እንዳትገባበት አዝሃለሁ ብሎ ገሰጸው፡፡ 26 መንፈሱም ካንፈራገጠው በኋላ ጮኾ ወጣ፡፡ ብዙዎች ሞተ እስኪሉ ድረስም እንደ ሞተ ሰው ሆነ፡፡ 27 ኢየሱስ ግን እጁን ይዞ አስነሳው፤ እርሱም ተነሣ፡፡ 28 ወደ ቤት በገቡ ጊዜም ደቀመዛሙርቱ እኛ ልናስወጣው ያልቻልነው ለምንድነው? ብለው ለብቻው ጠየቁት፡፡ 29 ኢየሱስም እንዲህ ዓይነቱ ወገን በጸሎት ካልሆነ በስተቀር አይወጣም አላቸው፡፡ 30 ከዚያም ወጥተው በገሊላ በኩል አለፉ፤ በዚያ መሆኑን ማንም እንዲያውቅ አይፈልግም ነበር፡፡ 31 ደቀመዛሙርቱንም እንዲህ ሲል አስተማራቸው፤ የሰው ልጅ በሰዎች እጅ ታልፎ ይሰጣል፣ ይገድሉታልም፣ ከተገደለ ከሶስት ቀን በኋላም ይነሣል አላቸው፡፡ 32 ነገር ግን የተናገራቸውን አላስተዋሉም፤ እንዳይጠይቁትም ፈርተው ነበር፡፡ 33 ወደ ቅፍርናሆም መጡ፤ በቤት ሳሉም መንገድ ላይ ስለምን ጉዳይ ነበር የምትነጋገሩት ብሎ ደቀመዛሙርቱን ጠየቃቸው፡፡ 34 ከእነርሱ ማን ይበልጥ እንደሆነ ተከራክረው ነበርና ዝም አሉ፡፡ 35 ተቀምጦም አሥራ ሁለቱን ጠራቸው፣ እንዲህም አላቸው፣ ከእናንተ የመጀመሪያ ሊሆን የሚወድ የሁሉ መጨረሻና አገልጋይ ይሁን፤ 36 ትንሽ ልጅ በመካከላቸው አቁሞና አቅፎት እንዲህ አላቸው፤ 37 ማንም እንደዚህ ካሉት ታናናሽ ልጆች አንዱን በስሜ የሚቀበል እኔን ይቀበላል፣ እኔንም የሚቀበል የሚቀበለው የላከኝን ነው እንጂ እኔን አይደለም፡፡ 38 ዮሐንስም መምህር ሆይ! አንድ ሰው በስምህ አጋንንትን ሲያስወጣ አየነው፤ ስለማይከተለንም ከለከልነው አለው፡፡ 39 ኢየሱስ ግን በስሜ ተአምራትን አድርጎ ፈጥኖ በእኔ ላይ ክፉ ሊናገር የሚችል የለምና አትከልክሉት፤ 40 የማይቃወመን ሁሉ ከእኛ ጋር ነው አለው፡፡ 41 እውነት እላችኋለሁ የክርስቶስ በመሆናችሁ ምክንያት አንድ ብርጭቆ ውሃ እንድትጠጡ የሚሰጣችሁ ዋጋውን አያጣም፡፡ 42 በእኔ ከሚያምኑ ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን ከእምነቱ የሚያስት ሰው ትልቅ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ላይ ታሥሮ በጥልቅ ባህር ላይ ቢጣል ይሻለው ነበር፡፡ 43 እጅህ ለመሰናከልህ ምክንያት የምትሆን ከሆነ ቆርጠህ ጣላት፤ ሁለት እጅ ኖሮህ እሳቱ ወደማይጠፋበት ወደ ሲዖል ከምትሔድ አካልህ ጎሎ ወደ ሕይወት ብትገባ ይሻልሃልና፡፡ 4445 እግርህ ለመሰናከልህ ምክንያት የሚሆን ከሆነ ቆርጠህ ጣለው፤ ሁለት እግር ኖሮህ ወደ ሲዖል ወደ እሳቱ ከምትጣል አንድ እግር ኖሮህ ወደ ሕይወት ብትገባ ይሻልሃል፡፡ 4647 ዐይንህ ለመሰናከልህ ምክንያት የምትሆን ከሆነ አውጥተህ ጣላት፤ 48 ሁለት ዐይን ኖሮህ ትሉ ወደማይሞትበት፣ እሳቱ ወደማይጠፋበት ከምትገባ አንድ ዐይና ሆነህ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ብትገባ ይሻልሃል፡፡ 49 እያንዳንዱ ሰው በእሳት ይቀመማል፡፡ 50 ጨው መልካም ነው፤ የጨውነት ጣዕሙን ቢያጣ ግን ምን ታደርጉታላችሁ? በእያንዳንዳችሁ ሕይወት የጨውነት ጣዕም ይኑርባችሁ! እርስ በርሳችሁም በሰላም ኑሩ፡፡
ተለወጠ "ወደ ሌላ ቅርጽ ተለወጠ" ወይም "የበለጠ የተለመ ሆኖ ታያቸው" (UDB) እንደ ብርሃን አንጸባራቂ "በጣም ነጭ" አጣቢም በምድር ላይ እንደዚያ ሊያነጣው "ማንጽያ" የሚባለው ከልብስ ላይ ቆሻሻን ለማንጻት እና ነጭ ለማድረግ የሚያገለግል ኬሚካል ነው፡፡ “የሚያነጻ” ቆሻሻን የሚያነጻ ሰው፡፡
ፈሩ "በጣም ፈሩ"
ማርቆስ 9፡ 7-8
ይህ የሚወደው ልጄ ነው፡፡ እርሱን ስሙት፡፡ እግዚአብሔር “ስለሚወደው ልጁ”፣ የእግዚአብሔር ልጅ ስለሆነው ስለ ልጁ ያለውን ፍቅር የገለጸበት መንገድ ነው፡፡ የሚወደው ልጄ ይህ የእግዚአብሔር ልጅ የሚለው የኢየሱስ ወሳኝ የሆነ የማዕረግ ስም ነው፡፡
ስለዚህም ይህንን ነገር በልባቸው ይጠበቅት ነበር "ይህ ነገር ሲሆን ላልተመለከተ ለማንም ሰው ሳይናገሩ፣ ስለዚህ ነገር ከማንም ጋር አይነጋገሩም ነበር፡፡" ከሞት መነሳት "ከሞተ በኋላ ተመልሶ እንደገና በሕይወት መኖር"
ኤልያስማ ይህንን በእርግጥ አድርጓል . . . ሰዎችም ጠልተውታል? ኤልያስ ከሰማይ እንደሚመጣ፣ ከዚያም መስሑ የሆነው የሰው ልጅ መጥቶ ይነግሣል እንዲሁም ይገዛል ተብሎ አስቀድሞ ትንቢት ተነግሯል፡፡ ሌሎች ትንቢታዊ መልዕክቶችም የሰው ልጅ መከራን እንዲቀበል እና በሰዎች እንዲጠላ የትንቢት መልዕክት ተናግረዋል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ እነዚህ ሁለት ትንቢታዊ መልዕክቶች እንዴት አንድ ሊሆኑ እንደሚችሉ አልገባቸው ስለዚህም ግራ ገብቷቸዋል፡፡ ኤልያስ ይመጣል በትንቢት መልዕክቶች ብዙ ጊዜ ሁለትዮሽ ፍጻሜ አላቸው፡፡
ስከራከሩ "ስወያዩ" ወይም "ስጨቃጨቁ" ወይም "ስጠያየቁ"
ከእርሱ ውስጥ ለማውጣት "ከልጄ ውስጥ ለማስወጣት" ወይም "እርኩስ መንፈሱን ለመማባረር" እታገሳችኋለሁ "እችላችኋለሁ" ወይም "አልፋችኋለሁ"
አዘነላቸው "አሳዘኑት" ወይም "ራራላቸው"
ኢየሱስም እንዲህ አለው፣ “ቢቻልህስ”? ለሚያምን ሁሉ ይቻለዋል”፡፡ ኢየሱስ የሰውዬውን ጥርጣሬ ገሰጸው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ኢየሱስ ሰውዬውን እንዲህ አለው፣ “ስለምን ከቻልክ ትላለህ”? ለምያምንስ ሁሉ ይቻለዋል፡፡” ወይም "ኢየሱስ ሰውዬውን እንዲህ አለው፣ “ከቻልክስ” ማለት የለብህም!” ለምያምንስ ሁሉ ይቻለዋል፡፡”
ልጁ የሞተ ይመስል ነበር "ልጁ የሞተ ይመስል ነበር" ወይም "ልጁ የሞተ ሰው ይመስል ነበር"
እንዲህ ዓይነቱን በጸሎት ካልሆነ ማስወጣት አይቻልም ቃ“አይቻልም” እና “ካልሆነ በስተቀር” የሚሉት ቃላት ሁለቱም አሉታዊ ቃላት ናቸው፡፡ በአንዳንድ ቋንቋዎች ውስጥ አዎንታዊ ቃላትን መጠቀሙ አግባብ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “እንዲህ ዓይነቱን ማስወጣት የሚቻው በጸሎት ብቻ ነው፡፡”
በዚያ አልፎ ሄደ "በዚያ አለፈ" ወይም "በዚያ አለፈ" ሦስት ቀናት "3 ቀናት"
እርኩስ መናፈስትን ማስወጣት "ዳቢሎስን ማስወጣት"
እንዳይጠፋ "እንዳይጠፋ" የሚለው ቃል አሉታዊ ነው፡፡ በአንዳንድ ቋንቋዎች ውስጥ አዎናታዊ ዓረፍተ ነገሮችን መጠቀም የተለመደ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ይቀበላል" (ተመልከት:
የወፍጮ ድንጋይ እህል ለመፍጨት የሚያገለግል ትልቅ ድንጋይ የማይጠፋ እሳት "የማጥፋ እሳት"
እንዲሁም ወደ ሲኦል ይወረወራል "እንዲሁም እግዚአብሔር ወደ ሲኦል ይወረውረዋል"
ትላቸው "የሞተውን አካላቸውን የሚበላ ትል"
1 ኢየሱስም ከዚያ ተነስቶ ከዮርዳኖስ ወንዝ ማዶ ወደ ይሁዳ አውራጃዎች መጣ፡፡ ብዙ ህዝብም በአንድ ላይ ሆነው እንደገና ወደ እርሱ መጡ፡፡ እንደልማዱም ያስተምራቸው ጀመር፡፡ 2 ፊሪሳውያንም ወደ ኢየሱስ መጥተው ሊፈትኑት አንድ ሰው ሚስቱን መፍታት ተፈቅዶለታል ሲሉ ጠየቁት፡፡ 3 እርሱም መልሶ ሙሴ ምን ብሎ አዘዛችሁ አላቸው፡፡ 4 እነርሱም የፍቺውን ጽፈት ሰጥቶ ይፍታት ብሎ ደንግጓል አሉት፡፡ 5 ኢየሱስ ግን ሙሴ ስለልባችሁ ድንዛዜ ይህን ትዕዛዝ ሰጣችሁ እንጂ 6 ከፍጥረት መጀመሪያ ግን እግዚአብሔር ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው፡፡ 7 በዚህም ምክንያት ሰው እናቱንና አባቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይጣበቃል 8 ሁለቱም አንድ ስጋ ይሆናሉ ስለዚህም አንድ ሥጋ እንጂ ከእንግዲህ ሁለት አይደሉም 9 እንግዲህ እግዚአብሔር ያጣመረውን ሰው አይለየው አላቸው፡፡ 10 በቤትም ሳሉ ደቀመዛሙርቱ ስለጉዳዩ እንደገና ጠየቁት፡፡ 11 ኢየሱስም ማንም ሚስቱን ፈቶ ሌላይቱን ቢያገባ በሚስቱ ላይ ያመነዝራል፡፡ 12 እንዲሁም እርሷም ራሷ ባሉዋን ትታ ሌላ ሰው ካገባች ታመነዝራለች አላቸው ፡፡ 13 ህዝቡም እንዲዳስሳቸው ህጻናትን ወደ ኢየሱስ ያመጡ ነበር፡፡ ደቀመዛሙርትም ገሰጹዋቸው፡፡ 14 ኢየሱስ ግን ባየ ጊዜ በቁጣ ተሞልቶ ህጻናትን ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ ተው አትከልክሏቸው፡፡ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደነዚህ ላሉት ናትና አላቸው፡፡ 15 እውነት እላችኋለሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት እንደ ህጻን ሆኖ የማይቀበላት ሊገባባት አይችልም፡፡ 16 ህጻናቱንም አቅፎ እጁን ጭኖ ባረካቸው፡፡ 17 በመንገድም ሳሉ አንድ ሰው ወደእርሱ ሮጠና በፊቱ ተንበርክኮ ቸር መመህር ሆይ የዘላለምን ህይወት እንድወርስ ምን ማድረግ ይገባኛል? ብሎ ጠየቀው ፡፡ 18 ኢየሱስም ለምን ቸር ትለኛለህ ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር የለም አለው፡፡ 19 ትዕዘዛትን ታወቃለህ አትግደል አትስረቅ አታመንዘር በሀሰት አትመስክር አታታልል አባትህንና እናትህን አክብር አለው፡፡ 20 እርሱም መምህር ሆይ እነኚህን ሁሉ ከልጅነቴ ጀምሮ ጠብቄአለሁ አለው፡፡ 21 ኢየሱስም አይቶ ወደደውና አንዲት ነገር ቀርታሀለች ሂድ ያለህን ሁሉ ሽጥና ለድሆች ስጥ መዝገብም በሰማይ ይቆይሀል መጥተህም ተከተለኝ አለው፡፡ 22 እርሱም ብዙ ሀብት ነበረውና በሰማው ነገር ፊቱ ተቁሮ እያዘነ ሄደ፡፡ 23 ኢየሱስም ዙሪያውን ተመለከተና ደቀመዛሙርቱን ለሀብታሞች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት እንዴት ጭንቅ ነው አላቸው፡፡ 24 ደቀመዛሙርቱም በንግግሩ እጅግ ተገረሙ፡፡ ኢየሱስ እርሱ ግን መልሶ ልጆች ሆይ በሀብታቸው ለሚታመኑ ወደ እግዚአብሔር መንግስት መግባት እንዴት ከባድ ነው አላቸው፡፡ 25 ሀብታም ሰው ወደ መንግስተ ሰማያት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢሾልክ ይቀላል አላቸው፡፡ 26 ደቀመዛሙርቱም እጅግ ተገርመው እንግዲያውስ ማን ሊድን ይችላል አሉት፡፡ 27 ኢየሱስም ወደ እነርሱ ተመከተና ለሰዎች ይህ አይቻልም ነገር ግን ለእግዚአብሔር ይቻላል ለእግዚአብሔር ሁሉ ይቻላልና አላቸው፡፡ 28 ጴጥሮስም ጌታ ሆይ እኛ ሀሉን ትተን ተከልንህ ይለው ጀመር፡፡ 29 ኢየሱስም እውነት እላችኋለሁ ስለኔና ስለ ወንጌል ቤቱን ወንዱሞቹን ወይም እህቶቹንወይም እናቱን ወይም አባቱን ወይም ልጆቹን ወይም መሬቱን የሚተው 30 በዚህ ዓለም መቶ እጥፍ ቤቶችን ወንድሞችን እህቶችን እናቶችን ልጆችንና መሬት ከስደት ጋር በሚመጣውም አለም የዘላለምን ህይወት የማይቀበል የለም 31 ነገር ግን ብዙዎች ፊተኞች ኋለኞች ኋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ አላቸው፡፡ 32 ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄዱ ሳለ ኢየሱስ ከፊት ከፊታቸው ይሄድ ነበር፡፡ እጅግም ተገርመው ነበር የሚከተሉትም በጣም ፈርተው ነበር፡፡ አስራሁለቱን እንደገና ወስዶ ሊደርስበት ያለውን ነገር ይነግራቸው ጀመር፡፡ 33 እነሆ ወደ ኢየሩሳሌም እንሄዳለን የሰው ልጅም ለካህናት አለቆችና ለጻፎች አልፎ ይሰጣል እነርሱም ሞትን ይፈርዱበታል ለአህዛብም አሳልፈው ይሰጡታል፡፡ 34 አህዛብም/ፈሪሳዊያን ይቀልዱበታል ይተፉበታል ይገርፉታል ይገድሉታልም ከሶስት ቀን በኋላም ይነሳል እያለ ይነግራቸው ጀመር፡፡ 35 የዘብድዮስ ልጆች ያዕቆብና ዮሀንስ ወደ ኢየሱስ ቀርበው መምህር ሆይ የምንጠይቅህን ሁሉ እንድታደርግልን እንለምንሀለን አሉት፡፡ 36 እርሱም ምን እንዳደርግላችሁ ትፈልጋለችሁ አላቸው፡፡ 37 እነርሱም በክብርህ በምትሆንበት ጊዜ አንዳችን በቀኝህ አንዳችን በግራህ እንድንቀመጥ ፍቀድ አሉት፡፡ 38 ኢየሱስ ግን የምትለምኑትን አታውቁም እኔ የምጠጣውን ጽዋ ልትጠጡ እኔ የምጠመቀውን ጥምቀት ልትጠመቁ ትችላላችሁን አላቸው፡፤ 39 እነርሱም እንችላለን አሉት፡፡ ኢየሱስም እኔ የምጠጣውን ጽዋ ትጠጣላችሁ እኔ የምጠመቀውን ጥምቀት ትጠመቃላችሁ 40 ነገር ግን በግራዬና በቀኜ መሆን ለተዘጋጀላቸው ነው እንጂ እኔ የምሰጠው አይደለም አላቸው፡፡ 41 አሥሩ ደቀማዘሙርትም ይህን በሰሙ ጊዜ በያዕቆብና በዮሀንስ ላይ ተቆጡ፡፡ 42 ኢየሱስም ወደ እርሱ ጠርቶ የአህዛብ አለቆች በሚመሩዋቸው ላይ እንደሚሠለጥኑባቸው ታላላቆቻቸውም እንደሚገዙዋቸው ታውቃላችሁ፡፡ 43 በእናንተ ዘንድ ግን እንዲህ አይደለም ነገር ግን ከእናንተ ማንም የበላይ(ታላቅ) ለመሆን የሚፈልግ የሁሉ አገልጋይ ይሁን 44 ፊተኛ ለመሆን የሚፈልግም የሁሉ ባሪያ ይሁን 45 የሰው ልጅም ሊያገለግል ነፍሱንም ለብዙዎች ቤዛ ሊያደርግ እንጂ እንዲያገልግሉት አልመጣም አላቸው፡፡ 46 ኢየሱስና ደቀመዛሙርቱም ወደ ኢያሪኮ መጡ፡፡ ከደቀመዛሙርቱና ከብዙ ህዝብ ጋር ከኢያሪኮ በመውጣት ላይ ሳለ የጤሚዮስ ልጅ ዓይነ ስወሩ ለማኝ በርጠሚዮስ በመንገድ ዳር ተቀምጦ ይለምን ነበር፡፡ 47 የናዝሬቱ ኢየሱስ እያለፈ መሆኑን ሲሰማ የዳዊተ ልጅ ኢየሱስ ሆይ እራራልኝ እያለ ጮኸ፡፡ 48 ብዙዎችም ዝም እንዲል ገሰፁት፡፡ እርሱ ግን አብዝቶ የዳዊት ልጅ ሆይ እራራልኝ ብሎ ጮኸ፡፡ 49 ኢየሱስም ቆመና ጥሩት አለ፡፡ እነርሱም አይዞህ መምህሩ ይጠራሀልና ተነሳ አሉት፡፡ 50 በርጠሚዮስም ልብሱን ጥሎ እየዘለለ ወደ ኢየሱስ መጣ፡፡ 51 ኢየሱስም ምን እንዳደርገልህ ትወዳለህ አለው፡፡ ዓይነ ስውሩም ሰው መምህር ሆይ ማየት እንድችል አለው፡፡ 52 ኢየሱስም መንገድህን ሂድ እምነትህ አድኖሀል አለው፡፡ ወዲያውም አየ ኢየሱስንም ተከትሎ ሄደ፡፡
እናንተ ልበ ደንዳኖች "እናንተ እልከኞች"
ከእንግዲህ ሁለት አይደሉም ግን አንድ ሥጋ ይሆናሉ ይህ እንደ ባል እና ምስት ያላቸውን አካላዊ ትሥሥር የሚያሳይ ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡
ሕጻናት ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ ፍቀዱላቸውለ ፈጽሞ አትከልክሏቸው፡፡ እነዚህ ሁለት ዓረፍተ ነገሮች ተመሳሳይ ትርጉም ሲኖራቸው በድጋሜ የተጻፈውም አጽኖት ለመስጠት ሲባል ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ሕጻናት ወደ እኔ እንዲመጡ አድርጓቸው፡፡” አትከልክሏው ይህ በላሁት አሉታዊ ንግግር ነው፡፡ በአንዳንድ ቋንቋዎች ውስጥ አዎንታዊ ቃላትን መጠቀም የተለመደ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ፍቀዱላቸው፡፡”
መልካም ብለህ ለምን ትረጠራኛለህ? አማራጭ ትርጉም: "በዚህ ንግግር ውስጥ በተዘዋዋሪ መንገድ የሚታስተፈላልፈው መልዕክት በጥንቃቄ ማወቅ ይኖርብሃል )
ሀብታም ወደ እግዚአብሔር መንግስት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ውስጥ በትሾልክ ይቀላል፡፡ ለግመል በመርፌ ቀዳዳ ውስጥ ማለፍ ፈጸሞ የማይቻላት ነገር ነው፡፡ እንደዚሁም ሀብታም ሰዎች እግዚአብሔርን የሕይወታቸውን ንጉሥ አድርጎ መቀበል በጣም አስቸጋር ነው፡፡ የመርፌ ዐይን/ ቀዳዳ “የመርፌ ዐይን” በመርፌ አናት ላይ የሚገኝ ቀዳዳ ነው፡፡
ታዲያ ማን ሊድን ይችላል? "ስለዚህ ማንም ሊድን አይችልም፡፡"
ከተውቱ መካል . . . የማይቀበል አይኖርም "ከተውት መካከል . . . የማይቀበል አይኖርም፡፡" ለእኔ ሲል "ለእኔ ጥቅም" ወይም "ለእኔ ጥቅም ሲል" ይህንን ዓለም "ይህን ሕይወት" ወይም "በአሁኑ ዘመን" በሚመጣው ዘመን "በሚመጣው ሕይወት" ወይም "በሚመጣው ጊዜ"
የሰው ልጅን አሳልፈው ይሰጡታል "ሰዎች የሰው ልጅ አሳልፈው ይሰጡታል" ወይም "ሰዎች የሰው ልጅን አሳለፈው ይሰጡታል"
የሚጠጣው ጽዋ ኢየሱስ ይህንን ሀረግ የተጠቀመው ስለሚቀበለው መከራ ለመግለጽ ነው፡፡ የሚጠመቀውን ጥምቀት ኢየሱስ ይህንን ሀረግ የተጠቀመው ስለሚቀበለው መከራ ለመግለጽ ነው፡፡
ገዥዎች ተብለው በሚጠሩት "ገዥዎች ተብለው በሌሎች በሚቆጠሩት" ተቆጣጣሪዎች "የሚቆጣጠሩ" ወይም "ኃይል ያላቸው" መለማመድ "የሚጠቀሙ"
ትልቅ የሚሆን "የሚከበር" ወይም "የሚሞገስ" ማንም "ዬትኛውም ሰው" የሰው ልጅ ሊገለገል ሳይሆን "የሰው ልጅ ሰዎች እንዲገለግሉት አልመጣም"
በርጤሜዎስ የአንድ ሰው ስም ጤሜዎስ ይህ በመንገድ ላይ ስለለምን የነበረው ለማኝ አባት ነው፡፡
እንዲጠሩት አዘዘ "ሰውዬውን ይጠሩት ዘንድ አዘዛቸው" ጠንከር በል "አትፍራ"
መመልከት "የማየት ክህሎት" ወዲያው "በዚያን ጊዜ" ወይም "ያለምንም መዘግየት"
1 ከደብረ ዘይት ተራራ ወደ ኢየሩሳሌም፣ ወደ ቤተ ፋጌና ወደ ቢታንያ በቀረቡ ጊዜ ኢየሱስ ከደቀመዛሙርቱ ሁለቱን ላካቸው፡፡ 2 እንዲህም አላቸው፣ ፊት ለፊታችን ወዳለው መንደር ሂዱ፤ወዲያው እንደ ገባችሁም ማንም ሰው ተቀምጦበት የማያውቅ ውርንጫ መንገድ ዳር ታስሮ ታገኛላችሁ፡፡ ፍቱትና አምጡልኝ፤ 3 ማንም ለምን ይህን ታደርጋላችሁ ቢላችሁ ለጌታ ያስፈልገዋል በሉት፤ እርሱም ይለቅቀዋል አላቸው፡፡ 4 እነርሱም ሄዱ፤ አንድ ውርንጫ ከቤት ውጭ በመንገድ ዳር ታስሮ አገኙ፤ ፈቱትም፡፡ 5 በአካባቢው ከቆሙት አንዳንዶቹ ሰዎች ለምን ፈታችሁት? አሏቸው፡፡ 6 እነርሱም ልክ ኢየሱስ እንዳላቸው ነገሯቸው፤ ለቀቋቸውም፡፡ 7 ደቀመዛሙርቱም ውርንጫውን ወደ ኢየሱስ አመጡት፤ ልብሳቸውንም አለበሱት፤ ኢየሱስም ተቀመጠበት፡፡ 8 ብዙ ሰዎችም ልብሳቸውን ፣ሌሎችም ከየቦታው ቅርንጫፎችን ቆርጠው በሚሄድበት መንገድ ላይ አነጠፉ፡፡ 9 ከፊት የቀደሙት ከኋላውም የተከተሉት ሆሳእና! በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ 10 የሚመጣው የአባታችን የንጉሥ ዳዊት መንግስት የተባረከ ነው፤ ሆሳእና በአርያም እያሉ ጮኹ፡፡ 11 ኢየሩሳሌም እንደ ደረሰ ወደ ቤተመቅደስ ገባ፡፡ በአካባቢው ያለውን ሁሉ ተመለከተ፤መሽቶም ነበርና ከዐሥራ ሁለቱ ጋር ወደ ቢታንያ ሄደ፡፡ 12 በማግስቱም ከቢታንያ እንደ ወጡ ተራበ፤ 13 አንዲት ቅጠሏ ያቆጠቆጠ በለስ ከርቀት አየ፡፡ ምናልባት አንዳች አገኝባት ይሆናል በማለት ወደ እርሷ መጣ፡፡ ሲደርስ ግን በለስ የሚያፈራበት ጊዜ ስላልነበረ ከቅጠል በቀር ምንም አላገኘባትም፡፡ 14 ስለዚህም ማንም ሰው ለዘላለም ምንም ፍሬ አያግኝብሽ ብሎ ረገማት፡፡ ደቀመዛሙርቱም ሰሙት፡፡ 15 ወደ ኢየሩሳሌምም እንደ መጡ ወደ ቤተመቅደስ ገባ፤ በዚያም የሚሸጡትንና የሚገዙትን አባረረ፤የገንዘብ ለዋጮችን ጠረጴዛ የርግብ ሻጮችንም መቀመጫቸውን ገለበጠባቸው፡፡ 16 ማንም ሰው በቤተ መቅደስ ውስጥ ዕቃ ይዞ እንዳይመላለስ ከለከለ፡፡ 17 አስተማራቸውም፤ ቤቴ የአሕዛብ ሁሉ የጸሎት ቤት ይባላል ተብሎ አልተጻፈምን? እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት አላቸው፡፡ 18 ሊቀ ካህናቱና ጸሓፍትም፣ይህን ሲናገር ሲሰሙ ሕዝቡ ሁሉ በትምህርቱ ተደንቀው ስለ ተከተሉት ፈርተው ነበርና እንዴት እንደሚገድሉት ማሰብ ጀመሩ፡፡ 19 ኢየሱስም በየምሽቱ ከከተማ ይወጣ ነበር፡፡ 20 በማለዳ ሲያልፉም በለሲቱ ከሥሯ ደርቃ አገኟት፡፡ 21 ጴጥሮስም አስታውሶ መምህር ሆይ! እነሆ፤የረገምሃት በለስ ደርቃለች አለው፡፡ 22 ኢየሱስም እንዲህ አለው፡፡ በእግዚአብሔር እመን፤ 23 እውነት እላችኋለሁ፣ ማንም በልቡ ሳይጠራጠር ይህን ተራራ ከዚህ ተነቅለህ ወደ ባሕር ውስጥ ተወርወር ቢልና የተናገረው እንደሚፈጸም በልቡ ቢያምን ይሆንለታል፡፡ 24 ስለዚህ እላችኋለሁ፤የጸለያችሁትንና የለመናችሁትን ነገር ሁሉ እንደምትቀበሉ ብታምኑ ይሆንላችሁማል፡፡ 25 ለጸሎት ስትቆሙ፣ በማንም ላይ ቅርታ ቢኖራችሁ፣ የሰማዩ አባታችሁ ኀጢአታችሁን ይቅር እንዲላችሁ ይቅር በሉ፡፡ 26 እናንተ ግን ይቅር ባትሉ በሰማያት ያለው አባታችሁ ደግሞ የቅር አይላችሁም፡፡ 27 በድጋሚም ወደ ኢየሩሳሌም መጡ፡፡ ኢየሱስ ወደ ቤተመቅደስ ሲገባም ሊቀ ካህናት፣ጸሓፍትና ሽማግሌዎችም ወደ ኢየሱስ መጥተው፣ 28 እነዚህን ነገሮች የምታደርገው በምን ሥልጣን ነው? ወይም እነዚህን ነገሮች እንድታደርግ ሥልጣን የሰጠህ ማን ነው? አሉት፡፡ 29 ኢየሱስም አንድ ጥያቄ ጠይቃችኋለሁ እናንተም መልሱልኝ፤ እኔም እነዚህን ነገሮች በምን ሥልጣን እንደማደርግ እነግራችኋለሁ አላቸው፡፡ 30 መልሱልኝ፤ የዮሐንስ ጥምቀት ከሰማይ ነው? ወይስ ከሰው? አላቸው ፡፡ 31 እነርሱም እርስ በርሳቸው ተመካከሩ፤ ከሰማይ ነው ብንል ታዲያ ለምን አላመናችሁበትም? ይለናል፤ 32 ነገር ግን ከሰው ነው ብንል ደግሞ ሰዉ ሁሉ ዮሐንስ ነቢይ ነው ብሎ አምኖበታል ብለው ሕዝቡን ፈሩ፡፡ 33 ለኢየሱስም አናውቅም ብለው መለሱለት፡፡ ኢየሱስም እኔም እነዚህን ነገሮች በምን ሥልጣን እንደማደርግ አልነግራችሁም አላቸው፡፡
ቤተ ፋጌ የመንደሯ ስም
ሆሣዕና የዚህ ቃል ትርጉም ምን እንደሆነ ግልጽ አይደለም ይሁን እንጂ እንኳ ደህና መጡ እና ምስጋና ጋር ተያያዥነት ባለው መልኩ ቢተረጎም መልካም ነው፤ ማለትም “እግዚአብሔር ይመስገን” (UDB)፡፡
“ቤተ ለአሕዛቡ ሁሉ የጸሎት ቤት ይባልል” ተብሎ አልተጻፈምን? "በቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ እግዚአብሔር “ቤቴ ከሁሉም ሕዝቦች የመጡ ሰዎች የሚጸልዩበት ቤት ይሆናል” በማለት የተናገረው ተጽፏል፤ ነገር ግን እናንት ወሮበላዎች ለእናንተ መደበቂያ ዋሻ አደረጋችሁት!"
“ቤተ ለአሕዛቡ ሁሉ የጸሎት ቤት ይባልል” ተብሎ አልተጻፈምን? "በቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ እግዚአብሔር “ቤቴ ከሁሉም ሕዝቦች የመጡ ሰዎች የሚጸልዩበት ቤት ይሆናል” በማለት የተናገረው ተጽፏል፤ ነገር ግን እናንት ወሮበላዎች ለእናንተ መደበቂያ ዋሻ አደረጋችሁት!"
በልቡ ሳይጠራጠር ቢያምን "ሳይጠራጠር" የሚለው ቃል ባለሁት አሉታዊ ቃል ነው፡፡ ትርጉሙም “በእውነት ቢያምን” ማለት ነው፡፡ እነዚህ ሁለት ሀረጎች ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው አጽኖት ለመስጠት ሲባል ብቻ ጥቅም ላይ የዋሉ ናቸው፡፡ አንዳንድ ቋንቋዎች አጽኖት የሚቀጠሙት ሌላ መንገድ ነው፡፡ አማርጭ ትርጉም፡ “በእውነት ቢያምን”
ቆማችሁ ስትጸልዩ በዕብራዊን ባሕል መሠረት ወደ እግዚብሔር የሚደረግ ጸሎት የሚደረገው ተቁሞ ነው፡፡
እነዚህ ነገሮች የሚታደርገው በምን ሥልጣን ነው “እነዚህ ነገሮች” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስ በቤተ መቅደሱ ውስጥ የነበሩት የሽያጮችን ጠረጴዛዎች መገለባበጡን እና የሚያድርጉትን እና የሚያስተምሩትን ነገር በመቃወም መነናገሩን የሚያመለክት ቃል ነው፡፡ እነዚህ ነገሮች የሚታደርገው በምን ሥልጣን ነው እንዲሁም እነዚህ ነገሮች እንዲታደረግ ሥልጣን ማን ሰጠህ አማራጭ ትርጉም፡ "እነዚህን ነገሮች ለማድረግ ሥልጣን የለህም ምክንያቱም እኛ ይህንን ሥልጣን አልሰጠንህም"
የዮሐንስ ጥምቀት ከሰማይ ወይም ከሰዎች ናት? ምንም እንኳ ኢየሱስ ለዚህ ጥያቄ ምላሹ ምን እንደሆነ ቢያውቅም ይህን ጥያቄ የጠየቃቸው የሃይማኖት መሪዎቹ ለእርሱ ሥልጣን የጠየቁት ጥያቄ መሠረቱ ምን አመክኒዬ እንደሆነ ለመፈተን ነው፡፡
1 ኢየሱስም በምሳሌ ይነግራቸው ጀመር፡፡ አንድ ሰው የወይን ተክል ተከለ፤በዙሪያው ዐጥር ሠራ፤ለወይን መጭመቂያ የሚሆን ጕድጓድ ቈፈረ፤ማማም ሠራ፡፡ ለገበሬዎችም አከራይቶ ወደ ሌላ አገር ሄደ፡፡ 2 በወቅቱ የወይኑን ፍሬ እንዲቀበል አንድ አገልጋይ ወደ ገበሬዎቹ ላከ፡፡ 3 እነርሱም አገልጋዩን ያዙት፤ ደብድበውም ባዶ እጁን ሰደዱት፡፡ 4 በድጋሚም ሌላ አገልጋይ ላከ፤እነርሱም ፈነከቱት፤ አሳፈሩትም፡፡ 5 ሌላም አገልጋይ ወደ እነርሱ ላከ፤ እርሱንም ገደሉት፡፡ ብዙዎች ሌሎችንም ላከ፤ አንዳንዶቹን ደበደቡ፤ ሌሎቹንም ገደሉ፡፡ 6 የወይኑ ተክል ባለቤት አንድ ተወዳጅ ልጅ ነበረው፤ልጄን ያከብሩታል በማለት በመጨረሻ እርሱን ላከው፡፡ 7 ገበሬዎቹ ግን እርስበርሳቸው እንዲህ አሉ፡፡ ይህ ወራሹ ነው ኑ እንግደለው ሀብቱ ሁሉ የእኛ ይሆናል ተባባሉ፡፡ 8 ልጁንም ያዙት፤ ገደሉት፤ከወይኑ ቦታ ውጭም ጣሉት፡፡ 9 የወይኑ ተክል ባለቤት በዚህ ጊዜ ምን ያደርጋል? ይመጣና ገበሬዎቹን ያጠፋቸዋል፤የወይን ቦታውንም ለሌሎች ይሰጣቸዋል፡፡ 10 ይህን የመጽሓፍ ቃል አላነበባችሁምን? እነሆ ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማእዘን ድንጋይ ሆነ፤ 11 ይህ ከጌታ ነው፤ ለዐይኖቻችንም ድንቅ ነው፡፡ 12 ኢየሱስ ምሳሌውን የተናገረው ስለ እነርሱ እንደ ሆነ ስለ ተገነዘቡ እጃቸውን ሊጭኑበት ፈለጉ፤ነገር ግን ሕዝቡን ስለ ፈሩ፤ትተውት ሄዱ፡፡ 13 እነርሱም በንግግር እንዲያጠምዱት አንዳንድ ፈሪሳውያንና ከሄሮድስ ወገን የሆኑ ሰዎችን ላኩ፡፡ 14 ወደ እርሱ በመጡ ጊዜ እንዲህ አሉት፤መምህር ሆይ፣ አንተ እውነተኛ እንደ ሆንህ ለማንም በይሉኝታ እንደማታደርግ፣ለሰው ፊትም እንደማታዳላ ነገር ግን የእግዚአብሔርን መንገድ በእውነት እንደምታስተምር እናውቃለን፡፡ ለቄሳር ግብር መክፈል ተገቢ ነው? ወይስ አይደለም? 15 እንክፈል ወይስ አንክፈል? አሉት፡፡ ኢየሱስ ግን ግብዝነታቸውን ዐውቆ ለምን ትፈትኑኛላችሁ? አላቸው፡፡ እንዳየው አንደ ዲናር አምጡልኝ አላቸው፡፡ 16 እነርሱም አመጡለት፡፡ ኢየሱስም ይህ ምስል ቅርጹም የማን ነው? አላቸው፡፡ እነርሱም የቄሳር ነው አሉት፡፡ 17 ኢየሱስም እንግዲህ የቄሳርን ለቄሳር የእግዚአብሔርንም ለእግዚአብሔር ስጡ አላቸው፡፡ እጅግም ተገረሙበት፡ 18 ትንሣኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዱቃውያን ወደ እርሱ መጥተው እንዲህ ብለው ጠየቁት፡፡ 19 መምህር ሆይ፣ ሙሴ፣ አንድ ሰው ልጅ ሳይወልድ ሚስቱን ትቶ ቢሞት፣ ወንድሙ እርስዋን አግብቶ ለወንድሙ ዘር ይተካለት ብሎ ጽፎልናል፡፡ 20 ሰባት ወንድማማቾች ነበሩ፡፡ የመጀመሪያው ሚስት አገባ፤ ዘር ሳይተካም ሞተ፡፡ 21 ሁለተኛውም አገባት፤ እርሱም ዘር ሳይተካለት ሞተ፡፡ ሦስተኛውም እንዲሁ፡፡ 22 ሰባቱም ለወንድማቸው ዘር አልተኩም፡፡ ከሁሉም በኋላ ሴቲቱም ደግሞ ሞተች፡፡ 23 ታዲያ ይህች ሴት በትንሣኤ የየትኛው ሚስት ትሆናለች? አሉት፡፡ ሰባቱም አግብተዋት ነበርና፡፡ 24 ኢየሱስም የምትስቱት መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኀይል ስለማታውቁ አይደለምን? 25 በትንሳኤ ጊዜ ሰዎች አያገቡም፤ አይጋቡም፤ ነገር ግን በሰማይ እንደ መላእክት ይሆናሉ እንጂ፡፡ 26 ነገር ግን ሙታን እንደሚነሡ በሚነድደው ቁጥቋጦ ውስጥ እኔ የአብርሃም፣ የይስሐቅ፣ የያእቆብ አምላክ ነኝ ሲል እግዚአብሔር ለሙሴ የተናገረውን አላነበባችሁምን? እጅግ ትስታላችሁ፡፡ 27 እርሱ የሕያዋን አምላክ እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም፡፡ 28 ከጸሓፍት አንዱ መጣና በአንድነት ሆነው ሲጠይቁት እንዴት በጥሩ ሁኔታ እንደ መላሰላቸው አይቶ፣ ከሕግ ፊተኛው የትኛው ነው? ብሎ ኢየሱስን ጠየቀው፡፡ 29 ኢየሱስም ፊተኛው፣ እስራኤል ሆይ ስማ! አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው፤ 30 አንተም አምላክህን እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህ፣በፍጹም አሳብህ፣ በፍጹምም ኀይልህ ውደድ የምትለዋ ናት፡፡ 31 ሁለተኛዋም ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የምትለዋ ናት፡፡ ከእነዚህ የሚበልጥ ምንም ሌላ ትእዛዝ የለም አለው፡፡ 32 ሰውዬውም መምህር ሆይ፣በእውነት መልካም ብለሃል፤ እርሱ አንድ ነው፤ከእርሱም በቀር ሌላ የለም፤ እርሱን በፍጹም ልብ፣ በፍጹም ማስተዋል፣ 33 በፍጹም ኀይል መውደድና ባልንጀራን እንደ ራስ መውደድ ሁሉንም ዓይነት መስዋእትና የሚቃጠል መሥዋእት ከማቅረብ ይበልጣል አለ፡፡ 34 ኢየሱስም ሰውዬው በማስተዋል እንደ መለሰለት ባየ ጊዜ አንተ ከእግዚአብሔር መንግስት የራቅህ አይደለህም አለው፡፡ ከዚያ በኋላ ማንም ሰው ምንም ጥያቄ ሊጠይቀው አልደፈረም፡፡ 35 ኢየሱስም መለሰላቸው፤ በቤተ መቅደስ ውስጥ ሲያስተምር፣ ጸሓፍት ክርስቶስ የዳዊት ልጅ ነው የሚሉት እንዴት ነው? አለ፡፡ 36 ዳዊት ራሱ በመንፈስ ቅዱስ ጌታ ጌታዬን ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው፡፡ 37 ዳዊት ራሱ ጌታዬ ብሎ ይጠራዋል፤ ታዲያ እንዴት ልጁ ይሆናል? ሕዝቡም በደስታ ይሰማው ነበር፡፡ 38 ኢየሱስም እንዲህ አለ፡፡ ከጸሓፍት ተጠንቀቁ፤ የተንዘረፈፈ ልብስ ለብሰው መሄድን ይወድዳሉ፤ እነርሱ በገበያ ቦታ ሰላምታን፣ 39 በምኩራብም የክብር ወንበር፣ በግብዣም የክብር ቦታ ላይ መቀመጥ ይወድዳሉ፡፡ 40 ለይምሰል ጸሎት በማስረዘም የመበለቶችን ቤት ይበዘብዛሉ፡፡ እነዚህ የባሰ ፍርድ ይቀበላሉ፡፡ 41 ኢየሱስም በመባ መቀበያው ፊት ለፊት ተቀመጠ፡፡ ብዙ ሰዎች በመባ መቀበያው ውስጥ ገንዘብ ሲጨምሩ ተመለከተ፡፡ ብዙ ሃብታሞች ብዙ ገንዘብ ይጨምሩ ነበር፡፡ 42 ከዚያም አንዲት ድኻ መበለት መጥታ ሁለት ናስ ጨመረች፤ይህም የብር ሩብ ነው፡፡ 43 እርሱም ደቀመዛሙርቱን ወደ ራሱ ጠርቶ እንዲህ አላቸው፡፡ እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ይህች መበለት በመባ መቀበያው ውስጥ ገንዘባቸውን ከጨመሩት ሁሉ አብልጣ ሰጠች፡፡ 44 እነርሱ ከትርፋቸው ሰጥተዋልና፡፡ እርስዋ ግን ከጉድለቷ ሰጠች፤ ያላትን ሁሉ ሰጠች፤ ኑሮዋን እንኳ ሳይቀር ሁሉንም ሰጠች፡፡
የወይን እርሻውን አከራይቶ ሄደ የእርሻው ባለቤት ወይኑን ይንከባከቡለት ለሌሎች ሰዎች ሰጠ፡፡
ገበሬዎቹ ከባለቤቱ የወይን እርሻውን ለመንከባከብ የተረከቡት ገበሬዎች
ማርቆስ 12፡ 8-9 ስለዚህ የወይን እርሻው ባለቤት ምን ያድረጋል? አማራጭ ትርጉም: "የወይን እርሻው ባለቤት ምን እንደሚያደርግ እነግራችኋለሁ፡፡
ማርቆስ 12፡ 10-12 ይህን የቅዱስ መጽሐፍ ክፍል አላነበባችሁምን? አማራጭ ትርጉም፡ "በእነዚህ የቅዱስ መጽሐፍ ክፍል ውስጥ የሚገኙትን እነዚህን ቃላት በጥንቃቄ አስቡ፡፡"
ስለምን ትፈትኑኛላችሁ? "እኔን መከሰስ ያስችላችሁ ዘንድ ትክክል ያልሆነ ነገር እስኪናገር ድረስ እየፈለጋችሁ መሆኑን አውቃለሁ፡፡" ዲናር ይህ ገንዝብ የአንድ ቀን የሥራ ደሞዝን ያክላል፡፡
አንድ አመጡለት "ፈርሳዊያን እና ሄሮዶሳዊያን የሮም መንግስት ፍራንክ አመጡለት" የቄሣርን ለቄሣር ስጡ አማራጭ ትርጉም፡ "የሮም መንግስት የሆነውን ነገር ለሮም መንግስት ስጡ፣" .
ሙሴ እንዲህ ብሎ ጽፎልናል፣ 'የእንድ ሰው ወንድም . . . ለወንድሙ ልጅ ይውለድለት፡፡' አማራጭ ትርጉም: "ሙሴ እንዲህ ሲል ጽፏል የአንድ ሰው ወንድም ከሞተ . . ለወንድሙ ልጅ ይውለድለት፡፡
በትንሳዔ ጊዜ፣ ከሞት ሲነሳ የማን ምስት ትሆናለች? አማራጭ ትርጉም፡ "በትንሳዔ ጊዜ፣ ከሞት ሲነሳ የእነዚህ ሰባት ወንድመማማቾች ምስት መሆን እትችልም!"
ስህተታሁ ይህ አይደለምን . . . የእግዚአብሔር ኃይል? "የተሳሳታችሁት በዚህ ምክንያት ነው . . . የእግዚአብሔር ኃይል፡፡"
ከሞት ይነሳሉ "እግዚአብሔር ያስነሳቸዋል፣"
ታዲያ ጸሐፍት እንዴት ክርስቶስ የዳዊት ልጅ ነው ይላሉ? አማራጭ ትርጉም: "የአይሁድ ሕግ ክርስቶስ የዳዊት ልጅ ነው ብለው የሚያስተምሩት እነዚህ ሰዎች ተሳተዋል!" የዳዊተ ልጅ “ልጅ” የሚለው ቃል በዚህ ሥፍራ ጥቅም ላይ የዋለው ዘር የሚለውን ለማመለከት ነው፡፡ ታዲያ እንዴት የዳዊት ልጅ ሊሆን ይችላል? አማራጭ ትርጉም፡ "የዳዊት ልጅ መሆን አይችም!"
እውነት እውነት እላችኋለሁ ይህንን በ MRK 11:23 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡ የመባ ሳጥን ይህ ሳጥን በቤተ መቅደሱ ውስጥ መባ ለመሰብሰብ የሚው ሳጥን ነው፡፡ የተትረፈረፈ "በጣም ብዙ" ድህነት "እጥረት" ወይም "ድህነት"
1 ኢየሱስ ከቤተመቅደስ ሲወጣ ሳለ ከደቀመዛሙርቱ አንዱ መምህር ሆይ፤ እንዴት ያሉ ድንጋዮችና እንዴት ያሉ ሕንጻዎቹ እንደሆኑ ተመልከት! አለው፡፡ 2 እርሱም እነዚህን ታላላቅ ሕንጻዎች ታያለህን? ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ እንደዚህ አይቀርም አለው፡፡ 3 ኢየሱስ በደብረዘይት ተራራ ላይ በቤተመቅደሱ ትይዩ ተቀምጦ ሳለ ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ፣ ዮሐንስና እንድርያስ 4 ንገረን፣ እነዚህ ነገሮች የሚሆኑት መቼ ነው? እነዚህ ነገሮች ሁሉ የሚፈጸሙበት ምልክቱስ ምንድነው? ብለው ለብቻው ጠየቁት፤ 5 ኢየሱስም ማንም እንዳያስታችሁ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ አላቸው፡፡ 6 ብዙዎች እኔ ክርስቶስ ነኝ! እያሉ በስሜ ይመጣሉና ብዙዎችንም ያስታሉ፡፡ 7 ጦርነትንና የጦርነትን ወሬ በምትሰሙበት ጊዜ አትታወኩ፤ እነዚህ ነገሮች የግድ መፈጸም አለባቸው፤ ነገር ግን መጨረሻው ገና ነው፡፡ 8 ሕዝብ በሕዝብ ላይ፣ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፡፡ በተለያዩ ቦታዎች የምድር መንቀጥቀጥ፣ ረሃብም ይሆናል፡፡ እነዚህ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው፡፡ 9 እናንተ ግን ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፡፡ ወደ ሸንጎዎቻቸው ያቀርቧችኋል፣ በምኩራቦች ውስጥ ትደበደባላችሁ፡፡ ለእነርሱ ምስክር እንዲሆን በእኔ ምክንያት በገዢዎችና በነገሥታት ፊት ትቆማላችሁ፡፡ 10 አስቀድሞ ወንጌል ለሕዝቦች ሁሉ ይሰበካል፡፡ 11 ወደ ፍርድ በሚያቀርቧችሁና አሳልፈው በሚሰጧችሁ ጊዜ አስቀድማችሁ ምን እንደምትናገሩ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በዚያች ሰዓት የምትናገሩት ይሰጣችኋልና፤ የሚናገረውም መንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ እናንተ አይደላችሁም፡፡ 12 ወንድም ወንድሙን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፣ አባትም ልጁን፤ ልጆችም ወላጆቻቸውን በመቃወም ተነስተው ይገድሏቸዋል፡፡ 13 ስለስሜም በሰዎች ሁሉ ትጠላላችሁ፡፡ ነገር ግን እስከ መጨረሻው የሚጸና እርሱ ይድናል፡፡ 14 የጥፋትን እርኩሰት በማይገባው ቦታ ቆሙ ስታዩት (አንባቢው ያስተውል) በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ፤ 15 በቤቱ ጣሪያ ላይ ያለም አንዳች ይወስድ ዘንድ አይውረድ፣ ወደ ቤትም አይግባ፤ 16 በእርሻም ያለ ልብሱን ይወስድ ዘንድ ወደ ኋላው አይመልከት፡፡ 17 ነገር ግን በእነዚያ ወራት ለእርጉዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው! 18 በክረምት እንዳይሆን ጸልዩ፡፡ 19 እግዚአብሔር ከፈጠረው ከፍጥረት መጀመሪያ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ያልሆነ ወደፊትም የማይሆን ታላቅ መከራ በእነዚያ ቀናት ይሆናልና፡፡ 20 ጌታ ቀኖቹን ባያሳጥር ኖሮ ሥጋን የለበሰ ሁሉ አይድንም ነበር፡፡ ነገር ግን ስለመረጣቸው ስለ ምርጦቹ ሲል ቀኖቹን አሳጠረ፡፡ 21 አንድ ሰው እነሆ ክርስቶስ በዚህ ነው ወይም እነሆ በዚያ ነው ቢላችሁ አትመኑት፡፡ 22 ሐሰተኛ ክርስቶሶችና ሐሰተኛ ነብያት ይነሣሉና፤ ቢቻላቸው የተመረጡትን ለማሳት ድንቆችንና ምልክቶችን ያሳያሉ፡፡ 23 ነገር ግን አስተውሉ፤ እነሆ አስቀድሜ ሁሉንም ነገር ነግሬአችኋለሁ፡፡ 24 ከመከራው በኋላ በእነዚያ ቀናት ፀሐይ ትጨልማለች፣ ጨረቃም ብርሃንዋን አትሰጥም፣ 25 ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ፣ በሰማያት ውስጥ ያሉ ኃይላትም ይናወጣሉ፡፡ 26 እነርሱም የሰው ልጅ በደመና ውስጥ በታላቅ ኃይልና ክብር ሲመጣ ያዩታል፡፡ 27 ከምድር ጫፍ እስከ ጫፍ ለእርሱ የተመረጡትን ከአራቱም ነፋሳት በአንድ ላይ እንዲሰበስቡለት መላዕክትን ይልካቸዋል፡፡ 28 ምሳሌውን ከበለስ ዛፍ ተማሩ፤ ቅርንጫፏ ሲለሰልስ፣ ቅጠሏም ሲያቆጠቁጥ ያን ጊዜ በጋ መቃረቡን ታውቃላችሁ፡፡ 29 እናንተም ደግሞ እነዚህ ነገሮች ሲፈጸሙ በምታዩበት ጊዜ የሰው ልጅ በበር ላይ መሆኑን ታውቃላችሁ፡፡ 30 እውነት እላችኋለሁ፣ እነዚህ ነገሮች እስኪፈጸሙ ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም፡፡ 31 ሰማይና ምድር ያልፋል፣ ቃሌ ግን አያልፍም፡፡ 32 ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያች ሰዓት ግን ከአባት በስተቀር የሰማይ መላዕክትም ቢሆኑ፣ ልጅም ቢሆን ማንም አያውቅም፡፡ 33 ጊዜው መቼ እንደሆነ አታውቁምና አስተውሉ፣ ንቁና ጸልዩ፡፡ 34 ነገሩ ለአገልጋዮቹ ሥልጣን፣ ለእያንዳንዳቸውም የሥራ ድርሻ በመስጠት ዘበኛውም ደግሞ እንዲጠብቅ አዝዞት ቤቱን ትቶ ወደ ሩቅ ሀገር የሚሔድን ሰው ይመስላል፡፡ 35 35የቤቱ ጌታ በምሽት፣ ወይም በእኩለ ሌሊት፣ ወይም ዶሮ ሲጮህ፣ ወይም ጠዋት ላይ ምን ጊዜ እንደሚመጣ አታውቁምና እንግዲህ ንቁ! 36 በድንገት ሲመጣ እንቅልፍ ላይ ሆናችሁ እንዳያገኛችሁ፡፡ 37 ለእናንተ የምነግራችሁን ለሁሉም እናገራለሁ፣ንቁ!
ይህንን ትልቅ ሕንጻ ትመለከታለህን? አማራጭ ትርጉም፡ “እነዚህ ሕንጻዎች እንዴት እንደሚያምሩ ተመልከት፡፡
እነዚህ ነገሮች "አሁን የነገርከኝ ነገሮች"
በእኔ ስም ብዙ ሰዎች ይመጣሉ “ስም” የሚለው ቃል የኢየሱስን ስልጣን የሚያሳይ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ ብዙዎች የእኔ ስልጣን እና ከእኔ ፈቃድ እንደጋኙ በመናገር ይመጣሉ፣"
ወሬ "የስህተት ትምህርት" ወይም "ወሬ"
ለእነርሱ ምስክር ይሆናቸው ዘንድ “ለእነርሱ ምስክር ይሆናቸው ዘንድ” የሚለው ሀረግ “እውነት እንደሆነ ለማሳየት” ወይም “እውነቱ ዬቱ እንደሆነ ለማረጋገጥ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡
አባት ልጁን "አባት ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፡፡" እስከመጨረሻ የሚጸና ሰው እርሱ ይድናል አማራጭ ትርጉም፡ "እስከመጨረሻ የሚጸናውን እግዚአብሔር ያድነዋል፡፡"
የጥፋት እርኩሰት "ክፉ የሆነ የጣኦት አምልኮ" ወይም "እርባና ያሌለው ክፋት"
the elect, those he chose “እርሱ የመረጣቸው” የሚለው ሀረግ “የተመረጡት” ከሚለው ጋር ተመሳሳይ ትርጉም አለው፡፡ እነዚህ ሁለቱ በአንድነት እግዚአብሔር እነዚህ ሕዝቡን መምረጡን አጽኖት በመስጠት ይናገራሉ፡፡
የተመረጠ ሰዎች እንዲቀደሱ እግዚአብሔር ይመርጣል፣ ጥሩ መንፈሳዊ ፍሬን እንዲያፈሩ እርሱ ራሱ ሰዎችን ይለያል፡፡ ለዚህም ነው “የተመረጡት” ተብለው የሚጠሩት፡፡
ፀሐይ ይጨልማል "እግዚአብሔር ፀሐይ እንዲትጨልም ያደርጋል፡፡" በሰማይ ያሉት ኃይላት ሁሉ ይናወጣሉ "እግዚአብሔር በሰማይ ያሉት ኃይላት ሁሉ ያናውጣልይናወጣሉ"
እውነት እውነት እላችኋለሁ ኢየሱስ ያስተማራቸው ነገር ሁሉ እርሱ በተናገረው መንገድ እየተፈጸመ መሆኑን አጽኖት በመስጠት በመናገር ላይ ነው፡፡ ያልፋሉ "ያበቃሉ" Father “አባት” የሚለው ቃል በቋንቋችሁ በተለምዶ ለሰው አባት መጠሪያነት የሚትጠቀሙበትን ቃል ተጠቀሙ፡፡
አስተውሉ “አስተውሉ” ወይም “እያስተዋላችሁ” የሚለው ቃል ኃጢአትን እና ክፋትን ሁል ጊዜ መጠንቀቅ እና በንቃት መጠበቅን ያመለክታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ “ሁል ጊዜ ዝግጄ መሆንን” ማለትም ሊሆን ይችላል፡፡
የአውራ ዶሮ ጩኽት አውራ ዶሮ ጥዋት በማለዳ የሚያሰማው ጩኸት ነው፡፡ የአውራ ዶሮ በጥዋት የሚያሰማው ጩኸት የአውራ ዶሮ በጥዋት የሚያሰማው ጩኸት
1 ከሁለት ቀን በኋላ የፋሲካና የቂጣ በዓል ነበር፡፡ የካህናት አለቆችና ጸሓፍት እንዴት አድርገው በተንኮል ይዘው ሊገድሉት እንደሚችሉ ያስቡ ነበር፡፡ 2 ነገር ግን የህዝብ ሁከት እንዳይሆን በበዓል ቀን አይሁን ተባብለው ነበር፡፡ 3 እርሱም በቢታኒያ በለምጻሙ በስምዖን ቤት በማዕድ ተቀምጦ ሳለ አንዲት ሴት ዋጋው እጅግ የከበረ ሽቱ የያዘ የአልባስጥሮስ ጠርሙስ ይዛ መጣች፡፡ ጠርሙሱንም ሰብራ ሽቱውን በኢየሱስ በራሱ ላይ አፈሰሰች ፡፡ 4 ነገር ግን ከመካከላቸው አንዳንዶቹ እንዲህ ያለው የሽቱ ማባከን ያስፈለገው ለምንድነው በማለት የተበሳጩ አንዳንድ ሰዎች ነበሩ 5 ይህ ቅባት ከሦስተ መቶ ሽልንግ በላይ ተሸጦ ለድሆች ሊሰጥ ይቻል ነበር እያሉ በእርሷ ላይ አጉረመረሙ፡፡ 6 ኢየሱስ ግን ተዋት ለምን ታስቸግሯታላችሁ እርሷ መልካምን ነገር አድርጋልኛለች፡፡ 7 ድሆች ሁሉጊዜ ከእናንተ ጋር ናቸው በፈለጋችሁም ጊዜ መልካም ልታድጉላቸው ትችላላችሁ እኔን ግን ሁልጊዜ አታገኙኝም፡፡ 8 እርሷ ከመቃብር በፊት ሰውነቴን ሽቱ በመቀባት የምትችለውን አድርጋለች፡፡ 9 ደግሞም እውነት እላችኋለሁ ይህ ወንጌል በዓለም ዙሪያ በሚሰበክበት ጊዜ ሁሉ ይህች ሴት ያደረገችው ነገር ለመታሰቢያዋ ይነገራል አላቸው፡፡ 10 ከአስራ ሁለቱ አንዱ የሆነው የአስቆሮቱ ይሁዳ እንዴት አሳልፎ ይሰጠው ዘንድ ወደ ካህናት አለቆች ሄደ 11 እነርሱም በሰሙ ጊዜ ደስ አላቸው ገንዘብም ሊሰጡት ቃል ገቡለት፡፡እርሱም አሳልፎ ሊሰጠው አመቺ ጊዜ ይጠብቅ ነበር፡፡ 12 የፋሲካን መስዋዕት በሚያቀርቡበት በቂጣ በዓል የመጀመሪው ቀን ደቀመዛሙርቱ ፋሲካን ትበላ ዘንድ የት እናዛገጅልህ ብለው ጠየቁት፡፡ 13 እርሱም ከደቀመዛሙርቱ ሁለቱን ልኮ ወደ ከተማ ሂዱ ወዲያውም አንድ ሰው ውሃ ተሸክሞ ታገኛላችሁ ተከትላችሁትም ሂዱና 14 ወደሚገባበት ቤት ገብታችሁ የቤቱን ባለቤት መምህሩ ከደቀመዛሙርቴ ጋር ፋሲካን እበላ ዘንድ የእንግዳ ክፍሌ የትኛው ነው ብሎሀል ብላችሁ ጠይቁት 15 እርሱ ራሱ በሰገነት ላይ ያለ በቤት ዕቃ የተደራጀና የተዘጋጀ ሰፊ አዳራሽ ያሳያችኋል በዚያም አዘጋጁልን ፡፡ 16 ደቀመዛሙርቱም ወጥተው ወደ ከተማ መጡ ልክ እንዳላቸውም አገኙ ፋሲካንም አዘጋጁ፡፡ 17 በመሸም ጊዜ ከአስራ ሁለቱ ጋር መጣ፡፡ 18 ተቀምጠውም በመመገብ ላይ ኢየሱስ አውነት እላችኋለሁ በማዕድ ከኔ ጋር ያለ ከእናንተ አንዱ አሳልፎ ይሰጠኛል አላቸው፡፡ 19 እነርሱም እጅግ አዝነው በየተራ እኔ እሆንን ይሉት ጀምር፡፡ 20 ኢየሱስም ከእኔ ጋር ወደ ወጥ ሳህኑ የሚነክረውና ከአስራሁለቱ አንዱ ነው አላቸው፡፡ 21 የሰው ልጅስ ስለ እርሱ እንደተጻፈው ይሄዳል የሰው ልጅ አሳልፎ ለሚሰጠው ለዚያ ሰው ግን ወዮለት ባይወለድ ይሻለው ነበር አላቸው፡፡ 22 እየተመገቡም ሳለ እንጀራን አንስቶ ከባረከ በኋላ ቆርሶ ሰጣቸውና ውሰዱና ብሉ ይህ ስጋዬ ነው አላቸው፡፡ 23 እንዲሁም ጽዋውን አንስቶ አመስግኖ ለደቀመዛሙርቱ ሰጣቸው ሁሉም ጠጡ፡፡ 24 እርሱም ይህ ለብዙዎች የሚፈስ የቃል ኪዳን ደሜ ነው ፡፡ 25 እውነት እላችኋለሁ በእግዚአብሔር መንግስት እንደገና እንደ አዲስ እስከምጠጣበት ቀን ድረስ ከዚህ ወይን ከዚህ በኋላ አልጠጣም፡፡ 26 መዝሙርም ከዘመሩም በኋላ ወደ ደብረ ዘይት ተራራ ሄዱ፡፡ 27 ኢየሱስም እረኛውን እመታለው በጎቹም ይበታተናሉ ተብሎ እንደተጻፈ ሁላችሁ ትሰናከላላችሁ 28 ከተነሳሁ በኋላ ግን ወደ ገሊላ እቀድማችኋለሁ አላቸው፡፡ 29 ጴጥሮስም ሁሉ ቢሰናከሉ እኔ ግን አልሰናከልም አለው፡፡ 30 ኢየሱስም አውነት እልሃለሁ ዛሬ ሌሊት ዶሮ ሁለት ጊዜ ሳይጮህ ሶስት ጊዜ ትክደኛለህ አለው፡፡ 31 እርሱ ግን እጅግ እየጮኸ እስከሞት እንኳ ቢሆን አልክድህም አለው፡፡ ሌሎቹም እንደዚያው አሉ፡፡ 32 ጌቴ ሴማኒ ወደሚባል ሥፍራም መጡ፡፡ ደቀመዛሙርቱንም እስክ ጸልይ ድረስ በዚህ ተቀመጡ አላቸው፡፡ 33 ኢየሱስም ጴጥሮስን ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ ሄደ እጅግ ሊያዝንና ሊተክዝ ጀመረ፡፡ 34 ነፍሴ እስከሞት ድረስ እጅግ አዝናለች በዚህ ሆናችሁ ትጉ ንቁም አላቸው፡፡ 35 ጥቂትም ፈቀቅ ብሎ ሄደ፤ በግንባሩም ተደፍቶ የሚቻል ከሆነ ይህች ሰዓት ሰዓቲቱ እንድታልፍ መጸለይ ጀመረ፡፡ 36 አባት ሆይ ለአንተ ሁሉ ይቻላል ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ ነገር ግን የእኔ ሳይሆን የአንተ ፈቃድ ይሁን አለ፡፡ 37 ወደ እነርሱም መጣ ተኝተውም አገኛቸው ጴጥሮስንም ስምዖን ተኝተሀልን ለአንድ ሰዓት እንኳ ልትተጋ አልቻልክምን፡፡ 38 ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፡፡ መንፈስ ዝግጁ ነው ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው፡፡ 39 ተመልሶም ሄደና ያንኑ ቃል ደግሞ ጸለየ፡፡ 40 እንደገና ወደ ደቀመዛሙርቱ በመጣ ጊዜ አሁንም ተኝው አገኛቸው አይናቸው በእንቀልፍ ከብዶ ስለነበር የሚመልሱለትንም አያውቁም ነበር፡፡ 41 ለሦስተኛም ጊዜ ወደ እነርሱ መጣና እንግዲህስ ይበቃል ተኙ እረፉም የሰው ልጅ ለኃጢአተኞች አልፎ ይሰጥ ዘንድ ሰዓቲቱ ደርሳለች ፡፡ 42 ተነሱ እንሂድ እነሆ አሳልፎ የሚሰጠኝ በደጅ ነው አላቸው፡፡ 43 ወዲያውም ገና በመናገር ላይ ሳለ ከአስራ ሁለቱ አንዱ የነበረው የአስቆሮቱ ይሁዳ መጣ ፡፡ ከእርሱም ጋር ከካህናት አለቆች፣ ከጸሓፍትና ከሽማግሌዎች ዘንድ የተላኩ ብዙ ህዝብ ሠይፍና ቆመጥ ይዘው መጡ፡፡ 44 አሳልፎ የሚሰጠውም የምስመው እርሱ ነውና ያዙት በጥንቃቄ ውሰዱት ብሎ ምልክት ሰጥቷቸው ነበር፡፡ 45 በመጣም ጊዜ በቀጥታ ወደ ኢየሱስ ቀርቦ መምህር ሆይ ብሎ ሳመው፡፡ 46 እነርሱም ይዘው ወሰዱት፡፡ 47 ነገር ግን በዚያ ከቆሙት መካከል አንዱ ሰይፉን መዘዘ፤ የሊቀ ካህናቱን አገልጋይ ጆሮም ቆረጠው፡፡ 48 ኢየሱስም መልሶ ወንበዴ እንደምትይዙ ሰይፍና ቆመጥ ይዛችሁ ልትይዙኝ መጣችሁን 49 በየዕለቱ በቤተ መቅደስ እያስተማርከ ከእናንተ ጋር በነበርኩ ጊዘ አልያዛችሁኝም፡፡ ነገር ግን የተጻፈው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሆኗል አላቸው፡፡ 50 ሁሉም ትተውት ሸሹ፡፡ 51 እርቃኑን ከበፍታ በተሰራ ጨርቅ የሸፈነ አንድ ወጣት ይከተለው ነበር ሊይዙትም ባሉ ጊዜ 52 የበፍታ ጨርቁን ነጠላውን ትቶ ራቁቱን አመለጠ፡፡ 53 ኢየሱስንም ወደ ሊቀ ካህናቱ ይዘውት መጡ፡፡ የካህናት አለቆች፣ ሽማግሌዎችና ጸሓፍትም አብረውት መጡ፡፡ 54 ጴጥሮስም እስከ ሊቀካህናቱ ግቢ ድረስ በሩቅ ሆኖ ይከተለው ነበር፡፡ ከዚያም ከጠበቃዊዎች ጋር እሳት እየሞቀ ተቀመጠ፡፡ 55 ሊቀ ካህናቱና ጉባኤው ሁሉ በኢየሱስ ላይ ሞት የሚያስፈርድበት ምክንያት ይፈልጉ ነበር ነገር ግን ሊያገኙ አልቻሉም፡፡ 56 ብዙዎች በሀሰት ቢመሰክሩበትም ምስክርነታቸው እርስ በእርሱ የሚጣረስ ነበር፡፡ 57 ሦስት ሰዎችም ተነስተው በሀሰት መሰከሩበት እንዲህም አሉ 58 ይህንን በእጅ የተሰራ ቤተመቅደስ በሶስት ቀን አፍርሼ እንደገና በሶስት ቀን ውስጥ በእጅ ያልተሰራ ሌላ ቤተመቅደስ እሰራለሁ ሲል ሰምተነዋል ፡፡ 59 የእነርሱም ምስክርነት ቢሆን እርስ በእርሱ የሚጣረስ ነበረ፡፡ 60 ሊቀ ካህናቱም ተነስቶ በመካከል ቆመና ለሚመሰክሩብህ መልስ አትሰጥምን ብሎ ጠየቀው፡፡ 61 ኢየሱስ ግን ዝም አለ መልስም አልሰጠም፡፡ ሊቀ ካህናቱም በድጋሚ የቡሩኩ ልጅ መሲሁ አንተ ነህን ብሎ ጠየቀው 62 ኢየሱሰም አዎ ነኝ የሰው ልጅ በኃይሉ ቀኝ ተቀምጦ በሰማይ ደመና ሲመጣ ታዩታላችሁ አለው፡፡ 63 ሊቀካህናቱም ልብሱን ቀደደና ከእንግዲህ ምን ሌላ ምስክር ያስፈልጋል 64 እግዚአብሔርን ሲሳደብ ሰምታችኋል ታዲያ ምን ታስባለችሁ ፡፡ ሁሉም ሞት ይገባዋል አሉ፡፡ 65 አንዳነዶቹም ይተፉበት ፊቱንም ሸፍነው ትንቢት ተናገር እያሉ ያሾፉበት ጀመር፡፡ መኮንኖችም በእጃቸው እየጎሰሙ ወሰዱት፡፡ 66 ጴጥሮስም በሊቀ ካህናቱ ግቢ እሳት በመሞቅ ላይ ሳለ 67 አንዲት የሊቀ ክህናቱ የቤት ውስጥ ሠራተኛ አየችውና አንተ በትክክል ከናዝሬቱ ኢየሱስ ጋር ነበርክ አለችው፡፡ 68 እርሱ ግን የምትይውን አላውቀውም ምን እንደምታወሪም አልገባኝም ብሎ ካደ፡፡ ወደ ዋናው በር መግቢያ በሄደ ጊዜ ዶሮ ጮኸ 69 ሠራተኛይቱም አይታው በዚያ ላሉት ወታደሮች ይህ ከእነርሱ አንዱ ነው አለቻቸው፡፡ 70 እርሱ ግን እንደገና ካደ፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ በዚያ ከቆሙት መካከል አንዳንዶቹ ጴጥሮስን አንተ የገሊላ ሰው ስለሆንክ በትክክል ከእነርሱ አንዱ ነህ አሉት፡፡ 71 እርሱም የምትሉትን ሰው አላውቀውም ብሎ መማልና መራገም ጀመረ፡፡ 72 ወዲያውም ለሁለተኛ ጊዜ ዶሮ ጮኸ ጴጥሮስም ኢየሱስ ዛሬ ሌሊት ዶሮ ሁለት ጊዜ ሳይጮህ ሶስት ጊዜ ትክደኛለህ ያለውን ቃል አስታወሰ ነገሩንም ባሰበ ጊዜ አለቀሰ፡፡
ለምጻሙ ስምዖን ይህ ሰው ከከዚህ በፊት ለምጽ ያለበት ቢሆንም አሁን ግን ታሞ አይደለም፡፡ አልባስጥሮስ ይህ ለስላሳ “ነጭ ድንጋይ” ነው፡፡ የዚህ ሁሉ ብክነት ምክንያቱ ምንድ ነው? አማራጭ ትርጉም፡ "እንዲህ ዓይነቱን ውድ ሽቶ ለማባከን የሚሆን ምንም በቂ ምክንያት የለም፡፡” ይህ ሽቶ ልሸጥ ይችላል "ይህንን ሽቶ ሽጠን” ወይም “ይህንን ሽቶ ሽጣ” ሦስት መቶ ዲናር "300 ዲናር፡፡" ዲናር የሮማዊያን የብር ሳንቲም ነው፡፡
ስለምን ታደክሙአታላችሁ? አማራጭ ትርጉም፡ “ልታስቸግሯት አይገባም፡፡"
ማርቆስ 14፡10-11 የአስቆሮቱ ይሁዳ ይህንን በ [MRK 3:17]
የእንግዳ ማረፍያ ክፍል an extra room for visitors ለእንግዶች ማረፊያነት የሚዘጋጅ ትርፍ ክፍል
በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ ሳለ በምግብ የጠረጴዛ ዙሪያ እንግዶች ተቀምጠው ሳለ፡፡ አንድ በአንድ ይህ ማለት “ተራ በተራ” እያንዳንዱ ደቀ መዝሙር እንዲህ ሲል ጠየቀው፡፡ እኔ አይደለሁም "በእርግጠኝነት ጠላቶችህ እንዲይዙህ የማግዛቸው እኔ አይደለሁም!"
ማርቆስ 14፡ 22-25
መዝሙር፡፡ የመዝሙር ዓይነት ነው፡፡ በዚህ ወቅት የብሉይ ኪዳን መዝሙር መዘመር ባሕል ነበር፡፡
መዝሙር፡፡ የመዝሙር ዓይነት ነው፡፡ በዚህ ወቅት የብሉይ ኪዳን መዝሙር መዘመር ባሕል ነበር፡፡
እውነት እውነት አልሃለሁ ይህንን በ MRK 11:22 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ትክደኛለህ "አላውቀውም ትላለህ”
ነፍስ “ነፍስ” የሚለው ቃል አንዳንድ ጊዜ ሙሉ ሰውን ለማመልከት በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል፡፡
ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ "እያለፈበት ያለውን መከራ መቋቋም የሚያስችለው ጥንካሬ ያስፈልገዋ፡፡” አባ "አባ" የግሪክ ቃል ሲሆን ልጆች አባታቸውን ለመጥራት የሚጠቀሙበት ቃል ነው፡፡ ይህ ቅርብ የሆነ ግነንኙነት መኖሩን ያሳያል፡፡ ይህ ቃል ኢየሱስ አባቱን የጠራበትን መንገድ የሚሳይ በመሆኑ ይህንን የግሪክ ቃል በትርጉማችሁ ውስጥ እንዳለ መስቀመጡ አስፈላጊ ነው፡፡ ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ ጽዋ የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስ ለሸከመው ያለውን የእግዚአብሔር ቁጣን ነው፡፡ ኢየሱስ . . .. አንዲህ አለ፣ "አባ አባት . . . ይህን ጽዋ ከእነተ አሳልፍ፡፡ ይሁን እንጂ የኔ ፈቃድ ሳይሆን የአንተ ፈቃድ ይሁን፡፡" ኢየሱስ አባቱን ለሰው ልጆች ኃጢአት ሲል የሚቀበለውን መከራ ይተውለት ዘነድ አባቱን ይጠይቃል፡፡ ነገር ግን አባቱ የእርሱን ብቸኛ፣ ፍጹም ልጅ መስዋእትነት ለእርሱ የማይቆጠር ቅድስና ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ የመስቀልን መከራ ተቀበለ፡፡ አባት ይህ የእግዚአብሔር አባት ወሳኝ የማዕረግ ስሙ ነው፡፡
ተኝተው አገኛቸው "ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ እና ዮሐንስ ተንኝተው አገኛቸው" ስምኦን ተኝተሃልን "አትተኙ ንቁ ቢዬአችሁ ሳለ አንተ ስምኦን ተኝታችኋልን ነቅታቹ ለአንድ ሰዓት እንኳ መጠበቅ አቃታችሁን? "ነቅታችሁ መቆየት ፈጽሞ አቃታችሁን" መንፈስስ ተዘጋጅታለች፥ ሥጋ ግን ደካማ ነው "አእምሮዋችሁ ማድረግ የሚፈልገውን ነገር አካላችሁ ማድረግ አይችልም፡፡" ሥጋ "አካል"
ተኝተው አገኛቸው "ጴጥሮስ፣ ዮሐንስ እና ያዕቆብ ተኝተው ነበር" አሁንም ተኝታችኋልን? አማራጭ ትርጉም፡ "አሁንም ተኘንታችኋልን1 እረፍት እያደረጋችሁ ነውን!"
እጃቸውን ጫኑበት "ያዙት"
ወንበዴ እንደምትይዙ ሰይፍና ጐመድ ይዛችሁ ልትይዙኝ መጣችሁን? "ወንበዴ ለመያዝ እንደሚመጣ ሰው ሰይፍ እና ጎመድ ይዛችሁ እኔን ለመያዝ መጣችሁ፡፡”
ነጠላ ከጥጥ ፈትል የሚሠራ ልብስ
ሰምተነዋል “እኛ” የሚለው ቃል በኢየሱስ ላይ በሐሰት የመሰከሩበትን ሰዎችን ያመለክታል፡፡
ከእርሱ መካከል ቆሞ ነበር "ከካህናት አለቆች፣ ጸሐፍት እና ሽማግሌዎች መካከል ቆሞ" እኔ ነኝ ይህ ቃል በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥ እግዚአብሔር ራሱን የጠራበት ቃል ነው፡፡
ልብሱን ቀደደ ኢየሱስ በተናገረው ቃል መቆጣጡት የሚያሳይ ምልክት ነው ሁሉም ፈረዱበት "ሸንጎው ሙሉ ለሙሉ በኢየሱስ ላይ ፈረደ"
ከእነርሱ መካከል አንዱ "ከደቀ መዛሙርቱ መካከል አንዱ"
ተሰበረ “ተሰበረ” የሚለው ቃል በጣም መደንገጡን ወይም በጣም ማዘኑን የሚያሳይ ነው፡፡
1 ወዲያውኑም በማለዳ የካህናት አለቆች ከሽማግሌዎች፣ ከጸሓፍት፣ ከሸንጎም አባሎችም ሁሉ ጋር ተማከሩ፤ ኢየሱስን አስረው ወሰዱትና ለጲላጦስ አሳልፈው ሰጡት። 2 ጲላጦስም፣አንተ የአይሁድ ንጉሥ ነህን? ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስም ሲመልስ አንተ እንዳልከው ነኝ አለው። 3 የካህናት አለቆችም ብዙ ክስ አቀረቡበት። 4 ጲላጦስም ስንት ክስ እንዳቀረቡብህ ተመልከት! ምንም አትመልስምን? ብሎ እንደገና ጠየቀው። 5 ኢየሱስ ግን ጲላጦስ እስኪደነቅ ድረስ ምንም መልስ አልሰጠም። 6 በየበዓሉ ሕዝቡ ጲላጦስ እንዲፈታላቸው የጠየቁትን አንድ እስረኛ የመፍታት ልማድ ነበረው። 7 በዚያም ኹከት ቀስቅሰው ግድያ ከፈጸሙ ሰዎች ጋር የታሰረ አንድ በርባን የሚባል ሰው ነበር። 8 ሕዝቡም ወደ ጲላጦስ ቀርበው የተለመደውን እንዲያደርግላቸው ጠየቁት። 9 ጲላጦስም "የአይሁድን ንጉሥ" እንድፈታላችሁ ትፈልጋላቸሁን? አላቸው። 10 እንዲህ ያለው የካህናት አለቆች ኢየሱስን አሳልፈው የሰጡት በቅናት መሆኑን ያውቅ ስለ ነበር ነው። 11 የካህናት አለቆች ግን በእርሱ ፈንታ በርባን እንዲፈታላቸው ጲላጦስን እንዲጠይቁ ሕዝቡን ቀሰቀሱ። 12 ጲላጦስም መልሶ ታዲያ በዚህ የአይሁድ ንጉሥ ብላችሁ በምትጠሩት ሰው ላይ ምን ላድርግበት? አላቸው። 13 እነርሱም "ስቀለው!" እያሉ እንደገና ጮኹ። 14 ጲላጦስም "ለምን? ምን በደል ፈጽሟል?" አላቸው። እነርሱም "ስቀለው!" እያሉ አብዝተው ጮኹ። 15 ጲላጦስም ሰዎቹን ደስ ለማሰኘት ብሎ በርባንን ፈቶ ለቀቀላቸው፤ኢየሱስን ግን አስገርፎ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጠው። 16 ወታደሮቹም ኢየሱስን ፕራይቶሪዮን ወደሚባለው ግቢ ወሰዱት፤ወታደሮቹንም ሁሉ ጠሩ፤ 17 ሐምራዊ ልብስ አለበሱት፤ የእሾኽ አክሊልም በራሱ ላይ ደፉበት፡፡ 18 "የአይሁድ ንጉሥ ሆይ! ሰላም ለአንተ ይሁን!" እያሉ ሰላምታ ይሰጡት ነበር። 19 በመቃ ዐናቱን እየመቱ፤ ምራቃቸውን ተፉበት፤ በፊቱም ተንበርክከው ሰገዱለት። 20 አላግጠውበትም ሐምራዊውን ልብስ አወለቁበት፤ የራሱንም ልብስ አልብሰው፤ሊሰቅሉ ወሰዱት። 21 በመንገድ ሳሉም የቀሬና ሰው የሆነውን የእስክንድርንና የሩፎስን አባት ስምዖንን ከገጠር ሲመጣ አግኝተው፤ የኢየሱስን መስቀል ተሸክሞ ከእነርሱ ጋር እንዲሄድ አስገደዱት። 22 ከዚያም በኋላ ኢየሱስን ጎልጎታ ተብሎ ወደሚጠራው ቦታ ወሰዱት፤ ትርጉሙም፡- "የራስ ቅል ስፍራ" ማለት ነው። 23 ከከርቤ ጋር የተቀላቀለ የወይን ጠጅም ሰጡት፤ እርሱ ግን አልጠጣውም። 24 ከዚያም ሰቀሉት፤ ልብሶቹንም ማን ምን እንደሚወስድ ዕጣ ተጣጥለው ተከፋፈሉ። 25 ከጧቱ ሦስት ሰዓት ሲሆን ሰቀሉት፡፡ 26 "የአይሁድ ንጉሥ" የሚል የክስ ጽሑፍ በመስቀሉ ዐናት ተጽፎ ነበር። 27 ከኢየሱስም ጋር ሁለት ወንበዴዎችን አንዱን በቀኙ፣አንዱንም በግራው ሰቀሉ። 28 መጽሓፍ "ከዐመፀኞች ጋር ተቈጠረ፤" የሚለው ቃል ተፈጸመ። 29 በአጠገቡ ያልፉ የነበሩትም ሰዎች ራሳቸውን በንቀት እየነቀነቁ እንዲህ በማለት ይሰድቡት ነበር፣ "አንተ ቤተ መቅደስን አፍርሰህ በሦስት ቀን የምትሠራ ሆይ! 30 እስቲ አሁን ራስህን አድን፤ከመስቀልም ውረድ!" 31 እንደዚሁም የካህናት አለቆች ከጸሓፍት ጋር ሆነው እርስበርሳቸው እንዲህ እያሉ ያፌዙበት ነበር፤ "ሌሎችን አድኖአል፤ ራሱን ማዳን ግን አይችልም" አሉ፡፡ 32 "አይተን እንድናምንበት መሲሑ የእስራኤል ንጉሥ እስቲ አሁን ከመስቀል ይውረድ" ከእርሱ ጋር የተሰቀሉት ወንበዴዎችም ይሰድቡት ነበር። 33 ከቀኑም ስድስት ሰዓት ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድሪቱ ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ። 34 ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን ኢየሱስ፣ "ኤሎሄ፣ ኤሎሄ፣ ላማሰበቅታኒ፤" ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ትርጓሜውም "አምላኬ፣ አምላኬ ለምን ተውከኝ?" ማለት ነው። 35 በዚያም ቆመው ከነበሩት ሰዎች አንዳንዶቹ ሰምተው "እነሆ! ኤልያስን ይጣራል፤" አሉ። 36 ከእነርሱም አንዱ ሮጠና ሆምጣጤ በሰፍነግ ሞላ፤ "ኤልያስ መጥቶ ያወርደው እንደ ሆነ እንይ" አለ።እንዲጠጣውም በመቃ ላይ አድርጎ ለኢየሱስ ሰጠው፡፡ 37 ከዚያም ኢየሱስ በታላቅ ድምፅ ጮኸ፤ መንፈሱንም ሰጠ። 38 የቤተ መቅደሱም መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ተቀዶ ከሁለት ተከፈለ። 39 በመስቀሉ ፊት ለፊት ቆሞ የነበረ የመቶ አለቃ ኢየሱስ እንዴት መንፈሱን እንደ ሰጠ ባየ ጊዜ፣ "ይህ ሰው በእርግጥ የእግዚአብሔር ልጅ ነበር፤" አለ። 40 በሩቅ ሆነው የሚመለከቱ ሴቶችም በዚያ ነበሩ። ከእነርሱም መካከል መግደላዊት ማርያም፣ የታናሹ ያዕቆብና የዮሳ እናት ማርያም፣ሰሎሜም ነበሩ። 41 እነርሱ ኢየሱስ በገሊላ በነበረበት ጊዜ ይከተሉትና ያገለግሉት ነበር። እንዲሁም ከኢየሱስ ጋር ወደ ኢየሩሳሌም የመጡ ሌሎች ብዙ ሴቶችም ነበሩ። 42 መሽቶ ስለ ነበርና የሰንበት ዋዜማና ለሰንበት የመዘጋጃ ጊዜ ስለ ነበር፡፡ 43 የተከበረ የሸንጎ አባል የነበረ ዮሴፍ የሚባል የአርማትያስ ሰው መጣ። እርሱም የእግዚአብሔርን መንግሥት የሚጠባበቅ ሰው ነበር። በድፍረትም ወደ ጲላጦስ ፊት ቀርቦ የኢየሱስን አስከሬን እንዲሰጠው ለመነው። 44 ጲላጦስም "እንዴት እንዲህ በቶሎ ሞተ?" ብሎ ተደነቀ። የመቶ አለቃውንም ጠርቶ፣ "ከሞተ ቈይቶአልን?" ሲል ጠየቀው። 45 የኢየሱስን መሞት ከመቶ አለቃው ከሰማ በኋላ አስከሬኑን እንዲወስድ ለዮሴፍ ፈቀደለት። 46 ዮሴፍም የከፈን ልብስ ገዛ፤ የኢየሱስን አስከሬን ከመስቀል አውርዶ ገነዘው፤ ከዐለት ተወቅሮ በተዘጋጀ መቃብር ውስጥ አስቀመጠው። ትልቅ ድንጋይም አንከባሎ የመቃብሩን መግቢያ ዘጋ። 47 መግደላዊት ማርያምና የዮሳ እናት ማርያምምሰ ኢየሱስን የት እንዳኖሩት አዩ።
አንተ አልክ "አንተ ራስህ መሰከርክ፡፡"
ማርቆስ 15፡ 9-11 ለቀቁት "እንዲሄድ ፈቀዱለት" ወይም "ፈቱት"
ማርቆስ 15፡ 12-13
ኢየሱስን ገረፉት በልዩ መግረፊያ ኢየሱስን እንዲያመው አድርገው ገረፉት አሳልፈው ሰጡት ይህንን በ MRK 15:1 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
የወታደሮች ካንፕ ይህ ወታደሮች የሞቆዩበት ሥፍራ ነው፡፡ ጭፍራ "በጣም ብዙ” ወይም “ ብዙ” ቀይ ልብስም አለበሱት፥ ይህ የመሳለቅ ምልክት ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ቀለም ያለው ልብስ የነገስታት ልብስ ሲሆን ይህንን ዓይነት ልብስ እርሱን በማልበስ “የአይሁድ ንጉሥ” በሚለው የኢየሱስ የማዕረግ ስሙ ላይ እየጠሳለቁ ነበር፡፡" እንዲህ እያሉ ይሰግዱለትም ጀመር፣ “የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን እያሉ እጅ ይነሱት ጀመር፤” እንደገና ወታደሮቹ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉሥ መሆኑን ስላላመኑበት በኢየሱስ ላይ ይሳለለቁ ነበር፡፡
ወንበዴዎች "የታጠቁ ዘራፊዎች"
የሚቆመጥት ወይን "ኮምጣጤ" የቤተ መቅደሱ መጋረጃ ለሁለት ተቀደደ የቤተ መቅደሱን መጋረጃ እግዚብሔር ሁለት ቦታ ቀደደው፡፡
የእግዚአብሔር ልጅ ይህ የኢየሱስ ወሳኝ የሆነ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ሰሎሜ
መከፈኛ ጨርቅ ከጥጥ ተክል የተሠራ ልብስ (ይህንን በ14፡ 51-52 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡) ኢየሱስ የተቀበረበት ሥፍራ "ዮሴፍ እና ሌሎች የኢየሱስን በድን የቀበሩበት ሥፍራ"
1 ሰንበት ካለፈ በኋላም መጥተው ይቀቡት ዘንድ መግደላዊት ማርያም፣ የያዕቆብ እናት ማርያምና ሰሎሜ ሽቶ ገዙ፡፡ 2 ከሳምንቱም በመጀመሪያው ቀን ጎህ በቀደደ ጊዜ ወደ መቃብሩ መጡ፡፡ 3 እርስ በርሳቸውም ድንጋዩን ከመቃብሩ መግቢያ ማን ያንከባልልናል ይባባሉ ነበር፡፡ 4 አሻግረው ሲመለከቱም ድንጋዩ እጅግ ትልቅ ነበርና ተንከባሎ አዩት፡፡ 5 ወደ መቃብሩም ገብተው የሚያንጸባርቅ ነጭ ልብስ የለበሰ አንድ ወጣት በስተቀኝ ተቀምጦ አዩና ተገረሙ፡፡ 6 እርሱም አትገረሙ፣ የምትፈልጉት ተሰቅሎ የነበረውን የናዝሬቱን ኢየሱስን ነው፡፡ ያኖሩበትን ቦታ ተመልከቱ፤ እርሱ በዚህ የለም፣ ተነሥቷል፡፡ 7 ነገር ግን ሂዱ፣ ለጴጥሮስና ለደቀመዛሙርቱም እንደነገራችሁ ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል፣ በዚያም ታዩታላችሁ ብላችሁ ንገሯቸው አላቸው፡፡ 8 እነርሱም መገረምና ፍርሃት ወድቆባቸው ነበርና ከዚያ ወጥተው ከመቃብሩ ሸሹ፡፡ ፈርተውም ነበርና ለማንም አንዳች አልተናገሩም፡፡ 9 ከሳምንቱም በመጀመሪያው ቀን በማለዳ በተነሳ ጊዜ ሰባት አጋንንት አውጥቶላት ለነበረችው ለመግደላዊት ማርያም አስቀድሞ ታያት፡፡ 10 እርሷም ከኢየሱስ ጋር የነበሩት እያዘኑና እያለቀሱ ሳሉ ሄዳ ነገረቻቸው፡፡ 11 እነርሱም ሕያው እንደሆነና ለእርሷም እንደታያት በሰሙ ጊዜ አላመኑም፡፡ 12 ከእነዚህ ነገሮች በኋላም ከእነርሱ ሁለቱ ወደ ገጠር በመሄድ ላይ ሳሉ ኢየሱስ በሌላ ሰው መልክ ተገለጠላቸው፡፡ 13 እነርሱም ሄደው ለተቀሩት ነገሯቸው፤ እነርሱንም አላመኗቸውም፡፡ 14 ከዚያም በማዕድ ተቀምጠው ሳሉ ለአሥራ አንዱ ለራሳቸው ኢየሱስ ተገለጠላቸውና ስለ ልባቸው ጥንካሬና ከትንሳኤው በኋላ ያዩትን ስላላመኗቸው ወቀሳቸው፡፡ 15 እንዲህም አላቸው፣ ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፣ ወንጌልንም ለፍጥረት በሙሉ ስበኩ አላቸው፡፡ 16 ያመነና የተጠመቀም ይድናል፣ ያላመነ ግን ይፈረድበታል፡፡ 17 ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሏቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፣ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ፣ 18 እባቦችን ይይዛሉ፣ የሚገድል ነገር እንኳን ቢጠጡ አይጎዳቸውም፣ እጆቻቸውን በህሙማን ላይ ይጭናሉ እነርሱም ይፈወሳሉ፡፡ 19 ጌታ ኢየሱስ ይህንን ካላቸው በኋላ ወደ ሰማይ ወጥቶም በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ፡፡ 20 እነርሱም ወጥተው በየቦታው ሰበኩ፡፡ ጌታም ቃሉን ተከትለው በሚመጡ ምልክቶች እያጸና ከእነርሱ ጋር ይሠራ ነበር፡፡ አሜን፡፡
ቆንጆ ሽታ የሚሸት "ጥሩ መዓዛ ያለው"
ተነስቷል! "እርሱ ተነስቷል" ወይም "እግዚአብሔር ከሞት አስነስቶታል!" ወይም "ከሞት በራሱ ተነስቷል!"
በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን "በሰንበት"
የልብ ድንዳኔ አማራጭ ትርጉም፡ "ለማመን አለመፈለግ"
ማርቆስ 16፡ 17-18
No text
1 ብዙዎች በእኛ ዘንድ ስለተፈጸሙት ጉዳዮች ታሪኩን በቅደም ተከተል ለማስቀመጥ ሞክረዋል፣ 2 ይህም የዓይን ምስክሮችና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት በመጀመሪያ ለእኛ ባስተላለፉልን መሠረት ነበር፡፡ 3 ስለሆነም፣ እጅግ የተከበርክ ቴዎፍሎስ ሆይ፣ እኔም የእነዚህን ነገሮች ሂደት ከመጀመሪያው በትክክል ከመረመርኩ በኋላ፣ በቅደም ተከተላቸው መጻፍ መልካም መስሎ ታየኝ፡፡ 4 ይህንንም ያደረግሁት ስለ ተማርኸው ነገር እውነቱን ታውቅ ዘንድ ነው፡፡ 5 በይሁዳ ገዢ፣ በሄሮድስ ዘመን ከአብያ ክፍል የሆነ ዘካርያስ የሚባል አንድ ካህን ነበረ፡፡ ሚስቱም ከአሮን ልጆች የነበረችና ስሟም ኤልሳቤጥ የሚባል ነበር፡፡ 6 ሁለቱም በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ፣ የእግዚአብሔርን ሕግጋትና ትእዛዛት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየጠበቁ ይኖሩ ነበር፡፡ 7 ነገር ግን ኤልሳቤጥ መካን ስለነበረች ልጅ አልነበራቸውም፣ በዚህ ጊዜ ደግሞ ሁለቱም አርጅተው ነበር፡፡ 8 በዚህን ጊዜ፣ ዘካርያስ በክፍሉ ተራ የክህነት አገልግሎቱን እየፈጸመ በእግዚአብሔር ፊት የሚሆንበት ጊዜ ደረሰ፡፡ 9 የትኛው ካህን እንደሚያገለግል ለመምረጥ በሚፈጸመው ልምድ መሠረት፣ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ገብቶ ዕጣን ዕጣ ደረሰው፡፡ 10 እርሱ ዕጣን በሚያጥንበት ወቅት፣ ሕዝቡ ሁሉ በውጭ ይጸልይ ነበር፡፡ 11 በዚህን ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠለትና በዕጣኑ መሠዊያ በስተቀኝ ቆመ፡፡ 12 ዘካርያስ በተመለከተው ጊዜ ደነገጠ፣ ፍርሃትም በእርሱ ላይ ወደቀ፡፡ 13 ነገር ግን መልአኩ፣ “ጸሎትህ ተሰምቶአልና ዘካርያስ ሆይ፣ አትፍራ፡፡ ሚስትህ ኤልሳቤጥ ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፤ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ፡፡ 14 ሐሴትና ደስታ ይሆንልሃል፣ ብዙዎችም በእርሱ መወለድ ሐሴት ያደርጋሉ፡፡ 15 በእግዚአብሔር ፊት ታላቅ ይሆናልና፣ ወይን ጠጅ ወይም የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ከእናቱ ማሕፀን ጀምሮም በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ ይሆናል፡፡ 16 ከእስራኤል ሕዝብም ብዙዎቹ ወደ ጌታ ወደ አምላካቸው ይመለሳሉ፡፡ 17 በእግዚአብሔርም ፊት በኤልያስ መንፈስና ኃይል ይመላለሳል፡፡ ይህንንም የሚያደርገው የማይታዘዙት በጻድቃን ጥበብ ይሄዱ ዘንድ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች ለመመለስና የተዘጋጁትን ሕዝብ ለእግዚአብሔር ያዘጋጅ ዘንድ ነው” አለው፡፡ 18 ዘካርያስም፣ “እኔ ያረጀሁ በመሆኔና ሚስቴም ዕድሜዋ የገፋ በመሆኑ፣ ይህንን እንዴት ማወቅ እችላለሁ?” አለ፤ 19 መልአኩም፣ “እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፤ ይህንን የምሥራች እነግርህ ዘንድ ተልኬያለሁ፡፡ 20 እነሆ፣ እነዚህ ነገሮች እስኪፈጸሙ ድረስ ጸጥ ትላለህ፣ መናገርም አትችልም፡፡ ይህም የሚሆነው በትክክለኛው ጊዜ የሚፈጸመውን ቃሌን ስላላመንክ ነው፡፡” 21 በዚህን ጊዜ ሕዝቡ ዘካርያስን እየተጠባበቁ ነበር፣ ለረጅም ጊዜ በቤተ መቅደስ በመቆየቱም ተደነቁ፡፡ 22 በወጣ ጊዜ ግን ሊያነጋግራቸው አልቻለም፤ እነርሱም በቤተ መቅደስ በነበረበት ጊዜ ራእይ እንደ ተገለጠለት ተገነዘቡ፡፡ ለእነርሱ ምልክት ብቻ እየሰጣቸው ጸጥ ብሎ ቆየ፡፡ 23 የአገልግሎቱም ወቅት እንዳበቃ ወደ ቤቱ ለመመለስ ተነሣ፡፡ 24 ከዚህም ወቅት በኋላ ሚስቱ ኤልሳቤጥ ፀነሰች፤ ለአምስት ወራትም ራሷን ሰወረች፣ እንደዚህም አለች፣ 25 “በሕዝብ ዘንድ የነበረብኝን ነቀፌታ ለማስወገድ ብሎ በሞገስ ተመልክቶኝ እግዚአብሔር ለእኔ ያደረገልኝ ይህንን ነው፡፡” 26 ስድስት ወሯ በነበረ ጊዜ መልአኩ ገብርኤል ናዝሬት ወደተባለች የገሊላ ከተማ ተላከ፡፡ 27 የተላከውም ዮሴፍ ለተባለ ከዳዊት ነገድ ለሆነ ሰው ወደ ታጨች አንዲት ድንግል ነበር፡፡ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበር፡፡ 28 ወደ እርሷም መጣና እንደዚህ አላት፣ “እጅግ የተከበርሽ ሆይ፣ ሰላም ለአንቺ ይሁን! እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነው፡፡” 29 እርሷ ግን በንግግሩ በጣም ግራ ተጋባች፣ ምን ዓይነት ሰላምታ ሊሆን እንደሚችልም በማሰብ ተደነቀች፡፡ 30 መልአኩም፣ “ማርያም ሆይ፤ አትፍሪ፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስ አግኝተሻል፤ 31 እነሆ፣ ፅንስ በማሕፀንሽ ውስጥ ይፀነሳል፣ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፡፡ ስሙንም ‘ኢየሱስ’ ትይዋለሽ፡፡ 32 እርሱም ታላቅ ይሆናል፣ የልዑልም ልጅ ይባላል፡፡ እግዚአብሔር አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፡፡ 33 በያዕቆብም ቤት ላይ ለዘላለም ይነግሣል፣ ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም፡፡" 34 ማርያምም ለመልአኩ፣ “ከማንም ወንድ ጋር ተኝቼ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል?” አለችው፡፡ 35 መልአኩም እንደዚህ በማለት መለሰላት፣ “መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፣ የልዑል ኃይልም በአንቺ ላይ ያርፋል፤ ከዚህ የተነሣም የሚወለደው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል፡፡ 36 እነሆ፣ ዘመድሽም ኤልሳቤጥ በእርጅናዋ ወንድ ልጅ ፀንሳለች፤ መካን ትባል ለነበረችው ለእርሷ ይህ ስድስተኛ ወሯ ነው፡፡ 37 ለእግዚአብሔር የሚሳነው ምንም ነገር የለምና፡፡” 38 ማርያምም፣ “እነሆ፣ የእግዚአብሔር ባሪያው ነኝ፤ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ፡፡” ከዚያ በኋላም መልአኩ ትቷት ሄደ፡፡ 39 ከዚያ በኋላ፣ ማርያም ተነሥታ በእነዚያ ቀናት በኮረብታማው አገር በይሁዳ ወዳለች ወደ አንዲት ከተማ በፍጥነት ሄደች፡፡ 40 ወደ ዘካርያስም ቤት ሄደችና ለኤልሳቤጥ ሰላምታ አቀረበችላት፡፡ 41 ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ፣ እንደዚህ ሆነ፣ በማሕፀኗ ያለው ፅንስ ዘለለ፣ ኤልሳቤጥም በመንፈስ ቅዱስ ተሞላች፡፡ 42 ድምፅዋን ከፍ በማድረግ ጮክ ብላ፣ “ከሴቶች መካከል አንቺ የተባረክሽ ነሽ፣ የማሕፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው፡፡ 43 የጌታዬ እናት ወደ እኔ እንድትመጣ ይህ ለምን ሆነ? 44 እነሆ፣ የሰላምታሽ ድምፅ ወደ ጆሮዬ በመጣ ጊዜ በማሕፀኔ ውስጥ ያለው ሕፃን በደስታ ዘለለ፡፡ 45 ከጌታ የተነገሩላት ነገሮች እንደሚፈጸሙ የምታምን እነሆ እርሷ የተባረከች ናት፡፡” 46 ከጌታ የተነገሩላት ነገሮች እንደሚፈጸሙ የምታምን እነሆ እርሷ የተባረከች ናት፡፡” 46. ማርያምም፣ “ነፍሴ እግዚአብሔርን ታመሰግናለች፣ 47 መንፈሴም በመድኃኒቴ በእግዚአብሔር ሐሴት ታደርጋለች፡፡ 48 የሴት ባሪያውን ውርደት ተመልክቶአልና፡፡ እነሆ፣ ከዚህ በኋላ ትውልድ ሁሉ የተባረከች ይሉኛል፡፡ 49 ብርቱ የሆነ እርሱ ለእኔ ታላቅ ነገር አድርጎልኛልና፣ ስሙም ቅዱስ ነው፡፡ 50 ለሚያከብሩት ምሕረቱ ከትውልድ እስከ ትውልድ ነው፡፡ 51 በክንዱ ብርታትን ገልጾአል፣ ስለ ልባቸው ሐሳብ የሚታበዩትን በትኖአቸዋል፡፡ 52 ገዢዎችን ከዙፋናቸው አውርዷቸዋል፣ ዝቅ ያሉትንም ከፍ አድርጓቸዋል፡፡ 53 የተራቡትን በመልካም ነገር አጥግቧቸዋል፣ ባለጠጎችን ግን ባዶአቸውን ሰድዷቸዋል፡፡ 54 ምሕረት ማድረጉን ያስታውስ ዘንድ ለባሪያው ለእስራኤል ረድኤቱን ልኮለታል፣ 55 ይህንንም ያደረገው (ለአባቶቻችን እንደተናገረው) ለአብርሃምና ለዘሩ ለዘላለም፡፡” 56 ማርያም ከኤልሳቤጥ ጋር ሦስት ወራት ያህል ተቀመጠች፣ ከዚያ በኋላም ወደ ቤቷ ተመለሰች፡፡ 57 በዚያን ጊዜ ኤልሳቤጥ የምትወልድበት ወቅት ደረሰ፣ ወንድ ልጅም ወለደች፡፡ 58 ጎረቤቶቿና ዘመዶቿ እግዚአብሔር ምሕረቱን እንዳበዛላት ሰሙ፣ ከእርሷም ጋር ደስ አላቸው፡፡ 59 ልጁን የሚገርዙበት ስምንተኛው ቀን በመጣ ጊዜ፣ በአባቱ ስም ዘካርያስ ብለው ሊሰይሙት ፈልገው ነበር፡፡ 60 እናትዬዋ ግን መልስ ሰጠቻቸው፣ “አይሆንም፣ ስሙ ዮሐንስ ይሆናል” አለች፡፡ 61 እነርሱም ለእርሷ፣ “ከዘመዶችሽ መካከል በዚህ ስም የተጠራ የለም” አሏት፡፡ 62 በምን ስም እንዲጠራ እንደሚፈልግ አባቱን በምልክት ጠየቁት፡፡ 63 አባቱም ሰሌዳ እንዲያቀርቡለት ጠየቀና፣ “ስሙ ዮሐንስ ነው” ብሎ ጻፈ፡፡ በዚህም ሁሉም ተደነቁ፡ 64 ወዲያውኑም አንደበቱ ተከፈተ፣ ምላሱም ተፈትቶ ተናገረ፣ እግዚአብሔርንም አመሰገነ፡፡ 65 በዙሪያቸውም በሚኖሩት ሰዎች ዘንድ ፍርሃት መጣባቸው፣ የእነዚህም ነገሮች ዜና በኮረብታማው በይሁዳ አገር ሁሉ ተሠራጨ፡፡ 66 ዜናውን የሰሙትም ሁሉ፣ የእግዚአብሔር እጅ ከእርሱ ጋር ነበርና “እንግዲህ ይህ ልጅ ምን ሊሆን ይሆን?” እያሉ ነገሩን በልባቸው ጠበቁት፡፡ 67 አባቱም ዘካርያስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ፣ 68 “የእስራኤል አምላክ፣ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን፣ የመቤዠት ሥራ በመሥራት ሕዝቡን ረድቶታልና፡፡ 69 ከባሪያው ከዳዊት ዝርያዎች መካከል ለባሪያው ለዳዊት ቤት የድነት ቀንድ አስነሥቶልናል፡፡ 70 ይህም በጥንት ዘመን በነበሩት በቅዱሳን ነቢያቱ እንደ ተናገረው ነው፡፡ 71 ከጠላቶቻችንና ከሚጠሉን ሁሉ ያድነናል፡፡ 72 ይህንን የሚያደርገው ለአባቶቻችን ምሕረቱን ለማሳየትና ቅዱስ ኪዳኑን፣ 73 ማለትም ለአባታችን ለአብርሃም የማለውን መሐላ ለማስታወስ ነው፡፡ 74 መሐላውን የማለውም እኛ ከጠላቶቻችን ድነን በዘመኖቻችን ሁሉ በእርሱ ፊት በመሆን ያለ ፍርሃት፣ 75 በቅድስናና በጽድቅ እርሱን እንድናገለግለው ነው፡፡ 76 አዎን፣ አንተም ሕፃን የእርሱን መንገድን ለማዘጋጀት በጌታ ፊት ስለምትሄድና ሕዝብንም ለመምጣቱ ስለምታሰናዳ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፡፡ 77 ለኃጢአቶቻቸው ይቅርታ የሚያገኙትን የድነት ዕውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ፡፡ 78 ይህም ከእግዚአብሔር አምላካችን መልካም ምሕረት የተነሣ ከእርሱ የተነሣ የፀሐይ ብርሃን በእኛ ላይ እንዲያርፍብንና 79 በጨለማና በሞት ጥላ ላሉት እናበራላቸው ዘንድ ነው፡፡ ይህንንም እግሮቻችንን በሰላም መንገድ ይመራው ዘንድ ያደርገዋል፡፡” 80 ልጁም አደገ፣ በመንፈሱም ጠነከረ፣ ለእስራኤልም እስኪገለጥ ድረስ በምድረ በዳ ኖረ፡፡
ሉቃስ ለምን ወደ ቴዎፍሎስ እንደሚጽፍ ያብራራል፡፡
“በእኛ መካከል ስለተፈጸሙት ነገሮች” ወይም “በእኛ መካከል ተከስተው ሰለነበሩት ነገሮች”
ቴዎፍሎስ ማን እንደነበር በእርግጠኝነት የሚያውቅ ሰው የለም፡፡ ቴዎፍሎስ ክርስቲያን የነበረ ከሆነ ግን “እኛ” የሚለው ገላጭ እርሱንም ያካትት የነበረ ይሆናል፣ ካልሆነ ግን እርሱን የሚያካትት አይሆንም፡፡ (አካታች “እኛ” እና አግላይ እና አካታች “እኛ” የሚለውን ይመልከቱ)
“የዓይን እማኝ” ማለት አንድ ነገር ሲከሰት በዓይኑ የተመለከተ ማለት ነው፣ አገልጋይ ማለት ደግሞ የእግዚአብሔርን መልዕክት ለሰዎች በመናገር እግዚአብሔርን የሚያገለግል ሰው ነው፡፡ እንዴት የቃሉ አገልጋዮች እንደተባሉ ግልጽ አድርጎ መናገር ያስፈልጋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የተከሰተውን የተመለከቱና መልዕክቱን በመናገር እግዚአብሔርን ያገለገሉ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“ቃሉ” የሚለው ቃል የሚወክለው ከብዙ ቃላት የተገነባ አንድን መልዕክት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የመልዕክቱ አገልጋዮች” ወይም “የእግዚአብሔር መልዕክት አገልጋዮች” (ወካይ የሚለውን ይመልከቱ)
“ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ የተመረመረ።” ሉቃስ በትክክል ምን እንደተከሰተ ለማወቅ በጥንቃቄ ምርምር አድርጓል፡፡ እርሱ ሰለተከሰቱት ነገሮች የጻፋቸው ነገሮች ትክክል መሆናቸውን ለማረጋገጥ ድርጊቱን በዓይናቸው ከተመለከቱ ከተለያዩ ሰዎች ጋር በመነጋገር የድርጊቶቹን እርግጠኝነት እንዳረጋገጠ ይገመታል፡፡
ሉቃስ ይህንን ያለው ለቴዎፍሎስ የነበረውን ክብርና አክብሮት ለማሳየት ፈልጎ ነው፡፡ ይህ ክፍል በባህላችሁ የተከበሩ ሰዎች የሚሰጣቸውን ስያሜ በመቀየር መጻፍ ይቻላል፡፡ አንዳንድ ሰዎች ሰላምታን በመጠቀም “ለቴዎፍሎስ” ወይም “የተወደድክ ቴዎፍሎስ” ብለው መጻፍን ይመርጣሉ፡፡
“የተከበርክ” ወይም “ክቡር”
የዚህ ሥም ትርጉም “የእግዚአብሔር ወዳጅ” ማለት ነው፡፡ ይህ ስም የዚህን ሰው ባሕርይ የሚገልጽ ስያሜ ሊሆን ይችላል፣ ወይም ትክክለኛው የዚህ ሰው መጠሪያም ሊሆን ይችላል፡፡ በርካታ ትርጉሞች እንደ መጠርያ ስም አድርገው ተርጉመውታል፡፡ (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
መልዓኩ የዮሐንስን ውልደት ተነበየ
ዘካርያስ እና ኤልሳቤጥን ለመጀመርያ ጊዜ እናያቸዋለን፡፡ ቀጥሎ ያሉት ጥቅሶች ሰለ እነርሱ የጀርባ ታሪክ የበለጠ መረጃ ይነግሩናል፡፡ (የጀርባ ታሪክ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ሐረግ በታሪኩ ውስጥ ከተሰጠው የጀርባ ታሪክ መረጃ ወደ ሌላ ታሪክ ትኩረት እንደተቀየረ የሚያሳይ ሐረግ ነው፡፡
ይህ ዘካርያስ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ መሆኑን፣ የክህነት ስራዎቹም እግዚአብሔርን የማምለክ ስርዓት አካላት መሆናቸውን ያሳያል፡፡ (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“የእርሱ ቡድን ተራ ሲሆን” ወይም “የእርሱ ቡድን የማገልገል ጊዜያቸው በደረሰ ጊዜ”
ይህ ዓረፍተ ነገር ስለ ካህናት ስራዎች መረጃን ይሰጣል፡፡ (የጀርባ ታሪክ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“ባሕላዊው መንገድ” ወይም “ሁልጊዜ እንደሚያደርጉት”
ምልክት ያለበትን ድንጋይ ወደ መሬት በመጣል እንደ እጣ በማውጣት አንድን ነገር ለመወሰን እንዲረዳቸው ይጠቀሙ ነበር፡፡ ካህናቱ በሚያወጡት እጣ ውስጥ የትኛው ካህንን ለተለያዩ ስራዎች መምረጥ እንዳለባቸው እግዚአብሔር ምሪትን እንደሚሰጣቸው ያምኑ ነበር፡፡
ካህናቱ በየጠዋቱና በየማታው ጣፋጭ ሽታ ያለውን እጣን በመቅደሱ ውስጥ በሚገኝ መሰዊያ ላይ በማቃጠል ለእግዚአብሔር እንደ መስዋዕት ያቀርቡ ነበር፡፡
“ብዙ ቁጥር ያለው ሕዝብ” ወይም “ብዙ ሰዎች”
ቅጥር ግቢው ቤተ መቅደሱ ዙሪያ የሚገኝ የተከለለ ቦታ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ከቤተ መቅደሱ ሕንጻ ውጪ” ወይም “ከቤተ መቅደሱ ውጪ ባለው ቅጥር ግቢ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ዘካርያስ በቤተ መቅደሱ ውስጥ ስራውን እያከናወነ እያለ የእግዚአብሔር መልዓክ መልዕክትን ሊሰጠው ይመጣል፡፡
ይህ ቃል በታሪክ ውስጥ ለሚከሰት ክስተት መጀመርያን ያሳያል፡፡
“በድንገት ወደ እርሱ መጣ” ወይም “በድንገት ከዘካርያስ ጋር ነበር” ይህ መልዓኩ በእርግጥም ከዘጋርያስ ጋር እንደነበርና ራዕይ እንዳልነበር ያሳያል፡፡
እነዚህ ሁለት ሐረጎች አንድ ዓይነት ትርጉም ያላቸው ሲሆኑ፣ ዘካርያስ ምን ያህል እንደፈራ ያሳያሉ፡፡
“ዘካርያስ መልዓኩን ባየው ጊዜ” ዘካርያስ የፈራው የመልዓኩ መልክ አስፈሪ ስለነበር ነው፡፡ ዘካርያስ ክፉ የሆነ ነገር አልሰራም፣ ስለዚህ መልዓኩ ቅጣት ይጥልብኛል ብሎ አልፈራም፡፡
x
“የዚህም ምክንያት ታላቅ ስለሚሆን ነው” ዘካርያስና “ብዙዎች” ደስ የሚላቸው ዮሐንስ “በእግዚአብሔር ፊት ታላቅ” ስለሚሆን ነው፡፡ ተከትሎ ያለው የቁጥር 15 ክፍል እግዚአብሔር ዮሐንስ እንዴት እንዲኖር እንደሚፈልግ ይናገራል፡፡
“ደስታ” እና “ተድላ” የሚሉት ቃላት ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው፣ ይህም ምን ያህል ደስታ እንደሚሆን ትኩረት ለመስጠት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ታላቅ ደስታ ይሆንልሃል” ወይም “እጅግ ደስተኛ ትሆናለህ” (ጥምር ቃል የሚለውን ይመልከቱ)
“በመወለዱ ምክንያትም”
“ለጌታ እጅግ ጠቃሚ ሰው ይሆናል” ወይም “እግዚአብሔር እርሱን እጅግ ጠቃሚ ሰው አድርጎ ያየዋል”
ይህ በአድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “መንፈስ ቅዱስ ኃይልን ይሰጠዋል” ወይም “መንፈስ ቅዱስ ምሪትን ይሰጠዋል፡፡” ይህ አርፍተ ነገር ክፉ መንፈስ ሰውን እንደሚያረገው አይነት እንዳይመስል ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“ገና በእናቱ ማሕጸን ውስጥ ሳለ” ወይም “ገና ሳይወለድ”
እዚህ ላይ “ይመለሳሉ” የሚለው ቃል አንድ ሰው ንስሃ ገብቶ እግዚአብሔርን ማምለክ መጀመርን የሚያመለክት ዘይቤ ነው፡፡ ይህም በአድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እርሱም ብዙዎች የእስራኤል ሕዝቦችን ንስሐ እንዲገቡና አምላካቸው እግዚአብሔርን እንዲያመለኩ ያደርጋል” (ተለዋጭ ዘይቤ እና ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ጌታ ከመምጣቱ በፊት፣ ጌታ እንደሚመጣ ለሰዎች ይሰብካል፡፡
እዚህ ላይ “ፊት” የሚለው ቃል የአንድን ሰው ሕልውና የሚያሳይ ፈሊጥ ነው፡፡ በአንዳንድ ትርጉሞች ላይ ተጽፎ ላይገኝ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ጌታ” (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)
“ኤልያስ በነበረው መንፈስና ኃይል፡፡” “መንፈስ“ የሚለው የእግዚአብሔርን መንፈስ ወይም ኤልያስ የነበረውን አስተሳሰብ ሊያሳይ ይችላል፡፡ “መንፈስ” የሚለው ቃል የሞትን ወይም የክፉን መንፈስ በሚለው እንዳይተረጎም ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
“አባቶች ስለ ልጆቻቸው እንዲያስቡ ደግሞ ጠየቃቸው” ወይም “አባቶች ከልጆቻቸው ጋር ያላቸውን ግንኙነት ያድሱ ዘንድ”
እዚህ ላይ ልብ አቅጣጫውን እንደሚቀይር ነገር ተደርጎ ተቀምጧል፡፡ ይህ የአንድ ሰው አስተሳሰብን ስለመቀየር ያመለክታል፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“የማይታዘዙትን ወደ ጻድቃን ጥበብ ለመመለስ” ወይም “የማይታዘዙት ጠቢብ እንዲሆኑና የጻድቅ ሰዎችን ተግባር እንዲፈጽሙ ለማሳመን”
ይህ የሚያሳየው ጌታን የማይታዘዙትን ሰዎች ነው፡፡
ሕዝቡ ምን ለማድረግ እንደሚዘጋጁ በግልጽ ማሳየት ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “መልዕክቱን ለማመን የተዘጋጁ ሕዝቦችን ለጌታ ማሰናዳት” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“የተናገርኸው ነገር እንደሚፈጸም በእርግጠኝነት ማወቅ የምችለው እንዴት ነው?” እዚህ ላይ “ማወቅ” የሚለው ቃል በልምድ መማር ማለት ነው፣ ይህን ሃሳብ ያነሳው ዘካርያስ እንደ ማረጋገጫ ምልክት ጠይቆ ስለነበር ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “ይህ ነገር እንደሚፈጸም ለእኔ ለማረጋገጥ ምን ልታደርግ ትችላለህ”
ይህ ለዘካርያስ እንደ ተግሳጽ ተደርጎ ተጽፏል፡፡ ከእግዚአብሔር ቀጥታ የመጣው የገብርኤል መገኘት ብቻ ለዘካርያስ በቂ ማረጋገጫ መሆን ነበረበት፡፡
x
ይህ በታሪኩ ውስጥ ቤተ መቅደስ ውስጥ ከተከሰተው ነገር ከቤተ መቅደስ ውጪ ወደተከሰተው ነገር ትኩረቱ መቀየሩን ያሳያል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ይህ እየተከሰተ በነበረ ጊዜ” ወይም “መልዓኩና ዘካርያስ እየተነጋገሩ በነበረ ጊዜ”
እነዚህ ነገሮች በተመሳሳይ ሰዓት የተከሰቱ እንደሆን ይገመታል፣ የዘካርያስ ምልክቶችም ሕዝቡ እርሱ ራዕይን እንዳይ እንዲገነዘቡ አድርገዋቸዋል፡፡ የነዚህን ቅደም ተከተል መቀየር አድማጩ የበለጠ መረዳት እንዲኖረው ሊያደርግ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ዘካርያስ ምልክቶችን ያሳያቸው ነበር ዲዳም ሆኖ ኖረ፡፡ ስለዚህ በቤተ መቅደስ ውስጥ ሳለ ራዕይን እንደተመለከተ ሕዝቡ ተገነዘበ”
ቀድሞ የተሰጠው መግለጫ ገብርኤል በእርግጥም ወደ ዘካርያስ ወደ ቤተ መቅደሱ እንደመጣ ያሳያል፡፡ ሕዝቡ ይህንን ባለማወቅ ዘካርያስ ራዕይ እንደተመለከተ አሰቡ፡፡
“እነዚህ ቀናት” የሚለው ሐረግ ዘካርያስ በቤተመቅደስ ውስጥ ያገለገለባቸውን ቀናት ያመለክታል፡፡ ይህ ምንን እንደሚያመለክት የበለጠ ግልጽ አድርጎ ማስረዳት ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ዘካርያስ በቤተመቅደስ ካገለገለበት ጊዜ በኋላ” (የአዲስ ሁነት መግቢያ እና ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለጸ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“የዘካርያስ ሚስት”
“ከቤት አልወጣችም” ወይም “ ብቻዋን ቆየች”
ይህ ጌታ ልጅ ማርገዝ እንድትችል እንዳስቻላት ያሳያል፡፡
ይህ አዎንታዊ የሆነ ግነት ነው፡፡ ጌታ ባደረገላት ነገር በጣም ደስተኛ ናት፡፡
እዚህ ላይ “መመልከት” የሚለው ፈሊጥ ፈሊጥ ሲሆን ትርጉሙም “መንከባከብ” ወይም “በሚገባ መያዝ“ ማለት ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “በርህራሄ ተመለከተኝ” ወይም “አዘነልኝ” (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ እርሷ ልጆች ባለመውለዷ ይሰማት የነበረውን ነቀፋ ያሳያል፡፡
መልዓኩ ማርያም እርሱን አይታ እንድትፈራ አይፈልግም ምክንያቱም እግዚአብሔር መልካም መልዕክትን እንዲያደርስ ስለላከው ነው፡፡
“ሞገስን ማግኘት” የሚለው ፈሊጥ በአንድ ሰው ዘንድ መልካም ተቀባይነትን ማግኘት ነው፡፡ የአርፍተ ነገሩን ቅደም ተከተል በመቀየር እግዚአብሔርን የድርጊቱ ባለቤት አድርጎ ማሳየት ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር ጸጋውን ሊሰጥሽ ወስኗል” ወይም “እግዚአብሔር ቸርነቱን ላንቺ እያሳየ ነው” (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)
ማርያም “ወንድ ልጅን” ትወልዳልች ስሙም “የልዑል ልጅ” ይባላል፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ ከሰው እናት የተወለደ የሰው ልጅ ነው፣ እርሱ የእግዚአብሔርም ልጅ ነው፡፡ እነዚህ ቃላት በጥንቃቄ መተርጎም አለባቸው፡፡
የዚህ ትርጉሞች ሊሆኑ የሚችሉት 1) “ሰዎች … ብለው ይጠሩታል” 2) “እግዚአብሔር … ይጠራዋል” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ለሆነው ለኢየሱስ እጅግ ወሳኝ የሆነ ስያሜ ነው፡፡ (ልጅ እና አባትን መተርጎም የሚለውን ይመልከቱ)
ዙፋን የሚየያሳየው የንጉስን የመግዛት ስልጣን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “አባቱ ዳዊት ይገዛ እንደነበር እርሱም እንዲገዛ ስልጣንን ይሰጠዋል” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
“መጨረሻ አይኖርም” የሚለው አሉታዊ መግለጫ ለዘላለም የሚቀጥል መሆኑን አጽንኦት ይሰጣል፡፡ አርፍተ ነገሩ በአዎንታዊ ሐረግ መገለጽ ይችላል፡፡ “መንግስቱ እስከመጨረሻ አያበቃም” አማራጭ ትርጉም፡- (ምፀት የሚለውን ይመልከቱ)
ምንም እንኳ ማርያም ነገሩ እንዴት እንደሚከሰት ባይገባትም፣ መከሰቱን ግን አልተጠራጠረችም፡፡
ማርያም ይህንን ትህትና የተሞላበት አገላለጽ የተጠቀመችው እርሷ ከማንም ጋር ወሲባዊ ግንኙነት ፈጽማ እንደማታውቅ ለመግለጽ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ድንግል ነኝ” (ለስላሴ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
የማርያም እርግዝና የሚጀምረው መንፈስ ቅዱስ ወደ እርሷ በመምጣት ነው፡፡
“ይቆጣጠርሻል”
ማርያም ድንግል እያለች ከተፈጥሮ በላይ በሆነ ሁኔታ እንድታረግዝ የሚያደርጋት የእግዚአብሔር “ኃይል” ነበር፡፡ይህ አካላዊ ወይም ወሲባዊ ትርጉም ያለው እንዳይመስል ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል፣ ይህ ተዓምር ነበር፡፡
“እንደ ጥላ ይከልልሻል”
ይህ በአድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የሚወለደውንም ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ብለው ይጠሩታል” ወይም “የሚወለደውም ሕጻን ቅዱስ ይሆናል፣ ሰዎችም የእግዚአብሔር ልጅ ብለው ይጠሩታል፡፡ (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“ቅዱሱ ልጅ” ወይም “ቅዱሱ ሕጻን”
ይህ ለኢየሱስ የተሰጠ ልዩ መጠርያ ማዕረግ ነው፡፡ (ልጅ እና አባትን መተርጎም የሚለውን ይመልከቱ)
“ትኩረት ስጪ፣ ምክንያቱም አሁን የምነገርሽ ነገር እውነትና እጅግ ጠቃሚ ነው፣ ዘመድሽ”
ማርያም ዮሐንስን ልትወልድ የነበረችውን ዘመዷን ኤልሳቤጥን ለመጎብኘት ወደ እርሷ ሄደች፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ፈሊጥ ከተቀመጠችበት ተነሳች የሚለውን ትርጉም ብቻ ሳይሆን፣ “ተዘጋጀች” የሚለውንም ትርጉም ይይዛል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ጀመረች” ወይም “ተዘጋጀች” (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)
“በተራራ የተሞላው አካባቢ” ወይም “የእስራኤል ተራራማው ክፍል”
x
እነዚህ ሁለት ሐረጎች ተመሳሳይ ትርጉም ሲይዙ ኤልሳቤጥ ምን ያህል ደስተኛ እንደነበረች አጽንኦት ይሰጣሉ፡፡ሁለቱን አደባልቆ አንድ ሐረግ ማድረግ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በአድናቆት ጮኸች” (ጥምር ቃል የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ፈሊጥ “ድምፁዋን አጩሃ ተናገረች” የሚለውን ትርጉም የያዘ ነው፡፡ (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)
“ከሴቶች መካከል” የሚለው ፈሊጥ “ከሌላ ሴት በሙሉ የተሻለች” የሚለውን ትርጉም ይይዛል፡፡ (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)
የማርያም ልጅ እዚህ ላይ አንድ ተክል እንደሚያፈራው ፍሬ ተደርጎ ተጽፏል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በማሕጸንሽ ውስጥ ያለው ሕጻን” ወይም “የምታረግዥው ሕጻን” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
ኤልሳቤጥ መልስ ፈልጋ ጥያቄን እየጠየቀች አይደለም፡፡ የጌታ እናት ወደ እርሷ በመምጣቷ ምን ያህል እንደተደነቀችና ደስተኛ እንደነበረች እያሳየች ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የጌታዬ እናት ወደ እኔ መምጣቷ እንዴት የሚደንቅ ነው!” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ኤልሳቤጥ ማርያምን “የጌታዬ እናት” ብላ እንደጠራቻት “አንቺ” የሚለውን መግለጫ በመጨመር የበለጠ ግልጽ ማድረግ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “አንቺ የጌታዬ እናት” (አንደኛ፣ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ መደብ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ኤልሳቤጥ ቀጥላ ለምትናገረው አስገራሚ ነገር ማርያም ትኩረት እንድትሰጥ የሚናገር ቃል ነው፡፡
የአንድን ነገር ድምጽ መስማትን “ድምጹ ወደ ጆሮ ደረሰ” በማለት ሊገለጽ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የሰላምታሽን ድምጽ በሰማሁ ጊዜ” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
“በድንገት በደስታ ተንቀሳቀሰ” ወይም “በጣም ከመደሰቱ የተነሳ በኃይል ዞረ”
ኤልሳቤጥ ለማርያም ስለ ራሷ ስለ ማርያም ነበር የምትነግራት። አማራጭ ትርጉም፡-“ከጌታ የተነገረሽን የምታምኚ አንቺ የተባረክሽ ነሽ” (አንደኛ፣ ሁለተኛና ወይም ሶስተኛ መደብ እና ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
በተደራጊ ቅርጽ የተቀመጠው ግስ በአድራጊ ቅርጽ መቀመጥ ይችላል። አማራጭ ትርጉም፡- “ስላመነች እግዚአብሔር ይባርካታል” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“እነዚህ ነገሮቸ በእርግጠኝነት ይፈጸማሉ” ወይም “እነዚህ ነገሮች እውን ይሆናሉ”
መልእክቱን ሲናገር የሰማችው መልአኩ ገብርኤልን ነው (ሉቃስ 1፡26 ይመልከቱ)፣ ነገር ግን መልእክቱ (“እነዚህ ነገሮች”) በዋነኛነት የመጣው ከጌታ ነበር። ይህ በገቢር ቅርጽ ሊጻፍ ይችላል። አማራጭ ትርጉም፡- “ከጌታ የሰማችው መልእክት” ወይም “መልአኩ የነገራት የጌታ መልእክት” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ እና ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ማርያም ለአምላኳና ለአዳኟ የምስጋናን መዝሙር መዘመር ትጀምራለች፡፡
ሁለቱም “ነፍስ” እና “መንፈስ” የአንድ ሰው መንፈሳዊ ማንነት አካላት ናቸው፡፡ ማርያም አምልኮዋ ከውስጥ የመነጨ እንደሆነ ለማሳየት እንደዚህ ብላለች፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የውስጥ ማንነቴ ያምሰግናል … ልቤም እጅግ ሐሴትን አድርጓል” ወይም “አመሰግናለሁ … ሐሴትም አደርጋለሁ” (ወካይ የሚለውን ይመልከቱ)
“በ … እጅግ ደስታ ተሰምቷታል” ወይም “በ … እጅግ ተደስታለች”
“እኔን ያዳነኝ እግዚአብሔር” ወይም “የሚያደነኝ እግዚአብሔር”
“ምክንያቱም እርሱ”
“በእንክብካቤ ተመለከተ” ወይም “በጥንቃቄ”
“ድህነት።” የማርያም ቤተሰብ ሃብታም አልነበረም፡፡
ይህ ሐረግ ተከትሎ ለሚመጣው ንግግር ትኩረት እንዲሰጥ ያደርጋል፡፡
“አሁንና ለወደፊቱ”
“በእያንዳንዱ ትውልድ ያሉ ሕዝቦች በሙሉ”
“ኃይለኛው እግዚአብሔር”
እዚህ ላይ “ሰሙ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሙሉ የእግዚአብሔር ማንነትን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እርሱም” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
“የእግዚአብሔር ምህረት”
“ከአንድ ትውልድ እስከ ቀጣይ ትውልድ” ወይም “በእያንዳንዱ ትውልድ ውስጥ” ወይም “በማንኛውም ጊዜ ላይ ለሚኖሩ ሕዝቦቸ”
x
ዙፋን ማለት ገዢ የሚቀመጥበት ወንበር ነው፣ ወንበሩ የስልጣኑም ምልክት ነው፡፡ ገዢ ከዙፋኑ ከወረደ በኋላ ሊገዛበት የሚችል ስልጣን የለውም ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የገዢዎችን ስልጣን ወስዷል” ወይም “ገዢዎች መግዛትን እንዲያቆሙ አድርጓቸዋል” (ወካይ የሚለውን ይመልከቱ)
በዚህ የቃላት መግለጫ መሰረት፣ ከፍተኛ ስፍራ ያላቸው ሰዎች ዝቅተኛ ስፍራ ካላቸው ይልቅ እጅግ ከፍ ያሉ እንደሆኑ ያሳያል። አማራጭ ትርጉም፡- “ትሁት ሰዎችን ታላቅ አደረጋቸው” ወይም “ሌሎች ሰዎች ያላከበሯቸውን ሰዎች እርሱ አከበራቸው፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“በድህነት ውስጥ ያሉትን።” ይህ በሉቃስ 1:48 ላይ እንዴት እንደተተረጎመ ተመልከት፡፡
በእነዚህ ተቃራኒ ድርጊቶች መካከል ያለው ልዩነት ከተቻለ በትርጉሙ ላይ ግልጽ ይደረግ፡፡
የዚህ ትርጉም ሊሆኑ የሚችሉት 1) “ለተራቡት ጥሩ የሚበላ ምግብ ሰጣቸው” ወይም 2) “ለተቸገሩት መልካምን ነገር ሰጣቸው”
ዩዲቢ የሚባለው ትርጉም ስለ እስራኤል የተቀመጠው መረጃ ሳይቀየር እንዲተላለፍ የእነዚህን ቁጥሮች ቅደም ተከተል በመቀያየር አንድ የመሸጋገርያ ቁጥር አድርጓቸዋል፡፡ (የጥቅስ ድልድዮች የሚለውን ይመልከቱ)
x
ኤልሳቤጥ ልጇን ትወልደዋለች ከዛም ዘካርያስ ለሕጻኑ ስም ያወጣለታል፡፡
“ማርያም ወደ ቤቷ (ወደ ማርያም) ቤት ተመለሰች” ወይም “ማርያም ወደ ራሷ ቤት ተመለሰች”
ይህ ቃል በታሪኩ ውስጥ ቀጣይ ክስተት መጀመሩን ይናገራል፡፡
“ልጇን ወለደች”
“የኤልሳቤጥ ጎረቤቶችና ዘመዶች”
x
ይህ ሐረግ እዚህ ላይ ዋናው የታሪክ መስመር ተቆርጦ ሌላ ታሪክ ሊነገር መጀመሩን ለማሳየት ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ እዚህ ላይ ሉቃስ አዲስ ታሪክ መናገር ይጀምራል፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ስምንተኛው ቀን” የሚለው ቃል ከሕጻኑ ውልደት በኋላ ያለውን ቀን ያሳያል ይህም ከመጀመርያው ቀን ጀምሮ ወይም ሕጻኑ ከተወለደበት ጀምሮ ተቆጥሮ ያለውን ቀን ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በሕጻኑ ሕይወት በስምንተኛው ቀን” (ደረጃ የሚያሳይ ቁጥር የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ብዙ ጊዜ አንድ ሰው ልጁን በሚገርዝበት ጊዜ ወዳጆቹ በዚያ ተገኝተው ከቤተሰቡ ጋር ሆነው የሚያከብሩበት ስነ ስርዓት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ለሕጻኑ የግርዘት ሥርዓት መጡ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“… ብለው ስም ሊያወጡለት ነበር” ወይም “… የሚል ስም ሊሰጡት ፈልገው ነበር”
“የአባቱን ስም”
“በዚያ ስም” ወይም “በተመሳሳይ ስም”
እነዚህ ሁለት ሐረጎች ዘካርያስ በድንገት መናገር መቻሉን አጽንኦት ይሰጣሉ፡፡ (ፈሊጥ እና ትይዩነት የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ ሐረጎች በአድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላሉ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር አፉን ከፈተለት ምላሱንም ፈታለት” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“ከዘካርያስ እና ኤልሳቤጥ አካባቢ ይኖሩ በነበሩ ላይ ሁሉ” ለምን ፈርተው እንደነበር ግልጽ ማድረግ አስፈላጊ ሊሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ከእነርሱ አካባቢ ይኖሩ የነበሩት ሁሉ እግዚአብሔር ለዘካርያስ እንዲህ በማድረጉ በእግዚአብሔር እጅግ ተደነቁ“ (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“ሁሉ” የሚለው ቃል ጅምላ ፍረጃ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እነርሱ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ” ወይም “በዚያ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ብዙ ሰዎች” (ግነት እና ጅምላ ፍረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“እነዚህ ነገሮች መከሰታቸው … ተዳረሰ” የሚለው ሐረግ ሰዎች ስለ እነርሱ ማውራታቸውን የሚያሳይ ዘይቤ ነው፡፡ ጥቅም ላይ የዋለው ተደራጊ ቅርጽ በአድራጊ ቅርጽ መቀየር ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እነዚህ ነገሮች በሙሉ በይሁዳ ተራራማው ከተማ ይኖሩ በነበሩ ሰዎች ይወሩ ነበር” ወይም “በይሁዳ ተራራማው ከተማ የሚገኙ ሕዝቦች ስለ እነዚህ ነገሮች ያወሩ ነበር” (ተለዋጭ ዘይቤ እና ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“ስለተከሰቱት ነገሮች የሰሙ በሙሉ”
ስለ ተከሰቱ ነገሮች ነገር ደጋግሞ ማሰላሰልና ማሰብ ነገሮቹን በልብ ውስጥ በጥንቃቄ እንደማኖር ተደርጎ ይታሰባል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ስለ እነዚህ ነገሮች በጥንቃቄ ያስቡና ያሰላስሉ ነበር” ወይም “ስለ እነዚህ ክስተቶች ደጋግመው ያስቡ ነበር” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“እየጠየቁ በልባቸው አኖሯቸው”
“ይህ ሕጻን አድጎ ምን ዓይነት ልዩ ሰው ይሆን ይሆን?” ይህ ጥያቄ ሰዎቹ ስለ ሕጻኑ በሰሙት ነገሮች ያደረባቸውን መገረም ለመግለጽ የተጠቀሙበት መንገድ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ይሄ ልጅ አድጎ ምን ዓይነት ልዩ ሰው ይሆን ይሆን?” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
“የአምላክ እጅ” የሚለው ሐረግ የአምላክን ኃይል ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የአምላክ ኃይል ከእርሱ ጋር ነበር” ወይም “አምላክ በእርሱ ውስጥ በኃይል ይሰራ ነበር” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
ዘካርያስ በልጁ በዮሐንስ ላይ ምን እንደሚሆን ተናገረ፡፡
ይህ በአድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “መንፈስ ቅዱስ አባቱን ዘካርያስን ሞላው፣ ዘካርያስም ትንቢት ተናገረ” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
የዮሐንስ አባት
በራሳችሁ ቋንቋ ውስጥ ቀጥተኛ ጥቅሶቸን የማስተዋወቂያ የተለመዱ መንገዶችን አስብ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ትንቢትን ተናገረ እንዲህም አለ” ወይም “ትንቢትን ተናገረ፣ የተናገረውም እንዲህ ነው … “ (ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ ጥቅሶች የሚለውን ይመልከቱ)
በራሳችሁ ቋንቋ ውስጥ ቀጥተኛ ጥቅሶቸን የማስተዋወቂያ የተለመዱ መንገዶችን አስብ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ትንቢትን ተናገረ እንዲህም አለ” ወይም “ትንቢትን ተናገረ፣ የተናገረውም እንዲህ ነው … “ (ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ ጥቅሶች የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “እስራኤል” የሚያመለክተው የእስራኤልን ሕዝብ ነው፡፡ በእግዚአብሔር እና በእስራኤል መካከል ያለው ግንኙነት የበለጠ ቀጥተኝነት ባለው መልኩ ሊብራራ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በእስራኤልን ላይ የሚገዛው አምላክ እግዚአብሔር” ወይም “እስራኤል የምታመልከው አምላክ እግዚአብሔር” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“የእግዚአብሔር ሕዝብ”
የአንድ እንስሳ ቀንድ ራስን የመከላከል አቅሙን የሚያመለክት ምሳሌ ነው፡፡ ማስነሳት ማለት ደግሞ ያልነበረን ማኖር ወይም አንድን ድርጊት መጀመርን ያሳይል፡፡ እዚህ ላይ መሲሑ እስራኤልን የማዳን ኃይል እንዳለው እንደ ቀንድ ምሳሌ ተደርጎ ተመስሏል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “(እግዚአብሔር) እኛን የማዳን ኃይል ያለውን ሰው ሰጥቶናል” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“የዳዊት ቤት” የሚወክለው ቤተሰቡን ነው በተለይም ደግሞ ዘሮቹን ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በአገልጋዩ በዳዊት ቤተሰብ” ወይም “የአገልጋዩ ዳዊት ዘር የሆነ” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
“እግዚአብሔር እንዳለው”
እግዚአብሔር በነብያቱ አፍ ተናገረ የሚለው የሚያመለክተው እግዚአብሔር ነብያቱን እርሱ እንዲላቸው የፈለገውን እንዲናገሩ ማድረጉን ያሳያል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ድሮ የኖሩትን ቅዱሳን ነብያቱን እንዲናገሩ ያደረጋቸውን” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
“ማዳን” የሚለው ረቂቅ ቃል “መታደግ” እና “ማትረፍ” በሚሉት ግሶች ተለውጦ መገለጽ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ድሮ የኖሩትን …. እርሱም ከጠላቶቻችን ይታደገናል፡፡” (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ ሁለት ቃላት ተመሳሳይ ትርጉም ይይዛሉ፣ የተደጋገሙትም ጠላቶቻቸው ምን ያህል ይቃወሟቸው እንደነበረ አጽንኦት ለመስጠት ነው፡፡ (ትይዩነት የሚለውን ይመልከቱ)
እጅ የሚለው ቃል አንድ ሰው ኃይሉን የሚለማመድበትን እጅ የሚወክል ምትክ ስም ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ኃይል” ወይም “ቁጥጥር” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
“ለ … መሃሪ መሆን” ወይም “ለ … እንደ ምህረቱ ማድረግ”
እዚህ ላይ “አስታወሰ” የሚለው ቃል ቃለኪዳንን መጠበቅ ወይም አንድን ነገር መፈጸምን ያሳያል፡፡
እነዚህ ሁለት ሐረጎት ተመሳሳይ ትርጉምን ይይዛሉ፡፡ መደጋገማቸው እግዚብሔር ለአብርሃም የገባው ቃልኪዳን ምን ያህል ከባድ እንደሆነ ያሳያል፡፡ (ትይዩነት የሚለውን ይመልከቱ)
“እኛ … ማድረግ እንድንችል አደረገ”
ይህ በአድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ከጠላቶቻችን እጅ ካስመለጠን በኋላ ያለ ፍርሃት እርሱን እንድናገለግለው” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
x
ዘካርያስ ይህንን ሐረግ ቀጥታ ለልጁ መናገር መጀመሩን ለማሳየት ይጠቀማል፡፡ በራሳችሁ ቋንቋ ይህንን ንግግር ለመጀመር የሚሆን መንገድ መጠቀም ይቻላል፡፡
ሰዎች እርሱ ነብይ እንደሆነ ይረዳሉ፡፡ ይህ በአድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሰዎች አንተ ነብይ መሆንህን ያውቃሉ” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ ቃላት እግዚአብሔርን ለመግለጽ የምንጠምባቸው ለስላሴ ዘይቤያዊ ቃላት ናቸው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የበላይ የሆነውን የሚያገለግል” ወይም “የበላይ ለሆነው ለእግዚአብሔር የሚናገር” (ለስላሴ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
ጌታ ከመምጣቱ በፊት እርሱ ሄዶ ጌታ ወደ እነርሱ እነደሚመጣ ይነግራቸዋል፡፡ ይህንን በሉቃስ 1፡17.
የአንድ ሰው “ፊት” የዛን ሰው መገኘት ይወክላል፡፡ ብዙ ጊዜ በትርጉሞች ላይ ተጽፎ አይገኝም፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ጌታ” ይህን በሉቃስ 1:17 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡. (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ዮሐንስ ሰዎች የጌታን መልዕክት እንዲሰሙና እንዲያምኑ ያዘጋጃቸዋል የሚለውን መልዕክት የያዘ ዘይቤ ነው፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“እውቀት ትሰጣለህ” የሚለው ሐረግ ማስተማር የሚለውን ትርጉም የያዘ ዘይቤ ነው፡፡ “ድነት” እና “ምህረት” የሚሉት ረቂቅ ቃላት “ማዳን” እና “ይቅር ማለት“ በሚሉት ቃላት ሊገለጹ ይችላሉ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ለሰዎች በኃጢአታቸው ይቅር መባል መዳናቸውን ያስተምራል” ወይም “ለሰዎች እንዴት እግዚአብሔር ኃጢአታቸውን ይቅር በማለት እንዳዳናቸው ያስተምራል” (ምትክ ስም እና ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)
የእግዚአብሔር ምህረት ሰዎችን እንደሚረዳ መግለጽ አስፈላጊ ሊሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ምክንያቱም እግዚአብሔር ለእኛ ሩህሩህና መሃሪ ስለሆነ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ብርሃን ብዙ ጊዜ የእውነት ምሳሌ ነው፡፡ እዚህ ላይ አዳኙ ለእኛ የሚሰጠው መንፈሳዊ እውነት ዓለምን ሁሉ በብርሃን የሚሞላ የጸሐይ ብርሃን ተደርጎ ተመስሏለ፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“እውቀት መስጠት” ወይም “መንፈሳዊ ብርሃንን መስጠት”
ጨለማ እዚህ ላይ የመንፈሳዊ እውነት እጦትን ወይም አለመገኘትን ይወክላል፡፡ እዚህ ላይ መንፈሳዊ እውነት የሌላቸው ሰዎች በጨለማ ውስጥ እንደተቀመጡ ተደርገው ተመስለዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እውነትን የማያውቁ ሕዝቦች” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ ሁለት ሐረጎች አንድ ላይ በመሆን እግዚአብሔር ምህረቱን ለእነርሱ ከማድረጉ በፊት ሰዎች ላይ የነበረውን ጥልቅ ጨለማ አስከፊነት ይገልጻሉ፡፡ (ጥምር ቃል የሚለውን ይመልከቱ)
ጥላ ብዙ ጊዜ ሊመጣ ያለውን ነገር ይገልጻል፡፡ እዚህ ላይ እየመጣ ያለን ሞትን ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሊሞቱ ያሉ” (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “መምራት” የሚለው ቃል ማስተማር ለሚለው ቃል ዘይቤ ነው፣ “የሰላም መንገድ” የሚለው ደግሞ ከእግዚአብሔር ጋር በሰላም መኖርን የሚወክል ዘይቤ ነው፡፡ “እግሮቻችንን” የሚለው ቃል የአንድን ሰው ሙሉ ማንነት የሚወክል ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ከእግዚአብሔር ጋር በሰላም መኖርን ያስተምረናል”(ተለዋጭ ዘይቤ እና ወካይ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ዮሐንስ እያደገ ስለመጣባቸው አመታት ይናገራል፡፡
ይህ ቃል ዋናው የታሪክ መስመር መቋረጡን ያመለክታል፡፡ ሉቃስ ስለ ዮሐንስ ውልደት ከመናገር በፍጥነት ወጥቶ ዮሐንስ አድጎ ያደርግ ስለነበረው አገልግሎት ይናገራል፡፡
“በመንፈስ እየበሰለ መጣ” ወይም “ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት አጠነከረ”
“በምድረ በዳ ኖረ” ሉቃስ ዮሐንስ በምን እድሜ ላይ በምድረ በዳ መኖር እንደጀመረ አይናገርም፡፡
ይህ ከጊዜ ጋር በተያያዘ ያቆመበትን ነጥብ የግድ አያመለክትም፡፡ ዮሐንስ በአደባባይ መስበክ ከጀመረ በኋላም እንኳ ቢሆን በምድረ በዳ ይኖር ነበር፡፡
“በአደባባይ መስበክ እስከሚጀምር ድረስ”
ይህ በጠቅላላው “ጊዜውን” እና “ሁኔታውን” ለመናገር ጥቅም ላይ ነው የዋለው፡፡
1 በዚያን ጊዜ አውግስጦስ ቄሣር በዓለም የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ ይቆጠሩ ዘንድ ዐዋጅ አወጣ፡፡ 2 ይህም ቄሬኔዎስ የሶርያ ገዥ በነበረበት ጊዜ የተደረገ የመጀመሪያው የሕዝብ ቆጠራ ነበር፡፡ 3 ስለዚህ እያንዳንዱ ሰው ለሕዝብ ቆጠራው ወደየራሱ ከተማ ሄደ፡፡ 4 ዮሴፍም የዳዊት ቤተሰብ ዝርያ ስለነበረ በገሊላ ከነበረችው ከናዝሬት ተነሥቶ የዳዊት ከተማ ወደምትባለው የይሁዳ ከተማ ወደ ነበረችው ወደ ቤተ ልሔም ተጓዘ፡፡ 5 ይመዘገብ ዘንድ ለእርሱ ታጭታ ከነበረችውና የመውለጃዋን ቀን እየተጠባበቀች ከነበረችው ከማርያም ጋር ወደዚያ ስፍራ ሄደ፡፡ 6 እዚያም በነበሩበት ጊዜ የምትወልድበት ወቅት ደረሰ፡፡ 7 የበኩር ልጅዋ የሆነውን ወንድ ልጅ ወለደች፣ በመታቀፊያ ጨርቅም በሚገባ ጠቀለለችው፡፡ በእንግዳ መቀበያውም ስፍራ ስላልነበረ በእንስሳት መመገቢያ ግርግም ውስጥ አስተኛቸው፡፡ 8 በዚያው አካባቢ በሌሊት የበግ መንጎቻቸውን እየጠበቁ በመስክ የነበሩ እረኞች ነበሩ፡፡ 9 በድንገትም የእግዚአብሔር መልአክ ለእነርሱ ተገለጠላቸው፣ የእግዚአብሔርም ክብር በእነርሱ ዙሪያ አበራላቸው፤ እነርሱም በጣም ፈሩ፡፡ 10 ከዚያ በኋላ መልአኩ፣ “ለሕዝብ ሁሉ ታላቅ ደስታ የሚሆን የምሥራች ይዤላችሁ መጥቻለሁና አትፍሩ፡፡ 11 ዛሬ በዳዊት ከተማ፣ አዳኝ ተወልዶላችኋል፤ እርሱም ክርስቶስ ጌታ ነው፡፡ 12 ለእናንተም ይህ ምልክት ይሰጣችኋል፣ ሕፃን በመታቀፊያ ጨርቅ ተጠቅልሎ፣ በግርግም ተኝቶ ታገኛላችሁ፡፡” 13 በድንገትም ከመልአኩ ጋር ብዙ የሰማይ ሠራዊት እግዚአብሔርን እያመሰገኑ፣ 14 “ከፍ ባለ ስፍራ ለሚኖረው ለእግዚአብሔር ክብር፣ በምድርም እርሱ ደስ በሚሰኝባቸው ሕዝቦች መካከል ሰላም ይሁን፡፡” ይሉ ነበር፡፡ 15 መላእክቱም ከእነርሱ ተለይተው ወደ ሰማይ በሄዱ ጊዜ፣ እረኞቹ እርስ በርሳቸው፣ “ወደ ቤተልሔም እንሂድና፣ እግዚአብሔር ለእኛ የገለጠልንን ይህንን የሆነውን ነገር እንመልከት፡፡” ተባባሉ፡፡ 16 በችኮላ ወደዚያ ሄደው ማርያምንና ዮሴፍን አገኝዋቸው፣ ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ ተመለከቱት፡፡ 17 ይህንን ከተመለከቱ በኋላ ስለዚህ ልጅ የተባለውን ለሕዝቡ አስታወቁ፡፡ 18 ያዳመጡአቸውም ከእረኞቹ በተነገራቸው ነገር ተደነቁ፡፡ 19 ስለሰማችው ነገር ሁሉ ማርያም እያሰላሰለች በልብዋ ትጠብቀው ነበር፡፡ 20 ልክ እንደ ተነገራቸው ስለ ሰሙትና ስላዩት ስለ ማንኛውም ነገር እረኞቹ እግዚአብሔርን እያከበሩና እያመሰገኑ ተመለሱ፡፡ 21 ሕፃኑ የሚገረዝበት ስምንተኛው ቀን በደረሰ ጊዜ በማሕፀን ከመፀነሱ በፊት በመልአኩ በተሰጠው ስም ኢየሱስ ብለው ጠሩት፡፡ 22 በሙሴ ሕግ መሠረት የመንጻታቸው ወራት በተፈጸመ ጊዜ በእግዚአብሔር ፊት ያቀርቡት ዘንድ በኢየሩሳሌም ወዳለው ወደ ቤተ መቅደሱ 23 ይህም፣ “ማሕፀንን የሚከፍት ማንኛውም ወንድ ለእግዚአብሔር የተቀደሰ ይሆናል” ተብሎ በሕጉ እንደ ተጻፈው ነው፡፡ 24 በእግዚአብሔር ሕግም በተነገረው መሠረት መሥዋዕት ማለትም ‘ሁለት ዋኖሶች ወይም ሁለት የርግብ ጫጩቶች’ ያቀርቡ ዘንድ መጡ፡፡ 25 በኢየሩሳሌምም የሚኖር ስሙ ስምዖን የተባለ ሰው ነበር፡፡ ይህ ሰው ጻድቅና የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ የሚያከብር ነበር፤ ለእስራኤል መጽናኛም የሚሆነውን ይጠባበቅ ነበር፣ መንፈስ ቅዱስም በእርሱ ላይ ነበር፡፡ 26 እግዚአብሔር የቀባውን ሳያይ እንደማይሞት በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ነበር፡፡ 27 የሕጉ ሥርዓት የሚጠይቀውን ሊያደርጉለት ወላጆቹ ሕፃኑ ኢየሱስን ይዘው በመጡበት ቀን በመንፈስ ቅዱስ ተመርቶ ወደ ቤተ መቅደስ መጣ፡፡ 28 ከዚያም ስምዖን በእጆቹ አቅፎት፣ እግዚአብሔርን እያመሰገነ፣ 29 “ጌታ ሆይ፣ እንግዲህ፣ ባሪያህን እንደ ቃልህ በሰላም አሰናብተው፣ 30 ዓይኖቼ ማዳንህን አይተዋልና 31 ይህም ድነት አንተ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸው ነው፡፡ 32 እርሱም ለአሕዛብ መገለጥ ብርሃን፣ ለሕዝብህም ለእስራኤል ክብር ነው፡፡” 33 የልጁም አባትና እናት ስለ እርሱ እየተነገረ ባለው ነገር ተደነቁ፡፡ 34 ከዚያ በኋላ ስምዖን ባረካቸውና እናቱን ማርያምን፣ “በጥንቃቄ አድምጪ! ይህ ልጅ በእስራኤል ለብዙዎች ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ምክንያት፣ ክፉም ለተናገሩበት ምልክት የሚሆን ነው፡፡ 35 የብዙዎች የልባቸው ሐሳብ ይገለጥ ዘንድ የአንቺም የራስሽ ልብ በሰይፍ የሚወጋ ይሆናል፡፡” 36 ሐና የተባለች ነቢይትም በዚያ ነበረች፤ እርሷም ከአሴር ነገድ የሆነ የፋኑኤል ልጅ ነበረች፡፡ ዕድሜዋ እጅግ የገፋ ሲሆን ከጋብቻዋ በኋላ ከባልዋ ጋር ለሰባት ዓመታት ቆይታለች፡፡ 37 ከዚያ በኋላ ለሰማንያ አራት ዓመታት መበለት ሆና ኖራለች፡፡ ከቤተ መቅደስ በፍጹም ሳትለይ ቀንና ሌሊት በጾምና በጸሎት እግዚአብሔርን ታመልክ ነበር፡፡ 38 ልክ በዚያን ሰዓት ወደ እነርሱ መጥታ እግዚአብሔርን ማመስገን ጀመረች፡፡ የኢየሩሳሌምን መቤዠት ለሚጠባበቁ ለማንኛዎቹም ሰዎች ስለ ልጁ ትናገር ነበር፡፡ 39 እንደ እግዚአብሔር ሕግ እንዲያደርጉ የሚፈለግባቸውን ማንኛውንም ነገር ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ገሊላ ወደ ራሳቸው ከተማ ወደ ናዝሬት ተመለሱ፡፡ 40 ልጁ አደገ፣ ጠነከረ፣ በጥበብም ጨመረ፤ የእግዚአብሔር ጸጋም በ እርሱ ላይ ነበረ፡፡ 41 ወላጆቹም ለፋሲካ በዓል በየዓመቱ ወደ ኢየሩሳሌም ይሄዱ ነበር፡፡ 42 አሥራ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ በተለመደው ጊዜ እንደገና በዓሉን ለማክበር ሄዱ፡፡ 43 ለበዓሉ መቆየት ያለባቸውን ሁሉንም ቀናት ከቆዩ በኋላ ወደ ቤታቸው መመለስ ጀመሩ፡፡ ልጁ ኢየሱስ ግን በኢየሩሳሌም ቀረ፣ ወላጆቹም ይህንን አላወቁም ነበር፡፡ 44 ከእነርሱ ጋር ይጓዙ ከነበሩት መንገደኞች ጋር የነበረ መስሏቸው ስለነበረ የአንድ ቀን መንገድ ተጓዙ፡፡ ከዚያ በኋላም በዘመዶቻቸውና በወዳጆቻቸው ዘንድ ፈለጉት፡፡ 45 ባላገኙትም ጊዜ ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሰው በዚያ ሊፈልጉት ጀመሩ፡፡ 46 ከሦስት ቀን በኋላ እያዳመጣቸውና ጥያቄዎችን እየጠየቃቸው በመምህራን መካከል ተቀምጦ በቤተ መቅደስ ውስጥ አገኙት፡፡ 47 ያዳመጡት ሁሉ በማስተዋሉና በሚሰጣቸው መልሶች ተገረሙ፡፡ 48 ባዩትም ጊዜ ተደነቁ፡፡ እናቱም እርሱን፣ “ልጄ ሆይ፣ ለምን እንደዚህ አደረግኸን? አድምጠኝ፣ እኔና አባትህ ተጨንቀን አንተን ስንፈልግህ ነበርን” አለችው። 49 እርሱም፣ “ለምን ነበር የፈለጋችሁኝ? በአባቴ ቤት እሆን ዘንድ እንደሚገባኝ አታውቁምን?” 50 ነገር ግን እንደዚያ ሲል ምን ማለቱ እንደነበረ አልገባቸውም፡፡ 51 ከዚያ በኋላ ከእነርሱ ጋር ወደ ናዝሬት ተመለሰ፣ ይታዘዝላቸውም ነበር፡፡ እናቱም ይህንን ሁሉ ነገር በልቧ ትጠብቀው ነበር፡፡ 52 ኢየሱስ ግን በጥበብና በሰውነት ቁመና ማደጉን ቀጠለ፣ በእግዚአብሔርና በሰዎችም ፊት ያለው ሞገስ እየጨመረ ሄደ፡፡
ይህ ማርያምና ዮሴፍ በኢየሱስ ውልደት ወቅት ለምን በጉዞ ላይ እንደነበሩ ጠቅላላ የጀርባ መረጃን ይሰጣል፡፡
ይህ ቃል የታሪኩ አዲስ ክፍል መጀመሩን ይናገራል፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ሐረግ ቦታው የአዲስ ታሪክ ጅማሬ እንደሆነ ያሳያል፡፡ ቋንቋችሁ ለታሪክ መጀመርያ የተለየ መግለጫ ካለው እሱን መጠቀም ይቻላል፡፡ አንዳንድ ትርጉሞች ይህንነ ሐረግ አያካትቱትም፡፡
“ንጉሥ አውግስጦስ” ወይም “አጼ አውግስጦስ” አውግስጦስ የሮም ግዛት የመጀመርያው ንጉሥ ነበር፡፡ (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል እና የአዲስና የቀድሞ ተሳታፊዎች መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ትዕዛዝ በተለያዩ መልዕክተኞት አማካኝነት በግዛቱ ውስጥ እንደተሰራጨ ይገመታል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ትዕዛዝ ያለበትን ጽሑፍ በመልዕክተኞች ላከ” (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በዓለም ላይ የሚኖሩትን ሕዝቦች በሙሉ እንዲመዘግቡ” ወይም “በዓለም ላይ የሚገኙ ሕዝቦችን በሙሉ እንዲቆጥሩና ስማቸውን እንዲመዘግቡ” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ዓለም” የሚለው ቃል አውግስጦስ ቄሣር ይገዛ የነበረውን የዓለም ክፍል ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በግዛቱ ውስጥ” ወይም “የሮም ዓለም” (ወካይ የሚለውን ይመልከቱ)
ቄሬኔዎስ የሦርያ ክፍለ ሐገርን እንዲገዛ የተሾመ ሰው ነው፡፡ (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
“ሁሉም ጉዞ ጀመሩ” ወይም “ሁሉም እየሄዱ ነበር”
ይህ የሰዎች አባቶችና አያቶች ይኖሩበት የነበረውን ከተማ ይወክላል፡፡ ሰዎች በተለያየ ከተሞች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “አባትና አያቶቻቸው ይኖሩበት ወደነበረው ከተማ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“በመዝገብ ውስጥ ስማቸውን ለማስመዝገብ” ወይም “መንግስት እያደረገ ባለው ቆጠራ ውስጥ ለመካተት”
ዩዲቢ የሚባለው ትርጉም አርፍተ ነገሮቹን ለማሳጠር እነዚህን ሁለት ቁጥሮች አንድ ላይ በማድረግ አንድ የመሸጋገርያ ቁጥር አድርገዋቸዋል፡፡ (የጥቅስ ድልድዮች የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ዮሴፍን በታሪኩ ውስጥ እንደ አንድ ተሳታፊ አድርጎ ያስተዋውቀዋል፡፡ (የአዲስና የቀድሞ ተሳታፊዎች መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
“የዳዊት ከተማ” የሚለው ሐረግ ቤተልሔም ምን አይነት ወሳኝ ከተማ እንደሆነች የሚያሳይ የቤተልሔም ከተማ ስም ነው፡፡ ምንም እንኳ ትንሽ ከተማ ብትሆንም ንጉሥ ዳዊት የተወለደው በዚች ከተማ ነው፣ መሲሑም በዚው ከተማ እንደሚወለድ የሚናገር ትንቢት ነበር፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የንጉሥ ዳዊት ከተማ ወደነበረችው ወደ ቤተልሔም” ወይም “ንጉሥ ዳዊት ወደተወለደበት ከተማ ወደ ቤተልሔም” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“ምክንያቱም ዮሴፍ የዳዊት ዘር ስለነበር”
ይህ ማለት በሕዝብ ቆጠራው ውስጥ እንዲያካትቱት ለመንግስቱ ሹማምንት ለማሳወቅ ማለት ነው፡፡ የሚቻል ከሆነ የመንግስት የሕዝብ ቆጠራን የሚገልጽ ቃል ተጠቀም፡፡
ማርያም ከዮሴፍ ጋር ከናዝሬት ተነስታ ተጉዛ ነበር፡፡ ሴቶችም እንደወንዶች ቀረጥ ይጣልባቸው ስለነበረ እርሷም አብራ ተጉዛ መመዝገብ ነበረባት፡፡ (የአዲስና የቀድሞ ተሳታፊዎች መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
“እጮኛው” ወይም “ለእርሱ ቃል ገብታለት የነበረች” እጮኛ የነበሩ ጥንዶች በሕግ እንደተጋቡ ተደርገው ይታሰባሉ ነገር ግን በመካከላቸው ምንም አይነት አካላዊ ግንኙነት አይኖርም ነበር፡፡
ይህ የኢየሱስን ውልደትን እና ለበግ ጠባቂዎች የመላዕክቱን ብስራት ይናገራል፡፡
ዩዲቢ የሚባለው ትርጉም (እነ ዮሴፍ) የቆዩበትን ቦታ ዝርዝር መረጃ ለመጠበቅ ሲባል እነዚህን ቁጥሮች ቅደም ተከተላቸውን በመቀያየር አንድ መሸጋገርያ ቁጥር አድርጓቸዋል፡፡ (የጥቅስ ድልድዮች የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ሐረግ በታሪኩ ውስጥ ቀጣዩ ክስተት መጀመሩን ያሳያል፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
“ማርያምና ዮሴፍ በቤተልሔም እያሉ”
“ልጇን የምትገላገልበት ጊዜ ደረሰ”
በአንዳንድ ባህሎች እናቶች ልጆቻቸውን በጨርቅ ወይም በብርድ ልብስ በመጠቅለል እንዲመቻቸው ያደርጋሉ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሙሉ ሰውነቱን በጨርቅ ጠቀለለችው” ወይም “በብርድ ልብስ አጥብቃ ጠቀለለችው” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በተለየ ሁኔታ የሚሰራ እንስሶች እንዲበሉ መኖ ወይም ሌላ የከብት ምግብ የሚቀመጥበት የምግብ ማስቀመጫ ሳጥን ነገር ነው፡፡ ንጹህ እንደነበረና ለስላሳና ጠንከር ያለ ለሕጻኑ የሚመች መተኛ የሚሆን የሳር ድርቆሽ ክምር እንደነበረው ይገመታል፡፡ ከብቶች ከዋናው ቤት ሳይርቅ ቅርብ የሆነ ቦታ ላይ መኖርያ ይሰራላቸዋል፣ ይህም እነርሱን ለመመገብና ለመጠበቅ እንዲመች ነው፡፡ ማርያምና ዮሴፍ በእንስሳት መኖርያ ውስጥ ነበር ይቆዩ የነበረው፡፡
“በእንግዶ ማረፍያ ክፍል ውስጥ እነርሱ ሊያርፉ የሚችሉበት ቦታ አልነበረም” ቦታ ያለመኖሩ ምክንያት ብዙ ሰዎች ለመመዝገብ ወደ ቤተልሔም መጓዛቸው እንደሆነ ይገመታል፡፡ ሉቃስ ይህንን እንደ ተጨማሪ የጀርባ መረጃ ይናገራል፡፡ (የጀርባ ታሪክ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“ከጌታ የተላከ መልዓክ” ወይም “ጌታን ያገለግል የነበረ መልዓክ”
“ወደ እረኞቹ መጣ”
የብርሃኑ ምንጭ ከመልዓኩ መታየት ጋር በተመሳሳይ ሰዓት መጥቶ የነበረው የጌታ ክብር ነው፡፡.
“መፍራት አቁሙ”
“የሰማይ ሰራዊት” የሚለው ሐረግ ቃል በቃል የመላዕክትን ሰራዊትን፣ ወይም የተቀናጀ የመላዕክትን ስብስብ ሊወክል ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ከሰማይ ብዙ መላዕክት” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“ለእግዚአብሔር ምስጋናን በመስጠት”
የዚህ ትርጉም ሊሆኑ የሚችሉት 1) ”በከፍታ ለሚኖረው ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን ወይም” 2) “ከፍ ያለ ክብር ለእግዚአብሔርን ይሁን”
“በምድር ያሉ እግዚአብሔር የሚደሰትባቸው ሰዎች ሰላምን ያግኙ”
ይህ ሐረግ መልዓክቶቹ ከሄዱ በኋላ እረኞቹ ወዳደረጉት ነገር የታሪኩን ትኩረት ይቀይራል፡፡
“ከእረኞቹ”
“አንዱ ለሌላው”
እረኞቹ እርስ በርሳቸው እየተነጋገሩ ስለነበር፣ “እኛ” የሚል መደብ ያላቸው ቃላት በአካታች ቅርጻቸው ጥቅም ላይ መዋል አለባቸው፡፡ (አካታች “እኛ” የሚለውን ይመልከቱ)
“ማድረግ አለብን”
ይህ የሚወክለው የሕጻኑን ውልደት እንጂ የመላዕክቱን መታየት አይደለም፡፡
ይህ ሰዎች እንስሶች የሚበሉትን እንደ ሳር ድርቆሽ አይነት ምግብ እንዲበሉ የሚያስቀምጡበት የተለየ ሳጥን ነገር ነው፡፡ ይህ በሉቃስ 2:7 ላይ እንዴት እንደተተረጎመ ይመልከቱ፡፡
ይህ በአድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “መላዕክቱ ለእረኞቹ የነገሯቸውን” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“ሕጻኑ”
ይህ በአድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እረኞቹ የነገሯቸውን” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
አንድ ሰው አንድ ነገር ዋጋ እንዳለው ወይም የከበረ እንደሆነ ካሰበ ልቡ ውስጥ “ይጠብቀዋል፡፡” ማርያም ስለ ልጇ የተነገሩትን ነገሮች በሙሉ እጅግ የከበሩና ትልቅ ዋጋ እንዳላቸው ታስብ ነበር፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በጥንቃቄ ታሰላስል ነበር” ወይም “በደስታ ታስበው ነበር” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
እግዚአብሔር ለአይሁዳውያን የሰጠው ሕግ ወንድ ሕጻናትን መቼ መገረዝ እንዳለባቸውና ወላጆቹ ደግሞ ምን ዓይነት መስዋዕት ማምጣት እንዳለባቸው ይነግሯቸዋል፡፡
ይህ ሐረግ አዲስ ክስተት ከመከሰቱ በፊት ያለፈውን ጊዜ ይናገራል፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
“በሕጻኑ ሕይወት በስምንተኛው ቀን ማለቂያ።” ልጁ የተወለደበት ቀን እንደ አንደኛ ቀን ይቆጠራል፡፡
ይህ ከዚህ አዲስ ክስተት በፊት ያለፈውን ጊዜ ያሳያል፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር ያዘዘው የቀን ብዛት” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“እነርሱ በስርዓቱ መሰረት ንጹሕ እንዲሆኑ።” እዚህ ላይ የእግዚአብሔርን ድርሻም ማብራራት ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር እንደገና ንጹሃን እንደሆኑ እስኪቆጥራቸው” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
x
ማርያምና ዮሴፍ በቤተ መቅደስ ውስጥ እያሉ ሁለት ሰዎች ያገኛሉ፣ እነዚህም ሰዎች እግዚአብሔርን የሚያመሰግነውና ስለሕጻኑ ትንቢትን የተናገረው ስምኦንና ነብይቷ ሃና ናቸው፡፡
“እነሆ” የሚለው ቃል በታሪኩ ውስጥ አዲስ ውስጥ አዲስ ሰውን ያስተዋውቃል፡፡ ቋንቋችሁ ይህንን ማሳያ የራሱ መንገድ ሊኖረው ይችላል፡፡ (የአዲስና የቀድሞ ተሳታፊዎች መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ ረቂቅ ቃላት እንደ ድርጊት ተደርገው መገለጽ ይችላሉ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ጽድቅን ይፈጽም ነበር፣ እግዚአብሔርንም ይፈራ ነበር” ወይም “የእግዚአብሔርን ሕግ ይታዘዝ ነበር እግዚአብሔርንም ይፈራ ነበር፡፡
“እስራኤል” የሚለው ቃል የእስራኤልን ሕዝብ የሚወክል ምትክ ስም ነው፡፡ “ማጽናናት” ማለት አንድን ሰው “ማበረታታት” ነው፡፡ “የእስራኤል መጽናናት” ማለት ክርስቶስ ወይም መሲሑ ለእስራኤል ሕዝብ የሚያመጣውን መጽናናት የሚወክል ሐረግ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የእስራኤል ሕዝብን የሚያጽናናው” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
“መንፈስ ቅዱስ ከእርሱ ጋር ነበር” እግዚአብሔር በተለየ መንገድ ከእርሱ ጋር ነበር፣ በሕይወትም ጥበብና ምሪትን ይሰጠው ነበር፡፡
ይህ በአድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “መንፈስ ቅዱስ አሳይቶት ነበር” ወይም “መንፈስ ቅዱስ ነግሮት ነበር” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“ሳይሞት በፊት በጌታ የተቀባውን መሲህ ያየዋል”
ይህ በአድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “መንፈስ ቅዱስ እንደመራው” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
አንዳንድ ቋንቋዎች “ሄደ” ሊሉ ይችላሉ፡፡
“ወደ ቤተ መቅደስ ቅጥር ግቢ ውስጥ” ወደ ቤተ መቅደስ ሕንጻ ውስጥ መግባት የሚችሉት ካህናት ብቻ ናቸው፡፡ (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“የኢየሱስ ወላጆች”
“እንደ እግዚአብሔር ሕግ ልማድ”
“ስምኦን ሕጻኑን ኢየሱስን ወደ እጆቹ አስገባው” ወይም “ስምኦን ኢየሱስን በእጆቹ ያዘው”
“እኔ አገልጋይህ ነኝ፣ በሰላም አሰናብተኝ” ስምኦን ስለራሱ ነበር የሚያወራው፡፡
ይህ “መሞት” ለሚለው ቃል ለስላሴ ዘይቤ ነው፡፡ (ለስላሴ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“ቃል” የሚለው “ቃልኪዳን” ለሚለው ምትክ ስም ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እንደገባኸው ቃልኪዳን” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ አገላለጽ “በግሌ አይቻለሁ” ወይም “እኔ እራሴ አይቻለሁ” (ወካይ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ አገላለጽ ድነትን የሚያመጣውን ሰው ስምኦን በእጁ ይዞት የነበረውን ሕጻኑን ኢየሱን ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የላክከውን አዳኝ” ወይም “እንዲያድን የላክከውን” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
የቀደመው ሐረግ እንደተተረጎመት አተረጓጎም፣ ይህ “አንተ የላክኸውን” ወደሚለው ሊለወጥ ይችላል።
“ያሰብከውን” ወይም “እንዲከሰት ያደረግከውን”
ይህ ዘይቤ ሕጻኑ ሰዎች የእግዚአብሔርን ፈቃድ ማወቅና መረዳት እንዲችሉ ይረዳቸዋል የሚለውን ይገልጻል፡፡ እዚህ ላይ የአሕዛብ የእግዚአብሔርን ፈቃድ መረዳት ሰዎች አንድን ቁስ ለማየት ብርሃንን እንደሚጠቀሙት ተደርጎ ተመስሎ ቀርቧል፡፡ አሕዛብ የሚመለከቱት ምን እንደሆነ በግልጽ ማሳየት አለብህ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ይህ ሕጻን ብርሃን ሰዎች አጥርተው መመልከት እንዲችሉ እንደሚያደርግ፣ ልክ እንደዛ እርሱም አሕዛብ የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንዲሁ እንዲያውቁ ይረዳቸዋል” (ተለዋጭ ዘይቤ እና ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
የሚገለጠው ነገር ምን እንደሆነ በግልጽ ማስቀመጥ አስፈላጊ ሊሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የእግዚአብሔርን እውነት የሚገልጥ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“እርሱ ለሕዝብህ ለእስራኤል ክብር መምጣት ምክንያት ይሆናል”
ይህ በአድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ስምኦን ስለ እርሱ በተናገራቸው ነገሮች” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“ለሕጻኑ እናት ለማርያም እንዲህ አላት፡፡“ ማርያም የስምኦን እናት የሆነች መስሎ እንዳይታይ ጥንቃቄ ማድረግ ይጠይቃል፡፡
ስምኦን ይሄን አገላለጽ የሚጠቀመው ለማርያም ቀጥሎ የሚነግራት ነገር እጅግ ጠቃሚ እንደሆነ ለማሳየት ነው፡፡
“መውደቅ” እና “መነሳት” የሚሉት ቃላት ከእግዚአብሔር መራቅ እና ወደ እግዚአብሔር መጠጋት የሚሉትን ትርጉም ይዘዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ይህ ሕጻን በእስራኤል ለብዙዎች ከእግዚአብሔር የመራቅና ለብዙዎችም ወደ እግዚአብሔር የመቅረብ ምክንያት ይሆናል” (ተለዋጭ ዘይቤ እና ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“ብዙ ሰዎች ስለሚቃወሙት ስለ እግዚአብሔር መልዕክት ምልክት”
ይህ ዘይቤ ማርያም ወደፊት የሚሰማትን ጥልቅ የሆነ ሀዘን ያሳያል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሐዘንሽ ልብሽ በሰይፍ እንደተወጋ ያህል እጅግ ጥልቅ ይሆናል“ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ልብ” የሚለው ቃል የሰዎችን ውስጣዊ ማንነት ይወክላል፡፡ ይህ በአድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የብዙ ሰዎችን ሃሳብ ይገልጥ ዘንድ” ወይም “ብዙ ሰዎች በድብቅ የሚያስቡን ይገልጥ ዘንድ” (ምትክ ስም እና ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ማርያም ዮሴፍና ኢየሱስ ቤተልሔም ከተማን ለቅቀው ኢየሱስ ልጅነቱን ወደሚያሳልፍባት ወደ ናዝሬት ከተማ ይመለሳሉ፡፡
ይህ በአድራጊ ቅርጽ መቀመጥ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የእግዚአብሔር ሕግ እንዲያደርጉ የሚያዝዘውን” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ 12 ዓመት ሲሞላው ከቤተሰቡ ጋር ወደ ኢየሩሳሌም ሄደ፡፡ በዚያም እያለ የቤተ መቅደስ መምህሮችን ጥያቄዎች ይጠይቃቸው ነበር፣ እርሱም የእነርሱን ጥያቄዎች ይመልስላቸው ነበር፡፡
ይህ ተጨማሪ የጀርባ መረጃ ነው፡፡ (የጀርባ ታሪክ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“የኢየሱስ ወላጆች”
ኢየሩሳሌም በእስራኤል ከሚገኙ ከሌሎች ቦታዎች በመሬት ከፍታ ከፍ ብላ የምትገኝ ከተማ ነበረች፣ ስለዚህ ወደ ኢየሩሳሌም ስለመሄድ ሲወራ “መውጣት” ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡
“በተለመደው ሰዓት” ወይም “በየዓመቱ ያደርጉ እንደነበረው”
“ክብረ በዓሉ የሚከበርባቸው ቀናት ካለፉ በኋላ” ወይም “ክብረ በዓሉ መከበር ላለበት ቀናት አክብረው ከጨረሱ በኋላ”
x
ይህ ሐረግ በታሪኩ ውስጥ የተከሰተን ወሳኝ ክስተት ያሳያል፡፡ ቋንቋችሁ እንደዚህ ዓይነትን ነገር ማሳያ መንገድ ካለው እሱን መጠቀም ይቻላል፡፡
ይህ የመቅደሱ ቅጥር ግቢን ያሳያል፡፡ ወደ ቤተ መቅደስ ውስጥ መግባት የሚችሉት ካህናት ብቻ ነበሩ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በመቅደሱ ቅጥር ግቢ ውስጥ” ወይም “በቤተ መቅደስ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ቃለ በቃል መሃል ላይ ማለት አይደለም፡፡ ይልቁንም “አብሮ ሆኖ” ፣ “በእነርሱ መካከል” ወይም “በእነርሱ ተከብቦ” የሚለውን ትርጉም ይይዛል፡፡
“የኃይማኖት መምህሮች” ወይም “ስለ እግዚአብሔር ለሰዎች ያስተምሩ የነበሩ”
12 ዓመቱ የሆነና፣ የኃይማኖት ትምህርት ያልተማረ አንድ ልጅ በጥሩ ሁኔታ ጥያቄዎችን መመለስ መቻሉ እንዴት እንደሆነ አልገባቸውም፡፡
“ምን ያህል ማስተዋል በመቻሉ” ወይም “ስለ እግዚአብሔር ብዙ ማስተዋል በመቻሉ”
“እንዴት በጥሩ ሁኔታ እንደመለሰላቸው” ወይም “ጥያቄዎቻቸውን በጥሩ ሁኔታ በመመለሱ”
“ማርያምና ዮሴፍ ኢየሱስን ሲያገኙት”
ይህ ቀጥተኛ ያልሆነ ተግሳጽ ነው ይህም እነርሱ ወደ ቤት ሲሄዱ አብሯቸው ስላልነበረ ነው፡፡ ይህ ስለ እርሱ እንዲጨነቁ አድርጓቸው ነበር፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እኛን እንዲህ እንድንሆን ማድረግ አልነበረብህም!” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ቃል ብዙ ጊዜ አንድ አዲስ ወይም ወሳኝ የሆነ ሁነት ሊጀምር መሆኑን ለማሳየት ጥቅም ላይ የሚውል ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ይህ አዲስ ድርጊት የት እንደሚጀምር ላማሳየት ሊጠቅም ይችላል፡፡ በቋንቋችሁ ውስጥ በእንዲህ ዓይነት መንገድ ጥቅም ላይ የሚውል ሀረግ ካለው እዚህ ላይ ለመጠቀም አግባብነት ያለው መሆኑን አስብ።
ኢየሱስ ወላጆቹን በለስላሴው ለመገሰጽ ሁለት ጥያቄዎችን ይጠቀማል፣ እነርሱ ያልተረዱት በሰማይ ያለው አባቱ የሰጠው ዓላማ እንዳለም ይነግራቸዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ስለ እኔ መጨነቅ የለባችሁም” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ወላጆቹ አባቱ ሊያደርገው የሰጠው ዓላማ እንዳለ ማወቅ እንዳለባቸው ለመንገር ሁለተኛውን ጥያቄ ይጠቀማል፡፡ “(ማድረግ) እንዳለብኝ ማወቅ ነበረባችሁ” አማራጭ (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
የዚህ ትርጉም ሊሆኑ የሚችሉ 1) ኢየሱስ እነዚህን ቃላት በጥንቃቄ መርጦ የተናገረው አባቱ የሰጠውን ስራ እየሰራ እንደሆነ ለማሳየት ነው፣ ወይም 2) እነዚህ ቃላት ኢየሱስ የነበረበትን ቦታ፣ “የአባቴ ቤት” የሚያስረዳ ፈሊጥ ነው፡፡ ቀጣዩ ቁጥር የኢየሱስ ወላጆች ኢየሱስ የሚነግራቸውን ነገሮች አልተረዱትም ስለሚል ይህን ከዚህ በላይ ለማብራራት ባይሞከር ጥሩ ነው፡፡
የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ፣ በ12 አመቱ የእውነት አባቱ የማርያም ባል የነበረው ዮሴፍ ሳይሆን እግዚአብሔር እንደነበር አስተውሎ ነበር፡፡ (ልጅ እና አባትን መተርጎም የሚለውን ይመልከቱ)
“ኢየሱስ ከማርያምና ከዮሴፍ ጋር ወደ ቤት ተመለሰ”
“ለእነርሱ ይታዘዝ ነበር” ወይም “ሁልጊዜ ለእነርሱ ይታዘዝ ነበር”
እዚህ ላይ “ልብ” የሚለው ቃል የአንድን ሰው ውስጣዊ ማንነት ወይም አእምሮ የሚያሳይ ምትክ ስም ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በጥንቃቄ እነዚህን ሁሉ ነገሮች ታስብ ነበር” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ )
“ጠቢብና ጠንካራ ሆነ” እነዚህ አእምሮአዊና አካላዊ እድገትን ያመለክታሉ፡፡
ይህ መንፈሳዊና ማሕበራዊ እድገትን ያሳያል፡፡ እነዚህ ተነጣጥለው መጻፍ ይችላሉ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር አብዝቶ ባረከው፣ በሰዎችም ዘንድ የበለጠ የተወደደ ሆነ”
1 ጢባርዮስ ቄሣር በነገሠ በአሥራ አምስተኛው ዓመት፣ ጴንጤናዊው ጲላጦስ የይሁዳ ገዥ፣ ሄሮድስ የገሊላ አራተኛው ክፍል ገዥ፣ ወንድሙ ፊልጶስ የኢጡርያስና የጥራኮኒዶስ የአራተኛው ክፍል ገዥ፣ ሊሳኒዮስም የሳቢላኒስ አራተኛው ክፈል ገዥ 2 እንደዚሁም ሐናና ቀያፋ ሊቃነ ካህናት በነበሩበት ጊዜ የእግዚአብሔር ቃል ለዘካርያስ ልጅ ለዮሐንስ በምድረ-በዳ መጣ፡፡ 3 ለኃጢአት ይቅርታ የንስሓን ጥምቀት እየሰበከ በዮርዳኖስ ወንዝ አውራጃ ሁሉ ተመላለሰ፡፡ 4 ይህም በነቢዩ በኢሳይያስ መጽሐፍ፣ “በምድረ-በዳ የሚጣራ ሰው ድምፅ፣ ‘የእግዚአብሔርን መንገድ አዘጋጁ፣ ጎዳናውንም አቅኑ፡፡ 5 ሸለቆ ሁሉ ይሞላል፣ ተራራውና ኮረብታው ደልዳላ ይሆናል፣ ጠማማው መንገድ ቀና ይሆናል፣ ሸካራውም መንገድ የተመቸ ይሆናል፡፡ 6 ሰዎችም ሁሉ የእግዚአብሔርን ማዳን ያያሉ፡፡’” 7 ስለዚህ በእርሱ ለመጠመቅ ይመጣ ለነበረው ከፍተኛ ቁጥር ላለው ሕዝብ ዮሐንስ እንደዚህ አላቸው፣ “እናንተ የመርዘኛ እባብ ልጆች፣ ሊመጣ ካለው ቁጣ እንድትሸሹ ማን አስጠነቀቃችሁ? 8 ለንስሓ የሚሆን ፍሬ አፍሩ፣ እርስ በርሳችሁም፣ ‘አባታችን አብርሃም አለን’ አትበሉ፣ ምክንያቱም ከእነዚህ ድንጋዮች እንኳን እግዚአብሔር ለአብርሃም ልጆችን ሊያስነሣለት ይችላል፡፡ 9 መጥረቢያ በዛፎች ግንድ ሥር ተቀምጦአል፤ ስለዚህ መልካም ፍሬ የማያፈራ ዛፍ ሁሉ ተቆርጦ ወደ እሳት ውስጥ ያጣላል፡፡” 10 ከዚያ በኋላ ተሰብስበው የነበሩት ሰዎች እንደዚህ ብለው ጠየቁት፣ “እንግዲህ ምን እናድርግ?” 11 እርሱም እንደዚህ ብሎ መለሰላቸው፣ “አንድ ሰው ሁለት ልብስ ካለው ምንም ለሌለው ለሌላ ሰው ይስጠው፤ ትርፍ ምግብ ያለውም እንደዚሁ ያድርግ፡፡” 12 ከዚያ በኋላም አንዳንድ ቀረጥ ሰብሳቢዎች ለመጠመቅ መጡና እንደዚህ አሉት፣ “መምህር ሆይ፣ እኛስ ምን ማድረግ ይገባናል?” 13 እርሱም እንደዚህ አላቸው፣ “መሰብሰብ ከሚገባችሁ ገንዘብ በላይ አትሰብስቡ፡፡” 14 አንዳንድ ወታደሮችም እንደዚህ ብለው ጠየቁት፣ “እኛስ፣ ምን ማድረግ ይገባናል?” እርሱም እንደዚህ አላቸው፣ “ከማንም ላይ አስገድዳችሁ ገንዘብ አትውሰዱ፣ ማንንም በሐሰት አትክሰሱ፡፡ የምታገኙትም ደመወዝ ይብቃችሁ፡፡” 15 ሕዝቡ የክርስቶስን መምጣት እየተጠባበቁ ሳሉ፣ ሰዎች ሁሉ በልባቸው እርሱ ክርስቶስ ይሆን እያሉ ስለ ዮሐንስ ይደነቁ ነበር፡፡ 16 እንደዚህ በማለት ዮሐንስ ለሁሉም መልስ ሰጣቸው፣ “እኔ በበኩሌ በውሃ አጠምቃችኋለሁ፣ የጫማውን ማሠሪያ መፍታት እንኳን የማይገባኝ ከእኔ ይልቅ ብርቱ የሆነ ይመጣል፡፡ እርሱ በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ያጠምቃችኋል፡፡ 17 አውድማውን ፈጽሞ ያጠራውና ስንዴውን ወደ ጎተራ ያስገባ ዘንድ የሚያበራይበት መንሽ በእጁ ነው፡፡ ገለባውን ግን በማይጠፋ እሳት ያቃጥለዋል፡፡” 18 ሌሎች ብዙ ምክሮችንም በመምከር፣ የምሥራቹን ቃል ለሕዝቡ ሰበከላቸው፡፡ 19 የወንድሙን ሚስት ሄሮዳይዳን ስላገባና ስላደረጋቸውም ሌሎች ክፉ ሥራዎች የአራተኛው ክፍል ገዥ የነበረውን ሄሮድስንም ገሰጸው፡፡ 20 ሄሮድስ ግን ከዚህም የባሰ ክፉ ሥራ ሠራ፣ ዮሐንስን ወህኒ ቤት አስገብቶ ቆለፈበት፡፡ 21 ሰዎች ሁሉ በዮሐንስ እየተጠመቁ ሳሉ፣ ኢየሱስም ደግሞ ተጠመቀ፡፡ እየጸለየም ሳለ ሰማያት ተከፈቱ፡፡ 22 መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል በአካል በእርሱ ላይ አረፈ፣ በዚህም ጊዜ ከሰማይ፣ “አንተ፣ ውድ ልጄ ነህ፤ በአንተ እጅግ ደስ ይለኛል፡፡” የሚል ድምፅ መጣ፡፡ 23 በዚህን ጊዜ ኢየሱስ ራሱ ማስተማር ሲጀምር ዕድሜው ሰላሳ ዓመት ገደማ ነበር፡፡ (ይገመት እንደነበረው) እርሱ የኤሊ ልጅ የነበረው የዮሴፍ ልጅ 24 ኤሊም የማቲ ልጅ፣ የሌዊ ልጅ፣ የሚልኪ ልጅ፣ የዮና ልጅ፣ የዮሴፍ ልጅ፣ 25 የማታትዩ ልጅ፣ የአሞጽ ልጅ፣ የናሆም ልጅ፣ የኤሲሊም ልጅ፣ የናጌ ልጅ፣ 26 የማኦት ልጅ፣ የማታትዩ ልጅ፣ የሰሜይ ልጅ፣ የዮሴፍ ልጅ፣ የዮዳ ልጅ፣ 27 የዮናን ልጅ፣ የሬስ ልጅ፣ የዘሩባቤል ልጅ፣ የሰላትያል ልጅ፣ የኔር ልጅ፣ 28 የሚልኪ ልጅ፣ የሐዲ ልጅ፣ የዮሳስ ልጅ፣ የቆሳም ልጅ፣ የኤልሞዳም ልጅ፣ የኤር ልጅ፣ 29 የዮሴዕ ልጅ፣ የአልዓዛር ልጅ፣ የዮራም ልጅ፣ የማጣት ልጅ፣ የሌዊ ልጅ፣ 30 የስምዖን ልጅ፣ የይሁዳ ልጅ፣ የዮሴፍ ልጅ፣ የዮናም ልጅ፣ የኤልያቄም ልጅ፣ 31 የሜልያ ልጅ፣ የማይናን ልጅ፣ የማጣት ልጅ፣ የናታን ልጅ፣ የዳዊት ልጅ፣ 32 የእሴይ ልጅ፣ የኢዮቤድ ልጅ፣ የቦዔዝ ልጅ፣ የሰልሞን ልጅ፣ የነአሶን ልጅ፣ 33 የአሚናዳብ ልጅ፣ የአራም ልጅ፣ የአሮኒ ልጅ፣ የኤስሮም ልጅ፣ የፋሬስ ልጅ፣ የይሁዳ ልጅ፣ 34 የያዕቆብ ልጅ፣ የይስሐቅ ልጅ፣ የአብርሃም ልጅ፣ የታራ ልጅ፣ የናኮር ልጅ፣ 35 የሴሮህ ልጅ፣ የራጋው ልጅ፣ የፋሌቅ ልጅ፣ የአቤር ልጅ፣ የሳላ ልጅ፣ 36 የቃይንም ልጅ፣ የአርፋክስድ ልጅ፣ የሴም ልጅ፣ የኖኅ ልጅ፣ የላሜህ ልጅ፣ 37 የማቱሳላ ልጅ፣ የሄኖክ ልጅ፣ የያሬድ ልጅ፣ የመላልኤል ልጅ፣ የቃይናን ልጅ፣ 38 የሄኖስ ልጅ፣ የሴት ልጅ፣ የአዳም ልጅ፣ የእግዚአብሔር ልጅ፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስ እንደ ተነበየው፣ ዮሐንስ መልካም ዜናን ለህዝቡ መስበክ ጀመረ፡፡
እነዚህ ጥቅሶች የኢየሱስ የአክስት ልጅ ዮሐንስ አገልግሎቱን ሲጀምር ምን እየተደረገ እንደሆነ ለመናገር የጀርባ ታሪክ መረጃን ይሰጣሉ፡፡
“ጢባርዮስ ቄሳር ለአስራ አምስት አመታት በመራ በዚያ ጊዜ” (ደረጃ የሚያሳይ ቁጥር የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ የወንድ ስሞች ናቸው፡፡ (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ የግዛት ስሞች ናቸው፡፡ (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
“ሐና እና ቀያፋ እንደ ሊቀ ካህናት ባንድነት በሚያገለግሉበት ጊዜ፡፡” ሐና ሊቀ ካህን ነበር፣ ሮማውያን አማቹን ቀያፋን እንደ ሊቀ ካህን እንዲተካው ከሾሙት በኋላ እንኳን ሳይቀር አይሁዶችም ለእርሱ እውቅና መስጠታቸውን ቀጥለዋል፡፡”
ጸሐፊው የእግዚአብሔር መልእክት እርሱን ወደሚያዳምጡት ሰዎች የሚንቀሳቀስ ሰው እንደሆነ አድርጎ ይናገራል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር መልእክቱን ተናገረ”
“ጥምቀት” እና “ንስሀ” የሚሉት ስሞች እንደ ድርጊት ሊገለፁ ይችላሉ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እርሱም ሰዎች ንስሀ እየገቡ እንደሆነ ለማሳየት መጠመቅ እንዳለባቸው ሰበከ” (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)
እነርሱ እግዚአብሔር ኃጢአታቸውን ይቅር እንዲል ንስሀ ይገባሉ፡፡ “ይቅርታ” የሚለው ስም እንደ ድርጊት ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ኃጢአታቸው ይቅር እንዲባል” ወይም “እግዚአብሔር ኀጢአታቸውን ይቅር እንዲል” (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)
ጸሐፊው ሉቃስ መጥምቁ ዮሐንስን የሚመለከት ምንባብ ከነቢዩ ኢሳይያስ ጠቀሰ፡፡
እነዚህ ቃላቶች ከነቢዩ ኢሳይያስ የተወሰደ ጥቅስ ያቀርባሉ፡፡ እነርሱ በገቢር/አድራጊ ቅርፅ ሊገለፁ ይችላሉ፣ የትዘለሉት ቃላቶችም መቅረብ ይችላሉ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ይህ ነቢዩ ኢሳይያስ የእርሱን ቃላት በያዘውን መጽሐፍ እንደፃፈው እንደዚያው ሆነ” ወይም “ዮሐንስ ነቢዩ ኢሳይያስ በመፅሀፉ የፃፈውን መልእክት ፈፀመ” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ እና አስጨምሬ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ እንደ አረፍተ ሀሳብ ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በበረሃ ውስጥ የሚጮኽ የአንድ ሰው ድምፅ ተሰማ” ወይም “እነርሱ በበረሃ ውስጥ የሚጮኽ የአንድ ሰው ድምፅ ሰሙ”
ሁለተኛው ትእዚያዝ ለመጀመሪያው በይበልጥ ዝርዝር ይጨምርለታል ወይም ያብራራዋል፡፡
“ለጌታ መንገዱን አዘጋጁ፡፡” ይህን ማድረግ የጌታ መልእክት ሲመጣ ለመስማት መዘጋጀትን ይወክላል፡፡ ሰዎች ከኀጢአታቸው ንስሀ በመግባት ይህን ያደርጉታል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እርሱ ሲመጣ የጌታን መልእክት ለመስማት ተዘጋጅ” ወይም “ንስሀ ግባ፣ ለሚመጣው ጌታ የተዘጋጀህ ሁን” (ተለዋጭ ዘይቤ እና ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“መተላለፊያ” ወይም “ጎዳና”
ሰዎች በጣም ወደ እነርሱ እየመጣ ላለ ከፍተኛ ስልጣን ያለው ሰው መንገድ ሲያዘጋጁ፣ ከፍተኛ ቦታዎችን ይቆርጡና መንገዱ ደልዳላ እንዲሆን ዝቅተኛ ቦታዎችን ይሞላሉ፡፡ ይህ በፊተኛው ጥቅስ ውስጥ የተጀመረው ተለዋጭ ዘይቤ አካል ነው፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በመንገዱ ውስጥ ዝቅተኛ ቦታውን ሁሉ ይሞላሉ” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ተራራውን እና ኮረብታውን ሁሉ ደልዳላ ያደርጋሉ” ወይም “በመንገዱ ውስጥ ከፍተኛ ቦታውን ሁሉ ያስወግዳሉ” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ እንደ ድርጊት ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር እንዴት ሰዎችን ከኃጢአት እንደሚያድን ማወቅ” (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ዮሐንስ እነርሱን እንዲያጠምቃቸው” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ተለዋጭ ዘይቤ ነው፡፡ እዚህ ላይ “ልጆች” “የወላጆቹ ባህርይ ያለው” ማለት ነው፡፡ እፉኝቶች ክፋትን የሚወክሉ እና አደገኛ የሆኑ መርዛማ እባቦች ናቸው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እናንተ ክፉ መርዛማ እባቦች” ወይም “እናንተ እንደ መርዛማ እባብ ክፉ ናችሁ” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
እርሱ በእርግጥ መልስ እንዲሰጡ እየጠበቀ አልነበረም፡፡ ዮሐንስ ህዝቡን እየገሰፀ ነበር ምክንያቱም እግዚአብሔር እንዳይቀጣቸው እነርሱን እንዲያጠምቅ እየጠየቁት ነበር ነገር ግን ኃጢአት መስራታቸውን ማቆም አልፈለጉም፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ከእግዚአብሔር ቁጣ በእንዲህ ዓይነት መንገድ መሸሽ አትችሉም!” ወይም “ከእግዚአብሔር ቁጣ በመጠመቅ ብቻ ማምለጥ አትችሉም!” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
“ቁጣ” የሚለው ቃል እዚህ ላይ የእግዚአብሔርን ቅጣት ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል ምክንያቱም የእርሱ ቁጣ ይቀድመዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር እየላከ ካለው ቅጣት” ወይም “እርሱ ሊተገብረው ካለው ከእግዚአብሔር ቁጣ” (ምትክ ስም እና ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
በዚህ ተለዋጭ ዘይቤ ውስጥ፣ የሰው ባህርይ ከፍሬ ጋር ተነፃፅሯል፡፡ ልክ ተክል ለተክሉ አይነት ተገቢ የሆነ ፍሬ እንዲያፈራ እንደሚጠበቅ ሁሉ እርሱ ንስሀ እንደገባ የሚናገር ሰው በፅድቅ እንዲኖር ይጠበቃል፡፡. አማራጭ ትርጉም፡- “ንስሀ እንደገባህ የሚያሳይ የፍሬ አይነት አፍራ“ ወይም “ከኃጢአትህ መመለሰስህን የሚያሳዩ መልካም ነገሮችን አድርግ” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“ለራሳችሁ መናገር” ወይም “ማሰብ”
“አብርሀም የእኛ የዘር ግንድ ነው” ወይም “እኛ የአብርሀም ተወላጅ ነን፡፡” ይህንን ለምን እንደሚሉ ግልፅ ካልሆነ፣ የተጠቀሰውን መረጃ ደግሞ መጨመር ትችላለህ፡- “እግዚአብሔር እኛን እንዳይቀጣን” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“ለአብርሃም ልጆች መፍጠር”
ዮሐንስ ምናልባትም በዮርዳኖስ ባህር ያሉትን ትክክለኛ ድንጋዮች እያመለከተ ነበር፡፡
የዛፎችን ስር መቁረጥ እንዲችል ቦታው ላይ ያለ ምሳር ሊጀምር ስላለው ቅጣት ተለዋጭ ዘይቤ ነው፡፡ በገቢር/አድራጊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር ምሳሩን በዛፎች ስር እንዳስቀመጠ ሰው እንደዛው ነው” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ እና ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “እሳት” ለቅጣት ተለዋጭ ዘይቤ ነው፡፡ ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እርሱ ማንኛውንም ዛፍ ይቆርጣል… እናም ወደ እሳት ውስጥ ይጥለዋል” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ እና ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
ዮሐንስ ሰዎች ከህዝቡ ውስጥ ለሚጠይቁት ጥያቄዎች መልስ መስጠት ጀመረ፡፡
x
ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ዮሐንስ እነርሱን እንዲያጠምቃቸው” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“ተጨማሪ ገንዘብ አትጠይቁ” ወይም “ተጨማሪ ገንዘብ አትውሰዱ፡፡” ቀረጥ ሰብሳቢዎች መሰብሰብ ከነበረባቸው ገንዘብ ተጨማሪ እየሰበሰቡ ነበር፡፡ ዮሐንስ ያንን ማድረግ እንዲያቆሙ ነገራቸው፡፡
ይህ የቀረጥ ሰብሳቢዎቹ ስልጣን ከሮም እንደመጣ ለማሳየት ተገብሮ/ተሳቢ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሮማውያን እንድትወስዱ ስልጣን ከሰጧችሁ” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“እኛ ወታደሮችስ፣ ምን ማድረግ አለብን?” “እኛ” እና “ለኛ” የሚሉት ቃላት ውስጥ ዮሐንስ አልተካተተም፡፡ ወታደሮቹ ዮሐንስ ለሰተበሰበው ህዝብ እና ለቀረጥ ሰብሳቢዎች ምን ማድረግ እንዳለባቸው እንደተናገረ አመልክተዋል እነርሱም እንደ ወታደሮች ምን እንደሚያደርጉ ማወቅ ይፈልጋሉ፡፡ (አግላይ እና አካታች “እኛ” የሚለውን ይመልከቱ)
ወታደሮቹ ገንዘብ ለማግኘት ሲሉ በሰዎች ላይ ሐሰተኛ ክስ እያዘጋጁ የነበረ ይመስላል፡፡ ይህ በትክክል ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በተመሳሳይ መንገድ፣ ከእነርሱ ገንዘብ ለማግኘት ማንንም ሰው በሀሰት አትክሰሱ” ወይም “ንፁሁን ሰው ህገወጥ ነገር ሰርቷል ብላችሁ አትናገሩ”
“በክፍያችሁ የረካችሁ ሁኑ”
“ምክንያቱም ሕዝቡ፡፡” ይህ ወደ ዮሐንስ መጥተው የነበሩትን ሰዎች ያመለክታል፡፡
“ሁሉም ሰው ስለ ዮሐንስ ምን ማሰብ እንዳለበት እርግጠኛ አልነበረም፤ ራሳቸውንም “እርሱ ክርስቶስ ይሆንን?” ብለው ጠየቁ” ወይም “ማንም ሰው ስለ ዮሐንስ ምን ማሰብ እንዳለበት እርግጠኛ አልበነረም ምክንያቱም እርሱ ምናልባት ክርስቶስ ይሆናል ብለው እያሰቡ ነበር፡፡”
ታላቅ ሰው ስለ መምጣቱ ዮሐንስ የሰጠው መልስ ዮሐንስ ክርስቶስ እንዳልሆነ በግልፅ ያመለክታል፡፡ ይህንን ለአንባቢው በትክክል መግለፅ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ዮሐንስ ለሁሉም እንዲህ በማለት እርሱ ክርስቶስ እንዳልሆነ ያብራራል” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“እኔ ውሀን በመጠቀም አጠምቃለሁ” ወይም “እኔ በውሀ አማካኝነት አጠምቃለሁ”
“የእርሱን ጫማ ጠፍር እንኳን ለማላላት በቂ ያልሆንሁ፡፡” የጫማን ጠፍር መፍታት የባሪያ ተግባር ነበር፡፡ የሚመጣው እርሱ በጣም ታላቅ ስለሆነ ዮሐንስ የእርሱ ባሪያ ለመሆን እንኳን የሚገባ እንዳልሆነ እየተናገረ ነበር፡፡
ይህ ተለዋጭ ዘይቤ ሰውን ከውሀ ጋር የሚያገናኘውን የውሀ ጥምቀት እነርሱን ከመንፈስ ቅዱስ እና ከእሳት ጋር ከሚያገናኘው መንፈሳዊ ጥምቀት ጋር ያወዳድራል፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “እሳት” የሚለው ቃል ሊያመለክት የሚችለው 1) ፍርድ ወይም 2) ማንጻት፡፡ “እሳት” የሚልወን እንዳለ መተው ይመረጣል። (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“መንሽ ይዟል ምክንያቱም እርሱ ዝግጁ ነው፡፡” ዮሐንስ ክርስቶስ በህዝብ ላይ ለመፍረድ ስለመምጣቱ ሲናገር እርሱ የስንዴውን ፍሬ ከገለባው ለመለየት የተዘጋጀ ገበሬ እንደሆነ አድርጎ ይናገራል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እርሱ ዝግጁ እንደሆነ ገበሬ በህዝብ ላይ ለመፍረድ ዝግጁ ነው” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የስንዴውን ፍሬ ከገለባው ለመለየት ስንዴውን ወደ አየር የሚበትን መሳሪያ ነው፡፡ ከባድ ፍሬዎች ወደ ታች ይወድቃሉ የማይፈለገው ገለባ ደግሞ በንፋስ ይወሰዳል፡፡ ከሹካ መሰል ማበጠርያ ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡
አውድማ የመውቃት ዝግጅት ላይ ስንዴው የሚከመርበት ቦታ ነበር፡፡ አውድማውን “ማጥራት” ፍሬዎቹን ወቅቶ መጨረስ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የእርሱን ፍሬዎች ወቅቶ መጨረስ”
ስንዴው የሚጠበቅ እና የሚከማች ተቀባይነት ያለው አዝመራ ነው፡፡
ገለባው ለምንም ጠቃሚ አይደለም፣ ስለዚህ ሰዎች ያቃጥሉታል፡፡
x
ኢየሱስ አገልግሎቱን የጀመረው በጥምቀቱ ነው፡፡
የቀደመው ጥቅስ ሄሮድስ ዮሐንስን ወህኒ ቤት አስገባው ይላል፡፡ በቁጥር 21 ላይ የጀመረው መግለጫ ዮሐንስ ከመታሰሩ በፊት የተከሰተ እንደሆነ ግልፅ ማድረግ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡ ዩዲቢ የሚባለው ትርጉም ቁጥር 21ን “ነገር ግን ዮሐንስ ወህኒ ቤት ከመግባቱ በፊት” ብሎ በመጀመር ግልጽ ያደርገዋል፡፡ (የሁነቶች ቅደም ተከተል የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ሀረግ በታሪኩ ውስጥ የአዲስ ክስተት ጅማሬን ያመላክታል፡፡ የአንተ ቋንቋ ይህንን ለማድረግ መንገድ ካለው፣ እርሱን እዚህ ላይ ለመጠቀም ማሰብ ትችላለህ፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
“ዮሐንስ ህዝቡን ሁሉ ባጠመቀበት ጊዜ፡፡” “ህዝቡ ሁሉ” የሚለው ሀረግ ከዮሐንስ ጋር የነበሩትን ህዝብ ያመለክታል፡፡ (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ዮሐንስ ደግሞ ኢየሱስን አጠመቀው” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“ሰማይ ክፍት ሆነ፡፡” ይህ ከተራ የደመና መጥራት የበለጠ ነው፣ ነገር ግን ምን ማለት እንደሆነ ግልፅ አይደለም፡፡ ምናልባትም በሰማይ ውስጥ ቀዳዳ ታየ ማለት ነው፡፡
“መንፈስ ቅዱስ በሰውነት ቅርፅ በኢየሱስ ላይ እንደ ርግብ ወረደ”
እዚህ ላይ “ድምፅ ከሰማይ መጣ” የሚለው ሰዎች በምድር ላይ ሆነው እግዚአብሔር ከሰማይ ሲናገር መስማታቸውን ይወክላል፡፡ እግዚአብሔር ለኢየሱስ ተናገሮ እንደነበረ ግልፅ ማድረግ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ድምፅ ከሰማይ ተናገረ” ወይም “እግዚአብሔር ከሰማይ ኢየሱስን እንዲህ በማለት ተናገረ” (ምትክ ስም እና ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ለኢየሱስ አስፈላጊ ስም ነው፣ የእግዚአብሔር ልጅ፡፡ (ልጅ እና አባትን መተርጎም የሚለውን ይመልከቱ)
ሉቃስ የኢየሱስን የዘር ግንድ አባቱ ነው ተብሎ በሚታሰበው በዮሴፍ መስመር በኩል ይዘረዝራል፡፡
እዚህ ላይ ይህ ሀረግ ጥቅም ላይ የዋለው መረጃው ከታሪክ ወደ ኢየሱስ እድሜ እና የዘር ግንድ የጀርባ ታሪክ መለወጡን ለማመልከት ነው፡፡ (የጀርባ ታሪክ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“30 አመት” (ቁጥሮች የሚለውን ይመልከቱ)
“እርሱ የዮሴፍ ልጅ እንደሆነ ይታሰብ ነበር” ወይም “ሰዎች እርሱ የዮሴፍ ልጅ ነው ብለው ያምኑ ነበር”
በአንተ ቋንቋ ሰዎች በብዛት የዘር ግንድ እንዴት እንደሚዘረዝሩ አስብ፡፡ በሙሉ ዝርዝሩ ውስጥ አንድ አይነት አፃፃፍ መጠቀም አለብህ፡፡ ሊሆኑ የሚችሉ አቀራረቦች 1) “የኤሊ ልጅ ማን ነበር፣ የማቲ ልጅ ማን ነበር፣ የሌዊ ልጅ ማን ነበር” ወይም 2) “ዮሴፍ የኤሊ ልጅ ነበር፣ ኤሊ የማቲ ልጅ ነበር፣ ማቲ የሌዊ ልጅ ነበር” ወይም 3) “የኤሊ አባት ማቲ ነበር፣ የማቲ አባት ሌዊ ነበር” (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የኢየሱስ የዘር ግንድ ዝርዝር ቀጣይ ነው፡፡ የፊተኛው ቁጥር ላይ የተጠቀምክበትን አንድ አይነት አቀራራብ ተጠቀም፡፡ (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የኢየሱስ የዘር ግንድ ዝርዝር ቀጣይ ነው፡፡ የፊተኛው ቁጥር ላይ የተጠቀምክበትን አንድ አይነት አቀራራብ ተጠቀም፡፡ (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
ሰላትያል የሚለው ስም ሺያልትያል ለሚለው ስም ሌላ የቃላት አፃፃፍ ሊሆን ይችላል (አንዳንድ የእንግሊዘኛ ትርጉሞች እንደሚጠቀሙት)፣ ነገር ግን በሚገባ መለየት አስቸጋሪ ነው፡፡
ይህ የኢየሱስ የዘር ግንድ ዝርዝር ቀጣይ ነው፡፡ የፊተኛው ቁጥር ላይ የተጠቀምክበትን አንድ አይነት አቀራራብ ተጠቀም፡፡ (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የኢየሱስ የዘር ግንድ ዝርዝር ቀጣይ ነው፡፡ የፊተኛው ቁጥር ላይ የተጠቀምክበትን አንድ አይነት አቀራራብ ተጠቀም፡፡ (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የኢየሱስ የዘር ግንድ ዝርዝር ቀጣይ ነው፡፡ የፊተኛው ቁጥር ላይ የተጠቀምክበትን አንድ አይነት አቀራራብ ተጠቀም፡፡ (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
“አዳም፣ በእግዚአብሔር የተፈጠረ” ወይም “አዳም፣ ከእግዚአብሔር የነበረ” ወይም “አዳም፣ የእግዚአብሔር ልጅ፣ ማለት የምንችለው”
1 ከዚያ በኋላ፣ ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ ከዮርዳኖስ ወንዝ ተመለሰ፤ መንፈስም ወደ ምድረ-በዳ መራው፡፡ 2 በዚያም ለአርባ ቀናት በዲያብሎስ ተፈተነ፡፡ በእነዚያም ቀናት ምንም አልበላም፣ ያም ወቅት በተጠናቀቀ ጊዜ ተራበ፡፡ 3 ዲያብሎስም፣ “የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ይህ ድንጋይ እንጀራ እንዲሆን እዘዝ” አለው፡፡ 4 ኢየሱስም፣ “’ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም’ ተብሎ ተጽፎአል፡፡” ብሎ መለሰለት፡፡ 5 ከዚያ በኋላም ዲያብሎስ ከፍ ወዳለ ስፍራ ወሰደውና፣ በቅጽበት የዓለም መንግሥታትን ሁሉ አሳየው፡፡ 6 ዲያብሎስም ለእርሱ፣ “እነዚህን ሁሉ መንግሥታት ከክብራቸው ሁሉ ጋር እንድትገዛ እኔ ሥልጣን እሰጥሃለሁ፤ ይህንን ማድረግ የምችለው እገዛቸው ዘንድ ለእኔ ስለተሰጡኝ ነው፣ እኔም ለምፈልገው ለማንኛውም ሰው ልሰጣቸው እችላለሁ፡፡ 7 ስለዚህ በፊቴ ብትሰግድልኝና ብታመልከኝ፣ ይሄ ሁሉ የአንተ ይሆናል አለው። 8 ኢየሱስ ግን እንደዚህ ብሎ መለሰለት፣ “’እግዚአብሔር አምላክህን አምልክ፣ እርሱንም ብቻ አገልግል’ ተብሎ ተጽፎአል፡፡” 9 ከዚህ በኋላ ዲያብሎስ ወደ ኢየሩሳሌም ወስዶ በቤተ መቅደሱ ሕንፃ እጅግ ከፍተኛ ስፍራ አቆመውና፣ 10 “’ይጠብቁህና ይንከባከቡህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዛቸዋል’ 11 ደግሞም፣ ‘እግርህም ከድንጋይ ጋር እንዳይጋጭ በእጆቻቸው ወደ ላይ ይይዙሃል’ ተብሎ ተጽፎአልና፣ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ራስህን ከዚህ ላይ ወርውር፡፡” አለው፡፡ 12 ኢየሱስም፣ “’እግዚአብሔር አምላክህን መፈታተን የለብህም’ ተብሎአል፡፡” ብሎ መለሰለት፡፡ 13 ዲያብሎስም ኢየሱስን መፈተኑን ባበቃ ጊዜ፣ እስከ ሌላ ጊዜ ድረስ ትቶት ሄደ፡፡ 14 ከዚያ በኋላ ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተሞልቶ ወደ ገሊላ ተመለሰ፤ በዚያ አካባቢ በነበሩት ስፍራዎች ሁሉ የእርሱ ዝና ተሰራጨ፡፡ 15 በምኩራቦቻቸው አስተማረ፣ ሰዎችም ሁሉ ያመሰግኑት ነበር፡፡ 16 አንድ ቀንም ወዳደገበት ከተማ ወደ ናዝሬት መጣ፡፡ እንደ ልማዱም በሰንበት ቀን ወደ ምኩራብ ገባ፣ የእግዚአብሔርንም ቃል ያነብ ዘንድ ቆመ፡፡ 17 የነቢዩ የኢሳይያስ የመጽሐፍ ጥቅልል ተሰጥቶት ስለነበረ፣ ጥቅልሉን ሲከፍተው፣ 18 “ለድሆች የምሥራቹን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ላይ ነው፤ ለምርኮኞች ነፃነትን፣ ለዕውሮች ብርሃናቸው እንደሚመለስላቸው ፣ የተጨቆኑትም መፈታትን እንደሚያገኙ 19 የእግዚአብሔርን የሞገስ ዓመት ዐውጅ ዘንድ ልኮኛል፡፡” የሚለውን ስፍራ አገኘ፡፡ 20 ከዚያ በኋላ የመጽሐፉን ጥቅልል ዘጋና ለምኩራቡ አገልጋይ ሰጥቶ ተቀመጠ፡፡ 21 “እናንተ እየሰማችሁ ይህ የእግዚአብሔር ቃል ተፈጸመ፡፡” እያለ ሊነግራቸው ጀመረ፡፡ 22 በዚያ የነበሩ ሰዎች ሁሉ የተናገረውን አስተዋሉ፣ ከአንደበቱም በሚወጣው የጸጋ ቃል ሁሉም ተገረሙ፡፡ እነርሱም፣ “ይህ የዮሴፍ ልጅ ነው፣ አይደለም እንዴ?” ይሉ ነበር፡ 23 ኢየሱስም፣ “በእርግጥ ‘ሐኪም ሆይ፣ ራስህን አድን፤ በቅፍርናሆም እንደምታደርግ የሰማነውን በዚህም በትውልድ ከተማህ አድርግ’ የሚለውን ይህንን ምሳሌ ትመስሉብኛላችሁ፡፡” 24 ደግሞም እንደዚህ አላቸው፣ “እውነት እላችኋለሁ፣ ማንኛውም ነቢይ በገዛ አገሩ ተቀባይነት የለውም፡፡ 25 ነገር ግን እኔ እውነት እላችኋለሁ፣ ለሦስት ዓመታት ተኩል ሰማይ ተዘግቶ ዝናብ ባልነበረበትና በምድሪቱም ሁሉ ረሃብ በነበረበት በኤልያስ ዘመን በእስራኤል ብዙ መበለቶች ነበሩ፡፡ 26 ነገር ግን ኤልያስ በሲዶና አጠገብ በሰራፕታ ትኖር ወደነበረችው መበለት ብቻ እንጂ ከእነርሱ ወደ አንዲቱም አልተላከም፡፡ 27 በነቢዩ በኤልሳዕ ዘመንም በእስራኤል ብዙ ለምጻሞች ነበሩ፣ ነገር ግን ከሶርያዊው ከንዕማን በቀር ከእነርሱ አንዳቸውም አልተፈወሱም፡፡” 28 በምኩራብ የነበሩት ሰዎች ሁሉ እነዚህን ነገሮች በሰሙ ጊዜ በቁጣ ተሞሉ፡፡ 29 ተነሥተው ከከተማይቱ እንዲወጣ አስገደዱት፣ ከገደል ጫፍም ገፍትረው ይጥሉት ዘንድ ከተማይቱ ወደ ተመሠረተችበት ወደ ኮረብታው ጫፍ ገፍተው ወሰዱት። 30 ነገር ግን በመካከላቸው አልፎ ጉዞውን ቀጠለ፡፡ 31 ከዚያ በኋላም በገሊላ ወደምትገኝ ወደ ቅፍርናሆም ከተማ ሄደ፡፡ 32 በሥልጣን ይናገር ስለነበረ፣ በትምህርቱ ተገረሙ፡፡ 33 በዚያን ቀን በምኩራብ ውስጥ ርኩስ መንፈስ የነበረበት ሰው ነበረ፤ እርሱም በታላቅ ድምፅ ጮኸ፡፡ 34 “የናዝሬቱ ኢየሱስ ሆይ፣ ከአንተ ጋር ምን አለን? ልታጠፋን መጣህን? ማን እንደሆንክ አውቄሃለሁ፣ አንተ የእግዚአብሔር ቅዱስ ነህ፡፡” 35 ኢየሱስም ጋኔኑን፣ “ፀጥ ብለህ ከእርሱ ውጣ!” ብሎ ገሠጸው፡፡ ጋኔኑ በሰዎቹ መካከል በጣለው ጊዜ፣ ምንም ጉዳት ሳያደርስበት ከእርሱ ወጣ፡፡ 36 ሰዎች ሁሉ በጣም ተደነቁ፣ እርስ በርሳቸውም ስለሆነው ነገር መነጋገር ቀጠሉ፡፡ እነርሱም፣ “እነዚህ እንዴት ያሉ ቃላት ናቸው? ርኩሳን መናፍስትን በሥልጣንና በኃይል ያዛቸዋል፣ እነርሱም ይወጣሉ፡፡” 37 የእርሱም ዝና በአካባቢው ባሉት አውራጃዎች በማንኛውም ስፍራ ወጣ፡፡ 38 ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ከምኩራብ ወጥቶ ወደ ስምዖን ቤት ገባ፡፡ በዚያን ጊዜ የስምዖን አማት በከፍተኛ ትኩሳት ታማ ነበር፣ እነርሱም ስለ እርሷ ተማፀኑት፡፡ 39 ስለዚህ በአጠገብዋ ቆሞ ትኩሳቱን ገሠጸው፣ ትኩሳቱም ቆመ፡፡ ወዲያውኑም ተነሥታ ልታገለግላቸው ጀመረች፡፡ 40 ፀሐይም በጠለቀች ጊዜ ሰዎች በተለያዩ ደዌዎች የተያዙትን በሽተኞች ወደ እርሱ አመጡ፡፡ እርሱም እጆቹን በእያንዳንዳቸው ላይ ጭኖ ፈወሳቸው፡፡ 41 አጋንንትም፣ “አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ” እያሉ በመጮኽ ከብዙዎች ወጡ፡፡ ኢየሱስ አጋንንትን ገሠጻቸው፣ እንዲናገሩም አልፈቀደላቸውም፣ ምክንያቱም እርሱ ክርስቶስ መሆኑን አውቀው ነበርና፡፡ 42 ንጋትም በሆነ ጊዜ ወደ ገለልተኛ ስፍራ ሄደ፡፡ ብዙ የሕዝብ አጀብ እየፈለጉት ነበርና፣ እርሱ ወደነበረበት ስፍራ መጡ፡፡ እነርሱንም ትቷቸው እንዳይሄድ ሊያስቀሩት ሞከሩ፡፡ 43 እርሱ ግን እንደዚህ አላቸው፣ “የእግዚአብሔርን መንግሥት የምሥራች ለብዙ ከተሞች መስበክ ይገባኛል፣ ምክንያቱም ወደዚህ የተላክሁት ለዚህ ነው፡፡” 44 ከዚያ በኋላ በመላው ይሁዳ ባሉት ምኩራቦች መስበኩን ቀጠለ፡፡
ኢየሱስ ለ40 ቀን ፆመ፣ ዲያቢሎስም ኃጢአት እንዲያደርግ እርሱን ማሳመን ለመሞከር ተገናኘው፡፡
ዮሐንስ ኢየሱስን ካጠመቀው በኋላ፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “መንፈስ እርሱን መራው” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ብዙ እትሞች የተፈተነው 40 ቀኑን በሙሉ ነው ይላሉ፡፡ ይህንን ግልፅ ለማድረግ ዩዲቢ የሚባለው ትርጉም “እርሱ እዚያ በነበረበት ጊዜ፣ ዲያቢሎስ እርሱን መፈተን ቀጥሏል” ብሎ ገልፆታል፡፡
“40 ቀን” (ቁጥሮች የሚለውን ይመልከቱ)
ዲያቢሎስ ኢየሱስ “የእግዚአብሔር ልጅ” እንደሆነ ለማረጋገጥ ይህንን ተአምራት እንዲያደርግ ተገዳደረው፡፡ (ልጅ እና አባትን መተርጎም የሚለውን ይመልከቱ)
ዲያቢሎስ በእጁ ድንጋይ ይዟል ወይም በአቅራቢያው ወዳለ ድንጋይ ጠቁሟል፡፡
ኢየሱስ የዲያቢሎስን ተግዳሮት አለመቀበሉ በመልሱ ላይ በግልፅ ይታያል፡፡ ዩዲቢ የሚባለው ትርጉም እንዳደረገው፣ ለአንባቢዎችህ ይህንን በትክክል መግለፅ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ኢየሱስ ‘አይሆንም፣ ይህንን አላደርግም ምክንያቱም . . . ብቻ . . . ተብሎ ተፅፏል’ ብሎ መለሰ።” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
የተጠቀሰው በብሉይ ኪዳን ከሙሴ ፅሁፎች ውስጥ ነው፡፡ ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሙሴ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ፅፏል” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“እንጀራ” የሚለው ቃል በአጠቃላይ ምግብን ያመለክታል፡፡ ምግብ ከእግዚአብሔር ጋር ሲወዳደር፣ ብቻውን፣ ሰውን በህይወት ለማቆየት በቂ አይደለም፡፡ ኢየሱስ ለምን ድንጋዩን ወደ እንጀራ እንደማይቀይር ለመናገር መጽሐፍ ቅዱስን ጠቀሰ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሰዎች በእንጀራ ብቻ መኖር አይችሉም” ወይም “ሰውን እንዲኖር የሚያደርገው እንጀራ ብቻ አይደለም” ወይም “እግዚአብሔር ከእንጀራ ይበልጥ ጠቃሚ የሆኑ ነገሮች አሉ ብሏል” (ወካይ የሚለውን ይመልከቱ)
እርሱ በተራራ ላይ ኢየሱስን መራው፡፡ (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“በቅፅበት” ወይም “ባንዳፍታ”
ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል፡፡ ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች “እነርሱ” የሚለው የሚያመለክተው 1) የግዛቶቹ ስልጣን እና ውበት ወይም 2) ግዛቶቹ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ እግዚአብሔር እነርሱን ለእኔ ሰጥቶኛል “ (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለጸ መረጃ እና ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ ሁለት ሀረጎች በጣም ተመሳሳይ ናቸው፡፡ መጣመር ይችላሉ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እኔን ለማምለክ የምትሰግድ ከሆነ” (ጥምር ቃል የሚለውን ይመልከቱ)
“እነዚህን ሁሉ ግዛቶች ከነ ውበታቸው ለአንተ እሰጥሀለሁ”
ይህ የቤተ መቅደስ ጣሪያ ጠርዝ ነበር፡፡ አንድ ሰው ከዚህ ከወደቀ፣ በጠና ይጎዳል ወይም ይሞታል፡፡
ዲያቢሎስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ እንዲያረጋግጥ እየተገዳደረው ነው፡፡
ይህ ለኢየሱስ ጠቃሚ ስም ነው፡፡ (ልጅ እና አባትን መተርጎም የሚለውን ይመልከቱ)
“ወደ መሬት ዝለል”
ከመዝሙረ ዳዊት የጠቀሰው ጥቅስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆነ እርሱ አይጎዳም ማለት እንደሆነ ዲያቢሎስ ያመለክታል፡፡ ዩዲቢ የሚባለው ትርጉም እንዳደረገው፣ ይህ በትክክል ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “አንተ አትጎዳም፣ ምክንያቱም ተብሎ ተፅፏል” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ጸሐፊው ፅፏል” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“እርሱ” እግዚአብሔርን ያመለክታል፡፡ ዲያቢሎስ ኢየሱስ ከህንፃው እንዲዘል ለማሳመን በመጣር ከመዝሙረ ዳዊት ጥቅስ በከፊል ጠቅሷል፡፡
ኢየሱስ ለምን ዲያቢሎስ እርሱ እንዲያደርግ የነገረውን እንደማያደርግ ለዲያቢሎስ ተናገረ፡፡ የእርሱ ለማድረግ ፈቃደኛ አለመሆን በትክክል ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “አይሆንም፣ ይህን አላደርግም፣ ምክንያቱም ተብሎአል” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ከኦሪት ዘዳግም ውስጥ የሙሴን ፅሁፍ ጠቀሰ፡፡ ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሙሴ ብሏል” ወይም “ሙሴ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብሏል” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ኢየሱስ ከቤተ መቅደሱ በመዝለል እግዚአብሔርን መፈታተን የለበትም፣ ወይም 2) ዲያቢሎስ እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ለማየት ኢየሱስን መፈታተን የለበትም፡፡ ይህንን ጥቅስ ትርጉሙን ለማብራራት ከመሞከር ይልቅ እንደ ተገለፀው መተርጎም የተሻለ ነው፡፡
“ሌላ አመቺ ጊዜ እስከሚገኝ”
ይህ ዲያቢሎስ በፈተናው ስኬታማ ነበር የሚል መልእክት አያስተላልፍም። ኢየሱስ እያንዳንዱ ሙከራውን ተቋቁሟል፡፡ ይህ በትክክል ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ኢየሱስ ኃጢአት እንዲያደርግ ለማሳመን መሞከሩን ጨረሰ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ወደ ገሊላ ተመለሰ፣ በምኩራብ አስተማረ፣ እዚያ ላሉ ሰዎችም እርሱ የነቢዩ ኢሳይያስን ትንቢት እየፈፀመ እንደሆነ ነገራቸው፡፡
ይህ በታሪኩ ውስጥ አዲስ ሁነትን ይጀምራል፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
“መንፈስም ኃይል እየሰጠው ነበር፡፡” የሰው ልጆች በተለምዶ ማድረግ የማይችሉትን ነገር እንዲያደርግ እያስቻለው፣ እግዚአብሔር በልዩ መንገድ ከኢየሱስ ጋር ነበር፡፡
“ስለ ኢየሱስ ሰዎች ዝናውን አስፋፉ” ወይም “ሰዎች ለሌሎች ሰዎች ስለ ኢየሱስ ተናገሩ” ወይም “ስለ እርሱ ያለ እውቀት ከሰው ወደ ሰው ተላለፈ፡፡” ኢየሱስን የሰሙ ሰዎች ለሌላ ሰዎች ስለ እርሱ ተናገሩ፣ ከዚያም እነዚህ ሌላ ሰዎች ለበለጡ ሌላ ሰዎች ስለ እርሱ ተናገሩ፡፡
ይህ በገሊላ ዙሪያ ያሉ ቦታዎችን እና አካባቢዎችን ያመለክታል፡፡
“እያንዳንዱ ሰው ስለ እርሱ ታላቅ ነገርን ተናገረ” ወይም “ሁሉም ሰው ስለ እርሱ በመልካም መንገድ ተናገረ”
“ቤተሰቦቹ እርሱን ያሳደጉበት” ወይም “ልጅ እያለ የኖረበት”
“በእያንዳንዱ ሰንበት እንደሚያደርገው፡፡” በሰንበት ቀን ወደ ምኩራብ መሄድ የእርሱ የአብዛኛውን ጊዜ ልምምድ ነበር፡፡
ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “አንድ ሰው የነቢዩ ኢሳይያስን መጽሐፍ ሰጠው” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በብራና ላይ የተፃፈውን የኢሳይያስን መጽሐፍ ያመለክታል፡፡ ኢሳይያስ መልእክቱን ከብዙ አመት በፊት ፅፎታል፣ እናም ሌላ ሰው ፅሁፎቹን ወደ ብራና ገልብጧል፡፡
“እነኚህ ቃላቶች ያሉበት የብራናው ስፍራ፡፡” ይህ አረፍተ ነገር ወደ ቀጣዩ ቁጥር ይቀጥላል፡፡
“መንፈስ ቅዱስ በልዩ መንገድ ከእኔ ጋር ነው፡፡” አንድ ሰው ይህንን ሲል፣ የእግዚአብሔርን ቃል ነው የምናገረው እያለ ነው፡፡
በብሉይ ኪዳን፣ ሰው ልዩ ተግባር ለማድረግ ስልጣን እና ሀይል ሲሰጠው የስርአት መፈጸሚያ ዘይት በሰውየው ላይ ይፈስ ነበር፡፡ ኢየሱስ ይህንን ተለዋጭ ዘይቤ መንፈስ ቅዱስ እርሱን ለዚህ ስራ ለማዘጋጀት በእርሱ ላይ እንደነበር ለማመላከት ተጠቀመበት፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “መንፈስ ቅዱስ በኃይል ሊሞላኝ በእኔ ላይ ነው” ወይም “መንፈስ ቅዱስ ስልጣን እና ሀይልን ሰጠኝ” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“ድሀ ሰዎች”
“ምርኮኛ ሆነው ለተያዙ ህዝቦች በነፃ መሄድ አንደሚችሉ መንገር” ወይም “የጦርነት ታሳሪዎችን ነፃ ማውጣት”
“ለታወሩት ማየትን መስጠት” ወይም “የታወሩት እንደገና ማየት እንዲችሉ ማድረግ”
“በግፍ የሚሰቃዩትን ነፃ ማውጣት”
“እግዚአብሔር ህዝቡን ለመባረክ ዝግጁ እንደሆነ ለእያንዳንዱ ሰው መናገር” ወይም “ይህ እግዚአብሔር ቸርነቱን የሚያሳይበት አመት እንደሆነ ማስታወቅ”
ብራና ውስጡ ያለውን ፅሁፍ ለመጠበቅ እንደ ቱቦ በመጠቅለል ነበር የሚዘጋው፡፡
ይህ መጽሐፍ ቅዱስ የያዙትን ብራናዎች በተገቢው ጥንቃቄ እና ክብር የሚያወጣ እና የሚያስቀምጥ የምኩራብ ሰራተኛን ያመለክታል፡፡
ናዝሬት ኢየሱስ ያደገበት ከተማ ነው፡፡
ኢየሱስ በምኩራብ ውስጥ ለሚያዳምጡት ህዝብ እነርሱ ስለሚያውቋቸው ነቢያት፣ ስለ ኤልያስ እና ኤልሳዕ አስታወሳቸው፡፡ (የጀርባ ታሪክ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“በእውነት እነግራችኋለሁ፡፡” ኢየሱስ ይህንን ሀረግ የተከታዩን አረፍተ ሀሳብ ጥቅም፣ እውነት እና ትክክለኛነት አፅንኦት ለመስጠት ይጠቀመዋል፡፡
መበለቶች ባሎቻቸው የሞተባቸው ሴቶች ናቸው፡፡
ኢየሱስ እየተናገራቸው ያሉት ህዝብ ኤልያስ ከእግዚአብሔር ነቢያት አንዱ እንደሆነ ያውቁ ነበር፡፡ አንባቢዎችህ ያንን ካላወቁ፣ ይህንን ያልተገለፀ መረጃ እንደ ዩዲቢ የሚባለው ትርጉም ግልፅ ማድረግ ትችላለህ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ኤልያስ በእስራኤል ውስጥ እየተነበየ በነበረበት ጊዜ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ተለዋጭ ዘይቤ ነው፡፡ ሰማይ ከእርሱ ምንም ዝናብ እንዳይወርድ የተዘጋ ጣሪያ እንደሆነ ተደርጎ ተስሏል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ከሰማይ ምንም ዝናብ ባልወረደ ጊዜ” ወይም “ከቶ ምንም ዝናብ በሌለ ጊዜ” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“አሳሳቢ የምግብ እጥረት፡፡” ራብ ሰብሎች ለህዝቡ በቂ ምግብ የማያፈሩበት ረጅም ጊዜ ነው፡፡
በሰራፕታ ከተማ የሚኖሩ ህዝቦች አህዛብ ነበሩ፣ አይሁድ አልነበሩም፡፡ ኢየሱስን እያዳመጡ ያሉት ሰዎች የሰራፕታ ህዝብ አህዛብ እንደሆኑ ይገባቸዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሰራፕታ ውስጥ ለምትኖር ከአህዛብ ወገን የሆነች መበለት” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለጸ መረጃ እና ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
ሶርያዊ ከሶርያ አገር የሆነ ሰው ነው፡፡ የሶርያ ህዝቦች አህዛብ ነበሩ፣ አይሁድ አልነበሩም፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ከሶሪያ የሆነው አህዛቡ ንዕማን” (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
የናዝሬት ህዝብ እግዚአብሔር በአይሁድ ፋንታ አህዛብ የረዳበትን መጽሐፍ ኢየሱስ ስለጠቀሰ በእጅጉ ተናደው ነበር፡፡
“ከተማውን እንዲለቅ አስገደዱት” ወይም “ከከተማው ወደ ውጪ በሀይል ገፉት”
“የገደል ጠርዝ”
“በተሰበሰው ህዝብ መካከል” ወይም “ እርሱን ለመግደል በሚሞክሩት ህዝብ መካከል”
“እርሱ ሄደ” ወይም “በራሱ መንገድ ሄደ” ኢየሱስ ህዝቡ እርሱ እንዲሄድ ለማስገደድ ከሚሞክሩበት ቦታ ይልቅ እርሱ ለመሄድ ያቀደበት ቦታ ሄደ፡፡
ከዚያም ኢየሱስ ወደ ቅፍርናሆም ሄደ፣ እዚያ ምኩራብ ውስጥ ላሉ ሰዎች አስተማረ፣ ርኩስ ጋኔንም ግለሰቡን ለቆ እንዲወጣ አዘዘ፡፡
“ከዚያም ኢየሱስ፡፡” ይህ አዲስ ሁነትን ያመለክታል፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
“ወረደ” የሚለው ሀረግ እዚህ ላይ ጥቅም ላይ የዋለው ቅፍርናሆም ከናዝሬት በከፍታው ዝቅ ያለ ስለሆነ ነው፡፡
“ቅፍርናሆም፣ በገሊላ ውስጥ ሌላ ከተማ”
በእጅጉ መደነቅ
“ሥልጣን እንዳለው ሰው ተናገረ” ወይም “የእርሱ ቃላት ትልቅ ኃይል ነበራቸው”
ይህ ሀረግ በታሪኩ ውስጥ የአዲስ ገፀ ባህርይ መግባትን ለማመላከት ይጠቅማል፤ በዚህ ጊዜ፣ ርኩስ መንፈስ የተቆጣጠረውን ሰው፡፡ (የአዲስና የቀድሞ ተሳታፊዎች መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
“ግልፅ ያልሆነ ርኩስ መንፈስ የተቆጣጠረው” ወይም “በክፉ መንፈስ ቁጥጥር ስር ያለ”
“በሀይል ጮኸ”
ይህ ጠብ አጫሪ መልስ “እኛ ምን የጋራ ነገር አለን?” ወይም “እኛን ለማስቸገር አንተ ምን መብት አለህ?” የሚል ትርጉም ያለው ፈሊጥ ነው፡፡ (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ጥያቄ እንደ አረፍተ ሀሳብ ሊጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የናዝሬቱ ኢየሱስ፣ አንተ ከእኛ ጋር ምን አለህ!” ወይም “እኛ ከአንተ ጋር ምንም የለንም፣ የናዝሬቱ ኢየሱስ!” ወይም “አንተ እኛን ለማስቸገር ምንም መብት የለህም፣ የናዝሬቱ ኢየሱስ!” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
“ኢየሱስ ርኩስ መንፈሱን ተቆጣው፣ እንዲህ በማለት” ወይም “ኢየሱስ በሀይል ርኩስ መንፈሱን ተናገረው”
ርኩስ መንፈሱ ግለሰቡን መቆጣጠር እንዲያቆም አዘዘው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ብቻውን ተወው” ወይም “በዚህ ሰው ውስጥ ከዚህ በኋላ አትኑር”
ኢየሱስ ርኩስ መንፈስ ሰውን ትቶ እንዲወጣ ለማዘዝ ስልጣን ስላለው ህዝቡ እንዴት ተደንቀው እንደነበር እየገለፁ ነበር፡፡ ይህ እንደ አረፍተ ሀሳብ ሊጸፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እነዚህ ቃላት ድንቅ ናቸው!” ወይም “የእርሱ ቃላት ድንቅ ናቸው!” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
“እርሱ ግልፅ ያልሆነውን መንፈስ ለማዘዝ ስልጣን እና ሀይል አለው”
ይህ በታሪኩ ውስጥ በተከሰቱ ክስተቶች አማካኝነት ስለተፈጠረው ነገር የሚናገር መግለጫ ነው፡፡ (የታሪክ መጨረሻ የሚለውን ይመልከቱ)
“ስለ ኢየሱስ ወሬዎች መስፋፋት ጀመሩ” ወይም “ህዝቡ ስለ ኢየሱስ ዝና ማስፋፋት ጀመሩ”
ኢየሱስ አሁንም ቅፍርናሆም ውስጥ ነው፣ ነገር ግን አሁን የስምዖንን አማት እና ብዙ ሰዎችን በፈወሰበት በስምኦን ቤት ውስጥ ነው፡፡
ይህ አዲስ ሁነትን ይገልፃል፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
“የስምዖን ሚስት እናት”
ይህ “በጣም ታማ ነበር” የሚል ትርጉም ያለው ፈሊጥ ነው፡፡ (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)
x
“እጆቹን አስቀመጠ” ወይም “ነካ”
ኢየሱስ አጋንንት ከተቆጣጠራቸው ሰዎች አጋንንቶች እንዲለቁ እንዳደረገ ያመለክታል፡፡ ይህ በትክክል ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ኢየሱስ ደግሞ አጋንንቶች እንዲወጡ አስገደዳቸው” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው፣ ምናልባትም የፍርሀት ወይም የንዴትን ጩኸትን ያመለክታሉ፡፡ አንዳንድ ትርጉሞች አንድ ስያሜን ብቻ ይጠቀማሉ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “መጮህ” ወይም “መንጫጫት” (ጥምር ቃል የሚለውን ይመልከቱ)
ሕዝቡ ኢየሱስ በቅፍርናሆም እንዲቆይ ቢፈልጉም፣ በሌላ የአይሁድ ምኩራቦች ለመስበክ ሄደ፡፡
“ፀሐይ ስትወጣ”
“ሰው ለቅቆ የሄደበት ቦታ” ወይም “ምንም ሰው የሌለበት ቦታ”
“በሌላ ብዙ ከተማ ላሉ ሰዎች”
ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ይህ እግዚአብሔር እኔን እዚህ የላከበት ምክንያት ነው” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ገሊላ ውስጥ ስለነበር፣ “ይሁዳ” የሚለው ስም እዚህ ላይ ምናልባትም በዚያን ጊዜ አይሁዶች የኖሩበትን ክልል በሙሉ ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “አይሁዶች የኖሩበት”
1 ሕዝቡ ከበውት የእግዚአብሔርን ቃል እያዳመጡ ሳሉ፣ ኢየሱስ በጌንሳሬጥ ሐይቅ ዳር ቆሞ ነበር፡፡ 2 ሁለት ጀልባዎች በሐይቁ ጥግ በኩል ሲጎተቱ ተመለከተ፡፡ ዓሣ አጥማጆቹ ከጀልባዎቹ ወርደው መረቦቻቸውን እያጠቡ ነበር፡፡ 3 ኢየሱስ የስምዖን ወደ ነበረችው ከጀልባዎቹ ወደ አንዲቱ ገባና ከምድር ጥቂት ፈቀቅ አድርጎ ወደ ውሃ ውስጥ እንዲያስገባት ጠየቀው፡፡ ከዚያ በኋላም በጀልባዋ ውስጥ ተቀምጦ ሕዝቡን ማስተማር ጀመረ፡፡ 4 ንግግሩንም በጨረሰ ጊዜ ለስምዖን፣ “ጀልባይቱን ወደ ጥልቁ ውሃ ፈቀቅ አድርጋትና ዓሣ ለማጥመድ መረቦቻችሁን ጣሉ፡፡” አለው፡፡ 5 ስምዖንም፣ “ጌታ ሆይ፣ ሌሊቱን ሁሉ ስንሠራ አደርን ምንም አላጠመድንም፣ ነገር ግን በቃልህ መረቡን እጥላለሁ፡፡” ብሎ መለሰለት፡፡ 6 ይህንን ባደረጉ ጊዜ እጅግ ብዙ ዓሣ ያዙ፣ መረቦቻቸውም ሊቀደዱ ደረሱ፡፡ 7 ስለዚህ እንዲመጡና እንዲረዷቸው በሌላ ጀልባ የነበሩትን ጓደኞቻቸውን በጥቅሻ ጠሩ፡፡ እነርሱም መጥተው ሁለቱንም ጀልባዎች እስኪሰጥሙ ድረስ ሞሉአቸው፡፡ 8 ስምዖን ጴጥሮስ ግን ይህንን በተመለከተ ጊዜ በኢየሱስ ጉልበት ሥር ዝቅ ብሎ በመንበርከክ፣ “ጌታ ሆይ፣ እኔ ኃጢአተኛ ሰው ነኝና ከእኔ ተለይ” አለው፡፡ 9 እንደዚህም ያለው ስላጠመዷቸው ዓሣዎች እርሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት ሁሉ ተደንቀው ስለነበረ ነው፡፡ 10 በዚያም ከነበሩት መካከል የዘብዴዎስ ልጆች ዮሐንስና ያዕቆብ አብረውት ነበሩ፡፡ ኢየሱስም ለስምዖን፣ “ከእንግዲህ ሰውን የምታጠምድ ትሆናለህና፣ አትፍራ፡፡” አለው፡፡ 11 ጀልባቸውን ወደ ምድር ባመጧት ጊዜ ሁሉንም ትተው ተከተሉት፡፡ 12 ከከተማዎቹ በአንዲቱ በነበረ ጊዜ፣ መላ ሰውነቱ በለምጽ የተመታ ሰው በዚያ ነበረ፡፡ ኢየሱስንም ባየ ጊዜ በፊቱ ወድቆ፣ “ብትፈቅድስ፣ ልታነጻኝ ትችላለህ፡፡” ብሎ ለመነው፡፡ 13 በዚያን ጊዜ ኢየሱስ እጁን ዘርግቶ ዳሰሰውና፣ “እፈቅዳለሁ፣ ንጻ” አለው፡፡ ወዲያውኑም ለምጹ ከእርሱ ተወገደ፡፡ 14 ለማንም እንዳይነግር አስጠነቀቀው፣ ነገር ግን፣ “ሂድና ራስህን ለካህን አሳይ፣ ሙሴ ባዘዘውም መሠረት ለእነርሱ ምስክር ይሆን ዘንድ ለመንጻትህ መሥዋዕት አቅርብ፡፡” አለው፡ 15 ነገር ግን ስለ እርሱ ያለው ዝና ከዚያም ርቆ ወጣ፤ ብዙም የሕዝብ አጀብ ሲያስተምር ለመስማትና ከሕመሞቻቸው ለመፈወስ በአንድነት ወደ እርሱ መጡ፡፡ 16 እርሱ ግን ወደ ገለልተኛ ስፍራዎች ሄዶ በዚያ ይጸልይ ነበር፡፡ 17 ያስተምር ከነበረባቸውም ከእነዚያ በአንዱ ቀን ከገሊላና ከይሁዳ መንደሮችና አውራጃዎች እንዲሁም ከኢየሩሳሌም ከተማ መጥተው በዚያ የተቀመጡ ፈሪሳውያንና የሕግ መምህራን ነበሩ፡፡ ይፈውስም ዘንድ የእግዚአብሔር ኃይል በእርሱ ላይ ነበረ፡፡ 18 በዚያን ጊዜ ጥቂት ሰዎች ሰውነቱ የደነዘዘ ሰው በቃሬዛ ይዘው መጡ፤ በኢየሱስ ፊትም ያደርጉት ዘንድ ወደ ውስጥ የሚያስገቡበትን መንገድ ይፈልጉ ነበር፡፡ 19 ከሕዝቡም ብዛት የተነሣ ሊያስገቡ የሚችሉበትን መንገድ አላገኙም፤ ስለዚህ ወደ ቤቱ ጣሪያ ላይ ወጥተው፣ ሰውዬውን በቃሬዛው ላይ እንዳለ በጣሪያው አሳልፈው በሰዎቹ መካከል ከኢየሱስ ፊት አወረዱት፡፡ 20 ኢየሱስ እምነታቸውን ተመልክቶ፣ “አንተ ሰው፣ ኃጢአትህ ተሰርዮልሃል” አለው፡፡ 21 ፈሪሳውያንና ጸሐፍት፣ “የስድብ ቃል የሚናገር ይህ ማን ነው? እግዚአብሔር ብቻ ካልሆነ በስተቀር፣ ኃጢአትን ይቅር ማለት የሚችል ማን ነው?” በማለት መጠየቅ ጀመሩ፡፡ 22 ነገር ግን ኢየሱስ ምን እንዳሰቡ አውቆ፣ “በልባችሁ ይህንን ለምን ትጠይቃላችሁ? 23 የትኛውን ማለት ይቀላል፡- ‘ኃጢአትህ ተሰረየችልህ’ ማለት ወይስ ‘ተነሣና ሂድ’ ማለት? 24 ነገር ግን ለሰው ልጅ በምድር ላይ ኃጢአትን ይቅር ለማለት ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ፣ ለአንተ፣ ‘ተነሣና ቃሬዛህን ተሸክመህ ወደ ቤትህ ሂድ’ ብዬ እናገራለሁ፡፡" 25 ከዚያ በኋላ በእነርሱ ፊት ተነሣ፣ ተኝቶበት የነበረውንም ቃሬዛ ተሸክሞ እግዚአብሔርን እያከበረ ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡ 26 ሰዎች ሁሉ ተገረሙ፣ እግዚአብሔርንም አከበሩ፡፡ “በዛሬው ዕለት ያልተለመደ ነገር አየን” እያሉ በፍርሃት ተሞሉ፡፡ 27 እነዚህ ነገሮች ከሆኑ በኋላ፣ ኢየሱስ ከዚያ ወጥቶ በቀረጥ መሰብሰቢያው ስፍራ ተቀምጦ የነበረውን ሌዊ የተባለውን ቀረጥ ሰብሳቢ ተመለከተ፡፡ እርሱንም፣ “ተከተለኝ” አለው፡፡ 28 ስለዚህ ሌዊ ሁሉንም ትቶ ተነሥቶ ተከተለው፡፡ 29 ከዚያ በኋላ፣ ሌዊ በቤቱ ለኢየሱስ ታላቅ ግብዣ አደረገለት፣ በዚያም ብዙ ቀረጥ ሰብሳቢዎችና በማዕድ ቀርበው ከእነርሱ ጋር የሚመገቡ ሌሎች ሰዎችም ነበሩ፡፡ 30 ነገር ግን ፈሪሳውያንና ጻሐፍት በደቀመዛሙርቱ ላይ፣ “ከቀረጥ ሰብሳቢዎችና ከሌሎች ኃጢአተኛ ሰዎች ጋር ለምን ትበላላችሁ ትጠጣላችሁም?” እያሉ ያጉረመርሙባቸው ነበር፡፡ 31 ኢየሱስም እንደዚህ በማለት መለሰላቸው፣ “በመልካም ጤንነት ላይ ያሉ ሐኪም አያስፈልጋቸውም፣ ሐኪም የሚያስፈልጋቸው የታመሙ ብቻ ናቸው፡፡ 32 እኔ የመጣሁት ጻድቃንን ለንስሐ ለመጥራት ሳይሆን ኃጢአተኞችን ወደ ንስሐ ለመጥራት ነው፡፡” 33 እነርሱም ፣ “የዮሐንስ ደቀመዛሙርት ይጾማሉ ይጸልያሉም፣ የፈሪሳውያን ደቀመዛሙርትም እንደዚሁ ያደርጋሉ፡፡ የአንተ ደቀመዛሙርት ግን ይበላሉ፣ ይጠጣሉም፡፡” አሉት፡፡ 34 ኢየሱስም ፣ “ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሚዜዎቹን እንዲጾሙ ሊያደርጋቸው የሚችል አለን? 35 ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወቅት ይመጣል በእነዚያ ቀናት ይጾማሉ፡፡” 36 ከዚያ በኋላ ኢየሱስ በምሳሌ ተናገራቸው፣ “ማንም ሰው ከአዲስ ልብስ ላይ እራፊ ቀዶ አሮጌ ልብስ አይጥፍም፡፡ እንደዚህ የሚያደርግ ከሆነ፣ ከአዲሱ ልብስ ላይ እራፊ ይቀዳል፣ ነገር ግን ከአዲሱ ልብስ ላይ የተቀደደው እራፊ ከአሮጌው ልብስ ጋር አብሮ አይሄድም፡፡ 37 እንደዚሁም፣ ማንም ሰው በአሮጌው አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ አያስቀምጥም፡፡ እንደዚህ ቢያደርግ፣ አዲሱ ወይን ጠጅ አቁማዳውን ያፈነዳዋል፣ ወይን ጠጁም ይፈሳል፣ አቁማዳውም ይበላሻል፡፡ 38 ነገር ግን አዲስ ወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ይቀመጣል፡፡ 39 ማንም ሰው አሮጌውን ወይን ጠጅ ከጠጣ በኋላ አዲሱን የወይን ጠጅ አይፈልግም፣ ‘አሮጌው ይሻላል’ ይላልና፡፡”
ኢየሱስ በስምዖን ጴጥሮስ ጀልባ በጌንሳሬጥ ሀይቅ ላይ አስተማረ፡፡
ይህ ሀረግ የታሪኩ አዲስ ክፍል መጀመሩን ለማመላከት እዚህ ላይ ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ የአንተ ቋንቋ ይህንን የማድረግ መንገድ ካለው፣ እዚህ ላይ እርሱን ለመጠቀም ማሰብ ትችላለህ፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “እግዚአብሔር እነርሱ እንዲሰሙ የሚፈልገውን መልእክት ማዳመጥ” ወይም 2) “ስለ እግዚአብሔር የሆነውን የኢየሱስ መልእክት ማዳመጥ”
እነዚህ ቃላት የገሊላን ባህር ይወክላሉ፡፡ ገሊላ በሀይቁ ምዕራብ ጎን ነው፣ የጌንሳሬጥ መሬት በምስራቅ ጎን ነበር፣ ስለዚህ በሁለቱም ስሞች ይጠራ ነበር፡፡ አንዳንድ የእንግሊዘኛ እትሞች ይህንን እንደ ትክክለኛ የውሀው አካል ስም “የጌንሳሬጥ ሀይቅ” ብለው ይተረጉሙታል፡፡
አሳ ማጥመጃ መረባቸውን እንደገና ለአሳ መያዣነት ለመጠቀም እያፀዱ ነበር፡፡
“የስምዖን ንብረት የነበረው ጀልባ”
“ስምዖንን ጀልባውን ከባህር ዳርቻው ራቅ እንዲያደርገው ጠየቀ”
መቀመጥ ለአስተማሪ የተለመደ ሁኔታ ነበር፡፡
“ጀልባው ውስጥ እንደተቀመጠ ሆኖ ህዝቡን አስተማረ፡፡” ኢየሱስ ከባህር ዳርቻው አጭር ርቀት ላይ በሚገኘው ጀልባው ውስጥ ነበር እናም በባህር ዳርቻው ላይ ለነበሩ ሰዎች እየተናገረ ነበር፡፡
“ኢየሱስ ሕዝቡን ማስተማር ሲጨርስ”
“ምክንያቱም አንተ ይህንን እንዳደርግ ስለነገርከኝ”
ከባህር ዳርቻው ለመጣራት በጣም ሩቅ ነበሩ፣ ስለዚህ ምናልባትም እጃቸውን በማውለብለብ፣ የሰውነት እንቅስቃሴን አደረጉ፡፡
“ጀልባዎቹ መስጠም ጀመሩ፡፡” ምክንያቱ በትክክል ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “አሳው በጣም ከባድ ስለነበር ጀልባዎቹ መስጠም ጀመሩ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “በኢየሱስ ፊት ተንበረከከ” ወይም 2) “በኢየሱስ እግር ስር ሰገደ” ወይም 3) “የኢየሱስ እግር ስር ባለው መሬት ላይ ተኛ፡፡” ጴጥርስ በአጋጣሚ አልወደቀም፡፡ ይህንን የክብር እና የትህትና ምልክት እንዲሆን ለኢየሱስ አድርጎታል፡፡ (ምሳሌያዊ ድርጊት የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ሰው” የሚለው ቃል “ጎልማሳ ወንድ” ለማለት እንጂ በይበልጥ አጠቃላይ ለሆነው “የሰው ልጅ” አይደለም፡፡
“ብዙ ቁጥር ያለው አሳ”
“አሳ በማጥመድ ንግዱ ውስጥ የስምዖን ባልንጀሮች”
አሳን የማጥመድ ምስል ክርስቶስን እንዲከተል ሕዝብን ለመሰብሰብ እንደ ተለዋጭ ዘይቤ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሰዎችን ታጠምዳለህ” ወይም “ለእኔ ሰውን ትሰበስባለህ” ወይም “ሰዎች የእኔ ደቀ መዝሙር እንዲሆኑ ታመጣለህ” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ሌላ ስሙ ባልተጠቀሰ ከተማ ለምፃም ፈወሰ፡፡
ይህ ሐረግ በታሪኩ ውስጥ አዲስ ክስተት መከሰቱን ያሳያል፡፡
“ቆዳው በለምጽ የተሸፈነ ሰው።” ይህ በታሪኩ ውስጥ አዲስ ገጸ ባሕርይን ያስተዋውቃል፡፡ (የአዲስና የቀድሞ ተሳታፊዎች መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “በፊቱ ተደፋ” የሚለው ሰገደ የሚለውን ትርጉም የያዘ ፈሊጥ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ተንበርክኮ በፊቱ መሬቱን ነካ” ወይም “በመሬት ላይ ሰገደ” (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)
“የምትፈልግ ከሆነ”
እዚህ ላይ ሰውየው ኢየሱስ እንዲፈውሰው እየጠየቀው እንደሆነ መረዳት ይቻላል፡፡ ይህ በግልጽ መቀመጥ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ማንጻት ስለምትችል እባክህ አንጻኝ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ሥርዓታዊ ንጽህናን ያመለክታል፣ ሰውየው በለምጹ ምክንያት ንጹህ እንዳልነበረ መረዳት ይቻላል፡፡ ካለበት በሽታም ኢየሱስ እንዲፈውሰው እየጠየቀው ነበር፡፡ ይህ ግልጽ በሆነ መንገድ መቀመጥ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ካለብኝ ለምጽ ፈውሰኝ … የተፈወስክ ሁን” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“ከዚያ ጊዜ ኋላ ለምጽ አልነበረበትም”
ይህ በቀጥታ በጥቅስ መልክ መተርጎም ይቻላል፡፡ “ለማንም እንዳትናገር።” በግልጽ መቀመጥ የሚችል ሌላም ያልተገለጸ መረጃ አለ። አማራጭ ትርጉም፦ “መፈወስህን ለማንም እንዳትናገር” (ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ ጥቅሶች እና አስጨምሬ የሚለውን ይመልከቱ)
x
“ስለ ኢየሱስ ይወራ የነበረ ወሬ።” ይህ “ኢየሱስ ለምጽ ያለበትን ሰው የመፈወሱ ወሬ” ወይም “ኢየሱስ በሽተኞችን ስለመፈወሱ ወሬ” ሊሆን ይችላል፡፡
“ስለ እርሱ የነበረው ወሬ እስከ ሩቅ ቦታዎች ድረስ ተዳረሰ” ይህ በገቢር ቅርጽ መጻፍ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሰዎች በሌሎች ቦታዎች ለሚገኙ ሰዎች ስለ እርሱ ያወሩ ነበር” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“ባዶ ቦታዎች” ወይም “ሌሎች ሰዎች የማይገኙባቸው ቦታዎች” “
ኢየሱስ አንድ ህንጻ ላይ ያስተምር በነበረበት በአንድ ቀን ሰዎች አንድ ሽባ የነበረ ሰውን ኢየሱስ እንዲፈውሰው አመጡለት፡፡
ይህ ሐረግ በታሪኩ ውስጥ አዲስ ክፍል መጀመሩን ያሳያል፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ በታሪኩ ውስጥ አዲስ ሰዎች ናቸው፡፡ ቋንቋችሁ አዲስ ሰዎች መሆናቸውን የሚናገር አገላለጽ ሊኖረው ይችላል፡፡ (የአዲስና የቀድሞ ተሳታፊዎች መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
መተኛ ምንጣፍ ወይም አልጋ ወይም ቃሬዛ
“ራሱን ማንቀሳቀስ የማይችል የነበረ”
በአንዳንድ ቋንቋዎች የዚህን ቅደም ተከተል መቀየር የተለመደ ሊሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሰውየውን ወደ ውስጥ ማስገባት አልቻሉም ምክንያቱም የሰው ጭንቅንቁ ከባድ ስለነበር ነው፣ ስለዚህ”
ሰዎቹ መግባት ያልቻሉበት ምክንያት ክፍሉ በሰዎች ተጨናንቆ ስለነበርና ለእነርሱ የሚሆን ቦታ ስላልነበር እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ (አስጨምሬ የሚለውን ይመልከቱ)
ቤቶች ጠፍጣፋ የሆነ ጣርያ ነበራቸው፣ አንዳንድ ቤቶች ደግሞ ወደ እነዚህ ጣርያዎች መውጫነት የሚያገለግሉ መሰላሎች ወይም ደረጃዎች ነበሯቸው፡፡ ይህን በግልጽ ማሳየት ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ወደ ጠፍጣፋው የቤት ጣርያ ወጡ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“ከኢየሱስ ፊት ለፊት” ወይም “ኢየሱስ ከነበረበት ቀጥታ ፊትለፊት”
ኢየሱስ ሽባውን ሰው መፈወስ እንደሚችል ሰዎቹ እንደሚያምኑ ግልጽ ነው፡፡ ይህን በግልጽ ማሳየት ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ኢየሱስም ሰዎቹ እርሱ ሰውየውን ሊፈውሰው እንደሚችል እንዳመኑ ሲረዳ እንዲህ አለው” (አስጨምሬ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ስሙን ከማያውቁት ሰው ጋር ሲነጋገሩ ሰዎች የሚጠቀሙት የተለመደ ቃል ነው፡፡ አግባብ የሌለው አነጋገር አልነበረም፣ ግን የተለየ አክብሮትም አያሳይም፡፡ አንዳንድ ቋንቋዎች ይህን ለማሳየት “ወዳጄ” እና “ጌታዬ” የመሰሉ ቃላትን ሊጠቀሙ ይችላሉ፡፡
ይህ በገቢር ቅርጽ መጻፍ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ይቅር ተብለሃል” ወይም “ኃጢአትህን ይቅር ብዬሃለሁ” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“ስለዚህ ነገር ተወያዩ” ወይም “ስለዚህ ነገር ምክንያቶችን ሰጡ።” የጠየቁትን ጥያቄ በግልጽ ሊብራራ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ኢየሱስ ኃጢአትን ይቅር ለማለት ስልጣን ያለው መሆኑንና አለመሆኑን መወያያት ጀመሩ” (አስጨምሬ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ሐረግ የሚያሳየው እነርሱ ድምጽ ሳያወጡ እያሰላሰሉ እንደነበር ኢየሱስ ግን ይናገሩ የነበረውን ሳይሆን ያስቡ የነበረውን እንደተረዳ ያሳያል፡፡
ይህ በአረፍተ ሃሳብ መቀመጥ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በልባችሁ ውስጥ ስለዚህ ነገር ምንም አይነት ሙግት ውስጥ መግባት የለባችሁም” ወይም “ኃጢአትን ይቅር የማለት ስልጣን እንዳለኝ መጠራጠር የለባችሁም” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ልብ” የሚለው ቃል የሰውን አእምሮ ወይም የውስጥ ማንነት የሚወክል ምትክ ስም ነው፡፡ (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
ጻፎቹ እርሱ ኃጢአትን ይቅር የማለት ስልጣን እንዳለው ወይም እንደሌለው የሚያረጋግጥላቸው ነገር ምን እንደሆነ እንዲያስቡ ይህን ጥያቄ ይጠይቃቸዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እኔ 'ኃጢአትህ ተሰረየችልህ' አልኩ፣ እናንተ 'ተነስና ተመላለስ' ማለት ይከብዳል ብላችሁ ታስቡ ይሆናል ምክንያቱም ሰውየውን መፈወስ መቻሌና አለመቻሌ በሰውየው ተነስቶ መሄድና አለመሄድ ይታወቅ ነበር፡፡” ወይም “እናንተ 'ተነስና ሂድ' ከማለት 'ኃጢአትህ ተሰረየችልህ' ማለት ይቀላል ብላችሁ ታስቡ ይሆናል፡፡ (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ በንግግር ያልተገለጸው እንድምታ አንድ ነገር “መናገር ይቀላል ምክንያቱም ምን እንደተከናወነ ማንም ማወቅ አይችልም” ነገር ግን ሌላውን ነገር “መናገር ይከብዳል ምክንያቱም ሁሉም ሰው ምን እንደተከናወነ ያውቃል።” ሰዎች የሰውየው ኃጢአት ተሰርዮለት እንደሆነ ሰዎች ማየት አይችሉም፣ ነገር ግን ሰውየው ከተነሳና ከተራመደ እንደተፈወሰ ሁሉም ያውቃሉ፡፡ (አስጨምሬ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ለጻፎቹና ለፈሪሳውያኑ ነበር ሲያወራ የነበረው፡፡ “እናንተ” የሚለው የባለቤት መግለጫ ብዙ ቁጥርን ያመለክታል፡፡ (የሁለተኛ መደብ ቅርጾች የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ስለራሱ ነበር የሚያወራው፡፡
ኢየሱስ ይህን የተናገረው ለሽባው ሰው ነው፡፡ “አንተ” የሚለው የድርጊት ተቀባይ ገላጭ ነጠላ ቁጥር ነው፡፡
“በፍጥነት ተነሳ” ወይም “ቶሎ ተነሳ”
እዚህ ላይ ሰውየው መፈወሱን መናገር አስፈላጊ ሊሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሰውየውም ተፈወሰ! ተነሳም”
x
ኢየሱስ ቤቱን ለቅቆ በወጣ ጊዜ ሌዊ የሚባል አንድ አይሁዳዊ ቀረጥ ቀራጭን እንዲከተለው ጥሪ ያቀርብለታል፡፡ ሌዊ ባዘጋጀው ትልቅ ድግስ ላይ የኢየሱስ መታደም ጻፎችና ፈሪሳውያንን እጅግ ያናድዳቸዋል፡፡
“እነዚህ ነገሮች” የሚለው ሐረግ ቀደም ባሉ ቁጥሮች ላይ የተከሰቱትን ነገሮች ይወክላል፡፡ ይህ አዲስ ክስተት መጀመሩን ያሳያል፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
“አንድ ቀራጭን በትኩረት ተመለከተ” ወይም “አንድ ቀራጭን አጥብቆ ተመለከተ”
አንድን ሰው “መከተል” ማለት የዚያ ሰው ደቀ መዝሙር መሆን ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ደቀ መዝሙሬ ሁን” ወይም “እንደ አስተማሪ ተከተለኝ” (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)
“የቀራጭነት ስራውን ትቶ”
በድግሱ ላይ ኢየሱስ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን ጋር ያወራ ጀመር፡፡
“በሌዊ ቤት”
በግብዣ ላይ የግሪክ የአመጋገብ ዘይቤ መደገፊያ ባለው መቀመጫ ላይ ተጋድመውና በመቀመጫቸው በግራ በኩል ባለው ድጋፍ ላይ ትራስ አስቀምጠው እዚያ ላይ በመደገፍ ነበር። አማራጭ ትርጉም፡- “በአንድ ላይ ምመብላት” ወይም “በማዕድ መብላት” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“ለኢየሱስ ደቀ መዛሙርት”
ጻፎችና ፈሪሳውያን የኢየሱስ ደቀመዛሙርት ከኃጢአተኞች ጋር አብረው መብላታቸውን ለመቃወም ይህንን ጥያቄ ይጠይቃሉ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ከኃጢአተኞች ጋር አብራችሁ መብላት የለባችሁም” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ፈሪሳውያንና ጻፎች ኃይማኖተኛ ሰዎች ኃጢአተኛ ብለው ከሚያስቧቸው ሰዎች ጋር አብረው መሆን እንደሌለባቸው ያምኑ ነበር፡፡ “እናንተ” የሚለው ገላጭ ብዙ ቁጥር አመልካች ነው፡፡ (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
x
“የኃይማኖት መሪዎቹ ለኢየሱስ … አሉት”
ኢየሱስ ሰዎቹ ከዚህ ቀደም የሚያውቁትን ነገር ደግመው እንዲያስቡ በማለት ይሄንን ጥያቄ ይጠይቃቸዋል፡፡ ይህ በአረፍተ ሃሳብ መልክ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሙሽራው ከእነርሱ ጋር እያለ ዕድምተኞቹ ጹሙ የሚላቸው ማንም የለም” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
“እንግዶቹ” ወይም “ወዳጆች” እነዚህ ከሚያገባ ወንድ ጋር ሆነው አብረው ደስታውን የሚጋሩ ሰዎች ናቸው፡፡
መጾም ሐዘንን ማሳያ ነው፡፡ የኃይማኖት መሪዎቹ ሙሽራው አብሯቸው እያለ ዕድምተኞቹ ሊጾሙ እንደማይችሉ ገብቷቸዋል፡፡ (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“በቅርብ” ወይም “አንድ ቀን”
ኢየሱስ ራሱን ከአንድ ሙሽራ ጋር ደቀ መዛሙርቱን ደግሞ ከሚዜዎች ጋር በንጽጽር ያቀርባል፡፡ ዘይቤውን አያብራራውም ስለዚህ ትርጉም ላይ እጅግ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ብቻ ዘይቤው ይብራራ፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ በሌዊ ቤት ተገኝተው ለነበሩት ጻፎችና ፈሪሳውያን አንድ ታሪክ ይነግራቸዋል፡፡ (ተምሳሌቶች የሚለውን ይመልከቱ)
ማንም ቦጭቆ . . . አይጠቀምም . . . እርሱ . . . እርሱ” ወይም “ሰዎች ቀድደው . . . አይጠቀሙበትም . . . እነርሱ . . . እነርሱ
ማደስ
ይህ ግምታዊ አርፍተ ነገር ለምን አንድ ሰው በዚያ መንገድ አንድን ልብስ እንደማያድስ ምክንያትን ይሰጣል፡፡ (ግምታዊ ሁኔታዎች የሚለውን ይመልከቱ)
“አይገጥምም” ወይም “ተመሳሳይ አይሆንም”
“የወይን ፍሬ ጭማቂ።” ይህ ያልፈላ የወይን ጠጅን ይወክላል፡፡
እነዚህ ከእንስሳ ቆዳ የተሰሩ መያዣ ከረጢቶች ናቸው፡፡ “የወይን ከረጢቶች” ወይም “ከቆዳ የተሰሩ ከረጢቶች” ተብለው መጠራትም ይችላሉ፡፡
አዲሱ ወይን ሲፈላና ቆዳውን ሲወጥረው ያረጀውን ቆዳ ያፈነዳዋል ምክንያቱም መለጠጥ ስለማይችል ነው፡፡ ኢየሱስ ይናገር የነበረውን ያዳምጡ የነበሩ ሰዎች ስለ ወይን መፍላትና ይዞታ መጨመር የሚረዱ ሰዎች ነበሩ፡፡ (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ቅርጽ ሊጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ወይኑ ከከረጢቶቹ ውስጥ ወጥቶ ይፈስሳል” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“አዲስ አቁማዳዎች” ወይም “አዲስ የወይን ከረጢቶች” ይህ ጥቅም ላይ ያልዋለ አቁማዳን ይወክላል፡፡
ይህ ዘይቤ የኃይማኖት መምህሮችን አሮጌ ትምህርት ከኢየሱስ አዲስ ትምህርት ጋር አነጻጽሮ ያቀርባል፡፡ የዚህ ንግግር ዋና ነጥብ የድሮ ትምህርትን መስማት የለመዱ ሰዎች ኢየሱስ የሚያስተምረውን አዲስ ትምህርት ለመስማት ፈቃደኛ አለመሆናቸው ነው፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“የፈላ ወይን ጠጅ”
“ስለዚህም አዲሱን ወይን ለመሞከር ፈቃደኛ አይሆንም” የሚለውን መጨመር አስፈላጊ ሊሆን ይችላል፡፡ (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
1 በሰንበት ቀን በእህል እርሻ መካከል በሚያልፍበት ጊዜ ደቀመዛሙርቱ እሸት እየቀጠፉና በእጆቻቸው እያሹ እህሉን ይቅሙ ነበር፡፡ 2 ገር ግን ከፈሪሳውያን አንዳንዶቹ፣ “በሰንበት ቀን ማድረግ ያልተፈቀደውን የምታደርጉት ለምንድን ነው?” አሏቸው፡፡ 3 ኢየሱስም ለእነርሱ፣ “ዳዊት በተራበ ጊዜ እርሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት ያደረጉትን እንኳ አላነበባችሁምን? 4 ወደ እግዚአብሔር ቤት ገብቶ ከተቀደሰው ኅብስት ጥቂት ወሰደ፤ ካህናትም ብቻ ይበሉ ዘንድ የተፈቀደላቸውን ለራሱ በላ። አብረውት ከነበሩትም ለአንዳንዶቸ ይበሉ ዘንድ ሰጣቸው” አላቸው፡፡ 5 ከዚያ በኋላም፣ “የሰው ልጅ የሰንበት ጌታ ነው” አላቸው፡፡ 6 በሌላም ሰንበት ቀን ወደ ምኩራብ ገብቶ በዚያ የነበሩትን ሰዎች አስተማራቸው፡፡ በዚያም የቀኝ እጁ የሰለለች አንድ ሰው ነበረ፡፡ 7 አንድ የተሳሳተ ነገር ሲያደርግ ተመልክተው ለመክሰስ ምክንያት ያገኙ ዘንድ በሰንበት ቀን አንድን ሰው ይፈውስ እንደሆነ ፈሪሳውያንና ጸሐፍት በትኩረት ይመለከቱት ነበር፡፡ 8 እርሱ ግን ምን እንደሚያስቡ አውቆ፣ እጁ የሰለለችበትን ሰውዬ፣ “ተነሣና በሰዎች ሁሉ መካከል ቁም” አለው፡፡ ስለዚህም ሰውዬው ተነሣና በዚያ ስፍራ ቆመ፡፡ 9 ኢየሱስም፣ “ እኔም እናንተን እጠይቃችኋለሁ፡- በሰንበት ሕጋዊ የሚሆነው መልካም ማድረግ ነው ክፉ፣ ሕይወት ማድን ነው ወይስ ማጥፋት?” 10 ከዚያም ዞር ብሎ ሁሉንም ተመለከታቸውና ለሰውዬው፣ “እጅህን ዘርጋ” አለው፤ ዘረጋውም፣ እጁም ዳነለት፡፡ 11 ከዚያ በኋላም በቁጣ ተሞልተው፣ በኢየሱስ ላይ ምን እንደሚያደርጉበት እርስ በርሳቸው ተነጋገሩ፡፡ 12 በዚያም ወቅት ኢየሱስ ለመጸለይ ወደ ተራራ ወጣ፣ ሌሊቱንም ሁሉ ወደ እግዚአብሔር መጸለዩን ቀጠለ፡፡ 13 በነጋም ጊዜ ደቀመዛሙርቱን ወደ እርሱ ጠራ፣ ከእነርሱም ‘ሐዋርያት’ ብሎ የሰየማቸውን አሥራ ሁለቱን መረጠ፡፡ 14 የሐዋርያቱም ስም፣ ስምዖን (ጴጥሮስ ብሎ የሰየመው) ወንድሙ እንድርያስ፣ ያዕቆብ፣ ዮሐንስ፣ ፊልጶስ፣ በርተሎሚዎስ፣ 15 ማቴዎስ፣ ቶማስ፣ ያዕቆብ የእልፍዮስ ልጅ፣ ቀናተኛ የተባለው ስምዖን፣ 16 የያዕቆብ ልጅ ይሁዳና ከዳተኛ የሆነው ይሁዳ አስቆሮቱ ናቸው፡፡ 17 ከዚያ በኋላም ኢየሱስ ከተራራው ወረደና በደልዳላ ቦታ ላይ ቆመ፡፡ ከደቀመዛሙርቱ በርከት ያሉት፣ ከይሁዳና ከኢየሩሳሌም እንዲሁም ከጢሮስና ከሲዶና ባሕር ዳርቻ ብዙ ሰዎች በዚያ ነበሩ፡፡ 18 ወደዚያ የመጡት እርሱን ሊያዳምጡትና ከበሽታዎቻቸው ሊፈወሱ ነበር፡፡ በርኩሳን መናፍስት ሲጨነቁ የነበሩም ሰዎች ተፈወሱ፡፡ 19 የሚፈውስ ኃይል ከእርሱ ይወጣ ስለነበረ፣ በሕዝቡ መካከል ያለ እያንዳንዱ ሰው እርሱን ለመንካት ጥረት ያደርግ ነበር፤ እርሱም ሁሉንም ፈወሳቸ. 20 ከዚያ በኋላም ወደ ደቀመዛሙርቱ ተመለከተና፣ እንደዚህ አላቸው፣ “የእግዚአብሔር መንግሥት ለእናንተ ናትና፣ እናንተ ድሆች የተባረካችሁ ናችሁ፡፡ 21 አሁን የምትራቡ የተባረካችሁ ናችሁ፣ ትጠግባላችሁና፡፡ አሁን የምታለቅሱ የተባረካችሁ ናችሁ፣ ትስቃላችሁና፡፡ 22 ሰዎች በሚጠሏችሁና በሚያገሏችሁ ጊዜ እንደዚሁም በሰው ልጅ ምክንያት ስማችሁን በክፉ ሲያነሱ የተባረካችሁ ናችሁ፡፡ 23 አባቶቻቸው ነቢያትን እንደዚሁ አድርገውባቸው ነበርና ፣ በዚያን ቀን ሐሴት አድርጉ፣ በደስታም ዝለሉ፣ ምክንያቱም በሰማይ በእርግጥ ታላቅ ብድራት ይኖራችኋል፡፡ 24 እናንተ አሁኑኑ መጽናናትን ተቀብላችኋልና፣ ነገር ግን እናንተ ባለጠጎች ወዮላችሁ! 25 በኋላ ትራባላችሁና፣ እናንተ አሁን የጠገባችሁ ወዮላችሁ! በኋላ ስለምታለቅሱና ዋይ፣ ዋይ ስለምትሉ፣ እናንተ አሁን የምትስቁ ወዮላችሁ! 26 ሰዎች ሁሉ ስለ እናንተ መልካም በሚናገሩላችሁ ጊዜ ወዮላችሁ! ምክንያቱም አባቶቻቸው ለሐሰተኛ ነቢያት እንደዚያ ያደርጉላቸው ነበርና፡፡ 27 ለእናንተ ለምታደምጡ ግን እላችኋለሁ፣ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፣ ለሚጠሏችሁም መልካም አድርጉላቸው፡፡ 28 የሚረግሟችሁን መርቁ፣ ለሚያንገላቷችሁም ጸልዩላቸው። 29 አንድ ጉንጭህን ለሚመታህ ሌላውንም ጉንጭህን አዙርለት፡፡ አንድ ሰው ነጠላህን የሚወስድብህ ከሆነ፣ እጀ ጠባብህን አትከልክለው፡፡ 30 ለሚለምንህ ሁሉ ስጥ፣ አንድ ሰው የአንተ የሆነውን የሚወስድብህ ከሆነ፣ እንዲመልስልህ አትጠይቀው፡፡ 31 ሰዎች እንዲያደርጉልህ የምትፈልገውን ሁሉ አንተም ለእነርሱ ልታደርግላቸው ይገባሃል፡፡ 32 ኃጢአተኞችም እንኳን የሚወዷቸውን ይወዳሉና የሚወዷችሁን የምትወዱ ከሆነ፣ ምን ምስጋና ትቀበላላችሁ? 33 ኃጢአተኞችም እንደዚያው ያደርጋሉና መልካም ለሚያደርጉላችሁ ብቻ መልካም የምታደርጉ ከሆናችሁ፣ ምን ምስጋና ትቀበላላችሁ? 34 እንደሚመልሱላችሁ ለምትጠብቋቸው ብቻ የምታበድሩ ከሆናችሁ፣ ምን ምስጋና አላችሁ? የሰጡትን ያንኑ ያህል ለመቀበል ተስፋ አድርገው፣ ኃጢአተኞችም እንኳን ለኃጢአተኞች ያበድራሉ፡፡ 35 ነገር ግን ጠላቶቻችሁን ውደዱ፣ መልካምም አድርጉላቸው፤ ምንም ነገር ስለመቀበል ሳትጨነቁ አበድሯቸው፣ ዋጋችሁም ታላቅ ይሆናል፡፡ እርሱ ራሱ ለማያመሰግኑና ለክፉ ሰዎች ቸር ነውና፣ እናንተም የልዑል ልጆች ትባላላችሁ፡፡ 36 አባታችሁ መሐሪ እንደሆነ ሁሉ እናንተም መሐሪዎች ሁኑ፡፡ 37 አትፍረዱ አይፈርድባችሁም፤ አትኮንኑ አትኮነኑምም፤ ሌሎችን ይቅር በሉ፣ እናንተም ይቅር ትባላላችሁ፡፡ 38 ለሌሎች ስጡ፣ ለእናንተም የተጠቀጠቀ፣ የተነቀነቀ፣ በእቅፎቻችሁም ተርፎ የሚፈስ መልካም መስፈሪያ ተሰፍሮ ይሰጣችኋል፡፡ ለሌሎች ለመስፈር በምትጠቀሙበት በዚያው መስፈሪያ ለእናንተም ይሰፈርላችኋል፡፡" 39 ከዚያም ይህን ምሳሌ ነገራቸው፣ በኋላም፣ “አንድ ዕውር ሌላውን ዕውር ሊመራው ይችላልን? እንደዚያ ቢያደርግ፣ ሁለቱም ጉድጓድ ውስጥ ይገቡ የለምን? 40 ደቀመዝሙር ከመምህሩ አይበልጥም፤ ነገር ግን አንድ ሰው ፈጽሞ ከተማረ እንደ መምህሩ ይሆናል፡፡ 41 በወንድምህ ዓይን ያለውን ትንሽ ጉድፍ ለምን ትመለከታለህ? ለምንስ በራስህ ዓይን ያለውን ግንድ አትመለከትም? በራስህ ዓይን ውስጥ ያለውን ግንድ ሳትመለከት፣ 42 ለወንድምህ፣ ‘ወንድሜ ሆይ፣ ዓይንህ ውስጥ ያለውን ጉድፍ ላውጣልህ’ እንዴት ትለዋለህ? አንተ ግብዝ! በመጀመሪያ በዓይንህ ውስጥ ያለውን ግንድ አውጣ፣ ከዘያም በወንድምህ ዓይን ውስጥ ያለውን ጉድፍ ለማውጣት አጥርተህ ታያለህ፡፡ 43 የተበላሸ ፍሬ የሚያፈራ መልካም ዛፍ የለምና፣ መልካም ፍሬም የሚያፈራ የተበላሸ ዛፍ የለም፡፡ 44 እያንዳንዱ ዛፍ የሚታወቀው በሚያፈራው ፍሬ ነውና፤ ከእሾህ የበለስ ፍሬ አይለቀምም፣ ከቀጋ ቁጥቋጦም የወይን ፍሬ አይቆረጥም፡፡ 45 መልካሙ ሰው በልቡ ካከማቸው መልካም ሀብት መልካም የሆነውን ነገር ያወጣል፤ ክፉም ሰው በልቡ ካከማቸው ክፉ ክምችት ክፉ የሆነውን ያወጣል፡፡ በልቡ ሞልቶ ከተረፈው በአፉ ይናገራልና፡፡ 46 ለምንስ ‘ጌታ ሆይ፣ ጌታ ሆይ’ ትሉኛላችሁ? ለምናገራቸውስ ነገሮች ለምን አትታዘዙም? 47 ወደ እኔ የሚመጣና ለቃሌ የሚታዘዝ ምን እንደሚመስል እነግራችኋለሁ እነግራችኋለሁ፣ 48 መሬቱን በጥልቁ ከቆፈረ በኋላ መሠረቱን በዓለት ላይ በማድረግ ቤቱን እንደሚገነባ ሰው ነው፡፡ ጎርፍ በመጣ ጊዜ የውሃው ሙላት ያን ቤት ገፋው፣ ሆኖም በሚገባ ተገንብቶ ነበርና አልነቀነቀውም፡፡ 49 ነገር ግን ቃሌን ሰምቶ የማይታዘዘው ሰው ቤቱን ያለ መሠረት በመሬቱ አፈር ላይ እንደ ሠራው ሰው ነው፤ ጎርፉ በመጣ ጊዜ ቤቱን መታው፣ ወዲያውኑም ፈረሰ፣ ውድም ብሎም ጠፋ፡፡”
“እናንተ” የሚለው የድርጊት ባለቤት መግለጫ ባለ ብዙ ቁጥር ሲሆን ደቀ መዛሙርቱን ይወክላል፡፡ (የሁለተኛ መደብ ቅርጾች የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ሐረግ በታሪኩ ውስጥ አዲስ ክስተት መጀመሩን ያሳያል፡፡ ቋንቋችሁ ይህን ማሳያ መንገድ ካለው እሱን መጠቀም ይመከራል፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ ሰዎች የበለጠ ስንዴ ለማብቀል ስንዴ ዘርተውባቸው የሚገኙ ሰፋፊ የመሬት ክፍልፋዮች ናቸው፡፡
ይህ ረዥም ሳር የሚመስል የአንድ ጥራጥሬ ተክል ጫፍ ላይ የሚገኝ የተክሉ ክፍል ነው፡፡ ሊበሉ የሚችሉና የበሰሉ የተክሉ ፍሬዎችን ይይዛል፡፡
ይህን የሚያደርጉት የጥሬውን ፍሬዎች ለመለየት ነው፡፡ ይህ ግልጽ ተደርጎ መቀመጥ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በእጃቸው መሃል አድርገው ያሹአቸው ገለባውን ከፍሬው ለመለየት ነው (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህን ጥያቄ የጠየቁት ደቀ መዛሙርቱን ሕግን በመጣስ ሊከሷቸው ፈልገው ነው፡፡ ይህ በአረፍተ ሃሳብ መቀመጥ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በሰንበት ቀን ጥራጥሬ መቅጠፍ ከእግዚአብሔር ሕግ ጋር ይቃረናል” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ፈሪሳውያን አንድ እፍኝ ጥራጥሬን አሽቶ መብላትን የሚያክል ትንሽ ድርጊትን ራሱ ስራ እንደመስራት ይቆጥሩ ነበር፡፡ ይህ በግልጽ መቀመጥ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ስራን እየሰራችሁ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ፈሪሳውያን ከቅዱስ መጻሕፍት ባለመማራቸው ይገስጻቸዋል፡፡ ይህ በአረፍተ ሃሳብ መልክ ሊጻፍ ይችላል፡፡. አማራጭ ትርጉም፡- “ካነበባችሁት ነገር መማር ነበረባችሁ …. እርሱ ራሱ” ወይም “በእርግጠኝነት አንብባችኋል … እርሱ ራሱ” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ጻፎችና ፈሪሳውያን ኢየሱስ በሰንበት ቀን አንድ ሰውን ሲፈውስ ይመለከታሉ፡፡
ይህ ሌላ የሰንበት ቀን ሲሆን ኢየሱስም በምኩራብ ነበር፡፡
ይህ ሐረግ በታሪኩ ውስጥ አዲስ ክስተት መጀመሩን ያሳያል፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በታሪኩ ውስጥ አዲስ ገጸ ባህሪይን ያስተዋውቃል፡፡ (የአዲስና የቀድሞ ተሳታፊዎች መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
የሰውየው እጅ መዘርጋት እንዳይችል ሆኖ ተጎድቶ ነበር፡፡ የሰውየው እጅ ቡጢ በሚመስል ሁኔታ ታጥፎ የነበረ እንደነበርና መታጠፉም ትንሽና የተሸበሸበ እንዳስመሰለው ይገመታል፡፡
“በትኩረት ኢየሱስን እየተመለከቱት ነበር”
“ማግኘት ፈልገው”
“ከሁሉም ፊት።” ኢየሱስ ሰውየው ሁሉም ሰው ሊያየው በሚችልበት ቦታ ላይ እንዲቆም ፈልጎ ነበር፡፡
“ለፈሪሳውያኑ አላቸው”
ኢየሱስ ይህንን ጥያቄ ለፈሪሳውያን የሚጠይቃቸው በሰንበት ቀን ሰው መፈወሱ ትክክል እንደነበረ ፈሪሳውያን እንዲያምኑ ለማድረግ ነው፡፡ ስለዚህ የዚህ ጥያቄ ዓላማ መልስ ፍለጋ አይደለም፣ ይልቁንም እውነት እንደሆነ የሚያውቁትን ነገር እንዲያምኑ ለማድረግ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ኢየሱስ “እጠይቃችኋለሁ” ይላል፣ ስለዚህ ይህ ጥያቄ እንደሌሎች መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች በአረፍተ ሃሳብ ቅርጽ ተቀይሮ መጻፍ የሚችል አይደለም፡፡ ይህ ጥያቄ የጥያቄነት ቅርጹን ጠብቆ መተርጎም አለበት፡፡ (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ለሊቱን ሙሉ ከጨረሰ በኋላ አስራ ሁለት ሐዋርያትን ይመርጣል፡፡
ይህ ሐረግ የታሪኩ አዲስ ክፍል መጀመሩን ያሳያል፡፡ (የአዲስ ሁነት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
“በዚያን ጊዜ” ወይም “ይህ ከሆነ ብዙም ሳይቆይ” ወይም “በዚያን ጊዜ አካባቢ አንድ ቀን”
“ኢየሱስ ወጣ”
“ጠዋት በሆነ ጊዜ” ወይም “በቀጣዩ ቀን”
“አስራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርት መረጠ”
“ደግሞም ሐዋርያት አድረጋቸው” ወይም “እናም ሐዋርያት አድርጎ ሾማቸው”
ሉቃስ የሐዋርያቱን የስም ዝርዝር ጻፈ፡፡ ዩኤልቢ የሚባለው ትርጉም የስም ዝርዝሩን ለመጀመር እነዚህን ቃላት ይጠቀማል፡፡ (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“የስምኦን ወንድም እንድርያስ”
x
ምንም እንኳ ኢየሱስ በተለየ ሁኔታ በቀጥታ የተናገረው ለደቀ መዛሙርቱ ቢሆንም በአካባቢው ሆነው ሲሰሙ የነበሩ ብዙ ሰዎች ነበሩ፡፡
“ከመረጣቸው ከአስራ ሁለቱ ጋር” ወይም “ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት ጋር”
ይህ በገቢር ቅርጽ ሊጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ኢየሱስ እንዲፈውሳቸው” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በገቢር ቅርጽ ሊጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ኢየሱስ በእርኩስ መንፈስ ይሰቃዩ የነበሩ ሰዎችንም ፈወሰ” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“በእርኩስ መናፍስት ይቸገሩ የነበሩ” ወይም “በክፉ መናፍስት ቁጥጥር ስር የነበሩ”
“ሰዎችን ለመፈወስ ኃይል ነበረው” ወይም “ኃይሉን ሰዎችን ለመፈወስ ይጠቀም ነበር”
ይህ ቃል ሶስት ጊዜ ይደገማል፡፡ በእያንዳንዱ ጊዜም እግዚአብሔር ለተወሰኑ ሰዎች የሚያደርገውን ቸርነት ወይም እነዚያ ሰዎች ያሉበት ሁኔታ አዎንታዊ ወይም ጥሩ እንደሆነ ይናገራል፡፡
“ድሃ የሆናችሁ እናንተ የእግዚአብሔርን ቸርነት ትቀበላላችሁ” ወይም “ድሃ የሆናችሁ እናንተ ትጠቀማላችሁ”
መንግስት የሚለው ቃል መግለጫ የሌላቸው ቋንቋዎች “እግዚአብሔር ንጉሳችሁ ነውና” ወይም “እግዚአብሔር ገዢያችሁ ነውና” ሊሉ ይችላሉ፡፡
x
“የእግዚአብሔርን ቸርነት ትቀበላላችሁ” ወይም “ትጠቀማላችሁ” ወይም “እንደዛ መሆን ለእናንተ ምንኛ መልካም ነው”
“ሲቃወሟችሁ”
“ከሰው ልጅ ጋር የተያያዛችሁ ስለሆናችሁ” ወይም “የሰው ልጅንም ስለሚቃወሙት”
“እነዚህን ነገሮች ሲያደርጓችሁ” ወይም “ያ ነገር በተከሰተ ጊዜ”
ይህ ፈሊጥ “እጅግ ደስተኛ ሁኑ” ማለት ነው፡፡ (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)
“ትልቅ ክፍያ” ወይም “መልካም ስጦታዎች”
“ምንኛ ክፉ ነገር ይጠብቃችኋል!” ወይም “ምንኛ የከፋ ሐዘን ውስጥ ትገቡ ይሆን”
እዚህ ላይ “ሰዎች” የሚለው ቃል ሁሉንም የሕዝብ ክፍል ያካትታል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሕዝብ ሁሉ ሲናገሩላችሁ” ወይም “ሁሉም ሰው ሲናገሩላችሁ” (ተባዕታይ ቃላቶች ሴቶችን ሲጨምር የሚለውን ይመልከቱ)
“አባቶቻቸውም ለሐሰት ነቢያት መልካምን ነገር ይናገሩላቸው ነበር”
ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱና አብረው ሆነው ይሰሙ ለነበሩት ሕዝብ መናገሩን ይቀጥላል፡፡
ኢየሱስ አሁን ለደቀመዛሙርት ብቻ ሳይሆን በዚያ ለነበሩት ሰዎች ለሁሉም መናገር ይጀምራል፡፡ (የአዲስና የቀድሞ ተሳታፊዎች መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ ያሉት እያንዳንዱ ትዕዛዛት በቀጣይነት መደረግ ያለባቸው ናቸው፣ አንድ ጊዜ ብቻ የሚደረጉ አይደሉም፡፡
ይህ መውደድ ያለባቸው ጠላቶቻቸውን ብቻና ወዳጆቻቸውን መውደድ የለባቸውም ለማለት አይደለም፡፡ ይህ በግልጽ መቀመጥ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ወዳጆቻችሁን ብቻ ሳይሆን ጠላቶቻችሁንም ውደዱ” (አስጨምሬ የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ ሁለት ሐረጎች ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው፣ ዋናው ነጥብ ላይም አጽንኦት ይሰጣሉ፡፡ (ጥምር ቃል የሚለውን ይመልከቱ)
የሚባርከው እግዚአብሔር ነው፡፡ ይህ ግልጽ ተደርጎ መቀመጥ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር እንዲባርካቸው ጠይቁ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
x
“ማንም ሰው ቢመታህ”
“አንደኛውን ጉንጭህን”
የሚያጠቃው ሰውዬ በሰውየው ላይ ምን እንደሚያደርስ ግልጽ አድርጎ መጻፍ ሊያስፈልግ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ፊትህን አዙረህ ሌላኛውን ጉንጭህንም እንዲመታህ ስጠው” (አስጨምሬ የሚለውን ይመልከቱ)
“ከመውሰድ አታግደው”
“ማንም ሰሰው አንድን ነገር ቢጠይቅህ ስጠው”
“መልሶ እንዲሰጥህ አትጠብቅ” ወይም “መልሶ እንዲሰጥህ አትጠይቀው”
በአንዳንድ ቋንቋዎች ቅደም ተከተሉን መለወጥ የተለመደ ሊሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ለሰዎች ማድረግ ያለባችሁ እናንተ እነርሱ እንዲያደርጉባችሁ እንደምትፈልጉት ነው” ወይም “ለሰዎች ማሰብ ያለባችሁ እነርሱ ለእናንተ እንዲያስቡ በምትፈልጉት መንገድ ነው”
“ምን ዋጋ ታገኛላችሁ?” ወይም “ያንን በማድረጋችሁ ምን አይነት ምስጋናን ታተርፋላችሁ” ይህ በአረፍተ ሃሳብ ቅርጽ ሊጻፍ ይችላል፡፡. አማራጭ ትርጉም፡- “ያንን በማድረጋችሁ ምንም ሽልማትን አታገኙም” ወይም “ያንን በማድረጋችሁ እግዚአብሔር ምንም ሽልማትን አይሰጣችሁም” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
የሙሴ ሕግ አይሁዳውያን እርስ በርስ በተበዳደሩት ገንዘብ ላይ ወለድን እንዳይቀበሉ ያዝዛል፡፡ (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“የሰጣችሁት ሰው የሰጣችሁትን ነገር እንዲመልስላችሁ ሳትጠብቁ” ወይም “የሰጣችሁት ሰው ምንም ነገር እንዲመልስላችሁ ሳትጠብቁ”
“ታላቅን ሽልማት ትቀበላላችሁ” ወይም “መልካም ክፍያን ታገኛላችሁ” ወይም “ባደረጋችሁት ነገር ምክንያት ጥሩ ስጦታን ታገኛላችሁ”
“ልጆች” የሚለውን ቃል በቋንቋችሁ ውስጥ የተለመደ የአንድ ሰውን ልጅ ለመግለጽ ጥቅም ላይ በሚውለው ቃል ተርጉሞ ማቅረብ ተመራጭ ነው፡፡
ልጆች የሚለው ቃል ብዙ ቁጥር መሆኑን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ምክንያቱም “የልዑል ልጅ” ከሚለው ከኢየሱስ ማዕረግ ጋር መመሳሰል ስለሌለበት ነው፡፡
“እርሱን የማያመሰግኑና ሰዎችና ክፉዎች የሆኑ”
ይህ እግዚአብሔርን ይወክላል፡፡ ይህን በቋንቋችሁ ውስጥ ስጋዊ አባትን በሚወክለው ቃል መተርጎም ቢቻል ይመረጣል፡፡
“ሰው ላይ አትፍረዱ” ወይም “የመረረ ነቀፋ በሰው ላይ አታድርሱ”
“ስለዚህም እናንተ”
x
ኢየሱስ የሚሰጠው ማን እንደሆነ ግልጽ አድርጎ አይናገርም፡፡ ሊሆን የሚችለው፡ 1) “የሆነ ሰው ይሰጣችኋል” ወይም 2) “እግዚአብሔር ይሰጣችኋል” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ ኢየሱስ እግዚአብሔርን ወይም በቸርነት የሚሰጡትን ሰዎችን እንደ አንድ ቸር ነጋዴ አድርጎ ያቀርባቸዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር የተጨቆነ የተነቀነቀና የተትረፈረፈ መጠን ያለውን ሞልቶ በጭናችሁ ላይ ያፈስሳል” ወይም “ቸር የጥራጥሬ ነጋዴ ጥራጥሬን ጨቁኖና ነቅንቆ መጠኑም ሞልቶ እስኪፈስ ድረስ ብዙ አድርጎ እንደሚሰጥ፣ ለእናንተም በቸርነት እንዲሁ ይሰጧችኋል፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“ትልቅ መጠን ያለው”
ኢየሱስ ማን እንደሚሰፍርላቸው በግልጽ አይናገርም፡፡ ትርጉም ሊሆኑ የሚችሉት፡ 1) “እነርሱ ይሰፍሩላችኋል” ወይም “እግዚአብሔር ይሰፍራችኋል” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ የንግግሩን ዋና ሃሳብ ለማጠንከር አንዳንድ ምሳሌዎችን ይጨምራል፡፡ (ተምሳሌቶች የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ሰዎቹ ኪዚህ በፊት ያውቁ የነበረውን ነገር ደግመው እንዲያስ ለማድረግ ይህን ጥያቄ ይጠይቃቸዋል፡፡ ይህ በአረፍተ ነገር ቅርጽ ደግሞ መጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሁላችንም አንድ ዕውር ሰው ሌላ ዕውር ሰውን መንገድ ሊመራ እንደማይችል እናውቃለን” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ይሄን ጥያቄ የጠየቀው ሰዎቹ የሌላን ሰው ኃጢአት ከመመልከታቸው በፊት የራሳቸውን ኃጢአት መመልከት እንዳለባቸው ለመሞገት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በራስህ አይን ውስጥ ያለውን ምሰሶ ትተህ በወንድምህ አይን ያለውን … አትመልከት” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ዘይቤ ሌላ አማኝ የሚያደርጋቸውን ጥቃቅን ስህተቶችን ይወክላል፡፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“ጠብታ” ወይም “ጉድፍ” ወይም “የአቧራ ብናኝ”፡፡ የሰው አይን ውስጥ ሊገባ የሚችል በጣም ትንሽ ነገርን የሚወክል ቃል ካለ እሱን መጠቀም ይቻላል፡፡
እዚህ ላይ “ወንድም” የሚለው ሌላ አይሁዊን ወይም በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምን ሌላ ሰውን ይወክላል፡፡
ይህ ዘይቤ የአንድ ሰውን ትልልቅ የሚባሉ ጥፋቶችን የሚወክል ነው፡፡ ግንድ በአንድ ሰው አይን ውስጥ ቃል በቃል ሊገባ አይችልም፡፡ ኢየሱስ አጋንኖ የሚያወራው አንድ ሰው የሰውን ጥቃቅን ጥፋቶች ከማየቱ በፊቱ የራሱን ትልልቅ ጥፋቶች መመልከት እንዳለበት አጽንኦት ለመስጠት ነው፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ እና ግነት እና ጅምላ ፍረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“ምሰሶ” ወይም “ሳንቃ”
ኢየሱስ ይሄን ጥያቄ የሚጠይቀው ሰዎቹ የሰው ኃጢአት ላይ ትኩረት ከማድረግ ይልቅ በራሳቸው ኃጢአቶች ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው ለመሞገት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በአይንህ … ማለት የለብህም” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ሰዎች አንድን ዛፍ መልካም ወይ ክፉ መሆኑንና ምን ዓይነት ዛፍ መሆኑን ከሚያፈራው ፍሬ ማወቅ ይችላሉ፡፡ ኢየሱስ አንድን ሰው ከሚያደርገው ድርጊት ምን ዓይነት ሰው እንደሆነ ማወቅ እንደምንችል ለማሳየት ይሄንን ንግግር እንደ ዘይቤ ይጠቀመዋል፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“ምክንያቱም ስላለ” ይህ የሚያሳየው ቀጥሎ የሚናገረው ነገር ወንድሞች ላይ ለምን መፍረድ እንደማይገባ ምክንያቱን እንደሚያመለክት ነው፡፡
“ጤናማ ዛፍ”
እየበሰበሰ ያለ ፍሬ ወይም መጥፎ ወይም ዋጋ የሌለው ፍሬ
እዚህ ላይ ኢየሱስ የአንድ ሰውን ሃሳብ ሰውየው ካለው ከመልካም ወይም ከክፉ መዝገብ ጋር አነጻጽሮ ያቀርባል፡፡ መልካም ሰው መልካም ሃሳቦችን ሲያስብ መልካም ድርጊቶችን በመፈጸም ይጠመዳል፡፡ ክፉ ሰው ክፉ ሃሳቦችን ሲያስብ ክፋት ያለባቸውን ድርጊቶች በመስራት ይጠመዳል፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “መልካም” የሚለው ቃል ጻድቅ ወይም መልካም ሥነ ምግባር ያለው የሚለውን ይወክላል፡፡
እዚህ ላይ “ሰው” የሚለው ወንድ ወይም ሴት የሆነን ሰው ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡-“መልካም ሰው” (ተባዕታይ ቃላቶች ሴቶችን ሲጨምር የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ የአንድ ሰው መልካም ሃሳቦች በዚያ ሰው ልብ ውስጥ እንደሚቀመጥ እንደ መዝገብ ተደርጎ ተመስሏል፡፡ “ልብ” የሚለው ደግሞ የአንድን ሰው ውስጣዊ ማንነት ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በውስጡ ከሚያኖረው ከመልካም ነገር” ወይም “እርሱ ዋጋ የሚሰጣቸው መልካም ነገሮች” (ተለዋጭ ዘይቤ እና ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
መልካም የሆነውን ያፈራል ማለት መልካም ስራዎችን ይሰራል የሚለውን የሚያሳይ ዘይቤ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “መልካም የሆነውን ይሰራል” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
x
ኢየሱስ እርሱ የሚያስተምረውን የሚቀበልን ሰው በድንጋይ መሰረት ላይ ቤቱን ሰርቶ ጎርፍ ቤቱን ከማያፈርስበት ሰው ጋር አነጻጽሮ ያቀርባል፡፡ (ተነፃፃሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ እርሱ የሚናገረውን ሰምቶ የማይታዘዘውን ሰው ቤቱን ያለመሰረት ሰርቶ ጎርፍ በመጣ ጊዜ ቤቱ ከሚፈርስበት ሰው ጋር አነጻጽሮ ያቀርባል፡፡ (ተነፃፃሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“ግን” የሚለው ቃል ቀድሞ ከተነገረው ቤቱን መሰረት ላይ ከሰራው ሰው ጋር ጠንካራ የተቃራኒ ንጽጽር መኖሩን ያሳያል፡፡
አንዳንድ ሰዎች መሰረት ያለው ቤት ጠንካራ እንደሆነ ላያውቁ ይችላሉ፡፡ ተጨማሪ መረጃ መስጠት አስፈላጊ ሊሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ነገር ግን ቤቱን ከመስራት በፊት መሬትን ቆፍሮ መሰረትን አልገነባም ነበር” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ቤቱን ከመሬት ጋር የሚያገናኘው የሕንጻው ክፍል፡፡ ኢየሱስ በኖረበት ጊዜ የነበሩ ሰዎች መሬቱን አለት ድንጋይ እስከሚያገኙ ድረስ ቆፍረው በአለቱ ላይ ነበር ቤቱን ይገነቡ የነበረው፡፡ አለቱ የቤቱ መሰረት ነበር፡፡
1 ኢየሱስ ለሕዝቡ የሚናገረውን ሁሉ ከጨረሰ በኋላ፣ ወደ ቅፍርናሆም ገባ። 2 እጅግ የሚወደውና ሞት አፋፍ ላይ የደረሰ አገልጋይ የነበረው አንድ የመቶ አለቃ ነበረ። 3 ስለ ኢየሱስ በሰማ ጊዜ መጥቶ አገልጋዩን ከመሞት እንዲያድንለት እንዲለምኑት የአይሁድ ሽማግሌዎችን ወደ እርሱ ላካቸው። 4 እነርሱ ወደ ኢየሱስ በቀረቡ ጊዜ፣ "ለእርሱ ይህን ልታደርግለት የተገባ ነው፣ 5 ምክንያቱም ሕዝባችንን ይወዳል፣ ምኩራብ የሠራልንም እርሱ ነው" በማለት አጥብቀው ለመኑት። 6 ስለዚህ ኢየሱስ ዐብሮአቸው መንገዱን ቀጠለ። ነገር ግን ወደ ቤቱ ለመድረስ ጥቂት በቀረው ጊዜ፣ የመቶ አለቃው፣ እንዲህ ብለው እንዲነግሩት ወዳጆቹን ወደ ኢየሱስ ላካቸው፤ “ጌታ ሆይ፣ አትድከም፣ ምክንያቱም አንተ ወደ ቤቴ ልትገባ የተገባሁ አይደለሁም፤ 7 ከዚህ የተነሣ እኔም ራሴ ወደ አንተ ለመምጣት የምገባ አድርጌ እንኳ ራሴን አልቈጥረውም። ነገር ግን ቃል ብቻ ተናገር አገልጋዬ ይፈወሳል፤ 8 እኔም ደግሞ ባለ ሥልጣን ነኝና፤ በእኔ ሥር ወታደሮች አሉኝ፤ አንዱን 'ሂድ' ስለው ይሄዳል፤ ሌላውን 'ና' ስለው ይመጣል። 9 ኢየሱስ ይህን በሰማ ጊዜ፣ በመቶ አለቃው ተደንቀ፣ ይከተሉት ወደነበሩት ሰዎችም ዞር ብሎ፣ “በእስራኤልም እንኳ እንዲህ ያለ እምነት ያለው ሰው አላገኘሁም” አላቸው። 10 ከዚያም የተላኩት ሰዎች ወደ መቶ አለቃው ቤት ተመልሰው፣ አገልጋዩን ጤናማ ሆኖ አገኙት። 11 ከጥቂት ጊዜ በኋላ ኢየሱስ ናይን ወደ ምትባል ከተማ እየተጓዘ ነበር። ከእርሱም ጋር ደቀ መዛሙርቱና ብዙ ሕዝብ ዐብረውት ይሄዱ ነበር። 12 ወደ ከተማይቱም በቀረበ ጊዜ፣ እነሆ፣ ለእናቱ ብቸኛ ልጅ የነበረ ሰው ሞቶ አስከሬኑን ሰዎች ተሸክመው እየሄዱ ነበር። የልጁ እናት መበለት ነበረች፤ በርከት ያሉ ለቀስተኞችም ተከትለዋት ነበር። 13 ጌታም ተመልክቷት እጅግ ዐዘነላትና፣ “አታልቅሺ” አላት። 14 ከዚያም ወደ ቃሬዛው ተጠግቶ ነካው ቃሬዛውን የተሸከሙትም ቆሙ። ኢየሱስ፣ “አንተ ወጣት ተነሥ እልሃለሁ” አለ። 15 ወጣቱም ተነሥቶ መናገር ጀመረ፤ ከዚያም ኢየሱስ ልጁን ለእናትዮዋ ሰጣት። 16 ከዚያም ሁሉንም ፍርሀት ያዛቸው። “ታላቅ ነቢይ በመካከላችን ተነሥቶአል" "ደግሞ እግዚአብሔር ሕዝቡን ጎበኝቶአል” በማለት እግዚአብሔርን አመሰገኑ። 17 ይህ የኢየሱስ ዝና በመላው ይሁዳና በዙሪያው ባለው አገር ሁሉ ተሰማ። 18 የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ስለ እነዚህ ነገሮች ሁሉ አወሩለት። 19 ከዚያም ዮሐንስ፣ “የምትመጣው አንተ ነህን ወይስ ሌላ እንጠብቅ?” ብለው እንዲጠይቁት ከእነርሱ ሁለቱን ወደ ኢየሱስ ላካቸው። 20 ሰዎቹም ወደ ኢየሱስ ቀርበው፣ "'የምትመጣው አንተ ነህን ወይስ ሌ እንጠብቅ?' ብለን እንድንጠይቅህ መጥምቁ ዮሐንስ ልኮናል" አሉ። 21 በዚያኑ ሰዓት ኢየሱስ ብዙ ሰዎችን ከተለያየ ደዌና በሽታ ፈወሰ። በአጋንንት የተያዙትን ነጻ አወጣ፣ ዐይነ ስውራንም ማየት እንዲችሉ አደረገ። 22 ኢየሱስ መልእክተኞቹን፣ “ወደ ዮሐንስ ተመልሳችሁ ሂዱና ያያችሁትንና የሰማችሁትን እንዲህ ብላችሁ ንገሩት፣ ዐይነ ስውራን ያያሉ፣ ሽባዎች ይራመዳሉ፣ ለምጻሞች ይነጻሉ፣ መስማት የተሳናቸው ይሰማሉ፣ ሙታን ይነሣሉ፣ ለድኾችም ወንጌል እየተሰበከ ነው። 23 በማደርጋቸው ነገሮች በእኔ ሳይሰናከል በእምነቱ የሚጸና ሰው የተመሰገነ ነው” አላቸው። 24 የዮሐንስ መልእክተኞች ከሄዱ በኋላ ኢየሱስ ስለ ዮሐንስ ለሕዝቡ እንዲህ ይላቸው ጀመር፣ “ምን ልታዩ ወደ በረሐ ወጣችሁ በነፋስ የሚወዛወዘውን ሸንበቆ ለማየት ነውን? 25 ወይስ የወጣችሁት የሚያማምሩ ልብሶች የለበሱትን ለማየት ነውን? እነሆ፣ የሚያማምሩ ልብሶችን ለብሰው በድሎት የሚኖሩ ሰዎች የሚገኙት በአብያተ መንግሥታት ነው። 26 ልታዩ የወጣችሁት ግን ነቢይን ከሆነ፣ እንግዲያውስ ያያችሁት ነቢይን ብቻ ሳይሆን ከነቢያትም የበለጠውን ነው። 27 ስለ እርሱ፣ ‘እነሆ፣ በፊታችሁ መንገድን የሚጠርግ መልእክተኛዬን እልካለሁ’ ተብሎ ተጽፏል። 28 እላችኋለሁ፣ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከዮሐንስ የሚበልጥ ማንም የለም፤ ቢሆንም በእግዚአብሔር መንግሥት ከሁሉም የሚያንሰው ይበልጠዋል። 29 ይህን በሰሙ ጊዜ ቀራጮች እንኳ ሳይቀሩ ሕዝቡ ሁሉ እግዚአብሔር ጻድቅ እንደ ሆነ ተናገሩ፤ ምክንያቱም እነርሱን ያጠመቃቸው ዮሐንስ ነበር። 30 በዮሐንስ ያልተጠመቁት ፈሪሳውያንና የአይሁድ የሕግ ዐዋቂዎች ግን በራሳቸው ፈቃድ የእግዚአብሔርን ጥበብ ተቃወሙ። 31 እንግዲያውስ የዚህን ትውልድ ሰዎች ከምን ጋር አመሳስላቸዋለሁ? ምንስ ይመስላሉ? 32 እርስ በርሳቸው በገበያ እየተጠራሩ፥ ‘እንቢልታ ነፋንላችሁ እናንተም አልዘፈናችሁም፣ ሙሾ አወጣንላችሁ እናንተም አላለቀሳችሁም’ እንደሚባባሉ ልጆች ናቸው። 33 መጥምቁ ዮሐንስ እንጀራ ሳይበላና ወይን ጠጅ ሳይጠጣ ቢመጣ፣ ‘ጋኔን አለበት’ አላችሁት፣ 34 የሰው ልጅ እየበላና እየጠጣ ቢመጣ፦ ‘በላተኛና ጠጪ፣ የቀራጮችና የኃጢአተኞች ወዳጅ!’ አላችሁት። 35 ጥበብ ግን በልጆቿ ሁሉ ትክክል እንደ ሆነች ታወቀች። 36 አንድ ፈሪሳዊም በቤቱ ዐብሮት እንዲመገብ ኢየሱስን ጋበዘው ኢየሱስ ግብዣውን ተቀብሎ ወደ ማዕዱ ቀረበ። 37 እነሆ፣ በዚያ ከተማ በመጥፎ ምግባሯ የታወቀች እንዲት ሴት ኢየሱስ በፈሪሳዊው ቤት ተጋብዞ በማዕድ እንደ ተቀመጠ ተረድታ የአልባስጥሮስ ሽቱ ብልቃጥ ይዛ ወደ ቤቱ ገባችና 38 ከኢየሱስ በስተኋላ ከእግሩ አጠገብ ቆማ ማልቀስ ጀመረች። ከዚያም በእንባዋ እግሩን ማራስና በፀጉሯም ማበስ ቀጠለች፣ እግሩንም ትስመው በሽቱም ትቀባው ነበር። 39 ኢየሱስን የጋበዘው ፈሪሳዊ ይህንን ባየ ጊዜ፣ "ይህ ሰው በእርግጥ ነቢይ ቢሆን ኖሮ እየነካችው ያለችው ሴት ምን ዓይነት ሴት እንደ ሆነች ባወቀም ነበር" ብሎ በልቡ ዐሰበ። 40 ኢየሱስም መልሶ ፈሪሳዊውን፣ “አንድ የምነግርህ ነገር አለኝ” አለው። ፈሪሳዊውም፣ “መምህር ሆይ፣ ተናገር” አለው። 41 ኢየሱስ፣ “ከአንድ አበዳሪ ገንዘብ የተበደሩ ሁለት ሰዎች ነበሩ፣ አንደኛው የአምስት መቶ ዲናር ሌላኛው ደግሞ የሃምሳ ዲናር ዕዳ ነበረባቸው፤ 42 የሚከፍሉት ስላልነበራቸው ሁለቱንም ዕዳቸውን ማራቸው። ስለዚህ ዕዳቸው ከተማረላቸው ከእነዚህ ከሁለቱ ማንኛቸው አብዳሪውን የበለጠ የሚወደው ይመስልሃል? አለው። 43 ስምዖንም መልሶ፣ “ብዙ የተተወለቱ ይመስለኛል” አለው። ኢየሱስ፣ “በትክክል መልሰሃል” አለው። 44 ኢየሱስም ወደ ሴትዮይቱ ዞር ብሎ ስምዖንን እንዲህ አለው፣ “ይህችን ሴት ትመለከታታለህ? እኔ ወደ ቤትህ ገብቼ ለእግሬ ውሃ እንኳን አላቀረብህልኝም፣ እርሷ ግን በእንባዋ እግሬን አራሰች፣ በፀጉሯም አበሰችው፤ 45 አንተ አልሳምኸኝም፣ እርሷ ግን ከመጣሁበት ጊዜ ጀምሮ እግሬን ከመሳም አላቋረጠችም። 46 አንተ ራሴን ዘይት አልቀባኸኝም፣ እርሷ ግን እግሬን ሽቱ ቀባች፣ 47 ስለዚህ ለበዛው ኃጢአቷ ብዙ ምሕረትን አግኝታለችና አብዝታ ወዳለች። ጥቂት ኃጢአቱ ይቅር የተባለለት ግን ጥቂት ይወዳል” አለው። 48 ከዚያም ወደ ሴቱቱ ዞር ብሎ፣ “ኃጢአትሽ ተሰርዮልሻል” አላት። 49 በዚያም ተቀምጠው የነበሩት እርስ በርሳቸው፣ “ኃጢአትን ይቅር የሚል ይህ ማን ነው?” አሉ። 50 ከዚያም ኢየሱስ ሴቲቱን፣ “እምነትሽ አድኖሻል። በስላም ሂጂ” አላት።
ኢየሱስ የመቶ አለቃውን አገልጋይ ወደፈወሰበት ወደ ቅፍርናሆም ይገባል።
የአነጋገር ዘይቤ የሆነው “እየሰሙት”፣ እርሱ የተናገረውን እንዲሰሙት ስለመፈለጉ አጽንዖት ይሰጣል። እ.ት፡ “ይሰሙት ለነበሩት ሰዎች” ወይም “ለተገኘው ሕዝብ” ወይም “ሕዝቡ እንዲሰሙ” (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)
ይህ በታሪኩ ውስጥ አዲስ ሁነትን ይጀምራል። (አዲስ ሁነትን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
“የመቶ አለቃው ከፍ ያለ ቦታ የሚሰጠው” ወይም “ያከብረው የነበረ”
“አብሮት ሄደ”
ድርብ አሉታው ሊቀየር ይችላል። አ.ት፡ “ወደ ቤቱ ሲቃረብ” (ድርብ አሉታ የሚለውን ተመልከት)
የመቶ አለቃው ኢየሱስን በትህትና እያነጋገረው ነበር። አ.ት፡ “ወደ ቤቴ ለመምጣት ራስህን አታድክም” ወይም “ላስቸግርህ አልፈልግም”
ይህ የአነጋገር ዘይቤ ሲሆን ትርጉሙ “ወደ ቤቴ መምጣት” ማለት ነው። የአንተ ቋንቋ “ወደ ቤቴ መምጣት” የሚል ትርጉም ያለው የአነጋገር ዘይቤ ካለው እዚህ ጋ ልትጠቀምበት ያስፈልግህ እንደሆነ አስብበት። (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ በመናገር ብቻ አገልጋዩን ሊፈውሰው እንደሚችል የመቶ አለቃው ተረድቷል። እዚህ ጋ “ቃል” የሚያመለክተው ትዕዛዝን ነው። አ.ት፡ “ትዕዛዝ ብቻ ስጥ”
እዚህ ጋ “አገልጋይ” ተብሎ የተተረጎመው ቃል አብዛኛውን ጊዜ የሚተረጎመው “ወንድ ልጅ” ተብሎ ነው። ይህ ምናልባት አገልጋዩ ታዳጊ ወጣት እንደ ነበረ ወይም የመቶ አለቃው ለእርሱ ያለውን ፍቅር ይጠቁም ይሆናል።
“እኔም ደግሞ የምታዘዘው የበላይ አለኝ”
“በሥልጣኔ ሥር”
እዚህ ጋ “አገልጋይ” ተብሎ የተተረጎመው ቃል ለአገልጋይ የተለመደ ቃል ነው።
“በመቶ አለቃው ተደነቀ”
ኢየሱስ ይህንን ያለው ሊነግራቸው ስላለው አስገራሚ ነገር አጽንዖት ለመስጠት ነው።
ይህ የሚያመለክተው፣ ኢየሱስ የአይሁድ ሕዝብ እንዲህ ያለ እምነት እንዲኖራቸው መጠበቁን፣ እነርሱ ግን እንዳልነበራቸው ነው። አሕዛብ እንዲህ ያለ እምነት እንዲኖራቸው አልጠበቀም፣ ሆኖም ይህ ሰው ነበረው። ይህንን ጠቋሚ መረጃ መጨመር ይኖርብህ ይሆናል። አ.ት፡ “እንደዚህ አሕዛብ የሚታመንብኝን አንድም እስራኤላዊ አላገኘሁም!”
እነዚህ የመቶ አለቃው የላካቸው ሰዎች መሆናቸው ግልጽ ነው። ይህ በአ.ት፡ “ሮማዊው ባለሥልጣን ወደ ኢየሱስ ልኳቸው የነበሩ ሰዎች”
ኢየሱስ የሞተውን ሰው ወደ ፈወሰበት ወደ ናይን ከተማ በመሄድ ላይ ነው።
የከተማይቱ ስም ነው። (ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)
“እነሆ” የሚለው ቃል በታሪኩ ውስጥ ስላለው የሞተ ሰው ሊያስተዋውቀን ያነቃናል። የአንተ ቋንቋ ይህንን አሳብ መግለጫ መንገድ ይኖረው ይሆናል። አ.ት፡ “አንድ የሞተ ሰው ነበር፣ እርሱም” (አዲስና ነባር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊተረጎም ይችላል። አ.ት፡ “ሰዎች የሞተውን ሰው ተሸክመው ከከተማይቱ ይወጡ ነበር” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“ብዙ ሕዝብ ነበሩ፤ ተሸክመውት ወጡ፤ እርሱም ለእናቱ ብቸኛ ልጇ ነበር፣ እርሷም መበለት ነበረች”። ይህ ስለ ሟቹ ሰውና ስለ እናቱ ዳራዊ መረጃ ነበር። (ዳራዊ መረጃ የሚለውን ተመልከት)
ባሏ የሞተባትና ሁለተኛ ያላገባች ሴት
“በጣም አዘነላት”
x
ይህ ኢየሱስ ሞቶ የነበረውን ሰው በመፈወሱ ምክንያት የሆነውን ነገር ይነግረናል።
“ሁሉም ፍርሐት ሞላባቸው”። ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ሁሉም በጣም ፈሩ” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ያመለክቱ የነበሩት ወደ አንድ ማንነቱ ወዳልታወቀ ነቢይ ሳይሆን ወደ ኢየሱስ ነበር። እዚህ ጋ “ተነሥቷል” የሚለው ቃል “እንዲሆን ተደርጓል” ለሚለው የአነጋገር ዘይቤ ነው። ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “እግዚአብሔር ከእኛ አንዱን ታላቅ ነቢይ አድርጎታል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ እና የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)
የዚህ የአነጋገር ዘይቤ ትርጉም “አስቧቸዋል” የሚል ነው። (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)
“ይህ ወሬ” የሚያመለክተው ሕዝቡ በቁጥር 16 ላይ ይናገሩት የነበሩትን ነገር ነው። ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ሕዝቡ ይህንን የኢየሱስን ዝና አሰራጩት” ወይም “ሕዝቡ የኢየሱስን ዝና ለሌሎች ነገሯቸው”
“ይህ ዝና” ወይም “ይህ መልዕክት”
ዮሐንስ ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱን ኢየሱስን እንዲጠይቁት ይልካቸዋል።
ይህ በታሪኩ ውስጥ ስላለው አዲስ ሁነት ያስተዋውቃል። (አዲስ ሁነትን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
“ለዮሐንስ ነገሩት”
“ኢየሱስ ሲያደርጋቸው የነበሩትን ነገሮች ሁሉ”
ይህ ዐረፍተ ነገር፣ አንድ ግልጽ የሆነ ትዕምርተ ጥቅስ እንዲኖረው እንደገና ሊጻፍ ይችላል። አ.ት፡ “ሰዎቹ ‘እየመጣህ ያለኸው አንተ ነህ? ወይስ ሌላ እንጠብቅ’ ብለው እንዲጠይቁት አጥማቂው ዮሐንስ የላካቸው መሆኑን ተናገሩ” ወይም “ሰዎቹ፣ ‘እየመጣህ ያለኸው አንተ ትሆን እንደሆን ወይም ሌላ መጠበቅ ይኖርብን እንደሆን እንድንጠይቅህ አጥማቂው ዮሐንስ ወደ አንተ ልኮናል’ አሉት”። (ግልጽ የሆነና ያልሆነ ትዕምርተ ጥቅስ ተመልከት)
“ሌላ እንጠብቅ?” ወይም “ሌላን ሰው እንጠባበቅ?”
“በዚያን ጊዜ”
ፈውሱን እንደገና መናገር ይጠቅም ይሆናል። አ.ት፡ “ከክፉ መናፍስት ፈወሳቸው” ወይም “ሰዎችን ከክፉ መናፍስት ነጻ አወጣቸው” (See: Ellipsis)
“ለዮሐንስ መልዕክተኞች እንዲህ አላቸው” ወይም “ዮሐንስ ለላካቸው መልዕክተኞች እንዲህ አላቸው”
“ለዮሐንስ ንገሩት”
“የሞቱ ሰዎች እንደገና በሕይወት እንዲኖሩ ተደርገዋል”
“ድኾች ሰዎች”
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “በሥራዎቼ ምክንያት በእኔ ማመኑን የማያቋርጠውን ሰው እግዚአብሔር ይባርከዋል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“የማያቋርጡ ሰዎች የተባረኩ ናቸው” ወይም “ማንም የማያቋርጥ ሰው የተባረከ ነው” ወይም “የ . . . ማንም ቢሆን የተባረከ ነው”። ይህ አንድ ተለይቶ የታወቀ ሰው አይደለም።
የዚህ ድርብ አሉታ ትርጉም “በእኔ ማመኑን የሚቀጥል” (ድርብ አሉታ የሚለውን ተመልከት)
“ሙሉ በሙሉ በእኔ የሚታመን”
x
“ነቢያት ስለ እርሱ የጻፉለት ነቢይ እርሱ ነው” ወይም “ከረጅም ዓመታት በፊት ነቢያት የጻፉለት ሰው ዮሐንስ ነው”
በዚህ ቁጥር ኢየሱስ ከትንቢተ ሚልክያስን በመጥቀስ፣ ሚልክያስ የተናገረለት መልዕክተኛ ዮሐንስ መሆኑን ይናገራል።
የዚህ የአነጋገር ዘይቤ ትርጉም፣ “በፊት ለፊትህ” ወይም “ከአንተ ቀድሞ እንዲሄድ” (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)
በትዕምርተ ጥቅሱ ውስጥ እግዚአብሔር የሚናገረው ለመሲሑ ስለ ነበረ “የአንተ” የሚለው ቃል ነጠላ ቁጥር ነው።
ኢየሱስ የሚናገረው ለሕዝቡ ስለሆነ “አንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥርን አመልካች ነው። ኢየሱስ ይህንን የሚለው ቀጥሎ ለሚናገረው አስገራሚ እውነት አጽንዖት ለመስጠት ነው።
“ሴቶች ከወለዷቸው መካከል”። ይህ ሰዎችን ሁሉ የሚያመለክት ዘይቤአዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “በሕይወት ከነበሩት ሰዎች ሁሉ” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“የሚበልጠው ዮሐንስ ነው”
ይህ የሚያመለክተው እግዚአብሔር በሚመሠርተው መንግሥት ውስጥ አባል የሚሆነውን ማንኛውንም ሰው ነው።
በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ የሰዎች መንፈሳዊ ሁኔታ መንግሥቱ ከመመሥረቱ በፊት ከነበራቸው የሚበልጥ ይሆናል። አ.ት፡ “የመንፈሳዊ ሕይወታቸው ደረጃ ከዮሐንስ ይልቅ ከፍ ያለ ይሆናል”
የዚህ መጽሐፍ ደራሲ የሆነው ሉቃስ ሰዎች ለዮሐንስና ለኢየሱስ ስላሳዩት ምላሽ አስተያየቱን ይሰጣል።
ለበለጠ ግልጽነት የዚህ ቁጥር ቅደም ተከተል ሊስተካከል ይችላል። አ.ት፡ “ቀረጥ ሰብሳቢዎቹን ጨምሮ በዮሐንስ የተጠመቁ ሰዎች ሁሉ ይህንን በሰሙ ጊዜ እግዚአብሔር ጻድቅ መሆኑን መሰከሩ”
“እግዚአብሔር ጻድቅ መሆኑን አሳይቷል አሉ” ወይም “እግዚአብሔር በጽድቅ አድርጓል ብለው መሰከሩ”
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ዮሐንስ እንዲያጠምቃቸው ፈቅደው ነበርና” ወይም “ዮሐንስ አጥምቋቸው ነበርና” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“እግዚአብሔር እንዲያደርጉ የፈለገባቸውን አልተቀበሉም” ወይም “እግዚአብሔር የነገራቸውን ላለመታዘዝ መረጡ”
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ዮሐንስ እንዲያጠምቃቸው አልፈቀዱም ነበር” ወይም “የዮሐንስን ጥምቀት አልተቀበሉም” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ ስለ አጥማቂው ዮሐንስ ለሕዝቡ መናገሩን ይቀጥላል።
ኢየሱስ ንጽጽርን ለማስተዋወቅ እነዚህን ጥያቄዎች ይጠይቃል። እነዚህ እንደ መግለጫ ሊጻፉ ይችላሉ። አ.ት፡ “ይህንን ትውልድ የማነጻጽረውና ምን እንደሚመስሉ የምገልጸው እንደዚህ ነው” (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
እነዚህ ንጽጽር መሆኑ የተነገረባቸው ሁለት መንገዶች ናቸው።
ኢየሱስ በሚናገርበት ጊዜ በሕይወት የነበሩ ሰዎች ማለት ነው።
እነዚህ ቃላት የኢየሱስ ንጽጽር ጅማሬዎች ናቸው። ሕዝቡ፣ በሌሎች ልጆች ሥራ በፍጹም እንደማይረኩ ልጆች መሆናቸውን ኢየሱስ ይናገራል። (ተነጻጻሪ የሚለውን ተመልከት)
ሰዎች ሸቀጦቻቸውን ለመሸጥ የሚመጡበት ሰፊ ሜዳ
“እናንተ ግን ከሙዚቃው ጋር አልዘፈናችሁም”
“እናንተ ግን ከእኛ ጋር አላለቀሳችሁም”
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች፣ 1) “አዘውትሮ መጾም” ወይም 2) “የተለመደውን ምግብ አለመብላት” የሚሉት ናቸው።
ኢየሱስ የሚጠቅሰው ሕዝቡ ስለ ዮሐንስ ይናገሩ የነበሩትን ነው። ይህ ያለ ቀጥተኛ ትዕምርተ ጥቅስ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “አጋንንት አለበት ትላላችሁ” ወይም “አጋንንት እንዳለበት አድርጋችሁ ትከሱታላችሁ” (ግልጽ የሆነና ያልሆነ ትዕምርተ ጥቅስ ተመልከት)
ኢየሱስ ወደ ራሱ ማመልከቱን ሕዝቡ እንደሚረዱ ጠብቋል። አ.ት፡ “የሰው ልጅ የሆንኩ እኔ” (አንደኛ፣ ሁለተኛ ወይም ሦስተኛ መደብ የሚለውን ተመልከት)
ይህ ቀጥተኛ እንዳልሆነ ትዕምርተ ጥቅስ ተደርጎ ሊተረጎም ይችላል። አ.ት፡ “እርሱ ከኃጢአተኞች … ሆዳምና ሰካራም ሰው ነው ትላላችሁ” ወይም “ከኃጢአተኞች… በመብላቱና ብዙ በመጠጣቱ ምክንያት ትከሱታላችሁ” (ግልጽ የሆነና ያልሆነ ትዕምርተ ጥቅስ ተመልከት)
“የሰው ልጅ” የሚለውን “የሰው ልጅ የሆንኩ እኔ” ብለህ ተርጉመህ ከሆነ አንደኛ መደብን በመጠቀም ቀጥተኛ እንዳልሆነ መግለጫ አድርገህ መናገር ትችላለህ። አ.ት፡ “ከኃጢአተኞች… ሆዳምና ሰካራም እንደሆንኩ ትናገራላችሁ” (ቀጥተኛ የሆነና ያልሆነ ትዕምርተ ጥቅስ እና አንደኛ፣ ሁለተኛ ወይም ሦስተኛ መደብ የሚለውን ተመልከት)
“ንፉግ በላተኛ ነው” ወይም “ባለማቋረጥ ብዙ ምግብ ይበላል”
“ጠጪ” ወይም “ባለማቋረጥ የሚያሰክር መጠጥ አብዝቶ ይጠጣል”
ይህ ምናልባት ጥበበኞች ሰዎች ሕዝቡ ኢየሱስንና ዮሐንስን መቃወም እንዳልነበረባቸው የሚገነዘቡ መሆናቸውን ለማስተማር ኢየሱስ ከሁኔታው ጋር ያዛመደው ምሳሌአዊ አነጋገር ይሆናል።
ፈሪሳዊው በቤቱ እንዲበላ ኢየሱስን ይጋብዘዋል።
አንድ ፈሪሳዊ በቤቱ ምግብ እንዲበላ ኢየሱስን ይጋብዘዋል።
ይህ የታሪኩ አዲስ ክፍል መጀመሩን፣ በታሪኩ ውስጥም ፈሪሳዊውን ማስተዋወቁን ያመለክታል። (አዲስ ሁነትን ማስተዋወቅ፣ አዲስና ነባር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
“ገበታው ጋ ለመብላት ተቀመጠ”። ወንዶች በምግቡ ዙሪያ በምቾት ጋደም ማለታቸውና እንዲህ ያለውን እራት ዘና ብለው መብላታቸው የተለመደ ነበር።
“እነሆ” የሚለው ቃል በታሪኩ ውስጥ ስላለ አዲስ ሰው ያነቃናል። የአንተ ቋንቋ ይህንን የሚገልጽበት መንገድ ይኖረው ይሆናል። (አዲስ ሁነትን ማስተዋወቅ፣ አዲስና ነባር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
“በኃጢአት የተሞላ የኑሮ ዘይቤ የነበራት” ወይም “በኃጢአት ስለመኗሯ መጥፎ ምስክርነት የነበራት”። ምናልባት በሴተኛ አዳሪነት ትተዳደር የነበረች ሴት ትሆን ይሆናል።
“ከለስላሳ ድንጋይ የተሠራ ብልቃጥ”። አልባስጥሮስ ለስላሳና ነጭ የሆነ ድንጋይ ነው። ሰዎች ዋጋቸው ውድ የሆኑ ነገሮችን በአልባስጥሮስ ብልቃጦች ውስጥ ያስቀምጡ ነበር።
“ከሽቶ ጋር የተዋሐደ”። ዘይቱ ጥሩ መዓዛ እንዲኖረው ያስደረገው አንዳች ነገር ነበረበት። ሰዎች ጥሩ መዓዛ እንዲኖራቸው በራሳቸው ላይ ያስነኩት ወይም በልብሳቸው ላይ ይረጩት ነበር።
“በጸጉሯ”
“ሽቶ ቀባቻቸው”
“ለራሱ እንዲህ አለ”
ኢየሱስ ኃጢአተኛ የሆነች ሴት እንድትነካው በመፍቀዱ ነቢይ እንዳልሆነ ፈሪሳዊው አሰበ። አ.ት፡ “ኢየሱስ ነቢይ አለመሆኑ ግልጽ ነው፣ ምክንያቱም ነቢይ ቢሆን ኖሮ እየነካችው ያለችው ሴት ኃጢአተኛ መሆኗን ያውቅ ነበር”
ስምዖን፣ ኃጢአተኛ የሆነ ሰው እርሱን እንዲነካው አንድ ነቢይ በፍጹም መፍቀድ አይኖርበትም ብሎ ገምቷል። ይህ የግምቱ አካል በግልጽ መነገር ይችላል። አ.ት፡ “እርሷ ኃጢአተኛ ናት፣ እርሱ እንድትነካው መፍቀድ አይኖርበትም”
ይህ ኢየሱስን ወደ ቤቱ የጋበዘው ፈሪሳዊ ስም ነበር። ይህ ስምዖን ጴጥሮስ አይደለም።
ኢየሱስ ለፈሪሳዊው ስምዖን ለሚነግረው ነገር አጽንዖት ለመስጠት ታሪክ ይነግረዋል። (ምሳሌዎች የሚለውን ተመልከት)
“ሁለት ሰዎች ከአንድ የገንዘብ አበዳሪ ገንዘብ ተበደሩት”
“የ ‘500 ቀናት’ ደሞዝ”። “ዲናር” የዲናሪየስ ብዙ ቁጥር ነው። “ዲናሪየስ” ከብር ማዕድን የሚሠራ ሳንቲም ነበር። (መጽሐፍ ቅዱሳዊው ገንዘብ እና ቁጥሮች የሚለውን ተመልከት)
“ሌላኛው ተበዳሪ ሃምሳ ዲናር ተበደረ” ወይም “የ ’50 ቀን’ ደሞዝ”
ኢየሱስ የስምዖንን ደካማ እንግዳ አቀባበል ከሴቲቱ ተግባር ጋር ማነጻጸሩን ይቀጥላል።
“ከዚያም ሴቲቱን እንዲህ አላት”
“ይቅር ተብለሻል”። ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ኃጢአትሽን ይቅር ብዬሻለሁ” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“በማዕዱ ዙሪያ በአንድነት ጋደም ብለው” ወይም “በአንድነት ሲመገቡ”
የሃይማኖት መሪዎች ኃጢአትን ይቅር ማለት የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ መሆኑን ያውቃሉ፣ ኢየሱስ እግዚአብሔር እንደነበረ ግን አላመኑም። ይህ ጥያቄ ምናልባት ወቀሳ እንዲሆን ሳይታሰብ አልቀረም። አ.ት፡ “ይህ ሰው ማን እንደሆነ ነው የሚያስበው? ኃጢአትን ይቅር ማለት የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ ነው!” ወይም “ይህ ሰው እርሱ ብቻ ኃጢአትን ይቅር ለማለት የሚችለውን እግዚአብሔርን ለመሆን የሚሞክረው ለምንድነው?”
“በእምነትሽ ምክንያት ድነሻል”። የነገር ስም የሆነው “እምነት” እንደ ድርጊት ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ስላመንሽ ድነሻል” (የነገር ስም የሚለውን ተመልከት)
1 ከዚያ በኋላ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን መንግሥት የምሥራች ወንጌል እየሰበከና እያወጀ ወደ ልዩ ልዩ ከተሞችና መደሮች መጓዝ ጀመረ። በጒዞውም ወቅት ዐሥራ ሁለቱ፣ 2 እንዲሁም ከርኩሳን መናፍስትና ከሕመማቸው የተፈወሱ አንዳንድ ሴቶች ዐብረውት ሄዱ፤ እነርሱም ሰባት አጋንንት የወጡላት መግደላዊት ማርያም፣ 3 እንደ የሄሮድስ ቤተ መንግሥት አዛዥ የነበረው የኩዛ ሚስት የነበረችው ዮሐና፣ ሶስና ሌሎችም ብዙ ሴቶች ነበሩ፤ እነዚህ ኢየሱስንና ደቀ መዛሙርቱን በገንዘባቸው ያገለግሉ ነበር። 4 ከብዙ የተለያዩ ከተሞች የመጡትን ጨምሮ ብዙ ሕዝብ በተሰበሰቡ ጊዜ፣ በምሳሌ ተጠቅሞ እንዲህ ብሎ ነገራቸው፤ 5 “አንድ ዘሪ ዘሩን ሊዘራ ወጣ።እንደ ዘራም አንዳንዱ ዘር በመንገድ ዳር ወደቀና ተረገጠ፣ የሰማይ ወፎችም መጥተው በሉት። 6 ሌላው ዘርም በጭንጫ መሬት ላይ ወደቀ፤ በበቀለም ጊዜ እርጥብ አፈር ስላልነበረው ወዲያው ደረቀ። 7 ሌላውም ዘር በእሾህ መካከል ወደቀ እሾሁም ከዘሩ ጋር ዐብሮት አደገና አነቀው። 8 ከዘሩ አንዳንዱ ግን በመልካም ዐፈር ላይ ወደቀ መቶ እጥፍ ፍሬም አፈራ።" ኢየሱስ ይህንን ከተናገረ በኋላ ጮኽ ብሎ፣ "ጆሮ ያለው ይስማ” አለ። 9 ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ ይህ ምሳሌ ምን ማለት እንደ ሆነ ጠየቁት፤ 10 ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፤ "ለእናንተ የእግዚአብሔርን መንግሥት ምሥጢር የማወቅ ዕድል ተሰጥቷችኋል፣ ለተቀሩት ሕዝብ ግን 'እያዩ ስለማያዩ፣ እየሰሙም ስለማያስተውሉ' የሚማሩት በምሳሌ ነው። 11 ትርጕም እንደዚህ ነው፣ ዘሩ የእግዚአብሔር ቃል ነው። 12 በመንገድ ዳር የወደቁት ሰምተው እንዳይድኑ ዲያብሎስ መጥቶ የሰሙትን ቃል ከልባቸው የሚወሰድባቸው ናቸው። 13 በድንጋይ መካከል የወደቁትም ቃሉን በሰሙ ጊዜ በደስታ የሚቀበሉትና መስማት እንጂ፣ በቃሉ ሥር ስላልሰደዱ ለጊዜው አምነው ፈተና በመጣባቸው ጊዜ፣ እምነታቸውን የሚክዱ ናቸው። 14 በእሾኽ መካከል የወደቀው ዘር ቃሉን የሰሙ ሰዎች ሲሆኑ፣ በኑሮ ሂደታቸው ወቅት በምድራዊ ሕይወት ዐሳብና በባለጠግነት ምቾት የሚታነቁ በመሆናቸው ፍሬ ወደ ማፍራት የማይመጡ ናቸው። 15 ነገር ግን በመልካሙ ዐፈር ላይ የወደቁት በመልካምና በቅን ልብ ካደመጡ በኋላ ቃሉን አጥብቀው የሚይዙ በመጽናት ፍሬ የሚያፈሩ ናቸው። 16 እንግዲህ፣ አንድ ሰው መብራት ካበራ በኋላ ጎድጓዳ ነገር ውስጥ ወይም ከአልጋ ሥር አያደርገውም። ከዚያ ይልቅ ሁሉም ሰው ብርሃኑን ማየት ይችል ዘንድ ከፍ ባለ ስፍራ ላይ ያስቀምጠዋል። 17 ምክንያቱም የሚታወቅ እንጂ የሚደበቅ፣ ታውቆ ወደ ብርሃን የሚወጣ እንጂ ምሥጢር የሚሆን ነገር የለም። 18 ስለዚህ እንዴት እንደምትሰሙ ተጠንቀቁ፣ ምክንያቱም ላለው ሁሉ የበለጠ ይሰጠዋል፣ ከሌለው ደግሞ እንዳለው የሚመስለው እንኳ ይወሰድበታል።" 19 ከዚያም የኢየሱስ እናትና ወንድሞቹ ወደ እርሱ መጡ፣ ነገር ግን ከሕዝቡ ብዛት የተነሣ ወደ እርሱ መቅረብ አልቻሉም። 20 ስለሆነም፣ ‘እናትህና ወንድሞችህ ሊያነጋግሩህ ፈልገው እየጠበቁህ ናቸው’ የሚል መልእክት አመጡለት። 21 ነገር ግን ኢየሱስ መልሶ፣ “እናቴና ወንድሞቼ የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተው የሚያደርጉት ናቸው” አላቸው። 22 ከዕለታት አንድ ቀን ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ በጀልባ ሲሳፈሩ ኢየሱስ፣ "ሐይቁ ማዶ እንሻገር" አላቸው። ከዚያም እነርሱ መቅዘፍ ጀመሩ። 23 ነገር ግን እየቀዘፉ ሳሉ ኢየሱስ እንቅልፍ ወሰደውና በታላቅ ነፋስ የታጀበ ማዕበል በሐይቁ ላይ ስለተነሣ ጀልባቸው ውስጥ ውሃ መግባት ጀመረ'፤ታላቅ አደጋም በፊታቸው ተደቀነ። 24 ከዚያም የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ መጥተው፣ "መምህር ሆይ፣ መምህር ሆይ፣ መሞታችን ነው" በማለት ቀሰቀሱት። እርሱም ከእንቅልፉ ነቅቶ ነፋሱንና የሚናወጠውን ማዕበል ገሰጸ ጸጥ አደረጋቸው። 25 ከዚያም ኢየሱስ፣ “እምነታችሁ የት አለ?” አላቸው። ፍርሃት ይዟቸውና በጣም ተደንቀው እርስ በርሳቸው፣ “ነፋሳትንና ባሕርን የሚያዝ እነርሱም የሚታዘዙለት ይህ ማን ነው?" ተባባሉ። 26 ከገሊላ ባሕር በስተ ማዶ በሌላው አንጻር ወደ ነበረው ወደ ጌርጌሴኖን ክልል ደረሱ። 27 ኢየሱስ ከጀልባው ወርዶ ወደ ምድር በተሻገረ ጊዜ፣ አጋንንት የነበሩበት አንድ ሰው አገኘው። ይህ ሰው ለረጅም ጊዜ ልብስ ለብሶ አያውቅም፤ በመቃብር ስፍራ እንጂ፣ በቤትም ውስጥ አልኖረም። 28 ኢየሱስን ባየው ጊዜ ጮኾ በፊቱ ተደፋ፤ በታላቅም ድምፅ፣ “የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ሆይ! እኔ ከአንተ ምን ጉዳይ አለኝ? እንዳታሠቃየኝ እለምንሃለሁ” አለው። 29 እንደዚህም ያለበት ምክንያት ብዙ ጊዜ ይይዘውና ያሠቃየው የነበረውን ርኩስ መንፈስ ከእርሱ እንዲወጣ ኢየሱስ አዞት ስለነበር ነው። ምንም እንኳ በብረት ሰንሰለት የታሰረና በቁጥጥር ስር እንዲውል የተደረገ ቢሆንም፣ እስራቱን ይበጥስ፣ በአጋንንቱም ግፊት ወደ በረሐ እየሄደ ይንከራተት ነበር። 30 ከዚያም ጊዜም ኢየሱስ፣ “ስምህ ማን ነው?” ብሎ ጠየቀው፤ እርሱም ብዙ አጋንንት ገብተውበት ነበርና ስሜ፣ "ጭፍራ" ነው ብሎ መለሰ። 31 በውስጡ የነበሩት አጋንንት ወደ ጥልቁ እንዲሄዱ እንዳያዛቸው መለመናቸውን ቀጠሉ። 32 በዚያም ብዙ ዐሳማዎች በኮረብታው ላይ ለግጦሽ ተሰማርተው ነበር፤ አጋንንቱም ወደ ዐሳማዎቹ ይገቡ ዘንድ እንዲፈቅድላቸው ለመኑት። ኢየሱስ የለመኑትን እንዲያደርጉ ፈቀደላቸው። 33 ስለዚህ አጋንንቱ ከሰውዬው ወጥተው ዐሳማዎቹ ውስጥ ገቡ። ዐሣማዎቹን ከኮረብታው ተጣድፈው ቁልቁል ወረዱ፣ ወደ ሐይቁም ውስጥ ገብተው ሰጠሙ። 34 ዐሳማዎቹን ሲያሰማሩ የነበሩት ሰዎች ይህን በተመለከቱ ጊዜ ወደ ከተማውና ወደ ገጠሮች ሁሉ ሸሽተው በመሄድ ዜናውን አሠራጩ። 35 ስለዚህ ይህንን የሰሙት ሰዎች የሆነውን ለማየት ወጡ፤ ወደ ኢየሱስም በመጡ ጊዜ አጋንንት የወጡለትን ሰው አገኙት። ሰውዬውም ልብስ ለብሶ ወደ አእምሮውም ተመልሶ በኢየሱስ እግር ሥር ተቀምጦ ሲያዩት፣ ፍርሃት ያዛቸው። 36 ከዚያም የሆነውን ነገር ያዩ ሰዎች በአጋንንት ቁጥጥር ሥር የነበረው ሰው እንዴት እንደ ዳነ ለሌሎች ተናገሩ። 37 የጌርጌሴኖን ክልልና የዚያ አካባቢ ሰዎች ሁሉ ታላቅ ፍርሃት ይዟቸው ስለ ነበረ፣ ኢየሱስ ከእነርሱ እንዲሄድ ለመኑት፤ እርሱም ከዚያ ስፍራ ወደ መጣበት ለመመለስ ወደ ጀልባይቱ ገባ። 38 አጋንንት የወጡለት ሰው ዐብሮት ለመሄድ ኢየሱስን ለመነው። 39 ኢየሱስ ግን፣ “ወደ ቤተ ሰብህ ተመልሰህ እግዚአብሔር ያደረገልህን ታላላቅ ነገሮች ሁሉ ተርክላቸው” ብሎ አሰናበተው። ሰውየውም ኢየሱስ ያደረገለትን ታላላቅ ነገሮች በከተማው ሁሉ እየመሰከረ ጒዞውን ቀጠለ። 40 ሁሉም ይጠብቁት ነበርና ኢየሱስ ሲመለስ ሕዝቡ ተቀበሉት። 41 እነሆም ከምኲራብ መሪዎች አንዱ ኢያኢሮስ የተባለ ሰው መጣ፤ እርሱም በኢየሱስ እግር ላይ ወድቆ ወደ ቤቱ ይመጣ ዘንድ ለመነው። 42 ወደ ቤቱ እንዲመጣ የፈለገው ዐሥራ ሁለት ዓመት የሆናት እንድያ ልጁ በሞት አፋፍ ላይ ስለነበርች ነው። ነገር ግን ወደዚያ እየሄደ በነበረበት ጊዜ፣ ብዙ ሕዝብ በመጨናነቅ ይጋፉት ነበር። 43 በዚያም ለዐሥራ ሁለት ዓመት ደም ሲፈሳት የነበረች፣ ገንዘቧን ሁሉ ለሐኪሞች ብትከፍልም አንዳቸውም ያልፈወሷት አንዲት ሴት ነበረች። 44 እርሷ ከኢየሱስ በስተኋላ መጥታ የልብሱን ጫፍ ነካች፤ የፈሳት የነበረው ደምም ወዲያው ቆመ። 45 ኢየሱስ፣ “የነካኝ ማን ነው?” አለ። ሁሉም አልነካንህም ብለው በተናገሩ ጊዜ፣ ጴጥሮስ፣ “ጌታ ሆይ፣ ሕዝቡ እኮ እየገፋፉህና እያጨናነቁህ ነው” አለው። 46 ኢየሱስ ግን፣ “ከእኔ ኅይል እንደ ወጣ ዐውቄአለሁና አንድ ሰው ነክቶኛል” አለ። 47 ሴቲቱ ያደረገችውን መደበቅ እንዳልቻለች ባስተዋለች ጊዜ፣ ሴቲቱ እየተንቀጠቀጠች መጣችና በኢየሱስ እግር ሥር ወድቃ በሰዎች ሁሉ ፊት እርሱን ለምን እንደነካችውና እንዴት ወዲያው እንደ ተፈወሰች ተናገረች። ከዚያም ኢየሱስ ሴቲቱን፥ 48 “ልጄ ሆይ እምነትሽ አድኖሻል በሰላም ሂጂ” አላት። 49 እርሱም ገና እየተናገረ ሳለ ከምኲራብ አለቃው ቤት አንድ ሰው መጥቶ፣ “ልጅህ ሞታለች። መምህሩን አታድክመው” አለ። 50 ኢየሱስ ግን ይህን በሰማ ጊዜ፣ “እመን ብቻ እንጂ አትፍራ፣ እርሷም ትድናለች” አለው። 51 ከዚያም እርሱ ወደዚያ ቤት በመጣ ጊዜ፣ ከጴጥሮስ፣ ከዮሐንስ፣ ከያዕቆብ እንዲሁም ከልጅቱ አባትና ከእናትዋ በስተቀር ማንም ዐብሮት እንዲገባ አልፈቀደም። 52 በዚያ ስፍራ የነበሩት ሰዎች ሁሉ ያለቅሱ ዋይ ዋይም ይሉ ነበር። እርሱ ግን፣ “አታልቅሱ ልጅትዋ ተኝታለች እንጂ አልሞተችም” አለ። 53 እነርሱ ግን መሞቷን ዐውቀው ስለ ነበር፣ በንቀት ሳቁበት። 54 እርሱ ግን የልጅቱን እጅ ይዞ፣ “አንቺ ልጅ ተነሽ” አላት። 55 ነፍስዋም ተመለሰች፣ ወዲያውኑም ብድግ አለች። እርሱም የምትበላው እንዲሰጧት አዘዘ። 56 ወላጆቿም ተደነቁ፤ እርሱ ግን ስለሆነው ነገር ለማንም እንዳይናገሩ አዘዛቸው።
እነዚህ ቁጥሮች ኢየሱስ በጉዞ ላይ እያለ ስለ ሰበከው ስብከት ዳራዊ መረጃ ይሰጣሉ።
ይህ ሐረግ እዚህ ጋ ጥቅም ላይ የዋለው የታሪኩን አዲስ ክፍል ለማመልከት ነው። (አዲስ ሁነትን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ኢየሱስ ከክፉ መናፍስት ነጻ ያወጣቸውና ከበሽታ ፈውሷቸው የነበሩ” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ሦስቱ ሴቶች ተጠቅሰዋል፡ ማርያም፣ ዮሐና፣ እና ሶስና (ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ሰዎች መግደላዊት ብለው የሚጠሯት ማርያም … ኢየሱስ ሰባት አጋንንት አስወጥቶላት የነበረች” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ዮሐና የኩዛ ሚስት ስትሆን ኩዛ ደግሞ የሔሮድስ ቤት ኃላፊ ነበር። “የሔሮድስ ቤት ኃላፊ የሆነው የኩዛ ሚስት ዮሐና” (ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)
“ኢየሱስንና ደቀ መዛሙርቱን በገንዘብ ይደግፉ ነበር”
ኢየሱስ ስለ መሬቱ ምሳሌ ለሕዝቡ ይነግራቸዋል። የምሳሌውን ትርጉም ለደቀ መዛሙርቱ ያብራራላቸዋል። (ምሳሌዎች የሚለውን ተመልከት)
“ወደ ኢየሱስ ይመጡ ነበር”
“አንድ ገበሬ እርሻ ላይ ዘር ለመዝራት ሄደ” ወይም “አንድ ገበሬ ጥቂት ዘር እርሻ ላይ ለመዝራት ሄደ”
“ከዘሩ ጥቂቱ ወደቀ” ወይም “ጥቂት ዘሮች ወደቁ”
x
ኢየሱስ ለሕዝቡ ምሳሌዎቹን መናገሩን ያበቃል።
የገበሬው ዘር መብቀል እንዳይችል ማዕድናቱን ሁሉ፣ ውሃውንና የፀሐይ ብርሃኑን የእሾኹ ተክል ወሰደው።
“ምርት አበቀለ” ወይም “ብዙ ዘር አበቀለ”
ይህ ማለት ከተዘራው ዘር ከመቶ ዕጥፍ በላይ የሆነ ማለት ነው።
በአንዳንድ ቋንቋዎች በሁለተኛ መደብ መጠቀም በይበልጥ የተለመደ ይሆናል። “የሚሰማ ጆሮ ያላችሁ እናንተ፣ ስሙ” (አንደኛ፣ ሁለተኛ፣ ወይም ሦስተኛ መደብ የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ መናገር ይጀምራል።
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “የ… እውቀት እግዚአብሔር ሰጥቷችኋል” ወይም “የእግዚአብሔርን … መረዳት እንድትችሉ እግዚአብሔር አድርጓችኋል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
እነዚህ የተደበቁ እውነቶች ናቸው፣ አሁን ግን ኢየሱስ ገልጧቸዋል።
“ለሌሎች ሰዎች”። ይህ የሚያመለክተው የኢየሱስን ትምህርት ያልተቀበሉትንና እርሱን ያልተከተሉትን ሰዎች ነው።
“ቢያዩም አይገነዘቡም”። ይህ ከነቢዩ ከኢሳይያስ የተጠቀሰ ጥቅስ ነው። አንዳንድ ቋንቋዎች የግሱን ባለቤት ማስታወቅ ያስፈልጋቸው ይሆናል። አ.ት፡ “ነገሮችን ቢያዩም አያስተውሏቸውም” ወይም “የሚሆኑትን ነገሮች ቢያዩም ምን ትርጉም እንዳላቸው አያስተውሉም”
“ቢሰሙም አያስተውሉም”። ይህ ከነቢዩ ከኢሳይያስ የተጠቀሰ ጥቅስ ነው። አንዳንድ ቋንቋዎች የግሱን ባለቤት ማስታወቅ ያስፈልጋቸው ይሆናል። አ.ት፡ “ትምህርትን ቢሰሙም እውነቱን አያስተውሉም”
ኢየሱስ ስለ መሬት የተናገረውን ምሳሌ ትርጉም ለደቀ መዛሙርቱ ማብራራት ይጀምራል።
“ዘሩ ከእግዚአብሔር የመጣው መልዕክት ነው”
“በመንገድ ዳር የወደቀው ዘር እርሱ”። ኢየሱስ ከሰዎች ጋር በማገናኘት ዘሩ ምን እንደሚሆን ይናገራል። አ.ት፡ “በመንገድ ዳር የወደቀው ዘር ሰዎችን ይወክላል” ወይም “በምሳሌው ውስጥ በመንገድ ዳር የወደቀው ዘር ሰዎችን ይወክላል” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ዘሩ ሰው የሆነ ይመስል ኢየሱስ ስለ ሰዎች አንድ ነገር ለማሳየት በመፈለግ ስለ ዘር ይናገራል። አ.ት፡ “ሰዎች ላይ የሚሆነውን ያሳያል” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ “ልባቸው” የሰዎችን አዕምሮ ወይም ውስጣዊ ማንነት የሚያመለክት ፈሊጣዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “ዲያብሎስ ይመጣና የእግዚአብሔርን መልዕክት ከውስጠኛው አስተሳሰባቸው ይወስደዋል” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ይህ ዘሩን የሚለቅም ወፍ በምሳሌው ውስጥ ዘይቤአዊ አነጋገር ነው። ይህንን ስዕል ማሳየት የሚችልን ቃል በቋንቋህ ለመጠቀም ሞክር። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ይህ የዲያብሎስ ዓላማ እስከ ሆነ ድረስ እንደሚከተለው ሊተረጎም ይችላል። አ.ት፡ “ዲያብሎስ፣ ‘አምነው መዳን የለባቸውም’ ብሎ ስለሚያስብ” ወይም “እንዳያምኑና እግዚአብሔር እንዳያድናቸው” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“በዐለታማ አፈር ላይ የወደቁት እነዚያ”። ኢየሱስ ከሰዎች ጋር በማገናኘት ዘሩ ምን እንደሚሆን ይናገራል። አ.ት፡ “በዐለታማው መሬት ላይ የወደቀው ዘር ሰዎችን ይወክላል” ወይም “በምሳሌው ውስጥ በዐለታማው መሬት ላይ የወደቀው ዘር ሰዎችን ይወክላል” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“ዐለታማው መሬት”
“መከራ በሚገጥማቸው ጊዜ”
የአነጋገር ዘይቤው ትርጉም “ማመናቸውን ያቆማሉ” ወይም “ኢየሱስን መከተላቸውን ያቆማሉ” የሚል ነው። (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)
“በእሾህ መካከል የወደቀው ዘር ሰዎችን ይወክላል” ወይም “በምሳሌው ውስጥ በእሾህ መካከል የወደቀው ዘር ሰዎችን ይወካላል” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “የዚህ ሕይወት ፍላጎት፣ ባለጸግነትና ደስታ ያንቃቸዋል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ሰዎች የሚጨነቁላቸው ነገሮች
“በዚህ ሕይወት ሰዎች የሚደሰቱባቸው ነገሮች”
ይህ ዘይቤአዊ አነጋገር የሚያመለክተው አረሙ የቡቃያውን ብርሃንና ማዕድናት በማቋረጥ ከዕድገት እንደሚገታቸው ነው። አ.ት፡ “አረም መልካሙን ቡቃያ ከማደግ እንደሚገታው የዚህ ሕይወት ፍላጎት፣ ብልጽግና እና ደስታም እነዚህን ሰዎች ፍሬአማ ከመሆን ይገታቸዋል” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“የደረሰ ፍሬ አያፈሩም”። ብስል ፍሬ የመልካም ሥራ ዘይቤአዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “የበሰለ ፍሬ እንደማያፈራ ተክል እነርሱም መልካም ሥራ አይሠሩም” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“በመልካም መሬት ላይ የወደቀው ዘር ሰዎችን ይወክላል” ወይም “በምሳሌው ውስጥ በመልካም መሬት ላይ የወደቀው ዘር ሰዎችን ይወክላል” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“መልዕክቱን ሰምተው”
እዚህ ጋ “ልብ” የሰውን አሳብ ወይም ፍላጎት የሚያመለክት ፈሊጣዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “በመልካምና ቅን ምኞት”
“በትዕግስት በመጽናት ፍሬ የሚሰጡ” ወይም “በማያቋርጥ ጥረት ፍሬ የሚሰጡ”። ፍሬ የመልካም ሥራ ዘይቤአዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “መልካም ፍሬ እንደሚያፈራ ጤነኛ ተክል በመጽናት መልካም ሥራን ይሠራሉ” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ በሌላ ምሳሌ መናገሩን ይቀጥላል፣ ከዚያም ቤተሰቦቹ በእርሱ ሥራ ውስጥ ስለሚኖራቸው ሚና አጽንዖት በመስጠት ለደቀ መዛሙርቱ መናገሩን ያበቃል።
ይህ ሌላ ምሳሌ የመጀመሩ ምልክት ነው። (ምሳሌዎች የሚለውን ተመልከት)
ይህ ድርብ አሉታ እንደ አዎንታዊ ንግግር ሊጻፍ ይችላል። አ.ት፡ “የተደበቀ ነገር ሁሉ እንዲታወቅ ይደረጋል” (ድርብ አሉታ የሚለውን ተመልከት)
ይህ ድርብ አሉታ እንደ አዎንታዊ ንግግር ሊጻፍ ይችላል። አ.ት፡ “ምስጢር የሆነው ነገር ሁሉ ወደ ብርሃን ይመጣል፣ እንዲታወቅም ይደረጋል” (ድርብ አሉታ የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ እየተናገረ ያለው ስለ ማስተዋልና ስለ ማመን መሆኑን ከዐውዱ በግልጽ መረዳት ይቻላል። ይህ በግልጽ ሊነገርና ወደ አድራጊ ድምፅ ሊቀየር ይችላል። አ.ት፡ “ማስተዋል ላለው ለማንም ቢሆን የበለጠ ማስተዋል ይሰጠዋል” ወይም “እግዚአብሔር እውነትን የሚያምኑትን እነዚያን የበለጠ እንዲያስተውሉ ደግሞ ያስችላቸዋል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ እየተናገረ ያለው ስለ ማስተዋልና ስለ ማመን መሆኑን ከዐውዱ በግልጽ መረዳት ይቻላል። ይህ በግልጽ ሊነገርና ወደ አድራጊ ድምፅ ሊቀየር ይችላል። አ.ት፡ “ማንም ማስተዋል የሌለው ሰው አለኝ የሚለውን ማስተዋል እንኳን ያጣዋል” ወይም “ነገር ግን እውነትን የማያምኑትን እነዚያን ተረድተነዋል የሚሉትን ጥቂቱን ማስተዋል እንኳን እንዳያስተውሉ ያደርጋቸዋል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
እነዚህ ከኢየሱስ በኋላ ከማርያምና ከዮሴፍ የተወለዱ፣ የኢየሱስ ታናናሽ ወንድሞች የነበሩ ሌሎች ወንዶች ልጆች ናቸው። የኢየሱስ አባት እግዚአብሔር፣ የእነርሱ አባት ደግሞ ዮሴፍ እስከ ሆነ ድረስ በሙያዊ አገላለጽ በእናቱ በኩል ወንድሞቹ ናቸው። ይህ ዝርዝር በአግባቡ አልተተረጎመም።
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ሰዎች ነገሩት” ወይም “አንድ ሰው ነገረው” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“ሊያዩህ ይፈልጋሉ”
ይህ ዘይቤአዊ አነጋገር የሚገልጸው ከኢየሱስ ለመስማት የሚመጡ ሰዎች ለእርሱ የቤተሰቡን ያህል አስፈላጊዎች መሆናቸውን ነው። አ.ት፡ “የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተው የሚታዘዙት እነርሱ ለእኔ እንደ እናቴና ወንድሞቼ ናቸው” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“እግዚአብሔር የተናገረው መልዕክት”
ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ የጌንሳሬጥን ሐይቅ ለመሻገር በጀልባ ይጠቀማሉ። ደቀ መዛሙርቱ በሚነሣው ማዕበል አማካይነት ስለ ኢየሱስ ኃይል በይበልጥ ይማራሉ።
ይህ የጌንሳሬጥ ሐይቅ ነው፣ የገሊላ ባህር ተብሎም ይጠራል።
የዚህ አገላለጽ ትርጉም፣ ሐይቁን ለመሻገር በጀልባቸው መጓዝ ጀመሩ የሚል ነው።
“ሲሄዱ ሳሉ”
“ማንቀላፋት ጀመረ”
“በጣም ታላቅ የሆነ ዐውሎ ንፋስ ጀመረ” ወይም “በጣም ኃይለኛ ንፋስ በድንገት መንፈስ ጀመረ”
ኃይለኛው ንፋስ ብርቱ ሞገድ በማስነሣት የጀልባዋን ጎንና ጎን በውሃ እንዲገፋት አደረገ። ይህ በግልጽ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ንፋሱ ከፍተኛ ሞገድ በመፍጠር ጀልባቸውን በውሃ መሙላት ጀመረ”
በቀጥታ ተናገረው
“አስፈሪው ሞገድ”
“ንፋሱና ማዕበሉ ቆመ” ወይም “ጸጥ አሉ”
ኢየሱስ ለእነርሱ ስለሚያደርግላቸው ጥበቃ ስላልታመኑት በእርጋታ ይገስጻቸዋል። ይህ እንደ መግለጫ ሊጻፍ ይችላል። አ.ት፡ “እምነት ሊኖራችሁ ይገባል!” ወይም “ልትታመኑብኝ ይገባል!” (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
“… የሚታዘዙለት ይህ ምን ዓይነት ሰው ነው?” ይህ ጥያቄ ኢየሱስ ማዕበሉን መቆጣጠር መቻሉ የፈጠረባቸውን ድንጋጤና ግራ መጋባት ይገልጻል። (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
ይህ ወደ ሁለት ዐረፍተ ነገር ሊቀየር ይችላል። “እንግዲህ ይህ ማነው? እርሱ ያዛቸዋል … ይታዘዙታል!”
ኢየሱስ ከአንድ ሰው ብዙ አጋንንት ወዳወጣበት ወደ ጌርጌሴኖን ባህር ዳርቻ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር መጣ።
ጌርጌሶናዊያን ጌርጌሴኖን የምትባል ከተማ ሰዎች ነበሩ። (ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)
“ከገሊላ ሐይቅ በወዲያኛው ማዶ”
“አንድ ሰው ከጌርጌሴኖን ከተማ”
ሰውየው አጋንንት ነበሩበት፤ አጋንንት የኖሩት በከተማው ላይ አልነበረም። አ.ት፡ “አንድ ሰው ከከተማ. . . ይህ ሰው አጋንንት ነበሩበት”
“አጋንንት ተቆጣጥረውት የነበረ” ወይም “አጋንንት የተቆጣጠሩት”
ይህ አጋንንት ስለነበሩበት ሰው ዳራዊ መረጃ ነው። (ዳራዊ መረጃ የሚለውን ተመልከት)
“ልብስ አይለብስም ነበር”
ይህ ሰዎች ሬሳ የሚያኖሩበት፣ ምናልባት አንድ ሰው ለመጠለያነት የሚጠቀምበት ዋሻ ወይም አነስተኛ ግንብ ሊሆን ይችላል።
“አጋንንት የነበሩበት ሰው ኢየሱስን ባየው ጊዜ”
“በታላቅ ድምፅ ጮኸ” ወይም “በስቃይ ጮኸ”
“በኢየሱስ ፊት በምድር ላይ ወደቀ”። የወደቀው በድንገት አይደለም።
“በጩኸት ተናገረ” ወይም “ከፍ ባለ ድምፅ ጮኸ”
የዚህ የአነጋገር ዘይቤ ትርጉም “ለምን ታስቸግረኛለህ?” ማለት ነው። (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)
ይህ ለኢየሱስ አስፈላጊ ማዕረግ ነው። (አባትን እና ልጅን መተርጎም የሚለውን ተመልከት)
“ሰውየውን ከተቆጣጠረው ብዙ ጊዜ ሆኖት ነበር” ወይም “ወደ እርሱ ከገባበት ብዙ ጊዜ ሆኖት ነበር”። ይህ የሚናገረው ኢየሱስ ከሰውዬው ጋር ከመገናኘቱ በፊት አጋንንቱ ብዙ ጊዜ ያደርገው የነበረውን ነው።
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ሰዎች በሰንሰለትና በእግር ብረት ቢያስሩትና ቢጠብቁትም እንኳን” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ይህንን ብዙ ቁጥር ያላቸውን ወታደሮች ወይም ሰዎች በሚያመለክት ቃል ተርጉመው። አንዳንድ ትርጉሞች “ሰራዊት” ይሉታል። አ.ት፡ “የሻለቃ ጦር” ወይም “ብርጌድ”
“ኢየሱስን ይለምነው ጀመር”
ይህ ስለ አሳማዎቹ ለማስተዋወቅ የተጨመረ ዳራዊ መረጃ ነው። (ዳራዊ መረጃ የሚለውን ተመልከት)
“ኮረብታው ላይ ሣር እየተመገቡ በአቅራቢያው ነበሩ”
እዚህ ጋ፣ “ስለዚህ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው አጋንንቱ ከሰውየው የወጡት ኢየሱስ ወደ አሳማዎቹ እንዲገቡ ስለነገራቸው መሆኑን ለማብራራት ነው።
በጣም በፍጥነት ሮጡ
“መንጋው… ሰመጡ”። አሳማዎቹ ራሳቸው ውሃው ውስጥ ስለ ነበሩ ማንም እንዲሰምጡ አላደረጋቸውም።
“አጋንንት የለቀቁትን ሰው አዩት”
“ጤነኛ” ወይም “ትክክለኛ ጠባይ ሲያሳይ”
እዚህ ጋ፣ “እግሮች አጠገብ ተቀምጦ” የአነጋገር ዘይቤ ሲሆን ትርጉሙ “በአጠገቡ በትህትና ተቀምጦ” ወይም “በፊት ለፊቱ ተቀምጦ”። አ.ት፡ “በኢየሱስ ፊት ለፊት መሬት ላይ ተቀምጦ” (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስን ፈርተውት እንደነበረ በግልጽ መናገር ጠቃሚ ሊሆን ይችላል። አ.ት፡ “ኢየሱስን ፈርተውት ነበር”
“እነዚያ የሆነውን ነገር ያዩት”
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “አጋንንት ይዞት የነበረውን ሰው ኢየሱስ ፈውሶት ነበር” ወይም “አጋንንት ተቆጣጥሮት የነበረውን ሰው ኢየሱስ ፈውሶት ነበር” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“ያ የጌርጌሴናውያን አካባቢ” ወይም “ጌርጌሴናውያን ሰዎች ይኖሩበት የነበረ አካባቢ”
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “በጣም ፈሩ” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
መዳረሻው ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ወደ ሐይቁ ማዶ ተመልሰህ ሂድ”
በእነዚህ ቁጥሮች የተፈጸሙት ሁነቶች ኢየሱስ በጀልባ ከመሄዱ በፊት ነው። ይህንን መነሻው ላይ ግልጽ አድርጎ መናገር ሊጠቅም ይችላል። አ.ት፡ “ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ ከመሄዳቸው በፊት ሰውዬው” ወይም “ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ የጀልባ ጉዞአቸውን ከመጀመራቸው በፊት ሰውዬው”
“ቤተሰቦችህ” ወይም “ዘመዶችህ”
“እግዚአብሔር ስላደረገልህ ነገር ሁሉ ንገራቸው”
ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ ከሐይቁ በሌላኛው በኩል ከገሊላ በተመለሱ ጊዜ 12 ዓመት የሆናትን የምኩራብ አለቃውን ልጅ፣ እንዲሁም 12 ዓመት ደም ሲፈሳት የነበረችውን ሴት ፈወሳቸው።
እነዚህ ቁጥሮች ስለ ኢያኢሮስ ዳራዊ መረጃ ይሰጣሉ። (ዳራዊ መረጃ የሚለውን ተመልከት)
“ሕዝቡ በደስታ ሰላምታ ሰጡት”
“በአካባቢው በነበረ ምኩራብ አለቆች ከሆኑት አንዱ” ወይም “በዚያች ከተማ በምኩራብ የተገናኘው የሕዝቡ መሪ”
ሊሆኑ የሚችሉት ትርጉሞች፣ 1) “በኢየሱስ እግር ስር ሰገደ” ወይም 2) “በኢየሱስ እግር አጠገብ በምድር ላይ ወደቀ”። ኢያኢሮስስ የወደቀው በድንገት አይደለም። ይህንን ያደረገው ለኢየሱስ ስላለው ትህትና እና አክብሮት ምልክት እንዲሆን ነው የሚሉት ናቸው።
“ልትሞት ነው”
አንዳንድ ተርጓሚዎች ኢየሱስ ከኢያኢሮስ ጋር ለመሄድ መስማማቱን በቅድሚያ መናገር ይኖርባቸዋል። አ.ት፡ “ስለዚህ ኢየሱስ ከእርሱ ጋር ለመሄድ ተስማማ። በመንገድ ላይ እያለ”
“ሰዎቹ በኢየሱስ ዙሪያ ተጠጋግተው ከበውት ነበር”
ይህ በታሪኩ ውስጥ አንድ አዲስ ገጸ ባህርይ ያስተዋውቃል። (አዲስና ነባር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
“ደም ይፈሳት የነበረች”። ተገቢው ጊዜ ባይሆንም እንኳን ምናልባት በማህፀን እያለች ጀምሮ ሳትደማ አልቀረችም። አንዳንድ ባህሎች እንደዚህ ያለውን ሁኔታ በትህትና የሚያመላክቱበት መንገድ ይኖራቸዋል።
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ነገር ግን ማንም ሊፈውሳት አልቻለም” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“የመጎናጸፊያውን ዘርፍ ነካች”። አይሁዳውያን ወንዶች በእግዚአብሔር ሕግ እንደታዘዘው የክብረ በዓል ልብሶቻቸው አካል በማድረግ በመጎናጸፊያዎቻቸው ላይ መነሳንስ ይደርቡ ነበር። እርሷ የነካችው ይህንን ሊሆን ይችላል።
ጴጥሮስ ይህንን ሲል የትኛውም ሰው ኢየሱስን ሊነካው ይችል እንደነበር ማመልከቱ ነው። አስፈላጊ ከሆነ ይህ ግልጽ ያልሆነ መረጃ ግልጽ ሊደረግ ይችላል። አ.ት፡ “በዙሪያህ ብዙ ሕዝብ ከቦ እያጋፋህ ነው፣ ስለዚህ ከእነርሱ አንዱ ነክቶህ ይሆናል”
ይህንን ሆነ ተብሎ የተደረገውን “መንካት” ከሕዝቡ ድንገተኛ መንካት መለየት ሊጠቅም ይችላል። አ.ት፡ “አንድ ሰው ሥራዬ ብሎ ነክቶኛል”
ኢየሱስ ኃይል አላጣም ወይም አልደከመም፣ ነገር ግን የእርሱ ኃይል ሴቲቱን ፈውሷታል። አ.ት፡ “የሚፈውስ ኃይል ከእኔ እንደወጣ አውቃለሁ” ወይም “ኃይሌ አንድ ሰው እንደ ፈወሰ ተሰምቶኛል”
“ያደረገችውን በምስጢር መያዝ እንደማትችል”። ምን እንዳደረገች መናገር ሊጠቅም ይችላል። አ.ት፡ “ኢየሱስን የነካችው እርሷ የመሆኗን ምስጢር መያዝ እንደማትችል”
“በፍርሐት እየተንቀጠቀጠች መጣች”
ሊሆኑ የሚችሉት ትርጉሞች፣ 1) “በኢየሱስ ፊት ሰገደች” ወይም 2) “በኢየሱስ እግር ላይ በምድር ላይ ተደፋች”። የወደቀችው በድንገት አይደለም። ይህ ለኢየሱስ የቀረበ የትህትና እና የአክብሮት ምልክት ነው የሚሉት ናቸው።
“ሕዝቡ ሁሉ እያዩ”
ይህ አንዲትን ሴት በደግነት የመናገሪያ መንገድ ነበር። የአንተ ቋንቋ ይህንን ደግነት የሚያሳይበት ሌላ መንገድ ይኖረው ይሆናል።
“በእምነትሽ ምክንያት ጤነኛ ሆነሻል”። የነገር ስም የሆነው “እምነት” እንደ ድርጊት ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ስላመንሽ ተፈውሰሻል” (የነገር ስም የሚለውን ተመልከት)
ይህ የአነጋገር ዘይቤ “ደህና ሁኚ” የማለትና በዚያው ጊዜ ቡራኬን የመስጠት መንገድ ነው። አ.ት፡ “ስትሄጂም ከእንግዲህ አትጨነቂ” ወይም “እየሄድሽ እያለሽ እግዚአብሔር ሰላምን ይስጥሽ” (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)
“ኢየሱስ ገና ለሴቲቱ እየተናገረ እያለ”
ይህ ኢያኢሮስን ያመለክታል (ሉቃስ 8:41 ን ተመልከት)።
ይህ መግለጫ ልጅቱ ስለሞተች ኢየሱስ ከአሁን በኋላ ምንም ነገር ለማድረግ እንደማይችል ያመለክታል።
ይህ ኢየሱስን ያመለክታል።
“ደህና ትሆናለች” ወይም “እንደገና በሕይወት ትኖራለች”
“ወደ ቤት በመጡ ጊዜ”። ኢየሱስ ከኢያኢሮስ ጋር ወደዚያ ሄደ። ደግሞም አንዳንድ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ከእነርሱ ጋር ሄዱ።
ይህ በአዎንታዊነት ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ኢየሱስ ለጴጥሮስ፣ ለዮሐንስ፣ ለያዕቆብ፣ ለልጅቱ አባትና እናት ብቻ ከእርሱ ጋር ወደ ውስጥ እንዲገቡ ፈቀደላቸው”
ይህ የሚያመለክተው ኢያኢሮስን ነው።
ይህ በዚያ ባህል የተለመደ የሐዘን መግለጫ መንገድ ነበር። አ.ት፡ “በዚያ የነበሩት ሰዎች ሁሉ ልጅቱ ሞታ ስለነበር ድምፃቸውን ከፍ አድርገው በማልቀስ ምን ያህል እንዳዘኑ በመግለጽ ላይ ነበሩ”
“ልጅቱ መሞቷን ስላወቁ ሳቁበት”
“ኢየሱስ የልጅቱን እጅ ያዘ”
“መንፈሷ ወደ አካሏ ተመለሰ”። አይሁድ ሕይወት ማለት የመንፈስ ወደ ሰው ውስጥ መምጣት እንደነበር ተረድተዋል። አ.ት፡ “እንደገና መተንፈስ ጀመረች” ወይም “ወደ ሕይወት ተመለሰች” ወይም “እንደገና ሕያው ሆነች”
ይህ በተለየ ሁኔታ መነገር ይችል ነበር። አ.ት፡ “ለማንም እንዳይነግሩ”
1 ኢየሱስም ዐሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ጠርቶ በአጋንንት ሁሉ ላይና በሽታዎችን የመፈወስ ሥልጣን ሰጣቸው። 2 የእግዚአብሔርን መንግሥት እንዲሰብኩና በሽተኞችን እንዲፈውሱ ላካቸው። 3 እንዲህም አላቸው፤ “ለጒዞአችሁ በትርም ቢሆን፣ የገንዘብም ቦርሳ ቢሆን፣ ስንቅም ቢሆን፣ ገንዘብ ወይም ቅያሬ ልብስ፣ ምንም ነገር አትያዙ። 4 ከዚያ ስፍራ እስከምትወጡ በገባችሁበት ቤት በዚያ ቆዩ። 5 “የማይቀበሏችሁ ቢኖሩ ከዚያ ከተማ ስትወጡ ምስክር እንዲሆንባቸው ከእግሮቻችሁ ጫማ ላይ አቧራውን አራግፉ።” 6 ከዚያም እነርሱ ከዚያ ተነሥተው የምሥራቹን ወንጌል እየሰበኩ፣ በሄዱባቸውም ስፍራዎች ሁሉ በሽተኞችን እየፈወሱ ያልፉ ነበር። 7 የአራተኛው ክፍል ገዢ ሄሮድስ እየተደረገ የነበረውን ሁሉ በሰማ ጊዜ፣ በጣም ተሸበረ፣ ምክንያቱም ‘አንዳንዶቹ መጥምቁ ዮሐንስ ከሞት ተነሥቷል፤ 8 በሌሎች ዘንድ ደግሞ ኤልያስ ተገልጧል፤ እንደ ገና ሌሎች ከጥንት ነቢያት አንዱ ሕያው ሆኖ ተነሥቷል’ ይሉ ነበር። 9 ሄሮድስም “የዮሐንስን ራስ እኔ አስቈርጬዋለሁ፣ እንዲህ ያለ ነገር የምሰማበት ይህ ማን ነው?” አለ። ሄሮድስም ኢየሱስን ለማየት ጥረት ያደርግ ነበር። 10 የተላኩት በተመለሱ ጊዜ፣ ያደረጉትን ሁሉ ነገሩት። ኢየሱስ ራሱ ሐዋርያቱን አስከትሎ ቤተ ሳይዳ ወደምትባል ከተማ ሄደ። 11 ነገር ግን፣ ሕዝቡ ስለዚህ ጉዳይ ሰሙና ተከተሉት፣ እርሱም ተቀብሏቸው ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ነገራቸው፣ መፈወሰ የሚያስፈልጋቸውንም ፈወሳቸው። 12 ቀኑ ወደ መገባደድ ተቃረበ፣ ዐሥራ ሁለቱም ወደ እርሱ መጡና “ያለንበት ቦታ ምንም የሌለበት ምድረ በዳ በመሆኑ ሕዝቡ በአካባቢው ወዳሉት መንደሮችና ገጠሮች ሄደው ማረፊያ ቦታና ምግብ እንዲያገኙ አሰናብታቸው” አሉት። 13 እርሱ ግን፣ “የሚበሉትን እናንተ ስጧቸው” አላቸው። እነርሱም፣ “ወጣ ብለን ለዚህ ሁሉ ሕዝብ ምግብ ካልገዛን በስተቀር አሁን ያለን ከአምስት እንጀራና ከሁለት ዐሣ የበለጠ አይደለም” አሉት። 14 በዚያ አምስት ሺህ ያህል ሰዎች ነበሩ። እርሱም ደቀ መዛሙርቱን፣ “ሃምሳ ሃምሳ ሆነው በቡድን እንዲቀመጡ አድርጓቸው” አላቸው። 15 ስለዚህ እርሱ እንዳላቸው አደረጉ፣ ሕዝቡም ሁሉ ተቀመጡ። 16 እርሱም አምስቱን እንጀራና ሁለቱን ዐሣ ይዞ ወደ ሰማይ አሻቅቦ ከተመለከተ በኋላ ባርኮ፣ ቈርሶም ለሕዝቡ እንዲያቀርቡላቸው ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው። 17 ሁሉም በልተው ጠገቡ፣ የተራረፈውም የምግብ ፍርፋሪ ተሰበሰበና ዐሥራ ሁለት ቅርጫት ሙሉ ሆነ። 18 ኢየሱስ ብቻውን ይጸልይ በነበረበት አንድ ወቅት ደቀ መዛሙርቱ ከእርሱ ጋር ነበሩና፣ “ሕዝቡ እኔ ማን እንደሆንሁ ነው የሚናገሩት?” ብሎ ጠየቃቸው። 19 እነርሱም፣ “አጥማቂው ዮሐንስ ፣ ሌሎች ደግሞ ኤልያስ፣ እንደ ገና ሌሎች ጥንት ከነበሩት ነቢያት አንዱ ከሙታን ተነሥቶ ነው ይላሉ” አሉት። 20 “እናንተ ግን እኔን ማን ትሉኛላችሁ?” አላቸው። ጴጥሮስ፣ “አንተ ከእግዚአብሔር የመጣህ ክርስቶስ ነህ” ብሎ መለሰ። 21 ነገር ግን ኢየሱስ ይህን ለማንም እንዳይነግሩ በማስጠንቀቅ አዘዛቸው። 22 በተጨማሪም የሰው ልጅ ብዙ መከራ መቀበል እንደሚገባው በሽማግሌዎች፣ በካህናት አለቆችና በሕግ መምሕራን ተቀባይነት እንደማያገኝ፣ እንደሚሞትና በሦስተኛው ቀን ከሙታን እንደሚነሣ በቅድሚያ አስታወቃቸው። 23 ለሁሉም እንዲህ አላቸው፤ "እኔን መከተል የሚፈልግ ራሱን ይካድ ዕለት ዕለትም መስቀሉን ተሸክሞ ይከተለኝ። 24 ሕይወቱን ሊያድን ጥረት የሚያደርግ ሰው ካለ ያጠፋታል፣ ስለ እኔ ብሎ ሕይወቱን የሚጥል ደግሞ ያድናታል። 25 አንድ ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ የራሱን ሕይወት ግን ቢያጣ ምን ይጠቅመዋል? 26 በእኔና በቃሌ የሚያፍር ሁሉ የሰው ልጅ በራሱ፣ በአባቱ፣ እንዲሁም በቅዱሳን መላእክቱ ክብር በሚመጣበት ጊዜ ያፍርበታል። 27 እኔ ግን በእውነት እላችኋለሁ፣ እዚህ ከቆማችሁት መካከል አንዳንዶቻችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት እስከምታዩ ድረስ ሞትን አትቀምሱም። 28 ኢየሱስ ይህን ከተናገረ ከስምንት ቀን ገደማ በኋላ ጴጥሮስን፣ ዮሐንስን፣ እንዲሁም ያዕቆብን ይዞ ለመጸለይ ወደ ተራራ ወጣ። 29 እየጸለየም ሳለ የፊቱ መልክ ተለወጠ ልብሱም በጣም ከመንጣቱ የተነሣ አንፀባረቀ። 30 እነሆ፣ ሁለት ሰዎች ከእርሱ ጋር ይነጋገሩ ነበር! 31 እነርሱም በክብር የተገለጡት ሙሴና ኤልያስ ነበሩ። በኢየሩሳሌም ሊፈጽም ስላለው ከዚህ ሕይወት ስለ መለየቱ ይነጋገሩ ነበር። 32 ጴጥሮስና ዐብረውት የነበሩት እንቅልፍ ከብዶባቸው ነበር። ሙሉ በሙሉ በነቁ ጊዜ ግን የኢየሱስን ክብርና ዐብረውት የነበሩትን ሁለቱን ሰዎች አዩ። 33 እነርሱ ከኢየሱስ ተለይተው ሲሄዱ፣ ጴጥሮስ፣ “ጌታ ሆይ፣ ለእኛ በዚህ መሆን መልካም ነው፣ አንድ ለአንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ አንድ ደግሞ ለኤልያስ ሦስት ዳሶችን ልንሠራ ይገባናል” አለው። ስለ ምን እየተናገረ እንደ ነበረ አላስተዋለም። 34 ከዚያም እርሱ ይህን እየተናገረ ሳለ ደመና መጥቶ ጋረዳቸው፤ በዙሪያቸው ከነበረው ደመና የተነሣ ፈሩ። 35 ከደመናው ውስጥ፣ “የመረጥሁት ልጄ ይህ ነው፣ እርሱን ስሙት” የሚል ድምፅ መጣ። 36 የድምፁ መሰማት ባበቃ ጊዜ፣ ኢየሱስ ብቻውን ነበረ። እነርሱም ዝም አሉ፤ በነዚያ ቀናት ስላዩአቸው ስለ እነዚያ ነገሮች ምንም ነገር ለማንም አልተናገሩም። 37 ከተራራው በወረዱ ማግስት ብዙ ሕዝብ ተሰብስበው ወደ እርሱ መጡ። 38 እነሆም፣ ከሕዝቡ መካከል አንድ ሰው፣ “መምህር ሆይ፣ ብቸኛ የሆነውን አንድ ልጄን ትመለከትልኝ ዘንድ እለምንሃለሁ። 39 ክፉ መንፈስ በላዩ ሲመጣበት በድንገት ይጮኻል፣ እየጣለ ያንፈራግጠዋል፤ አረፋም በአፉ ይደፍቃል። በጭንቅ ለቅቆት ይሄዳል፣ በሚሄድበት ጊዜ ክፉኛ ያቈስለዋል። 40 ክፉውን መንፈስ እንዲያወጡለት ደቀ መዛሙርትህን ለመንኋቸው፣ እነርሱ ግን አልቻሉም” በማለት ጮኸ። 41 ኢየሱስ እንደዚህ በማለት መልስ ሰጠ፣ “ክፉና ጠማማ ትውልድ፣ ከእናንተ ጋር የምኖረውና የምታገሣችሁ እስክ መቼ ነው? ልጅህን ወደዚህ አምጣው።” 42 ልጁ እየመጣ ሳለ ጋኔኑ ጣለው፣ እጅግም አንፈራገጠው። ኢየሱስ ግን ርኩሱን መንፈስ ገሠጸውና ልጁን ፈወሰው፣ ለአባቱም መልሶ ሰጠው። 43 ሁሉም በእግዚአብሔር ታላቅነት ተደነቁ። ነገር ግን ሁሉም እርሱ ባደረጋቸው ነገሮች ሁሉ እየተደነቁ ሳሉ፣ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን፣ 44 "የነገርኋችሁን እነዚህን ነገሮች በጥልቀት አስተውሉ፤ ምክንያቱም የሰውን ልጅ በሰዎች እጅ አሳልፈው ይሰጡታል" አላቸው። 45 ነገር ግን ተሰውሮባቸው ስለ ነበረ፣ ይህ አባባሉ ምን እንደ ሆነ ስላልተረዱት ሊገባቸው አልቻለም። ስለዚያ አባባል እርሱን መጠየቅ ፈሩ። 46 ከዚያም ከእነርሱ መካከል ከሁሉም እጅግ ታላቅ የሆነው ማን ነው የሚለውን ጥያቄ በሚመለከት ክርክር ተነሣ። 47 ኢየሱስ ግን በልባቸው ምን እያሰላሰሉ እንደ ነበሩ ባወቀ ጊዜ፣ አንድ ትንሽ ልጅ ይዞ በአጠገቡ አቆመው፣ እንዲህም አላቸው፤ 48 "እንደዚህ ያለውን ሕፃን በስሜ የሚቀበል፣ እኔን ይቀበላል። እኔን የሚቀበል ከሆነ ደግሞ የላከኝን ይቀበላል። ስለሆነም፣ በመካከላችሁ ከሁላችሁም የሚያንስ እርሱ ታላቅ ነውና።” 49 ዮሐንስ መልሶ እንዲህ አለ፤ “ጌታ ሆይ፣ አንድ ሰው በስምህ አጋንንት ሲያወጣ አየነው፣ ከእኛ ጋር ስላልሆነ ከለከልነው።" 50 ኢየሱስ ግን፣ “አትከልክሉት፣ ምክንያቱም የማይቃወማችሁ ከእናንተ ጋር ነው” አላቸው። 51 ወደ ሰማይ የሚሄድበት ጊዜ እየተቃረበ ሲመጣ፣ ወደ ኢየሩሳሌም ለመሄድ ቈርጦ ተነሣ። 52 ከእርሱ ቀደም ብለው እንዲሄዱ መልእክተኞች ላከ፤ እነርሱም ሊያዘጋጁለት ዘንድ ወደ ሳምራውያን መንደር ገቡ። 53 ነገር ግን ወደ ኢየሩሳሌም ለመሄድ ፊቱን አንቅቶ ስለ ነበር፣ በዚያ የነበሩት ሕዝብ አልተቀበሉትም። 54 ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ ያዕቆብና ዮሐንስ ይህን ባዩ ጊዜ፣ “ጌታ ሆይ፣ እሳት ከሰማይ ወርዶ እንዲያጠፋቸው እንድናዝ ትወዳለህን?” አሉት። 55 እርሱ ግን ዘወር ብሎ ገሰጻቸው። 56 ከዚያም ወደ ሌላ መንደር ሄዱ። 57 እየሄዱ ሳሉም አንድ ሰው፣ “ወደምትሄድበት ሁሉ እከተልሃለሁ” አለው። 58 ኢየሱስ፣ “ቀበሮዎች ጒድጓድ አላቸው፣ የሰማይ ወፎችም ጎጆ አላቸው፤ የሰው ልጅ ግን ራሱን የሚያስጠጋበት መጠለያ የለውም” አለው። 59 ከዚያም ለሌላውን ሰው፣ “ተከተለኝ” አለው። ሰውዬው ግን፣ “ጌታ ሆይ፣ በቅድሚያ እንድሄድና አባቴን እንድቀብር ፍቀድልኝ” አለው። 60 እርሱ ግን፣ ሙታናቸውን እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው፣ አንተ ግን በየስፍራው ሁሉ ሄደህ የእግዚአብሔርን መንግሥት አውጅ” አለው። 61 ሌላ ሰው ደግሞ፣ “ጌታ ሆይ፣ እከተልሃለሁ ነገር ግን በቅድሚያ የቤተ ሰቤን አባላት እንድሰናበት ፍቀድልኝ” አለው። 62 ኢየሱስ ግን፣ “ዕርፍ በእጁ ይዞ ወደ ኋላ የሚመለከት ለእግዚአብሔር መንግሥት የተገባ አይደለም” አለው።
ኃይል እንዲሰጣቸው በገንዘብና ባላቸው ነገር እንዳይታመኑ ኢየሱስ ያስታውሳቸዋል፣ ከዚያም ወደ ተለያየ ስፍራ ይልካቸዋል።
እነዚህ ሁለት ቃላት በአንድ ላይ ጥቅም ላይ የዋሉት፣ አሥራ ሁለቱ ሰዎች ለመፈወስ ችሎታና መብት እንደነበራቸው ለማሳየት ነው። ይህንን ሐረግ እነዚህን ሁለቱንም አሳቦች በሚይዙ ውሁድ ቃላት ተርጉማቸው።
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች፣ 1) “እያንዳንዱን አጋንንት” 2) “ሁሉንም ዓይነት አጋንንት” የሚሉት ናቸው።
ሕመም
“ወደተለያየ ስፍራ ላካቸው” ወይም “እንዲሄዱ ነገራቸው”
“ኢየሱስ ለአሥራ ሁለቱ እንዲህ አላቸው”። ይህ የሆነው ከመሄዳቸው በፊት መሆኑን መናገር ሊጠቅም ይችላል። አ.ት፡ “ከመሄዳቸው በፊት ኢየሱስ እንዲህ አላቸው”
“ምንም ነገር ይዛችሁ አትሂዱ” ወይም “ምንም ነገር አታምጡ”
“ለመንገዳችሁ” ወይም “በምትጓዙበት ጊዜ”። ወደ ኢየሱስ እስኪመለሱ ድረስ ከመንደር ወደ መንደር በሚዘዋወሩበት ጊዜ ለጉዞአቸው ምንም ነገር መውሰድ አይኖርባቸውም።
ሰዎች ተራራ ሲወጡ ወይም ጎርበጥባጣ መንገድ ላይ ሲሄዱ ሚዛናቸውን ለመጠበቅ እንዲሁም አጥቂዎችን ለመከላከል የሚጠቀሙበት ረዘም ያለ ዘንግ ነው።
መንገደኛ ለጉዞው የሚፈልጋቸውን ነገሮች ለመያዣነት የሚጠቀምበት ቦርሳ
እዚህ ጋ፣ ይህ ጥቅም ላይ የዋለው በጥቅሉ “ምግብ”ን ለማመልከት ነው።
“ወደምትገቡበት ወደ ማናቸውም ቤት”
“በዚያ ሰንብቱ” ወይም “በዚያ ቤት ውስጥ ለጊዜው በአንግድነት ኑሩ”
“ያንን ከተማ ለቃችሁ እስክትሄዱ ድረስ” ወይም “ያንን ስፍራ እስክትለቁ ድረስ”
“ሰዎች በማይቀበሏችሁ በየትኛውም ከተማ ማድረግ የሚኖርባችሁ ይህንን ነው፡ በምትለቁበት ጊዜ”
“የእግሮቻችሁን አቧራ አራግፉ” በዚያ ባህል ውስጥ ተቀባይነት የማጣት ብርቱ መግለጫ ነው። የዚያ ከተማ አቧራ እንኳን በእነርሱ ላይ እንዲቆይ እንደማይፈልጉ ማሳያ ነው። (See: Symbolic Action)
“ኢየሱስ የነበረበትን ስፍራ ትተው ሄዱ”
“በሚሄዱበት ሁሉ እየፈወሱ”
እነዚህ ቁጥሮች ስለ ሔሮድስ መረጃ ለመስጠት ጣልቃ ይገባሉ።
ይህ ሐረግ በዋናው የታሪክ መስመር ላይ ቆም እንዲባል ምልክት ይሰጣል። እዚህ ጋ ሉቃስ ስለ ሔሮድስ ዳራዊ መረጃ ይናገራል። (ዳራዊ መረጃ የሚለውን ተመልከት)
ይህ የሚያመለክተው የእስራኤልን አንድ አራተኛ ይገዛ የነበረውን ሔሮድስ አንቲጳስን ነው።
ተደናገረ፣ መረዳት አቃተው
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “አንዳንድ ሰዎች ተናግረዋል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“ተናግረዋል” የሚለውን ቃል ቀደም ብሎ ካለው ሐረግ መገንዘብ ይቻላል። አ.ት፡ “ሌሎች ደግሞ ከጥንት ነቢያቶች አንዱ ተነሥቷል አሉ”
ዮሐንስ ከሙታን ሊነሣ አይችልም ብሎ ገምቷል። ይህ በግልጽ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ራሱን ስለቆረጥኩት ዮሐንስ ሊሆን አይችልም። ስለዚህ፣ ይህ ሰው ማነው?”
x
ደቀ መዛሙርት ወደ ኢየሱስ ቢመለሱና የጋራ ጊዜ ለማሳለፍ ወደ ቤተሳይዳ ቢሄዱም እንኳን ሕዝቡ ለመፈወስና ትምህርቱን ለመስማት ኢየሱስን ይከተላል። ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ እያሉ ኢየሱስ እንጀራና ዓሣ ሊያቀርብላቸው ተአምራት ያደርጋል።
“ሐዋርያት ኢየሱስ ወደነበረበት ተመልሰው መጡ”
ይህ የሚያመለክተው ወደ ሌሎች ከተሞች በሄዱ ጊዜ የሰጡትን ትምህርትና ፈውስ ነው።
ይህ የአንድ ከተማ ስም ነው። (ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)
“ቀኑ ሊያልቅ ሲል” ወይም “በቀኑ ማለቂያ አቅራቢያ”
እንጀራ፣ በተቦካ ዱቄት ቅርጽ ወጥቶለት የሚጋገር ነው።
በአንተ ቋንቋ “በስተቀር”ን ለመረዳት አስቸጋሪ የሚሆን ከሆነ አዲስ ዐረፍተ ነገር ማድረግ ትችላለህ። “ሁለት ዓሣ። ይህን ሁሉ ሕዝብ ለመመገብ ሄደን ምግብ መግዛት ይኖርብናል”
“5000 ያህል ወንዶች” ይህ ቁጥር በዚያ ሊገኙ የሚችሉትን ሴቶችና ሕፃናት አያካትትም። (ቁጥሮች የሚለውን ተመልከት)
“እንዲቀመጡ ንገሯቸው”
“ለእያንዳንዱ 50” (ቁጥሮች የሚለውን ተመልከት)
“ይህንኑ” የሚያመለክተው በሉቃስ 9፡4 ኢየሱስ እንዲያደርጉት የነገራቸውን ነው። ሕዝቡ ሃምሳ ሃምሳ ሆነው በቡድን እንዲቀመጡ ነገሯቸው።
“ኢየሱስ አምስቱን እንጀራ ይዞ”
ይህ የሚያመለክተው ወደ ላይ፣ ወደ ጠፈር መመልከቱን ነው። አይሁድ ሰማይ ከጠፈር በላይ እንደሆነ ያምኑ ነበር።
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ ብቻ በአጠገቡ ሆነው እየጸለየ ነው፣ ኢየሱስ ማን እንደሆነ መነጋገር ይጀምራሉ። ኢየሱስ በቅርቡ እንደሚሞትና እንደሚነሣ ይነግራቸዋል፣ ሊያደርጉት በጣም ከባድ ቢሆንም እንኳን እንዲከተሉት አጥብቆ ያሳስባቸዋል።
ይህ ሐረግ እዚህ ጋ ጥቅም ላይ የዋለው የአዲስ ሁነት ጅማሬን ለማመልከት ነው። (አዲስ ሁነትን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
“ብቻውን ሲጸልይ”። ደቀ መዛሙርቱ ከኢየሱስ ጋር ነበሩ፣ ነገር ግን እርሱ በግሉና ለብቻው ይጸልይ ነበር።
እዚህ ጋ የጥያቄውን አካል እንደገና መናገር ሊጠቅም ይችላል። አ.ት፡ “አንዳንዶች አጥማቂው ዮሐንስ ነህ ይላሉ”
ይህ ምላሽ ከኢየሱስ ጥያቄ ጋር እንዴት እንደሚገናኝ ማብራራት ሊጠቅም ይችላል። አ.ት፡ “ጥንት ከነበሩት ነቢያት አንዱ ሆነህ ተነሥተሃል”
“ወደ ሕይወት ተመልሷል”
“ከዚያም ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አላቸው”
“ለማንም እንዳይናገሩ” ወይም “ለማንም መናገር እንደሌለባቸው”። ይህ እንደ ቀጥተኛ ትዕምርተ ጥቅስ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ለማንም አትንገሩ” አላቸው። (ግልጽ የሆነና ያልሆነ ትዕምርተ ጥቅስ ተመልከት)
“ሰዎች የሰውን ልጅ ታላቅ መከራ እንዲቀበል ያደርጉታል”
ኢየሱስ ወደ ራሱ እያመለከተ ነው። አ.ት፡ “የሰው ልጅ የሆንኩ እኔ … እኔ እነሣለሁ” (አንደኛ፣ ሁለተኛ፣ ወይም ሦስተኛ መደብ የሚለውን ተመልከት)
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ሽማግሌዎቹ፣ የካህናት አለቆችና ጸሐፊዎች ይጥሉታል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ይገድሉታል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“ከሞተ ከሦስት ቀን በኋላ” ወይም “በሞተ በሦስተኛው ቀን”
“እንደገና በሕይወት እንዲኖር ይደረጋል”። ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “እግዚአብሔር እንደገና በሕይወት እንዲኖር ያደርገዋል” ወይም “እንደገና በሕይወት ይኖራል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
x
አንዳንዶቻቸው የእግዚአብሔርን መንግሥት ከማየታቸው በፊት እንደማይሞቱ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ከነገራቸው ከስምንት ቀን በኋላ ኢየሱስ ከጴጥሮስ፣ ያዕቆብና ዮሐንስ ጋር ለመጸለይ ወደ ተራራ ይወጣል፣ ኢየሱስ ወደ አንጸባራቂ መልክ በሚለወጥበት ጊዜ ሁሉም አንቀላፍተዋል።
ይህ የሚያመለክተው በሚቀጥሉት ቁጥሮች ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቶቹ የሚነግራቸውን ነው።
እዚህ ጋ፣ “እነሆ” የሚለው ቃል ቀጥሎ ለሚነገረው አስገራሚ መረጃ ትኩረት እንድንሰጥ ያነቃናል። አ.ት፡ “በድንገት”
ይህ ሐረግ ሙሴና ኤልያስ ምን ይመስሉ እንደነበሩ መረጃ ይሰጣል። አንዳንድ ቋንቋዎች እንደ ተናጠል አንቀጽ ሊተረጉሙት ይችላሉ። አ.ት፡ “በደማቅ ክብር ተገለጡ” ወይም “እጅግ ያንጸባርቁ ነበር”
“ስለ እርሱ መለየት” ወይም “ኢየሱስ ይህንን ዓለም እንዴት እንደሚተው”። ይህ ስለ ሞቱ በትህትና የተነገረበት መንገድ ነበር። አ.ት፡ “ስለ ሞቱ”
እዚህ ጋ፣ ይህ ቃል ጥቅም ላይ የዋለው በዋናው የታሪክ መስመር ላይ የተደረገውን ቆምታ ለማመልከት ነው። እዚህ ጋ ሉቃስ ስለ ጴጥሮስ፣ ያዕቆብና ዮሐንስ መረጃ ይሰጣል። (ዳራዊ መረጃ የሚለውን ተመልከት)
የዚህ የአነጋገር ዘይቤ ትርጉም “በጣም አንቀላፍተው” የሚል ነው።
ይህ የሚያመለክተው የከበባቸውን አንጸባራቂ ብርሃን ነው። አ.ት፡ “አንጸባራቂ ብርሃን ከኢየሱስ ሲመጣ አዩ” ወይም “በጣም ብሩኅ የሆነ ብርሃን ከኢየሱስ ወጥቶ ሲመጣ አዩ”
ይህ ሙሴንና ኤልያስን ያመለክታል።
“ሙሴና ኤልያስ በመሄድ ላይ እያሉ”
የሚቀመጡበት ወይም የሚተኙበት ቀለል ያለ፣ ጊዜያዊ ስፍራ
“እነዚህን ነገሮች ጴጥሮስ በመናገር ላይ እያለ”
እነዚህ ጎልማሳ ደቀ መዛሙርት የፈሩት ደመናውን አልነበረም። ይህ ሐረግ የሚጠቁመው ከደመናው ጋር አንድ ያልተለመደ ዓይነት ፍርሃት እንደመጣባቸው ነው። አ.ት፡ “ደንግጠው ነበር”
ደመናው ያደረገው ነገር ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ደመናው ከበባቸው”
ድምፁ የእግዚአብሔር ብቻ እንደሚሆን ግልጽ ነው። አ.ት፡ “ከደመናው ውስጥ እግዚአብሔር ተናገራቸው”
ይህ ለእግዚአብሔር ልጅ፣ ለኢየሱስ አስፈላጊ የሆነ ማዕረግ ነው። (አባትና ልጅን መተርጎም የሚለውን ተመልከት)
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “እኔ የመረጥኩት” ወይም “እኔ መርጬዋለሁ” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ይህ ከሁነቱ የተነሣ በራሱ በታሪኩ ውስጥ ከታሪኩ በኋላ ስለሆነው ነገር የሚናገር መረጃ ነው (የታሪኩ መጨረሻ የሚለውን ተመልከት)።
የመጀመሪያው ሐረግ ወዲያው የሰጡትን ምላሻቸውን ሲያመለክት ሁለተኛው በቀጣዮቹ ቀናት ያደረጉትን ያመለክታል።
ከኢየሱስ አንጸባራቂ መገለጥ በኋላ በቀጣዩ ቀን ደቀ መዛሙርት ሊፈውሱት ያልቻሉትን በአጋንን ተይዞ የነበረውን ልጅ ይፈውሰዋል።
“እነሆ” የሚለው ቃል በታሪኩ ውስጥ ለተነገረው አዲስ ሰው ያነቃናል። የአንተ ቋንቋ ይህንን መግለጽ የሚያስችል መንገድ ይኖረው ይሆናል። እንግሊዝኛው “በሕዝቡ መካከል አንድ ሰው ነበረ” የሚለውን ይጠቀማል። (አዲስና ነባር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
“አየኸው” የሚለው ቃል በሰውዬው ታሪክ ውስጥ ክፉዉን መንፈስ ያስተዋውቀናል። የአንተ ቋንቋ ይህንን መግለጽ የሚያስችል መንገድ ይኖረው ይሆናል። አ.ት፡ “ክፉ መንፈስ አለ” (አዲስና ነባር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
x
“ኢየሱስ እንዲህ በማለት መለሰለት”
ኢየሱስ ይህንን የተናገረው ለደቀ መዛሙርቱ ሳይሆን ተሰብስቦ ለነበረው ሕዝብ ነው።
“ምግባረ ብልሹ ትውልድ”
እዚህ ጋ በእንግሊዝኛ “ዩ” የተባለው ብዙ ቁጥር ነው። ሰዎች ባለማመናቸው ኢየሱስ ሐዘኑን ለመግለጽ እነዚህን ጥያቄዎች ይጠይቃል። እንደ መግለጫ ሊጻፉ ይችላሉ። አ.ት፡ “ለረጅም ጊዜ ከእናንተ ጋር ነበርኩ፣ እናንተ ግን አታምኑም። እስከ መቼ ልታገሳችሁ ያስፈልገኝ እንደሆነ እደነቃለሁ” (Forms of You እና ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ የእንግሊዝኛው “የአንተን” የሚለው ቃል ነጠላ ቁጥር ነው። ኢየሱስ እየተናገረ ያለው በቀጥታ አስታውቆት ለነበረው ለአባትየው ነው።
ኢየሱስ ተአምራትን አደረገ፣ ሆኖም ከፈውሱ ጀርባ የነበረው ኃይል እግዚአብሔር እንደሆነ ሕዝቡ ተገንዝቧል።
“ኢየሱስ ሲያደርግ የነበረው ነገር ሁሉ”
ይህ የአነጋገር ዘይቤ ሲሆን ትኩረት መስጠት አለባቸው ማለት ነው። አ.ት፡ “በጥንቃቄ ስሙ፣ አስታውሱም” ወይም “ይህንን አትርሱ” (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)
ይህ ከአድራጊ አንቀጽ ጋር ሊነገር ይችላል። እዚህ ጋ “እጅ” የሚያመለክተው ኃይልን ወይም መቆጣጠርን ነው። አ.ት፡ “የሰውን ልጅ ይክዱታል፣ በሰዎች ቁጥጥር ስር እንዲሆንም ያደርጉታል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ እና ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ በሦስተኛ መደብ የሚናገረው ስለ ራሱ ነው። “እጅ” የሚለው ቃል እጅ ያላቸውን ሰዎች ወይም በፈሊጣዊ አነጋገር እነዚያን እጆች የሚጠቀመውን ኃይል ገላጭ ነው። እነዚህ ሰዎች ማን እንደሆኑ ግልጽ ማድረግ ያስፈልግህ ይሆናል። አ.ት፡ “የሰው ልጅ የሆንኩ እኔ በሰዎች እጅ እካዳለሁ” ወይም “የሰው ልጅ ተክዶ ለጠላቶቹ ኃይል ይሰጣል” ወይም “የሰው ልጅ የሆንኩ እኔ ተክጄ ለጠላቶቼ ታልፌ እሰጣለሁ”
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “እግዚአብሔር ትርጉሙን ከእነርሱ ሰወረው” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ደቀ መዛሙርት ከመካከላቸው ማን እጅግ ታላቅ እንደሚሆን መከራከር ይጀምራሉ።
“በደቀ መዛሙርት መካከል”
እዚህ ጋ “ልባቸው” አዕምሮአቸውን የሚያመለክት ፈሊጣዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “በአዕምሮአቸው የሚያስቡትን አውቆ” ወይም “ሲያስቡት የነበረውን አውቆ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስን ወክሎ አንድ ነገር የሚያደርገውን ሰው ነው። አ.ት፡ “በእኔ ምክንያት” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ይህ ዘይቤአዊ አነጋገርም እንደ ንጽጽር ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “በስሜ፣ እኔን የሚቀበለኝ ያህል ነው” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“የላከኝ እግዚአብሔር”
“እግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ አድርጎ የሚቆጥረው እርሱ”
“ዮሐንስ እንዲህ ሲል መለሰ” ወይም “ዮሐንስ ለኢየሱስ መለሰለት”። ኢየሱስ የሁሉ ታላቅ ስለ መሆን ለተናገረው ለዮሐንስ ምላሽ እየሰጠ ነበር። እርሱ የሰጠው ለጥያቄ መልስ አይደለም።
ኢየሱስ ሳይሆን ዮሐንስ ስለ ራሱ ይናገራል፣ ስለዚህ እዚህ ጋ “እኛ” አግላይ ነው። (አግላይና አካታች “እኛ” የሚለውን ተመልከት)
ይህ ማለት ሰውዬው በኢየሱስ ኃይልና ሥልጣን ሲናገር ነበር። (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ይህ በአዎንታዊነት ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “እንዲቀጥል ፍቀዱለት”
አንዳንድ የዘመናችን ቋንቋዎች ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው አባባሎች አሏቸው። አ.ት፡ “አንድ ሰው እናንተን ከመሥራት ካላገዳችሁ እየረዳችሁ እንዳለ ያህል ነው” ወይም “አንድ ሰው እናንተን በመቃወም ካልሠራ ከእናንተ ጋር እየሠራ ነው”
በዚህ ጊዜ ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም ለመሄድ መወሰኑ ግልጽ ሆነ።
“የሚያርግበት ሰዓት በመጣ ጊዜ” ወይም “የሚያርግበት ሰዓት በደረሰ ጊዜ”
የዚህ የአነጋገር ዘይቤ ትርጉም “ቁርጥ ውሳኔ አደረገ” የሚል ነው። አ.ት፡ “አዕምሮውን አሠራው” ወይም “ወሰነ” (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)
ይህ ማለት እርሱ ወደዚያ እንዲደርስ የመናገሪያ ስፍራን፣ ማደሪያ ቦታንና ምግብን ጨምሮ ዝግጅት ማድረግን ያካትታል።
“በዚያ እንዲቆይ አልፈለጉም”
ሳምራውያንና አይሁድ እርስ በእርሳቸው ይጠላሉ ነበር። በመሆኑም ኢየሱስ ወደ አይሁድ ዋና ከተማ ወደ ኢየሩሳሌም በሚያደርገው ጉዞ ሳምራውያን አልረዱትም።
“ሳምራውያን ኢየሱስን እንዳልተቀበሉት አዩ”
እንደ ኤልያስ ያሉ ነቢያት እግዚአብሔርን በሚቃወሙ ሰዎች ላይ የፈረዱት እንደዚህ እንደነበር ስለሚያውቁ ያዕቆብና ዮሐንስ ይህንን የፍርድ አማራጭ አቀረቡ።
“ኢየሱስ ዘወር አለና ያዕቆብንና ዮሐንስን ገሰጻቸው”። ደቀ መዛሙርት እንደ ጠበቁት ኢየሱስ በሳምራውያን ላይ አልፈረደባቸውም።
ኢየሱስ ከሰዎች ጋር መንገድ እየሄደ መናገሩን ቀጥሏል።
ኢየሱስ ይህንን በማለት ሰውዬው የእርሱ ደቀ መዝሙር እንዲሆንና ከእርሱ ጋር እንዲሄድ እየጠየቀው ነው።
የሰውዬው አባት ስለ ሞተ ወዲያው ሊቀብር ወይስ አባቱ እስኪሞት ለረጅም ጊዜ ቆይቶ ከዚያ በኋላ ሊቀብረው እንዲችል ፈልጎ ይሆን ግልጽ አይደለም። ዋናው ነጥብ ሰውየው ኢየሱስን ከመከተሉ በፊት አስቀድሞ አንድ ነገር ማድረግ ይፈልጋል።
“ያንን ከማድረጌ በፊት እንድሄድ ፍቀድልኝ”
ኢየሱስ በቀጥታ የሞቱ ሰዎች ሌሎች የሞቱ ሰዎችን ይቀብራሉ ማለቱ አይደለም። ሊሆኑ የሚችሉ “የሙታን” ትርጉሞች፣ 1) በቅርቡ የሚሞቱትን የሚያመለክት ዘይቤአዊ አነጋገር ነው፣ ወይም 2) ኢየሱስን የማይከተሉትንና በመንፈስ የሞቱትን የሚያመለክት ዘይቤአዊ አነጋገር ነው የሚሉት ናቸው። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ይህ በጥቅሉ የሞቱትን ሰዎች ያመለክታል። አ.ት፡ “የሞቱ ሰዎች” (ስማዊ ቅጽል የሚለውን ተመልከት)
“ደቀ መዝሙር እሆናለሁ” ወይም “አንተን ለመከተል ዝግጁ ነኝ”
“ያንን ከማድረጌ በፊት በቤቴ ላሉት ሰዎቼ ልሄድ መሆኔን እንድነግራቸው ፍቀድልኝ”
ኢየሱስ የእርሱ ደቀ መዝሙር ስለ መሆን ለሰውዬው ለማስተማር በምሳሌ ይመልስለታል። ኢየሱስን ከመከተል ይልቅ ትኩረቱን ከእርሱ በፊት በነበሩ ሰዎች ላይ የሚያደርግ ሰው ለእግዚአብሔር መንግሥት ተስማሚ አይደለም ማለቱ ነው።
እዚህ ጋ፣ “እጁን በ - የሚያደርግ” የአነጋገር ዘይቤ ሲሆን ሰውዬው አንድ ነገር ለማድረግ ይጀምራል ማለት ነው። አ.ት፡ “ማንም እርሻውን ለማረስ ጀምሮ” (የአነጋገር ዘይቤ እና የማይታወቁትን ተርጉማቸው የሚለውን ተመልከት)
ማንም እያረሰ ወደ ኋላው የሚመለከት ማረሻውን መሄድ በሚገባው አቅጣጫ መምራት አይችልም። ያ ሰው በአግባቡ ለማረስ ወደ ፊት መመልከቱ ላይ ማተኮር አለበት።
“ለእግዚአብሔር መንግሥት ጠቃሚ” ወይም “ለእግዚአብሔር መንግሥት ተስማሚ”
1 ከዚህ በኋላ ጌታ፣ ሌሎች ሰባ ሰዎችን ሾመ፤ እርሱ ራሱ ሊሄድባቸው ወዳሰባቸው ከተማዎችና ስፍራዎች ሁሉ ቀድመውት እንዲሄዱ ሁለት ሁለት አድርጎ ላካቸው፤ 2 እንዲህም አላቸው፣ "መከሩ ብዙ ነው፣ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፡፡ ስለዚህ ወደ መከሩ ሠራተኞችን እንዲክ የመከሩን ጌታ በአስቸኳይ ለምኑት። 3 እንግዲህ ሂዱ፣ እነሆ፣ በተኲላዎች መካከል እንደ በጎች እልካችኋለሁ፡፡ 4 ለመንገዳችሁ ምንም አትያዙ፤ የገንዘብ ቦርሳም ቢሆን የመንገደኛ ሻንጣም ቢሆን፣ ጫማም ቢሆን አትያዙ፣ በመንገድም ላይ ለማንም ሰላምታ አትስጡ፡፡ 5 ወደ ማንኛውም ሰው ቤት ስትገቡ፣ በቅድሚያ 'ሰላም ለዚህ ቤት ይሁን' በሉ፡፡ 6 በዚያ ቤት ያለው ሰው የሰላም ሰው ከሆነ ሰላማችሁ ያርፍበታል፣ የሰላም ሰው ካልሆነ ደግሞ ሰላማችሁ ይመለስላችኋል፡፡ 7 ያቀረቡላችሁን እየበላችሁና እየጠጣችሁ በገባችሁበት በዚያው ቤት ቆዩ፣ ምክንያቱም ሠራተኛ ደመወዙን ማግኘት ይገባዋል፡፡ ከቤት ወደ ቤት ግን አትዘዋወሩ፡፡ 8 ወደ ማንኛውም ከተማ ስትገቡና እነርሱም ሲቀበሏችሁ፣ ያቀረቡላችሁን ብሉ፡፡ 9 በዚያም ያሉትን ሕመምተኞች ፈውሱ፣ 'የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ ቀርባለች' ብላችሁም ንገሩአቸው፡፡ 10 ነገር ግን ወደ ማንኛውም ከተማ ስትገቡ እነርሱ ባይቀበሏችሁ፣ ወደ ጐዳናዎቻቸው ውጡና፣ 11 'በጫማችን ላይ የተጣበቀውን የከተማችሁን አቧራ እንኳ በእናንተ ላይ ምስክር ይሆንባችሁ ዘንድ እናራግፈዋለን! የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ እንደ ቀረበ ግን ይህንን እወቁ' በሏቸው፡፡ 12 እላችኋለሁ፣ በፍርድ ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶምና ለገሞራ ይቀልላቸዋል፡፡ 13 ወዮልሽ ኮራዚን! ወዮልሽ ቤተ ሳይዳ! በእናንተ ዘንድ የተደረጉት ታላላቅ ታምራት በጢሮስና በሲዶና ተደርገው ቢሆን ኖሮ፣ የሐዘን ልብስ ለብሰውና ራሳቸውን አዋርደው ከረጅም ጊዜ በፊት ንስሐ በገቡ ነበር፡፡ 14 ነገር ግን በፍርድ ወቅት ከእናንተ ይልቅ ለጢሮስና ለሲዶና ይቀልላቸዋል። 15 አንቺስ ቅፍርናሆም፣ እስከ ሰማይ ከፍ እንዳልሽ ታስቢ ይሆን? እንደዚያ አታስቢ፣ እስከ ሲዖል ድረስ ትወርጃለሽ። 16 እናንተን የሚሰማችሁ እኔን ይሰማኛል፣ እናንተንም የማይቀበል እኔን አይቀበለኝም፣ እኔን የማይቀበል ደግሞ የላከኝን አይቀበልም፡፡ 17 ሰባዎቹም ደስ እያላቸው ተመለሱና፣ ጌታ ሆይ፣ አጋንንት እንኳ በስምህ ታዘዙልን" አሉት፡፡ 18 ኢየሱስ፣ "ሰይጣን እንደ መብረቅ ከሰማይ ሲወድቅ አየሁ 19 እነሆ፣ እባቦችንና ጊንጦችን እንድትረግጡ በጠላትም ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችኋለሁ፣ በምንም ዓይነት መንገድ ምንም አይጐዳችሁም፡፡ 20 የሆነ ሆኖ መናፍስት ስለተገዙላችሁ በዚህ ብቻ ደስ አይበላችሁ፤ ነገር ግን ስማችሁ በሰማይ ስለ ተጻፈ የላቀ ደስታ ይሰማችሁ።" 21 በዚያን ጊዜ ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ እጅግ ሐሤት አደረገና፣ "የሰማይና የምድር ጌታ፣ አባት ሆይ፣ እነዚህን ነገሮች ከጥበበኞችና ከሚያስተወሉ ሰውረህ እንደ ሕፃናት ለሆኑት ላልተማሩት ለእነዚህ ስለ ገለጽህላቸው አመሰግንሃለሁ፡፡ አዎ፣ አባት ሆይ፣ ይህ በፊትህ ዘንድ መልካም ሆኖአልና። 22 ሁሉም ነገር ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቶኛል፣ ከአባትም በቀር ልጁ ማን እንደ ሆነ የሚያውቅ የለም፣ አባትም ማን እንደ ሆነ ከልጁ ወይም ልጁ ሊገልጥለት ከፈለገው ሰው በቀር ማንም የሚያውቅ የለም።" 23 ኢየሱስ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መለስ ብሎ፣ ለእነርሱ ብቻ፣ "እናንተ የምታዩትን የሚያዩ የተባረኩ ናቸው፡፡ 24 ብዙ ነቢያትና ነገሥታት እናንተ ያያችሁትን ለማየት ፈልገው ሳያዩ፣ እናንተም የሰማችሁትን ሊሰሙ ፈልገው ሳይሰሙ ቀርተዋል" አለ። 25 እነሆ፣ አንድ የአይሁድ የሕግ መምህር ሊፈትነው ፈልጎ ብድግ አለና፣ "መምህር ሆይ፣ የዘላለምን ሕይወት ለመውረስ ምን ማድረግ ይገባኛል?" በማለት ጠየቀው፡፡ 26 ኢየሱስ፣ "በሕጉ የተጻፈው ምንድን ነው? የተረዳኸው እንዴት ነው?" አለው። 27 እርሱም፣ "ጌታ አምላክህን በሙሉ ልብህ፣ በሙሉ ነፍስህ፣ በሙሉ ኃይልህ፣ በሙሉ ዐሳብህም ውደድ፤ ባልንጀራህንም እንደ ራስህ አድርገህ ውደድ" ብሎ መለሰ፡፡ 28 ኢየሱስም፣ "በትክክል መልሰሃል፡፡ ይህን አድርግ በሕይወትም ትኖራለህ" አለው። 29 መምህሩ ግን ራሱን ሊያጸድቅ ወዶ፣ ኢየሱስን፣ "ባልንጀራዬ ማን ነው?" ብሎ ጠየቀው፡፡ 30 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፤ "አንድ ሰው ከኢየሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ እየሄደ ሳለ ወንበዴዎች አግኝተውት ንብረቱን ዘረፉት፣ ደበደቡት፣ በሞት አፋፍ ላይ እያለም ጥለውት ሄዱ። 31 እንደ አጋጣሚ አንድ ካህን በዚያ መንገድ ሲሄድ ሰውዬውን ተመለከተውና በሌላ በኩል አድርጎ አልፎት ሄደ። 32 በተመሳሳይ ሁኔታ አንድ ሌዋዊም ወደዚያ ስፍራ መጥቶ በሌላ በኩል አድርጎ አልፎ ሄደ። 33 አንድ ሳምራዊ ግን እየተጓዘ ሳለ ሰውዬው ወደነበረበት መጣ። ባየውም ጊዜ በርኅራኄ ልቡ ተነካ። 34 ወደ እርሱም ጠጋ ብሎ መድኃኒት ካደረገለት በኋላ ቊስሉን በጨርቅ አሰረለት። እርሱ ይጓጓዝበት በነበረበትም አህያ ላይ አስቀምጦት ወደ አንድ የእንግዶች ማረፊያ አመጣው፣ እንክብካቤም አደረገለት። 35 በማግስቱ ሁለት ዲናር ከኪሱ አውጥቶ ለእንግዳ ማረፊያው ኅላፊ ሰጠውና፣ "ተንከባከበው፣ ከዚህ በላይ ወጪ የሚያስወጣህ ከሆነ በምመለስበት ጊዜ ያወጣኸውን ትርፍ ወጪ እመልስልሃለሁ" አለው። 36 "ከእነዚህ ከሦስቱ በወንበዴዎች እጅ ለወደቀው ባልንጀራ የሆነለት የትኛው ይመስልሃል?" አለው። 37 መምህሩም፣ "የራራለቱ ነው" አለ። ኢየሱስም፣ "አንተም ሂድና ይህንኑ አድርግ" አለው። 38 እየተጓዙ ሳሉም ወደ አንድ መንደር ገባ፤ ማርታ የምትባልም አንዲት ሴት በቤትዋ ተቀበለችው" 39 እርሷም ማርያም የተባለች በኢየሱስ እግር ሥር ተቀምጣ ቃሉን የምትሰማ እኅት ነበረቻት" 40 ማርታ ግን ምግብ ለማዘጋጀት ባደረገችው ጥረት በጣም ውጥረት በዛባት። ወደ ኢየሱስም ዘንድ መጥታ፣ "ጌታ ሆይ፣ እኔ ብቻዬን ሥራ ስሠራ፣ እኅቴ እኔን ሳትረዳኝና ስትተወኝ አንተ ዝም ትላለህን? እንግዲያውስ እንድታግዘኝ ንገራት" አለችው። 41 ጌታ ግን፣ "ማርታ፣ ማርታ ስለ ብዙ ነገር ትጨነቂያለሽ፣ 42 የሚያስፈልገው ግን አንድ ነገር ነው፡፡ ማርያም በጣም ትክክል የሆነውን ምርጫ መርጣለች፣ ይህም ደግሞ ከእርሷ አይወሰድባትም›› ብሎ መለሰላት፡፡
ኢየሱስ ተጨማሪ 70 ሰዎችን በፊቱ አስቀድሞ ይልካቸዋል። እነዚያ 70ዎቹ በደስታ ይመለሳሉ፣ ኢየሱስም ለሰማይ አባቱ የምስጋናን ምላሽ ያቀርባል።
እዚህ ጋ ይህ ቃል ጥቅም ላይ የዋለው በታሪኩ ውስጥ አዲስ ሁነትን ለማመልከት ነው። (አዲስ ሁነትን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
“70”። አንዳንድ ትርጉሞች “ሰባ ሁለት” ወይም “72” ይላሉ። ይህንን የሚናገር የግርጌ ማስታወሻ መጨመር ያስፈልግህ ይሆናል። (ቁጥሮች የሚለውን ተመልከት)
“ሁለት ሰዎችን የያዘ ቡድን አድርጎ ላካቸው” ወይም “በእያንዳንዱ ቡድን ሁለት ሰዎችን አድርጎ ላካቸው”
በእውነቱ ይህ የተነገረው ሰዎቹ ከመሄዳቸው በፊት ነው። አ.ት፡ “እንዲህ ብሏቸው ነበር” ወይም “ከመሄዳቸው በፊት ነገራቸው” (የሁነቶች ቅደም ተከተል የሚለውን ተመልከት)
“ሰብሉ ብዙ ነው፣ የሚያስገቡት ሠራተኞች ግን በቂዎች አይደሉም”። ኢየሱስ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመግባት የተዘጋጁ ሰዎች ብዙዎች ናቸው፣ ሕዝቡን ለማስተማርና ለመርዳት የሚሄዱ ደቀ መዛሙርት ግን በቂዎች አይደሉም” ማለቱ ነበር። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“ወደ ከተሞቹ ሂዱ” ወይም “ወደ ሕዝቡ ሂዱ”
ተኩላዎች በጎችን ያጠቃሉ፣ ይገድላሉም። በመሆኑም የዚህ ዘይቤአዊ አነጋገር ትርጉም ኢየሱስ በሚልካቸው ደቀ መዛሙርት ላይ ጉዳት ለማድረስ የሚሞክሩ ሰዎች ይኖራሉ የሚል ነው። የሌላ የዱር አውሬ ስም ሊተካ ይችላል። አ.ት፡ “በምልካችሁ ጊዜ ተኩላዎች በጎችን እንደሚያጠቁ ሰዎች ሊጎዱአችሁ ይፈልጋሉ”
“ቦርሳ፣ የመንገደኛ ሻንጣ፣ ወይም ጫማ ከእናንተ ጋር አትውሰዱ”
“በመንገድ ላይ ማንንም ሰላም አትበሉ”። ኢየሱስ በፍጥነት ወደ መንደሮች እንዲሄዱና ይህንን ሥራ እንዲሠሩ አጽንዖት እየሰጠ ነበር። እርሱ ባለጌ እንዲሆኑ እየነገራቸው አልነበረም።
ይህ ሰላምታና ባርኮት ነበር። እዚህ ጋ “ቤት” የሚያመለክተው በቤቱ ውስጥ የሚኖሩትን ነው። አ.ት፡ “በዚህ ቤተሰብ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ሰላምን ይቀበሉ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“ሰላማዊ ሰው”። ይህ ከእግዚአብሔርና ከሰዎች ጋር ሰላም እንዲኖረው የሚፈልግ ሰው ነው።
እዚህ ጋ፣ “ሰላም” የሚቆይበትን እንደሚመርጥ ሕያው ነገር ተደርጎ ተገልጿል። አ.ት፡ “የባረካችሁበት ሰላም ይኖረዋል” (ሰውኛ የሚለውን ተመልከት)
ሙሉዉን ሐረግ እንደገና መናገር ሊጠቅም ይችላል። አ.ት፡ “በዚያ የሰላም ሰው ከሌለ” ወይም “የቤቱ ባለቤት ሰላማዊ ሰው ካልሆነ”
እዚህ ጋ፣ “ሰላም” ትቶ መሄድ እንደሚመርጥ ሕያው ነገር ተደርጎ ተገልጿል። አ.ት፡ “ያ ሰላም ይኖራችኋል” ወይም “የባረካችሁበትን ሰላም አይቀበልም” (ሰውኛ የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ በዚያ በሚቆዩበት ጊዜ ሁሉ አዳራቸውን በዚያው ቤት እንዲያደርጉ እንጂ ቀኑን ሙሉ እቤት ውስጥ ቆዩ ማለቱ አልነበረም። አ.ት፡ “በዚያው ቤት ማደራችሁን ቀጥሉ”
ይህ ኢየሱስ በሚልካቸው ሰዎች ላይ ሲተገብረው የነበረ ጥቅል መርህ ነው። ሕዝቡን እስካስተማሩና እስከ ፈወሱ ድረስ ሕዝቡ ማደሪያና ምግብ ሊያቀርቡላቸው ይገባል።
ከቤት ወደ ቤት መዘዋወር ማለት ወደ ተለያዩ ቤቶች መሄድ ማለት ነው። እርሱ ይናገር የነበረው በተለያየ ቤት ስለ ማደር መሆኑን ግልጽ ማድረግ ይቻላል። “በየምሽቱ በተለያየ ቤት አትደሩ”
“ከተቀበሏችሁ”
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “የትኛውንም የሚሰጧችሁን ምግብ ብሉ” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ይህ በጥቅሉ የታመሙትን ሰዎች ያመለክታል። አ.ት፡ “የታመሙትን ሰዎች” (ስማዊ ቅጽል የሚለውን ተመልከት)
“የከተማዪቱ ሰዎች ከተቃወሟችሁ”
ይህ የከተማዪቱን ሰዎች እንደማይቀበሏቸው የሚያሳይ ምልክታዊ ድርጊት ነው። አ.ት፡ “ልክ እናንተ እንዳልተቀበላችሁን እኛም በጥንቃቄ አንቀበላችሁም። እግሮቻችን ላይ የሚጣበቀውን የከተማችሁን አቧራ እንኳን እንተውላችኋለን” (ምልክታዊ ድርጊት የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ እነዚህን ሰዎች ሁለት ሁለት አድርጎ በቡድን እስከ ላካቸው ድረስ ይህንን የሚናገሩት ሁለት ሰዎች መሆን አለባቸው። ስለዚህ ሁለትነትን ገላጭ “እኛ” የሚል ቃል ያለው ቋንቋ ሊጠቀምበት ይችላል። (አግላይ እና አካታች “እኛ” የሚለውን ተመልከት)
“ይህንን ግን እወቁ” የሚለው ሐረግ ማስጠንቀቂያን ያስተዋውቃል። “እናንተ ባትቀበሉንም የእግዚአብሔር መንግሥት የመቅረቡን ሐቅ አይቀይረውም!”
የነገር ስም የሆነው “መንግሥት” ከግሥ ጋር “ንግሥና” ወይም “አገዛዝ” ተብሎ መገለጽ ይችላል። ተመሳሳዩን ዐረፍተ ነገር በሉቃስ 10፡8 ላይ እንዴት እንደ ተረጎምከው ተመልከት። አ.ት፡ “በቅርቡ በሁሉም ስፍራ እግዚአብሔር እንደ ንጉሥ ይገዛል” ወይም “እግዚአብሔር በዙሪያችሁ ሁሉ በመግዛት ላይ ስለመሆኑ ማረጋገጫ አለ” የሚሉት ናቸው (የነገር ስም የሚለውን ተመልከት)።
ኢየሱስ ይህንን ይናገራቸው የነበሩት ይልካቸው ለነበሩት ለ70ዎቹ ሰዎች ነው። ይህንን ያለው አንድ በጣም አስፈላጊ የሆነ ነገር ሊነግራቸው እንዳለ ለማሳየት ነበር።
ደቀ መዛሙርት ይህ የሚያመለክተው በኃጢአተኞች ስለሚፈረድበት የመጨረሻው ጊዜ መሆኑን ሳይረዱ አይቀሩም።
“እግዚአብሔር በዚያች ከተማ ላይ የሚፈርደውን ያህል በሰዶም ላይ አይፈርድም”። አ.ት፡ “እግዚአብሔር በሰዶም ሕዝብ ላይ ከሚፈርድበት በበለጠ በዚያች ከተማ ሕዝብ ላይ ይፈርዳል” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ የኮራዚንና የቤተሳይዳ ከተማ ሰዎች በዚያ ሆነው ይሰሙት ይመስል ይናገራቸዋል፣ እነርሱ ግን በዚያ የሉም። (ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ እና ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ እየገለጸ ያለው ባለፈ ጊዜ ሊሆን ስለሚችል ነገር ግን ስላልሆነ ሁኔታ ነው። አ.ት፡ “እኔ ለእናንተ ያደረግሁትን ተአምራት አንድ ሰው ለጢሮስና ለሲዶና ሰዎች አድርጎ ቢሆን ኖሮ”
“በዚያ ይኖሩ የነበሩ ክፉዎች ሰዎች በመቀመጥ ስለ ኃጢአታቸው መጸጸታቸውን ያሳዩ ነበር”
“ማቅ ለብሰው፣ አመድ ላይም ተቀምጠው”
ለምን እንደሚፈረድባቸው በግልጽ መናገር ሊጠቅም ይችላል። አ.ት፡ “ምንም እንኳን ተአምራትን ሳደርግ ብታዩም ንሰሐ ስላልገባችሁና በእኔ ስላላመናችሁ እግዚአብሔር በጢሮስና በሲዶና ሕዝብ ላይ ከሚፈርድባቸው እጅግ በሚበልጥ ሁኔታ ይፈርድባችኋል”
“እግዚአብሔር በእያንዳንዱ ላይ በሚፈርድበት በመጨረሻው ቀን”
በዚህ ጊዜ ኢየሱስ ይሰሙት ይመስል በቅፍርናሆም ከተማ ለሚኖሩ ሰዎች ይናገራል፣ እነርሱ ግን አይሰሙትም። (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ ስለ ትዕቢታቸው የቅፍርናሆምን ሰዎች ለመገሰጽ ጥያቄ ይጠይቃቸዋል። አ.ት፡ “በእርግጥ ወደ ሰማይ አታርጊም!” ወይም “እግዚአብሔር አያከብርሽም!” (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ እና አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ይህ አገላለጽ “እጅግ ከፍ አልሽ” ማለት ነው።
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ወደ ሲዖል ትወርጃለሽ” ወይም “እግዚአብሔር ወደ ሲዖል ይልክሻል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
አንዳንድ ቋንቋዎች የተከፈተው ተለዋዋጭ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም እንደሚያደርገው ሰባዎቹ በእውነቱ አስቀድመው ሄደው እንደነበር መናገር ይኖርባቸዋል። ይህ ግልጽ መደረግ የሚችል የተሰወረ መረጃ ነው።
ይህ ለእግዚአብሔር አስፈላጊ የሆነ ማዕረግ ነው። (አባት እና ልጅን መተርጎም የሚለውን ተመልከት)
“ሰማይ” እና “ምድር” ያለውን ነገር ሁሉ ይወክላል። አ.ት፡ “በሰማይና በምድር ባለው ሁሉ ላይ እና ሁሉ ነገር ላይ የበላይ”
ይህ የሚያመለክተው ስለ ደቀ መዛሙርቱ ሥልጣን ቀደም ሲል ኢየሱስ ያስተማረውን ነው። “እነዚህ ነገሮች” በማለት ብቻ አንባቢው ትርጉሙን እንዲወስን መተው በጣም የተሻለ ሊሆን ይችላል።
“ጥበበኛ” እና “አስተዋይ” የሚሉት ቃላት ስማዊ ቅጽሎች ሲሆኑ እንዲህ ያለ ስብዕና ያላቸውን ሰዎች የሚያመለክቱ ናቸው። እነዚህ ሰዎች፣ እግዚአብሔር እውነትን ስለ ሰወረባቸው እነርሱ ነን ቢሉም እንኳን በእውነቱ ጥበበኞችና አስተዋዮች አልነበሩም። አ.ት፡ “ጥበበኞችና አስተዋዮች እንደሆኑ ከሚያስቡ ሰዎች” (ቅኔ እና ስማዊ ቅጽል የሚለውን ተመልከት)
ይህ የሚያመለክተው ብዙ ባይማሩም እንኳን ትንንሽ ልጆች የሚያምኗቸውን ሰዎች በፈቃዳቸው በሚሰሟቸው መልኩ የኢየሱስን ትምህርቶች ለመቀበል ፈቃደኞች የሚሆኑትን ሰዎች ነው። አ.ት፡ “በጥቂቱ የተማሩ፣ ነገር ግን ትንንሽ ልጆች እንደሚያደርጉት እግዚአብሔርን የሚሰሙ ሰዎች”
“ይህንን ማድረግ አስደስቶሃል”
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “አባቴ ሁሉንም ነገር አሳልፎ ሰጥቶኛል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
እነዚህ በእግዚአብሔርና በኢየሱስ መካከል ያለውን ዝምድና የሚገልጹ አስፈላጊ ማዕረጎች ናቸው። (አባት እና ልጅን መተርጎም የሚለውን ተመልከት)
x
“ለብቻቸው” የሚለው ቃል እርሱ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ብቻ እንደነበረ ያመላክታል። አ.ት፡ “ከዚያ በኋላ፣ ብቻውን ከደቀ መዛሙርቱ ጋር በሆነ ጊዜ፣ ወደ እነርሱ ዘወር ብሎ እንዲህ አላቸው”
ይህ ምናልባት ኢየሱስ ያደርጋቸው የነበሩትን መልካም ሥራዎችና ተአምራቶች ያመለክት ይሆናል። አ.ት፡ “እኔ ሳደርግ የምታዩትን ለሚያዩ ለእነዚያ እንዴት መልካም ነ
ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስ እነዚያን ነገሮች ገና እንዳላደረጋቸው ነው። አ.ት፡ “ሆኖም፣ ገና ስላላደረግዃቸው ሊያዩአቸው አልቻ
ይህ ምናልባት የኢየሱስን ትምህርት ያመለክት ይሆናል። አ.ት፡ “እኔ ስናገር የሰማችኋቸውን ነገሮች”
ይህ ኢየሱስ ገና እንዳላስተማረ ያመለክታል። አ.ት፡ “ሆኖም፣ ማስተማር ባለመጀመሬ ሊሰሟቸው አልቻሉም”
ኢየሱስ ሊፈትነው ለሞከረው አይሁዳዊ መምህር በምሳሌ ይመልስለታል። (ምሳሌዎች የሚለውን ተመልከት)
ይህ በታሪኩ ውስጥ ለአዲስ ሁነትና ለአዲስ ሰው ትኩረት እንድንሰጥ ያነቃናል። (አዲስ ሁነትን ማስተዋወቅ፣ አዲስና ነባር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
“ኢየሱስን ለመገዳደር”
ኢየሱስ መረጃ እየፈለገ አይደለም። እርሱ እነዚህን ጥያቄዎች ያቀረበው የአይሁዳዊ መምህሩን እውቀት ለመፈተን ነው። አ.ት፡ “ሙሴ በሕጉ ላይ ምን እንደጻፈና ትርጉሙ ምን ይሆናል ብለህ እንደምታስብ ንገረኝ” (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
ይህ በአድርጊ ድምፅ ሊጠየቅ ይችላል። አ.ት፡ “ሙሴ በሕጉ ላይ የጻፈው ምን ነበር?” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“በእርሱ ውስጥ ምን አነበብክ?” ወይም “ምን እንደሚል ተረዳህ?”
ሰውዬው ሙሴ በሕጉ የጻፈውን እየጠቀሰ ነው።
እዚህ ጋ፣ “ልብ” እና “ነፍስ” የአንድን ሰው ውስጣዊ ማንነት የሚያመለክቱ ፈሊጣዊ አነጋገሮች ናቸው። እነዚህ አራት ሐረጎች በአንድ ላይ ጥቅም ላይ የዋሉት “ሙሉ በሙሉ” ወይም “በቅንነት” ለማለት ነው።
ይህ ተነጻጻሪ በበለጠ ግልጽነት ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ራስህን የምትወደውን ያህል ባልንጀራህን ውደደው” (ተነጻጻሪ የሚለውን ተመልከት)
“ሆኖም መምህሩ ራሱን የሚያጸድቅበትን መንገድ ለማሰብ ፈለገ፣ ስለዚህ እንዲህ አለ” ወይም “ሆኖም፣ መምህሩ ጻድቅ ሆኖ መታየት በመፈለግ እንዲህ አለ”
ይህ የትኛውም ሰው ያቀደው ነገር አልነበረም።
ይህ አገላለጽ በታሪኩ ውስጥ አንድ አዲስ ሰው ያስተዋውቃል፣ ሆኖም ማንነቱን በስም አይገልጸውም። (አዲስና ነባር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
“ካህኑ የቆሰለውን ሰው ባየው ጊዜ”። ካህን በጣም ሃይማኖተኛ ሰው ነው፣ በመሆኑም የቆሰለውን ሰው እንደሚረዳው አድማጮች ይገምታሉ። እርሱ እንደተገመተው ስላላደረገ፣ ትኩረታቸውን ወደዚህ ያልተጠበቀ ውጤት ለመሳብ ይህ ሐረግ “ነገር ግን ባየው ጊዜ” ተብሎ ሊነገር ይችላል።
ሰውዬውን እንዳልረዳው ያመለክታል። አ.ት፡ “የቆሰለውን ሰው አልረዳውም፣ ነገር ግን በመንገዱ በወዲያኛው በኩል ተሻግሮ ሄደ”
ሌዋዊው በቤተ መቅደስ ያገለግል ነበር። ባልንጀራው የሆነውን አይሁዳዊ ሰው መርዳት ይጠበቅበት ነበር። ይህንን አላደረገምና ሁኔታው ቢነገር ሊጠቅም ይችላል። አ.ት፡ “ሌዋዊ በሌላ በኩል … አልረዳውምም”
ይህ በታሪኩ ውስጥ ስሙን ሳይጠቅስ አንድን አዲስ ሰው ያስተዋውቃል። ከሰማርያ መሆኑን ብቻ እናውቃለን። (አዲስና ነባር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
አይሁዶች ሳምራውያንን ይንቋቸው ስለነበር የቆሰለውን አይሁዳዊ ሰው አይረዳውም ብለው ገምተዋል።
“ሳምራዊው የቆሰለውን ሰው ባየው ጊዜ”
“አዘነለት”
በመጀመሪያ ዘይቱንና ወይኑን በቁስሎቹ ላይ ማድረግ ነበረበት። አ.ት፡ “ወይንና ዘይት በቁስሎቹ ላይ ጨምሮ በጨርቅ ጠቀለላቸው” (የሁነቶች ቅደም ተከተል የሚለውን ተመልከት)
ወይን የተጠቀመው ቁስሉን ለማጽዳት ሲሆን ዘይቱ ምናልባት ማመርቀዝን ለመከላከል ሳይሆን አይቀርም። ይህ እንደሚከተለው ሊነገር ይችላል፤ አ.ት፡ “ቁስሉ እንዲፈወስ ዘይትና ወይን በላዩ ላይ ማፍሰስ”
“የራሱ የጭነት እንስሳ”። ይህ ከባድ ጭነት እንዲሸከም የተጠቀመበት እንስሳ ነበር። ምናልባት አህያ ሳይሆን አይቀርም።
“የሁለት ቀን ደሞዝ”። “ዲናር” የ”ዲናሪየስ” ብዙ ቁጥር ነው። (በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሰ ገንዘብ የሚለውን ተመልከት)
“የሆቴሉ ጠባቂ” ወይም “የሆቴሉን ኃላፊነት የወሰደው ሰው”
ይህ ቅደም ተከተል እንደገና ሊስተካከል ይችላል። አ.ት፡ “በምመለስበት ጊዜ የምታወጣውን የትኛውንም ተጨማሪ ወጪ እኔ እከፍልሃለሁ”
ኢየሱስ እህቷ ማርያም እርሱን በጥሞና ወደምታዳምጥበት ወደ ማርታ ቤት ይመጣል።
“በጣም ሥራ በዛባት” ወይም “እጅግ ሥራ በዛባት”
ማርያም ብዙ የሚሠራ ሥራ ባለበት ጊዜ ጌታ እርሱን እንድትሰማው በመፍቀዱ ማርታ ቅሬታ እያቀረበች ነው። እርሷ ጌታን ታከብረዋለች፣ በመሆኑም ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ በመጠቀም ቅሬታዋን በበለጠ ትህትና ታቀርባለች። (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ አጽንዖት ለመስጠት የማርታን ስም ይደግመዋል። አ.ት፡ “የተወደድሽ ማርታ” ወይም “አንቺ ማርታ”
ኢየሱስ ማርያም የምታደርገውን ማርታ ከምታደርገው ጋር እያነጻጸረ ነው። ይህንን ግልጽ ማድረግ ሊጠቅም ይችላል። አ.ት፡ “በእርግጠኝነት አስፈላጊ የሆነው ብቸኛው ነገር የእኔን ትምህርት መስማት ነው” ወይም “ምግብ ከማዘጋጀት ይልቅ የእኔን ትምህርት መስማት በይበልጥ አስፈላጊ ነው”
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች፣ 1) “ይህንን ዕድል ከእርሷ አልወስድባትም” ወይም 2) “እኔን ስትሰማኝ የምታገኘውን አትጥለውም” የሚሉት ናቸው (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
1 ኢየሱስ በአንድ ስፍራ መጸለዩን በፈጸመ ጊዜ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ እንዲህ አለው፣ “ጌታ ሆይ፣ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርቱን እንዳስተማረ እኛን መጸለይ አስተምረን” አለ። 2 ኢየሱስም፣ “በምትጸልዩበት ጊዜ፣ 'በሰማይ የምትኖር አባታችን ሆይ፣ ስምህ ይቀደስ መንግሥትህ ትምጣ 3 የዕለት እንጀራችን በየዕለቱ ስጠን። 4 እኛን የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን። ወደ ፈተናም አታግባን በሉ'" አላቸው። 5 ኢየሱስም፣ “ከእናንተ ወዳጅ ያለው በእኩለ ሌሊት ውድ ወዳጁ ዘንድ በመሄድ 6 ‘አንድ ወዳጄ ከሌላ ስፍራ ወደ እኔ መጥቶ የማስተናግድበት ምንም ስለሌለኝ፣ ሦስት እንጀራ አበድረኝ የማይለው ማነው’? 7 በቤት ውስጥ ያለው ወዳጁ ‘አታስቸግረኝ፤ በሩ ተዘግቶአል ልጆቼም ከእኔ ጋር በአልጋ ላይ ተኝተዋል። ለመነሣትና ለአንተ እንጀራ ለመስጠት አልችልም’ ይለዋልን? 8 ምንም እንኳን ወዳጁ ስለሆናችሁ ተነሥቶ እንጀራ ባይሰጣችሁም ያለ ዕረፍት ስለነዘነዛችሁት ብቻ ተነስቶ የምትፈልጉትን ያህል እንጀራ ይሰጣችኋል፤ 9 ለምኑ ይሰጣችኋል፣ ፈልጉ ታገኛላችሁ፣ አንኳኩ ይከፈትላችኋል፤ 10 የሚለምን ሰው ሁሉ ይቀበላልና የሚፈልግም ሰው ያገኛል፣ ለሚያንኳኳም ይከፈትለታል። 11 አባት ከሆናችሁት ከእናንተ ዓሣ ሲለምነው በዓሣ ፈንታ እባብ ወይም 12 ዕንቁላል ሲለምነው በዕንቁላሉ ፈንታ ጊንጥ የሚሰጠው ማን ነው? 13 ስለዚህ፣ እናንተ ክፉዎች ስትሆኑ፣ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠትን የምታውቁ ከሆነ፣ በሰማይ የሚኖረው አባታችሁማ ለሚለምኑት መንፈስ ቅዱስን እንዴት አብልጦ አይሰጣቸውም?” 14 በኋላ ኢየሱስ ጋኔን እያወጣ ነበር፤ እርሱም ድዳ ነበር። ጋኔኑም በወጣ ጊዜ ድዳው ሰውዬ ተናገረ፤ ሕዝቡም ተደነቁ። 15 ነገር ግን ከሕዝቡ አንዳንዶቹ፣ “አጋንንትን የሚያወጣው የአጋንንት አለቃ በሆነው በብዔል ዜቡል ነው” አሉ። 16 ሌሎች ሊፈትኑት ፈልገው ከሰማይ ምልክት እንዲያሳያቸው ጠየቁት። 17 ኢየሱስ ግን ዐሳባቸውን አውቆ፣ “እርስ በርሱ የሚከፋፈል መንግሥት ይፈርሳል፤ እርስ በርሱ የሚለያይ ቤተ ሰብም ይወድቃል። 18 ሰይጣን ራሱን በራሱ የሚቃረን ከሆነ መንግሥቱ እንዴት ይጸናል? እናንተ ግን እኔን አጋንንትን የሚያወጣው በብዔል ዜቡል ነው ትሉኛላችሁ። 19 እኔ በቡዔል ዜቡል አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ የእናንተ ተከታዮች የሚያወጧቸው በማን ነው? ከዚህም የተነሣ እነርሱ ፈራጆች ይሆኑባችኋል። 20 እኔ ግን በእግዚአብሔር ኃይል አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ፣ እንግዲያውስ የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ መጥቷል። 21 21 በሚገባ የታጠቀ ብርቱ ሰው ቤቱን በሚጠብቅበት ጊዜ የቤቱ ንብረት ያለ ስጋት ይሆናል፤ 22 ከእርሱ የበረታ ሰው ሲያሸንፈው ግን ያ ከእርሱ የበረታው ሰው መሣሪያውን ይቀማዋል፣ የቤቱንም ሀብት ይበዘብዛል። 23 ከእኔ ጋር ያልሆነ ይቃወመኛል፣ ከእኔ ጋርም የማይሰበስብ ይበትናል። 24 ርኩስ መንፈስ ከሰው በሚወጣበት ጊዜ ውሃ በሌለባቸው ስፍራዎች እየተዘዋወረ ማረፊያ ይፈልጋል። ምንም ማረፊያ ሲያጣ ‘ወደ ወጣሁበት ቤት እመለሳለሁ’ ይላል። 25 በሚመለስበት ጊዜ ያንን ቤት ተጠርጎና ጸድቶ ያገኘዋል። 26 ከዚያም ከእርሱ ይልቅ የከፉ ሰባት ሌሎችን ከእርሱ ጋር ይዞ ይሄድና ሁሉም በዚያ ሰው ውስጥ ገብተው ይኖራሉ። ከዚያም ያ ሰው በመጨረሻ የሚገጥመው ሁኔታ ከመጀመሪያው ይልቅ የከፋ ይሆናል። 27 ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች በሚናገርበት ጊዜ፣ ከሕዝቡ መካከል አንዲት ሴት ድምጿን ከፍ አድርጋ፣ “አንተን የተሸከመችህ ማኅፀንና የጠባሃቸው ጡቶች የተባረኩ ናቸው” አለችው። 28 እርሱ ግን፣ “የተባረኩትስ የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተው የሚጠብቁት ናቸው” አለ። 29 የሕዝቡም ቊጥር እየጨመረ ሲሄድ፣ እንዲህ ማለት ጀመረ፣ “ይህ ትውልድ ክፉ ትውልድ ነው። ምልክት ይፈልጋል፤ ሆኖም ከዮናስ ምልክት በቀር ሌላ ምልክት አይሰጠውም። 30 ልክ ዮናስ ለነነዌ ሰዎች ምልክት እንደ ሆነላቸው፣ የሰው ልጅም ለዚህ ትውልድ ምልክት ይሆናልና። 31 የደቡብ ንግሥት በፍርድ ወቅት ከዚህ ትውልድ ጋር ትነሣና ትፈርድበታለች፣ ምክንያቱም የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳርቻ መጥታለችና፤ እነሆም ከሰሎሞን የሚበልጥ በዚህ አለ። 32 32 የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ይነሡና ይፈርዱበታል፣ ምክንያቱም በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋል፤ እነሆም ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ። 33 አንድ ሰው መብራት ካበራ በኋላ ብርሃኑ በማይታይበት ሰዋራ ስፍራ አያስቀምጠውም ወይም እንቅብ በላዩ ላይ አይደፋበትም። ነገር ግን ወደዚያ ቤት የሚገቡ እንዲታያቸው ከፍ ባለ ስፍራ ላይ ያስቀምጠዋል። 34 ዓይን የሰውነት መብራት ነው። ዓይንህ ጤናማ ከሆነ፣ መላ ሰውነትህ በብርሃን የተሞላ ይሆናል። ዓይንህ ሕመምተኛ ከሆነ ግን መላ ሰውነትህ ጨለማ ይሆናል። 35 ስለዚህ በአንተ ውስጥ ያለው ብርሃን ጨለማ እንዳይሆን ተጠንቀቅ። 36 እንግዲህ መላ ሰውነትህ ምንም ጨለማ የሌለበትና በብርሃን የተሞላ ከሆነ፣ በዚያን ጊዜ በሙሉ ብርሃኑ መብራት በአንተ ላይ እንደሚያበራ ያህል ይሆናል። 37 ንግግሩንም ሲያበቃ አንድ ፈሪሳዊ በቤቱ ምግብ ይመገብ ዘንድ ጋበዘው፤ ኢየሱስም ከፈሪሳዊው ቤት ሄዶ ለማዕድ ቀረበ። 38 ኢየሱስ ወደ ማዕድ ከመቅረቡ በፊት እጁን ባለመታጠቡ ፈሪሳዊው ተደነቀ። 39 ጌታ ግን እንዲህ አለው፤ “እንግዲህ፣ እናንተ ፈሪሳውያን የጽዋውንና የወጭቱን ውጭ ታጸዳላችሁ፣ ውስጣችሁ ግን በስስትና በክፋት የተሞላ ነው። 40 እናንተ ማስተዋል የሌላችሁ ሰዎች፣ ውጪውን የፈጠረ የውስጡንስ አልፈጠረምን? 41 በውስጥ ያለውን ለድኾች ስጡ፣ ከዚያም ሁሉም ነገር ንጹሕ ይሆንላችኋል። 42 ነገር ግን እናንተ ፈሪሳውያን ወዮላችሁ! ምክንያቱም ካመረታችሁት አዝሙድና ጤና አዳም ዐሥራት እያወጣችሁ ፍትሕንና የእግዚአብሔርን ፍቅር ንቃችሁ ትተዋላችሁ። ሌላውን ነገር ማድረግ ሳትተዉ ፍትሕ ማድረግንና የእግዚአብሔርን ፍቅር መጠበቅ ያስፈልጋችኋል። 43 እናንተ ፈሪሳውያን ወዮላችሁ! በምኲራቦች የክብር መቀመጫዎችንና በገበያ ስፍራም የከበሬታ ሰላምታን ትወዳላችሁና። 44 ሰዎች የማን እንደሆኑ ሳያውቁ የሚረማመዱባቸው መቃብሮችን ትመስላላችሁና ወዮላችሁ!" 45 የአይሁድ የሕግ መምህር የነበረ አንድ ሰው፣ “መምህር ሆይ፣ በምትናገረው ነገር እኛንም እየሰደብኸን ነው” ብሎ መለሰለት። 46 ኢየሱስም እንዲህ አለ፣ “እናንተም የሕግ መምህራን፣ ለመሸከም የሚከብድ ሸክም በሰዎች ላይ ትጭናላችሁና፣ እናንተ ግን እነዚያን ሸክሞች በአንድ ጣታችሁ እንኳ አትነኳቸውምና ወዮላችሁ! 47 የገደሏቸው የእናንተ አባቶች ሆነው ሳለ እናንተ ግን የቀደሙ ነቢያትን መቃብር የምታንጹ ናችሁና ወዮላችሁ!። 48 ከዚህም የተነሣ አባቶቻችሁ በሠሩት ሥራ ምስክሮችና ከእነርሱም ጋር የምትስማሙ ናችሁና፣ ምክንያቱም እናንተ የመታሰቢያ መቃብራቸውን የምታንጹላቸው ነቢያት በእርግጥም በአባቶቻችሁ የተገደሉ ነበር። 49 በዚህ ምክንያት በእግዚአብሔር ጥበብ እንዲህ ተብሏል፣ ‘ነቢያትንና ሐዋርያትን ወደ እነርሱ እልካለሁ፣ እነርሱም አንዳንዶችን ያሳድዳሉ ይገድሉማል። 50 ስለሆነም ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ለፈሰሰው የነቢያት ሁሉ ደም ይህ ትውልድ ተጠያቂ ነው’። 51 ተጠያቂ የሚሆነውም ከአቤል ጀምሮ በመሠዊያውና በቤተ መቅደሱ መካከል እስከ ተገደለው እስከ ዘካርያስ ድረስ ለፈሰሰው የነቢያት ደም ነው። አዎን፣ ይህ ትውልድ ተጠያቂ ነው እላችኋለሁ። 52 52 እናንተ የአይሁድ የሕግ መምህራንም የዕውቀትን ቊልፍ ጨብጣችሁ ሳላችሁ እናንተ ራሳችሁ የማትገቡ፣ ሊገቡ ያሉትን እንዳይገቡ የምትከለክሉ ናችሁና ወዮላችሁ! 53 ኢየሱስ ከዚያ ለመሄድ እንደተነሣ፣ የአይሁድ የሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን ተቃወሙት፣ ብዙ ጉዳዮችን አስመልክተው ከእርሱ ጋር ተከራረኩ። 54 ይህንም ያደረጉት ራሱ በተናገረው ቃል ሊያጠምዱት ፈልገው ስለነበረ ነው።
ይህ የቀጣዩ ታሪክ ክፍል ጅማሬ ነው። ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እንዲጸልዩ ያስተምራቸዋል።
ይህ ሐረግ ጥቅም ላይ የዋለው የታሪኩን አዲስ ክፍል እንደተጀመረ ለማመልከት ነው። የአንተ ቋንቋ ይህንን የሚያደርግበት መንገድ ካለው እዚህ ጋ ልትጠቀምበት እንደምትችል አስብ። (አዲስ ሁነትን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
ደቀ መዛሙርት ጥያቄ ከመጠየቃቸው በፊት ኢየሱስ ጸሎቱን መጨረሱን መናገር የበለጠ አግባብነት ሊኖረው ይችላል። አ.ት፡ “በአንድ ቦታ ኢየሱስ ይጸልይ ነበር። ጸሎቱን በጨረሰ ጊዜ ከ … አንዱ
“ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አላቸው”
ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ በሚጸልዩበት ጊዜ “አባት” በማለት የእግዚአብሔር አብን ስም እንዲያከብሩ ኢየሱስ አዘዛቸው። (አባት እና ልጅን መተርጎም የሚለውን ተመልከት)
“ሁሉም ስምህን እንዲያከብሩት አድርግ”። “ስም” ብዙ ጊዜ የሚያመለክተው ሙሉውን ሰው ነው። አ.ት፡ “ሰዎች ሁሉ ያክብሩህ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
እግዚአብሔር በሁሉም ላይ የመግዛቱ አሠራር እርሱ ራሱ እግዚአብሔር እንደሆነ ተደርጎ ተነግሯል። አ.ት፡ “ናና በሁሉም ላይ ግዛ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ እንዴት መጸለይ እንዳለባቸው ለደቀ መዛሙርቱ ማስተማሩን ቀጥሏል።
እነዚህ ትዕዛዛዊ አንቀጾች ናቸው፣ ሆኖም ከትዕዛዝ ይልቅ እንደ ልመና ተደርገው መተርጎም አለባቸው። ይህንን ግልጽ ለማድረግ “እባክህን” የመሳሰለ ቃል መጨመር ሊጠቅም ይችላል። አ.ት፡ “… እባክህን ስጠን፣ እባክህን … ይቅር በለን … እባክህን አትምራን”
እንጀራ ውድ ያልሆነ፣ ሰዎች በየዕለቱ የሚበሉት ምግብ ነበር። እዚህ ጋ ጥቅም ላይ የዋለው በጥቅሉ ምግብን ለማመልከት ነው። አ.ት፡ “በየዕለቱ የምንፈልገውን ምግብ”
“በአንተ ላይ ኃጢአት ስለማድረጋችን ይቅር በለን” ወይም “የእኛን ኃጢአት ይቅር በል”
“እኛም ደግሞ ይቅር እንላለንና”
“በእኛ ላይ ኃጢአት ያደረገውን” ወይም “የማይገባውን ነገር ያደረገብንን”
ይህ በአዎንታዊነት ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ከፈተና አርቀን”
ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ስለ ጸሎት ማስተማሩን ቀጥሏል።
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርትን ለማስተማር ጥያቄ ይጠይቃል። አ.ት፡ “አስቡ፣ ከእናንተ አንዱ … በፊቱ ሊያቀርብለት” ወይም “እንዳላችሁ አስቡ … በፊቱ ሊያቀርብለት” (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
“ሦስት እንጀራ እንድበደር ፍቀድልኝ” ወይም “ሦስት እንጀራ ስጠኝና በኋላ እከፍልሃለሁ”። እንግዳ ተቀባዩ ለእንግዳው የሚያቀርብለት ምንም የተዘጋጀ ምግብ የለውም።
እንጀራ አብዛኛውን ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በጥቅሉ ምግብን እንዲወክል ሆኖ ነው። አ.ት፡ “የሚበላ የበሰለ በቂ ምግብ” ወይም “አንድ ሰው የሚበላው የተዘጋጀ በቂ ምግብ”
ጎብኚው ሩቅ ከሆነ ቤቱ መምጣቱ ታውቋል። አ.ት፡ “ሲጓዝ ውሎ አሁን ወደ ቤቴ መጥቷል”
“የምሰጠው ምንም የተዘጋጀ ምግብ”
x
ኢየሱስ የእርሱ ደቀ መዛሙርት ባለማቋረጥ እንዲጸልዩ ለማበረታታት እነዚህን ትዕዛዞች ይሰጣቸዋል። አንዳንድ ቋንቋዎች ከእነዚህ ግሦች ጋር ተጨማሪ መረጃ ደግሞ ይፈልጉ ይሆናል። በዚህ ዐውድ በይበልጥ ተስማሚ የሚሆነውን “እናንተ” የሚለውን ቃል ተጠቀሙ። አ.ት፡ “የሚያስፈልጋችሁን መለመናችሁን ቀጥሉበት … ከእግዚአብሔር የምትፈልጉትን መፈለጋችሁን ቀጥሉ … አግኙት … በሩን ማንኳኳታችሁን ቀጥሉ”
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “እግዚአብሔር እርሱን ይሰጣችኋል” ወይም “ትቀበሉታላችሁ” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
በር ማንኳኳት በቤቱ ውስጥ ያለው ሰው እናንተ በውጪ መቆማችሁን እንዲያውቅ ለጥቂት ጊዜ በሩን መምታት ነው። ደግሞም በባህልህ ሰዎች ወደ ቤት መድረሳቸውን ለማሳየት በሚጠቀሙበት ለምሳሌ “መጠራት” ወይም “መሳል” ወይም “ማጨብጨብ” የመሳሰሉትን መንገዶች በመጠቀም መተርጎም ይቻላል። እዚህ ጋ፣ ትርጉሙ አንድ ሰው እግዚአብሔር መልስ እስኪሰጠው ድረስ ጸሎቱን መቀጠል አለበት የሚል ነው። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “እግዚአብሔር በሩን ይከፍትላችኋል” ወይም “እግዚአብሔር ወደ ውስጥ ያስገባችኋል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ ስለ ጸሎት ለደቀ መዛሙርቱ ማስተማሩን ይጨርሳል።
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለማስተማር በጥያቄ ይጠቀማል። ይህ እንደ መግለጫ ደግሞ ሊጻፍ ይችላል። አ.ት፡ “አባቶች ከሆናችሁት ከእናንተ ማንም … ዓሣ” (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለማስተማር በጥያቄ ይጠቀማል። ይህ እንደ መግለጫ ደግሞ ሊጻፍ ይችላል። አ.ት፡ “እንቁላል ቢለምናችሁ በፍጹም ጊንጥ አትሰጡትም” (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
ጊንጥ ከሸረሪት ጋር ይመሳሰላል፣ ነገር ግን እርሱ መርዛማ መናደፊያ ጭራ አለው። አንተ ባለህበት አካባቢ ጊንጥ የማይታወቅ ከሆነ “መርዛማ ሸረሪት” ወይም “የሚናደፍ ሸረሪት” ብለህ ልትተረጉመው ትችላለህ። (የማይታወቁትን ተርጉማቸው የሚለውን ተመልከት)
“እናንተ ክፉ የሆናችሁት . . . ካወቃችሁ” ወይም “ኃጢአተኞችም እንኳን ብትሆኑ፣ እናንተ . . . ታውቃላችሁ”
ኢየሱስ ከዲዳው ሰው አጋንንትን ካወጣ በኋላ ጥያቄ ይቀርብለታል።
ደራሲው የአዲስ ሁነት ጅማሬን ለማመልከት ይህንን ቃል ይጠቀማል። (አዲስ ሁነትን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
ልዩ መረጃ መጨመር ሊረዳ ይችል ይሆናል። አ.ት፡ “ኢየሱስ ከአንድ ሰው አጋንንትን ያወጣ ነበር” ወይም “ኢየሱስ፣ አጋንንት ሰውየውን እንዲለቀው ያደርግ ነበር”
አጋንንቱ ሰዎችን ከመናገር የሚከለክልበት ኃይል ነበረው። አ.ት፡ “ሰውየው መናገር እንዳይችል አድርጎት የነበረው አጋንንት”
ድርጊቱ የቱ ጋ እንደሚጀምር ለማመልከት ይህ ቃል እዚህ ጋ ጥቅም ላይ ውሏል። የአንተ ቋንቋ ይህንን የሚያደርግበት መንገድ ካለው ያንን እዚህ ጋ ስለመጠቀም ማሰብ ይኖርብሃል። አጋንንቱ ከሰውዬው በወጣ ጊዜ ከሕዝቡ አንዳንዶቹ ኢየሱስን ነቀፉት፣ ይህም ኢየሱስ ስለ ክፉ መናፍስት ወዳስተማረው ትምህርት የሚመራ ሆነ።
ልዩ መረጃ መጨመር ሊረዳ ይችል ይሆናል። አ.ት፡ “አጋንንቱ ከሰውዬው በወጣ ጊዜ” ወይም “አጋንንቱ ሰውዬውን በለቀቀው ጊዜ”
“መናገር የማይችል የነበረው ሰው በዚህ ጊዜ ተናገረ”
“አጋንንትን የሚያወጣው የአጋንንት አለቃ በሆነው በብኤልዜቡል ኃይል ነው”
ኢየሱስ ለሕዝቡ ምላሽ መስጠት ይጀምራል።
“ሌሎች ሰዎች ኢየሱስን ፈተኑት”። ሥልጣኑ ከእግዚአብሔር መሆኑን እንዲያረጋግጥላቸው ፈለጉበት።
“ከሰማይ ምልክት እንዲሰጣቸው ለመኑት” ወይም “ከሰማይ ምልክት እንዲሰጣቸው በመጠየቅ”። ሥልጣኑ ከእግዚአብሔር መሆኑን እንዲያረጋግጥላቸው የፈለጉት እንዲህ ባለ መንገድ ነበር።
እዚህ ጋ፣ “መንግሥት” የሚያመለክተው በውስጡ የሚኖረውን ሕዝብ ነው። ይህም ደግሞ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “በአንድ መንግሥት ውስጥ የሚኖሩ ሕዝቦች እርስ በእርሳቸው ከተዋጉ መንግሥታቸውን ያጠፋሉ” (ፈሊጣዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ “ቤት” የሚያመለክተው ቤተሰብን ነው። አ.ት፡ “የቤተሰብ አባላት እርስ በእርስ ከተጣሉ ቤተሰባቸውን ይበታትኑታል” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“ተሰባብሮ ይወድቅና ይጠፋል”። ይህ የሚደረመስ ቤት ስዕል የሚያመለክተው የቤተሰብ አባላት እርስ በእርስ በሚጣሉበት ጊዜ ቤተሰቡ የሚጠፋ መሆኑን ነው። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ፣ “ሰይጣን” የሚያመለክተው እርሱን የሚከተሉትን አጋንንትን እንዲሁም ራሱን ሰይጣንን ነው። አ.ት፡ “ሰይጣንና በመንግሥቱ ያሉ አባላቱ እርስ በእርሳቸው ከተዋጉ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ ሕዝቡን ለማስተማር ጥያቄ ይጠይቃል። ይህ እንደ መግለጫ ሊተረጎም ይችላል። አ.ት፡ “ሰይጣን . . . ከሆነ መንግሥቱ አይጸናም” ወይም “ሰይጣን . . . መንግሥቱ ይፈራርሳል”። (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
“አጋንንትን ከሰዎች የማወጣው በብኤልዜቡል ኃይል እንደሆነ ትናገራላችሁና”። የክርክሩ ቀጣይ ክፍል በግልጽ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “አጋንንትን ከሰዎች የማወጣው በብኤልዜቡል ኃይል እንደሆነ ትናገራላችሁና። ያ ደግሞ ሰይጣን እርስ በእርሱ ተከፋፍሏል ማለት ነው”
“ነገር ግን እኔ . . . ተከታዮቻችሁ አጋንንት ከሰዎች እንዲወጡ በማን ኃይል ያስገድዷቸዋል?” ኢየሱስ ሕዝቡን ለማስተማር ጥያቄዎችን ይጠይቃል። ኢየሱስ የሚጠይቀው ጥያቄ ትርጉም ግልጽ ሊደረግ ይችላል። አ.ት፡ “ነገር ግን እኔ . . . እንግዲያውስ ተከታዮቻችሁም ደግሞ አጋንንትን የሚያወጡት በብኤልዜቡል ኃይል ነው ብለን መስማማት አለብን። ይሁን እንጂ ይህ እውነት እንደሆነ አታምኑም”።
“እኔ በብኤልዜቡል ኃይል አጋንንትን እንደማወጣ ስለማለታችሁ በእግዚአብሔር ኃይል አጋንንትን የሚያወጡ ተከታዮቻችሁ ይፈርዱባችኋል”
“የእግዚአብሔር ጣት” የእግዚአብሔርን ኃይል ያመለክታል። (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“ይህ የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ መምጣቷን ያሳያል”
ይህ ኢየሱስ ብርቱ ሰው ሆኖ የሌላውን ብርቱ ሰው ንብረት ይወስድ ይመስል እርሱ ሰይጣንን እና አጋንንቶቹን ስለ ማሸነፉ የሚናገር ነው። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“የሰውዬውን የጦር መሣሪያና መከላከያ ያስወግዳል”
“ማንም የእርሱን ነገር ሊሰርቅበት አይችልም”
“ሀብቱን ይሰርቀዋል” ወይም “የሚፈልገውን ነገር ሁሉ ይወስዳል”
ይህ የሚያመለክተው የትኛውንም ሰው ወይም የሰዎች ቡድን ነው። “ከእኔ ጋር ያልሆነ ማንም ቢሆን ይቃወመኛል፣ ከእኔ ጋር የማይሰበስብ ማንም ቢሆን ይበትናል” ወይም “ከእኔ ጋር ያልሆኑት እነርሱ ይቃወሙኛል፣ ከእኔ ጋር የማይሰበስቡ እነዚያም ይበትናሉ”
“እኔን የማይደግፈኝ” ወይም “ከእኔ ጋር የማይሠራ”
“እኔን በመቃወም ይሠራል”
ከእኔ ጋር የማይሰበስብ ይበትናል ኢየሱስ የሚያመለክተው እርሱን የሚከተሉ ደቀ መዛሙርትን መሰብሰብን ነው። ይህ በግልጽ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ሰዎች መጥተው እንዲከተሉኝ የማያደርግ ማንም ቢኖር ከእኔ እንዲርቁ ያደርጋቸዋል”
ይህ ክፉ መናፍስት የሚቅበዘበዙበትን “ኦና ሥፍራ” ያመለክታል።
“መንፈስ በዚያ ምንም ዓይነት እረፍት በሚያጣበት ጊዜ”
ይህ ለመኖሪያነት የተጠቀመበትን ሰውዬ ያመለክታል። አ.ት፡ “ወደ ኖርኩበት ሰው” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ይህ ዘይቤአዊ አነጋገር ተጠርጎ በጸዳውና ነገሮች ተስተካክለው በተቀመጡበት ቤት ስለተመሰለው ሰው ይናገራል። ቤቱ እስካሁን ድረስ ባዶ እንደሆነ ያመላክታል። ይህ ግልጽ ካደረገው መረጃ ጋር በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ሰውዬው ልክ አንድ ሰው ጠርጎ ያጸዳውና ሁሉንም ነገር በተገቢው ቦታ አድራጅቶ በማስቀመጥ የተወውን ቤት መስሎ ያገኘዋል” ወይም “ሰውዬው የጸዳና የተደራጀ፣ ነገር ግን የተተወ ቤት መስሎ ያገኘዋል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ እና ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“መጀመሪያ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እርኩሱ መንፈስ ሳይለቀው በፊት የነበረውን የሰውዬውን ሁኔታ ነው። አ.ት፡ “መንፈሱ ሳይለቀው በፊት ከነበረው ሁኔታ ይልቅ የከፋ”
x
ኢየሱስ ሕዝቡን ማስተማሩን ይቀጥላል።
“ብዙ ሰዎች ሕዝቡ ላይ ሲጨመሩ” ወይም “ሕዝቡ እየበዛ ሲሄድ”
እዚህ ጋ፣ “ትውልድ” በውስጡ ያለውን ሕዝብ ያመለክታል። አ.ት፡ “በዚህ ዘመን ያሉ ሰዎች ክፉዎች ናቸው። ለራሳቸው … ይፈልጋሉ” ወይም “በዚህ ዘመን የምትኖሩ ሰዎች ክፉዎች ናችሁ። ለእናንተ … ትፈልጋላችሁ”
ስለሚፈልገው የምልክት ዓይነት መረጃው ግልጽ ሊደረግ ይችላል። አ.ት፡ “ከእግዚአብሔር መምጣቴን ለማረጋገጥ ተአምራት እንዳደርግ ይፈልግብኛል”
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “እግዚአብሔር አንድም ምልክት አይሰጠውም” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“በዮናስ የሆነው” ወይም “እግዚአብሔር ለዮናስ ያደረገለት ተአምር”
ይህ ማለት ዮናስ ለነነዌ ሕዝብ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምልክት ሆኖ እንዳገለገለ ኢየሱስም በተመሳሳይ መንገድ በዚያ ዘመን ለነበሩት አይሁድ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምልክት ሆኖ ያገለግላል።
ኢየሱስ ወደ ራሱ እያመለከተ ነው።
“ዛሬ በሕይወት ያሉ ሰዎች”
ይህ የሳባን ንግሥት ያመለክታል። ሳባ ከእስራኤል በስተደቡብ የነበረ መንግሥት ነው።
“ተነሥታ በዚህ ዘመን ሰዎች ላይ ትፈርዳለች”
ይህ የአነጋገር ዘይቤ በጣም ሩቅ ከሆነ ቦታ መጥታለች የሚል ትርጉም አለው። አ.ት፡ “በጣም ረጅም ርቀት ተጉዛ መጥታለች” ወይም “በጣም ሩቅ ከሆነ ቦታ መጥታለች” (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ እየተናገረ ያለው ስለ ራሱ ነው። አ.ት፡ “ከሰለሞን የምበልጠው እኔ እዚህ አለሁ”
ኢየሱስ እየተናገረ ያለው ስለ ራሱ ነው። አ.ት፡ “እኔ ከሰለሞን እበልጣለሁ”
ይህ ጥንታዊቷን የነነዌ ከተማ የሚያመለክት መሆኑን በግልጽ መንገር ያግዝ ይሆናል። አ.ት፡ “በጥንታዊቷ የነነዌ ከተማ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች”
ይህ ወንዶችንና ሴቶችን ያካትታል። አ.ት፡ “ሕዝብ” (ተባዕታዊ ቃል በምታገኝበት ጊዜ እንስታዊንም ጨምርበት የሚለውን ተመልከት)
“የዚህ ዘመን ሕዝብ”
“የነነዌ ሕዝብ ንሰሐ ገብተዋልና”
ኢየሱስ እየተናገረ ያለው ስለ ራሱ ነው። እርሱን እንዳልሰሙት በግልጽ መንገሩ ሊጠቅም ይችላል። አ.ት፡ “ከዮናስ የምበልጥ ብሆንም እንኳን እናንተ ገና ንሰሐ አልገባችሁም”
ኢየሱስ ሕዝቡን ማስተማሩን ይጨርሳል።
ከቁጥር 33 – 36 ያሉት ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ እንዲታዘዙትና ከሌሎች ጋር እንዲካፈሉት ስለሚፈልገው “ብርሃን” ስለሆነው ትምህርቱ የተናገረባቸው ዘይቤአዊ አነጋገሮች ናቸው። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“ይደብቀዋል ወይም ከቅርጫት በታች ያስቀምጠዋል”
በዚህ አንቀጽ ውስጥ መገንዘብ በሚቻለው ባለቤትና ግሥ ላይ መጨመር ይቻላል። አ.ት፡ “ነገር ግን አንድ ሰው በመብራት ማስቀመጫው ላይ ያስቀምጠዋል” ወይም “ነገር ግን አንድ ሰው በጠረጴዛ ላይ ያስቀምጠዋል”
በዚህ የዘይቤአዊ አነጋገር ክፍል ውስጥ ልክ ዐይን ለሰውነት ብርሃንን እንደሚያቀርብ ኢየሱስ ሲያደርግ የሚያዩአቸው ነገሮች ማስተዋልን ያቀርቡላቸዋል። አ.ት፡ “ዐይንህ ልክ እንደ ሰውነት መብራት ነው” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ዐይን የማየት ችሎታ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው። (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ሰውነት ለሰው ሕይወት ነው።
እዚህ ጋ፣ “ዐይን” የማየት ችሎታ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “የማየት ችሎታህ ጤነኛ በሚሆንበት ጊዜ” ወይም “በሚገባ በምታይበት ጊዜ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ሰውነትህን በሙሉ ብርሃን ይሞላዋል” ወይም “ሁሉንም ነገር አጥርተህ ለማየት ትችላለህ” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ፣ “ዐይን” የማየት ችሎታ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “የማየት ችሎታህ በሚታወክበት ጊዜ” ወይም “በሚገባ ማየት በማትችልበት ጊዜ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“ምንም ነገር ለማየት አትችልም”
“ብርሃን ነው ብለህ የምታስበው ጨለማ ሆኖ እንዳይገኝ አረጋግጥ” ወይም “የትኛው ብርሃን፣ የትኛው ደግሞ ጨለማ መሆኑን ስለ ማወቅህ እርግጠኛ ሁን”
ኢየሱስ ተመሳሳዩን እውነት በተነጻጻሪ ይናገራል። እርሱ እውነትን ሰለ ተሞሉ ሰዎች በድምቀት እንደሚያበሩ መብራቶች አድርጎ ይናገርላቸዋል። (ተነጻጻሪ የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ በፈሪሳዊ ቤት እንዲበላ ተጋበዘ።
ደራሲው የአዲስ ሁነት ጅማሬን ለማመልከት እነዚህን ቃላት ይጠቀማል። (አዲስ ሁነትን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
ይህ የፈሪሳዊውን ቤት ያመለክታል።
ወንዶች በምግቡ ዙሪያ በምቾት ጋደም ማለታቸውና እንዲህ ያለውን እራት ዘና ብለው መብላታቸው የተለመደ ነበር። በአንተ ቋንቋ ሰዎች በሚበሉበት ጊዜ ሰውነታቸውን እንዴት ባለ ሁኔታ እንደሚያሳርፉት ገላጭ ቃል ካለው ያንን ቃል በመጠቀም መተርጎም ያስፈልግህ ይሆናል። አ.ት፡ “ለመብላት ተቀመጡ”
በሥርዓቱ መሠረት ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት ንጹሕ ለመሆን እጆቻቸውን መታጠብ እንዳለባቸው የሚናገር መመሪያ ፈሪሳውያን ነበራቸው። አ.ት፡ “እጆቹን መታጠብ” ወይም “በሃይማኖታዊው ሥርዓት ንጹህ ለመሆን እጆቹን መታጠብ”
ኢየሱስ ዘይቤአዊ አነጋገርን በመጠቀም ለፈሪሳዊው መናገር ይጀምራል። እርሱ ሲኒና ጎድጓድ ሳህኖችን የሚያነጹበትን መንገድ ራሳቸውን ከሚያነጹበት ጋር ያነጻጽራል። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
የዕቃ መያዣዎቹን ውጫዊ ገጽ ማጠብ የፈሪሳውያን የሃማኖታዊ ሥርዓታቸው አካል ነበር።
ይህ የዘይቤአዊ አነጋገር ክፍል የሳህኑን ውጫዊ ገጽታ ለማጽዳት የሚያደርጉትን ጥንቃቄ ቸል ከሚሉት ውስጣዊ ሁኔታቸው ጋር ያነጻጽራል።
እዚህ ጋ ኢየሱስ የሚናገራቸው ሁሉ ወንዶች ፈሪሳውያን ቢሆኑም እንኳን ይህ አገላለጽ ወንዶችን ወይም ሴቶችን ሊያመለክት ይችላል።
እግዚአብሔር በውስጣቸው ስላለው ነገር እንደሚገደው ባለማስተዋላቸው ኢየሱስ ፈሪሳውያንን በጥያቄ ይገስጻቸዋል። ይህ እንደ መግለጫ ሊተረጎም ይችላል። አ.ት፡ “ውጪውን የሠራው እርሱ ውስጡንም ደግሞ ሠርቶታል!” (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
ይህ በሲኒዎቻቸውና በጎድጓዳ ሳህኖቻቸው ሊያደርጉት የሚገባቸውን ያመለክታል። አ.ት፡ “በሲኒዎቻችሁና በጎድጓዳ ሳህኖቻችሁ ውስጥ ያለውን ለድኾች ስጡ” ወይም “ለድኾች ለጋሾች ሁኑ”
“ሙሉ በሙሉ ንጹሕ ትሆናላችሁ” ወይም “በውስጣችሁና በውጪአችሁ ሁሉ ንጹሕ ትሆናላችሁ”
“ከአዝሙድ፣ ከጤና አዳምና ከሌሎች የጓሮ ዕጾቻችሁ አንድ አሥረኛውን ለእግዚአብሔር ትሰጣላችሁ”። ከገቢያቸው ላይ አሥረኛውን ከመስጠት አንጻር ፈሪሳውያን እንዴት ያለ ጽንፍ እንደነበራቸው ኢየሱስ ምሳሌ እየሰጠ ነበር።
እነዚህ ዕጾች ናቸው። ሰዎች ከእነዚህ ቅጠላ ቅጠሎች ቀንጥሰው ጣዕም እንዲሰጥ ምግባቸው ላይ ይጨምራሉ። ሰዎች አዝሙድና ጤና አዳም ምን እንደሆኑ ካላወቁ እነርሱ የሚያውቁትን የዕጽ ስም ወይም “ዕጾች” የሚል ጥቅል አገላለጽ መጠቀም ትችላለህ። (የማይታወቁትን ተርጉማቸው የሚለውን ተመልከት)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች፣ 1) “ከሌላ ከእያንዳንዱ አትክልት” 2) “ከሌላ የጓሮ ዕጽ ሁሉ” ወይም 3) “ከሌላ የጓሮ ተክል ሁሉ” የሚሉት ናቸው።
“እግዚአብሔርን ለመውደድ” ወይም “ለእግዚአብሔር የሆነ ፍቅር”። የሚወደደው እግዚአብሔር ነው።
“ሳትተዉ” ይህ ሁልጊዜ መደረግ እንዳለበት አጽንዖት ይሰጣል። ይህ በአዎንታዊነት ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ሌሎቹንም መልካም ነገሮች እንዲሁ አዘውትራችሁ ለማድረግ” (ምጸት የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ ፈሪሳውያንን መናገሩን ያበቃል።
“ምርጥ መቀመጫዎች”
“ሰዎች በልዩ አክብሮት ሰላምታ እንዲሰጧችሁ ትወዳላችሁ”
ፈሪሳውያን ምልክት እንደሌለበት መቃብር ናቸው፣ ምክንያቱም በሃይማኖት ሥርዓት ንጹሕ ይመስላሉ፣ ነገር ግን በዙሪያቸው ያሉት እንዲረክሱ ያደርጋሉ። (ተነጻጻሪ የሚለውን ተመልከት)
እነዚህ መቃብሮች አስክሬን የሚቀበርባቸው የተቆፈሩ ጉድጓዶች ናችው። እነዚህ ሌሎች ሰዎች ያዩአቸው ዘንድ እንደተለመደው ሰዎች በመቃብር ሥፍራ የሚያስቀምጧቸው ነጭ ድንጋዮች የሏቸውም።
አይሁድ በመቃብር ላይ በሚሄዱበት ጊዜ በሃይማኖታዊው ሥርዓት ይረክሳሉ። እነዚህ ምልክት የሌለባቸው መቃብሮች በድንገት እንዲረክሱ ያደርጓቸዋል። ይህ በግልጽ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ሳያስተውሉት እና በሃይማኖታዊ ሥርዓት እርኩስ ይሆናሉ”
ኢየሱስ ለአይሁዳዊው መምህር ምላሽ መስጠት ይጀምራል።
ይህ በታሪኩ ውስጥ አዲስ ገጸ ባህርይን ያስተዋውቃል። (አዲስና ነባር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ በፈሪሳውያን ላይ የሰጠው አስተያየት የአይሁድ የሕግ መምህራንንም የሚመለከት መስሏል።
ኢየሱስ ከፈሪሳውያን ጋር የሕግ መምህራኑንም ተግባር ለመኮነን መፈለጉን ግልጽ ያደርጋል።
“ሊሸከሙት የማይችሉትን ከባድ ሸክም በሕዝብ ላይ ትጭናላችሁ”። ኢየሱስ የሚናገረው አንድ ሰው ከባድ ነገሮችን እንዲሸከሙት ለሕዝብ ይሰጣቸው ይመስል ብዙ መመሪያዎችን ስለሚሰጣቸው ሰው ነው። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች፣ 1) “ሕዝቡ እነዚያን ከባድ ሸክሞች እንዲሸከም ለመርዳት ምንም ነገር አታደርጉም” ወይም 2) “እነዚያን ሸክሞች ራሳችሁ ለመሸከም ምንም ጥረት አታደርጉም”
ኢየሱስ ፈሪሳውያንን እና የሕግ መምህራንን እየገሰጻቸው ነው። ስለ ነቢያት መገደል ያውቃሉ፣ ነገር ግን እነርሱን ስለመግደላቸው አባቶቻቸውን አይኮንኑም። አ.ት፡ “ስለዚህ፣ እነርሱን ከማውገዝ ይልቅ ታጸናላችሁ፣ ትስማማላችሁም”
ይህ ቀደም ሲል የሕግ መምህራን መመሪያዎችን በሕዝቡ ላይ ስለመጫናቸው የተነገረውን መግለጫ ወደ ኋላ ያመለክታል።
“ጥበብ” ስለ እግዚአብሔር ሆና መናገር እንደቻለች ተደርጋ ተወስዳለች። አ.ት፡ “እግዚአብሔር በጥበቡ እንዲህ አለ” ወይም “እግዚአብሔር በጥበብ ተናገረ” (ሰውኛ የሚለውን ተመልከት)
“ለሕዝቤ ነቢያትንና ሐዋርያትን እልክላቸዋለሁ”። ኢየሱስ ይናገራቸው ለነበሩ አይሁድ አድማጮች፣ እግዚአብሔር ለአባቶቻቸው ነቢያትንና ሐዋርያትን እንደሚልክ አስቀድሞ አስታውቋቸው ነበር።
“ሕዝቤ ከነቢያትና ከሐዋርያት አንዳንዶቹን ያሳድዳሉ፣ ይገድላሉም”። ኢየሱስ ይናገራቸው ለነበሩ አይሁድ አድማጮች እግዚአብሔር ለአባቶቻቸው ነቢያትንና ሐዋርያትን እንደሚያሳድዱና እንደሚገድሉ አስቀድሞ አስታውቋቸው ነበር።
ኢየሱስ ይናገራቸው የነበሩ ሰዎች በአባቶቻቸው ስለ ተገደሉት ነቢያት ተጠያቂዎች ይሆናሉ። አ.ት፡ “ስለዚህ ሰዎች ስለ ገደሏቸው ነቢያት ሞት በሙሉ እግዚአብሔር ይህንን ትውልድ ተጠያቂ ያደርገዋል” (ፈሊጣዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“ደም… ፈሰሰ” በተገደሉ ጊዜ የተረጨውን ደም ያመለክታል። አ.ት፡ “የነቢያትን መገደል” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ይህ ምናልባት በብሉይ ኪዳን ስለ ጣዖት አምልኮአቸው የእስራኤልን ሕዝብ የገሰጻቸው ካህን ይሆን ይሆናል። ይህ የአጥማቂው ዮሐንስ አባት አይደለም።
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ሕዝቡ የገደሉት” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ኢየሱስ ለአይሁዳዊው መምህር የሚሰጠውን ምላሽ ያበቃል።
ኢየሱስ የእግዚአብሔር እውነት በቤት ውስጥ እንዳለ፣ መምህራን ለመግባት እምቢ እንዳሉና ሌሎች ደግሞ ቁልፉን አግኝተው እንዳይገቡ እንዳልፈቀዱላቸው ይናገራል። ይህ ማለት መምህራኑ እግዚአብሔርን በእውነት አያውቁትም፣ ሌሎችንም ደግሞ እርሱን ከማወቅ ይከለክሏቸዋል ማለት ነው። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ይህ ወደ ቤት ወይም ወደ ዕቃ ማስቀመጫ ክፍል የመግቢያውን መንገድ ይወክላል።
“እናንተ ራሳችሁ እውቀት ለማግኘት አትገቡም”
ይህ ኢየሱስ በፈሪሳዊው ቤት የሚበላበት የታሪኩ የመጨረሻ ክፍል ነው። የታሪኩ ዋነኛው ክፍል ካለቀ በኋላ ስለሆነው ነገር እነዚህ ቁጥሮች ለአንባቢው ይናገራሉ።
“ኢየሱስ ከፈሪሳዊው ቤት ወጥቶ ከሄደ በኋላ”
ጸሐፊዎችና ፈሪሳውያን ከኢየሱስ ጋር የተከራከሩት የእግዚአብሔርን ሕግ ስለ ማፍረሱ ሊከሱት እንዲችሉ ለማጥመድ በመሞከር እንጂ አመለካከታቸውን ለማስከበር አልነበረም።
ይህ ማለት ሊከሱት ይችሉ ዘንድ ኢየሱስ አንድ የተሳሳተ ነገር እንዲናገር ፈልገዋል። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
1 ይህ እየሆነ ሳለ እርስ በርሳቸው እስኪረጋገጡ ድረስ በብዙ ሺህ የሚቈጠሩ ሰዎች ተሰብስበው ባሉበት ደቀ መዛሙርቱን እንዲህ ይላቸው ጀመር። "ግብዝነት ከሆነው የፈሪሳውያን እርሾ ተጠንቀቁ።" 2 ነገር ግን የሚገለጥ እንጂ ምንም የተሰወረ፣ የሚታወቅ እንጂ ምንም የተደበቀ ነገር የለም፡፡ 3 በጨለማ የተናገራችሁት ማንኛውም ነገር በብርሃን የሚሰማ፣ በጓዳ በጆሮ የተናገራችሁትም በከፍተኛ መድረኮች ላይ የሚታወጅ ይሆናል፡፡ 4 ለእናንተ ለወዳጆቼ፣ እንዲህ እላችኋለሁ፤ ሥጋን የሚገድሉትን ከዚያ በኋላ ግን ምንም ማድረግ የማይችሉትን አትፍሩ። 5 ማንን መፍራት እንደሚገባችሁ እኔ እነግራችኋለሁ። ከገደለ በኋላ ወደ ገሃነም እሳት የመጣል ሥልጣን ያለውን እርሱን ፍሩት። አዎን፣ እርሱን ፍሩት ብዬ እላችኋለሁ። 6 ሁለት ድንቢጦች ዝቅተኛ ዋጋ ባላቸው ሳንቲሞች ይሸጡ የለምን? ሆኖም ከእነርሱ አንዷም እንኳ በእግዚአብሔር ፊት የተዘነጋች አይደለችም። 7 ነገር ግን የእናንተ የራሳችሁ ፀጉሮች እንኳ የተቈጠሩ ናቸው። አትፍሩ፣ እናንተ ከብዙ ድንቢጦች የላቀ ዋጋ አላችሁ። 8 በሰዎች ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ይመሰክርለታል፤ 9 በሰዎች ፊት የሚክደኝ ግን በእግዚአብሔር መላእክት ፊት የሚካድ ይሆናል ብዬ እነግራችኋለሁ፡፡ 10 በሰው ልጅ ላይ የተቃውሞ ንግግር የተናገረ ማንኛውም ሰው ይቅርታ ያገኛል፣ በመንፈስ ቅዱስ ላይ የስድብ ቃል የሚናገር ግን ይቅርታ አያገኝም፡፡ 11 በምኲራቦች፣ በገዢዎችና በባለ ሥልጣኖች ፊት በሚያቀርቧችሁ ጊዜ ለቀረበባችሁ ክስ እንዴት መልስ መስጠት እንደሚገባችሁ ወይም ምን ማለት እንዳለባችሁ አትጨነቁ፤ 12 መንፈስ ቅዱስ በዚያ ወቅት ምን መናገር እንደሚገባችሁ ይነግራችኋልና" 13 ከሕዝቡም መካከል አንድ ሰው፣ "መምህር ሆይ፣ ወንድሜ ርስት እንዲያካፍለኝ ንገረው" አለ። 14 ኢየሱስም፣ "አንተ ሰው፣ በእናንተ ላይ ዳኛ ወይም አደራዳሪ አድርጎ የሾመኝ ማን ነው?" አለው። 15 ለእነርሱም እንዲህ አላቸው፣ "ስግብግብነት ከሞላባቸው ምኞቶች ራሳችሁን ጠብቁ፣ ምክንያቱም የአንድ ሰው ሕይወት በሀብቱ ብዛት ላይ የተመሠረተ አይደለም" 16 ከዚያም ኢየሱስ እንዲህ በማለት ምሳሌ ነገራቸው፤ "የአንድ ሰው ዕርሻ ከፍተኛ ምርት አስገኘለት፤ 17 እርሱም፣ 'የተመረተውን እህል የማከማችበት የለኝምና ምን ማድረግ ይገባኛል?' ብሎ በልቡ ዐሰበ። 18 እንዲህም አለ፤ 'እንግዲያውስ እንደዚህ አደርጋለሁ፣ ጐተራዎቼን አፍርሼ በምትኩ ትልልቅ ጐተራዎችን እሠራለሁ፣ የተመረተውን እህልና ሌሎች ንብረቶቼንም ሁሉ አከማችባቸዋለሁ። 19 ነፍሴንም፣ "ነፍሴ ሆይ፣ ለብዙ ዘመን የሚበቃ ብዙ ሀብት ተከማችቶልሻልና አትጨነቂ ብዪ፣ ጠጪ ደስም ይበልሽ እላታለሁ'" አለ። 20 እግዚአብሔር ግን እንዲህ አለው፤ "አንተ ሞኝ ሰው፣ ዛሬ ማታ ከአንተ ልትወሰድ ነፍስህ ትፈለጋለች፣ ያዘጋጀሃቸው ነገሮች ታዲያ ለማን ይሆናሉ?" 21 በእግዚአብሔር ፊት ባለ ጠጋ ያልሆነ ለራሱ ግን ሀብትን የሚያከማች ሰው ይህን ይመስላል። 22 ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እንዲህ አላቸው፤ "ስለዚህ እላችኋለሁ፣ ምን እንበላለን ብላችሁ ስለ ሕይወታችሁ ወይም ምን እንለብሳለን ብላችሁ ስለ ሰውነታችሁ አትጨነቁ፡፡ 23 ምክንያቱም ሕይወት ከምግብ ሰውነትም ከልብስ ይበልጣልና፡፡ 24 የማይዘሩትን ወይም የማያጭዱትን ቁራዎችን ተመልከቱ። መጋዘን ወይም ጐተራ የላቸውም፤ እግዚአብሔር ግን ይመግባቸዋል። ከወፎች ይልቅ እናንተ ምን ያህል የላቀ ግምት ያላችሁ ናችሁ? 25 ከእናንተስ ተጨንቆ በዕድሜው ላይ አንዲት ቀን መጨመር የሚችል ማን ነው? 26 ታዲያ፣ ታናሽ የሆነውን ነገር እንኳ ማድረግ የማትችሉ ከሆነ ስለ ሌላው ጉዳይ ለምን ትጨነቃላችሁ? 27 እንዴት እንደሚያድጉ አበቦችን ተመልከቱ፡፡ አይሠሩም ወይም አይፈትሉም። ሆኖም፣ ሰሎሞን እንኳ በዚያ ሁሉ ክብሩ ከእነዚህ እንደ አንዱ እንዳልለበሰ እኔ እነግራችኋለሁ። 28 ዛሬ ታይቶ ነገ ወደ ቆሻሻ ማከማቻ እንደሚጣለው ሣር በሜዳ ላይ ያለውን እግዚአብሔር እንደዚህ የሚያለብሰው ከሆነ፣ እምነታችሁ ትንሽ የሆነውን እናንተንማ ምን ያህል የበለጠ አያለብሳችሁም? 29 የምትበሉትንና የምትጠጡትን በመፈለግ አትጨነቁ። 30 በዓለም ውስጥ ባሉት አገሮች የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ እነዚህን ይፈልጋሉና፣ እናንተም እነዚህን እንደምትፈልጉ አባታችሁ ያውቃል። 31 ነገር ግን የእርሱን መንግሥት ፈልጉ፣ እነዚህም ነገሮች ይጨመሩላችኋል። 32 አንተ ታናሽ መንጋ፣ መንግሥትን ሊሰጥህ አባትህ እጅግ ደስ ይለዋልና አትፍራ። 33 ንብረቶቻችሁን ሽጡና ለድኾች ስጡ። በማያረጅ ከረጢት ሌቦች ሊቀርቡትና ብል ሊያጠፋው የማይቻለውን የማያልቀውን ሀብት በሰማይ አከማቹ። 34 ንብረታችሁ ባለበት ልባችሁም በዚያ ይሆናልና። 35 የሥራ ልብሳችሁን በአጭር ታጥቃችሁ በተጠንቀቅ ቁሙ፣ መብራታችሁም የበራ ይሁን፤ 36 በሚመጣበትና በሩን በሚያንኳኳበት ጊዜ ፈጥነው በሩን እንደሚከፍቱለት ጌታቸው ከሠርግ ሲመለስ እንደሚጠባበቁ ሰዎች ሁኑ። 37 በሚመጣበት ጊዜ ነቅተው ሲጠብቁ ጌታቸው የሚያገኛቸው እነዚያ አገልጋዮች የተመሰገኑ ናቸው። በእርግጥ እላችኋለሁ፣ እርሱም የሥራ ልብሱን ለብሶ ምግብ ለመመገብ እንዲቀመጡ ያደርጋቸውና ወደ እነርሱ መጥቶ ያገለግላቸዋል። 38 ከሌሊቱ በስድስት ሰዓት ወይም በዘጠኝ ሰዓትም እንኳ ቢሆን ሲመጣ ተዘጋጅተው የሚያገኛቸው እነዚያ አገልጋዮች የተመሰገኑ ናቸው። 39 በተጨማሪ ይህን እወቁ፤ የአንድ ቤት ጌታ ሌባ የሚመጣበትን ሰዓት የሚያውቅ ቢሆን ኖሮ የቤቱ በር እንዲሰበር ባልፈቀደም ነበር፡፡ 40 እናንተም እንደዚሁ ዝግጁ ሁኑ፣ ምክንያቱም የሰው ልጅ የሚመጣበትን ሰዓት አታውቁም።" 41 ጴጥሮስ፣ "ጌታ ሆይ፣ ይህንን ምሳሌ የተናገርኸው ለእኛ ብቻ ነው ወይስ ለሌሎችም ሰዎች ሁሉ ነው?" አለ። 42 ጌታም እንዲህ አለ፣ "ታዲያ ለሌሎቹ አገልጋዮቹ የተመደበላቸውን ምግብ በትክክለኛው ጊዜ ይሰጣቸው ዘንድ ጌታው የሾመው ታማኝና ብልህ አስተዳዳሪ ማን ነው? 43 ጌታው በሚመጣበት ጊዜ ይህን ሲያደርግ የሚያገኘው ያ አገልጋይ የተመሰገነ ነው" 44 እውነት እላችኋለሁ፣ ባለው ንብረት ሁሉ ላይ ይሾመዋል። 45 ያ አገልጋይ ግን በልቡ፣ 'የጌታዬ የመመለሻ ወቅት ይዘገያል' ቢልና ወንድና ሴት አገልጋዮችን መደብደብ፣ መብላትና መጠጣት እንዲሁም መስከር ቢጀምር፣ 46 የዚያ አገልጋይ ጌታ ባልጠበቀው ቀንና ባላወቀው ሰዓት ይመጣል፣ ይቆራርጠዋል፣ ካልታመኑት ጋርም ይደባልቀዋል። 47 የጌታውን ፈቃድ ያወቀውና እንደ ፈቃዱ ሆኖ ለመገኘት ያልተዘጋጀውና ፈቃዱን ያልፈጸመው ያ አገልጋይ ከፍተኛ ቅጣት ይቀጣል። 48 ነገር ግን ያላወቀና ቅጣት የሚያስከትልበትን ተግባር የፈጸመ ጥቂት ይቀጣል። ብዙ ከተሰጠው ከማንኛውም ሰው ብዙ ይጠበቅበታል፣ ከፍ ያለ አደራ ከተሰጠውም፣ ከእርሱ ብዙ ይፈለግበታል። 49 የመጣሁት በምድር ላይ እሳት ለመለኰስ ነው፣ ሆኖም አሁኑኑ ተቀጣጥሎ ባገኘው ደስ ባለኝ ነበር። 50 ነገር ግን የምጠመቀው ጥምቀት አለኝ፣ ያንንም ጥምቀት እስከምፈጽመው ምን ያህል በጭንቀት እጠባበቀዋለሁ! 51 በምድር ላይ ሰላምን ለማምጣት እንደ መጣሁ ታስባላችሁን? እንደዚያ አታስቡ፣ እነግራችኋለሁ፣ የመጣሁት ይልቁኑ መለያየትን ላመጣ ነው፡፡ 52 ከእንግዲህ ወዲህ በአንድ ቤት ውስጥ አምስት ሰዎች ቢኖሩ ሦስቱ በሁለቱ ላይ፣ ሁለቱም በሦስቱ ላይ የሚነሡና የሚለያዩ ይሆናሉ፡፡ 53 አባት በልጅ ላይ ልጅም በአባት ላይ፤ አማት በምራት ላይ፣ ምራትም በአማት ላይ ይነሡና ይለያያሉ፡፡ 54 ደግሞም ኢየሱስ ለሕዝቡ እንዲህ አላቸው፤ "በምዕራብ በኩል ደመና ሲያንጃብብ በምትመለከቱበት ጊዜ ወዲያውኑ፣ 'ሊያካፋ ነው' ትላላችሁ፣ እንዳላችሁትም ይሆናል። 55 የደቡብ ነፋስም ሲነፍስ፣ 'የሚያቃጥል ሙቀት ሊመጣ ነው' ትላላችሁ፣ እንዳላችሁትም ይሆናል። 56 እናንተ ግብዞች፣ የምድርንና የሰማይን መልክ እንዴት እንደምትተረጒሙ ታውቃላችሁ፣ ታዲያ የአሁኑን ወቅት እንዴት እንደምትተረጒሙ እንዴት አታውቁም? 57 እናንተ ራሳችሁ ትክክል የሆነውን ለምን አትፈርዱም? 58 ከባላጋራህ ጋር ወደ ከተማው አስተዳዳሪ በምትሄድበት ጊዜ፣ በመንገድ ላይ ቅራኔህን ለመፍታት ጥረት ማድረግ አለብህና፣ ይህን ባታደርግ ዳኛው ለዕለቱ ተረኛ መኰንን አሳልፎ ይሰጥሃል፣ ተረኛው መኰንንም ወደ ወንጀለኛ ማረፊያ ክፍል ያስገባሃል። 59 ዕዳህን ሙሉ በሙሉ እስካልከፈልህ ድረስ ከዚያ በፍጹም እንደማትወጣ እኔ እነግርሃለሁ።"
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን በሺህ በሚቆጠሩ ሰዎች ፊት ማስተማር ጀመረ
ይህ ምናልባት ጸሐፍት እና ፈሪሳውያን እርሱን ለማጥመድ መንገድ በሚፈልጉበት ጊዜ ሊሆን ይችላል፡፡ ጸሐፊው እነዚህን ቃላት የተጠቀመው አዲስ የሚጀምረውን ትዕይንት ለመግለጽ ነው፡፡ (አዲስ ትዕይንትን ማስተዋወቅ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የታሪኩን መቼት የሚያሳይ ዳራ የመረጃ ዳራ ነው፡፡ (የመረጃ ዳራ የሚለውን ይመልከቱ)
"ነገር ግን" የሚለው ቃል ስለ ፈሪሳውያን ግብዝነት ለመግለጽ ይህንን ሀረግ ከቀደመው ሀረግ ጋር ያያይዛል፡፡ (አያያዥ ቃላት የሚለውን ይመልከቱ)
"ማናቸውም የተደበቀ ነገር ይገለጣል፡፡" ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ሰዎች በሌሎች ሰዎች በድብቅ የተደረገን ማናቸውንም ነገር ይደርሱበታል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ከዐረፍተ ነገሩ የመጀመሪያ ክፍል ጋር ተመሳሳይ ትርጉም ያለው እውነቱን ላይ ትኩረት የሚሰጥ አገላለጽ ነው፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ሰዎች ሌሎች ሰዎች ሊደብቁ ስለሚሞክሩት ነገር በሙሉ ማወቅ ይችላሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ስፍራ "ጨለማ" የሚለው "ምሽት" ለሚለው ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት/ ሲሆን ይህም "በግል" ለሚለው ሜቶኖሚ ነው፡፡ እንደዚሁም "ብርሃን" የሚለው "ቀን" ለሚለው ሜቶኖሚ ሲሆን ይህም "ሕዝብ" ለሚለው ሜቶኖሚ ነው፡፡ "ይሰማል" የሚለው ሀረግ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "በምሽት ብቻችሁን ሆናችሁ የተናገራችሁትን፣ ሰዎች በቀን ብርሃን ይሰሙታል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ለሌላ ሰው ማንሾካሾክ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/የነገሩን ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)
"በተዘጋ ክፍል፡፡" ይህ የግል ንግግርን ያመለክታል፡፡ "በግል" ወይም "በድብቅ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡
"ከፍ ባለ ድምጽ ይነገራል፡፡" ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ሰዎች ያሰሙታል/ይናገሩታል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡(አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
በእሥራኤል ቤቶች ጠፍጣፋ ጣራ/ሰገነት አላቸው፤ ስለዚህም ሰዎች ወደዚያ ላይ ወጥተው ሊቆሙ ይችላሉ፡፡ ሰዎች እንዴት በቤት ጫፍ ላይ እንደሚወጡ ለመገመት አንባቢው ግር የሚለው ከሆነ፤ ይህ አጠቃላይ በሆነ መንገድ፣ "ሁሉም ሰው ሊሰማው በሚችለው ከፍ ባለ ስፍራ" በሚል ሊተረጎም ይችላል፡፡
ኢየሱስ በዚህ ሁኔታ ደቀ መዛሙርቱ እንዳይፈሩ ዳግም ንግግሩን በአዲስ መልክ ለማቅረብ
"ከዚህ በላይ ጉዳት ሊያደርሱ አይችሉም"
x
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለማስተማር ጥያቄ ይጠቀማል፡፡ "አምስት ድንቢጦች በሁለት ሳንቲም ብቻ እንደሚሸጥ ታውቃላችሁ፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
ጥራጥሬ የሚመገቡ፣ በጣም ትንንሽ ወፎች
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር እና በአዎንታዊ መልክ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "እግዚአብሔር ከእነርሱ አንዲቱን አንኳን በፍጹም አይረሳም" ወይም "እግዚአብሔር በእርግጥ እያንዳንዷን ድንቢጥ እንኳን አይረሳም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ እን ምፀት የሚሉትን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "እግዚአብሔር በራሳችሁ ላይ ስንት ፀጉር እንዳለ እንኳን ያውቃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ለፍርሃቱ ምክንያት የሚሆነው ነገር አልተገለጸም፡፡ ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) "በሚደርስባችሁ ነገር አትፍሩ" ወይም 2) "ስለዚህ ሊጎዷችሁ የሚችሉ ሰዎችን እትፍሩ፡፡"
"እናንተ ለእግዚአብሔር ከብዙ ድንቢጦች ይልቅ ዋጋ አላችሁ"
ኢየሱስ ወደ አዲስ ርዕስ ለመግባት፣ በዚህ ሁኔታ ስለ ንስሃ ለማስተማር አድማጮቹን ዳግም እንዲህ ይላቸዋል፡፡
የሚመሰከረው ነገር በግልጽ ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ስለ እኔ ለሌሎች የሚመሰክር እርሱ የእኔ ደቀ መዝሙር ነው" ወይም "ለእኔ ታዛዥ መሆኑን ለመናገር አሻፈረኝ የሚል፣ እርሱ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ የሚናገረው ስለ ራሱ ነው፡፡ "እኔ፣ የሰው ልጅ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡
"በሰዎች ፊት የሚክደኝ እርሱ፡፡" የተደረገው ክህደት ምን እንደሆነ ግልጽ ሊደረግ ይችላል፡፡ "የእኔ ደቀ መዝሙር መሆኑን በሌሎች ፊት እውቅና ለምጠት ያልፈቀደ" ወይም "ለእኔ ታዛዥ መሆኑን ለመናገር ያልፈቀደ እርሱ" (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
"ተቀባይነት አያገኝም፡፡" ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "የሰው ልጅ እርሱን ይክደዋል" ወይም "የእኔ ደቀ መዝሙር አይደለም እላለሁ/እክደዋለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"ስለ ሰው ልጅ ክፉ ነገር የሚናገር ሁሉ"
"ይቅርታ ይቀበላል፡፡" ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "እግዚአብሔር ይምረዋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"በመንፈስ ቅዱስ ላይ ክፉ የሚናገር"
ይህ በአድራጊ ግስ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ነገር ግን እርሱ… እርሱን እግዚአብሔር ይቅር አይለውም" ወይም "ነገር ግን እርሱ… እግዚአብሔር እርሱን ለዘለዓለም ጥፋተኛ ያደርገዋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ እና ምፀት የሚሉትን ይመልከቱ)
እነርሱን ወደ ፍርድ ማን እንደሚያቀርባቸው አልተገለጸም
"በሀይማኖት መሪዎች ፊት ለጥያቄ ወደ ሸንጎ ሲያቀርቧችሁ"
ይህንን በአንድ ዐረፍተ ነገር ማጣመር አስፈላጊ ሊሆን ይችላል፡፡ "በአገሪቱ አቅም/ሀይል ያላቸው ሌሎች ሰዎች"
"በዚያን ጊዜ" ወይም "ከዚያም"
ይህ በኢየሱስ ትምህርት መሃል ጣልቃ የገባ ድርጊት ነው፡፡ አንድ ሰው ኢየሱስን አንድ ነገር እንዲያደርግ ይጠይቀውል እርሱም ለሰውየው መልስ ይሰጠዋል፡፡
በዚያ ባህል ውስጥ፣ ብዙውን ጊዜ አባት ከሞተ በኋላ ውርስ ይተላለፋል፡፡ የተናጋሪው ሰው አባት መሞቱን ማረጋገጥ ሊያስፈልግ ይችላል፡፡ "አሁን አባታችን ስለ ሞተ ድርሻዬን ከሀብቱ አካፍለኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ለዚህ ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ይህ እንግዳ የሆነን ለማመልከት የሚውል ነው፤ ወይም 2) ኢየሱስ ሰውየውን እየገሰጸው ነው፡፡ የእናንተ ቋንቋ ከእነዚህ በአንዱ መንገዶች በአንዱ ሰዎችን ሊገልጽ የሚችልበት መንገድ ሊኖረው ይችላል፡፡ አንዳንዶች ይህን ቃል ከነጭርሱ ሳይተረጉሙት ይቀራሉ፡፡
ኢየሱስ ጥያቄውን የተጠቀመበት ሰውየውን ለመገሰጽ ነው፡፡ አንዳንድ ቋንቋዎች "አንተ" ወይም "የአንተ" ለሚለው ብዙ ቁጥርን ይጠቀማሉ፡፡ "እኔ የእናንተ ዳኛ ወይም ፈራጅ አይደለሁም፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ስፍራ "እነርሱ" የሚለው ቃል ምናልባት በዚያ የተሰበሰበውን ሕዝብ ሁሉ ሊያመለክት ይችላል፡፡ "ኢየሱስ በዚያ ለተሰበሰቡት እንዲህ አላቸው"
"ከማናቸውም አይነት ራስ ወዳድነት ተጠበቁ፡፡" "ከአፍቅሮተ ንዋይ ራሳችሁን አርቁ" ወይም "የንዋይ ፍቅር እንዳይገዛችሁ ራሳችሁን ጠብቁ"
ይህ እውነታን የሚያንጸባርቅ አጠቃለይ ሀሳብ ነው፡፡ አንደን ሰው ለይቶ አያመለክትም፡፡ አንዳንድ ቋንቋዎች ይህን የሚገልጹበት መንገድ አላቸው፡፡
"ምንም ያህል ሀብት ያለው መሆኑ" ወይም "የቱንም ያህል ንብረት ይኑረው"
ኢየሱስ በምሳሌ ትምህርቱን ማስተማሩን ቀጠለ፡፡ (ግብረ ገባዊ ምሳሌ የሚለውን ይመልከቱ)
ምናልባት ኢየሱስ እሰከዚህም ድረስ ለተሰበሰበው ሕዝብ በሙሉ እየተናገረ ነበር፡፡
"በጣም ጥሩ አዝነራ ሰጠ"
ይህ ጥያቄ የሚያንጸባርቀው ሰውየው ምን ማድረግ እንዳለበት በውስጡ ያስብ የነበረውን ነው፡፡ "ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላውቅም፣ ምክንያቱም ሰብሌን ሁሉ የማከማችበት በቂ ስፍራ የለኝም!" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
ገበሬዎች የሰበሰቡትን አዝመራ የሚያከማቹበት
ሀብት
ለራሴ እንዲህ እላለሁ፣ ‘ለአመታት የሚበቃ…አለኝ፡፡ እርፍ ልበል… ደስ ይበለኝ፡፡'" ወይም "ለራሴ እንዲህ እላለሁ ለአመታት የሚበቃ አለኝ… ስለዚህ ማረፍ እችላለሁ…ደስ ይበለኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/የነገሩን ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ በምሳሌ ማስተማሩን ሲጨርስ እግዚአብሔር እንዴት ለባለጸጋው ሰው ምላሽ እንደጠቀሰ ይጠቅሳል፡፡
"ነፍስ" የአንድን ሰው ሕይወት ያመለክታል፡፡ "ዛሬ ምሽት ትሞታለህ" ወይም "ዛሬ ምሽት ነፍስህን ከአንተ እወስዳታለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዩፊሚዝም/ የማያስደስትን ቃል ሻል ባለ ቃል መተካት እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)
"አንተ ያከማቸኸው ለማን ይሆናል?" ወይም "አንተ የሰበሰብከው ለማን ይሆናል?" እግዚአብሔር ይህንን ጥያቄ የተጠቀመበት ሰውየው የሰበሰባቸው ነገሮች የእርሱ እንደማይሆኑ እንዲረዳ ለማድረግ ነው፡፡ "አንተ የሰበሰብካቸው ነገሮች የሌላ ሰው ይሆናሉ!" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
"ዋጋ ያላቸውን ነገሮች ማከማቸት"
ጊዜውን እና ሃብቱን እግዚአብሔር ዋጋ ለሚሰጣቸው ነገሮች አልተጠቀመበትም
ኢየሱስ በተሰበሰበው ሕዝብ ፊት ደቀ መዛሙርቱን ማስተማሩን ቀጠለ፡፡
"በዚህም ምክንያት" ወይም "ይህ ታሪክ ከሚያስተምረው የተነሳ"
"እኔ አስፋላጊ የሆነ ነገር ልነግራችሁ እፈልጋለሁ" ወይም "ይህንን የምነግራችሁን ነገር በጥንቃቄ ልትሰሙ ይገባል"
"ስለ ሕይወታችሁ እና ስለምትበሉት" ወይም "ለሰውነታችሁ ስለምትለብሱት ልብስ"
ይህ በአጠቃላይ ስለ እሴት የሚነገር ሀሳብ ነው፡፡ "ሕይወት ከምትመገቡት ምግብ ይልቅ ይበልጥ ጠቃሚ ነው"
"ሰውነታችሁ ከምትለብሱት ልብስ ይልቅ ይበልጥ ጠቃሚ ነው"
"አበቦች እንዴት እንደሚያድጉ አስተውሉ"
ሊሊ አበቦች በሜዳ የሚያድጉ ውብ ተክሎች ናቸው፡፡ በቋንቋችሁ እነዚህን የአበባ አይነቶች የምትገልጹበት መንገድ ከሌለ እነዚህን አበቦች የሚመስሉ የሌሎችን አበቦች ስያሜ መጠቀም ትችላላችሁ ወይም "አበቦች" ብላችሁ መተርጎም ትችላላችሁ፡፡ (የማይታወቁትን መተረጎም የሚለውን ይመልከቱ)
ክርን ወይም ፈትልን ለልብስነት ማዘጋጀት "መፍተል" ይባላል፡፡ ይህንን ይበልጥ ግልጽ ማድረግ ሊያስፈልግ ይችላል፡፡ "እነርሱ ልብስ ለማበጀት አይፈትሉም" ወይም "እነርሱ የስፍ ክር አያዘጋጁም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
"ታላቅ ሀብት የነበረው፣ ሰሎሞን" ወይም "ውብ ልብሶችን የለበሰው፣ ሰሎሞን"
"ምን እንበላለን ምን እንጠጣለን ብላችሁ አትጨነቁ" ወይም "ብዙ ስለ መብላት እና መጠጣት አትጨነቁ
እዚህ ስፍራ "ሕዝብ/አገር" የሚለው የሚያመለክተው "የማያምኑትን" ነው፡፡ "የሌሎች አገራት ሰዎች ሁሉ" ወይም "በዓለም የሚገኙ የማያምኑ ሁሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ለእግዚአብሔር የተሰጠ ዋና ማዕረግ ነው፡፡(ልጅ እና አባት የሚሉትን መተረረጎም የሚለውን ይመልከቱ)
x
እነርሱ የተቀበሉትን መግለጹ አስፈላጊ ሊሆን ይችላል፡፡ "ከሽያጭ ካገኛችሁት ለደሆች ስጡ" (ኢሊፕሲስ- የተተወ/የተዘለለ የሚለውን ይመልከቱ)
በሰማያት ከረጢት/የገንዘብ ቦርሳ እና ሀብት የሚሉት ተመሳሳይ ነገሮች ናቸው፡፡ እነዚህ ሁለቱም ነገሮች በሰማያት የእግዚአብሔርን በረከት ይወክላሉ፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ለድሆች በመስጠት የሚገኝ ነው፡፡ "በዚህ መንገድ ለራሳችሁ በሰማይ ታዘጋጃላችሁ"
"ቀዳዳ የማይኖረው/የማይቀደድ የገንዘብ ቦርሳ/ ከረጢት"
"የማይጠፋ" ወይም "እየመነመነ/ እያደር እያነሰ የማይሄድ"
"ሌቦች የማይደርሱበት"
"ብል የማይበላው"
"ብል" ጨርቅን እየቀደደ የሚበላ ትንሽ ነፍሳት ነው፡፡ ምናልባት እንደ ጉንዳን ወይም ምስጥ የመሰሉ ሌሎች ነፍሳትን መጠቀም ሊያስፈልጋችሁ ይችላል፡፡
"ልባችሁ ሃብታችሁ በተጠራቀመበት በዚያ ላይ ያተኩራል"
እዚህ ስፍራ "ልብ" የሚያመለክተው የሰውን አሳተሳሰብ ነው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ግብረገባዊ ምሳሌ መናገር ጀመረ፡፡ (ግብረገባዊ ምሳሌ የሚለውን ይመልከቱ)
ሰዎች ረጅም ልብስ ይለብሱ ነበር፡፡ በሚሰሩበት ወቅት እንዳያስቸግራቸው በቀበትዋቸው ያሥራሉ፡፡ "ልብሳችሁን በአጭር ታጥቃችሁ ለማገልገል ተዘጋጁ" ወይም "ለብሳችሁ ለማገልገል ተዘጋጁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "መብራታችሁ ይብራ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን አገልጋዮች የጌታቸውን መመለስ በሚጠባበቁበት መንገድ የእርሱን መመለስ እንዲጠብቁ ያዛቸዋል፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
"እንዴት ለእነርሱ መልካም ይሆናል"
"እርሱ በሚመለስበት ጊዜ ጌታቸውን ሲጠበቁት የሚያገኛቸው" ወይም "ጌታቸው በሚመለስበት ጊዜ ዝግጁ የሆኑ"
አገላጋዮቹ ታማኞች ስለነበሩ እና ጌታቸውን ለማገልገል ዝግጁ ስለነበሩ፣ አሁን ጌታቸው እነርሱን በማገልጋል ዋጋቸውን ይከፍላቸዋል/ይሸልማቸዋል፡፡
ሁለተኛው ሰዓት ከምሽቱ ሶስት ሰዓት እስከ እኩለ ሌሊት ያለው ነው፡፡ "በውድቅት ሌሊት" ወይም "ከእኩለ ለሊት አስቀድሞ"
ሶስተኛው ሰዓት ከእኩለሌሊት እስከ ሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ያለው ነው፡፡ "ወይም ሌሊት ዘግይቶ ቢመጣም እንኳን"
"መቼ እንደሆነ ቢያውቅ"
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ሌባ ቆፍሮ ወደ ቤቱ እንዲገባ ባልተወም/ዝም ብሎ ባላየ/ ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
በሰው ልጅ እና በሌባ መሃል ያለው ብቸኛው መመሳሰል የትኛቸውም መቼ እንደሚመጡ ሰዎች አለማወቃቸው በመሆኑ ሁሌም ዝግጁ መሆን ይገባቸዋል፡፡
"ምን ጊዜ እንደሆነ ጊዜውን አታውቁም"
ኢየሱስ ስለ ራሱ እየተናገረ ነው፡፡ "እኔ፣ የሰው ልጅ መቼ እንደምመጣ"
በቁጥር 42 ኢየሱስ ሌላ ግብረገባዊ ምሳሌ መናገር ይጀምራል፡፡
በቁጥር 41፣ ጴጥሮስ ስለ ቀደመው ምሳሌ ሲጠይቅ በታሪኩ ፍሰት መቆሚያ ይፈጠራል፡፡
ኢየሱስ የጴጥሮስን ጥያቄ በተዘዋዋሪ ለመመለስ ጥያቄ ይጠቀማል፡፡ ታማኝ አስተዳዳሪ መሆን የሚፈልጉ ምሳሌው ስለ እነርሱ እንደሆነ እንዲረዱ ይጠብቃል ፡፡ "ትክክለኛው ጊዜ…ለሆኑ ሁሉ ይህን ተናግሪያለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ አገልጋዮች እንዴት በታማኝነት የጌታቸውን መመለስ መጠበቅ እንዳለባቸው ሌላ ምሳሌ ይናገራል፡፡ (ግብረገባዊ ምሳሌዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የሚያመለክተው ጌታው በሌሎች አገልጋዮች ላይ ሀላፊ ያደረገውን አገላጋይ ነው
እዚህ ስፍራ "ልብ" ለአንድ ሰው አስተሳሰብ ወይም ውስጣዊ ማንነት ሜቶኖሚ/ ነው፡፡ "በውስጡ እንዲህ ብሎ ቢያስብ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
"አለቃዬ በቶሎ አይመለስም"
እዚህ ስፍራ "ወንድ እና ሴቶች አገልጋዮች" ተብለው የተተረጎሙት ቃላት "ወንድ ልጆች" እና "ልጃገረዶች" ተብለው ተተርጉመዋል፡፡ ይህ አገልጋዮቹ ወጣቶች እንደነበሩ ወይም በጌታቸው ዘንድ ተወዳጆች እንደነበሩ ሊያመለክት ይችላል፡፡
"ቀን" እና "ሰዓት" ከእስከ ያለውን ማናቸውንም ጊዜ ሲያመለክት፣ "በስተቀር" እና "ያውቃል" የሚሉት ቃላትም ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው፤ ስለዚህም እዚህ ስፍራ ሁለቱ ሀረጎች፣ ለአገላጋዮቹ የጌታቸው መምጣት ፍጹም በድንገት እንደሚሆን ትኩረት ለመስጠት በንጽጽር የቀረቡ ናቸው፡፡ ሆኖም፣ የእናተ ቋንቋ "ማወቅ" እና "መጠባበቅ" ወይም "ቀን" እና "ሰዓት" ለሚሉት ቃላት ልዩነት የሌለው ካልሆነ በስተቀር ሀረጋቱ በአንድነት ተጣምረው መቅረብ የለባቸውም፡፡ "አገልያዩ እርሱን በማይጠባበቅበት ጊዜ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ከጽንፍ ጽንፍ እና ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚሉትን ይመልከቱ)
ለዚህ ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ይህ ጌታው በአገልጋዩ ላይ የሚያደርሰው ከባድ ቅጣት ተጋኖ የተገለጸበት ነው፣ ወይም 2) ይህ አገልጋዩ የሚደርስበት የቅጣት ሁኔታ የሚገደል እና የሚቀበር መሆኑን ይገልጻል፡፡ (ኩሸት እና አጠቃላይ አስተያየት የሚሉት ይመልከቱ)
x
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ማስተማር ቀጥሏል፡፡
"በምድር ላይ እሳት ለመጣል መጥቻለሁ" ወይም "በምድር ላይ እሳት ለመለኮስ መጥቻለሁ፡፡" ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ኢየሱስ የመጣው ሰዎችን ለመዳኘት ነው ወይም 2) ኢየሱስ የመጣው ሰዎችን ለማንጻት ነው፣ ወይም 3) ኢየሱስ የመጣው በሰዎች መሃል ልዩነትን ለማምጣት ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ አጋኖ የሚያጎላው፣ እርሱ ምን ያህል ይህ ሊሆን እንደፈለገ ነው፡፡ "አስቀድሞ ነድዶ ቢሆን በጣም በወደድኩ" ወይም "አስቀድሞ ጀምሮ ቢሆን ኖሮ እወድ ነበር" (ቃለ አጋኖዎች የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ስፍራ "ጥምቀት" የሚያመለክተው ኢየሱስ ሊቀበል ያለውን መከራ ነው፡፡ በጥምቀት ውሃ የሰውን ሁለመና እንደሚሸፍን፣ መከራ ኢየሱስን ያጥለቀልቀዋል፡፡ "በክፍተኛ የመከራ ጥምቀት ውስጥ ማለፍ ይኖርብኛል" ወይም "ሰው ሲጠመቅ በውሃ ውስጥ እንደሚሸፈን በመከራ መጥለቅለቅ ይኖርብኛል" (ዘይቤያዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)
"ነገር ግን" የሚለው ቃል የዋለው እርሱ በመከራ ውስጥ ከማለፉ አስቀድሞ በምድር ላይ እሳት ሊጥል አለመቻሉን ለማሳየት ነው፡፡
ይህ አጋኖ የሚያጎላው እርሱ ምን ያህል ተጨንቆ እንደነበረ ነው፡፡ "እጅግ ተጨንቄያለሁ፣ ይህን የመከራ ጥምቀት እስክፈጽም ድረስ ይኸው ይሆናል" (ቃለ አጋኖዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ የተሳሳተ መረዳታቸውን እንዲያርሙ እንደሚያደርግ ሊያሳውቃቸው ጥያቄ ያነሳል፡፡ በሁለተኛው ዐረፍተ ነገር የተተወውን "እኔ የመጣሁት" የሚሉ ቃላት መጨመር ሊያስፈልጋችሁ ይችላል፡፡ "በምድር ላይ ሰላም ለማምጣት የመጣሁ ይመስላችኋል፣ ነገር ግን እላችኋለሁ ለዚህ አልመጣሁም፡፡ ይልቁንም፣ መለያየትን ለማምጣት መጥቻለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
"ጠላትነት" ወይም "አለመስማማት"
ይህ በአንድ ቤተሰብ ውስጥ እንኳን ለሚኖረው የመከፋፈል አይነት ምሳሌ ነው
ይህ ሰዎችን እንደሚያመለክት መግለጽ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡ "በአንድ ቤት ውስጥ አምስት ሰዎች ይኖራሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (የተተወ/የተዘለለ የሚለውን ይመልከቱ)
"ይቀዋወማል…ይቀዋወማል…ይቀዋወማል…ይቀዋወማል…ይቀዋወማል…ይቀዋወማል..ይቀዋወማል…ይቀዋወማል"
ኢየሱስ ለተሰበሰበው ሕዝብ መናገር ይጀምራል፡፡
ይህ ሁኔታ በተለምዶ በእሥራኤል ዝናብ ይመጣል ማለት ነው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
"ዝናብ ይመጣል" ወይም "ሊዘንብ ነው"
ይህ ሁኔታ በተለምዶ በእሥራኤል ሞቃታማ የአየር ንብረት ይመጣል ማለት ነው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
"ምድር እና ሰማይ"
ኢየሱስ ይህንን ጥያቄ ያነሳው የተሰበሰበውን ሕዝብ ለመገሰጽ ነው፡፡ ኢየሱስ ይህን ጥያቄ የተጠቀመው እነርሱን ለማሳመን ነው፡፡ ይህ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "ወቅቱን መተረጎም መቻል ይኖርባችኋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ጥያቄውን ያነሳው የተሰበሰበውን ሕዝብ ለመገሰጽ ነው፡፡ ይህ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "እናንተ ራሳችሁ ትክክለኛ የሆነውን መለየት ይኖርባችኋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
"በራሳችሁ ተነሳሽነት"
ኢየሱስ የተሰበሰበውን ሕዝብ ለማስተማር መላምታዊ ሁኔታ ይጠቀማል፡፡ የእርሱ ትምህርት፣ ማቃለል የሚችሉትን ነገር ዳኛ ፊት ሳይቀርቡ ችግራቸውን እንዲያቃልሉ ማስተማር ነው፡፡ ይህን ግልጽ ለማድረግ መሆን የማይገባውን መሆን እንደማይገባው በግለጽ ደግሞ መጻፍ ይቻላል፡፡ "ማድረግ የሚገባችሁ ከሆነ…የመጨረሻዋን ገንዘብ
x
1 በዚያን ጊዜ አንዳንድ ሰዎች ወደ ኢየሱስ መጥተው፣ የገሊላ ሰዎች ለእግዚአብሔር መሥዋዕት በሚያቀርቡበት ጊዜ፣ ጲላጦስ ስለ ገደላቸውና ደማቸውንም ከመሥዋዕታቸው ጋር ስላደባለቀባቸው ሰዎች ነገሩት፡፡ 2 ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፤ "እነዚያ የገሊላ ሰዎች ይህ ሁሉ የደረሰባቸው በዙሪያቸው ካሉት ከሌሎች የገሊላ ሰዎች ይልቅ ኅጢአተኞች ስለ ነበሩ ነውን? 3 አይደለም፤ እናንተም ንስሓ ካልገባችሁ እንዲሁ ትጠፋላችሁ ። 4 ወይም በሰሊሆም ግንብ ተደርምሶባቸው የሞቱ ዐሥራ ስምንት ሰዎች በኢየሩሳሌም ዙሪያ ካሉ ሰዎች ይልቅ ኃጢአተኞች ስለ ነበሩ ነውን? 5 አይደለም፤ ሁላችሁም ንስሓ ባትገቡ ትጠፋላችሁ።" 6 ኢየሱስ ይህን ምሳሌ ተናገረ፤ "አንድ ሰው በወይን አትክልት ቦታው የበለስ ዛፍ ተከለ፤ ፍሬዋንም ፈልጎ ወደ በለሲቱ መጣ፤ ነገር ግን ምንም ፍሬ አላገኘባትም። 7 እርሱም ለአትክልተኛው እንዲህ አለው፤ "ተመልከት! ሦስት ዓመት ሙሉ ፍሬ ፈልጌ ወደ በለሲቱ መጣሁ፤ ግን ምንም ፍሬ አላገኘሁባትም፡፡ ቊረጣት ስለምን መሬትን ታበላሻለች።" 8 አትክልተኛውም መልሰና እንዲህ አለ፣ "ለዚህ ዓመት ተዋት ዙሪያዋን ኮትኩቼ ማዳበሪያ አደርግላትና 9 በሚቀጥለው ዓመት ታፈራ ይሆናል፤ ባታፈራ ግን ቊረጣት።" 10 ኢየሱስም በሰንበት ቀን በአንዱ ምኲራብ እያስተማረ ነበር። 11 ለዐሥራ ስምንት ዓመት ርኩስ መንፈስ ያጐበጣት አንዲት ሴት በዚያ ነበረች፡፡ እርስዋም ከመጒበጧ የተነሣ ቀና ብላ መቆም አትችልም ነበር፡፡ 12 ኢየሱስም ባያት ጊዜ ጠራትና፣ "ተነሺና ከበሽታሽ ተፈወሺ" አላት። 13 በእጁ ዳሰሳት፣ ወዲያውኑም ቀጥ ብላ ቆመች፤ እግዚአብሔርንም 14 አመሰገነች፡፡ የምኲራቡ አለቃ ግን በሰንበት በመፈወሷ ተቈጣና ለሕዝቡ እንዲህ አለ፤ "ከሳምንቱ ቀኖች ሥራ የሚሠራባቸው ስድስት ቀኖች አሉ፤ ሄዳችሁ በእነዚያ ቀኖች ተፈወሱ እንጂ በሰንበት ቀን አይሆንም አላቸው።" 15 ጌታ እንዲህ ብሎ መለሰለት፤ "እናንት ግብዞች! በሰንበት ቀን ከእናንተ መካከል በሬውን ወይም አህያውን ከታሰረበት በረት አወጥቶ ውኅ የማያጠጣው ማን ነው? 16 ይህች የአብርሃም ዘር የሆነች ለዐሥራ ስምንት ዓመት በሰይጣን ታስራ የኖረች ሴት በሰንበት ቀን ከበሽታዋ መፈታት አይገባትምን?" 17 ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች በተናገረ ጊዜ፣ ይቃወሙት የነበሩ ሁሉ አፈሩ፣ ሕዝቡ ግን በተደረገው ድንቅ ነገር ሁሉ ደስ አላቸው። 18 ከዚያም ኢየሱስ እንዲህ አለ፤ "የእግዚአብሔር መንግሥት በምን ትመሰላለች? ከምንስ ጋር አነጸጽራታለሁ? 19 አንድ ሰው የሰናፍጭ ዘር በአትክልት ቦታው እንደተከላት ዛፍዋም አድጋ፣ ወፎች በቅርንጫፎችዋ ላይ ጎጆአቸውን ሠርተው ማረፊያ ያደረጉባት ዛፍ ትመሰላለች።" 20 እንደ ገናም እንዲህ አለ፤ "የእግዚአብሔርን መንግሥት በምን ላነጻጽራት እችላለሁ? 21 የእግዚአብሔር መንግሥት አንዲት ሴት ሊጡን ሁሉ እስኪያቦካ ድረስ በሶሦስት መስፈሪያ ዱቄት ውስጥ የሰወረችውን እርሾ ትመስላለች።" 22 ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ ሳለ በየከተማውና በየገጠሩ እያስተማረ ያልፍ ነበር፡፡ 23 አንድ ሰው፣ "ጌታ ሆይ፤ የሚድኑት ጥቂት ሰዎች ብቻ ናቸውን?" ብሎ ጠየቀው፡፡ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፤ 24 "በጠባብዋ በር ለመግባት ታገሉ፣ ብዙዎች በዚህች በር ሊገቡ ይሞክራሉ ነገር ግን ሊገቡባት አይችሉም። 25 የቤቱ ጌታ በሩን ይዘጋል፤ እናንተም በደጅ ቆማችሁ፤ አንኳኩታችሁ፣ 'ጌታ ሆይ፤ ጌታ ሆይ፤ እንድንገባ ክፈትልን' ትላላችሁ፡፡ እርሱ መልሶ 'ከየት ነው የመጣችሁት? እኔ አላውቃችሁም' ይላችኋል፡፡ 26 ከዚያም እናንተ፣ 'ጌታ ሆይ፣ ከአንተ ጋር አብረን በልተናል፤ አብረንም ጠጥተናል፤ በአደባባዮቻችንም አስተምረሃል' ትላላችሁ፡፡ 27 እርሱ ግን እንዲህ ይመልሳል፤ 'ከየት እንደ መጣችሁ አላውቅም ፤ እናንተ ዐመፀኞች ከእኔ ራቁ እላችኋለሁ፡፡' 28 በእግዚአብሔር መንግሥት አብርሃምን፤ይስሐቅን፤ ያዕቆብን፤ ነቢያትንም በምታዩበት ጊዜ፤ እናንተ ግን በውጪ ትጣላላችሁ ከዚያም ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል፡፡ 29 ብዙ ሰዎች ከምሥራቅና ከምዕራብ፤ ከሰሜንና ከደቡብ መጥተው በእግዚአብሔር መንግሥት በማዕድ ተቀምጠው ይደሰታሉ፡፡ 30 ይህንም እወቁ ኋለኞች ፊተኞች፤ ፊተኞችም ኋለኞች ይሆናሉ፡፡" 31 ከዚያ በኋላ፣ አንዳንድ ፈሪሳውያን ወደ እርሱ ቀርበው፣ "ሄሮድስ ሊገድልህ ይፈልጋልና ከዚህ ወጥተህ ወደ ሌላ ስፍራ ሂድ" አሉት፡፡ 32 ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፤ "ሂዱና ለዚያ ቀበሮ፣ 'ዛሬና ነገ አጋንንትን አወጣለሁ፤ በሽታኞችን እፈውሳለሁ፤ በሦስተኛም ቀን ሥራዬን እፈጽማለሁ' ይላል በሉት" 33 ይሁን እንጂ ዛሬና ነገ ከዚያም በኋላ ነቢይ ከኢየሩሳሌም በቀር በሌላ ስፍራ መሞት ስለሌበት ወደ ኢየሩሳሌም መንገዴን መቀጠል አለብኝ" አለ። 34 አንቺ ኢየሩሳሌም! ኢየሩሳሌም ሆይ! ነቢያትን የምትገድዪ፤ መልእክተኞችሽንም የምትወግሪ ነሽ፡፡ ዶሮ ጫጩቶችዋን ከክንፎችዋ ሥር እንደምትሰበስብ እኔም ልጆችሽን ለመሰብሰብ ስንት ጊዜ ፈለግሁ፡፡ እናንተ ግን አልፈለጋችሁም፡፡ 35 እነሆ፣ ቤታችሁ ባዶ ሆኖ ቀርቶአል፡፡ እላችኋለሁ፣ እናንተ 'በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረከ ነው' እስከምትሉ ድረስ አታዩኝም፡፡"
ኢየሱስ እስከ አሁን ድረስ ለተሰበሰበው ሕዝብ እየተናገረ ነው፡፡ ከተሰበሰበው ህስብ መሃል አንዳንዱ እርሱን ስጠይቀው እርሱም ምላሽ መስጠት ጀመረ፡፡ ይህ በሉቃስ 12፡1 ላይ የጀመረውን ታሪክ ይቀጥላል፡፡
ይህ ሀረግ፣ ኢየሱስ የተሰበሰበውን ሕዝብ በሚያስተምርበት ወቅት እሰከ ምዕራፍ 12 መጨረሻ ድረስ ያለውን ትዕይንት ያያይዛል፡፡
እዚህ ስፍራ "ደም" የሚያመለክተው የገሊላ ሰዎችን ሞት ነው፡፡ ምናልባት እነርሱ የተገደሉት መስዋዕታቸውን በሚያቀርቡበት ጊዜ ሊሆን ይችላል፡፡ በዩዲቢ ውስጥ እንደቀረበው ብልጽ ሊደረግ ይችላል፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ምናልባት ጲላጦስ ህዝቡን የገደለው ራሱ ሳይሆን ወታደሮችን ልኮ ሊሆን ይችላል፡፡ "እንስሳትን መስዋዕት በማቅረብ ላይ እያሉ የጲላጦስ ወታደሮች የገደሏቸው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
"እነዚህ ገሊላውያን ይበልጥ በ…መንገድ ኃጢአተኞች ነበሩን? አይደለም፣ እኔ እላችኋለሁ" ወይም "ይህ እነዚህ ገሊላውያን ይበልጥ በ…መንገድ ኃጢአተኞች እንደሆኑ ያረጋግጣልን? አይደለም፣ እኔ እላችኋለሁ" ኢየሱስ ይህንን ጥያቄ የተጠቀመበት የህዝቡን መረዳት ለመገዳደር ነው፡፡ "እናንተ እነዚህ ገሊላውያን በ…መንገድ ይበልጥ ኃጢአተኞች እንደሆኑ ታስባላችሁ ነገር ግን አልነበሩም" ወይም "እነዚህ ገሊላውያን በ…መንገድ ይበልጥ ኃጢአተኞች እንደሆኑ አታስቡ" (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ስፍራ "እኔ እላችኋለሁ" የሚለው ትኩረት የሚሰጠው "አይደለም" የሚለውን ነው፡፡ "በእርግጥ እነርሱ ይበልጥ ኃጢአተኞች አልነበሩም" ወይም "መከራ ስለደረሰባቸው ይህ ይበልጥ ኃጢአተኛ መሆናቸው ያረጋግጣል ብላችሁ ማሰባችሁ ስህተት ነው"
"ሁላችሁም ደግሞ ትሞታላችሁ፡፡" "በተመሳሳይ መንገድ" የሚለው ሀረግ ተመሳሳይ ነገር ይደርስባቸዋል ማለት እንጂ በተመሳሳይ መልክ ይሞታሉ ማለት አይደለም፡፡
መሞት
ይህ ኢየሱስ መከራ ስለ ደረሰባቸው ሰዎች የሰጠው ሁለተኛ ምሳሌ ነው፡፡ "ወይም እነዚያን ተመልከቱ" ወይም "ስለ እነዚያ አስቡ"
"18 ሰዎች" (ቁጥሮች የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በኢየሩሳሌም ውስጥ የሚገኝ ስፍራ ስም ነው፡፡ (ስሞች እንዴት ይተረጎማሉ የሚለውን ይመልከቱ)
"ይህ እነርሱ በኢየሩሳሌም… ይበልጥ ኃጢአተኞች እንደሆኑ ያረጋግጣልን? እኔ እላችኋለሁ፣ አይደለም፡፡" ኢየሱስ ይህንን ጥያቄ የተጠቀመበት የህዝቡን መረዳት ለመገዳደር ነው፡፡ "እነርሱ በኢየሩሳሌም…ይበልጥ ኃጢአተኛ እንደሆኑ ታስባላችሁ፣ እኔ ግን አልነበሩም እላለሁ" ወይም "እነርሱ በኢየሩሳሌም… ይበልጥ ኃጢአተኞች ነበሩ ብላችሁ ማሰብ የለባችሁም እላለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
x
ኢየሱስ ለተሰበሰበው ሕዝብ የመጨረሻ ሃሳቡን ለማብራራት ግብረገባዊ ምሳሌ መናገር ጀመረ፣ "ነገር ግን ንስሃ ባትገቡ፣ እናንተ ሁላችሁም ደግሞ ትጠፋላችሁ፡፡" (ግብረገባዊ ምሳሌ የሚለውን ይመልከቱ)
የወይን ተክሉ ባለቤት በወይን እርሻው ውስጥ ሌላ ሰው የበለስ ዛፍ ተከለበት፡፡
ሰውየው ጥያቄውን የተጠቀመበት ዛፏ ጥቅም እንደማትሰጥ እና አትክልተኛው ሊቆርጣት እንደሚገባ ትኩረት ለመስጠት ነው፡፡ "መሬቱን እንድታበላሽ አትፍቀድ/ መሬቱን ታበላሽ ዘንድ አትተዋት፡፡" (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ግብረገባዊ ምሳሌውን መናገሩን ጨረሰ፡፡ ይህ በሉቃስ 12፡1 የተጀመረው ታሪክ መጨረሻ ነው፡፡
"በዛፊቱ ላይ አንዳች አታድርግ" ወይም "አትቁረጣት"
"በአፈሩ ላይ ማዳበሪያ ጨምር፡፡" ማዳበሪያ/ፍግ የእንስሳ ኩበት ነው፡፡ አፈሩ ለተክሎች እና ለዛፍ መልካም እንዲሆን ሰዎች ይህን በመሬት ላይ ይጨምራሉ፡፡ "በላዩ ማዳበሪያ መጨመር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
x
እነዚህ ቁጥሮች ለዚህኛው የታሪኩ ክፍል መቼት እና ወደ ታሪኩ ለምትገባው ሽባ ሴት የመረጃ ዳራ ይሰጣሉ፡፡ (የመረጃ ዳራ የሚለውን ይመልከቱ)
ጸሐፊው ይህንን ቃል የተጠቀመበት የአዱሱን ትዕይንት ጅማሬ ለማመልከት ነው፡፡ (የአዲስ ትዕይንት መግቢያ የሚለውን ይመልከቱ)
"በሰንበት ዕለት፡፡" አንዳንድ ቋንቋዎች "ሰንበት" ይላሉ፤ ምክንያቱም የትኛው የተለየ የሰንበት ዕለት እንደነበር አናውቅም፡፡
"አንቺ ሴት፣ ከድካምሽ ተፈውሰሻል፡፡" ይህ "አንቺ ሴት፣ ከድካምሽ ፈውሼሻለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው በአድራጊ ግስ ሊገለጽ ይችላል፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህን በመናገር፣ ኢየሱስ እርሷን ፈወሳት፡፡ ይህ ነገር እንዲሆን ማድረጉን፣ ወይም ማዘዙን በሚያሳይ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "አንቺ ሴት፣ አሁን እኔ ከድካምሽ ፈውሼሻለሁ" ወይም "አንቺ ሴት፣ ከድካምሽ ነጻ ሁኚ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሃሳቦች- ሌላ ጥቅሞች የሚለውን ይመልከቱ)
"እርሱ ነካት"
ይህ አድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ቀና ብላ ቆመች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"በአንድ የሰንበት ዕለት፡፡" አንዳንድ ቋንቋዎች "በሰንበት" ይላሉ፤ ምክንያቱም የትኛው የተለየ የሰንበት ዕለት እንደ ነበር አናውቅም፡፡
"ጌታ ለሸንጎ መሪው ምላሽ ሰጠ"
ኢየሱስ በቀጥታ ከምኩራብ መሪው ጋር ተናገረ፣ ነገርግን የብዙ ቁጥሩ ሌሎችንም የሃይማኖት መሪዎች ጭምር ያጠቃልላል፡፡ ይህ ይበልጥ ግልጽ ሊደረግ ይችላል፡፡ "አንተ እና እንንተ የሃይማኖት መሪዎቻችሁ ግብዞች ናችሁ" (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ጥያቄውን የተጠቀመበት አስቀድሞ ስለሚያውቁት ነገር እንዲያስቡበት ለማድረግ ነው፡፡ "ከእናንተ እያንዳንዱ በሬውን ወይም አህያውን በሰንበት ከታሰረበት ፈትቶ ወደ ሚጠጣበት ስፍራ ይወስደዋል፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ ሰዎች ውሃ በመስጠት የሚንከባከቧቸው እንስሳት ናቸው
x
"ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች በሚናገርበት ጊዜ"
"ኢየሱስ ያደርጋቸው የነበሩ አስደናቂ ነገሮች"
ኢየሱስ በምኩራብ ለነበሩ ሰዎች ግብረገባዊ ምሳሌ መናገር ጀመረ፡፡ (ግብረገባዊ ምሳሌ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ሁለትን ጥያቄዎች የተጠቀመባቸው ሊያስተምር ያለውን ነገር ለማስተዋወቅ ነው፡፡ "የእግዚአብሔር መንግሥት ምን እንደምትመስል እነግራችኋለሁ…ከምን ጋር ላነጻጽራት እችላለሁ፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ከቀደመው ጥያቄ ጋር በመሰረቱ ተመሳሳይ ነው፡፡ አንዳንድ ቋንቋዎች ሁለቱንም ጥያቄዎች ሊጠቀሙ ይችላሉ፣ አንዳንዶቹ ደግሞ አንዱን ጥያቄ ብቻ ይጠቀማሉ፡፡(ትይዩ ንጽጽራዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ከሰነፍጭ ጋር ያነጻጽራል፡፡ "የእግዚአብሔር መንግሥት የሰናፍጭን ፍሬ ትመስላለች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ በምኩራብ ለነበሩ ሰዎች መናገሩን ጨረሰ፡፡ ይህ የዚህ ታሪክ ክፍል መጨረሻ ነው፡፡
ኢየሱስ ቀጥሎ ሊያስተምር ያለውን ለማስተዋወቅ ሌላ ጥያቄ ያነሳል፡፡ "ከእግዚአብሔር መንግሥት ጋር ላነጻጽር የምችለውን ሌላ ነገር እነግራችኋለሁ፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ የእግዚአብሔርን መንግሥት በዳቦ ሊጥ ውስጥ ከሚገኝ እርሾ ጋር ያነጻጽራል፡፡ "የእግዚአብሔርን መንግሥት እንደ እርሾ ናት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
ብዙ ሊጥ ለማቡካት በጣም ትንሽ እርሾ ብቻ ያስፈልጋል፡፡ ይህ በዩዲቢ ውስጥ እንደሚገኘው ግልጽ ሊደረግ ይችላል፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
አንድ እጅ/ልኬታ የሚባለው ወደ 13 ኪሎ ግራም የሚጠጋ በመሆኑ፣ይህ ብዙ መጠን ያለው ዱቄት ነው፡፡ የእናንተ ባህል ዱቄትን ለመለካት የሚጠቀምበትን መለኪያ መጠቀም ትችላላችሁ፡፡ "ብዙ መጠን ያለው ዱቄት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡
ኢየሱስ ለጥያቄው ምላሽ የሰጠው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ስለ መግባት ዘይቤያዊ አገላለጽ በመጠቀም ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "እግዚአብሔር የሚያድነው ጥቂት ሰዎችን ብቻ ነውን?" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"በጠባቡ በር ለመግባት ትጉ፡፡" ኢየሱስ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ስለ መግባት የሚናገረው፣ ወደ ቤት እንደሚያስገባ ትንሽ በር አድርጎ ነው፡፡ ኢየሱስ ለሰዎች ስብስብ እንደመናገሩ በዚህ ትእዛዝ ውስጥ "እናንተ" የሚለው ተውላጠ ስም ብዙ ቁጥር ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር እና አንተ የሚለው ተውላተ ስም መልኮች የሚለውን ይመልከቱ)
በሩ ጠባብ መሆኑ የሚያመለክተው በውስጡ ማለፍ አስቸጋሪ መሆኑን ነው፡፡ ይህን ውስንነት በሚያሳይ መንገድ ተርጉሙት፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ለመግባት ከባድ ከመሆኑ የተነሳ፣ መግባት እንደማይችሉ ተጠቁሟል፡፡ ቀጣዩ ሀረግ ከባድነቱን ያብራራል፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ስለ መግባት መናገሩን ቀጥሏል፡፡
"ባለቤቱ ከ…በኋላ"
ይህ በቀደመው ቁጥር ላይ ጠባብ በር ያለውን ቤት ባለቤት ያመለክታል፡፡ ይህ እግዚአብሔርን እንደ እግዚአብሔር መንግሥት ገዢ የሚያቀርብ ዘይቤ ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ለተሰበሰበው ሕዝብ እየተናገረ ነበር፡፡ "እናንተ" የሚለው ተውላጠ ስም ብዙ ቁጥር ነው፡፡ እነርሱ በጠባቡ በር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንደማይገቡ እየተናገረ ነው፡፡ (አንተ የሚለውን ተውላጠ ስም መልኮች ይመልከቱ)
"በሩን ትመታላችሁ፡፡" ይህ የባለቤቱን ትኩረት ለማግኘት የሚደረግ ጥረት ነው፡፡
"ከእኔ ራቁ"
ኢየሱስ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ስለ መግባት መናገሩን ቀጥሏል፡፡ ይህ የዚህ ንግግር መጨረሻ ነው፡፡
እነዚህ ድርጊቶች ታላቅ ጸጸትን እና ሀዘንን የሚያመለክቱ ትዕምርታዊ ድርጊቶች ናቸው፡፡ "ከታላቅ ጸጸታቸው የተነሳ የተከተለ ለቅሶ እና ጥርስ ማፋጨት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ትምዕርታዊ/ምልክታዊ ድርጊት የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ለተሰበሰበው ሕዝብ ወደ ሰማዩ መንግስት እንደማይገቡ አድርጎ መናገሩን ቀጥሏል፡፡
"ነገር ግን እናንተ ራሳችሁ ወደ ውጭ ትጣላላችሁ፡፡" ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ነገር ግን እግዚአብሔር ወደ ውጭ ይጥላችኋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ማለት "ከሁሉም አቅጣጫ፡፡" ማለት ነው፡፡
የእግዚአብሔርን መንግሥት ደስታ እንደ ግብዣ መግለጽ የተለመደ ነበር፡፡ "በእግዚአብሔር መንግሥት ይጋበዛሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
የመጀመሪያ መሆን የሚወክለው አስፈላጊ ወይም የተከበረ መሆንን ነው፡፡ "እጅግ አስፈላጊ ይሆናሉ…የመጨረሻዎቹ ይሆናሉ" ወይም "እግዚአብሔር ያከብራቸዋል…እግዚአብሔር ያሳፍራቸዋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በዚህ የታሪክ ክፍል ቀጣዩ ትዕይንት ነው፡፡ አንዳንድ ፈሪሳውያን ስለ ሄሮድስ ቢነግሩትም ኢየሱስ ግን ወደ ኢየሩሳሌም በመሄድ ላይ ነው፡፡
"ኢየሱስ ንግግሩን እንደጨረሰ ወዲያውኑ"
ይህንን ለኢየሱስ እንደ ተሰጠ ማስጠንቀቅያ ተርጉሙት፡፡ ወደ አንድ ስፍራ እንዲሄድ እና ራሱን እንዲያድን እየመከሩት ነበር፡፡
ሄሮድስ ሰዎች ኢየሱስን እንዲገድሉት ያዛል፡፡ "ሄሮድስ አንተን እንዲገድሉ ወታደሮቹን መላክ ይፈልጋል"
ኢየሱስ ሄሮድስን ቀበሮ ብሎ እየጠራው ነበር፡፡ ቀበሮ ትንሽ የሆነ የዱር ውሻ ነው፡፡ ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ሄሮድስ በፍጹም የሚያስፈራው አልነበረም 2) ሄሮድስ አሳሳች ነበር፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
"የሆነ ሆኖ" ወይም "ሆኖም" ወይም "የሆነው ቢሆንም"
የአይሁድ መሪዎች እግዚአብሔርን እንደሚያገለግሉ ይናገራሉ፡፡ ሆኖም ግን አባቶቻቸው ብዙ የእግዚአብሔርን ነቢያት በኢየሩሳሌም ውስጥ ገድለዋል፣ እናም ኢየሱስ እርሱንም በዚህ እንደሚገድሉት ያውቃል፡፡ "የአይሁድ መሪዎች የእግዚአብሔርን መልዕክተኞች የገደሉት እዚህ ኢየሩሳሌም ውስጥ ነው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ምጸት የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ለፈሪሳውያን ምላሽ መስጠቱን አበቃ፡፡ ይህ የዚህኛው ታረክ ክፍል መጨረሻ ነው፡፡
ኢየሱስ የኢየሩሳሌም ሰዎች በዚያ ሆነው እንደሚሰደሙት አድርጎ ይናገራል፡፡ ኢየሱስ ይህን ሁለት ጊዜ የደገመው ለእነርሱ ምን ያህል እንዳዘነ ለማሳየት ነው፡፡ (ቃለ አጋኖ የሚለውን ይመልከቱ)
ከተማን መናገር እንግዳ ነገር ከሆነ፣ ኢየሱስ በከተማይቱ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን እየተናገረ እንደሆነ ገልጽ ማድረግ ትችላላችሁ፡ "እናንተ ነቢያትን የገደላችሁ እና ወደ እናንተ የተላኩትን በድንጋይ የወገራችሁ ህዝቦች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "እግዚአብሔር ወደ እናንተ የላካቸውን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"እኔ እጅግ አብዝቼ ፈለግሁ፡፡" ይህ ጉልህ ማድረግ እንጂ ጥያቄ አይደለም፡፡
የኢየሩሳሌም ሰዎች የተገለጹት የእርሷ "ልጆች" ተደርገው ነው፡፡ "የአንቺን ሕዝብ ለመሰብሰብ" ወይም "የእየሩሳሉምን ሰዎች ለመሰብሰብ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የሚገልጸው ዶሮ እንዴት ጫጬቶቿን በክንፎችዋ ሸፍና ከጥፋት እንደምትጠብቅ ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ወደፊት በቶሎ ለሚሆን ነገር ትንቢት ነው፡፡ ይህ ማለት እግዚአብሔር የኢየሩሳሌምን ሰዎች መጠበቁን አቁሟል፣ ስለዚህም ጠላት ሊያጠቃቸው እና ሊያባርራቸው ይችላል ማለት ነው፡፡ ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) እግዚአብሔር እነርሱን ይበትናቸዋል፡፡ "እግዚአብሔር ይተዋችኋል" ወይም 2) ከተማቸው ባዶ ትሆናለች፡፡ "ቤታችሁ ወና ይሆናል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
"እንዲህ የምትሉበት ጊዜ እስኪመጣ ድረስ እኔን አታዩኝም" ወይም "በሚቀጥለው ጊዜ እኔን ስታዩ፣ እንዲህ ትላላችሁ"
እዚህ ስፍራ "ስም" የሚለው የሚያመለክተው የጌታን ሀይል እና ስልጣን ነው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
1 በሰንበት ቀን ኢየሱስ ከፈሪሳዊያን አለቆች ወደ እንዱ ቤት እንጀራ ሊበላ በገባ ጊዜ፣ የሚያደርገውን ለማየት በቅርበት ይጠባበቁት ነበር፡፡ 2 በዚያም በእጅና በእግር ዕብጠት የሚሠቃይ አንድ ሰው በኢየሱስ ፊት ነበር። 3 ኢየሱስ የአይሁድ ሕግ ዐዋቂዎችንና ፈሪሳውያንን፣ "በሰንበት ቀን መፈወስ በሕግ ይፈቀዳል ወይስ አይፈቀድም? "ብሎ ጠየቃቸው፡፡ 4 እነርሱ ግን ዝም አሉ፡፡ ኢየሱስ የታመመውን ሰው ይዞ ፈወሰውና አሰናበተው፡፡ 5 ቀጥሎም ኢየሱስ፣ "ከእናንተ ልጅ ወይም በሬ በሰንበት ቀን በጒድጓድ ውስጥ ቢወድቁ ወዲያውኑ የማያወጣቸው ማን ነው?" አላቸው። 6 እነርሱ ለእነዚህ ነገሮች መልስ መስጠት አልቻሉም፡፡ 7 ኢየሱስ በግብዣ ቦታ የከበሬታ ወንበር ለመያዝ ሲሽቀዳደሙ በተመለከት ጊዜ እንዲህ በማለት አንድ ምሳሌ 8 ነገራቸው፤ "አንድ ሰው ወደ ሰርግ ግብዣ ቢጠራህ በመጀመሪያ በከበሬታ ቦታ አትቀመጥ፣ ምናልባት በዚያ ቦታ የሚቀመጥ ከአንተ ይልቅ ክብር የሚሰጠው ሰው ተጋብዞ ይሆናል፡፡ 9 ሁለታችሁንም የጋበዛችሁ ሰው መጥቶ፣ 'ይህን ቦታ ለሌላ ሰው ልቀቅለት' ይልሃል፣ ከዚያም አንተ በሃፍረት ወደ ዝቅተኛ ቦታ ትሄዳለህ፡፡ 10 ነገር ግን ወደ ግብዣ ስትጠራ በዝቅተኛ ቦታ ተቀመጥ፤ አንተን የጋበዘህ ሰው መጥቶ፤ ወዳጄ ሆይ፣ 'ወደ ከፍተኛ ስፍራ መጥተህ ተቀመጥ' ይልሃል፡፡ ከዚያም በተጋባዦቹ ፊት ሁሉ የተከበርህ ትሆናለህ፡፡ 11 ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርግ ዝቅ ዝቅ ይላል፡፡ ራሱንም ዝቅ ዝቅ የሚያደርግ ደግሞ ከፍ ከፍ ይላል፡፡ 12 ኢየሱስ ደግሞ ጋባዡን ሰው ደግሞ እንዲህ አለው፤ "የምሳ ወይም የራት ግብዣ በምታደርግበት ጊዜ መልሰው ይጋብዙኛል በማለት ብድራትን በመፈለግ ወዳጆችህን ወይም ወንድሞችህን ወይም ዘመዶችህን ወይም ሀብታም ጎረቤቶችህን አትጋብዝ፡፡ 13 ነገር ግን ግብዣ በምታደርግበት ጊዜ ድሆችን፣ የአካል ጒዳተኞችን፣ ሽባዎችንና ዐይነ ስውራንን ጥራ፡፡ 14 ይህን በማድረግህ እነርሱ መልሰው ሊከፍሉህ ስለማይችሉ፣ የተባረክህ ትሆናለህ፡፡ በጻድቃን ትንሣኤ ቀንም እግዚአብሔር ብድራትህን ይከፍልሃል፡፡ 15 በማዕድ ተቀምጠው ከነበሩት አንዱ ኢየሱስ የተናገራውን ሰምቶ፣ "በእግዚአብሔር መንግሥት ማዕድ ተቀምጦ እንጀራ የሚበላ ሰው የተባረከ ነው" አለው፡፡ 16 ኢየሱስ ግን እንዲህ አለው፤ "አንድ ሰው ትልቅ የእራት ግብዣ አዘጋጅቶ ብዙ ሰዎችን ጋበዘ፡፡ 17 የግበዣውም ዝግጅት በተጠናቀቀ ጊዜ ወደ እራት ግብዣው ወደ ተጋበዙት ሰዎች፣ 'ሁሉ ተዘጋጅቶአልና ወደ ግብዣው ኑ' ብሎ መልእክተኞችን ላከ፡፡ 18 ነገር ግን እያንዳንዱ ተጋባዥ ከግብዣው ለመቅረት ምክንያት መደርደር ጀመረ፡፡ የመጀመሪያው፤ "መሬት ስለ ገዛሁ ሄጄ ማየት አለብኝባ ይቅርታ አድርግልኝ አለው፡፡ 19 ሌላው፣ 'አምስት ጥማድ በሬዎችን ገዝቻለሁ፣ እነርሱን ልፈትናቸው ስለምሄድ፤ ይቅርታ አድርግልኝ' አለው፡፡ 20 ሌላኛውም ሰው፣ 'ሚስት አግብቼ ሙሽራ ስልሆንሁ፣ ልመጣ አልችልም' አለ፡፡" 21 አገልጋዩ ለጌታው እነዚህን ነገሮች ነገረው። ከዚያም የቤቱ ጌታ ተቈጥቶ አገልጋዩን 'ቶሎ ሄደህ በከተማው አውራ ጐዳናዎች ስላች መንገዶች ሁሉ ያሉ ድኾችን፣ አካል ጉዳተኞችን፣ ዐይነ ስውራንን፣ ሽባዎችን ሁሉ ወደዚህ እንዲገቡ ጥራቸው' አለው። 22 አገልጋዩም አለው፤ 'ጌታ ሆይ፤ ያዘዝኸኝን ሁሉ አድርጌአለሁ፤ አሁንም ትርፍ ቦታ አለ።' 23 ጌታውም አገልጋዩን፣ 'ወደ ጎዳናዎችና ወደ ገጠር መንገዶች ውጣ፤ ቤቴም እንዲሞላ ያገኘሃቸውን ሁሉ እንዲገቡ ግድ በላቸው። 24 "እላችኋለሁ፣ በመጀመሪያ ከተጋበዙት ከእነዚያ ሰዎች መካከል አንድ ሰው እንኳ ከእራቴ አይቀምስም' አለው። 25 ሕዝብም ከኢየሱስ ጋር አብረው እየሄዱ ሳለ፣ እርሱ ዞር ብሎ እንዲህ አላቸው፤ 26 "ማንም ወደ እኔ ሊመጣ የሚወድ አባቱንና እናቱን፣ ሚስቱንና ልጆቹን፣ ወንድሞቹንና እኅቶቹን፣ እንዲያውም የራሱንም ሕይወት ስንኳ ስለ እኔ ብሎ ካልተወ ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም፡፡ 27 የራሱንም መስቀል ተሸክሞ የማይከተለኝ ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም፡፡" 28 ከእናንተ አንድ ሰው ሕንጻ መሥራት ቢፈልግ ለማጠናቀቅ የሚያስፈልገውን ገንዘብ በመጀመሪያ ተቀምጦ የማይተምን ማን ነው? 29 መሠረቱን ሠርቶ መደመደም ቢያቅተው በዚያ የሚያልፉት ሁሉ ፣ 30 'ይህ ሰው መገንባት ጀምሮ መደምደም አቃተው እያሉ ይዘብቱበታል' ፡፡ 31 ወይም አንድ ንጉሥ ከሌላ ንጉሥ ጋር ሊዋጋ በሚነሣበት ጊዜ ሃያ ሺህ ሰራዊት አስከትቶ የሚመጣበትን በአሥር ሺህ ሰራዊት ለመመከት ተቀምጦ የማይመክር ማን አለ? 32 መመከት የማይችል ከሆነ የሌላው ሰራዊት ገና ከሩቅ ሳለ መልእክተኛ ልኮ ዕርቅ ይጠይቃል፡፡ 33 እንዲሁም ከእናንተ ማንም ያለውን ሁሉ የማይተው ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም፡፡ 34 ጨው መልካም ነው፤ ነገር ግን ጨው ጣዕም ካጣ እንዴት ተመልሶ እንደ ገና የጨውነት ጣዕም ሊኖረው ይችላል? 35 ለመሬትም ሆነ ለማዳበሪያነት የማይጠቅም በመሆኑ ወደ ውጪ ይጣላል፡፡ የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ!"
ይህ የሆነው በሰንበት ሲሆን፣ ኢየሱስ በፈሪሳዊው ቤት ውስጥ ነው፡፡ ቁጥር 1 ቀጥሎ ለሚከናወነው ትእይነት የመረጃ ዳራ ይሰጣል፡፡ (የመረጃ ዳራ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ አዲስ ትዕይንትን ያመለክታል፡፡ (የአዲስ ትዕይንት ትውውቅ የሚለውን ይመልከቱ)
"ለመብላት" ወይም "ለምሳ/ለምግብ፡፡" እንጀራ የምግቡ ዋና ክፍል ነበር፣ እናም በዚህ ዐረፍተ ነገር ውስጥ ገበታውን ለማመልከት ውሏል፡፡ (ስኔክቲክ/የነገሩን ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)
ይከሱት ዘንድ አንዳች ስህተት ይሰራ ይሆናል ብለው ይጠባበቁ
"እነሆ" የሚለው ቃል በታሪኩ ውስጥ አዲስ ሰው እንደሚተዋወቅ ያነቃናል፡፡ ቋንቋችሁ ይህንን የሚገልጽበት መንገድ ሊኖረው ይችላል፡፡ እንግሊዝኛው "በዚያ በእርሱ ፊትለፊት አንድ ሰው ነበር" የሚለውን ይጠቀማል፡፡ (አዲስ እና ነባር ተሳታፊዎችን ማስተዋውቅ የሚለውን ይመልከቱ)
x
የሃይማኖት መሪዎቹ የኢየሱስኝ ጥያቄ መመለስ አልፈቀዱም፡፡
"ስለዚህ ኢየሱስ በእብጠት በሽታ የሚሰቃየውን ሰው ይዞ ፈወሰው"
ኢየሱስ ጥያቄውን የተጠቀመበት እነርሱ በሰንበት ቀንም ቢሆን እንኳን ልጃቸውን ወይም በሬያቸውን እንደሚረዱ እንዲያምኑ ስለፈለገ ነው፡፡ ስለዚህ፣ ለእርሱ ሰዎችን በሰንበትም ቢሆን መፈወስ ትክክል ነበር፡፡ "ከእናንተ መሃል ልጅ ወይም በሬ ቢኖረው…በእርግጥ ፈጥናችሁ ታወጡታላችሁ፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ምሳ በጋበዘው ፈሪሳዊው ቤት ከነበሩ እንግዶች ጋር መናገሩን ቀጠለ፡፡
እነዚህ ሰዎች እነማን እንደሆኑ እና ይህን በአድራጊ ዐረፍተ ነገር መግለጹ አስፈላጊ ሊሆን ይችላል፡፡ "ከፈሪሳዊያን አለቆች አንዱ ወደ ግብዣ የጠራቸው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"ለተከበሩ ሰዎች የተዘጋጀ ወንበር" ወይም "ከፍ ላሉ ሰዎች የተዘጋጁ ወንበሮች"
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "አንድ ሰው በሚጋብዝህ ጊዜ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
በእነዚህ ስፍራዎች "አንተ" የሚሉት ተውላጠ ስሞች ነጠላ ቁጥር ናቸው፡፡ ኢየሱስ በዚያ የተሰበሰቡትን የሚያናግራቸው እያንዳንዳቸውን በግለሰብ ደረጃ እንደሚናገር አድርጎ ነው፡፡ (አንተ የሚለውን ተውላጠ ስም መልኮች ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ምናልባት ደጋሹ ከአንተ ይልቅ የተከበረ ሰው ጋብዦ ሊሆን ይችላል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
በዚህ ስፍራ "እናንተ" የሚለው የሚያመለክተው አንድን የክብር ስፍራ የሚፈልጉ ሁለት ሰዎችን ነው፡፡
"ታፍራለህ ደግሞም"
ኢየሱስ በፈሪሳዊው ቤት ለሚገኙ ሰዎች መናገሩን ቀጥሏል፡፡
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ " አንድ ሰው በሚጋብዝህ ወቀት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"ዝቅ ያለ ደረጃ ላለው ሰው የተዘጋጀ ስፍራ/መቀመጫ"
"የከበሩ ሰዎች/ታላላቆች ወደተቀመጡበት ወንበር ሂድ"
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "በዚይን ጊዜ የጋበዘህ ሰው ያከብርሃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"ራሱን ከፍ የሚያደርግ" ወይም "ከፍ ባለ ስፍራ የሚያስቀምጥ"
"ራሱን ትሁት የሚያደርግ" ወይም "ከፍ ከፍ ይደረጋል፡፡" ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "እግዚአብሔር ያከብረዋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"ራሱን ዝቅ ለማድረግ የሚፈቅድ" ወይም "ራሱን ዝቅ ባለ ስፍራ የሚያስቀምጥ"
"ይከብራል" ወይም "ከፍ ያለ ስፍራ ይሰጠዋል፡፡" ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "እግዚአብሔር ከፍ ያደርገዋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ በፈሪሳዊው ቤት መናገሩን ቀጥሏል፤ ነገር ግን የሚናገረው በቀጥታ ለጋባዡ ነበር፡፡
"ቤቱ ግብዣ የጠራውን ፈሪሳዊ"
"አንተ" የሚለው ነጠላ ቁጥር ነው፤ ምክንያቱም ኢየሱስ በቀጥታ የሚናገረው ለጋበዘው ፈሪሳዊ ነው፡፡ (አንተ የሚለውን ተውላጠ ስም መልኮች ይመልከቱ)
ይህ ምናልባት እነዚህን ሰዎች ፈጽሞ መጋበዝ አይችሉም ማለት ላይሆን ይችላል፡፡ ሌሎችንም/ድሆችንም ደግሞ መጋበዝ ነበረባቸው ማለት ይመስላል፡፡ "…ብቻ አትጋብዝ" ወይም "ሁሌም…ብቻ አትጋብዝ"
"ምክንያቱም እነርሱ"
"ወደ እራት ወይም ግብዣ ይጠሩሃል"
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "በዚህ መንገድ መልሰው ይከፍሉሃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ እርሱን ቤቱ ለጋበዘው ፈሪሳዊ መናገሩን ይቀጥላል
በማዕድ ከተቀመጡት መሃል አንዱ ከኢየሱስ ጋር ተነጋገረ እናም ኢየሱስ ለእርሱ በግብረገባዊ ምሳሌ ምላሽ ሰጠው፡፡ (ግብረገባዊ ምሳሌ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ አዲስ የሆነ አንድ ሰውን ያስተዋውቃል፡፡ (አዲስ እና ነበር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ይመልከቱ)
ሰውየው ስለ አንድ የተለየ ሰው እየተናገረ አይደለም፡፡ "እርሱ የተባረከ ነው" ወይም "ይህ ለእያንዳንዱ እንዴት መልካም ነው"
"እንጀራ" የሚለው ቃል የዋለው በአጠቃሌ መዕዱን ለማመልከተ ነው፡፡ "ከዚህ ማዕድ የሚበላ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/የነገሩን ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ግብረ ገባዊ ምሳሌ መናገር ጀመረ፡፡ (ግብረ ገባዊ ምሳሌ የሚለውን ይመልከቱ)
አንባቢው ምናልባት የዚያ ሰው አገልጋዮች መዕደስ እንዳዘጋጁ እና እንግዶችን እንደጋበዙ መገመት መቻል ይኖርበታል፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ሀረግ ስለማንነቱ ምንም መረጃ ስላልሰጠ ሰው ማጣቀሻ መንገድ ነው፡፡
"ብዙ ሰዎች ጋበዘ" ወይም "ብዙ እንግዶች ጠራ"
ኢየሱስ ግብረገባዊ ምሳሌውን መናገሩን ቀጠለ፡፡
የተጋበዙት ሰዎች ሁሉ ለአገልጋዩ ወደ ግብዣው ሊመጡ የማይችሉባቸውን ምክንጠቶች ሰጡ፡፡
"ወደ እራት መምጣት ያልቻሉበትን መናገር"
አንባቢያን፣ እነዚህ ሰዎች በቀጥታ ጌታቸው ለላከው አገልጋይ እንደተናገሩ መገንዘብ መቻል ይኖርባቸዋል (ሉቃስ 14፡17) ፡፡ "የመጀመሪያው እንዲህ ሲል መልዕክት ላከ…ሌላው እንዲህ ሲል መልዕክት ላከ… ሌላውም ሰው እንዲህ ሲል መልዕክት ላከ" ወይም "የመጀመሪያው አገላጋዩ እንዲህ እንዲል ነገረው…ሌላኛው አገልጋዩ እንዲህ እንዲል ነገረው… ሌላው ሰው አገልጋዩ እንዲህ እንዲል ነገረው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
"እባክህ ይቅርታ አድርግልኝ" ወይም "እባክህን ይቅርታዬን ተቀበል"
በሬዎች የእርሻ መሳሪያ ለመሳብ/ለማረስ በጥንድ ይጠመዳሉ፡፡ "10 በሬዎች በእርሻዬ ላይ ተጠምደዋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
በቋንቋችሁ የተለመደውን አገላለጽ ተጠቀሙ፡፡ አንዳንድ ቋንቋዎች "አግብቻለሁ" ወይም "ሚስት ወስጃለሁ" ሊሉ ይችላሉ፡፡
"ግብዣ በጠራቸው ሰዎች ተቆጣ"
"እራት እንዲበሉ ወደዚህ ጥሯቸው"
በውስጠ ታዋቂነት ያለውን አገልጋዩ ጌታው ያዘዘውን ማድረጉን የሚያሳየውን በግልጽ መጻፍ አስፈለዘጊ ሊሆን ይችላል፡፡ "አገልጋዩ ወደ ውጭ ሄዶ ያን አድርጎ ተመልሶ መጥቶ እንዲህ አለ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "አንተ ያዘዝከውን አድርጌያለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ግብረ ገባዊ ምሳሌውም መናገር ጨረሰ፡፡
ይህ የሚያመለክተው መንገዶችን እና ከከተማ ውጭ ያሉ መተላለፊያዎችን ነው፡፡ "አውራ መንገዶች እና ከከተማ ውጭ የሚገኙ መተላለፊያ መንገዶች"
"እንዲመጡ ግድ በሏቸው"
"እነርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ማናቸውንም አገልጋዮቹ የሚያገኟቸውን ሰዎች ነው፡፡ "ያገኟችኋቸውን ሁሉ ግድ በሏቸው"
"ሰዎች ቤቴን ይሞሉ ዘንደ"
"እናንተ" የሚለው ቃል ብዙ ቁጥር ነው፤ ስለዙሀ ይህ ማንን እንደሚያመለክት ግልጽ አይደለም፡፡ (አንተ የሚለውን ተውላጠ ስም መልኮች ይመልከቱ)
እዚህ ስፍራ "ወንዶች" የሚለው "አዋቂ ወንዶች" ማለት እንጂ በአጠቃላይ ሰዎችን ማለት አይደለም፡፡
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "እኔ የጋበዝኳቸው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"ያዘጋጀሁትን እራት ይበላሉ"
ኢየሱስ ከእርሱ ጋር ይጓዝ የነበረውን የተሰበሰበውን ሕዝብ ማስተማር ጀምሯል፡፡
እዚህ ስፍራ "መጥላት" የሚለው ሰዎች ሌለውን አስበልጠው ለኢየሱስ ለሚያሳዩት አነስ ያለ ፍቅር በግነት የቀረበ አገላለጽ ነው፡፡ "ማንም ወደ እኔ መጥቶ አባቱን ከሚወደው በላይ እኔን ካልወደደ…እርሱ የእኔ ደቀመዝሙር መሆን አይችልም" ወይም "አንድ ሰው አባቱን ከሚወደው በላይ እኔን መውደድ ከቻለ ብቻ …እርሱ የእኔ ደቀመዝሙር መሆን ይችላል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ኩሸት እና አጠቃላይ አስተያየት እንደዚሁም ጥንድ አሉታ የሚሉትን ይመልከቱ)
ይህ በአዎንታዊ ግሶች ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ማንም የእኔ ደቀመዝሙር መሆን ቢፈልግ፣ የራሱን መስቀል ሊሸከም እና ሊከተለኝ ይገባል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ጥንድ አሉታዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ እያንዳንዱ ክርስቲያን መሰቀል አለበት ማለቱ አይደለም፡፡ ሮማውያን ብዙውን ጊዜ ለሮም ያላቸውን ታማኝነት እንዲያሳዩ ወንጀለኛ ሰዎች ራሳቸው የሚሰቀሉበትን መስቀል እንዲሸከሙ ያደርጉ ነበር፡፡ የዚህ ዘይቤ ትርጉም እነርሱም ለእግዚአብሔር መገዛት እና የኢየሱስ ደቀመዝሙር ለመሆን መከራ ለመቀበል ፈቃደኛ መሆን እንደሚገባቸው ያሳያል፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር እና ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚሉትን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ለተሰበሰበው ሕዝብ ደቀመዝሙር ለመሆን የሚጠይቀውን ዋጋ ማወቅ እንደሚያስፈልግ ማብራራቱን ቀጥሏል፡፡
ኢየሱስ ይህን ጥያቄ የተጠቀመበት ሰዎች አንድን ሥራ ለመሥራት ለሥራው የሚያስፈልገውን እንደሚያሰሉ ለማሳየት ነው፡፡ "አንድ ሰው ህንጻ ማነጽ ቢፈልግ፣ በመጀመሪያ ተቀምጦ ህንጻውን ሊደመደምበት የሚያበቃው ገንዘብ እንዳለው ይወስናል፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ትልቅ ህንጻ ሊሆን ይችላል፡፡ "ትልቅ ህንጻ" ወይም "ጎላ ብሎ የሚያይ ግንብ"
ተጨማሪ መረጃ መስጠት ሊረዳ ይችላል፡፡ "አስቀድሞ ዋጋውን ካላወቀ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (የተተወ/የተዘለለ የሚለውን ይመልከቱ)
"መሰረቱን ሲገነባ" ወይም "የህንጻውን የመጀመሪያ ክፈል ሲያጠናቅቅ"
መጨረስ ያልቻለው በቂ ገንዘብ ስለሌለው መሆኑ ይታወቃል፡፡ እንዲህ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ለመጨረስ በቂ ገንዘብ አልነበረውም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ለተሰበሰበው ሕዝብ ደቀመዝሙር ለመሆን የሚጠይቀውን ዋጋ ማወቅ አስፈላጊ እንደሆነ ማብራራቱን ቀጥሏል፡፡
ኢየሱስ ይህን ቃል የተጠቀመው ሰዎች አንድ ውሳኔ ከማድረጋቸው አስቀድሞ ውሳኔው የሚጠይቀውን ዋጋ ሌላ ሁኔታ ለማስተዋወቅ ነው፡፡
ኢየሱስ የተሰበሰበውብ ሕዝብ ዋጋ ስለመተመን ለማስተማር ሌላ ጥያቄ ያነሳል፡፡ " አንድ ንጉሥ… በመጀመሪያ ተቀምጦ… ከአማካሪዎቹ ምክር እንደሚቀበል ታውቃላችሁ፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1)"በጥንቃቄ ማሰብ" ወይም 2) "አማካሪዎቹን መስማት"
"10,000…20,000" (ቁጥሮች የሚለውን ይመልከቱ)
ተጨማሪ መረጃዎችን መግለጽ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡ "ሌላውን ንጉሥ ለማሸነፍ እንደማይችል ከተገነዘበ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (የተተወ/የተዘለለ የሚለውን ይመልከቱ)
"ጦርነቱን ለማጠናቀቅ የሚያስፈልጉ" ወይም "ጦርነቱን ለማጠናቀቅ ሌላው ንጉሥ እርሱ እንዲያደርግ የሚፈልገው"
ይህ በአዎንታዊ ግሶች ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ያላችሁን ሁሉ የምትተዉ ብቻ ደቀመዝሙሬ መሆን ትችላላችሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ጥንድ አሉታ የሚለውን ይመልከቱ)
"ያለውን ሁሉ ከኋላው የሚጥል"
ኢየሱስ የተሰበሰበውን ህዘውብ ማስተማሩን አጠናቀቀ፡፡
"ጨው ጠቃሚ ነው፡፡" ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ ሊሆኑ ለሚፈልጉ ትምህርት እየሰጠ ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ይህን ጥያቄ የተጠቀመው የተሰበሰበውን ሕዝብ ለማስተማር ነው፡፡ "ዳግም ጣዕም ሊሰጠው አይችልም፡፡" ወይም "ማንም ዳግም ጣዕም ሊሰጠው አይችልም፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)
ሰዎች አትክልት ስፍራዎችን እና እርሻን ለማልማት ማዳበሪያ ይጠቀማሉ፡፡ ጣዕም የሌለው ጨው አንዳች ጥቅም የለውም፤ ከፍግ ጋር ለመደባለቅ እንኳን አይጠቅምም፡፡ "የማዳበሪያ ቁልል" ወይም "ማዳበሪያ/ፍግ"
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገል ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ወደ ውጭ ይጥሉታል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
በአንዳንድ ቋንቋዎች ሁለተኛ መደብን መጠቀም ይበልጥ ተፈጥሯዊ ሊሆን ይችላል፡፡ "እናንተ መስሚያ ጆሮ ያላችሁ ስሙ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አንደኛ፣ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ መደብ የሚለውን ይመልከቱ)
ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) "እያንዳንዱ" ጤናማ ጆሮ እስካላቸው ድረስ፣ ወይም 2) "የመረዳት ችሎታ ያለው ሁሉ፣" እግዚአብሔርን ለመስማት ፈቃደኛ የሆኑትን ያሚያመለክት ነው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
"እርሱ በሚገባ መስማት አለበት" ወይም "እርሱ እኔ ለምናገረው ትኩረት መስጠት አለበት"
1 አንድ ቀንም ቀረጥ ሰብሳቢዎችና ሌሎች ኅጢአተኞች ሁሉ ኢየሱስን ለመስማት መጡ። 2 ፈሪሳውያንና የሕግ መምህራን፣ "ይህ ሰው ኅጢአተኞችን ይቀበላል፤ ከእነርሱም ጋር ይበላል" በማለት እርስ በርሳቸው አጒረመረሙ። 3 ኢየሱስ እንዲህ በማለት ይህን ምሳሌ ነገራቸው፤ 4 "ከእናንተ መካከል መቶ በጎች ያሉት ከዚያም ከእነርሱ አንዱ ቢጠፋበት ዘጠና ዘጠኙን በዱር ትቶ የጠፋበትን እስኪያገኘው ድረስ ሊፈልግ የማይሄድ ማንነው? 5 ባገኘውም ጊዜ ከመደሰቱ የተነሣ በጫንቃው ይሸከመዋል። 6 ወደ ቤቱም ሲመለስ ወዳጆቹንና ጎረቤቶቹን በአንድነት ጠርቶ፣ 'የጠፋብኝን በጌን አግኝቻለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ' ይላቸዋል። 7 እንዲሁም ንስሓ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሓ በሚገባ በአንድ ኅጢአተኛ በሰማይ ታላቅ ደስታ እንደሚሆን እነግራችኋለሁ። 8 ወይስ ዐሥር የብር ሳንቲሞች ያላት ሴት ከዐሥሩ አንዱ ቢጠፋበት፣ እስከምታገኛው ድረስ መብራት አብርታ፣ ቤቷንም ሁሉ ጠርጋ በትጋት የማትፈልግ ሴት ማን ናት? 9 ባገኘችም ጊዜ ወዳጆቿንና ጎረቤቶቿን ሁሉ በአንድነት ጠርታ፣ 'የጠፋብኝን የብር ሳንቲሜን አግኝቻለሁና ኑ ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ' ትላቸዋለች። 10 "እንደዚሁም ንስሓ በሚገባ በአንድ ኅጢአተኛ በእግዚአብሔር መላአክት ፊት ታላቅ ደስታ እንደሚሆን እነግራችኋለሁ።" 11 ከዚያም ኢየሱስ እንዲህ አለ፣ "አንድ ሰው ሁለት ወንዶች ልጆች ነበሩት፤ 12 ታናሹ ልጅም አባቱን፣ 'አባቴ ሆይ፣ በኋላ ከሀብትህ ከሚደርሰኝ ድርሻዬን ስጠኝ' አለው። አባቱም ሀብቱን ለሁለቱም ልጆቹ አካፈላቸው። 13 ከጥቂት ቀናትም በኋላ ታናሹ ልጅ ድርሻውን ይዞ ወደ ሩቅ አገር ሄደ። እዚያም ገንዘቡን ሁሉ አላግባብ እየጨፈረ አባከነ። 14 እርሱም ያለውን ሁሉ ከጨረሰ በኋላ በዚያ አገር ጽኑ ራብ ሆነ። ከዚህም የተነሳ ችግር ላይ ወደቀ። 15 በዚያም አገር ዐሳማ ያረባ ወደ ነበረ ወደ አንዱ ሰው ዘንድ ሄዶ ተቀጠረ። ሰውዬው ዐሳማዎችን እንዲጠብቅለት አሰማራው። 16 እርሱም የሚበላውን ምግብ የሚሰጠው ስላልነበረ፣ ዐሳማዎቹ ከሚመገቡት መኖ ለመብላት ይፈልግ ነበር። 17 እርሱም አንድ ቀን ወደ ልቡ ተመልሶ እንዲህ አለ፤ 'ምግብ የሚተርፋቸው የአባቴ ቤት ሠራተኞች ስንት ናቸው? 18 እኔ ግን እዚህ የምበላውን አጥቼ በራብ እሞታለሁ! ተነሥቼ ወደ አባቴ ቤት ልሂድና እንዲህ ልበለው፤ "አባቴ ሆይ፣ በእግዚአብሔርና በአንተ ፊት ኅጢአት አድርጌአለሁ። 19 ከእንግዲህ ልጅህ ተብዬ መጠራት አይገባኝም፤ ከአገልጋዮችህ እንደ አንዱ ቊጠረኝ።" 20 ስለዚህ ታናሹ ልጅ ተነሥቶ ወደ አባቱ መጣ። ልጁ ገና ከሩቅ እየመጣ ሳለ፤ አባቱ አይቶ በርኅራኄ ሮጦ ተቀበለውና ዐቅፎ ሳመው። 21 ልጁ፣ 'አባቴ ሆይ፣ በእግዚአብሔርና በአንተ ፊት ኅጢአት አድርጌአለሁ። ከእንግዲህ ልጅህ ተብዬ ልጠራ አይገባኝም' አለ። 22 አባቱም አገልጋዮቹን እንዲህ አላቸው፤ "ፈጥናችሁ ምርጡን ልብስ አምጡና አልብሱት፣ በጣቱ ቀለበት፣ በእግሩም ጫማ አድርጉለት። 23 ከዚያም የሰባውን ወይፈን አምጡና ዕረዱት። እንብላ፤ እንደሰት። 24 ይህ ልጄ ሞቶ ነበረ አሁን በሕይወት አለ፤ ጠፍቶም ነበረ ተገኝቶአል።" ይደሰቱም ጀመር። 25 ታላቁ ልጅ በዕርሻ ቦታ ነበረ። ወደ ቤትም በተቃረበ ጊዜ፣ ሙዚቃና ጭፈራ ሰማ። 26 ከአገልጋዮቹ አንዱን ጠርቶ፤ ምን እየሆነ እንዳለ ጠየቀው። አገልጋዩም፣ 'ወንድምህ መጥቶአል። 27 በደኅና ስለተመለሰም አባትህ የሰባውን ወይፈን አርዶለታል' አለው። 28 ታላቁ ልጅ ይህን ሰምቶ ተቈጣ፤ ወደ ቤትም ሊገባ አልፈለገም። አባቱም ወጥቶ እንዲገባ ለመነው። 29 እርሱ ግን አባቱን እንዲህ አለው፤ 'እነሆ፣ ይህን ሁሉ ዘመን እንደ ባሪያ አገለገልሁህ፤ ከትእዛዝህ አንዱንም ሳላጎድል ከአንተ ጋር ኖርሁ፤ ከባልንጀሮቼ ጋር እንድደሰት አንዲት የፍየል ግልገል እንኳ አልሰጠኸኝም፤ 30 ነገር ግን ይህ ልጅህ ገንዘብህን ሁሉ ከሴተኛ አዳሪዎች ጋር አባክኖ ሲመጣ፣ የሰባውን ወይፈን አረድህለት።' 31 አባቱ እንዲህ አለው፤ “ልጄ ሆይ፣ አንተ ሁልጊዜ ከእኔ ጋር ነህ፤ ያለኝ ሁሉ የአንተ ነው። 32 ነገር ግን ይህ ወንድምህ ሞቶ ነበር፤ አሁን በሕይወት አለ፤ ጠፍቶም ነበር ተገኝቶአል። ስለዚህ ልንበላና ልንደሰት ይገባናል።'
ይህ መቼ እንደተፈጸመ አናውቅም፤ ይህ የሆነው አንድ ዕለት ኢየሱስ እያስተማረ ሳለ ነው፡፡
የአዲስ ተዕይንት ጅማሬ ምልክቶችን ያሳያል፡፡ (አዲስ ትዕይንትን ማስተዋወቅ የሚለውን ይመልከቱ)
በርካታ ግብር ሰብሳቢዎች እንደነበሩ በግነት የተገለጸ ነው፡፡ "ብዙ ግብር ሰብሳቢዎች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ኩሸት እና አጠቃላይ አስተያየት የሚሉትን ይመልከቱ)
"ይህ ሰው ኃጢአተኞች እንዲቀርቡት ይፈቅዳል" ወይም "ይህ ሰው ከጢአተኞች ጋር ህብረት ያደርጋል"
ስለ ኢየሱስ እየተናገሩ ነበር፡፡
እንኳን/ጭምር የሚለው ኢየሱስ ኃጢአተኞች ወደ እርሱ እንዲቀርቡ መፍቀዱ እጅግ መጥፎ ነገር ነው ብለው ማሰባቸውን ያሳያል፤ ይልቁንም ከእነርሱ ጋር መመገቡ ከዚያም የከፋ ነገር እንደሆነ ያስቡ ነበር፡፡
ኢየሱስ ብዙ ምሳሌዎችን መናገር ጀመረ፡፡ እነዚህ ማንም ሰው ሊገጥመው የሚችላቸው ግብረገባዊ ምሳሌዎች መላምታዊ ሁኔታዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ስለተለያዩ ሰዎች የሚናገሩ አይደለም፡፡ የመጀመሪያው ግብረገባዊ ምሳሌ አንድ ሰው ከበጎቹ አንዱ ቢጠፋ ያ ሰው ምን እንደሚያደርግ የሚገልጽ ነው፡፡ (ግብረገባዊ ምሳሌዎች እና መላምታዊ ሁኔታዎች የሚሉትን ይመልከቱ)
እዚህ ስፍራ "እነርሱ" የሚለው የሚያመለክተው የሃይማኖት መሪዎችን ነው፡፡
ኢየሱስ ጥያቄውን የተጠቀመበት፣ ሰዎቹ ከበጎቻቸው መሃል አንዱ ቢጠፋ ፍለጋ እንደሚሄዱ ሊያሳስባቸው ነው፡፡ "እናንተ እያንዳንዳችሁ … እስክታገኙት ድረስ…በእርግጥ ፍለጋ ታደርጋላችሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
ምሳሌያዊ አነጋገሩ "ከእናንተ መሃል ማን" በሚል እንደመጀመሩ፣ አንዳንድ ቋንቋዎች ምሳሌያዊ አነጋገሩን በሁለተኛ መደብ ይቀጥላል፡፡ "መቶ በጎች ቢኖራችሁ፣ ከእናንተ መሃል ማን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አንደኛ፣ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ መደብ የሚለውን ይመልከቱ)
"100… 99" (ቁጥሮች የሚለውን ይመልከቱ)
"የበጉ ባለቤት ወደ ቤቱ ስመለስ" ወይም "ወደ ቤት ሲመለስ፡፡" የበጉን ባለቤት በቀደመው ቁጥር እንዳደረጋችሁት አመልክቱ፡፡
"በተመሳሳይ መንገድ" ወይም "እረኛው እና ወዳጆቹ እንደዚሁም ጎረቤቶቹ ደስ እንደሚሰኙ"
"በሰማይ ያሉት ሁሉ ደስ ይላቸዋል"
ኢየሱስ ፈሪሳውያኑ ንስሃ እንደማያስፈልጋቸው ማሰባቸው ስህተት መሆኑን በምጸት ይናገራል፡፡ የእናንተ ቋንቋ ይህን ሃሳብ ለመግለጽ የተለያ መንገድ ሊኖረው ይችላል፡፡ "እንደ እናንተ የመሰሉ ጻድቃን ነን ብለው የሚያስቡ ንስሃ መግባት የማይፈልጉ ዘጠና ዘጠኝ ሰዎች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ኩሸት እና አጠቃላይ አስተያየት የሚለውን ይመልከቱ)
"99" (ቁጥሮች የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ሌላ ግብረገባዊ ምሳሌ መናገር ይጀምራል፡፡ ይህኛው 10 የብር ሳንቲሞች ስላላት ሴት ነው፡፡
ኢየሱስ ይህንን ጥያቄ የተጠቀመበት ሰዎቹ የብር ሳንቲም ቢጠፋባቸው፣ ያንን በእርግጥ በትጋት እንደሚፈልጉ ለማስታወስ ነው፡፡ "የትኛዋም ሴት…በእርግጥ ፋኖስ ትለኩሳለች… እናም እስክታገኘው ድረስ በትጋት የጠፋባትን ትፈልጋለች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ መላምታዊ ሁኔታ እንጂ በዕውን ስላለች አንዲት ሴት የሚናገር ታሪክ አይደለም፡፡ አንዳንድ ቋንቋዎች ይህን የሚያሳዩበት መንገድ አላቸው፡፡ (መላምታዊ ሁኔታ የሚለውን ይመልከቱ)
"በተመሳሳይ መንገድ" ወይም "ሰዎች ከሴቲቱ ጋር ደስ እንደሚላቸው" ንስሃ በሚገባ አንድ ኃጢአተኛ "አንድ ኃጢአተኛ ንስሃ በሚገባበት ጊዜ"
ኢየሱስ ሌላ ግብረገባዊ ምሳሌ መናገር ጀመረ፡፡ ይህም አባቱን ከሚደርሰው ውርስ ድርሻውን ስለጠየቀው ወጣት ነው፡፡ (ግብረገባዊ ምሳሌ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ አዲስ ገጸባህሪን በግብረገባዊ ምዋሌው ውስጥ ያስተዋውቃል፡፡ አንዳንድ ቋንቋዎች "አንድ ሰው ነበረ" ብለው ይጀምራሉ፡፡ (አዲስ እና ነባር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ይመልከቱ)
ልጁ አባቱ ወዲያውኑ ድርሻውን እንዲሰጠው ፈልጓል፡፡ ወዲያውኒ ሊደረግ የሚፈልገውን በትዕዛዝ መልክ መግለጽ የሚችል ቃል በቋንቋ ካለ ያንን መልክ መጠቀም አለባችሁ፡፡
"በምትሞትበት ጊዜ ልታወርሰኝ ያቀድከውን የሀብት መጠን"
"በሁለቱ ልጆቹ መሃል"
"ያሉትን ነገሮች ጠቀለለ" ወይም "ያሉትን ነገሮች በቦርሳው ውስጥ አደረገ"
"ድርጊቶች ስለሚያስከትሉት ውጤት ባለማሰብ መኖር" ወይም "ልቅ አኗኗር"
x
"እርሱ" የሚለው ቃል ታናሹን ልጅ ያመለክታል፡፡
"ከ…ዘንድ ሥራ ያዘ" ወይም "ለ…መሥራት/ማገልግል ጀመረ"
"የዚያ አገር ሰው"
"ለሰውየው አሳሞች ምግብ ለመስጠት"
"አግኝቶ ሊበላ በጣም ይፈልግ ነበር፡፡" ይህ የሆነው በመራቡ ምክንያት እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ እንዲህ ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ቢያገኝ በደስታ እስኪመገብ ድረስ በጣም ተርቦ ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ ዐሰር ናቸው፡፡ "የባቄላ ግልፋፊ" ወይም "የባቄላ/በቆሎ ልባስ" በሚለው ወስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ያልታወቀውን መተረጎም የሚለውን ይመልከቱ)
የዚህ ፈሊጣዊ አነጋገር ትርጉም፣ ከፍ ያለ ስህተት እንደፈጸመ እና እውነታው ምን እንደነበረ አስተዋለ፡፡ "በግልጽ ሁኔታውን ተረዳ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የማጋነኑ አንዱ ክፍል ነው፤ እናም ጥያቄ አልነበረም፡፡ "የአባቴ አጋልጋዮች ሁሉ ከሚያስፈልጋቸው በላይ ምግብ አላቸው"
ይህ ምናልባት ማጋነን አይደለም፡፡ ወጣቱ ሰው በእርግጥም ተረቧል፡፡
የአይሁድ ሰዎች አንዳንድ ጊዜ "እግዚአብሔር" የሚለውን ቃል "ሰማይ" በሚል ተክተው ይጠቀማሉ፡፡ "በእግዚአብሔር ፊት በደልኩ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
"ልጅህ ተብዬ ልጠራ አይገባኝም፡፡" ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ልጄ ብለህ ልትጠራኝ አይገባኝም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"እንደ አንድ አገልጋይህ ቅጠረኝ" ወይም "ቅጠረኝ እኔም ከሰራተኞችህ እንደ አንዱ እሆናለሁ፡፡" ይህ ጥያቄ ነው፤ ትዕዛዝ አይደለም፡፡ በዩቢዲ ውስጥ እንደሚገኘው "እባክህ" የሚለው ቢጨመር ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡
"ስለዚህ ከሄደበት አገር ወደ አባቱ ተመለሰ፡፡" "ስለዚህ" የሚለው ቃል የሆነውን ድርጊት አስቀድሞ በሆነው ሌላ ነገር ምክንየት እንደሆነ ያመለክታል፡፡ በዚህ ሁኔታ፣ ወጣቱ ሰው ሲቸግረው ወደ ቤት ለመመለስ ወሰነ፡፡
"ገና ከቤቱ ሩቅ ስፍራ ሳለ" ወይም "ገና ከአባቱ ቤት ሩቅ ስፍራ ሳለ"
"ለእርሱ ርህራሄ ነበረው" ወይም "እጅግ ከልቡ ይወደው ነበር"
አባቱ ይህን ያደረገው እንደሚወደው ለልጁ ለማሳየት እና ልጁ ተመልሶ ቤት በመምጣቱ ስለተደሰተ ነበር፡፡ ሰዎች አባት ወንድ ልጁን ማቀፉ ወይም መሳሙ እንግዳ ነገር ወይም ስህተት ነው ብለው የሚያስቡ ከሆነ፣ በባህላችሁ አባቶች ለወንድ ልጃቸው ያላቸውን ፍቅር የሚገልጹበትን መንገድ ተክታችሁ መተርጎም ትችላላችሁ፡፡ "እርሱን በፍቅር ተቀበለው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡
የአይሁድ ሰዎች አንዳንድ ጊዜ "እግዚአብሔር" የሚለውን ቃል "ሰማይ" በሚል ተክተው ይጠቀማሉ፡፡ ይህ በሉቃስ 15፡18 ላይ እንዴት እንደተተረጎመ ይመልከቱ፡፡ "እግዚአብሔርን በደልኩ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊተረጎም ይችላል፡፡ ተመሳሳይ የሆነው ሀረግ በሉቃስ 15፡18 ላ እንዴት እንደ ተተረጎም ይመልከቱ፡፡"ልጄ ብለህ ልትጠራኝ አይገባኝም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"በቤት ካለው ምርጡን ልብስ፡፡" "ምርጡን ኮት" ወይም "ምርጡን ጨርቅ"
ቀለበት ወንዶች ከጣታቸው መሃል በአንዱ የሚያጠልቁት የስልጣን ምልክት ነበር፡፡
በዘመኑ ባለጸጋ ሰዎች ነጠላ ጫማ ያደርጉ ነበር፡፡ ሆኖም፣ በብዙ ባህሎች የዚህ ዘመናዊ አቻ የሆነው "ጫማ" ነው፡፡
ጥጃ ገና በሬ ያለሆነ ነው፡፡ ሰዎች ጥጃዎች በሚገባ እንያድጉ ጥሩ አድረገው ይቀለቀቧቸዋል፤ ከዚያም የተለየ ድግስ ሲኖርባቸው ይመገቧቸዋል/አርደው ይበሏቸዋል፡፡ "የሰባውን ፍሪዳ" ወይም "በሚገባ ያባነውን ወይፈን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ለምን ፍሪዳው እንደታረደ በውስጠታዋቂነት ያለው መረጃ ግልጽ ሊደረግ ይችላል፡፡ "አርዳችሁ ስሩት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ዘይቤ የሚናገረው የኮበለለውን ልጅ እንደሞተ አድርጎ ነው፡፡ "ልጄ ከሞተ በኋላ ዳግም ህያው እንደሆነ ይቆጠራል" ወይም "ልጄ ሞቶ እንደነበረ እና አሁን ዳግም ህያው እንደሆነ ይሰማኛል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ዘይቤ የሚናገረው የልጁን መኮብለል/መሄድ እንደጠፋ አድርጎ ነው፡፡ "ልጄ ጠፍቶ ነበር አሁን ግን አገኘሁት" ወይም "ልጄ ጠፍቶ ነበር አሁን ቤት ተመለሰ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ስፍራ ይህ ቃለ የዋለው በዋናው የታሪክ መስመር ማቆሚያ ለማበጀት ነው፡፡ እዚህ ስፍራ ኢየሱስ ስለ ታላቁ ልጅ አዲሱን የታሪኩን ክፍል መናገር ይጀምራል፡፡
እርሱ ውጭ በመስክ ላይ እንደነበረ ተጠቅሷል፣ ምክንያቱም በዚያ በሥራ ላይ ነበር፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ስፍራ "አገልጋይ" ተብሎ የተተረጎመው ቃል በቀጥታ "ልጅ" በሚል ተተርጉሟል፡፡ ይህ አገልጋዩ በጣም ወጣት እንደሆነ ያመለክታል፡፡
"ምን እየሆነ ነበር"
ጥጃ ገና በሬ ያለሆነ ነው፡፡ ሰዎች ጥጃዎች በሚገባ እንያድጉ ጥሩ አድረገው ይቀለቀቧቸዋል፤ ከዚያም የተለየ ድግስ ሲኖርባቸው ይመገቧቸዋል/አርደው ይበሏቸዋል፡፡ይህ ሀረግ በሉቃስ 15፡23 ላይ እንዴት እንደ ተተረጎመ ይመልከቱ፡፡ "የሰባው/ምርጡ ጥጃ" "ያሰባነው ወይፈን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
"ለብዙ አመታት"
"ለአንተ እጅግ በከባዱ ሰራሁ" ወይም "ለአንተ እንደ ባሪያ በከባዱ ሰራሁ"
"በፍጹም ከትእዛዝህ አልወጣሁም" ወይም "ሁልጊዜም አድርግ ያልከኝን ሁሉ አድርጌያለሁ"
ትንሽ ፍየል ከሰባ ጥጃ ያነሰች እና ዋጋዋም ዝቅተኛ ነበረች፡፡ "ትንሽ ፍየል እንኳን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
"ያ የአንተ ልጅ፡፡" ትልቁ ልጅ ወንድሙን በዚህ መንገድ የሚገልጸው ምን ያህል እንደተናደደ ለማሳየት ነው፡፡
ምግብ ለገንዘብ ዘይቤያዊ አገላለጽ ነው፡፡ አንድ ሰው ምግብን ከተመገበው በኋላ፣ ምግቡ ዳግመኛ አይበላም፡፡ ወንድሙ ከወሰደው ገንዘብ አንዳች አልተረፈም፤ ምንም ነገር አልቀረም፡፡ "ሀብትህን ሁሉ አባከነ" ወይም "ገንዝብህን ሁሉ በተነ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ወንድሙ ገንዘቡን ያባከነው እንደዚህ ነው ብሎ ገምቷል፣ ወይም 2) ስለ ጋለሞቶች የተናገረው "በሄደበት ሩቅ አገር" ወንድሙ የሰራቸውን የኃጢአተኝነት ድርጊቶች ለማጋነን ነው (ሉቃስ 15፡13)፡፡ (ኩሸት እና አጠቃላ አስተያየት የሚሉትን ይመልከቱ)
ጥጃ ገና በሬ ያለሆነ ነው፡፡ ሰዎች ጥጃዎች በሚገባ እንያድጉ ጥሩ አድረገው ይቀለቀቧቸዋል፤ ከዚያም የተለየ ድግስ ሲኖርባቸው ይመገቧቸዋል/አርደው ይበሏቸዋል፡፡ይህ ሀረግ በሉቃስ 15፡23 ላይ እንዴት እንደ ተተረጎመ ይመልከቱ፡፡ "የሰባው/ምርጡ ጥጃ" "ያሰባነው ወይፈን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
1 ደግሞም ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አለ፤ "አንድ ሀብታም ሰው ነበረ፤ እርሱም በንብረቱ ሁሉ ላይ የሾመው አስተዳዳሪ ነበረው። ይህ አስተዳዳሪ ሀብተ ያባክናል ተብሎ ለሀብታሙ ተነገረው። 2 ስለዚህ ሀብታሙ ሰው አስተዳዳሪውን ጠርቶ፣ 'ይህ ስለ አንተ የምሰማው ነገር ምንድን ነው? ከዚህ በኋላ ለእኔ አስተዳዳሪ ልትሆን ስለማትችል ንብረቴን አስረክበኝ' አለው። 3 አስተዳዳሪው እንዲህ ብሎ አሰበ፤ 'እንግዲህ ጌታዬ ከአስተዳደር ሥራዬ ስለሚያሰናብተኝ፣ ምን ባደርግ ይሻለኛል? ዓቅም ስለሌለኝ፣ ከእንግዲህ መሬት በመቈፈር ለመተዳደር አልችልም፤ መለመንም ያሳፍረኛል። 4 ከአስተዳዳሪነት ሥራዬ ስሰናበት፣ ሰዎች በቤታቸው እንዲቀበሉኝ ካሁኑ ምን እንደማደርግ ዐውቃለሁ።' 5 ከዚያም አስተዳዳሪው የጌታውን ተበዳሪዎች አንድ በአንድ ጠርቶ፣ የመጀመሪያውን ሰው 'ያለብህ ዕዳ ምን ያህል ነው?' ብሎ ጠየቀው። 6 እርሱም፣ 'አንድ መቶ ማድጋ ዘይት አለብኝ' አለ። አስተዳዳሪውም፣ 'በፈረምኸው ውል ላይ ዐምሳ ማድጋ ብለህ ጻፍ' አለው። 7 ሌላውንም፣ 'አንተስ ስንት ዕዳ አለብህ?' ብሎ ጠየቀው። እርሱም፣ 'መቶ ኩንታል ስንዴ አለብኝ' አለ፤ በፈረምኸው ውል ላይ ሰማንያ ኩንታል ብለህ ጻፍ' አለው። 8 ጌታውም እምነት ያጎደው አስተዳዳሪ ያደረገውን ሰምቶ፤ በብልኅነቱ በመደነቅ እንዲህ አለ፤ 'በዚህ ዓለም እግዚአብሔርን የማያውቁ ሰዎች እግዚአብሔርን ከሚያውቁ ሰዎች ይልቅ በዓለማዊ ሥራቸው ብልኆች ናቸው። 9 ስለዚህ እላችኋለሁ፣ በዓለም ባላችሁ ሀብት ለራሳችሁ ወዳጆችን አፍሩበት፤ ምክንያቱም ሀብታችሁ ባለቀ ጊዜ በዘላለም ቤቶች ይቀበሉአችኋል። 10 በጥቂቱ የታመነ ሰው በብዙ ላይ የታመነ ይሆናል፤ በጥቂቱ የሚያምፅ በብዙም ዐመፀኛ ይሆናል። 11 ስለዚህ በዚህ ዓለም ሀብት ካልታመናችሁ እውነተኛውን ሀብትማ ማን አምኖ ይሰጣችኋል? 12 እንደዚሁም በሌላ ሰው ሀብት ካልታመናችሁ የራሳችሁን ማን ይሰጣችኋል? 13 ሁለት ጌቶችን ማገልገል የሚችል ማንም የለም፤ አንዱን ይተዋል፤ ሌላውን ይወዳል፤ አለበለዚያም ለአንዱ ራሱን የሰጠ ይሆናል፤ሌላውን ደግሞ ይንቃል። ስለሆነም ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም። 14 ገንዘብን የሚወዱ ፈሪሳውያን ይህን ሁሉ ሰምተው፣ በኢየሱስ ላይ አፌዙበት። 15 እርሱም እንዲህ አላቸው፤ "እናንተ በሰው ፊት ራሳችሁን እንደ ጻድቃን ትቈጥራላችሁ፣ እግዚአብሔር ግን ልባችሁን ያውቃል። በሰዎች ፊት የከበረ በእግዚአብሔር ፊት የተጠላ ነው።" 16 ሕግና ነቢያት እስከ መጥምቁ ዮሐንስ ድረስ ሲሠራባቸው ኖረዋል። ከዚያ በኋላ ግን የእግዚአብሔር መንግሥት ወንጌል ተሰብኳል። ሰው ሁሉ ወደዚህ ለመግባት ይጋፋል። 17 ነገር ግን ከሕግ አንድ ነጥብ ዋጋ ከሚያጣ ሰማይና ምድር ቢያልፍ ይቀላል። 18 ማንም ሚስቱን ፈትቶ ሌላይቱን የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል፤ ከባሏ የተፋታችውንም የሚያገባ ያመነዝራል። 19 ኢየሱስ እንዲህ አለ፤ "ሐምራዊና ቀጭን የሐር ልብስ የለበሰ በየቀኑም በምቾትና በደስታ የሚኖር ሀብታም ሰው ነበረ። 20 ሰውነቱ በቊስል የተወረረ አልዓዛር የሚባል ለማኝም በሀብታሙ ሰው ደጅ ይተኛ ነበር። 21 አልዓዛርም ከሀብታሙ ማዕድ የተረፈውን ፍርፋሪ ሊመገብ ይመኝ ነበር። ውሾች እንኳ እየመጡ ቊስሉን ይልሱ ነበር። 22 ከጊዜ በኋላ ለማኙ ሞተ፤መላእክትም መጥተው ወደ አብርሃም አጠገብ ወሰዱት። ሀብታሙም ሞተ፤ ተቀበረም። 23 ሀብታሙ በሲኦል እየተሠቃየ ሳለ፣ ቀና ብሎ አብርሃም አልዓዛርን በዕቅፉ ይዞት አየ። 24 እርሱም፣ 'አብርሃም አባት ሆይ፣ ራራልኝ በዚህ ነበልባል እየተሠቃየሁ ስለ ሆነ፣ አልዓዛር የጣቱን ጫፍ በውሃ ነክሮ ምላሴን እንዲያቀዘቅዝልኝ እባክህ አልዓዛርን' ላክልኝ ብሎ ጮኸ። 25 አብርሃም ግን እንዲህ አለው፤ "ልጄ ሆይ፣ አንተ በምድር የሕይወት ዘመንህ መልካም ነገሮችን እንደተቀበልህና በደስታ እንደ ኖርህ፤ አልዓዛርም ክፉ ነገሮችን ሲቀበል እንደ ኖረ አስታውስ። አሁን ግን አልዓዛር እዚህ በምቾት ሲኖር፣ አንተ በሥቃይ ላይ ትገኛለህ። 26 ከሁሉ በላይ ከዚህ ወደ እናንተ ለማለፍ የሚፈልጉ እንዳይሻገሩ እዚያ ያሉትም ወደ እኛ እንዳይመጡ በእኛና በእናንተ መካከል ትልቅ ገደል አለ።' 27 ሀብታሙ ሰው እንዲህ አለ፤ 'አባት ሆይ፣ እንግዲያውስ አልዓዛርን ወደ አባቴ ቤተ ሰብ እንድትሰደው እለምንሃለሁ፤ 28 ምክንያቱም አምስት ወንድሞች አሉኝና እነርሱ ወደዚህ ሥቃይ ቦታ እንዳይመጡ ያስጠንቅቃቸው።' 29 አብርሃም ግን፣ 'ወንድሞችህ ሙሴና ነቢያት አሏቸው፤ እነርሱንም ይስሙአቸው' ብሎ መለሰለት። ነገር ግን 30 ሀብታሙ ሰው፣ 'አብርሃም አባት ሆይ፣ እንደዚህ አይደለም፤ አንድ ሰው ከሙታን ተነሥቶ ሄዶ ቢነግራቸው ንስሓ ይገባሉ' አለ። 31 አብርሃም ግን ሙሴንና ነቢያትን የማይሰሙ ከሆነ፣ አንድ ሰው ከሙታን ተነሥቶ ቢነግራቸው እንኳ አያምኑም' አለው።
ኢየሱስ ሌላ ግብረገባዊ ምሳሌ መናገር ጀመረ፡፡ ይህም ስለ አንድ ጌታ እና ገንዘቡን ስለሚያበድርለት አስተዳዳሪ ነበር፡፡ ይህም ቢሆን በሉቃስ 15፡3 ውስጥ የጀምረው ተመሳሳይ ታሪክ ክፍል እና በተመሳሳይ ቀን የተናገረው ነው፡፡ (ግብረገባዊ ምሳሌ የሚለውን ይመልከቱ)
ምንም እንኳን የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ተሰብስቦ ከሚያደምጠው ሕዝብ ውስጥ ቢሆኑም፣ የመጨረሻው ክፍል ፈሪሳውያንን እና ጸሐፍትን ያመለክታል፡፡
ይህ በግብረገባዊ ምሳሌው ውስጥ አዲስ ገጸባህሪን ያስተዋውቃል፡፡ (አዲስ እና ነበር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ሰዎች ለባለጸጋው ሰው ነገሩት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"የባለጸጋውን ሰው ንብረት በንዝህላልነት እያስተዳደረ እንደሆነ"
ባለጸጋው ሰው ጥያቄውን ያነሳው የሃብቱን አስተዳዳሪ ለመገሰጽ ነው፡፡ "እያደረግህ የምትገኘውን ሰምቻለሁ፡፡" (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
አስተዳዳሪው፣ ያሉትን አማራጮች ለመመልከት ሲል ይህንን ጥያቄ ያነሳው ለራሱ ነው፡፡ "ስለዚህ ሥራ…ማድረግ ያለብኝን ማሰብ ያስፈልገኛል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይልከቱ)
ይህ የሚያመለክተው ባለጸጋውን ሰው ነው፡፡ አስተዳዳሪው ባሪያ አልነበረም፡፡ "ቀጣሪዬ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡
"መሬት ለመቆፈር አቅም የለኝም" ወይም "መቆፈር/ማረስ አልችልም"
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "የማስተዳደር ሥራዬን ሳጣ" ወይም "ጌታዬ የአስተዳዳሪነት ሥራዬን ሲወስድብኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ እነዚያ ሰዎች ሥራ፣ ወይም ለኑሮ የሚያስፈልገውን ሌሎች ነገሮች እንደሚሰጡት ያመለክታል፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
"የአለቃው ንብረት ብድር የነበረባቸው ሰዎች" ወይም "የእርሱ አለቃ ሀብት በእጃቸው የነበረ ሰዎች፡፡" በዚህ ታሪክ ውስጥ ተበዳሪዎች/ባለዕዳዎቹ የነበረባቸው የወይራ ዘይት እና ስንዴ ነበር፡፡
"ተበዳሪው/ባለዕዳው አለ… አስተዳዳሪው ለባለዕዳው እንዲህ አለው"
ይህ ወደ 3,000 ሊትር የወይራ ዘይት ነው፡፡ (መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን የነበረ የመጠን መለኪያ)
"100…50…80" (ቁጥሮች የሚለውን ይመልከቱ)
"የውል ወረቀት" አንድ ሰው ምን ያህል እንዳለበት የሚያሳይ ወረቀት ነው፡፡
"አስተዳዳሪው ለሌላው ተበዳሪ እንዲህ አለ…ተበዳሪው/ባለዕዳው እንዲህ አለ…አስተዳዳሪው ባለእዳውን አለው
ይህን ወደ ዘመናዊ መለኪያ መለወጥ ትችላላችሁ፡፡ "ሃያ ሺህ ኪሎ ስንዴ" ወይም "አንድ ሺህ ቅርጫት ስንዴ" (መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን የነበረ የመጠን መለኪያ)
"ሰማንያ ዳውላ ስንዴ ብለህ ጻፍ፡፡" ይህን ወደ ዘመናዊ መለኪያ መለወጥ ትችላላችሁ፡፡ "አሥራ ስድስት ሺህ ኪሎ ስንዴ" ወይም "ስምንት መቶ ቅርጫት ብለህ ጻፍ"
ኢየሱስ ስለ ባለሃብቱ እና ሃብቱን ያበድርለት ስለነበረው አስተዳዳሪ የሚናገረውን ምሳሌ ጨረሰ፡፡ በቁጥር 9 ላይ፣ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ማስተማሩን ቀጠለ፡፡
ጽሁፉ ጌታው እንዴት የአሰተዳዳሪውን ድርጊት እንዳወቀ አይናገርም
"አወደሰ" ወይም "በመነልካም አየው" ወይም "ተቀበለው/አጸደቀለት"
"በዘዴ አደረገ" ወይም "ምክንያታዊ በሆነ መንገድ አደረገ"
ይህ የሚያመለክተው ስለ እግዚአብሔር ስለማያውቁ ወይም ግድ ስለማይላቸው ትክክለኛ እንዳልሆነው አስተዳዳሪ ያሉትን ነው፡፡ "የዚህ ዓለም ሰዎች" ወይም "ዓለማውያን ሰዎች"
እዚህ ስፍራ "ብርሃን" እግዚአብሔራዊ/ቅዱስ ለሆኑ ነገሮች ሁሉ ዘይቤያዊ አነጋገር ነው፡፡ "የእግዚአብሔር ሰዎች" ወይም "ቅዱሳን ሰዎች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
"እኔ" የሚለው የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው፡፡ "እኔ ግን እላችኋለሁ" የሚለው ሀረግ የታሪኩን ማጠቃላያ ያሳያል፤ አሁን ኢየሱስ ሰዎቹ እንዴት ታሪኩን በህይወታቸው ተግባራዊ እንደሚያደርጉት ይነግራቸዋል፡፡
እዚህ ስፍራ ትኩረት የተሰጠው ገንዘብን ሌሎችን ለመርዳት ስለመጠቀም ነው፡፡ "በዓለማዊ ሃብት እነርሱን በመርዳት ሰዎችን ወዳጆቻችሁ አድርጓቸው"
ለዚህ ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ኢየሱስ ገንዘብን "ጻድቅ ያልሆነ" ብሎ ሲጠራው ግነት እየተጠቀመ ነው፤ ምክንያቱም ዘላለማዊ ዋጋ የለውም፡፡ "ዘላለማዊ ዋጋ የሌለውን ገንዘብን በመጠቀም" ወይም "ምድራዊ ገንዘብን በመጠቀም" ወይም 2) ኢየሱስ ገንዘብን "ጻድቅ ያልሆነ" ብሎ በመጥራት ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት/ ይጠቀማል፤ ምክንያቱም ሰዎች አንዳንድ ጊዜ ገንዘብን ትክክል ባልሆነ መንገድ ያገኙታል ወይም ጠቀሙበታል፡፡ "ትክክለኛ ባልሆነ መንገድ ያገኛችሁትን ገንዘብ በመጠቀም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት እና ኩሸት እንደዚሁም አጠቃላ አስተያየት የሚሉትን ይመልከቱ)
ይህ የሚያመለክተው 1) ገንዘባቸውን ሌሎችን ለመርዳት ባዋሉት ደስ የሚሰኝ በሰማይ ያለ እግዚአብሔር፣ ወይም 2) በገንዘባችሁ የረዳችኋቸው ወዳጆቻችሁ፡፡
ይህ የእግዚአብሔር መኖሪያን፣ ሰማይን ያመለክታል፡፡
"አንድ አገልጋይ አይችልም"
"ሁለት የተለያዩ ጌቶችን በአንድ ጊዜ ማገልግል እንደማይችል" በውስጠ ታዋቂነት ተጠቁሟል
እነዚህ ሁለት ሀረጎች በመሰረቱ ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ብቸኛው እና ዋናው ልዩነታቸው በመጀሪያው ሀረግ የመጀመሪያው ጌታ ይጠላል፣ ሁለተኛው ጌታ በሁለተኛው ሀረግ ይጠላል፡፡
በቁጥር 14 ላይ ፈሪሳውያን በኢየሱስ ላይ እንዳፉዙበት የመረጃ ዳራ እንደሚጥ ይህ በኢየሱስ ትምህርት ማቆሚያ/ማረፊያ ነው፡፡ በቁጥር 15 ኢየሱስ ትምህርቱን ይቀጣላል ደግሞም ለፈሪሳውያን ምላሽ ይሰጣል፡፤ (የመረጃ ዳራ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ቃል ወደ መረጃ ዳራው ያመለክታል
"ገንዘብ እንዲኖራቸው የሚወዱ" ወይም "ለገንዘብ በጣም ስስታም የነበሩ"
"ፈሪሳውያን በኢየሱስ ላይ አፌዙ"
"ኢየሱስ ለፈሪሳውያን እንዲህ አላቸው"
"ራሳችሁን በሰዎች ፊት መልካም አድርጋችሁ ለማሳየት ትሞክራላችሁ"
እዚህ ስፍራ "ልቦች" የሚለው የሚያመለክተው የሰዎችን ፍላጎት ነው፡፡ "እግዚአብሔር እውነተኛ ፍላጎቶቻችሁን ያውቃል" ወይም "እግዚአብሔር ለምን እንደምታደርጉ አንቀሳቃሽ ምክንያታችሁን/ሰበበ ነገራችሁን ያውቃል" (ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ሰዎች በጣም ጠቃሚ ናቸው ብለው የሚያስቧቸው ነገሮች እግዚአብሔር የሚጠላቸው ናቸው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ እስከዚያ ጊዜ ድረስ የተጻፈውን የእግዚአብሔርን ቃል ሁሉ በአጠቃላይ ያመለክታል
x
"ማንም ሚስቱን የሚፈታ" ወይም "ማንም ሚስቱን የሚፈታ ሰው"
"በዝሙት ምክንያት ጥፋተኛ መሆን"
"አንዲት ሴት ያገባ ወንድ"
ኢየሱስ ህዝቡን ማስተማሩን እየቀጠለ ሳለ፤ አንድ ታሪክ መናገር ጀመረ፡፡ ይህም ስለ አልዓዛር እና ስለ አንድ ሀብታም ነው፡፡
እነዚህ ቁጥሮች ኢየሱስ ስለ ሀብታሙ ሰው እና አልዓዛር የሚናገረውን ታሪክ የመረጃ ዳራ ይሰጣሉ፡፡ (የመረጃ ዳራ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ኢየሱስ ታሪኩን መናገር ሲጀምር የሚያስተምራቸውን መረዳት እንዲችሉ ለታሪኩ ጅማሬ ምልከት ይሰጣል
ይህ ሀረግ በኢየሱስ ታሪክ ውስጥ አንድን ሰው ያስተዋውቃል፡፡ ይህ ሰው በእውን የነበረ ይሁን ወይስ ኢየሱስ ሊያስተምር የፈለገውን ነጥብ ግልጽ ለማድረግ በዚህ ታሪክ ውስጥ ብቻ የሚገኝ ስለመሆኑ ግልጽ አይደለም፡፡ (አዲስ እና ነበር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ይመልከቱ)
x
እዚህ ስፍራ ይህ ሀረግ የዋለው በታሪኩ ውስጥ መሸጋገሪያ ሆኖ ነው፡፡ የእናንተ ቋንቋ ይህን ለማድረግ መንገድ ካለው እዚህ ላይ ልትጠቀሙበት ትችላላችሁ፡፡ (አዲስ ትዕይንትን ማስተዋወቅ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "መላዕክት ወሰዱት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ባለጸጋው ከአብርሃም ዘር አንዱ ነበር
"አልዓዛር ወደ አባቴ ቤት እንዲሄድ ንገረው" ወይም "እባክህ፣ ወደ አባቴ ቤት እርሱን ላከው"
ይህ በቤት ውስጥ የሚገኙ ሰዎችን ያመለክታል፡፡ "ቤተሰቤ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
"አልዓዛር እንዲያስጠነቅቃቸው"
"በስቃይ የምንጨነቅበት ይህ ስፍራ" ወይም "በአስጨናቂ ስቃይ ውስጥ የምንገኝበት ይህ ስፍራ"
ኢየሱስ ስለ ባለጸጋው ሰው እና አልዓዛር የሚናገረውን ታሪክ ጨረሰ፡፡
ይህ ጽሁፋቸውን ያመለክታል፡፡ "ሙሴ እና ነቢያት የጻፉት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
"ወንድሞችህ ለሙሴ እና ነቢያት ትኩረት መስጠት አለባቸው"
ይህ ያልተፈጸመ ሁኔታን ይገልጻል፣ ነገር ግን ያባለጸጋ ሰው ይህ ቢሆን ይወዳል፡፡ "አንድ ሰው ከሙታን መሃል ወደ እነርሱ ቢሄድ" ወይም "አንድ የሞተ ሰው ተነስቶ ሄዶ ቢያስጠነቅቃቸው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (መላምታዊ ሁኔታዎች የሚለውን ይመልከቱ)
አስቀድሞ ከሞቱት ሁሉ ውስጥ፡፡ ይህ ሁኔታ የሚገልጸው በዓለም ከርሰ ምድር የተቀበሩ ሙታንን ሁሉ ነው፡፡
እዚህ ስፍራ "ሙሴ እና ነቢያቱ" የሚለው የሚወክለው እነርሱ የጻፏቸውን ነገሮች ነው፡፡ "ሙሴ እና ነቢያት ለጻፉት ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
አብርሃም መላምታዊው ሁኔታ ቢሆን/ቢፈጸምም የሚገሆነውን ይገልጻል፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ከሙታን ተመልሶ የመጣም ሰው ቢሆን እነርሱን ማሳመን አይችልም" ወይም "አንድ ሰው ከሞት ተመልሶ ቢመጣም እነርሱ አያምኑም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (መላምታዊ ሁኔታዎች እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)
x
1 ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አላቸው፤ "ወደ ኅጢአት የሚያመሩ ነገሮች መምጣታቸው የማይቀር ነው። ነገር ግን ለኅጢአት ምክንያት ለሚሆነው ሰው ወዮለት። 2 በእምነት ደካማ ከሆኑት ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን ከማስናከል ይልቅ ትልቅ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ባሕር ቢጣል ይሻለዋል። 3 ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። ወንድምህ ቢበድልህ ገሥጸው፤ ተመልሶ ከተጸጸተ ይቅር በለው፤ በቀንም ሰባት ጊዜ እንኳ ቢበድልህና ሰባት ጊዜ ተመላልሶ፤ 4 'ስለ ሠራሁት ኅጢአት ተጸጸትሁ' እያለ ወደ አንተ ቢመለስ ይቅር ልትለው ይገባል።" 5 ሐዋርያት ጌታን፣ "እምነት ጨምርልን" አሉት። 6 ጌታም እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፣ "የሰናፍጭን ዘር ያህል እምነት ቢኖራችሁ፤ ይህን የሾላ ዛፍ፣ 'ከመሬት ተነቅለህ ወደ ባሕር ተተከል' ብትሉት ይታዘዝላችኋል። 7 "በዕርሻ ወይም በበጎች እረኝነት የተሰማራ አገልጋይ ካላችሁ፣ አገልጋዩ ከሥራ ደክሞ ሲመለስ፣ ወዲያውኑ "ና ተቀመጥና እራትህን ብላ የሚለው ከእናንተ ማን ነው?" 8 "እራቴን አዘጋጅልኝ፤ እስክበላና እስክጠጣም ወገብህን ታጥቀህ ቆመህ አስተናግደኝ፤ ከዚያ በኋላ አንተ ደግሞ ትበላለህ ትጠጣለህም አይለውምን?" 9 ታዲያ አገልጋዩ የታዘዘውን ስለ ፈጸመ ጌታው ያመሰግነዋልን? 10 እንዲሁም እናንተም የታዘዛችሁትን ሁሉ ከፈጸማችሁ በኋላ የማንጠቅም አገልጋዮች ነን፤ 'የፈጸምነውም የታዘዝንውን ግዳጃችንን ብቻ ነው' ማለት አለባችሁ።" 11 ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄዱ ሳለ፣ ሰማርያንና ገሊላን በሚያዋስነው መንገድ ያልፉ ነበር። 12 ኢየሱስም ወደ አንዲት መንደር በገባ ጊዜ ዐሥር ለምጻሞች አገኙት። እነርሱም ከእርሱ ርቀው ቆሙና 13 ድምፃቸውን ከፍ አድርገው፣ "ኢየሱስ ሆይ፣ መምህር ሆይ፣ እባክህ ማረን" እያሉ ጮኹ። 14 ኢየሱስ ባያቸው ጊዜ፣ "ሂዱና ራሳችሁን ለካህናት አሳዩ" አላቸው። እነርሱም እየሄዱ ሳሉ፣ ከለምጻቸው ነጹ። 15 ከእነርሱ አንዱ ከለምጹ መፈወሱን ባየ ጊዜ፣ ጮክ ብሎ እግዚአብሔርን እያከበረ ተመለሰ። 16 በኢየሱስ እግር ሥር በግንባሩ ተደፍቶ አመሰገነው። እርሱም የሰማርያ ሰው ነበር። 17 ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አለ፣ "ዐሥሩም ለምጻሞች ተፈውሰው አልነበረምን? ታዲያ ዘጠኙ የት አሉ? 18 ከዚህ ከባዕድ ሰው በቀር እግዚአብርሔን ለማመስገን ተመልሶ የመጣ ሌላ የለምን?" 19 ኢየሱስ ሰውየውን፣ "ተነሥና ሂድ እምነትህ አድኖሃል" አለው። 20 ፈሪሳውያን ኢየሱስን፣ "የእግዚአብሔር መንግሥት መቼ ትመጣለች?" ብለው ለጠየቁት ጥያቄ እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፤ "የእግዚአብሔር መንግሥት የምትታይ አይደለችም።" ወይም'እነሆ፣ እዚህ ናት' 21 ወይም 'እነሆ፣እዚያ ናት' የምትባል አይደለችም። ምክንያቱም የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናት።" 22 ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አላቸው፤" ከሰው ልጅ ቀኖች አንዱን ለማየት የምትናፍቁበት ቀን ይመጣል። ነገር ግን አታዩትም። 23 ሰዎች፣ 'እነሆ፣ ክርስቶስ እዚህ ነው! ወይም እዚያ ነው!' ይሉአችኋል። ነገር ግን እነርሱን ሰምታችሁ አትፈልጉ፤ አትከተሉአቸውም። 24 መብረቅ በሰማይ ላይ ሲበርቅ ከዳር እስከ ዳር እንደሚያበራ፣ የሰው ልጅም በሚመጣበት ቀን እንዲሁ ይሆናል። 25 ነገር ግን ይህ ከመሆኑ በፊት የሰው ልጅ ብዙ መከራ ሊቀበል ይገባል። በዚህ ዘመን ሰዎችም ሊናቅና ሊነቀፍ ግድ ነው። 26 በኖኅ ዘመን እንደሆነው፣ በሰው ልጅ ዘመንም እንዲሁ ይሆናል። 27 ኖኅ ወደ መርከብ እስከገባበት ቀን ድረስ ሰዎች ሲበሉና ሲጠጡ፣ ሲያገቡና ሲጋቡና ነበር። ነገር ግን በዚያን ጊዜ የጥፋት ውሃ መጥቶ ሁሉንም አጠፋቸው። 28 እንደዚሁም በሎጥ ዘመን ሰዎች ይበሉ፣ ይጠጡ፣ ይሸጡ ይገዙ፣ አትክልት ይተክሉና ቤትም ይሠሩ እንደ ነበረ ይሆናል። 29 ሎጥ ከሰዶም በወጣበት ቀን ግን እሳትና ዲን ከሰማይ ዘንቦ ሁሉንም አጠፋ። 30 የሰው ልጅ በሚገለጥበት ቀንም እንዲሁ ይሆናል። 31 በዚያ ቀን በቤቱ ጣሪያ ላይ ያለ ሰው በቤቱ ውስጥ ያለውን ዕቃ ለመውሰድ አይውረድ። በዕርሻም ቦታ ያለ ሰው ወደ ቤቱ አይመለስ። 32 የሎጥን ሚስት አስታውሱአት። ሕይወቱን ሊያድን በራሱ መንገድ ለመሄድ የሚፈልግ ሁሉ ያጣታል። 33 ነገር ግን ሕይወቱን ለጌታ አሳልፎ የሚሰጥ ሁሉ ያድናታል። 34 ይህን እላችሏለሁ፣ "በዚያች ሌሊት ሁለት ሰዎች በአንድ ዐልጋ ላይ ይተኛሉ። 35 ከእነርሱም አንዱ ይወሰዳል፤ ሌላው ይቀራል። እንዲሁም ሁለት ሴቶች በአንድ ቦታ አብረው ይፈጫሉ፤ 36 አንድዋ ትወሰዳለች ሌላዋ ትቀራለች። ሁለት ሰዎች በአንድ ዕርሻ ቦታ ያርሳሉ፤አንዱ ይወሰዳል፤ ሌላው ይቀራል።" 37 ደቀ መዛሙርቱም ኢየሱስን፦ 'ጌታ ሆይ፤ ወዴት?' ብለው ጠየቁት። እርሱም፦ "በድን ባለበት አሞራዎች ይሰበባሉ።" ሲል መለሰላቸው።
ኢየሱስ ማስተማሩን ቀጥሏል፣ ነገር ግን ንግግሩን ወደ ደቀ መዛሙርቱ መልሷል፡፡ ይህ አሁንም የታሪኩ ተመሳሳይ ክፍል ሲሆን በሉቃስ 15፡3 ላይ የጀመረውን ታሪክ በዚያው ቀን ማስተማሩን ቀጥሏል፡፡
"ሰዎች ኃጢአት እንዲሰሩ የሚፈታተኑ ነገሮች በእርግጥ ይፈጠራሉ"
"ፈተናዎች እንዲመጡ ምክንያት ለሚሆን ሰው" ወይም "ሰዎች እንዲፈተኑ ምክንያት ለሚሆን ሰው"
ይህ መላምታዊ ሁኔታን ያስተዋውቃል፡፡ ይህ ማለት ይህ ሰው ሰዎች ኃጢአት እንዲሰሩ ምክንያት በመሆኑ የሚደርስበት ቅጣት ባህር ውስጥ ከመስመጥ የከፋ ይሆናል፡፡ (መላምታዊ ሁኔታዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ዙሪያ አስረው ቢወረውሩት" ወይም "በአንድ ሰው አንገት ዙሪያ ከባድ ድንጋይ ተደርጎ ቢወረወር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ ቃላት ሴቶችን እና ወንዶችንም ያመለክታሉ፡፡ (ጡንቻማነት የሚገልጹ ቃላት ሴቶችን ሲያካትት የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በጣም ትልቅ፣ ከባድ ክብ ድንጋይ ሲሆን እህል ለመፍጨት የሚያገለግል ነው፡፡ "ከባድ ድንጋይ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡
ይህ እዚህ ስፍራ የሚያመለክተው እምነታቸው ገና ደካማ የሆነውን ነው፡፡ "እነዚህ እምነታቸው ትንሽ የሆነ ሰዎች"
ይህ ይሁን ሳይባል የሚፈጸምን ኃጢአት የማመልከቻ መንገድ ነው፡፡ "ኃጢአት መፈጸም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡
ይህ ምናልባት ወደፊት ሊሆን ስለሚችል ድርጊት የሚናገር ሁኔታዊ ዐረፍተ ነገር ነው፡፡
እዚህ ስፍራ "ወንድም" የሚለው ቃል የዋለው ተመሳሳይ እምነት ያለው ሰው በሚለው ስሜት ነው፡፡ "መሰል አማኝ"
"የሰራው ስህተት እንደሆነ በብርቱ ንገረው" ወይም "እርሱን አርመው"
ይህ መላምታዊ ሁኔታ ነው፡፡ ይህ ፈጽሞ ላያጋጥም ይችላል፣ ነገር ግን ቢያጋጥም እንኳን ኢየሱስ ሰዎች ይቅር እንዲሉ ይናገራል፡፡(መላምታዊ ሁኔታ የሚለውን ይመልከቱ)
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስት ሰባት ቁጥር ለሙሉነት ምሳሌ/ምልክት ነው፡፡ "በቀን ውስጥ ብዙ ጊዜ፣ ደግሞም በእያንዳንዱ ጊዜ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ደቀ መዛሙርቱ ከእርሱ ጋር በሚናገሩበት ወቅት የተፈጠረ አጭር ጊዜ በኢየሱስ ትምህርተ መሃል አለ፡፡ ከዚያም ኢየሱስ ማስተማሩን ቀጠለ፡፡
"እባክህ የበለጠ እምነት ስጠን" ወይም "በእምነታችን ላይ ተጨማሪ እምነት ስጠን"
የሰናፍጭ ፍሬ በጣም ትንሽ ፍሬ ነው፡፡ ኢየሱስ ትንሽ እምነት እንኳን እንደሌላቸው እያመለከተ ነው፡፡ "የሰናፍጭ ፍሬ የሚያክል ትንሽ እምነት እንኳን ቢኖራችሁ፣ እናንተ" ወይም "እምነታችሁ የሰናፍጭ ፍሬ ያህል አይደለም- ነገር ግን ቢሆን ኖሮ፣ እናንተ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ እና ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚሉትን ይመልከቱ)
የዚህ አይነት ዛፍ የሚታወቅ ካልሆነ፣ ሌላ አይነት ዛፍ መተካት ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡ "የሾላ ዛፍ" ወይም "ዛፍ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (የማይታወቀውን መተርጎም የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ራሳችሁ ነቅላችሁ ራሳችሁ በባህር ትከሉት" ወይም "ከመሬት ነቅላችሁ በውቅያኖስ ወለል ትከሉት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"ዛፉ ይታዘዛችኋል፡፡" ይህ ውጤት ቅድመ ሁኔታዊ ነው፡፡ ይህ የሚሆነው እምነት ካላቸው ብቻ ነው፡፡
ኢየሱስ ማስተማሩን ጨረሰ፡፡ ይህ የዚህ ታሪክ የመጨረሻው ክፍል ነው፡፡
ኢየሱስ 10 ለምጽ ያለባቸውን ሰዎች ፈወሰ፡፡ ቁጥር 11 እና 12 የመረጃ ዳራ እና የሁኔታዎችን መቼ እና የት ይሰጣል፡፡ (የመረጃ ዳራ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ስፍራ ይህ ሀረግ የዋለው የአዲስ ትዕንት ጅማሬን ለማመልከት ነው፡፡ የእናንተ ቋንቋ ይህን ለማድረግ መንገድ ካለው እዚህ ስፍራ ልትጠቀሙበት ትችላላችሁ፡፡ (አዲስ ትዕይንትን ማስተዋወቅ የሚለውን ይመልከቱ)
"ኢየሱስ እና ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሩሳሌም እተጓዙ ሳለ"
ይህ ሀረግ መንደሯን ለይቶ አይናገርም፡፡
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ለምጽ ያለባቸው አስር ሰዎች አገኙት" ወይም "አስር ለምጽ ያለባቸው ሰዎች አገኙት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የክብር ምልክት ነው፣ ምክንያቱም ለምጽ ያለባቸው ወደ ሌሎች መቅረብ አይፈቀድላቸውም ነበር፡፡ በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
x
ለምጽ ያለባቸው ከለምጻቸው ስለ መፈወሳቸው ከካህናትን ማረጋገጫ ማግኘት ነበረባቸው፡፡ "ይመረምሯችሁ ዘንድ ራሳችሁን ለካህናት አሳዩ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ሰዎች ሲፈወሱ፣ ከዚያ ወዲያ የመንጻት ስርዓት አያደርጉም፡፡ ይህ ይበልጥ ግልጽ ሊደረግ ይችላል፡፡ "እነርሱ ከለምጻቸው ነጽ ተፈውሰው እና ንጹህ ሆነው ነበር" ወይም "እነርሱ ከለምጻቸው ተፈውሰው ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
"እንደ ተፈወሰ አወቀ" ወይም "ኢየሱስ እንደፈወሰው አወቀ"
"ወደ ኢየሱስ ተመልሶ መጣ"
"እግዚአብሔርን ጮሆ አመሰገነ"
"ተንበርክኮ በኢየሱስ እግር ስር በፊቱ ወደቀ፡፡" ይህንን ያደረገው ኢየሱስን ለማክበር ነው፡፡ (ምልክታዊ/ትዕምርታዊ ድርጊት የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ኢየሱስ አስሩን ለምጻሞች ስለ ፈወሰበት ታሪክ የመጨረሻው ክፈል ነው፡፡
ኢየሱስ አንዱ ሰው ስላደረገው ምላሽ ሰጠ፣ የተናገረው ግን በዙሪያው ለነበሩ ሰዎች ነበር፡፡ "ስለዚህም ኢየሱስ ለተሰበሰበው ሕዝብ እንዲህ አለ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ከሶስቱ ቃለምልልሳዊ ጥያቄዎች የመጀመሪያው ነው፡፡ ኢየሱስ እነዚህን ጥያቄዎች የተጠቀመባቸው ከተፈወሱት መሃል እግዚአብሔርን ለማክበር የመጣው አንዱ ብቻ በመሆኑ ምን ያህል እንደተደነቀ እና እንዳዘነ በዙሪያው ለነበሩ ሰዎች ለማሳየትነው፡፡ "አስር ሰዎች ተፈውሰው ነበር፡፡" ወይም "እግዚአብሔር አስር ሰዎችን ፈወሰ፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ከዚህ ባዕድ በስተቀር ለእግዚአብሔር ክብር ለመስጠት ማንም ተመልሶ አልመጣም!" ወይም "እግዚአብሔር አስር ሰዎች ፈወሰ፣ ሆኖም ይህ ባዕድ ብቻ ለእግዚአብሔር ክብር ለመስጠት ተመልሶ መጣ!" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
ሳምራውያን አይሁድ ያለሆነ ዝርያ አላቸው፤ እናም እነርሱ እግዚአብሔርን አይሁዶች በሚያመልኩበት ተመሳሳይ መንገድ አያመልኩም፡፡
"በእምነትህ ምክንያት ድነሃል/እምነትህ አድኖሃል፡፡" "እምነት" የሚለው ሀሳብ "እምነት" በሚለው ግስ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "በማመንህ ምክንያት፣ ዳግም ደህና ሆነሃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የት እንደሆነ እንኳን አናውቅም፤ ይህ የሆነው አንድ ቀን ኢየሱስ ከፈሪሳውያን ጋር በሚነጋገርበት ጊዜ ነው፡፡
ይህ የአዲሱ ትዕይንት መጀመሪያ ነው፡፡ አንዳንድ ትርጉሞች "አንድ ቀን" ወይም "አንድ ወቅት" በማለት ይጀምራሉ፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "አንድ ዕለት ፈሪሳውያን ኢየሱስን እንዲህ ሲሉ ጠየቁት፣ ‘የእግዚአብሔር መንግሥት መቼ ትመጣለች?'" (አዲስ ትዕይንትን ማስተዋወቅ እና አድራጊ ወይም ተደራጊ እንደዚሁም ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ ጥቅሶች የሚሉትን ይመልከቱ)
"መንግሥት" የሚለው ስም ጽንሰ ሀሳብ "መግዛት" በሚለው ግስ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "እግዚአብሔር በውስጣችሁ ይገዛል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይምለከቱ)
ኢየሱስ እርሱን ከሚጠሉ የሃይማኖት መሪዎች ጋር ይነጋገር ነበር፡፡ ለዚህ ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) "እናንተ" የሚለው ቃል ሰዎችን በአጠቃላይ ያመለክታል፡፡ "የእግዚአብሔር መንግሥት በሰዎች ውስጥ ናት" ወይም 2) "በውስጣችሁ" የሚለው ቃል የተተረጎመው "በመሃላችሁ" በሚል ነው፡፡ "የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡
"ነገር ግን በመጀመሪያ የሰው ልጅ መከራ መቀብል ይኖርበታል፡፡" ኢየሱስ ስለ ራሱ በሶስተኛ መደብ እየተናገረ ነው፡፡ (አንደኛ፣ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ መደብ የሚሉትን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር መገለጽ ይኖርበታል፡፡ "የዚህ ትውልድ ሰዎች እርሱን መቃወም/ ማስወገድ ይኖርባቸዋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"ሰዎች ነገሮችን በማከናወን ላይ ሳሉ…ሰዎች ተመሳሳይ ነገሮችን እያደረጉ ሳሉ"
"የኖህ ዘመን" ይህ እግዚአብሔር የዓለምን ሕዝብ ከመቅጣቱ አስቀድሞ ኖህ በኖረበት ዘመን ያለውን ወቅት ያመለክታል፡፡ "ኖህ ይኖር በነበረበት ዘመን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡
"የሰው ልጅ ቀናት" የሚለው የሚያመለክተው ልክ የሰው ልጅ ከመምጣቱ አስቀድሞ ያለውን ወቅት ነው፡፡ "የሰው ልጅ ሊመጣ ባለበት ጊዜ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው"
ሰዎች መደበኛ ነገሮችን ያደርጋሉ፡፡ እግዚአብሔር ሊፈርድባቸው እንደሆነ አያውቁም ወይም ለዚህ ግድ አይላቸውም፡፡
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ወላጆች ሴት ልጆቻቸውን እንዲያገቡ ለወንዶች ይፈቅዳሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"ታንኳ" ወይም "ጀልባ"
ይህ ኖህን እና በመርከቧ ውስጥ የነበሩ ቤተሰቦቹን አያጠቃልልም፡፡ "በጀልባዋ ውስጥ ያልገቡትን ሁሉ አጠፋ"
"የሎጥ ዘመን" የሚለው የሚያመለክተው እግዚአብሔር የሰዶም እና ገሞራን ከተሞች ከመቅጣቱ አስቀድሞ ያለውን ጊዜ ነው፡፡ "ሌላው ምሳሌ በሎጥ ዘመን እንዴት እንደሆነ የሚያሳይ ነው" ወይም "ሎጥ በኖረበት ዘመን ሰዎች ያደርጉት እንደነበረ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
"የሰዶም ሰዎች ይበሉ እና ይጠጡ ነበር"
"እሳት እና የሚነድ ዲን እንደ ዝናብ ከሰማይ ወረደ"
ይህ ሎጥን እና ቤተሰቡን አይጨምርም፡፡ "በከተማይቱ የነበሩትን ሁሉ አጠፋ"
"እንደዚያው ይሆናል፡፡" በተመሳሳይ መንገድ እንደዚያው ሰዎች የተዘጋጁ አይሆኑም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "የሰው ልጅ በሚገለጽበት ጊዜ" ወይም "የሰው ልጅ በሚመጣበት ጊዜ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ስለ ራሱ እየተናገረ ነው፡፡ "እኔ፣ የሰው ልጅ፣ እገለጻለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አንደኛ፣ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ መደብ የሚለውን ይመልከቱ)
"ማንም በቤት ጣራ ላይ የሚገኝ ወደ ታች አይውረድ" ወይም "ማንም ሰው በቤቱ ጣራ ላይ ቢሆን ወደ ታች መውረድ የለበትም"
የቤቶቻቸው ጣራ ጠፍጣፋ ነበር በዚያ ላይ መራመድ ወይም መቀመጥ ይችሉ ነበር፡፡
"ሃብቱን" ወይም "ያሉትን ነገሮች"
"በሎጥ ሚስት ላይ ደርሶ የነበረውን አስታውሱ" ይህ ማስጠንቀቂያ ነው፡፡ እርሷ ወደ ሰዶም እን ገሞራ ዘወር ብላ ስትመለከት እግዚአብሔር ከሰዶም ሰዎች ጋር እርሷን ቀጣት፡፡ "የሎጥ ሚስት ያደረገችውን አታድርጉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (የተተወ/የተዘለለ እና ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚሉትን ይመልከቱ)
"ሕይወታቸውን ለማትረፍ የሚሞክሩ ሰዎች ያጧታል" ወይም "ማንም የቀድሞ ሕይወቱን መንገድ መጠበቅ የሚሞክር ሕይወቱን ያጣል"
"ነገር ግን ሕይወታቸውን የሚጥሉ ሰዎች ያድኗታል" ወይም "ነገር ግን ማንም ያለፈውን የአኗኗር መንገዱን የሚተው ሕይወቱን ያድናል"
ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ መናገሩን ሲቀጥል፣ የሚነግራቸው ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ትኩረት ይሰጥ ነበር፡፡
ይህ የሚያመለክተው፣ እርሱ፣ የሰው ልጅ በምሽት ቢመጣ ምን እንደሚሆን ነው፡፡
ትኩረቱ እነዚህ ሁለት ሰዎች ላይ አይደለም፣ ነገር ግን አንዳንድ ሰዎች ይወሰዳሉ ሌሎች ይተዋሉ በሚለው ላይ ነው፡፡
"መከዳ" ወይም "ጎጆ"
"አንዱ ሰው ይወሰዳል ሌላው ሰው ይቀራል፡፡" ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "እግዚአብሔር አንዱን ሰው ይወስደዋል ሌላውን ይተዋል" ወይም "መላዕክት አንዱን ይወስዳሉ ሌላውን ይተዋሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ትኩረቱ በእነዚህ ሁለት ሴቶች ወይም በክንዋኔያቸው ላይ አይደለም፣ ነገር ግን አንዳንድ ሰዎች መወሰዳቸው ሌሎች መተዋቸው/ሳይወሰዱ መቅረታቸው ላይ ነው፡፡
"እህል አብሮ መፍጨት"
ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስን ስለ ትምህርቱ ጠየቁት እርሱም መለሰላቸው፡፡
"ጌታ ሆይ፣ ይህ የት ይሆናል?"
የዚህ አባባል ትርጉም፣ "ይህ ግልጽ ይሆናል" ወይም "ይህን ነገር በሚሆንበት ጊዜ ታውቁታለችሁ፡፡" "የጥንብ አንሳዎች መሰብሰብ በድን መኖሩን እንደሚያሳይ፣ እንደዚሁ ሁሉ እነዚህ ነገሮች የሰው ልጅ መምጫ መሆኑን ያሳያሉ" (ምሳሌያዊ አነጋገሮች የሚለውን ይመልከቱ)
ጥንብ አንሳዎች በአንድነት የሚበሩ እና ያገኙትን በድን ስጋ የሚመገቡ ትላልቅ ወፎች ናቸው፡፡ እነዚህን ወፎች በዚህ መንገድ መግለጽ ትችላላችሁ ወይም ይህንን የሚያደርጉ በአካባቢያችሁ የሚገኙ ወፎችን ስም መጠቀም መጠቀም ትችላላችሁ፡፡ (የማይታወቁትን መተረጎም የሚለውን ይመልከቱ)
1 ከዚያም ኢየሱስ ሳይታክቱ ዘወትር መጸለይ እንደሚገባቸው እንዲህ ሲል አንድ ምሳሌ ነገራቸው፤ 2 "በአንድ ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ፤ ሰውንም የማያከብር አንድ ዳኛ ነበረ። 3 አንዲት ባል የሞተባት ሴትም በዚያ ከተማ ነበረች። እርስዋም ዘወትር ወደ ዳኛው እየመጣች፣ 'ከባላጋራዬ ጋር ስላለኝ ክርክር ፍረድልኝ' ትለው ነበር። 4 ዳኛውም ለረጅም ጊዜ ሊረዳት ፈቃደኛ አልነበረም። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን ወደ ልቡ ተመልሶ እንዲህ ብሎ አሰበ፤ 5 'ምንም እንኳ እግዚአብሔርን ባልፈራ፣ ሰውንም ባላከብር፣ ይህች ባል የሞተባት ሴት አዘውትራ በመምጣት እንዳታታክተኝ እፈርድላታለሁ።' " 6 ከዚያም ጌታ እንዲህ አለ፤ "ቅንነት የሌለው ዳኛ የሚናገረውን ስሙ። 7 ታዲያ እግዚአብሔር ቀንና ሌሊት ወደ እርሱ ለሚጮኹት ምርጦቹ አይፈርድላቸውምን? 8 ደግሞስ አይታገሣቸውምን? እላችኋለሁ በቶሎ ይፈርድላቸዋል። ነገር ግን የሰው ልጅ በሚመጣበት ጊዜ በምድር እምነትን ያገኝ ይሆን?" 9 ከዚያም ኢየሱስ ጻድቃን እንደ ሆኑ በራሳቸው ለሚመኩና ሌሎችንም ለሚንቁ ይህን ምሳሌ ተናገረ፤ 10 "ሁለት ሰዎች ለመጸለይ ወደ ቤተ መቅደስ ሄዱ፤ አንዱ ፈሪሳዊ ሲሆን፣ ሌላው ቀራጭ ነበረ። 11 ፈሪሳዊው ቆሞ እንዲህ በማለት ስለ ራሱ ጸለየ፤ 'እግዚአብሔር ሆይ፣ እኔ እንደ ሌሎች ሰዎች ቀማኛ፣ ዐመፀኛ፣ አመንዝራ፣ ወይም እንደዚህ ቀራጭ እንኳ ስላልሆንሁ አመሰግንሃለሁ። 12 በሳምንት ሁለት ጊዜ እጾማለሁ፣ ከማገኘውም ሁሉ ዐሥራት አወጣለሁ።' 13 "ቀራጩ ግን ከርቀት ቆሞ ዐይኑን ወደ ሰማይ ሳያነሣ ደረቱን እየመታ፣ 'አምላኬ ሆይ፣ እኔን ኅጢአተኛውን ማረኝ!' ይል ነበር። እላችኋለሁ፣ 14 "ከሌላው ይልቅ ጻድቅ ሆኖ ይህ ሰው ወደ ቤቱ ተመለሰ ፤ ምክንያቱም ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳል፤ ራሱን የሚያዋርድ ከፍ ከፍ ይላል።" 15 እንዲዳስሳቸው ሰዎች ልጆቻቸውን ወደ እርሱ ያመጡ ነበር። ደቀ መዛሙርቱ ይህን ባዩ ጊዜ ገሠጹአቸው። 16 ኢየሱስ ግን ሕፃናትን ወደ እርሱ ጠራቸውና፣ "ሕፃናት ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ ተውአቸው አትከልክሏቸውም። የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ እነዚህ ላሉት ናትና። 17 እውነት እላችኋለሁ፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት እንደ ሕፃን በየዋህነት ያልተቀበላት ፈጽሞ አይገባባትም" አለው። 18 ከአለቆች አንዱ ኢየሱስን፣ "ቸር መምህር ሆይ፣ የዘላለምን ሕይወት ለማግኘት ምን ማድረግ ይገባኛል?" ብሎ ጠየቀው። 19 ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰለት፤ "ለምን ቸር ብለህ ትጠራኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በስቀር ቸር የለም። 20 ትእዛዛትን ሁሉ ታውቃቸዋለህ፤ እነርሱም፣ 'አትግደል፣ አታመንዝር፣ አትስረቅ፣ በሐሰት አትመስክር፣ እናትህንና አባትህን አክብር የሚሉ ናቸው።" 21 አለቃውም ፣ "እነዚህንማ ከሕፃንነቴ ጀምሬ ጠብቄአቸዋለሁ።" 22 ኢየሱስ ይህን በሰማ ጊዜ፣ ሰውየውን፣ "እንግዲያውስ ገና አንድ ነገር ማድረግ ይቀርሃል፤ ያለህን ሁሉ ሸጠህ ገንዘቡን ለድኾች ስጣቸው፤ በመንግሥተ ሰማያት ሀብት ይኖርሃል። ከዚያም በኋላ መጥተህ ተከተለኝ" አለው። 23 ሀብታሙ ሰውዬ ግን በጣም ባለጠጋ ስለ ነበረ፣ ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ። 24 ከዚያም ኢየሱስ ሰውየው እንዳዘነ አይቶ፣ "ሀብታም ለሆኑ ሰዎች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት እንዴት አስቸጋሪ ነው! 25 ሀብታም ሰው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢያልፍ ይቀላል" አለ። 26 የሰሙትም ሰዎች፣ "እንግዲያውስ ማን ሊድን ይችላል?" አሉ። 27 ኢየሱስ፣ "በሰው ዘንድ የማይቻል ነገር በእግዚአብሔር ዘንድ ይቻላል" ብሎ መለሰ። 28 ጴጥሮስ፣ "እነሆ፣ እኛ ያለንን ሁሉ ትተን ተከትለንሃል" አለው። 29 ከዚያም ኢየሱስ፣ "እውነት እላችኋለሁ፣ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ብሎ ቤቱን ወይም ሚስቱን፣ ወይም ወንድሞቹን፣ ወይም ወላጆቹን ወይም ልጆቹን የተወ 30 በዚህ ዓለም ብዙ ዕጥፍ በሚመጣውም ዓለም የዘላለምን ሕይወት የማያገኝ ማንም የለም" አላቸው። 31 ኢየሱስ ዐሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ከሰበሰበ በኋላ እንዲህ አላቸው፤ "አሁን ወደ ኢየሩሳሌም መሄዳችን ነው፤ ስለ ሰው ልጅ በነቢያት አስቀድሞ የተነገሩት ሁሉ ይፈጸማሉ። 32 እርሱ ለአሕዛብ ተላልፎ ይሰጣል፤ እነርሱም ያላግጡበታል፤ ያዋርዱታል፤ ይተፉበታልም። 33 ከገረፉትም በኋላ ይገድሉታል፤ በሦስተኛውም ቀን ከሞት ይነሣል።" 34 ደቀ መዛሙርቱ ግን ከዚህ ሁሉ ከተናገራቸው ነገሮች አንዱንም አልተረዱም። ይህ ቃልም ተሰውሮባቸው ነበር፤ ስለተባሉትም ነገሮች ምንም አልተረዱም። 35 ኢየሱስ ወደ ኢያሪኮ በቀረበ ጊዜ፣ አንድ ዐይነ ስውር ምጽዋት እየለመነ በመንገድ ዳር ተቀምጦ ይለምን ነበር፤ 36 ሕዝብ ሲያልፉ ሰምቶም እየሆነ የነበረውን ነገር ጠየቀ። 37 እነርሱም፣ የናዝሬቱ ኢየሱስ በዚህ በኩል እያለፈ መሆኑን ነገሩት። 38 ስለዚህ ዐይነ ስውሩ፣ "የዳዊት ልጅ ኢየሱስ ሆይ፣ እባክህ ማረኝ" እያለ ጮኸ። 39 እፊት እፊት ይሄዱ የነበሩት፣ "ዝም በል!" ብለው ዐይነ ስውሩን ገሠጹት። እርሱ ግን ድምፁን የበለጠ ከፍ አድርጎ፣ "የዳዊት ልጅ ሆይ፣ እባክህ ማረኝ" ብሎ ጮኸ። 40 ኢየሱስ ቆሞ ሰውየውን ወደ እርሱ እንዲያመጡት አዘዛቸው ። ከዚያም ዐይነ ስውሩ ወደ እርሱ በቀረበ ጊዜ፣ ኢየሱስ፣ 41 "ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ?" ብሎ ጠየቀው። "ጌታ ሆይ፣ ማየት እፈልጋለሁ" አለ። 42 ኢየሱስም፣ "እይ። እምነትህም አድኖሃል" አለው። ዐይነ ስውሩም ወዲያውኑ ማየት ቻለ። 43 እግዚአብሔርን እያመሰገነ ኢየሱስን ተከተለ። ሕዝቡ ሁሉ ይህን አይተው ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገኑ።
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ማስተማሩን ሲቀጥል ግብረገባዊ ምሳሌ መናገሩን ጀመረ፡፡ ይህ በሉቃስ 17፡20 ላይ የተጀመረው ታሪክ ክፍል ነው፡፡ ቁጥር 1 ኢየሱስ ሊናገር ያለውን ግብረገባዊ ምሳሌ ገለጻ ይሰጠናል፡፡ (ምሳሌያዊ አነጋገሮች የሚለውን ይመልከቱ)
"ከዚያም ኢየሱስ"
እዚህ ስፍራ "እርሱ እንዲህ አለ፤ ሳይታክቱ፡፡" በሚል አዲስ ዐረፍተ ነገር ሊጀምር ይችላል፡፡
እዚህ ስፍራ "አንዲት ከተማ" የሚለው አድማጭ ቀጥሎ የሚቀርበው ትረካ በከተማ ውስጥ እንደሚካሄድ እንዲያወቅ የማድረጊያ መንገድ ነው፣ ሆኖም የከተማይቱ ስም ጠቃሚ ፡፡ (የጽሁፍ አይነቶች የሚለውን ይመልከቱ)
"ስለ ሌሎች ሰዎች ግድ የማይለው"
ኢየሱስ ይህንን ሀረግ የተጠቀመበት አዲስ ገጸባህሪ ወደ ታሪኩ ለማስገባት/ማስተዋወቅ ነው፡፡ (አዲስ እና ነበር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ይመልከቱ)
መበለት ባሏ የሞተባት እና ደግማ ያላገበች ሴት ናት፡፡ ኢየሱስ ስለዚህች ሴት ማንም የሚረዳት እና በጉዳትዋ የሚደርስላት ሰው እንደሌላት አድርጎ አስቧታል፡፡
"እርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ዳኛውን ነው፡፡
" ከባላጋራዬ ጋር ስላለብኝ ጉዳይ ትክክለኛ ፍርድ ስጠኝ"
"ጠላቴ" ወይም "ሊጎዳኝ የሚሞክር ሰው፡፡" ይህ በሙግት ውስጥ ያለ ባለጋራ ነው፡፡ መበለቲቱ ሰውየውን ትክሰሰው ወይስ ሰውየው መበለቲቱን ይክሰሳት ግልጽ አይደለም፡፡
እዚህ ስፍራ ይህ በአጠቃላይ "ሰዎችን" ያመለክታል፡፡ (ጡንቻማነት የሚገልጹ ቃላት ሴቶችን ሲያካትት የሚለውን ይመልከቱ)
"ስለምትጨቀጭቀኝ"
"ታታክተኛለች"
"ሳታቋርት በመምታት"
ኢየሱስ ራሳቸውን ጻድቅ አድርገው ለሚመለከቱ ለሌሎች ሰዎች ሌላ ግብረገባዊ ምሳሌ መናገር ጀመረ፡፡ (ግብረገባዊ ምሳሌ የሚለውን መልከቱ)
"ከዚያም ኢየሱስ"
"ለአንዳንድ ሰዎች"
"ራሳቸውን ጻድቅ አድርገው ያሳመኑ"ነ ወይም "ራሳቸውን ጻድቅ አድርገው የሚያዩ"
በጣም የማይወዱ ወይም የሚጠሉ
"ወደ ቤተ መቅደስ አደባባይ"
የዚህ ሀረግ የግሪኩ ጽሁፍ ትርጉም ግልጽ አይደለም፡፡ ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) "ፈሪሳዊው ቆሞ ስለ ራሱ በዚህ መንገድ ጸለየ" ወይም 2) "ፈሪሳዊው ቆሞ በግሉ እንዲህ ጸለየ፡፡"
ዘራፊዎች ሰዎችን በማስገደድ ወይም የጠየቁትን የማይሰጧቸው ከሆነ እንደሚጎዷቸው ሌሎችን በማስፈራራት የሚሰርቁ ሰዎች ናቸው፡፡
ፈሪሳዊው ቀረጥ ሰብሳቢዎች እንደዘራፊዎች ኃጢአተኞች፣ በደለኞች እና ዘማውያን ናቸው ብሎ ያምናል፡፡ ይህ ይበልጥ ግልጽ ሊደረግ ይችላል፡፡ "እናም እኔ በእርግጥ እንደዚህ ሰዎችን እንደሚያታልል ኃጢአተኛ ቀረጥ ሰብሳቢ አይደለሁም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
"ካገኘሁት ነገር"
ኢየሱስ ምሳሌውን መናገሩን ጨረሰ፡፡ በቁጥር 14፣ ምሳሌው የሚያስተምረውን ነገር ያብራራል፡፡
"ከፈሪሳዊው ሩቅ ቆሞ፡፡" ይህ ዝቅ የማለት ምልክት ነው፡፡ ራሱን ከፈሪሳዊው አጠገብ መቆም እንደሚገባው ሰው አልቆጠረም፡፡
"ዐይኖቹን ማንሳት" ማለት ወደ አንድ ነገር መመልክት ማለት ነው፡፡ "ወደ ሰማይ ተመለከተ" ወይም "ወደ ላይ ተመለከተ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የከፍተኛ ሀዘን አካላዊ መግለጫ ምልክት ነው፣ ደግሞም የዚህን ሰው ንስሃ መግባት እና ራሱን ዝቅ ማድረጉን ያሳያል "ሀዘኑን ለማሳየት ደረቱን መታ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ትምዕርታዊ/ምልክታዊ ድርጊት የሚለውን ይመልከቱ)
"እግዚአብሔር ሆይ፣ እባክህ እኔን ማረኝ፡፡ እኔ ኃጢአተኛ ነኝ" ወይም "እግዚአብሔር ሆይ፣ ብዙ ኃጢአት ብፈጽምም እባክህ ይቅር በለኝ"
ጻድቅ የሆነበት ምክንያት እግዚአብሔር ኃጢአቱን ይቅር ስላለው ነው፡፡ "እግዚአብሔር ቀረጥ ሰብሳቢውን ማረው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በሉቃስ 17፡20 ላይ የጀመረው ታሪክ ተከታይ ትዕይንት ነው፡፡ ኢየሱስ ልጆችን ተቀብሎ ስለ እነርሱ ተናገረ፡፡
ይህ የተለየ ዐረፍተ ነገር ሆኖ ሊተረጎም ይችላል፡ "ዳሰሳቸው፡፡ ነገር ግን"
"ደቀ መዛሙርቱ የልጆቹ ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ኢየሱስ እንዳያመጧቸው ለማስቆም ሞከሩ"
"ኢየሱስ ሰዎቹ ህጻናቶቻቸውን ወደ እርሱ እንዲያመጡ ተናገረ"
እነዚህ ሁለት ዐረፍተ ነገሮች ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው፤ በአንድነት የተጣመሩት ትኩረት ለመስጠት ነው፡፡ አንዳንድ ቋንቋዎች በተለየ መንገድ ትኩረት ይሰጣሉ፡፡ "እናንተ በእርግጥ ልጆች ወደ እኔ እንዲመጡ መፍቀድ አለባችሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በሉቃስ 17፡20 ላይ የጀመረው ታሪክ ተከታይ ትዕይንት ነው፡፡ ኢየሱስ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ስለ መግባት ከአንድ የሃይማኖት መሪ ጋር መነጋገር ጀመረ፡፡
ይህ በታሪኩ ውስጥ አንድ አዲስ ገጸባህሪ ያስተዋውቃል፡፡ ይህ ሰው በስልጣኑ ብቻ እንዲታውቅ/እንዲለይ ሆኗል፡፡ (አዲስ እና ነበር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ይመልከቱ)
"ምን ማድረግ ይኖርብኛል" ወይም "ከእኔ ምን ይጠበቃል"
"መጨረሻ የሌለው ሕይወት መቀበል፡፡" "መውረስ" የሚለው ቃል ብዙውን ጊዜ የሚያመለክተው አንድ ሰው ሲሞት ለልጆቹ የሚተውላቸውን ሃብት ነው፡፡ ስለዚህ፣ ይህ ዘይቤ እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ተረድቷል እናም እግዚአብሔር የዘለዓለም ሕይወት እንዲሰጠው ይፈልጋል ማለት ሊሆን ይችላል፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ይህን ጥያቄ የሚጠይቀው የሃይማኖት መሪው ለጠየቀው ጥያቄ በቁጥር 18 ላይ እርሱ የሰጠውን መልስ መሪው እንደማይወደው ስለሚያውቅ ነው፡፡ ኢየሱስ መሪው የእርሱን ጥያቄ እንዲመልስለት አይጠብቅም፡፡ ኢየሱስ የሚፈልገው እርሱ ለመሪው ጥያቄ የሰጠው ምላሽ የመጣው፣ ብቻውን መልካም ከሆነው ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደሆነ እንዲረዳ ነው፡፡ "ከእግዚአብሔር በስተቀር ማንም መልካም እንዳልሆነ አንተ ታውቃለህ፣ ስለዚህ እኔን መልካም ማለት እኔን ከእግዚአብሔር ጋር መነጻጸር ነው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
"የሰው ነፍስ አታጥፋ"
"እነዚህን ትዕዛዛት ሁሉ"
"ኢየሱስ ሰውየው ያንን ሲናገር ሲሰማ"
"ለእርሱ መልስ ሰጠው"
"አሁንም አንድ ተጨማሪ ነገር ማድረግ ያስፈልግሃል" ወይም "እሰከ አሁንም ገና ያላደረግከው አንድ ነገር አለ"
"ያለህን ንብረት ሁሉ ሽጥ" ወይም "የራስህ የሆነውን ነገር ሁሉ ሽጥ"
"ገንዘቡን ለድሃ ሰዎች ስጥ"
እዚህ ስፍራ "በሰማይ ሀብት" የሚለው የሚያመለክተው የእግዚአብሔርን በረከት ነው፡፡ "በሰማይ የእግዚአብሔርን በረከት ታገኛለህ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)
"ደቀ መዝሙሬ ሆነህ ተከተለኝ"
ይህ ቃለአጋኖ ነው ፣ ጥያቄ አይደለም፡፡ "ወደ እግዚአብሔር መንግሥት….ይህ በጣም ጭንቅ ነው!" (ቃለ አጋኖ የሚለውን ይመልከቱ)
ግመል በመርፌ ቀዳዳ ማለፍ አይችልም፡፡ ኢየሱስ ምናልባትም ሃብታም ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባቱ እጅግ አስቸጋሪ ነው ለማለት ኩሸት እየተጠቀመ ይሆናል፡፡ (ኩሸት እና አጠቃላይ አስተያየት የሚሉትን ይመልከቱ)
x
"ኢየሱስን የሰሙት ሰዎች እንዲህ አሉ"
መልስ እየጠየቁ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ ነገር ግን ጥያቄውን ያነሱት ኢየሱስ በተናገረው መደነቃቸውን ለማጉላት ነው ማለት ይቻላል፡፡ "ከሆነ ማንም ከኃጢአት ሊድን አይችልም!" ወይም በአድራጊ ዐረፍተ ነገር፡ "እንዲህ ከሆነ እግዚአብሔር ማንንም አያድንም!" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)
"ሰዎች ማድረግ የማይችሉትን እግዚአብሔር ማድረግ ይችላል" ወይም "ሰዎች የማያደርጉትን፣ እግዚአብሔር ማድረግ ይችላል"
ይህ ወደ መንግስተ ሰማይ ስለመግባት የሚደረገው የመጨረሻው ንግግር ነው፡፡
ይህ ሀረግ የሚያመለክተው ደቀ መዛሙርቱን ብቻ ነው፣ እናም ከሃብታሙ መሪ ጋር ያነጻጽራል፡፡
"እኛ ትተናል" ወይም "እኛ ሁሉን ከኋላችን ትተን
"ሀብታችንን ሁሉ" ወይም "ያለንን ንብረት ሁሉ"
ኢየሱስ ይህንን አገላለጽ የተጠቀመው ሊናገር ስላለው ነገር አስፈላጊነት ትኩረት ለመስጠት ነው፡፡
ይህ አገላለጽ ደቀ መዛሙርቱን ብቻ ሳይሆን ነገር ግን ተመሳሳይ መስዋዕትነት የከፈለን ሁሉ ለማካተት የታቀደ ነው፡፡
ይህ በአዎንታዊ መልክ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ማንም…የተወ…ይቀበላል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ጥንድ አሉታዎች የሚለውን ይመልከቱ)
"ደግሞም በሚመጣው ዓለም የዘለዓለም ሕይወት"
ይህ በዚህ የታሪክ ክፍል በሉቃስ 17፡20 የጀመረው ቀጣይ ትዕይንት ነው፡፡ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ብቻ እየተናገረ ነው፡፡
ኢየሱስ አሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርት ብቻቸውን ከሌሎች ሰዎች ፈቀቅ አድርጎ ወስዶ
ይህ በኢየሱስ አገልግሎት ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ ጉልህ ለውጥ ያመለክታል
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ነቢያት ጽፈውት የነበረ/ነቢያት የጻፉት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የብሉይ ኪዳን ነቢያትን ያመለክታል፡፡
ኢየሱስ ስለ ራሱ "የሰው ልጅ" በማለት ይናገራል፡፡ " እኔ፣ የሰው ልጅ፣… እኔ…ራሴ…ራሴ…እኔ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አንደኛ፣ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ መደብ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ይሆናል" ወይም "ይከሰታል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "የአይሁድ መሪዎች ለአህዛብ አሳልፈው ይሰጡታል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ያፌዙበታል፣ በሀፍረት ያንገላቱታል፣ ደግሞም ይተፉበታል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ከሞቱ በኋላ ሶስተኛውን ቀን ያመለክታል፡፡ ሆኖም፣ ደቀ መዛሙርቱ ይህንን አልተረዱም፣ ስለዚህም ይህንን ገለጻ ይህ ቁጥር ሲተረጎም አለመጨመሩ ይመረጣል፡፡ (ተከታታይ ቁጥሮች የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ቁጥር የዋናው ታሪክ ክፍል አይደለም፣ ነገር ግን ስለዚህ ታሪክ ከፍል አስተያየት ነው፡፡ (የታሪክ መጨረሻ/ማጠቃለያ የሚለውን ይመልከቱ)
"እነርሱ ከእነዚህ ነገሮች መሃል አንዳች አልገባቸውም"
ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስ በኢየሩሳሌም እንዴት እንደሚሰቃይ እና እንደሚሞት የሰጠውን ገለጻ፣ እና እርሱ ከሞት እንደሚነሳ ነው፡፡
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ ነገር ግን ቃሉን ከእነርሱ የሰወረው እግዚአብሔር ይሁን ወይም ኢየሱስ ግልጽ አይደለም፡፡ "ኢየሱስ መልእክቱን ከእነርሱ ሰወረው" ወይም "እግዚአብሔር ኢየሱስ ለእነርሱ ይነግራቸው የነበረውን መልዕክት ትርጉም እንዳይረዱት ከለከላቸው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
x
ኢየሱስ ወደ ኢያሪኮ ሲቃረብ ዐይነስውሩን ሰው ፈወሰ፡፡ ይህ ቁጥር የመረጃ ዳራ እና ታሪኩ መቼ እና የት ስፍራ እንደተፈጸመ መረጃ ይሰጣል፡፡ (የመረጃ ዳራ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ስፍራ ይህ ሀረግ የዋለው የታሪኩን አዲስ ክፍል ጅማሬ ለማመልከት ነው፡፡ (አዲስ ትዕይንት ማስተዋወቅ የሚለውን ይመልከቱ)
"አንድ ዐይነስውር ተቀምጦ ነበር፡፡" እዚህ ስፍራ "አንድ" የሚለው ይህ ሰው ለታሪኩ ጠቃሚ ሆኖ መተዋወቁን ሲያመለክት ሉቃስ በስም አልጠቀሰውም፡፡ በታሪኩ ውስጥ አዲስ ተሳታፊ ነው፡፡ (አዲስ እና ነበር ተሳታፊዎችን ማስተዋወቅ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ስፍራ አዲስ ዐረፍተ ነገር መጀመር ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡ "መለመን፡፡ በሰማ ጊዜ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡
"በሕዝብ ጭንቅንቅ ውስጥ የሚገኙት ሰዎች ለዐይነ ስውሩ ነገሩት"
ኢየሱስ የመጣው በገሊላ ከምትገኘው፣ ከናዝሬት ከተማ ነው
"እርሱን እያለፈ እየሄደ ነበር"
ይህ ቃል አስቀድሞ በሆነ አንድ ሌላ ነገር ምክንየት የሆነን ትዕይንት ያመለክታል፡፡ በዚህ ሁኔታ፣ የተሰበሰበው ሕዝብ ለዐይነ ስውሩ ኢየሱስ እያለፈ እንደሆነ ነግረውታል፡፡
"ተጣራ" ወይም "ጮኸ"
ኢየሱስ የእሥራኤል ታላቅ ንጉስ፣ የዳዊት ትውልድ ነበር
"ራራልኝ" ወይም "ርህራሄህን አሳየኝ"
"ከተሰበሰበው ሕዝብ ከፊት ይሄዱ የነበሩ ሰዎች"
"ጸጥ እንዲል" ወይም "እንዳይጮህ"
ይህ ማለት ይበልጥ ድምጹን ከፍ አድርጎ ጮኸ ማለት ሊሆን ይችላል ወይም ይበልጥ ሳያቋርጥ በጽናት ጮኸ ማለት ይሆናል፡፡
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ሰዎቹ ዐይነስውሩን ወደ እርሱ እንዲያመጡት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"ማየት እችል ዘንድ"
ይህ ትዕዛዝ ነው፣ ነገር ግን ኢየሱስ ሰውየው ምንም ነገር እንዲያደርግ አላዘዘውም፡፡ ኢየሱስ ሰውየውን የፈወሰው እንዲፈወስ እርሱን በማዘዝ ነው፡፡ "አንተ አሁን ብራህንህን አግኝተሃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ትዕዛዞች - ሌሎች አጠቃቀሞች የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ ቃላት ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት/ ናቸው፡፡ ኢየሱስ ሰውየውን የፈወሰው በሰውየው እምነት ምክንያት ነበር፡፡ "እኔ አንተን የፈወስኩህ አንተ በእኔ በማመንህ ምክንያት ነው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
"ለእግዚአብሔር ክብር መስጠት" ወይም "እግዚአብሔርን ማወደስ/ማመስገን"
1 ኢየሱስ ኢያሪኮ ከተማ ገብቶ እያለፈ ሳለ፣ 2 ዘኬዎስ የሚባል አንድ የቀራጮች አለቃና ሀብታም ሰው ወዳለበት ስፍራ ደረሰ። 3 ዘኬዎስ ኢየሱስ የትኛው እንደ ሆነ ለማየት ይሞክር ነበር፣ 4 ነገር ግን አጭር ስለ ነበረ፣ ከሕዝቡ ብዛት የተነሣ አሻግሮ ማየት አልቻለም ነበር። ስለዚህ ኢየሱስ በዚያ መንገድ ያልፍ ስለነበር፣ ከሕዝቡ ቀድሞ ሮጠና ሊያየው በእንድ ሾላ ዛፍ ላይ ወጣ። 5 ኢየሱስ ወደ ስፍራው በደረሰ ጊዜ፣ ቀና ብሎ ተመለከተና፣ “ዘኬዎስ ሆይ፣ ዛሬ ወደ ቤትህ መሄድ እፈልጋለሁና ቶሎ ውረድ” አለው። 6 ስለዚህ ዘኬዎስ በፍጥነት ወርዶ በደስታ በቤቱ ተቀበለው። 7 ይህን የተመለከቱት ሰዎች ሁሉ፣ “በኃጢአተኛ ሰው ቤት ገባ” በማለት አጒረመረሙ። 8 ዘኬዎስ ተነሥቶ ቆመና ጌታን፣ “ጌታ ሆይ፣ የሀብቴን ግማሽ ለድሆች እሰጣለሁ፣ ያታለልሁት ሰው ካለ፣ የወሰድሁበትን አራት ዕጥፍ እመልስለታለሁ” አለው። 9 ኢየሱስ እንዲህ አለው፣ "ዛሬ ድነት ለዚህ ቤት መጥቷል። ምክንያቱም፣ እርሱ ደግሞ የአብርሃም ልጅ ነው። 10 የሰው ልጅ የመጣው የጠፉትን ሰዎች ሊፈልግና ሊያድን ነውና” አለ። 11 እነርሱ እነዚህን ነገሮች እንደ ሰሙ፣ ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም እየተቃረበ ስለ ነበር ሕዝቡ የእግዚአብሔር መንግሥት ወዲያው የሚገለጥ መሰላቸው። 12 ስለዚህ ኢየሱስ ንግግሩን በምሳሌ በመቀጠል እንዲህ አለ፣ “አንድ መኰንን የመንግሥት ሹመት ተቀብሎ ሊመጣ ወደ ሩቅ አገር ሄዶ ነበር። 13 ከዚያም፣ ከአገልጋዮቹ ዐሥሩን ጠርቶ ዐሥር ምናን ሰጣቸውና፣ “እስክመጣ ድረስ ይህን ነግዱበት” አላቸው። 14 ነገር ግን የአገሩ ሰዎች ይጠሉት ስለ ነበር፣ 'ይህ ሰው ተመልሶ በእኛ ላይ ገዥ እንዲሆን አንፈልግም' በማለት ተወካዮቻቸውን ከኋላው ላኩበት። 15 መኰንኑም ሹመቱን ተቀብሎ ሲመለስ፣ ነግደው ያተረፉትን ትርፍ ለመተሳሰብ ገንዘቡን የሰጣቸው አገልጋዮቹ እንዲጠሩለት አዘዘ። 16 የመጀመሪያው አገልጋይ ወደፊቱ ቀረበና፣ 'ጌታ ሆይ፣ ምናንህ ተጨማሪ ዐሥር ምናን አትርፎልሃል' አለው። 17 ጌታውም፣ “ደግ አድርገሃል፣ አንተ ታታሪ አገልጋይ። በጥቂቱ ስለ ታመንህ፣ በዐሥር ከተሞች ላይ ገዥ ትሆናለህ' አለው። 18 ሁለተኛውም ቀርቦ፣ 'ጌታ ሆይ፣ ምናንህ ዐምስት አትርፏል' አለው። 19 ጌታውም፣ 'በዐምስት ከተሞች ላይ ገዥ ሁን' አለው። 20 ሌላኛውም መጣና፣ 'ጌታ ሆይ፣ በደንብ አድርጌ በጨርቅ ጠቅለዬ ያስቀመጥሁት ምናንህ ይኸውልህ፣ 21 ይህን ያደረግሁት አንተ ጨካኝ ሰው መሆንህን ስላወቅሁ ፈርቼ ነው። አንተ ያላስቀመጥኸውን የምትጠይቅ ያልዘራኸውን የምታጭድ ነህ' አለው። 22 ጌታውም፣ እንዲህ አለው፤ 'አንተ ክፉ አገልጋይ፣ በአፍህ ቃል እፈርድብሃለሁ። ካላስቀመጥሁበት የምፈልግ፣ ካልዘራሁበት የማጭድ ጨካኝ ሰው መሆኔን ያወቅህ ከሆነ፣ 23 ታዲያ ስመለስ ገንዘቤን ከነትርፉ እንዳገኝ ለምን በባንክ አላስቀመጥኸውም?” 24 ከዚያም ጌታው በዚያ ለቆሙት ሰዎች፣ “ምናኑን ውሰዱበት፣ ዐሥር ላለውም ጨምሩለት' አላቸው፤ 25 እነርሱም፣ 'ጌታ ሆይ፣ አስር ምናን አለው እኮ' አሉት። 26 ጌትየውም፣ 'ላለው ይጨምርለታል፣ ከሌለው ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል። 27 በእነርሱ ላይ ገዥ እንዳልሆን የተቃወሙትን እነዚህን ጠላቶቼን ግን አምጡና በፊቴ ግደሏቸው' አለ። 28 ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች ከተናገረ በኋላ፣ ፊቱን ወደ ኢየሩሳሌም በማቅናት መንገዱን ቀጠለ። 29 ደብረ ዘይት በሚባለው ተራራ አጠገብ ወደሚገኝ ቤተ ፋጌና ቢታንያ በተቃረበ ጊዜ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱን 30 እንዲህ ብሎ ላካቸው፤ "ወደሚቀጥለው መንደር ሂዱ። ስትገቡ፣ ማንም ያልተቀመጠበትን አንድ የአህያ ውርንጫ ታስሮ ታገኛላችሁ። ፍቱትና አምጡልኝ። 31 ማንም፣ 'ለምን ትፈቱታላችሁ?' ብሎ ቢጠይቃችሁ፣ 'ለጌታ ያስፈልገዋል' በሉት" አላቸው። 32 የተላኩትም ወደ ስፍራው በደረሱ ጊዜ፣ ኢየሱስ እንደ ነገራቸው፣ የአህያውን ውርንጫ ታስሮ አገኙት። 33 ውርንጫውን እየፈቱ እያለ ባለቤቶቹ፣ 'ውርንጫውን ለምን ትፈቱታላችሁ?' አሉ። 34 እነርሱም፣ “ለጌታ ያስፈልገዋል” ብለው መለሱለት። 35 ወደ ኢየሱስ አመጡትና ልብሳቸውን በውርንጫው ጀርባ ላይ አንጥፈው ኢየሱስ እንዲቀመጥበት አደረጉ። 36 ኢየሱስ በሚሄድበት ጊዜ፣ ከፊቱ ባለው መንገድ ላይ ልብሶቻቸውን ያነጥፉለት ነበር። 37 ከደብረ ዘይት ተራራ ቁልቁል ወደሚወስደው መንገድ በቀረበ ጊዜ፣ ቊጥራቸው ብዙ የሆነ ደቀ መዛሙርት፣ ስላዩአቸው ድንቅ ነገሮች ሁሉ ደስ እያላቸው፣ “በጌታ ስም የሚመጣ ንጉሥ የተባረከ ነው! በሰማይ ሰላም፣ 38 ክብርም በአርያም ይሁንለት!” እያሉ በከፍተኛ ድምፅ እግዚአብሔርን አመሰገኑ። 39 በሕዝቡ መካከል የነበሩ አንዳንድ ፈሪሳውያን፣ “መምህር ሆይ፣ ደቀ መዛሙርትህን ገሥጻቸው” አሉ። 40 ኢየሱስም፣ “ልንገራችሁ፣ እነዚህ ዝም ቢሉ ድንጋዮችም እንኳ ይጮኻሉ” አላቸው። 41 ኢየሱስ ወደ ከተማይቱ በተቃረበ ጊዜ እንዲህ በማለት አለቀሰላት፤ 42 “ለአንቺ ሰላም የሚያመጣልሽን ነገር ምነው ዛሬ ባወቅሽ ኖሮ! አሁን ግን ከዐይንሽ ተሰውሮብሻል። 43 ጠላቶችሽ ዙሪያሽን ቅጥር ሠርተው የሚከቡሽና ከሁሉም አቅጣጫ የሚያስጨንቁሽ ጊዜያት ይመጣሉ። 44 አንቺንና ልጆችሽንም በምድር ላይ ይፈጠፍጣሉ። እነርሱም ድንጋይ በድንጋይ ላይ እንደተነባበረ አይተዉም፣ ምክንያቱም እግዚአብሔር ሊያድንሽ መፈለጉን አላወቅሽምና።” 45 ኢየሱስ ወደ ቤተ መቅደስ ገባና በዚያ ይሸጡ የነበሩትን ያባርራቸው ጀመር፣ 46 ከዚያም፣ “የአባቴ ቤት 'የጸሎት ቤት ይሆናል' ተብሎ ተጽፏል፣ እናንተ ግን የወንበዴዎች መሸሸጊያ አደረጋችሁት” አለ። 47 ስለዚህ ኢየሱስ በየዕለቱ በቤተ መቅደስ ያስተምር ነበር። ታዲያ የካህናት አለቆች፣ የሕግ መምህራንና የሕዝቡ መሪዎች ሊገድሉት ፈለጉ። 48 ነገር ግን ሕዝቡ ከልብ ያደምጡት ስለ ነበር መንገድ አላገኙም።
ከቁጥር 1-2 ያለው ለቀጣዩ ትዕይንት የመረጃ ዳራ መስጠት ይጀመራል፡፡ (የመረጃ ዳራ የሚለውን ይመልከቱ)
ቁጥር 3 ለተከታዩ ትዕይንት፣ በሉቃስ 19፡1-2 የቀረበውን መረጃ ያሟላል፡፡ (የመረጃ ዳራ የሚለውን ይመልከቱ)
"ዘኬዎስ ይሞክር ነበር"
"ምክንያቱም እርሱ አጭር ነበር"
ጸሐፊው ለትዕይንቱ ዳራ መስጠቱን ጨርሶ አሁን ትዕይንቱን ራሱን መግለጽ ጀምሯል፡፡
"የሾላ ዛፍ፡፡" ወደ 2.5 ሳናቲሜትር መጠን ያለው ትንሽ ክብ ፍሬ ያፈራል፡፡ "የሾላ ዛፍ" ወይም "ዛፍ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡
"ዛፉ" ወይም "ዘኬዎስ የነበረበት"
"ስለዚህም ዘኬዎስ ፈጥኖ"
አይሁዶት ቀረጥ ሰብሳቢ ይጠላሉ፤ ደግሞም ማንም መልካም ሰው ከእነርሱ ጋር ህብረት ማድረግ ይኖርበታል ብለው አያስቡም፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
"ኢየሱስ ወደ ኃጢአተኛ ሰው ቤት ገባ"
"ኃጢአተኛነቱ በግልጽ የሚታወቅ" ወይም "የለየለት ኃጢአተኛ"
"ይህ ኢየሱስን ያመለክታል"
"ከእነርሱ የወሰደኩትን አራት እጠፍ አድርጌ እመልሳለሁ"
መዳን ከእግዚአብሔር እንደሚመጣ ይታወቃል፡፡ "እግዚአብሔር ይህንን ቤት አዳነ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች እና ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚሉትን ይመልከቱ)
እዚህ ስፍራ "ቤት" የሚለው ቃል የሚያመለክተው በቤቱ ወይም በቤተሰቡ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን ነው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
"ይህም ሰው ደግሞ" ወይም "ዘኬዎስም ጭምር"
ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) "የአብርሃም ትውልዶች/ዘር" እና 2) "እንደ አብርሃም እምነት ያለው ሰው፡፡"
ኢየሱስ ስለ ራሱ እየተናገረ ነው፡፡ "እኔ፣ የሰው ልጅ፣ የመጣሁት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡
"ከእግዚአብሔር የራቁትን ሰዎች" ወይም "በኃጢአታቸው ከእግዚአብሔር የራቁትን"
ኢየሱስ ለተሰበሰበው ሕዝብ በግብረገባዊ ምሳሌ ማስተማር ጀመረ፡፡ ቁጥር 11 ኢየሱስ ለምን ግብረገባዊ ምሳሌውን እንደሚናገር የመረጃ ዳራ ይሰጣል፡፡ (ግብረገባዊ ምሳሌ እና የመረጃ ዳራ የሚሉትን ይመልከቱ)
አይሁዶች መሲሁ ወደ ኢየሩሳሌም እንደመጣ በቶሎ የእግዚአብሔርን መንግሥት ይመሰርታል ብለው ያምኑ ነበር፡፡ "ኢየሱስ በቶሎ በእግዚአብሔር መንግስት ላይ መግዛት ይጀምራል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
"ከገዢው መደብ አባል የሆነ አንድ ሰው" ወይም "ከከፍተኛ ቤተሰብ የሆነ አንድ ሰው"
ይህ ታናሽ ንግሥና ያለው ታላቅ ንግሥና ወዳለው መሄዱን ያሳያል፡፡ ታላቁ ንጉሥ ለታናሹ ንጉሥ በራሱ መንግሥት ላይ እንዲገዛ መብት እና ሥልጣን ይሰጠዋል፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ በሉቃስ 19፡11 የጀመረውን ግብረገባዊ ምሳሌ መናገሩን ቀጠለ፡፡
"ልዑሉ ጠራቸው፡፡" ሰውየው ይህንን ያደረገው የንጉሥነትን ማዕረግ/የእርሱን መንግሥት ለመቀበል ከመሄዱ አስቀድሞ እንደሆነ መግለጹ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡ "ከመሄዱ አስቀድሞ ጠራቸው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡
"ለእያንዳንዳቸው አንድ ምናን ሰጣቸው"
አንድ ምናን 600 ግራም ነው፤ ምናላባት ሰጣቸው ብር የተሰኘውን ማዕድን ሳይሆን አይቀርም፡፡ አንድ ምናን የ100 ቀን ሥራ ደሞዝ ያክላል፤ ሰዎች ወደ አራት ወራት ለሚጠጋ ጊዜ ሰርተው የሚያገኙት ክፍያ ነው፡፡ ስለዚህ አስር ምናን አንድ የቀን ሥራተኛ በሶስተ አመታት የሚከፈለው የክፍያ መጠን ነው፡፡ "አስር ከፍ ያለ ዋጋ ያላቸው ሳንቲሞች" ወይም "እጅግ ከፍተኛ የገንዘብ መጠን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ቁጥሮች እና ክብደት መለኪያ የሚሉትን ይመልከቱ)
"በዚህ ገንዘብ መነገድ" ወይም "ይህንን ገንዘብ ተጨማሪ ለማግኘት መጠቀም"
"የእርሱ አገር ሰዎች"
"እነርሱን የሚወክሉ ሰዎች ስብስብ/ቡድን" ወይም "በርካታ መልዕክተኞች"
እዚህ ስፍራ ይህ ሀረግ የዋለው በታሪኩ ውስጥ አስፈላጊ ትዕይንተን ለማመልከት ነው፡፡ የእናንተ ቋንቋ ይህንን ለማድረግ መንገድ ካለው፣ እዚህ ላይ ያንን መጠቀም ትችላላችሁ፡፡
"ከነገሠ በኋላ"
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ወደ እርሱ እንዲመጡ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"ምን ያህል ገንዘብ እንዳስገኙ"
ኢየሱስ በሉቃስ 19፡11 የጀመረውን ግብረገባዊ ምሳሌ መናገሩን ቀጠለ፡፡
"የመጀመሪያው አገልጋይ" (ተከታታይ ቁጥሮች የሚለውን ይመልከቱ)
"ልዑሉ ፊት ቀረቡ"
አገልጋዩ ያተረፈ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ "ምናንህ ተጨማሪ አስር ምናን እንዲያተርፍ አድርጌያለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
አንድ ምናን 600 ግራም ነው፤ ምናልባት የሰጣቸው ብር የተሰኘውን ማዕድን ሳይሆን አይቀርም፡፡ አንድ ምናን የ100 ቀን ሥራ ደሞዝ ያክላል፤ ሰዎች ወደ አራት ወራት ለሚጠጋ ጊዜ ሰርተው የሚያገኙት ክፍያ ነው፡፡ ይህ በሉቃስ 19፡13 ላይ እንዴት እንደ ተተረጎመ ይመልከቱ፡፡ (መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን የክብደት መለኪያ የሚለውን ይመልከቱ)
"አንተ መልካም ሰርተሃል፡፡" ቋንቋችሁ ቀጣሪ በትክክል መሰራቱን የሚያረጋግጥበት አገላለጽ/ሀረግ ሊኖር ይችላል፡፡ "ጥሩ ሰርተሃል" እንደሚለው አይነት፡፡
ይህ ልዑሉ በግልጽ ብዙ ገንዘብ ብሎ የማይቆጥረውን፣ አንድ ምናን ያመለክታል፡፡
ኢየሱስ በሉቃስ 19፡11 የጀመረውን ግብረገባዊ ምሳሌ መናገሩን ቀጠለ፡፡
"ሁለተኛው አገልጋይ" (ተከታታይ ቁጥሮች የሚለውን ይመልከቱ)
አገልጋዩ ያተረፈ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ "ጌታ ሆይ፣ ምናንህ ተጨማሪ አምስት ምናን እንዲያተርፍ አድርጌያለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
አንድ ምናን 600 ግራም ነው፤ ምናልባት የሰጣቸው ብር የተሰኘውን ማዕድን ሳይሆን አይቀርም፡፡ አንድ ምናን የ100 ቀን ሥራ ደሞዝ ያክላል፤ ሰዎች ወደ አራት ወራት ለሚጠጋ ጊዜ ሰርተው የሚያገኙት ክፍያ ነው፡፡ ይህ በሉቃስ 19፡13 ላይ እንዴት እንደ ተተረጎመ ይመልከቱ፡፡ (መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን የክብደት መለኪያ የሚለውን ይመልከቱ)
"በአምስት ከተሞች ላይ ስልጣን ይኖርሃል"
ኢየሱስ በሉቃስ 19፡11 የጀመረውን ግብረገባዊ ምሳሌ መናገሩን ቀጠለ፡፡
"ሌላው አገልጋይ መጣ"
አንድ ምናን 600 ግራም ነው፤ ምናልባት የሰጣቸው ብር የተሰኘውን ማዕድን ሳይሆን አይቀርም፡፡ አንድ ምናን የ100 ቀን ሥራ ደሞዝ ያክላል፤ ሰዎች ወደ አራት ወራት ለሚጠጋ ጊዜ ሰርተው የሚያገኙት ክፍያ ነው፡፡ ይህ በሉቃስ 19፡13 ላይ እንዴት እንደ ተተረጎመ ይመልከቱ፡፡ (መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን የክብደት መለኪያ የሚለውን ይመልከቱ)
x
ኢየሱስ በሉቃስ 19፡11 የጀመረውን ግብረገባዊ ምሳሌ መናገሩን ቀጠለ፡፡
የእርሱ "ቃላት" የሚለው የሚያመለክተው እርሱ የተናገረውን በሙሉ ነው፡፡ "አንተ በተናገርከው መሰረት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
ልዑሉ አገልጋዩ ስለ እርሱ የተናገረውን ይደግማል፡፡ ነገሩ እውነት ነው እያለ አይደለም፡፡ "አንተ እኔን ጨካኝ ሰው ነው ብለሃል"
ልዑሉ ይህንን ጥያቄ የተጠቀመው ክፉውን አገልጋይ ለመገሰጽ ነው፡፡ "እንዲወልድ ገንዘቤን በ… ማስቀመጥ ነበረብህ፡፡" (ቃለምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)
"ገንዘቤን ለባንክ ማበደር፡፡" ባንክ በሌላቸው ባህሎች ይህንን "ገንዘቤን ለሰው ማበደር" በሚል ሊተረጉሙ ይችላሉ፡፡
ባንክ የሰዎችን ገንዘብ በአስተማማኝነት የሚይዝ የንግድ ተቋም ነው፡፡ ባንክ ያንን ገንዘብ በትርፍ ለሌሎች ያበድራል፡፡ ስለዚህም በባንኩ ገንዘባቸው ላስቀመጡ፣ ተጨማሪ መጠን ወይም ወለድ፣ ይከፍላል፡፡
"ተቀማጩን ገንዘብ ከሚያስገኘው ወለድ ጭምር እወስድ ነበር" ወይም "ከእርሱ ትርፍ አገኝበት ነበር"
ትርፍ ገንዘባቸውን በባንክ ላስቀመጡ ሰዎች የሚከፍለው ገንዘብ ነው፡፡
ኢየሱስ በሉቃስ 19፡11 የጀመረውን ግብረገባዊ ምሳሌ መናገሩን ቀጠለ፡፡
ልዑል ይነግሣል፡፡ ይህ በሉቃስ 19፡12 ላይ እንዴት እንደ ተተረጎመ ይመልከቱ፡፡
ኢየሱስ በሉቃስ 19፡11 የጀመረውን ግብረገባዊ ምሳሌ መናገሩን ቀጠለ፡፡
ይህ የንጉሡ ንግግር ነበር፡፡ አንዳንድ ተርጓሚዎች ይህንን ቁጥር "ንጉሡም እንዲህ ሲል መለሰ፣ ‘እኔ ለእናንተ እላችኋለሁ'" ወይም "ነገር ግን ንጉሡ ‘ይህን እላችኋለሁ'" ብለው ሊጀምሩ ይችላሉ፡፡
እርሱ ያለው ምናኑን በታማኝነት በመጠቀም ያገኘው ገንዘብ መሆኑ በውስጠ ታዋቂነት ተጠቁሟል፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "የተሰጠውን በሚገባ ለተጠቀመ ሁሉ፣ እኔ ተጨማሪ እሰጠዋለሁ" ወይም "እኔ የሰጠሁትን ሁሉ በሚገባ ለሚጠቀም ሁሉ እኔ ተጨማሪ እሰጠዋለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)
ገንዘብ ሳይኖረው የቀረበት ምክንያት ምናኑን በታማኝነት አለመጠቀሙ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ "እኔ የሰጠሁትን በሚገባ ከማይጠቀምበት ሰው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "እኔ ከእርሱ እወስድበታለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ጠላቶች የተባሉት በቀጥታ በዚያ እስከሌሎ ድረስ፣ አንዳንድ ቋንቋዎች "እነዚያ የእኔ ጠላቶች" ሊሉ ይችላሉ፡፡
ይህ ስለ ዘኬዎስ የታሪኩ መጨረሻ ክፍል ነው፡፡ ይህ ቁጥር ከዚህ ታሪክ ክፍል በኋላ ኢየሱስ ምን እንዳደረገ ይነግረናል፡፡ (የታሪክ መጨረሻ የሚለውን ይመልከቱ)
"ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች በተናገረ ጊዜ"
ኢየሩሳሌም ከኢያሪኮ ከፍ ብላ ትገኛለች፣ ስለዚህ እሥራኤላውያን ወደ ኢየሩሳሌም እንውጣ ማለታቸው የተለመደ ነበር
ኢየሱስ ኢየሩሳሌም ደረሰ፡፡
እዚህ ስፍራ ይህ ሀረግ የዋለው በታሪኩ ውስጥ አስፈላጊ ትዕይንተን ለማመልከት ነው፡፡ የእናንተ ቋንቋ ይህንን ለማድረግ መንገድ ካለው፣ እዚህ ላይ ያንን መጠቀም ትችላላችሁ፡፡ (አዲስ ትዕይንት ማስተዋወቅ የሚለውን ይመልከቱ)
"እርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው፡፡ የእርሱ ዳመዛሙርትም አብረውት ይጓዙ ነበር፡፡
ቤተ ፋጌ በደብረዘይት ተራራ የነበረች (ዛሬም ያለች) መንደር ስትሆን፣ ከቄድሮን ሸለቆ ባሻገር ትገኛለች፡፡ (ስሞች እንዴት ይተረጎማሉ የሚለውን ይመልከቱ)
"ደብረዘይት የሚባል ተራራ/ኮረብታ" ወይም "‘የወይራ ፍሬ ተራራ' ተብሎ የሚጠራ ኮረብታ"
"ውርንጭላ አህያ" ወይም " ገና እያደገ የሚገኝ ለመጋለቢያ የሚውል እንስሳ"
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ማንም ያልተቀመጠበት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ገና ያልተጠየቀን ጥያቄ ስለመመለስ ይነግራቸዋል፡፡ ሆኖም፣ በመንደሯ የሚኖሩ ሰዎች ጥያቄውን ይጠይቃሉ፡፡ (መላምታዊ ሁኔታዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ውስጣዊ ጥቅሱ እንደ ቀጥተኛ እንዳልሆነ ጥቅስ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "ማንም ለምን ትፈቱታላችሁ ብሎ ቢጠይቃችሁ፣ እንዲህ በሉ" (በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ እና ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ ጥቅሶች)
ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ኢየሱስ የላካቸው ሁለቱ ደቀ መዛሙርት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"የውርጫው ባለቤቶች"
"መጎናጸፊያቸውን በውርንጫው ላይ አደረጉ፡፡" መደረቢያዎች ውጫዊ ልብስ ናቸው፡፡
"ኢየሱስን በውርንጫው ላይ አስቀመጡት"
"ሰዎች መደረቢያዎቻቸውን አነጠፉ፡፡" ይህ ክብርን የመስጠት ምልክት ነው፡፡ (ትምዕርታዊ/ምልክታዊ ድርጊት የሚለውን ይመልከቱ)
"ኢየሱስ እየቀረበ ሲመጣ፡፡" የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ከእርሱ ጋር ይጓዙ ነበር፡፡
"መንገዱ ከደብረዘይት ተራራ ቁልቁል ሲሄድ"
"ኢየሱስ ሲሰራ ባዩት ታላላቅ ነገሮች"
ይህን ይናገሩ የነበረው ስለ ኢየሱስ ነበር፡፡
እዚህ ስፍራ "ስም" የሚለው የሚያመለክተው ስለ ሀይል እና ስልጣን ነው፡፡ እንደዚሁም፣ "ጌታ" የሚለው የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ነው፡፡ (ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
"በሰማይ ሰላም ይሁን" ወይም "በሰማይ ሰላም ማየት እንሻለን"
"በላይ ክብር ይሁን" ወይም "ክብር በላይ ማየት እንፈልጋለን፡፡" "በላይ" የሚለው ቃል የሚመለክተው ሰማይን ነው፤ ይህም በሰማይ ለሚኖረው ለእግዚአብሔር ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት/ ነው፡፡ "ሁሉም በሰማይ ላለው ለእግዚአብሔር ክብር ይስጥ" (ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)
"በብዙ ሕዝብ መሃል"
"ደቀ መዛሙርትህ እነዚህን ነገሮች ማድረግ እንዲያቆሙ ንገራቸው"
ኢየሱስ ይህን ያለው ቀጥሎ ለሚናገረው ትኩረት ለመስጠትነው
ይህ መላምታዊ ሁኔታ ነው፡፡ ኢየሱስ ፡"አይ፣ እኔ አልገስጻቸውም፣ እነዚህ ሰዎች ዝም ቢሉ እንኳን… ይጮሃሉ" ብሎ ሲናገር ይህ ምንን እንደሚያመለክት አንደንድ ትርጉሞች ይህን ግልጽ ማድረግ ሊያስፈልጋቸው ይችላል፡፡ (መላምታዊ ሁኔታዎች እና ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚሉትን ይመልከቱ)
"ድንጋዮች ለምስጋና ድምጻቸውን ያሰማሉ"
ይህ የሚያመለክተው ኢየሩሳሌምን ነው
x
ኢየሱስ መናገሩን ቀጥሏል
ቀጥሎ የሚሆነው ለኢየሱስ ሀዘን ምክንያት ነው
ይህ የሚያመለክተው አስጨናቂ ወቅት እንደሚያጋጥማቸው ነው፡፡ አንዳድ ቋንቋዎች "ስለሚመጣው" ጊዜ አይናገሩም፡፡ "እነዚህ ነገሮች ወደፊት በአንቺ ላይ ይደርሳሉ፡ ጠላቶችሽ…" ወይም "በቶሎ አስጨናቂ ጊዜ ይገጥምሻል፡፡ ጠላቶችሽ…"
"አንቺ" የሚለው ቃል ነጠላ ቁጥር ነው፣ ምክንያቱም ኢየሱስ ለከተማይቱ የሚናገረው እንደ ሴት አድርጓት፡፡ ነገር ግን ይህ በእናንተ ቋንቋ ተፈጥሯዊ ካልሆነ የከተማዋን ሰዎች ለማመልከት "እናንተ" የሚለውን ብዙ ቁጥር መጠቀም ትችላላችሁ፡፡ (አንተ የሚለውን ተውላጠ ስም መልኮች እና የስርአተ ነጥብ ምልክት/ቃለአጋኖ የሚሉትን ይመልከቱ)
ይህ የሚያመለክተው ሰዎች ከከተማዋ ውጭ እንዳይገቡ የሚያግድን ግንብ ነው፡፡
ኢየሱስ ለከተማይቱ ሰዎች የሚናገረው ለከተማይቱ ለራሷ እንደሚናገር አድርጎ ነው፡፡ በከተማዋ ለሚኖሩ ሰዎች የሴትየዋ ልጆች እንደሆኑ እና ስለዚህም የከተማዋ ልጆች እንደሆኑ አድርጎ ነው፡፡ ከተማይቱን መምታት ቅጥሯን እና አጥሯን መደምሰስ ማለት ሲሆን፣ልጆችዋን መምታት ማትም በውስጧ የሚኖሩትን ሰዋች መግደል ማለት ነው፡፡ "ሙሉ ለሙሉ ይደመስሱሻል፣ ደግሞም በውስጥሽ የሚኖሩትን ሁሉ ይገድላሉ" ወይም "ከተማችሁን ሙሉ ለሙሉ ይደመስሳሉ፣ ደግሞም ሁላችሁንም ይገድላሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (የስርአተ ነጥብ ምልክት/ቃለአጋኖ የሚለውን ይመልከቱ)
"አንዲትንም ድንጋይ በስፍራዋ አይተዉም፡፡" ይህ ጠላቶች በድንጋይ የተገነባችውን ከተማ ሙሉ ለሙሉ እንሚደመስሱ በኩሸት ለመግለጽ የቀረበ ነው፡፡ (ኩሸት እና አጠቃላይ አስተያየት የሚሉትን ይመልከቱ)
"እውቅና አልሰጠሸም"
ይህ በዚህ የታሪክ ክፍል ቀጣዩ ትዕይንት ነው፡፡ ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ወደ ቤተመቅደስ ገባ፡፡
ቤተ መቅደሱ ወደሚገኝበት ወደ ኢየሩሳሌም እንደገባ ግልጽ ማድረግ ሊያስፈልጋችሁ ይችላል፡፡ "ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ ከዚያም ወደ ቤተመቅደሱ አደባባይ ሄደ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ወደ ቤተ መቅደስ ህንጻ መግባት የሚፈቀድላቸው ካህናት ብቻ ነበሩ፡፡ "ወደ ቤተመቅደስ አደባባይ ሄደ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
"አባረረ" ወይም "በሃይል አስወጣ"
ይህ ከኢሳይያስ የተወሰደ ጥቅስ ነው፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ቅዱሳት ጽሁፎች ይናገራሉ" ወይም "ነቢያት በቅዱሳት ጽሁፎች እነዚህን ቃሎች ጽፈዋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)
"የእኔ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ሲሆን "ቤት" የሚለው ቤተመቅደስን ያመለክታል፡፡
"ሰዎች ወደ እኔ የሚጸልዩበት ስፍራ"
x
ይህ የዚህ ታሪክ መጨረሻ ክፍል ነው፡፡ እነዚህ ቁጥሮች ዋናው የታሪኩ ክፍል ከተጠናቀቀ በኋላ ስለሚቀጥለው ድርጊት ይናገራሉ፡፡ (የታሪክ መጨረሻ የሚለውን ይመልከቱ)
"በቤተ መቅደስ አደባባይ/አጥር ግቢ" ወይም "በቤተ መቅደስ"
"ኢየሱስ ለሚናገረውን ከፍ ያለ ትኩረት ይሰጡ ነበር"
1 አንድ ቀን እንዲህ ሆነ፣ ኢየሱስ ሕዝቡን በቤተ መቅደሱ ውስጥ ያስተምርና ወንጌልን ይሰብክ በነበረ ጊዜ፣ የካህናት አለቆችና የሕግ መምህራን ከሽማግሌዎች ጋር ወደ እርሱ መጡ። 2 "እነዚህን ነገሮች የምታደርገው በምን ሥልጣን ነው? ወይም ይህን ሥልጣን የሰጠህ እርሱ ማን ነው?" አሉት። 3 እርሱም እንዲህ በማለት መለሰላቸው፤ "እኔም አንድ ጥያቄ እጠይቃችኋለሁ፣ እስቲ መልሱልኝ። 4 የዮሐንስ ጥምቀት ከሰማይ ነበር ወይስ ከሰዎች?" 5 እርስ በርሳቸው ተመካከሩና፣ "'ከሰማይ ነው ብንል፣ 'ታዲያ ለምን አላመናችሁትም ይለናል። 6 ነገር ግን 'ከሰው ነው ብንል' ሕዝቡ ዮሐንስን ነቢይ አድርገው ስለሚቆጥሩ ይወግሩናል" አሉ። 7 ስለዚህ ከየት እንደ ሆነ አናውቅም ብለው መለሱለት። 8 ኢየሱስ፣ "እኔም እነዚህን ነገሮች በምን ሥልጣን እንደማደርግ አልነግራችሁም" አላቸው። 9 ለሕዝቡ ይህን ምሳሌ ነገራቸው፣ "አንድ ሰው ያዘጋጀውን የወይን ዕርሻ ለወይን ገበሬዎች አከራይቶ ረጅም ጊዜ ሊቆይ ወደ ሌላ አገር ሄደ። 10 ምርቱ የሚሰበሰብበት ጊዜ ሲደርስ ከወይኑ የሚገባውን ፍሬ ለማግኘት ወደ ገበሬዎቹ አንድ አገልጋይ ላከ። ነገር ግን የወይኑ ገበሬዎች አገልጋዩን ደብድበው ባዶ እጁን መልሰው ላኩት። 11 እርሱም አሁንም ሌላ አገልጋይ ላከባቸው፣ ይህንም ደብድበውና አዋርደው ባዶ እጁን መልሰው ላኩት። 12 እንደ ገና ሦስተኛ አገልጋይ ቢልክባቸው፣ እርሱንም አቈሳስለው አውጥተው ጣሉት። 13 ስለዚህ የወይኑ ዕርሻ ባለቤት፣ 'ምን ላድርግ? የምወደውን ልጄን እልከዋለሁ። ምናልባት እርሱን ያከብሩት ይሆናል' አለ። 14 ነገር ግን የወይኑ ገበሬዎች ባዩት ጊዜ፣ 'ወራሹ ይህ ነው። ዕርሻው የእኛ እንዲሆን እንግድለው' ብለው እርስ በርስ ተመካከሩ። 15 ከዕርሻው ቦታ አወጡትና ገደሉት። እንግዲህ የዕርሻው ባለቤት ምን ያደርግባቸዋል? መጥቶ እነዚህን የወይን ገበሬዎች ይደመስሳቸዋል፣ 16 ዕርሻውንም ለሌሎች ይሰጣል" አላቸው። እነርሱም ይህን በሰሙ ጊዜ፣ "እግዚአብሔር እንዲህ ያለውን ነገር ያርቀው!" አሉ። 17 ኢየሱስ ግን ተመለከታቸውና፣ 'ግንበኞች የናቁት ድንጋይ የማዕዘን ራስ ሆነ' "የሚለው ይህ የመጽሐፍ ቃል ምን ማለት ነው? 18 በዚህ ድንጋይ የሚደናቀፍ ሁሉ ይሰባበራል። ነገር ግን ድንጋዩ የሚወድቅበት ሁሉ ይደቃል" አለ። 19 ስለዚህ፣ የሕግ መምህራንና የካህናት አለቆች በዚያን ሰዓት ሊይዙት ፈለጉ፣ ምክንያቱም ይህን ምሳሌ የተናገረው በእነርሱ ላይ እንደ ሆነ አውቀዋልና። 20 ነገር ግን ሕዝቡን ፈሩ። በዐይነ ቁራኛ እየተከታተሉት፣ ለፍርድና ለገዢው ሥልጣን የሚዳርገውን ስሕተት ከንግግሩ ሊያገኙበት ራሳቸውን ጻድቃን አስመስለው የሚቀርቡ ሰላዮችን ላኩበት። 21 እነርሱ እንዲህ በማለት ጠየቁት፤ "መምህር ሆይ፣ አንተ በትክክል እንደምትናገርና እንደምታስተምር፣ ደግሞም በማንም እንደማትመራ፣ነገር ግን ስለ እግዚአብሔር መንገድ እውነቱን እንደምታስተምር እናውቃለን። 22 ለቄሣር ግብር መክፈል ተፈቅዷል ወይስ አልተፈቀደም?" 23 ኢየሱስ ግን ተንኰላቸውን ተረዳ፣ እንዲህም አላቸው፣ 24 "አንድ ዲናር አሳዩኝ። በላዩ ያለው የማን ጽሑፍና ምስል ነው?" እነርሱም፣ "የቄሣር ነው" አሉት። 25 "እንግዲያውስ የቄሣር የሆኑትን ነገሮች ለቄሣር፣ የእግዚአብሔርን ነገሮች ለእግዚአብሔር ስጡ" አላቸው። 26 የሕግ መምህራንና የካህናት አለቆች በሕዝቡ ፊት በንግግሩ ሊያጠምዱት አልቻሉም። ምንም እስከማይናገሩ ድረስ በመልሱ ተደነቁ። 27 የሙታን ትንሣኤ የለም የሚሉ አንዳንድ ሰዱቃውያን ወደ እርሱ በመጡ ጊዜ፣ 28 እንዲህ ብለው ጠየቁት፤ "መምህር ሆይ፣ ሙሴ አንድ ሰው ሚስት አግብቶ ልጅ ሳይወልድ ቢሞት ወንድሙ የዚያን ሰው ሚስት አግብቶ ልጅ ለእርሱ እንዲወልድለት ጽፎልናል። 29 ሰባት ወንድማማች ነበሩ፤ የመጀመሪያው ሚስት አገባና ልጅ ሳይወልድ ሞተ፤ 30 ሁለተኛውም እንደዚሁ አግብቷት ልጅ ሳይወልድ ሞተ። 31 ሦስተኛውም አገባት፤ በዚህ ዓይነት ሰባቱም ሴቲቱን አግብተው ልጅ ሳይወልዱ ሞቱ። 32 በመጨረሻ ሴቲቱም ሞተች። 33 ታዲያ በትንሣኤ ቀን ይህች ሴት የማንኛቸው ሚስት ትሆናለች? ምክንያቱም ሰባቱም አግብተዋታልና።" 34 ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፤ "የዚህ ዓለም ሰዎች ያገባሉ፣ ይጋባሉም። 35 ነገር ግን የሙታን ትንሣኤንና የዘላለም ሕይወትን ለመቀበል የተገባቸው አያገቡም፣ አይጋቡምም። 36 እንደ መላእክት ስለ ሆኑ፣ ከእንግዲህ ወዲያ ሊሞቱ አይችሉም። የትንሣኤ ልጆች እንደ መሆናቸው መጠን የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው።" 37 ነገር ግን ሙታን ስለ መነሣታቸው ሙሴ እንኳ በቊጥቋጦው ስፍራ፣ጌታን የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅ አምላክና የያዕቆብ አምላክ ብሎ በመጥራቱ አሳይቷል። 38 አሁን እርሱ የሕያዋን እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም፣ ምክንያቱም ለእርሱ ሁሉም ሕያዋን ናቸው።" 39 ከሕግ መምህራን አንዳንዶች፣ "መምህር ሆይ፣ ጥሩ አድርገህ መልሰሃል" አሉት። 40 ደግሞም ተጨማሪ ጥያቄዎችን ለመጠየቅ ማንም አልደፈሩም። 41 ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፣ "እንግዲህ ሰዎች ክርስቶስን የዳዊት ልጅ ነው የሚሉት እንዴት ነው? 42 ዳዊት ራሱ በመዝሙር መጽሐፍ፣ "ጌታ ለጌታዬ ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ 43 እስከማደርግልህ ድረስ 'በቀኜ ተቀመጥ' ይላልና። 44 ስለዚህ ዳዊት ክርስቶስን ጌታ ይለዋል፣ታዲያ የዳዊት ልጅ እንዴት ይሆናል?" 45 ሕዝቡ ሁሉ እየሰሙ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አላቸው፣ 46 "ረጅም ቀሚስ ለብሰው መመላለስ ከሚፈልጉ፣ በገበያ ቦታዎችም ልዩ ሰላምታ፣ በምኲራቦች ከፍተኛ ስፍራ፣ በግብዣ ቦታዎችም የከበሬታ መቀመጫ እንዲሰጣቸው ከሚወዱ የሕግ መምህራን ተጠንቀቁ። 47 ደግሞም እነርሱ ረጅም የሆኑ የማስመሰል ጸሎቶችን እየጸለዩ የመበለቶችን ቤት አለአግባብ ይበዘብዛሉ። እነዚህ የባሰ ቅጣት ይቀበላሉ።"
የካህናት አለቆች፣ ጸሐፍትና ሽማግሌዎች በቤተ መቅደስ ኢየሱስን ጠየቁት
ይህ ሐረግ እዚህ ጥቅም ላይ የዋለው የታሪኩ አዲስ ጅማሬን ለማመልከት ነው፡፡
‹‹በቤተ መቅደሱ ግቢ›› ወይም፣ ‹‹በቤተ መቅደስ ውስጥ››
ኢየሱስ ለካህናት አለቆች፣ ለጸሐፍትና ለሽማግሌዎች መልስ ሰጠ፡፡
‹‹ኢየሱስ መለሰ››
‹‹እኔ እጠይቃችኃለሁ›› የሚለው ዐረፍተ ነገር ነው፡፡ ‹‹እናንተም ንገሩኝ›› ትእዛዝ ነው፡፡
የዮሐንስ ሥልጣን ከሰማይ መሆኑን ኢየሱስ ያውቃል፤ ስለዚህም የጠየቀው መረጃ እንዲሰጡት አይደለም፡፡ የጠየቀው የአይሁድ መሪዎች የሚያስቡትን ሰሚዎቹ ፊት እንዲናገሩ ነው፡፡ ጥያቄው መልስ የማያሻው ቢሆንም፣ እንደ ጥያቄ መተርጐም ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የዮሐንስ ሰዎችን የማጥመቅ ሥልጣን ከሰማይ የመጣ ይመስላችኃል ወይስ ከሰው?›› ወይም፣ ‹‹ዮሐንስ ሰዎችን እንዲያጠምቅ የነገረው እግዚአብሔር ነው ወይስ ሰው?
‹‹ከእግዚአብሔር›› አይሁድ እግዚአብሔርን፣ ‹‹ያህዌ›› በሚለው ስሙ መጥራት አይፈልጉም፡፡ ስለ እርሱ ሲናገሩ ብዙውን ጊዜ፣ ‹‹ሰማይ›› በሚለው ቃል ይጠቀማሉ፡፡
‹‹ስለዚህ የካህናት አለቆች፣ ጸሐፍትና ሽማግሌዎች መለሱ›› ‹‹ስለዚህ›› የሚለው ቃል መጀመሪያ ከሆነው ነገር የተነሣ የተፈጸመ ነገር መኖሩን ያመለክታል፡፡ በዚህ ጊዜ ሉቃስ 20፥5-6 ላይ ተመካክረው የነበረ ቢሆንም መልስ መስጠት አልቻሉም፡፡
ይህን በቀጥተኛ ጥቅስ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እነርሱም፣ ‹ከየት እንደሆነ አናውቅም› አለ››
‹‹የዮሐንስ ጥምቀት ከየት እንደ መጣ›› አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የዮሐንስ የማጥመቅ ሥልጣን ከየት እንደ መጣ›› ወይም፣ ‹‹ሰዎችን እንዲያጠምቅ ለዮሐንስ ማን ሥልጣን እንደ ሰጠው››
‹‹እኔም ብሆን አልነግራችሁም›› ኢየሱስ መልሱን ሊነግሩት ፈቃደኛ እንዳልሆኑ ሆነ አውቋል፤ ስለዚህ እርሱም ተመሳሳይ ነገር አደረገ፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እናንተ እንዳልተናገራችሁ እኔም አልነግራችሁም››
ኢየሱስ በቤተ መቅደስ ለሰዎች ምሳሌ መናገር ጀመረ፡፡
‹‹በከፈሉት መጠን የወይን ገበሬዎች እንዲጠቀሙበት ፈቀደ›› ወይም፣ ‹‹ገበሬዎቹ እንዲጠቀሙበትና በኃላ እንዲከፍሉት ፈቀደ›› ክፍያው በገንዘብ ወይም በምርቱ መጠን ሊሆን ይችላል፡፡
እነዚህ የወይን ፍሬ የሚያመርቱ ሰዎች ናቸው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ወይን የሚያለሙ ገበሬዎች››
‹‹ሊከፍሉት የተስማሙበት ጊዜ›› ይህ ምርቱ ሲደርስ ሊሆን ይችላል፡፡
‹‹ከፍሬው ጥቂቱን›› ወይም፣ ‹‹ከእርሻው ካመረቱት ጥቂቱን›› ይህም ከፍሬው የሠሩት ነገር ፍሬውን ሸጠው ያገኙት ገንዘብ ሊሆን ይችላል፡፡
ባዶ እጅ፣ ‹‹ምንም› ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ምንም ሳይከፍሉ ሰደዱት›› ወይም፣ ‹‹ፍሬ ሳይሰጡ ሰደዱት››
‹‹አገልጋዩን ደበደቡት››
‹‹አሳፈሩት››
በዶ እጅ፣ ‹‹ምንም›› ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሳይከፍሉ ሰደዱት›› ወይም፣ ‹‹ፍሬ ሳይሰጡ ሰደዱት››
‹‹ያም ሆኖ ሦስተኛ አገልጋይ›› ወይም፣ — ‹‹ያም ሆኖ›› የሚለው ባለ ርስቱ ሁለተኛውን አገልጋይ መላክ እንዳልነበረበት ግን እርሱ ከዚያም አልፎ ሦስተኛውን አገልጋይ እንደ ላከ ያመለክታል፡፡
‹‹አገልጋዩን ጐዱት››
‹‹ከወይን እርሻው ቦታ አወጡት››
ጥያቄው የወይኑ እርሻ ባለቤት ምን ማድረግ እንዳለበት በጥንቃቄ ማሰቡን አጽንዖት ይሰጣል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የማደርገው ይህን ነው››
‹‹የወይን ገበሬዎቹ የባለቤቱን ልጅ ሲያዩ››
ፈቃድ እየጠየቁ አልነበረም፤ ይህን ያሉት ወራሹን ለመግደል ሌሎችን ለማበረታታት ነው፡፡
ኢየሱስ ለሕዝቡ የሚናገረውን ምሳሌ አበቃ
‹‹የወይን እርሻው ገበሬዎች ልጁ ከወይኑ እርሻ እንዲወጣ አስገደዱት››
ኢየሱስ ይህን የጠየቀው የእርሻው ባለቤት ገበሬዎች ላይ የሚያደርገውን በተመለከተ የሰሚዎቹን ትኩረት ለመሳብ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እንግዲህ፣ ባለቤቱ እነርሱ ላይ የሚያደርገውን ስሙ››
‹‹እንዲህስ አይሁን››
ኢየሱስ ሕዝቡን ማስተማር ቀጥሏል፡፡
‹‹ኢየሱስ ግን ትኩር ብሎ አያቸው›› ወይም፣ ‹‹እርሱ ግን በቀጥታ አያቸው›› ይህን ያደረገው የነገራቸውን በመረዳታቸው ተጠያቂዎች መሆናቸውን ለማስገንዘብ ነው፡፡
ኢየሱስ ጥያቄውን ያቀረበው ሕዝቡን ለማስተማር ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ድንጋይ… ግንበኞች›› ተብሎ የተጻፈውን መረዳት ይኖርባችኃል፡፡››
‹‹ይህ ቃል››
ይህ ከመዝሙር መጽሐፍ ትንቢቶች ሦስት ተለዋጭ ዘይቤዎች የመጀመሪያው ነው፡፡ ይህኛው መሲሑ ግንበኞች የናቁት ድንጋይ፣ እግዚአብሔር ግን በጣም ጠቃሚ ያደረገው ድንጋይ መሆኑን ያመለክታል፡፡
ይህ የሚያመለክተው መሲሑ ኢየሱስን የናቁትን የሃይማኖት መሪዎች ነው፡፡
‹‹የሕንፃው ዋና ድንጋይ›› ወይም፣ ‹‹ከሕንፃው በጣም ጠቃሚ የሆነው ድንጋይ››
ይህ ሁለተኛው ተለዋጭ ዘይቤ መሲሑን የናቁ ሰዎች ድንጋይ ላይ ወድቀው እንደሚጐዱ ሰዎች መሆናቸውን ይናገራል፡፡
ይህ ድንጋይ ላይ የመውደቅ ውጤት ነው፡፡ በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እስኪደቅ ይሰባበራል››
‹‹ድንጋዩ የሚወድቅበት ግን›› ይህ ሦስተኛው ተለዋጭ ዘይቤ እነርሱ ላይ ወድቆ እንደሚፈጭ ግዙፍ ድንጋይ መሲሑ የናቁት ላይ እንደሚፈርድ ያመለክታል፡፡
በዚህ ቁጥር፣ ሰው ላይ ‹‹እጅ መጫን›› ሰውየውን ማሰር ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ኢየሱስን የሚያስሩበት መንገድ ፈለጉ››
‹‹ወዲያው››
ወዲያውኑ ኢየሱስን ያላሰሩት በዚህ ምክንያት ነበር፡፡ ሕዝቡ ኢየሱስን ያከብሩት ነበር፤ እርሱን ካሰሩት ሕዝቡ እነርሱ ላይ የሚያደርገውን የሃይማኖት መሪዎቹ ፈሩ፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሕዝቡን ስለ ፈሩ አላሰሩትም››
‹‹ጸሐፍትና የካህናት አለቆች ኢየሱስን የሚከታተሉ ሰላዮች ላኩ››
‹‹አንዳች መጥፎ ነገር ሲናገር ኢየሱስን መክሰስ ስለ ፈለጉ››
‹‹ግዛት›› እና ‹‹ሥልጣን›› አገረ ገዥው ኢየሱስ ላይ እንዲፈርድ እንደሚፈልጉ ለማመልከት ሁለት መንገዶች ናቸው፡፡ በአንዱ ወይም በሁለቱ አገላለጾች ሊተረጐም ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ገዢው ኢየሱስን እንዲቀጣ››
ይህ በዚህ የታሪኩ ክፍል የቀጣዩ ሁኔታ ጅማሬ ነው፡፡ ቤተ መቅደሱ ውስጥ ኢየሱስ በካህናት አለቆች ከተጠየቀ ወዲህ ጥቂት ጊዜ ሆኖት ነበር፡፡ አሁን ሰላዮቹ ኢየሱስን እየጠየቁት ነው፡፡
‹‹ሰላዮቹ ኢየሱስን ጠየቁት››
ሰላዮቹ ኢየሱስን ለማሳሳት እየሞከሩ ነው፡፡ ስለ ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች አያምኑም፡፡
‹‹እኛ›› የሚያመለክተው ሰላዮቹን ነው፡፡
‹‹ኢየሱስ ግን ምን ያህል ተንኰለኞች መሆናቸውን አወቀ›› ወይም፣ ‹‹ኢየሱስ ግን ሊያጠምዱት እንደሚሞክሩ አወቀ›› ‹‹የእርሱ›› የሚያመለክተው ሰላዮቹን ነው፡፡
ይህ የአንድ ቀን ደመወዝ የሚሆን የሮማውያን የብር ሳንቲም ነው፡፡
ሊያጠምዱት ለሚሞክሩ ሰዎች መልስ እንዲሆን ኢየሱስ በጥያቄ ተጠቀመ
‹‹ምስልና ስም››
ይህ የሰላዮቹ ተልዕኮና ሉቃስ 20፥1 ላይ ተጀምሮ የነበረው ታሪክ ማብቂያ ነው፡፡
‹‹ከዚያም ኢየሱስ እንዲህ አላቸው››
‹‹ቄሣር›› የሚያመለክተው የሮም ገዢን ነው፡፡
ካለፈው ሐረግ፣ ‹‹ስጡ›› የሚለውን መረዳት ይቻላል፡፡ እዚህ ላይ መደገም ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እና ለእግዚአብሔር ስጡ››
‹‹ሰላዮቹ እርሱ ከተናገረው አንዳች ጥፋት ማግኘት አልቻሉም››
ምንም እንኳ ይህ የሆነው ቤተ መቅደሱ ግቢ ውስጥ ሊሆን ቢችልም፣ በእርግጠኝነት አናውቅም፡፡ ኢየሱስ ከአንዳንድ ሰዱቃውያን ጋር እየተነጋገረ ነው፡፡
ሰዱቃውያን ማንም ሰው ከሞት አይነሣም የሚሉ የአይሁድ ወገን መሆናቸውን ይህ ሐረግ ያመለክታል፡፡ አንዳንድ ሰዱቃውያን በትንሣኤ እንደሚያምኑ፣ አንዳንዶቹ ግን እንደማያምኑ አይደለም የሚያመለክተው፡፡
‹‹አንድ ሰው ሚስት ያለው ወንዱሙ ልጅ ሳይወልድ ቢሞትበት››
x
ሰዱቃውያን ኢየሱስን መጠየቅ አበቁ
ቁጥር 29-32 ላይ ሰዱቃውያን ለኢየሱስ አጭር ታሪክ ነግረውታል፡፡ ይህ እንደ ምሳሌ የፈጠሩት ታሪክ ነው፡፡ ቁጥር 33 ላይ ስለ ነገሩት ታሪክ ኢየሱስን ጠየቁት፡፡
ይህ እውነት ሊሆን ይችላል፤ ምናልባትም ኢየሱስን ለመፈተን የፈጠሩትም ሊሆን ይችላል፡፡
‹‹የመጀመሪው ወንድም… ሁለተኛው ወንድም… ሦስተኛው ወንድም››
ኢየሱስ ለሰዱቃውያን መልስ መስጠት ጀመረ
‹‹የዚህ ዓለም ሰዎች›› ወይም፣ ‹‹የዚህ ዘመን ሕዝብ›› ይህ በሰማይ ካሉ ወይም ከትንሣኤ በኃላ ከሚኖሩት ጋር ሲነጻጸር ነው፡፡
በዚያ ባሕል ሰዎች ሴቶችን እንደሚያገቡ ሴቶችም ባሎቻቸውን እንደሚያገቡ ይናገራሉ፡፡ ይህን በሌላ መልኩ መናገር ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ይጋባሉ››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እግዚአብሔር ይገባችኃል የሚላቸው የዚያ ዘመን ሰዎች››
x
የኢየሱስ ለሰዱቃውያን መልስ መስጠት አበቃ
‹‹እንኳ›› የሚለው ቃል ቅዱሳት መጻሕፍት ሙታን ይነሣሉ ቢሉ እንኳ ሊደነቁ እንደማይችሉ፣ ሙሴ እንዲህ ያለ ነገር ይጽፋል ብለው ግን በፍጹም እንደማይጠብቁ ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የሞቱ ሰዎች እንደሚነሡ ሌላው ቀርቶ ሙሴ እንኳ አመልክቷል፡፡››
x
‹‹አንዳንድ ጸሐፍት ኢየሱስን አሉት›› ሰዱቃውያን ለኢየሱስ ጥያቄ ሲያቀርቡ ጸሐፍትም እዚያ ነበሩ፡፡
ይህ የሚያመለክተው ጸሐፍትን ወይም ሰዱቃውያንን ወይም ሁለቱንም መሆን አለ መሆኑ ግልጽ አይደለም፡፡ ዐረፍተ ነገሩን በአጠቃላይ መተው ይሻላል፡፡
ጥያቄ ለማቅረብ… ፈርተዋል›› ወይም፣ ‹‹ጥያቄ ማቅረብ አልደፈሩም›› የኢየሱስን ያህል መረዳት እንደሌላቸው ተረድተዋል፤ ያንን መናገር ግን አልፈለጉም፡፡ ይህን የበለጠ ግልጽ ማድረግ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የእርሱ አስተዋይ መልስ በድጋሚ ጅል አድርጐ እንዳያቀርባቸው ስለ ፈሩ ከእንግዲህ የተንኮል ጥያቄ አልጠየቁም››
ኢየሱስ ለጸሐፍት ጥያቄ አቀረበ
‹‹እንዴት ልጁ ነው… አሉ›› ኢየሱስ ጥያቄውን ያቀረበው ስለ መሲሑ ማንነት ጸሐፍት እንዲያስቡ ለማድረግ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እስቲ ልጁ… ነው ማለታቸውን እናስብ›› ወይም፣ ‹‹ልጁ ነው… ሲሉ ስለ እነርሱ መናገር እፈልጋለሁ››
ነቢያት፣ የሃይማኖት መሪዎችና በጠቅላላው የአይሁድ ሕዝብ መሲሑ የዳዊት ልጅ እንደሆነ ያውቃሉ፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሁሉም ይላል›› ወይም፣ ‹‹ሰዎች ይላሉ››
አሁን ኢየሱስ ትኩረቱን በቀጥታ ደቀመዛሙርቱ ላይ አድርጐ በዋናነት ስለ እነርሱ መናገር ጀመረ
‹‹ተጠበቁ››
ረጅም ቀሚስ ምን ያህል አስፈላጊ መሆናቸውን ያሳያል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አስፈላጊ ቀሚሳቸውን ለብሰው መዞር የሚወዱ››
‹‹የመበለቶችንም ቤት ይበላሉ›› ጸሐፍት የመበለቶችን ቤት የሚበሉ የተራቡ እንስሳት እንደ ሆኑ ተነግሯል፡፡ ‹‹ቤት›› የመበለቶቹን መኖሪያና ንብረታቸውን ሁሉ የሚያደርጉበትን ቦታ ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ከመበለቶቹም ንብረታቸውን ሁሉ ይወስዳሉ››
‹‹ዳድቅ እንደሆኑ ለማሳየት ረጅም ጸሎት ያደርጋሉ›› ወይም፣ ‹‹ሰዎች እንዲያዩዋቸው ረጅም ጸሎት ያደርጋሉ››
‹‹የበለጠ ከባድ ፍርድ ይቀበላሉ›› ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እግዚአብሔር በእርግጥ በጽኑ ይቀጣቸዋል››
1 ኢየሱስ ቀና ብሎ ሲመለከት ሀብታም ሰዎች በመባ መሰብሰቢያ ሣጥን ውስጥ ገንዘብ ሲጨምሩ አየ። 2 አንዲት ድኻ መበለት ደግሞ ሁለት ሳንቲሞችን ስትጨምር አየ። 3 ስለዚህ እንዲህ አለ፣ "እውነት እላችኋለሁ፣ ይህች ድኻ መበለት ከሁሉም የበለጠ ሰጠች። 4 እነዚህ ሁሉ የሰጡት ስጦታ ከተትረፈረፈ ሀብታቸው ነው። ይህች መበለት ግን በድኽነቷ መተዳደሪያዋን ሁሉ ሰጠች።" 5 አንዳንዶች ቤተ መቅደሱ በተዋቡ ድንጋዮች እንዴት እንዳማረና እንዳጌጠ ሲናገሩ ሰምቶ እንዲህ አለ፣ 6 "እነዚህ የምታዩአቸው ነገሮች፣ እንዲህ እንደተነባበሩ የማይቆዩበትና የሚፈራርሱበት ጊዜ ይመጣል" አለ። 7 ስለዚህ፣ "መምህር ሆይ፣ እነዚህ ነገሮች የሚሆኑት መቼ ነው? እነዚህ ነገሮች እንደሚፈጸሙ ምልክቱስ ምንድን ነው?" በማለት ጠየቁት። 8 ኢየሱስ፣ "እንዳትስቱ ተጠንቀቁ። ምክንያቱም ብዙዎች 'እኔ ኢየሱስ ነኝ፣ ደግሞም 'ጊዜው አሁን ነው' እያሉ በስሜ ይመጣሉ። አትከተሏቸው። 9 ስለ ጦርነቶችና ሁከቶች ስትሰሙ አትሸበሩ፣ እነዚህ ነገሮች አስቀድመው መፈጸም ይኖርባቸዋል፣ ነገር ግን መጨረሻው ወዲያው አይሆንም" ብሎ መለሰ። 10 ከዚያም እንዲህ አላቸው፣ "ሕዝብ በሕዝብ ላይ ይነሣል፣ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣል። 11 ታላቅ የመሬት መንቀጥቀጥ ይሆናል፣ ደግሞም በተለያዩ ቦታዎች ራብና ቸነፈር ይከሠታል። አስፈሪ ሁነቶችና ታላላቅ ምልክቶች ከሰማይ ይገለጣሉ። 12 ነገር ግን ከእነዚህ ሁሉ ነገሮች አስቀድሞ እናንተን ይይዟችኋል፣ ያሳድዷችኋል፣ ለምኩራቦችና ለወህኒ ቤቶች አሳልፈው በመስጠት ስለ ስሜ በገዦችና በነገሥታት ፊት ያቆሟችኋል። 13 ይህም ለእናንተ ለመመስከር ዕድልን ይሰጣችኋል። 14 ስለዚህ፣ አስቀድማችሁ ምን መከላከያ እናቀርባለን በማለት አትናወጡ፣ 15 ምክንያቱም በዚያን ጊዜ ጠላቶቻችሁ ሊቋቋሙትና ሊቃወሙት የማይችሉትን ቃልና ጥበብ እሰጣችኋለሁ። 16 ነገር ግን በወላጆች፣ በወንደሞች፣ በዘመዶችና በጓደኞች ተላልፋችሁ ትሰጣላችሁ፣ ከእናንተም አንዳንዶቹን ይገድላሉ። 17 በስሜ ምክንያት በሰው ሁሉ ትጠላላችሁ። 18 ነገር ግን ከራሳችሁ ጠጒር አንዲቱ እንኳ አትጠፋም። 19 በትዕግሥታችሁም ነፍሳችሁን ታተርፋላችሁ። 20 ኢየሩሳሌም በሠራዊት ተከብባ ስታዩ ጥፋቷ መቃረቡን እወቁ። 21 በዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ፣ በከተማይቱ መካከል ያሉትም ለቀው ይሂዱ፣ በገጠር ያሉት ደግሞ ወደ ከተማይቱ አይግቡ። 22 የተጻፈው እንዲፈጸም እነዚህ ጊዜያት የበቀል ጊዜያት ናቸውና። 23 በእነዚያ ቀኖች ለእርጉዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው! በምድሪቱ ላይ ታላቅ መከራ፣ በዚህ ሕዝብም ላይ ቊጣ ይወርዳል። 24 በሰይፍም ስለት ይወድቃሉ፤ ወደ ተለያዩ ሕዝቦች ሁሉ ምርኮኞች ተደርገው ይወሰዳሉ፤ የአሕዛብ ዘመን እስኪፈጸም ድረስ፣ ኢየሩሳሌም በአሕዛብ የተረገጠች ትሆናለች። 25 በፀሐይ፣ በጨረቃና በከዋክብት ምልክቶች ይታያሉ። በምድር ላይ ያሉ ሕዝቦች ከባሕርና ከማዕበል ድምፅ የተነሣ ተስፋ በመቊረጥ ይጨነቃሉ። 26 ከፍርሃትና በዓለም ላይ ሊከሰቱ ያሉትን ነገሮች ከመሥጋት የተነሣ የሚዝሉ ሰዎችም ይኖራሉ። ምክንያቱም የሰማያት ኅይላት ይናወጣሉና። 27 ከዚያም የሰው ልጅ በኅይልና በታላቅ ክብር በደመና ሲመጣ ያዩታል። 28 ነገር ግን እነዚህ ነገሮች መፈጸም ሲጀምሩ፣ መዳናችሁ ስለ ቀረበ ንቁ፣ ቀና ብላችሁ ተመልከቱ። 29 ኢየሱስ አንድ ምሳሌ ነገራቸው፤ “የበለስ ዛፍና ሌሎች ዛፎችን ተመልከቱ። 30 ቀንበጥ ሲያወጡ፣ በጋ እንደተቃረበ ታውቃላችሁ። 31 ልክ እንደዚሁም እነዚህ ነገሮች መፈጸማቸውን ስታዩ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ ቀረበ ታውቃላችሁ። 32 እውነቱን እነግራችኋለሁ፣ እነዚህ ሁሉ ነገሮች ከመፈጸማቸው በፊት ይህ ትውልድ አያልፍም። 33 ሰማይና ምድር ያልፋሉ፣ ቃሌ ግን አያልፍም። 34 ልቅ በሆነ አኗኗር፣ በስካርና በጭንቀት ልባችሁ እንዳይከብድ ተጠንቀቁ። ምክንያቱም ያ ቀን እንደ ወጥመድ በድንገት ይመጣባችኋል። 35 በምድር በሚኖሩት ሁሉ ላይም ይመጣባቸዋል። 36 ነገር ግን ከሚከሠቱት ከአነዚህ ነገሮች ሁሉ እንድታመልጡና በሰው ልጅም ፊት ለመቆም እንድትበረቱ ሁልጊዜ ነቅታችሁ ጸልዩ። 37 ስለዚህ ኢየሱስ በየቀኑ በቤተ መቅደስ ያስተምር፣ ሌሊቱን ደግሞ ወደ ደብረ ዘይት ተራራ እየወጣ ያሳልፍ ነበር። 38 በቤተ መቅደስም ሲያስተምር ሰዎች ሁሉ ሊሰሙት በማለዳ ይመጡ ነበር።
ይህ በታሪኩ ቀጣይ ጉዳይ ነው፡፡ ሰዱቃውያን እርሱን በጠየቁበት ቀን (ሉቃስ 20፥27) ወይም በሌላ ቀን ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ማስተማር ጀመረ
ስጦታዎቹ ምን እንደሆኑ መግለጽ ያስፈልግህ ይሆናል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የገንዘብ ስጦታዎች››
ሰዎች ገንዘባቸውን ለእግዚአብሔር የሚሰጡበት ቤተ መቅደስ ውስጥ ካሉ ሳጥኖች አንዱ፡፡
ይህ ወደ ታሪኩ አዲስ ገጸ ባሕርይ ለማስተዋወቅ የተለመደ መንገድ ነው፡፡
‹‹ሁለት ትንንሽ ሳንቲሞች›› ወይም፣ ‹‹ሁለት የናስ ሳንቲሞች›› እነዚህ ሰዎች የሚጠቀሙባቸው ዝቅተኛ ዋጋ ያላቸው ሳንቲሞች ናቸው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሁለት ሳንቲሞች›› ወይም፣ ‹‹ዝቅተኛ ዋጋ ያላቸው ሁለት ትንንሽ ሳንቲሞች››
x
ስለ መበለቷ ከመናገር ኢየሱስ ስለ ቤተ መቅደሱ ወደ ማስተማር ዞረ፡፡
ሰዎች ለእግዚአብሔር የሚሰጧቸው ነገሮች
ይህ የሚያመለክተው ያማረውን ቤተ መቅደስና ጌጦቹን ሁሉ ነው፡፡
‹‹ጊዜ ይመጣል›› ወይም፣ ‹‹አንድ ቀን››
እዚህ ላይ አዲስ ዐረፍተ ነገር መጀመር ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሌላው ላይ የሚቀር ሁሉም ይፈርሳሉ›› ወይም፣ ‹‹ሌላው ላይ የሚቀር ጠላቶች እያንዳንዱን ድንጋይ ያፈርሳሉ››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እያንዳንዱ ድንጋይ ከቦታው ይነሣል፤ ሁሉም ይፈርሳሉ››
እዚህ ላይ አዲስ ዐረፍተ ነገር መጀመር ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሌላው ላይ የሚቀር ሁሉም ይፈርሳሉ›› ወይም፣ ‹‹ሌላው ላይ የሚቀር ጠላቶች እያንዳንዱን ድንጋይ ያፈርሳሉ››
‹‹ደቀ መዛሙርት ኢየሱስን ጠየቁት›› ወይም፣ ‹‹የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ጠየቁት››
ይህ ጠላቶች ቤተ መቅደሱን እንደሚያፈርሱ ኢየሱስ የተናገረውን ያመለክታል፡፡
ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እየተናገረ ነበር፡፡ ‹‹እናንተ›› ብዙ ቁጥር ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሐሰት እንዳታምኑ›› ወይም፣ ‹‹ማንም እንዳያሳስታችሁ››
እርሱን እንወክላለን የሚሉ ሰዎች በእርሱ ስም ይመጣሉ፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እኔ ነኝ እያሉ›› ወይም፣ ‹‹የእኔ ሥልጣን እንዳለው እየተናገረ››
‹‹እኔ ክርስቶስ ነኝ›› ወይም፣ ‹‹እኔ መሲሑ ነኝ››
‹‹አትመኗቸው›› ወይም፣ ‹‹ደቀ መዛሙርቶቻቸው አትሁኑ››
እዚህ ላይ፣ ‹‹ጦርነት›› በአገሮች መካከል የሚደረግ ውጊያን፣ ‹‹ዐመፅ›› ሰዎች ከመሪዎቻቸው ጋር ወይም በአገራቸው ካሉት ሌሎች ጋር የሚያደርጉትን ግጭት ሊያመለክት ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ጦርነትና ረብሻ›› ወይም፣ ‹‹ጦርነትና አብዮት››
‹‹እነዚህ ነገሮች አያሸብሯችሁ›› ወይም፣ ‹‹አትፍሩ››
ይህ የመጨረሻውን ፍርድ ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ከጦርነቱና ከዐመፁ በኃላ ወዲያውኑ የዓለም ፍጻሜ አይሆንም›› ወይም፣ ‹‹እነዚህ ነገሮች ከተፈጸሙ በኃላ ወዲያው ዓለም አይጠፋም››
‹‹የማንኛውም ነገር መጨረሻ›› ወይም፣ ‹‹የዘመን መጨረሻ››
‹‹ከዚያም ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አለ›› ይህ ካለፈው ቁጥር የቀጠለ የኢየሱስ ንግግር በመሆኑ፣ አንዳንድ ቋንቋዎች፣ ‹‹ከዚያም እንዲህ አላቸው›› የሚለውን አይጠቀሙም፡፡
እዚህ ላይ፣ ‹‹ሕዝብ›› የሕዝብ ሰዎችን፣ ‹‹ይነሣል›› የሚለው ደግሞ፣ ‹‹ያጠቃል›› የሚለውን የሚወክል ሊሆን ይችላል፡፡ ‹‹ሕዝብ›› የሚለው ቃል አጠቃላይ ሕዝቦችን እንጂ፣ አንድን ሕዝብ ማለት አይደለም፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አንድ ሕዝብ የሌላውን ሕዝብ ያጠቃል›› ወይም፣ ‹‹የአንዳንድ ሕዝቦች ሌሎችን ሕዝቦች ያጠቃሉ››
ይህ አገሮችን ሳይሆን የተለያዩ ብሔሮችን ይወክላል፡፡
‹‹ይነሣል›› የሚለው ቃል ካለፈው ሐረግ ውስጠ ታዋቂ ሲሆን፣ ያጠቃል ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹መንግሥት በመንግሥት ላይ ይነሣል›› ወይም፣ ‹‹የአንዳንድ መንግሥታት ሕዝብ የሌላውን መንግሥታት ሕዝብ ይጠቃሉ››
‹‹ይኖራል›› የሚለው ቃል ካለፈው ሐረግ ውስጠ ታዋቂ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በብዙ ቦታዎች ራብና ቸነፈር ይሆናል›› ወይም፣ ‹‹በተለያዩ ቦታዎች የራብና የበሽታ ጊዜ ይሆናል››
ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስ የተናገራቸው ነገሮች እንደሚሆኑ ነው፡፡
‹‹ይይዟችኋል›› ይህ አገላለጽ ደቀ መዛሙርቱ ላይ ሥልጣን የሚኖራቸውን ሰዎች ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ያሥሩዋችኋል››
‹‹ሰዎች ያደርጋሉ›› ወይም ‹‹ጠላቶች ያደርጋሉ››
ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እየተናገረ ነበር፡፡ ‹‹እናንተ›› ብዙ ቁጥር ነው፡፡
‹‹ለምኩራብ መሪዎች አሳልፈው ይሰጧችኃል››
‹‹እስር ቤት ያስገቧችኋል›› ወይም፣ ‹‹ያሳስሩዋችኋል››
እዚህ ላይ፣ ‹‹ስም›› የሚያመለክተው ኢየሱስ ራሱን ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በእኔ ምክንያት›› ወይም፣ ‹‹እኔን ስለ ተከተላችሁ››
‹‹ስለ እኔ ምስክርነታችሁን እንድትነግሯቸው››
‹‹በዚህ ምክንያት›› ከሉቃስ 21፥10 ጀምሮ ኢየሱስ የተናገረውን ማንኛውንም ነገር ይመለከታል፡፡
እዚህ ላይ፣ ‹‹ልብ›› የሰዎቹን አእምሮ ይወክላል፤ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አእምሮአችሁን እንዳታዘጋጁ›› ወይም፣ ‹‹በቁርጥ እንዳትወስኑ››
‹‹ለሚነሣባችሁ ክስ ራሳችሁን ለመከላከል ምን እንደምትሉ ከጊዜው በፊት አታስቡ››
‹‹ከተቃዋሚዎቻችሁ አንዱ እንኳ፣ መቋቋምና ማስተባበል የማይችለው ጥበብ››
‹‹የምትናገሩትን ጥበብ እሰጣችኃለሁ››
ይህን በአንድ ዐረፍተ ነገር ማጣመር ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የጥበብ ቃል›› ወይም፣ ‹‹ጠቢብ ቃሎች››
ይህን በሌላ መልኩ መተርጐም ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሌላው ቀርቶ፣ ወላጆቻችሁ፣ ወንድሞቻችሁ፣ ዘመዶቻችሁና ጓደኞቻችሁ እንኳ ለባለ ሥልጣናት አሳልፈው ይሰጧችኋል፡፡››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሰራዊት ኢየሩሳሌምን ይከብባል››
‹‹በቅርቡ ትጠፋለች›› ወይም፣ ‹‹በቅርቡ ያጠፏታል››
‹‹ከአደጋ አምልጡ››
ይህ የሚያመለክተው ከኢየሩሳሌም ውጪ ያለውን ገጠር እንጂ፣ አገሩን በሙሉ አይደለም፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ከከተማ ውጪ››
‹‹ወደ ኢየሩሳሌም ግቡ››
‹‹እነዚህ የቅጣት ቀኖች ናቸው›› ወይም፣ ‹‹ይህ እግዚአብሔር ይህቺን ከተማ የሚቀጣበት ቀን ይሆናል››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ከብዙ ጊዜ በፊት በቅዱሳት መጻሕፍት ነቢያት የጻፉዋቸው ነገሮች ሁሉ››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ይሆናል››
‹‹ልጆቻቸውን ለሚያጠቡ እናቶች››
ይህም ማለት፣ 1) በምድሪቱ የሚኖሩ መከራ ይደርስባቸዋል፤ ወይም 2) ምድሪቱ ላይ መከራ ይደርስባታል፡፡
‹‹ሕዝቡ ላይ ቁጣ የሚሆንበት ጊዜ›› እግዚአብሔር ይህን ቁጣ ያመጣል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ይህ ሕዝብ ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ይመጣል›› ወይም፣ ‹‹እግዚአብሔር በጣም ይቆጣል ይህንም ሕዝብ ይቀጣል››
‹‹በሰይፍ ስለት ይገደላሉ›› እዚህ ላይ፣ ‹‹በሰይፍ ስለት ይገደላሉ›› የሚለው በጠላት ወታደሮች መገደልን ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የጠላት ወታደሮች ይገድሏቸዋል››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ጠላቶቻቸው ይይዟቸዋል፤ ወደ ሌሎች አገሮችም ይወስዷቸዋል››
‹‹ሁሉ›› የሚለው ወደ ብዙ አገሮች እንደሚወሰዱ አጽንዖት ለመስጠት ጥቅም ላይ የዋለ ግነት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ወደ ሌሎች ብዙ አገሮች››
ይህም ማለት፣ 1) አሕዛብ ኢየሩሳሌምን ድል አድርገው ይይዟታል፡፡ ወይም 2) አሕዛብ የኢየሩሳሌም ከተማን ይጠፋሉ ወይም 3) አሕዛብ የኢየሩሳሌምን ሕዝብ ይደመስሳሉ፡፡
ተለዋጭ ዘይቤው ኢየሩሳሌም የሌላ አገር ሰዎች እንደሚራመዱባትና በእግራቸውም እንደሚያደቋት ይናገራል፡፡ ይህ ባርነትን ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በአሕዛብ ድል ትሆናለች›› ወይም፣ ‹‹በሌላ ሕዝብ ትደመሰሳለች››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የአሕዛብ ወቅት እስኪያበቃ››
‹‹ሕዝቦች›› ውስጣቸው ያሉትን ሰዎች ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሰዎች ይጨነቃሉ››
x
ኢየሱስ ስለ ራሱ እየተናገረ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እኔ፣ የሰው ልጅ ስመጣ››
‹‹በደመና ውስጥ ሲመጣ››
እዚህ ላይ፣ ‹‹ኀይል›› ዓለም ላይ ለመፍረድ የእርሱን ሥልጣን የሚያመለክት ሊሆን ይችላል፡፡ ‹‹ክብር›› ደማቅ ብርሃንን ሊያመለክት ይችላል፡፡ አንዳንዴ እግዚአብሔር በደማቅ ብርሃን ታላቅነቱን ያሳያል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ኀያልና ክቡር›› ወይም፣ እርሱ ኀያልና እጅግ ክቡር ይሆናል››
ሰዎች ሲፈሩ እንዳይታዩ ወይም ጉዳት እንዳይደርስባቸው በጣም ዝቅ ይላሉ፡፡ የሚያስፈራቸው ነገር ሳይኖር ግን ይነሣሉ፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በልበ ሙሉነት ቁሙ››
ራስን ቀና ማድረግ ወደ ላይ ማየት ማለት ነው፡፡ ራሳቸውን ወደ ላይ ቀና ሲያደርጉ አዳኛቸው ወደ እነርሱ ሲመጣ ያያሉ፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ተመልከቱ››
የሚያድን እግዚአብሔር አንዳንዴ እርሱ የሚያደርገው መዳን እንደሆነ ተነግሯል፡፡ ‹‹መዳን›› የሚለው ቃል የነገር ስም ስለሆነ እንደ ግሥ ሊተረጐም ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እግዚአብሔር ቶሎ ስለሚያድናችሁ››
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ማስተማሩን ሲቀጥል ምሳሌ እየነገራቸው ነው፡፡
‹‹አዲስ ቅጠል ማደግ ሲጀምር››
‹‹በጋ ሊጀምር ነው›› በእስራኤል በጋ የሚመጣው የበለስ ዛፍ ቅጠሎችን ማቆጥቆጥ ተከትሎ ሲሆን፣ በለስ የሚያፈራበት ጊዜ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የመከር ጊዜ ሊጀምር ነው››
የበለስ ቅጠሎች ማቆጥቆጥ በጋ መምጣቱን እንደሚያመለክቱ፣ ኢየሱስ የተናገራቸው ምልክቶች መታየትም የእግዚአብሔር መንግሥት መምጣቱን ያመለክታሉ፡፡
‹‹እግዚአብሔር በቅርቡ መንግሥቱን ይመሠርታል›› አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እግዚአብሔር በቅርቡ ንጉሥ ሆኖ ይገዛል››
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ማስተማር ቀጥሏል፡፡
ይህ አገላለጽ ኢየሱስ የሚናገረው ጠቃሚ መሆኑን አጽንዖት ይሰጣል፡፡
ይህም ማለት፣ 1) ኢየሱስ የተናገራቸውን የመጀመሪያ ምልክቶች የሚያይ ትውልድ ወይም 2) ኢየሱስ እየተናገረ የነበረው ትውልድ፡፡ የመጀመሪያው የበለጠ ይመረጣል፡፡
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ይህ ሲሆን በሕይወት ይኖራል››
‹‹ሰማይና ምድር መኖራቸው ያበቃል›› እዚህ ላይ፣ ‹‹ሰማይ›› ከበላይ ያለውን ጠፈርና ሕዋ ያመለክታል፡፡
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ለዘላለም ይኖራል››
‹‹ልብ›› የሰውን አእምሮና ሐሳብ ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እንዳትያዙ››
ኀጢአት ሰው የሚሸከመው ሸክም እንደሆነ እዚህ ላይ ኢየሱስ ይናገራል፡፡
‹‹ብዙ ወይን ጠጅ መጠጣት እናንተ ላይ የሚያመጣው›› ወይም፣ ‹‹ስካር››
‹‹ስለዚህ ሕይወት በብዛት መጨነቅ››
እንስሳው ሳይጠብቀው ወጥመድ በድንገት እንደሚዘጋበት፣ ያም ቀን ሰዎች ባልጠበቁት ቀን ይሆናል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ወጥመድ እንስሳው ላይ በድንገት እንደሚዘጋ፣ ያም ቀን ባልጠበቃችሁት ጊዜ ይሆናል››
ላልተዘጋጁና ላልጠበቁ ሰዎች የዚያ ቀን መምጣት በድንገት ይሆናል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሕይወት፤ ካልተጠነቀቃችሁ ያ ቀን በድንገት ይዘጋባችኃል››
ይህ የሚያመለክተው መሲሑ የሚመለስበትን ቀን ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የሰው ልጅ የሚመጣበት ቀን››
‹‹ሁሉንም ይመለከታል›› ወይም፣ ‹‹በዚያ ቀን የሚሆነው ሁሉም ላይ ተፅዕኖ ይኖረዋል፡፡››
የላይኛው የምድር ክፍል እንደ የሰው ፊት ተነግሯል፡፡ ይህ ውጫዊ ክፍል ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በምድር ሁሉ ገጽታ ላይ›› ወይም፣ ‹‹በመላው ምድር ላይ››
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ማስተማር አበቃ
‹‹ለእኔ መምጣት ተዘጋጁ››
ይህም ማለት፣ 1) ‹‹እነዚህን ነገሮች ሁሉ መታገሥ እንድትችሉ›› ወይም 2) ‹‹እነዚህን ነገሮች ማስወገድ እንድትችሉ››
‹‹የሚሆኑት እዚህ ነገሮች›› ኢየሱስ ስደትን፣ ጦርነትንና ምርኮን የመሳሰሉ አስፈሪ ነገሮች እንደሚሆኑ ነግሮአቸው ነበር፡፡
‹‹በልበ ሙሉነት በሰው ልጅ ፊት እንድትቆሙ›› ይህ የሰው ልጅ በሁሉም ላይ ሲፈርድ የሚሆነውን የሚያመለክት ሊሆን ይችላል፡፡ ያልተዘጋጀ ሰው የሰው ልጅን ስለሚፈራ በልበ ሙሉነት ፊቱ አይቆምም፡፡
ይህ ሉቃስ 20፥1 ላይ የጀመረው ታሪክ ክፍል የመጨረሻ ነው፡፡ እነዚህ ቁጥሮች የዋናው ታሪክ ክፍል እስኪያበቃ ድረስ ቀጣይ ስለሆነው ድርጊት ይናገራሉ፡፡
‹‹እያስተማረ በነበረ ቀን›› ወይም፣ ‹‹በየቀኑ ሲያስተምር›› ቀጥሎ ያሉት ቁጥሮች እርሱ ከመሞቱ በፊት በነበረው ሳምንት ኢየሱስና ሕዝቡ ስላደረጓቸው ነገሮች ይናገራሉ፡፡
ቤተ መቅደስ ውስጥ መግባት የሚፈቀድላቸው ካህናት ብቻ ነበሩ፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በቤተ መቅደስ›› ወይም፣ ‹‹ቤተ መቅደሱ ግቢ ውስጥ››
‹‹በሌሊት እርሱ ከከተማ ውጪ ሄዶ›› ወይም፣ ‹‹በየሌሊቱ ይሄድ ነበር››
‹‹ሁሉ›› የሚለው የተሰበሰበው ሕዝብ ብዙ እንደ ነበር አጽንዖት ለመስጠት ግነት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በጣም ብዛት ያለው ሕዝብ ከተማው ውስጥ›› ወይም፣ ‹‹ከተማው ውስጥ ያለው ሁሉም ሰው››
‹‹በየጠዋቱ ይመጡ ነበር››
‹‹ሲያስተምር ለመስማት››
1 ፋሲካ የተባለው የቂጣ በዓል ተቃርቦ ነበር። 2 የካህናት አለቆችና የሕግ መምህራን ሕዝቡን ይፈሩ ስለ ነበር፣ ኢየሱስን እንዴት አድርገው እንደሚገድሉት ተመካከሩ። 3 ሰይጣን ከዐሥራ ሁለቱ አንዱ በሆነው በአስቆሮቱ ይሁዳ ገባበት። 4 አርሱም ኢየሱስን እንዴት አድርጎ አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ከካህናት አለቆችና ከሕዝብ መሪዎች ጋር ተነጋገረ። 5 እነርሱም ደስ አላቸው፣ ገንዘብም ሊሰጡት ተስማሙ። 6 እርሱም ኢየሱስን ለእነርሱ አሳልፎ ለመስጠት ሕዝብ የሌሉበትን ምቹ ጊዜ ይፈልግ ነበር። 7 የፋሲካ በግ መሥዋዕት የሚደረግበት የቂጣ በዓል ደረሰ። 8 ኢየሱስም ጴጥሮስንና ዮሐንስን፣ “ሂዱና የፋሲካ ምግብ እንድንበላ አዘጋጁልን” ብሎ ላካቸው። 9 እነርሱም፣ “የት እንድናዘጋጅልህ ትፈልጋለህ?” ብለው ጠየቁት። 10 እንዲህም ብሎ መለሰላቸው፣ “አድምጡ፣ ወደ ከተማው በገባችሁ ጊዜ የውሃ እንስራ ተሸክሞ የሚመጣ ሰው ያገኛችኋል። ይህን ሰው ወደሚገባበት ቤት ተከትላችሁ ግቡ። 11 ከዚያም ለቤቱ ባለቤት፣ 'መምህሩ እንዲህ ይልሃል፤" የፋሲካን እራት ከደቀ መዛሙርቴ ጋር የምበላበት የእንግዳ ክፍል የት ነው?' በሉት።” 12 እርሱም በፎቁ ላይ ሰፊና በሚገባ የተሰናዳ ክፍል ያሳያችኋል። ዝግጅቱንም በዚያ አድርጉ። 13 ስለዚህ ወጥተው ሲሄዱ፣ ሁሉም ነገር እርሱ እንደተናገረው ሆኖ አገኙት። ከዚያም የፋሲካውን ምግብ አዘጋጁ። 14 ሰዓቱ ሲደርስ፣ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ዐብሮ ተቀመጠ። 15 ከዚያም እንዲህ አላቸው፤ “መከራ ከመቀበሌ በፊት ይህን የፋሲካ እራት ከእናንተ ጋር ለመብላት በእጅጉ እጓጓ ነበር። 16 በእግዚአብሔር መንግሥት እስከሚፈጸም ድረስ ከዚህ ምግብ ዳግመኛ እንደማልበላ እነግራችኋለሁና።" 17 ከዚያም ኢየሱስ ጽዋውን አንሥቶ አመሰገነና እንዲህ አላቸው፤ “ይህን ውሰዱና ተካፈሉት። 18 እላችኋለሁ፣ የእግዚአብሔር መንግሥት እስክትመጣ ድረስ ከዚህ ወይን ፍሬ ዳግመኛ አልጠጣም።” 19 እንጀራውን ወሰደ፣ ካመሰገነ በኋላ እንዲህ በማለት ቈርሶ ሰጣቸው፣ “ይህ ለእናንተ የተሰጠው ሥጋዬ ነው። እኔን እያሰባችሁ ተመገቡት።” 20 በተመሳሳይ ሁኔታም፣ ከእራት በኋላ ጽዋውን አነሣና እንዲህ አለ፣ “ይህ ጽዋ ስለ እናንተ የፈሰሰ በደሜ የሚሆን ዐዲስ ኪዳን ነው። 21 ነገር ግን እኔን አሳልፎ የሚሰጠኝ ከእኔ ጋር በማዕድ እየበላ መሆኑን ልብ በሉ። 22 የሰው ልጅስ እንደተወሰነለት ይሆናል። ነገር ግን አሳልፎ ለሚሰጠው ለዚያ ሰው ወዮለት!" 23 በዚህ ጊዜ እርስ በርሳቸው ይህን ነገር የሚያደርግ ማን እንደ ሆነ ተጠያየቁ። 24 ከዚያም ከሁሉም የሚበልጥ ማን ሊሆን እንደሚገባው በመካከላቸው ጠብ ተነሣ። እርሱ እንዲህ አላቸው፣ 25 “የአሕዛብ ነገሥታት በሕዝብ ላይ ይገዛሉ፣ በእነርሱ ላይ ሥልጣን ያላቸውንም የተከበሩ ገዦች ይሏቸዋል። 26 ነገር ግን በእናንተ ዘንድ እንዲህ አይሁን። ይልቅ ከእናንተ ታላቅ የሆነ እንደ ታናሽ ይሁን። እጅግ ተፈላጊ የሆነ እንደሚያገለግል ሰው ይሁን። 27 በማዕድ ከተቀመጠውና ከሚያገለግለው የትኛው ታላቅ ነው? በማዕድ የተቀመጠ አይደለምን? እኔ ግን በእናንተ መካከል እንደሚያገለግል ሰው ነኝ። 28 ነገር ግን እናንተ በፈተናዬ ከእኔ ጋር ጸንታችኋል። አብ ለእኔ መንግሥትን እንደ ሰጠኝ፣ 29 በመንግሥቴ በእኔ ማዕድ እንድትበሉና እንድትጠጡ መንግሥትን እሰጣችኋለሁ። 30 ደግሞም በዙፋን ተቀምጣችሁ በዐሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች ላይ ትፈርዳላችሁ። 31 ስምዖን ሆይ፣ ስምዖን ሆይ፣ ተጠንቀቅ፤ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥርህ ፈልጎ ጠይቋል። 32 ነገር ግን እኔ እምነትህ እንዳይጠፋ ጸለይሁልህ። ዳግመኛ ከተመለስህ በኋላ ወንድሞችህን አበርታቸው።” 33 ጴጥሮስ፣ “ጌታ ሆይ፣ ወደ እስር ቤትም ይሁን ወደ ሞት ከአንተ ጋር ለመሄድ ዝግጁ ነኝ” አለው። 34 ኢየሱስ፣ “ዛሬ ዶሮ ሳይጮኽ አላውቀውም ብለህ ሦስት ጊዜ እንደምትክደኝ እነግርሃለሁ” ብሎ መለሰለት። 35 ከዚያም ኢየሱስ፣ “ያለ ገንዘብ ቦርሣ፣ ወይም ያለ ስንቅ ወይም ያለ ጫማ በላክኋችሁ ጊዜ ያጣችሁት ነገር ነበርን?” አላቸው። እነርሱ፣ “ምንም አላጣንም" ብለው መለሱለት። 36 ከዚያም እንዲህ አላቸው፣ “አሁን ግን የገንዘብ ቦርሣ ያለው ቦርሣውን፣ ደግሞም ስንቁን ይያዝ። ጎራዴ የሌለው ልብሱን ሽጦ ጎራዴ ይግዛ። 37 እላችኋለሁ፣ 'ከወንበዴዎች እንደ አንዱ ተቈጠረ' ተብሎ ስለ እኔ የተጻፈው መፈጸም አለበት። ይህ ስለ እኔ የተነገረው አሁን እየተፈጸመ ነው።" 38 ከዚያም እነርሱ፣ “ጌታ ሆይ፣ ተመልከት፣ እዚህ ሁለት ጎራዴዎች አሉ” አሉት። እርሱም “ይበቃል” አላቸው። 39 ከእራት በኋላ ኢየሱስ ብዙ ጊዜ እንደሚያደርገው ወደ ደብረ ዘይት ተራራ ሄደ፣ ደቀ መዛሙርቱም ተከተሉት። 40 እዚያ በደረሱ ጊዜ፣ “ወደ ፈተና እንዳትገቡ ጸልዩ” አላቸው። 41 ከእነርሱ የድንጋይ ውርወራ ያህል ራቅ ብሎ ሄደና ተንበርክኮ፣ 42 “አባት ሆይ፣ ብትወድ ይህን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፣ ነገር ግን የአንተ ፈቃድ እንጂ የእኔ ፈቃድ አይሁን” በማለት ጸለየ። 43 የሚያበረታታው መልአክም ከሰማይ መጣለት። 44 በጣር ውስጥ ሆኖ በጣም እየቃተተ ጸለየ፣ ላቡም እንደ ትልልቅ የደም ጠብታዎች ወደ መሬት ይንጠባጠብ ነበር። 45 ከጸሎቱ ተነሥቶ ወደ ደቀ መዛሙርቱ በመጣ ጊዜ ከሐዘን የተነሣ ተኝተው አገኛቸውና፣ 46 “ለምን ትተኛላችሁ? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ተነሡና ጸልዩ” አላቸው። 47 ገና እየተናገረ እያለ ብዙ ሰዎች ከዐሥራ ሁለቱ አንዱ የሆነው ይሁዳ እየመራቸው መጡ። ይሁዳም ሊስመው ወደ ኢየሱስ ቀረበ፤ 48 ነገር ግን ኢየሱስ፣ “ይሁዳ ሆይ፣ የሰውን ልጅ በመሳም አሳልፈህ ትሰጣለህን?” አለው። 49 በኢየሱስ ዙሪያ የነበሩት እየሆነ ያለውን ነገር ባዩ ጊዜ፣ 50 “በጎራዴ እንምታቸውን?” አሉ። ከዚያም ከመካከላቸው አንዱ በጎራዴ የሊቀ ካህኑን አገልጋይ ቀኝ ጆሮ መታና ቈረጠው። 51 ኢየሱስ፣ “ይህ ይብቃ” አለ። የአገልጋዩንም ጆሮ ዳሰሰ፣ ፈወሰውም። 52 ኢየሱስ ሊያጠቁት ለመጡ የካህናት አለቆችና የቤተ መቅደስ መሪዎች እንዲሁም ሽማግሌዎች እንዲህ አላቸው፤ “ወንበዴን እንደሚይዝ ሰው ጐራዴና ዱላ ይዛችሁ ትመጡብኛላችሁን? 53 በየዕለቱ በቤተ መቅደስ ከእናንተ ጋር ሳለሁ አልያዛችሁኝም። ነገር ግን ይህ የእናንተና የጨለማው ሥልጣን ጊዜ ነው።” 54 ያዙትና ወሰዱት፣ ወደ ሊቀ ካህናቱ ቤትም አመጡት። ጴጥሮስ ግን ከርቀት ተከተለው። 55 በግቢው መሓል እሳት ካቀጣጠሉና ዐብረው ከተቀመጡ ጴጥሮስ መጥቶ በመካከላቸው ተቀመጠ። 56 በእሳቱ ብርሃን እንደተቀመጠም አንዲት ገረድ አየችውና በቀጥታ ተመልክታው፣ “ይህ ሰው ደግሞ ከእርሱ ጋር ነበር” አለች። 57 ጴጥሮስ ግን፣ “ሴትዮ፣ የምትዪውን ሰው አላውቀውም” ብሎ ካደ። 58 ከጥቂት ጊዜ በኋላ ደግሞ፣ ሌላ ሰው አየውና፣ “አንተም ከእነርሱ አንዱ ነህ” አለው። ነገር ግን ጴጥሮስ፣ “አንተ ሰው፣ እኔ አይደለሁም” አለ። 59 ከአንድ ሰዓት ያህል ጊዜ በኋላ፣ ሌላ ሰው፣ “በእውነት ይህ ሰው ደግሞ ገሊላዊ ስለ ሆነ ከእርሱ ጋር ነበረ” በማለት በጥብቅ ተናገረ። 60 ነገር ግን ጴጥሮስ፣ “አንተ ሰው የምትለውን አላውቅም” አለ። ይህን እየተናገረ እያለ ወዲያው ዶሮ ጮኸ። 61 ጌታም ዞር አለና ጴጥሮስን ተመለከተው። ጴጥሮስም፣ ጌታ “ዛሬ ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ” ያለውን ቃል አስታወሰ። 62 ጴጥሮስ ወደ ውጭ ወጣና መራራ ልቅሶ አለቀሰ። 63 ከዚያም ኢየሱስን ይጠብቁ የነበሩት ሰዎች እያላገጡበት ደበደቡት። ዐይኖቹን ከሸፈኑ በኋላ፣ 64 “እስቲ ትንቢት ተናገር። አሁን የመታህ ሰው ማን ነው?” በማለት ጠየቁት። 65 እየተሳደቡ፣ ሌሎች ብዙ ነገሮችን በኢየሱስ ላይ ተናገሩ። 66 እንደነጋም የሕዝቡ ሽማግሌዎች፣ ከካህናት አለቆችና ከሕግ መምህራን ጋር ዐብረው ተሰበሰቡ። ከዚያም ኢየሱስን ወደ ሸንጎው ፊት አቀረቡትና፣ 67 “ክርስቶስ ከሆንህ ንገረን” አሉት። እርሱ ግን፣ “እኔ ብነግራችሁ አታምኑም፣ 68 ደግሞም ብጠይቃችሁ አትመልሱም። 69 ነገር ግን ከአሁን ጀምሮ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር ኅይል ቀኝ ይቀመጣል” አላቸው። 70 ሁሉም በአንድነት፣ “እንግዲህ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነሃ?” አሉት። ኢየሱስም፣ “እኔ እንደ ሆንሁ እናንተ ትናገራላችሁ” አላቸው። እነርሱ፣ 71 “እንግዲህ ለምን ምስክር እንፈልጋለን? ሲናገር እኛ ራሳችን ከአፉ ሰምተነዋል” አሉ።
ይሁዳ ኢየሱስን አሳልፎ ለመስጠት ተስማማ፡፡ እነዚህ ቁጥሮች ስለዚህ ሁኔታ ዳራ የሚሆን መረጃ ይሰጣሉ፡፡
ቃሉ እዚህ ጥቅም ላይ የዋለው አዲስ ሁኔታን ለማስተዋወቅ ነው፡፡
ይህ በዓል በዚህ ስም የተጠራው በዚህ ጊዜ አይሁድ እርሾ የገባበት እንጀራ ስለማይበሉ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ያልቦካ እንጀራ የሚበሉበት በዓል››
‹‹ለመጀመር ዝግጁ ነበር››
ካህናትና ጸሐፍት ኢየሱስን ለመግደል ሥልጣን አልነበራቸውም፣ ሌሎች እንዲገድሉት ግን ተስፋ አድርገዋል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ኢየሱስን እንዴት እንደሚያስገድሉት›› ወይም፣ ‹‹ሌሎች ኢየሱስን እንዲገድሉ ለማድረግ››
ይህም ማለት፣ 1) ‹‹ሕዝቡ የሚያደርገው ስላስደነገጣቸው›› ወይም 2) ‹‹ሕዝቡ ኢየሱስን ንጉሥ ያደርጉታል ብለው ስለ ፈሩ››
ይህ የዚህ ታሪክ ክፍል ጅማሬ ነው፡፡
ይህ በጋኔን ከመያዝ ጋር ተመሳሳይ ሊሆን ይችላል፡፡
‹‹የካህናት መሪዎች››
የቤተ መቅደሱ ጥበቃ ኀላፊዎች
‹‹ኢየሱስን ለማሰር እንዴት እንደሚረዳቸው››
‹‹የካህናት አለቆችና ሹሞቹ ደስ አላቸው››
‹‹ለይሁዳ ገንዘብ ሊሰጡት››
‹‹በሐሳቡ ተስማማ››
ይህ የታሪኩ ክፍል ካበቃ በኃላ ቀጣይ ሂደት ነበር፡፡
‹‹ሊወስደው››
‹‹በድብቅ›› ወይም፣ ‹‹በዙሪያው ሰዎች ሳይኖሩ››
‹‹ኢየሱስ ለጴጥሮስ ለዮሐንስ መለሰላቸው››
ኢየሱስ ይህን ቃል የተጠቀመው ልብ ብለው እንዲያደምጡና እርሱ የነገራቸውንም ሁሉ እንዲያደርጉ ሊነግራቸው ነው፡፡
‹‹ውሃ በእንስራ የተሸከመ›› እንስራውን የተሸከመው በትከሻው ሊሆን ይችላል፡፡
‹‹ተከተሉትና ወደ ቤት ግቡ››
‹‹የእንግዳ ክፍል ወዴት ነው?›› በማለት የሚጀምረው ጥቅስ መምህሩ ኢየሱስ ለቤቱ ባለቤት መናገር የፈለገው ቀጥተኛ ጥቅስ ነው፡፡ ቀጥተኛ ባልሆነ ጥቅስ ሊተረጐም ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እርሱና ደቀመዛሙቱ ፋሲካን እንዲበሉ መምህራችን የእንግዳ ክፍል ወዴት ነው? ይልሃል›› ወይም፣ ‹‹ከእኛና ከተቀሩት ደቀ መዛሙርት ጋር ፋሲካን የሚበላበትን የእንግዳ ክፍል እንድታሳየን መምህራችን ጠይቆሃል››
ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው
‹‹የፋሲካን ምግብ እንድበላ››
ኢየሱስ ለጴጥሮስና ለዮሐንስ መመሪያ መስጠት ቀጥሏል፡፡
‹‹የቤቱ ባለቤት ያሳያችኋል››
‹‹ፎቅ ቤት›› ማኅበረ ሰብህ ሌሎች ክፍሎች ላይ የሚሠራ ቤት ከሌለው ከተማ ውስጥ ያሉት ሕንፃዎች የሚጠሩበትን ቃል ማሰብ ትችላለህ፡፡
x
ይህ ስለ ፋሲካው ታሪክ ቀጣዩ ሁኔታ ነው፡፡ ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ የፋሲካን ምግብ ለመብላት ተቀምጠዋል፡፡
‹‹ምግብ የሚበላበት ጊዜ ሲደርስ››
‹‹ኢየሱስ ተቀመጠ››
‹‹በጣም እፈልግ ነበር››
ኢየሱስ ስለ ሞቱ እያመለከተ ነው፡፡ እዚህ ላይ፣ ‹‹መከራ›› የሚለው ቃል ያልተለመደ አስቸጋሪ ወይም የስቃይ ሁኔታ ማለት ነው፡፡
ኢየሱስ ይህን ሐረግ የተጠቀመው ቀጥሎ የሚነግራቸው ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አጽንዎች ለመስጠት ነው፡፡
‹‹ወይን ጠጅ የነበረበትን ጽዋ አነሣ››
‹‹ለእግዚአብሔር ምስጋና ከሰጠ በኋላ››
‹‹ለሐዋርያት እንዲህ አለ››
ጽዋውን ሳይሆን ጽዋው ውስጥ የነበረውን ነው መከፋፈል ያለባቸው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እርስ በርሳችሁ ጽዋው ውስጥ ያለውን ወይን ጠጅ ተከፋፈሉ›› ወይም፣ ‹‹እያንዳንዳችሁ ጽዋ ውስጥ ካለው የወይን ጠጅ ጠጡ፡፡››
ይህን ሐረግ የተጠቀመው ቀጥሎ ኢየሱስ ለሚናገረው አስፈላጊ ነገር አጽንዖት ለመስጠት ነው፡፡
ይህ የሚያመለክተው የወይኑ ፍሬ ተጨምቆ የሚወጣውን ጭማቂ ነው፡፡ ወይን ጠጅ የሚሠራው ከተብላላው የወይን ፍሬ ጭማቂ ነው፡፡
‹‹እግዚአብሔር መንግሥቱን እስኪመሠርት›› ወይም፣ ‹‹እግዚአብሔር መንግሥቱ ውስጥ እስኪገዛ››
ይህ እንጀራ እርሾ የለውም፤ ጠፍጣፋ ነው፡፡
‹‹ቆረሰው›› ወይም፣ ‹‹ከፋፈለው›› ብዙ ቁርጥራጮች እንዲኖሩት ከፋፍሎት ይሆናል፤ ወይም ሐዋርያቱ እርስ በርሳቸው እንዲከፋፈሉት ለሁለት ከፍሎ ሰጥቷቸው ይሆናል፡፡ የሚቻል ከሆነ ሁለቱንም የሚያመለክት አገላለጽ ተጠቀም፡፡
ይህም ማለት፣ 1) ‹‹ይህ እንጀራ ሥጋዬ ነው›› ወይም 2) ‹‹ይህ እንጀራ የእኔን ሥጋ ይወክላል››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ለእናንተ የምሰጠው ሥጋዬ›› ወይም፣ ‹‹ለእናንተ መሥዋዕት የምሰጠው ሥጋዬ››
‹‹ይህን እንጀራ ብሉ››
x
ኢየሱስ ለሐዋርያቱ መናገር ቀጥሏል
‹‹አሳልፎ የሚሰጠኝ ሰው››
‹‹በእግጥ የሰው ልጅ ይሄዳል›› ወይም፣ ‹‹የሰው ልጅ ይሞታል››
ኢየሱስ ስለ ራሱ በሦስተኛ ሰው ደረጃ እየተናገረ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እኔ የሰው ልጅ በእርግጥ እሄዳለሁ››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እግዚአብሔር እንደ ወሰነው›› ወይም፣ ‹‹እግዚአብሔር እንዳቀደው››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የሰውን ልጅ አሳልፎ ለሚሰጠው ሰው ወዮለት›› ወይም፣ ‹‹የሰው ልጅን አሳልፎ ለሚሰጠው ሰው ምንኛ ከባድ ይሆንበታል››
‹‹ከዚያ ሐዋርያት እርስ በርስ ይከራከሩ ጀመር››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በጣም አስፈላጊ ማን እንደሆነ›› ወይም፣ ‹‹ሰዎች በጣም አስፈላጊ ብለው የሚያስቡት››
‹‹ኢየሱስ ለሐዋርያት እንዲህ አላቸው››
‹‹አሕዛብ ላይ በኀይል ይገዛሉ››
ምናልባትም ሕዝቡ ገዦዎቹ ለሕዝቡ መልካም እያደረጉ ነው ብለው አያስቡም፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹መጠራት ይወዳሉ›› ወይም፣ ‹‹ራሳቸውን ይጠራሉ››
ኢየሱስ ሐዋርያትን ማስተማር ቀጥሏል
‹‹እንዲህ ማድረግ የለባችሁም››
በዚያ ባሕል ትልልቅ ሰዎች ይከበሩ ነበር፡፡ ብዙ ጊዜ መሪዎቹ ትልልቅ ሰዎች ስለ ነበሩ፣ ‹‹ሽማግሌዎች›› ይባሉ ነበር፡፡ ታናሹ ሰው መሪ የመሆን ዕድሉ ዝቅ ያለ ነው፤ አስፈላጊነቱም ዝቅ ያለ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ዝቅ ያለ አስፈላጊ››
‹‹አገልጋይ››
ይህ ቁጥር 26 ላይ ኢየሱስ የሰጠውን ትእዛዝ ከቁጥር 27 ሙሉ ጋር ያያይዛል፡፡ ኢየሱስ አገልጋይ በመሆኑ በጣም ትልቅ የተባለው ማገልገል አለበት ማለት ነው፡፡
‹‹ታላቅ የተባለው የትኛው ነው… ያገልግል›› ኢየሱስ ይህን ጥያቄ ያነሣው በእውነት ታላቅ የሆነው የትኛው እንደሆነ ለሐዋርያት ለመግለጽ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ታላቁ ማን እንደሆነ እንድታስቡ እፈልጋለሁ… ያገልግል››
‹‹የሚመገበው››
ደቀ መዛሙርቱን ለማስተማር ኢየሱስ ሌላ ጥያቄ አነሣ፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እርግጥ ነው፤ በማእድ የተቀመጠው ከአገልጋዩ ይበልጣል!››
‹‹እኔ ከእናንተ ጋር ያለሁት አገልጋይ ለመሆን ነው›› ወይም፣ ‹‹እኔ ከእናንተ ጋር ያለሁ አገልጋይ እንዴት መሆን እንዳለበት ላሳያችሁ ነው›› እዚህ ላይ፣ ‹‹ያም ሆኖ›› የሚለው ቃል ሰዎች ኢየሱስ ነው ብለው በሚያስቡትና እርሱ በእርግጥ በሆነው መካከል ንጽጽር ስላለ ነው፡፡
‹‹በመከራዬ ከእኔ ጋር ቆይታችኋል››
አንዳንድ ቋንቋዎች የቅደም ተከተል ለውጥ ያስፈልጋቸው ይሆናል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አባቴ ለእኔ መንግሥት እንደ ሰጠኝ እኔም መንግሥት እሰጣችኋለሁ››
‹‹በእግዚአብሔር መንግሥት መሪዎች አደርጋችኋለሁ›› ወይም፣ ‹‹በመንግሥቱ ውስጥ እንድትገዙ ሥልጣን እሰጣችኋለሁ›› ወይም፣ ‹‹ነገሥታት አደርጋችኋለሁ››
‹‹የእርሱ መንግሥት ውስጥ እንድገዛ አባቴ ለእኔ ሥልጣን እንደ ሰጠኝ››
ንጉሦች ዙፋን ላይ ይቀመጣሉ፡፡ ዙፋን ላይ መቀመጥ የመግዛት ምሳሌ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እንደ ነገሥታት ትሠራላችሁ›› ወይም፣ ‹‹የነገሥታትን ሥራ ትሠራላችሁ››
ኢየሱስ በቀጥታ ለስምዖን እየተናገረ ነው፡፡
ኢየሱስ ስሙን ሁለቴ የጠራው ሊነግረው የፈለገው ነገር በጣም አስፈላጊ መሆኑን ለማሳየት ነው፡፡
‹‹እናንተ›› ሐዋርያቱን ሁሉ ይመለከታል፡፡ ‹‹እናንተ›› ለሚለው የተለየ አጠራር ያላቸው ቋንቋዎች ብዙ ቁጥርን መጠቀም አለባቸው፡፡
ይህ ማለት አንዳች ጥፋት ለማግኘት ሰይጣን ደቀ መዛሙትን መፈተን ፈለገ ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ስንዴ በወንፊት እንደሚያበጠር ሰው ሊያበጥራችሁ››
እዚህ ላይ፣ ‹‹አንተ›› በተለይ ስምዖንን ነው፡፡ ‹‹አንተ›› ለሚለው የተለየ አጠራር ያላቸው ቋንቋዎች ነጠላ ቁጥርን መጠቀም አለባቸው፡፡
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በእምነት እንድትዘልቅ›› ወይም፣ ‹‹በእኔ በማመን እንድትዘልቅ››
እዚህ ላይ ‹‹ወደ ኋላ መመለስ›› እንደ ገና ማመንን የሚያመለክት ተለዋጭ ዘይቤ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እንደ ገና በእኔ ማመን ስትጀምር›› ወይም፣ ‹‹እንደ ገና እኔን ማገልገል ስትጀምር››
ይህ ሌሎቹ ደቀ መዛሙርትን ይመለከታል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አማኝ ወገኖችህን›› ወይም፣ ‹‹ሌሎች ደቀ መዛሙትን››
የዐረፍተ ነገሩን ክፍሎች መገልበጥ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አላውቀውም ብለህ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ ዶሮ ሳይጮኽ››
x
ኢየሱስ ትኩረቱን ለሁሉም ደቀ መዛሙርት ወደ መናገር መልሷል፡፡
ኢየሱስ ጥያቄውን ያነሣው በጒዞ ላይ በነበሩ ጊዜ ሕዝቡ የሚያስፈልጋቸውን ይሰጧቸው እንደ ነበር እንዲያስታወሱ ሐዋርያቱን ለመርዳት ነበር፡፡ ኢየሱስ ይህን የጠየቀው መረጃ በመጠበቅ ባይሆንም፣ ደቀ መዛሙርቱ ምንም እንዳልጐደለባቸው የሚያደርጋቸው ዐረፍተ ነገር ብቻ እስካልሆነ ድረስ በጥያቄ መልኩ ተርጒመው፡፡
ኢየሱስ ለሐዋርያቱ እየተናገረ ነው፡፡ ስለዚህ፣ ‹‹እናንተ›› ለሚለው የተለየ አገላለጽ ያላቸው ቋንቋዎች በብዙ ቁጥር መጠቀም አለባቸው፡፡
ኰሮጆ ገንዘብ መያዣ ቦርሳ ነው፡፡ እዚህ ላይ ጥቅም የዋለው፣ ‹‹ገንዘብን›› ለማመልከት ነው፡፡
‹‹የተጓዥ ቦርሳ›› ወይም፣ ‹‹የምግብ መያዣ››
ለአንዳንድ ሰሚዎች ለውይይቱ ተጨማሪ ገለጻ መስጠት አስፈላጊ ሊሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ምንም አልጐደለብንም›› ወይም፣ ‹‹የሚያስፈልገን ሁሉ ነበረን››
ኢየሱስ ሰይፍ ስለሌለው አንድ ሰው እየተናገረ አይደለም፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሰይፍ የሌለው ማንኛውም መጐናጸፊያውን መሸጥ አለበት››
‹‹ኮት›› ወይም፣ ‹‹ከላይ የሚለበስ››
ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር መነጋገር አበቃ
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ነቢይ ስለ እኔ የጻፈው››
የሚሆነውን ሁሉ እግዚአብሔር ቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ እንዲጻፍ ማድረጉን ሐዋርያት ይረዳሉ፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እግዚአብሔር ይፈጽማል›› ወይም፣ ‹‹እግዚአብሔር እንዲጻፍ ያደርጋል››
እዚህ ላይ ኢየሱስ ከቅዱሳት መጻሕፍት ጠቀሰ፡፡ ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሰዎች ከዐመፀኖች ጋር እንደሆነ ቆጠሩት››
‹‹ሕግ የሚተላለፉ›› ወይም፣ ‹‹ወንጀለኞች››
ይህም ማለት፣ 1) ‹‹ነቢይ ስለ እኔ አስቀድሞ የተናገረው መሆን አለበት፡፡ ወይም፣ 2) ‹‹ሕይወቴ ለፍጻሜ ቀርቧል››
ይህ ቢያንስ ሁለቱን የኢየሱስ ሐዋርያት ይመለከታል፡፡
x
ኢየሱስ ለመጸለይ ወደ ደብረ ዘይት ተራራ ሄደ
‹‹እንዳትፈተኑ›› ወይም፣ ‹‹ኀጢአት ለማድረግ ምንም ነገር እንዳይፈትናችሁ››
‹‹አንድ ሰው ድንጋይ መወርወር የሚችልበት ርቀት ያህል›› አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አጭር ርቀት›› ወይም በግምት፣ ‹‹ሰላሣ ሜትር ያህል›› ርቀት፡፡
ኢየሱስ የእያንዳንዱን ሰው ኀጢአት መስቀል ላይ ሊሸከም ነው፡፡ ሌላ መንገድ ይኖር እንደሁ በመጠየቅ ወደ አባቱ እየጸለየ ነው፡፡
ይህ በጣም አስፈላጊ የእግዚአብሔር መጠሪያ ነው፡፡
አሁን እርሱ ላይ የሚደርሰው መራራ ነገር ያለበት ጽዋ መጠጣት እንደ ሆነ ኢየሱስ ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ይህን ጽዋ እንዳልጠጣ ፍቀድልኝ›› ወይም፣ ‹‹የሚሆነው ነገር እኔ ላይ እንዳይደርስ››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እንደ እኔ ፈቃድ ሳይሆን፣ እንደ አንተ ፈቃድ የሆነውን አድርግ››
‹‹ለኢየሱስ ታየው››
‹‹አደፋፈረው››
‹‹በጣም እየተሰቃየ ሳለ ጸለየ››
‹‹የበለጠ ጸለየ››
‹‹ላቡ እንደ ብዙ የደም ነጠብጣብ መሬት ላይ ፈሰሰ››
‹‹ኢየሱስ ከጸሎት ሲነሣ እርሱ›› ወይም፣ ከጸሎት በኃላ ኢየሱስ ተነሣ፣ እርሱ››
‹‹በሐዘን ደክመው ስለ ነበር እንደ ተኙ አየ››
ይህም ማለት፣ 1) ‹‹በዚህ ጊዜ መተኛታችሁ ገርሞኛል›› ወይም 2) ‹‹በዚህ ጊዜ መተኛት አልነበረባችሁም››
‹‹እንዳትፈተኑ›› ወይም፣ ‹‹ኀጢአት ለማድረግ ምንም ነገር እንዳይፈትናችሁ››
‹‹እነሆ›› የሚለው ቃል ለታሪኩ አዲስ ሰዎች ያነቃናል፡፡ ቋንቋህ ይህን ማድረግ የሚችልበት መንገድ ይኖረዋል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ብዙ ሰዎች ሲመጡ ታየ››
ይሁዳ ኢየሱስ የነበረበትን ለሰዎች እያሳየ ነው፡፡ ለሕዝቡ ምን ማድረግ እንዳለባቸው አልተናገረም፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ወደ ኢየሱስ እየመራቸው››
‹‹እየሳመ ሰላም አለው›› ወይም፣ ‹‹በመሳም ሰላም አለው›› ሰዎች ቤተ ሰባቸው ወይም ጓደኛቸው የሆነውን ሰው ሰላም ሲሉ አንድ ጉንጫቸውን ወይም ሁለቱንም ጉንጮቻቸውን ይስሟቸዋል፡፡ አንባቢዎችህ ወንድ ሌላውን ወንድ መሳሙ እንደ ነውር የሚቆጥሩ ከሆነ፣ ‹‹የጓደኝነት ሰላምታ ሰጠው›› በሚል አጠቃላይ መንገድ መተርጐም ትችላለህ፡፡
በመሳም እርሱን አሳልፎ በመስጠቱ ይሁዳን ለመገሠጽ ኢየሱስ በጥያቄ ተጠቀመ፡፡ በተለምዶ መሳም የፍቅር ምልክት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የሰው ልጅን አሳልፈህ የምትሰጠው በመሳም ነውን?››
ኢየሱስ በዚህ አገላለጽ የተጠቀመው ስለ ራሱ ለመናገር ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እኔ፣ የሰው ልጅን››
ይህ የሚያመለክተው የኢየሱስን ደቀ መዛሙርት ነው፡፡
ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስን ለመያዝ እየመጡ የነበሩትን ካህናትና ወታደሮቹን ነው፡፡
ጥያቄው እያደረጉ የነበረው ውጊያ አይደለም፤ (የሰይፍ ውጊያ) በምን ዐይነት መሣሪያ መጠቀማቸውም አይደለም (ይዘው የመጡት ሰይፍ፤ ሉቃስ 22፥38) ይሁን እንጂ፣ ትርጒምህ ይዘው ስለ መጡት መሣሪያ መናገር አለበት፡፡
‹‹ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ››
‹‹የሊቀ ካህናቱን አገልጋይ በሰይፍ መታ››
‹‹ከዚህ የበለጠ አታድርግ››
‹‹ጆሮው የተቆረጠውን አገልጋይ ዳሰሰ››
‹‹እኔ ወንበዴ እንደሆንሁ በማሰብ ሰይፍና ቆመጥ ይዛችሁ ወጣችሁን? ‹‹ኢየሱስ ይህን ጥያቄ ያቀረበው የአይሁድ መሪዎችን ለመገሠጽ ነበር፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እኔ ወንበዴ እንዳይደለሁ ታውቃላችሁ፤ ግን ሰይፍና ቆመጥ ይዛችሁ መጣችሁብኝ››
‹‹በየቀኑ በመካከላችሁ ነበርሁ››
ቤተ መቅደስ ውስጥ የሚገቡ ካህናት ብቻ ናቸው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በቤተ መቅደስ አደባባይ›› ወይም፣ ‹‹በቤተ መቅደስ››
በዚህ ቁጥር እጆችን መጫን ሰውየውን ማሰር ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ልታሰሩኝ››
‹‹የእናንተ ጊዜ›› ወይም፣ ‹‹የምትሠሩበት ጊዜ››
ዐረፍተ ነገሩን ሁለት ጊዜ መድገም ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የጨለማ ሥልጣን ጊዜ››
ይህ የሚናገረው ስለ ሰይጣን አገዛዝ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የጨለማ ግዛት ጊዜ›› ወይም፣ ‹‹ሰይጣን የሚሠራበት ጊዜ››
‹‹እርሱን ከያዙበት አትክልት ቦታ ኢየሱስን ወሰዱት››
‹‹ወደ ሊቀ ካህናቱ ቤት ግቢ››
‹‹አንዳንድ ሰዎች እሳት አነደዱ›› እሳቱ በቀዝቃዛው ሌሊት ሕዝቡ ሙቀት እንዲያገኙ ነበር፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አንዳንድ ሰዎች ሙቀት ለማግኘት እሳት አነደዱ››
ይህ የሊቀ ካህናቱ ቤት ግቢ ነው፡፡ ዙሪያውን አጥር ቢኖረውም ጣራ አልነበረውም፡፡
‹‹ከእነርሱ ጋር››
እሳቱ አጠገብ ተቀመጠ፤ ብርሃኑ ፊቱ ላይ አበራ
‹‹ጴጥሮስን ትኩር ብላ በመመልከት ግቢው ውስጥ ለነበሩት ሰዎች እንዲህ አለች››
ሴትዮዋ ጴጥሮስ ከኢየሱስ ጋር እንደ ነበር ለሰዎቹ እየነገረች ነው፡፡ ምናልባትም የጴጥሮስን ስም አታውቅም፡፡
‹‹ጴጥሮስ ግን እውነት አይደለም አለ››
ጴጥሮስ የሴትዮዋን ስም አያውቅም፡፡ ‹‹ሴትዮ›› ሲል እየሰደባት አልነበረም፡፡ ሰዎች እየሰደባት እንደሆነ የሚያስቡ ከሆነ፣ አንድ ሰው የማያውቃትን ሴት ሲጠራ ተቀባይነት ያለው ባሕል መጠቀም ትችላለህ፤ ወይም ቃሉን ተወው፡፡
‹‹አንተም ከኢየሱስ ጋር ከነበሩት አንዱ ነህ››
ጴጥሮስ የሰውየውን ስም አያውቅም፡፡ ‹‹አንተ ሰው›› ሲለው እየሰደበው አልነበረም፡፡ ሰዎች እየሰደበው እንደሆነ የሚያስቡ ከሆነ፣ አንድ ሰው የማያውቀውን ሰው ሲጠራ ተቀባይነት ያለው ባሕል መጠቀም ትችላለህ፤ ወይም ቃሉን ተወው፡፡
‹‹በጥብቅ አለ›› ወይም፣ ‹‹ጮኽ ብሎ አለ››
እዚህ ላይ፣ ‹‹ይህ ሰው›› የሚያመለክተው ጴጥሮስን ነው፡፡ ተናጋሪው ምናልባት የጴጥሮስን ስም አያውቅም፡፡
ሰውየው ጴጥሮስን ገሊላዊ ያለው በአነጋገሩ ሊሆን ይችላል፡፡
ጴጥሮስ የሰውየውን ስም አያውቅም፡፡ ‹‹ሰውዬ›› ብሎ ሲጠራው እየሰደበው አልነበረም፡፡ ሰዎች እየሰደበው እንደሆነ የሚያስቡ ከሆነ ሰዎች የሚያውቁን ሰው ሲጠራ ተቀባይነት ባለው ባሕል ተጠቀም፡፡ ወይም ቃሉን ተወው፡፡ ሉቃስ 22፥58 እንዴት እንደ ተረጐምህ ተመልከት፡፡
‹‹ምን እያልህ እንደሆነ አላውቅም›› ይህም ማለት ጴጥሮስ ከሰውየው ጋር በፍጹም አልተስማማም ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የምትለው በፍጹም እውነት አይደለም›› ወይም፣ ‹‹የምትለው በፍጹም ውሸት ነው››
‹‹ጴጥሮስ እየተናገረ ሳለ››
ብዙ ጊዜ ዶሮ የሚጮኸው ጠዋት ፀሐይ ከመውጣቷ በፊት ነው፡፡ ሉቃስ 22፥34 ተመሳሳዩን ሐረግ እንዴት እንደ ተረጐምህ ተመልከት፡፡
‹‹ጌታም ዘወር ብሎ ጴጥሮስን ተመለከተው››
ጴጥሮስ አሳልፎ እንደሚሰጠው ሲናገር፣ ‹‹ኢየሱስ ያለው››
x
‹‹ማየት እንዳይችል ዐይኖቹን ሸፈኑ››
ጠባቂዎቹ ኢየሱስ ነቢይ መሆኑን አያምኑም በዐይኑ ባያይም፣ እውነተኛ ነቢይ ማን እንደ መታው እንደሚያውቅ ያምናሉ፡፡ ኢየሱስን ነቢይ በማለት ቢጠሩትም እያፌዙበትና ነቢይ ነው ብለው እንደማያምኑ እያሳዩ ነበር፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ነቢይነትህን አሳይ፤ ማን እንደ መታህ ንገረን!›› ወይም፣ ‹‹እ ነቢይ፣ ማን ነው የመታህ?››
‹‹ከእግዚአብሔር ቃል ተናገር!›› እነርሱ ማለት የፈለጉት ኢየሱስ ዐይኖቹ በመሸፈናቸው ማየት ስለማይችል የመታው ማን እንደሆነ እግዚአብሔር ለኢየሱስ እንዲነግረው ነው፡፡
አሁን ቀጣዩ ቀን ነው፤ ኢየሱስን በሸንጐው ፊት አቀረቡት
‹‹በሚቀጥለው ጠዋት ሲነጋ››
ይህም ማለት፣ 1) ‹‹ሽማግሌዎቹ ኢየሱስን ሸንጐው ፊት አቀረቡት›› ወይም 2) ‹‹ጠባቂዎቹ ኢየሱስን ወደ ሽማግሌዎቹ ሸንጐ ወሰዱት›› አንዳንድ ቋንቋዎች ‹‹እነርሱ›› የሚለውን ተውላጠ ስም በመጠቀም ወይም፣ ‹‹እንዲሁ፣ ‹‹ኢየሱስን ወደ ሸንጐው ወሰዱት›› በማለት የወሰደው ማን እንደ ነበር አይናገሩም፡፡
ኢየሱስ ለሸንጐው መናገር ቀጥሏል
‹‹ከዚህ ቀን›› ወይም፣ ‹‹ከዛሬ ጀምሮ››
ኢየሱስ በዚህ አባባል የሚጠቀመው ስለ ራሱ ለመናገር ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የሰው ልጅ፣ እኔ››
‹‹በእግዚአብሔር ቀኝ›› መቀመጥ ከእግዚአብሔር ታላቅ ሥልጣንና ክብር የመቀበል ምሳሌ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በእግዚአብሔር ኀይል ጐን፣ በክብር ስፍራ ይቀመጣል››
‹‹ኀያል እግዚአብሔር›› እዚህ ላይ፣ ‹‹ኀይል›› የላቀ ሥልጣን ያመለክታል፡፡
ሸንጐው ይህን የጠየቀው የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ማለቱን በትክክል ኢየሱስ እንዲያረጋግጥ ስለ ፈለጉ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ታዲያ፣ እንደዚያ ስትል የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ማለትህ ነውን?››
ይህ የኢየሱስ አስፈላጊ መጠሪያ ነው፡፡
‹‹አዎን፣ እናንተ እንዳላችሁት ነው?››
ጥያቄ ያቀረቡት ለአጽንዖት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ከእንግዲህ ሌላ ምስክር አያስፈልገንም››
‹‹ከአፉ›› የሚለው ከአነጋገሩ ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን እንደሚያምን ሲናገር ሰምተነዋል››
1 ሕዝቡ በጠቅላላ ተነሥተው ቆሙ፣ ኢየሱስንም በጲላጦስ ፊት አቀረቡት። 2 “ይህ ሰው ራሱን ክርስቶስ፣ ንጉሥ ነኝ ሲልና ለቄሣር ግብር እንዳይከፈል በመከልከል አገር ሲበጠብጥ አግኝተነዋል” በማለት ይከሱት ጀመር። 3 ጲላጦስ፣ “አንተ የአይሁድ ንጉሥ ነህን?” በማለት ጠየቀው። ኢየሱስም፣ “አንተ አልህ” ብሎ መለሰለት። 4 ጲላጦስ የካህናት አለቆችንና የተሰበሰቡትን ሕዝብ፣ “በዚህ ሰው ምንም ስሕተት አላገኘሁበትም” አላቸው። 5 እነርሱ ግን፣ “ከገሊላ ጀምሮ በመላው ይሁዳ፣ እስከዚህ ስፍራም እንኳ እያስተማረ ሕዝቡን ያነሣሣል” በማለት አጥብቀው ተናገሩ። 6 ስለዚህ ጲላጦስ ይህን በሰማ ጊዜ ሰውየው ገሊላዊ እንደ ሆነ አጠያየቀ። 7 ከሄሮድስ ሥልጣን በታች እንደ ሆነ ተረድቶ በዚያው ሰሞን ኢየሱስን በኢየሩሳሌም ወደ ነበረው ሄሮድስ ላከው። 8 ሄሮድስ ኢየሱስን ባየው ጊዜ በጣም ደስ አለው፣ ምክንያቱም ለረጅም ጊዜ ሊያየው ሲፈልግ ነበር። ስለ እርሱ ሰምቶ የነበረ ሲሆን፣ አንዳንድ ተአምራት ሲያደርግ ለማየትም ተስፋ ነበረው። 9 ሄሮድስ ኢየሱስን በብዙ ቃሎች ቢጠይቅም፣ ኢየሱስ ግን ምንም መልስ አልሰጠውም። 10 በዚህ ጊዜ የካህናት አለቆችና የሕግ መምህራን ተነሥተው ቆሙና በኅይለ ቃል ከሰሱት። 11 ሄሮድስ ከወታደሮቹ ጋር በመሆን ኢየሱስን ሰደበው፣ አላገጠበትም፤ ጥሩ ልብስ ካለበሰው በኋላ መልሶ ወደ ሄሮድስ ላከው። 12 ከዚያን ቀን ጀምሮ ሄሮድስና ጲላጦስ ወዳጆች ሆኑ (ከዚያ በፊት አንዱ የአንዱ ጠበኞች ነበሩ)። 13 ከዚያም ጲላጦስ የካህናት አለቆችን፣ ገዢዎችንና ሕዝቡን አንድ ላይ ጠራ፤ 14 እንዲህም አላቸው፤ “ ይህን ሰው ሰዎችን ለክፉ ድርጊት የሚያነሣሣ አድርጋችሁ ወደ እኔ አመጣችሁት፣ እኔም በፊታችሁ ከጠየቅሁት በኋላ ፣ እነሆ፣ እርሱን በምትከሱባቸው ነገሮች ምንም ጥፋት አላገኘሁበትም። 15 ሄሮድስም ቢሆን ምንም ነገር አላገኘበትም፤ ምክንያቱም መልሶ ወደ እኛ ልኮታልና፤ እነሆ፣ እርሱን ለሞት የሚያደርስ በዚህ ሰው የተፈጸመ ምንም ጥፋት አላገኘሁበትም። 16 ስለዚህ ቀጥቼው እለቀዋለሁ።" ጲላጦስም በበዓሉ ለአይሁድ አንድ እስረኛ የመፍታት ግዴታ ነበረበት። 1718 ነገር ግን እነርሱ በአንድነት፣ “ይህን ሰው አስወግደው፣ በርናባስን ለእኛ ፍታልን!" በማለት ጮኹ። 19 በርናባስ በከተማይቱ ውስጥ አንድ ዐይነት ዐመፅና ግድያ በመፈጸም የታሰረ ሰው ነበር። 20 ጲላጦስ ኢየሱስን ሊፈታ ፈልጎ እንደ ገና ሕዝቡን አነጋገራቸው። 21 ነገር ግን ሕዝቡ፣ “ስቀለው፣ ስቀለው” እያሉ ጮኹ። 22 ለሦስተኛ ጊዜም እንዲህ አላቸው፤ “ለምን? ይህ ሰው የሠራው ክፋት ምንድን ነው? ለሞት ቅጣት የሚያበቃ ነገር አላገኘሁበትም። ስለዚህ ቀጥቼው እለቀዋለሁ።” 23 እነርሱ ግን ኢየሱስ እንዲሰቀል በመጠየቅ ሳያቋርጡ አብዝተው ጮኹ። ጩኸታቸውም ጲላጦስን አሳመነው። 24 ስለዚህ ጲላጦስ ፍላጎታቸውን ለማሟለት ወሰነ። 25 እንዲፈታላቸው የጠየቁትን፣ በዐመፅና በግድያ ምክንያት የታሰረውን ሰው ለቀቀላቸው። ኢየሱስን ግን ለፈቃዳቸው አሳልፎ ሰጠው። 26 እየወሰዱት ሳሉ፣ ከገጠር ይመጣ የነበረ ስምዖን የተባለ የቀሬናን ሰው ያዙና ኢየሱስ ይሸከመው የነበረውን መስቀል አሸከሙት። 27 እጅግ ብዙ ሕዝብና ለእርሱ የሚያዝኑና የሚያለቅሱ ሴቶች ይከተሉት ነበር። 28 ኢየሱስም ወደ እነርሱ ዞር ብሎ፣ “የኢየሩሳሌም ሴቶች ሆይ፣ ለእኔ ሳይሆን ለራሳችሁና ለልጆቻችሁ አልቅሱ” አለ። 29 እነሆ፣ 'መካን የሆኑና ያልወለዱ ማኅፀኖች እንዲሁም ያላጠቡ ጡቶች የተባረኩ ናቸው' የሚሉባቸው ቀኖች ይመጣሉና። 30 ከዚያም ተራሮችን፣ 'በላያችን ውደቁ፣ ኮረብቶችንም ክደኑን ማለትይጀምራሉ።' 31 ዛፉ እርጥብ እያለ ይህን ነገር ካደረጉ፣ በሚደርቅበት ጊዜ ምን ይሆናል?" 32 ሌሎች ሁለት ወንጀለኞችም ከእርሱ ጋር ሊገደሉ ተወሰዱ። 33 የራስ ቅል ወደሚባል ቦታ በደረሱ ጊዜ፣ እርሱን ከሌሎች ሁለት ወንጀለኞች ጋር ሰቀሉት፥ አንደኛው በቀኙ ሌላኛው በግራው ነበሩ። 34 ኢየሱስ፣”አባት ሆይ፣ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው” አለ። ዕጣ ተጣጥለውም ልብሱን ተከፋፈሉ። 35 “ሌሎችን አዳነ፣ እርሱ በእግዚአብሔር የተመረጠ ክርስቶስ ከሆነ አስኪ ራሱን ያድን” በማለት ገዢዎቹ እየዘበቱበት ሳለ ሕዝቡ ቆመው ያዩ ነበር። 36 ወታደሮቹም ወደ እርሱ ቀርበው፣ 37 “አንተ ንጉሥ ከሆንህ ራስህን አድን” በማለት እያሾፉበት ኮምጣጤ ሰጡት። 38 “የአይሁድ ንጉሥ” የሚል ምልክትም ከበላዩ ተደርጎ ነበር። 39 ከተሰቀሉት ወንጀለኞች አንዱ፣ "አንተ ክርስቶስ ነህን? ራስህንም እኛንም አድን” በማለት ሰደበው። 40 ሌላኛው ግን እየገሠጸው፣ “ከፍርድ በታች ሆነህ እግዚአብሔርን አትፈራምን? እኛ በዚህ ያለነው እንደ ሥራችን ስለ ሆነ፣ ትክክል ነው፣ 41 ነገር ግን ይህ ሰው ምንም ጥፋት አላደረገም” ብሎ መለሰለት። 42 ቀጥሎም፣ “ኢየሱስ ሆይ፣ በመንግሥትህ ስትመጣ አስታውሰኝ” አለ። 43 ኢየሱስ፣ “እውነት እልሃለሁ፣ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትሆናለህ” አለው። 44 ጊዜው ስድስት ሰዓት ገደማ ነበር፣ የፀሐይ ብርሃን በመቋረጡ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ላይ ጨለማ ሆነ። 45 ከዚያም የቤተ መቅደሱ መጋረጃ ከመሐል ተቀደደ። 46 ኢየሱስ፣ “አባት ሆይ፣ ነፍሴን በእጅህ አኖራለሁ” በማለት በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህን ከተናገረ በኋላ ሞተ። 47 መቶ አለቃው የተደረገውን ነገር ባየ ጊዜ፣ “ይህ ሰው በእውነት ጻድቅ ነበር” በማለት እግዚአብሔርን አከበረ። 48 ሁኔታውን ለማየት እጅግ ብዙ ሰዎች በመጡ ጊዜ፣ የተደረጉትን ነገሮች አይተው ደረታቸውን እየደቁ ተመለሱ። 49 ነገር ግን ከገሊላ ጀምሮ የተከተሉት አንዳንድ ወንዶችና ሴቶች ከርቀት ቆመው ይህን ድርጊት ይከታተሉ ነበር። 50 እነሆ፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት መምጣት የሚጠባበቅ፣ ከአይሁድ ከተማ፣ ከአርማቲያ የሆነ ዮሴፍ የሚባል 51 (በውሳኔያቸውና በድርጊታቸው ያልተስማማ) አንድ መልካምና ጻድቅ ሰው ነበረ። 52 ይህ ሰው ወደ ጲላጦስ በመቅረብ የኢየሱስን አስከሬን እንዲሰጠው ጠየቀው። 53 አስክሬኑን አውርዶ በጥሩ የተልባ እግር ጨርቅ ከፈነውና ማንም ባልተቀበረበት ከድንጋይ በተወቀረ መቃብር ውስጥ አኖረው። 54 ጊዜው የዝግጅት ቀን የነበረ ሲሆን፣ ሰንበትም እየገባ ነበር። 55 ከእርሱ ጋር ከገሊላ የመጡ ሴቶች ተከትለውት በመሄድ መቃብሩንና አስከሬኑ እንዴት እንዳረፈ አዩ። 56 ከዚያም ተመልሰው ቅመማ ቅመምና ቅባቶችን አዘጋጁ። ሰንበት ስለ ነበር በሕጉ መሠረት ዐረፉ።
ኢየሱስ ጲላጦስ ፊት ቀረበ
‹‹የአይሁድ መሪዎች ሁሉ›› ወይም፣ ‹‹የሸንጐው አባሎች ሁሉ››
‹‹ቆሙ›› ወይም፣ ‹‹በእግራቸው ቆሙ››
አንድ ሰው ፊት መቅረብ እርሱ ሥልጣን ውስጥ መግባት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የጲላጦስን ፍርድ ለማግኘት››
‹‹እኛ›› የሚያመለክተው ጲላጦስን ወይም እዚያ የነበሩትን ሳይሆን የሸንጐውን አባሎች ነው፡፡
‹‹ሕዝባችንን ሲያሳስት›› ወይም፣ ‹‹ሐሰት በመናገር ሕዝባችንን ሲያውክ››
‹‹ግብር እንዳይከፍል ሲናገር››
ቄሳር የሮምን ንጉሥ ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ለንጉሥ››
‹‹ጲላጦስ ኢየሱስን ጠየቀው››
ይህም ማለት፣ 1) እንዲህ ሲል ኢየሱስ እርሱ የአይሁድ ንጉሥ መሆኑን እያመለከተ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አዎን፣ አንተ እንዳልኸው ነኝ›› ወይም፣ ‹‹አዎን፣ አንተ እንዳልኸው ነው›› ወይም 2) ኢየሱስ ይህን ሲል፣ የአይሁድ ንጉሥ በማለት የጠራው ጲላጦስ እንጂ፣ እርሱ አለመሆኑን እያመለከተ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ያንን ያልኸው አንተ ራስህ ነህ››
ብዙ ሕዝብ
‹‹ይህን ሰው በምንም ዐይነት በደለኛ ሆኖ አላገኘሁትም››
‹‹በመካከል ሲረብሽ››
ይህን እንደ አዲስ ዐረፍተ ነገር መጻፍ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በይሁዳ ሁሉ፤ በገሊላ አሁን ደግሞ እዚህ ያውካል››
‹‹ኢየሱስ በገሊላ ማስተማር መጀመሩን ሰምተናል››
ጲላጦስ ኢየሱስ የመጣበትን ማወቅ የፈለገው ኢየሱስ ዝቅ ወዳለ ባለሥልጣን እንዲቀርብ ስለ ፈለገ ነው፡፡ ከገሊላ ከሆነ በገሊላ ላይ ሥልጣን ያለው ሄሮድስ ስለሆነ ሄሮድስ ኢየሱስ ላይ መፍረድ ነበረበት፡፡
x
‹‹ሄሮድስ በጣም ደስ አለው››
‹‹ሄሮድስ ኢየሱስን ለማየት ይመኝ ነበር››
‹‹ሄሮድስ ስለ ኢየሱስ ሰምቶ ነበር››
‹‹ሄሮድስ ተስፋ ያደርግ ነበር››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አንዳንድ ተአምራት ሲያደርግ ለማየት››
‹‹ሄሮድስ ኢየሱስን ብዙ ጥያቄዎች ጠየቀው››
‹‹መልስ አልሰጠውም›› ወይም፣ ‹‹ለሄሮድስ መልስ አልሰጠውም››
‹‹ጸሐፍት እዚያ ቆመው ነበር››
‹‹አጥብቀው ኢየሱስን ከሰሱት›› ወይም፣ ‹‹ኢየሱስን በብዙ ዐይነት ወንጀል ከሰሱት››
‹‹ሄሮድስና ሰራዊቱ››
‹‹ያማረ ልብስ አለበሰው›› ትርጒሙ ይህ ለኢየሱስ ክብርን ወይም ማሰብን እንደማያሳይ ማመልከት አለበት፡፡ ይህን ያደረጉት ኢየሱስ ላይ ለማፌዝና በእርሱ ለመቀለድ ነበር፡፡
ከዚህ የምናገኘው መረጃ የተወዳጁት ኢየሱስ ላይ እንዲፈርድ ጲላጦስ ማድረጉን ሄሮድስ በማድነቁ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በእርሱ ላይ እንዲፈርድ ጲላጦስ ኢየሱስን ወደ ሄሮድስ ስለላከው በዚያ ቀን ሄሮድስና ጲላጦስ ተወዳጁ››
x
‹‹የካህናት አለቆችንና ገዦችን፣ የሕዝቡንም ጉባኤ ስብሰባ ጠራ››
ጲላጦስ ብዙ ሕዝብ አልጠራም፡፡ ኢየሱስ ላይ የሚሆነውን ለማየት ሕዝቡ እዚያው ነበሩ፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እዚያ የነበረውን ሕዝብ››
ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው፡፡
‹‹በፊታችሁ ኢየሱስን መረመርሁ›› ይህ ማለት የሚሆነውን ሁሉ እያዩ ነበር ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እዚሁ እናንተው ፊት ኢየሱስን መረመርሁት››
‹‹በደለኛ ነው ብዬ አላስብም››
ጲላጦስ ለአይሁድ መሪዎችና ለሕዝቡ መናገር ቀጥሏል፡፡
እዚህ አጭር ዐረፍተ ነገር ውስጥ ያልተካተተ መረጃ መጨመር ሊጠቅም ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሄሮድስም ቢሆን በደለኛ ነው ብሎ አያስብም›› ወይም፣ ‹‹ሄሮድስም ቢሆን ንጹሕ ነው ብሎ ያስባል፡፡
‹‹ሄሮድስም ቢሆን ምክንያቱም›› ወይም፣ ‹‹ሄሮድስም እንዲሁ፤ ምክንያቱም እኛ እናውቃለን››
‹‹ሄሮድስ ኢየሱስን ወደ እኛ መለሰው›› — ‹‹እኛ›› የሚለው ጲላጦስን፣ ወታደሮቹን፣ ካህናትና ጸሐፍትንና እንጂ፣ ጲላጦስንና እየሰሙ የነበሩን ሰዎች አያመለክትም፡፡
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ለሞት ፍርድ የሚያደርስ ምንም አላደረገም››
ጲላጦስ ኢየሱስ ላይ ጥፋት ባለማግኘቱ ሳይቀጣው ሊፈታው ይገባ ነበር፡፡ ይህ ዐረፍተ ነገር ትርጒሙ ውስጥ ምክንያታዊ እንዲሆን ማድረግ አስፈላጊ አይደለም፡፡ ሕዝቡን በመፍራቱ ብቻ ንጹሕ መሆኑን የሚያውቀውን ኢየሱስን ጲላጦስ ቀጣው፡፡
ቁጥር 19 በርባን ማን እንደ ነበር መረጃ ይሰጠናል፡፡
‹‹ሕዝቡ ሁሉ በአንድነት ጮኹ››
‹‹ይህን ሰው ወዲያ በለው፤ ፍታልን!›› ወታደሮቹ ኢየሱስን እንዲገድሉ እየጠየቁት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ይህን ሰው ወዲያ ብለህ ግደለው፤ ፍታው››
‹‹እኛ›› የሚለው የሚያመለክተው ሕዝቡን ብቻ እንጂ፣ ጲላጦስንና ወታደሮቹን አይደለም፡፡
ይህ ስለ በርባን ማንነት ሉቃስ የሚሰጠን ማስረጃ ነው፡፡
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሮማውያን አስረውት ነበር››
‹‹የከተማው ሰዎች የሮም መንግሥት ላይ እንዲያምፁ ለማነሣሣት በመሞከር››
‹‹በድጋሚ ተናገራቸው›› ወይም፣ ‹‹ለሕዝቡና ለሃይማኖት መሪዎች እንደ ገና ነገራቸው››
‹‹ኢየሱስን ነጻ ማድረግ ስለ ፈለገ››
‹‹ጲላጦስ ለሦስተኛ ጊዜ እንደ ገና ለሕዝቡ አላቸው››
ጲላጦስ ይህን ጥያቄ ያቀረበው ኢየሱስ ንጹሕ መሆኑን ሕዝቡ እንዲረዱ ለማስቻል ነበር፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ይህ ሰው ምንም ያደረገው በደል የለም››
‹‹ለሞት የሚያበቃው ምንም አላደረገም››
እርሱ ንጹ በመሆኑ ሉቃስ 23፥16 ላይ ጲላጦስ ያለ ምንም ቅጣት ሊፈታው ይገባ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ፣ የሕዝቡን ቁጣ ለማብረድ ኢየሱስን መቅጣት ፈለገ፡፡
‹‹ነጻ እለቀዋለሁ››
‹‹ሕዝቡ አጥብቀው ለመኑት››
‹‹በጩኸት››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የጲላጦስ ወታደሮች ኢየሱስን እንዲሰቅሉ››
‹‹ጲላጦስ እሺ እስኪል ድረስ ሕዝቡ ጩኹ››
‹‹ሕዝቡ የጠየቁትን ለማድረግ››
ጲላጦስ በርባንን ከእስር ፈተው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ጲላጦስ ሕዝቡ የለመኑትን በርባንን ፈታው››
ይህ በዚያ ጊዜ በርባን የት እንደ ነበር ዳራ መረጃ ነው፡፡ ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሮማውያን በግድያ አስረውት… የነበረውን››
‹‹ሕዝቡ የፈለጉትን እንዲያደርጉበት ጲላጦስ ወታደሮቹ ኢየሱስን እንዲያመጣላቸው አዘዘ፡፡
‹‹ወታደሮቹ ጲላጦስ ከነበረበት ኢየሱስን እየወሰዱ ሳለ››
ሮማውያን ወታደሮች ሰዎች ሸክም እንዲሸከሙ የማስገደድ ሥልጣን ነበራቸው፡፡ ይህን ስምዖን እንደ ታሰረ ወይም አንዳች በደል መፈጸሙን በሚያሳይ መልኩ አትተርጉም፡፡
‹‹ከቀሬና ከተማ የሆነ ስምዖን የሚባል ሰው››
‹‹ከገጠር ወደ ኢየሩሳሌም እየመጣ የነበረ››
‹‹መስቀሉን ትከሻው ላይ አኖሩ››
‹‹ከኢየሱስ ኋላ ተከተለ››
‹‹በጣም ብዙ ሰዎች››
ሴቶቹ የብዙ ሕዝብ አካል እንጂ፣ በራሳቸው ብዙ ሕዝብ አልነበሩም፡፡
‹‹ለኢየሱስ አለቀሱ››
ይህ ማለት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ነበሩ ማለት አይደለም፡፡ ከእርሱ ኋላ ኋላ ይሄዱ ነበር ማለት ብቻ ነው፡፡
ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስ ወደ ሴቶቹ ዘወር ማለቱንና በቀጥታ ለእነርሱ መናገሩን ነው፡፡
‹‹የከተማው ሴቶች›› ማለት ከተማው ውስጥ የሚኖሩ ሴቶች ማለት ነው፡፡ ይህ ነውር ሳይሆን ከሌላው አካባቢ ሴቶች ለይቶ ለማመልከት የሚያገለግል አባባል ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እናንተ ከኢየሩሳሌም የሆናችሁ ሴቶች››
አንድ ሰው አንዳች ነገር እየሆነ ያለበትን ሰው ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እኔ ላይ እየደረሰ ስላለው መከራ አታልቅሱ፤ ይልቁን፣ በእናንተና በልጆቻችሁ ላይ ስለሚደርሰው መከራ አልቅሱ›› ወይም፣ ‹‹እኔ ላይ በደረሰው መከራ እያለቀሳችሁ ነው፤ እናንተና ልጆቻችሁ ላይ በሚደርሰው የከፋ ነገር ይበልጥ ታለቅሳላችሁ››
ኢየሱስ ለሕዝቡ መናገሩን አበቃ
ይህ የኢየሩሳሌም ሴቶች ለራሳቸው የሚያለቅሱበትን ምክንያት ያቀርባል፡፡
‹‹በቅርቡ ጊዜ ይመጣል››
‹‹ሰዎች እንዲህ የሚሉበት››
‹‹ልጆች የሌሉዋቸው ሴቶች››
ገለጻዎቹ የተሰጡት፣ ‹‹መካኖችን›› የበለጠ ለመግለጽ ነው፡፡ እነዚህ ሴቶች አልወለዱም፤ ልጆች ጡት አላጠቡም፡፡ ሁለቱንም ከመካንነት ጋር ማያያዙ ይጠቅማል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ልጆች ያልወለዱ፣ ወይም ጡት ያላጠቡ መካኖች››
በዚያ ጊዜ
ሐረጉን አጭር ለማድረግ ቃላት ተትተዋል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ተራሮችን ይሉዋቸዋል››
ኢየሱስ ይህን ጥያቄ ያቀረበው በመልካሙ ጊዜ ይህን ያህል መጥፎ ነገር ካደረጉ፣ ወደ ፊት በሚመጣው ክፉ ጊዜ ደግሞ ከዚህ የከፋ ነገር እንደሚያደርጉ ሕዝቡ መገንዘብ እንዲችሉ ለመርዳት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ዛፉ ደረቅ በሚሆንበት ጊዜ የበለጠ መጥፎ ነገር እንደሚያደርጉ እርግጠኛ መሆን ትችላላችሁ››
እርጥብ ዛፍ የመልካም ነገር ምሳሌ ነው፡፡ ቋንቋህ ተመሳሳይ ምሳሌ ካለው እዚህ ተጠቀምበት፡፡
ደረቅ ዛፍ ለመቃጠል ብቻ የሚጠቅም ነገርን የሚያመለክት ምሳሌ ነው፡፡
ይህ የሚያመለክተው ሮማውያንን ወይም የአይሁድ መሪዎችን ሊሆን ይችላል፡፡ ከሁለት አንዱን ብቻ አይደለም፡፡
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ወታደሮቹ ሁለት ወንጀለኞች እንዲገደሉ ከኢየሱስ ጋር ወሰዱ››
‹‹ወንጀለኞች የነበሩ ሁለት ሌሎች ሰዎች›› ወይም፣ ‹‹ሁለት ወንጀለኞች›› ሉቃስ ‹‹ሌሎች ወንጀለኞች›› ማለት አልፈለጉም፤ ምክንያቱም ምንም እንኳ እንደ ወንጀለኛ ቢቆጠርም፣ ኢየሱስ ንጹሕ ሰው ነበር፡፡ ሉቃስ ሌሎቹን ሁለት ሰዎች እንጂ፣ ኢየሱስን ወንጀለኛ አላለም፡፡
‹‹እነርሱ›› የሚያመለክተው ወታደሮቹን፣ ወንጀለኞቹንና ኢየሱስን ነው፡፡
‹‹የሮም ወታደሮች ኢየሱስን ሰቀሉት››
‹‹አንዱን ወንጀለኛ በኢየሱስ ቀኝ ሌላውን ወንጀለኛ በኢየሱስ ግራ ጐን ሰቀሉ››
‹‹እነርሱ›› የሚያመለክተው ኢየሱስን የሰቀሉ ሰዎች ነው፡፡ ኢየሱስ ወደ አባቱ የጸለየው ለሰቀሉት ሰዎች በመራራት ነበር፡፡
ይህ ጠቃሚ የእግዚአብሔር መጠሪያ ነው፡፡
‹‹ምክንያቱም ምን እያደረጉ እንደሆነ አያስተውሉም›› የሮም ወታደሮች የእግዚአብሔርን ልጅ እየሰቀሉ እንደ ነበር አይረዱም፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እየሰቀሉ ያለው ማን እንደሆነ በእርግጥ አይረዱም፡፡
ወታደሮቹ ቁማር በሚመስል አሠራር ተሳተፉ፡፡ ‹‹ቁማር ተጫወቱ››
‹‹እያንዳንዱን የኢየሱስ ልብስ ቁራጭ ማን መውሰድ እንዳለበት ለመወሰን ወታደሮቹ ዕጣ ጣሉ››
‹‹ሕዝቡ እዚያ ቆመው ነበር››
ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው፡፡
ሉቃስ የመሪዎቹን ስላቅ ቃሎች አስፍሮአል፡፡ ኢየሱስ ሌሎቹን የሚያድንበት ብቸኛ መንገድ በመሞት እንጂ፣ ራሱን በማዳን አይደለም፡፡
‹‹ኢየሱስ ራሱን ማዳን መቻል አለበት›› ይህን ያሉት በኢየሱስ ለማፌዝ ነው፡፡ ራሱን ማዳን እንደሚችል አያምኑም፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ራሱን ከመስቀል በማዳን ማንነቱን ሲያረጋግጥ ማየት እንፈልጋለን››
‹‹እግዚአብሔር የመረጠው እርሱ››
ኢየሱስ
‹‹ወደ ኢየሱስ ተጠግቶ››
‹‹ኢየሱስ እንዲጠጣ የኮመጠጠ ወይን ጠጅ ቀረበለት›› ኮምጣጣ ወይን ጠጅ ማንኛውም ሰው የሚጠጣው ተራ መጠጥ ነው፡፡ ንጉሥ ነኝ ይል ለነበረው ርካሽ መጠጥ በመስጠት ወታደሮቹ በኢየሱስ እያፌዙ ነበር፡፡
ወታደሮቹ በኢየሱስ እያፌዙ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የአይሁድ ንጉሥ ነህ ብለን አናምንም፤ ግን ከሆንህ ራስህን በማዳን ስህተታችንን አሳየን››
‹‹ኢየሱስ መስቀል ዐናት ላይ የነበረ ጽሑፍ››
ምልክቱን ከእርሱ በላይ በማድረግ ሰዎቹ ኢየሱስ ላይ እያፌዙ ነበር፡፡ ንጉሥ ነው ብለው አያስቡም፡፡
‹‹ኢየሱስን ሰደቡት››
ወንጀለኛው ጥያቄውን ያቀረበው በኢየሱስ ለማፌዝ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ክርስቶስ ነኝ ብለሃል፤ ራስህን አድን›› ወይም፣ ‹‹አንተ በእርግጥ ክርስቶ ከሆንህ ራስህን ማዳን ነበረብህ››
ወንጀለኛው ኢየሱስ ከመስቀል እንደሚያድናቸው በእርግጥ አያስብም፡፡
‹‹ሌላው ወንጀለኛ ገሠጸው››
ወንጀለኛው ጥያቄውን ያቀረበው ሌላውን ወንጀለኛ ለመገሠጽ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እግዚአብሔርን መፍራት አለብህ ምክንያቱም እርሱን በቀጡበት መንገድ አንተንም እየቀጡህ ነው፡፡ ወይም፣ ‹‹እንደ እርሱ ሁሉ አንተም መስቀል ላይ ተሰቅለህ ሳለ እርሱ ላይ በማፌዝህ እግዚአብሔንር አትፈራም ማለት ነው››
‹‹እኛ›› የሚያመለክተው ሁለቱን ወንጀለኞች እንጂ፣ ኢየሱስን ወይም ሌሎችን ሰዎች አይደለም፡፡
‹‹በእውነት እኛ ይህ ቅጣት ይገባናል››
ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው
‹‹ወንጀለኛውም አለ››
‹‹እኔንም አስበኝ፤ በመልካም እየኝ››
‹‹ወደ መንግሥትህ ስትመጣ›› ማለት መግዛት ስትጀምር ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እንደ ንጉሥ መግዛት ስትጀምር››
‹‹በእውነት›› የተጨመረው ኢየሱስ ለተናገረው አጽንዖት ለመስጠት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ዛሬ ያንን እንድታውቅ እፈልጋለሁ››
‹‹ቀትር አካባቢ›› ይህ ቀኑ በ12 ሰዓት መቆጠር በሚጀምርበት ባሕል ያለውን ያመለክታል፡፡
‹‹ምድሩ ሁሉ ጨለማ ሆነ››
እስከ 3 ሰዓት ‹‹ይህ የሚያመለክተው ቀኑ 12 ሰዓት ላይ መቆጠር የሚጀምርበትን ባሕል ነው፡፡
ይህ ፀሐይ ጠለቀች ማለት አይደለም፡፡ ይልቁን ቀኑ አጋማሽ ላይ የፀሐይ ብርሃን ጨለመ ማለት ነው፡፡ ፀሐይ ጠለቀች የሚል ሳይሆን ፀሐይ ጨለመች የሚል አገላለጽ ተጠቀም፡፡
‹‹ቤተ መቅደስ ውስጥ ያለው መጋረጃ›› ይህ ቅዱሳት ቅዱሳኑን ከተቀረው መቅደስ የሚለይ መጋረጃ ነው፡፡
x
‹‹በጣም ጮኸ›› ይህን ቀደም ሲል ከነበረው ቁጥር ሁኔታ ጋር ማያያዙ መልካም ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ያ በሚሆንበት ጊዜ ኢየሱስ በጣም ጮኸ››
ይህ በጣም አስፈላጊ የእግዚአብሔር መጠሪያ ነው፡፡
‹‹በእጅህ›› የሚለው የእግዚአብሔርን ጥበቃ ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹መንፈሴን ለአንተ ጥበቃ እሰጣለሁ›› ወይም፣ ‹‹አንተ እንድትጠብቀው በማወቅ፣ መንፈሴን ለአንተ እሰጣለሁ››
‹‹ኢየሱስ ይህን ካለ በኋላ››
‹‹ኢየሱስ ሞተ››
ይህ በሌሎች ሮማውያን ወታደሮች ላይ ኀላፊነት ላለው ሮማዊ ባለ ሥልጣን የሚሰጥ መጠሪያ ነው፡፡ ስቅለቱን ይከታተል ነበር፡፡
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የሆነውን ነገር ሁሉ››
‹‹ይህ ሰው ምንም በደል አልፈጸመም›› ወይም፣ ‹‹ይህ ሰው ያደረገው መጥፎ ነገር የለም››
በጣም ብዙ ሰዎች
‹‹ተሰብስበው የነበሩ››
‹‹ይህን ሁኔታ ያዩ›› ወይም፣ ‹‹እየሆነ ያለውን የተመለከቱ››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የሆነውን››
‹‹እየመቱ ወደ ቤታቸው ተመለሱ››
ይህ የሐዘንና የፀፀት ምልክት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ማዘናቸውን ለማሳየት የገዛ ራሳቸውን ደረት እየመቱ››
‹‹ከኢየሱስ ጋር ተጓዙ››
‹‹ከኢየሱስ ጥቂት ራቅ ብሎ››
‹‹የሆነው››
ዮሴፍ ጲላጦስን የኢየሱስን ሥጋ ለመነው፡፡ ይህ ስለ ዮሴፍ ታሪክ መረጃ ይሰጠናል፡፡ ምናልባትም ዩዲቢ እንዳደረገው ይህን መረጃ ከመሸጋገሪያ ጥቅስ ጋር መጻፍ ይጠቅም ይሆናል፡፡
‹‹እነሆ›› የሚለው ቃል የአዲስ ሰው ታሪክ እንድንሰማ ያዘጋጀናል፡፡ ቋንቋህ ይህን የሚያደርግበት መንገድ ይኖረዋል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹… የሆነ ሰው ነበር››
‹‹የአይሁድ ሸንጐ››
ውሳኔው ምን እንደ ነበር መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ኢየሱስን ለመግደል ባደረጉ ውሳኔም ሆነ እርሱን በመግደል ድርጊታቸው››
‹‹የይሁዳ ከተማ›› ማለት ይሁዳ ውስጥ ነበረች ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ይሁዳ ውስጥ ያለች አርማትያስ የምትባል ከተማ››
‹‹ይህ ሰው ወደ ጲላጦስ ሄዶ የኢየሱስን ሥጋ ለመቅበር እንዲሰጠው ጠየቀ››
‹‹ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ከመስቀል አወረደ››
‹‹ሥጋውን በንጹሕ በፍታ ልብስ ጠቀለለው›› በዚያ ዘመን ይህ የተለመደ አቀባበር ሥርዐት ነበር፡፡
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አንድ ሰው ገደል ላይ ካለ ዐለት የፈለፈለው››
ይህን በአዲስ ዐረፍተ ነገር መተርጐም ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ከዚያ በፊት የማንም ሰው ሥጋ ባልተቀመጠበት››
‹‹ሰንበት ለሚባለው ዕረፍት አይሁድ የሚዘጋጁበት ቀን››
ለአይሁድ ቀኑ የሚጀምረው ፀሐይ ስትጠልቅ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ፀሐይ ጠልቃ ሰንበት የሚጀምርበት ጊዜ ቀርቦ ነበር››
‹‹ከገሊላ አውራጃ ከኢየሱስ ጋር የተጓዙ››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ከዮሴፍና አብረውት ከነበሩ ሰዎች ኋላ በመሄድ፣ ሴቶቹ መቃብሩንና ሰዎቹ የኢየሱስን ሥጋ መቃብሩ ውስጥ እንዴት እንዳኖሩት አዩ››
‹‹ሴቶቹ ወደ ቤት ተመለሱ››
እርሱ በሞተበት ቀን ሴቶቹ መዓዛ ያለው ሽቱና ቅባት በማድረግ ኢየሱስን ለማክበር ጊዜ ስላልነበራቸው በሳምንቱ መጀመሪያ ቀን ጠዋት ያንን ለማድረግ ሄዱ፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የኢየሱስ ሥጋ ላይ ለማኖር ሽቱና ቅባት አዘጋጁ››
‹‹ሴቶቹ ምንም አልሠሩም››
‹‹እንደ አይሁድ ሕግ›› ወይም፣ ‹‹የአይሁድ ሕግ እንደሚያዝዘው›› በሕጉ መሠረት በሰንበት ሥጋን ለማዘጋጀት አይፈቀድላቸውም፡፡
1 በሳምንቱ በመጀመሪያው ቀን ሴቶች ያዘጋጁትን ሽቱ ይዘው በጣም ማልደው ወደ መቃብሩ መጡ። 2 ድንጋዩ ከመቃብሩ ተንከባሎ አገኙት። 3 ወደ ውስጥ ገቡ፣ ነገር ግን የጌታ ኢየሱስን ሥጋ አላገኙም። 4 ስለዚህ ነገር ግራ ተጋብተው ሳሉ፣ የሚያብረቀርቅ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች በድንገት ከአጠገባቸው ቆመው አገኙ። 5 ሴቶቹ በፍርሃት ተሞልተውና ወደ መሬት አቀርቅረው ሳሉ፣ ሰዎቹ ፣“ስለምን ሕያውን ከሙታን መካከል ትፈልጋላችሁ? 6 እርሱ በዚህ የለም፣ ተነሥቷል! ገና በገሊላ ሳለ፣ 7 እንዴት በኃጢአተኞች ሰዎች እጅ ተላልፎ እንደሚሰጥ፣ እንደሚሰቀልና በሦስተኛው ቀን እንደሚነሣ የነገራችሁን አስታውሱ" አሏቸው። 8 ሴቶቹ ቃሎቹን አስታወሱ፣ 9 ከመቃብሩም ተመለሱና እነዚህን ነገሮች ሁሉ ለዐሥራ አንዱና ለተቀሩትም ነገሩ። 10 መግደላዊት ማርያም፣ ዮሐናና የያዕቆብ እናት ማርያም እንዲሁም ሌሎች ሴቶች ሁኔታውን ለሐዋርያት ነገሯቸው። 11 ነገር ግን ይህ ንግግር ለሐዋርያቱ ቀልድ ስለ መሰላቸው፣ ሴቶቹን አላመኗቸውም፣ 12 ሆኖም ግን ጴጥሮስ ተነሣና እየሮጠ ወደ መቃብሩ ሄደ፣ ከዚያም አጎንብሶ ወደ ውስጥ ሲመለከት፣ የተልባው እግር ጨርቅ ለብቻው ተቀምጦ አየ። ከዚያ በኋላ ጴጥሮስ ምን ተፈጥሮ ይሆን ብሎ እያሰበ ወደ ቤቱ ተመለሰ። 13 እነሆ፣ ከእነርሱ ሁለቱ በዚያው ቀን ከኢየሩሳሌም ስድሳ ምዕራፍ ርቆ ወደሚገኝ ኤማሁስ ወደሚባል መንደር እየተጓዙ ነበር። 14 ስለሆኑት ነገሮች ሁሉ በመንገዳቸው ላይ እርስ በርስ ይነጋገሩ ነበር። 15 እየተነጋገሩና እየተጠያየቁ በመሄድ ላይ ሳሉ፣ ኢየሱስ ወደ እነርሱ ተጠግቶ ይሄድ ነበር። 16 ነገር ግን እርሱን እንዳያውቁት ዐይኖቻቸው ተይዘው ነበር። 17 ኢየሱስ፣ “እናንተ ሁለታችሁ እየተጓዛችሁ የምትነጋገሩት ስለምንድን ነው?” አላቸው። ያዘኑ መስለው ቆም አሉ። 18 ስሙ ቀለዮጳ የተባለ ከሁለቱ አንዱ፣ “በኢየሩሳሌም ሰሞኑን የተደረጉትን ነገሮች የማታውቅ አንተ ብቻ ነህን?" ብሎ መለሰለት። 19 ኢየሱስም፣ “ነገሮቹ ምንድን ናቸው?” አላቸው። 20 እነርሱም እንዲህ ብለው መለሱለት፣ “የካህናት አለቆችና ገዢዎቻችን ኢየሱስ የተባለውን ናዝራዊና ነቢይ እንዴት አድርገው እንደ ፈረዱበትና ለሞትና ለስቅላት አሳልፈው እንደ ሰጡት ነዋ። 21 እስራኤልን ነጻ ያወጣል ብለን ተስፋ ያደረግነው እርሱን ነበር። አዎን፣ ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ይህ ነገር ከሆነ አሁን ሦስተኛ ቀኑ ነው” 22 ነገር ግን ጠዋት ወደ መቃብሩ የሄዱ ከእኛ ጋር የሆኑ አንዳንድ ሴቶች አስገረሙን። 23 ሥጋውን ባላገኙ ጊዜ፣ በመቃብሩ ውስጥ ሥጋውን እንዳላገኙና እርሱ ሕያው ሆኗል ብለው የነገሯቸውን የመላእክት ራእይ አይተናል አሉ። 24 ከእኛ ጋር ካሉት ወንዶችም አንዳንዶች ወደ መቃብሩ ሄደው ልክ ሴቶቹ እንዳሉት ሆኖ አገኙት። ነገር ግን እርሱን አላዩትም”። 25 ኢየሱስም፣ “ነቢያት የተናገሩትን ሁሉ ለማመን የዘገያችሁ እናንተ ሞኞች! 26 ክርስቶስ በእነዚህ ነገሮች መሠቃየቱና ወደ ክብሩ መግባቱ ግድ መሆኑን አታውቁምን?" አላቸው። 27 ከዚያም ከሙሴ ጀምሮ እስከ ነቢያት መጻሕፍት፣ በመጻሕፍት ሁሉ ስለ እርሱ የተነገረውን ተረጐመላቸው። 28 ወደሚሄዱበት መንደር በተቃረቡ ጊዜ፣ ኢየሱስ ቀደም ቀደም እያለ መሄድ ጀመረ። 29 ነገር ግን እነርሱ፣ “ቀኑ እየመሸ ጊዜውም እያለፈ ስለ ሆነ ከእኛ ጋር እደር” ብለው ጎተጎቱት። ስለዚህ ኢየሱስ ከእነርሱ ጋር ሊያድር ሄደ። 30 ለመብላት ከእነርሱ ጋር በማዕድ በተቀመጠ ጊዜ፣ እንጀራውን ወሰደና ከባረከው በኋላ ቈርሶ ሰጣቸው። 31 በዚህ ጊዜ ዐይኖቻቸው ተከፈቱና አወቁት። እርሱ ግን ከዐይናቸው ተሰወረባቸው። 32 እርስ በርሳቸው፣ “በመንገድ ላይ አብረን ሳለን ሲያናግረንና መጻሕፍትን ሲከፍት ልባችን በውስጣችን ይቃጠልብን አልነበርምን?” ተባባሉ። 33 በዚያው ሰዓት ተነሥተው ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። ዐሥራ አንዱና ከእነርሱ ጋር የነበሩትም ተሰብስበው እንዲህ እያሉ አገኟቸው፤ 34 “ጌታ በእርግጥ ተነሥቷል፣ ለስምዖንም ታይቷል።” 35 ከዚያም በመንገድ ላይ የሆነውን ነገርና ኢየሱስ በማዕድ እንጀራን በሚቈርስበት ጊዜ እንዴት እንደ ታያቸው ተናገሩ። 36 እነዚህን ነገሮች እየተናገሩ እያሉ ኢየሱስ ራሱ በመካከላቸው ቆሞ፣ “ሰላም ለእናንተ ይሁን" አላቸው። 37 እነርሱም ስለ ተሸበሩና በፍርሃት ስለ ተዋጡ መንፈስ ያዩ መሰላቸው። 38 ኢየሱስ፣ “ለምን ትጨነቃላችሁ? ለምንስ በልባችሁ ጥያቄዎች ይነሣሉ? 39 እኔው ራሴ ስለ መሆኔ እጆቼንና እግሮቼን እዩ። ዳሳችሁም እዩኝ። በእኔ እንደምታዩት መንፈስ ሥጋና አጥንት የለውም" አላቸው። 40 ይህን ተናግሮ እጆቹንና እግሮቹን አሳያቸው። 41 ከደስታ የተነሣ ማመን ተስኗቸው ግራ ተጋብተው ሳሉ፣ ኢየሱስ፣ “የሚበላ ጥቂት ነገር ይኖራችኋል?” አላቸው። 42 የተጠበሰ ዐሣ ሰጡት። 43 ኢየሱስም ወስዶ በፊታቸው በላው። 44 እንዲህም አላቸው፤ “ከእናንተ ጋር በነበርሁ ጊዜ በሙሴ ሕግ፣ በነቢያትና በመዝሙራት የተጻፈው ሁሉ መፈጸም እንደሚገባው ነግሬአችሁ ነበር።” 45 ከዚያም መጻሕፍትን ይረዱ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው። 46 እንዲህ አላቸው፤ “እንግዲህ ክርስቶስ መሠቃየት፣ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን መካከል መነሣት እንደሚገባው በመጻሕፍት ተጽፏል። 47 ደግሞም ንስሐና የኃጢአት ይቅርታ ከኢየሩሳሌም ጀምሮ ለአሕዛብ ሁሉ በስሙ መሰበክ አለበት። 48 እናንተ የእነዚህ ነገሮች ምስክሮች ናችሁ። 49 እነሆ፣ የአባቴን ተስፋ በእናንተ ላይ እልካለሁ። ኅይልን ከላይ እስከምትቀበሉ ድረስ በዚህ ከተማ ሆናችሁ ተጠባበቁ።" 50 ከዚያም ኢየሱስ ወደ ቢታንያ እስከሚቃረቡ ድረስ ይዟቸው ሄደ። እጆቹንም አነሣና ባረካቸው፤ 51 እየባረካቸውም ሳለ ወደ ሰማይ ከፍ ከፍ አለ። 52 ስለዚህ እነርሱ ሰገዱለት፣ እጅግ ደስ እያላቸውም ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። 53 በቤተ መቅደስም ያለ ማቋረጥ እግዚአብሔርን ያመሰግኑ ነበር።
ሴቶቹ የኢየሱስ ሥጋ ላይ ለማድረግ ሽቱ ይዘው ወደ መቃብሩ ተመለሱ፡፡
‹‹ከእሑድ ጠዋት በፊት››
‹‹ሴቶቹ ወደ መቃብሩ ደረሱ››
ከገደል ዐለት ተፈልፍሎ የተሠራ መቃብር፡፡
ይህ ሉቃስ 23፥56 ላይ ያዘጋጁት ሽቱ ነው፡፡
‹‹ድንጋዩን አዩ››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሰው ድንጋዩን አንከባልሎት››
ይህ የመቃብሩን መግቢያ በር መዝጋት የሚችል ትልቅ፣ የተጠረበና ክብ ትልቅ ድንጋይ ነው፡፡ ያንን ለማንከባለል ብዙ ሰው ይጠይቃል፡፡
ያላገኙት እዚያ ስላልነበረ መሆኑን በግልጽ ማመልከት ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የጌታ ኢየሱስ ሥጋ እዚያ አልነበረም››
መላእክት ተገልጠው ለሴቶቹ መናገር ጀመሩ
ይህ ሐረግ ጥቅም ላይ የዋለው ታሪኩ ውስጥ አዲስ ሁኔታ መጀመሩን ለማመልከት ነው፡፡ ቋንቋህ ይህን የሚያደርግበት መንገድ ካለው እዚህ ላይ ተጠቀምበት፡፡
‹‹በጣም ፈሩ››
‹‹ወደ መሬት በጣም ዝቅ›› ይህ የሚያመለክተው ለሰዎቹ ያላቸውን አክብሮት ነው፡፡
x
መላእክቱ ለሴቶቹ መናገር አበቁ
‹‹ግን እርሱ እንደ ገና ሕያው ሆኖአል›› እዚህ ላይ፣ ‹‹ተነሣ›› የሚለው፣ ‹‹እንደ ገና ሕያው መሆንን›› ያመለክታል፡፡ ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ምክንያቱም እግዚአብሔር እንደ ገና ሕያው አድርጐታል››
‹‹የነገራችሁን አስታውሱ››
‹‹እናንተ›› ብዙ ቁጥር ሲሆን ሴቶቹንና በተጨማሪም ሌሎቹን ደቀ መዛሙርት ሊያመለክት ይችላል፡፡
ይህ ቀጥተኛ ያልሆነ ጥቅስ መጀመሪያ ነው፡፡ ዩዲቢ ላይ እንዳለው በቀጥተኛ ጥቅስ ሊተረጐም ይችላል፡፡
‹‹ይገባዋል›› የሚለው እንደዚያ እንዲሆን እግዚአብሔር በመወሰኑ በእርግጥ መሆኑ የማይቀር ነገር ማለት ነው፡፡ ይህን በሌላ መልኩ መተርጐም ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እርሱን ለሚሰቅሉ ክፉ ሰዎች የሰውን ልጅ አሳልፈው መስጠታቸው አስፈላጊ ነበር››
እዚህ ላይ፣ ‹‹እጅ›› ኀይል ወይም ቁጥጥርን ያመለክታል፡፡
አይሁድ ማንኛውንም የቀኑን ክፍል እንደ ቀን ይቆጥራሉ፡፡ ስለዚህም የተቀበረበትንና የሰንበትን ቀን በማስከተሉ ኢየሱስ የተነሣበት ቀን ‹‹ሦስተኛ ቀን›› ተብሏል፡፡
ሴቶቹ መቃብሩ ውስጥ ያዩትን ለሐዋርያት ለመናገር ሄዱ፡፡
እዚህ ላይ፣ ‹‹ቃል›› ኢየሱስ የተናገረውን ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ኢየሱስ የተናገረውን አስታውሱ››
‹‹ዐሥራ አንዱ ሐዋርያትና ከእነርሱ ጋር የነበሩ ደቀ መዛሙርት››
ይሁዳ ከዐሥራ ሁለቱ ተለይቶ ኢየሱስን አሳልፎ በመስጠቱ ሉቃስ ዐሥራ አንዱን ሲያመለክት ይህ የመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡
ቃሉ እዚህ ጥቅም ላይ የዋለው በዋናው ታሪክ መስመር የገባ መኖሩን ለማመልከት ነው፡፡ እዚህ ላይ ሉቃስ ከመቃብር መጥተው እዚያ የሆነውን ለሐዋርያት የተናገሩ የአንዳንድ ሴቶችን ስም ይሰጣል፡፡
‹‹ሐዋርያቱ ሴቶቹ ጅል ነገር እየተናገሩ እንደሆነ አሰቡ››
ይህ ሐረግ ጴጥሮስን ከሌሎቹ ሐዋርያት ያነጻጽራል፡፡ ሴቶቹ የተናገሩትን አላቃለለውም፤ ግን ለራሱ ለማየት ወደ መቃብሩ ሮጠ፡፡
ይህ አነጋገር፣ ‹‹ማድረግ ጀመረ›› ማለት ነው፡፡ ማድረግ በጀመረ ጊዜ ጴጥሮስ ተቀምጦ ይህን ወይም ቆሞ የነበረ መሆኑ አስፈላጊ አይደለም፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ጀመረ››
ከዐለት የተፈለፈለው መቃብር በጣም ዝቅ ያለ ስለ ነበር ውስጡ ያለውን ለማየት ጴጥሮስ ዝቅ ማለት ነበረበት፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ከወገቡ ጐንበስ ብሎ››
‹‹በፍታው ብቻ›› ይህ የሚያመለክተው ሉቃስ 23፥53 ላይ ሲቀበር ኢየሱስ ላይ ተጠቅልሎ የነበረውን ጨርቅ ነው፡፡ የኢየሱስ ሥጋ እዚያ አለመኖሩን ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ኢየሱስ ተጠቅልሎበት የነበረው ጨረቅ፣ ኢየሱስ ግን እዚያ አልነበረም››
‹‹ወደ ቤቱ ተመለሰ››
ሁለት ደቀ መዛሙርት በኤማሁስ መንገድ ላይ ናቸው፡፡
ጸሐፊው ይህን ቃል የተጠቀመው አዲስ ሁኔታ መጀመሩን ለማመልከት ነው፡፡
‹‹ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱ››
‹‹በዚያው ዕለት›› ይህ የሚያመለክተው ሴቶች መቃብሩ ባዶ ሆኖ ያገኙበትን ቀን ነው፡፡
ይህ የከተማ ስም ነው፡፡
‹‹ዐሥራ አንድ ኪሎ ሜትር›› አንድ፣ ‹‹ስታዲያ›› 185 ሜትር ነው፡፡
ይህ ሐረግ እዚህ ጥቅም ላይ የዋለው ድርጊቱ የተጀመረበትን ለማመልከት ነው፡፡ የጀመረው ኢየሱስ ወደ እነርሱ የቀረበ ጊዜ ነበር፡፡ ቋንቋህ ይህን የሚያደርግበት መንገድ ካለው እዚህ ተጠቀምበት፡፡
‹‹ራሱ›› የሚለው ቃል ለእነርሱ የተገለጠው፣ ስለ እርሱ እየተናገሩ የነበረው ኢየሱስ እንደ ነበር አጽንዖት ይሰጣል፡፡ እስከዚህ ጊዜ ድረስ ሴቶቹ መላእክቱን ቢያዩም ኢየሱስ ያየ ሰው አልነበረም፡፡
‹‹እንዳያውቁት ዐይናቸው ተጋርዶ ነበር›› የሰዎቹ ኢየሱስን የማወቅ ችሎታ እንደ መጋረጃ ተጋርዶ እንደ ነበር ተነግሯል፡፡ ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ ኢየሱስን እንዳያውቁ ዐይናቸውን የያዘው እግዚአብሔር እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እርሱን እንዳያውቁት አንዳች ነገር ሆኖ ነበር›› ወይም፣ ‹‹እግዚአብሔር እንዳያውቁት አድርጓቸው ነበር››
‹‹ለሁለቱ ሰዎች ኢየሱስ አላቸው››
ይህ የሰው ስም ነው፡፡
ቀለዮጳ ይህን ጥያቄ ያቀረበው ይህ ሰው በኢየሩሳሌም የተደረገውን ባለማወቁ መገረሙን ለመግለጽ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አንተ ብቻ መሆን አለብህ… በቀኖች››
ሁለቱ ሰዎች ለኢየሱስ መናገር ቀጥለዋል፡፡
ሮማውያን አይሁድን ይገዙ ነገር፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ከጠላቶቻችን ከሮማውያን እስራኤልን ነጻ የሚያደርግ››
ይህ ለምን እስራኤልን ነጻ ያደርጋል ብለው እንደማያምኑ ተጨማሪ ምክንያት ያቀርባል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ያ የሚቻል አይመስልም ምክንያቱም››
ሁለቱ ሰዎች ለኢየሱስ መናገር አብቅተዋል፡፡
ይህ ኢየሱስን በተመለከተ የሆኑ ነገሮችን ሰዎቹ መረዳት ላለመቻላቸው ሌላ ምክንያት ያቀርባል፡፡
‹‹የእኛ ወገን የሆኑ››
በመቃብሩ የነበሩት ሴቶች ናቸው
‹‹በራእይ መላእክት››
ኢየሱስ ለሁለቱ ደቀ መዛሙርት እየተናገረ ነው፡፡
‹‹ልብ›› የሰውን አእምሮ ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አእምሮአችሁ ለማመን የዘገዬ›› ወይም፣ ‹‹ለማመን የዘገያችሁ››
x
ከሁኔታው ሁለቱ ሰዎች ኢየሱስ ወደ ሌላ ቦታ የሚሄድ መስሏቸው ነበር፡፡ ምናልባትም እነርሱ ወደ መንደር ለመግባት ሲታጠፉ ኢየሱስ መንገዱን ቀጥሎ ይሆናል፡፡ ኢየሱስ በንግግሩ እንዳሳሳታቸው የሚያመለክት ፍንጭ የለም፡፡
ግድ ያሉት ለምን እንደሆነ መግለጽ ያስፈልግ ይሆናል፡፡ ምናልባትም ይህ ሐሳቡን ከመለወጡ በፊት ከእርሱ ጋር ረጅም ጊዜ መነጋገር መፈለጋቸውን የሚያመለክት ግነት ይሆናል፡፡ ‹‹ግድ አሉት›› ጉልበትንም የሚጨምር ቢሆንም፣ በቃላቸው ብቻ አጥብቀው ለመኑት ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ከእነርሱ ጋር እንዲያድር አጥብቀው ለመኑት››
የአይሁድ ቀን የሚያበቃው ፀሐይ ስትጠልቅ ነው
‹‹ኢየሱስ ወደ ቤት ገባ››
‹‹ከሁለቱ ደቀ መዛሙርት ጋር አደረ››
ይህ ሐረግ እዚህ ጥቅም ላይ የዋለው ታሪኩ ውስጥ አስፈላጊ ሁኔታ መጀመሩን ለማመልከት ነው፡፡ ቋንቋህ ይህን የሚያደርግበት መንገድ ካለው እዚህ ተጠቀምበት፡፡
ይህ እርሾ የገባበት እንጀራ ነው፡፡ በአጠቃላይ ምግብን የሚያመለክት አይደለም፡፡
‹‹ስለ እርሱ አመሰገነ›› ወይም፣ ‹‹ስለ እርሱ እግዚአብሔርን አመሰገነ፡፡
‹‹ዐይናቸው›› ማስተዋላቸውን ይወክላል፡፡ ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ከዚያም አስተዋሉ›› ወይም፣ ‹‹ከዚያም ተረዱ››
‹‹ለይተው ዐወቁት›› እነዚህ ደቀ መዛሙርት ከሞቱም በፊት ያወቁት ነበር፡፡
ይህም ማለት በድንገት ከዚያ ጠፋ ማለት ነው፡፡ የማይታይ ሆነ ማለት አይደለም፡፡
በጥያቄ የተጠቀሙት ከኢየሱስ ጋር በተገኙ ጊዜ ምን ያህል ተገርመው እንደ ነበር አጽንዖት ለመስጠት ነው፡፡ ከኢየሱስ ጋር ይነጋገሩ በነበረ ጊዜ የተሰማቸውን ሲገልጡ ውስጣቸው እሳት ይቀጣጠል እንደ ነበር ተናግረዋል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ልባችን ይቃጠል ነበር… ቅዱሳት መጻሕፍት››
ሁለቱ ሰዎች እርስ በርስ ይነጋገሩ ነበር፡፡ ‹‹እኛ›› የሚለው ቃል ሁለትን ያመለክታል፤ ይህን ልዩነት የሚቀበሉ ቋንቋዎችን ያካትታል፡፡
ኢየሱስ መጽሐፍ ወይም ጥቅልል ጽሑፍ አልከፈተም፡፡ ‹‹ከፈተ›› የሚለው የሚያመለክተው የእነርሱን መረዳት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ቅዱሳት መጻሕፍትን ሲገልጥልን›› ወይም፣ ‹‹ቅዱሳት መጻሕፍትን ለማስተዋል ሲያስችለን››
ሁለቱ ሰዎች ስለ ኢየሱስ ለመናገር ኢየሩሳሌም ወደ ነበሩት ዐሥራ አንዱ ደቀ መዛሙርት ሄዱ፡፡
‹‹እነርሱ›› የሚለው ሁለቱን ሰዎች ያመለክታል፡፡
‹‹ብድግ አሉ›› ወይም፣ ቆሙ››
‹‹ዐሥራ አንዱ… ከእነርሱ ጋር የነበሩት ሁለቱን ሰዎች አሉአቸው››
ይህ የኢየሱስን ሐዋርያት ያመለክታል፡፡ ይሁዳ ከእንግዲህ ከእነርሱ ጋር አልተቆጠረም
‹‹ስለዚህ ሁለቱ ሰዎች ነገሩአቸው››
ይህ የሚያመለክተው ወደ ኤማሁስ እየሄዱ በነበረ ጊዜ ኢየሱስ ሲገለጥላቸው የሆነውን ነው፡፡
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ኢየሱስን እንዴት እንዳወቁት››
‹‹ኢየሱስ እንጀራውን ሲቆርስ›› ወይም፣ ‹‹ኢየሱስ እንጀራውን ሲባርክ››
ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ታየ፡፡ ቀደም ሲል ሁለቱ ሰዎች ሥራ አንዱ ወደ ነበሩበት ቤት ሲደርሱ ኢየሱስ ከእነርሱ ጋር አልነበረም፡፡
‹‹ራሱ›› የሚለው ቃል ኢየሱስና ኢየሱስ በተገለጠ ጊዜ የነበረው መገረም ላይ ያተኩራል፡፡ ብዙዎቻቸው ከትንሣኤው በኋላ አላዩትም ነበር፡፡
‹‹በእነርሱ መካከል››
‹‹ሰላም ይሁንላችሁ›› ወይም፣ ‹‹እግዚአብሔር ሰላም ይስጣችሁ›› ‹‹እናንተ›› የሚለው ብዙ ቁጥር ነው፡፡
‹‹ግን›› ጠንካራ ንጽጽር ያመለክታል፡፡ ኢየሱስ በሰላም እንዲሆኑ ነግሮአቸው ነበር፤ እነርሱ ግን በጣም ፈርተዋል፡፡
‹‹ተሸበሩ፤ ፈሩ›› ሁለቱ ሐረጐች ተመሳሳይ ቢሆኑም በአንድነት የቀረቡት ምን ያህል እንደ ፈሩ አጽንዖት ለመስጠት ነው፡፡
‹‹መንፈስ እንዳዩ አሰቡ›› ኢየሱስ በእርግጥ ሕያው መሆኑን ገና አልተረዱም፡፡
እዚህ ላይ የሚያመለክተው የሞተ ሰው መንፈስን ነው፡፡
ኢየሱስ በጥያቄ የተጠቀመው ሊያጽናናቸው ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አትፍሩ››
ኢየሱስ በጥያቄ የተጠቀመው በመጠኑ ሊገሥጻቸው ነው፡፡ እርሱ ሕያው መሆኑን እንዳይጠራጠሩ ኢየሱስ ነገራቸው፡፡ ‹‹ልብ›› የሰውን አእምሮ ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በአእምሮአችሁ አትጠራጠሩ›› ወይም፣ ‹‹መጠራጠራችሁን አቁሙ››
እርሱን በመዳሰስ መንፈስ እንዳይደለ እንዲያረጋግጡ ኢየሱስ ጠየቃቸው፡፡ እነዚህን ሁለት ዐረፍተ ነገሮች ማጣመርና ቅደም ተከተላቸውን መለወጥ ይጠቅም ይሆናል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ዳሰሱኝና ሥጋና አጥንት እንዳለኝ እዩ፣ መንፈስ ግን ያ የለውም››
ይህ አካልን ለማመልከት የተለመደ መንገድ ነው፡፡
እጆቹና እግሮቹ በተሰቀለ ጊዜ የሚስማር ምልክት ስለሚኖራቸው በእርግጥ ኢየሱስ መሆኑን ያረጋግጣሉ፡፡ ይህን የበለጠ ግልጽ ማድረግ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በእጆቹና በእግሮቹ ላይ የነበሩ ቁስሎች››
‹‹በጣም ደስ ብሎአቸው ስለ ነበር በእርግጥ እውነት መሆኑን ገና አላመኑም ነበር››
ኢየሱስ ይህን ያደረገው አካል እንዳለው ለማሳየት ነበር፡፡ መንፈሶች ምግብ አይበሉም፡፡
‹‹በእነርሱ ፊት›› ወይም፣ ‹‹እነርሱ እያዩ››
‹‹በፊት ከእናንተ ጋር እያለሁ››
ይህን በሌላ መልኩ መተርጐም ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እግዚአብሔር የተጻፈውን ሁሉ ይፈጽመዋል… መዝሙሮች›› ወይም፣ ‹‹እግዚአብሔር የተጻፈውን ሁሉ ያደርገዋል… መዝሙሮች እንዲፈጸሙ››
‹‹በሙሴ ሕግ›› ‹‹በነቢያት›› እና፣ ‹‹በመዝሙር መጻሕፍት›› የዕብራይስጡ መጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የተለመዱ ስሞች ናቸው፡፡ ይህን በሌላ መልኩ መግለጽና የተለመዱ መጠሪያዎች መጠቀም ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ሙሴ በሕግ የጻፈው ሁሉ፣ ነቢያት የጻፉት ሁሉ፣ በመዝሙር መጻሕፍት ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ››
‹‹አእምሮአቸውን ከፈተላቸው›› ቅዱሳት መጻሕፍትን መረዳት አስቻላቸው ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ከዚያም ቅዱሳት መጻሕፍትን እንዲረዱ አስቻላቸው››
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ይህ ከብዙ ጊዜ በፊት ሰዎች የጻፉት ነው››
በዚህ ቁጥር፣ ‹‹መነሣት›› እንደ ገና ሕያው መሆን ማለት ነው፡፡ ‹‹ከሙታን›› የሚለው ከምድር በታች ያሉ የሞቱ ሰዎችን ሁሉ ያመለክታል፡፡
አይሁድ ማንኛውንም የቀን ክፍል እንደ ቀን ይቆጥራሉ፡፡ ስለዚህም የተቀበረበትንና የሰንበትን ቀን ቀድሞ በመምጣቱ ኢየሱስ የሞተበት ቀን፣ ‹‹ሦስተኛ ቀን›› ተብሏል፡፡ ሉቃስ 24፥7 ላይ ይህን እንዴት እንደ ተረጐምህ ተመልከት፡፡
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹የክርስቶስ ተከታዮች ንስሐ መግባትና ለኃጢአታቸው በኢየሱስ ስም የእግዚአብሔር ይቅርታ እንደሚያስፈልጋቸው በየአገሩ ላሉ ሕዝብ ሁሉ መስበክ አለባቸው››
‹‹ስሙ›› የእርሱን ሥልጣን ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በክርስቶስ ሥልጣን››
‹‹ለየአገሩ ሁሉ›› ወይም፣ ‹‹ለሰው ዘር ሁሉ››
‹‹ከኢየሩሳሌም አንሥቶ››
ኢየሱስ ለደቀመዛሙርት መናገር ቀጥሏል፡፡
‹‹ስለ እኔ ያያችሁት እውነት መሆኑን ለሌሎች መናገር አለባችሁ›› ደቀመዛሙርት የኢየሱስን ሕይወት፣ ሞትና ትንሣኤ ተመልክተዋል፤ ስለዚህ እርሱ ያደረገውን ለሌሎች መናገር ይችላሉ፡፡
‹‹አባቴ እሰጣችኋለሁ ያለውን እሰጣችኋለሁ›› እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን እንደሚሰጥ ቃል ገብቷል፡፡ ዩዲቢ ይህን የበለጠ ግልጽ ያደርገዋል፡፡
ይህ አስፈላጊ የእግዚአብሔር መጠሪያ ነው፡፡
ሰው ልብስ እንደሚለብስ የእግዚአብሔር ኀይል ይሸፍናቸዋል፡፡ ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ኀይል ትቀበላላችሁ››
‹‹ከሰማይ›› ወይም፣ ‹‹ከእግዚአብሔር››
‹‹ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ከከተማ ውጪ ወሰዳቸው››
ይህ ካህናት ሕዝብን ሲባርኩ የሚያደርጉ ነው፡፡
‹‹እንዲህ ተደረገ›› ይህ ታሪኩ ውስጥ አዲስ ሁኔታ ያስተዋውቃል፡፡
‹‹እግዚአብሔር ለእነርሱ መልካም እንዲያደርግ እየጠየቀ ሳለ››
x
እነዚህ ቁጥሮች ታሪኩ ፍጻሜ ላይ ደቀ መዛሙርቱ ያደረጉትን ቀጣይ ድርጊት ይነግሩናል፡፡
‹‹ደቀ መዛሙርቱ ለኢየሱስ ሰገዱ››
‹‹ከዚያም ተመለሱ››
ይህ ሁልጊዜ ወደ ቤተ መቅደሱ ግቢ ይሄዱ እንደ ነበር ለመግለጽ ግነት ነው፡፡
ወደ ቤተ ቅደስ መግባት የሚፈቀድላቸው ካህናት ብቻ ነበሩ፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ቤተ መቅደሱ ግቢ ውስጥ››
‹‹እግዚአብሔርን አመሰገኑ››
1 በመጀመሪያ ቃል ነበረ፤ ቃልም ከእግዚአብሔር ጋር ነበረ፤ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ፤ 2 ይህም ቃል ከመጀመሪያው ከእግዚአብሔር ጋር ነበር፡፡ 3 ሁሉም ነገር የተሠራው በእርሱ አማካይነት ነው፤ ከተሠሩት ነገሮች ሁሉ ያለ እርሱ የተሠራ አንድም ነገር አልነበረም፡፡ 4 በእርሱ ሕይወት ነበረ፤ያም ሕይወት የሰው ሁሉ ብርሃን ነበር፡፡ 5 ብርሃኑ በጨለማ ይበራል፤ ጨለማም ሊያጠፋው አልቻለም፡፡ 6 ከእግዚአብሔር የተላከ ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበር፡፡ 7 ሁሉም በእርሱ እንዲያምኑ እርሱ ስለ ብርሃን ሊመሰክር መጣ። 8 ስለ ብርሃን ሊመሰክር መጣ እንጂ ዮሐንስ ራሱ ብርሃን አልነበረም፡፡ 9 ወደ ዓለም የሚመጣውና ለሰው ሁሉ ብርሃን ሰጭ የሆነው እውነተኛ ብርሃን እየመጣ ነበር፡፡ 10 እርሱ በዓለም ውስጥ ነበር፤ ዓለሙም የተሠራው በእርሱ ነው፤ ዓለም ግን አላወቀውም፤ 11 የራሱ ወደ ሆኑት መጣ፤ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም፡፡ 12 ለተቀበሉት ሁሉ ግን በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች የመሆንን መብት ሰጣቸው፡፡ 13 እነርሱም ከደምና ከሥጋ ወይም ከሰው ፈቃድ አልተወለዱም፤ ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ፡፡ 14 ቃል ሥጋ ሆነ፤ በመካከላችንም ዐደረ፤ እኛም ጸጋና እውነት የተሞላውን ከአብ ዘንድ ያለውን የአንድያ ልጁን ክብር አየን፡፡ 15 ዮሐንስ ስለ እርሱ መሰከረ፤ ድምፁንም ከፍ አድርጎ፣ «ከእኔ በኋላ የሚመጣው እርሱ ከእኔ ይበልጣል፤ 'ከእኔ በፊት ነበርና' ያልኋችሁ ይህ ነው» ይል ነበር፡፡ 16 ከእርሱ ሙላት ሁላችንም በጸጋ ላይ ጸጋ ተቀበልን፤ 17 ሕግ በሙሴ በኩል ተሰጥቶ ነበር፤ ጸጋና እውነት ግን በኢየሱስ በኩል መጣ፡፡ 18 በየትኛውም ጊዜ እግዚአብሔርን ያየው አንድም ሰው የለም፤ ነገር ግን በአባቱ ዕቅፍ ያለውና እርሱ ራሱ እግዚአብሔር የሆነው አንድያ ልጁ እርሱ እግዚአብሔርን እንዲታወቅ አደረገው፡፡ 19 አይሁድ ከኢየሩሳሌም ካህናትንና ሌዋውያንን ልከው፣ «አንተ ማን ነህ?» ብለው በጠየቁት ጊዜ፣ የዮሐንስ ምስክርነት ይህ ነው፡፡ 20 እርሱ በግልጽ ተናገረ አልካደምም፤ ነገር ግን፣ «እኔ ክርስቶስ አይደለሁም» ብሎ መለሰላቸው። 21 ስለዚህ እነርሱም፣ «ታዲያ ማን ነህ? ኤልያስ ነህን?» ብለው ጠየቁት፤ እርሱ፣ «አይደለሁም» አላቸው። እነርሱ፣ «ነቢዩ ነህን?» አሉት፤ እርሱ፣ «አይደለሁም» አለ፡፡ 22 ከዚያም እነርሱ፣ «ለላኩን መልስ መስጠት እንድንችል፣ አንተ ማን ነህ? ስለ ራስህስ ምን ትላለህ?» አሉት፡፡ 23 እርሱ፣ «ልክ ነቢዩ ኢሳይያስ እንዳለው፡- 'የጌታን መንገድ አስተካክሉ' እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ እኔ ነኝ» አላቸው፡፡ 24 ከፈሪሳውያን የተላኩ ሰዎችም ነበሩ። 25 እነርሱ፣ «ክርስቶስ፣ ኤልያስ ወይም ነቢዩ ካልሆንህ፣ ታዲያ ለምን ታጠምቃለህ?» ብለው ጠየቁት፡፡ 26 ዮሐንስ፣ «እኔ በውሃ አጠምቃለሁ፤ ይሁን እንጂ እናንተ የማታውቁት በመካከላችሁ ቆሟል፤ 27 ከእኔ በኋላ የሚመጣው እርሱ ነው፤ እኔ የጫማውን ማሰሪያ ለመፍታት እንኳ የማልበቃ ነኝ» በማለት መለሰላቸው፤ 28 ይህ ሁሉ የሆንው ዮሐንስ ሲያጠምቅ በነበረበት በዮርዳኖስ ማዶ በምትገኘው በቢታንያ ነበር፡፡ 29 በማግስቱ ዮሐንስ ኢየሱስ ወደ እርሱ ሲመጣ ተመልክቶ እንዲህ አለ፤ «እነሆ፣ የዓለምን ኀጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ ይኸውና! 30 'ከእኔ በኋላ የሚመጣው ከእኔ በፊት ስለ ነበረ ከእኔ ይበልጣል' ብዬ ስለ እርሱ የነገርኋችሁ እርሱ ነው፡፡ 31 እኔ አላወቅሁትም ነበር፤ ነገር ግን እርሱ ለእስራኤል ይገለጥ ዘንድ እኔ በውሃ እያጠመቅሁ መጣሁ፡፡» 32 ዮሐንስ እንዲህ ሲል መሰከረ፤ የእግዚአብሔር መንፈስ ከሰማይ እንደ ርግብ ሲወርድና በእርሱ ላይ ሲያርፍ አየሁ፡፡ 33 እኔ አላወቅሁትም ነበር፤ ነገር ግን በውሃ እንዳጠምቅ የላከኝ እርሱ፣ 'መንፈስ ሲወርድበትና ሲያርፍበት የምታየው፣ በመንፈስ ቅዱስ የሚያጠምቀው እርሱ ነው' አለኝ፡፡ 34 እኔ ይህን አይቻለሁ፤ እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነም መስክሬአለሁ፡፡» 35 ደግሞም በማግስቱ፣ ዮሐንስ ከሁለት ደቀ መዛሙርቱ ጋር ቆሞ ሳለ፣ 36 ኢየሱስን በአጠገባቸው ሲያልፍ አዩት፤ ዮሐንስም፣ «እነሆ፣ የእግዚአብሔር በግ» አለ፡፡ 37 ሁለቱ ደቀ መዛሙርት፣ ዮሐንስ ይህን ሲናገር ሰምተው ኢየሱስን ተከተሉት፤ 38 ከዚያም ኢየሱስ መለስ ብሎ ሲከተሉት አየና፣ «ምን ትፈልጋላችሁ?» አላቸው፡፡ እነርሱ፣ «ረቢ የት ነው የምትኖረው?» አሉት። ረቢ ማለት 'መምህር' ማለት ነው። 39 እርሱ፣ «ኑና እዩ» አላቸው፡፡ ከዚያም እነርሱ መጥተው የሚኖርበትን አዩ፤ በዚያም ቀን ዐብረውት ዋሉ፤ ሰዓቱም ዐሥረኛው ሰዓት ያህል ሆኖ ነበርና፡፡ 40 ዮሐንስ ሲናገር ሰምተው ኢየሱስን ከተከተሉት ከሁለቱ አንዱ የስምዖን ጴጥሮስ ወንድም እንድርያስ ነበረ፡፡ 41 እርሱ በመጀመሪያ የራሱን ወንድም ጴጥሮስን አገኘውና፣ «መሲሑን አግኝተነዋል» አለው። መሲሕ 'ክርስቶስ ማለት ነው'፡፡ 42 ወደ ኢየሱስም አመጣው፡፡ ኢየሱስ ጴጥሮስን ተመለከተውና፣ «አንተ የዮና ልጅ ስምዖን ነህ፤ ኬፋ ትባላለህ» አለው። ኬፋ 'ጴጥሮስ ማለት ነው'፡፡ 43 በማግስቱ፣ ኢየሱስ ወደ ገሊላ ሊሄድ በፈለገ ጊዜ፣ ፊልጶስን አግኝቶ፣ «ተከተለኝ» አለው፡፡ 44 ፊልጶስም ጴጥሮስና እንድርያስ ከሚኖሩበት ከተማ ከቤተ ሳይዳ ነበር፡፡ 45 ፊልጶስ ናትናኤልን አገኘውና፣ «ሙሴ በሕግ፣ ነቢያትም በትንቢት የጻፉለትን የዮሴፍን ልጅ የናዝሬቱን ኢየሱስ አግኝተነዋል» አለው፡፡ 46 ናትናኤል፣ «ከናዝሬት መልካም ነገር ይወጣልን?» አለው፡፡ ፊልጶስም መጥተህ እይ አለው፡፡ 47 ኢየሱስ፣ ናትናኤል ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ ስለ እርሱ፣ «እነሆ፣ ተንኰል የሌለበት እውነተኛ እስራኤላዊ!» አለ። 48 ናትናኤል፣ «እንዴት ታውቀኛለህ?» አለው፡፡ኢየሱስም፣ «ገና ፊልጶስ ሳይጠራህ ከበለስ ዛፍ ሥር ሳለህ አየሁህ» ብሎ መለሰለት፡፡ 49 ናትናኤል፣ «አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ፤ አንተ የእስራኤል ንጉሥ ነህ!» ብሎ መለሰለት፡፡ 50 ኢየሱስ፣ «ከበለስ ዛፍ ሥር ሳለህ አየሁህ ስላልሁህ አመንህን? ገና ከዚህ የሚበልጡ ነገሮችን ታያለህ» ብሎ መለሰለት፡፡ 51 ኢየሱስ፣ «እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ፣ ሰማያት ሲከፈቱ መላእክትም በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ» አለ፡፡
ይህ እግዚአብሔር ሰማያትንና ምድርን ከመፈጠሩ በፊት የነበረውን በጣም የመጀመሪያ ጊዜን ያመለክታል።
ይህ ኢየሱስን ያመለክታል ፡፡ ከተቻለ እንደ “ቃሉ” ይተርጉሙ። በቃሉዎ ውስጥ “ቃል” አንስታይ ከሆነ ፣ “ቃል ተብሎ የተጠራው” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል ፡፡
ይህ ከነቃ ግስ ጋር ሊተረጎም ይችላል። አት: - “እግዚአብሔር ሁሉንም ነገሮች በእርሱ አድርጎ ሠራው” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር / ገባሪ ወይም አንቀፅ)
ይህ ከነቃ ግስ ጋር ሊተረጎም ይችላል። አት: - “እግዚአብሔር ያለ እሱ ምንም ነገር አልሠራም” ወይም “እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር ከሱ ጋር አደረገ” (ይመልከቱ።
እዚህ “ሕይወት” ሁሉም ነገር እንዲኖረን የሚያደርግ ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - “ቃል ተብሎ የተጠራው እርሱ ሁሉ በሕይወት እንዲኖር ያደረገው” (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ ለ “ሕይወት” አጠቃላይ ቃል ይጠቀሙ ፡፡ የበለጠ ዝርዝር መሆን ካለብዎ እንደ “መንፈሳዊ ሕይወት” ይተረጉሙ ፡፡
“ብርሃን” ማለት የእግዚአብሔር መገለጥ ዘይቤ ነው ፡፡ በጨለማ ውስጥ ያለውን ነገር እንደሚገልጥ ብርሃን ስለ እግዚአብሔር እውነቱን ገልጦልን ነበር (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር) ፡፡
ጨለማ ብርሃንን ሊያበራ እንደማይችል ሁሉ ፣ ክፉ ሰዎችም እንደ ብርሃን ያለ እግዚአብሔርን የእግዚአብሔርን እውነት ለመግለጥ አልከለከሉም ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እዚህ “ብርሃን” በኢየሱስ ውስጥ የእግዚአብሔር መገለጥ ምሳሌ ነው ፡፡ አት: - “ኢየሱስ እውነተኛውን የእግዚአብሔር ብርሃን እንዴት እንደ ሆነ አሳይ” (የበለስ_ማይታፎርን ይመልከቱ)
እዚህ “ብርሃን” ኢየሱስን እውነተኛ የእግዚአብሔር መገለጥን የሚወክል ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - "እንደ እውነተኛ ብርሃን" (ይመልከቱ: የበለስ_ማይታፎር)
ምንም እንኳን እርሱ በዚህ ዓለም ውስጥ ቢሆን ፣ እና እግዚአብሔር ሁሉንም ነገሮች በእርሱ አማካይነት የፈጠረው ፣ ሰዎች አሁንም አላወቁም ”
“ዓለም” በዓለም ለሚኖሩት ሁሉ የሚታወቅ ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - “ሕዝቡ በእርግጥ እርሱ ማን እንደሆነ አላወቁም ነበር” (ይመልከቱ ፡፡
የገዛ አገሩ መጣ ፤ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም ”
ይህ ማለት አንድን ሰው መቀበል ማለት ነው ፡፡ አንድ ሰው እንግዳ ሲቀበሉ ይቀበሏቸዋል እናም ከእነሱ ጋር ወዳጅነት ለመመሥረት ተስፋ በማድረግ በክብር ይቀበላቸዋል ፡፡
ይህ ማለት ኢየሱስን እንደ አዳኝ ማመን እና እሱን በሚያከብር መንገድ መኖር ማለት ነው ፡፡
“ስም” የሚለው ቃል ለኢየሱስ ማንነት እና ስለ እርሱ ሁሉም ነገር የሚጠቁም ቃል ነው ፡፡ አት: - “ኢየሱስ”
ሥልጣናቸውን ሰጣቸው ወይም “ለእነሱ አስችሎታል”
“ልጆች” የሚለው ቃል ከእግዚአብሄር ጋር ያለንን ግንኙነት የሚወክል ዘይቤያዊ አነጋገር ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ ኢየሱስን የሚያመለክተው ዘይቤ ነው ፡፡ እግዚአብሔር ምን ዓይነት አምላክ መሆኑን የሚገልጥ እሱ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
የማይገባን በእኛ ላይ ደግነት የተሞላ "
ዮሐንስ እየተናገረ ያለው ስለ ኢየሱስ ነው ፡፡ “ከእኔ በኋላ ይመጣል” የሚለው ሐረግ ማለት የዮሐንስ አገልግሎት ቀድሞውኑ ተጀምሮ የኢየሱስ አገልግሎት በኋላ ይጀምራል ፣ ከዮሐንስ በኋላ ፡፡
ከእኔ ይበልጣል ”ወይም“ ከእኔ ይበልጥ አስፈላጊ ነው ”
እርሱ ከእኔ በፊት ነበረና
ይህ ቃል ማለቂያ የሌለውን የእግዚአብሔርን ጸጋ ያመለክታል ፡፡
"በበረከት በበረከት"
ይህ ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
እዚህ ላይ “አይሁዶች” የሚለው ቃል “የአይሁድ መሪዎችን” ይወክላል ፡፡ አት: - “የአይሁድ መሪዎች ከኢየሩሳሌም ወደ እርሱ ላኩ” (የበለስ_ስኔክዶቼን ይመልከቱ)
ሁለተኛው ሐረግ በአሉታዊ ቃላት ውስጥ የመጀመሪያው ሐረግ የሚናገረው ተመሳሳይ በሆነ አነጋገር ነው ፡፡ ይህ ዮሐንስ እውነቱን እንደሚናገር ያጎላል ፡፡ አት: - "እሱ በነፃነት እውነቱን ነግሯቸዋል" (የበለስ_ፓሎሊዝም እና የበለስ_ቁጥር ችግሮች) ይመልከቱ
አንተ ክርስቶስ አይደለህምን? ታዲያ አንተ ክርስቶስ አይደለህምን? ምን ይሆናል? ምን ታደርጋለህ?
ዮሐንስ ከካህናቱና ከሌዋውያኑ ጋር መነጋገሩን ቀጠለ ፡፡
“ካህናቱና ሌዋውያኑ ዮሐንስን”
ዮሐንስ ሳይሆን ካህናቱ እና ሌዋውያኑ (ተመልከት የበለስ_ቁጥር)
"ዮሐንስ አለ"
ዮሐንስ እየተናገረ ያለው የኢሳይያስ ትንቢት ስለ ራሱ ነው ፡፡ እዚህ “ድምፅ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በምድረ በዳ የሚጮኸውን ሰው ነው ፡፡ አት: - "እኔ በምድረ በዳ የምጮኽ እኔ ነኝ" (የበለስ_አስማሚነት ይመልከቱ)
እዚህ “መንገድ” የሚለው ቃል እንደ ዘይቤ ጥቅም ላይ ውሏል ፡፡ አት: - “አስፈላጊ ለሆነ ሰው የሚጠቀመውን መንገድ እንደሚያዘጋጁ ሰዎች ለጌታ መምጣት ዝግጁ ይሁኑ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ዮሐንስን የጠየቁት ሰዎች ይህ የመነሻ መረጃ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ ዳራ | የጀርባ መረጃ)
ቁጥር 28 ስለታሪኩ መቼት ዳራ ይነግረናል ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
ከሄድኩ በኋላ ይነግራችኋል ”
የባሪያ ወይም የአገልጋይነት ሥራ ‹ጫማውን መፍታት› ሥራው ዘይቤ ነው ፡፡ ዮሐንስ እየተናገረው ያለው ለኢየሱስ የአገልጋይ የሆነውን በጣም መጥፎ ተግባር እንኳን ለማከናወን ብቁ እንዳልሆነ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ የእግዚአብሔርን ፍጹም መስዋት የሚወክል ዘይቤ ነው ፡፡ ኢየሱስ “የእግዚአብሔር በግ” ተብሎ ተጠርቷል ምክንያቱም የሰዎችን ኃጢአት ለመክፈል ስለተሠዋ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
“ዓለም” የሚለው ቃል ዘይቤያዊ አነጋገር ሲሆን በዓለም ያሉ ሰዎችን ሁሉ ያመለክታል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ጥበብ)
በ 1፡14 ውስጥ እንዳደረጉት ይተረጉሙ ፡፡
"መውረድ"
ይህ ሐረግ ምሳሌ ነው። “መንፈስ” ልክ እንደ ርግብ በሰው ላይ እንደሚወርድ ርምጃ ይወርዳል። (ይመልከቱ: የበለስ_ሲሚል)
“ሰማይ” የሚለው ቃል “ሰማዩን” ያመለክታል ፡፡
የዚህ ጽሑፍ አንዳንድ ቅጂዎች “የእግዚአብሔር ልጅ” ይላሉ ፣ ሌሎች “የእግዚአብሔር የተመረጠ” ይላሉ (ይመልከቱ:
ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
ይህ ሌላ ቀን ነው። ዮሐንስ ኢየሱስን ያየው ሁለተኛው ቀን ነው ፡፡
ይህ የእግዚአብሔርን ፍጹም መስዋት የሚወክል ዘይቤ ነው ፡፡ ኢየሱስ “የእግዚአብሔር በግ” ተብሎ ተጠርቷል ምክንያቱም የሰዎችን ኃጢአት ለመክፈል ስለተሠዋ ነው ፡፡ በ 1 29 ውስጥ ይህንን ተመሳሳይ ሐረግ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
"ሰዓት 10" ይህ ሐረግ ከሰዓት በፊት ፣ ጨለማ ከመጀመሩ በፊት ፣ ወደ ሌላ ከተማ ምናልባትም 10 ሰዓት አካባቢ ለመጓዝ ዘግይቶ የሚዘገይ ጊዜን ያመለክታል ፡፡
እነዚህ ቁጥሮች ስለ እንድርያስ እና ወንድሙን ጴጥሮስን ወደ ኢየሱስ እንዳመጣ መረጃ ይሰጡናል ፡፡ ይህ የሆነው በ 1 37 ውስጥ ኢየሱስ የት እንደሚቀመጥ ለማየት ከመሄዱ በፊት ነበር ፡፡
ይህ መጥምቁ ዮሐንስ አይደለም። “ዮሐንስ” በጣም የተለመደ ስም ነበር ፡፡
ይህ ስለ ፊል ፊሊጶስ የዳራ መረጃ ነው። (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
"ናትናኤል ፊልጶስን“
ይህ ማስታወሻ አፅን .ትን ለመጨመር በጥያቄ መልክ ይታያል። አት: - “ምንም ጥሩ ነገር ከናዝሬት ሊወጣ አይችልም!” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር | አጻጻፍ ጥያቄ)
ይህ በአዎንታዊ መንገድ ሊገለጽ ይችላል ፡፡ አት: - “ሙሉ በሙሉ እውነተኛው ሰው” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር | ጥቅስ)
ናታኒኤል ኢየሱስ ከዚህ በፊት ሳያውቀው ሳያውቅ ኢየሱስ “የእግዚአብሔር ልጅ” ነው ብሏል ፡፡
ይህ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
ይህ ማስታወሻ አፅን .ት ለመስጠት በጥያቄ መልክ መልክ ይታያል። 'ከበለሱ በታች አየሁህ በማየህ አምናለሁ!
የሚከተለው የሚከተለው አስፈላጊ እና እውነት መሆኑን በቋንቋዎ አፅንዎት በመስጠት ይህንን ይተረጉሙ ፡፡
1 በሦስተኛውም ቀን በገሊላ ቃና ሰርግ ነበረ፤ የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች። 2 ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱም ወደ ሰርጉ ተጠርተው ነበር፡፡ 3 የወይን ጠጁ ባለቀ ጊዜ፣ የኢየሱስ እናት ኢየሱስን፣ «የወይን ጠጅ እኮ ዐልቆባቸዋል» አለችው፡፡ 4 ኢየሱስ መልሶ፣ «አንቺ ሴት፣ ከዚህ ጋር እኔ ምን ጉዳይ አለኝ? ጊዜዬ እኮ ገና አልደረሰም» አላት፡፡ 5 እናቱ ለአሳላፊዎቹ፣ እርሱ «የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ» አለቻቸው፡፡ 6 በዚያ፣ ለአይሁድ የመንጻት ሥርዐት የሚያገለግሉ እያንዳንዳቸው ሁለት ወይም ሦስት እንስራ የሚይዙ ስድስት የድንጋይ ጋኖች ነበሩ፡፡ 7 ኢየሱስ፣ «ጋኖቹን ውሃ ሙሉአቸው» አላቸው፡፡ እነርሱም እስከ አፋቸው ሞሉአቸው፡፡ 8 ከዚያም ኢየሱስ አሳላፊዎቹን፣ «ጥቂት ቅዱና ለመስተንግዶው ኀላፊ ስጡት» አላቸው፤ እነርሱም እንዳላቸው አደረጉ፡፡ 9 የመስተንግዶው ኀላፊ፣ ወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ ቀመሰው፤ ከየት እንደ መጣ ግን አላወቀም፤ ውሃውን የቀዱት አሳላፊዎች ግን ያውቁ ነበር፡፡ እርሱም ሙሽራውን ጠርቶ 10 «ሰው ሁሉ መልካሙን ወይን ጠጅ በመጀመሪያ ያቀርባል፤ መናኛውን ሰዎች ከሰከሩ በኋላ ነው የሚያቀርበው፤ አንተ ግን መልካሙን የወይን ጠጅ እስካሁን ድረስ አቈይተሃል» አለው፡፡ 11 ይህ በገሊላ ቃና የተደረገው ተአምር ኢየሱስ ካደረጋቸው ተአምራዊ ምልክቶች የመጀመሪያ ነው፤ ክብሩንም ገለጠ፤ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ። 12 ከዚህ በኋላ ከእናቱ፣ ከወንድሞቹና ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ቅፍርናሆም ወረደ፤ በዚያም ጥቂት ቀናት ቈዩ፡፡ 13 የአይሁድ ፋሲካ ቀርቦ ስለ ነበረ፣ ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ፡፡ 14 በቤተ መቅደስ ውስጥ በሬዎችን፣ በጎችንና ርግቦችን ሲሸጡ የነበሩ ሰዎችን አገኘ፡፡ ገንዘብ ለዋጮችም ደግሞ በዚያ ተቀምጠው ነበር፡፡ 15 እርሱም የገመድ ጅራፍ አበጅቶ በጎችንና ከብቶችን ጭምር ሁሉንም ከቤተ መቅደስ አስወጣቸው፤ የገንዘብ ለዋጮችንም ገንዘብ በተነ፤ ጠረጴዛዎቻቸውንም ገለባበጠ። 16 ርግብ ሻጮችንም፣ «እነዚህን ከዚህ አስወጧቸው፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት ማድረጋችሁን አቁሙ!» አላቸው። 17 ደቀ መዛሙርቱ፣ «ለቤትህ ያለኝ ቅናት ይበላኛል» ተብሎ የተጻፈውን አስታወሱ፡፡ 18 ከዚያም የአይሁድ ባለ ሥልጣኖች፣ «እነዚህን ነገሮች ለማድረግ መብት እንዳለህ ምን ምልክት ታሳየናለህ?» በማለት መለሱለት፡፡ 19 ኢየሱስ፣ «ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፤ እኔ በሦስት ቀን አስነሣዋለሁ» ብሎ መለሰ፡፡ 20 ከዚያም አይሁድ፣ «ይህን ቤተ መቅደስ ለመገንባት ዐርባ ስድስት ዓመት ፈጅቶአል፤ አንተ በሦስት ቀን መልሰህ ታስነሣዋለህ?» አሉት። 21 ይሁን እንጂ፣ እርሱ ቤተ መቅደስ ብሎ የተናገረው፣ ስለ ራሱ ሰውነት ነበር። 22 ከሙታን ከተነሣም በኋላ፣ ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስ ይህን እንደ ተናገረ አስታወሱ፤ መጻሕፍትንና ኢየሱስ የተናገረውንም ቃል አመኑ። 23 በፋሲካ በዓል በኢየሩሳሌም ሳለ፣ ያደረጋቸውን ተአምራት አይተው ብዙዎች በስሙ አመኑ። 24 ሆኖም፣ ኢየሱስ ሰዎችን ሁሉ ያውቅ ስለ ነበር፣ እነርሱን አላመናቸውም፤ 25 ደግሞም በሰው ውስጥ ያለውን ያውቅ ስለ ነበር፣ ማንም ስለ ሰው እንዲመሰክርለት አያስፈልገውም ነበር።
ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱ ወደ ሠርግ ተጋብዘዋል ፡፡ እነዚህ ቁጥሮች ስለ ታሪኩ መቼት መነሻ (ዳራ) ይሰጣሉ ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
ብዙ ተርጓሚዎች ይህንን ፊልሙን የሚያነቡት ኢየሱስ ፊል Philipስን እና ናትናኤልን እንዲከተሉት ከጠራ በሦስተኛው ቀን ነው ፡፡ የመጀመሪያው ቀን በዮሐንስ 1 35 ውስጥ እና ሁለተኛው በዮሐንስ 1፡43 ውስጥ ይገኛል ፡፡
ይህ በገባ ቅርጸት ሊገለጽ ይችላል ፡፡ አት: - “አንድ ሰው ኢየሱስንና ደቀ መዛሙርቱን ወደ ሠርጉ ጋብዛቸው” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ይህ ማርያምን ያመለክታል ፡፡ አንድ ልጅ እናቱን በ “ቋንቋዎ” እናቱን “ሴት” ብሎ መጥራቱ ተገቢ ያልሆነ ከሆነ ፣ ጨዋ የሆነ ሌላ ቃል ይጠቀሙ ፣ ወይም ይተውት።
ይህ ጥያቄ አፅን toት እንዲሰጥ ተጠየቀ ፡፡ አት: - “ይህ ከእኔ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም” ወይም “ምን ማድረግ እንዳለብኝ መንገር የለብዎትም” ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
“ጊዜ” የሚለው ቃል ተዓምራትን በመፈፀም እርሱ መሲህ መሆኑን ለማሳየት ለኢየሱስ ትክክለኛ ጊዜ የሚወክል ቃል ነው ፡፡ አት: - “አንድ ትልቅ ነገር የማደርግበት ጊዜ ገና አይደለም”
"ከ 80 እስከ 120 ሊ." “ሜትሬት” 40 ሊትር ያህል ፈሳሽ ነበር። (ይመልከቱ: መተርጎም_ብላumeም)
ይህ ማለት "ወደ ላይኛው ጫፍ" ወይም "ሙሉ በሙሉ" ማለት ነው ፡፡
ይህ ለምግብ እና ለመጠጣት ኃላፊ የሆነውን ሰው ያመለክታል ፡፡
ይህ የዳራ መረጃ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
ከመጠን በላይ አልኮል በመጠጣት ምክንያት ርካሽ በሆነ ወይን ጠጅ እና ውድ በሆነ ወይን መካከል ያለውን ልዩነት መናገር አለመቻል
ይህ ቁጥር የዋናው የታሪክ መስመር አካል አይደለም ፣ ይልቁንም ስለ ታሪኩ አስተያየት ይሰጣል ፡፡ (ይመልከቱ: ጽሑፍ_አዳዲስ | የአዲስ ክስተት መግቢያ)
ይህ የቦታ ስም ነው
እዚህ “ክብር” የኢየሱስን ታላቅ ኃይል ያመለክታል ፡፡ አት: - "ኃይሉን አሳይቷል"
ይህ ማለት ከከፍተኛ ቦታ ወደ ዝቅተኛ ቦታ ተጓዙ ማለት ነው ፡፡ ካና ከ ቅፍርናሆም በስተደቡብ ምዕራብ እና ከፍታ ላይ ነው ፡፡
“ወንድሞች” የሚለው ቃል ወንድሞችንና እህቶችን ያጠቃልላል ፡፡ ሁሉም የኢየሱስ ወንድሞችና እህቶች ከእርሱ በዕድሜ ያነሱ ነበር።
ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ ወደ ቤተ መቅደስ ወደ ኢየሩሳሌም ወጡ።
ይህ ማለት ከዝቅተኛ ቦታ ወደ ከፍተኛ ቦታ ተጓዙ ማለት ነው ፡፡ ኢየሩሳሌም የተገነባው በአንድ ኮረብታ ላይ ነው።
የሚቀጥለው ቁጥር እነዚህ ሰዎች በቤተመቅደሱ ግቢ ውስጥ እንደነበሩ ግልፅ ያደርግልናል ፡፡ አካባቢው ለአምልኮ እንጂ ለንግድ አይደለም ፡፡
ሰዎች በቤተ መቅደሱ አደባባይ ውስጥ እንስሳትን እየገዙ ለእግዚአብሔር መስዋእት ያደርጉ ነበር ፡፡
የአይሁድ ባለሥልጣናት ገንዘባቸውን ከ “ገንዘብ ለዋጮች” ልዩ ገንዘብ እንዲለውጡ እንስሳትን ለመሥዋዕት ለመግዛት የሚፈልጉ ሰዎችን ይጠይቁ ነበር ፡፡
ይህ ቃል በመጀመሪያ በተከናወነው ሌላ ነገር ምክንያት የተከሰተ ክስተትን ያመለክታል ፡፡ በዚህ ጊዜ ፣ ኢየሱስ ገንዘብ ለዋጮችን በቤተ መቅደስ ውስጥ ሲቀመጥ አየ ፡፡
በአባቴ ቤት ውስጥ ነገሮችን መግዛት እና መሸጥ አቁም ”
ይህ ኢየሱስ ቤተ መቅደሱን ለማመልከት የተጠቀመበት ሐረግ ነው ፡፡
ይህ ኢየሱስ ለእግዚአብሔር የሚጠቀም አንድ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
ይህ በገባ ቅርጸት ሊገለጽ ይችላል ፡፡ አት: - "አንድ ሰው ጽ writtenል" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ ቃል የሚያመለክተው ቤተ መቅደሱን የእግዚአብሔርን ቤት ነው ፡፡
“ይበላል” የሚለው ቃል “እሳት” የሚለውን ዘይቤ ያመለክታል ፡፡ ኢየሱስ ለቤተ መቅደሱ ያለው ፍቅር በውስጣቸው እንደሚቃጠል እሳት ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ አንድ ነገር እውነት መሆኑን የሚያረጋግጥ ክስተት የሚያመለክት ነው።
ይህ ኢየሱስ በቤተ መቅደስ ገንዘብ ለዋጮች ላይ ያደረጋቸውን ድርጊቶች ይመለከታል ፡፡
ኢየሱስ የገዛ አካሉን ከሦስት ቀናት በኋላ እንደሚሞትና እንደሚነሳ መቅደስ ነው ፡፡ ይህንን ማፍረስ እና ህንፃን መገንባትን በሚገልፅ መንገድ ይተርጉሙ። ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ ትክክለኛውን የቤተ መቅደስ ግንባታ እንዲያፈርሱ እያዘዛቸው አይደለም። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ ማለት “እንደገና መገንባት” ወይም “መመለስ” ማለት ነው ፡፡
ቁጥር 21 እና 22 የዋናው የታሪክ መስመር አካል አይደሉም ፣ ይልቁንም በታሪኩ ላይ አስተያየት ሰጡ እና በኋላ ስለሚሆነው ነገር ይናገራሉ ፡፡ (ይመልከቱ: Writ_endofstory)
ለአርባ ስድስት ዓመታት ... ሶስት ቀናት - "46 ዓመት ... 3 ቀናት" (ይመልከቱ: በትርጉም_ቁጥር)
የአይሁድ ባለሥልጣናት ኢየሱስ ቤተ መቅደሱን አፍርሶ በሦስት ቀናት ውስጥ እንደገና ለመገንባት እንደሚፈልግ ለማሳየት የአይሁድ ባለሥልጣናት የተገነዘቡ መሆናቸውን ለማስረዳት ይህ አስተያየት በጥያቄ መልክ ይታያል ፡፡ አት: - "በሦስት ቀናት ውስጥ እንደገና መገንባት አይችሉም!" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እዚህ “ማመን” ማለት አንድን ነገር መቀበል ወይም እውነት መሆኑን ማመን ነው ፡፡
ይህ በ 2 17 ውስጥ ያለውን የኢየሱስን አባባል ይመለሳል ፡፡
"አሁን" የሚለው ቃል በታሪኩ ውስጥ ወደ አንድ አዲስ ክስተት ያስተዋወቀን ፡፡
እዚህ “ስም” የኢየሱስን ማንነት የሚወክል ስም ነው ፡፡ አት: - “በእሱ አመኑ” ወይም “በእርሱ አመኑ” (ዩዲቢ) ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ጥበብ)
ተአምራት “ምልክቶች” ሊባሉም ይችላሉ ምክንያቱም እግዚአብሔር በአጽናፈ ዓለሙ ላይ ሙሉ ስልጣን ያለው ሁሉን ቻይ መሆኑን ለማሳየት እንደ ማስረጃ ተደርገው ይወሰዳሉ ፡፡
1 ከፈሪሳውያን ወገን የሆነ፣ ስሙ ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ የአይሁድ ሸንጎ አባል ነበር ፤ 2 ይህ ሰው በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ፣ «መምህር ሆይ፣ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ክሆነ ሰው በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህን ምልክቶች ማንም ማድረግ ስለማይችል፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ የመጣህ መምህር መሆንህን እናውቃለን» አለው። 3 ኢየሱስ፣ «እውነት እልሃለሁ፣ ሰው ዳግም ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም» ብሎ መለሰለት። 4 ኒቆዲሞስ፣ «ሰው ካረጀ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ወደ እናቱ ማኅፀን ዳግመኛ ገብቶ ሊወለድ ይችላልን?» አለው። 5 ኢየሱስ መልሶ፣ «እውነት፣ እውነት፣ እልሃለሁ፣ ሰው ከውሃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም። 6 ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፤ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው። 7 'ዳግም መወለድ አለባችሁ' ስላልሁህ አትደነቅ፤ 8 ነፋስ ወደ ፈለገው ይነፍሳል፤ ድምፁን ትሰማለህ፣ ነገር ግን ከየት እንደ መጣ፣ ወዴትም እንደሚሄድ አታውቅም፤ ከመንፈስም የተወለደ ሁሉ እንደዚሁ ነው።» 9 ኒቆዲሞስ፣ «ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል?» በማለት መለሰ። 10 ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፤ «አንተ የእስራኤል መምህር ሆነህ ሳለ እነዚህን ነገሮች አታውቅምን? 11 እውነት፣ እውነት፣ እልሃለሁ፤ የምናውቀውን እንናገራለን፤ ያየነውንም እንመሰክራለን፤ እናንተ ግን ምስክርነታችንን አትቀበሉም። 12 ስለ ምድራዊው ነገር ነግሬአችሁ ያላመናችሁ፣ ስለ ሰማያዊው ነገር ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ? 13 ከሰማይ ከወረደው ከሰው ልጅ በቀር፣ ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም። 14 ሙሴ እባብን በምድረ በዳ እንደ ሰቀለ፣ እንዲሁ የሰው ልጅ ሊሰቀል ይገባዋል። 15 ይህም በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው ነው። 16 በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስከ መስጠት ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና፤ 17 እግዚአብሔር ልጁን ወደ ዓለም የላከው በዓለም ላይ ለመፍረድ ሳይሆን፣ ዓለምን በእርሱ ለማዳን ነው። 18 በእርሱ የሚያምን ሁሉ አይፈረድበትም፤ በእርሱ የማያምን ግን በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ፣ አሁኑኑ ተፈርዶበታል። 19 የፍርዱ ምክንያት ይህ ነው፤ ብርሃን ወደ ዓለም መጣ፤ ሰዎች ግን ሥራቸው ክፉ ስለ ነበረ፣ ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ወደዱ፤ 20 ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላል፤ ድርጊቱም እንዳይገለጥበት ወደ ብርሃን አይመጣም። 21 እውነትን በተግባር ላይ የሚያውል ሰው ግን ሥራው እግዚአብሔርን በመታዘዝ የተፈጸመ መሆኑ በግልጽ እንዲታይ ወደ ብርሃን ይመጣል።» 22 ከዚህ በኋላ ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ ወደ ይሁዳ አገር ሄዱ፤ በዚያ ከእነርሱ ጋር ቆየ፤ ያጠምቅም ነበር፤ 23 በዚህ ጊዜ ዮሐንስም በሳሌም አቅራቢያ ሄኖን በተባለ ስፍራ ብዙ ውሃ ስለ ነበረ፣ ያጠምቅ ነበር፤ ሰዎችም ወደ እርሱ እየመጡ ይጠመቁ ነበር። 24 ምክንያቱም ዮሐንስ ገና በወኅኒ አልተጣለም ነበር። 25 ከዚያም በዮሐንስ ደቀ መዛሙርትና በአንድ አይሁዳዊ መካከል ስለ መንጻት ሥርዐት ክርክር ተነሣ። 26 ደቀ መዛሙርቱ ወደ ዮሐንስም መጥተው፣ «መምህር ሆይ፣ በዮርዳኖስ ማዶ ከአንተ ጋር የነበረው ስለ እርሱ የመሰከርክለት ሰው፣ እነሆ እያጠመቀ ነው፤ ሁሉም ወደ እርሱ እየሄዱ ነው አሉት።» 27 ዮሐንስ መልሶ እንዲህ አለ፤ «ሰው ከሰማይ ካልተሰጠው በቀር ምንም ነገር ሊቀበል አይችልም። 28 'እኔ ክርስቶስ አይደለሁም' ነገር ግን 'ከእርሱ በፊት ተልኬአለሁ' ማለቴን እናንተ ራሳችሁ ትመሰክራላችሁ። 29 ሙሽሪት ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው፤ አጅቦት ቆሞ የሚሰማው ሚዜው በሙሽራው ድምፅ እጅግ ደስ ይለዋል። አሁን ይህ ደስታዬ ፍጹም ሆኖእል። 30 እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ይገባል። 31 ከላይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው፤ ከምድር የሆነው የምድር ነው የምድሩንም ይናገራል። ከሰማይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው። 32 እርሱ ያየውንና የሰማውን ይመሰክራል፤ ነገር ግን ምስክርነቱን ማንም አይቀበልም። 33 ምስክርነቱን የተቀበለ ሰው የእግዚአብሔርን እውነተኝነት አረጋግጧል። 34 እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል፤ እግዚአብሔር መንፈሱን ሰፍሮ አይሰጥምና። 35 አብ ወልድን ይወዳል ሁሉንም ነገር በእጁ ሰጥቶታል። 36 በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ ለልጁ የማይታዘዝ ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በላዩ ይሆናል እንጂ ሕይወትን አያይም።»
ኒቆዲሞስ ኢየሱስን ለማየት መጣ ፡፡
ይህ ቃል የታሪኩን አዲስ ክፍል ለማመልከት እና ኒቆዲሞስን ለማስተዋወቅ እዚህ ጥቅም ላይ ውሏል ፡፡ (ይመልከቱ: መጻፍ_ድርድር)
እዚህ እኛ “እኛ” ብቸኛ ነው ፣ የሚያመለክተው ኒቆዲሞስን እና የአይሁድ ምክር ቤት አባላት ብቻ ነው ፡፡
ኢየሱስ እና ኒቆዲሞስ መናገራቸውን ቀጠሉ ፡፡
በ 1፡48 እንደተረጎማችሁት ተርጉሙት
“ከላይ የተወለደው” ወይም “ከእግዚአብሔር የተወለደ”
“መንግሥት” የሚለው ቃል ለእግዚአብሔር አገዛዝ ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር የሚገዛበት ቦታ” (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
ኒቆዲሞስ ይህ ሊሆን እንደማይችል ጎላ አድርጎ ለመግለጽ ይህንን ጥያቄ ተጠቅሟል ፡፡ አት: - “ሰው በእርግጥ ከሸመገለ በኋላ እንደገና ሊወለድ አይችልም!” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ኒቆዲሞስ ይህንን ጥያቄ ሁለተኛ ልደት የማይቻል ነው የሚለውን እምነት ለማጉላት ተጠቅሞበታል ፡፡ በርግጥ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ እናቱ ማህፀን ውስጥ መግባት አይችልም! (የበለስ.
"እንደገና" ወይም "ሁለት ጊዜ"
ሕፃን ሲያድግ የሴቶች አካል
በ 3 3 ውስጥ እንዳደረጉት በተመሳሳይ መንገድ መተርጎም ይችላሉ ፡፡
ሁለት ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች አሉ-1) “በውሃ እና በመንፈስ ተጠመቁ” ወይም 2) “በአካል እና በመንፈሳዊ የተወለዱ” (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
“መንግሥት” የሚለው ቃል በአንድ ሰው ሕይወት ውስጥ ለእግዚአብሔር አገዛዝ ምሳሌ ነው ፡፡ አት: - “በሕይወቱ ውስጥ የእግዚአብሔርን አገዛዝ ሊያይ አይችልም” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ኢየሱስ ለኒቆዲሞስ መናገሩን ቀጠለ ፡፡
“መወለድ አለብዎት”
በምንጭ ቋንቋው ውስጥ ነፋስና መንፈስ አንድ ዓይነት ቃል ናቸው ፡፡ እዚህ ያለው ተናጋሪ ነፋሱን እንደ ሰው አድርጎ ይመለከታል ፡፡ አት: - “መንፈስ ቅዱስ በፈለገው ቦታ እንደሚነፍስ ነፋስ ነው” (ይመልከቱ ፡፡
ይህ ጥያቄ በመግለጫው ላይ አፅን addsት ይሰጣል ፡፡ AT: "ይህ ሊሆን አይችልም!" ወይም ይህ ሊከሰት አልቻለም! (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ ጥያቄ በመግለጫው ላይ አፅን addsት ይሰጣል ፡፡ አት: - አንተ የእስራኤል መምህር ነህ ፣ ስለዚህ እነዚህን ነገሮች አለመረዳታቸውን ተገርሜያለሁ! " (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
በ 1 48 ውስጥ እንዳደረገው ይህንን ይተረጉሙ ፡፡
ኢየሱስ “እኛ” ሲል ኒቆዲሞስንም አላካተተም ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ኢየሱስ ለኒቆዲሞስ ምላሽ መስጠቱን ቀጠለ ፡፡
ይህ ጥያቄ የኒቆዲሞስን ክህደት ያጎላል ፡፡ አት: - “ስለ ሰማያዊ ነገሮች ብነግራችሁ በእርግጥ አታምኑም!” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
በሁለቱም ቦታዎች "እናንተ" ነጠላ አመልካች ነው
መንፈሳዊ ነገሮች
ይህ ማለት እግዚአብሔር የሚኖርበት ቦታ ማለት ነው
ይህ የምስል አነጋገር ምሳሌ (ምሳሌ) ይባላል። ሙሴ በምድረ በዳ የነሐሱን እባብ እንደ “እንዳነሳ” አንዳንድ ሰዎች ኢየሱስን “ከፍ ከፍ” ያደርጉታል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ሲሚል)
ዓለም በልጁ እንዲድን ነው እንጂ ፣ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አልላከውምና ማውገዝ
ይህ ዓይነቱ ፍቅር ከእግዚአብሔር የሚመጣ እና ለሌሎች መልካም ላይ ያተኮረ ፍቅር ነው ፣ ምንም እንኳን በራሱ የማይጠቅም ቢሆንም። እግዚአብሔር ራሱ ፍቅር እና የእውነተኛ ፍቅር ምንጭ ነው ፡፡
እነዚህ ሁለት ሐረጎች ማለት አንድ ዓይነት ማለት ናቸው ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአጽን saidት የተሰጠው ፣ በመጀመሪያ በአሉታዊ እና ከዚያም በአዎንታዊ ነው ፡፡ አንዳንድ ቋንቋዎች ትኩረትን በተለየ መንገድ ሊያመለክቱ ይችላሉ። AT: - እግዚአብሔር ልጁን ወደ ዓለም የላከው እውነተኛው ምክንያት እሱን ለማዳን ነበር (ይመልከቱ። የበለስ ምሳሌዎች እና በለስ
"መቅጣት"
የ"ነጻ" ብይን
ይህ አስፈላጊ የኢየሱስ ርዕስ ነው
ኢየሱስ ለኒቆዲሞስ ምላሽ መስጠቱን ጨረሰ
“ብርሃን” የሚለው ቃል በኢየሱስ ውስጥ ለተገለጠው የእግዚአብሔር እውነት ዘይቤ ነው ፡፡ “ዓለም” “በዓለም” ውስጥ ለሚኖሩት ሰዎች ሁሉ ተመሳሳይ ቃል ነው ፡፡ አት: - እንደ ብርሃን ያለ ሰው የእግዚአብሔርን እውነት ለሕዝቡ ገለጠ "(ይመልከቱ።
እዚህ “ጨለማ” በክርስቶስ ውስጥ የእግዚአብሔር መገለጥ “ብርሃን” ያልተቀበለ አካባቢ ለዚህ ምሳሌ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: በለስ
ይህ በገባ ቅርጸት ሊገለጽ ይችላል ፡፡ አት: - "ብርሃኑ እርሱ የሚያደርገውን ነገር እንዳያሳይ" ወይም ብርሃን ስራውን እንዳያበራ "(ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር / ገባሪ ወይም ህይዎት)
ይህ በገባ ቅርጸት ሊገለጽ ይችላል ፡፡ አት: - “ሰዎች ተግባሩን በግልፅ ሊያዩ ይችላሉ” ወይም “ሁሉም ሰው የሚያደርገውን ነገር በግልፅ ሊያይ ይችላል” (ይመልከቱ።
ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስ ከኒቆዲሞስ ጋር ከተነጋገረ በኋላ ነው ፡፡ ይህንን በ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ።
ይህ ቃል "ምንጮች" ማለት ነው ፡፡ (ይመልከቱ: መተርጎም_ቁጥር)
ከዮርዳኖስ ወንዝ አጠገብ ያለ መንደር ወይም መንደር (ይመልከቱ: መተርጎም_ቁጥር)
በዚያ ስፍራ ብዙ ምንጮች ነበሩና ”
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። AT “ዮሐንስ ያጠምቃቸዋል” ወይም “እያጠመቀ ነበር” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር) ፡፡
ግልጽ ለማድረግ ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለጽ ይችላል። አት: - “የዮሐንስ ደቀ መዛሙርትና አንድ አይሁዳዊ ይከራከሩ ጀመር” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ቃላትን በመጠቀም የሚደረግ ትግል
በዚህ ሐረግ ውስጥ “ተመልከት” “በትኩረት!” የሚል ትርጉም ያለው ትእዛዝ ነው ፡፡ AT: - “እነሆ እርሱ ያጠምቃል” ወይም “እነሆ እሱ እሱ ያጠምቃል” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
"ማንም ካልሆነ በስተቀር ማንም ኃይል የለውም"
እዚህ “ሰማይ” እግዚአብሔርን ለማመልከት እንደ ተውላጠ ስም ጥቅም ላይ ውሏል ፡፡ ይህ በገባ ቅርጸት ሊገለጽ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ሰጠው” (የበለስ_ቁልፍ እና የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ “አንተ” ብዙ ነው ፣ እናም ዮሐንስ የሚናገራቸውን ሰዎች ሁሉ ያመለክታል። አት: - “ሁላችሁም” ወይም “ሁላችሁም” (የበለስ_አዎን ይመልከቱ) (ይመልከቱ: በለስ
ይህ በገባ ቅርጸት ሊገለጽ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር በፊቱ እንድመጣ ልኮኛል” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
መጥምቁ ዮሐንስ መናገሩን ቀጠለ ፡፡
እዚህ ላይ “ሙሽራይቱ” እና “ሙሽራይቱ” ዘይቤዎች ናቸው ፡፡ ኢየሱስ እንደ “ሙሽራይቱ” ነው ፣ ዮሐንስም “የሙሽራው” ጓደኛ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እንግዲያውስ በጣም ደስ ብሎኛል” ወይም “ስለዚህ እጅግ በጣም ደስ ይለኛል” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
“የእኔ” የሚለው ቃል የሚናገረውን መጥምቁ ዮሐንስን ነው ፡፡
“እርሱ” እሱ እያደገ የሚሄደው የሙሽራውን የኢየሱስን ነው ፡፡
"ከሰማይ የሚመጣ ከሁሉ ይልቅ የከበረ ነው"
ዮሐንስ ለማለት የፈለገው ዮሐንስ በምድር ላይ ስለተወለደ ና ኢየሱስ ከሰማይ ስለሆነና ከእሱ ይልቅ የከበረ ነው። "በዚህ ምድር የተወለደ ሁሉ በዚህ ምድር እንዳሉት ሁሉ ነው ደግሞም በዚህ ምድር ስለሚሆነው ይናገራል"
ይህ ልክ በመጀመሪያው ዓረፍተ ነገር እንደተገለጸው ነው። ዮሐንስ ለማጠንከር ይህንን ይናገራል።
ዮሐንስ ስለኢየሱስ እየተናገረ ነው። "ከሰማይ የሆነው በሰማይ ስላየው እና ስለሰማው ይናገራል።"
ጥቂቶች ብቻ ኢየሱስን እንዳመኑ ለማሳየት ዮሐንስ እዚህ ጋር ያጋንናል። "እጅግ ጥቂት ሰዎች በእርሱ ያምናሉ።"
"ኢየሱስ የሚናገረውን ያሚያምን ማንኛውም ሰው"
"ያስረግጣል" ወይም "ይስማማል"
መጥምቁ ዮሐንስ ንግግሩን ይጨርሳል።
"ይህ ኢየሱስ፥ እግዚአብሔር እንዲወክለው የላከው"
"የመንፈሱን ሙሉ ኃይል የሰጠው ለእሱ ነውና"
ኢነዚህ በእግዚአብሔር እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚገልጹ አስፈላጊ መጠሪያዎች ናቸው
ይህ ማለት በእሱ ስልጣን ወይም ቁጥጥር ሥር መደረግ ማለት ነው።
"የሚያምን ሰው" ወይም "የሚያምን ማንኛውም ሰው"
“ቁጣ” የሚለው ቃል “ቅጣት” ከሚለው ግስ ጋር ሊተረጎም ይችላል። አት: - “እግዚአብሔር ይቀጣዋል”
1 ፈሪሳውያን ኢየሱስ ከዮሐንስ የበለጠ ብዙ ሰዎችን ደቀ መዛሙርት እንደሚያደርግና እንደሚያጠምቅ ሰሙ፤ ኢየሱስም ይህን ዐወቀ፤ 2 (ያጠምቁ የነበሩት ደቀ መዛሙርቱ እንጂ እርሱ ባይሆንም)፣ ኢየሱስ መስማታቸውን ባወቀ ጊዜ 3 የይሁዳን ምድር ለቅቆ ወደ ገሊላ ሄደ። 4 በሰማርያም በኩል ማለፍ ነበረበት። 5 ከዚያም በሰማርያ ከተማ፣ ያዕቆብ ለልጁ ለዮሴፍ በሰጠው ቦታ አጠገብ ወደምትገኝ፣ ሲካር ወደምትባል ቦታ መጣ። 6 በዚያም የያዕቆብ የውሃ ጒድጓድ ነበረ፤ ኢየሱስ ከጒዞው ብዛት ደክሞት ስለ ነበር፣ በውሃው ጒድጓድ አጠገብ ተቀመጠ፤ ጊዜውም እኩለ ቀን አካባቢ ነበር። 7 አንዲት ሳምራዊት ሴት ውሃ ልትቀዳ ስትመጣ፣ ኢየሱስ፣ «እባክሽ የምጠጣው ውሃ ስጪኝ» አላት። 8 ደቀ መዛሙርቱ ምግብ ለመግዛት ወደ ከተማ ሄደው ነበር። 9 ሳምራዊቷም ሴት፣ «አንተ አይሁዳዊ ሆነህ፣ እኔን ሳምራዊቷን ሴት እንዴት ውሃ አጠጪኝ ትለኛለህ?» አለችው። አይሁድ ከሳምራውያን ጋር አይተባበሩም ነበርና። 10 ኢየሱስ፣ «የእግዚአብሔርን ስጦታና ውሃ አጠጪኝ የሚልሽ ማን እንደሆነ ዐውቀሽ ቢሆን ኖሮ ፣ አንቺው በጠየቅሽው፣ እርሱም ሕያው ውሃ በሰጠሽ ነበር» ብሎ መለሰላት። 11 ሴትዮዋም እንዲህ አለችው፤ «ጌታ ሆይ፣ አንተ መቅጃ የለህም፤ ጒድጓዱም ጥልቅ ነው፤ ታዲያ ሕያዉን ውሃ ከየት ታገኛለህ? 12 አንተ፣ ይህን ጒድጓድ ከሰጠን፣ ከአባታችን ከያዕቆብ ትበልጣለህን? እርሱ ራሱ፣ ልጆቹና ከብቶቹም ከዚሁ ጒድጓድ ጠጥተዋል። 13 ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰላት፤ «ከዚህ ውሃ የሚጠጣ ሁሉ እንደ ገና ይጠማል፤ 14 እኔ ከምሰጠው ውሃ የሚጠጣ ግን ፈጽሞ ዳግመኛ አይጠማም፤ ይልቁንም፣ እኔ የምሰጠው ውሃ፣ ከውስጡ የሚፈልቅ የዘላለም ሕይወት ውሃ ምንጭ ይሆናል።» 15 ሴትዮዋም፣ «ጌታዬ፤ ከእንግዲህ እንዳልጠማና ውሃ ለመቅዳት ወደዚህ እንዳልመጣ፣ ይህን ውሃ ስጠኝ» አለችው። 16 ኢየሱስም፣ «ሂጂ፣ ባልሽን ጥሪና ወደዚህ ተመልሰሽ ነይ» አላት። 17 ሴትዮዋ፣ «ባል የለኝም» በማለት መለሰች፤ ኢየሱስ፣ 'ባል የለኝም' በማለትሽ ልክ ነሽ፤ 18 አምስት ባሎች ነበሩሽና፤ አሁን ከአንቺ ጋር ያለው ሰው ባልሽ አይደለም፤ ስለዚህ እውነቱን ተናግረሻል» ብሎ መለሰ። 19 ሴትዮዋ፣ «ጌታ ሆይ፣ አንተ ነቢይ እንደ ሆንህ ይገባኛል፤ 20 አባቶቻችን በዚህ ተራራ ላይ ሰገዱ፤ እናንተ ግን ሰው መስገድ ያለበት በኢየሩሳሌም ነው ትላላችሁ» አለችው። 21 ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰላት፤ «አንቺ ሴት፣ በዚህ ተራራም ሆነ በኢየሩሳሌም ለአብ የማትሰግዱበት ጊዜ እየመጣ መሆኑን እመኚኝ። 22 እናንተ ሳምራውያን ለማታውቁት ትሰግዳላችሁ። እኛ ግን፣ ድነት ከአይሁድ ስለ ሆነ፣ ለምናውቀው እንሰግዳለን። 23 ይሁን እንጂ፣ በእውነት የሚሰግዱ ለአብ በመንፈስና በእውነት የሚሰግዱበት ጊዜ እየመጣ ነው፤ አሁንም መጥቶአል፤ አብ እንደዚህ በእውነት የሚሰግዱለትን ሰዎች ይፈልጋልና። 24 እግዚአብሔር መንፈስ ነው፤ የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ይገባል።» 25 ሴትዮዋ፣ «ክርስቶስ የሚባል መሲሕ እንደሚመጣ ዐውቃለሁ፤ እርሱ ሲመጣ ሁሉንም ነገር ይነግረናል» አለችው። 26 ኢየሱስ፣ «አሁን እያነጋገርሁሽ ያለሁት እኔ እርሱ ነኝ» አላት። 27 ልክ በዚህ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ተመልሰው መጡ፤ ኢየሱስ ከሴት ጋር በመነጋገሩ ተገረሙ፤ ይሁን እንጂ፣ ማንም፣ «ምን ትፈልጋለህ? ወይም ከእርስዋ ጋር ለምን ትነጋገራለህ?» ያለው የለም። 28 ሴትዮዋ እንስራዋን ትታ ወደ ከተማ ተመለሰች፤ ለሕዝቡም፣ 29 «ያደረግሁትን ነገር ሁሉ የነገረኝን ሰው ኑና እዩ፤ እርሱ ክርስቶስ ይሆንን?» አለች፤ 30 ሕዝቡ ከከተማ ወጥተው እርሱ ወዳለበት መጡ። 31 በዚህም መሐል ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስን፣ «መምህር ሆይ፣ ምግብ ብላ» አሉት። 32 እርሱ ግን፣ «እናንተ የማታውቁት፣ የምበላው ምግብ አለኝ» አላቸው። 33 ስለዚህ ደቀ መዛሙርቱ እርስ በርስ፣ «ምግብ ያመጣለት ሰው ይኖር ይሆን?» ተባባሉ። 34 ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፤ «የእኔ ምግብ የላከኝን ፈቃድ ማድረግና ሥራውንም መፈጸም ነው። 35 እናንተ 'መከር ገና አራት ወር ቀርቶታል፤ ከዚያም መከሩ ይመጣል' ትሉ የለምን? ቀና በሉና ዕርሻዎቹን ተመልከቱ፣ መከሩ ደርሷልና እያልኋችሁ ነው፤ 36 የሚያጭድ ደመወዙን ይቀበላል፤ ለዘላለም ሕይወት የሚሆን ፍሬም ይሰበስባል፤ ስለዚህ የሚዘራውም፣ የሚያጭደውም አብረው ይደሰታሉ። 37 'አንዱ ይዘራል፣ ሌላውም ያጭዳል' የሚለው አባባል እውነት የሚሆነው በዚህ ምክንያት ነው። 38 እኔ ያልደከማችሁበትን እንድታጭዱ ላክኋችሁ፤ ሌሎች በሥራ ደከሙ፤ እናንተም በእነርሱ ሥራ ገባችሁ።» 39 ሴትዮዋ፣ «ያደረግሁትን ሁሉ ነገረኝ» ብላ ስለ እርሱ በሰጠችው ምስክርነት የተነሣ፣ በዚያች ከተማ ከሚኖሩ ሳምራውያን ብዙዎቹ በእርሱ አመኑ። 40 ስለዚህ፣ ሳምራውያኑ ወደ እርሱ በመጡ ጊዜ፣ ከእነርሱ ጋር እንዲቈይ ለመኑት፤ እዚያም ሁለት ቀን ቈየ። 41 ከቃሉም የተነሣ ሌሎች ብዙ ሰዎች አመኑ። 42 ሴትዮዋንም፣ «የምናምነው አንቺ ስለ ነገርሽን ቃል ብቻ አይደለም፤ እኛ ራሳችን ሰምተነዋል፤ ይህ ሰው በእውነት የዓለም አዳኝ እንደ ሆነ እናውቃለን» ይሏት ነበር። 43 ከእነዚያ ሁለት ቀናት በኋላም ከዚያ ተነሥቶ ወደ ገሊላ ሄደ። 44 ነቢይ በገዛ አገሩ እንደማይከበር ኢየሱስ ራሱ ተናግሮ ነበርና። 45 ወደ ገሊላ በደረሰ ጊዜ፣ የገሊላ ሰዎች በደስታ ተቀበሉት፤ እነርሱ በፋሲካ በዓል ወደዚያ ሄደው ስለ ነበር፣ በኢየሩሳሌም ያደረጋቸውን ነገሮች ሁሉ አይተው ነበር። እነርሱ ደግሞ ወደ በዓሉ ሄደው ነበርና። 46 ኢየሱስም ውሃውን የወይን ጠጅ ወዳደረገባት፣ በገሊላ ወደምትገኘው ወደ ቃና ከተማ ዳግመኛ መጣ፤ በቅፍርናሆምም ልጁ የታመመበት አንድ ከንጉሣዊ ቤተ ሰብ የሆነ ሹም ነበር፤ 47 እርሱም ኢየሱስ ከይሁዳ ወደ ገሊላ መምጣቱን በሰማ ጊዜ፣ ወደ እርሱ ሄደና በሞት አፋፍ ላይ የሚገኘውን ልጁን መጥቶ እንዲፈውስለት ለመነው። 48 ከዚያም ኢየሱስ፣ «እናንተ ሰዎች ምልክቶችንና ድንቆችን ካላያችሁ አታምኑም» አለው። 49 ሹሙ፣ «ጌታ ሆይ፤ ልጄ ከመሞቱ በፊት እባክህ ውረድ» አለው። 50 ኢየሱስ፣ «ሂድ፤ ልጅህ በሕይወት ይኖራል» አለው። ሰውየው ኢየሱስ የተናገረውን ቃል አምኖ ሄደ። 51 በመንገድ ላይ ሳለም፣ አገልጋዮቹ አገኙትና ልጁ ተሽሎት በሕይወት እንዳለ ነገሩት። 52 እርሱም ልጁ የተሻለው በስንት ሰዓት ላይ እንደ ነበረ ጠየቃቸው። እነርሱም፣ «ትኵሳቱ የለቀቀው ትናንት በሰባተኛው ሰዓት ላይ ነበር» አሉት። 53 አባትየውም፣ ኢየሱስ «ልጅህ በሕይወት ይኖራል» ብሎት የነበረው በዚያ ሰዓት እንደ ነበረ ተገነዘበ፤ ስለዚህ እርሱ ራሱና ቤተ ሰቡ በሙሉ በኢየሱስ አመኑ። 54 ይህም ኢየሱስ ከይሁዳ ወደ ገሊላ በመጣ ጊዜ ያደረገው ሁለተኛው ምልክት ነው።
ስለ ኢየሱስ እና ስለ ሳምራዊቷ ሴት የሚቀጥለው ታሪክ ይህ ክፍል ነው፡፡ እነዚህ ቁጥሮች ለዚህ የታሪኩ ክፍል ዳራ መረጃን ይሰጣሉ ፡፡
"ኢየሱስ ያደርገው ነበር ... ዮሐንስ (ምንም ቢሆን. . . ነበር)፣ ፈሪሳውያንም ስላገኘው ስኬት ሰሙ ፡፡ ፈሪሳውያኑ እንደሰሙ ባወቀ ጊዜ ከገሊላ ሄደ።
በዋና ዋና ክስተቶች ውስጥ እረፍትን ለማመልከት “አሁን” የሚለው ቃል እዚህ ጥቅም ላይ ውሏል ፡፡ እዚህ ላይ ዮሐንስ የትረካው አዲስ ክፍል መንገር ይጀምራል ፡፡
ተለጣፊው ተውላጠ ስም “ራሱ” አጽን addsት የሚሰጠው እሱ የሚያጠምቀው ኢየሱስ ሳይሆን ደቀመዛሙርቱ ነው።
ሰሜናዊው የእስራኤል ሰሜናዊ ክፍል ውስጥ ሰማርያ የከተማዋ እና የአከባቢዋ ስም ነበር ፡፡ ክልሉ የሚገኘው በምዕራብ በሳሮን ሜዳ መካከል እና በስተ ምሥራቅ በዮርዳኖስ ወንዝ መካከል ነው ፡፡
በብሉይ ኪዳን ፣ ሰማርያ የሰሜናዊው የእስራኤል መንግሥት ዋና ከተማ ነበረች ፡፡ በኋላም በዙሪያዋ ያለው ክልል ሰማርያ ተባለ ፡፡
አሦራውያን ሰሜናዊውን የእስራኤል መንግሥት ሲቆጣጠሩ የሰማርያ ከተማን በመቆጣጠር አብዛኞቹን ሰሜናዊውን የእስራኤልን ግዛቶች ለቀው በመሄድ ወደ አሦር የተለያዩ ከተሞች ተጓዙ ፡፡
የተንቀሳቀሱትን እስራኤላውያን ለመተካት አሦራውያን ብዙ የውጭ አገር ዜጎች ወደ ሰማርያ ምድር አመጡ።
በዚያ አካባቢ የቀሩት አንዳንድ እስራኤላውያን ወደዚያ የሄዱት የባዕድ አገር ሰዎችን አገቡ ፤ ዘሮቻቸውም ሳምራውያን ተብለዋል።
አይሁዶች ሳምራውያንን ይንቃቸው ነበር ምክንያቱም እነሱ በከፊል አይሁድ ብቻ ስለነበሩ እና ቅድመ አያቶቻቸው አረማዊ አማልክትን ያመልኩ ስለነበረ ነው ፡፡
በአዲስ ኪዳን ጊዜያት የሰማርያ ክልል በሰሜን በኩል በገሊላ አውራጃ እንዲሁም በደቡብ በኩል በይሁዳ ምድር ይገኝ ነበር ፡፡
ያዕቆብ የይስሐቅና የርብቃ ምንታ ልጆች ታናሽ ልጅ ነበር ፡፡
የያዕቆብ ስም “ተረከዙን ይይዛል” ማለት ሲሆን ትርጉሙም “ያታልላል” ማለት ነው ፡፡ ያዕቆብ ሲወለድ መንትያ ወንድሙን ኤሳው ተረከዙን ተረከዙ ፡፡
ከብዙ ዓመታት በኋላ ፣ እግዚአብሔር የያዕቆብን ስም “እስራኤል” ብሎ ቀይሮታል ፣ ማለትም “ከእግዚአብሔር ጋር ታገለ” ፡፡
ያዕቆብ ብልህ እና አታላይ ነው ፡፡ የበኩር ወንድሙ ኤሳው የበኩር ልጅ በረከትን እና ውርስ መብቶችን ለመውሰድ መንገዶችን አገኘ ፡፡
ኤሳው ተቆጥቶ ሊገድለው አሰበ ፣ ስለዚህ ያዕቆብ የትውልድ አገሩን ለቅቋል ፡፡ ሆኖም ከዓመታት በኋላ ያዕቆብ ከሚስቱና ከልጆቹ ጋር ኤሳው ወደሚኖርበት ወደ ከነዓን ምድር ተመለሰ ፡፡ ቤተሰቦቻቸውም እርስ በእርሱ ተቀራርበው በሰላም ኖረዋል ፡፡
ያዕቆብ አሥራ ሁለት ወንዶች ልጆች ነበሩት። ዘሮቻቸው አሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች ሆኑ።
ያዕቆብ የሚባል ሌላ ሰው በማቴዎስ የትውልድ ሐረግ የዮሴፍ አባት እንደሆነ ተዘርዝሯል ፡፡
ዮሴፍ የአስራ አንድ ልጅ ሲሆን የእናቱ የራሔል የመጀመሪያ ልጅ ነው፡፡
ዮሴፍ የአባቱ ተወዳጅ ልጅ ነበር ፡፡
ወንድሞቹ ቀኑበት ለባርነት ሸጡት ፡፡
ዮሴፍ በግብፅ በነበረበት ጊዜ በሐሰት ተወንጅሎ እስር ቤት ገባ ፡፡
ዮሴፍ ብዙ ችግሮች ቢያጋጥሙትም ለአምላክ ታማኝ ነበር።
እግዚአብሔር በግብፅ ወደ ሁለተኛው ከፍተኛ የሥልጣን ስፍራ ያመጣውና ምግብ በማይኖርበት ጊዜ ሰዎችን ለማዳን ተጠቅሞበታል ፡፡ የግብፅ ሕዝብም ሆነ የገዛ ቤተሰቡ በረሃብ እንዳያጡ ተደረገ ፡፡
ይህ በትእዛዝ ሳይሆን በትህትና የተሞላ ጥያቄ ነው ፡፡
ምክንያቱም ሄደው ስለነበር ደቀ መዛሙርቱ ውሃ እንዲያጠጡ አልጠየቃቸውም ፡፡
“እሱ” የሚለው ቃል ኢየሱስን ያመለክታል ፡፡
ይህ አስተያየት የሳምራዊቷን ሴት ኢየሱስ እንድትጠጣት የጠየቀችውን አስገራሚ ለመግለጽ በጥያቄ መልክ ይታያል ፡፡ አት: - "አንተ አይሁዳዊ ከሆንክ ሳምራዊውን መጠጥ እንድትጠጣ ትጠይቀዋለህ!"
"አይቀራረቡም"
ኢየሱስ “የሕይወት ውሃ” የሚለውን ዘይቤ ተጠቅሞ በአንድ ሰው ውስጥ አዲስ ሕይወትን ለመለወጥ እና ለማምጣት በሰው ውስጥ ለሚሠራው መንፈስ ቅዱስ ይጠቅሳል ፡፡
ይህ ማስታወሻ የሚከናወነው ትኩረት ለመጨመር በጥያቄ መልክ ነው ፡፡ አት: - “ከአባታችን ከያዕቆብ አልበልጡም… ከብቶች!”
"ቅድመ አባታችን ያዕቆብ"
“ከእሱ የመጣውን ውሃ ጠጡ”
"ውሃን እንደገና መጠጣት ያስፈልገዋል"
እዚህ “ምንጭ” የሚለው ቃል ለሕይወት የሚሰጥ ውሃ ዘይቤ ነው። "እኔ የምሰጠው ውሃ በእሱ ውስጥ እንደ ምንጭ ምንጭ ይሆናል ፡፡"
እዚህ “ሕይወት” የሚያመለክተው እግዚአብሔር ብቻ ሊሰጥ የሚችለውን “መንፈሳዊ ሕይወት” ነው ፡፡
በዚህ ዐውድ፣ ሳምራዊቷ ሴት ኢየሱስን “ጌታው” ብላ ትጠራዋለች ፣ ይህም የመከባበር ወይም የትህትና ቃል ነው።
መያዥያ እና ገመድ በመጠቀም “ውሃ ይምጡ” ወይም “ከጉድጓዱ ውስጥ ውሃ ይነሱ”
ኢየሱስ ሴቲቱ እውነቱን የምትናገር መሆኗን አፅንኦት ለመስጠት ይህንን ቃል ይደጋግምል ፡፡
በዚህ ዐውድ፣ ሳምራዊቷ ሴት ኢየሱስን “ጌታው” ብላ ትጠራዋለች ፣ ይህም የመከባበር ወይም የትህትና ቃል ነው።
"ነብይ እንደሆንክ እረዳለሁ"
"ቀደምት አባቶቻችን"
አንድን ሰው ለማመን ሰውዬው የተናገረውን ማመን እውነት ነው ፡፡
ኢየሱስ ማለት እግዚአብሔር ራሱንና ትእዛዛቱን የገለጠው ለሳምራውያን ሳይሆን ለአይሁድ ሰዎች ነው ማለት ነው ፡፡ በቅዱሳት መጻሕፍት አማካይነት የአይሁድ ህዝብ ከሳምራውያን እግዚአብሔር የተሻለው ማን እንደሆነ ያውቃሉ ፡፡
ከኃጢአት የዘላለም መዳን የሚመጣው የአይሁድ አምላክ የሆነው እግዚአብሔር አብ ነው ፡፡
ይህ ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡
ይህ ማለት የአይሁድ ህዝብ ሌሎችን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋል ማለት አይደለም ፡፡ ይህ ማለት እግዚአብሔር አይሁዶችን እንደ ልዩ ህዝቡ አድርጎ ስለ መዳንነቱ የሚናገር ልዩ ህዝብ አድርጎ መረጠ ማለት ነው ፡፡ አት: - “አይሁዶች ሁሉ ስለ እግዚአብሔር ማዳን ያውቃሉና።”
ኢየሱስ ሳምራዊቷን ሴት ማነጋገሩን ቀጠለ።
ሆኖም ግን ፣ አሁን ለእውነተኛ አምላኪዎች ትክክለኛ ጊዜ ነው ”
ይህ ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡
“በትክክለኛው መንገድ ስገዱ”
እነዚህ ሁለቱም ቃላት “እግዚአብሔር የተነገረለት ንጉሥ” ማለት ነው ፡፡
"ኢየሱስ ይህን ሲል ደቀ መዛሙርቱ ከከተማ ተመለሱ"
አንድ አይሁዳዊ ከማያውቃት ሴት ጋር መነጋገሩ ያልተለመደ ነበር ፣ በተለይም ያ ሴት ሳምራዊቷ።
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ደቀመዛምርቱ ሁለቱንም ጥያቄዎች ለኢየሱስ ጠይቀዋል ወይም 2) “ሴቲቱን 'ምን ... ምን ትፈልጋለች?' ወይም ኢየሱስን ለምን ጠየቃት?
ይህ የተጋነነ ነው ፡፡ ሳምራዊቷ ሴት በኢየሱስ ላይ በጣም ከመደነቋ የተነሳ ስለ እሱ ሁሉንም ነገር አስቀድሞ ማወቅ አለበት ብላ ታምናለች። አት: - “ከዚህ በፊት አግኝቼው የማላውቀውም እንኳ ስለ እኔ በጣም ብዙ የሚያውቀውን ሰው እዩ!”
ይህ የተጋነነ ነው ፡፡ ሳምራዊቷ ሴት በኢየሱስ ላይ በጣም ከመደነቋ የተነሳ ስለ እሱ ሁሉንም ነገር አስቀድሞ ማወቅ አለበት ብላ ታምናለች። አት: - “ከዚህ በፊት አግኝቼው የማላውቀውም እንኳ ስለ እኔ በጣም ብዙ የሚያውቀውን ሰው እዩ!”
"ሴቲቱ ወደ ከተማ በሄደችበት ጊዜ"
"ደቀ መዛሙርቱ ለኢየሰስ እየነገሩት ነበር" ወይንም "ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስን እያበረታቱት ነበር"
እዚህ ላይ ኢየሱስ የተናገረው ቃል በቃል ስለ “ምግብ” አይደለም ፣ ነገር ግን ደቀመዛሙርቱን ለመንፈሳዊ ትምህርት እያዘጋጃቸው ነው
እዚህ ላይ “ምግብ” “የእግዚአብሔርን ፈቃድ መታዘዝ” የሚያሳይ ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - “ምግብ የተራበውን ሰው እንደሚጠግብ ሁሉ ፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ መታዘዝ እኔን ያረካኛል”
"ይህ በመካከላችሁ ካሉት ታዋቂ አባባሎች አንዱ አይደለም"
“እርሻዎች” እና “ለመከር ደርሷል” የሚሉት ቃላት ዘይቤዎች ናቸው ፡፡ “መስኩ” የአይሁድ ያልሆኑ ሰዎችን ወይም አህዛብን ይወክላል። “ለመከር ደርሷል” የሚሉት ቃላት አሕዛብ ማሳ ለመሰብሰብ እንደተዘጋጁ ሁሉ አሕዛብ የኢየሱስን መልእክት ለመቀበል ዝግጁ ናቸው ማለት ነው ፡፡ አት: - “እነዚህ የአይሁድ ያልሆኑ ሰዎች ተመልከቷቸው! ተመልከቱ!
ኢየሱስ “በእርሻው ውስጥ ለሚሠሩ” ሽልማታቸውን እንዳገኙና መልእክቱን እንደሚካፈሉ ኢየሱስ ጠቁሟል ፡፡ መልእክቱን የተቀበሉ ደግሞ እግዚአብሔር የሚሰጠውን የዘላለም ሕይወት ይቀበላሉ ፡፡
ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ መናገሩን ቀጠለ።
"መዝራት" እና "መከር" የሚሉት ቃላት ዘይቤዎች ናቸው ፡፡ የዘራውም ሰው የኢየሱስን መልእክት ያካፍላል ፡፡ የሰበሰበውም ሰዎቹ የኢየሱስን መልእክት እንዲቀበሉ ይረዳል ፡፡ አት: - “አንድ ሰው ዘሩን ይተክላል ፣ ሌላውም ሰው እህል ያጭዳል።”
"አሁን በስራቸው ውስጥ ትሳተፋለህ" (UDB)
በሆነ ሰው ማመን “ማመን” በዚያ ሰው ማመን ነው ፡፡ እዚህም ቢሆን ይህ ማለት እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ያምናሉ ማለት ነው ፡፡
ይህ ግንነት ነው ፡፡ ሴትየዋ በኢየሱስ እጅግ የተደነቀች ሲሆን ስለ እሷ ሁሉንም ነገር እንደሚያውቅ ተሰማት። አት: - “ስለ ሕይወቴ ብዙ ነገረኝ”
እዚህ “ቃል” ኢየሱስ ያስተላለፈውን መልእክት የሚያመለክተው ቃል ነው ፡፡
“ዓለም” በዓለም ለሚኖሩት ሰዎች ሁሉ የሚያመለክተው ዘይቤ ነው። አት: - “የዓለም ሕዝብ ሁሉ”
ኢየሱስ ወደ ገሊላም በወረደበት ወንድ ልጅን ያፈገፈበት ቀጣዩ ክፍል ነው ፡፡ ቁጥር 44 ኢየሱስ ቀደም ሲል ስለ ተናገረው ነገር ዳራ መረጃን ይሰጠናል ፡፡
ከይሁዳ
ተለጣፊው ተውላጠ ስም “ራሱ” ኢየሱስ “እንዳወጀ” ወይም ይህን እንደተናገረው አፅንኦት ለመስጠት ተጨምሯል ፡፡ ይህንን በአፍ መፍቻ ቋንቋዎ ለአንድ ሰው ትኩረት በሚሰጥ መንገድ መተርጎም ይችላሉ ፡፡
"ሰዎች ለገዛ አገራቸው ነቢይ አክብሮት ወይም ክብር አያሳዩም"
ይህ በዓል ፋሲካ ነው
ይህ ቃል በዋናው የታሪክ መስመር ላይ ዕረፍትን ለማመልከት እና ወደ ታሪኩ አዲስ ክፍል ለመቀየር እዚህ ላይ ይውላል ፡፡ ይህንን በቋንቋዎ የሚያደርጉበት መንገድ ካለዎት እሱን ለመጠቀም ሊያስቡበት ይችላሉ ፡፡
በንጉስ አገልግሎት ውስጥ ያለ ሰው ነው
ካልሆነ በስተቀር… ካላመኑ ”ድርብ አሉታዊ ነው። በአንዳንድ ቋንቋዎች ይህንን መግለጫ በአዎንታዊ መልኩ መተርጎም የበለጠ ተፈጥሮአዊ ነው ፡፡ አት: - “ተአምር ካዩ ብቻ ነው የሚያምኑት”
እዚህ “ቃል” ኢየሱስ የተናገረውን መልእክት የሚያመለክተን ቃል ነው ፡፡ አት: - “መልእክቱን አመኑ”
ይህ ቃል በተመሳሳይ ጊዜ የሚከሰቱ ሁለት ሁነቶችን ለማመልከት ያገለግላል ፡፡ ባለስልጣኑ ወደ ቤት እየተመለሰ እያለ አገልጋዮቹ በመንገድ ላይ ሊገናኙት እየመጡ ነበር ፡፡
አጣቃቂ ተውላጠ ስም “ራሱ” እዚህ ጥቅም ላይ የዋለው “እሱ” የሚለውን ቃል ለማጉላት ነው ፡፡ ይህንን በቋንቋዎ የሚያደርጉበት መንገድ ካለዎት እሱን ለመጠቀም ሊያስቡበት ይችላሉ ፡፡
ተአምራት “ምልክቶች” ሊባሉም ይችላሉ ምክንያቱም አመላካቾች ወይም ማስረጃዎች በአጽናፈ ዓለሙ ሁሉ ላይ ሙሉ ስልጣን ያለው አምላክ መሆኑን ለማሳየት ነው ፡፡
1 ከዚህ በኋላ የአይሁድ በዓል ነበረ፤ ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ። 2 በኢየሩሳሌምም በበጎች በር አጠገብ፣ አምስት ጣሪያ ያላቸው መመላለሻዎች ነበሩ። በዚያ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ የሚባል አንድ መጠመቂያ ነበረ። 3 በእነዚህ መመላለሻዎች ወለል ላይ በጣም ብዙ ሕሙማን፣ ዐይነ ስውሮች፣ አንካሶች ወይም ሽባዎች ተኝተው ነበር። 4[1] «ዐልፎ ዐልፎ የጌታ መልአክ መጥቶ ውሃውን በሚያናውጥበት ጊዜ፣ ቀድሞ ወደ መጠመቂያው የገባ ሰው ከሚሠቃይበት ከማንኛውም በሽታ ይፈወስ ነበር» የሚለውን ክፍል እንድትተዉት እንመክራለን። 5 በዚያም ለሠላሳ ስምንት ዓመት ሽባ ሆኖ የኖረ አንድ ሰው ነበረ። 6 ኢየሱስ ሰውየውን እዚያ ተኝቶ ባየው ጊዜ፣ ለረጅም ጊዜ በዚያ መቆየቱን ዐውቆ፣ «መዳን ትፈልጋለህን?» አለው። 7 ሕመምተኛውም ሰው መልሶ፣ «ጌታ ሆይ፣ ውሃው በሚናወጥበት ጊዜ መጠመቂያው ውስጥ የሚያስገባኝ ሰው የለኝም፤ ለመግባትም ስሞክር ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል» አለው። 8 ኢየሱስ፣ «ተነሥ! የተኛህበትን ምንጣፍ ተሸክመህ ሂድ» አለው። 9 ሰውየው ወዲያውኑ ተፈወሰ፤ የተኛበትንም ምንጣፍ ተሸክሞ ሄደ። ያም ቀን ሰንበት ነበረ። 10 ስለዚህ የአይሁድ መሪዎች የተፈወሰውን ሰው፣ «ሰንበት ነው፤ ምንጣፍህን ልትሸከም አልተፈቀደልህም» አሉት። 11 እርሱ ግን፣ «ያ ያዳነኝ ሰው፣ 'የተኛህበትን ምንጣፍ ተሸክመህ ሂድ'» አለኝ ብሎ መለሰላቸው። 12 እነርሱም፣ «የተኛህበትን ምንጣፍ ተሸክመህ ሂድ» ያለህ ሰው ማን ነው?» ብለው ጠየቁት። 13 የተፈወሰው ሰው ግን ኢየሱስ ከአጠገቡ ፈቀቅ ስላለና በስፍራው ብዙ ሕዝብ ስለ ነበር፣ ማን እንደ ፈወሰው አላወቀም። 14 በኋላ ኢየሱስ ያን ሰው በቤተ መቅደስ አግኝቶት፣ «እነሆ፣ ተፈውሰሃል፤ ከዚህ የባሰ ነገር እንዳይደርስብህ ከእንግዲህ ኀጢአት አትሥራ» አለው። 15 ሰውየው ሄዶ የፈወሰው ኢየሱስ መሆኑን ለአይሁድ መሪዎች ነገራቸው። 16 ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች በሰንበት ስላደረገ፣ የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን ያሳድዱት ነበር። 17 ኢየሱስ፣ «አባቴ እስካሁን እየሠራ ነው፤ እኔም እሠራለሁ» አላቸው። 18 በዚህ ምክንያት አይሁድ ኢየሱስ ሰንበትን ስለ ሻረ ብቻ ሳይሆን፣ እግዚአብሔርን አባቴ ነው በማለት፣ ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር እኩል ስላደረገ፣ ሊገድሉት አጥብቀው ይፈልጉ ነበር። 19 ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አላቸው፤ «እውነት እላችኋለሁ፣ አብ ሲያደርግ ያየውን ነው እንጂ ወልድ ከራሱ ምንም ሊያደርግ አይችልም፤ አብ የሚያደርገውን ሁሉ ወልድም ያንኑ ያደርጋልና። 20 አብ ወልድን ይወዳልና፣ የሚያደርገውንም ሁሉ ያሳየዋል፤ እናንተም ትደነቁ ዘንድ ከዚህ የሚበልጥ ነገር ያሳየዋል። 21 አብ ሙታንን እንደሚያስነሣና ሕይወትንም እንደሚሰጣቸው፣ ወልድም ደግሞ ለሚፈልገው ሁሉ ሕይወትን ይሰጣል። 22 አብ በማንም ላይ አይፈርድም፤ ነገር ግን ፍርድን ሁሉ ለወልድ ሰጥቶታል፤ 23 ይኸውም፣ ሁሉ አብን እንደሚያከብሩት ወልድን ያከብሩት ዘንድ ነው፤ ወልድን የማያከብር፣ የላከውን አብንም አያከብርም። 24 እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ፤ ቃሌን የሚሰማ፣ በላከኝም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ ከሞት ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ አይፈረድበትም። 25 እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ ሙታን የእኔን፣ የእግዚአብሔርን ልጅ ድምፅ የሚሰሙበት ጊዜ እየመጣ ነው፤ አሁንም መጥቶአል፤ የሚሰሙትም በሕይወት ይኖራሉ። 26 አብ በራሱ ሕይወት እንዳለው ሁሉ፣ ወልድም በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሰጥቶታልና፤ 27 ወልድ የሰው ልጅ ስለ ሆነ፣ አብ የመፍረድን ሥልጣን ለወልድ ሰጥቶታል። 28 በዚህ አትደነቁ፤ በመቃብር ውስጥ ያሉ ሁሉ ድምፁን የሚሰሙበት ጊዜ ይመጣል፤ 29 መልካም የሠሩ ለሕይወት ትንሣኤ፣ ክፉ የሠሩም ለፍርድ ትንሣኤ ይወጣሉ። 30 እኔ ከራሴ ምንም ማድረግ አልችልም፤ የምፈርደው በሰማሁት መሠረት ነው፤ የላከኝን ፈቃድ እንጂ የራሴን ፈቃድ ስለማልሻም፣ ፍርዴ ትክክል ነው። 31 እኔው ስለ ራሴ ብመሰክር፣ ምስክርነቴ እውነት አይደለም። 32 ስለ እኔ የሚመሰክር ሌላ አለ፤ እርሱ ስለ እኔ የሚሰጠውም ምስክርነት እውነት እንደ ሆነ ዐውቃለሁ። 33 ወደ ዮሐንስ ልካችሁ ነበር፤ እርሱም ስለ እውነት መስክሮአል፤ 34 ይሁን እንጂ፣ እኔ የሰው ምስክርነት የምቀበል አይደለሁም፤ ነገር ግን ይህን የምናገረው እናንተ እንድትድኑ ነው። 35 ዮሐንስ እየነደደ ብርሃን የሚሰጥ መብራት ነበረ፤ እናንተም ለጥቂት ጊዜ በብርሃኑ ሐሤት ልታደርጉ ፈለጋችሁ። 36 እኔ ያለኝ ምስክርነት ግን ከዮሐንስ ምስክርነት ይበልጣል፡፡ አብ እንድፈጽመው የሰጠኝ፣ እኔም እየሠራሁት ያለሁት ሥራ አብ እንደ ላከኝ ይመሰክራል። 37 የላከኝ አብ እርሱ ስለ እኔ መስክሮአል፤ እናንተም ከቶ ድምፁን አልሰማችሁም፤ መልኩንም አላያችሁም፤ 38 እርሱ በላከው አላመናችሁምና ቃሉ በእናንተ አይኖርም። 39 በእነርሱ የዘላለምን ሕይወት የምታገኙ ስለሚመስላችሁ፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን ትመረምራላችሁ፤ እነርሱም ስለ እኔ ይመሰክራሉ፤ 40 እናንተ ወደ እኔ መጥታችሁ ሕይወት ማግኘት አትፈልጉም። 41 እኔ ከሰው ክብር አልቀበልም፤ 42 ነገር ግን የእግዚአብሔር ፍቅር በእናንተ ውስጥ እንደሌለ ዐውቃለሁ። 43 እኔ በአባቴ ስም መጥቼ አልተቀበላችሁኝም፤ ሌላው በራሱ ስም ቢመጣ ግን ትቀበሉታላችሁ። 44 እናንተ አንዳችሁ ከሌላችሁ ክብር የምትቀበሉ፣ ነገር ግን ከአንዱ አምላክ የሚመጣውን ክብር የማትሹ ከሆነ፣ እንዴት ልታምኑ ትችላላችሁ? 45 በአብ ፊት የምከሳችሁ እኔ አልምሰላችሁ፤ የሚከሳችሁ ሌላ አለ እርሱም ተስፋ ያደረጋችሁበት ሙሴ ነው። 46 ሙሴን ብታምኑ ኖሮ፣ እኔን ባመናችሁ ነበር፤ ምክንያቱም እርሱም የጻፈው ስለ እኔ ነው። 47 ታዲያ እርሱ የጻፈውን ካላመናችሁ፣ ቃሌን እንዴት ታምናላችሁ?»
በታሪኩ ውስጥ ቀጣዩ ክስተት ይህ ነው ፣ ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም በመሄድ ሰው ፈወሰ ፡፡ እነዚህ ጥቅሶች የታሪኩን መቼት በተመለከተ ዳራ መረጃን ይሰጣሉ ፡፡
ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስ የባለስልጣንን ልጅ ከፈወሰ በኋላ ነው ፡፡ ይህንን በዮሐንስ 22 እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ።
“አይሁዶች በዓል ያከብሩ ነበር”
ኢየሩሳሌም በኮረብታማ አናት ላይ ትገኛለች። ወደ ኢየሩሳሌም የሚወስዱ መንገዶች ወደ ትናንሽ ኮረብታዎች ወጡ ፡፡ በኮረብታ ላይ ከመራመድ ይልቅ ቋንቋዎ ወደ ኮረብታ ለመውጣት የተለየ ቃል ካለው እዚህ ሊጠቀሙበት ይችላሉ ፡፡
ይህ ሰዎች በውሃ የሞሉበት መሬት ነበር ፡፡ ገንዳዎቹን አንዳንድ ጊዜ በወጥ ቤቶቹ ወይም በሌሎች የድንጋይ ሥራዎች ያገ theyቸው ነበር ፡፡
"ቤተሳይዳ" ማለት የምህረት ቤት ማለት ነው
ቢያንስ አንድ ግድግዳ ያጣና ከህንፃዎች ጋር ተያይዞ የተሠራ ጣሪያ
"ብዙ ሰዎች"
ቁጥር 5 በኩሬው አጠገብ ያለውን ሰው ወደ ታሪኩ ያስተዋውቃል።
የቤተሳይዳ ገንዳ ጋር
38 ዓመት
"እሱ ተረዳ" ወይንም "እሱ ገባው"
እዚህ “ጌታየ” የሚለው ቃል የትህትና መጠሪያ መልክ ይዟል።
ይህ በገባ ቅርጸት ሊተረጎም ይችላል ፡፡ አት: - “መልአክ ውሃውን ሲያንቀሳቅስ”
ይህ ሰዎች በውሃ የሞሉበት መሬት ነበር ፡፡ ገንዳዎቹን አንዳንድ ጊዜ በወጥ ቤቶቹ ወይም በሌሎች የድንጋይ ሥራዎች ያገinedቸው ነበር ፡፡ በ 5፡1 ውስጥ “ገንዳ” እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
"ሰውየው እንደገና ጤናማ ሆነ"
"ያ ቀን ደግሞ የእግዚአብሔር የእረፍት ቀን ነበር"
ለጀርባ መረጃ ትኩረትን ለመሳብ እዚህ “ደግሞ” ጥቅም ላይ ውሏል። ይህ ክስተት በሰንበት መያዙን የሚያጎላ ነው።
በሰንበት አልጋውን ተሸክሞ ሰውየውን ሲመለከቱ አይሁዶች (በተለይም የአይሁድ መሪዎች) ተቆጡ ፡፡
“የእግዚአብሔር የእረፍት ቀን ነው”
"ጤናማ ያደረገኝ ያ ሰውዬ"
“የአይሁድ መሪዎች የተፈወሰውን ሰው ጠየቁ”
"ኢየሱስ የፈወሰውን ሰው አገኘው"
ለሚቀጥሉት ቃላት ትኩረት ለመሳብ “ተመልከት” የሚለው ቃል እዚህ ጥቅም ላይ ውሏል ፡፡
ዮሐንስ አሁን የአይሁድ መሪዎች ለኢየሱስ የነበራቸውን ማጠቃለያ መግለጫ “አሁን” የሚል ነው ፡፡
ይህ ሌሎች ሰዎችን ለማገልገል የተደረገውን ማንኛውንም ጨምሮ የጉልበት ሥራን ያመለክታል ፡፡
እዚህ ላይ “አይሁዶች” “የአይሁድ መሪዎችን” የሚወክል መመርመሪያ ነው ፡፡ አት: - “የአይሁድ መሪዎች”
እርሱም “እንደ እግዚአብሔር ነው” ወይም “እንደ እግዚአብሔር ባለ ብዙ ስልጣን” ማለቱ ፡፡
ኢየሱስ ለአይሁድ መሪዎች መናገሩን ቀጠለ ፡፡
በ 1፡49 ላይ እንደተረጎማችሁት ተርጉሙት
"ትገረማላችሁ" ወይም "ትደነግጣላችሁ"
“ለ” የሚለው ቃል ንፅፅርን ያሳያል። የእግዚአብሔር ልጅ (እግዚአብሔር ወልድ) እግዚአብሔር አብ እንደሚሰጥ ሕይወት ይሰጣል ፡፡
እነዚህ በእግዚአብሔር እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚገልፁ አስፈላጊ አርዕስት ናቸው ፡፡
በ1፡49 ላይ እንደተረጎማችሁት ተርጉሙት
እዚህ “ቃል” የኢየሱስን መልእክት የሚወክል ቃል ነው ፡፡ አት: - “መልእክቴን የሚሰማ”
ይህ በአዎንታዊ ሁኔታ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ንፁህ ሆኖ ይፈረድበታል”
የሚከተለው የሚከተለው አስፈላጊ እና እውነት መሆኑን በቋንቋዎ አፅንኦት በመስጠት ይህንን ይተረጉሙ ፡፡ ይህንን በ1፡49 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
የእግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ድምፅ ሙታንን ከመቃብር ያስነሳል ፡፡
ይህ የኢየሱስ አስፈላጊ መጠሪያ ነው
“ለ” የሚለው ቃል ንፅፅርን ያሳያል። የእግዚአብሔር ልጅ እንደ አብ ሕይወት እንዲሰጥ የእግዚአብሔር ልጅ ኃይል አለው ፡፡
እነዚህ በእግዚአብሔር እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚገልፁ አስፈላጊ አርዕስት ናቸው
ይህ መንፈሳዊ ሕይወት ማለት ነው
የእግዚአብሔር ልጅ የእግዚአብሔር አብ ለመፍረድ ስልጣን አለው ፡፡
“ይህ” ኢየሱስ ፣ የሰው ልጅ እንደመሆኑ ፣ የዘላለምን ሕይወት የመስጠት እና ፍርድን የማስፈፀም ኃይል እንዳለው ያሳያል።
"ድሜጼን ይሰማሉ"
“እሱ” የሚለው ቃል እግዚአብሔር አብን ያመለክታል ፡፡
ስለ እኔ ስለ ሰዎች የሚናገር ሌላ ሰው አለ ”
ይህ የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ነው ፡፡
ስለ እኔ የሚናገረው ሁሉ እውነት ነው ”
“የሰዎች ምስክርነት አያስፈልገኝም”
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “ስለዚህ እግዚአብሔር ሊያድንህ ይችላል”
እዚህ “አምፖል” ዘይቤ ነው ፡፡ ዮሐንስ የእግዚአብሔር መብራት ቅድስት ብርሃንን እንደሚሰጥ በተመሳሳይ መንገድ አሳይቷል ፡፡ አት-ዮሐንስ “የሚነድና የሚያበራ መብራት ነበር”
እግዚአብሔር አብ እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስን ወደ ምድር ልኮታል ፡፡ ኢየሱስ አብ እንዲያከናውን የሰጠውን ኢየሱስ ፈጸመ ፡፡
ተለጣፊው ተውላጠ ስም “ራሱ” አፅንኦት የሰጠው አብን እንጂ ያነሰ አስፈላጊ ያልሆነ መሰከረ ፡፡
ይህ ለእግዚአብሔር ዋና መጠሪያ ነው
እዚህ ላይ ኢየሱስ ተዓምራቶቹ ስለ እርሱ “ይመሠክራሉ” ወይም “ለህዝቡ ይናገሩ” ብሏል ፡፡ አትቲ: - "እኔ የማደርጋት እግዚአብሔር የላከኝ ሰዎችን ያሳያል"
“ካነበብካቸው የዘላለም ሕይወት ታገኛለህ” ወይም “ቅዱሳት መጻሕፍት የዘላለም ሕይወት እንዴት ማግኘት እንደምትችል ይነግሩሃል”
"መልዕክቴን ለማመን እምቢ አላችሁ"
"መቀበል"
ይህ ማለት 1) “በእውነት እግዚአብሔርን አትወዱም” ወይም 2) “በእውነት የእግዚአብሔርን ፍቅር አልተቀበሉም” ማለት ነው ፡፡
እዚህ ላይ “ስም” የሚለው ቃል የእግዚአብሔርን ኃይል እና ስልጣንን የሚያመላክት ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - “እኔ በአባቴ ሥልጣን መጥቻለሁ” (UDB) ፡፡
ይህ የእግዚአብሔር አስፈላጊ መጠሪያ ነው።
“ስም” የሚለው ቃል ስልጣንን የሚወክል ስም ነው ፡፡ አት: - “በገዛ ሥልጣኑ ቢመጣ”
ይህ ማስታወሻ አፅን .ትን ለመጨመር በጥያቄ መልክ ይታያል። አት: - "ክብርን በመቀበልዎ ማመን የሚቻልበት ምንም መንገድ የለም ... እግዚአብሔር!"
ሙሴ እዚህ ላይ ለሕጉ የቆመ ምሳሌ ነው ፡፡ “በሙሴ ተስፋ ባደረግህበት ሕግ በሙሴ አንተን ይወቅሳል”
ይህ ማስታወሻ አፅን .ት ለመስጠት በጥያቄ መልክ መልክ ይታያል። አት: - “ጽሑፎቹን አታምኑም ፣ ስለዚህ ቃሌን በጭራሽ አታምኑም!”
1 ከዚህ በኋላ ኢየሱስ የጥብርያዶስ ባሕር ወደሚባለው ወደ ገሊላ ባሕር ማዶ ተሻገረ፡፡ 2 ብዙ ሰዎች ሕመምተኞችን በመፈወስ ያደረጋቸውን ተአምራት ስላዩ ተከተሉት፡፡ 3 ኢየሱስ ወደ ተራራ ወጥቶ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር በዚያ ተቀመጠ፡፡ 4 የአይሁድ የፋሲካ በዓልም ተቃርቦ ነበር፡፡ 5 ኢየሱስ ብዙ ሕዝብ ወደ እርሱ ሲመጣ ባየ ጊዜ፣ ፊልጶስን፣ ‹‹ይህ ሁሉ ሕዝብ እንዲበላ እንጀራ ከየት እንግዛ?›› አለው፡፡ 6 ኢየሱስ ይህን ያለው ፊልጶስን ሊፈትን ነበር እንጂ፣ እርሱ ራሱ ሊያደርግ ያሰበውን ያውቅ ነበር፡፡ 7 ፊልጶስ፣ ‹‹ይህ ለእያንዳንዱ ሰው ቍራሽ እንዲደርሰው የሁለት መቶ ዲናር እንጀራ እንኳ ብንገዛ አይበቃም›› አለ፡፡ 8 ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ፣ የስምዖን ጴጥሮስ ወንድም የሆነው እንድርያስም ኢየሱስን፣ 9 ‹‹አምስት የገብስ እንጀራና ሁለት ዓሣ የያዘ አንድ ልጅ እዚህ አለ፤ ነገር ግን ይህ ለዚህ ሁሉ ሕዝብ ምን ይጠቅማል?›› አለው፡፡ 10 ኢየሱስ፣ ‹‹ሕዝቡ እንዲቀመጡ አድርጉ›› አላቸው፡፡ ስፍራውም በሣር የተሸፈነ ነበር፡፡ ስለዚህ ቍጥራቸው አምስት ሺህ የሚያህል ወንዶች ተቀመጡ፡፡ 11 ከዚያም ኢየሱስ እንጀራውንና ሁለቱን ዓሣ ይዞ ባረከና ለተቀመጡት ዐደለ፡፡ በተመሳሳይ መንገድ ከዓሣውም የሚፈልጉትን ያህል ዐደላቸው፡፡ 12 ሕዝቡ በጠገቡ ጊዜ፣ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን፣ ‹‹አንዳችም እንዳይጣል የተረፈውን ፍርፋሪ ሰብስቡ›› አላቸው፡፡ 13 ስለዚህ ደቀ መዛሙርቱ ሕዝቡ ከበሉ በኋላ የተረፈውን ዐሥራ ሁለት መሶብ ሙሉ የገብስ እንጀራ ፍርፋሪ ሰበሰቡ፡፡ 14 ከዚያም ሕዝቡ ኢየሱስ ያደረገውን ይህን ምልክት ባዩ ጊዜ፣ ‹‹ይህስ በእውነት ወደ ዓለም የሚመጣው ነቢይ ነው›› አሉ፡፡ 15 ኢየሱስም ሊመጡና ይዘው በግድ ሊያነግሡት እንደ ፈለጉ በተረዳ ጊዜ፣ እንደ ገና ለብቻው ወደ ተራራ ጫፍ ወጣ፡፡ 16 በመሸም ጊዜ፣ ደቀ መዛሙርቱ ወደ ባሕሩ ወረዱ፤ 17 በጀልባ ተሳፍረው ወደ ቅፍርናሆም በባሕር ላይ መጓዝ ጀመሩ፡፡ ጊዜው መሽቶ ነበር፤ ኢየሱስም ገና ወደ እነርሱ አልመጣም ነበር፡፡ 18 በዚህ ጊዜ ባሕሩ ከኀይለኛ ነፋስ የተነሣ ይታወክ ነበር፡፡ 19 ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ ሃያ አምስት ወይም ሠላሳ ምዕራፍ ያህል እንደ ቀዘፉ፣ ኢየሱስ በባሕር ላይ እየሄደ እነርሱ ወዳሉበት ጀልባ ሲቃረብ አይተውት ፈሩ፡፡ 20 ይሁን እንጂ እርሱ፣ ‹‹እኔ ነኝ አትፍሩ›› አላቸው፡፡ 21 ከዚያም ጀልባዋ ላይ እንዲወጣ ፈቀዱለት፣ ጀልባዋም ወዲያው ወደሚሄዱበት ስፍራ ደረሰች፡፡ 22 በማግስቱም በማዶ ቆመው የነበሩ ሕዝብ አንድም ጀልባ በባሕሩ ላይ እንዳልነበረ አዩ፤ በዚያ የነበረው አንድ ጀልባ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ያልተሳፈረበት ብቻ ነበር፤ ደቀ መዛሙርቱም ብቻቸውን ከዚያ ሄደው ነበር፡፡ 23 ይሁን እንጂ ጌታ አመስግኖ ሰዎቹን እንጀራ ካበላበት ስፍራ አጠገብ፣ ከጥብርያዶስ የመጡ አንዳንድ ጀልባዎች እዚያ ነበሩ፡፡ 24 ሕዝቡም፣ ኢየሱስም ሆነ ደቀ መዛሙርቱ እዚያ እንዳልነበሩ በተረዱ ጊዜ፣ ራሳቸው በጀልባዎቹ ተሳፍረው ኢየሱስን ፍለጋ ሄዱ፡፡ 25 በባሕሩ ማዶ ኢየሱስን ባገኙት ጊዜ፣ ‹‹መምህር ሆይ፤ ወደዚህ የመጣኸው መቼ ነው?›› አሉት፡፡ 26 ኢየሱስ እንዲህ ሲል መለሰላቸው፤ ‹‹እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ፣ እኔን የምትፈልጉኝ ምልክቶችን ስላያችሁ ሳይሆን፣ እንጀራውን በልታችሁ ስለ ጠገባችሁ ነው፡፡ 27 ለሚጠፋ ምግብ አትሥሩ፤ ይልቁን ወልድ ለሚሰጣችሁ ዘላለም ለሚኖር ሕይወት ሥሩ፤ እግዚአብሔር አብ ማኅተሙን በእርሱ ላይ አትሞአልና፡፡›› 28 ከዚያም፣ ‹‹የእግዚአብሔርን ሥራ እንድንሠራ ምን እናድርግ?›› አሉት፡፡ 29 ኢየሱስ፣ ‹‹የምትሠሩት የእግዚአብሔር ሥራ እርሱ በላከው ማመን ነው›› ብሎ መለሰላቸው፡፡ 30 ስለዚህ እነርሱ እንዲህ አሉት፤ ‹‹አይተን እንድናምንህ ምን ተአምር ትሠራለህ? ምንስ ታደርጋለህ? 31 ‹እንዲበሉ ከሰማይ እንጀራ ሰጣቸው› ተብሎ እንደ ተጻፈ፣ አባቶቻችን በምድረ በዳ መና በሉ፡፡›› 32 ከዚያም ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፤ ‹‹እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ፤ መና እንድትበሉ ከሰማይ የሰጣችሁ ሙሴ አልነበረም፤ ነገር ግን ከሰማይ እውነተኛ እንጀራ የሚሰጣችሁ አባቴ ነው፤ 33 ከሰማይ የሚወርድና ለዓለም ሕይወትን የሚሰጥ የእግዚአብሔር እንጀራ ነውና፡፡›› 34 ስለዚህ፣ ‹‹ጌታ ሆይ፣ ይህን እንጀራ ዘወትር ስጠን›› አሉት፡፡ 35 ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ ‹‹እኔ የሕይወት እንጀራ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ አይራብም፤ በእኔ የሚያምንም ከቶ አይጠማም፡፡ 36 ነገር ግን እኔን አይታችሁ አሁንም ገና ስላላመናችሁብኝ ይህን አልኋችሁ፡፡ 37 አባቴ የሰጠኝ ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል፤ እኔም አባቴ የሰጠኝን ከቶ ወደ ውጭ አላባርርም፡፡ 38 ከሰማይ የወረድሁት የራሴን ፈቃድ ለማድረግ ሳይሆን የላከኝን ፈቃድ ለመፈጸም ነውና፡፡ 39 የላከኝም ፈቃድ፣ እርሱ ከሰጠኝ ሁሉ አንድም ሳይጠፋ፣ በመጨረሻው ቀን እንዳስነሣቸው ነው፡፡ 40 የአባቴ ፈቃድ፣ ወልድን አይቶ በእርሱ ያመነ ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው ነው፡፡ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ፡፡›› 41 ከዚያም የአይሁድ መሪዎች፣ ‹‹እኔ ከሰማይ የወረድሁ የሕይወት እንጀራ ነኝ›› በማለቱ አጕረመረሙበት፡፡ 42 እነርሱ፣ ‹‹ይህ ኢየሱስ የዮሴፍ ልጅ አይደለምን? አባቱንና እናቱንስ የምናውቃቸው አይደሉምን? ታዲያ፣ እንዴት ከሰማይ ወረድሁ ይለናል?›› ተባባሉ፡፡ 43 ኢየሱስ እንዲህ ሲል መለሰላቸው፤ ‹‹እርስ በርስ ማጕረምረማችሁን ተዉት፡፡ 44 አብ ከሳበው በቀር ወደ እኔ የሚመጣ የለም፤ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ፡፡ 45 በነቢያት፣ ‹ሁሉም ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ› ተብሎ እንደ ተጻፈ፣ ከአብ የሰማና የተማረ ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል፡፡ 46 ከእግዚአብሔር ከሆነው በቀር አብን ያየ ማንም የለም፤ እርሱ አብን አይቶታል፡፡ 47 እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ፤ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፡፡ 48 እኔ የሕይወት እንጀራ ነኝ፡፡ 49 አባቶቻችሁ በበረሐ መና በሉ፣ ሞቱም፡፡ 50 ሰው በልቶት እንዳይሞት፣ ከሰማይ የወረደ እንጀራ ይህ ነው፡፡ 51 ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፡፡ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፡፡ ለዓለም ሕይወት እንዲሆነው የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው፡፡›› 52 አይሁድ በዚህ አባባሉ ተቈጥተው፣ ‹‹ይህ ሰው እንዴት እንድንበላ ሥጋውን ሊሰጠን ይችላል?›› በማለት እርስ በርስ ተከራከሩ፡፡ 53 ከዚያም ኢየሱስ፣ ‹‹እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ፤ የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችሁ፣ ደሙንም ካልጠጣችሁ የራሳችሁ የሆነ ሕይወት አይኖራችሁም›› አላቸው፡፡ 54 ‹‹ሥጋዬን የሚበላ፣ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፤ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ፤ 55 ሥጋዬ እውነተኛ መብል፣ ደሜም እውነተኛ መጠጥ ነውና፡፡ 56 ሥጋዬን የሚበላ፣ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል፤ እኔም በእርሱ እኖራለሁ፡፡ 57 ሕያው አብ እንደ ላከኝና እኔ ከአብ የተነሣ እንደምኖር፣ የሚበላኝም ከእኔ የተነሣ ሕያው ይሆናል፡፡ 58 አባቶቻችን በልተውት እንደ ሞቱ ዐይነት ሳይሆን፣ ይህ ከሰማይ የወረደ እንጀራ ነው፡፡ ይህን እንጀራ የበላ ለዘላለም ይኖራል፡፡›› 59 ኢየሱስ ይህን የተናገረው በቅፍርናሆም፣ በምኵራብ ሲያስተምር ነበር፡፡ 60 ከዚያም ከደቀ መዛሙርቱ ብዙዎቹ ይህን ሲሰሙ፣ ‹‹ይህ ጠንካራ ትምህርት ነው፤ ማን ሊቀበለው ይችላል?›› አሉ፡፡ 61 ኢየሱስ በዚህ ማጕረምረማቸውን በገዛ ራሱ ስላወቀ፣ ‹‹ይህ አሰናከላችሁ እንዴ? 62 ታዲያ፣ የሰው ልጅ ቀድሞ ወደ ነበረበት ስፍራ፣ ተመልሶ ወደ ላይ ሲወጣ ብታዩ ምን ልትሉ ነው? 63 ሕይወት የሚሰጠው መንፈስ ነው፤ ሥጋ ለምንም አይጠቅምም፡፡ እኔ የነገርኋችሁ ቃላት መንፈስ ናቸው፤ ሕይወትም ናቸው፡፡ 64 ይሁን እንጂ፣ ከእናንተ መካከል የማያምኑ አንዳንዶች አሉ›› አለ፡፡ ከመጀመሪያው በእርሱ የማያምኑ እነማን እንደ ሆኑና የሚከዳው ማን እንደ ሆነ ያውቅ ነበርና፡፡ 65 ደግሞም፣ ‹‹ከአብ ከተሰጠው በቀር ማንም ወደ እኔ ሊመጣ አይችልም ያልኋችሁ ለዚህ ነው›› አለ፡፡ 66 ከዚህ በኋላ፣ ከደቀ መዛሙርቱ ብዙዎቹ ትተውት ወደ ኋላቸው ተመለሱ፤ አብረውትም አልተጓዙም፡፡ 67 ኢየሱስ ዐሥራ ሁለቱን፣ ‹‹እናንተም ትታችሁኝ ልትሄዱ ትፈልጋላችሁን?›› አላቸው፡፡ 68 ስምዖን ጴጥሮስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፤ ‹‹ጌታ ሆይ፣ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም ሕይወት ቃል አለህ፤ 69 እኛም አምነናል፤ አንድያ የእግዚአብሔር ቅዱስ መሆንህንም ዐወቀናል፡፡›› 70 ኢየሱስ፣ ‹‹እኔ ዐሥራ ሁለታችሁንም መርጫችሁ የለም ወይ? ከእናንተም መካከል አንዱ ዲያብሎስ ነው›› አላቸው፡፡ 71 ይህን ያለው ከዐሥራ ሁለቱ አንዱ ስለ ሆነውና ኋላም ኢየሱስን አሳልፎ ስለ ሰጠው፣ ስለ አስቆሮቱ ስምዖን ልጅ፣ ስለ ይሁዳ ነው፡፡
ይህ የታሪኩ ቀጣይ ክፍል ነው ፡፡ ኢየሱስ ከኢየሩሳሌም ወደ ገሊላ ተጓዘ። ብዙ ሰዎች ወደ ተራራማ መንገድ ተከትለውታል ፡፡ እነዚህ ቁጥሮች የዚህን የታሪኩን ክፍል መቼት ይናገራሉ ፡፡
"እነዚህ ነገሮች" የሚለው ሃረግ የሚመለከተው በ5፡1 ባሉት ሁኔታዎች ነው።
በጥቅሱ ውስጥ ኢየሱስ በጀልባ እንደተጓዘ እና ደቀመዛሙርቱን ከእርሱ ጋር እንደወሰደው ነው ፡፡ አትቲ: - "ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር በጀልባ በጀልባ ተጓዘ"
"ብዙ ሰዎች"
ይህ የሚያመለክተው እግዚአብሔር በሁሉ ነገር ላይ ሁሉ የበላይ ነው ፡፡
በታሪኩ ውስጥ ያለው ተግባር በቁጥር 5 ይጀምራል ፡
ዮሐንስ ታሪኩ የተከናወኑበትን ጊዜ ዳራ ለመናገር በታሪኩ ውስጥ ስለተከናወኑት ሁነቶች መናገር በአጭሩ ያቆማል ፡፡
ኢየሱስ ዳቦ ከየት እንደሚገዛ ፊል ፊሊጶስን የጠየቀበትን ምክንያት ዮሐንስ በታሪኩ ውስጥ ስለተከናወኑት ሁነቶች መናገር በአጭሩ ያቆማል ፡፡
“ዲናርየስ” የሚለው ቃል የ“ዲናር” ብዙ ነው “የሁለት መቶ ቀን ደሞዝ የሚያስከፍለው ዳቦ መጠን” ፡፡
አምስት የገብስ የገብስ ዳቦ። ገብስ የተለመደ እህል ነበር።
ይህ አስተያየት ሁሉንም ሰው ለመመገብ የሚያስችል በቂ ምግብ የላቸውም የሚል ለማጉላት በጥያቄ መልክ ይታያል ፡፡ አት: - “እነዚህ ጥቂት ዳቦዎች እና አሳዎች ብዙ ሰዎችን ለመመገብ በቂ አይደሉም!”
"ተኙ"
ይህ ክስተት ስለተከናወነበት ስፍራ ዳራ ለመስጠት ዮሐንስ ዮሐንስ በታሪኩ ውስጥ ስለተከናወኑት ሁነቶች በአጭሩ መናገሩ አቁሟል ፡፡
ምንም እንኳን ህዝቡ ሴቶችን እና ሕፃናትን ያካተተ (6 4) ቢሆንም ፣ እዚህ ላይ ዮሐንስ ወንዶቹን እየቆጠረ ነው ፡፡
ኢየሱስ ወደ እግዚአብሔር አብ ጸለየ እናም ዓሳውና ዳቦውን አመሰገነ ፡፡
ኢየሱስ ከሕዝቡ ተለይቷል። ኢየሱስ በተራራ ላይ ስለ መሰማቱ ስለ ተናገረው የታሪክ ክፍል መጨረሻ ይህ ነው ፡፡
"ደቀ መዛሙርቱ ተሰበሰቡ"
ሰው ያልበላው ምግብ
ኢየሱስ አምስት ሺህ ሰዎችን በአምስት የገብስ ዳቦና ሁለት ዓሣ መመገቡ
ወደ ዓለም ይመጣል ሙሴ የተናገረው ልዩ ነቢይ
በታሪኩ ውስጥ ይህ ቀጣዩ ክስተት ነው ፡፡ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት በጀልባ ወደ ሐይቁ ሄዱ።
ይህ የበስተጀርባ መረጃ መሆኑን ለማሳየት የእርስዎን ቋንቋ መንገድ ይጠቀሙ።
ጀልባዎች ብዙውን ጊዜ በእያንዳንዱ ጎን አብረው አብራሪዎች የሚሠሩ ሁለት ፣ አራት ወይም ስድስት ሰዎች ነበሩ። ባህልዎ ጀልባ ወደ ብዙ የውሃ አካላት እንዲሻገር ለማድረግ የተለያዩ መንገዶች ሊኖሩት ይችላል ፡፡
አምስት ወይም ሰላሳ ስታድየም - “ስታዲየም” 185 ሜትር ነው ፡፡ አት: - “አምስት ወይም ስድስት ኪሎሜትሮች”
"መፍራታችሁን አቁሙ"
ኢየሱስ ወደ ጀልባው እንደገባ የሚያመለክተው ነው ፡፡ አትቲ: - “በደስታ ወደ ጀልባው ተቀብለውታል”
"የገሊላ ባህር"
ይህ የጀርባ መረጃ መሆኑን ለማሳየት የርስዎን ቋንቋ ይጠቀሙ።
እዚህ ፣ ጆን ተጨማሪ የበስተጀርባ መረጃዎችን ይሰጣል ፡፡ በሚቀጥለው ቀን ኢየሱስ ሕዝቡን ከሰበሰበ በኋላ ከጥብርያዶስ ሰዎች ጋር የነበሩ አንዳንድ ጀልባዎች ኢየሱስን ለማየት መጡ ፡፡ ሆኖም ፣ ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱ ከዚያ በፊት ሌሊቱን ለቀዋል ፡፡
ሰዎቹ ኢየሱስን ለማግኘት ወደ ቅፍርናሆም ሄዱ ፡፡ ባዩት ጊዜ ጥያቄዎች ይጠይቁ ጀመር ፡፡
በ1፡49 ላይ እንደተረጎማችሁት ተርጉሙት
1 ከዚህ በኋላ ኢየሱስ አይሁድ ሊገድሉት ይፈልጉ ስለ ነበር፣ ወደ ይሁዳ መሄድ አልፈለገም፤ ስለዚህ እዚያው በገሊላ ውስጥ ይመላለስ ነበር፡፡ 2 የአይሁድ የዳስ በዓል የሚከበርበትም ጊዜ ተቃርቦ ነበር፡፡ 3 ስለዚህ ወንድሞቹ እንዲህ አሉት፤ ‹‹ተነሥተህ ከዚህ ስፍራ ወደ ይሁዳ አውራጃ ሂድ፤ ደቀ መዛሙርትህም ደግሞ አንተ የምትሠራውን ሥራ ይዩ፡፡ 4 በሕዝብ ፊት መታወቅ የሚፈልግ ሰው የሚሠራውን ሥራ በድብቅ አያደርግም፡፡ እነዚህን ነገሮች የምታደርግ ከሆነ፣ ራስህን ለዓለም አሳይ፡፡›› 5 ምክንያቱም ወንድሞቹ እንኳ ገና አላመኑበትም ነበር፡፡ 6 ስለዚህ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፤ ‹‹ጊዜዬ ገና ነው፡፡ ለእናንተማ ጊዜው ሁሉ የተመቸ ነው፡፡ 7 ዓለም እናንተን ሊጠላችሁ አይችልም፡፡ እኔን ግን በክፉ ሥራው ስለምመሰክርበት፣ ይጠላኛል፡፡ 8 እናንተ ወደ በዓሉ ውጡ፤ እኔ ግን ጊዜዬ ገና ስላልደረሰ፣ ወደ በዓሉ አልሄድም፡፡›› 9 እርሱ ይህን ካላቸው በኋላ፣ በገሊላ ቈየ፡፡ 10 ነገር ግን ወንድሞቹ ወደ በዓሉ ከሄዱ በኋላ እርሱም በግልጽ ሳይሆን በስውር ወደዚያው ሄደ፡፡ 11 አይሁድ በበዓሉ ላይ ሊፈልጉት ሄደው፣ ‹‹እርሱ ያለው የት ነው?›› አሉ፡፡ 12 በሕዝቡም መካከል ብዙ ውይይት ተነሥቶ ነበር፡፡ አንዳንዶቹ፣ ‹‹እርሱ ጥሩ ሰው ነው›› አሉ፤ ሌሎቹም፣ ‹‹አይደለም፣ ሕዝቡን እያሳተ ነው›› አሉ፡፡ 13 ይሁን እንጂ፣ አይሁድን ስለ ፈሩ፣ ስለ እርሱ በግልጽ የተናገረ ማንም አልነበረም፡፡ 14 በበዓሉ አጋማሽ ላይ፣ ኢየሱስ ወደ ቤተ መቅደስ ወጥቶ ማስተማር ጀመረ፡፡ 15 አይሁድም እየተደነቁ፣ ‹‹ይህ ሰው እንዴት ይህን ሁሉ ዐወቀ? ትምህርት እንኳ አልተማረም›› ይሉ ነበር፡፡ 16 ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፤ ‹‹የማስተምረው ከራሴ አይደለም፤ ነገር ግን ትምህርቴ ከላከኝ ነው›፡፡ 17 ማንም የእርሱን ፈቃድ ለማድረግ ቢፈልግ፣ ይህ ትምህርት ከእግዚአብሔር የመጣ መሆኑን ወይም ከራሴ የምናገር መሆኑን ያውቃል፡፡ 18 ከራሱ የሚናገር የራሱን ክብር ይፈልጋል፤ የላከውን ክብር የሚፈልግ ግን እውነተኛ ነው፤ ሐሰትም የለበትም፡፡ 19 ሙሴ ሕግ ሰጥቶአችሁ አልነበረምን? ነገር ግን ከእናንተ ሕጉን የሚጠብቅ አንድም ሰው የለም፡፡ ለመሆኑ፣ ልትገድሉኝ የምትፈልጉት ለምንድን ነው?›› 20 ሕዝቡ፣ ‹‹ጋኔን አለብህ፤ አንተን ማን ሊገድል ይፈልጋል?›› ብለው መለሱ፡፡ 21 ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፤ ‹‹አንድን ሥራ በመሥራቴ ሁላችሁም በዚህ ትደነቃላችሁ፡፡ 22 ሙሴ ግዝረትን ሰጣችሁ፤ ይህም የመጣው ከአባቶች እንጂ ከሙሴ አልነበረም፤ ስለሆነም፣ በሰንበት ቀን ሰውን ትገርዛላችሁ፡፡ 23 ሰውን በሰንበት ቀን ስትገርዙ የሙሴ ሕግ የማይሻር ከሆነ፣ እኔ በሰንበት ቀን የሰውን መላ አካል ስላዳንሁ ለምን በእኔ ላይ ትቈጣላችሁ? 24 መልክ በማየት ሳይሆን በቅንነት ፍረዱ፡፡›› 25 ከኢየሩሳሌም ከመጡት አንዳንዶቹ እንዲህ አሉ፤ ‹‹ሊገድሉት የሚፈልጉት ይህን ሰው አልነበረም? 26 ተመልከቱ፤ እንዲህ በግልጽ እየተናገረ ምንም አይሉትም፡፡ ገዦቹ እርሱ በትክክል ክርስቶስ መሆኑን ዐውቀው ይሆን? 27 እኛ ግን ይህ ሰው ከየት እንደ መጣ እናውቃለን፤ ክርስቶስ ሲመጣ ግን ማንም ከየት እንደ መጣ አያውቅም፡፡›› 28 ኢየሱስ በቤተ መቅደስ ሲያስተምር ድምፁን ከፍ አድርጎ እንዲህ አለ፤ ‹‹እኔን ታውቁኛላችሁ፤ ከየት እንደ መጣሁም ታውቃላችሁ፤ ሆኖም በራሴ አልመጣሁም፤ የላከኝ ግን እውነተኛ ነው፤ እርሱን ደግሞ እናንተ አታውቁትም፡፡ 29 እኔ ከእርሱ ዘንድ ስለ መጣሁ፣ ዐውቀዋለሁ፤ የላከኝም እርሱ ነው፡፡›› 30 እነርሱም በዚህ ጊዜ ሊይዙት ሞከሩ፤ ነገር ግን የነካው አንድም ሰው አልነበረም፤ ምክንያቱም የተወሰነለት ሰዓት ገና ነበር፡፡ 31 ይሁን እንጂ፣ በሕዝቡ መካከል ብዙዎች በእርሱ አመኑ፡፡ ያመኑትም፣ ‹‹ክርስቶስ ሲመጣ ይህ ሰው ከሠራው ተአምር የሚበልጥ ሊሠራ ይችላልን?›› አሉ፡፡ 32 ፈሪሳውያን ሕዝቡ ስለ ኢየሱስ በሹክሹክታ የሚያወሩትን ሰሙ፤ የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያንም ሊያስይዙት የጥበቃ ሰዎችን ላኩበት፡፡ 33 ኢየሱስ፣ ‹‹ለጥቂት ጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ፤ ከዚያም ወደ ላከኝ እሄዳለሁ፡፡ 34 ትፈልጉኛላችሁ፤ ግን አታገኙኝም፡፡ እናንተ ወደምሄድበት መምጣት አትችሉም›› አላቸው፡፡ 35 ስለዚህ አይሁድ እርስ በርሳቸው እንዲህ ተባባሉ፤ ‹‹ይህ ሰው እንዳናገኘው ወዴት ሊሄድ ነው? ተበትነው በግሪክ ወዳሉት ሰዎች ሄዶ እነርሱን ሊያስተምር ይሆን? 36 ‹ትፈልጉኛላችሁ፤ ግን አታገኙኝም፡፡ እናንተ እኔ ወደምሄድበት መምጣት አትችሉም› ያለውስ ቃል ምን ማለት ነው?›› 37 በታላቁ የበዓሉ ቀን፣ በመጨረሻው ቀን፣ ኢየሱስ ቆሞ ድምፁን ከፍ በማድረግ፣ ‹‹የተጠማ ማንም ቢኖር፣ ወደ እኔ መጥቶ ይጠጣ፡፡ 38 ቅዱሳት መጻሕፍት እንደ ተናገሩት፣ በእኔ የሚያምን የሕይወት ውሃ ወንዝ ከውስጡ ይፈልቃል›› አለ፡፡ 39 ይህን ያለው ግን በእርሱ የሚያምኑት ወደ ፊት ስለሚቀበሉት፣ መንፈስ ቅዱስ ነው፤ ኢየሱስ ገና ስላልከበረ፣ መንፈስ ቅዱስ ገና አልተሰጠም ነበር፡፡ 40 ከሕዝቡ አንዳንዶቹ ይህን ቃል ሲሰሙ፣ ‹‹ይህ በእርግጥ ነቢዩ ነው›› አሉ፡፡ 41 ሌሎቹ ደግሞ፣ ‹‹እርሱ ክርስቶስ ነው›› አሉ፡፡ አንዳንዶቹ ግን፣ ‹‹ክርስቶስ ከገሊላ እንዴት ይመጣል! 42 ቅዱሳት መጻሕፍት ክርስቶስ ከዳዊት ዘር፣ የዳዊት ከተማ ከሆነችው ከቤተ ልሔም እንደሚመጣ ተናግረው የለምን?›› አሉ፡፡ 43 ስለዚህ እርሱን በተመለከተ በመካከለቸው መለያየት ተከሠተ፡፡ 44 ከእነርሱ አንዳንዶቹ ሊይዙት ፈልገው ነበር፤ ነገር ግን ማንም አልነካውም፡፡ 45 ከዚያም የጥበቃ ሰዎቹ ወደ ካህናት አለቆችና ወደ ፈሪሳውያን ተመልሰው መጡ፤ የላኳቸውም፣ ‹‹ለምንድን ነው ይዛችሁ ያላመጣችሁት?›› አሏቸው፡፡ 46 የጥበቃ ሰዎቹ፣ ‹‹ከዚህ ቀደም እንደዚህ የተናገረ አልነበረም›› አሏቸው፡፡ 47 ፈሪሳውያንም እንዲህ አሏቸው፤ ‹‹እናንተም ሳታችሁን? 48 ከገዦቹ ወይም ከፈሪሳውያን በእርሱ ያመነ አለ? 49 ነገር ግን ሕጉን የማያውቅ ይህ ሕዝብ የተረገመ ነው፡፡›› 50 ከፈሪሳውያን አንዱ፣ ከዚህ በፊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረው ኒቆዲሞስ፣ 51 ‹‹መጀመሪያ ከሰውየው ሳይሰማና የሚሠራውን ሳያውቅ፣ የእኛ ሕግ በሰው ላይ ይፈርዳልን?›› አላቸው፡፡ 52 እነርሱ፣ ‹‹አንተም ደግሞ ከገሊላ ነህ ወይ? ነቢይ ከገሊላ እንደማይመጣ መርምረህ ዕወቅ›› አሉት፡፡ 53 ከዚያም እያንዳንዱ ሰው ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ (*53 የጥንት ቅጆች በዮሐንስ 7፡53-8፡11 ላይ ያለውን ክፍል አያካትቱም፡፡)
1 ኢየሱስ ወደ ደብረ ዘይት ሄደ። 2 ጠዋት በማለዳ ተመልሶ ወደ ቤተ መቅደስ መጣ፤ ሕዝቡም ሁሉ ወደ እርሱ መጡ፤ እርሱም ተቀምጦ አስተማራቸው። 3 የሕግ መምህራንና ፈሪሳውያንም ስታመነዝር የተያዘችን ሴት አምጥተው፤ በመካከላቸው አቆሟት። 4 ከዚያም ኢየሱስን እንዲህ አሉት፤ «መምህር ሆይ፣ ይህች ሴት ስታመነዝር እጅ ከፍንጅ የተያዘች ናት፤ 5 ሙሴ በሕጉ እንዲህ ያሉትን በድንጋይ እንድንወግር አዞናል፤ አንተስ ስለ እርሷ ምን ትላለህ?» 6 ይህን ያሉት እርሱን ወጥመድ ውስጥ ለማስገባትና ለመክሰስ ፈልገው ነው፤ ኢየሱስ ግን ጎንበስ ብሎ በጣቱ መሬት ላይ ጻፈ። 7 ጥያቄ ማቅረባቸውን በቀጠሉ ጊዜም፣ ተነሥቶ ቆመና፣ “ከእናንተ መካከል ኃጢአት የሌለበት ሰው በመጀመሪያ ይውገራት” አላቸው። 8 ዳግመኛም ጐንበስ ብሎ፣ በጣቱ መሬት ላይ ጻፈ። 9 ይህንም በሰሙ ጊዜ፣ ከታላቅ ጀምረው አንድ ባንድ ወጥተው ሄዱ። በመጨረሻ ኢየሱስ በመካከላቸው ቆማ ከነበረችው ሴት ጋር ለብቻው ቀረ። 10 ኢየሱስ ተነሥቶ በመቆም፣ “አንቺ ሴት፤ የከሰሱሽ ሰዎች የት ናቸው? አንድም የፈረደብሽ የለም?” አላት። 11 እርሷም፣ “ጌታ ሆይ፣ አንድም የለም” አለች። ኢየሱስ፣ “እኔም አልፈርድብሽም፤ ሂጂ ከአሁን በኋላ ግን ደግመሽ ኀጢአት አትሥሪ” አላት። 12 ደግሞም ኢየሱስ ሕዝቡን፣ “እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ ቢኖር የሕይወት ብርሃን ያገኛል እንጂ፣ በጨለማ አይመላለስም” አላቸው። 13 ፈሪሳውያንም፣ “አንተው ስለ ራስህ ስለምትመሰክር፤ ምስክርነትህ እውነት አይደለም” አሉት። 14 ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰላቸው፤ “እኔ ስለ ራሴ ብመሰክር እንኳ ምስክርነቴ እውነት ነው። ከየት እንደ መጣሁ፣ ወዴትም እንደምሄድ ዐውቃለሁ፤ እናንተ ግን እኔ ከየት እንደ መጣሁ ወይም ወዴት እንደምሄድ አታውቁም። 15 እናንተ በሥጋዊ ዐይን ትፈርዳላችሁ፤ እኔ በማንም አልፈርድም። 16 ብፈርድም እንኳ፣ ብቻዬን አይደለሁም፤ ከላከኝ አብ ጋር ስለ ሆንሁ፣ ፍርዴ እውነት ነው። 17 አዎን፤ በሕጋችሁ የሁለት ሰዎች ምስክርነት እውነት እንደ ሆነ ተጽፎአል። 18 እኔ ስለ ራሴ እመሰክራለሁ፤ የላከኝም አብ ስለ እኔ ይመሰክራል።” 19 እነርሱም፣ “አባትህ የት ነው ያለው?” አሉት። ኢየሱስም፣ “እናንተ እኔንም ሆነ አባቴን አታውቁንም፤ እኔን ብታውቁኝ ኖሮ አባቴንም ባወቃችሁት ነበር” አላቸው። 20 ይህንም የተናገረው በቤተ መቅደሱ ግምጃ ቤት አጠገብ ሆኖ ሲያስተምር ነበር፤ ሆኖም ሰዓቱ ገና ስላልደረሰ፣ ማንም አልያዘውም። 21 ደግሞም፣ “እኔ ተለይቻችሁ እሄዳለሁ፤ እናንተም ትፈልጉኛላችሁ፤ ግን በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ። እኔ ወደምሄድበት መምጣት አትችሉም” አላቸው። 22 አይሁድም፣ “ይህ 'እኔ ወደምሄድበት መምጣት አትችሉም' የሚለው ራሱን ሊገድል ዐስቦ ይሆን?” አሉ። 23 ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፤ “እናንተ ከታች ናችሁ፤ እኔ ግን ከላይ ነኝ። እናንተ ከዚህ ዓለም ናችሁ፤ እኔ ግን ከዚህ ዓለም አይደለሁም። 24 በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ ያልኋችሁ ለዚህ ነው። ምክንያቱም እኔ ነኝ ስላችሁ ካላመናችሁ፣ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ።” 25 እነርሱም፣ “ለመሆኑ፣ አንተ ማን ነህ?” አሉት። ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤”ከመጀመሪያው እንደ ነገርኋችሁ ነኝ። 26 ብዙ የምናገረውና ስለ እናንተም የምፈርደው አለኝ። ይሁን እንጂ የላከኝ እርሱ እውነተኛ ነው፤ እኔም ከእርሱ የሰማሁትን፣ ያንኑ ለዓለም እናገራለሁ።” 27 እነርሱ ግን ስለ አብ እየነገራቸው እንደ ነበር አልተረዱም። 28 ኢየሱስ እንዲህ አለ፤ “የሰውን ልጅ ወደ ላይ ከፍ ስታደርጉት፣ በዚያን ጊዜ እኔው እንደ ሆንሁና ከራሴ አንድም ነገር እንደማላደርግ ታውቃላችሁ። አብ እንዳስተማረኝ ይህን እናገራለሁ። 29 የላከኝ እርሱ ከእኔ ጋር ነው፤ ብቻዬንም አልተወኝም፤ እኔ ሁልጊዜ እርሱን ደስ የሚያሰኘውን ነገር አደርጋለሁና።” 30 ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች በተናገረ ጊዜ ብዙ ሰዎች በእርሱ አመኑ። 31 ኢየሱስ በእርሱ ያመኑትን አይሁድ፣ “እናንተ በቃሌ ብትኖሩ፣ በርግጥ ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤ 32 እውነትን ታውቃላችሁ፤ እውነትም ነጻ ያወጣችኋል” አላቸው። 33 እነርሱም፣ “እኛ የአብርሃም ዘሮች ነን፤ የማንም ባሪያ ሆነን አናውቅም፤ ታዲያ እንዴት ‘ነጻ ትወጣላችሁ’ ትለናለህ?” አሉት። 34 ኢየሱስ እንዲህ ሲል መለሰላቸው፤ “እውነት እላችኋለሁ፤ ኃጢአት የሚሠራ ሁሉ የኃጢአት ባሪያ ነው። 35 ባሪያ ለዘለቄታ በቤት አይኖርም፤ ልጅ ግን ለዘለቄታ ይኖራል። 36 ስለዚህ ልጁ ነጻ ካወጣችሁ፣ በርግጥ ነጻ ትወጣላችሁ። 37 የአብርሃም ዘር መሆናችሁን ዐውቃለሁ፤ ቃሌን ስላልተቀበላችሁ፣ ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ። 38 አባቴ ጋ ያየሁትን እናገራለሁ፤ እናንተም ደግሞ ከአባታችሁ የሰማችሁትን ታደርጋላችሁ።” 39 እነርሱም መልሰው፣ “አባታችንስ አብርሃም ነው” አሉት። ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፤ “የአብርሃም ልጆችስ ብትሆኑ ኖሮ፣ የአብርሃምን ሥራ በሠራችሁ ነበር። 40 አሁን ግን ከእግዚአብሔር የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን ሰው ለመግደል ትፈልጋላችሁ። አብርሃምኮ ይህን አላደረገም። 41 እናንተ ግን የአባታችሁን ሥራ ትሠራላችሁ።” እነርሱም፣ “እኛ በዝሙት የተወለድን አይደለንም፤ አንድ አባት እግዚአብሔር አለን” አሉት። 42 ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ “እግዚአብሔር አባታችሁ ቢሆን ኖሮ፣ እኔ ከእግዚአብሔር ወጥቼ ስለ መጣሁ፣ በወደዳችሁኝ ነበር፤ በራሴም ፈቃድ አልመጣሁም፤ ነገር ግን እርሱ ላከኝ። 43 ቃሌን የማትረዱት ለምንድን ነው? ምክንያቱም ቃሌን መስማት ስለማትችሉ ነው። 44 እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ፤ የአባታችሁንም ፍላጎት ለማድረግ ትመኛላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያውም ነፍሰ ገዳይ ነበር፤ እውነት በእርሱ ዘንድ ስለሌለም፣ በእውነት አይጸናም። ሐሰትንም ሲናገር ከራሱ አፍልቆ ይናገራል፤ ምክንያቱም እርሱ ሐሰተኛ፣ የሐሰትም አባት ነው። 45 እኔ ግን እውነትን ስለምናገር አታምኑኝም። 46 ከእናንተ ስለ ኃጢአት የሚወቅሰኝ ሰው ማን ነው? እውነትን የምናገር ከሆነስ፣ ታዲያ ለምን አታምኑኝም? 47 ከእግዚአብሔር ስላልሆናችሁ፣ ቃሉን አትሰሙም።” 48 አይሁድም፣ “እንግዲህ ጋኔን ያደረብህ ሳምራዊ ነህ በማለታችን እውነት አልተናገርንምን?” በማለት መለሱለት። 49 ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፤ “እኔ ጋኔን የለብኝም፤ እኔ አባቴን አከብረዋለሁ እንጂ፣ እናንተ ግን ታዋርዱኛላችሁ። 50 እኔ የራሴን ክብር አልሻም፤ የሚሻና የሚፈርድ አንድ አለ። 51 እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ፤ ቃሌን የሚጠብቅ ማንም ቢኖር፣ እርሱ ሞትን በፍጹም አያይም።” 52 አይሁድም፣ “አሁን ጋኔን እንዳለብህ ዐወቅን። አብርሃምም ነቢያትም ሞተዋል፤ አንተ ግን 'ማንም ቃሌን ቢጠብቅ ሞትን አይቀምስም' ትላለህ። 53 አንተ ከሞተው ከአባታችን፣ ከአብርሃም ትበልጣለህን? ነቢያትም ሞተዋል። ለመሆኑ፣ አንተ ማን ነኝ ልትል ነው?” አሉት። 54 ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ “እኔ ራሴን ባከብር፣ ክብሬ ከንቱ ነው፤ እኔን የሚያከብረኝ እናንተ አምላካችን ነው የምትሉት አባቴ ነው። 55 እናንተ እርሱን አላወቃችሁትም፤ እኔ ግን ዐውቀዋለሁ። እኔ ‘አላውቀውም’ ብል እንደ እናንተው ሐሰተኛ እሆናለሁ። ነገር ግን እኔ ዐውቀዋለሁ፤ ቃሉንም እጠብቃለሁ። 56 አባታችሁ አብርሃም ቀኔን በማየቱ ደስ አለው፤ አይቶም ሐሤት አደረገ።” 57 አይሁድም፣ “ገና ዐምሳ ዓመት ያልሞላህ፣ አንተ አብርሃምን አይተሃልን?” አሉት። 58 ኢየሱስም፣ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ አብርሃም ከመወለዱ በፊት እኔ አለሁ” አላቸው። 59 እነርሱም፣ ሊወግሩት ድንጋይ አነሡ፤ ኢየሱስ ግን ራሱን ሰውሮ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ሄደ።
1 ኢየሱስ በመንገድ ሲያልፍ ፣ ከተወለደ ጀምሮ ዐይነ ስውር የነበረ አንድ ሰው አየ። 2 ደቀ መዛሙርቱ፣ “መምህር ሆይ፤ ይህ ሰው ዐይነ ስውር ሆኖ እንዲወለድ ያደረገው የራሱ ኀጢአት ነው ወይስ የወላጆቹ?” አሉት። 3 ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰላቸው፤ “የእግዚአብሔር ሥራ በእርሱ እንዲገለጥ ነው እንጂ፣ እርሱ ወይም ወላጆቹ ኀጢአት አልሠሩም። 4 የላከኝን ሥራ ቀን ሳለ መሥራት ይገባናል። ማንም ሊሠራ የማይችልበት ሌሊት እየመጣ ነው። 5 በዓለም እስካለሁ፣ የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ።” 6 ኢየሱስ ይህን ካለ በኋላ፣ መሬት ላይ እንትፍ ብሎ፣ በምራቁ ጭቃ ሠራ፤ በጭቃውም የሰውየውን ዐይን ቀባ። 7 ሰውየውንም፣ “ሂድና በሰሊሆም መጠመቂያ ታጠበ” አለው፣ ‘ሰሊሆም’ የተላከ ማለት ነው። ሰውየውም ወደዚያው ሄዶ ታጠበ፤ ዐይኑም እያየለት ተመልሶ መጣ። 8 የሰውየው ጐረቤቶችና ቀድሞ ለማኝ ሆኖ ያዩት ሰዎችም፣ “ይህ ሰው ተቀምጦ ሲለምን የነበረው ሰው አይደለምን?” አሉ። 9 አንዳንዶቹ፣ “እርሱ ነው” አሉ፤ ሌሎችም፣ “ይመስለዋል እንጂ እርሱ አይደለም” አሉ። እርሱ ግን፣ “እኔው ነኝ” አለ። 10 እነርሱም፣ “ታዲያ፣ ዐይኖችህ እንዴት ተከፈቱልህ?” አሉት። 11 እርሱም እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፤ “ኢየሱስ የሚባለው ሰው ጭቃ ሠርቶ ዐይኔን ቀባ፤ ከዚያም፣ ‘ወደ ሰሊሆም ሄደህ ታጠብ’ አለኝ። እኔም ሄጄ ታጠብሁ፤ ዐይኖቼም በሩ።” 12 እነርሱም፣ “ታዲያ፣ እርሱ የት ነው?” አሉ። እርሱም፣ “እኔ አላውቅም” ብሎ መለሰላቸው። 13 እነርሱም ዐይነ ስውር የነበረውን ሰው ወደ ፈሪሳውያን ወሰዱት። 14 ኢየሱስ ጭቃ ሠርቶ የሰውየውን ዐይን የከፈተው በሰንበት ቀን ነበረ። 15 ፈሪሳውያንም ዐይኑ እንዴት እንደ ተከፈተለት እንደ ገና ሰውየውን ጠየቁት። እርሱም፣ “ዐይኖቼን ጭቃ ቀባ፤ ታጠብሁና ማየት ቻልሁ” አላቸው። 16 ከፈሪሳውያን አንዳንዶቹ፣ “ይህ ሰው ሰንበትን ስለማያከብር፣ ከእግዚአብሔር አይደለም” አሉ። ሌሎቹም፣ “ኀጢአተኛ የሆነ ሰው እንዴት እንደዚህ ያለ ተአምር ይሠራል?” አሉ። ስለዚህ በመካከላቸው መከፋፈል ተፈጠረ። 17 እንደ ገናም ዐይነ ስውሩን ሰው፣ “ዐይንህን ስለ ከፈተው ሰው ምን ትላለህ?” አሉት። ዐይነ ስውሩም፣ “ነቢይ ነው” አለ። 18 ፈሪሳውያንም ዐይነ ስውር የነበረው ሰው ዐይኖች መከፈታቸውን አሁንም ስላላመኑ፣ ዐይኑ የበራለትን ሰው ወላጆች አስጠሩ። 19 ወላጆቹንም፣ “ይህ ዐይነ ስውር ሆኖ የተወለደ ነው የምትሉት ሰው ልጃችሁ ነውን? ከሆነስ፣ አሁን እንዴት ማየት ቻለ?” ብለው ጠየቋቸው። 20 ወላጆቹም እንዲህ ሲሉ መለሱላቸው፤ “ይህ ልጃችን መሆኑንና ዐይነ ስውር ሆኖ መወለዱን እናውቃለን። 21 አሁን እንዴት ማየት እንደ ቻለ ግን አናውቅም፤ ዐይኑን የከፈተለት ማን እንደ ሆነም አናውቅም። እርሱን ጠይቁት፤ ጕልማሳ ነው፤ ስለ ራሱ መናገር ይችላል።” 22 ወላጆቹ እንዲህ ያሉት አይሁድን ስለ ፈሩ ነበር። ምክንያቱም አይሁድ፣ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ ነው የሚል ሰው ካገኙ፣ ከምኵራብ ሊያስወግዱት ቀደም ብለው ተስማምተው ነበር። 23 ወላጆቹ፣ “እርሱ ጕልማሳ ነው፤ ራሱን ጠይቁት” ያሉትም በዚህ ምክንያት ነበር። 24 ዐይነ ስውር የነበረውን ሰው እንደ ገና አስጠርተው፣ “ለእግዚአብሔር ክብር ስጥ፤ እኛ ይህ ሰው ኀጢአተኛ እንደ ሆነ እናውቃለን” አሉት። 25 ሰውየውም፣ “እኔ እርሱ ኀጢአተኛ መሆኑን አላውቅም። ነገር ግን አንድ ነገር ዐውቃለሁ፤ ዐይነ ስውር ነበርሁ፤ አሁን ግን እያየሁ ነው” አላቸው። 26 እነርሱም፣ “ያደረገልህ ምንድን ነው? ዐይኖችህንስ የከፈተው እንዴት ነው?” አሉት። 27 እርሱም፣ “አስቀድሜ ነግሬአችሁ ነበር! እናንተ ግን አትሰሙም። እንደ ገና መስማትስ ለምን ፈለጋችሁ? እናንተም የእርሱ ደቀ መዛሙርት ለመሆን ትፈልጋላችሁን?” ብሎ መለሰ። 28 ሰደቡትና እንዲህ አሉ፤ “አንተ የእርሱ ደቀ መዝሙር ነህ፣ እኛ ግን የሙሴ ደቀ መዛሙርት ነን። 29 እግዚአብሔር ሙሴን እንደ ተናገረው እናውቃለን፤ ይህ ሰው ግን ከየት እንደ መጣ አናውቅም።” 30 ሰውየውም፣ “ይህ ሰው ከየት እንደ መጣ አለማወቃችሁ የሚገርም ነው፤ ይሁን እንጂ፣ ዐይኔን የከፈተው እርሱ ነው። 31 እግዚአብሔር ኀጢአተኞችን እንደማይሰማ እናውቃለን፤ ነገር ግን እግዚአብሔርን የሚያመልክና ፈቃዱን የሚያደርግ ሰው ሁሉ እግዚአብሔር ይሰማዋል። 32 ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ፣ ዐይነ ስውር ሆኖ የተወለደን ሰው ዐይን የከፈተ ሰው ከቶ አልተሰማም። 33 ይህ ሰው ከእግዚአብሔር ባይሆን ኖሮ፣ አንድም ነገር ማድረግ ባልቻለ ነበር።” 34 እነርሱም፣ መልሰው “አንተ ሁለንተናህ በኀጢአት የተወለደ፣ አሁን አንተ እኛን ታስተምረናለህን?” አሉት። ከዚያም ከምኵራብ አስወጡት። 35 ኢየሱስም ሰውየውን ከምኵራብ እንዳስወጡት ሰማ። ሰውየውንም አግኝቶ፣ “በሰው ልጅ ታምናለህን?” አለው። 36 እርሱም፣ “ጌታ ሆይ፣ አምንበት ዘንድ እርሱ ማን ነው?” አለው። 37 ኢየሱስም፣ “አይተኸዋል፤ አሁን እንኳ ከአንተ ጋር እየተነጋገረ ያለው እርሱ ነው” አለው። 38 ሰውየውም፣ “ጌታ ሆይ፣ አምናለሁ” አለ። ከዚያም ሰገደለት። 39 ኢየሱስም፣ “የማያዩ እንዲያዩ፣ የሚያዩም እንዳያዩ፣ ለፍርድ ወደዚህ ዓለም መጣሁ” አለ። 40 ከእነርሱም ጋር ከነበሩት አንዳንድ ፈሪሳውያን ይህን ሰምተው፣ “እኛም ደግሞ ዐይነ ስውራን ነን ወይ?” አሉት። 41 ኢየሱስም ፣ “ዐይነ ስውራን ብትሆኑማ፣ ኀጢአት ባልሆነባችሁ ነበር። ነገር ግን፣ ‘እናያለን’ ስለምትሉ፣ ኀጢአታችሁ እንዳለ ይኖራል።”
ይህ የታሪኩ ቀጣይ ክፍል ነው ፡፡ ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ እየተጓዙ ሳሉ አንድ ዓይነ ስውር አገኘ።
እዚህ “ኢየሱስ” ለኢየሱስ እና ለደቀመዛሙርቱ የማይነገር ምሳሌ ነው ፡፡ አት: - “ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱ ሲያልፉ”
ይህ ጥያቄ ኃጢአት ሁሉንም በሽታዎች እና ሌሎች የአካል ጉድለቶችን ያስከተለ የጥንት የአይሁድን እምነት ያንፀባርቃል ፡፡ ራቢዎች በተጨማሪም ሕፃን ገና በማህፀን ውስጥ እያለ ኃጢአት መሥራቱን አስተምረዋል ፡፡ AT: - “መምህር ፣ ኃጢአት አንድን ሰው ዕውር እንዲለው እንደሚያደርገው እናውቃለን። ይህ ሰው ዕውር ሆኖ እንዲወለድ ያደረገው ይህ ኃጢአት ነው? ይህ ሰው ራሱ ኃጢአት ሠርቷል ወይንስ ወላጆቹ ኃጢአት ሠሩ?”
ይህ “እኛ” ኢየሱስን እና የሚናገራቸውን ደቀመዛሙርትን ያካትታል ፡፡
እዚህ “ቀን” እና “ሌሊት” ዘይቤዎች ናቸው ፡፡ ኢየሱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ሥራ የቀን ጊዜን ፣ ሰዎች በተለምዶ የሚሰሩበትን ጊዜ እና የሌሊት ጊዜን የእግዚአብሔርን ሥራ ማከናወን ለማይችሉበት ጊዜ እያወዳደረ ነው ፡፡
እዚህ “ዓለም” በዓለም ለሚኖሩት ሰዎች የሚያገለግል ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - “በዚህ ዓለም ሰዎች መካከል”
ኢየሱስ ጣቶቹን አፈር እና ምራቅ ለማደባለቅ ተጠቅሞበታል። አት: - “ጣቶቹን ጭቃ እና ምራቅ ለመደባለቅ ጣቶቹን ተጠቅሞ ነበር
ዮሐንስ በግሪክኛ ተናጋሪ ታዳሚዎችን የሚጠቅሙ አንዳንድ ተጨማሪ መረጃዎችን እንዲያቀርብ በታሪክ መስመሩ ውስጥ አጭር እረፍቱ እዚህ ይገኛል ፡፡
"አይኖቹን ገንዳ ውስጥ አጠባቸው"
ይህ አስተያየት የሰዎችን አስገራሚነት ለመግለጽ በጥያቄ መልክ ይታያል። AT: - “ይህ ሰው ቁጭ ብሎ ይለምን የነበረው እርሱ ነው!”
ቁጥር 14 ኢየሱስ ሰውየውን መቼ እንደፈወሰ ዳራውን ይነግረናል ፡፡
ታዲያ ለምን ማየት ቻልክ? ወይም “አሁን እንዴት ታያለህ?”
ጣቶቼን በጭቃ ይሸፍኑ ነበር ፡፡ በ 9: 6 ውስጥ ተመሳሳይ ሐረግ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
ቁጥር 14 ኢየሱስ ሰውየውን መቼ እንደፈወሰ ዳራውን ይነግረናል ፡፡
ሰዎቹም ሰውዬው ወደ ፈሪሳውያን እንዲሄድ ጠየቁት ፡፡ እነሱ እንዲሄድ በአካል አላስገደዱትም ፡፡
“የአይሁድ የእረፍት ቀን”
ፈሪሳውያንም ደግሞ ጠየቁት።
በቁጥር 18 ውስጥ ዮሐንስ ስለ አይሁዶች ክህደት የበስተጀርባ መረጃን ሲያቀርብ ፣ ከዋናው የታሪክ መስመር ዕረፍት አለ ፡፡
ይህ ማለት ኢየሱስ በአይሁድ የእረፍት ቀን ምንም ሥራ ስለሌለ ህጉን አይታዘዝም ማለት ነው ፡፡
ይህ አስተያየት የኢየሱስ ምልክቶች ምልክቶች ኃጢአተኛ አለመሆኑን ለማጉላት በጥያቄ መልክ ይታያል ፡፡ AT: "አንድ ኃጢአተኛ እንደዚህ ያሉትን ምልክቶች ማድረግ አይችልም!"
"እነሱ" የሚያመለክተው የአይሁድ መሪዎችን ነው
"እሱ አዋቂ ሰው ነው" ወይም "አሁንም ልጅ አይደለም"
በቁጥር 22 ውስጥ ዮሐንስ የሰውየውን ወላጆች አይሁዶች ስለሚፈሩ የበስተጀርባ መረጃ ሲያቀርብ ዮሐንስ ከዋናው የታሪክ መስመር ዕረፍት አለ ፡፡
እዚህ ላይ “አይሁዶች” ኢየሱስን ለተቃወሙት “የአይሁድ መሪዎች” አንድ ማሳያ ነው ፡፡ አት: - "የአይሁድ መሪዎች ምን ሊያደርግባቸው ፈሩ?"
ይህ በእራሱ ወይም በሌሎች ላይ የመጉዳት አደጋ ሲኖር አንድ ሰው የሚሰማውን ደስ የማይል ስሜት ያመለክታል ፡፡
"እሱ ሰው ነው" ወይም "እሱ ከእንግዲህ ልጅ አይደለም።" ይህንን በ 9 19 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
እዚህ “እነሱ” የሚያመለክተው አይሁዶችን ነው ፡፡ (9 16)
ይህ ሰዎች መሐላ በሚፈጽሙበት ጊዜ ይጠቀሙበት የነበረው ፈሊጥ ነው ፡፡ አት: - “በእግዚአብሔር ፊት እውነቱን ይናገሩ!” በእግዚአብሔር ፊት እውነቱን ተናገሩ!
ኢየሱስን ነው የሚያመለክተው
እውሩን ነው የሚያመለክተው
አይሁዶች ዕውር የነበረውን ሰው ማናገራቸውን ቀጠሉ ፡፡
ይህ አስተያየት የአይሁድ መሪዎች የተከሰተውን እንደገና እንዲነግራቸው የጠየቁት ሰው ያስገረመውን ለመግለጽ በጥያቄ መልክ ይታያል ፡፡ አት: - "እኔ ምን እንዳደረብኝ እንደገና ለመስማት መፈለግህ አስደንቆኛል!"
የአይሁድ መሪዎች የመፈወስ ኃይል እንዳለው ሲገነዘቡ የኢየሱስን ሥልጣን ሲጠራጠሩ ሰውየው ተገረመ ፡፡ አት: - “ሥልጣኑን የት እንዳገኘ አታውቅም”
"የኃጢአተኞች ጸሎትን አይመልስም ... እግዚአብሔር ጸሎቱን ይሰማል"
ዓይነ ስውር የነበረው ሰው ለአይሁድ መናገሩን ቀጠለ ፡፡
ይህ ቀጥተኛ መግለጫ ነው። በገባ ቅርጸት ሊተረጉሙት ይችላሉ። አት: - “ከተወለደበት ጊዜ ዕውር የነበረውን ዕውር የፈውስ ማንም ሰው ከቶ አይሰማም”
ይህ ዓረፍተ ነገር ድርብ አሉታዊ ንድፍን ይጠቀማል። እንደዚህ ያለ ነገር ሊያከናውን የሚችለው ከእግዚአብሔር አንድ ሰው ብቻ ነው! ”
ይህ ማስታወሻ አፅን .ትን ለመጨመር በጥያቄ መልክ ይታያል ፡፡ ደግሞም የሚያመለክተው ሰውየው በወላጆቹ ኃጢአት ምክንያት ዕውር ሆኖ መወለዱን ነው ፡፡ አት: - "የተወለዱት በወላጆችዎ ኃጢአት ምክንያት ነው። እኛን ለማስተማር ብቃት የላችሁም!"
ከሙኩራባቸው አስወጡት
ይህ የታሪኩ ቀጣይ ክፍል ነው ፡፡ ኢየሱስ የፈወሰውን ሰው አገኘና እሱንና ሕዝቡን አነጋገረው ፡፡
ይህ የታሪኩ ቀጣይ ክፍል ነው ፡፡ ኢየሱስ የፈወሰውን ሰው አገኘና እሱንና ሕዝቡን አነጋገረው ፡፡
“ዓለም” የሚለው ቃል “በዓለም ለሚኖሩት ሰዎች” የሚለው አገላለጽ ነው ፡፡ አት: - “በዚህ ዓለም ሰዎች መካከል ለመኖር መጣ”
እዚህ “ማየት” እና “ዕውርነት” ዘይቤዎች ናቸው ፡፡ ኢየሱስ በመንፈሳዊ ዓይነ ስውር በሆኑና በአካላዊ ዓይነ ስውር በሆኑት ሰዎች መካከል ይለያል ፡፡ AT: “ስለሆነም በመንፈሳዊ ዕውሮች የሆኑ ግን እግዚአብሔርን ማየት የሚፈልጉት እሱን ሊያዩ ይችላሉ ፣ እናም ቀድሞውንም እግዚአብሔርን ያታልላሉ ብለው በሐሰተኛነት ላይ ይቆያሉ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር) ፡፡
እኛ በመንፈሳዊ ዕውራን የሆንን ይመስልሃል?
እዚህ “ዕውር” የእግዚአብሔርን እውነት አለማወቅ ምሳሌ ነው ፡፡ አት: - "የእግዚአብሔርን እውነት ማወቅ ከፈለግክ ፣ ዓይንህን ማየት ይችል ነበር ፡፡"
1 “እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ፤ ወደ በጎች በረት በበር ሳይሆን፣ በሌላ መንገድ ተንጠላጥሎ የሚገባ እርሱ ሌባና ወንበዴ ነው። 2 በበር የሚገባ ግን የበጎች እረኛ ነው። 3 በር ጠባቂውም ለእርሱ ይከፍትለታል። በጎቹም ድምፁን ይሰማሉ፤ እርሱም የራሱን በጎች በስማቸው ጠርቶ፣ ወደ ውጭ ይመራቸዋል። 4 የራሱን ሁሉ ካወጣቸው በኋላ፣ ፊት ፊታቸው ይሄዳል፤ በጎቹም ድምፁን ስለሚያውቁ ይከተሉታል። 5 ባዕድ የሆነውን አይከተሉትም፤ ይልቁንም የባዕዱን ድምፅ ስለማያውቁት ይሸሹታል።” 6 ኢየሱስ ይህን ምሳሌ ነገራቸው፤ እነርሱ ግን የነገራቸው ስለ ምን እንደ ሆነ አልገባቸውም። 7 ኢየሱስም እንደ ገና እንዲህ አላቸው፤ እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ፤ የበጎች በር እኔ ነኝ። 8 ከእኔ በፊት የመጡ ሁሉ ሌቦችና ወንበዴዎች ናቸው፤ በጎቹ ግን አላዳመጡአቸውም። 9 በሩ እኔ ነኝ። ማንም በእኔ በኩል ቢገባ፣ ይድናል፤ ይገባል፣ ይወጣልም፤ መሰማሪያም ያገኛል። 10 ሌባው የሚመጣው ሊሰርቅ፣ ሊገድልና ሊያጠፋ ብቻ ነው። እኔ ግን ሕይወት እንዲኖራቸውና እንዲትረፈረፍላቸው መጥቻለሁ። 11 መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ለበጎቹ ሲል ነፍሱን ይሰጣል። 12 እረኛ ያልሆነው ተቀጣሪ በጎቹም የእርሱ ያልሆኑት፣ ቀበሮ መምጣቱን ሲያይ በጎቹን ጥሎ ይሸሻል ። ቀበሮም ነጥቆአቸው ይሄዳል፤ ይበታትናቸውማል። 13 የሚሸሸውም ተቀጣሪ ስለ ሆነና ለበጎቹ ደንታ ስለሌለው ነው። 14 መልካም እረኛ እኔ ነኝ፤ የእኔ የሆኑትን ዐውቃቸዋለው፤ የእኔ የሆኑትም ያውቁኛል። 15 አብ እንደሚያውቀኝ፤ እኔም አብን ዐውቀዋለው፤ ነፍሴንም ስለ በጎች እሰጣለሁ። 16 ከዚህ በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ። እነዚያን ደግሞ ማምጣት አለብኝ፤ እነርሱ ድምፄን ይሰማሉ። አንድ መንጋ ይሆናሉ፤ እረኛቸውም አንድ ይሆናል። 17 አባቴ የሚወደኝ ለዚህ ነው፤ መልሼ ልወስደው እንድችል ነፍሴን እሰጣለሁ ። 18 ነፍሴን ማንም ከእኔ አይወሰድም፤ ግን እኔው ራሴ እሰጣለሁ ። ለመስጠት ሥልጣን አለኝ፤ መልሼ ለመውሰድም ሥልጣን አለኝ። ይህን ትእዛዝ ከአባቴ ተቀብያለሁ።” 19 ከዚህ አባባል የተነሣም በአይሁድ መካከል እንደ ገና መከፋፈል ተፈጠረ። 20 ብዙዎች፣ “ጋኔን ስላለበት ዐብዶአል፤ ለምን ታዳምጡታላችሁ?” አሉ። 21 ሌሎችም፣ “ንግግሩ ጋኔን ያለበት ሰው ንግግር አይደለም። ጋኔን ያለበት ሰው የዐይነ ስውርን ዐይን መክፈት ይችላልን?” አሉ። 22 በኢየሩሳሌምም የቤተ መቅደስ መታደስ በዓል ደርሶ ነበር። 23 ጊዜው ክረምት ነበረ፤ ኢየሱስም በቤተ መቅደስ በሰሎሞን መተላለፊያ ይመላለስ ነበር። 24 ከዚያም አይሁድ ወደ እርሱ ተሰብስበው፣ «እስከ መቼ ድረስ ልባችንን ታንጠለጥላለህ? አንተ ክርስቶስ ከሆንህ፣ በግልጽ ንገረን» አሉት። 25 ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አላቸው፤ “ነገርኋችሁኮ፤ እናንተ ግን አታምኑም፤ በአባቴ ስም የማደርጋቸው ሥራዎች እነዚህ ስለ እኔ ይመሰክራሉ። 26 እናንተ ግን በጎቼ ስላልሆናችሁ አታምኑም። 27 በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ፤ እኔ ዐውቃቸዋለሁ፤ እነርሱም ይከተሉኛል። 28 የዘላለም ሕይወት እሰጣቸዋለው፤ ፈጽሞም አይጠፉም፤ ነጥቆ ከእጄ የሚያወጣቸው ማንም የለም። 29 እነርሱን ለእኔ የሰጠ አባቴ ከሌሎች ሁሉ ይበልጣል፤ ስለዚህ ከአብ እጅ ነጥቆ ሊያወጣቸው የሚችል ማንም የለም። 30 እኔና አብ አንድ ነን።” 31 አይሁድ ሊወግሩት እንደ ገና ድንጋይ አነሡ። 32 ኢየሱስም መልሶ፣ «ከአብ የሆነ ብዙ መልካም ሥራ አሳይቻችኋለሁ፤ ከእነዚህ ሥራዎች ውስጥ በየትኛው ምክንያት ትወግሩኛላችሁ?” አላቸው። 33 አይሁድም መልሰው፣ «የምንወግርህ በየትኛውም መልካም ሥራ ምክንያት አይደለም፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር ላይ በምትሰነዝረው የስድብ ቃል ምክንያት ነው፤ አንተ ሰው ሆነህ ሳለህ፣ ራስህን አምላክ እያደረግህ ስለ ሆነ ነው» አሉት። 34 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፤ «በሕጋችሁ፣ ‘አማልክት ናችሁ አልሁ’ ተብሎ አልተጻፈምን? 35 የእግዚአብሔር ቃል የመጣላቸውን አማልክት ናችሁ ካላቸው፣ የመጻሕፍት ቃል አይሻርምና፣ 36 እኔ ‘የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ’ ስላልሁ፣ አብ ቀድሶ ወደ ዓለም የላከውን እንዴት የስድብ ቃል ሰነዘረ ትሉታላችሁ? 37 እኔ የአባቴን ሥራዎች የማላደርግ ከሆንሁ አትመኑኝ። 38 ነገር ግን የማደርጋቸው ከሆንሁ፣ በእኔ ባታምኑ እንኳ፣ አብ በእኔ እንዳለ፣ እኔም በአብ እንዳለሁ እንድታውቁና እንድትረዱ፣ በሥራዎቹ እመኑ።» 39 እነርሱም ኢያሱስን እንደ ገና ለመያዝ ሞከሩ፣ እርሱ ግን ከእጃቸው አምልጦ ሄደ። 40 ኢየሱስ ዮርዳኖስን ተሻግሮ፣ ዮሐንስ በመጀመሪያ ሲያጠምቅበት ወደ ነበረው ቦታ እንደ ገና ሄደ፤ በዚያም ቆየ ። 41 ብዙ ሰዎች ወደ ኢየሱስ መጡ። እነርሱም፣ «በርግጥ ዮሐንስ ምንም ተአምር አልሠራም፤ ነገር ግን ዮሐንስ ስለዚህ ሰው የተናገረው ሁሉ እውነት ነው» ይሉ ነበር። 42 በዚያም ብዙ ሰዎች በኢያሱስ አመኑ።
እየሱሰ ምሳሌያዊ አነጋገር መናገር ጀመረ
እየሱስመ ፈሪሳውያንን ማነገር ቀጠለ፨ ይህ ታሪክ በ9፡35 ጋር አንድ ነው፨
እንደ 1፡49 ይተርጎም
እረኛው በጎቹን የሚያኖሩበት አጥር
ሁለት አንድ አይነት ትረጉም ያለው ቃል ክብደት ለመጨመር መጠቀም
እረኛው ሳይኖር በማታ በር እንዲጠብቅ የተቀጠረ
በጎቹ ድምጹን ለይተው ይሰማሉ
ከፊታቸው ይራመዳል
ድምጹተን ይለዩታል
ሊሆን የሚችለው 1) ደቀመዛሙርቱ አልገባቸውም 2) የተሰበሰቡትም አልገባቸውም
ይህ መግለጫ የእረኛው ነው ዘይቤዎችን በመጠቀም። እረኛው የእየሱስ ምሳሌ ነው፨ በጉ የእየሱስ ተከታዮችን ሲወክል፥ እንግዶች ደግሞ የአይሁድ መሪዎች እና ፈሪሳውያን፤ ሰዎቹን ለማታለል የሞከሩት
ኢየሱስ የተናገራቸውን ምሳሌዎች ትርጉም ማብራራት ይጀምራል ፡፡
እዚህ “በር” ይህ የእግዚአብሔር ህዝብ በእርሱ ፊት በሚኖርባቸው በጎች ወደ ስፍራው ለመድረስ የሚያስችል ኢየሱስ ነው ፡፡ አት: - “በጎቹ ወደ በግ በጎች ለመግባት እንደሚጠቀሙበት በር ነኝ”
ይህ ፈሪሳውያንንና ሌሎች የአይሁድ መሪዎችን ጨምሮ ሕዝቡን ያስተማሩ ሌሎች አስተማሪዎች ናቸው ፡፡ አት: - “ከኔ ስልጣን ውጭ የመጡ አስተማሪዎች ሁሉ” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
በር ምሳሌያዊ ነው፨
ለምለም ማለት በጎች የሚበሉት ሳር ያለበት
ይህ ድርብ አሉታዊ ነው። በአንዳንድ ቋንቋዎች አወንታዊ መግለጫን መጠቀም የበለጠ ተፈጥሮአዊ ነው። አት: “የሚመጣው ለመስረቅ ብቻ ነው”
እዚህ በምሳሌ የተገለጸው በጉ ነው፤ የእግዚአብሄርን ሕዝብ ይወክላል፨ በጎቸን ሊሰርቅ ሊገል እነ ሊያተፋ
እነሱ የሚለው ቃል የሚያመለክተው በጉን ነው፨ ሕይወት ደግሞ የዘላለም ሕይወትነ ያመለክታል፨
እየሱስ ስለ መልካሙ እረኛ ምሳሌያዊ ነግግሩን ቀጠለ
መልካም እረኛ በምሳሌ የሚወክለው እየሱስን ነው፨
አንድነ ነገር መተው ማለት መቆጣጠር አለመቻልን ተስፋ መቁረጥን ያሳያል፨ መለስተኛ የሞት መንገድ
የተቀጠረ አገልጋይ የአይሁድ መሪዎችና አስተማሪዎች ዘይቤ
እዚህ ላይ በግ የሚለው የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይወክላል፨ እየሱስም አለ እንደ ተቀጠረ እረኛ በጎቹን እንደሚተው፤ የአይሁድ መሪዎችና አስተማሪዎች ለእግዚአብሄር ሕዝቦች ግድ የላቸውም
ለእየሱሰ መልካም እረኛ ነኝ የሚለው ምሳሌያዊ ነው
አብም እንደሚያውቀኝ አኔም አብን እንደማውቅ እናንተም ታውቁኛላችሁ፨ አባት የሚለው ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው
ይህ ለየሱስ ስለ በጎቹ ራሱን ኣሳልፎ እንደሚሰጥ
ሌላ በግ ማለት አይሁድ ያልሆኑ ተከታዮች እንዳሉት ለመግለጽ
እዜህ መንጋና በግ ምሳሌያዊ ናቸው፨ አይሁድ እና አይሁድ ያይደሉት አንድ መንጋ ይሆናሉ፨ አርሱም በጎቹን እንደሚንከባከብ እረኛ ይሆናል፨
እየሱስም ለሕዝቡ መናገሩን ጨረሰ፨
የእግዚአብሔር ዘላለማዊ እቅድ ልጁ ስለሰው ለጆች ሐጢአት ሲል ሕይወቱን አሳልፎ እንዲሰጥ ነው፨ የእየሱስ የመስቀል ሞት የሚያሳየን የአባትና የልጁን ፍቅር ነው
ይህ ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ርእስ ነው፨
ይህ አይነት ፍቅር የሚገኘው ከእግዚአብሔር ሲሆን የሚያተኩረውም ለሌሎች መልካመን በማድረግ፤ለርሱ ምንም ትርፍ ባይኖረውም፨ ይህ አይነት ፍቅር የሚጨነቀው የፈለጉትንም ቢሰሩ ስለሌሎች ነው፨
እየሱስ በመለስተኛ አባባል እንደሚሞትና እንደገናም በሕይወት እንደሚኖር
እራሴ የሚለው የሚገልጸው እየሱስ እራሱ ሕይወቱን እንደሚያኖር ነው፨ ከሱ ማንም አይወስድበትም፨
አባተ እንድሰራው ያዘዘኝ ይህንን ነው፨ አባት የሚለው ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ነው፨
ይህ ጥቅስ የሚነግረን አይሁዶች ለኢየሱስ የመለሱለትን ነው፨
ይህ አስተያየት በጥያቄ መለክ የሚያመለክተው ሕዝቡ ትኩረት ሰጥተው ዕርሱን ዕነዳይሰሙት ነው፨
ይህ አስተያተ በጥያቄ መልክ የቀረበው ለጉዳዩ ትኩረት ለመስጠት ነው፨
ይህ የሚቀጥለው ከፍል ታሪክ ነው፨ የመታደስም በአል ስለነበር አይሁዶቹ ኢየሱስን መጠየቅ ጀመሩ፨ ቁጥር 22 እና 23 ስለታሪኩ አመጣጥ መነሻ ይሰጣሉ፨
ይህ ለ8 ቀን የሚቆይ በክረምት ጊዘ የሚከበር በኣል እግዚአብሄር ያደረገውነ ተአምራት ትንሽ የቀረችውን ዘይት በመቅረዝ ለ8 ቀን ስለበራ፨ መቅረዙን የሚያበሩት የአይሁድን ቤተ መቅደስ ለእግዚአብሄር ለመለየት ነው፨ አንድ ነገር ሲለይ ለተለየ ነገር ቢቻ ለመጠቀም ቃል መግባት ነው፨
እየሱስ ይራመድ የነበረው ከቤተመቅደሱ ውጪ ባለው ግቢ ነበር
ይህ ቅርጽ በሕነጻ መግቢያ ጋር የተያያዘ ሶሆን ጣራ ሲኖረው ግርግዳ ግን የለውም
እዚህ ላይ “አይሁዶች” ኢየሱስን ለተቃወሙት የአይሁድ መሪዎች ምሳሌ ነው ፡፡ AT: “የአይሁድ መሪዎችም ከበቡት”
ይህ ፈሊጥ ነው ፡፡ አት: - "እንድንደነቅ ያደርገናል" (UDB) ወይም "በእርግጠኝነት እንዳናውቅ ያድርገንን?"
እየሱስመ ለአይሁዶች መመለስ ጀመረ
ስም የሚለው የእግዚአብሔር ሐይል ነው፨ አበት የሚለው ቃል ለእግዚአብሄር ኣስፈላጊ ነው፨ ዔሱስ ያደረጋቸው ተአምራት በአባቱ ሀይልና ስልጣን ነው፨
ልክ በፍርድቤት ቀርቦ እንደሚመሰከር ሰው ተአምራቶቹ ስለእርሱ ይመሰክራሉ
በጎቼ የሚለው ቃል የኢየሱስ ተከታዮችን ይገልጻል
በግ የሚለው ቃል ለእየሱሰ ተከታዮች የሚጠቀሙበት ዘይቤ ነው፨ ዘይቤውም እየሱስ እረኛ እንደሆን ይገልጻል፨
አጅ የሚለው የእየሱስን ተከላካይነት እና ጥበቃ
አባት የሚለው ቃል ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ነው
እጅ የሚለው የእግዚአብሄርን ይዞታ እና ጥበቃ
እየሱስ የእግዚአብሄር ልጅ እና እግዚአብሄር አባት አንድ ናቸው፨ አባት የሚለው ቃል ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ነው
“አይሁዶች” የሚለው ቃል ኢየሱስን ለሚቃወሙት የአይሁድ መሪዎች መፈክር ነው ፡፡ አትቲ: - “የአይሁድ መሪዎች እንደገና ድንጋይ መከሩን ጀመሩ”
እየሱስም ተአምራቶችን በእግዚአብሄር ያሳይ ነበር፨ አባት የሚለው ቃል ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ነው
ይህ ጥያቄ ጠንካራ ነው፨ እየሱስ የአይሁድ መሪዎች መልካም ስራ ስለሰራ በድንጋይ ሊወግሩት እንዳልሆነ ያውቃል፨
“አይሁዶች” የሚለው ቃል ኢየሱስን የሚቃወሙትን የአይሁድ መሪዎች የሚወክል የመከራከሪያ መግለጫ ነው ፡፡ AT: - “የአይሁድ ተቃዋሚዎች መለሱ” ወይም “የአይሁድ መሪዎች መለሱለት”
እግዚአብሄር ነኝ ኣልክ
በጥያቄ ምልክት የቀረበው አጽንኦት ለመስጠት ነው፨
እዚህ ላይ ኢየሱስ ተከታዮቹን “አማልክት” ብሎ የሚጠራውን ጥቅስ ይጠቅሳል ፣ ምናልባትም በምድር ላይ እሱን እንዲወክሉ ስለመረጣቸው ፡፡
እግዚአብሄርም ቃሉን ተናገረ
ትርጉሙ ሊሆን የሚችለው፡ 1) ቃሉን ማን መለወ አይችልም 2) ቃሉ ሁሌም እውነት ነው
ይህ የእግዚአብሄርነና የእየሱስን ግኑኝነት የሚገልጽ አስፈላጊ ርእስ ነው
እየሱስም ለአይሁዶች መልስ መስጠቱን ጨረሰ
አባት የሚለው ቃል ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ነው
እመኑኝ የሚለው ቃል እየሱስ ያለው እውነት እንደሆን መቀበል ወይም ማመን
እመኑ የሚለው እየሱስ እየሰራ ያለው ከአባቱ እንደሆነ እንዲያወቁ
በእግዚአብሄርና በእየሱስ መካከል ያለውነ ግንኙነት የሚገልጽ
እጅ የሚለው የአይሁድ መሪዎችን
እየሱሰ በምእራብ ጆርዳን ወንዝ ነበረ
እየሱስመ ለጥቂት ጊዜ በምስራቅ ጆረዳነ ቆየ
ዮሀንስ ምልክት አለማድረጉ እውነት ቢሆንም ስለዚህ ሰው የተናገረው ምልክት እነደሚያደርግመ እውነት ነው
ተአምራቶቹ አንድ ነገር እውነት እነደሆነና ለዛ ሰውም ምስጋና መስጠት
አመኑ የሚለው እየሱስ ያለውን ማመንና መቀበል
1 አልዓዛር የተባለ አንድ ሰውም ታሞ ነበር። እርሱም ማርያምና እኅትዋ ማርታ በሚኖሩበት መንደር በቢታንያ ይኖር ነበር። 2 ወንድምዋ የታመመባትም የጌታ ኢየሱስን እግር ሽቱ የቀባችውና በጠጕርዋ ያበሰችው ናት። 3 ከዚያም እኅትማማቹ፣ ‹‹እነሆ፣ የምትወደው ታሞአልና በፍጥነት ድረስ›› በማለት ወደ ኢየሱስ ላኩበት። 4 ኢየሱስ መልእክቱን በሰማ ጊዜ፣ ‹‹ይህ የእግዚአብሔር ልጅ እንዲከብርበት ለእግዚአብሔር ክብር የሚሆን ነው›› አለ። 5 ኢየሱስ ማርታንና እኅቷን እንዲሁም አልዓዛርን ይወድ ነበር፡፡ 6 ስለሆነም አልዓዛር መታመሙን በሰማ ጊዜ፣ ኢየሱስ በነበረበት ቦታ ሁለት ተጨማሪ ቀናት ቆየ፡፡ 7 ከዚህ በኋላም ደቀ መዛሙርቱን፣ “ወደ ይሁዳ ዳግመኛ እንሂድ” አላቸው፡፡ 8 ደቀ መዛሙርቱ፣ “መምህር ሆይ፣ አይሁድ አሁን ሊወግሩህ ነበር፣ እንደ ገና ወደዚያ ተመልሰህ ትሄዳለህን?” አሉት፡፡ 9 ኢየሱስም፣ “በአንድ ቀን ውስጥ አሥራ ሁለት የብርሃን ሰዓታት አሉ አይደለምን? አንድ ሰው በቀን የሚራመድ ከሆነ የቀኑን ብርሃን ስለሚመለከት፣ አይደናቀፍም፡፡ 10 በሌሊት የሚራመድ ከሆነ ግን ብርሃኑ በእርሱ ውስጥ ስለሌለ፣ ይደናቀፋል፡፡” 11 ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች ተናገረ፣ ከእነዚህም ነገሮች በኋላ፣ “ወዳጃችን አልዓዛር አንቀላፍቷል፣ እኔ ግን ከእንቅልፉ ላነቃው እሄዳለሁ” አላቸው፡፡ 12 ስለዚህ ደቀ መዛሙርቱ፣ “ጌታ ሆይ፣ ተኝቶስ ከሆነ ይድናል” አሉት፡፡ 13 ኢየሱስም የተናገረው አልዓዛር ስለ መሞቱ ነበር፣ እነርሱ ግን ዕረፍት ለማድረግ ስለ መተኛቱ የተናገረ መስሎአቸው ነበር፡፡ 14 ከዚያም ኢየሱስ በግልጽ፣ “አልዓዛር ሞቷል 15 እናንተ ታምኑ ዘንድ እኔ እዚያ ባለመኖሬ ስለ እናንተ ደስ ብሎኛል” አላቸው፡፡ 16 ዲዲሞስ የተባለው ቶማስ ባልደረቦቹ ደቀ መዛሙርትን፣ “ከኢየሱስ ጋር እንሞት ዘንድ እኛም ከእርሱ ጋር እንሂድ” አላቸው፡፡ 17 ኢየሱስ በመጣ ጊዜ፣ አልዓዛር በመቃብር ውስጥ አራት ቀን መቆየቱን ተረዳ፡፡ 18 ቢታንያ አሥራ አምስት ኪሎ ሜትር ብቻ የምትርቅ ለኢየሩሳሌም ቅርብ ስፍራ ነበረች፡፡ 19 ስለ ወንድማቸው ሞት ሊያጽናኗቸው ከአይሁድ ብዙዎቹ መጥተው ነበር፡፡ 20 ከዚያም ማርታ ኢየሱስ እንደ መጣ በሰማች ጊዜ፣ ልትቀበለው ወጣች፣ ማርያም ግን በቤት ተቀምጣ ነበር፡፡ 21 ከዚያም ማርታ ኢየሱስን፣ “ጌታ ሆይ፣ አንተ እዚህ ብትኖር ኖሮ ወንድሜ ባልሞተም ነበር፡፡ 22 አሁንም ቢሆን የምትለምነውን ሁሉ እግዚአብሔር እንደሚሰጥህ ዐውቃለሁ” አለችው፡፡ 23 ኢየሱስ፣ “ወንድምሽ ይነሣል” አላት፡፡ 24 ማርታ፣ “በመጨረሻው ቀን በሚሆነው በትንሣኤ ከሞት እንደሚነሣ ዐውቃለሁ” አለችው፡፡ 25 ኢየሱስ፣ “እኔ ትንሣኤና ሕይወት ነኝ፣ በእኔ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፡፡ 26 በእኔ የሚኖርና የሚያምንብኝ ሁሉ ፈጽሞ አይሞትም፤ ይህን ታምኛለሽን?” አላት፡፡ 27 እርሷም፣ “አዎን፣ ጌታ ሆይ፣ አንተ ወደ ዓለም ልትመጣ ያለኸው ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆንህ አምናለሁ” አለችው፡፡ 28 ማርታ ይህን ከተናገረች በኋላ እኅቷን ማርያምን በግል ለማነጋገር ትጠራት ዘንድ ሄደችና፣ “መምህሩ እዚህ ነው፣ ሊያነጋግርሽ ይፈልጋል” አለቻት፡፡ 29 ማርያም ይህን እንደ ሰማች በፍጥነት ተነሥታ ወደ ኢየሱስ ሄደች፡፡ 30 ኢየሱስም ማርታን ባገኘበት ስፍራ ነበር እንጂ ገና ወደ መንደሩ አልገባም ነበር፡፡ 31 ከዚያም በቤት ውስጥ ሆነው ማርያምን ሲያጽናኗት የነበሩት አይሁድ ፈጥና ስትወጣ ባዩአት ጊዜ፣ ወደ መቃብር ሄዳ በዚያ ልታለቅስ መስሏቸው ተከተሏት፡፡ 32 ከዚያም ማርያም ኢየሱስ ወደ ነበረበት መጥታ ስታየው በእግሩ ሥር ወድቃ፣ “ጌታ ሆይ፣ አንተ እዚህ ብትሆን ኖሮ፣ ወንድሜ ባልሞተም ነበር” አለችው፡፡ 33 ኢየሱስ እርሷና ዐብረዋት የነበሩት አይሁድ ሲያለቅሱ ተመልክቶ በመንፈሱ ቃትቶና ተጨንቆ፣ 34 “ወዴት አኖራችሁት?” አላቸው፡፡ እነርሱም፣ “ጌታ ሆይ፣ መጥተህ እይ” አሉት፡፡ 35 ኢየሱስ አለቀሰ፡፡ 36 ከዚያም አይሁድ፣ “አልዓዛርን ምን ያህል ይወደው እንደ ነበረ ተመልከቱ!” አሉ፡፡ 37 ከእነርሱ አንዳንዶቹ ግን፣ “ዓይነ ስውር የነበረውን ሰውዬ ዓይን የከፈተ ይህ ሰው የሞተውን ይህን ሰው እንዳይሞት ማድረግ አይችልም ነበር?” አሉ፡፡ 38 ከዚያም ኢየሱስ አሁንም በውስጡ እየቃተተ ወደ መቃብሩ ሄደ፡፡ መቃብሩ ዋሻ ነበረ፣ ድንጋይም ተገጥሞበት ነበር፡፡ 39 ኢየሱስ፣ “ድንጋዩን አንሡት” አለ፡፡ የሟቹ የአልዓዛር እኅት ማርታም ኢየሱስን፣ “ከሞተ አራት ቀን ስለሆነው፣ በአሁኑ ጊዜ ገላው ይበሰብሳል” አለችው፡፡ 40 ኢየሱስ ማርታን፣ “ብታምኚስ፣ የእግዚአብሔርን ክብር እንደምታዪ አልነገርሁሽምን” አላት፡፡ 41 ስለዚህ ድንጋዩን አነሡት፡፡ ኢየሱስም ሽቅብ እየተመለከተ፣ “አባት ሆይ፣ ስለ ሰማኸኝ አመሰግንሃለሁ፤ 42 ሁልጊዜም እንደምትሰማኝ ዐውቃለሁ፣ ነገር ግን ይህን ያልሁት አንተ እንደላክኸኝ ያምኑ ዘንድ እዚህ በዙሪያዬ ስለቆመው ሕዝብ ነው” አለ፡፡ 43 ይህን ካለ በኋላ ድምፁን ከፍ አድርጎ፣ “አልዓዛር ሆይ፣ ውጣ!” አለ፡፡ 44 የሞተው ሰው እጁና እግሩ በመገነዣ ጨርቅ እንደ ተጠቀለለ፣ ፊቱም በጨርቅ እንደ ተሸፈነ ወጣ፡፡ ኢየሱስ፣ “ፍቱትና ይሂድ” አላቸው፡፡ 45 ከዚያም ወደ ማርያም ከመጡትና ይህን ከተመለከቱት አይሁድ አብዛኛዎቹ በእርሱ አመኑ፤ 46 ነገር ግን ከእነርሱ አንዳንዶቹ ወደ ፈሪሳውያን ሄደው ኢየሱስ ያደረገውን ነገሯቸው፡፡ 47 ከዚያም ሊቀ ካህናቱና ፈሪሳውያን ጉባዔ ጠርተው፣ “ምን እናድርግ? ይህ ሰው ብዙ ምልክቶችን እያደረገ ነው፡፡ 48 እንደዚሁ የምንተወው ከሆነ፣ ሮማውያን መጥተው ስፍራችንና አገራችንንም ይወስዳሉ” አሉ፡፡ 49 ሆኖም በዚያ ዓመት ሊቀ ካህን የነበረ ከእነርሱ መካከል ቀያፋ የተባለው አንዱ፣ “እናንተ ምንም አታውቁም፤ 50 አገሪቱ በመላ ከምትጠፋ አንድ ሰው ስለ ሕዝቡ ቢሞት የተሻለ እንደሆነ ከግምት ውስጥ አላስገባችሁም” አላቸው፡፡ 51 እርሱ ይህን የተናገረው ከራሱ አልነበረም፣ ይልቁንም በዚያ ዓመት ሊቀ ካህን ስለ ነበረ፣ ኢየሱስ ስለ ሕዝቡ፣ 52 ደግሞም ስለ ሕዝቡ ብቻ ሳይሆን ነገር ግን በልዩ ልዩ ስፍራ የተበታተኑትን የእግዚአብሔርን ልጆች ይሰበስብ ዘንድ መሞት እንደሚገባው ትንቢት ተናገረ፡፡ 53 ስለዚህ ከዚያ ቀን ጀምሮ ኢየሱስን እንዴት መግደል እንዳለባቸው ዕቅድ አወጡ፡፡ 54 ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ በአይሁድ መካከል በግልጽ መውጣትና መግባቱን ትቶ ኤፍሬም ወደ ተባለው በበረሐው አጠገብ ወዳለው ከተማ ሄደ፡፡ እዚያ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ቈየ፡፡ 55 የአይሁድ የፋሲካ በዓልም ቀርቦ ነበረና ብዙዎች ራሳቸውን ያነጹ ዘንድ ከፋሲካው በፊት ከየገጠሩ ወደ ኢየሩሳሌም ይሄዱ ነበር፡፡ 56 ኢየሱስን እየፈለጉት፣ በቤተ መቅደስ ቆመው ሳሉ፣ “ምን ይመስላችኋል? ወደ በዓሉ አይመጣ ይሆን?” እያሉ እርስ በርሳቸው ይነጋገሩ ነበር፡፡ 57 ሊቀ ካህናቱና ፈሪሳውያኑም ኢየሱስን ይይዙት ዘንድ እርሱ የት እንዳለ ያወቀ ማንኛውም ሰው ጥቆማ እንዲያቀርብ ትእዛዝ አስተላለፉ፡፡
ይህ የሚቀጥለው ክፍል ታሪክ ስለ አልአዛር ነው፨ ይህ ጥቅሰ እሱን ሲያስተዋውቅ ስለእህቱ ሜሪእና ስለአልአዛር የኃላ መግለጫ ኣስተዋውቃል
የማርታን እህት ሜሪን ዮሀንስ እያስተዋወቀ ቀጥሎ ምን እንደሚሆን መግለጫ ያጋራ ነበር
እየሱሰስ እንዲመጣ ጠየቁት
እዚህ ፍቀር የሚያመለክተው ወንድማዊ ፍቅር ተፈጠሮአዊ የሰው ፍቅር በጓደኞች እና በዘመድ
እየሱስም ያመለከተው በአልአዛር ምን እንደሚሆንና ስለበሽታው ነው፨
የስጋ ሞትን ያመለክታል
እየሱሰ ውጤቱ ምን እንደሚሆን ያውቅ ነበር
የእግዚአብሄር ልጅ የሚለው ለእየሱስ አስፈላጊ ነው
የኃላ ታረክ መግለጫ
ይህ ነጥብ በጥያቄ መልክ የሆነው ደቀመዛሙርቱ አጽንኦት ሰተው እየሱስ ወደ እንዳይሄድ ስለፈለጉ ነው፨
እየሱስን የሚቃወሙ የአይሁድ መረዎች ማደንዘዣ ነበር
በጥያቄ መልክ የሆነው አጽንኦት ለመስጠት ነው፨
በቀን ብርሀን የሚመላሱ በደንብ ስለሚያዩ አይሰናከሉም፨ ብርሀን የእውነት መግለጫ ነው፨እየሱሰ ዕያለ ያለው እውነትን መሰረት አድረገው የሚኖሩ እግዚአብሄር ያዘዛቸውን መፈጸም ይችላሉ
እየሱስ ለደቀመዛሙርቱ መናገሩን ቀጠለ
ጭለማ የሚያመለክተው ከዕግዚአብሄር ብርሀን ውጪ መመላለስን ነው
ትርጉሙ ሊሆን የሚችለው 1) አያይም ወይም የእግዚአብሄር ብርሀን የለውም
ተኝቷል የሚለው ፈሊጠእ አልአዛር ሞቶአል፨ በናንተ ቋነቋ አባባል ካለ መጠቀም ትችላላችሁ
ከእንቅልፉ ላስነሳው እየሱሰ አልአዛርን ወደህይወት እንደሚመልሰው እቅዱን እያሳየ ነው፨ ናንተ ቋነቋ አባባል ካለ መጠቀም ትችላላችሁ
በቁጥር 13 ላየ ዮሃንስ ለደቀመዛሙርቱ እየሱስ ስለ አላዛር ማንቀላፋት የተናገረውነ እንዳልገባቸው
ደቀመዛሙርቱ እየሱስ ያለው አልገባቸውምና የመሰላቸው አልአዛር እርፍተ እያረገ ነው ይሻለዋልም
እንዲገባቸው እየሱሰ ቃል በቃል ነገራቸው
እየሱስም ደቀመዛሙርቱን ማናገር ቀጠለ
ለጥቅማችሁ
በዚያ አልነበርኩም፨ ስለዚህም ምክንያት በኔ ታምናላችሁ
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - "ዲዲሞስ ብለው የጠሩት"
የወንድ ስም መንታ ማለት ነው
ኤየሱስም በቢታንያ ነው፨ ይህ ቁጥር ከኃላ ያለውነ መረጃና እየሱስ ከመምጣቱ በፊት ያለውን ይገለጻል
ይህንን ኣሁን እንደሆነ መተርጎም ትችላላችሁ፨ የአልኣዘርን አስክሬን ከ4 ቀን በፈት በመቃብር እነዳኖሩት አወቀ፡
ሶስት ኪሊሜትር ይርቃል፨ ስታዲየም 185 ሜትር ነው
አልአዛር ታናሽ ወንድማቸው ነው፨ ሶስተኛ ወንድማቸው፨
አልአዛር ታናሽ ወንድም ነው፨ የኔ ታናሽ ወንድም በህይወት ይኖር ነበር
አልአዛር ታናሽ ወንድም ነው፨ ያንቺ ታናሽ ወንድምሽ አሁን ይነሳል፨
እንደገና በሕይወት ይኖራል
ሞት የሚያመለክተው ስጋ ሞትን ነው
ይኖራል የሚለው መንፈሳዊ ሕይወትን ነው፨
በእኔ የሚያምኑ ሁሉ በመንፈስ ከእግዚአብሄር አይለያዩም ወይም በእኔ የሚያምኑ በመንፈስ ከእግዚአብሄር ጋር ለዘላለም ይኖራሉ
ሞት የሚያመለክተው መንፈሳዊ ሞትን ነው
ማርታ ለእየሱስ አለች
ማርታም እየሱስ ጌታ የእግዚአብሄር ልጅ መሲሁ እንደሆነ ኣመነች
ይህ ለእየሱስ አሰፈላጊ ርዕስ ነው
ሜሪ የማርታ ታናሽ እህት ናት፨ ሄዳም ታናሽ እህቷን ሜሪን ጠራቻት፨
ይህ ርእሰ እየሱሰስን ያመለክታል
እንቺ እንድትመጪ ጠየቀ
ዮሀንስ በዚህ ክፍል ታሪኩን ኣቋርጦ እየሱስ ያለበትን አካባቢ መግለጫ ሰጠ
ሜሪ ክብር ለመስጠት በእየሱሰ እግር ላይ ወደቀች
አልአዛር የሜሪ ታናሽ ወንድሟ ነበር፨ ታናሽ ወንድሜ በህይወት ይኖረ ነበር፨
ዮሀንስ በዚህ ክፍል የእየሱስነን መታወክ መረበሽ ማዘን ይገልጻል፨ በጣም ተረብሾ ነበር፨
እየሱስ ማለቀስ ጀመረ ወይም እየሱስ አለቀሰ፨
ይህ የተለሳለሰ ጥያቄ ነወ። የት ቀበራችሁት?
ይህ ወንድማዊ ፍቅር ወይም የስ ው ፍቅር ለጓደኛ ወይም ለቤተሰብ አባል
ይህ ኣስተያየት እንደጥያቄ ያቀረቡት አይሁዶች እንዴት እየሱሰ አለአዛርን አለዳነውም ለማለት ነው፨ እውርን ያድናል ያበራል አልአዛርንም እነዳይሞት ሊያድነው በቻለ ነበር፨ ይህንን ሰው ከሞት ስላላዳለነው እውር ሆኖ የተወለደውንም አላዳነወም አዳነው ኣሉተ እንጂ
ይህ አባባል ነው፨ ዐይኑን አዳነው፨
ዮሀንስ ትንሽ ታሪኩን ኣቋርጦ አልኣዛርን የት እንደ ቀበሩት አስረዳ
ማርታና ሜሪ የ አልአዛር ታላቀ እህቶች ናቸው፨ ማርታ የ አልአዛር ታለቅ እህት
በዚህ ግዜ መጥፎ ሽታ ይኖራል ወይም አስከሬኑ መሽተት ጀምሮአል፨
ይህ አባባል በጥያቄ መልክ የሆነው እግዚአብሄር ቀጥሎ አስደናቂ ስራ ሊሰራ ስለሆን አጽንኦት ለመስጠት ነው፨ በኔ ብታምኚ የእግዚአብሄርን ስራ እንድታዪ ነግሪሽ ነበር
ይህ ወደላይ ማየትን ያመለክታል፨እየሱስ ወደ መንግሰተሰማያት ተመለከተ
እየሱሰ ቀጥታ ወደአባቱ መጸለዩ በአጠገቡ የነበሩት ጸሎቱን እንዲሰሙ ነው፨ አባ ስለሰማኀኝ ኣመሰግንሀለሁ፨ ወይም አባ ጸሎቴን ስለሰማህ አመሰግንሀሉ፨
ይህ ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ርእሰ ነው፨
አንተ እንደላከኝ እንዲያምኑ ጸለግሁ፨
ዕየሱስ ከጸለየም በሁዋላ
ጮኀ
በዚያን ግዜ ባህሉ የሞተን ሰው በረዥም ጨርቅ ይጠቀለል ነበር፨
እነሱ የሚለው በዚያ ተሰብስበው ለነበሩና ታምራቱን ላዩት
እነዚህ ቁጥሮች ኢየሱስ አልዓዛርን ከሞት ካስነሳ በኋላ ምን እንደ ሆነ ይነግሩናል።
ይህ የሚቀጥለው ክፍል ታሪክ ነው፨ የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን በአይሁድ ሽነጎ ተሰበሰቡ
ከቀሳወስቱ መካከል መሪዎቹም
የሸንጎው መሪዎችም ስለ እየሱስ እንደሚያወሩ የሳያል፨ ስለ እየሱስ ምን ማድረግ እንችላለን፨
የአይሁድ መሪዎችም ህዝቡ እየሱስነ ንጉሳቸው ያደርጉታል በለው ፈሩ፨ ሁሉም በርሱ ካመኑ በሮም ላይ ያምጻሉ፨
የሮም ጦር ሰራዊት የሮም ጦር ሰራዊት ይመጣሉ
ቤተ መቅደሳችንን እና ህእባችንን ያፈረሳሉ
አዲስ ሀሳብን ለማስተዋወቅ መንገዱ ይህ ነው፨ በራስህ ቋነቋ መግለጽ መንገድ ካለህ መጠቀም ትችላለህ፨
ቀያፋም እያጋነነ ለመናገር ነው እንደዛ ያለው፨ እየሆነ ያለውን ነገር አልገባችሁም፨ የምትናገሩት ምንም እንደማያውቅ ሆናችሁ ነው፨
ቀያፋ ማለት የፈለገው እየሱስ እንዲኖር ከተፈቀደ የሮም ጦር ሰራዊት የእስራኤልን ህዝብ ይገላሉ፨ ህዝብ የሚለው የሚያመለክተው እስራኤልን ህዝብ ነው፨ሮማውያን ህዝባችንን ሁሉ ከሚገሉ
በቁጥር 51 እና 52 ኬፋ ባያውቀውም ትንቢትን እየተናገረ ነበር፨ ይህ ለሚቀጥለው መግለጫ ነው፨
ህዝብ የሚለው የሚያመለክተው የእስራኤልን ህዝብ ነው
ይህ ኤሊፕሲስ ነው። “ሰዎች” የሚለው ቃል በጥቅሱ አውድ ተተክቷል ፡፡ አት: - “ወደ አንድ ህዝብ ይሰበሰባሉ”
ይህ የእግዚአብሄር የሆኑ ህዝቦችን በክርስቶሰ ያመኑት በመንፈስ የዕግዚአብሄር ልጆች የሆኑ
እየሱስም ከቢጣንያ ኤፍሪም ወደ ምትባል መንደር ሄደ፨ በቁጥር 55 ላይ የፋሲካ በዓል ደርሶ ስለነበር አይሁዶች ምን እንደሚሰሩ ይነግረናል፡፡
አይሁድ የሚለው የአይሁድ መሪዎችን ነው፨ በሚቃወሙተ አይሁዶች መካከል በግልጽ ይመላለሳል
ከከተማ ወጣ ያለ ጥቂት ህዝብ የሚኖሩበት
እየሱሰስና ደቀመዛሙርቱ ለጥቂት ጊዝ በኤፍሬም ቆዩ፨ በዚያ ከደቀመዛሙርቱ ጋር ለጥቂት ጊዜ ቆየ
ወጣ የሚለው ኢየሩሳለምን ከአካባቢው ካሉ ከተሞች ከፍታ ላይ መሆኗን ለማመልከት ነው
በቁጥር 57 ላይ የሆነው የተጻፈው ከቁጥር 56 በፊት ነው፨ ቅደም ተከተሉ አንባቢዎችን የሚያደናግር ከሆነ ቁጥሮቹን ማዋሀድ እና የ 57 ጽሁፍ ከ 56 በፊት ማድረግ ተችላለህ፨
እነዱ የሚለው ቃል ወደ የሩሳሌም የተጓዙትን አይሁዶች ለማመልከት ነው
ይህ የተሀድሶ ጥያቄ የሚገልጸው እየሱሰ ወደ ፋሲካ በዓል መምጣቱን በመጠራጠር ነበር፨ ሁለተኛወ ጥያቄ ታስባለህን ተናጋሪው እየሱሰ ወደ በአሉ ቢመጣ የመታሰር እድሉ ከፍተኛ ስለሆን ይገረም ነበር፨ እየሱስ ምናልባት ወደ በዓሉ አይመጣም። እታሰራለሁ ብሎ ይፈራል፨
ይህ መግለጫ የሚያስረዳው የአይሁደ አምላኪዎች እየሱስ በበዓሉ ለመገኛት ይመጣ ይሆን ብለው መገረም ነበረባቸው፨ በቋነቋህ
1 የፋሲካ በዓል ሊከበር ስድስት ቀናት ሲቀሩት ኢየሱስ ከሞት ያስነሣው አልዓዛር ወደ ነበረበት ወደ ቢታንያ መጣ፡፡ 2 ስለዚህ በዚያ እራት አዘጋጁለት፣ አልዓዛር ከኢየሱስ ጋር በማዕድ ከተቀመጡት ጋር ሲሆን ማርታ ደግሞ ታገለግላቸው ነበር፡፡ 3 ማርያም ከንጹሕ ናርዶስ የተሠራ በጣም ውድ የሽቱ ብልቃጥ ወስዳ የኢየሱስን እግር ትቀባ፣ በፀጉሩዋም ታብስ ስለነበር፣ ቤቱ በሽቱው መዓዛ ታወደ፡፡ 4 ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ ኢየሱስን አሳልፎ የሚሰጠው የአስቆሮቱ ይሁዳ፣ 5 “ይህ ሽቱ በሦስት መቶ ዲናር ተሸጦ ለድሆች ያልተሰጠው ለምንድን ነው?” አለ፡፡ 6 ይህን ያለው ለድሆች ተገዶላቸው ሳይሆን ሌባ ስለነበረ ነው፤ የገንዘብ ከረጢቱን የሚይዘው እርሱ ስለነበረ፣ ከዚያ ውስጥ ለራሱ ጥቂት ይወስድ ነበር፡፡ 7 ኢየሱስ፣ “የያዘችውን ለቀብሬ ቀን እንድታቆየው ፍቀዱላት፤ 8 ድሆች ምንጊዜም ከእናንተ ጋር ይሆናሉ፣ እኔን ግን ሁልጊዜ አታገኙኝም” አላቸው፡፡ 9 ብዙ የአይሁድ ሕዝብም ኢየሱስ በዚያ እንደነበረ ተረድተው ነበርና ወደዚያ መጡ፣ የመጡትም ለኢየሱስ ብቻ ብለው ሳይሆን ኢየሱስ ከሞት ያስነሣውን አልዓዛርንም ለማየት ጭምር ነበር፡፡ 10 የካህናት አለቆች አልዓዛርን ደግሞ ለመግደል በአንድነት የተንኮል ስምምነት አደረጉ፣ 11 ምክንያቱም ብዙ አይሁድ የሄዱትና በኢየሱስ ያመኑት ከእርሱ የተነሣ ነበር፡፡ 12 በማግስቱ ብዙ ሕዝብ ወደ በዓሉ መጡ። ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም መምጣቱን በሰሙ ጊዜ፣ 13 የዘንባባ ዛፍ ዝንጣፊ ይዘው፣ “ሆሣዕና! በጌታ ስም የሚመጣ የእስራኤል ንጉሥ የተባረከ ነው” እያሉ ሊቀበሉት ወጡ፡፡ 14 ኢየሱስ የአህያ ውርንጫ አገኘና ተቀመጠባት፣ ይህንን ያደረገው፣ 15 “የጽዮን ልጅ ሆይ፣ አትፍሪ፣ እነሆ፣ ንጉሥሽ በአህያ ውርንጫ ላይ ተቀምጦ ይመጣል” ተብሎ በተጻፈው መሠረት ነው፡፡ 16 ደቀ መዛሙርቱ በመጀመሪያ ይህን አልተረዱም ነበር፣ ኢየሱስ በከበረ ጊዜ ግን እነዚህ ነገሮች ስለ እርሱ ተጽፈው እንደነበረና እነርሱም እነዚህን ነገሮች ለእርሱ እንዳደረጉለት ተገነዘቡ፡፡ 17 ኢየሱስ አልዓዛርን ከመቃብር በጠራውና ከሞት ባስነሣው ጊዜ በዚያ የነበሩት ሕዝብም ለሌሎች መሰከሩላቸው፡፡ 18 ይህን ምልክት እንዳደረገ ሰምተው ነበርና ሊቀበሉት የወጡትም በዚህ ምክንያት ነበር፡፡ 19 ስለዚህ ፈሪሳውያን እርስ በርሳቸው፣ “ምንም ማድረግ እንደማትችሉ ተመልከቱ፣ ዓለሙ ተከትሎታል” ተባባሉ፡፡ 20 በበዓሉ ሊያመልኩ ከሄዱት መካከል አንዳንድ የግሪክ ሰዎችም ነበሩ፡፡ 21 እነዚህ በገሊላ ካለችው ከቤተሳይዳ ወደ ሆነው ወደ ፊልጶስ ዘንድ ሄደው፣ “ጌታ ሆይ፣ ኢየሱስን ማየት እንፈልጋለን” አሉት፡፡ 22 ፊልጶስ ሄዶ ለእንድርያስ ነገረው፣ እንድርያስና ፊልጶስም ዐብረው ሄዱና ለኢየሱስ ነገሩት፡፡ 23 ኢየሱስም፣ “የሰው ልጅ የሚከብርበት ሰዓት ደርሷል፤ 24 እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ፣ የስንዴ ዘር ወደ ምድር ወድቃ ካልሞተች ብቻዋን ትቀራለች፤ ከሞተች ግን ብዙ ፍሬ ታፈራለች፡፡” ብሎ መለሰላቸው፡፡ 25 ሕይወቱን የሚወድ ያጠፋታል፤ ነገር ግን በዚህ ዓለም እያለ ሕይወቱን የሚጠላ ለዘላለም ሕይወት እንድትጠበቅ ያደርጋታል። 26 ማንም ሊያገለግለኝ የሚወድ ይከተለኝ፤ እኔ ባለሁበት አገልጋዬም በዚያ ይሆናል። ማንም ቢያገለግለኝ አብ ያከብረዋል። 27 አሁን ነፍሴ ታውካለች ምን እላለሁ? 'አባት ሆይ፣ ከዚህ ሰዓት አድነኝ' ነገር ግን ስለዚህ ጉዳይ ወደዚህ ሰዓት መጥቻለሁ። 28 አባት ሆይ፣ ስምህን አክብረው።» ከዚያም ከሰማይ፣ «አክብሬዋለሁ ደግሞም አከብረዋለሁ» የሚል ድምፅ መጣ።። 29 ባጠገቡ ቆመው የነበሩትና ድምፁን የሰሙት ብዙ ሕዝብ ነጐድጓድ መሰላቸው። ሌሎች ደግሞ «መልአክ ተናግሮታል» አሉ። 30 ኢየሱስ መልሶ፣ «ይህ ድምፅ የመጣው ስለ እኔ ሳይሆን ስለ እናንተ ነው» አለ። 31 በዚህ ዓለም ላይ የሚፈረድበት ጊዜ አሁን ነው፤ አሁን የዚህ ዓለም ገዢ ወደ ውጭ ይጣላል። 32 እኔ ከምድር ከፍ ከፍ በምልበት ጊዜ፣ ሰውን ሁሉ ወደ ራሴ እስባለሁ።» 33 ይህን የተናገረው በምን ዓይነት ሁኔታ እንደሚሞት ለማመልከት ነበር። 34 ሕዝቡ፣ «ክርስቶስ ለዘላለም እንደሚኖር ከሕጉ ሰምተናል። ታዲያ 'የሰው ልጅ ከፍ ከፍ ማለት አለበት እንዴት ትላለህ?' ይህስ የሰው ልጅ ማን ነው?» ብለው መለሱለት። 35 ከዚያም ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፤ «አሁን ለጥቂት ጊዜ ብርሃን በመካከላችሁ አለ፤ ጨለማ እንዳይውጣችሁ በዚህ ብርሃን ተመላለሱ። በጨለማ የሚመላለስም ወዴት እንደሚሄድ አያውቅም። 36 የብርሃን ልጆች እንድትሆኑ ብርሃኑ እያለላችሁ በብርሃኑ እመኑ።» ኢየሱስ ይህን ከተናገረ በኋላ ከእነርሱ ተለየ፤ ተሰወረባቸውም። 37 ምንም እንኳ ኢየሱስ በሕዝቡ ፊት ብዙ ምልክቶችን ቢያደርግም በእርሱ አላመኑም። 38 ይህም ነቢዩ ኢሳይያስ፣ «ጌታ ሆይ የተናገርነውን ማን አመነ? የጌታስ ክንድ ለማን ተገለጠ?» በማለት የተናገረው ቃል እንዲፈጸም ነው። 39 በዚህም ምክንያት ማመን አልቻሉም፤ ኢሳይያስ እንደ ገና እንዲህ ብሏልና፤ 40 «ዐይኖቻቸውን አሳውሯል፤ ልባቸውንም አደንድኗል፤ ይህም የሆነው በዐይናቸው ዐይተው በልባቸው አስተውለውና ተመልሰው እንዳልፈውሳቸው ነው።» 41 ኢሳይያስ እነዚህን ነገሮች የተናገረው የኢየሱስን ክብር ስላየና ስለ እርሱም ስለ ተናገረ ነው፤ 42 የሆነ ሆኖ ከገዢዎች እንኳ ብዙዎች በኢየሱስ አምነዋል፤ ነገር ግን ፈሪሳውያን ከምኵራብ እንዳያግዷቸው በመፍራት ማመናቸውን አልገለጹም። 43 በእግዚአብሔር ከመመስገን ይልቅ በሰዎች ለመመስገን ወደዱ። 44 ኢየሱስ ድምፁን ከፍ አድርጎ እንዲህ አለ፤ «በእኔ የሚያምን በእኔ ብቻ የሚያምን ሳይሆን በላከኝም ያምናል፤ 45 እንደዚሁም እኔን የሚያይ የላከኝንም ያያል። 46 በእኔ የሚያምን በጨለማ ውስጥ እንዳይኖር ብርሃን ሆኜ ወደ ዓለም መጥቻለሁ፤ 47 ማንም ቃሌን ሰምቶ ባያደርገው የምፈርድበት እኔ አይደለሁም፤ ዓለምን ለማዳን እንጂ በዓለም ላይ ልፈርድ አልመጣሁምና። 48 እኔን የሚቃወምና ቃሌንም የማይቀበል የሚፈርድበት አለ፤ በመጨረሻው ቀን የሚፈርድበት እኔ የተናገርሁት ቃል ነው። 49 ምክንያቱም ይህ ቃል ከራሴ የተናገርሁት አይደለም፤ ይልቁን ምን እንደምልና እንደምናገር ትእዛዝ የሰጠኝ የላከኝ አብ ነው። 50 ትእዛዙም የዘላለም ሕይወት እንደሚያስገኝ አውቃለሁ፤ ስለዚህ የምናገረው ቃል አብ እንደ ነገረኝ የምናገረው ነው።»
ይህ የሚቀጥለው ታሪ ክፍል ነው፨ እየሱስ በቢታንያ በእራት ላይ ሳለ ሜሪ እግሮቹን በዘይት ቀባችው
የክብደት መለኪያ ነው፨ የአንድ ኪሎ ግራም አንድ ሶሰተኛ ነው፨
ጥሩ መአዛ ያለው ፈሰሽ ሲሆን ትሩ ሽታ ካላቸው አትክልቶች ዘይት የሚሰራ ነው፨
የደወል ቅርጽ ካለው አበባ የሚሰራ ሽቶ ሲሆን የሚገኘውም ኔፓል ቻይና ህንድ ተራራዎች ላይ ነው
ይህ ኣሁን እነደተደረገ መተርጎም ይቻላል፨ የሽቶው መአዛ ወይም ሽታወ ቤቱን ሞላው፨
የእየሱሰ ጠላቶች እንዲይዙት ያደረገው
ጥያቀያዊ አነጋገር ነው፨ እንደ ከባድ አረፍተነገር መተርጎም ተችላለህ፨ ይህ ሽቶ ለሶስተ ሞተ ዲናር ተሽጦ ገንዘቡን ለድሆች መስጠት ይቻል ነበር፨
በቁጥርም መተርጎም ትችላለህ፨ 300 ዲናር
ዮሀንስ ይሁዳ ስለምን ስለድሆች እንደጠየቀ ያስረደዳል፨ በቋንቋህ በተሻለ ማስረዳት ከቻልክ መጠቀም ትችላለህ፨
ይህነ ያለው ሌባ ስለነበረ ነው፨ ስለድሆች ግድ አልነበረውም፨
እሷ ያረገችው ለሞቱ እና ለቀብሩ ምን ያህል እንዳደነቀችኝ እንድታሳይ ተዉአት! በዚህ መንገድ ሰውነቴን ለቀብር አዘጋጅታለች
ዕየሱስ ይህንን ማለቱ ድሆችን ለመርዳት ብዙ ኣጋጣሚዎች አሉ፨ ድሆች ሁሌም በመካከላቸሁ አሉ፤ በፈለጋችሁ ግዜ ልትረዱአቸው ተችላላችሁ
ይህን ማለቱም እንደሚሞት ለመንገር ነው፨ እኔ ግን ሁሌም ከናንተ ጋር እዚህ የለሁም፨
ይህን ቃል የተጠቀመው ከዋናው ታሪክ ለማረፍ ነው ዮሃነስ አዲስ ሰዎች ከቢታኒያ ወደ እየሩሳለም አንድ መጡ ለመንገር ነው፨
የአላአዛር ከሞት መነሳት ብዙ አይሁዶች እንዲያምኑ ሆነ
ይህ የሚያመለክተው ብዙ አይሁዶች እየሱስ የእግዚአብሄር ልጅ እንደሆነ ኣመኑ፨ እምነታቸውነ በእየሱስ ላይ ጣሉ፨
ይህ የሚቀጥለው ታረክ ክፍለ ነው፨ እየሱስ ወደ እየሩሳለም ገበ ህዝቡም እንደ ንጉስ አከበሩት
ብዙ ህዝብ ሰብስብ
ይህ ማለት እግዚአብሄር አሁን ያድነን
ይህ የእግዚአብሄርን መልካም ፍላጎት ለሰው ያለውነ ያሳያል
እዘህ ስም የሚለው የሚያመለክተው በስልጣንና በኃይል ነው፨ በእግዚአብሄር የተወከለ ወይም በእግዚአብሄር ኃይል የመጣ
ዮሃነሰ እየሱስ አህያዋን እንዴት እንዳገኘ ያስረዳል፨ በአህያ ውርንጫ ተቀምጦ ወደ እየሩሳሌም እንደሚገባ ያስረዳል፨ የአህያ ውርነጫ አገኘ ተቀመጠባትም ወደ ከተማውም ገባ
አሁን እንደተደረገ ኣድርገህ መተርጎም ተችላለህ፨ ነቢዩ እንደጻፈው
የጽዮን ልጅ የሚያመለክተው የእስራኤልን ህዝብ ነው
ዮሀንስ ጻሀፊው እዚህ ላእ ኣቋርጦ ደቀመዛሙርቱ ቆይተው የገባቸውን ነገር መግለጫ ይሰጣል
ይህን ነገር የሚለው ነቢያቶች ስለ እየሱስ የጻፉትን ለማለት ነው
አሁን እንደተደረገ መተርጎም ቲችላለህ፨ ዕግዚአብሄር እየሱስነ ሲያከብረው
ይህንን ነገር የሚለው የሚያመለክተው እየሱስ በአህያ ውርንጫ ተቀምጦ ወደ እየሩሳለምነ ሲገባ እያወደሱት ዘንባባ ዝንጣፊ ያወዛውዜ ነበር
ይህ ቃል ትረካውን ቆም ለማድረግ ነው፨ ዮሃንስ እዚህ የሚያስረዳወው ብዙ ህዘብ የመጣው አልአዛርነ ከሞት እንዳስነሳው ስለሰሙ ነው፨
ለሎች ብዙ ምልክቶችን እንዳደረገ ሲያወሩ ሰሙ
ፈሪሳውያኑም ኢየሱስን ማቆም እንደማይቻል አሰቡ፨ እሱን ለማቆም ምንም ማድረግ አንችልም እንደማለት ይመስላል
ፈሪሳውያኑ እየሱስን ብዙ ሰው እነደተከተሉት ባዩ ግዜ ፍርሀት ውስጥ ስለነበሩ ዕያጋነኑ ገለጹ፨ ሁሉም የርሱ ደቀመዝሙር የሆነ ይመስላል፨
አለም የሚለው ለማጋነን የተጠቀሙበት የዓለም ህዝብ ሁሉ
የተወሰኑ የሚለው አዲሰ ገጸ ባህሪን ለማስተዋወቀ ነው
ዮሀንስ ግሪኮች በፋሲካ በዓል እግዚአብሄርን ለማምለክ ይሄዱ ነበር፨እግዚአብሄርነ በፋሲካ በዓል ለማክበር፨
በገሊላ ውስጥ ያለች ከተማ
ፊሊፖስና እንድርያስ የግሪክ ሰዎች ሊያዩት እንደሚፈልጉ ነገሩት፨ ግሪኮችም ምን እነዳሉት ነገሩት፨
እየሱስም ለፊሊፖስና እንድርያስ መለሰላቸው
እየሱስ ይህን ያለው እግዚአብሄር ልጁን በስቃይ በሞት እና ከሞት በማስነሳት የሚከብርበት ሰዓት ትክክለኛው ሰዓት እንደደረሰ ለማስረዳት ነው
የሚከተለው የሚከተለው አስፈላጊ እና እውነት መሆኑን በቋንቋዎ አፅን emphasiት በመስጠት ይህንን ይተረጉሙ ፡፡ በ 1 49 ውስጥ “በእውነት ፣ በእውነት” እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
እዚህ “የስንዴ እህል” ወይም “ዘር” ለኢየሱስ ሞት ፣ የቀብር እና የትንሳኤ ምሳሌ ነው። አንድ ዘር እንደተተከለ እና ብዙ ፍሬ ወደሚያፈራ ተክል እንደገና እንደሚበቅል ፣ እንዲሁ ከሞተ ፣ ከተቀበረ እና ከሞት ከተነሳ በኋላ ብዙ ሰዎች በኢየሱስ ያምናሉ።
ህይወቱን የሚወድ የሚያመለክተው የራስን ህይወት ከሌላወ ህይወት አስበልጦ ማየት፨ የራሱን ህይወት ከሌላው አስበልጦ የሚያየእ የዘላለም ህይወት አይቀበልም
እዚህ ላይ “ሕይወቱን የሚጠላ” የሚያመለክተው የሌሎችን ሕይወት ከሚወድደው በታች የሆነውን የራሱን ሕይወት የሚወድ ነው ፡፡ አት: - “የሌሎችን ሕይወት ከራሱ የበለጠ አስፈላጊ እንደሆነ አድርጎ የሚቆጥር ሁሉ ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላለም ይኖራል” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
እየሱስ እኔን የሚያገለግል ሁሉ ከርሱ ጋር በገነት ይኖራሉ ማለቱ ነው፨ እኔ በገነት ስሆን አገልጋዮቹ=ቼም በገነት ከኔ ጋር ይሆናሉ
አባት የሚለው ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ነው
ይህ አስተያየት እንደ ንግግራዊ ጥያቄ ነው። እየሱሰ ስቅለቱ እንዲያልፍለት ቢመኝም ለአባቱ ታዛዥ መሆንን መርጦ ለመሞት ወሰነ ከዚህ ሰዓት ኣድነኝ ብዪ አልጸልይም
ይህ ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ርእሰ ነው
ሰዓቱ የሚለው እየሱሰ በመስቀል ተሰቃይቶ የሚሞትበትነ ነው የሚያመለክተው
ስም የሚለው እግዚአብሄርን ነው የሚገልጸው፨ ክብርህ ይታይ ወይም ክብርህ ይገለጽ
የእግዚአብሄርን ነግግር ይወክላል፨ አንዳንድ ግዜ ሰዎች ወደ እግዚአብሄር ማመለክት ይፈራሉ ስለሚያከብሩት፨ እግዚአብሄር ከሰማይ ተናገረ
ድምጽ ከሰማይ ለምን እንደመጣ እየሱስ ኣስረዳ
ዐለም የሚለው በጠቅላላ የአለምን ሕዝብን ያመለክታል እግዚአብሄር በሰው ልጆች ላይ ሊፈርድ ሰዓቱ ኣሁን ነው
ገዢ የሚለው ሰይጣንን ያመለክታል፨ የዘህን አለም ገዢ ሰይጣንን የማፈርስበት ጊዜው ኣሁን ነው፨
በቁጥር 33 ላይ ዮሃነስ ወደ ላይ ከፍ ስለ ማለት እየሱስ የተናገረውን ይገልጻል
ስለ ስቅላቱ ነበር የሚለው፨ ሰዎች ወደ መስቀሉ ከፍ ሲያረጉኘ
በስቅላቱ እየሱስ ለሁሉም እንዲያምኑተ መንገድን ያዘጋጃል
ዮሀንስ የእየሱስን ቃል ሲያብራራ ሰዎች እንደሚሰቅሉት ገለጸ፨ ይህንንም ያለው እንዴት እንደሚሞት ሰዎች እንዲያዊቁት ነው፨
ከፍ ማለት መሰቀልን ያመለክታል፨ የሰው ልጅ በመስቀል ላይ ከፍ ሊል ወይም ለሰቀል ይገባዋል
ትርጉሙ ሊሆን የሚችለው 1) ይህ የሰው ልጅ ማን ነው? 2) ስለ የትኛው የሰው ልጅ ነው የምታወሩት?
እዚህ “ብርሃን” የእግዚአብሔርን እውነት የሚገልጥ የኢየሱስ ትምህርቶች ዘይቤ ነው ፡፡ “በጨለማ ውስጥ መሄድ” ያለ እግዚአብሔር እውነት መኖርን የሚያሳይ ዘይቤ ነው። አት: - ቃሌ እግዚአብሔር እንደሚፈልግህ እንዴት እንደምኖር እንድትረዳ ቃሌ እንደ ብርሃንህ ብርሃን ነው ፡፡ እኔ ከአንተ ጋር ገና አልሆንም ፡፡ አሁንም እኔ ከአንተ ጋር እያለሁ መመሪያዎቼን መከተል አለብህ ፡፡ ቃሌን ፣ በጨለማ ውስጥ እንደ መጓዝ ይሆናል ፣ ወዴት እንደምትሄድም አታይም ፡፡ ”(ይመልከቱ ፡፡
“ብርሃን” የእግዚአብሔርን እውነት የሚገልጥ የኢየሱስ ትምህርቶች ዘይቤ ነው ፡፡ “የብርሃን ልጆች” የኢየሱስን መልእክት የሚቀበሉ እና በእግዚአብሔር እውነት ለሚኖሩ ሰዎች ምሳሌ ነው። AT: - “እኔ ከእናንተ ጋር ሳለሁ የእግዚአብሔር እውነት በእናንተ ውስጥ እንዲኖር ቃሌን ተቀበል” (የበለስ_ማይታፎርን ይመልከቱ)
የሆንስ ታረኩን አቋርጦ በነቢዩ ኢሳያስ የተነገረውን ትንቢቱ እንደተፈጸመ ኣስረዳት ጀመረ
የነቢዩ የኢሳያስ ትንቢት የፈጸም ዘንደ
ይህ በጥያቄ መለክ የተጻፈው የነቢዩ ኢሳያስን መልእክት እንዳላመኑ ለመግለጽ ነው፨
የእግዚአብሄርን የማዳን ክንድ ኃይል ለመግለጽ
እግዚአብሄርም ልባቸውን ኣደነደነ፨ ግትር ኣደረጋቸው፨
አይሁዶች ልብ እንዲገባን የሚያደርግ የሰውነት ክፍል ነው ብለወ ያምናሉ
ሰዎች ወደ አይሁድ ማምለኪያ ቦታ እንዳይገቡ እነዳያደርጓቸው
ዕግዚአብሄር ከሚያከብራቸው በይላ ሰዎች እንዲያከብሩዋቸው ይፈልጉ ነበር
ዮሀናእስ ወደዋናው ትረካ ይመለሳል፨ ይሀ በሌላ ግዜ እየሱስ ለህዘቡ ሲናገር ነው፨
ብዙ ህዝበ ተሰብሰቦ እየሱስ ሲናገር ይሰሙ ነበር፨ እየሱስም ለተሰበሰበው ህዝብ ጮኸ
እሱ የሚለው እግዚአብሄርን ያመለክታል፨ እኔን ያየ የላከኝን እግዚአብሄርን ያያል፨
እየሱስም ለተሰበሰበው ህዝብ መናገሩን ቀጠለ
ብርሀን የሚለው የእየሱሰ ምሳሌ ነው፨ እውነትን ለማሳየት መጥቻለሁ፨
ጭለማ የዕግዚአብሄርን አውነት ኣቶ በድንቁርና መኖር፨ መንፈሳዊ እውር ሆኖ ላይቀጥል ይችላል፨
እዚህ “በዓለም ላይ መፍረድ” ማለት ኩነኔ ማለት ነው ፡፡ ኢየሱስ የመጣው ሰዎችን ለመኮነን አይደለም ፡፡ አት: - "ማንም ትምህርቴን ቢሰማና ቢቃወም አላውቀውም ፣ እኔ አላውቅም ፡፡ ሰዎችን ለመፍረድ አልመጣም ፡፡ ይልቁን በእኔ የሚታመኑትን ለማዳን ነው ፡፡"
እዚህ “ዓለም” በዓለም ውስጥ ያሉትን ሁሉንም ህዝብ የሚወክል ቃል ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ጥበብ)
እግዚአብሄር በኃጢአተኞች ላይ ሲፈርድ
እንደናገር የሰጠኝ ትዕዛዛት ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣል፨
ይህ የእግዚአብሔር አስፈላጊ መጠሪያ ነው
1 በዚህ ጊዜ ኢየሱስ ከፋሲካ በዓል በፊት ከዚህ ዓለም ተለይቶ ወደ አብ የሚሄድበት ሰዓት እንደ ደረሰ ስላወቀ፣ ቀድሞውኑ የሚወዳቸውን በዓለም ይኖሩ የነበሩትን የራሱን ወገኖች እስከ መጨረሻው ወደዳቸው። 2 ዲያብሎስም ኢየሱስን አሳልፎ እንዲሰጥ በስምዖን ልጅ በአስቆሮቱ ይሁዳ ልብ ክፉ ዐሳብ አስገባ። 3 ኢየሱስ አብ ሁሉን ነገር በእጁ አሳልፎ እንደ ሰጠው፣ ከእግዚአብሔር እንደ መጣ ወደ እግዚአብሔርም ተመልሶ እንደሚሄድ ዐወቀ፤ 4 ከእራት ላይ ተነሣ፤ መጎናጸፊያውንም አስቀመጠ፤ ከዚያም ፎጣ ወስዶ ወገቡ ላይ ከታጠቀ በኋላ 5 በሳሕን ውስጥ ውሃ ጨምሮ የደቀ መዛሙርቱን እግር ማጠብና በያዘውም ፎጣ ማበስ ጀመረ። 6 ወደ ስምዖን ጴጥሮስ መጣ፤ ጴጥሮስም «ጌታ ሆይ የእኔን እግር ልታጥብ ነውን?» አለው 7 ኢየሱስም «የማደርገውን አሁን አይገባህም፤ወደፊት ግን ትረዳዋለህ» በማለት መለሰለት 8 ጴጥሮስም «ፈጽሞ የእኔን እግር አታጥብም» አለው ኢየሱስም «እግርህን ካላጠብሁህ ከእኔ ጋር ዕድል ፈንታ አይኖርህም» ሲል መለሰለት 9 ስምዖን ጴጥሮስም «ጌታ ሆይ እንግዲያስ እግሬን ብቻ ሳይሆን እጄንና ራሴንም እጠበኝ» አለው 10 ኢየሱስም «ገላውን የታጠበ እግሩን ብቻ ከመታጠብ በስተቀር ሌላ ሰውነቱ ንጹህ ነው፤ እናንተ ንጹሓን ናችሁ ነገር ግን ይህን ስል ሁላችሁንም ማለቴ አይደለም» 11 ኢየሱስ «ሁላችሁም ንጹህ አይደላችሁም» ያለው ኣሳልፎ የሚሰጠው ማን እንደሆነ ያውቅ ስለነበረ ነው 12 ኢየሱስ እግራቸውን አጥቦ ከጨረሰ በኋላ ልብሱን ለብሶ ተቀመጠ፤ እነርሱንም፣ «ያደረግሁላችሁን ልብ ብላችኋል? 13 'መምህር' እና 'ጌታ' ትሉኛላችሁ። እንደዚያም ስለሆንሁ አባባላችሁ ትክክል ነው። 14 እኔ ጌታና መምህር ሆኜ እግራችሁን ካጠብሁ፣ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ልትተጣጠቡ ይገባል። 15 እኔ እንዳደረግሁላችሁ እንደዚያው ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ትቼላችኋለሁ። 16 እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ፣ አገልጋይ ከጌታው አይበልጥም ወይም የተላከ ሰው ከላኪው አይበልጥም። 17 እነዚህን ነገሮች ብታውቁና ብታደርጓቸው የተባረካችሁ ናችሁ። 18 የምናገረው ሁላችሁን በሚመለከት አይደለም፤ የመረጥኋቸውን አውቃለሁና፣ ነገር ግን እንደዚህ የምናገረው እንጀራዬን የበላ በእኔ ላይ ተረከዙን አነሣ የሚለው የመጽሐፉ ቃል እንዲፈጸም ነው። 19 ከመሆኑ በፊት አስቀድሜ የምነግራችሁ በሚፈጸምበት ጊዜ እኔ እንደሆንሁ እንድታምኑ ነው። 20 እውነት እውነት እላችኋለሁ እኔን የሚቀበል የላክሁትን ይቀበላል፤ እኔን የተቀበለ ደግሞ የላክኝን ይቀባላል» 21 ኢየሱስ ይህን በሚናገርበት ጊዜ በመንፈሱ ታወከ፤ «እውነት እውነት እላችኋለሁ ከእናንተ መካከል አንዱ አሳልፎ ይሰጠኛል» ብሎ በግልጽ ነገራቸው 22 ደቀ መዛሙርቱም ስለማን እየተናገረ እንደሆነ ስላልገባቸው እርስ በርስ ተያዩ። 23 ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የሆነው ኢየሱስ ይወደው የነበረው ደቀ መዝሙር ወደ ደረቱ ተጠግቶ ተቀምጦ ነበር። 24 ስለዚህ ስምዖን ጴጥሮስ ወደዚህ ደቀ መዝሙር ጠጋ ብሎ «ንገረን ለመሆኑ ስለ ማን ነው እየተናገረ ያለው?» በማለት ጠየቀው። 25 ወደ ኢየሱስ ደረት ተጠግቶ የተቀመጠው ደቀ መዝሙርም፣ «ጌታ ሆይ፣ ይህ የምትለው ሰው ማን ነው?» ብሎ ጠየቀው። 26 ከዚያም ኢየሱስ፣ «ይህን ቍራሽ እንጀራ ከወጭቱ አጥቅሼ የምሰጠው ያ ሰው እርሱ ነው» በማለት መለሰለት። ስለዚህ ቍራሹን እንጀራ አጥቅሶ ለአስቆሮቱ ይሁዳ ሰጠው። 27 ቍራሹንም እንጀራ ከተቀበለ በኋላ፣ ሰይጣን ገባበት። ከዚያም ኢየሱስ፣ «ለማድረግ ያሰብኸውን ፈጥነህ አድርግ» አለው። 28 ኢየሱስ ለይሁዳ እንደዚያ ለምን እንዳለው በማዕድ ላይ ከተቀመጡት ማንም ያወቀ የለም። 29 አንዳንዶቹ ይሁዳ ገንዝብ ያዥ ስለ ነበር፣ ኢየሱስ «ለበዓሉ የሚያስፈልጉንን ነገሮች ግዛ» ወይም ለድኾች ገንዘብ ስጥ ብሎ ነግሮታል ብለው ዐሰቡ። 30 ይሁዳ ቍራሹን እንጀራ ከተቀበለ በኋላ፣ ፈጥኖ ወጣ ምሽትም ነበረ። 31 ይሁዳ በሄደ ጊዜ፣ ኢየሱስ እንዲህ በማለት ተናገረ፤ «አሁን የሰው ልጅ ከብሯል፣ እግዚአብሔርም በእርሱ ከብሯል። 32 እግዚአብሔር በራሱ ያከብረዋል፣ ደግሞም ፈጥኖ ያከብረዋል። 33 ልጆች ሆይ፣ ከእንግዲህ ከእናንተ ጋር የምቆየው ለጥቂት ጊዜ ነው። እናንተ ትፈልጉኛላችሁ፣ ይሁን እንጂ፣ ለአይሁድ፣ 'እኔ ወደምሄድበት እናንተ ልትመጡ አትችሉም' እንዳልኋቸው፣ ለእናንተም የምናገረው እንደዚያ ነው። 34 እርስ በርሳችሁ እንድትዋደዱ ዐዲስ ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ፤ እኔ እንደ ወደድኋችሁ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ። 35 እርስ በርሳችሁም ብትዋደዱ የእኔ ደቀ መዛሙርት እንደ ሆናችሁ ሰዎች በዚህ ያውቃሉ።» 36 ስምዖን ጴጥሮስ «ጌታ ሆይ፣ ወዴት ልትሄድ ነው?» ሲል ጠየቀው። ኢየሱስ፣ «ወደምሄድበት አሁን ልትከተለኝ አትችልም፣ በኋላ ግን ትከተለኛለህ» በማለት መለሰለት። 37 ጴጥሮስ፣ «ጌታ ሆይ፣ አሁን ልከተልህ የማልችለው ለምንድን ነው? ስላንተ ሕይወቴን እንኳ አሳልፌ ለመስጠት ቈርጫለሁ» አለው። 38 ኢየሱስ፣ «ስለ እኔ ሕይወትህን አሳልፈህ ትሰጣለህን? እውነት፣ እውነት እልሃለሁ፣ ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ» ብሎ መለሰለት።
ገና የፋሲካ በዓል አልሆነምና እየሱሰ ከደቀመዛሙርቱ ጋር በራት ላይ ነበር፨ ይህ ታሪክ የሚያስረዳው የእየሱስንና የይሁዳን
ይህ ርዕሰ ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ነው፨
ይህ ዓየነት ፍቅር ከእግዚአብሄር የሚመጣ በሰዎች ምለካምነት ላይ ያተኮረ ራስን የማይጠቅም ቢሆን እንኳን። የፈለጉትን ስራ ቢሰሩ እንደዚህ ዓይነት ፍቅር ለሌሎች ይጨነቃል
በልቡ ኣኖረ የሚለው አንድ ሰው ስለአንደ ነገር እንዲያስብ ማድረግ፨ ሰይጣን ቀድሞዉኑ በስምኦን ልጅ በአስቆሮቱ ይሁዳ እየሱስን አሳለፎ እንዲሰጥ ኣሳስቦታል
ቁጥር ሶስት እየሱስ ስለሚያውቀው ነገር የገልጣል፨ ድርጊቱ በቁጥር አራት ላይ ይጀምራል
ይህ ርእስ ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ነው
እጁ የሚለው ኃይልና ስልጣንን ያመለክታል
እየሱሰ ሁሌም ከአባቱ ጋር ነበር እናም በምድር ስራውን ሲጨርስ ወደ አባቱ ይመለሳል
ሀገሩ አቧራ ስለነበር በባህሉ እራቱን የጋበዘው ሰው የእንግዶቹን እግር የሚጣጥብ አገልጋይ ያዘጋጃል
የፒተር ጥያቄ የሚያመለክተው እየሱስ እግሩን እንዲያጥብ ፈቃደኛ አልነበረም፨ ጌታ ሆይ የኔን የሀጢአተኛውን እግር ማጠብ አግባብ አይደለም፨
እየሱስ ፒተርን ለማግባባት ሁለት ኣፍራሾችን ተናገረ፨ ፒተር የእየሱስ ደቀመዝሙር ሆኖ መቀጠል ከፈለገ እግሩን ማሳጠብ አለበት፨ ካጠብኩህ ሁሌም የኔ ትሆናለህ፨
እየሱስም ስምኦን ፔጥሮስን ማናገር ቀጠለ
እየሱስ አንተ የሚለውን ቃል ሉሁለም ደቀ መዝሙር ይጠቀማል
መታጠብ ያሚለው እግዚአብሄር ሰውን በመንፈሳዊ ህይወት ሲያጥብ ለማመልከት ነው፨ የእግዚአብሄርን ምህረት ከተቀበልን አሁን የሚያስፈለገን ከእለት ኃጢአት መንጻት ነው
እየሱስ አሳልፎ የሚሰጠው ይሁዳ በሱ እንዳላመነ ለማሳየት ነው፨ ስለዚህም እግዚአብሄር ኃጢአቱን ይቀር አላለውም፨ ሁላችሁም የእግዚአብሄርን ይቅርታ አልተቀበላችሁም
ይህ አባባል በጥያቄ መልክ የሆነው እየሱስ ለደቀመዛሙረቱ ያደረገውን ያስተማረውን አጽንኦት ለመስጠት ነው፨ ለናንተ ያደረኩትን እንዲገባችሁ ነው፨
እየሱስ ደቀመዛሙረቱ ለርሱ ምን ያህል ከብር እንደሰጡት ለመግለጽ ነው፨ መምህር እና ጌታ ብለችሁ ሰትጠሩኝ ትልቅ ክብር አሳያችሁኝ
እየሱስ ለማለት የፈለገው ደቀመዛሙርቱ የሱን ምሳሌ እንዲከተሉና እርስ በርሳቸው እንዲገለገሉ ነው፨
እየሱስ ለደቀመዛሙርቱ መናገሩን ቀጠለ
በ1፡49 ላይ እንደተረጎማችሁት ተረጉሙት
በጣም እሰፈላጊ
መባረክ ማለት ጥሩ እና ጠቃሚ ነገር ለሰው እንዲሆን፨ እግዚአብሄር ይባርክሀል
ቃሉ ሊፈጸም ግድ ነው
እንጀራዪን የበላ የሚለው ጓደኛ መስሎ የነበረውነ ለመግለጽ ነው፨ ተረከዙን አነሳ የሚለውም አንድ ሰው ጠላት እንደሆነ ለማሳየት ነው፨ ጓደኛ መስሎ ይታይ የነበረው ጠላት ሆነ
እኔ ምነግራችሁ ምን ሊሆን እንደሚችል ነገሩ ከመሆኑ በፊት ነው
እኔ እኔ ነኝ ብዪ የነገርኃችሁን እንድታምኑ ወይም መሳያ እንደሆንኩ እንድታምኑ
እኔ እንደ ሆንሁ አምናለሁ ፣ ወይንም “እኔ ክርስቶስ እንደሆንኩ ታምኑ ይሆናል”
ተጨነቀ ተረበሸ
በ1፡49 ላይ እንደተረጎማችሁት ተርጉሙት
ደቀመዛሙርቱ እርስ በርስ በመገረም ተያዩ፨ እየሱስን ማን አሳልፎ የሰጣል?
ዮሀንስን ያመለክታል
በእየሱስ ጊዜ አይሁድ እንደ ግሪኮች
በእራት ጠረፔዛ ዙሪያ ጭንቅላትን
ይህ አይነት ፍቅር የሚመጣውከእግዚአብሄርና ስለሌላው መልካም ባማሰብ ለራስ እንኩዋን ጥቅም ባይኖር። ይህ አይነት ፍቅር ስለሌላው ይጨነቃል ምንም አይነት ነግረ ቢሰሩ
ይሁዳ ከ ኬሪዮት ከምትባል መንደር ነው
ይህ ቃል ጁዳ እንጀራውን እንደተቀበለ ወዲያውኑ
ይህ ማለት ሰይጣን ሙሉ በሙሉ ይሁዳን ተቆጣጠረ፨ ሰይጣን ተቆጣጠረው ወይም ሰይጠን ያዛወው ጀመር
ይሁዳን እያናገረ ነው
ልትሰራ ያሰብከውን በፍጥነት ስራው
ሂድና ለድሆች ገንዘብ ስጥ
ዮሃንስ ትኩረት ለመሳብ ይሁዳ ኃጢአቱን ወይም ጭለማ ነገሩን በጭለማ ውስጥ ለመስራት እንደወጣ ያሳያል። በድቅድቅ ጭለማ ወዲያውኑ ወጣ
አሁን ሕዝቡም የሰው ልጅ ክብር ከእግዚአብሔር ሲቀበልና እግዚአብሔርም ከሰው ልጅ ክብር ሲቀበል ያያሉ
እሱ የሚለው የስው ልጅን ነው የሚያመለክተው፨ እራሱ የሚለው የእግዚአብሔር አንጸባራቂ ነው፨ እግዚአብሔር ራሱ የሰውን ለጅ ያከብርዋል፨
ሕጻናት ልጆች ብሎ ደቀመዛሙርቱን መጥራት ይወዳል ልክ እንደራሱ ልጆች
አይሁድ የሚለው እየሱስነ የሚቃወሙትን የአይሁድ መሪዎቹን ነው፨ ለአይሁድ መሪዎች እንዳልኳቸው
እየሱስም ደቀመዛሙርቱን ማናገር ቀጠለ
ከእግዚአብሄር የሚመጣ ፍቅር ሲሆን ጥሩ የሚሰሩትን ይመለከታል ምንም እንኩዋን ለራስ ባይጠቅምም፨ ይህ ዓይነት ፍቅር ስለሌላው ይጨነቃል ምን ነግረ ቢሰሩ
እየሱስ በተናገረው አረፍተነገር ላይ ክብደት ለመጨመር ነው፨ ደቀመዛሙርቱ ለእያንዳንዳቸው ያላቸውን ፍቅር ለሚያዩ ሰዎች ነው፨ እያንዳነዱ ለእያነዳንዱ ያለውን ፍቅር ማወቅ
ሕይወቴን ልሰጥ ወይም ልሞት
እየሱስ በተናገረው አረፍተነገር ላይ አጽንኦት ለመስጠት ነው፨ ስለ አንተ እሞታለሁ አልክ እወነቱ ግን አታደርገውም
ዶሮከመጮሁ በፈት አላውቀውም ብለህ ሶስት ግዜ ትክደኛለህ
1 «ልባችሁ አይታወክ በእግዚአብሔር እመኑ፤ በእኔ ደግሞ እመኑ። 2 በአባቴ ቤት ብዙ የመኖሪያ ስፍራ አለ፤ እንደዚያ ባይሆን ኖሮ፣ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁ ብዬ አልነግራችሁም ነበር። 3 ሄጄም ስፍራ ካዘጋጀሁላችሁ በኋላ፣ እኔ ባለሁበት እናንተም እንድትሆኑ ዳግመኛ እመጣለሁ፣ ወደ ራሴም እወስዳችኋለሁ።` 4 ወዴት እንደምሄድ መንገዱን ታውቃላችሁ።» 5 ቶማስ ኢየሱስን፣ «ጌታ ሆይ፣ ወዴት እንደምትሄድ አናውቅም፣ መንገዱን እንዴት ማወቅ እንችላለን?» በማለት ጠየቀው። 6 ኢየሱስ እንዲህ አለው፤ «እኔ መንገድ፣ እውነትና ሕይወት ነኝ፤ በእኔ ካልሆነ በቀር ማንም ሰው ወደ አብ ሊመጣ አይችልም። 7 እኔን ብታውቁኝ ኖሮ አባቴንም ባወቃችሁት ነበር። ከአሁን ጀምሮ ታውቁታላችሁ አይታችሁትማል።» 8 ፊልጶስ ጌታ ኢየሱስን፣ «ጌታ ሆይ፣ አብን አሳየን ያ ለእኛ በቂያችን ነው» አለው። 9 ኢየሱስ፣ «ፊልጶስ ሆይ፣ ይህን ያህል ጊዜ ከእናንተ ጋር ኖሬ ገና ኣላወቅኸኝምን? እኔን ያየ አብን አይቷል፤ 'እንዴትስ አብን አሳየን' ትላለህ? 10 እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ አታምንምን? እየነገርኋችሁ ያለው ቃል ከራሴ የምናገረው አይደለም፤ ይልቁንስ ይህን ሥራ የሚሠራው በእኔ ውስጥ የሚኖረው አብ ነው። 11 እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ እመኑኝ፤ ሌላው ቢቀር ከምሠራው ሥራ የተነሣ እመኑኝ። 12 እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ፣ በእኔ የሚያምን እኔ የምሠራውን ሥራ እርሱም ይሠራል፤ እንዲያውም እኔ ወደ አብ ስለምሄድ፣ እኔ ከሠራሁት የሚበልጥ ሥራ ይሠራል። 13 አብ በልጁ ይከብር ዘንድ ማንኛውንም ነገር በስሜ ብትለምኑ እኔ አደርገዋለሁ። 14 ማንኛውንም ነገር በስሜ ብትለምኑ፣ እኔ አደርገዋለሁ። 15 የምትወዱኝ ከሆነ ትእዛዜን ትጠብቃላችሁ። 16 እኔም ለዘላለም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ እንዲሰጣችሁ አብን እለምናለሁ። 17 እርሱም የእውነት መንፈስ ነው፤ ዓለም ስለማያየው ወይም ስለማያውቀው አይቀበለውም። ይሁን እንጂ፣ ከእናንተ ጋር ስለሚኖርና በውስጣችሁም ስለሚሆን፣ እናንተ ታውቁታላችሁ። 18 ወላጅ እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፣ ዳግመኛ ወደ እናንተ እመጣለሁ። 19 ከጥቂት ጊዜ በኋላ ዓለም አያየኝም፤ እናንተ ግን ታዩኛላችሁ፤ እኔ ሕያው ነኝና እናንተም ሕያዋን ትሆናላችሁ። 20 በዚያን ቀን እኔ በአብ እንዳለሁ፣ እናንተ በእኔ እንዳላችሁ እኔም በእናንተ እንዳለሁ ታውቃላችሁ። 21 ትእዛዜ በውስጡ ያለ የሚያደርገውም የሚወደኝ እርሱ ነው፤ የሚወደኝንም አባቴ ይወደዋል፤ እኔም እወደዋለሁ፤ ራሴንም እገልጥለታለሁ። 22 የአስቆሮቱ ያልሆነው ይሁዳም ኢየሱስን፣ «ጌታ ሆይ፣ ለዓለም ሳይሆን ለእኛ ራስህን የምትገልጠው እንዴት ነው?» ብሎ ጠየቀው። 23 ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፤ «ማንም ሰው ቢወደኝ ቃሌን ይጠብቃል። አባቴም ይወደዋል፣ ወደ እርሱ እንመጣለን፣ መኖሪያችንንም በእርሱ እናደርጋለን። 24 የማይወደኝ ማንኛውም ሰው ቃሌን አይጠብቅም። የምትሰሙት ቃል የእኔ ሳይሆን፣ የላከኝ የአብ ቃል ነው። 25 በመካከላችሁ ሳለሁ እነዚህን ነገሮች ልብ እንድትሉ ነግሬአችኋለሁ። 26 የሆነ ሆኖ፣ አብ በስሜ የሚልከው አጽናኙ መንፈስ ቅዱስ ሁሉንም ነገር ያስተምራችኋል፤ እኔ የነገርኋችሁንም ነገር ሁሉ እንድታስታውሱ ያስችላችኋል። 27 ሰላምን እተውላችኋለሁ፤ ሰላሜንም እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጠው ሰላም ዓለም እንደሚሰጠው ዓይነት አይደለም። ልባችሁ አይጨነቅ፣ አይፍራም። 28 'እሄዳለሁ፣ ዳግመኛም ወደ እናንተ እመጣለሁ' ብዬ የነገርኋችሁን ቃል ሰምታችኋል። ከወደዳችሁኝስ ወደ አብ በመሄዴ ደስ ሊላችሁ ይገባ ነበር፤ ምክንያቱም አብ ከእኔ ይበልጣል። 29 ይህ ነገር በሚፈጸምበት ጊዜ ታምኑ ዘንድ አሁን ከመሆኑ በፊት አስቀድሜ ነገርኋችሁ። 30 የዚህ ዓለም ገዥ እየመጣ ስለሆነ ከዚህ በላይ ከእናንተ ጋር መነጋገር አልችልም።እርሱ በእኔ ላይ ምንም ሥልጣን የለውም፡ 31 ነገር ግን አብን እንደምወድ ዓለም ሁሉ ያውቅ ዘንድ በሰጠኝ ትዕዛዝ መሠረት አብ ያዘዝኝን አደርጋለሁ። ተነሱ ከዚህ እንሂድ»
ታሪኩ ከቀደመው ምዕራፍ ይቀጥላል፨ እየሱስም በጠረጴዛ ላይ ተቀምጦ ከደቀመዛሙርቱ ጋር ማውራቱን ቀጠለ
ይህ አባባል ነው፨ የታወከ ልብ ማለት መጨነቅ መረበሽ ማለት ነው፨ መጨነቅና መረበሻችሁን አቁሙ፨
ባባቴ ቤት ለመኖር ብዙ መኖሪያ አለ
ይህ የሚያመለክተው መንግሰተ ሰማይን ነው፤ እግዚአብሄር የሚኖርበት
ይህ ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ርዕስ ነው
ክፍል የሚለው ቃል ለነጠላ ክፍልም ወይም ለብዙ መኖሪያ ነው
እየሱስ በርሱ ለሚያምኑ ሁሉ በመንግስተ ሰማይ ቦታ ያዘጋጃል፨ አንተ የሚለው ቃል ለብዙ ነው ለሁሉም ደቀመዛሙርት
ወደዛ ለመድረስ እንዴት እናወቃለን?
ይህ አባባል የሚከተሉት ትርጉሞች ሊኖሩት ይችላል 1)የእግዚአብሄር መንገድ 2) ሰዎችን ወደ እግዚአበሔር የሚወስድ
ይህ አባባል የሚከተሉት ትርጉሞች ሊኖሩት ይችላል 1) እውነተኛ ሰው ወይም 2) ስለ እግዚአብሔር እውነትን የሚናገር ሰው
ይህ ኣባባል እየሱስ ለሰዎች ሕይወትን ይሰጣል ማለት ነው፨ ሰውን ሕያው የሚያደርግ
ሰዎች በእየሱስ በማመን ብቻ ከእግዚአብሔር ጋር መኖር ይችላሉ፨ በኔ ካልሆነ በስተቀር ማንም ከአባቴ ጋር መኖር አይችልም
ይህ ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ረዕስ ነው፨
አባት የሚለው ለእግዚአብሐር አስፈላጊ ርዕስ ነው
የህ አስተያየት በጥያቄ ምልክት የሆነው ለባባሉ አጽንኦት ለመስጠት ነው፨ ፊሊፕ ከናንተ ከደቀመዛሙርቴ ጋር ልጅም ጊዜ አብሪአችሁ ነበርኩ፨ እስከአሁን ድረስ ልታውቀኝ ይገባል፨
የእግዚአብሔር ልጅ የሆነውን እየሱሰን ማየት፤እግዚአብሔር አባትን ማየት ነው
ይህ አባባል በጥያቄ መልክ የቀረበው ለፊሊፕ ጥያቄ እየሱስ አጽንኦት ለመስጠት ነው፨ አብን አሳየን ማለት አይገባሕም ነበር፨
እየሱስ ፊሊፕን ጥያቄ ጠይቆት ከደቀመዛሙርቱ ጋር ንግግሩን ቀጠለ
ይህ አባባል በጥያቄ መልክ የቀረበው እያሱሰ ለፊሊፕ የተናገረውን ቃል አጽንኦት ለመስጠት ነው፨ ብወነት ማመን ነበረብሕ በእኔ
ይህ ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ረዕስ ነው
የምነግራቸሁ ከእኔ እይደለም ወይም የምነግራችሁ ቃል ከራሴ አይደለም
አንተ የሚለው ቃል ለብዙ ነው እየሱስ ለደቀመዛሙርቱ ሁሉ እየተናገረ ነው
ይህ አባባል የሚገልጸው እግዚአብሔር አባትና እየሱስ ልዩ ግኑኝነት አላቸው፨ እኔ ከኣባቴ ጋር አንድ ነኝ አባቴም ከእኔ ጋር አንድ ነው ኧይም እኔ ና አባቴ ለክ እንደ አንድ ነን
በ1፡49 ላይ እንደተረጎማችሁት ተርጉሙት
እየሱሰ የእግዚአብሄር ልጅ እንደሆነ ማመን
ስም የሚለው የእየሱስን ስልጣን ያመለክታል፨ በኔ ስልጣን የምትጠይቁትን ሁሉ
ለሁላችሁም የአባቴን ታለቀነት ከብር አሳይ ዘንድ
ይህ አባባል በእግዚአብሄርና በእየሱስ መካከል ያለውነ ግኑኝነት ለመግለጽ ኣስፈላጊ ነው
ስም የሚለው የእየሱስን ስልጣን ለመግለጽ ነው፨ የኔ ተከታይ ሆናችሁ ምንም ነገር ብትጠይቁኝ ኣደርግላችኃለሁ ወይም የፈለጋችሁትን ብትጠይቁኝ የኔ ስለሆናችሁ አደርግላችኃለሁ፨
ይህ መንፈስ ቅዱስን ያመለክታል
ስለ እግዚአብሄር እወነት ሰዎችን ያሚያስተምር መንፈስ ቅዱሰን ያመለክታል
አለም የሚለው እግዚአብሄርን የሚቀወሙትን ሁሉ ያመለክታል፨ በዚህ ዓለም ያሉ የማያምኑ ሁሉ አይቀበሉተም፨ እግዚአብሄርን የማያምኑ ሁሉ አይቀበሉትም፨
ደቀ መዛሙርቱን የሚያስብላቸው እንደሌለ ብቻቸውን እንደማይተዋቸው ይገልጻል፨
አለም የሚለው የሚየመለክተው የእግዚአብሄር ያልሆኑትን ነው፨ ያማያምኑትን
እግዚአብሄር አባት ና እየሱሰ እንደ አንድ ስው ይኖራሉ፨ አባቴና እኔ እንድ እንደሆን ታውቀላችሁ፨
ይህ ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ረዕስ ነው
እኔና አንተ ለክ እንደ አንድ ሰው ነን፨
ይህ ዓየነት ፍቅር የሚመጣው ከእግዚአብሐር ሲሆን ለሰዎች በጎ ማድረግ ላይ ያተኩራል፤ ለራሱ ጥቅም የማያሰገኝ ቢሆንም እንኩዋን፨ ይህ ዓይነት ፍቅር ምንም አየነት ነገር ቢሰሩ ለሌው ያስባል
የሚወደኝን ሁሉ አባቴም ይሰደዋል፨
ይሀ ለእግኢአብሄር አስፈላጊ ርእስ ነው
ይሁዳ የሚለው እየሱስን አሳለፍ የሰጠውን የአስቆሮቱ ይሁዳን አይደለም ግን ለላኛው ደቀ መዝሙር ነው
ማሳየት የሚለው ቃል እየሱስ እንዴት ድንቅ /እነደሆነ ያሳያል፨ ለምንድነው ረስህን ለኛ ብቻ የምትገልጸው ወይም ለምንድነው አንተ ድንቅ እነደሆነክ ለኛ ብቻ የምትገልጸው
ለይሁዳም መለሰ (ለአሰቆሮቱ አይደለም)
የሚወደኝ እንደሰራ ያዘዝኩትን ሁሉ ይሰራል፨
ይህ ዓየነት ፍቅር የሚመጣው ከእግዚአብሐር ሲሆን ለሰዎች በጎ ማድረግ ላይ ያተኩራል፤ ለራሱ ጥቅም የማያሰገኝ ቢሆንም እንኩዋን፨ ይህ ዓየነት ፍቅር ስለሌላው ይጨነቃል፤ ምንም ነገር ቢሰሩ፨
ይህ ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ረእስ ነው
እየሱስ ያዘዛቸውን ለሚፈጽሙ ሁሉ አባትና ልጅ ሕይወትን ያካፍላሉ፨ ኸእርሱ ጋር ልንኖር እንመጣለን ከርሱም የግል ግኑኝነት ይኖረናል፨
የነገርኃችሁ በሙሉ በእኔ በራሴ ወስኜ የነገረኃችሁ አይደለም፨
ቃል የሚለው የሚያመለክተው እየሱስ ከእግዚአብሄር ያመጣውን መልእከት ያመለክታል፨ መልእከት
አንተ የሚለው ቃል የሚያመለክተው ለሁሉም ደቀመዝሙር ሲናገር ነው
ይህ መንፈስ ቅዱስን ያመለክታል
ይህ ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ርእስ ነው
በስሜ ሚለው የእየሱስን ስልጣንና ኃይል ያመለክታል፨ በኔ ምክንያት ወይም ስለ እኔ
አለም የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔርን የማይወዱትን ነው
የታወከ የፈራ ልብ የሚያሳየው መፍራትነ መጨነቀን ነው፨ እየሱሰ እዚህ ላይ ልብን ልክ እንደሰው ነው የሚናገረው፨ መጨነቃችሁን አቁሙ፤ አትፍሩ
ይህ ዓየነት ፍቅር የሚመጣው ከእግዚአብሄር ነው ደግሞም ስለሌላው መልካም ይመኛል ለረሱ ባይጠቅመውም እንኩዋን፨ ይህ አይነት ፍቅር ስለሌለው ያሰባል ምንመ ነገር የሰሩ ቢሆን
እየሱስ ወደአባቱ እንደሚመለስ ይናገራል፨ ወደአባቴ አመለሳለሁ፨
እየሱስ የሚለው እኔ በምድር ላየ እሰካለሁ ድረስ አባቴ ከልጁ በላይ ስለጣን አለው፨ አባቴ እኔ በዚህ ምድር ከለኝ ስልጣን በላይ አለው፨
ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ርዕሰ ነው
1 እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ፤ ገበሬው ደግሞ አባቴ ነው። 2 እርሱም በእኔ ላይ ያለውን ፍሬ ያማያፈራውን ማንኛውንም ቅርንጫፍ ያስወግደዋል፤ ፍሬ የሚያፈራውን ግን ይበልጥ ያፈራ ዘንድ ያጠራዋል። 3 ከነገርኋችሁ ቃል የተነሣ እናንተ ንጹሓን ናችሁ። 4 በእኔ ኑሩ እኔም በእናንተ። ቅርንጫፍ በወይኑ ግንድ ላይ ካልኖረ በቀር በራሱ ፍሬ ማፍራት እንደማይችል ሁሉ፣ እናንተም በእኔ ካልኖራችሁ ፍሬ ማፍራት አትችሉም። 5 እኔ የወይን ግንድ ነኝ፤ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ የምኖርበት ያ ሰው ብዙ ፍሬ ያፈራል። ያለ እኔ ምንም ነገር ልታደርጉ አትችሉም። 6 ማንም ሰው በእኔ ባይኖር፣ እንደ ቅርንጫፍ ይወገዳል፣ ይደርቃልም፤ ሰዎች ሰብስበው ወደ እሳት ይጥሉታል፣ ይቃጠላልም። 7 በእኔ ብትኖሩ፣ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ፣ የምትፈልጉትን ማንኛውንም ነገር ለምኑ ይሰጣችኋል። 8 ብዙ ፍሬ ብታፈሩና ደቀ መዛሙርቴ ብትሆኑ በዚህ አባቴ ይከበራል። 9 አብ እንደ ወደደኝ እኔም ወደድኋችሁ፣ በፍቅሬ ኑሩ። 10 እኔ የአባቴን ትእዛዝ እንደጠበቅሁና በፍቅሩ እንደምኖር ሁሉ እናንተም ትእዛዜን ብትጠብቁ በፍቅሬ ትኖራላችሁ። 11 ደስታዬ በውስጣችሁ እንዲሆንና ደስታችሁም ፍጹም እንዲሆን እነዚህን ነገሮች ነግሬአችኋለሁ። 12 እኔ የምሰጣችሁ ትእዛዝ እኔ እንደ ወደድኋችሁ እርስ በርሳችሁ እንድትዋደዱ ነው። 13 ስለ ወዳጁ ሲል ሕይወቱን አሳልፎ እንዲሰጥ ግድ ከሚል የሚበልጥ ፍቅር ማንም ሰው የለውም። 14 ያዘዝኋችሁን ነገር ብታደርጉ ወዳጆቼ ናችሁ። 15 ከእንግዲህ አገልጋዮች ብዬ አልጠራችሁም፤ ምክንያቱም አገልጋይ ጌታው ምን እያደረገ እንዳለ አያውቅም። ከአባቴ የሰማሁትን ነገር ሁሉ እንድታውቁ ስለ ነገርኋችሁ፣ ወዳጆች ብያችኋለሁ። 16 እናንተ አልመረጣችሁኝም፤ ነገር ግን እኔ መረጥኋችሁ፤ ሄዳችሁ ፍሬ እንድታፈሩ፣ ፍሬአችሁም ዘላቂ ሆኖ እንዲቆይ ሾምኋችሁ። ይህም አብን በስሜ የምትለምኑትን ማንኛውንም ነገር እንዲሰጣችሁ ነው። 17 እርስ በርሳችሁ እንድትዋደዱ ይህን ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ። 18 ዓለም ቢጠላችሁ ከእናንተ በፊት እኔን እንደ ጠላኝ ዕወቁ። 19 ከዓለም ብትሆኑ ኖሮ ዓለም የራሱ እንደሆኑት አድርጎ በወደዳችሁ ነበር። ነገር ግን ከዓለም ስላይደላችሁ ከዓለምም ስለ መረጥኋችሁ ዓለም ይጠላችኋል። 20 'አገልጋይ ከጌታው አይበልጥም' በማለት የነገርኋችሁን ቃል ልብ በሉ፤ እኔን አሳድደውኝ ከሆነ፣ እናንተንም ያሳድዷችኋል፤ ቃሌን ጠብቀው ከሆነ፣ የእናንተንም ቃል ይጠብቃሉ። 21 የላከኝን እርሱን ስለማያውቁ፣ በስሜ ምክንያት ይህን ሁሉ ያደርጉባችኋል። 22 እኔ ባልመጣና ባልነግራቸው ኖሮ ኀጢአት ባልሆነባቸውም ነበር፤ ነገር ግን አሁን ለኀጢአታቸው የሚሰጡት ምክንያት የለም። 23 እኔን የሚጠላ አባቴንም ይጠላል። 24 ማንም ያልሠራውን ሥራ በመካከላቸው ሠርቼ ባላሳያቸው ኖሮ ኀጢአት ባልሆነባቸውም ነበር፤ አሁን ግን ሥራዬን አይተዋል፤ እኔንና አባቴንም ጠልተዋል። 25 ይህም የሆነው በሕጋቸው 'በከንቱ ጠሉኝ' ተብሎ የተጻፈው ቃል እንዲፈጸም ነው። 26 ከአብ የምልክላችሁ አጽናኝ፣ እርሱም ከአብ የሚወጣው የእውነት መንፈስ በሚመጣበት ጊዜ፣ ስለ እኔ ይመሰክራል። 27 ከመጀመሪያ ጀምሮ ከእኔ ጋር ስለ ነበራችሁ፣ እናንተም ትመሰክራላችሁ።
ካለፈው ምእራፍ የሚቀጥል ነው፨ እየሱሰሰ በጠረጴዛው ከደቀመዛሙርቱ ጋር ሆኖ ንግግሩን ቀጠለ፨
የወይን ግንድ የሚለው ገላጭ ነው፨ እየሱሰ ራሱን ከወይንግንድ ወይመ ቅርንጨፍ ያስመስላል፨ የሕየወት ምንጭ እርሱ ስለሆነ ሰዎች እርሱን በሚያስደስት መልክ እንዲኖሩ ይፈልጋል፨ እኔ ልክ ፍሬ እንደሚያፈራ የወይን ግንድ ነኝ
አትክልተኛ የሚለው አባባል ነው፨ አትክልተኛ ሰው ወይኑ በተቻለ መጠን ጥሩ ፍሬ እንዲይዝ የሚንከባከብ ነው፨ አባቴም ልክ እንደአትክልተኛ ነው፨
ይህ ርእስ ለእግዚአብሄር አስፈለጊ ርእስ ነው
ቅርንጫፍ የሚለው አባባል ለእየሱስ የሆነውን ሰው ሁሉ ያመለክታል፨ እግዚአብሄርን በሚያስደስት መልኩ እንዲኖሩ ስለ እነሱ ያሰባል፨
ቆሮጦ ያስወግደዋል
ቅርንጻቹን ይከረክመዋል
ንጹህ ቅርንጫፍ የሚለው ምሳሌያዊ አነጋገር ያጠራቸውን ለማለት ነው፨ እናንተ ንጸሁ ቅርንጫፎች ናችሁ ያዘዝኩዋችሁን ሁሉ ፈጽማችኃል፨
አንተ የሚለው በጽሁፉ የተገለጸው ለብዙዎች እየሱስን ለተከተሉ ደቀመዛሙርተ ነው
ከኔ ጋር ብትሆኑ እኔም ከናንተ ጋር እሆናለሁ፤ ወይም በኔ ኑሩ እኔም በናንተ እኖረለሁ
በእየሱስ መሆን ማለት በእየሱስ የሆኑት ሁሉ ለሁሉም ነገር በሱ ይደገፋሉ፨ ስለሁሉም ነገር ከኔጋር ከልሆነችሁና ካልተደገፋችሁኝ
የወይን ግንድ እየሱስን የሚያመለክተ ምሳሌ ነው፨ ቅርንጫፎቹ ደግሞ በእየሱስ የሚያምኑትን የርሱ የሆነትን ያመለክታል፨ እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተ ደግሞ በግንዱ እንዳለ ቅርንጫፎች ነችሁ
እርሱ ከእግዚአብሄር ጋር እንዳለ ሁሉ የእየሱሰ ተከታዮችም ከርሱ ጋር እንዳለ ይናገራል፨ ከኔ ጋር አብሮ የቆየ
ይህ ምሳሌያዎ አነጋገር የየሱስ ተከታዮች እርሱን የሚያስደስት ስራ የሚሰሩትን ነው፨ በግንድ ላይ ያለ ቅርንጫፍ ብዙ ፍሬ እንደሚያፈራ ከእየሱስ ጋር የሚቆዩቱ ሁሉ እግዚአብሄርን የሚያስደስተውነ ነገር ይሰራሉ፨ ብዙ ፍሬ ጣፈራላቸሁ፨
ይህ ምሳሌያዎ ንግግር የሚያመለክተው ከእየሱሰ ጋር የሌሉትና ፍር የማያፈሩትን ነው፨ የወይኑ ገበሬ ልክ ፍሬ እንደማይሰጠው ቅርንጫፍ ይጥለዋል፨
እሳቱም ያቃጣላቸዋል
እየሱስ የሚለው አማኞች ጸሎታቸው እንዲመለስ እግኢአብሄርን መጠየቅ አለባቸው፨ የምትፈልጉትን ጠይቁ፨
ያደርግለችኃል፨
አባቴን ሰዎች እንዲያከብሩት ይሆናል
ይህ ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ርዕስ ነው
ፍሬ የሚለው ምሳሌያዎ አነጋገር ነው እግዚአብሄርን ለማስደሰት መኖር
የኔ ደዘመዝሙር እንደሆናችሁ አሳዩ ወይም ደየኔ እንደሆናችሁ ኣሰዩ
እየሱስ አባቱ እግዚአብሄር ለሱ ያለውን ፍቅር ለሌችም አጋረ፡ አባት የሚለው ቃል ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ነው፨
ፍቅሬን ተቀበሉ
የእየሱስ ተከታዮች ሲታዘዙት ለርሱ ያላቸውን ፍቅር ያሳየሉ፨ እኔ የነገርኳችሁን ስታደርጉ በፍቅሬ ትኖራላችሁ እኔም አባተን ታዥዤ በፍቅሩ እንዳለሁ፨
አባት የሚለው ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ርዕስ ነው
ይህንን የነገርኃችሁ እኔ ያለኝን ደስታ እናንተም እንዲኖራችሁ ነው፨
እናንተም ፍጹም ደስተኞች እንድትሆኑ ወይም ደስታችሁ ምንም እንዳይጎለው፨
ይህ ዓይነት ፍቅር የሚመጣው ከእግዚአብሄር ሲሆን ስለ ሌላው ምለካምን የመኛል፨ ይህ ዓይነት ፍቅር ስለሌው ይጨነቃል ምንም አይነት ነገር ቢሰሩ፨ ከዚህ የሚበልጥ ሌላ ፍቅር የለም፨
ምድራዊ ኑሮን ያመለክታል
ያዘዝኳችሁን ብትፈጽሙ ወዳጀቼ እንደሆናችሁ እያሳያችሁ ነው፨
አባቴ የነገረኝን ሁሉ ነግሬአችኃለሁ፨
አባቴ የሚለው ለእግዚአብሄር አስፈላጊ ነው፨
እየሱሰ የሚለው የሱ ተከታይ የሆኑት ደቀመዛሙርቱ እነሱ መርጠው ሳይሆን እርሱ መርጠአቸው ነው፨ ደቀመዝሙሬ ለመሆን አልወሰናችሁም፨
ፍሬ የሚለው አባባል የሚገልጸው እየሱስን የሚያስደስት ኑርን ነው፨
የስራ ወጤታችሁ ዘላለማዊ እንዲሆን
ስም የሚያመለክተው የእየሱስን ስልጣን ነው፨ የኔ ስለሆናችሁ አባቴን ምንም ነገር ብትጠይቁ እርሱም ይሰጣችኃል፨
ይህ ረዕስ ለእግዚአብሐር አስፈላጊ ነው፨
ይህ ዓይነት ፍቅር የሚመጣው ከእግዚአብሄር ሲሆን ስለ ሌላው መልካምን ይመኛል፨ ይህ ዓይነት ፍቅር ስለሌላው ይጨነቃል ምንም አይነት ነገር ቢሰሩ፨ ያዘዝኃችሁን ደግሜ እላለሁ፡ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ
እየሱስ አለም የሚለው በጥቅሱ የገለጸው የእግዚአብሄር ያልሆኑትንና የሚጠሉትን ነው
ይህ ስለ ሰው ልጆች ወንድማዊ ፍቅር ለጓደኛ ወይም ቤተሰባዊ ጽቅር
ቃል የሚለው የየሱስን መልእክት ለመግለጽ ነው፨ የነገርኃችሁን መልእክት አስታውሱ፨
ስለ ስሜ የሚለው ኢየሱስን የሚገልጽ ነው፡፡ ሰዎች የሱን ተከታዮች የሱ ስለሆኑ ያሰሳድዱአቸዋል፨ የኔ ስለሆንክ/ስለሆንሽ
እየሱስ እዚህ ላይ የሚገልጸው የእግዚአብሄርን መልእክት ለሱ ለማያምኑ ማካፈሉን ነው፨ እኔ መጥቼ የእግዚአብሄርን መልእከት ስለነገረኳቸው በእግዚአብሄር የፍርድ ቀን ይቅርታ የላቸውም
የእግዚአብሄርን ልጅ መጥላት እግዚአብሄርን አባትን መጥላት ነው
ማንመ ያልሰራውን ስራ በመሀከላቸው ሰራሁ ኃጢአትመ ሆነባቸው
ምንም ኃጢአት ባልሆነባቸው
በህጋቸው ያለው ጥንቢት ይፈጸም ዘንድ
ይህ ብሉይ ኪዳንን ሲያመለክት የእግዚአብሄር ትእዛዝ ለሕዝቡ
መንፈስ ቅዱሰን ያመለክታል
እግዚአብሄር አባት መንፈስቅዱስን ወደአለም የላከው እየሱስ የእግዚአብሄር ልጅ እንደሆነ ለመግለጽ ነው
ለእግዚአብሄር አሰስፈላጊ ርዕስ ነው
የመንፈስ ቅዱደስ መጠሪያ ነው፨ ስለ እግዚአብሄር እና ስለ እኔ የሚናገር እውነተኛ መንፈስ
መመስከር ማለት ለሌሎች ስለ እየሱስ መንገር፨ እናንተም ለሌሎች ስለእኔ የምታወቁትን ንገሩ፨
ይህ የመጀመሪያ የሚለው አባባል የእየሱስ የመጀመሪያ አገልግሎት ቀናቶች፨ ማስተማርና ተአምር ማሳየት ከጀመርኩበት ቀን አንስቶ
1 «እነዚህን ነገሮች የምነግራችሁ እምነታችሁ እንዳይናወጥ ነው፡፡ 2 ከምኵራብ ያስወጡአችኋል፤ እናንተን የሚገድል ሁሉ ለእግዚአብሔር መልካም እንዳደረገ የሚያስብበት ጊዜ መምጣቱ አይቀርም፡፡ 3 እነዚህን ነገሮች የሚያደርጉት አብንም ሆነ እኔን ስለማያውቁ ነው፡፡ 4 ይህን የምነግራችሁ እነርሱ እነዚህ ነገሮች የሚፈጸሙበት ጊዜ በደረሰ ጊዜ፣ ነገሮቹን እንድታስተውሷቸውና እንዴት እንደነገርኋችሁ እንድታስቡ ነው፡፡ አብሬችሁ ስለ ነበርሁ ስለነዚህ ነገሮች ቀደም ሲል አልነገርኋችሁም፡፡ 5 ነገር ግን አሁን ወደ ላከኝ እመለሳለሁ፤ ያም ሆኖ ከእናንተ ማንም 'የት ነው የምትሄደው? ˋ ብሎ የሚጠይቀኝ የለም። 6 ምክንያቱም እነዚህን ነገሮች ስላልኋችሁ ልባችሁ በሐዘን ተሞልቷል፡፡ 7 ነገር ግን እውነቱን ልንገራችሁ፤ እኔ ብሄድ ይሻላችኋል፤ እኔ ካልሄድሁ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣም፤ እኔ ብሄድ ግን እርሱን እልክላችኋለሁ፡፡ 8 አጽናኙ በመጣ ጊዜ ስለ ኃጢአት፣ ስለ ጽድቅና ስለ ፍርድ ዓለምን ይወቅሳል፤ 9 ስለ ኀጢአት በእኔ ባለማመናቸው፤ 10 ስለ ጽድቅ እኔ ወደ አባቴ ስለምሄድና ከእንግዲህ ስለማታዩኝ፣ እንዲሁም 11 ስለ ፍርድ የዚህ ዓለም ገዢ ስለ ተፈረደበት ነው፡፡ 12 ብዙ የምነግራችሁ ነገር አለኝ፤ ነገር ግን አሁን ልትረዱአቸው አትችሉም፡፡ 13 ነገር ግን እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ፣ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ ምክንያቱም እርሱ ከራሱ አይናገርም፤ ነገር ግን ከእኔ የሰማውን ሁሉ እነዚያን ይናገራል፤ ደግሞም ሊመጡ ስላሉ ነገሮች ይነግራችኋል፡፡ 14 የእኔ የሆኑትን ነገሮች ወስዶ ስለሚነግራችሁም ያከብረኛል፡፡ 15 የአባቴ የሆነው ነገር ሁሉ የእኔ ነው፤ ስለዚህ ነው መንፈስ ቅዱስ የእኔ የሆኑትን ነገሮች ወስዶ ይነግራችኋል ያልኋችሁ፡፡ 16 ከጥቂት ጊዜ በኋላ ፈጽሞ አታዩኝም ደግሞም እንደ ገና ከጥቂት ጊዜ በኋላ ታዩኛላችሁ።» 17 ከደቀ መዛሙርቱ አንዳንዶቹ እርስ በርሳቸው ‹‹ወደ አባቴ ስለምሄድ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ፈጽሞ አታዩኝም ደግሞም እንደ ገና ከጥቂት ጊዜ በኋላ ታዩኛላችሁˋ እያለ የሚነግረን ነገር ምንድን ነው?›› ተባባሉ፡፡ 18 ከዚህም የተነሣ ‹‹ከጥቂት ጊዜ በኋላˋ ሲል ምን ማለቱ ነው። ምን እያለ እንደ ሆነ አናውቅም›› አሉ፡፡ 19 ኢየሱስም ሊጠይቁት በጣም እንደ ፈለጉ አይቶ፣ ‹‹ከጥቂት ጊዜ በኋላ ፈጽሞ አታዩኝም ደግሞም እንደ ገና ከጥቂት ጊዜ በኋላ ታዩኛላችሁˋ ስላልሁት ነገር እርስ በርሳችሁ ትጠያየቃላችሁን? 20 እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ፣ እናንተ ታለቅሳለችሁ ታዝናላችሁም፤ ዓለም ግን ደስ ይለዋል፤ እናንተ በሐዘን ትሞላላችሁ፣ ነገር ግን ሐዘናችሁ ወደ ደስታ ይለወጣል፡፡ 21 አንዲት ሴት የመውለጃዋ ወራት በደረሰ ጊዜ፣ የምጧን ሥቃይ እያሰበች ታዝናለች፤ ነገር ግን ከወለደች በኋላ ሕፃን ወደዚህ ዓለም በመምጣቱ ከሚሰማት ደስታ የተነሣ ጭንቀቷን ፈጽሞ አታስበውም፡፡ 22 ደግሞም አሁን ዐዝናችኋል፤ ነገር ግን ተመልሼ አያችኋለሁ፤ ልባችሁም ደስ ይለዋል፤ ደስታችሁንም ማንም ከእናንተ ሊወስድ አይችልም፡፡ 23 በዚያም ቀን ምንም ጥያቄ አትጠይቁኝም፤ እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ፣ ከአብ ዘንድ ማንኛውንም ነገር ብትለምኑ አብ ስለስሜ ይሰጣችኋል፡፡ 24 እስከ አሁን በስሜ ምንም አልለመናችሁም፣ ለምኑ፣ ደስታችሁም ሙሉ ይሆን ዘንድ ትቀበላላችሁ፡፡ 25 እስከ አሁን በምሳሌ ስነግራችሁ ነበር፤ ነገር ግን በምሳሌ የማልናገርበትና ለእናንተ ስለ አብ በግልጽ የምናገርበት ጊዜ ይመጣል፡፡ 26 በዚያን ቀን በስሜ ትለምናላችሁ፤ እኔም ስለ እናንተ ወደ አብ እለምናለሁ አልላችሁም፤ 27 ምክንያቱም አብ ራሱ እኔን ስለወደዳችሁኝና ከአብ ዘንድ እንደ መጣሁ ስላመናችሁ ይወዳችኋልና ነው፡፡ 28 ከአብ ወደዚህ ዓለም መጥቻለሁ፤ እንደ ገናም ይህን ዓለም ትቼ ወደ አብ እሄዳለሁ፡፡» 29 ደቀ መዛሙርቱ፣ ‹‹እነሆ፣ አሁን በግልጽ ተናገርህ፤ ምንም በምሳሌ አልተናገርህም፡፡ 30 አሁን ሁሉን እንደምታውቅና ማንም ጥያቄ ሊጠይቅህ እንደማያስፈልግ አውቀናል። በዚህም ምክንያት አንተ ከአብ እንደ መጣህ እናምናለን» አሉት፡፡ 31 ኢየሱስ፣ ‹‹አሁንስ አመናችሁ ማለት ነው?›› 32 እነሆ፣ እያንዳንዳችሁ እኔን ብቻዬን ትታችሁ ወደየቤታችሁ የምትበታተኑበት ጊዜ እየመጣ ነው፡፡ አዎን፣ በርግጥም መጥቷል፡፡ ነገር ግን አብ ከእኔ ጋር ስላለ ብቻዬን አይደለሁም፡፡ 33 በስሜ ሰላም እንዲሆንላችሁ እነዚህን ነገሮች ነግሬአችኋለሁ፡፡ በዓለም ውስጥ ስትኖሩ መከራ አለባችሁ ነገር ግን አይዟችሁ፣ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ፡፡»
ካለፈው ምዕራፍ የታሪኩ ክፍል ይቀጥላል ፡፡ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር በማዕድ ተቀመጠ ፤ አነጋገራቸውም።
እዚህ “መውደቅ” የሚለው ሐረግ የሚያመለክተው አንድ ሰው በኢየሱስ ላይ እምነት መጣልን ማቆም ነው። ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። AT: "ስለዚህ በሚገጥሙህ ችግሮች ምክንያት በእኔ ላይ መታመን እንዳታቋርጥ ነው ፡፡" (UDB) (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር ገባሪ)
አንድ ሰው ሊገድልህ እና እግዚአብሔርን ጥሩ ነገር እያደረገ ነው ብሎ የሚያስብ አንድ ቀን ይከሰታል።
አንዳንድ አማኞችን ይገድላሉ እግዚአብሔርን አብን ወይም ኢየሱስን አላወቁም።
ይህ የእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው
እዚህ “ሰዓት” ሰዎች የኢየሱስን ተከታዮች የሚያሳድዱበትን ጊዜ የሚገልጽ አገላለፅ ነው ፡፡ አት: - “ሲሰቃዩህ” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
ይህ የኢየሱስን አገልግሎት የመጀመሪያ ቀናት የሚያመለክተው ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - "በመጀመሪያ እኔን መከተል በጀመሩት ጊዜ" (የበለስ_ቁልፍ እሳቤውን ይመልከቱ)
ይህ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው ደቀመዛሙርቱ በጣም ያዘኑ ማለት ነው ፡፡ አት: - “አሁን በጣም አዝናችኋል” (የበለስ-ቪዲዮን ይመልከቱ)
ይህንን በአዎንታዊ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “እኔ ከሄድኩ ብቻ አፅናኙ ይመጣልሃል” (የበለስ_አድራሻዎች ይመልከቱ)
ይህ ኢየሱስ ከሄደ በኋላ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር የሚሆነው መንፈስ ቅዱስ ማዕረግ ነው ፡፡ ይህንን በ 14 25 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
መንፈስ ቅዱስ በመጣ ጊዜ ፣ ሰዎች ኃጢአተኞች መሆናቸውን ማሳየት ጀመረ ፡፡
ይህ መንፈስ ቅዱስን ያመለክታል ፡፡ በ 14 15 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
ይህ በዓለም ያሉትን ሰዎች የሚያመለክተው ዘይቤያዊ አነጋገር ነው (ይመልከቱ ፡፡
በእኔ ስለማያምኑ በኃጢያት ጥለዋል ፡፡
ወደ እግዚአብሔር ስመለስ ፣ እና ከእንግዲህ አያዩኝም ፣ ትክክለኛ ነገሮችን እንዳደረግሁ ያውቃሉ ፡፡
ይህ የእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው
"ይህን ዓለም የሚገዛውን ሰይጣንን እንደሚቀጣው ሁሉ እግዚአብሔር ተጠያቂ ያደርጋቸዋል እናም በኃጢአቶቻቸውም ይቀጣል ፡፡"
እዚህ “ገ ruler” ሰይጣንን ያመለክታል ፡፡ አት: - “ይህን ዓለም የሚገዛው ሰይጣን” በ 12 30 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
"ለእናንተ መልዕክቶች" ወይም "ለእናንተ ቃላት"
ይህ ለሰዎች ስለ እግዚአብሔር እውነቱን የሚናገር የመንፈስ ቅዱስ ስም ነው ፡፡
“እውነት” የሚያመለክተው መንፈሳዊ እውነትን ነው። አት-“ማወቅ ያለብዎትን መንፈሳዊ እውነት ሁሉ ያስተምራችኋል” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
እግዚአብሔር የሚያመለክተው እግዚአብሔር አብ መንፈሱን እንደሚናገር ነው ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር የሚናገረውን ሁሉ ይናገራል” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
እግዚአብሔር የሚያመለክተው እግዚአብሔር አብ መንፈሱን እንደሚናገር ነው ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር የሚናገረውን ሁሉ ይናገራል” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
ይህ አስፈላጊ የእግዚአብሔር ርዕስ ነው
መንፈስ ቅዱስ የኢየሱስ ቃላት እና ሥራዎች እውነት መሆናቸውን ለሰዎች ይነግራቸዋል። አት: - “ቃሌ እና ሥራዬ እውነት መሆኑን መንፈስ ቅዱስ ለሁሉም ይነግራቸዋል” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
“ቶሎ” ወይም “ብዙ ጊዜ ከማለፉ በፊት”
"እንደገና ፣ ብዙ ጊዜ ከማለፉ በፊት"
ደቀመዛሙርቱ ኢየሱስ ምን ማለቱ እንደሆነ እርስ በእርስ ሲጠየቁ ኢየሱስ በተናገረው ንግግር ዕረፍት አለ ፡፡
ደቀመዛምርቱ ይህ የሚያመለክተው የኢየሱስ በመስቀል ላይ መሞቱን ነበር ፡፡
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ይህ የሚያመለክተው የኢየሱስን ትንሣኤ ነው ወይም 2) ይህ በመጨረሻው የኢየሱስን መምጣት ሊያመለክት ይችላል።
ይህ የእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው
ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ መናገሩን ቀጠለ።
ኢየሱስ ይህንን ጥያቄ የሚጠቀመው ደቀመዛሙርቱ በተናገራቸው ነገር ላይ እንዲያተኩሩ ነው ፣ ስለሆነም የበለጠ አብራራ ፡፡ አትቲን: - "እኔ ስናገር ምን ማለቴ እንደሆነ እራሳችሁን ትጠይቃላችሁ ... እዩኝ ፡፡"
የሚከተለው የሚከተለው አስፈላጊ እና እውነት መሆኑን በቋንቋዎ አፅንzesት በሚሰጥበት መንገድ ይተረጉሙ ፡፡ ይህንን በ 1 48 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
እዚህ ላይ “ዓለም” እግዚአብሔርን ለሚቃወሙ ሰዎች ዘይቤያዊ አነጋገር ነው ፡፡ አት: - “እግዚአብሔርን የሚቃወሙ ግን ይደሰታሉ” (ይመልከቱ ፡፡
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “ግን ሀዘንህ ወደ ደስታ ይለወጣል” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ይህ ፈሊጥ ነው ልብን እንደሚናገር ልብን የሚናገር ፡፡ አት: - “በጣም ደስ ትሰኛለህ” ወይም “እጅግ ደስ ይልሃል” (ይመልከቱ ፡፡
የሚከተለው የሚከተለው አስፈላጊ እና እውነት መሆኑን በቋንቋዎ አፅንzesት በሚሰጥበት መንገድ ይተረጉሙ ፡፡ ይህንን በ 1 48 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
እዚህ “ስም” የሚለው ቃል የኢየሱስን ስብዕና እና ስልጣን የሚያመለክቱ ስሞች ነው ፡፡ AT: - “እኔ ከአብ አንዳች ብትለምኑ እርሱ እርሱ ስለ እናንተ ይሰጣችኋል” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ይህ አስፈላጊ የእግዚአብሔር ርዕስ ነው
እዚህ “ስም” የኢየሱስን ስብዕና እና ስልጣን የሚያመለክቱ ስሞች ናቸው ፡፡ ከኢየሱስ ጋር በመኖራቸው የተነሳ የአማኞች ጥያቄን ያከብራል ፡፡ አት: - “ተከታዮቼ ነሽ” ወይም “በሥልጣኔ ላይ ነኝ” (ይመልከቱ ፡፡
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “እግዚአብሔር ታላቅ ደስታ ይሰጥሃል” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
"ግልፅ በሆነ ቋንቋ"
"በቅርቡ ይከሰታል"
በግልፅ በምትረዱበት መንገድ ስለ አብ ይነግራችኋል ፡፡
ይህ አስፈላጊ የእግዚአብሔር ርዕስ ነው
እዚህ “ስም” ለኢየሱስ ስብዕና እና ስልጣን ምሳሌ ነው ፡፡ አት: - “እኔ ስለሆንክ ትጠይቃለህ” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
አንድ ሰው ወልድ ኢየሱስን የሚወደው ከሆነ አብንም ይወዳሉ ፣ ምክንያቱም አብ እና ወልድ አንድ ናቸው።
ይህ አስፈላጊ የእግዚአብሔር ርዕስ ነው
ከሞተ እና ትንሳኤው በኋላ ፣ ኢየሱስ ወደ እግዚአብሔር አብ ይመለሳል ፡፡
እዚህ "አባት" አስፈላጊ የእግዚአብሔር ርዕስ ነው
“ዓለም” በዓለም ለሚኖሩት ሰዎች የሚያመለክተው ዘይቤያዊ አነጋገር ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ጥበብ)
ደቀመዛሙርት ለኢየሱስ ምላሽ ሰጡ
ይህ ሀሳቦች ኢየሱስ በደቀመዛምርቱ ግራ እንደተጋባቸው ለማሳየት ደቀ መዛሙርቱ አሁን በእሱ ለመታመን ዝግጁ መሆናቸውን ለማሳየት በጥያቄ መልክ ይታያል ፡፡ አት: - ስለዚህ ፣ አሁን በመጨረሻ በእኔ ላይ ታመንኛለህ (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ መናገሩን ቀጠለ።
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “ሌሎች ይሰታተኑሃል (UDB) (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ የእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው
እዚህ “ሰላም” የሚያመለክተው ውስጣዊ ሰላም ነው ፡፡ አት: - ከእኔ ጋር ባለኝ ግንኙነት የተነሳ ውስጣዊ ሰላም እንዲኖራችሁ ”(ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
እዚህ “ዓለም” የሚያመለክተው አማኞች እግዚአብሔርን የሚቃወሙትን የሚቋቋሙትን ችግሮች እና ስቃዮች ነው ፡፡ አት: - "እኔ የዚህን ዓለም መከራዎች አሸንፌአለሁ" (የበለስ_ቁልፍ ሥዕልን ይመልከቱ)
1 ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች ከተናገረ በኋላ ወደ ሰማይ እያየ፣ ‹‹አባት ሆይ፣ ሰዓቱ ደርሷል፣ ያከብርህ ዘንድ ልጅህን አክብረው 2 ይህም ከአንተ ለተቀበላቸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት እንዲሰጣቸው በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ በሰጠኸው ሥልጣን ልክ ነው፡፡ 3 ብቻህን እውነተኛ አምላክ የሆንኸውን አንተን፣ የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲያውቁ ይህ የዘላለም ሕይወት ነው፡፡ 4 አባት ሆይ፣ እንዳከናውነው የሰጠኸኝን ሥራ በመፈጸም በምድር ላይ አከበርሁህ፡፡ 5 አሁን አባት ሆይ፣ ዓለም ሳይፈጠር በፊት በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር ከአንተ ጋር አክብረኝ፡፡ 6 ከዓለም ለሰጠኸኝ ለእነዚህ ሰዎች ስምህን ገለጥሁላቸው። የአንተ ነበሩ፣ ለእኔም ሰጠሃቸው፣ ቃልህንም ጠብቀዋል። 7 አሁን ከአንተ የተቀበልኋቸው ነገሮች ሁሉ በርግጥ ከአንተ እንደ መጡ አምነዋል፣ 8 የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና። እነርሱም ተቀብለውታል፤ ከአንተ እንደ መጣሁ አውቀዋል አንተ እንደላክኸኝም አምነዋል። 9 እነርሱ የአንተ ናቸውና አንተ ለሰጠኸኝ ለእነርሱ እንጂ ለዓለም አልጸልይም፡፡ 10 የእኔ የሆነው ሁሉ የአንተ ነው፤ የአንተ የሆነውም ነገር ሁሉ የእኔ ነው፤ እኔ በእነርሱ ከብሬአለሁ፡፡ 11 እኔ ወደ አንተ እመጣለሁና። ከእንግዲህ በዓለም አልኖርም፤ እነርሱ ግን በዓለም ውስጥ ናቸው፡፡ ቅዱስ አባት ሆይ፣ እኔና አንተ አንድ እንደ ሆንን አንድ እንዲሆኑ በሰጠኸኝ በስምህ ጠብቃቸው፡፡ 12 ከእነርሱ ጋር እያለሁ በሰጠኸኝ በስምህ ጠበቅኋቸው፡፡ በቅዱሳት መጻሕፍት የተባለው እንዲፈጸም ከጥፋት ልጅ በቀር ከእነርሱ አንዱም እንዳይጠፋ ጋረድኋቸው፡፡ 13 አሁን ወደ አንተ እመጣለሁ፤ ይህን በዓለም ሳለሁ የምናገረው፣ ደስታዬ በእነርሱ ሙሉ እንዲሆን ነው፡፡ 14 ቃልህን ሰጥቻቸዋለሁ፤ እኔ ከዓለም እንዳልሆንሁ እነርሱም ከዓለም አይደሉምና ዓለም ይጠላቸዋል፡፡ 15 ከክፉው እንድትጠብቃቸው እንጂ ከዓለም እንድታወጣቸው አልጸልይም፡፡ 16 እኔ ከዓለም እንዳይደለሁ እነርሱም ከዓለም አይደሉም፡፡ 17 በእውነት ቀድሳቸው፤ ቃልህ እውነት ነው፡፡ 18 አንተ ወደ ዓለም ላክኸኝ፣ እኔም ደግሞ እነርሱን ወደ ዓለም ልኬአቸዋለሁ፡፡ 19 እነርሱ በእውነት እንዲቀደሱ እኔ ራሴን ስለ እነርሱ ቀድሼአለሁ፡፡ 20 ከእነርሱ ምስክርነት የተነሣ በእኔ ስለሚያምኑት ሁሉ እንጂ ስለ እነዚህ ብቻ አልጸልይም፡፡ 21 ይህም አባት ሆይ፣ አንተ በእኔ እኔም በአንተ እንዳለሁ እነርሱም አንድ እንዲሆኑ ነው፡፡ ዓለም አንተ እንደ ላክኸኝ እንዲያምን እነርሱም በእኛ እንዲሆኑ እጸልያለሁ፡፡ 22 እኛ አንድ እንደ ሆንን እነርሱም አንድ እንዲሆኑ የሰጠኸኝን ክብር ሰጥቻቸዋለሁ፤ 23 ይህም እኔ በእነርሱ አንተም በእኔ ሆነህ እነርሱ በአንድነት ፍጹማን እንዲሆኑና ዓለም አንተ እንደ ላክኸኝ እኔን በወደድህበት ፍቅር እነርሱንም እንደ ወደድሃቸው እንዲያውቅ ነው። 24 አባት ሆይ፣ የሰጠኸኝ እነዚህ ስለ ወደድኸኝ ዓለም ከመፈጠሩ አስቀድሞ የሰጠኸኝን ክብር እንዲያዩ እኔ ባለሁበት እነርሱም ከእኔ ጋር እንዲሆኑ እወዳለሁ፡፡ 25 ጻድቅ አባት ሆይ፣ ዓለም አላወቀህም፤ እኔ ግን አውቅሃለሁ፤ እነዚህም አንተ እንደ ላክኸኝ አውቀዋል፡፡ 26 አንተን እንዲያውቁ አድርጌአለሁ፤ እኔን የወደድህበት ፍቅር በእነርሱም እንዲሆንና እኔም በእነርሱ እንድሆን ስምህን አስታውቃቸዋለሁ፡፡
ካለፈው ምዕራፍ የታሪኩ ክፍል ይቀጥላል ፡፡ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እያነጋገራቸው ነበር ፤ አሁን ግን ወደ አምላክ መጸለይ ጀመረ።
ይህ ወደላይ መፈለግ ማለት ፈሊጥ ነው ፡፡ አት: - “ወደ ሰማይ ቀና ብሎ ነበር።” (ዩ.አር.ቢ.) (ይመልከቱ: የበለስ_ ቪዲዮም)
ይህ ሰማይን ያመለክታል ፡፡
ለአምላክ ክብር መስጠት ይችል ዘንድ ኢየሱስ አብን እንዲያከብር እግዚአብሔር ጠየቀው ፡፡
እነዚህ በእግዚአብሔር እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚገልፁ አስፈላጊ አርዕስት ናቸው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
እዚህ ላይ “ሰዓት” የሚለው ቃል ኢየሱስ የሚሠቃይበትንና የሚሞተበትን ጊዜ የሚያመለክት ቃል ነው ፡፡ አት: - “የምሰቃይበት እና የምሞትበት ጊዜዬ ነው” (ይመልከቱ ፡፡
ይህ ሁሉንም ሰዎችን ያመለክታል።
የዘላለም ሕይወት ብቸኛውን እውነተኛውን አምላክ ፣ እግዚአብሔር አብንና እግዚአብሔር ወልድ ማወቅ ነው ፡፡
ይህ ስለ እግዚአብሔር ነገሮችን ከማወቅ ይልቅ እግዚአብሔርን ለመለማመድ ፈሊጥ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ ቪዲዮም)
እዚህ “ሥራ” የኢየሱስን አጠቃላይ ምድራዊ አገልግሎት የሚያመለክተን ዘይቤ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ጥበብ)
ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ስለሆነ ኢየሱስ “ዓለም ከመፈጠሩ በፊት” በእግዚአብሔር ዘንድ ክብር ነበረው ፡፡ AT: - “አባት ሆይ ፣ ዓለምን ከመፍጠሩ በፊት እንደነበረው ወደ አንተ በማምጣትህ አክብሮት ስጠኝ” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ይህ ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ መጸለይ ጀመረ ፡፡
እዚህ “ስም” የእግዚአብሔር ስብዕና የሚያመለክተን ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - "በእውነቱ ማን እንደሆናችሁ እና ማን እንደሆናችሁ አስተምራቸዋለሁ" (ዩ.አር.ቢ.) (ይመልከቱ: የበለስ_ጥበብ)
እዚህ “ዓለም” እግዚአብሔርን የሚቃወሙትን የዓለምን ሕዝቦች የሚያመለክተን ዘይቤ ነው ፡፡ ይህ ማለት እግዚአብሔር አማኞችን በመንፈሳዊ ከማያምኑ ሰዎች መለያሎታል ማለት ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ጥበብ)
ይህ መታዘዝ ማለት ፈሊጥ ነው ፡፡ አት: - "ትምህርትዎን ታዘዘ" (ይመልከቱ: የበለስ_ቪድዮ)
እዚህ ላይ “ዓለም” የሚለው ቃል እግዚአብሔርን የሚቃወሙ ሰዎችን የሚያመለክት ቃል ነው ፡፡ አት: - “እኔ ያልሆነውን እጸልያለሁ ፣ የእናንተ ያልሆነን ሰው” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ይህ በምድር ላይ መኖር እና እግዚአብሔርን ከሚቃወሙ ሰዎች መካከል መሆንን የሚያመለክተን ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - “የአንተ ያልሆኑ ሰዎች መካከል” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ከእግዚአብሄር ጋር የጠበቀ የጠበቀ ግንኙነት እንዲኖራቸው ኢየሱስ በእርሱ ላይ የሚታመኑትን እንዲጠብቃቸው አብን ይጠይቃል ፡፡
ይህ ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡
እዚህ ላይ “ስም” የሚለው ቃል የእግዚአብሄርን ጥበቃ እና የበላይነት የሚያመለክት ቃል ነው ፡፡ አት: - “እንደጠበቃችሁኝ በስምህ ጥበቃ ሥር ያድርጓቸው” ወይም “በሰጠኸኝ በስምህ ኃይል ጠብቅ” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
እዚህ “ስም” የእግዚአብሔርን ኃይል እና ጥበቃ የሚያመለክት ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - "በአንተ ጥበቃ አደረግኋቸው" (የበለስ_ቁልፍ ሥዕልን ተመልከት)
ከመካከላቸው አንድ የሆነው የጥፋት ልጅ ብቻ ነው ”
ይህ ኢየሱስን አሳልፎ የሰጠው ይሁዳ ነው ፡፡ አት: - “ከብዙ ጊዜ በፊት አጥፍተኸው ያጠፋኸው ሰው” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “በቅዱሳት መጻሕፍት ስለ እርሱ የተነገረውን ትንቢት ለመፈፀም” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
እዚህ “ዓለም” በዓለም ለሚኖሩት ሰዎች የሚያገለግል ዘይቤ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ጥበብ)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “ታላቅ ደስታን ይሰ giveቸው ዘንድ” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
እዚህ “ዓለም” እግዚአብሔርን የሚቃወሙትን ሰዎች የሚያመለክት አገላለጽ ነው ‹AT› ‹አንተን የሚቃወሙህ ሕዝቦቼን ጠሉ ምክንያቱም እኔ የእነሱ እንዳልሆንኩ እነሱ የማያምኑ ናቸው ፡፡ "(ይመልከቱ: የበለስ_ጥበብ)
በዚህ ምንባብ ፣ “ዓለም” እግዚአብሔርን ለሚቃወሙ ሰዎች ተምሳሊት ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ጥበብ)
ይህ የሚያመለክተው ሰይጣንን ነው ፡፡ አት: - “ከክፉው ከሰዓቱ ጠብቋቸው” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
እነሱን ለመለየት ዓላማው በግልጽ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ እዚህ “በእውነት” የሚለው ሐረግ የሚያስተምረው እውነቱን በማስተማር ነው ፡፡ አት: - “እውነቱን በማስተማር የራስህ ሕዝብ አድርጓቸው” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
“መልእክትህ እውነት ነው” ወይም “የምትናገረው ነገር እውነት ነው”
እዚህ ወደ “ዓለም” ማለት በዓለም ለሚኖሩት ሰዎች ማለት ነው ፡፡ አት: - “ለዓለም ሕዝብ” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “እነሱ በእውነት ራሳቸው ራሳቸውንም እንዲለያዩ (ያሳይሳሉ: የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
በኢየሱስ የሚያምኑ እነዚያ በሚያምኑበት ጊዜ ከአብ እና ከወልድ ጋር አንድ ይሆናሉ ፡፡
ይህ ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
እዚህ ላይ “ዓለም” እግዚአብሔርን ገና የማያውቁ ሰዎችን የሚያመለክት ቃል ነው ፡፡ አት: - “እግዚአብሔርን የማያውቁ ሰዎች” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
"እንዳከበርከኝ ተከታዮቼን አክብሬአለሁ"
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - "እኛ እንዳስተባበርሃሃቸው አንድ አድርገን እነሱን አንድ አድርገህ እንድትቀላቀል" (ተመልከት: የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
“በአንድነት እንዲኖሩ”
እዚህ “ዓለም” እግዚአብሔርን የማያውቁ ሰዎችን የሚያመለክት ቃል ነው ፡፡ አት: - “ሕዝቡም ሁሉ ያውቅ ዘንድ” (የበለስ.
ይህ ዓይነቱ ፍቅር የሚመጣው እራሱ የማይጠቅም ቢሆንም እንኳ ለሌሎች የመጣው የእግዚአብሔር ፍቅር ነው ፡፡ ምንም እንኳን ምንም ቢያደርጉ ይህ ዓይነቱ ፍቅር ለሌሎች ይንከባከባል ፡፡
ይህ ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
እዚህ "ያለሁበት" እዚህ ሰማይን ያመለክታል ፡፡ አት: - "ከእኔ ጋር በሰማይ" (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
"እና ታላቅነቴን ለማየት"
እዚህ ላይ ኢየሱስ ከፍጥረት በፊት ያለውን ጊዜ ይጠቅሳል ፡፡ አት: - “ዓለምን ከመፍጠሩ በፊት” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
ኢየሱስ ፀሎቱን ጨረሰ
እዚህ “አባት” ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
የእግዚአብሔር ዓለም ላልሆኑት ሰዎች “ዓለም” የሚለው አገላለጽ ነው ፡፡ አት: - “የአንተ ያልሆኑ ሰዎች ማን እንደሆናችሁ አያውቁም” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
“ስም” የሚለው ቃል እግዚአብሔርን ያመለክታል ፡፡ አት: - “ማን እንደ ሆንሽ ገለጥኋቸው”
ይህ ዓይነቱ ፍቅር የሚመጣው እራሱ የማይጠቅም ቢሆንም እንኳ ለሌሎች የመጣው የእግዚአብሔር ፍቅር ነው ፡፡ ምንም እንኳን ምንም ቢያደርጉ ይህ ዓይነቱ ፍቅር ለሌሎች ይንከባከባል ፡፡
1 ኢየሱስ ይህን ከተናገረ በኋላ ከቄድሮን ሸለቆ ማዶ የአትክልት ስፍራ ወደሚገኝበት ቦታ ሄደ፣ ከደቀ መዛሙርቱም ጋር ወደ አትክልት ስፍራው ገባ፡፡ 2 ኢየሱስ በተደጋጋሚ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደዚያ ስፍራ ይመጣ ስለ ነበር አሳልፎ ሊሰጠው ያለው ይሁዳ ቦታውን ያውቅ ነበር፡፡ 3 ከዚያም ይሁዳ ከካህናት አለቆችና ከፈሪሳውያን ብዙ ወታደሮችንና ጠባቂዎችን ከተቀበለ በኋላ ፋኖስ፣ ችቦና የጦር መሣሪያ ይዞ ወደ አትክልት ስፍራው መጣ፡፡ 4 ከዚያም እየደረሰበት ያለውን የተረዳው ኢየሱስ ወደ ፊት ወጥቶ፣ ‹‹ማንን ፈለጋችሁ?›› አላቸው፤ 5 እነርሱ፣ ‹‹የናዝሬቱ ኢየሱስን›› ብለው መለሱለት፡፡ ኢየሱስ፣ ‹‹እኔ ነኝ›› አላቸው፡፡ አሳልፎ የሰጠው ይሁዳም ከወታደሮቹ ጋር ቆሞ ነበር፡፡ 6 ስለዚህ ‹‹እኔ ነኝ›› ባላቸው ጊዜ ወደ ኋላ አፈግፍገው በምድር ላይ ወደቁ፡፡ 7 እንደ ገናም፣ ‹‹ማንን ፈለጋችሁ?›› አላቸው። እነርሱም፣ ‹‹የናዝሬቱ ኢየሱስን›› ብለው በድጋሚ መለሱለት፡፡ 8 ኢየሱስ፣ ‹‹እኔ ነኝ አልኋችሁ፤ ስለዚህ እኔን የምትፈልጉ ከሆነ እነዚህን እንዲሄዱ ተዉአቸው›› አላቸው፡፡ 9 ይህም ‹‹ከሰጠኸኝ ከእነዚህ አንዱም አልጠፋብኝም›› ተብሎ የተነገረው ቃል እንዲፈጸም ነው፡፡ 10 ከዚያም ስምዖን ጴጥሮስ የታጠቀውን ሰይፍ መዞ የሊቀ ካህናቱን አገልጋይ ቀኝ ጆሮውን ቈረጠ፡፡ የአገልጋዩም ስም ማልኮስ ነበረ፡፡ 11 ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ ‹‹ሰይፍህን ወደ ሰገባው መልስ፡፡ አብ የሰጠኝን ጽዋ መጠጣት የለብኝም እንዴ?›› አለው፡፡ 12 ስለዚህ ወታደሮቹና አዛዣቸው እንዲሁም የአይሁድ ጠባቂዎች ኢየሱስን ይዘው አሰሩት፡፡ 13 በዚያን ዓመት ሊቀ ካህናት የነበረው ቀያፋ ለሐና አማቹ ስለ ነበረ፣ በመጀመሪያ ወደ ሐና ወሰዱት ፡፡ 14 ቀያፋ አንድ ሰው ስለ ሕዝቡ ቢሞት ይሻላል ብሎ አይሁድን የመከረው ሰው ነው፡፡ 15 ጴጥሮስና አንድ ሌላ ደቀ መዝሙር ኢየሱስን ተከትለው ሄዱ፡፡ ሌላኛው ደቀ መዝሙር ከሊቀ ካህናቱ ጋር ይተዋወቅ ስለ ነበረ፣ ከኢየሱስ ጋር ወደ ሊቀ ካህናቱ አደባባይ ገባ፡፡ 16 ጴጥሮስ ግን በውጭ በር ላይ ቆሞ ነበር፡፡ ከሊቀ ካህናቱ ጋር የሚተዋወቀው ያ ደቀ መዝሙር በር የምትጠብቀውን አገልጋይ አናግሮ ጴጥሮስን ወደ ውስጥ አስገባው፡፡ 17 ከዚያም በር ትጠብቅ የነበረችው አገልጋይ ጴጥሮስን፣ ‹‹አንተ ከዚህ ሰው ደቀ መዛሙርት አንዱ አይደለህም እንዴ?›› አለችው፡፡ እርሱ፣ ‹‹አይደለሁም›› አለ፡፡ 18 ጊዜው ብርድ ስለ ነበረ፣ አገልጋዮችና ጠባቂዎች እሳት አቀጣጥለው ዙሪያውን ከበው እየሞቁ ነበር፡፡ ጴጥሮስም በዚያ ከእነርሱ ጋር ቆሞ እሳት ይሞቅ ነበር፡፡ 19 ከዚያም ሊቀ ካህናቱ ኢየሱስን ስለ ደቀ መዛሙርቱና ስለ አስተማረው ትምህርት ጠየቀው፡፡ 20 ኢየሱስ፣ ‹‹ለዓለም ሁሉ በግልጽ ስናገር ነበር፤ ሁልጊዜ አይሁድ ሁሉ በሚሰበሰቡበት በምኵራብና በቤተ መቅደስ ሳስተምር ነበር፤ በድብቅ የተናገርሁት ምንም ነገር የለም፣ 21 ታዲያ ለምን ትጠይቀኛለህ? የተናገርኋቸውን ነገሮች ስለሚያውቁ ሲሰሙኝ የነበሩትን ሰዎች ስለተናገርኋቸው ነገሮች ጠይቅ›› ብሎ መለሰለት፡፡ 22 ኢየሱስ ይህን በተናገረ ጊዜ፣ በዚያ ከቆሙት ጠባቂዎች መካከል አንዱ በጥፊ መታውና፣ ‹‹እንደዚህ ነው ለሊቀ ካህናቱ የምትመልሰው?›› አለው፡፡ 23 ኢየሱስ፣ ‹‹አንዳች ክፉ ነገር ተናግሬ ከሆነ መስክርብኝ፤ በትክክል መልሼ ከሆነ ግን ለምን ትመታኛለህ?›› አለው፡፡ 24 ሐናም ኢየሱስን እንደ ታሰረ ወደ ሊቀ ካህናቱ ወደ ቀያፋ ላከው፡፡ 25 ስምዖን ጴጥሮስም ቆሞ እሳት እየሞቀ ነበር። ሰዎቹ፣ ‹‹አንተ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ አይደለህም እንዴ?›› አሉት። ጴጥሮስ፣ ‹‹አይደለሁም›› ብሎ ካደ፡፡ 26 ጴጥሮስ ጆሮውን የቈረጠው ሰው ዘመድ የሆነ ከሊቀ ካህናቱ አገልጋዮች አንዱ፣ ጴጥሮስን፣ ‹‹አንተን በአትክልት ስፍራው ከእርሱ ጋር አላየሁህም እንዴ?›› አለው፡፡ 27 ጴጥሮስ እንደ ገና ካደ፣ ወዲያውም ዶሮ ጮኸ፡፡ 28 ከዚያም ኢየሱስን ከቀያፋ ወደ ገዢው ግቢ ወሰዱት። ጊዜው ማለዳ ነበረ፣ ይዘውት የመጡት አይሁድ እንዳይረክሱና ፋሲካን መብላት እንዲችሉ ወደ ገዢው ግቢ መግባት አልፈለጉም። 29 ስለዚህ ጲላጦስ ወደ ውጭ ወጥቶ፣ «በዚህ ሰው ላይ ያላችሁ ክስ ምንድን ነው?» ብሎ ጠየቃቸው። 30 እነርሱም፣ «ይህ ሰው ክፉ ባያደርግ ኖሮ ወደ አንተ አናመጣውም ነበር» አሉት። 31 ስለዚህ ጲላጦስ፣ «እናንተ ወስዳችሁ በሕጋችሁ መሠረት ፍረዱበት» አላቸው። አይሁድ፣ «እኛ ማንንም ሰው ለመግደል አልተፈቀደልንም» ብለው መለሱለት። 32 ይህንም ያሉት ኢየሱስ በእንዴት ዓይነት ሞት እንደሚሞት የተናገረው ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው። 33 ጲላጦስ ወደ ግቢው ተመልሶ ኢየሱስን ጠራውና፣ «አንተ የአይሁድ ንጉሥ ነህን?» አለው። 34 ኢየሱስ፣ «ይህን የምትጠይቀኝ ከራስህ ነው ወይስ ሌሎች እንድትጠይቀኝ ስለ ነገሩህ ነው?» አለው። 35 ጲላጦስ፣ «እኔ አይሁዳዊ አይደለሁም፤ ነኝ እንዴ? ለእኔ አሳልፈው የሰጡህ የገዛ አገርህ ሰዎችና የካህናት አለቆች ናቸው፣ ምን አድርገህ ነው?» አለው። 36 ኢየሱስ፣ «የእኔ መንግሥት ከዚህ ዓለም አይደለም፤ የእኔ መንግሥት ከዚህ ዓለም ቢሆን ኖሮ አይሁድ እንዳይዙኝ አገልጋዮቼ ይዋጉልኝ ነበር። በመሠረቱ የእኔ መንግሥት ከምድር አይደለም» ብሎ መለሰለት። 37 ጲላጦስ፣ «ታዲያ አንተ ንጉሥ ነህ?» አለው፤ ኢየሱስ፣ «እኔ ንጉሥ እንደ ሆንሁ አንተ ተናገርህ፤ የተወለድሁት ወደ ዓለምም የመጣሁት ስለ እውነት ለመመስከር ነው፤ ከእውነት የሆነ ሁሉ ድምፄን ይሰማል» ብሎ መለሰለት። 38 ጲላጦስ፣ «እውነት ምንድን ነው?» ካለ በኋላ፣ እንደ ገና ወደ አይሁድ ወጣና፣ «በዚህ ሰው ላይ ምንም ጥፋት አላገኘሁበትም። 39 እንደ ተለመደው በየዓመቱ በፋሲካ በዓል አንድ እስረኛ እለቅላችኋለሁ፣ ታዲያ የአይሁድን ንጉሥ ልፍታላችሁን?» አላቸው። 40 ከዚያም፣ እነርሱ፣ እንደ ገና ጮኸው «ይህን ሰው አይደለም፣ በርባንን ፍታልን» አሉ። በርባን ግን ወንበዴ ነበር።
አጠቃላይ መረጃ ይህ የኢየሱስን መያዙን የሚጨምር የታሪኩ ቀጣይ ክፍል ነው ፡፡ ቁጥር 1 የታሪኩን መቼት እና ቁጥር 2 ይነግረናል ስለ ይሁዳ ስለ ዳራ ዕውቀት ይነግረናል ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
በኢየሩሳሌም የሚገኘውን ቤተ መቅደስ ከቤተ መቅደሱ ተራራ ከወይራ ተራራ በሚለይበት ሸለቆ (ይመልከቱ: መተርጎም_ቁጥር)
ይህ የወይራ ዛፎች እሾህ ነበር። አት: - "የወይራ ዛፎች ባለበት ቦታ" (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
ኢየሱስ ከወታደሮች ፣ ከአለቆች እና ከፈሪሳውያን ጋር መነጋገር ጀመረ ፡፡
"ከዚያም በእርሱ ላይ የሚመጣውን ሁሉ ያውቅ የነበረው ኢየሱስ"
“የናዝሬቱ ኢየሱስ”
"እሱ" የሚለው ቃል በጽሑፉ ውስጥ ተሠርቶበታል ፡፡ አት: - እኔ እኔ ነኝ (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
አሳልፎ የሰጠው ማን ነው?
እዚህ “እሱ” የሚለው ቃል በዋናው ጽሑፍ ላይ አይገኝም ፣ ግን እሱ ተተክሏል። አት: - እኔ እኔ ነኝ (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
ሰዎቹ በኢየሱስ ኃይል መሬት ላይ ወደቁ። አት: - “በኢየሱስ ኃይል የተነሳ ወደቁ” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
“የናዝሬቱ ኢየሱስ”
በቁጥር 9 ውስጥ ዮሐንስ ስለ ቅዱሳት መጻሕፍት ስለሚፈፀመው የጀርባ ታሪክ ዮሐንስ ሲነግረን ከዋናው የታሪክ መስመር ዕረፍት አለ ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
እዚህ “እሱ” የሚለው ቃል በዋናው ጽሑፍ ላይ አይገኝም ፣ ግን እሱ ተተክሏል። አት: - እኔ እኔ ነኝ (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ቃል” ኢየሱስ የጸለየውን ቃል ያመለክታል ፡፡ ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት-“ወደ አባቱ በሚጸልይበት ጊዜ የተናገራቸውን ቃሎች ለመፈጸም ይህ ተፈጸመ” (የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ማልኮስ የሊቀ ካህኑ ወንድ አገልጋይ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: መተርጎም_ቁጥር)
ሹል ቢላውን ወይም ሹልቱን ይሸፍኑ ፣ ስለዚህ ቢላዋ ባለቤቱን አይቆርጠውም
ይህ አገላለጽ በኢየሱስ መግለጫ ላይ ትኩረት ለመጨመር በጥያቄ መልክ ይታያል ፡፡ AT: - "አብ የሰጠኝን ጽዋ እኔ በእውነት መጠጣት አለብኝ!" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እዚህ “ጽዋ” ኢየሱስ ሊታገሥ የሚገባውን ስቃይ የሚያመለክት ዘይቤ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
ቁጥር 14 ስለ ቀያፋ የዳራ መረጃ ይነግረናል ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
እዚህ ላይ “አይሁዶች” ኢየሱስን ለሚቃወሙ የአይሁድ መሪዎች ምሳሌ ነው ፡፡ አት: - “የአይሁድ መሪዎች” (የበለስ ሲኖዶዶክ ተመልከት)
ወታደሮቹ እንዳያመልጥ ለመከላከል የኢየሱስን እጆች አስሩ። አት-“እንዳያመልጥ ኢየሱስን ያዘውና አሰረው” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። AT: - “ሊቀ ካህኑ ያንን ደቀ መዝሙር አውቆ ከኢየሱስ ጋር መገናኘት ችሏል” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። AT: - “ሊቀ ካህናቱ ግን ያውቀው ሌላው ደቀመዝሙር” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ይህ አገልጋይ አገልጋዩ የሰጠችውን አስተያየት በጥልቀት እንድትገልፅ ለማስቻል በጥያቄ መልክ ነው። አት: - “እርስዎ ከታሰሩት ሰው ደቀ መዝሙርም አንዱ ነዎት! አይደል?” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እነዚህ የሊቀ ካህናቱ ባሪያዎች እና የቤተ መቅደስ ጠባቂዎች ነበሩ። አትቲ: - “ቀዝቅዞ ነበር ፣ ስለሆነም የሊቀ ካህናቱ ባሪያዎች እና የቤተመቅደሱ ጠባቂዎች ከሰል የድንጋይ ከሰል ሠሩ እና በዙሪያው ቆመው ይሞቁ ነበር (ዩ.ቢ.ቢ.)
ይህ ቃል እዚህ እሳት ውስጥ ስለሞቀቁት ሰዎች መረጃ ማከል እንዲችል ዮሐንስ በዋናው የታሪክ መስመር ላይ ዕረፍትን ለማመልከት እዚህ ያገለግል ነበር ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
እዚህ የታሪኩ መስመር ወደ ኢየሱስ ተለወጠ ፡፡
ይህ ካይፋስ ነበር። (18 12 ይመልከቱ)
እዚህ “ትምህርቱ” የሚያመለክተው ኢየሱስ ሕዝቡን ያስተማረውን ነው ፡፡ አት: - “ስለ ደቀመዛሙርቱ እና ሕዝቡን ያስተምር ነበር” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
“ዓለም” ኢየሱስ ሲያስተምር ለሰሙ ሰዎች ምሳሌ ነው ፡፡ እዚህ ላይ “ዓለም” ማጋነኑ ለኢየሱስ መግለጫ ትኩረት ይሰጣል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ እና የበለስ_ቁልፍbole)
እዚህ ላይ “ሁሉም አይሁድ” በኢየሱስ አባባል ላይ አፅን thatት የሚጨምር የተጋነኑ ናቸው ፡፡ አት: - “ብዙ አይሁዶች” (ይመልከቱ: የበለስ_ጥበብ)
ይህ አስተያየት ኢየሱስ በሚናገረው ላይ አፅን toት ለመስጠት በጥያቄ መልክ ይታያል ፡፡ አት: - "እነዚህን ጥያቄዎች አትጠይቁኝም!" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ ማስታወሻ አፅን .ትን ለመጨመር በጥያቄ መልክ ይታያል። አት: - “ለሊቀ ካህናቱ እንደዚህ ያለ መልስ ሊሰጡ አይገባም!” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ስህተት ነው ያልኩትን ንገረኝ
ይህ አስተያየት ኢየሱስ በሚናገረው ላይ አፅን toት ለመስጠት በጥያቄ መልክ ይታያል ፡፡ አት: - "ትክክል የሆነውን ነገር ብቻ ከተናገር ፣ መምታት የለብዎትም!" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እዚህ የታሪኩ መስመር ወደ ፒተር ተለወጠ ፡፡
ይህ ቃል ዮሐንስ ስለ ጴጥሮስ መረጃ እንዲያቀርብ በታሪኩ መስመር ላይ ዕረፍትን ለማመልከት ያገለግላል ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
ይህ ማስታወሻ አፅን .ትን ለመጨመር በጥያቄ መልክ ይታያል። አት: - “እርስዎም ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ ነሽ!” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ ማስታወሻ አፅን .ትን ለመጨመር በጥያቄ መልክ ይታያል። እዚህ “እሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው ፡፡ AT: - “ከወይራ ዛፍ ጋር ይዘው ከያዙት ሰው ጋር በአድባሩ ዛፍ ላይ አየሁህ! (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር)
እዚህ ላይ ጴጥሮስ የተናገረው ከኢየሱስ ጋር መሆኑን እና መካፈሉን መካድ ነው ፡፡ AT: - “ጴጥሮስ ኢየሱስን ኢየሱስን አውቀዋለሁ ወይም ከእርሱ ጋር እንደነበረ እንደገና ካደ ፡፡” (ይመልከቱ ፡፡
በዚህ ስፍራ አንባቢው ኢየሱስ ዶሮ ከመጮኽ በፊት ጴጥሮስን ይክዳል ብሎ የተናገረው አንባቢው እንደሆነ ይገመታል ፡፡ በዚህ ጊዜ “ዶሮው ኢየሱስ እንደሚፈጽም እንዳዘዘው ወዲያው ዶሮ ጮኸ” (ይመልከቱ ፡፡
እዚህ የታሪኩ መስመር ወደ ኢየሱስ ተለወጠ ፡፡ ወታደሮቹና የኢየሱስ ከሳሾች ወደ ቀያፋ አመጡት ፡፡ ቁጥር 28 ወደ ፕራይቶሪየም ውስጥ ያልገቡት ለምን እንደሆነ የዳራ መረጃ ይሰጠናል ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
እዚህ ኢየሱስን የሚያመለክተው ከቀያፋ ቤት እንደሆነ ነው ፡፡ AT: “ከዚያም ኢየሱስን ከቀያፋ ቤት ወሰዱት” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
Pilateላጦስ አይሁዳዊ ስላልነበረ የአይሁድ መሪዎች በዋናው መሥሪያ ቤት ከገቡ ርኩስ ይሆናሉ። ይህ ፋሲካን እንዳያከብሩ እንቅፋት ይሆንባቸዋል። ድርብ አሉታዊውን በአዎንታዊ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። AT: “እነሱ Pilateላጦስ አረማዊ ስለነበረ እነሱ ከ Pilateላጦስ ዋና መሥሪያ ቤት ውጭ ቆዩ።
ይህንን ድርብ አሉታዊ በአዎንታዊ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። AT: - “ይህ ሰው ክፉ አድራጊ ነው ፣ እኛ ለቅጣት ወደ አንተ አመጣነው” (ይመልከቱ ፡፡
እዚህ ያለው ሐረግ ለጠላት አሳልፎ መስጠት ማለት ነው ፡፡
በቁጥር 32 ውስጥ ኢየሱስ እንዴት እንደሚሞት የተነበየው የበስተጀርባ መረጃ ደራሲው እንደሚነግረን ደራሲው ከዋናው የታሪክ መስመር ዕረፍት አለ ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
እዚህ ላይ “አይሁዶች” ኢየሱስን ለሚቃወሙና እሱን ለያዙት የአይሁድ መሪዎች ምሳሌ ነው ፡፡ AT: - “የአይሁድ መሪዎች እንዲህ አሉት” (የበለስ_ሳይንሴክቼን ይመልከቱ)
በሮማውያን ሕግ መሠረት አይሁዶች አንድን ሰው ሊገድሉት አልቻሉም ፡፡ አት: - “በሮማውያን ሕግ መሠረት አንድን ሰው መግደል አንችልም” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “ኢየሱስ ቀደም ብሎ የተናገረውን ለመፈፀም” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
እንዴት እንደሚሞት በተመለከተ ”
ይህ አገላለጽ በጥያቄ መልክ መልክ Pilateላጦስ በአይሁድ ህዝብ ባህላዊ ጉዳዮች ላይ ግድ የለሽ መሆኑን አፅን canት ለመስጠት ያስችለዋል ፡፡ አት: - "እኔ በእርግጥ እኔ አይሁዳዊ አይደለሁም ፣ እናም ለእነዚህ ጉዳዮች ምንም ፍላጎት የለኝም!" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
“የእምነት ባልንጀሮችህ”
እዚህ “ዓለም” ኢየሱስን ለሚቃወሙ ሰዎች ተምሳሌት ነው ፡፡ ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “መንግሥቴ የዚህ ዓለም ክፍል አይደለም” (ዩ.አር.ቢ.) ወይም 2) “እኔ እንደ ንጉሣቸው የመግዛት ዓለም አያስፈልገኝም” ወይም “እኔ ንጉሥ የመሆን ስልጣን የለኝም ፡፡ . " (ይመልከቱ: የበለስ_ጥበብ)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - የአይሁድ መሪዎች እንዳይወዱኝ ይከለክለኝ ነበር (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
እዚህ ላይ “አይሁዶች” ኢየሱስን የሚቃወሙትን የአይሁድ መሪዎችን የሚያመላክት መግለጫ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: በለስ
እዚህ “ዓለም” በዓለም የሚኖሩ ሰዎችን የሚያመላክት የመውደቅ ምልክት ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ ሲኖዶክዬ)
እዚህ ላይ “እውነት” የሚያመለክተው ስለ እግዚአብሔር እውነቱን ነው ፡፡ አት: - “ስለ እግዚአብሔር እውነቱን ይናገሩ” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
ይህ ዘይቤያዊ አነጋገር ስለ እግዚአብሔር እውነተኛውን የሚወድ ማንኛውንም ሰው የሚያመለክት ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ ቪዲዮም)
እዚህ “ድምፅ” ኢየሱስ የተናገራቸውን ቃላቶች የሚያወሳስብ መግለጫ ነው። አት: - “የምናገረው ነገሮች” ወይም “እኔ” ይመልከቱ
ይህ አስተያየት በእውነቱ እውነት ምን እንደሆነ ማንም ማንም አያውቅም የሚለውን የ Pilateላጦስን እምነት ለማንፀባረቅ በጥያቄ መልክ ይታያል። እዚህ ያለው አስደንጋጭ ነገር ኢየሱስ እርሱ እውነት መሆኑን ነው ፡፡ አት: - "እውነት የሆነውን ማንም ሊያውቅ አይችልም!" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ እና በለስ_irony)
እዚህ ላይ “አይሁዶች” ኢየሱስን የሚቃወሙትን የአይሁድ መሪዎችን የሚያመላክት መግለጫ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: በለስ
ይህ ኤሊፕሲስ ነው። ተተኳሪ ቃላትን ማከል ይችላሉ ፡፡ አት: - አይ ፣ ይህን ሰው አትለቀቁ! ይልቁንስ በርባንን ፈታላቸው! (ይመልከቱ: የበለስ_ሊሴስ)
ዮሐንስ ስለ በርባን የጀርባ መረጃን ይሰጣል ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
1 ከዚያም ጲላጦስ ኢየሱስን ወስዶ አስገረፈው። 2 ወታደሮቹ የእሾኽ አክሊል ጐንጕነው በኢየሱስ ራስ ላይ አደረጉ። ሐምራዊ ልብስም አለበሱት። 3 ወደ እርሱ መጥተው፣ «የተከበሩ የአይሁድ ንጉሥ ሆይ!» አሉ በጥፊም መቱት። 4 ከዚያም ጲላጦስ እንደ ገና ወደ ወጥቶ ሕዝቡን፣ «ምንም ጥፋት እንዳላገኘሁበት እንድታውቁ እነሆ፣ ሰውየውን ወደ ውጭ አወጣላችኋለሁ» አላቸው። 5 ስለዚህ ኢየሱስ የእሾኽ አክሊል ደፍቶና ሐምራዊ ልብስ ለብሶ ወደ ውጭ ወጣ። ጲላጦስም፣ «እነሆ፣ ሰውየው!» አላቸው። 6 የካህናት አለቆችና ጠባቂዎቹ ኢየሱስን ባዩ ጊዜ፣ «ስቀለው፣ ስቀለው» እያሉ ጮኹ። ጲላጦስ፣ «እናንተ ወስዳችሁ ስቀሉት፤ እኔ ምንም ወንጀል አላገኘሁበትም» አላቸው። 7 አይሁድ፣ «እኛ ሕግ አለን፣ በሕጋችን መሠረትም ይህ ሰው ራሱን የእግዚአብሔር ልጅ አድርጓልና ሞት ይገባዋል» ብለው መለሱ። 8 ጲላጦስ ይህን ሲሰማ የበለጠ ደነገጠ፤ 9 ወደ ግቢውም ተመልሶ ኢየሱስን፣ «ከየት ነው የመጣኸው?» ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስ ግን ምንም አልመለሰለትም። 10 ጲላጦስም ኢየሱስን፣ «አናግረኝ እንጂ፤ ልፈታህም ሆነ ልሰቅልህ ሥልጣን እንዳለኝ አታውቅም እንዴ?» አለው። 11 ኢየሱስ፣ «ከላይ ባይሰጥህ ኖሮ በእኔ ላይ ምንም ሥልጣን ባልኖረህ ነበር። ስለዚህም ለአንተ አሳልፎ የሰጠኝ ኀጢአቱ የከፋ ነው» አለው። 12 ከዚህ መልሱ የተነሣ ጲላጦስ ሊፈታው ፈለገ፣ ነገር ግን አይሁድ፣ «ራሱን ንጉሥ ብሎ የሚጠራ ቄሣርን የሚቃወም ስለ ሆነ፣ ይህን ሰው ብትለቀው አንተ የቄሣር ወዳጅ አይደለህም» እያሉ ይጮኹ ነበር። 13 ጲላጦስ እነዚህን ቃላት በሰማ ጊዜ ኢየሱስን ወደ ውጭ አውጥቶ የድንጋይ ንጣፍ፣ በዕብራይስጥ ግን ገበታ ተብሎ በሚጠራ ስፍራ በፍርድ ወንበር ላይ ተቀመጠ። 14 ቀኑ ለፋሲካ በዓል ዝግጅት የሚደረግበትና ሰዓቱም ከቀኑ ስድስት ሰዓት አካባቢ ነበር። ጲላጦስ አይሁድን፣ «እነሆ፣ ንጉሣችሁ» አላቸው። 15 እነርሱም፣ «አስወግደው፣ አስወግደው፣ ስቀለው!» እያሉ ጮኹ። እርሱ፣ «ንጉሣችሁን ልስቀለውን?» አላቸው። የካህናት አለቆችም፣ «እኛ ከቄሣር በቀር ሌላ ንጉሥ አናውቅም» ብለው መለሱለት። 16 ስለዚህ ጲላጦስ ኢየሱስን እንዲሰቅሉት ፈቀደላቸው። 17 ከዚያም ኢየሱስን፣ የሚሰቀልበትን መስቀል አሸክመው የራስ ቅል፣ በዕብራይስጥ ደግሞ ጎልጎልታ ወደሚባል ቦታ ወሰዱት። 18 በዚያም ስፍራ ሰቀሉት፤ ሁለት ሌሎች ሰዎችንም በኢየሱስ ግራና ቀኝ ሰቀሉ። 19 ጲላጦስም ጽሑፍ አዘጋጅቶ በኢየሱስ መስቀል ላይ አስቀመጠ። ጽሑፉም፣ «የናዝሬቱ ኢየሱስ፣ የአይሁድ ንጉሥ» የሚል ነበር። 20 ኢየሱስ የተሰቀለበት ቦታ ለከተማው ቅርብ ስለ ነበር፣ ብዙ አይሁድ ጽሑፉን ያነቡት ነበር። ጽሑፉም የተጻፈው በዕብራይስጥ፣ በላቲንና በግሪክ ቋንቋዎች ነበር። 21 የአይሁድ የካህናት አለቆችም ጲላጦስን «እርሱ ራሱን 'የአይሁድ ንጉሥ ነኝ' ብሏል ብለህ ነው እንጂ፣ 'የአይሁድ ንጉሥ' ብለህ መጻፍ የለብህም» አሉት። 22 ጲላጦስም፣ «አንዴ የጻፍሁትን ጽፌአለሁ» አላቸው። 23 ወታደሮቹ ኢየሱስን ከሰቀሉት በኋላ ልብሱን ወስደው ለእያንዳንዳቸው እንዲዳረስ አድርገው አራት ቦታ ቈራረጡት፣ እጀ ጠባቡንም ወሰዱ። 24 እጀ ጠባቡ ግን ከላይ ጀምሮ ወጥ ሆኖ የተሠራ ነበረና እርስ በርሳቸው «ከምንቀደው ዕጣ እንጣጣልና የሚደርሰው ይውሰደው» ተባባሉ። ይህም የሆነው በቅዱስ መጽሐፍ፣ «ልብሴን ተከፋፈሉት በእጀ ጠባቤም ላይ ዕጣ ተጣጣሉበት» የተባለው ቃል እንዲፈጸም ነው። 25 ወታደሮቹ ይህን በሚያደርጉበት ጊዜ የኢየሱስ እናት ማርያም፣ የእናቱ እኅት፣ የቀለዮጳ ሚስት ማርያምና መግደላዊት ማርያም በዚያ በኢየሱስ መስቀል አጠገብ ቆመው ነበር። 26 ኢየሱስ እናቱንና ይወደው የነበረውን ደቀ መዝሙር አብረው ቆመው ባየ ጊዜ፣ እናቱን «አንቺ ሴት እነሆ፣ ከአጠገብሽ ያለው እንደ ልጅሽ ይሁንልሽ» አላት ፤ 27 ደቀ መዝሙሩንም፣ «እነኋት፣ በአጠገብህ ያለችው እንደ እናትህ ትሁንልህ» አለው። ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት። 28 ኢየሱስ ሁሉ እንደ ተፈጸመ ዐውቆ፣ በቅዱሳት መጻሕፍት የተጻፈው እንዲፈጸም፣ «ተጠማሁ» አለ። 29 በዚያም በሆምጣጤ የተሞላ ዕቃ ተቀምጦ ነበር፤ ወዲያውም በሆምጣጤ የተሞላ ሰፍነግ በሂሶጵ ወደ አፉ አስጠጉለት። 30 ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከጠጣ በኋላ «ተፈጸመ» አለ። ራሱንም አዘንብሎ ሞተ። 31 ቀኑ የመዘጋጀት ቀን በመሆኑና ሰንበትም በአይሁድ ዘንድ በጣም የሚከበር ስለነበረ በሰንበት ሥጋቸው በመስቀል ላይ መቆየት ስለሌለበት የሞት ፍርድ የተፈጸመባቸው ሰዎች እግሮቻቸው እየተሰበረ ሥጋቸው ከመስቀል እንዲወርድ አይሁድ ጲላጦስን ለመኑት። 32 ከዚያም ወታደሮቹ መጥተው ከኢየሱስ ጋር ከተሰቀሉት ሰዎች በመጀመሪያ የአንዱን፣ ቀጥሎም የሌላኛውን ሰው እግሮች ሰበሩ። 33 ወደ ኢየሱስ በመጡ ጊዜ ግን ሞቶ ስላገኙት እግሮቹን አልሰበሩም። 34 ይሁን እንጂ፣ ከወታደሮቹ አንዱ ጐኑን በጦር ወጋው፣ ወዲያውም ከጐኑ ደምና ውሃ ወጣ። 35 ይህን ያየው ሰው ስለዚህ መስክሯል፣ ምስክርነቱም እውነት ነው። እናንተም እንድታምኑ የተናገረው እውነት እንደ ሆነ ያውቃል። 36 እነዚህ ነገሮች የሆኑት «ከዐጥንቱ አንድም አይሰበርም» የሚለው የመጽሐፍ ቃል እንዲፈጸም ነው። 37 ደግሞም በሌላ መጽሐፍ፣ «የወጉትን ያዩታል» ተብሎ ተጽፎአል። 38 ከእነዚህ ነገሮች በኋላ አይሁድን ፈርቶ በድብቅ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የነበረውና ከአርማትያስ ከተማ የሆነው ዮሴፍ የኢየሱስን አስከሬን ለመውሰድ ጲላጦስን ለመነ። ጲላጦስም ፈቀደለት። ዮሴፍም መጥቶ የኢየሱስን አስከሬን ወሰደ። 39 በአንድ ወቅት በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረው ኒቆዲሞስም አንድ መቶ ነጥር ያህል የእሬትና የከርቤ ቅልቅል ይዞ መጣ። 40 ስለዚህ የኢየሱስን አስከሬን ወስደው በአይሁድ ባህል አስከሬን ከመቀበሩ በፊት እንደሚደረገው ልማድ አስከሬኑን ሽቱ በተቀባ በበፍታ ጨርቅ ገነዙት። 41 ኢየሱስ ከተቀበረበት ቦታ አጠገብ የአትክልት ስፍራ ነበረ፤ በዚያም ማንም ገና ያልተቀበረበት ዐዲስ መቃብር ይገኝ ነበረ። 42 ቀኑ ለአይሁድ የመዘጋጀት ቀን በመሆኑና መቃብሩም ቅርብ ስለ ነበር፣ የኢየሱስን አስከሬን በዐዲሱ መቃብር አኖሩት።
ካለፈው ምዕራፍ የታሪኩ ክፍል ይቀጥላል ፡፡ ኢየሱስ በአይሁድ እየተከሰሰ እያለ Pilateላጦስ ፊት ቆሟል።
Pilateላጦስ ራሱ ኢየሱስን አልተገረፈም። እዚህ “Pilateላጦስ” Pilateላጦስ ኢየሱስን እንዲገርፉት ላዘዘላቸው ወታደሮች አመፅ ነው ፡፡ አት-“በዚያን ጊዜ Pilateላጦስ ወታደሮቹን ኢየሱስን እንዲገርፉት አዘዘ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ስኔክዶቼ)
በተነሳው እጅ “ሰላም” ሰላምታ ማሰማት ቄሳርን ለመግለጽ ብቻ ነበር ፡፡ ወታደሮች ኢየሱስን በእሾህ አክሊል እና ሐምራዊውን ቀሚስ በመጠቀም ኢየሱስን ለማፌዝ ሲጠቀሙበት ፣ እሱ በእውነት ንጉስ መሆኑን አለመናገራቸው እንግዳ ነገር ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_አሮን)
Pilateላጦስ ይህንን ሁለቴ ሁለት ጊዜ ገል Jesusል አላምንም ኢየሱስን አላምንም ብሎ ወንጀለኛ የለም ፡፡ እሱ ሊቀጣው አይፈልግም ፡፡ አት: - “እሱን የምቀጣው ምንም ምክንያት አላየሁም” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
አክሊል እና ሐምራዊው ቀሚስ ነገሥታት የሚለብሷቸው ብቻ ናቸው ፡፡ ወታደሮች ኢየሱስን በዚህ መንገድ ያሾፉበት ነበር ፡፡ 19 1 ይመልከቱ ፡፡
እዚህ ላይ “አይሁዶች” ኢየሱስን ለተቃወሙት የአይሁድ መሪዎች ምሳሌ ነው ፡፡ አት: - “የአይሁድ መሪዎች ለ Pilateላጦስ ምላሽ ሰጡ” (ይመልከቱ። የበለስ.
ኢየሱስ “የእግዚአብሔር ልጅ” ነኝ ስላለ በመስቀል ሞት ሞት ተፈረደበት ፡፡
ይህ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
ይህ አስተያየት በጥያቄ መልክ ይታያል ፡፡ እዚህ ላይ Pilateላጦስ ፣ ኢየሱስ ራሱን ለመከላከል አጋጣሚውን አለመጠቀሙን አስገርሞታል ፡፡ አት: - "እኔን ለማነጋገር ፈቃደኛ እንዳልሆንኩ አምናለሁ" ወይም "መልስልኝ!" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ ማስታወሻ አፅን .ትን ለመጨመር በጥያቄ መልክ ይታያል። አት: - “ልፈታህ እንደምችል ማወቅ ወይም ወታደሮቼ እንዲሰቅሉህ ማዘዝ እችላለሁ!” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እዚህ “ኃይል” አንድን ነገር የማድረግ ችሎታ ወይም የሆነ ነገር እንዲከሰት የማድረግ ችሎታን የሚያመለክት ቃል ነው። (ይመልከቱ: የበለስ_ጥበብ)
ይህንን ድርብ አሉታዊ በአዎንታዊ እና ንቁ ቅርፅ መተርጎም ይችላሉ። AT: - "እናንተን መቃወም የምትችሉት እግዚአብሔር ስላደረጋችሁ ብቻ ነው" (የበለስ_ቁጥር ችግሮች እና የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ እግዚአብሔርን የሚያከብርበት መንገድ ነው ፡፡
እዚህ ያለው ሐረግ ለጠላት አሳልፎ መስጠት ማለት ነው ፡፡
እዚህ “ይህ መልስ” የኢየሱስን መልስ ያመለክታል ፡፡ አት-“Pilateላጦስ የኢየሱስን መልስ ሲሰማ” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
በጥንታዊው የ “ሙከራ” መልክ Pilateላጦስ ኢየሱስን ለመልቀቅ “ከባድ” ወይም “ብዙ ጊዜ” እንደሞከረ ያሳያል። አት: - “ኢየሱስን ለማስለቀቅ በጣም ተሞከረ” ወይም “ኢየሱስን ለመልቀቅ ደጋግሞ ሞክሮ ነበር” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
እዚህ ላይ “አይሁዶች” ኢየሱስን የሚቃወሙትን የአይሁድ መሪዎችን የሚያመላክት መግለጫ ነው ፡፡ በመነሻውም ፣ ‹የጩኸት› ቅርፅ የሚያመለክተው ደጋግመው ጩኸት ወይም ጩኸት መሆኑን ነው ፡፡ አት: - “የአይሁድ መሪዎች ግን መጮህ ጀመሩ” (የበለስ_ሳይንኮቻ እና የበለስ_ቁጥር ግልፅ) ይመልከቱ
“ቄሳርን ትቃወማለህ” ወይም “ንጉሠ ነገሥቱን ትቃወማለህ”
እርሱ ንጉሥ ነው ይላል
እዚህ “እሱ” Pilateላጦስን የሚያመለክተው ለ “Pilateላጦስ ወታደሮችን አዝዞ” ነው ፡፡ አት-“ወታደሮቹን ኢየሱስን እንዲያወጡአቸው አዘዘ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ስኔክዶቼ)
እንደ Pilateላጦስ ያሉ አስፈላጊ ሰዎች ኦፊሴላዊ ተግባራቸውን ባከናወኑበት ጊዜ ተቀመጡ ፣ በጣም አስፈላጊ ያልሆኑ ሰዎች ግን ተነሱ ፡፡
እንደ Pilateላጦስ ያለ አንድ ወሳኝ ሰው የፍርድ ውሳኔ በሚሰጥበት ጊዜ የተቀመጠበት ልዩ ወንበር ነው ፡፡ ቋንቋዎ ይህንን ተግባር የሚያብራራበት ልዩ መንገድ ካለው እዚህ ሊጠቀሙበት ይችላሉ ፡፡
ይህ አስፈላጊ ሰዎች ብቻ እንዲሄዱ የተፈቀደበት ልዩ የድንጋይ ጣሪያ ነው ፡፡ ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “ሰዎች የድንጋይ ንጣፍ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ውስጥ” (ተመልከት: የበለስ_ቁጥር)
ይህ የእስራኤል ሰዎች የሚናገሩትን ቋንቋ ያመለክታል ፡፡
Pilateላጦስ ወታደሮቹን ኢየሱስን ለመስቀል ወታደሮቹን ሲያዝዘው የተወሰነ ጊዜ አል andል ፡፡
ዮሐንስ ስለ መጪው ፋሲካ እና የቀኑ ሰዓት መረጃ እንዲሰጥ ይህ ቃል በታሪኩ መስመር ላይ ዕረፍትን ያሳያል ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
"እኩለ ቀን ላይ"
እዚህ ላይ “አይሁዶች” ኢየሱስን የሚቃወሙትን የአይሁድ መሪዎችን የሚያመላክት መግለጫ ነው ፡፡ አት: - “Pilateላጦስ ለአይሁድ መሪዎች።” (የበለስ.
እዚህ “እኔ” የሚለው በእርግጥ በእውነቱ ስቅለቱን የሚፈጽሙትን የ Pilateላጦስን ወታደሮች የሚያመላክት ምልክት ነው ፡፡ አትቲ: - "እኔ ወታደሮቼን ንጉ yourን በመስቀል ላይ በምስማር እንዲቸንክ እንዳነግራቸው በእርግጥ ትፈልጋለህ?" (ይመልከቱ: በለስ
እዚህ Pilateላጦስ ወታደሮቹ ኢየሱስን እንዲሰቅሉት አዘዘ ፡፡ ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት-“ስለዚህ Pilateላጦስ ወታደሮቹን ኢየሱስን እንዲሰቅሉት ወታደሮቹን አዘዘ” (የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “ሰዎች 'የራስ ቅል ቦታ' ብለው የጠሩበት ቦታ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ዕብራይስጥ የእስራኤል ሕዝብ ቋንቋ ነው ፡፡ ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - በዕብራይስጥ ‹ጎልጎታ› ብለው ይጠሩታል ፡፡
ይህ ኤሊፕሲስ ነው። የተተረጎሙትን ቃላት በመጨመር ይህንን መተርጎም ይችላሉ ፡፡ አት: - “ሌሎች ሁለት ወንጀለኞችም በመስቀሎቻቸው ላይ በምስማር ተቸነከሩ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ሊሴስ)
እዚህ “Pilateላጦስ” በምልክቱ ላይ ለፃፈው ሰው አመላካች ነው ፡፡ እዚህ “በመስቀል ላይ” የኢየሱስን መስቀል ያመለክታል ፡፡ አት: - “Pilateላጦስም በምልክቱ ላይ እንዲጽፍ ከኢየሱስ መስቀል ጋር እንዲያይም ሰው አዘዘው” (የበለስ.
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት-“ስለሆነም ያ ሰው ቃላቱን ጻፈ የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ኢየሱስ” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት-ወታደሮች ኢየሱስን የሰቀሉት ቦታ "(የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “ምልክቱን ያዘጋጀው ቃላቱን በ 3 ቋንቋዎች ጻፈ ፤ ዕብራይስጥ ፣ ላቲን እና ግሪክ” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ይህ የሮማውያን መንግሥት ቋንቋ ነበር።
የካህናት አለቆቹ በምልክቱ ላይ ስለ ቃሉ ለመግለጽ ወደ Pilateላጦስ ዋና መሥሪያ ቤት ተመልሰው መሄድ ነበረባቸው። AT: - “የካህናት አለቆቹ ወደ Pilateላጦስ ተመልሰው እንዲህ አሉ (UDB) (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
Pilateላጦስ በምልክቱ ላይ ያሉትን ቃላት እንደማይቀይር ገለጸ። አት: - ለመጻፍ የፈለግኩትን ጽፌያለሁ ፣ ግን አልለውጠውም! (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
በቁጥር 24 መጨረሻ ላይ ዮሐንስ ይህ ክስተት ጸሐፊነትን እንዴት እንደሚፈጽም ዮሐንስ ሲነግረን ከዋናው የታሪክ መስመር ዕረፍት አለ ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
ልብሱንም ይይዙት ነበር። ወታደሮች ቀሚሱን ለየብቻ አደረጉ እና አልከፋፈሉትም ፡፡ አት: - “ልብሱንም ለዩ” (UDB) (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ወታደሮቹ ቁማር ይጫወታሉ አሸናፊውም ሸሚዙን ይቀበላል ፡፡ አት: - “ለመልበስ ቁማር እንጫወት እና አሸናፊውም እንደዚሁ ይቀጥላል” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። “ይህ የተናገረው የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ተፈጸመ” ወይም “ይህ የተናገረው የቅዱስ መጽሐፉ ቃል እንዲፈጸም ይህ ሆነ”
ወታደሮች የኢየሱስን ልብስ በመካከላቸው የከፋፈሉት በዚህ ነበር ፡፡ አት: - “ተጫወቱ”
የዚህ ወንጌል ጸሐፊ ዮሐንስ ነው ፡፡
እዚህ “ልጅ” የሚለው ቃል ዘይቤ ነው ፡፡ ኢየሱስ ደቀ መዝሙሩ ዮሐንስ ለእናቱ እንደ ልጅ እንዲሆን ይፈልጋል ፡፡ አት-“ሴት ፣ እነሆ ልጅሽን እንደ ልጅ የሚያደርግልሽ ይኸውልሽ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር) ፡፡
እዚህ “እናት” የሚለው ቃል ዘይቤ ነው ፡፡ ኢየሱስ እናቱ ለደቀ መዝሙሩ ለ ዮሐንስ እናት እንደ እናት እንድትሆን ይፈልጋል ፡፡ አት: - “ይህችን ሴት እንደ እናትሽ አድርገሽ አስብ” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
“ከዚያች ቅጽበት” (ዩዲቢ)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - "እግዚአብሔር እንዲያደርግ ያዘዘውን ሁሉ እንዳደረገ ያውቅ ነበር" (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “አንድ ሰው የወይን ጠጅ የሞላበትን የወይን ጠጅ የሞላው ሙሉ ዕቃ በዚያ አኖረው” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
"መራራ ወይን"
እዚህ “እነሱ” የሚያመለክተው የሮማውያንን ዘበኞች ነው።
ብዙ ፈሳሽ ሊይዝ እና ሊይዝ የሚችል ትንሽ ነገር
“ሂሶፕ በሚባል ተክል ቅርንጫፍ ላይ”
ኢየሱስ መንፈሱን ለእግዚአብሔር መስጠቱን ዮሐንስ እዚህ ላይ አመልክቷል ፡፡ AT: “ራሱንም አዘንብሎ ለእግዚአብሔር መንፈሱን ሰጠው” ወይም “ራሱን አዘንብሎ ሞተ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
እዚህ ላይ “አይሁዶች” ኢየሱስን ለተቃወሙት የአይሁድ መሪዎች ምሳሌ ነው ፡፡ አት: - “የአይሁድ መሪዎች” (የበለስ ሲኖዶዶክ ተመልከት)
ይህ ከፋሲካ በፊት ሰዎች ለፋሲካ ምግብ የሚዘጋጁበት ጊዜ ነው ፡፡
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “የተገደሉትን ሰዎች እግሮች ሰብረው ሥጋዎቻቸውን ከመስቀል ላይ ያወርዳሉ” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - "ከኢየሱስ አጠገብ ሰቀሉት" (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ይህ ዓረፍተ ነገር ለታሪኩ ዳራ መረጃን ይሰጣል ፡፡ ዮሐንስ እዚያ እንደነበረ እና እሱ የፃፈውን እምነት ልንጥልበት እንደምንችል ለአንባቢዎች ይነግራቸዋል ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
“መመስከር” ማለት አንድ ሰው ስላየው ነገር መናገር ማለት ነው ፡፡ አት: - “ስላየው ነገር ሁሉ እውነቱን ተናግሯል” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
እዚህ “ማመን” ማለት አንድ ሰው በኢየሱስ ላይ እምነት መጣል ማለት ነው ፡፡ አት: - "ስለሆነም በኢየሱስ እንድታምኑ" (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
በእነዚህ ቁጥሮች ውስጥ ዮሐንስ እነዚህ ክስተቶች በቅዱሳት መጻሕፍት እንዴት እንደ ተከናወኑ ዮሐንስ ሲነግረን ከዋናው የታሪክ መስመር ዕረፍት አለ ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - "አንድ ሰው በቅዱሳት መጻሕፍት የጻፈውን ቃል ለመፈፀም" (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ ከመዝሙር 34 የተወሰደ ጥቅስ ነው ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ ፡፡ አት: - “ማንም አጥንቶቹን አይሰብርም” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ ከዝካርያስ 12 የተወሰደ ጥቅስ ነው ፡፡
አርማትያስ ትንሽ ከተማ ነበረች ፡፡ አት: - “ዮሴፍ ከአርማትያስ ከተማ” (ተመልከት: ትርጓሜ_ያሜ)
እዚህ ላይ “አይሁዶች” ኢየሱስን ለተቃወሙት የአይሁድ መሪዎች ምሳሌ ነው ፡፡ አት: - “የአይሁድ መሪዎችን መፍራት” (የበለስ_ስኔክዶቼን ይመልከቱ)
ዮሐንስ የአርማትያሱ ዮሴፍ የኢየሱስን አስከሬን ለመቅበር እንደሚፈልግ ዮሐንስ አመልክቷል ፡፡ አት: - የኢየሱስን አስከሬን ለቀብር ለመውሰድ ፈቃድ “(የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
ኒቆዲሞስ በኢየሱስ ከሚያምኑት ከፈሪሳውያን አንዱ ነበር ፡፡ ይህንን ስም በ 3 1 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
እነዚህ ሰዎች ሰውነትን ለመቃብር ለማዘጋጀት የሚጠቀሙባቸው ቅመሞች ናቸው ፡፡
"100" (ይመልከቱ: በትርጉም_ቁጥር)
“ሊራ” ከ 31 ግራም ጋር እኩል የሆነ የክብደት ልኬት ነው። በ 12 1 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
በዚህ ስፍራ ዮሐንስ ኢየሱስን ስለሚቀብሩበት መቃብር ያለበትን ስፍራ ዳራ መረጃ ለመስጠት እዚህ የታሪክ መስመሩ ውስጥ መግቻ ምልክት አድርጓል ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። AT: “ኢየሱስን በሰቀሉት ቦታ የአትክልት ስፍራ ነበር” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - "ማንም ሰው የተቀበረበት በዚህ ስፍራ አይደለም" (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
በአይሁድ ሕግ መሠረት አርብ ፀሐይ ከጠለቀች በኋላ ማንም መሥራት አይችልም። ይህ የሰንበት እና የፋሲካ መጀመሪያ ነበር። አት: - “ፋሲካው በዚያ ምሽት ሊጀመር ነው” (ዩአርቢ) (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
1 በሳምንቱ በመጀመሪያው ቀን ገና ጨለማ እያለ መግደላዊት ማርያም በሌሊት ወደ መቃብሩ መጣች፤ ድንጋዩ ከመቃብሩ ተንከባሎ አየች። 2 ስለዚህ ወዲያው እየሮጠች ተመልሳ ወደ ጴጥሮስና ኢየሱስ ይወደው ወደ ነበረው ደቀ መዝሙር መጥታ፣ «ጌታን ከመቃብሩ አውጥተው ወስደውታል፣ የት እንዳደረጉትም አናውቅም» አለቻቸው። 3 ከዚያም ጴጥሮስና ሌላኛው ደቀ መዝሙር ወደ መቃብሩ ሄዱ። 4 አብረው እየሮጡ ሳለ፣ ሌላኛው ደቀ መዝሙር ጴጥሮስን ቀድሞ ወደ መቃብሩ ደረሰ። 5 ጐንበስ ብሎ ወደ ውስጥ ሲመለከት፣ የበፍታ ጨርቁ ተቀምጦ አየ፣ ወደ ውስጥ ግን አልገባም። 6 ከእርሱም በኋላ ጴጥሮስ ደረሰና ወደ መቃብሩ ውስጥ ገባ። የበፍታ ጨርቁ ተቀምጦ አየ፣ 7 በኢየሱስ ራስ ላይ የነበረውንም ጨርቅ ከበፍታ ጨርቁ ጋር ዐብሮ ሳይሆን ለብቻው እንደ ተጠቀለለ በቦታው ተቀምጦ አየ። 8 ከዚያም ጴጥሮስ ቀድሞ ወደ መቃብሩ ደርሶ የነበረው ደቀ መዝሙር ወደ ውስጥ ገባና አይቶ አመነ። 9 ምክንያቱም እስከዚያን ሰዓት ድረስ ኢየሱስ ከሞት እንደሚነሣ በመጻሕፍት የተነገረውን ቃል አላስተዋሉም ነበር። 10 ስለዚህ ደቀ መዛሙርቱ ወደየቤታቸው ሄዱ። 11 ነገር ግን መግደላዊት ማርያም እያለቀስች ከመቃብሩ ውጭ ቆማ ነበር፤ እያለቀሰችም ጐንበስ ብላ ወደ መቃብሩ ውስጥ ተመለከተ። 12 የኢየሱስ አስከሬን ተጋድሞበት በነበረው ቦታ ላይ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት መላእክት፣ አንደኛው በራስጌ፣ ሌላው ደግሞ በእግርጌ ተቀምጠው አየች። 13 እነርሱም፣ «አንቺ ሴት፣ ለምን ታለቅሻለሽ?» አሏት፤ እርሷም፣ «ጌታዬን ስለወሰዱትና ወዴትም እንዳኖሩት ስለማላውቅ ነው።» አለቻቸው። 14 ይህን ብላ ዞር ስትል፣ ኢየሱስን እዚያው ቆሞ አየችው፤ እርሱ እንደ ሆነ ግን አላወቀችም ነበር። 15 ኢየሱስ፣ «አንቺ ሴት ለምን ታለቅሽያለሽ፣ ማንንስ እየፈለግሽ ነው?» አላት። እርሷም የአትክልት ስፍራው ጠባቂ መስሏት፣ «ጌታዬ የወሰድኸው አንተ ከሆንህ እባክህ የት እንዳስቀመጥኸው ንገረኝና ልውሰደው።» አለችው። 16 ኢየሱስም፣ «ማርያም» አላት። ዞር ብላ በአረማይክ ቋንቋ፣ «ረቡኒ» አለችው፤ ትርጓሜውም «መምህር» ማለት ነው። 17 ኢየሱስም«ገና ወደ አብ አልሄድሁምና አትንኪኝ፣ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ፣ ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ መሄዴ ነው ብለሽ ንገሪአቸው» አላት። 18 መግደላዊት ማርያምም ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጥታ፣ «ጌታን አየሁት» ብላ ኢየሱስ የነገራትን ሁሉ ነገረቻቸው። 19 በዚያው ቀን ማለትም ከሳምንቱ በመጀመሪያው ቀን ምሽት ላይ፣ ደቀ መዛሙርቱ አይሁድን ፈርተው በሮቹ ተዘግተው ሳለ ኢየሱስ በመካከላቸው ቆሞ፣ «ሰላም ለእናንተ ይሁን» አላቸው። 20 ይህንም ብሎ እጁንና ጐኑን አሳያቸው። ደቀ መዛሙርቱም ጌታን ባዩት ጊዜ፣ ደስ አላቸው። 21 እንደ ገናም ኢየሱስ፣ «ሰላም ለእናንተ ይሁን፣ አብ እንደ ላከኝ እኔም እልካችኋለሁ» አላቸው። 22 ይህንም ብሎ እፍ አለባቸውና፣ «መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ፣ 23 ኀጢአቱን ይቅር ያላችሁት ማንም ይቅር ይባልለታል፣ ኀጢአቱን የያዛችሁበት ማንም ይያዝበታል» አላቸው። 24 ኢየሱስ ወደ ደቀ መዛሙርቱ በመጣ ጊዜ፣ ከዐሥራ ሁለቱ አንዱ የሆነው ሌላ ስሙ ዲዲሞስ የሚባለው ቶማስ ዐብሮአቸው አልነበረም። 25 ኋላ ላይ ሌሎቹ ደቀ መዛሙርት፣ «ጌታን አየነው እኮ» አሉት። እርሱም፣ «የምስማር ምልክቱን በእጆቹ ላይ ካላየሁ፣ ጣቶቼንም በምስማር ምልክቱና እጄን በጐኑ ካላስገባሁ አላምንም» አላቸው። 26 ከስምንት ቀን በኋላ ደቀ መዛሙርቱ በቤት ውስጥ ነበሩ፤ ቶማስም ዐብሯቸው ነበረ። በሮቹ ተዘግተው ሳለ ኢየሱስ በመካከላቸው ቆሞ፣ «ሰላም ለእናንተ ይሁን» አላቸው። 27 ቶማስንም፣ «ጣቶችህን አምጣና እጆቼን ንካ፣ እጆችህንም ወደ ጐኔ አስገባ፣ እመን እንጂ የማታምን አትሁን» አለው። 28 ቶማስም፣ «ጌታዬና አምላኬ» ብሎ መለሰለት። 29 ኢየሱስ «አንተ ስላየኸኝ አመንህ፣ ሳያዩ የሚያምኑ የተባረኩ ናቸው» አለው። 30 ኢየሱስም በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፉ ብዙ ምልክቶችን በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ፤ 31 ነገር ግን ይህ የተጻፈው፣ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ እንድታምኑና አምናችሁም በስሙ ሕይወት እንድታገኙ ነው።
ኢየሱስ ከተቀበረ በኋላ በሦስተኛው ቀን ይህ ነው።
እሁድ
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “አንድ ሰው ድንጋዩን አንከባለለለ አየች” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ ሐረግ ዮሐንስ በመጽሐፉ ሁሉ ውስጥ ስለራሱ የሚናገርበት መንገድ ይመስላል ፡፡ እዚህ ላይ “ፍቅር” የሚለው ቃል ለወዳጅ ወይም ለቤተሰብ አባል የሆነውን የወንድማማች ፍቅር ወይም ፍቅር ያሳያል ፡፡
መግደላዊት ማርያም አንድ ሰው የጌታን ሥጋ ሰረቀ ብላ ታስባለች። አት: - “አንድ ሰው የጌታን ሥጋ ከመቃብር አውጥቶታል” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ዮሐንስ ስሙን ከማካተት ይልቅ ራሱን እዚህ “ሌላኛው ደቀመዝሙር” ብሎ በመጥራት ትህትናውን ያሳያል
ዮሐንስ ደቀ መዛሙርቱ ወደ መቃብሩ እንደሚሄዱ ዮሐንስ አመልክቷል ፡፡ አት: - “ወደ መቃብሩ ወጣ” (UDB) (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
እነዚህ ሰዎች የኢየሱስን አስከሬን ለመጠቅለል የሚጠቀሙባቸው የመቃብር ጨርቆች ነበሩ።
እነዚህ ሰዎች የኢየሱስን አስከሬን ለመጠቅለል የሚጠቀሙባቸው የመቃብር ጨርቆች ነበሩ። በ 20 3 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
እዚህ “ራሱ” የሚያመለክተው “የኢየሱስን ራስ” ነው። ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “አንድ ሰው የኢየሱስን ፊት የሚሸፍነው ጨርቅ” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ግን አንድ ሰው ከታጠቀው በፍታ ጨርቆቹ ላይ አነጥፈው ከዚያ አውጥተውትታል” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ዮሐንስ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ስሙን ከማካተት ይልቅ እራሱን “ሌላኛው ደቀመዝሙር” ብሎ በመጥራት ትህትናውን ገል expressል ፡፡
መቃብሩ ባዶ እንደ ሆነ ባየ ጊዜ ኢየሱስ ከሙታን መነሳቱን ያምናል ፡፡ በዚህ ጊዜ “እነዚህን ነገሮች አይቶ ኢየሱስ ከሙታን መነሳቱን ማመን ጀመረ” (ዩ.አር.ቢ.)
እዚህ “እነሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስ እንደገና ይነሳል የሚለውን የቅዱሳት መጻሕፍቱን ያልተገነዘቡ ደቀመዛሙርትን ነው ፡፡ አት: - - “አሁንም ደቀ መዛሙርቱ መጽሐፍ ቅዱስን አልተረዱም” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
ኢየሱስ ከሞት መነሳት አለበት አለ
ደቀመዛሙርቱ በኢየሩሳሌም መኖራቸውን ቀጠሉ ፡፡ አት: - “በኢየሩሳሌም ወደሚኖሩበት ተመልሰዋል” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
መላእክቱ ነጭ ልብስ ለብሰው ነበር ፡፡ አት: - “ሁለት መላእክት ነጭ ልብስ ለብሰው አየች” (UDB) (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
“ጠየቋት”
“የጌታዬን ሥጋ ወስደዋል”
"የት እንዳስቀመጡ አላውቅም"
ኢየሱስም ጠየቃት።
እዚህ “እሱ” የሚለው ቃል ኢየሱስን ያመለክታል ፡፡ አት: - “የኢየሱስን አስከሬን ከወሰዱ” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
የት እንዳስቀመጥክ ንገረኝ ”
መግደላዊት ማርያም የኢየሱስን አስከሬን ልትወስድና እንደገና ልትቀበር ትፈልጋለች ፡፡ አት: - እናም አስከሬን አገኛለሁ እንደገና እቀብራለሁ (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
“ራቢኒ” የሚለው ቃል ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱ የተናገሩበት ቋንቋ ረቢዎች ወይም መምህር በአረማይክ ቋንቋ ማለት ነው ፡፡
ኢየሱስ “ወንድሞች” የሚለውን ቃል ደቀመዛሙርቱን ለማመልከት ተጠቀመ ፡፡
ኢየሱስ ከሙታን ተነስቶ ወደ እግዚአብሔር ወደ አባቱ ወደ ሰማይ እንደሚሄድ ተንብዮ ነበር ፡፡ አትቲን: - “እኔ ከአባቴና ከአባትህ ፣ አምላኬና አምላካችሁ ወደ ሆነኝ ወደ ሰማይ እመለሳለሁ (ኦ.ሲ.ቢ. ይመልከቱ)
እነዚህ በኢየሱስ እና በእግዚአብሔር ፣ እንዲሁም በአማኞች እና በእግዚአብሔር መካከል ያለውን ግንኙነት የሚገልፁ አስፈላጊ አርዕስት ናቸው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
መግደላዊት ማርያም ደቀ መዛሙርቱ ወደሚኖሩበት ቦታ ሄደች ያየችውንና የሰማችውን ነገር ነገረቻቸው ፡፡ በዚህ ጊዜ-መግደላዊት ማርያም ደቀመዛሙርቱ ወደነበሩበት ሄዳ ትነግራቸው ነበር (ይመልከቱ ፡፡
ጊዜው አሁን ምሽት ሲሆን ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ተገለጠላቸው።
ይህ እሑድን ያመለክታል።
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “ደቀመዛሙርቱ ያሉበትን በሮች ዘግተው ነበር” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
እዚህ “አይሁዶች” ደቀመዛሙርቱን ሊይዝ ለሚችል የአይሁድ መሪዎች ምሳሌ ነው ፡፡ AT: - “የአይሁድ መሪዎች ይያ mightቸው ዘንድ ፈርተው ነበር” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ይህ ‹እግዚአብሔር ሰላም ይሰጣችኋል› ማለት ነው ፡፡
ኢየሱስ ቁስሎቹን ለደቀ መዛሙርቱ አሳያቸው ፡፡ አት: - በእጁና ከጎኑ ያሉትን ቁስሎች አሳየባቸው
ይህ ‹እግዚአብሔር ሰላም ይሰጣችኋል› ማለት ነው ፡፡
እግዚአብሔር አብ እግዚአብሔር አማኞችን አሁን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል አማኞችን የሚልክ ልጁን እግዚአብሔር ልኮታል ፡፡
ይህ ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “እግዚአብሔር ይቅር ይላል” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
"የሌላውን ኃጢአት ይቅር ካላለዎት" (ዩ.አር.ቢ.)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “እግዚአብሔር ይቅር አይላቸውም” (የበለስ_ቁጥርን ይመልከቱ)
ይህ ወንድ ‹ስም› ማለት ‹መንትዮች› ማለት ነው ፡፡ ይህ ስም በ 11 15 ውስጥ እንዴት እንደተተረጎመ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: መተርጎም_ቁጥር)
“እሱ” የሚለው ቃል ቶማስን ያመለክታል ፡፡
ይህንን ድርብ አሉታዊ በአዎንታዊ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “አምናለሁ… የእርሱን ጎን ካየሁ ብቻ” አምናለሁ (የበለስ_ቁጥር ችግሮች)
“የእርሱ” የሚለው ቃል ኢየሱስን ያመለክታል ፡፡
“የእርሱ” የሚለው ቃል ኢየሱስን ያመለክታል ፡፡
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - "በሮቹን በቆለፉ ጊዜ" (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ ‹እግዚአብሔር ሰላም ይሰጣችኋል› ማለት ነው ፡፡
“ያለ እምነት” ወይም “ያለ እምነት”
እዚህ “ማመን” ማለት በኢየሱስ ማመን ማለት ነው ፡፡ አት: - "በእኔ ታመኑ" (UDB) (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ቶማስ ኢየሱስ ስላየው ስላየ ህያው ነው ብሎ ያምናል ፡፡ አት: - “በሕይወት መኖሬ ታምናላችሁ” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
ይህ ማለት “እግዚአብሔር ለእነዚያ ታላቅ ደስታን ይሰጣል” (ዩ.ቢ.ቢ.) ፡፡
ይህ ማለት ኢየሱስን ያላዩ ናቸው ፡፡ አት: - "በህይወቴ ያላየኝ" (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
ታሪኩ ወደ መጨረሻው እየተቃረበ ሲመጣ ደራሲው ኢየሱስ ስላከናወናቸው በርካታ ነገሮች አስተያየት ሰጡ ፡፡ (ይመልከቱ: Writ_endofstory)
የሚለው ቃል እግዚአብሔር በአጽናፈ ዓለም ሁሉ ላይ ሙሉ ኃይል ያለው መሆኑን የሚያሳዩ ተዓምራቶችን ይመለከታል ፡፡
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “ደራሲው በዚህ መጽሐፍ ላይ የፃፋቸው ምልክቶች” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - "ደራሲው ግን ስለ እነዚህ ምልክቶች ጽ "ል" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
እዚህ “ሕይወት” ማለት ኢየሱስ ሕይወትን ይሰጣል ማለት ነው ፡፡ አት: - “ከኢየሱስ የተነሳ ሕይወት ሊኖርህ ይችላል” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ.
ይህ መንፈሳዊ ሕይወትን ያመለክታል ፡፡
1 እነዚህ ነገሮች ከተፈጸሙ በኋላ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንደ ገና በጥብርያዶስ ባሕር አጠገብ ተገለጠላቸው፤ ሁኔታውም እንደዚህ ነበር፦ 2 ስምዖን ጴጥሮስ ዲዲሞስ ከተባለው ከቶማስ፣ ከገሊላ አውራጃ ከቃና መንደር ከሆነው ከናትናኤል፣ ከዘብዴዎስ ልጆችና ከሌሎች ሁለት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ጋር ዐብረው ነበሩ። 3 ስምዖን ጴጥሮስ፣ «ዓሣ ለማጥመድ መሄዴ ነው» አላቸው። እነርሱም፣ «እኛም ከአንተ ጋር እንሄዳለን» አሉት። በጀልባ ተሳፍረው ሄዱ፤ ነገር ግን በዚያች ሌሊት ምንም ዐሣ አላጠመዱም። 4 ቀኑ እየነጋ ሳለ ኢየሱስ መጥቶ በባሕሩ ዳር ቆመ፤ እነርሱ ግን ኢየሱስ እንደ ሆነ አላወቁም ነበር። 5 ከዚያም ኢየሱስ «ልጆች ሆይ፣ የሚበላ ዐሣ አላችሁን?» አላቸው። «የለንም» ብለው መለሱለት። 6 ኢየሱስ፣ «መረባችሁን ከጀልባው በቀኝ በኩል ጣሉት ታገኙማላችሁ» አላቸው። እነርሱም እንደተባሉት መረባቸውን ጣሉ፤ ነገር ግን ከዐሣው ብዛት የተነሣ መረቡን ወደ ጀልባው ውስጥ መጐተት አቃታቸው። 7 ከዚያም ኢየሱስ ይወደው የነበረው ደቀ መዝሙር ስምዖን ጴጥሮስን፣ «ጌታ እኮ ነው» አለው። ጴጥሮስ ጌታ እኮ ነው የሚለውን ቃል በሰማ ጊዜ፣ መደረቢያውን ልብስ ታጥቆ ወደ ውሃው ውስጥ ዘሎ ገባ። 8 ሌሎቹ ደቀ መዛሙርት ግን ከምድር የነበራቸው ርቀት ሁለት መቶ ክንድ ያህል ብቻ ስለ ነበር ዐሣ የሞላውን መረብ እየጐተቱ በጀልባ ወደ ዳር መጡ። 9 ወደ መሬትም በደረሱ ጊዜ፣ በላዩ ላይ ዐሣ የተቀመጠበት ፍምና እንጀራ ተዘጋጅቶ አዩ። 10 ኢየሱስ፣ «እስኪ ካጠመዳችሁት ዐሣ ጥቂት ወደዚህ አምጡ» አላቸው። 11 ስምዖን ጴጥሮስም ሄዶ 153 ዐሣ የሞላውን መረብ ወደ ምድር ጐተተ፤ ምንም እንኳ የዐሣው ብዛት ከፍተኛ ቢሆንም፣ መረቡ ግን አልተቀደደም ነበር። 12 ኢየሱስ፣ «ኑ ቍርስ ብሉ» አላቸው። ኢየሱስ እንደ ሆነ አውቀው ነበርና ከደቀ መዛሙርቱ ማንም፣ «አንተ ማነህ?» ብሎ ሊጠይቀው የደፈረ አልነበረም። 13 ኢየሱስ እንጀራውን አንሥቶ ሰጣቸው፤ ዐሣውንም እንደዚያው አደረገ። 14 ከሞት ከተነሣ በኋላ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ሲገለጥላቸው ይህ ለሦስተኛ ጊዜ ነበር። 15 ቍርስ ከበሉ በኋላ፣ ኢየሱስ ስምዖን ጴጥሮስን፣ «የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፣ ከእነዚህ የበለጠ ትወደኛለህን?» አለው። ጴጥሮስ፣ «አዎን፣ ጌታ ሆይ፣ እንደምወድህማ አንተም ታውቃለህ» አለው። ኢየሱ፣ «ጠቦቶቼን መግብ» አለው። 16 እንደ ገና ለሁለተኛ ጊዜ፣ «የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ ትወደኛለህን?» አለው። ጴጥሮስ፣ «አዎን፣ ጌታ ሆይ፣ እንደምወድህማ አንተም ታውቃለህ» አለው። ኢየሱስ፣ «በጎቼን ጠብቅ» አለው። 17 ለሦስተኛ ጊዜ፣ «የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፣ ትወደኛለህ?» አለው። ለሦስተኛ ጊዜ «ትወደኛለህ ወይ?» ብሎ ስለ ጠየቀው ጴጥሮስ በጣም ዐዘነ። ቀጥሎም፣ «ጌታ ሆይ፣ አንተ ሁሉን ታውቃለህ፤ እንደምወድህም ታውቃለህ» አለው። ኢየሱስም «በጎቼን መግብ። 18 እውነት፣ እውነት እልሃለሁ፣ ወጣት እያለህ ልብስህን ራስህ ለብሰህ ወደምትፈልገው ቦታ ትሄድ ነበር፤ ስታረጅ ግን ሌላ ሰው ልብስህን አልብሶህ ወደማትፈልገው ቦታ ይወስድሃል፣ በዚያን ጊዜ አንተ እጅህን ከመዘርጋት ውጪ ሌላ ማድረግ የምትችለው ነገር አይኖርም» አለው። 19 ኢየሱስ ይህን የተናገረው ጴጥሮስ በምን ዓይነት አሟሟት እግዚአብሔርን እንደሚያከብር ለማመልከት ነው። ከዚያም ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ «ተከተለኝ» አለው። 20 ጴጥሮስም ዞር ብሎ በፋሲካ እራት ላይ እያሉ ወደ ኢየሱስ ደረት ጠጋ ብሎ፣ «አሳልፎ የሚስጥህ ማን ነው?» ብሎ የጠየቀውንና ኢየሱስ ይወደው የነበረውን ደቀ መዝሙር ሲከተላቸው አየው። 21 ጴጥሮስ ኢየሱስን፣ «ጌታ ሆይ፣ ይህ ሰውስ ምን ይሆናል?» አለው። 22 ኢየሱስ፣ «እኔ እስክመጣ እንዲቆይ ብፈልግስ አንተን ምን ይመለከትሃል? ዝም ብለህ ተከተለኝ» አለው። 23 በዚህ ምክንያት «ያ ደቀ መዝሙር አይሞትም» የሚል ወሬ በየ ስፍራው ተሠራጨ። ኢየሱስ ግን ለጴጥሮስ፣ «እኔ እስክመጣ እንዲቆይ ብፈልግስ አንተን ምን ይመለከትሃል?» አለው እንጂ ያ ደቀ መዝሙር አይሞትም አላለውም። 24 ስለ እነዚህ ነገሮች የመሰከረውና የጻፈው ይህ ደቀ መዝሙር ነው፣ ምስክርነቱም እውነት እንደ ሆነ እናውቃለን። 25 ከእነዚህ ሌላ ኢየሱስ ያደረጋቸው ብዙ ነገሮች አሉ። እያንዳንዱ ነገር ቢጻፍ ኖሮ ለሚጻፉት መጻሕፍት ማስቀመጫ ዓለም እንኳ የሚበቃ አይመስለኝም።
ኢየሱስ በጥብርያያስ ባሕር አጠገብ ለደቀ መዛሙርቱ እንደገና ተገለጠ ፡፡ ቁጥር 2 እና 3 ኢየሱስ ከመገለጡ በፊት በታሪኩ ውስጥ ምን እንደ ሆነ ይነግሩናል ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
"ከተወሰነ ጊዜ በኋላ"
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “ዲዲሞስ ብለን ከጠራነው ቶማስ ጋር (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ይህ ወንድ ‹ስም› ማለት ‹መንትዮች› ማለት ነው ፡፡ ይህ ስም በ 11 15 ውስጥ እንዴት እንደተተረጎመ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: መተርጎም_ቁጥር)
ይህ ‹ውድ ጓደኞቼ› ማለት የፍቅር መግለጫ ነው ፡፡
እዚህ “የተወሰኑት” ዓሦችን ያመለክታል ፡፡ አት: - “መረብህ ውስጥ አንዳንድ ዓሳ ትይዛለህ” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
መረቡን ጎትት "
ይህ ፍቅር ከእግዚአብሄር የሚመጣ እና ለሌሎች ጥቅም ላይ ያተኮረ ፍቅር ነው ፣ ምንም እንኳን በእራሱ የማይጠቅም ቢሆንም። ምንም ይሁን ምን እንዲህ ዓይነቱ ፍቅር ለሌሎች ይንከባከባል ፡፡
ጴጥሮስም ወደ ውሃው ዘልሎ ወደ ባሕሩ ዳርቻ ገባ ፡፡ አት: - “ወደ ባሕሩ ውስጥ ዘለለ ፤ እስከ ባሕሩ ዳርቻ ድረስ ጠመጠመ” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ይህ ፈሊጥ ነው ጴጥሮስ ማለት በፍጥነት ወደ ውሃው ውስጥ ዘለለ ማለት ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ ቪዲዮም)
ይህ የዳራ መረጃ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
"90 ሜትር." አንድ ክንድ ከግማሽ ሜትር ያነሰ ነበር ፡፡ (ይመልከቱ: translation_bdistance)
እዚህ “ወጣ” ማለት ስም Simonን ጴጥሮስ ወደ ጀልባው መመለስ ነበረበት ፡፡ አት: - "ስም Simonን ጴጥሮስ ወደ ጀልባው ተመለሰ" (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
መረቡን ወደ ባሕሩ ዳርቻ ጎትተው ”
ይህንን እንደ ገባሪ ቅጽ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “መረቡ አልተሰበረም” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ጠዋት ላይ ምግብ
ይህንን የስምምነት ቃል “ሶስተኛ” ን እንደ “የጊዜ ቁጥር 3” መተርጎም ይችላሉ ፡፡ (ይመልከቱ: ተርጉም_ordinal)
ኢየሱስ ከስም Simonን ጴጥሮስ ጋር ውይይት ይጀምራል ፡፡
እዚህ ላይ “ፍቅር” ሌሎችን የሚጠቅመው እንኳን ባይሆንም በሌሎች መልካም ላይ የሚያተኩር ከእግዚአብሔር የሚመጣውን የፍቅር ዓይነት ነው ፡፡
ጴጥሮስ መልስ ሲሰጥ ፣ “ፍቅር” የሚለውን ቃል የሚጠቀመው የወንድማማችነት ፍቅርን ወይም ለጓደኛ ወይም ለቤተሰብ አባል ፍቅርን ነው ፡፡
እዚህ “ጠቦቶች” ኢየሱስን ለሚወዱ እና ለሚከተሉት ሰዎች ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - "እኔ የምወዳቸውን ሰዎች መመገብ" (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
እዚህ “በጎች” ኢየሱስን ለሚወዱ እና ለሚከተሉት ሰዎች ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - "እኔ ለምከባከባቸው ሰዎች ይንከባከቡ" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
“እሱ” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው ፡፡ እዚህ “ሶስተኛ ጊዜ” ማለት “የጊዜ ቁጥር 3” ማለት ነው ፡፡ አት: - “ኢየሱስ ለሦስተኛ ጊዜ።” (ተመልከት: መተርጎም
በዚህ ጊዜ ኢየሱስ ይህንን ጥያቄ በጠየቀ ጊዜ “ፍቅርን” ለሚለው ቃል የሚያመለክተው የወንድማማች ፍቅርን ወይም ለጓደኛ ወይም ለቤተሰብ አባል ፍቅርን ለመግለጽ ነው ፡፡
የእኔን በጎቼን መመገብ የኢየሱስን የሚወክሉ እና እሱን የሚከተሉ ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - "እኔ ለመንከባከባቸው ሰዎች እንክብካቤ" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር) ክፍል
በ 1 48 ውስጥ እንዳደረገው ይህንን ይተረጉሙ ፡፡
ታሪኩን ከመቀጠል በፊት ዮሐንስ ዳራውን መረጃ እየሰጠ መሆኑን ለማሳየት ይህንን ቃል ይጠቀማል ፡፡ (ይመልከቱ: የአፃፃፍ_ኋላ)
እዚህ ላይ ዮሐንስ የሚያመለክተው ጴጥሮስ በመስቀል ላይ እንደሚሞት ነው ፡፡ አት-“ጴጥሮስ እግዚአብሔርን ለማክበር በመስቀል ላይ መሞቱን ለማመልከት” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
እዚህ “ተከተል” የሚለው ቃል “ደቀ መዝሙር መሆን” ማለት ነው ፡፡ አት: - “የእኔ ደቀ መዝሙር መሆንህን ቀጥል” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
ዮሐንስ ስሙን ከመጥቀስ ይልቅ ራሱን በመጽሐፉ ውስጥ ሁሉ በዚህ መንገድ ይጠቅሳል ፡፡
ይህ ዓይነቱ ፍቅር ከእግዚአብሔር የሚመጣ እና ሁል ጊዜም የሌሎችን መልካም ነገር የሚሻ ቢሆንም ፣ በራሱ የማይጠቅም ቢሆንም ፡፡ ምንም እንኳን ምንም ቢያደርጉ ይህ ዓይነቱ ፍቅር ለሌሎች ይንከባከባል ፡፡
ይህ ለመጨረሻው እራት ማጣቀሻ ነው ፡፡ (ተመልከት: 13: 1)
እዚህ “እሱ” የሚያመለክተው “ኢየሱስ ይወደው የነበረውን ደቀመዝሙር” ነው ፡፡
ጴጥሮስ በዮሐንስ ላይ የሚሆነውን ማወቅ ፈለገ ፡፡ AT: - “ጌታ ሆይ ፣ ይህ ሰው ምን ይሆናል?” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
"ኢየሱስም ጴጥሮስን"
እዚህ “እሱ” የሚያመለክተው በ 21 20 ውስጥ ‹ኢየሱስ የወደደውን ደቀመዝሙር› ነው ፡፡
ይህ የሚያመለክተው የኢየሱስን ዳግም ምጽዓት ፣ ከሰማይ ወደ ምድር መመለሱን ነው ፡፡
ይህ አስተያየት መለስተኛ ገጸ-ባህሪን ለመግለጽ በጥያቄ መልክ ይታያል። አት: - ያ ያንተ ጉዳይ አይደለም (UDB) ወይም “ስለዚህ ጉዳይ አትጨነቅ” (ተመልከት: የበለስ_ቁጥር)
እዚህ “ወንድሞች” ሁሉንም የኢየሱስ ተከታዮች የሚያመለክቱ ናቸው ፡፡
ይህ የዮሐንስ ወንጌል መጨረሻ ነው ፡፡ እዚህ ደራሲው ሐዋርያው ዮሐንስ ስለራሱ እና በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ስለ ጻፈው ለመዝጋት አስተያየት ይሰጣል ፡፡ (ይመልከቱ: Writ_endofstory)
“ደቀ መዝሙሩ ዮሐንስ”
እዚህ “መሰከረ” ማለት እሱ ራሱ የሆነ ነገር ያያል ማለት ነው ፡፡ አት: - “እነዚህን ሁሉ ያየ ማን ነው” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
እዚህ “እኛ” የሚያመለክተው በኢየሱስ የሚያምኑትን ነው ፡፡ አት: - "እኛ በኢየሱስ የምናምነው እናውቃለን" (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “አንድ ሰው ሁሉንም ቢጽፍላቸው” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ሰዎች ኢየሱስ በብዙ መጽሐፍት ከሚጽፉት የበለጠ ብዙ ተአምራትን ሠራ ፡፡ እዚህ ላይ ዮሐንስ የተጋነነ መጠቀምን ለማጉላት ጥቅም ላይ ውሏል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ፀሐይ መከላከያ) ld ራሱ መጽሐፎቹን መያዝ አልቻለም
ይህንን በገባ መልኩ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “ሰዎች ስላደረጋቸው ነገሮች ሊጽ thatቸው የሚችሏቸው መጽሐፍት”
1 ቴዎፍሎስ ሆይ፣ ኢየሱስ እስካረገበት ቀን ድረስ ለማድረግና ለማስተማር የጀመረውን ሁሉ የሚናገረውን የመጀመሪያውን መጽሐፍ ጻፍሁ፤ 2 ይህም የሆነው ጌታ ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት እርሱ የመረጣቸውን ሐዋርያትን ካዘዛቸው በኋላ ነበር፤ 3 ለምርጦቹ ከመከራው በኋላ ሕያው ሆኖ ተገልጦላቸዋል። አርባ ቀን እየታያቸው፣ ስለ እግዚአብሔር መንግሥትም እየተናገረ ቆየ። 4 ከእነርሱም ጋር ዐብሮ ሳለ ከኢየሩሳሌም እንዳይወጡ አዘዛቸው፤ ነገር ግን "ከእኔ የሰማችሁትን አብ የሰጠውን ተስፋ ጠብቁ፤ 5 በእርግጥ ዮሐንስ በውሃ አጥምቆ ነበር፤ እናንተ ግን በጥቂት ቀናት ውስጥ በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ" አለ። 6 ሐዋርያት በአንድነት ተሰብስበው ሳለ፣ “ጌታ ሆይ፣ ይህ የእስራኤልን መንግሥት የምትመልስበት ጊዜ ነውን?” ብለው ጠየቁት። 7 እርሱም እንደዚህ አላቸው፤ “አብ በገዛ ሥልጣኑ የወሰነውን ጊዜ ወይም ወቅት ማወቅ እናንተን አይመለከትም። 8 ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ ሲመጣ፣ ኀይልን ትቀበላላችሁ፤ በኢየሩሳሌምና በይሁዳ ሁሉ፣ በሰማርያና እስከ ምድር ዳርቻ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ።” 9 ጌታ ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች ከተናገረ በኋላ፣ ሐዋርያቱ እያዩት ወደ ላይ ዐረገ፤ ደመናም ከዐይናቸው ሰወረው። 10 ትኵር አድርገው ወደ ሰማይ እየተመለከቱ ሳለ፣ ድንገት ነጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች በአጠገባቸው ቆሙ። 11 እነርሱም፣ “እናንተ የገሊላ ሰዎች፣ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ለምን እዚህ ትቆማላችሁ? ወደ ሰማይ የወጣው ይህ ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ ባያችሁበት ሁኔታ ተመልሶ ይመጣል” አሏቸው። 12 ከዚያም በኋላ፣ የሰንበት ቀን ጕዞ ያህል ከሚያስሄደው፣ በኢየሩሳሌም አቅራቢያ ካለው ከደብረ ዘይት ተራራ ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሰው ሄዱ። 13 ሐዋርያት እዚያ ሲደርሱ፣ ወደሚቈዩበት፣ ወደ ላይኛው ሰገነት ወጡ። እነርሱም ጴጥሮስ፣ ዮሐንስ፣ ያዕቆብ፣ እንድርያስ፣ ፊልጶስ፣ ቶማስ፣ በርተሎሜዎስ፣ ማቴዎስ፣ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብ፣ ቀናተኛው ስምዖንና የያዕቆብ ልጅ ይሁዳ ነበሩ። 14 ሁሉም በአንድነት ሆነው፣ ሴቶቹ፣ የኢየሱስ እናት ማርያምና ወንድሞቹም ጭምር በጸሎት ይተጉ ነበር። 15 በዚያ ጊዜ ጴጥሮስ 120 ያህል በሚሆኑት ወንድሞች መካከል ቆመ፤ እንደዚህም አለ፤ 16 “ወንድሞች ሆይ፣ ኢየሱስን የያዙትንና መርቶ ያመጣውን ይሁዳን በሚመለከት መንፈስ ቅዱስ አስቀድሞ በዳዊት አፍ የተናገረው የመጽሐፍ ቃል ይፈጸም ዘንድ አስፈላጊ ነበር። 17 ይሁዳ ከእኛ እንደ አንዱ ተቈጥሮና የዚህን አገልግሎት ድርሻም ተቀብሎ ነበርና። 18 “ይሁዳም ለክፉ ሥራው በተከፈለው ዋጋ መሬት ገዛ። ከዚያም በግንባሩ ተደፋ፤ አካሉ ተሰነጠቀ፤ አንጀቱም ተዘረገፈ። 19 በኢየሩሳሌም ለሚኖሩ ሁሉ መሬቱ በቋንቋቸው አኬልዳማ [የደም መሬት] ተብሎ እንደሚጠራ ታወቀ። 20 በመዝሙር መጽሐፍ፦ መኖሪያው ወና ይሁን፤ የሚኖርበት አንድ ሰውም እንኳ አይገኝ፤ ሹመቱንም ሌላ ሰው ይውሰደው፤ ተብሎ ተጽፎአልና። 21 ስለዚህ ጌታ ኢየሱስ በመካከላችን በገባበትና በወጣበት ጊዜ ሁሉ ዐብረውን ከቈዩ ሰዎች፣ 22 ይኸውም ዮሐንስ ካጠመቀው ጥምቀት ጀምሮ ኢየሱስ ከእኛ እስካረገበት ቀን ድረስ፣ ከነበሩት ከእነዚህ አንዱ ከእኛ ጋር የትንሣኤው ምስክር ሊሆን ይገባል።” 23 ኢዮስጦስም የሚባለውን፣ በርስያን ተብሎ የሚጠራውን ዮሴፍንና ማትያስን፣ ሁለት ሰዎችን እንዲቀርቡ አደረጉ። 24 እንደዚህ ብለውም ጸለዩ፤ “ጌታ ሆይ፣ የሰዎችን ሁሉ ልብ አንተ ታውቃለህ፤ ስለዚህ ከእነዚህ ከሁለቱ የትኛውን እንደ መረጥኸው ግለጥ፤ 25 ይኸውም ይሁዳ ወደገዛ ስፍራው ትቶት በሄደው በዚህ አገልግሎትና ሐዋርያነት ውስጥ ስፍራ እንዲያገኝ ነው።” 26 ሐዋርያት ዕጣዎችን ለእነርሱ ጣሉ፤ ዕጣውም ለማትያስ ወደቀ፤ እርሱም ከዐሥራ አንዱ ሐዋርያት ጋር አንድ ሆኖ ተቈጠረ።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ሉቃስ ለቴዎፍሎስ ይህንን መጽሐፍ መጻፍ ለምን እንዳስፈለገው ያብራራል፡፡ ከዚህ መጽሐፍ በፊት በጻፈው መጽሐፉ ከዚህ መጽሐፍ በፊት የጻፈው መጽሐፍ የሉቃስ ወንጌልን ነው፡፡ ቴፍሎስ ሉቃስ ይህንን መጽሐፍ የጻፈው ቴዎፍሎስ ተብሎ ለሚጠራ ሰው ነው፡፡ አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች በባሕላቸው ደብዳቤ በሚጻፍበት ወቅት መግቢያው ላይ የሚጻፈውን ነገር በመከተል “ውድ ቴዎፍሎስ ሆሕ” በማለት ተርጉመውታል፡፡ ቴዎፍሎስ ማለት “የእግዚአብሔር ወዳጅ” ማለት ነው፡፡ እስከ አረገበት ቀን ድረስ ያለውን ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ያረገበት ወቅት ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት የሰጠውን ትዕዛዝ መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ በተወሰኑ ነገሮች ዙሪያ የተለያዩ መመሪያዎችን በመስጠት ሂደት ውስጥ መሪቶታል፡፡ ከመከራው በኋላ ይህ ኢየሱስ የተቀበለውን መከራን እና በመስቀል ላይ የሞተውን ሞት ያመለክታል፡፡ ሕያው ሆኖ እንደገና ለእነርሱ ታያቸው ኢየሱስ ከመጀመሪያዎቹ ዐሥራ ሁለት ደቀ መዛሙርት በተጨማሪ ለብዙ ሰዎች ከሞት ከተነሣ በኋላ ታይቷቸዋል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ይህ ሁኔታ የተፈጸመው ኢየሱስ ከሞት ከተነሣ በኋላ ለዐርባ ቀናት ለደቀ መዛሙርቱ በተያየበት ጊዜያት ነው፡፡ . . . ሳለ "እርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስ ነው፡፡ ከእነርሱ ጋር "እነርሱ" የሚያመለክተው ዐሥራ አንዱ ሐዋርያት ነው፡፡ የአባትን የተስፋ ቃል ይህ መንፈስ ቅዱስን የሚያመለክት ቃል ነው፡፡ በውሃ ያጠምቃችኋል . . . በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ ኢየሱስ መጠምቁ ዮሐንስ በውሃ ያጠመቀበት መንገድ እግዚብሔር በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ከሚጠምቅበት መንገድ ጋር ያነጻጽራል፡፡ መጥመቁ ዮሐንስ በእርግጥ በውሃ አጥምቋል "ዮሐንስ በእርግጥ ሰዎችን በውሃ አጥምቋል" ትጠመቃላችሁ አመራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር ያጠምቃችኋል"
ለእስራኤል መንግስትን የሚትመልስበት ወራት ይህ ነውን "እስራኤልን እንደገና ጠንካራ ሀገር የሚታደርግበት ጊዜ አሁን ነውን?" ጊዜው ወይም ዘመኑን "ጊዜውን ወይም ቀናቱን" ኃይል ትቀበላላችሁ "በመነንፈሳዊነት ትጠነክራላችሁ" እናም ምስክሮቼ ትሆናላችሁ አማራጭ ትርጉም፡ “የእኔ ምስክሮች ትሆኑ ዘንድ" እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ "በዓለም ዙሪያ" ወይም "እስከ ምድር ጥግ ድረስ"
እየተመለከቱት ሳለ "ሐዋርያቱ ወደ ሰማይ እየተመለከቱ ሳለ" ዳመናው ከዐይናቸው ጋረደው "ወደ ሰማይ አረገ እና ዳመናውም ከዐይናቸው ጋረደው ስለዚህም ከሊያዩት አልቻሉም" ወደ ሰማይ አተኩረው ሲያዩ ሳለ "ወደ ሰማይ እየተመለከቱ" ወይም “ሰማይ ሰማዩን ሲያዩ ሳለ” እናንተ የገሊላ ሰዎች ሆይ "እናንተ ሐዋርያት"
ከዚያም ተመለሱ "ሐዋርያቱ ተመለሱ" የሰንበት ጉዞ ያኸል ርቀት ይህ በፈርሳዊያን ደንብ መሰረት ሰዎች በሰንበት ማድረግ የተፈቀደላቸው ነገር ነበር፡፡ እዚያ በደረሱ ጊዜበ "በኢየሩሳሌም ውስጥ ወደሚገኘው ሊሄዱ ወደአሰቡት ስፍራ በደረሱ ጊዜ" ሰገነት "በቤት ውስጥ በከፍታ ላይ የሚገኝ ክፍል" ቀናተኛው ስምኦን "ለሀገሩ ይዋጋ የነበረው ስምኦን፡፡" ብዙ ቀናተኞች ነበሩ ነገር ግን ከእርሱ መካከል ሐዋርያ የሆነው ስምኦን ብቻ ነው፡፡ ቀናተኞች ሮማዊያን እስራኤልን መግዛት እንዲያቆሙ የሚታገሉ ሰዎች ናቸው፡፡ ሁልም በአንድ ልብ ሆነው ሳሉ ቡድኑ በአንድ ልብ ነበር፤ በመካከላቸው መከፋፍል አልነበረም፡፡ በትጋት እየጸለዩ ሳሉ "በአንድ ላይ ሆነው በትጋት ስጸልዩ ሳለ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ይህ ነገር ጴጥሮስ እና ሌሎች አማኞች በእንድነት በሰገነት ላይ ሳሉ የተፈጸመ ነገር ነው፡፡ በእነዚያ ቀን "ኢየሱስ ወደ ሰማይ ከተመለሰ በኋላ ባሉት እነዚያ ቀናት" በወንድሞች መካከል በዚህ ክፍል ውስጥ “ወንድሞች” የሚለው ቃል ብዙ ጊዜ የሚያመለክተው አማኞችን ሆኖ ወንዶችን እና ሴቶችን ያካትታል፡፡ በቅዱሳት መጻሕፍት የተነገረው ነገር ይፈጸም ዘንድ አስፈላጊ ነው ጴጥሮስ በዚህ ሥፍራ ላይ በተለይ ከይሁዳ ጋር ተያያዥነት ስላለውን ትንቢት እየተናገረ ነው፡፡ በዳዊት አፍ "የዳዊት ቃል፡፡" በዚህ ሥፍራ ላይ ጥቅም ላይ የዋለው “አፍ” የሚለው ቃል “ቃል” የሚያመልክት ሲሆን ዳዊት የተናገራቸውን ቃል ያመለክታል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስ በ ACT 1:16 ላይ ለአማኞች መናገር የጀመረውን ንግግር የቀጠለበት ክፍል ነው፡፡ አጠቃላይ መረጃ: በቁጥር 18-19 ውስጥ ይሁዳ ስላደረገው ነገር የኋላ ታሪክ የተሰጠበት እና እንዴት እንደሚተ የተገለጸበት ክፍል ነው፡፡ አሁን ይህ ሰው "አሁን ይሁዳ" ባደረገው ክፉ ነገር የተከፈለው ክፍያ በዚህ ክፍል “ክፍያ” የሚለው ነገር እና “ተግባር”፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ስላደረገው ክፉ ነገር የተከፈለው ክፍያ፡፡” በክፉ ተግባሩ "የኢየሱስን ጠላቶች ወደ እርሱ የመራበት ክፉ ተግባሩ፡፡" ይህ “ክፉ ተግባሩ” የሚለው ቃል በግልጽ ምንን እንደሚያመለክት ያሳያል፡፡
በግንባሩም ተደፍቶ ከመካከሉ ተሰነጠቀ አንጀቱም ሁሉ ተዘረገፈ፡፡ ሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎ ይሁዳ ራሱን አንቆ ሞተ ይላሉ፡፡ የደም መሬት . . . ተብሎ ይታወቅ ነበር፡፡ በሞት ምክንያት ሰዎች መሬቱን በአዲስ ስም ይጠሩት ጀምሯል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስ በ ACT 1:16 ላይ ለአማኞች መናገር የጀመረውን ንግግር የቀጠለበት ክፍል ነው፡፡ አጠቃላይ መረጃ: ከዚህ በፊት በተነገረው የይሁዳ ታሪክ መሠረት ጴጥሮስ ከመዝሙር መጽሐፍ ውስጥ ያልን ምንባብ በማስታወስ አሁን ላሉበት ሁኔታ ተስማሚ እንደሆነ አምኗል፡፡ ከብሉይ ኪዳን መጻሕፍት የተወሰደው ክፍል ማብቂያ ይህ ክፍል ነው፡፡ በመዝሙር መጽሐፍ ውስጥ እንዲህ ተብሎ ተጽፈዋል ጴጥሮስ ይህንን ሀረግ በመናገሩ ሰዎች ይህንን የተናገረው ከመዝሙር መጽሐፍ ላይ ወስዶ እንደሆነ ያውቃሉ፡፡ የመዝሙር መጽሐፍ ይህ መጽሐፍ የቅዱስ መጽሐፍ አንዱ ክፍል ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "የመዝሙር መጽሐፍ" ወይም "የመዝሙሮች መጽሐፍ፡፡" መሬቱ ወና እና ምድረ በዳ ከመሆኑ የተነሳ ሰዎች የመሬቱ ባለቤት ሞቷል ብለው ያስባሉ፡፡ እንዲሁም የሚኖርባት አይኑር መሬቱ የተረገመ ወይም ለሰዎች መኖሪያ የሚሆን አይሁን፡፡ የእርሱን የመሪነት ሥፍራ ሌላ ሰው ይውሰደው "በእርሱን የመሪነት ሥፍራ በሌላ ሰው ይተካ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስ በ ACT 1:16 ላይ ለአማኞች መናገር የጀመረውን ንግግር የቀጠለበት ክፍል ነው፡፡ ስለዚህ . . . አስፈላጊ ነው ጴጥሮስ ከመዝሙር መጽሐፍ የወሰደውን ክፍል ለምን በዚህ ሥፍራ መናገር እንዳለበት ማብራረቱን እንዳስፈለገው እና በዚህም መሠረት ምን ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ ከእኛ ጋር የነበረ . . . ለእርሱ ትንሳዔ ከእኛ ጋር ምስክር ሊሆን የሚችል ሰው ጴጥሮስ ይሁዳን እንደ ሐዋርያ ሊተካው የሚችለው ሰው ማሟላት የሚገባው መሥፈረት ምን እንደሆነ እየገለጸ ነው፡፡ ሁለት ሰዎችን ለምርጫ አቀረቡ ይሁዳን በሌላ ሰው ለመተካት በመሞከር ሂደታቸው ውስጥ ሁለት ለምርጫው ብቁ የሆኑ ሰዎችን አቀረቡ፡፡ ኢዮስጦስም የሚሉትን በርስያን የተባለውን ዮሴፍን ዮሴፍ በርስያን እና ኢዮስጦስ በተባሉ ሁለት ስሞች ይታወቃል፡፡
ጸለዩ "ከዚያም አማኞች ጸሎት አደረጉ" ጌታ ሆይ አንተ የሰዎችን ሁሉ ልብ ታውቃለህ "ጌታ ሆይ የሁሉንም ሰው የውስጥ መነሻ ምክንያን እና ሀሳብን ታውቃለህ" ይህንን አገልግሎት እና ሐዋርያነት እንዲተካ ከእነዚህ ሁለት ሰዎች መካከል ዬትኛውን አንተ እንደሚትመረጥ ግለጥልን "ስለዚህም ከሐዋርያቱ ጋር እንዲሆን ባዶ የሆነውን ቦታ እንዲተካ ከእነዚህ ሰዎች መካከል ማንን አንደመረጥክ እግዚአብሔር ሆይ አሳየን" ይሁዳ ወደ ገዛ ራሱ ስፍራ ይሄድ ዘንድ በተዋት ይሁዳ ኢየሱስን በመካዱ እና በበሞቱ ምክንያት ኃላፊነቱን ትቶ ሄዷል፡፡ ዕጣም ተጣጣሉላቸው፥ በዮሴፍ እና በማቴያስ መካከል ዕጣ ጣሉ ዕጣውም ለማትያስ ወደቀ የተጣለውም ዕጣ ማትያስ መመረጡን አመለከተ፡፡ ከአሥራ አንዱ ሐዋርያት ጋር ተቈጠረ። "ደቀ መዛሙርቱም እረሱን ከሐዋርያት መካከል እንዱ እንደሆነ ቆጠሩት"
1 በበዓለ ኀምሳ ቀን ሁሉም በአንድነት አንድ ስፍራ ላይ ነበሩ። 2 ድንገት እንደ ኀይለኛ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ከሰማይ መጣ፤ ተቀምጠውበት የነበረውን ቤትም ሞላው። 3 እንደ እሳት የተከፋፈሉ ልሳናት ታዩአቸው፤ በእያንዳንዳቸው ላይም ተቀመጡባቸው። 4 ሁሉም መንፈስ ቅዱስን ተሞሉ፤ መንፈስ ቅዱስ እንዲናገሩ እንደ ሰጣቸውም በሌሎች ቋንቋዎች መናገር ጀመሩ። 5 በዚያን ጊዜ ከሰማይ በታች ካለው ሕዝብ ሁሉ የመጡ፣ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች፣ በኢየሩሳሌም የሚኖሩ አይሁድ ነበሩ። 6 ይህ ድምፅ ሲሰማ፣ ብዙ ሕዝብ በአንድነት ተሰበሰበ፣ እያንዳንዱ ሰውም በገዛ ራሱ ቋንቋ ሲናገሩ በመስማቱ ግራ ተጋባ። 7 ሕዝቡ ተደነቁ፤ ተገረሙም፤ “እነዚህ የሚናገሩ ሰዎች ሁሉ በእውነት የገሊላ ሰዎች አይደሉምን? ብለውም ተናገሩ። 8 እያንዳንዳቸው በተወለድንበት ቋንቋ ሲናገሩ የምንሰማቸው ለምንድን ነው? 9 የጳርቴና፣ የሜድና የኢላሜጥ ሰዎች፣ በመስጴጦምያም፣ በይሁዳም፣ በቀጰዶቅያም፣ በጳንጦስም፣ በእስያም፣ 10 በፍርግያም፣ በጵንፍልያም፣ በግብፅም፣ በቀሬና በኩል በሚገኙት የሊቢያ ክፍሎች የምንኖርም፣ ከሮም የመጣን፣ 11 አይሁድና ወደ ይሁዲነት የገባን ቀርጤሳውያንና ዐረባውያን የሆንን እኛም፣ እነዚህ ሰዎች ስለ እግዚአብሔር ታላላቅ ሥራዎች በራሳችን ቋንቋዎች ሲናገሩ እንሰማቸዋለን።" 12 ሁሉም ተደነቁ፣ ግራ ተጋቡም፤ እርስ በርሳቸውም፣ “ይህ ነገር ምን ይሆን?” ተባባሉ። 13 ሌሎች ግን፣ “ዐዲስ ወይን ጠጅ ጠጥተው ጠግበው ነው” ብለውም በማፌዝ ተናገሩ። 14 ነገር ግን ጴጥሮስ ከዐሥራ አንዱ ጋር ቆሞ፣ ድምፁን ከፍ በማድረግ እንደዚህ አላቸው፤ “የይሁዳ ሰዎችና በኢየሩሳሌም የምትኖሩ ሁሉ፣ ይህ ለእናንተ የታወቀ ይሁን፤ የምናገረውንም አድምጡ። 15 እነዚህ ሰዎች እናንተ እንደምታስቡት አልሰከሩም፤ ምክንያቱም ገና ከቀኑ ሦስተኛ ሰዓት ነው። 16 ነገር ግን በነቢዩ በኢዩኤል ይህ ተነግሯል፦ 17 ‘በመጨረሻዎቹ ቀናት ይህ ይሆናል፣’ እግዚአብሔር እንደዚህ ይላል፤ ‘መንፈሴን ሥጋ በለበሱ ሁሉ ላይ አፈስሳለሁ፣ ወንዶች ልጆቻችሁና ሴቶች ልጆቻችሁ ትንቢት ይናገራሉ። ወጣቶቻችሁ ራእይ ያያሉ፤ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ። 18 በአገልጋዮቼና በሴት አገልጋዮቼ ላይም በእነዚያ ቀናት መንፈሴን አፈስሳለሁ፤ እነርሱም ትንቢት ይናገራሉ። 19 በላይ በሰማይ ድንቆችን፣ ምልክቶችንም በታች በምድር ላይ፣ ደምን፣ እሳትንና የጢስ ደመናን አሳያለሁ። 20 ታላቁና ገናናው የጌታ ቀን ከመምጣቱ በፊት፣ ፀሓይ ወደ ጨለማነት፣ ጨረቃም ወደ ደምነት ይለወጣሉ። 21 የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል።' 22 የእስራኤል ሰዎች ሆይ፣ እነዚህን ቃሎች ስሙ፦ ራሳችሁ እንደምታውቁት የናዝሬቱ ኢየሱስ፣ በመካከላችሁ እግዚአብሔር በእርሱ በኩል ባደረጋቸው ታላላቅ ተግባራት፣ በተኣምራትና በምልክቶች፣ ከእግዚአብሔር ለእናንተ መገለጡ የተረጋገጠ ሰው ነው። 23 አስቀድሞ በተወሰነው የእግዚአብሔር ዕቅድና በቀዳሚ ዕውቀቱ መሠረት፣ ዐልፎ ተሰጥቶአል፤ እናንተም በዐመፀኞች እጅ ሰቀላችሁት፤ ገደላችሁትም፤ 24 እግዚአብሔርም የሞትን ጣር ከእርሱ አጥፍቶ አስነሣው፤ ምክንያቱም ሞት እርሱን ይይዘው ዘንድ አልቻለም። 25 ዳዊት ስለ እርሱ እንዲህ ብሎ ይናገራልና፦ ‘ጌታን ሁልጊዜ በፊቴ አየሁት፤ በቀኜ ነውና አልናወጥም። 26 ስለዚህ ልቤ ተደሰተ፤ አንደበቴም ሐሤት አደረገ። ሥጋዬም በተስፋ ያድራል። 27 ነፍሴን በሲኦል አትተዋትም፤ ቅዱስህም መበስበስን እንዲያይ አትፈቅድም። 28 የሕይወትን መንገድ ገለጥህልኝ፤ በፊትህም ደስታን ታጠግበኛለህ።’ 29 ወንድሞች ሆይ፣ ስለ አባቶች አለቃ ስለ ዳዊት በግልጽ ልነግራችሁ እችላለሁ፤ እርሱ ሞቶአል፤ ተቀብሮአልም፤ መቃብሩም እስከ ዛሬ ድረስ በእኛ ዘንድ ነው። 30 ስለዚህ ዳዊት ነቢይ ነበረና ከዘሩ በዙፋኑ ላይ አንድን ሰው እንደሚያስቀምጥ እግዚአብሔር በመሐላ ለእርሱ ቃል ገብቶለት ነበር። 31 ዳዊት ይህን አስቀድሞ አየ፤ ስለ ክርስቶስ ትንሣኤም ተናገረ፦ ክርስቶስ በሲኦል አልቀረም፤ ሥጋውም መበስበስን አላየም። 32 ይህን ኢየሱስን እግዚአብሔር አስነሣው፤ ለዚህም እኛ ሁላችን ምስክሮች ነን። 33 ስለዚህ ከሙታን በመነሣትና በእግዚአብሔር ቀኝ በመቀመጥ፣ ከአብ ቃል የተገባውን መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ፣ እናንተ የምታዩትንና የምትሰሙትን ይህን አፈሰሰው። 34-35 ዳዊት ወደ ሰማይ አልወጣም፤ ነገር ግን እንዲህ ይላል፦ “ጌታ ለጌታዬ፣ ጠላቶችህን ለእግርህ መርገጫ እስከማደርጋቸው ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው።” 36 ስለዚህ፣ እናንተ የሰቀላችሁትን ይህን ኢየሱስን እግዚአብሔር ጌታም ክርስቶስም እንዳደረገው የእስራኤል ወገን ሁሉ በእርግጥ ይወቅ።" 37 ሕዝቡ ይህን ሲሰሙ ልባቸው ተነካና ለጴጥሮስና ለቀሩት ሐዋርያት፣ “ወንድሞች ሆይ፣ ምን እናድርግ?” አሉ። 38 ጴጥሮስም እንዲህ አላቸው፤ “ንስሓ ግቡ፤ እያንዳንዳችሁም ለኀጢአታችሁ ይቅርታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ መንፈስ ቅዱስንም በስጦታነት ትቀበላላችሁ። 39 የተስፋው ቃል ለእናንተና ለልጆቻችሁ፣ ጌታ አምላካችን ለሚጠራቸው ሩቅ ላሉት ሁሉም ነውና።” 40 ጴጥሮስ በሌሎች ብዙ ቃላት መሰከረ፤ “ከዚህ ክፉ ትውልድ ራሳችሁን አድኑ” በማለትም አስጠነቀቃቸው። 41 ከዚያም ሕዝቡ ቃሉን ተቀብለው ተጠመቁ፤ በዚያም ቀን ሦስት ሺሕ ያህል ሰዎች ተጨመሩ። 42 እነርሱም ሐዋርያት በሚያስተምሩት ትምህርትና በኅብረት፣ እንጀራውን በመቊረስና በጸሎትም ይተጉ ነበር። 43 በሰው ሁሉ ላይ ፍርሀት መጣ፤ ብዙ ድንቆችና ምልክቶችም በሐዋርያት እጅ ተደረጉ። 44 ያመኑት ሁሉ በአንድነት ነበሩ፤ ሁሉም ነገር የጋራ ነበር፤ 45 መሬታቸውንና ንብረታቸውን እየሸጡም ለሁሉም እንደሚያስፈልገው አካፈሉ። 46 በየቀኑም በአንድ ዐላማ በመቅደስ እየተጉ፣ በቤት ውስጥ እንጀራ እየቈረሱም ምግብን ልባዊ በሆነ ደስታና ትሕትና ዐብረው ይመገቡ ነበር፤ 47 እግዚአብሔርን አመሰገኑ፤ በሕዝቡም ሁሉ ዘንድ ከበሬታ ነበራቸው። ጌታም የሚድኑትን በየቀኑ በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር።
አጠቃላይ መረጃ: ይህ አዲስ ክንውን ነው፤ አሁን የጴንጤ ቆስጤ ቀን ነው፡፡ ሁሉም በአንድነት ተሰብስበው ነበር “እነርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በሉቃስ 1፡ 15-16 ላይ በአንድነት የነበሩትን 120 አማኞችን ምናልባት የሚያመለክት ነው፡፡ ይህ ቁጥር ዐሥራ ሁለቱንም ሐዋርያትን ያካትታል፡፡ ድንገት ይህ ቃል በድንገር የተፈጸመን ነገር የሚያመለክት ነው፡፡ ከሰማይ ድምፅ መጣ "ድምፅ ከሰማይ መጣ" ድንገት እንደሚነጥቅ አውሎንፋሽ ያለ "ከባድ ንፋስ እንደሚነፍስ" ወይም "በጣም ጠንካር ንፋስ እንደሚነፍስ" ቤቱን ሙሉ ለሙሉ ይህ ምናልባት ቤት ወይም ትልቅ ሕንጻ ሊሆን ይችላል፡፡ እሳት የሚመስል ልሳን አማራጭ ትርጉሞች 1) ከእሳት የተሠሩ ምሳላሶች የሚመስሉ ልሳኖች ወይም 2) ልሳን የሚመስሌ ትንንሽ የእሳት ነበልባሎች፡፡ ክራዝ ስነድ የምላስ ቅርጽ ይዞ እንደሚነድ ሁሉ፡፡ በሌሎች ቋንቋ ተናገሩ ከዚህ በፊት በማያውቋቸው ቋንቋዎች፡፡
አጠቃላይ መረጃ: ቁጥር 5 በዚያ ዘመን በኢየሩሳሌም ይኖሩ ስለነበሩት አይሁዶች የኋላ ታሪክ የሚነግረን ሲሆን ከእነዚህም ሰዎች መካከል አብዛኞቹ ይህ ሁኔታ በተፈረ ጊዜ በቦታው ነበሩ፡፡ አሁን ይህ ቃል ከታሪኩ ታሪኩን ለመረዳት የሚያስችል የኋላ ታሪክ መረጃ ወደ መስጠጥ መሻገሩን የሚያሳይ ነው፡፡ ፈርሃ እግዚአብሔር ያላቸው ሰዎች እግዚአብሔርን ማክበር እና ማምለክ የሚፈልጉ ሰዎች ከሰማይ በታች ያሉ ሕዝቦች ሁሉ "በዓለም ውስጥ ያሉ ሕዝቦች ሁሉ" ይህ ድምፅ በተሰማ ጊዜ ይህ ድምፅ የትልቅ አውሎንፋስ ድምፅ ይመስል ነበር፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ይህንን ድምፅ በሰሙ ጊዜ፡፡" ብዙ ሕዝብም "በጣ ብዙ ሕዝብም" ገሊላዊያን አማራጭ ትርጉም፡ "ከገሊላ"
ይህንን ስናገሩ የሚንሰማው ለምንድ ነው
አማራጭ ትርጉሞች 1) ሰዎች መልስ ማግኘት የሚፈልጓቸው እውነኛ ጥያቄዎች ሊሆኑ ይችላሉ ወይም 2) በሁኔታው ምን ያኸል እንዳስገረማቸው የሚያሳይ ሊሆን ይችላል፡፡ UDB ይህንን የተረጎመው አስገራሚ የሆነ ነገርን እንደተመለከቱ አድርጎ ነው፡፡
የጳርቴ . . . የኢላሜጤም ሰዎች፥
"ከጳርቴ፣ ከሜድ እና ከኢላሜጤም የመጡ ሰዎች"
ይሁዲነት
"በዘር አይሁዳዊያን ያልሆኑ ነገር ግን ወደይሁዲነት የገቡ ሰዎች" ወይም "የአይሁድ ሃይማኖት መከተል የጀመሩ ሰዎች"
ተገረሙ እና ግራ ገባቸው ሰዎች እየሆነ ስላለው ነገር ምን ማለት እንዳለባቸው ግራ መጋባታቸውን ያሳያል (UDB). አማራጭ ትርጉም፡ "ተደነቁ እና ግራ ተጋቡ፡፡" ይህ ምን ማለት ነው በሆነው ነገር ሰዎች ተገረሙ፡፡ ሌሎች ግን ያፌዙ ነበር፡፡ "ሌሎች ግን ይሳደቡ" ወይም "ይዘባበቱ ነበር" ወይን ጠጥተው ሰክረዋል አማራጭ ትርጉም፡ "ሰክረዋ፡፡" አንዳንዶች በሐዋርያቱ ላይ ይቀልዱባቸዋል ምክንያቱም በተዓምራት ለማመን ፍላጎት ስላሌላቸው ነው፡፡ አዲስ ወይን ከመደበኛው ወይን ይልቅ ጠንከር ያለ ወይን
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጴጥሮስ በጴንጤቆስጤ ቀን ለነበሩት አይሁዳዊያን መስበክ ጀመረ፡፡ ከዐሥራ አንዱ ጋር በመሆን ሁሉም ሐዋርያት የጴጥሮስን ንግግር በመደገፍ ተነሱ፡፡ ገና ከቀኑ ሦስት ሰዓት ነው "ገና ከጥቃቱ ዘጠኝ ሰዓት ነው" በቀኑ ሦስት ሰዓት "ከጥቃት ዘጠኝ ሰዓት" (UDB)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስ ለአይዳዊን መስበኩን ቀጥሏል፡፡ አጠቃላይ መረጃ: በዚህ ወቅት ጴጥሮስ ከዚህ ሁኔታ ጋር ተስማሚ የሆነ በነብይ ኢዮኤል አማካኝነት አስቀድሞ የተነገረ ትንቢትን አስታወሰ፡፡ በነቢዩ ኢዮኤል አማካኝነት የተነገረው ትንቢት ይህ ነው አማራጭ ትርጉም፡ "ይህ እግዚአብሔር የተናገረው እና ነብዩ ኢዮኤልን እነንዲጽፈው ያደረገው ነገር ነው" ወይም "ነብዩ ኢዮኤል እግዚአብሔር የተናገረውን ነገር እንዲህ ጽፎታል" ከአስቀድሞ የተነገረው አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር የተናገረው" ወይም "እግዚአብሔር ስለዚህ ነገር የተናረው" በመጨረሻው ዘመን አሁን ሊናገረው ያለው ነገር በመጨረሻው ዘመን እንደሚሆን የተነገረ ነው፡፡ ይህ እግዚአብሔር ከተናገረው ነገር የመጀመሪያው ክፍል ነው፡፡ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል” የሚለው ቃል በ UDB ውስጥ መጀመሪያ ላይ ሊመጣ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “በመጨረሻው ዘመን፡፡” በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ መንፈሴን አፈሳለሁ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር እግዚአብሔር መንፈሱን በሕዝቡ ላይ እንዴት በተተረፈረፈ መንገድ እንደሚሰጥ የሚያሳይ ነው፡፡ በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ “ሥጋ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሰዎች ሁሉ ሥጋ ለባሽ መሆናቸውን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ሁሉም ሰዎች፡፡”
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስ የነብይ ኢዮኤል መጽሐፍ ውስጥ መውሰዱን ቀጥሏል፡፡ አገልጋይ . . . ሴት አገልጋዮች በብሉይ ኪዳን ውስጥ የእግዚአብሔር ነቢያት እና ሌሎች እግዚአብሔርን የሚያመልኩ ሰዎች ብዙ ጊዜ የእርሱ “አገልጋዮች” ተብለው ይጠራሉ፡፡ መንፈሴን አፈሳለሁ እግዚአብሔርን መንፈሱን በልግስና ሰጥቷል፡፡ ትንቢት የእግዚአብሔርን እውነት ለመናገር እግዚአብሔር አነሳስተዋቸዋል፡፡ ትነት "ጤዛ" ወይም "ጭጋግ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስ ከነብዩ ኢዮኤል ትንቢት ወስዶ የተናገረውን ነገር የሚያበቃበት ጊዜ ነው፡፡ ፀሐይ ወደ ጨለማ ጨረቃም ወደ ደም ይለወጣሉ። የዚህ ሀረግ ቀጥተኛ ትርጉም አይታወቅም፡፡ በተቻላችሁ መጠን ወደ ቋንቋችሁ ስትተረጉሙ ቀጥተኛ ትርጉምን ለመከተል ሞክሩ፡፡ የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል አማራጭ ትርጉም፡ "የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል" የሚጠራ ጸሎት ወይም ልመና
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጴጥሮስ በ ACT 1:16 ላይ የጀመረውን ለአይሁዳዊያን መናገሩን የቀጠለበት ክፍል ነው፡፡ አስቀድሞ የታቀደ ዕቅድ እና የእግዚአብሔር ቅድመ እውቀት የክርስቶስ ሞት እንደ እግዚአብሔር ዕቅድ እና እውቀት መሠረት የተፈጸመ ነው፡፡ እናንተ “እናንተ” የሚለው የብዙ ቁጥር የተገለጸ ነው፡፡” አሳልፎ ተሰጠ "ሰዎች አሳልፎ ሰጡት" ወይም "ሰዎች አሳልፈው ሰጡት" ከእርሱ ላይ የሞትን ጣር አንስቷል "ከሞት ጣር ነጻ አውጥቶታል" ነጻ መውጣት ይህ ማለት አንድ ሰው በገመድ ከታሠረበት እንደሚፈታው መፈታት ማለት ነው፡፡ መያዝ ሞት ኃይል ኢየሱስን ይዞ መቆየት አልቻለም፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስ ለአይሁዳዊያን መናገሩን ቀጥሏል፡፡ አጠቃላይ መረጃ: በዚህ ሥፍራ ላይ ጴጥሮስ በዳዊት የተነገረውን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በማስታወስ ከኢየሱስ ክርስቶስ መሰቀል እና መቃብርን ፈንቅሎ ከመነሳቱ ጋር ያያይዘዋል፡፡ አየሁት ነገሮች ከመከናወናቸው በፊት እግዚአብሔር በእርሱ ሕይወት ውስጥ እየሠራ መሆኑን ዳዊት ተመልክቷል፡፡ በፊቴ "በእኔ መገኘት ውስጥ" ወይም "ከእኔ ጋር" በቀኜ ቀኝ እጅ ጠንካራ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ በቀኝ እጅ እንደሆነ የሚታሰብ ሰው ጠንካራ አገልጋይ ወይም ጠንካር አጋዥ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ልቤ ደስ አለው እዲሁም አንደበቴም ሐሴት አደረገ አማራጭ ትርጉም: "በጣም ደስ አለኝ እንዲሁም ሐሴት አደረኩኝ" ከዚህ በተጨናሪ ሥጋዬ በመተማመን ይኖራል አማራጭ ትርጉም፡ "ምንም እንኳ እኔ ሟች ቢሆንም በእግዚአብሔር ብቻ እተማመናለለሁ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስ ከዳዊት ንግግር ውስጥ መውሰዱን ያጠነናቀቀበት ሥፍራ ነው፡፡ ቅዱስህንም "ቅዱስህን" ወይም "ምርጥህን" መበስበስን ያይ ዘንድ የሞተው አካሉ ይበሰብስ ዘንድ በዚያ ለረጅም ጊዜ አትተወውመም፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ይበሰብስ ዘንድ፡፡" የአኗኗር ዘይቤ "ሕይወት ሰጭ እውነት"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጴጥሮስ በ ACT 1:16. ላይ ለአይዳዊያን ማደረግ የጀመረውን ንግግር ቀጥሏል፡፡ አባቶች ይህ ከብዙ ዘመናት በፊት ይኖሩ የነበሩትን አባቶችን ያመለክታል፡፡ ብዙ ጊዜ አባቶ ከአጠቃላይ ሕዝቡ በመጀመሪው ረድፍ ላይ የሚገኙትን ያመለክታል፡፡ መማል አንድ ሰው ስሚል መኃላው እውነት መሆኑን እያረጋገጠ ነው፡፡ መኃላ “መኃላ” አንድ ነገር ልክ ለመሆኑ ማረጋገጫ ዓረፍተ ነገር ነው፡፡ አስቀድሞ ተመለከተ ዳዊት አስቀድሞ ተመልክቶ ስለ መስሑ ተናገረ፡፡
የእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ይህ የመተማመን፣ የክብር፣ የሞገስ፣ መታመን፣ ኃይል እና ጥቅም የማግኛ ሥፍራ ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ይህ ጴጥሮስ በ ACT 1:16 ላይ ለአይዳዊያን ማደረግ የጀመረውን ንግግር የሚቋጭበት ክፍል ነው፡፡ ጌታ ጌታዬን እንዲህ አለው "ጌታ እግዚአብሔር ለጌታዬ (ለክርስቶስ) እንዲህ አለው" በቀኜ ተቀመጥ "የክብር፣ የተለየ ጥቅም፣ መታመን እና ኃይል የሚታገኝበት ሥፍራ ሥፍራ፣ ከእኔ አጠገብ ተቀመጥ፡፡" ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደረግ ድረስ "ጠላቶችህ ተሸናፊዎች እስካደረግ ድረስ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: አይሁዳዊያን ለጴጥሮስ ንግግር ምላሽ ሰጡ ጴጥሮስም መለሰላቸው፡፡ ልባቸው ተነካ ሉቃስ ይህንን ምሳሌያዊ ንግግር በመጠቀም አጽኖት በመስጠት ማስተላለፍ የፈለገው መልዕክት ይህንን ዓረፍተ ነገር መሰስማታቸው ምን ይኽል የሚያሳዝን መሆኑን ነው፡፡ ተስፋውም ለእናንተ ነው "ተስፋው ለእናንተ ነው
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ይህ በጴንጤ ቅስጤ ቀን የተፈጸመው ታርክ ክፍል ፍጻሜ ነው፡፡ አጠቃላይ መረጃ: ቁጥር 42 አማኞች ከጴኝጤ ቆስጤ ቀን በኋላ እንዴት ይኖሩ እንደነበር ማብራራት ይጀምራል፡፡ (ተመልከት: [[End of Story]]) መሰከረ በአዲስ ኪዳን መጽሐፍት ውስጥ “ምስክር” የሚለው ቃል ብዙ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው የኢየሱስ ተከታዬች የኢየሱስን ሕይወት፣ ሞት እና ትንሳዔ እንዴት ይናገሩ እንደነበር ለመግለጽ ነው፡፡ ጠማማ ትውልድ "በጣም ክፉ የሆነ ትውልድ" ተቀበለ "አምኗል" ወይም "ተቀብሏል" ተጠመቀ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት አጠመቋቸው፡፡ ወደ ሦስት ሺህ ይጠጋሉ አማራጭ ትርጉም፡ "ወደ 3,000 ሰዎች"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ይህ በጴንጤ ቅስጤ ቀን የተፈጸመው ታርክ ክፍል ፍጻሜ ነው፡፡ አጠቃላይ መረጃ: ቁጥር 42 አማኞች ከጴኝጤ ቆስጤ ቀን በኋላ እንዴት ይኖሩ እንደነበር ማብራራት ይጀምራል፡፡ (ተመልከት: [[End of Story]]) መሰከረ በአዲስ ኪዳን መጽሐፍት ውስጥ “ምስክር” የሚለው ቃል ብዙ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው የኢየሱስ ተከታዬች የኢየሱስን ሕይወት፣ ሞት እና ትንሳዔ እንዴት ይናገሩ እንደነበር ለመግለጽ ነው፡፡ ጠማማ ትውልድ "በጣም ክፉ የሆነ ትውልድ" ተቀበለ "አምኗል" ወይም "ተቀብሏል" ተጠመቀ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት አጠመቋቸው፡፡ ወደ ሦስት ሺህ ይጠጋሉ አማራጭ ትርጉም፡ "ወደ 3,000 ሰዎች"
ቀጠሉበት "አማኞች ቀጠሉ" በአንድ ዓላማ "በአንድ ልብ" እንጀራ መቁረስ ምግባቸውን በጋራ መመገብ፡፡ የልብ ትህትና ይህ ማለት ያለምንም ቅድመ እሳቤ፣ በግልጽ፣ ያለምንም የአካሄድ ስርዓት፣ ያለ ደረጃ ማለት ነው፡፡ ሞገስ ነበራቸው "በሰዎች ዘንድ ይከበሩ ነበር"
1 ጴጥሮስና ዮሐንስ በጸሎት ጊዜ፣ በዘጠኝ ሰዓት ወደ ቤተ መቅደስ ይወጡ ነበር። 2 ወደ ቤተ መቅደሱ ከሚገቡ ሰዎች ምጽዋት መለመን እንዲችል፣ ውብ ተብሎ በሚጠራው በቤተ መቅደሱ በር ላይ ሰዎች በየቀኑ በሸክም አምጥተው የሚያስቀምጡት፣ ከተወለደበት ጊዜ ጀምሮ ዐንካሳ የሆነ አንድ ሰው ነበረ። 3 ጴጥሮስንና ዮሐንስን ወደ ቤተ መቅደሱ ሊገቡ ሲሉ ባያቸው ጊዜ፣ ምጽዋት ለመነ። 4 ጴጥሮስ ዐይኖቹን ምጽዋት በሚለምነው ሰውዬ ላይ በማድረግ፣ ከዮሐንስ ጋር “ወደ እኛ ተመልከት” አለው። 5 ዐንካሳውም፣ ከእነርሱ አንድ ነገር ለመቀበል በመጠበቅ ወደ እነርሱ ተመለከተ። 6 ጴጥሮስ ግን፣ “ብርና ወርቅ የለኝም፤ ያለኝን ግን እሰጥሃለሁ። በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሣና ተራመድ” አለው። 7 ጴጥሮስ ቀኝ እጁን ያዘውና ወደ ላይ አነሣው፤ ወዲያውም እግሮቹና የቍርጭምጭሚቱ ዐጥንቶች ጥንካሬ አገኙ። 8 ዐንካሳው ሰውዬ ወደ ላይ ዘልሎ ቆመ፤ መራመድም ጀመረ፤ ከጴጥሮስና ከዮሐንስ ጋርም እየተራመደ፣ እየዘለለና እግዚአብሔርን እያመሰገነ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ። 9 ሰዎች ሁሉ ዐንካሳው እየተራመደ ሲሄድና እግዚአብሔርን ሲያመሰግን አዩት። 10 ምጽዋት ለመቀበል ውብ በሚባለው የቤተ መቅደሱ በር ላይ ይቀመጥ የነበረው ሰውዬ እንደ ሆነም ዐወቁ፤ በእርሱ ላይ ከሆነው የተነሣም በመደነቅና በመገረም ተሞሉ። 11 ሰውየው የጴጥሮስንና የዮሐንስን እጅ ይዞ ሳለ፣ የሰሎሞን መመላለሻ በሚባለው ደጅ ሰዎች ሁሉ በኀይል እየተደነቁ በአንድነት ወደ እነርሱ ሮጡ። 12 ጴጥሮስ ይህን ሲያይ ለሕዝቡ፣ “እናንተ የእስራኤል ሰዎች ሆይ፣ ለምን ትደነቃላችሁ? ይህን ሰው በገዛ ኀይላችን ወይም በመንፈሳዊነታችን እኛ እንዲራመድ እንዳደረግን ሁሉ፣ ለምን ዐይናችሁን አፍጥጣችሁ ትመለከታላችሁ? በማለት መልስ ሰጠ። 13 የአብርሃም፣ የይስሐቅና የያዕቆብ አምላክ፣ የአባቶቻችን አምላክ አገልጋዩን ኢየሱስን አክብሮታል። እርሱ አሳልፋችሁ የሰጣችሁትና ጲላጦስ ሊፈታው ወስኖ ሳለ፣ በፊቱ የካዳችሁት ነው። 14 ቅዱሱንና ጻድቁን ካዳችሁት፤ በእርሱም ፈንታ ነፍሰ ገዳይ እንዲፈታላችሁ ለመናችሁ። 15 እግዚአብሔር ከሙታን ያስነሣውን፣ የሕይወትን ጌታ ገደላችሁት፤ እኛም የዚህ ምስክሮች ነን። 16 በእርሱ ስም ማመን አሁን የምታዩትንና የምታውቁትን ይህን ሰው ብርቱ አድርጎታል። አዎ፣ በኢየሱስ ያለው እምነቱ በሁላችሁ ፊት ይህን ፍጹም ጤንነት ሰጠው። 17 አሁን ወንድሞች ሆይ፣ አለቆቻችሁም እንዳደረጉት ባለማወቅ ያደረጋችሁት እንደ ሆነ ዐውቃለሁ። 18 ነገር ግን እግዚአብሔር በነቢያቱ ሁሉ አፍ የእርሱ ክርስቶስ መከራ መቀበል እንዳለበት አስቀድሞ የተናገረውን አሁን ፈጸመው። 19 እንግዲህ ኀጢአታችሁ እንዲደመሰስ፣ ከጌታ ዘንድም የመታደስ ዘመን እንዲመጣ ንስሓ ግቡ፤ ተመለሱም፤ 20 ይኸውም ለእናንተ የመረጠውን ክርስቶስ የሆነውን ኢየሱስን እንዲልከው ነው። 21 እርሱ ሰማያት ሊቀበሉትና ነገሮች ሁሉ እስከሚታደሱበት ዘመን ድረስ ጠብቀው ሊያቈዩት የሚገባ፣ ከጥንት ጀምሮ በነበሩ ቅዱሳን ነቢያቱ አፍ የተነገረለት ነው። 22 ሙሴ በእርግጥ፣ ‘ጌታ እግዚአብሔር ከወንድሞቻችሁ መካከል እንደ እኔ ያለ ነቢይ ያስነሣል። የሚነግራችሁንም ሁሉ ስሙ’ አለ። 23 ያን ነቢይ የማይሰማ ሰው ሁሉ ከሕዝቡ መካከል ተለይቶ ይጠፋል። 24 አዎ፣ ከሳሙኤል ጀምሮና ከእርሱም በኋላ የተናገሩ ነቢያት ሁሉ ስለ እነዚህ ቀኖች ተናግረዋል። 25 እናንተ የነቢያትና ‘በዘርህ የምድር ሕዝቦች ሁሉ ይባረካሉ’ ብሎ ለአብርሃም እንደ ተናገረው፣ ከአባቶቻችሁ ጋር እግዚአብሔር ያደረገው ኪዳን ልጆች ናችሁ። 26 እግዚአብሔር አገልጋዩን ካስነሣ በኋላ በመጀመሪያ ወደ እናንተ ላከው፤ ይኸውም እያንዳንዳችሁን ከክፋታችሁ መልሶ ሊባርካችሁ ነው።
አያያዥ ዓረፍ ነገር: ይህ አዲስ ቀን ነው፤ ጴጥሮስ እና ዮሐንስ ወደ ቤተ መቅደሱ እየሄዱ ነው፡፡ ቁጥር 2 ላይ ስለ ሽባው ሰው የኋላ ታሪክ የተሰጠበት ነው፡፡ ወደ ቤተ መቅደሱ "በቤተ መቅደሱ አከባቢ" ወይም "ቤተ መቅደሱ፡፡" ካህናቱ ወደሚያገለግሉበት የውስጠኛው የሕንጻው ክፍል ገና አልገቡም፡፡ በዘጠኝ ሰዓት "ከሰዓት በኋላ ወደ ዘጠኝ ሰዓት ገደማ" (UDB) ምጽዋት “ምጽዋት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሰዎች ለድሆች የሚሰጡትን ገንዝብ ነው፡፡
እርሱን አተኩሮ እያየው "አተኩሮ እያየው" ወይም "ወደ እርሱ አተኩሮ እየተመለከተ" ሽባው ሰው ወደ እነርሱ እየተመለከ "ሽባው ሰው እነርሱን አተኩሮ እየተመለከተ" ብር እና ወርቅ ብር እና ወርቅ ገንዘብን የሚሉት ሀረጋት ለመወከል ጥቅም ላይ ይውላሉ፡፡ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም "በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል"
ወደ ቤተ መቅደሱ ገቡ ሰዎቹ ወደ ቤተ መቅደሱ ቅጥር ውስጥ ገቡ፡፡ ወደ ቤተ መቅደሱ ውስጥ መግባት የሚችሉት ካህናት ብቻ ነው፡፡
አስተዋሉ "ተመለከቱ" ወይም "አዩ" መልካም መግቢያ "መልካም ተብሎ የሚጠራ መግቢያ"
ሳለ "እያለ" የሰለሞን መመላለሻ ደጅ ተብሎ ከሚጠራው "የሰለሞን መመላለሻ ደጅ፡፡" ሰለሞን ከብዙ ዘመናት በፊት ይኖር የነበረ የእስራኤል ልንጉሥ ነው፡፡ መመላለሻ ደጅ በአንድ በኩል ክፍት የሆነ ራቅ ራቅ ተደርገው በተተከሉ ምሰሶዎች በተደገፉ ላይ በተመታ ጣሪያ ያለው ነው፡፡ እየተደነቁ "በጣም በመገረም" ወይም "በአድናቆት" ጴጥሮስ ይህንን ባየ ጊዜ "ጴጥሮስ የተሰበሰቡት ሰዎች ቁጥጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደረገ መሄዱን ስመለከት" ወይም "ጴጥሮስ ሕዝቡን ሲያይ" (UDB)
እናንተ የእስራኤል ሰዎች ሆይ "እናንተ እስራኤላዊያን" (UDB)፡፡ ይህን በማለት ጴጥሮስ ለሕዝቡ እየተናገረ መሆንኑ መመልከት ይቻላል፡፡ በዚህ አውድ ውስጥ “ሰዎች” የሚለው ቃል በዚያ ሥፍራ ላይ የተገኙትን ሰዎች ሁሉ ይወክላል፡፡ ስለምን ተደነቃችሁ? አማራጭ ትርጉም፡ "በዚህ ልትደነቁ አያስፈልግም" ዐይኖቻችሁ ስለምን በእኛ ላይ ሆነ አማራጭ ትርጉም፡ "ትኩረታችሁን በእኛ ላይ ማድረግ አያስፈልጋችሁም" ወይም "የትኩረት አቅጣጫችሁን በእኛ ላይ ለማድረግ ምንም ምክንያት የላችሁም" እኛ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጴጥሮስን እና ዮሐንስን ነው፡፡ እኛ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጴጥሮስን እና ዮሐንስ ነው፡፡ በእኛ ኃይል ወይም መለኮትነት ይህን ሰው በእግሩ ቆሞ እንዲሄድ ያደረግን ይመስል? አማራጭ ትርጉም፡ "በራሳችን ኃይል ወይም መለኮታዊ ጥበብ ይህንን አላደረግም"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስ በ ACT 3:12 ላይ የመጀመረውን ለአይሁዊያን ማናገሩን ቀጥሏል፡፡ እናንተ አሳልፋችሁ የሰጣችሁት "እናንተ ለጵላጦስ አሳልፋችሁ የሰጣችሁት" በጵላጦስ ፊት የከዳችሁት "ጵላጦስ ባለበት የከዳችሁት" እርሱ ሊፈታው በወደደ ጊዜ "ጵላጦስ ሊፈታው በፈለገ ጊዜ" ነፍሰ ገዳዩ እንዲፈታላችሁ ጠየቃችሁ አማራጭ ትርጉም፡ "ጵላጦስ ነፍሰ ገዳን እንዲፈታላችሁ ጠየቃችሁ"
የሕይወት ራስ "የሕይወትን ምንጭ" (UDB) ወይም "የሕይወት ገዥ" አሁን ይህ ቃል የተደራሲያኑን የትኩረት አቅጣጫ ወደ ሽባው ሰው ለመመለስ የሚያገለግል ነው፡፡ ይህ ሰው እንዲጠነክር ያደረገው "ይህ ሰው ደኸና እንዲሆን ያደረገው"
አሁን ጴጥሮስ የተደራሲያኑን የትኩረት አቅጣጫ ከሽባው ሰው ላይ በማንሰሳት እነርሱን በቀጥታ ወደመናገር እንደዞረ የሚያሳይ ነው፡፡
ተመለሱ "ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ" ይሰረዝ "ይደመሰስ ዘንድ" ወይም "ይፋቅ ዘንድ" እንግዲህ ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንድትመጣላችሁ "ጌታ መልሶ ያበረታችሁ ዘንድ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስ በ ACT 3:13 ላይ የመጀመረውን ለአይሁዊያን ማናገሩን ቀጥሏል፡፡ አጠቃላይ መረጃ: በቁጥር 22-23 ላይ ጴጥሮስ ሙሴ ስለመስሑ አስቀድሞ የተናገረውን ነገር በማንሳት ተናግሯል፡፡ ሰማይ ይቀበለው ዘንድ ከዚህ በፊት አደርገዋለሁ ብሎ እንደተናገረው ኢየሱስ ያለው በሰማይ ነው፡፡ ነገር ሁሉ እስከሚታደስበት ዘመን ድረስ "እግዚአብሔር ሁሉን ነገት እስከሚያድስበት ጊዜ ድረስ" ከጥንት ጀምሮ በቅዱሳን ነቢያቱ አፍ የተናገረው፥ "እግዚአብሔር ለቅዱስ ነቢያቱ ሁሉን ነገር እንደሚያድስ ተናግሯል" ከጥንት ጀምሮ በቅዱሳን ነቢያቱ "ከብዙ ዘመናት በፊት የኖሩት ቅዱስ ነቢያቱ" ነቢያ ያስነሣላችኋለ "አንድ ሰው ነቢይ እንዲሆን ይመርጣል" ትጠፋለች "ትወገዳለች" ወይም "ትወሰዳለች"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስ በ ACT 3:13 ላይ የመጀመረውን ለአይሁዊያን ማናገሩን ቀጥሏል፡፡ እርሱን የተከተሉት ሰዎች "ከሳሙኤል በኋላ የኖሩት ነቢያት" ስለእነዚህ ቀናት "ስለእነዚህ ጊዜያት" ወይም "አሁን እየሆኑ ስላሉት ነገሮች" እናንተ የነቢያቱ ልጆች ናችሁ "እናንተ የነቢያቱ ወራሾች ናችሁ፡፡" አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር በነቢያቱ አማካኝነት የገባውን ቃል ትቀበላላችሁ፡፡" እንዲሁም የኪዳኑን "እንዲሁም የኪዳኑ ልጆች ናችሁ፡፡" አማራጭ ትርጉም፡ "እግዚአብሔር በኪዳኑ አማከካኝነት የገባውን ቃል ትቀበላላችሁ፡፡" በዘርህ "ከአንተ ልጆች የተነሣ" እግዚአብሔር ባሪያውን ካስነሣ በኋላ "እግዚአብሔር ባሪያውን ከመረጠ በኋላ" ወይም "እግዚአብሔር ሥልጣንን ለባሪያው ከሰጠ በኋላ" ባያሪው ይህ የእግዚአብሔርን መስሕ የሚያመለክት ቃል ነው፡፡
1 ጴጥሮስና ዮሐንስ ለሕዝቡ እየተናገሩ ሳሉ፣ ካህናቱና የቤተ መቅደሱ ሹም፣ ሰዱቃውያንም ወደ እነርሱ መጡ። 2 እነርሱም፣ ጴጥሮስና ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ ሕዝቡን ያስተምሩና ከሙታን መነሣቱንም ያውጁ ስለ ነበረ፣ እጅግ ተበሳጩ። 3 ያዟቸውና በዚያ ጊዜ ምሽት ስለ ነበረ እስከሚቀጥለው ጧት ድረስ በወኅኒ አቈዩአቸው። 4 ነገር ግን መልእክቱን ከሰሙት ብዙ ሰዎች አመኑ፤ ያመኑት ሰዎች ቍጥርም ዐምስት ሺሕ ያህል ነበረ። 5 በሚቀጥለው ቀን እንደዚህ ሆነ፤ አለቆቻቸው፣ ሽማግሌዎቻቸውና የሕግ መምህራናቸው በኢየሩሳሌም ውስጥ በአንድነት ተሰበሰቡ። 6 ሊቀ ካህናቱ ሐና እዚያ ነበረ፤ ቀያፋም፣ ዮሐንስም፣ እስክንድሮስና የሊቀ ካህናቱ ዘመዶች ሁሉ ነበሩ። 7 ጴጥሮስንና ዮሐንስን በመካከላቸው አቁመውም፣ "በማን ሥልጣን ወይም በማንስ ስም ይህን አደረጋችሁ?" ብለው ጠየቋቸው። 8 ከዚያም ጴጥሮስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ እንዲህ አላቸው፤ “እናንተ የሕዝቡ አለቆች፣ ሽማግሌዎችም፣ 9 ለታመመ ሰው የተደረገ መልካም ነገርን በሚመለከት በዚህ ቀን እየተጠየቅን ከሆንን፣ ይህ ሰው በምን ዳነ? 10 ይህ ለእናንተ ለሁላችሁ፣ ለእስራኤልም ሕዝብ ሁሉ የታወቀ ይሁን፤ ይህ ሰው በፊታችሁ እዚህ በጤንነት የቆመው እናንተ በሰቀላችሁት፣ እግዚአብሔር ከሞት ባስነሣው በናዝሬቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ነው። 11 ኢየሱስ ክርስቶስ እናንተ ግንበኞች የናቃችሁት፣ ነገር ግን የማእዘን ራስ የሆነ ድንጋይ ነው። 12 በሌላ በማንም ድነት የለም፤ ልንድንበት የሚገባ በሰዎች መካከል የተሰጠ ሌላ ስም ከሰማይ በታች የለምና።” 13 የጴጥሮስንና የዮሐንስን ድፍረት ሲያዩ፣ ያልተማሩና ተራ ሰዎች እንደ ሆኑ ሲያውቁም፣ ጴጥሮስና ዮሐንስ ከኢየሱስ ጋር እንደ ነበሩ በማወቅ ተደነቁ። 14 የተፈወሰው ሰውዬ ዐብሯቸው ቆሞ ስላዩት፣ የአይሁድ መሪዎች በእነርሱ ላይ ምንም መናገር አልቻሉም። 15 ሐዋርያቱ ከሸንጎው ወጥተው እንዲሄዱ ካዘዙ በኋላ፣ እርስ በርሳቸው ተነጋገሩ። 16 እንደዚህም አሉ፤ “በእነዚህ ሰዎች ላይ ምን እናድርግ? በእነርሱ አማካይነት የታወቀ ተአምር የመፈጸሙ እውነታ በኢየሩሳሌም ለሚኖር ሁሉ ታውቆአልና፤ ልንክደው አንችልም። 17 ሆኖም ይህ በሕዝቡ መካከል የበለጠ እንዳይሠራጭ፣ በዚህ ስም ከእንግዲህ ለማንም እንዳይናገሩ እናስጠንቅቃቸው።” 18 ጴጥሮስንና ዮሐንስን ወደ ውስጥ ጠርተው በኢየሱስ ስም ፈጽሞ እንዳይናገሩም፣ እንዳያስተምሩም አዘዟቸው። 19 ነገር ግን ጴጥሮስና ዮሐንስ መልሰው እንዲህ አሏቸው፤ “ለእግዚአብሔር ከመታዘዝ ይልቅ እናንተን መታዘዝ በእግዚአብሔር ፊት ትክክል እንደ ሆነ እናንተ ፍረዱ። 20 እኛ ስላየናቸውና ስለ ሰማናቸው ነገሮች ለመናገር ዝም ማለት አንችልም።” 21 እንደ ገናም ጴጥሮስንና ዮሐንስን ካስጠነቀቋቸው በኋላ፣ ለቀቋቸው። እነርሱን ለመቅጣት ምንም ምክንያት ለማግኘት አልቻሉም፤ ምክንያቱም ሰዎቹ ሁሉ ለተደረገው እግዚአብሔርን ያመሰግኑ ነበር። 22 ይህ በተአምር የተፈወሰው ሰውዬ ከዐርባ ዓመት በላይ ዕድሜ ነበረው። 23 ከተለቀቁ በኋላ፣ ጴጥሮስና ዮሐንስ ወደ ራሳቸው ሰዎች መጡና የካህናት አለቆችና ሽማግሌዎች ያሏቸውን ሁሉ ነገሯቸው። 24 ሰዎቹ የነገሯቸውን ሲሰሙም፣ ድምፃቸውን በአንድነት ወደ እግዚአብሔር ከፍ አድርገው እንዲህ አሉ፤ “ጌታ ሆይ፣ አንተ ሰማያትን፣ ምድርንና ባሕርን፣ በውስጣቸው የሚገኘውንም ሁሉ የፈጠርህ ነህ፤ 25 በመንፈስ ቅዱስም በአገልጋይህ በአባታችን በዳዊት አፍ እንዲህ ብለሃል፦ ‘አሕዛብ ለምን አጕረመረሙ፣ ሕዝቡስ ከንቱ ነገርን ለምን ዐሰቡ? 26 በጌታ፣ በእርሱ መሲሕም ላይ የምድር ነገሥታት ተነሡ፣ አለቆችም በአንድነት ተሰበሰቡ።’ 27 በእውነት ሄሮድስና ጴንጤናዊው ጲላጦስ፣ ከአሕዛብና ከእስራኤል ሕዝብ ጋር በቀባኸው በቅዱሱ አገልጋይህ በኢየሱስ ላይ በዚህ ከተማ ውስጥ በአንድነት ተሰብስበዋል። 28 የተሰበሰቡትም እጅህና ዐሳብህ አስቀድመው የወሰኑት እንዲፈጸም ነው። 29 ጌታ ሆይ፣ አሁን ወደ ዛቻዎቻቸው ተመልከት፤ ለባሪያዎችህም ቃልህን በሙሉ ድፍረት እንዲናገሩ ስጥ። 30 ለመፈወስ እጅህን ስትዘረጋው፣ ምልክቶችና ድንቆች በቅዱሱ አገልጋይህ በኢየሱስ ስም ይደረጋሉ።" 31 ጸሎት ሲጨርሱ፣ ተሰብስበውበት የነበረው ስፍራ ተናወጠ፤ ሁሉም በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ፤ የእግዚአብሔርን ቃልም በድፍረት ተናገሩ። 32 ካመኑት እጅግ ብዙዎች አንድ ልብና አንድ ነፍስ ነበራቸው፤ ከእነርሱ አንድም ሰው፣ ያለው ማንኛውም ነገር የራሱ እንደ ሆነ አልተናገረም፤ ይልቁን ሁሉም ነገሮች የጋራ ነበሩ። 33 ሐዋርያቱም በታላቅ ኀይል ስለ ጌታ ኢየሱስ ትንሣኤ ምስክርነታቸውን ያውጁ ነበር፤ በሁሉም ላይ ታላቅ ጸጋ ነበረባቸው። 34 በመካከላቸው ችግረኛ ሰው አልነበረም፤ መሬት ወይም ቤት ያላቸው ሁሉ ሸጠው የሽያጩን ገንዘብ ያመጡትና፣ 35 በሐዋርያት እግር አጠገብ ያስቀምጡት ነበርና። አከፋፈሉም ይደረግ የነበረው እያንዳንዱ አማኝ በሚያስፈልገው መሠረት ነው። 36 ሌዋዊ የሆነው፣ ቆጵሮሳዊው ዮሴፍ ሐዋርያት በርናባስ የሚባል ስም ያወጡለት ሰው ነበር (ትርጕሙ የመጽናናት ልጅ ማለት ነው)። 37 እርሱ የነበረውን መሬት ሸጠው፤ ገንዘቡንም አምጥቶ በሐዋርያት እግር አጠገብ አስቀመጠው።
የሐዋርያት ሥራ 4፡ 1-3 የቤተ መቅደሱ ጠባቂዎች አለቃ የቤተ መቅዱስ ጠባቂዎች ኃላፊ ወደ እነርሱ መጣ "ቀረባቸው" ወይም "ወደ እርሱ መጣ" በጣም ፈሩ ጴጥሮስ ስለኢየሱስ እና ስለእርሱ ከሞት መነሳት አስተማረ፡፡ ይህ ሳዱቃዎያንንን አስጨነቃቸው ምክንያቱም ኢየሱስ ከሞት መነሳቱን አያምኑም ነበርና፡፡ የወንዶች ቁጥር ይህ የወንዶችን ቁጥር ብቻ የሚያመለክት ነው፡፡ ሴቶች እና ሕጻና በቁጥሩ ውስጥ አልተካተቱም፡፡ ጥዋት እንደሆነም ሰዎች መርማሪ ጥያቄ የሚጠየቁት ጥዋት ነው፤ ይህ የተለመደ ተግባር ነው፡፡ ወደ አምስት ሺህ ዓመት ገደማ "ወደ አምስት ሺህ ዓመታት ገደማ” ወይም “ወደ አምስት ሺህ ዓመታት አድገዋል”
በምን ኃይል "ሥልጣን ማን ሰጠህr" (UDB) ወይም "ስልጣን ማን ሰጠህ፡፡" ጴጥሮስ እና ዮሐንስ በራሳቸው ሰዎችን መፈወስ እንደማይችሉ ያውቃሉ፡፡ በማን ስም "ስልጣን የሰጠህ ማን ነው"
የእስራኤል ሰዎች ሆይ "እናንተ እስራኤላዊያን"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ጴጥሮስ ለአይሁድ የሃይማኖር መሪዎች በ ACT 4:8 ላይ መናገር የጀመረው ሀሳብ ይቋጫል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ድንጋይ ነው ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ አንድ የማዕዘን ድንጋይ መሠረት ለመጣል እና በሕንጻ ግንባታ ወቅት ለማነጻጸሪያ እንደሚያገለግል ሁሉ ኢየሱስም ለድነት ብቸኛው መሠረት ነው፡፡
የእነዚህ ሰዎች ድፈረት በተመለከቱ ጊዜ በዚህ ሥፍራ “እነዚህ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የመሪዎችን ቡድን ነው፡፡ እነርሱ . . . እንደሆኑ አወቁ "ተገነዘቡ" ወይም "አወቁ" ተራ ሰዎች መሆናቸው፡፡ they were ordinary በዚህ ሥፍራ "እነርሱ" የሚለው ቃ የሚያመለክተው ጴጥሮስን እና ዮሐንስን ነው፡፡ ያልተማሩ ሰዎች "ምንም ዓይነት ስልጠና ያልወሰዱ ሰዎች" ወይም "መደበኛ ትምህርት ያልተከታተሉ ሰዎች"
ሸንጎ በየሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ሸንጎ የሚለው ቃል አዘውትሮ ጥቅም ላይ ይውላል፡፡ ከየሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ከምዕራፍ 25፡12 በስተቀር ይህ ቃል የሚያመለክተው የአይሁን ሳንሄድረንን ነው፡፡ እነርሱ ይህ ቃል የሚያመለክተው ጴጥሮስን እና ዮሐንስን ነው፡፡
ትክክል ይሁን አይሁን "ጻድቅ እና እግዚአብሔርን የሚያከብር" ምንም ልናደረግ አንችልም "ለመናገር እንገዳደለን"
አጠቃላይ መረጃ: ቁጠር 22 ፈውስን ያገኘው ስለሽባው ሰው ዕድሜ የኃላ ታሪክ ይሰጠናል ከብዙ ማስጠንቀቂያ በኋላ መሪዎቹ ይህንን ማድረግ የሚቀጥሉ ከሆነ ተጨማሪ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው በመናር አስፈራሯው፡፡ እነርሱን ለመቅጣት የሚበቃ በዚ ምክንያት ማግኘት አላቻሉም የሰውዬውን መፈወስ የተመለኮቱ ሰዎች ረበሻ ሳያስነሱ መሪዎች ጴጥሮስ እና ዮሐንስን መቅጣት የሚችሉበት መንገድ ማግኘት አልቻሉም፡፡
የራሳቸው ወደ ሆኑ ሰዎች መጡ ወደ ሌሎች አማኞች ዘንድ ሄዱ፡፡ ድምጻቸውን በአንድነት ከፍ በማድግ በሀሳብ እና ልብ ሆነው፡፡ በአባታችን በዳዊት በእናንተ አገልጋይ አፍ በተነገረው መሠረት "በዳዊት አባታችን በእናተ አገልጋይ አማካኝነት በተነገረው መሠረት" አገልጋይ በብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔር ነቢያት እና እግዚአብሔርን የሚያመልከቱ ሌሎች ሰዎች ብዙ ጊዜ የእርሱ “አገልጋዮች” ተብለው ይጠራሉ፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: አማኞች በ ACT 4:25 ላይ የጀመሩትን ከንጉሥ ዳዊት የመዝሙር መጽሐፍ ውስጥ የወሰዱትን ሀሳብ ያጠናቅቃሉ፡፡ አብረው ተከማቹ "ኃይላቸውን በአንድነት አጣመሩ" ክርስቶስ ይህ ከመዝሙርት 2፡ 1-2 ክፍል የተወሰደ ነው፡፡ “መስሕ” የሚለው ቃል በዕብራይስጥ ቋንቋ ሲሆን ትርጓሜውም “ክረስቶስ” ማለት ነው፡፡ ይህም “የተቀባውም” ማለት ነው፡፡
ሄሮዶስ እና ጵላጦስ ከአሕዛቦች እና ከእስራኤል ሕዝብ ጋር በአንድነት በመሆኑን በመዝሙር መጽሐፍ ውስጥ ዳዊት ያካተተው አሕዛብን ብቻ ሲሆን ጴጥሮስ ግን መስሑን የተቃወሙትን እስራኤልን እና የእርሷ መሪዎች ከአሕዛብ ጋር በአንድነተን በዚህ ከተማ ውስጥ "በእየሩሳሌም ውስጥ" በእጅህ እና ውሳኔህ "ትወስናለህ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: አማኞቹ በ ACT 4:24 ላይ የተመሩትን ጸሎት ያጠናቅቃል፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል በድፍረት ይናገሩ ነበር ይህ ደቀ መዛሙርቱ በመንፈስ ቅዱስ ከመሞላታቸው የተነሳ የሆኑ ነገሮች ናቸው፡፡
ምስክርነት በአዲስ ኪዳን ውስጥ ይህ ቃል ብዙ ጊዜ የኢየሱስን ተከታዮች ሕይወቱን፣ ሞቱን እና ትንሣኤውን ለማመልከት ይውላል፡፡ ታላቅ ጸጋ በእነርሱ ላይ ነበር አማራጭ ትርጉሞች፡ 1) እግዚአብሔር ብዙ ስጦታዎችን ያፈስ ነበር እና አማኞቹም ሁሉ ትልቅ ድፍረት ነበራው፡፡ ወይም 2) አማኞች ሁሉ በእየሩሳሌም ውስጥ ባሉ አማኞቹ ሁሉ ዘንድ ትልቅ አክብሮት ነበራቸው፡፡
በሐዋርያቱ እግር ሥር ያኖሩ ነበር ይህ አማኞቹ . . መግለጫ ነበር፡ 1) በአደባባይ ልባቸው መለወጡን የሚያሳዩበት መንገድ ነው እና 2) ስጦታዎቹ በአግባቡ ጥቅም ላይ በማዋል ማስተዳደር እንዲችሉ ለሐዋርያቱ ስልጣን መስጠትን የሚያመለክት ነው፡፡
በሐዋርያቱ እግር ሥር ያኖሩ ነበር ይህ አማኞቹ . . መግለጫ ነበር፡ 1) በአደባባይ ልባቸው መለወጡን የሚያሳዩበት መንገድ ነው እና 2) ስጦታዎቹ በአግባቡ ጥቅም ላይ በማዋል ማስተዳደር እንዲችሉ ለሐዋርያቱ ስልጣን መስጠትን የሚያመለክት ነው፡፡
1 ሐናንያ የሚባል አንድ ሰውም ከሚስቱ ከሰጲራ ጋራ መሬት ሸጠ፤ 2 የሽያጩን ገንዘብ ከፊል መጠን አስቀረው (ሚስቱም ታውቅ ነበር)፤ ሌላውን የገንዘብ መጠን ግን አምጥቶ በሐዋርያት እግር አጠገብ አስቀመጠው። 3 ጴጥሮስ ግን ሐናንያን እንዲህ አለው፤ “ሐናንያ ሆይ፣ ለመንፈስ ቅዱስ እንድትዋሽና የመሬቱን ዋጋ ከፊል መጠን እንድታስቀር ሰይጣን ልብህን ለምን ሞላው? 4 መሬቱ ሳይሸጥ የአንተ እንደ ሆነ አይዘልቅም ነበርን? ከተሸጠ በኋላስ በአንተ ቊጥጥር ሥር አልነበረምን? በልብህ ይህን ነገር እንዴት ዐሰብህ? የዋሸኸው ለእግዚአብሔር እንጂ ለሰዎች አይደለም። 5 እነዚህን ቃሎች ሰምቶ፣ ሐናንያ ወደቀ፤ ሞተም። በሰሙት ሁሉ ላይም ታላቅ ፍርሀት መጣ። 6 ጐበዛዝቱ ወደ ፊት መጡና ከፈኑት፤ ወደ ውጭ አውጥተውም ቀበሩት። 7 ከሦስት ሰዓት ያህል በኋላ፣ ሚስቱ ምን እንደ ሆነ ሳታውቅ ወደ ውስጥ ገባች። 8 ጴጥሮስ፣ “መሬቱን ይህን ለሚያህል ዋጋ ሸጣችሁት ከሆነ ንገሪኝ” አላት። እርሷም፣ "አዎ፣ ይህን ለሚያህል ነው” አለችው። 9 ከዚያም ጴጥሮስ፣ “የጌታን መንፈስ ለመፈታተን እንዴት ተስማማችሁ? ተመልከቺ፣ ባልሽን የቀበሩት ሰዎች እግር በር ላይ ነው፤ አንቺንም ወደ ውጭ ያወጡሻል።” 10 እርሷም ወዲያው በጴጥሮስ እግር ሥር ወደቀች፤ ሞተችም፤ ጐበዛዝቱም ወደ ውስጥ ሲገቡ ሞታ አገኟት፤ ወደ ውጭ አወጧትና በባሏ አጠገብ ቀበሯት። 11 በቤተ ክርስቲያን ሁሉና እነዚህን ነገሮች በሰሙት ላይ ታላቅ ፍርሀት መጣ። 12 በሕዝቡ መካከል ብዙ ምልክቶችና ድንቆች በሐዋርያት እጅ ይደረጉ ነበር። ሁሉም በሰሎሞን ደጅ መመላለሻ በአንድነት ነበሩ። 13 ነገር ግን አንድም ሌላ ሰው እንኳ ከእነርሱ ጋር ለመተባበር ድፍረት አልነበረውም፤ ሆኖም ከሕዝቡ ከፍተኛ አክብሮት ነበራቸው። 14 አሁንም የበለጡ አማኞች፣ እጅግ ብዙ ወንዶችና ሴቶች ለጌታ ይጨመሩ ነበር፤ 15 በሽተኞችንም እንኳ ተሸክመው ወደ መንገድ እያመጡ በዐልጋና በቃሬዛ ላይ ያስቀምጧቸው ነበር፤ ይኸውም ጴጥሮስ ሲያልፍ በተወሰኑት ላይ ጥላው እንዲያርፍባቸውነው። 16 በሽተኞችንና በርኩሳን መናፍስት የሚሠቃዩትን በማምጣት በኢየሩሳሌም ዙሪያ ካሉ ከተሞች አያሌ ሰዎችም በአንድነት ተሰበሰቡ፤ በሽተኞችም ሁሉ ተፈወሱ። 17 ነገር ግን ሊቀ ካህናቱና ዐብረውት የነበሩትም ሁሉ ተነሡ (የሰዱቃውያን ወገን የሆነው ማለት ነው)፤ እነርሱም በቅናት ተሞልተው ነበር፤ 18 እጃቸውንም በሐዋርያት ላይ ጫኑ፤ በሕዝብ ወኅኒ ውስጥም አስገብተው አሰሯቸው። 19 ይሁን እንጂ፣ የጌታ መልአክ በሌሊት የወኅኒውን በሮች ከፈተ፤ ወደ ውጭ አውጥቶአቸውም እንዲህ አላቸው፤ 20 “ሂዱ፤ በቤተ መቅደስ ውስጥ ቁሙና የዚህን ሕይወት ቃሎች ሁሉ ለአሕዝቡ ተናገሩ።” 21 ይህን ሲሰሙም፣ ንጋት ላይ ወደ ቤተ መቅደስ ገቡና አስተማሩ። ነገር ግን ሊቀ ካህናቱና ከእርሱ ጋር የነበሩት መጡ፤ ሸንጎውንም በአንድነት፣ የእስራኤል ሕዝብ ሽማግሌዎችንም ጠሩ፤ ሐዋርያቱን እንዲያመጧቸውም ወደ ወኅኒው ላኩ። 22 ነገር ግን የተላኩት መኰንኖች በወኅኒው ውስጥ አላገኟቸውም፤ ተመልሰው በመሄድም እንዲህ ብለው ተናገሩ፣ 23 “ወኅኒው በደኅና እንደ ተቈለፈና ጠባቂዎችም በር ላይ እንደ ቆሙ አግኝተናል፤ በከፈትነው ጊዜ ግን በውስጡ ማንንም አላገኘንም።” 24 የመቅደሱ ጥበቃ ሹምና ሊቃነ ካህናቱ እነዚህን ቃላት ሲሰሙ፣ እስረኞችን በሚመለከት ምን እንደሚሆን እጅግ ግራ ተጋቡ። 25 ከዚያም አንድ ሰው መጣና፣ “ወኅኒ ውስጥ ያስገባችኋቸው ሰዎች ቤተ መቅደስ ውስጥ ቆመው ሕዝቡን እያስተማሩ ናቸው” ብሎ ነገራቸው። 26 ስለዚህ ሹሙ ከመኰንኖች ጋር ሄደ፤ መልሶም አመጣቸው፤ ያመጧቸው ግን በኀይል አልነበረም፤ ሕዝቡ በድንጋይ ይወግሯቸዋል ብለው ፈርተው ነበርና። 27 አምጥተዋቸው በነበረ ጊዜ፣ በሸንጎው ፊት አቆሟቸው። ሊቀ ካህናቱም ጠየቃቸው፤ 28 እንዲህም አላቸው፤ “በዚህ ስም እንዳታስተምሩ በጥብቅ አስጠንቅቀናችሁ ነበር፤ እናንተ ግን ኢየሩሳሌምን በትምህርታችሁ ሞልታችኋታል፤ የዚህን ሰው ደም በእኛ ላይ ለማምጣትም ትፈልጋላችሁ።” 29 ጴጥሮስና ሐዋርያቱ ግን መልሰው፣ “ለሰው ከመታዘዝ ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባል። 30 የአባቶቻችን አምላክ በዕንጨት ላይ በመስቀል የገደላችሁትን፣ ኢየሱስን አስነሣው። 31 አዳኝና የሁሉ የበላይ እንዲሆን፣ ለእስራኤል ንስሓንና የኀጢአት ይቅርታን ለመስጠት እግዚአብሔር በቀኙ ከፍ ከፍ አደረገው። 32 እኛና እግዚአብሔር ለሚታዘዙት የሰጠው መንፈስ ቅዱስ የእነዚህ ነገሮች ምስክሮች ነን።” 33 የሸንጎው አባሎች ይህን ሲሰሙ፣ በጣም ተናደዱ፤ ሐዋርያቱንም ለመግደል ፈለጉ። 34 ነገር ግን የሕግ መምህር የነበረና ሕዝቡም ሁሉ የሚያከብረው ገማልያል የሚባል አንድ ፈሪሳዊ ተነሥቶ፣ ሐዋርያት ለተወሰነ ጊዜ ውጭ እንዲቈዩ አዘዘ። 35 ከዚያም እንዲህ አላቸው፤ “የእስራኤል ሰዎች ሆይ፣ በእነዚህ ሰዎች ልታደርጉ ያሰባችሁትን በጥንቃቄ ተመልከቱት። 36 ከጥቂት ጊዜ በፊት ቴዎዳስ ትልቅ ሰው ነኝ በማለት ተነሥቶ ነበርና፤ አራት መቶ ያህል ወንዶችም ተከተሉት። እርሱ ተገደለ፤ ይታዘዙለት የነበሩትም ሁሉ ተበታትነው እንዳልነበሩ ሆኑ። 37 ከዚህም ሰው በኋላ፣ የገሊላው ይሁዳ በቈጠራው ቀናት ዐምፆ የተወሰኑ ሰዎችን አስከትሎ ሄደ። እርሱም ሞተ፤ እርሱን ይታዘዙት የነበሩትም ተበታተኑ። 38 አሁንም እነግራችኋለሁ፤ ከእነዚህ ሰዎች ተለዩ፤ እነርሱንም ተዉአቸው፤ ይህ ዐሳብ ወይም ሥራ የሰዎች ከሆነ፣ ይጠፋል። 39 የእግዚአብሔር ከሆነ ግን፣ ልታጠፏቸው አትችሉም፤ ከእግዚአብሔር ጋር ስትጋጩም እንኳ እንዳትገኙ።” እነርሱም በዐሳቡ ተስማሙ። 40 ከዚያም በኋላ፣ ሐዋርያቱን ወደ ውስጥ ጠርተው ገረፏቸው፤ በኢየሱስ ስም እንዳይናገሩም አዘዟቸውና ለቀቋቸው። 41 እነርሱም ስለ ስሙ ይዋረዱ ዘንድ የተገባቸው ሆነው ስለ ተቈጠሩ፣ ደስ እያላቸው ከሸንጎው ወጡ። 42 ከዚያ በኋላ በየቀኑ፣ በቤተ መቅደስና ከቤት ወደ ቤት፣ በተከታታይ ኢየሱስ፣ ክርስቶስ እንደ ሆነ ያስተምሩና ይሰብኩ ነበር።
አጠቃላይ መረጃ: ይህ የታሪኩ አዲስ ጅማሬ ክፍል ነው፡፡ ይህ ታሪክ የአናኒያ እና ሳጵራ ስለተባሉ ሁለት ሰዎች የኃላ ታርክ ይሰጠናል፡፡ አሁን "አሁን ግን፡፡" ይህ የታሪኩ አንዲስ ክፍል መጀመሩን ያሳያል፡፡ ይህ በቋንቋችሁ በንጽጽር ሊቀመጡ የሚችሉ ታሪክች መግቢያን በሚያሳዩ ቃላት ተተርጉሚ ሊቀመጥ ይችላል፡፡ የሆነ ሰው ይህንን ቃል በቋንቋችሁ አንድን ሰው ለማስተዋወቅ በሚትጠቀሙበት ቃል ለመተርጎም ጥረት አድርጉ፡፡ ከሽያጩ የጠወሰነ ገንዘብ ወስዶ ሸሸገ የሸጠበትን ገንዘብ ሙሉውን ለሐዋርያት ባለመናገሩ ታማኝ አልነበረም፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ከሰጣ ገንዘብ ውስጥ የተወሰነው በምስጥር አስቀመጠ፡፡" ይህንን ነገር ምስቱም ታውቅ ነበር አማራጭ ትርጉም፡ "ምስቱን ታውቅ ነበር እንዲሁም ይህንን በማድረጉ ተስማምታ ነበር" በሐዋርያቱ እግር ፉት አስቀመጡ ይህንን በ ACT 4:35 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
ሴጣን ስለምን ልባችሁን ሞላው . . . መሬቱን? ጴጥሮስ አናኒያስን ለመገሰጽ ይህንን ጥያቄ ጠይቆታል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ሴጣን እንድትዋሹ የሰጣችሁን ሽንገላ ልጽቀበለጽ ባልጸገባ ነበር፡፡" የእናንት አልነበረምን . . . በእናንተ ቁጥጥር ሥር አልነበረምን? ጴጥሮስ አናናይስን በገንዘቡ የፈለገውን የማድረግ መብት እንደነበረው ለማስታወስ ይህንን ጥያቄ ጠይቆታል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “የገዛ ገንዘብህን ኃላፊነት በተሞለው መልኩ የማስተዳደር ኃለፊነት አለብህ፡፡” እንዲህ ዓይነቱ ነገር በልብህ እንዴት ልታስብ ቻልክ? ጴጥሮስ ይህንንነ ጥያቄ የተጠቀመው አናናስን ለመገሰጽ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ገንዘብህን በመደበቅ ለማታለል መወሰን አልነበረብህም፡፡” ወጣቶቹ ወደ ፊት መጡ፡፡ "ወጣቶቹ ተነሱ፡፡" ይህ ተግባራዊ እርምጃ የመውሰድ መገለጫ ነው፡፡ ተሸክመው አወጡት እና ቀበሩት፡፡ አንድ ሰው ሲሞት በድኑን ለመቅበር የሚፈጸም ሂደት አለ፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ሥርዓት የተፈጸመለት አይመስልም፡፡
የተከሠተው ነገር ምንድ ነው "ባሏ ሞተ"
አያያዥ ዓረፈት ነገር: ይህ የአናናስ እና ሰጵራ ታሪክ የመጨረሻው ክፍል ነው፡፡ እንዴት አንች ሰጵራ የጌታን መንፈስ ለመፈተን ከእርሱ ጋር ትተባበሪያለሽ? ጴጥሮስ ይህንን ጥያቄ የጠየቃት ሁለቱ ኃጢአት ለማድረግ መስማማታቸውን ለማሳየት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "መንፈስን ለመፈትን የጋራ ስምምነት ላይ ደርሳችኋል!" ባልሽን የቀበሩት ሰዎች እግር በደጅ ነው በዚህ ሥፍራ ላይ “እግር” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አናኒያስን የቀበሩትን ሰዎች ነው፡፡ የመጨረሻ እስትንፋሷን ተነፈሰች ይህ በሌላ አገላለጽ “ሞተች” ለማለት ነው፡፡
የሰለሞን ደጅ መመላለሻ ይህ በቤተ መቅደሱ አጥር ግቢ ውስጥ ያለ ሥፍራ ነው፡፡ ማንም "የቤተ ክርስቲያን አካል ያልሆነ ማንም ሰው ማለት ነው" ይሯቸው ነበር "ለእነርሱ ታላቅ አክብሮት እና ፍርሃት ነበራቸው"
ጥላው በእነርሱ ላይ ያርፍ ዘንድ ይህ በተዘዋዋር መልኩ የሚያመለክተው የጴጥሮስ ጥላ ከነካቸው እንደሚፈወሱ ነው፡፡
ይሁን እንጂ በዚህ ሥፍራ ላይ ሌላ ለንጽጽር የቀረበ ታሪክ እንዳለ እንመለከታን፡፡ ይህንን በቋንቋችሁ ሌላ ለንጽጽር የቀረበ ታሪክን ለማስተዋወቅ በሚቻልበት መንገድ ልትተረጉሙት ትችላላችሁ፡፡ ቅንዓት "ቅንዓት" በሐዋርያት ላይ እጆቻቸውን ለመጫን "ሐዋርያቱን ለማሠር"
እየመራ አወጣቸው "ሐዋርያቱን ከእስር ቤት መርቶ አወጣቸው" በማለዳ ቤተ መቅዱስ በምሽት ተዘግቶ ነበር፡፡ ሐዋርያቱ በተቻለው መጠን መለአኩን ተከተሉት፡፡
በጣም ፈሩ "ግራ ተጋቡ" ወይም "ተምታታባቸው" ስለእነርሱ "አሁን ስለሰሙት ነገር" (ሐዋርያቱ በእስር ቤት ውስጥ እንደሌሉ ስለተነገራቸው ሪፖርት) እንድታሠሩ ያደረጋችኋቸው ሰዎች “እናንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥር የሚያሳይ ነው፡፡
ሥልጣን የሰጣችሁ በዚህ ሥፍራ “እናንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥርን የሚያመለክት ነው፡፡ ሙላችሁ በዚህ ሥፍራ “እናንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥርን የሚያመለክት ነው፡፡ የዚህ ሰው ደም በእኛ ላይ ለማድረግ ትጥራላችሁ "የዚህ ሰው መሞት ምክንያት እኛ እንደሆንን ታደርጋላችሁ"
ለእስራኤል ንሰሓን እና የኃጢአት ይቅርታ አማራጭ ትርጉመም፡ "እስራኤል ከኃጢአቷ ትመለስ ዘንድ እና የኃጢአት ይቅርታን የመቀበል እድል ታገኝ ዘንድ" እንዲሁም መንፈስ ቅዱስ በዚህ ሥፍራ ላይ መንፈስ ቅዱስ የተጠቀሰው የኢየሱስ ተዓምራታዊ ሥራዎች የሚያረጋግጥ አካል ሆኖ ነው፡፡
ተቆጡ ሐዋርያቱ ስለገሰጸዋቸው የሸንጎው አባላት በሐዋርያቱ ላይ በጣም ተቆጡ፡፡ በሰዎች ሁሉ ዘንድ የተከበረ አንድ የሕግ መምህር፣ ይህ ስለገማሊያ የኃላ ታሪክ ነው፤ ይህ መረጃ የተሰጠው አንባቢያን ይህ ሰው ማን እንደሆነ ያውቁ ዘንድ ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ: ገማሊያ የሸንጎ አባላትን እንዲህ አላቸው፡፡ በጥንቃቄ በቅርበት ተከታተሉ "ስለዚህ ነገር በጥንቃቄ አስቡ" (UDB)፣ ወይም "ስለዚህ ነገር ከፍተኛ ጥንቄ አድርጉ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ገማሊያ ለሸንጎ አባላት ያደረገውን ንግግር አጠናቋል፡፡
ከዚህማ አስጠሩአቸዋው በዚህ ሥፍራ ላይ “እነርሱ” የሚለው ቃል የሸንጎ አባላትን ነው፡፡ እንደ ክብር እንቆጥረዋለን ለኢየሱስ መከራን መቀበል ክብር ነው፡፡ ከዚህያን ጊዜ አንስቶ በየዕለቱ "ከዚያ ቀን በኋላ፣ በየዕለቱ፡፡" ይህ ሐዋርያቱ ከዚያን ዕለት በኋላ ባሉት ቀናት ውስጥ በየዕለቱ የሚያደርጓቸውን ነገሮች የሚያመለክት ነው፡፡ ሐዋርያቱ ይህንን ነገር ለማድረግ የተበረታቱት በዚህ ክፍል ውስጥ በተከሰተው ታርክ አማካኝነት ነው፡፡ በቀጣይነት ያስተምሩ ነበር አማራጭ ትርጉም: "ማስተማራቸውን ፈጽመው አላቆሙም"
1 በእነዚህ ወራት፣ የደቀ መዛሙርት ቊጥር እየበዛ በሄደ ጊዜ፣ ከግሪክ የመጡት አይሁድ በዕብራውያን ላይ ማጕረምረም ጀመሩ፤ ምክንያቱም መበለቶቻቸው በየዕለቱ የምግብ ዕደላ ላይ ቸል ተብለውባቸው ነበር። 2 ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ደቀ መዛሙርቱን ሁሉ ጠርተው እንዲህ አሏቸው፤ “የምግብ አገልግሎትን ለመስጠት ብለን የእግዚአብሔርን ቃል መተው ለእኛ ተገቢ አይደለም። 3 ስለዚህ ወንድሞች ሆይ፣ በዚህ ኀላፊነት ላይ ልንሾማቸው የምንችል መልካም አርአያነት ያላቸውን፣ መንፈስና ጥበብ የሞላባቸውን ሰባት ሰዎች ከእናንተ መካከል ምረጡ። 4 እኛ ግን፣ ሁልጊዜ በጸሎትና በቃሉ አገልግሎት እንቀጥላለን።” 5 ንግግራቸው ሕዝቡን ሁሉ ደስ አሰኘ። ስለዚህ እምነትና መንፈስ ቅዱስ የሞላበትን እስጢፋኖስን፣ ፊልጶስን፣ ጵሮኮሮስን፣ ኒቃሮናን፣ ጢሞናን፣ ጳርሜናንና ወደ ይሁዲነት ገብቶ የነበረውን አንጾኪያዊውን ኒቆላዎስን መረጡ። 6 አማኞቹ እነዚህን ሰዎች፣ በጸለዩላቸውና ከዚያም እጃቸውን በላያቸው በጫኑት በሐዋርያት ፊት አቀረቧቸው። 7 ስለዚህም የእግዚአብሔር ቃል አደገ፤ የደቀ መዛሙርት ቊጥርም በኢየሩሳሌም ውስጥ በብዛት ጨመረ፤ ከካህናትም ብዙዎቹ ለእምነት ታዛዦች ሆኑ። 8 እስጢፋኖስ ጸጋንና ኀይልን ተሞልቶ፣ በሕዝቡ መካከል ታላላቅ ድንቆችንና ምልክቶችን ያደርግ ነበር። 9 ነገር ግን ነጻ የወጡት ሰዎች ምኵራብ ከሚባለው ምኵራብ፣ ከቀሬናና ከእስክንድርያ፣ ከኪልቅያና ከእስያም የሆኑ ጥቂት ሰዎች ተነሡ። እነዚህ ሰዎች ከእስጢፋኖስ ጋር ይከራከሩ ነበር። 10 ነገር ግን ሰዎቹ እስጢፋኖስ የተናረገረበትን ጥበብና መንፈስ መቋቋም አልቻሉም። 11 ከዚያም፣ “እስጢፋኖስ በሙሴና በእግዚአብሔር ላይ የስድብ ቃል ሲናገር ሰምተናል” እንዲሉ አንዳንድ ሰዎችን በምስጢር አሳመኑ። 12 ሰዎቹን፣ ሽማግሌዎቹን፣ የሕግ መምህራኖቹንም አነሣሡ፤ እስጢፋኖስንም ይዘው ወደ ሸንጎው አቀረቡት። 13 እንዲህ ብለው የሚናገሩ ሐሰተኛ ምስክሮችንም አመጡ፤ “ይህ ሰው ይህን ቅዱስ ስፍራና ሕጉን ተቃውሞ መናገርን አያቆምም። 14 ምክንያቱም ይህ የናዝሬቱ ኢየሱስ ይህን ስፍራ ያፈርሰዋል፤ ሙሴም ያስተላለፈልንን ሥርዐትም ይለውጠዋል ሲል ሰምተነዋል።” 15 በሸንጎው ውስጥ የተቀመጡት ሁሉ አተኵረው ተመለከቱት፤ ፊቱም እንደ መልአክ ፊት ሆኖ አዩት።
አጠቃላይ መረጃ: ይህ የአዲስ ታሪክ መጀመሪያ ክፍል ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ታሪኩን ለመረዳት የሚያስችሉ የኃላ ታሪክ መመረጃዎች ተሰጥተዋል፡፡ አሁን በእነዚያ ቀናት ይህ የአዲስ ታሪክ መጀመሩን የሚያመለክት ነው፡፡ በእናንተ ቋንቋ አዲስ ታሪክ እንዴት እንደሚጀመር ከግንዛቤ ውስጥ አስገባ፡፡ ማብዛት "በብዛት መጨመር" ግሪካዊያን አይዶች ይህ አብዛኛውን ሕይወታውን ከእስራኤል ውጪ በሚገኙ የሮም ግዛቶች ውስጥ የኖሩትን እና የግሪክ ቋንቋ በመናገር ያደጉት አይሁዶችን ያመለክታል፡፡ ቋንቋቸው እና ባሕላቸው በእስራኤል ውስጥ ካደጉት ሰዎች በተወሰነ መልኩም ቢሆን ይለያል፡፡ ዕብራዊያን ይህ በእስራኤል ውስጥ የአራማይክ ቋንቋ እየተናገሩ ያደጉ አይሁዳዊያንን ያመለክታል፡፡ እስካሁን ድረስ ቤተ ክርስቲያን በውስጧ ያቀፈቻቸው አይሁዳዊያንን እና ወደ አይሁድ ሃይማኖት የተለወጡ ሰዎችን ብቻ ነው፡፡ ባል የሞተበት ሴት እውነተኛ ባል የሞተበት ሴት እንደገና ለማግባት በጣም ያረጀች እና ልደግፋት የሚችል የቅርብ ዘመድ ያሌላት ናት፡፡ ችላ መባል "ቸል መባል" ወይም "መተው፡፡" እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ነገር ግን የተረሱ ሰዎች በተለያዩ ሠስፍራ ነበሩ፡፡ የዕለት ምግብ ማደል ለሐዋርያቱ ከሚሰጠው ገንዘብ ከፊሉ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ላሉ ባሎቻቸው ለሞቱባቸው መበልቶች ምግብ ለመግዛት ይውል ነበር፡፡
ማዕድ ማገልገል ይህ ለሰዎች መግብ ማደለን ለማመልከት የዋለ ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ ጥሩ ምግባር ያላቸው፣ በመንፈስ እና በጥበብ የተሞሉትን አማራጭ ትርጉሞቹ እነዚህ ናቸው 1) እነዚህ ሦሰዎች ሦስት ልዩ ባሕርያት አሏቸው - መልካ ምግባ፣ መንፈስ የሞላባቸው እና ጥበብ የሞላባቸው ናቸው ወይም 2) እነዚህ ሰዎች ሁለት መልካም ባሕርያት አላቸው - መንፈስ የሞላባቸው እና ጥበብ የሞላባቸው ናቸው (UDB)፡፡ መልካም ምግባር "ሰዎች መልካምነታቸውን የሚያውቁላቸው ሰዎች" ወይም "ሰዎች የሚያምኗቸው ሰዎች" እናንተ ተግባራዊ ማድረግ በሚቻልበት ሥፍራ በቋንቋችሁ ብዙ ቁጥር አመልካች ቃን ተጠቀሙ፡፡ እኛ . . . እኛ ተግራዊ ማድረግ በሚቻልበት ሥፍራ የጠወሰኑ ሰዎችን ብቻ የሚያመለክትን ቃልን ተጠቀሙ፡፡
ንግግራቸው ሰዎችን አስደሰተ የተናሩት ነገር ተቀባይነት አገኘ እስጥፋኖስ . . . እና ኒቃሮናን እነዚህ የግሪክ ስሞች ናቸው፡፡ እነዚህ ስሞች የተመረጡት ሰዎች ብዙዎቹ ወይም ሙሉ ለሙሉ ከግሪካዊያን አይሁድ አማኞች ቡድን ውስጥ መሆኑን አመላካች ነው፡፡ ወደ አይሁድ ሃይማኖት የተለወጠ “ወደ አይሁድ ሃይማኖት የተለወጠ አሕዛብ” እጆቻቸውን ጫኑባቸው ባረኳቸው እንዲሁም ለሰባቱም ሥራውን መሥራት እንዲችሉ ኃላፊነት እና ስልጣን አካፈሏቸው፡፡
አጠቃላይ መረጃ: ይህ ዓረፍተ ነገር የቤተ ክርስቲያንን እድገት አስመልክቶ የተሰጠ የጊዜው መረጃ ነው፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ያድግ ነበር ተጽእኖው እየተስፋፋ መጠ፡፡ ለእምነት መታዘዝ "አዲሱን የእምነት መንገድ መከተል"
አጠቃላይ መረጃ: ይህ የአዲስ ታሪክ ጅማሬ ነው፡፡ እነዚህ ቁጥሮች ታሪኩን ለመረዳት ያስችሉ ዘንድ ስለእስጥፋኖስ እና ስለሌሎች ሰዎች የኃላ ታሪክ መረጃዎችን ይሰጣሉ፡፡ የነጻ ወጪዎች "ነጻ የወጡ ሰዎች” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ከተለያዩ በታዎች ከባርነት ነጻ የወጡ ሰዎችን ለማመልከት ነው፡፡ በዚያ ስፍራ ስማቸው የተጠቀሱት ሌሎች ሰዎች የምኩራቡ አባላት ይሁኑ አይሁኑ ወይም ከእስጥፋኖስ ጋር በነበረው ክርክር ውስጥ ተሳታፉዎች ብቻ ይሁኑ ምንም የሚታወቅ ነገር የለም፡፡ ከእስጥፋኖስ ጋር ይከራከሩ ነበር "ከእስጥፋኖስ ጋር ይከራከሩ ነበር" (UDB) ወይም "ከእስጥፋኖስ ጋር ይወያዩ ነበር"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: በ ACT 6:8 ላይ የተጀመረው የኃላ ታሪክ መረጃ የመስጠቱ ነገር እስከ ቁጥር 10 ድረስ ቀጥሏል፡፡ ከዚያም ይህ በታሪኩ ውስጥ የድርግቱ ጅማሬን የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ ልቋቋሙት "ለሙግት ሀሳቡ ምላሽ መስጠት አልተቻላቸውም" መንፈስ "መንፈስ ቅዱስ" በድብቅ በማሳመን "በምስጥር በማሳመን" የስድብ ቃላት አማራጭ ትርገጉሞች: "በእግዚአብሔር እና የሙሴ ሕግጋት ተቃውሞ መናገር"
ሕዝቡን ማነሳሳት "ሕዝቡ እንዲቆጣ ማነሳሳት" ያዙት "ያዙት" ፊቱ የመላእክት ፊት ይመስላል ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ምንም እንኳ በግልጽ “ስለማንጻባረቁ” ባይናገረም ማነጻጸሪያ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እንደ መላእክ ፊት ያበራ ነበር"
1 ሊቀ ካህናቱም፣ “እነዚህ ነገሮች እውነት ናቸውን?” አለ። 2 እስጢፋኖስ እንዲህ ብሎ መለሰ፦ “ወንድሞችና አባቶች ሆይ፣ አድምጡኝ፤ የክብር አምላክ ለአባታችን ለአብርሃም በካራን ከመኖሩ በፊት በመስጴጦምያ ሳለ ተገለጠለት፤ 3 እግዚአብሔርም፣ 'አገርህንና ዘመዶችህን ተውና እኔ ወደማሳይህ ምድር ሂድ' አለው። 4 ከዚያም በኋላ፣ ጊዜ አብርሃም ከከለዳውያን ምድር ወጥቶ በካራን ኖረ፤ ከዚያም፣ አባቱ ከሞተ በኋላ፣ እግዚአብሔር አሁን እናንተ ወደምትኖሩበት፣ ወደዚህ ምድር አመጣው። 5 ከዚህ ምድር ምንም ርስት፣ የእግር ጫማ ለማሳረፍ የሚበቃ እንኳ አልሰጠውም። ነገር ግን አብርሃም ገና ልጅ ያልነበረው ቢሆንም እንኳ፣ እግዚአብሔር ምድሪቱን ርስት አድርጎ ለእርሱና ከእርሱ በኋላ ለዘሮቹ እንደሚሰጥ ቃል ገባ። 6 እግዚአብሔር ለአብርሃም እንደዚህ እየተናገረው ነበር፤ ይኸውም ዘሮቹ ለተወሰነ ጊዜ በባዕድ ምድር እንደሚኖሩ፣ እዚያ ያሉ ኗሪዎችም በባርነት ውስጥ እንደሚያስገቧቸውና ለአራት መቶ ዓመታት እንደሚያስጨንቋቸው ነው። 7 ‘በባርነት የሚኖሩበትን ሕዝብም እፈርድበታለሁ፤ ከዚያም በኋላ ይወጣሉ፤ በዚህም ስፍራ ያመልኩኛል’ አለ እግዚአብሔር። 8 እግዚአብሔር ለአብርሃም የግዝረትን ኪዳን ሰጠው፤ አብርሃምም የይስሐቅ አባት ሆነ ይስሐቅንም በስምንተኛው ቀን ገረዘው፤ ይስሐቅ የያዕቆብ አባት ሆነ፤ ያዕቆብም የዐሥራ ሁለቱ አለቆች አባት። 9 አለቆች በዮሴፍ ላይ በቅናት ተነሣሥተው ወደ ግብፅ ሸጡት፤ እግዚአብሔር ግን ከእርሱ ጋር ነበረ፤ 10 ከመከራውም ሁሉ አዳነው፤ በግብፅ ንጉሥ በፈርዖን ፊትም ሞገስና ጥበብ ሰጠው። ፈርዖንም ዮሴፍን በግብፅና በቤቱ ባለው ሁሉ ላይ ገዥ አደረገው። 11 በመላው ግብፅና በከነዓን ራብና ትልቅ ጭንቀት መጣ፤ አባቶቻችንም ምንም ምግብ አላገኙም። 12 ነገር ግን ያዕቆብ እህል በግብፅ ውስጥ እንደ ነበረ ሲሰማ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ አባቶቻችንን ላካቸው። 13 በሁለተኛው ጊዜ ዮሴፍ ለወንድሞቹ ራሱን ገለጠ፤ የዮሴፍ ቤተ ሰብም ከፈርዖን ጋር ተዋወቀ። 14 ከዘመዶቹ ሁሉ ጋር፣ ሰባ ዐምስት ሰዎች ሆኖ ወደ ግብፅ እንዲመጣ፣ ለአባቱ ለያዕቆብ እንዲነግሩ ዮሴፍ ወንድሞቹን መልሶ ላካቸው። 15 ስለዚህ ያዕቆብ ወደ ግብፅ ወረደ፤ ከጊዜ በኋላም፣ እርሱና አባቶቻችን በዚያ ሞቱ። 16 ወደ ሴኬም ተወስደውም አብርሃም በሴኬም ከኤሞር ልጆች በብር ገዝቶት በነበረው መቃብር ተቀበሩ። 17 እግዚአብሔር ለአብርሃም ገብቶት የነበረው የተስፋ ቃል ጊዜ ሲቃረብ፣ ሕዝቡ በግብፅ ውስጥ በቍጥር እያደጉና እየበዙ ሄዱ፤ 18 በግብፅ ሌላ ንጉሥ፣ ስለ ዮሴፍ ያላወቀ ንጉሥ እስከ ተነሣ ድረስ። 19 ይኸው ንጉሥ ሕዝባችንን አታለለ፤ አባቶቻችንንም አስጨነቀ፤ ሕዝቡም ሕፃናታቸውን በሕይወት እንዳይኖሩ ወደ ውጭ መጣል ነበረባቸው። 20 በዚያ ጊዜ ሙሴ ተወለደ፤ እርሱ በእግዚአብሔር ፊት በጣም ያማረ ነበር፤ በአባቱ ቤትም ሦስት ወር አደገ። 21 ሙሴ ወንዝ ውስጥ ሲጣል፣ የፈርዖን ሴት ልጅ ወስዳ እንደ ልጇ አሳደገችው። 22 ሙሴ በግብፃውያን ትምህርት ሁሉ የሠለጠነ፣ በንግግሩና በሥራውም ታላቅ ሰው ነበር። 23 አርባ ዓመት ሲሆነው ግን ወንድሞቹን፣ የእስራኤልን ልጆች የመጐብኘት ዐሳብ ወደ ልቡ መጣ። 24 አንድ እስራኤላዊ ሲጠቃ አይቶ፣ ሙሴ ተከላከለለት፤ ያጠቃውንም ግብፃዊ ተበቀለው፤ 25 ሙሴ በእርሱ እጅ እግዚአብሔር እያዳናቸው መሆኑን ወንድሞቹ ያስተውላሉ ብሎ ዐሰበ፤ እነርሱ ግን አላስተዋሉም። 26 በሚቀጥለው ቀን ሙሴ እየተጣሉ ወደ ነበሩ እስራኤላውያን መጣ፤ እርስ በርስ ሊያስታርቃቸውም ሞከረ፤ ‘እናንተ ሰዎች ሆይ፣ ወንድማማቾች ናችሁ፤ እርስ በርስ ለምን ትጐዳዳላችሁ?’ አለ። 27 ባልንጀራውን የጐዳው ግን ሙሴን ገፈተረው፤ እንደዚህም አለው፤ 'በእኛ ላይ ገዥና ዳኛ ያደረገህ ማን ነው? 28 ግብፃዊውን ትናንት እንደ ገደልኸው እኔንም ልትገድለኝ ትፈልጋለህን?' 29 ሙሴ ይህን ከሰማ በኋላ ሸሽቶ ሄደ፤ የሁለት ልጆች አባት በሆነበት በምድያም ምድር መጻተኛ ሆነ። 30 አርባ ዓመት ሲያልፍ፣ በሲና ተራራ ምድረ በዳ፣ በቊጥቋጦ ውስጥ በእሳት ነበልባል መልአክ ታየው። 31 ሙሴ እሳቱን ሲያይ፣ በሚታየው ተደነቀ፤ ሊመለከተው ሲቀርብም፣ እንዲህ የሚል የጌታ ድምፅ መጣ፤ 32 ‘እኔ የአባቶችህ አምላክ፣ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅም አምላክ፣ የያዕቆብም አምላክ ነኝ።’ ሙሴ ተንቀጠቀጠ፣ መመልከትም አልቻለም። 33 ጌታም ለሙሴ እንዲህ አለው፤ ‘የቆምህበት ስፍራ ቅዱስ ነውና ጫማህን አውልቅ። 34 በግብፅ ውስጥ ያሉትን የሕዝቤን ሥቃይ በእርግጥ አይቻለሁ፤ የሥቃይ ጩኸታቸውን ሰምቻለሁ፤ ላድናቸውም ወርጃለሁና አሁን ና፤ ወደ ግብፅ እልክሃለሁ።’ 35 “በእኛ ላይ ገዥና ዳኛ ያደረገህ ማን ነው?” ባሉት ጊዜ ተቀባይነትን ያሳጡት ይህ ሙሴ፦ እግዚአብሔር ገዥም ታዳጊም አድርጎ የላከው ነው። እግዚአብሔር ሙሴን በቊጥቋጦው ውስጥ በታየው መልአክ እጅ ላከው። 36 በግብፅና በቀይ ባሕር፣ በአርባ ዓመታቱ ወቅትም በምድረ በዳ ተአምራትንና ምልክቶችን ካደረገ በኋላ፣ ሙሴ ሕዝቡን ከግብፅ አወጣቸው። 37 ‘እግዚአብሔር ከወንድሞቻችሁ መካከል እንደ እኔ ያለ ነቢይ ያስነሣላችኋል’ ብሎ ለእስራኤል ሕዝብ የተናገረው ያው ሙሴ ነው። 38 ይህ ሰው ሲና ተራራ ላይ ያናግረው ከነበረው መልአክ ጋር በምድረ በዳው በጉባኤ ውስጥ የነበረ ሰው ነው። ሰው ከአባቶችችን ጋር ነበረ፤ ለእኛ ሊሰጥ ሕያው ቃልን የተቀበለ ሰውም ነው። 39 ይህ አባቶቻችን ለመታዘዝ እንቢ ያሉት ሰው ነው፤ እነርሱም ገፉት፤ በልባቸውም ወደ ግብፅ ተመለሱ። 40 በዚያ ጊዜ አሮንን እንዲህ አሉት፤ ‘የሚመሩንን አማልክት ሥራልን። ከግብፅ ምድር መርቶ ያወጣን ይህ ሙሴ፣ ምን እንዳጋጠመው አናውቅም።' 41 ስለዚህ እስራኤላውያን በእነዚያ ቀኖች ጥጃ ሠርተው ለጣዖቱ መሥዋዕት አቀረቡ፤ ከእጆቻቸው ሥራ የተነሣም ደስ አላቸው። 42 እግዚአብሔር ግን ዘወር አለ፤ የሰማይ ከዋክብትን እንዲያመልኩም አሳልፎ ሰጣቸው፤ በነቢያት መጽሐፍ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፦ የእስራኤል ቤት ሆይ፣ አርባ ዓመት በምድረ በዳ፣ የታረዱ እንስሳትንና መሥዋዕቶችን አቀረባችሁልኝን? 43 የሞሎክን ድንኳን፣ ሬምፉም የሚባለውን አምላክ ኮከብም፣ ልታመልኳቸው የሠራችኋቸውን ምስሎችም ተቀበላችሁ፤ እኔም ከባቢሎን ወዲያ እሰድዳችኋለሁ።’ 44 አባቶቻችን የምስክሩ ድንኳን በምድረ በዳ ነበራቸው፤ ይኸውም ባየው ምሳሌ መሠረት መሥራት እንዳለበት እግዚአብሔር ሙሴን ሲያናግረው እንዳዘዘው ያለ ነው። 45 ይህ አባቶቻችን በተራቸው ከኢያሱ ጋር ወደ ምድሪቱ ያመጡት ድንኳን ነው። እግዚአብሔር በአባቶቻችን ፊት ባስወጣቸው አሕዛብ አገር ውስጥ ሲገቡ፣ ይህ ሆነ። እስከ ዳዊት ዘመን ድረስ እንደዚህ ነበር፤ 46 ዳዊት በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ አገኘ፤ ለያዕቆብ አምላክም ማደሪያ ስፍራን ለማግኘት ለመነ። 47 ነገር ግን ሰሎሞን ለእግዚአብሔር ቤት ሠራለት። 48 ይሁን እንጂ፣ ልዑሉ በእጅ በተሠሩ ቤቶች ውስጥ አይኖርም፤ ይህም ነቢዩ እንዲህ ብሎ እንደሚናገረው ነው፦ 49 ሰማይ ዙፋኔ፣ ምድርም የእግሬ መርገጫ ነው። ምን ዐይነት ቤት ልትሠሩልኝ ትችላላችሁ? ይላል ጌታ፤ ወይስ የማርፍበት ስፍራ የት ነው? 50 እጄ እነዚህን ሁሉ አልሠራችምን? 51 እናንተ ዐንገተ ደንዳኖች፣ ልባችሁንና ጆሮዎቻችሁን ያልተገረዛችሁ፣ ሁልጊዜ መንፈስ ቅዱስን ትቃወማላችሁ፤ አባቶቻችሁ እንዳደረጉትም ታደርጋላችሁ። 52 ከነቢያት የእናንተ አባቶች ያላሳደዱት የትኛው ነው? እነርሱ ከጻድቁ መምጣት ቀድመው የተናገሩ ነቢያትን ገድለዋል፤ እናንተም አሁን ጻድቁን የምትክዱና የምትገድሉ ሆናችኋል፤ 53 መላእክት ያጸኑትን ሕግ ብትቀበሉም አልጠበቃችሁትም።” 54 አሁን የሸንጎው አባላት እነዚህን ነገሮች ሲሰሙ፣ በልባቸው እጅግ ተቈጡ፣ ጥርሳቸውንም በእስጢፋኖስ ላይ አፋጩ። 55 እስጢፋኖስ ግን በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ፣ ወደ ሰማይ አተኵሮ ተመለከተ፣ የእግዚአብሔርንም ክብር አየ፤ ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየው። 56 እስጢፋኖስ፣ “እነሆ፣ ሰማያት ተከፍተው፣ የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየሁ” አለ። 57 የሸንጎው አባላት ግን በታላቅ ድምፅ ጮኹ፤ ጆሮአቸውንም በመድፈን በአንድነት እየሮጡ ወደ እስጢፋኖስ ሄዱ፤ 58 ከከተማው አውጥተውም በድንጋይ ወገሩት፤ ምስክሮችም ልብሳቸውን ሳውል በሚባል አንድ ወጣት እግር አጠገብ አኖሩ። 59 እስጢፋኖስን ሲወግሩት፣ ወደ እግዚአብሔር ይጣራ፣ “ጌታ ኢየሱስ ሆይ፣ ነፍሴን ተቀበል” እያለ ይናገርም ነበር። 60 ተንበረከከና በታላቅ ድምፅ፣ “ጌታ ሆይ፣ ይህን ኀጢአት አትቊጠርባቸው” ብሎ ጮኸ። ይህን ተናግሮም፣ አንቀላፋ።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: በ ACT 6:8 ላይ የተጀመረው ስለእስጥፋኖስ የተነገረው ታሪክ ይቀጥላል፡፡ አጠቃላይ መረጃ: በቁጥር 2 ላይ እስጥፋኖስ ለሊቀ ካህኑ እና ሸንጎው ምላሽ መስጠቱን ይጀምራል፡፡ ንግግሩንም የጀመረው በእስራኤል ታሪክ ውስጥ ስለተፈጸሙ ነገሮች በመናገር ነው፡፡ ወንድሞች እና አባቶች አድምጡኝ እስጥፋኖስ ንግግሩን የጀመረው ለእነርሱ አክብሮት እንዳለው በሚያሳይ መልኩ እንደዘመዶቹ ሰላምታ በማቅረብ ነው፡፡ አባታችን እስጥፋኖስ አድማጮቹን “አባታችን አብረሃም” በሚለው ንግግሩ ውስጥ አካቷቸዋል፡፡ ምድርህንና ዘመዶችህን ተው "የአንተን" የሚለው ቃል የሚያመለክተው አብረሃምን ነው (ነጠላ ቁጥር)፡፡
አሁን የምትኖርባት በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የአይሁድ ሸንጎን እና በሥፍራው ላይ ያሉትን የሚያደምጡትን ሰዎችን ነው፡፡ ርስቱ ይሆን ዘንድ መሬቱ ለዘላለም የአብረሃም ይሆን ዘንድ፡፡
ለእርሱ ባሮች ይሆናሉ "የአንተ ዘሮች ባሮች ይሆናሉ" ስለዚህም አብረሃም የይሳቅ አባት ሆነ ታሪኩ የአብረሃ ዘሮች ታሪክ መሸጋገሪያ ነው፡፡
አባቶች "የያዕቆብ ወንድ ልጆች" or "Joseph's older brothers"
ረሃብ ሆነ "ረሃብ መጣ፡፡" ምድርቷ ፍሬ መስጠት አቆመች፡፡ አባቶቻችን "የዮሴፍ ታላለቅ ወንድሞች" ስንዴ አማራጭ ትረጉም: "ምግብ" ራሱን ገለጠላቸው ዮሴፍ ለወንድሞቹ ማንነቱን ገለጠላቸው፡፡
እርሱ ራሱ እና አባቶቻችን "ያዕቆብ እና የእርሱ ልጆች፣ አባቶቻችን" ተሸክመው ወሰዱት "የያዕቆብ ልች የያዕቆብን እና የወንድ ልጆቹን አጽም ተሸክመው ወሰዱ" በብር "ገንዝብ"
የተስፋው ሰዓት እግዚአብሔር ለአብረሃም የገባው ቃል መፈጸሚያ ሰዓት በተቃረበ ጊዜ፡፡ ስለዮሴፍ የማያውቅ "ዮሴፍ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው የዮሴፍን መልካም ሥራ የማያውቅ የሚለውን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ዮሴፍ በግብጽ ምድር ውስጥ የነበረውን ስልጣን የማያውቅ፡፡" ሕዝባችንን "የእኛን" የሚለው ቃል እስጥፋኖስን እና ንግግሩን በማድመጥ ላይ ያሉትን ሰዎች የሚያካትት ነው፡፡ አባቶቻችን ጨቆናቸው "አባቶቻችንን አሰቃያቸው" ወይም "አባቶቻችንን በዘበዛቸው" ልጆቻችን አውጥተው ይጥሉ ነበር ልጆቻቸው ይሞቱ ዘንድ አውጥተው ይጥሉ ነበር
በዚያን ጊዜ ይህ አዲስ ሰውን (ሙሴን) ለማስተዋወቅ ጥቅም ላይ የዋለ ቃል ነው፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ያማረ ነው "በእግዚብሔር ፊት" የሚለው ቃል የሙሴን ቁንጅና ለማሳየት የገባ ቃል ነው፡፡ When he was thrown out ሙሴ “የተጣለው” ከፈርኦን ትዕዛዝ የተነሣ ነው፡፡ ወሰዱት "ለማሳደግ ወሰዱት" (መምናልባም ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ ሊሆን ይችላል) እንደ ገዛ ልጇ "የገዛ ልጇ እስኪመስል ድረስ"
ሙሴ ተማረ "ግብጻዊያን ሙሴን አስተማሩት" የግብጻዊያንን ጥበብ ሁሉ ይህ “ግብጻዊያን የሚያውቋቸውን ብዙ ነገሮች” ለማሳየት የቀረበ ግነት የሞላበት ንግግር ነው፡፡ በቃሉ እና በሥራው የበረታ "በተግባሩ እና በንግግሩ ውጤታማ የሆነ" ወይም "በቃሉ እና በተግባሩ" ኃይለኛ የሆነ (UDB) ወይም "በሚያደርቸው እና በሚናገራው ነገሮች ተጽእኖ ፈጣሪ የሆነ" ወንድሞቹን ጎበኛቸው የአኗኗር ሁኔታቸውን ለመመልከት ግብጻዊውን መታው ሙሴ ግብጻዊውን ሰው በኃይል መታው ስለዚህም ሰውዬው ሞተ፡፡ አሰበ "አሰላሰለ" በእጁ "በእርሱ በኩል" ሊያድናቸው አማራጭ ትርጉም: "ወዲያውም ልታደጋቸው"
እናነተ፣ ወንድማማቾች ናችሁ ይህ እርስ በእርሳቸው ስጣሉ የነበሩትን እስራኤላዊንን የሚያመለክት ነው፡፡ መጎዳት መጉዳት የሚለው ቃል አንድን ሰው ላይ ፍትሐዊ ያልሆነ ነገር ማድረግ ወይም ታማኝነት ማጉደል ማለት ነው፡፡ አንተን በእኛ ላይ ገዥ እና ፈራጅ ያደረገህ ማን ነው? ይህ ጥያቄ ጥቅም ላይ የዋለው ሙሴን ለመገሰጽ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በእኛ ላይ ምንም ዓይነት ስልጣን የለህም!" በእኛ ላይ ፈራጅ ያደረግ? እስራኤላዊያን ሙሴ የእነርሱ እንደሆነ አያስቡም ነበር፡፡
ይህንን ከሰማ በኋላ በዚህ ሥፍራ ላይ በተዘዋዋር መልኩ የተገለጸው መረጃ "ከዚያ አንድ ቀን በፊት ሙሴ ግብጻዊውን ሰው መግደሉን እስራኤላዊያን ሰምተዋል ማለት ነው፡፡" አርባ ዓመታት ካለፉ በኋላ "ሙሴ ከግብጽ ምድር ከሸሸ በኋላ አርባ ዓመታት ካለፉ በኋላ"
በተመለከተው ነገር ተደነቀ ሙሴ ቁጥቋጦው በእሳት አለመንደዱን በመመልከቱ በጣም ተደነቀ፡፡ ይህ የእስጥፋኖስን ንግግር በማድመጥ ላይ በነበሩት ሰዎች ዘንድ አስቀድሞ የታወቀ ነበር፡፡ ተጠግቶ ስመለከት . . . ሙሴ እጅግ ከመፍራቱ የተነሣ ወደ ቁጥቋጦው ለመመልከት አልደፈረም ይህ ምናልባት ሙሴ በመጀመሪያ ወደ ቁትቋጦው ምን እንደሆነ ለማየት መጠጋቱን ነገር ግን ከፍርሃቱ የተነሣ ወደ ኋላ መመለሱን የሚያሳይ ሊሆን ይችላል፡፡ በጣም ፈራ ሙሴ ከፍርሃቱ የተነሣ ተንቀጠቀጠ፡፡
የቆምክበት ሥፍራ የተቀደሰ ነው በዚህ ንግግር ውስጥ በተዘዋዋር መንገድ የተገለጠው መረጃ ሥፍራው የእግዚአብሔር መገኘት ያለበት፣ የእግዚአብሔር ሕልውና ያለበት ወይም በእግዚአብሔር የተቀደሰ ሥፍራ ነው፡፡ በእርግጠኝነት ተመለከተ "በእርግጠኝነት" “የመመልከቱን” ዓይነት በመግለጽ አጽኖት የሚሰጥ ነው፡፡ ሕዝቤን "የአብረሃም፣ የይሳቅ እና የያዕቆብ የልጅ ልጆች" እኔ ራሴ መጥቻለሁ "በግሌ ነጻ እንደወጡ ለማየት"
አጠቃላይ መረጃ: ቁጥር 35-38 ላይ ከሙሴ ጋር ተያያዥነት ያላቸው የተለያዩ ተከታታይ ሀረጎች ይገኛሉ፡፡ በእያንዳንዱ ሀረጎች መጀመሪያ ላይ “ይህ ሙሴ” ወይም “ይኼው ሙሴ” የሚለው ነገር እናገኛን፡፡ ከተቻለ ተመሳሳይ አጽኖት መስጠት ያስችል ዘንድ ተመሳሳይ ቃላትን እናንተ ተጠቀሙ፡፡ እነረሱ ያልተቀበሉት ይህ ሙሴ ይህ በ ACT 7:26-28 ላይ የተጠቀሰውን ያመለክታል፡፡ ገዥ እና ፈራጃ ያደረገህ ማን ነው? ይህንን በ ACT 7:26 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ገዥ እና ነጻ አውጪ "በእርሱ ላይ የሚገዛ እና ከባርነት ነጻ የሚያወጣ" በመለአክት እጅ "በመለአክት አማካኝነት" በአራባ ዓመታት ውስጥ "እስራኤላዊያን በምድረ በዳ ውስጥ በኖሩባቸው አርባ ዓመታት" (UDB) ከወንድሞቻችሁ መካከል "ከእናንተው ወንድሞች መካከል" (UDB)
አጠቃላይ መረጃ: ቁጥር 35-38 ላይ ከሙሴ ጋር ተያያዥነት ያላቸው የተለያዩ ተከታታይ ሀረጎች ይገኛሉ፡፡ በእያንዳንዱ ሀረጎች መጀመሪያ ላይ “ይህ ሙሴ” ወይም “ይኼው ሙሴ” የሚለው ነገር እናገኛን፡፡ ከተቻለ ተመሳሳይ አጽኖት መስጠት ያስችል ዘንድ ተመሳሳይ ቃላትን እናንተ ተጠቀሙ፡፡ ይህ በጉባኤው መካከል ያለ ሰው ነው፡፡ "ይህ ከእስራኤላዊን መካከል የነበረው ሙሴ ነው፡፡" (UDB) ይህ ለእኛ ለመስጠት ሕያው የሆነውን ቃል የተቀበለው ሰው ነው አማራጭ ትርጉም: "ይህ ለእኛ እንዲሰጥ እግዚብሔር ሕያው ቃልን የተናገረው ሰው ነው" ሕያው ቃላትን አማራጭ ትርጉሞች 1) "ጸንቶ የሚቆም ቃል" ወይም 2) "ሕይወት የሚሰጥ ቃላት፡፡" ከራሳቸው ገፍተው አራቁት ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ሙሴን አለመቀበላቸውን አጽኖት የሚሰጥ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ሙሴን መሪያቸው አድርው አልተቀበሉትም" በዚያ ጊዜ "ወደ ግብጽ ለመመለስ በወሰኑ ጊዜ"
አጠቃላይ መረጃ: በቁጥር 42 ላይ እስጥፋስ ከነቢያት መጽሐፍ፣ በተለይም ከአሞጽ መጽሐፍት መጥቀስ ጀመረ፡፡ የወርቅ ጥጃ ሠሩ "ጥጃ የሚመስል ሐውልት ሠሩ" በሰማይ የሚገኙ ክዋክብትን አመለኩ "ክዋክብትን እንደ አማልክት አድርገው ማምለክ ጀመሩ" የታደውን ከብት እና መስዋእትን አቀረባችሁልጅ . . . እስራኤል? እግዚአብሔር በዚህ ጥያቄ አማካኝነት ያቀረበው ሀሳብ እስራኤላዊያን በመሰዋእትን እርሱ አለማመለካቸውን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "እናንተ እስራኤላዊያን. . . የሚታድ መስዋእትን አላቀረባችሁልኝም፡፡" የእስራኤል ቤት ይህ አጠቃላይ እስራኤላዊንን የሚያመለክት ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ እስጥፋኖስ በ ACT 7:2 ላይ የጀመረውም ለሊቀ ካህኑ እና ሸንጎው ምላሽ የሰጠበትን ንግግሩን ቀጥሏል፡፡ እንዲሁም እስጥፋኖስ ከነቢያት መጽሐፍ በመውሰድ በ ACT 7:42 ላይ የጀመረውን ንግግር በዚህ ክፍል ውስጥ አጠናቋል፡፡ የሞልኮን ድንኳን ሞልኮን የተሰኘው የሐሰት አምላክ ድንኳን፡፡ ሬምፉም የሚሉትን የአምላካችሁን ኮከብ ይህ ኮከብ ሬምፋም የተሰኘው የሐሰት አምላክ ነው ይላሉ የሠራችኋቸውን ምስሎች የሞልኮን እና ሬምፋም አማልክት ምስሎችን ለማምለክ በእጆቻቸው አበጅተዋቸው ነበር፡፡ እኔም ከባቢሎን ወዲያ እሰዳችኋለሁ "ወደባቢሎን መድር እሰዳችኋለሁ"
የምስክር ድንኳን ዐሥርቱ ትዕዛዛትን በላዩ ላይ የያዘው ድንጋይ የሚቀመጥበት ድንኳን ቤት፡፡ የሀገርቱ ንብረቶች ይህ ምድርቷን፣ ሕንተጻዎቿን፣ ሰብሏን፣ እንስሳቶቿ እንዲሁም እስራኤላዊያን የያዝዋቸውን ሥፍራዎች ውስጥ ያሉትን ሀብቶች ያካትታል፡፡ ታቦቱ እስከ የእስራኤል ንጉሥ ዳዊት ዘመን ድረስ፣ የዳዊትን ዘመን ጨምሮ በድንኳን ውስጥ ነበር፡፡ የያዕቆብ አምላጅ ማደሪያ ሥፍራ ዳዊት ታቦቱ በእስራኤል ውስጥ ከቦታ ቦታ ከሚዘዋወር ይልቅ በእየሩሳሌም እንዲሆን ፈልጎ ነበር፡፡
አጠቃላይ መረጃ: በቁጥር 49 እና 50 ላይ እስጥፋኖስ ከነቢዩ እሳያስ መጽሐፍ በመጥቀስ ተናግሯል፡፡ በዚህ ጥቅስ ውስጥም እግዚአብሔር ስለራሱ ይናገራል፡፡ በእጅ የተሠራ ቤት ውስጥ "በሰዎች በተሠራ" ሰማይ ዙፋኔ ነው . . . ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት ነብዩ የእግዚአብሔር መገኘት ትልቅነት በማሳየት ምድርና ሞላዋ የእግዚአብሔር የእግሩ መረገጫ መሆኗ በማሳየት የሰው ልጅ በምድር ላይ ለእግዚአብሔር ማደሪያ ሥፍራ ማዘጋጀት እንደማይችል አሳይቷል፡፡ ለእኔ ምን ዓይነት ቤት ትሠሩልኛላችሁ? እግዚአብሔር በዚህ ጥያቄ መሠረት ያሳየው ዬትኛውም የሰው ልጅ ጥሬ የእግዚአብሔርን ባሕርይ ማሟላት እንደማይችል ነው!" ለእኔ ማረፊያ ሥፍራ ከየዬት ይገኛል? እግዚአብሔር ይህንን ጥያቄ የጠየቀው የሰው ልጅ ለእግዚአብሔር ማረፊያ ማዘጋጀት እንደማይችል ለማሳየት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ለእኔ በቂ ማረፊያ የሚሆን ሥፍራ የለም!" እነዚህ ሁሉ ነገሮች የፈጠርኳቸው እኔ አይደለሁምን? እግዚአብሔር ይህንን ጥያቄ የጠየቀው የሰው ልጅ የፈጠረው አንዳችም ነገር አለመኖሩን ለማሳየት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እጆቼ ይህንን ሁሉ ነገር ፈጥራለች!"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: እስጥፋኖስ ለካህናት አለቃው እና ለሸንጎው በ ACT 7:2 ላይ ምላሽ መስጠት የጀመረበትን ንግግር የሚበቃበት ነው፡፡ እናንተ አንገተ ደንዳኖች አንገተደ ደንዳኖች - እስጥፋኖስ ራሱን ከእርሱ እንደ አንዱ ማድረጉን ትቶ የአይሁድ መሪዎችን ወደ መገሰጽ ዞሯል፡፡
ልባችሁ ያልተገረዘ "የማይታዘዝ ልብ ያላችሁ፡፡" በዚህ ንግግር እስጥፋኖስ ምናልባት እነርሱ ከአሕዛብ ጋር እያነጻጸረ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህንን ንግግሩን ምናልባት እንደ ስድብ ልቆጥሩት ይችላሉ፡፡ ከነቢያት መካከል አባቶቻችሁ ያላሳደዷቸው ነቢያት ዬትኞቹ ናቸው? እስጥፋኖስ ይህንን ጥያቄ የጠየቀበት ምክንያት ከአባቶቻቸው ስህተት አለመማራቸውን ለማሳየት ነው፡፤ አማራጭ ትርጉም፡ "ቀደምት አባቶቻችሁ ሁሉንም ነቢያት ያሳድዱ ነበር!" ቅዱሱን ይህ ክርስቶስን፣ መስሑን ያመለክታል፡፡ የእርሱ ገዳዮች "የቅዱሱ ገዳዮች" ወይም "የክርስቶስ ገዳዮች"
እነዚህን ነገሮች ሰሙ ይህ ነገሩ የተለወጠበት ሥፍራ ነው፤ ስብከቱ ያበቃበት እንዲሁም ሸንጎም አጸፋዊ ምላሽ የሰጡበት ነው፡፡ በልባቸው ቆረጡ ይህ “ሁሉም በንግግሩ መበሳጨታቸውን” የሚያሳይ ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ ጥርሳቸውን አፋጩበት ይህ ከፍተኛ ንዴት ወይም ጥላቻ ማሳያ መንገድ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "በጣም ከመናደዳቸው የተነሣ ጥርሳቸውን አፋጩበት፡፡" ወደ ሰማይ ትኩር ብሎ እየተመለከ "ወደ ሰማይ እያየ፡፡" ይህንን ራዕይ የተመለከተው እስጥፋኖስ ብቻ ይመስላል፡፡ ከሕዝቡ መካከል ይህንን ያየ ሰው ያለ አይመስልም፡፡ የእግዚአብሔር ክብር "የእግዚአብሔር ክብር እንደ ብርሃን፡፡" አማራጭ ትርጉም፡ "ከእግዚአብሔር ዘንድ የሆነ ደማቅ ብርሃን፡፡" ኢየሱስ ቆሞ ተመለከተ ኢየሱስ በእግዚአብሔር ቀኝ “ሞ” እንደነበር አስተውሉ፡፡ ይህ ንጉሥ እንግዳ ሰው ሲመጣ በክብር ለመቀበል የሚደርገው ነገር ነው፡፡ የሰው ልጅ እስጥፋኖስ ኢየሱስን “የሰው ልጅ” ብሎ ይጠራዋል፡፡
ጆሮዋቸው ቆመ ከዚያ በኋላ እስጥፋኖስ የሚናገረውን ነገር ላለመስማት ጆሮዋቸውን ያዙ፡፡ ከከተማው ውጪ አወጡት "የሸንጎ አባላቱም እስጥፋኖስን በመያዝ ከከተማው ውጪ በጉልበት ይዘውት ወጡ" መደረቢያቸውን ይህ ከውጪ እንደ ጃኬት ወይም ኮት ከውጪ ተደርቦ የሚለበስ ልብስ ነው፡፡ በእግር ሥር "ፊት ለፊት" ለመጠበቅ ይመቻቸው ዘንድ
መንፈሴን ተቀበል "መንፈሴን ውሰድ" አንቀላፋ ይህ በጨዋ ደንብ “መሞቱን” ለመግለጽ ነው፡፡
1 ሳውል በእስጢፋኖስ ሞት ተስማምቶ ነበር። በዚያም ጊዜ በኢየሩሳሌም በነበረችዋ ቤተ ክርስቲያን ላይ ታላቅ ስደት ተነሣ፤ አማኞችም ሁሉ ከሐዋርያት በቀር በይሁዳና በሰማርያ ተበታተኑ። 2 በመንፈሳዊ ነገር የተጉ ሰዎች እስጢፋኖስን ቀበሩት፤ መሪር ልቅሶም አለቀሱለት። 3 ሳውል ግን ቤተ ክርስቲያንን በጣም ጐዳ፤ ከቤት ወደ ቤት በመሄድም ክርስቲያን ወንዶችንና ሴቶችን ጐትቶ አወጣቸው፤ ወኅኒ ቤት ውስጥም አስገባቸው። 4 የተበታተኑት አማኞች ግን ቃሉን እየሰበኩ በየቦታው ዞሩ። 5 ፊልጶስ ወደ ሰማርያ ከተማ ወረደ፣ ለሕዝቡም ክርስቶስን ሰበከላቸው። 6 እጅግ ብዙ ሰዎች ፊልጶስን ሲሰሙትና ያደረጋቸውንም ምልክቶች ሲያዩ፣ በአንድነት እርሱ ለተናገረው ትኵረት ሰጡ። 7 ምክንያቱም ከብዙ ሰዎች ርኩሳን መናፍስት እየጮኹ ወጥተው፣ አያሌ ሽባዎችና ዐንካሶችም ተፈውሰው ነበር። 8 ስለዚህ በዚያች ከተማ ውስጥ ብዙ ደስታ ነበር። 9 ነገር ግን በዚያች ከተማ ውስጥ ቀደም ሲል የጥንቈላ ሥራ ይሠራ የነበረ ሲሞን የሚባል ሰው ነበረ፤ ተፈላጊ ሰው እንደ ሆነ እየተናገረ የሰማርያን ሰዎች ያስደንቅ ነበር። 10 ሳምራውያን በሙሉ ከትንሹ እስከ ትልቁ፣ “ይህ ሰው ታላቅ የሚባለው የእግዚአብሔር ኀይል ነው” እያሉ በሚገባ ያደምጡት ነበር። 11 በጥንቈላ ሥራው ለረጅም ጊዜ ያስገርማቸው ስለ ነበር አደመጡት። 12 ስለ እግዚአብሔር መንግሥትና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ፊልጶስ የሰበከውን ወንጌል ሲያምኑ ግን ወንዶችም ሴቶችም ተጠመቁ። 13 ሲሞንም ደግሞ አመነ፤ ከተጠመቀም በኋላ ከፊልጶስ ጋር መሆንን ቀጠለ፤ የተደረጉ ምልክቶችንና ታላላቅ ተኣምራትን ባየ ጊዜም ተደነቀ። 14 በኢየሩሳሌም የነበሩ ሐዋርያት ሰማርያ የእግዚአብሔርን ቃል የተቀበለች መሆኗን ሲሰሙ፣ ጴጥሮስንና ዮሐንስን ላኩላቸው። 15 እነርሱም እዚያ ወርደው መንፈስ ቅዱስን እንዲቀበሉ ጸለዩላቸው። 16 መንፈስ ቅዱስ እስከዚያ ጊዜ ድረስ በማንኛቸውም ላይ አልወረደም ነበርና፣ እነርሱ በጌታ ኢየሱስ ስም ብቻ ተጠምቀው ነበር። 17 ከዚያም ጴጥሮስና ዮሐንስ እጃቸውን ጫኑባቸው፣ መንፈስ ቅዱስንም ተቀበሉ። 18 በሐዋርያት እጅ መጫን መንፈስ ቅዱስ እንደሚሰጥ ሲያይ፣ ሲሞን ገንዘብ አቀረበላቸው። 19 “እኔም እጁን የምጭንበት ሰው ሁሉ መንፈስ ቅዱስን መቀበል እንዲችል ይህን ሥልጣን ስጡኝ” አላቸው። 20 ነገር ግን ጴጥሮስ እንዲህ አለው፤ “የእግዚአብሔርን ስጦታ በገንዘብ ለማግኘት አስበሃልና ብርህ ከአንተ ጋር ይጥፋ። 21 ልብህ ለእግዚአብሔር የቀና አይደለምና በዚህ ጉዳይ ውስጥ ዕድል ወይም ድርሻ የለህም። 22 እንግዲህ ለዚህ ክፋትህ ንስሓ ግባ፤ ምናልባትም ለልብህ ዐሳብ ይቅር ይልህ እንደ ሆነ ጌታን ለምን። 23 በኀጢአት እስራትና በመራርነት መርዝ ውስጥ እንዳለህ አያለሁና።” 24 ሲሞንም መልሶ፣ “ከተናገራችኋቸው አንዱም በእኔ ላይ እንዳይፈጸም ወደ ጌታ ጸልዩልኝ” አላቸው። 25 ጴጥሮስና ዮሐንስ ከመሰከሩና የጌታን ቃል ከተናገሩ በኋላ፣ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፤ በመንገድም ለብዙ የሰማርያ መንደሮች ወንጌልን ሰበኩ። 26 የጌታ መልአክ ፊልጶስን፣ “ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ በሚወስደው መንገድ ወደ ደቡብ አቅጣጫ ተነሥና ሂድ” አለው። (ይህ መንገድ በበረሓ ውስጥ ነው።) 27 እርሱም ተነሣና ሄደ። እነሆ፣ በኢትዮጵያውያን ንግሥት በሕንደኬ ሥር ትልቅ ሥልጣን የነበረው አንድ ኢትዮጵያዊ ጃንደረባ ነበረ። ሰውዬው በንግሥቲቱ ንብረት ሁሉ ላይ ኀላፊነት ነበረው። ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር። 28 ከኢየሩሳሌም በመመለስ ላይ ሳለ፣ በሠረገላው ላይ ተቀምጦ ትንቢተ ኢሳይያስን እያነበበ ነበር። 29 መንፈስ ፊልጶስን፣ “ሂድ ወደዚህ ሠረገላ ቅረብ” አለው። 30 ፊልጶስ ወደ ጃንደረባው ሮጠ፣ ትንቢተ ኢሳይያስንም ሲያነብ ሰማው፤ “የምታነበውን ትረዳዋለህ?” አለው። 31 ኢትዮጵያዊውም፣ “የሚመራኝ ከሌለ እንዴት ልረዳው እችላለሁ?” አለው። ወደ ሠረገላው እንዲወጣና ዐብሮት እንዲቀመጥ ፊልጶስን ለመነው። 32 ኢትዮጵያዊው ያነበው የነበረ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ይህ ነው፦ “እንደ በግ ለመታረድ ተነዳ፤ በሸላቾቹ ፊት ዝም እንደሚል ጠቦት፣ አፉን አልከፈተም፤ 33 በውርደቱ ፍርዱ ተወገደ፤ ትውልዱን ማን ይናገራል? ሕይወቱ ከምድር ተወግዶአልና።” 34 ጃንደረባው ፊልጶስን፣ “እባክህ ነቢዩ ስለ ማን ነው የሚናገረው? ስለ ራሱ ወይስ ስለ ሌላ ነው?” አለው። 35 ፊልጶስም መናገር ጀመረ፤ ከዚህም ከኢሳይያስ መጽሐፍ ጀምሮ ስለ ኢየሱስ ሰበከው። 36 እየሄዱ ሳሉ ውሃ አለበት ዘንድ ደረሱ፤ ጃንደረባው፣ “ተመልከት፣ እዚህ ውሃ አለ፤ እንዳልጠመቅ ምን ይከለክለኛል?” አለ። 37 ፊልጶስም፣ “በፍጹም ልብህ ካመንህ፣ መጠመቅ ትችላለህ” አለ። ኢትዮጵያዊውም መልሶ፣ “ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አምናለሁ” አለ። 38 ኢትዮጵያዊው ሠረገላው እንዲቆም አዘዘና፣ ፊልጶስም ጃንደረባውም ወደ ውሃው ወረዱ፤ ፊልጶስም አጠመቀው። 39 ከውሃው ውስጥ ሲወጡ፣ የጌታ መንፈስ ፊልጶስን ወሰደው፤ ጃንደረባውም ከዚያ ወዲያ አላየውም፤ ደስ ብሎትም ጕዞውን ቀጠለ። 40 ነገር ግን ፊልጶስ በአዛጦን ታየ። በዚያ አገር ውስጥ በማለፍ ቂሣርያ እስኪደርስ ድረስ፣ ለከተሞች ሁሉ ወንጌልን ሰበከ።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ከቁጥር 1 ጀምሮ ስለ እስጥፋኖስ እየተነገረ ያለ ታሪክ ክፍል ነው፡፡ ሉቃስ በዚህ ሥፍራ ላይ የታሪኩን አቅጣጫ ከእስጥፋኖስ ወደ ሳኦል ይለውጣል፡፡ ስለዚህም በዚህ ሥፍራ ጀመሩ “ስለዚህም” የሚለው ቃል በታሪኩ ውስጥ ዋና ለውጥ መካሄዱን ያሳያል፡፡ እስጥፋኖስ በድንጋይ በመወገሩ ምክንያት ስደት እና ሐዋርያቱን ማሠር ተጀመረ፡፡ አማራጭ ትርጉም: "በዚያ ሥፍራ ከተፈጸመው ነገር የተነሳ ይህ ነገር መሆን ጀመረ" በዚያ ቀን ይህ ቃል የሚያመለክተው እስጥፋኖስ የሞተበትን ቀን ነው፡፡ አማኞች በየሥፍራው ተበተኑ ይህ በስደቱ ምክንያት ከእየሩሳሌም ወደ ተለያዩ ሥፍራዎች የተሰደዱትን ብዙ ወይም አብዛኞቹን አማኞች ለማመለክት ነው፡፡ ከሐዋርያት በስተቀር በዚህ መረጃ ውስጥ በተዘዋዋር መልኩ የተገለጸው ሀሳብ ሐዋርያቱ በእየሩሳሌም መቆየታቸውን እና ይህ ዓይነቱ ስደት በእነርሱ ላይ አለመድረሱን ነው፡፡ የተሰጡ ሰዎች "ፈረሃ እግዚአብሔር ያላቸው ሰዎች" ወይም "እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች" ታላቅ ኃዘን ሆነ "ስለእርሱ ታላቅ ለቅሶ አለቀሱ" (UDB) ወንዶችን እና ሴቶችን እየጎተቱ ሳኦል አይሁዳዊያን አማኞችን ከመኖሪያ ቤታው በጉልበት እየወሰደ በእስርቤት ውስጥ ያጉራው ነበር፡፡ እየጎተቱ "በኃይል እየወሰዱ"
የተበተኑት "ከታላቁ ስደት የተነሣ በየሥፍራው የተበተኑት፡፡" በየሥፍራው የመበተናቸው ምክንያት ከዚህ በፊት የተጠቀሰው ስድት ነው፡፡ የሰማሪያ ከተማ ሰዎች ሰማሪያ የሚለው ቃል የሚያመለክተው “ከተማዋን” (ULB) ወይም “ከተማ” (UDB) እንደሆ ግልጽ አይደለም፡፡
ብዙ ሰዎች "ከሰማሪያ ከተማ ብዙ ሰዎች በመጡ ጊዜ፡፡" ይህ ሥፍራ ከዚህ በፊት ተገልጾ ነበር፡፡ ትኩረት ሰጡት ሰዎች ትኩረት የሰጡበት ዋነኛ ምክንያት ከዚህ በፊት ፊልጶስ ባደረገው ፈውስ ነው፡፡ ይህ እንደሆነ ግንዛቤ ውስጥ ሊገባ ይገባዋል፡፡ እንዲሁም ሌሎች ብዙ ነበሩ ፊልጶስ ካደረገው ፈውስ የተነሳ ብዙ ሰዎች ደስ ይላቸው ነበር፡፡
አጠቃላይ መረጃ: ሲሞን በታሪኩ ውስጥ የተዋወቀበት ሥፍራ ነው፡፡ እንዲሁም በቁጥር 9 እስከ 11 ላይ የሲሞን የኃላ ታሪክ መረጃዎች ተሰጥተዋ፡፡ እርሱም ከሰማሪያዊን ወገን ነበር፡፡ ይሁን እንጂ አንድ ሰው ነበር . . . ስሙም ሲሞን ይባላል፡፡ ይህ በታሪኩ ውስጥ አዲስ ሰውን የማስተዋወቂያ መንገድ ነው፡፡ በቋንቋችሁ እንዲህ አዲስ ሰውን በታሪክ ውስጥ የሚታስተዋውቁበት መንገድ ይኖራልና ያንን መንገድ ተጠቀሙ፡፡ ከተማ "በሰማሪያ ከተማ ውስጥ" ሰማሪያዊያን ሁሉ ይህ ግነት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "በከተማው ውስጥ የሚኖሩ ብዙ ሰማሪያዊያን፡፡" ይህ ሰው ታላቅ ተብሎ የሚጠራ የአምላክ ኃይል እንዳለው ይሳተባል፡፡ ሰዎች ሲሞን ታላቅ ኃይል ተብሎ የሚታወቀው የመለኮት ኃይል ነው ብለው ይናገራሉ፡፡
አጠቃላይ መረጃ: ቁጥር 12 እና 13 ስሲሞን እና በኢየሱስ ስላመኑት አንዳንድ የሰማሪያ ሰዎች የኃላ ታሪክ መረጃን በውስጡ ይዟል፡፡ ተጠመቁ ፊልጶስ አዳዲስ አማኞችን አጠመቀ፡፡ ምልክቶች እና ታላለቅ ነገሮች መደረጋቸውን በተመለከተ ጊዜ እጅግ በጣም ተገረመ "በፊልጶስ እጅ ምልክቶች እና ታላላቅ ተዓምራት መደረጋቸውን ሲሞን በተመለከተ ጊዜ በጣም ተገረመ"
አሁን ይህ ቃል በታሪክ ውስጥ አዲስ ታክ ለመጀመሩ ምልክት ነው፡፡ ሰማሪያዊያን ይህ በሰማሪያ ግዛት ውስጥ የሚኖሩ ብዙ ሰዎች መታወቂያ ስም ነው እነርሱ ወደዚያ በመጡ ጊዜ "ጴጥሮስ እና ዮሐንስ ወደዚያ በመጡ ጊዜ" ጸለዩላቸው "ጴጥሮስ እና ዮሐንስ ለሰማሪያ አማኞች ጸለዩላቸው" መንፈስ ቅዱስን ይቀበሉ ዘንድ፡፡ "በሰማሪያ የሚገኙ አማኞች መንፈስ ቅዱስን ይቀበሉ ዘንድ" ብቻ ተጠምቀዋል "ፊልጶስ በሰማሪያ የሚገኙ አማኚችን በ . . . ብቻ አጥምቆዋቸዋል" ከዚያ ጴጥሮስ እና ዮሐንስ እጆቻቸውን ጫኑባቸው "እነርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው የእስጥፋኖስን የወንጌል መልዕክ ያመኑ የሰማሪያ ሰዎችን ነው፡፡
መንፈስ ቅዱስ የተሰጣቸው በሐዋርያቱ የእጅ መጫን ነው "ሐዋርያቱ በሕዝቡ ላይ እጆቻቸውን በመጫን መንፈስ ቅዱስን እንዲቀበሉ አድርገዋል" እጄን የሚጭንት ሰው ሁሉ መንፈስ ቅዱስን ይቀበል ዘንድ፡፡ "በሰዎች ላይ እጄን ስጭን መንፈስ ቅዱስን ይቀበሉ ዘንድ፡፡"
እርሱ . . . አንተ . . . እንተ እነዚህ ተውላጠ ስሞች ሁሉም የሚያመለክቱት ሲሞንን ነው፡፡ የእግዚአብሔር ስጦታ እጅ በመጫን ሰዎች መንፈስ ቅዱስ እንዲሞሉ የማድረግ ስጦታ ልብህ ትክክል አይደለ "አስተሳሰብህ ልክ አይደለም" ምክንያቱም መሻትህ "ምክንያቱም መንፈስ ቅዱስን ለሌሎች የመስጠትን ስጦታ ለመግዛት ትፈልጋለህና" በመራራነት ተበክለሃል ይህ “ከፍተኛ ቅናትን” የሚያለክት ምሳሌያዊ አገላለጽ ነው (UDB). ከኃጢአት ጋር የተቆራኘ "የኃጢአት እስረኛ" ወይም "ኃጢአት ማድረግ ብቻ የሚችል"
ከተናገርካቸው ውስጥ ዬትኛውም ይህ የሚያመለክተው የጴጥሮስን ተግሳጻዊ ንግግር ነው፣ “ብርህ ከአንተ ጋር ይጥፋ፡፡" የተናገራችሁት ነገር በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጴጥሮስን እና ዮሐንስን ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ይህ ስለ ሲሞን እና ሰማሪያዊያን ታሪክ ክፍል የመጨረሻው ነው፡፡ ሕያው ምስክሮች ጴጥሮስ እና ዮሐንስ ለሰማሪያዊያን ኢየሱስን በግላቸው እንደሚያውቁት ነገሯቸው፡፡ የጌታን ቃል ተናገሩ ጴጥሮስ እና ዮሐንስ ለሰማሪያ ሰዎች ቅዱሳት መጻሕፍት ስለ ኢየሱስ ምን እንደሚሉ አብራሩላቸው፡፡ በሰማሪያ ውስጥ የሚገኙ ብዙ መንደሮች "በብዙ የሰማሪያ መንደሮች ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች"
አጠቃላይ መረጃ: ይህ ስለ ፊልጶስ እና ከኢትዮጵያ የመጣው ሰው ታሪክ ክፍል ነው፡፡ ቁጥር 27 ከኢትዮጵያ የመጣው ሰው የኃላ ታሪክ መረጃን ይሰጣል፡፡ አሁን ይህ በታሪኩ ውስጥ ሽግግር መኖሩን ያሳያል፡፡ እነሆ “እነሆ” የሚለው ቃል በታሪኩ ውስጥ አዲስ ሰው መጨመሩን ያሳየናል፡፡ በቋንቋችሁ እንዲህ ያለውን ነገር ማድረጊያ መንገድ ይኖራል፡፡ ጃንደረባ በዚህ ክፍል ውስጥ ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው “ጃንደረባው” ከኢትዮጵያ የመጣ ክፈተኛ የመንግስት ባለስልጣን መሁን ለማሳየት እንጂ የሰውነት ክፍሉ መጉደሉን ለማሳየት አይደለም፡፡ ህንደኬ ይህ ከኢትዮጵያ የሆነችው ንግሥት የማዕረግ ስም ነው፡፡ ይህ ልክ የግብጽ ነገሥታት መጠሪያ ስም “ፈርኦን” እንደሆነው ሁሉ ማለት ነው፡፡ ሠረገላ "ሠረገላ" ወይም “ጋሪ” ሲሆን በዚህ አውድ ውስጥ ሠረገላ የሚለው ቃል ተስማሚ ይሆናል፡፡ ሠረገላ ብዙ ጊዜ ረጀም ጉዞ ለመጓዝ የሚያገለግል ነው፡፡ የነቢዩ ኢሳያስን መጽሐፍ እያነበበ ይህ በብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ውስጥ የሚገኘው የኢሳያስ መጽሐፍ ነው፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ከነቢዩ ኢሳያስ መጽሐፍ ውስጥ እያነበበ፡፡"
የምታበውን ነገር ትረዳዋለህን? ኢትዮጵያዊው ሰው የተማረ እና ማንበብ የሚችል ነው ነገር ግን መንፈሳዊ መረዳት የሚጎድለው ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “የሚታነበው ነገር ትርጉሙ ምን እንደሆነ ትረዳዋለህን?" አንድ ሌላ ሰው ካልመራኝ ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? ይህ በጥዬቄ መልክ የቀረበበት ምክንያት ከሰው እገዛ ውጪ መረዳት እንደማይችል አጽኖት ለመስጠጥ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "የሰው እገዛ ካላገኘሁ በስተቀር ይህ ሊሆን አይችልም" ፊልጶስ ወደ ሠረገላው ወጥቶ ከእርሱ ጋር እድቀመጥ ለመነው በዚህ ሥፍራ ላይ በተዘዋዋር መልኩ የተገለጸው መረጃ ፊልጶስ የተወሰነ መንገድ ከእርሱ ጋር ለመሄድ መስማማቱን ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ: ይህ ክፍል ከኢሳያስ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡ በሸላቶቹ ፊት ዝም እንደሚል በግ ሸላት ለተለያዩ አገልግሎቶች ይውል ዘንድ የበጎችን ጸጉር ከበጎች ላይ የሚሸልት ሰው ነው፡፡ በውርደቱ ጊዜ ፍትኃዊ እርምጃ አልወሰዱበትም "አዋረዱት እንዱም ፍትኃዊ በሆነ መልኩ አልዳኙትም"
ለእርሱ ስለ ኢየሱስ ይሰብከው ጀመር "ለጃንደረባ ስለ ኢየሱስ መልካሙን ዜና ያስተምረው ጀመር"
ከመጠመቅ የሚከለክለኝ ምን ነገር አለ? ጃንደረባው ይህንን ንግግር የተናገረው መጠመቅ መፈለጉን ለመግለጽ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እንዳትጠመቅ የሚከለክል ምንም ነገር የለም፡፡" and
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ይህ ስለ ፊልጶስ እና ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ታሪክ የመጨረሻው ክፍል ነው፡፡ ጃንደረባውም ከዚያን ጊዜ አንስቶ አላየውም "ጃንደረባው ከዚያን ጊዜ አንስቶ ፊልጶስን አላየውም" ፊልጶስ በአዛጦን ተገኘ፡፡ ፊልጶስ ኢትዮጵያዊውን ጃንደረባ ከተገናኘበት ሥፍራ ወደ አዛጦን እንዴት እንደተጓዘ ምንም ፍንጭ የለም፡፡ በድንጋ በጋዛ መንገድ ላይ ተሰወረና በአዛጢን ተገኘ፡፡ ወደቄሳሪያ እስኪመጣ ድረስ የፊልጶስ ታሪክ የሚያበቃው በቄሳሪያ ነው፡፡
1 ሳውል ግን በጌታ ደቀ መዛሙርት ላይ ለግድያም እንኳ እየዛተ ወደ ሊቀ ካህናቱ ሄደ፤ 2 የጌታን መንገድ ከሚከተሉት ወንዶችም ሆነ ሴቶች ቢያገኝ፣ ወደ ኢየሩሳሌም አስሮ እንዲያመጣቸው፣ ለምኵራቦች ደብዳቤ እንዲሰጠውም ሊቀ ካህናቱን ጠየቀ። 3 እየሄደ ሳለ ደማስቆ አጠገብ ሲደርስ፣ በድንገት ከሰማይ ብርሃን በዙሪያው በራበት፤ 4 በምድር ላይ ወደቀ፤ “ሳውል፣ ሳውል ለምን ታሳድደኛለህ” የሚል ድምፅ ሰማ። 5 ሳውልም፣ "ጌታ ሆይ፣ ማን ነህ?" ብሎ መለሰ፤ ጌታም፣ “አንተ የምታሳድደኝ ኢየሱስ ነኝ፤ 6 ነገር ግን ተነሥተህ ወደ ከተማው ግባ፤ ማድረግ ያለብህም ይነገርሃል” አለ። 7 ከዚያም ከሳውል ጋር የተጓዙት ሰዎች ድምፁን እየሰሙ፣ ማንንም ግን ሳያዩና ሳይነጋገሩ ቆሙ። 8 ሳውል ከወደቀበት ተነሣ፤ ዐይኑን ሲከፍትም ምንም ማየት አልቻለም፤ ስለዚህም በእጅ እየመሩ ወደ ደማስቆ አስገቡት። 9 ሦስት ቀን ዕውር ሆኖ ቆየ፤ አልበላም አልጠጣምም። 10 በዚያ ጊዜ ሐናንያ የሚባል አንድ ደቀ መዝሙር በደማስቆ ነበር፤ ጌታም ለእርሱ በራእይ፣ “ሐናንያ” አለው። እርሱም፣ “ጌታ ሆይ፣ እነሆኝ” አለ። 11 ጌታም መልሶ እንዲህ አለው፤ “ተነሥና ቀጥተኛ ወደሚባለው ጎዳና ሂድ፤ በይሁዳ ቤትም ሳውል የሚባል የጠርሴስ ሰውን ፈልግ፤ እርሱ እዚያ እየጸለየ ነውና፤ 12 እርሱ እንዲያይ ሐናንያ የሚባል ሰው ሲገባና በእርሱ ላይ እጁን ሲጭንበት በራእይ አይቶአል።” 13 ሐናንያም መልሶ እንዲህ አለ፤ “ጌታ ሆይ፣ ስለዚህ ሰው በኢየሩሳሌም ባሉት ሕዝብህ ላይ ምን ያህል ክፋት እንደ ፈጸመባቸው ከብዙዎች ሰምቻለሁ። 14 ስምህን የሚጠሩትን ሁሉ ለማሰር ከሊቀ ካህናቱ ሥልጣን ተቀብሎአል።” 15 ጌታ ግን መልሶ እንዲህ አለው፤ “ሂድ፤ እርሱ በአሕዛብ፣ በነገሥታትና በእስራኤል ልጆች ፊት ስሜን ለመሸከም የተመረጠ ዕቃየ ነውና፤ 16 ስለ ስሜ ሲል ምን ያህል መከራ መቀበል እንዳለበትም አሳየዋለሁና። 17 ስለዚህ ሐናንያ ሄደ፤ ወደ ቤትም ገባ፤ እጁን በሳውል ላይ በመጫንም፣ “ወንድሜ ሳውል ሆይ፣ ስትመጣ በመንገድ ላይ የተገለጠልህ ጌታ ኢየሱስ እንድታይና መንፈስ ቅዱስን እንድትሞላ ወዳንተ ልኮኛል።” 18 ወዲያው እንደ ቅርፊት ያለ ነገር ከሳውል ዐይን ወደቀ፤ ማየትም ጀመረ፤ ተነሥቶም ተጠመቀ፤ 19 በላ፣ በረታም። ሳውል በደማስቆ ውስጥ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ብዙ ቀን ቆየ። 20 ወዲያውም ኢየሱስን የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በምኵራብ ውስጥ ዐወጀ። 21 የሰሙትም ሁሉ በመደነቅ እንዲህ አሉ፤ “ይህ ሰው በኢየሩሳሌም ይህን ስም የሚጠሩትን ያጠፋው አይደለምን? የመጣውም አስሮ ወደ ሊቀ ካህናቱ ሊያቀርባቸው ነው።” 22 ሳውል ግን ለመስበክ በረታ፣ በደማስቆ ይኖሩ የነበሩ አይሁድንም ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን በማረጋገጥ ግራ አጋባቸው። 23 ከብዙ ቀን በኋላ፣ አይሁድ ሊገድሉት ዐሰቡ። 24 ሳውል ግን ዐሳባቸውን ዐወቀባቸው። ሊገድሉት የከተማይቱን በሮች ቀንም ሌሊትም ይጠብቁ ነበር። 25 ደቀ መዛሙርቱ ግን በግድግዳው በኩል በቅርጫት አወረዱት። 26 ሳውል ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሶ በመጣ ጊዜ፣ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ለመገናኘት ሞከረ፤ ነገር ግን ደቀ መዝሙር መሆኑን በመጠራጠር ሁሉም ፈሩት። 27 ይሁን እንጂ፣ በርናባስ ወስዶ ወደ ደቀ መዛሙርቱ አቀረበው። ሳውል ጌታን በመንገድ ላይ እንዴት እንዳየው፣ ጌታም እንደ ተናገረው፣ በኢየሱስ ስም ደማስቆ ውስጥ በድፍረት እንዴት እንደ ሰበከም ነገራቸው። 28 ሳውል ኢየሩሳሌም ውስጥ ሲገባና ከዚያም ሲወጣ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተገናኘ። በጌታ ኢየሱስ ስም በድፍረት ተናገረ፤ 29 ከግሪክ አይሁድ ጋርም ተከራከረ፤ ሊገድሉት ሙከራ ማድረጋቸውን ግን አላቋረጡም። 30 ወንድሞች ስለዚህ ባወቁ ጊዜ፣ ወደ ቂሣርያ አውርደው ወደ ጠርሴስ ላኩት። 31 ከዚያም በኋላ የይሁዳ ሁሉ፣ የገሊላና የሰማርያ ቤተ ክርስቲያን ሰላም ነበራት፣ ታነጸችም፤ እግዚአብሔርን በመፍራትና በመንፈስ ቅዱስ መጽናናት ቤተ ክርስቲያን በቍጥር አደገች። 32 ጴጥሮስም በየቦታው ሲዘዋወር፣ በልዳ ከተማ ወደሚኖሩ ቅዱሳንም ወረደ። 33 እዚያም፣ ሽባ በመሆኑ ስምንት ዓመት የአልጋ ቊራኛ የነበረን ኤንያ የሚባለውን አንድ ሰው አገኘ። 34 ጴጥሮስ፣ “ኤንያ ሆይ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ይፈውስሃል፤ ተነሥና ዐልጋህን አንጥፍ” አለው። ወዲያውም ተነሣ። 35 በልዳና በሰሮና የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ ሰውየውን አዩትና ወደ ጌታ ተመለሱ። 36 በኢዮጴም ጣቢታ የምትባል አንድ ደቀ መዝሙር ነበረች፤ የስሟ ትርጕም “ዶርቃ” ማለት ነው። ይች ሴት በመልካም ምግባርና ለድኾች በምታደርጋቸው የርኅራኄ ሥራዎች የተሞላች ነበረች። 37 በዚያም ወቅት ታመመችና ሞተች፤ ዐጥበውም ሰገነት ላይ አስቀመጧት። 38 ልዳ በኢዮጴ አጠገብ በመሆኑና ደቀ መዛሙርቱም የጴጥሮስን በዚያ መኖር ስለ ሰሙ፣ “ሳትዘገይ ወደ እኛ ና” ብለው በመለመን ሁለት ሰዎችን ወደ እርሱ ላኩ። 39 ጴጥሮስም ተነሣና ከተላኩት ጋር ሄደ። እዚያ ሲደርስ፣ ወደ ሰገነቱ አወጡት። መበለታቱም ሁሉ ዶርቃ ከእነርሱ ጋር ሳለች ትለብሳቸው የነበሩትን ቀሚሶችና ልብሶች እያሳዩትና እያለቀሱ በአጠገቡ ቆሙ። 40 ጴጥሮስ ሁሉንም ከክፍሉ አስወጣቸውና ተንበርክኮ ጸለየ፤ ከዚያም ወደ አስከሬኑ በመዞር፣ “ጣቢታ ሆይ፣ ተነሺ” አለ። ዐይኖቿን ከፈተች፤ ጴጥሮስንም ስታየው ተነሥታ ተቀመጠች። 41 ጴጥሮስም እጇን ይዞ አነሣት፤ አማኞችንና መበለታቱን ጠርቶም በሕይወት እንዳለች ሰጣቸው። 42 ይህ ጉዳይ በመላው ኢዮጴ የታወቀ ሆነ፤ ብዙ ሰዎችም በጌታ አመኑ። 43 ጴጥሮስ በኢዮጴ ቍርበት ፋቂ ከነበረ ስምዖን ከሚባል ሰው ጋር ብዙ ቀን ቆየ።
አጠቃላይ መረጃ: የታሪኩ ትኩረት ተመልሶ ወደ ሳኦል መሆን ይጀምራል፡፡ እነዚህ ቁጥሮ ሳኦል ከእስጥፋኖስ በድንጋይ ተወግሮ መሞት በኋላ ምን ስያደርግ እንደነበር የኃላ ታሪክ መረጃ ይሰጠናል፡፡ ደቀ መዛሙርቱን በመቃወም ያስፈራራቸው ነበር፣ እንዲሁም እንደሚገድላቸው ይናገር ነበር “ገዳይ” የሚለው ቃል ስም ቢሆንም እንደ ግሥ ግን ሊተረጎም ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ደቀ መዛሙርቱን ያስፈራራቸው እንዲሁም እንደሚገድላቸው ይዝት ነበር፡፡” ደብዳቤ ይሰጠው ዘንድ ጠየቀ "ሊቀ ካህኑን የድጋፍ ደብዳቤ እንዲሰጠው ጠየቀው" ካገኘ . . . ለማምጣረት “እርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሳኦልን ነው፡፡ በዚያ መንገድ የሚሄዱትን "የኢየሱስ ክርስቶስን ትምህርት የሚከተሉትን" አሥሮ ወደ ኢየሩሳሌም ያመጣቸው ዘንድ "እሰረኛ አድርጎ ወደ ኢየሩሳሌም ማምጣት ይችል ዘንድ፡፡" እነዚህ ቃላት በመጨመር ለጳውሎስ የተሰጠው ኃላፊነትን ይበልጥ ግልጽ ማድረግ ይቻላል “የአይሁድ መሪዎች ፍርድ መስጠጥ እና ይቀጧቸው ዘንድ”
እየተጓዘ እያለ ሳኦል ከእየሩሳሌም ወጥቶ ወደ ደማስቆ ተጓዘ፡፡ እንዲህ ሆነ ይህ በታሪኩ ውስጥ ለውጥ መሆኑን በማሳየት ከዚህ በፊት ያለሆነ አዲስ ነገር መፈጠሩን የሚያሳይ ነው፡፡ ከሰማይ ብርሃን በእርሱ ዙሪያ አበራ "በእርሱ ዙሪያ ብርሃን ከሰማይ በእርሱ ዙሪያ አበራ" በምድር ላይ ወደቀአማራጭ አማራጭ ትርጉሞች እኝህ ናቸው 1) "ሳኦል ራሱን ወደ ምድር ወረወረ" ወይም 2) "ብርሃኑ ሳኦልን በምድር ላይ እዲወድቅ አደረገው" ወይም 3) "ሳኦል ራሱን እንደ ሳተ ሰው ሆኖ በምድ ላይ ወደቀ፡፡" ሳኦል አወዳደቁ ድንገተኛ አልነበረም፡፡ ለምን ታሳድደኛለህ? ጌታ ሳኦልን በጥያቄ መልክ አድርጎ እየገሰጸው ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እያሳደድከኝ ነው!"
አንተ ማን ነህ ጌታዬ! ዚህ ሥፍራ ላይ ሳኦል ኢየሱስን እንደ ጌታ አድርጎ ገና አላወቀውም፡፡ ይህ በአንድ ልዕለ ተፈጥሮአዊ ኃይል ሥር መሆኑን እውቅና የሚሰጥ ንግግር ነው፡፡ ነገር ግን ተነሣና ወደ ከተማይቱ ግባ "ተነስና ወደ ደማስቆ ከተማ ግባ" ለአንተ ይነገርሃል አንድ ሰው ይነግርሃል አንተ በዚህ ሥፍራ ውስጥ “አንተ” የሚለው ቃል ነጠላ ቁጥር አመልካች ነው፡፡ ነገር ግን ማንንም አላየም ብርሃኑን ማየት የቻለው ሳኦል ብቻ ነበር፡፡ -
ሌላ ነገር ማየት አልቻለም የሳኦል ዐይች ታወሩ፡፡ መብላትም ሆነ መጠጣት አልቻለም እንደ “ሚጾም ሰው” "ለመብላትም ሆነ ለመጠጣት አልፈለገም" ወይም “እንዳልራበው ሰው” መብላትም ሀፐነ መጠጣት አልቻለም”
አጠቃላይ መረጃ: የታሪኩ አቅጣጫ አናኒያስ ተብሎ ወደሚጠራ ሰው ታሪክ ዞሯል፡፡ ይህ በየሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ቅስጥ ከዚህ በፊት ከተጠቀሰው ሰው ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ አሁን . . . አንድ ሰው ነበር ይህ በታሪክ ውስጥ አዲስ ገጸ ባሕርን ያስተዋውቃል፡፡ ደቀ መዛሙርት በኢየሱስ የሚያምን እና እርሱ የሚታዘዝ ማንኛውም ሰው የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ይባላል፡፡ አናናስ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የሆነው ሰው እግዚአብሔር በመታዘዝ ወደ ሳኦል በመሄድ በሳኦል ላይ እጁን በመጫን ፈወሰው፡፡ እናም እንዲህ አለ "እናም ሐናኒያ እንዲህ አለ" የይሁዳ ቤት ይሁዳ በደማስቆስ ውስጥ ሐናኒያ በእንግድነት የተቀመጠበት ቤት ባለቤት ነው፡፡ ምንም እንኳ በአዲስ ኪዳን ውስጥ የተለያዩ ሰዎች ይሁዳ በሚል ስም ቢጠሩም ይህ ሰው ግን የተጠቀሰው በዚህ ሥፍራ ላይ ብቻ ነው፡፡ የጤርሰስ ሰው "ከጤትሰስ ከተማ የመጣ ሰው"
ከካህናት አለቃ ዘንድ ስልጣን የተሰጠው ሰው በዚህ ዓረፍተ ነገር ውስጥ በተዘዋዋር መልኩ የተገለጸሰው ሀሳብ ሳኦል የተሰጠው ስልጣን በዚያ ዘመን በአይዶች ላይ ብቻ መሆኑን ያሳያል፡፡ እርሱ የእኔ የተመረጠ መሣሪያ ነው "የተመረጠ መሣሪያ" የሚለው ቃል ለአገልግሎት መለየትን የሚያሳይ ነው፡፡ አማርጭ ትርጉም፡ "ያገለገልኝ ዘንድ መርጬዋለሁ፡፡" ስሜን ይሸከም ዘንድ ይህ ከእየሱስ ጋር መወገንን ወይም ስለኢየሱስ መናገርን የሚገልጽ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ስለእኔ ይናገር ዘንድ" ስለእኔ ስም ይህ የአገላለት መንገድ ሲሆን ትርጉሙም "ለሰዎች ስለ እኔ ለመናገር፡፡"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ሐናኒያ ሳኦል ወደአረፈበት ቤት ሄደ፡፡ ሳኦል ከተፈወሰ በኋላ የታሪኩ አቅጣጫ ከሐናኒያ ወደ ሳኦል ተቀየረ፡፡ እጁን ጫነበት ሐናኒያ እጆቹን በሳኦል ላይ ጫነበት፡፡ የተገለጠለህ "አንተ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሳኦልን ነው (ነጠላ ቁጥር)፣ ምንም እንኳ በጉዞው ላይ ከሳኦል ጋር የነበሩ ሌሎች ሰዎች የነበሩ ቢሆንም ማለት ነው፡፡ ማየት ትችል ዘንድ እና በመንፈስ ቅዱስ ትሞላ ዘንድ ወደ አንተ ዘንድ ልኮኛል አማራጭ ትርጉም፡ "እንደገና ማየት ትችል ዘንድ እና በመንፈስ ቅዱስ ትሞላ ዘንድ ወደ አንተ ልኮኛል" ቅርፍት የሚመስል ነገር ከዐይኖቹ ላይ ወደቀ "የዓሣ ቅርፍት የሚመስል ነገር ከዐይኖቹ ላይ ወደቀ" ተነሣ እና ተጠመቀ አማራጭ ትርጉም: "ተነሣና ሐናኒያ አጠመቀው"
ወዲያውም ስለኢየሱስ መናገር ጀመረ በዚህ ሥፍራ ላይ "እርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሳኦል ነው፡፡ እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነው እያለ በዚህ ሥፍራ ላይ "እርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው፡፡ ሰኦል በኢየሱስ ካመነ በኋላ ኢየሱስ “የእግዚአብሔር ልጅ” መሆኑን ተናገረ፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ ይህ የኢየሱስ ወሳኝ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ይህንን ስናገር የሰሙ ሰዎች ሁሉ ይህ ግነት የሞላበት ንግግር “ንግግሩን የሰሙ ሰዎች ብዙዎቹ” የሚል ትርጉም አለው፡፡ በቋንቋችሁ ግነትን የሚትልጹበት መንገድ ከዚህ የሚለይ ከሆነ የእናንተ መንገድ ተጠቀሙ፡፡ ይህ ሰው በዚህ ስም የተጠሩትንና በእየሩሳሌም የሚኖሩትን ሰዎች የሚገድል አይደለምን? ይህ አሉታዊ እና ጥያቄያዊ ንግግር ሳኦል በእርግጥም አማኞችን ያሳድድ እንደነበረ አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ይህ ሰው ይህንን ኢየሱስ የሚለውን ስም የሚጠሩ ሰዎችን የሚያሳድድ ሰው ነው፡፡”
እርሱንም ለመግደል አይሁዶች በጋራ ተማከሩ በዚህ ሥፍራ ላይ "እርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሳኦልን ነው፡፡ ይሁን እንጂ ዕቅዳቸውን ሳኦል አስቀድሞ ደረሰበት፡፡ አማራጭ ትርጉም: "አንድ ሰው ለሳኦል እቅዳቸውን ገለጸለት" የከተማይቱን መግቢያ መውጫዎች ይጠብቁ ነበር ይህች ከተማ በቅጥር የታጠረች ነበረች፡፡ ሰዎች ወደ ከተማይቱ የሚገቡት እንዲሁም ከከተማይቱ የሚወጡት በቅጥሩ በር በኩል ብቻ ነበር፡፡ የእርሱ ደቀ መዛሙርት ሳኦል ስለኢየሱስ የተናረውን መልዕክት ያመኑት ሰዎች የእርሱን ትምህርት ይከተሉ ነበር፡፡
ይሁን እንደጂ ሁሉም እርሱን ይፈሩት ነበር በዚህ ሥፍራ ላይ "ሁሉም" የሚለው ቃል ግነት የተሞላበት ቃል ሆኒ ብዙዎች ወይም አብዛኞቹ ሰዎች ለማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "አብዛኞቹ ሰዎች" ነገር ግን ባርናባስ ወስዶት "ነገር ግን ባርናባስ ሳኦልን ወስዶት" ሳኦል በድፍረት የኢየሱስን ስም ይሰብክ ነበር ይህ ሳኦል ስለኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ያስተምር ወይም ይሰበክ እንደነበር የሚያሳይ ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡
ከእነርሱ ጋር ተገናኘ "ሳኦል ከሐዋርያቱ ጋር ተገናኘ" በጌታችን በኢየሰሱስ ስም ይህ የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ትምህርትን የሚያሳይ ነው፡፡ ከግሪካዊን አይሁዶች ጋር ይከራከር ነበር ሳኦል ከግሪክ አይሁዳዊን ጋር ይከራከር ነበር፡፡ ወደታች ወደ ቄሳሪያ ከእየሩሳሌም ወደ ቄሳሪያ የቦታ ከፈት ልዩት አለ፡፡ ይሁን እንጂ ወደ እየሩሳሌም እና ወደ ቤተ መቅዱሱ ወጣ እንዲሁም ከእየሩሳሌም ወረደ ማለት በዘመኑ የተለመደ ንግግር ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ: ቁጥር 31 ስለ ቤተ ክርስቲያን እድገት አጠቃላይ መረጃ ይሰጣል፡፡ በቁጥር 32 ላይ የታሪኩ አቅጣጫ ከሳኦል ወደ አዲስ የታሪኩ ክፍል ወደ ሆነው ወደ ጴጥሮስ ይዞራል፡፡ ከዚም እንዲህ ሆነ ይህ ሀረግ አዲስ የታሪኩ ክፍል መጀመሩን የሚበስር ነው፡፡ አደገ እግዚአብሔር እንዲያድግ አደረገው በጌታ ፍርሃት እየሄዱ "ጌታን ማክበራቸውን ቀጠሉ" በመንፈስ ቅዱስ መጽናናት "መንፈስ ቅዱስ ያበረታቸው እና ያበረታታቸው ነበር" በአጠቃላይ አከባቢው ይህ ጴጥሮስ በይሁዳ፣ ገሊላ እና ሰማሪያ አከባቢ ያሉ ብዙ አማኞቹን መጎብኘቱን ለማመልከት የቀረበ ግነት የሞላበት ገለጻ ነው፡፡ ልዳ ልዳ ከጆባ 18 ኪሜ በስተምስራቅ የሚትገኝ ከተማ ናት፡፡ በብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ውስጥ እና በአሁኗ እስራኤል ውስጥ ይህች ከተማ ሎድ ተብላ ትታወቅ ነበር፡፡
በዚያ አንድ ሰው አገኘ ጴጥሮስ ሆን ብሎ ሽባ የሆነ ሰውን እየፈለገ ሳይሆን ድንገት ከዚህ ሰው ጋር ተገናኘ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “በዚያም ጴጥሮስ አንድ ሰው አገኘ፡፡” በአልጋው ላይ ነበር . . . ሽባ ነበር ይህ ስለኤንያ የኃላ ታሪክ መረጃ ነው፡፡ የማይንቀሳቀስ መራመድ የማይችል፣ ምናልባትም ከወገቡ በታች መንቀሳቀስ የማይችል ሰው አልጋህን ያዝ "ምንጣፍህን ጠቅልል" (UDB) የኖረ ሰው ሁሉ ይህ “የኖሩ ብዙ ሰዎችን” ለማመልከት የዋለ ግነት የሞላበት ንግግር ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ: ይህ ስለጴጥሮስ የተነገረው ታሪክ ክፍል ውስጥ ያለ አዲስ ነገር ነው፡፡ ይህ ጠብታ ተብላ ስለምትጠራ አንዲት ሴት የኃላ ታሪክ መረጃ ነው፡፡ አሁን ይህ በታሪኩ ውስጥ አዲስ ጅማሬን ያስተዋውቃል፡፡ ደቀ መዝሙር ኢየሱስን ያመነ እና የእርሱን ትምህርት የሚታዘዝ ማንኛውም ሰው የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ተብሎ ይጠራል፡፡ ጠቢታ፣ “ዶርቃስ” ተብሎ ይተረጎማል፡፡ ጠቢታ የሚለው ስሟ በአረማይክ ቋንቋ ሲሆን ዶርቃስ የሚለው ስሟ ደግሚ በግሪክ ቋንቋ ነው፡፡ የሁለቱም ስሞች ትርጉም “ጋዜል” ነው፡፡ መልካም ሥራ የሞላበት "በጣም ብዙ መልካም ሥራዎችን መሥራት" በእነዚህ ቀናት እንዲህ ሆነ "ጴጥሮስ በልዳ እያለ እንዲህ ሆነ፡፡” ይህ በተዘዋዋር መልኩ የተገለጸ መረጃ ነው፡፡
ወደ እርሱ ሁለት ሰዎችን ላኩ "ደቀ መዛሙርቱ ሁለት ሰዎችን ወደ ጴጥሮስ ዘንድ ላኩ" ባልቴቶች ባል የሞተባቸው ሴቶች ከእነርሱ ጋር በነበረችበት ወቅት "ከደቀ መዛሙርቱ ጋር በሕይወት ሳለች" (UDB)
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ስለጠብታ የተነገረው ታሪክ የሚያበቃው በቁጥር 42 እና 43 ላይ ነው፡፡ ቁጥር 43 ታሪኩ ካለቀ በኋላ ጴጥሮስ ላይ ምን እንደደረሰበት ታሪኩ ይነግረናል፡፡ (ተመልከት: talink End of Story) ሁሉንም አስወጣቸው በዚህ ሁኔታ ውስጥ ጴጥሮስ ለጠብታ መጸለይ ይችል ዘንድ ሁሉንም ሰዎች ከቤት እንዲወጡ አደረገ፡፡ ይህ ነገር ታወቀ ጴጥሮስ ጠብታን ከሞት በተዓምራት የማስነሳቱ ነገር በጌታ አመኑ ይህ “በጌታ ኢየሱስ ወንጌል ማመናቸውን” የሚያሳይ ገለጻ ነው፡፡ ጴጥሮስም በዚያ ቆየ "ጴጥሮስም በዚያ እንዲቆይ ተደረገ"
1 በቂሣርያ ከተማ ውስጥ የኢጣሊቄ ክፍለ ሰራዊት በሚባል የመቶ አለቃ የሆነ ቆርኔሌዎስ የሚባል ሰው ነበረ። 2 እርሱም መንፈሳዊ፣ ከቤተ ሰቡ ጋር እግዚአብሔርን የሚያመልክ፣ ለአይሁድ ብዙ ገንዘብ የሚሰጥና ሁልጊዜ ወደ እግዚአብሔር የሚጸልይ ሰው ነበረ። 3 ከቀኑ በዘጠኝ ሰዓት የእግዚአብሔር መልአክ ወደ እርሱ ሲመጣ በራእይ በግልጽ ታየው። መልአኩ፣ “ቆርኔሌዎስ!” አለው። 4 ቆርኔሌዎስ መልአኩን አተኵሮ ተመለከተውና ፈርቶ እንዲህ አለ፤ “ጌታዬ ሆይ፣ ይህ ምንድን ነው?” መልአኩም መልሶ፣ “ጸሎትህና ምጽዋትህ በመታሰቢያነት ወደ እግዚአብሔር ደርሶአል። 5 ጴጥሮስም ተብሎ የሚጠራውን ስምዖን የሚባለውን ሰውየ ለማስመጣት አሁን ወደ ኢዮጴ ከተማ ሁለት ሰዎችን ላክ። 6 ሰውየው ቤቱ በባሕሩ አጠገብ ከሚገኝ ስምዖን ከሚባለው ከቆዳ ፋቂው ጋር አለ” አለው። 7 ያነጋግረው የነበረው መልአክ እንደ ሄደ፣ ቆርኔሌዎስ ከሚያገለግሉት ወታደሮች መካከል እግዚአብሔርን ያመልክ የነበረ አንድ ወታደርንና ከቤት አሽከሮቹ ሁለቱን ጠራ። 8 ቆርኔሌዎስ የሆነውን ሁሉ ነግሮአቸው ወደ ኢዮጴ ላካቸው። 9 በሚቀጥለው ቀን ስድስት ሰዓት አካባቢ፣ በጕዞ ላይ ሳሉና ወደ ከተማዋ ሲቃረቡ፣ ጴጥሮስ ሊጸልይ ወደ ሰገነቱ ወጣ። 10 ራበውና አንዳች ነገር ለመብላት ፈለገ፤ ነገር ግን ሰዎች ምግብ በማዘጋጀት ላይ ሳሉ፣ በተመስጦ ውስጥ ገባ፤ 11 ሰማይ ተከፍቶ፣ ትልቅ ሸማ የሚመስል አንድ መያዣ በአራቱ ጠርዞቹ ተይዞ ወደ ምድር ሲወርድም አየ። 12 በውስጡም አራት እግር ያላቸው እንስሳት ሁሉና በምድር ላይ የሚሳቡ ፍጡራን፣ የሰማይ ወፎችም ነበሩበት። 13 “ጴጥሮስ ሆይ፣ ተነሥና ዐርደህ ብላ” የሚል ድምፅ ለጴጥሮስ መጣ። 14 ጴጥሮስም፣ “ጌታ ሆይ፣ አይሆንም፤ ምክንያቱም እኔ ርኩስና አስጸያፊ የሆነ ምንም ነገር ፈጽሞ በልቼ አላውቅም” አለ። 15 እንደገናም ድምፅ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ጴጥሮስ መጣ፤ “እግዚአብሔር ቅዱስ ያደረገውን ርኩስ ብለህ አትጥራው” የሚል ድምፅ። 16 ይህም ሦስት ጊዜ ሆነ፤ ከዚያም መያዣው ወዲያው ወደ ሰማይ ተመልሶ ተወሰደ። 17 ጴጥሮስ ያየው ራእይ ምን ትርጕም ሊኖረው እንደሚችል በጣም ግራ ገብቶት ሳለ፣ ወደ ቤት የሚያስሄደውን መንገድ ጠይቀው ካገኙ በኋላ እነሆ፣ ቆርኔሌዎስ የላካቸው ሰዎች በበሩ ፊት ለፊት ቆሙ። 18 ድምፃቸውን ከፍ በማድረግም ጴጥሮስ የሚባለው ስምዖን በዚያ መኖሩንና አለመኖሩን ጠየቁ። 19 ጴጥሮስ ስለ ራእዩ በማሰብ ላይ ሳለ፣ መንፈስ ቅዱስ ጴጥሮስን እንዲህ አለው፤ “እነሆ፣ ሦስት ሰዎች ይፈልጉሃል። 20 ተነሥና ውረድ፤ ከእነርሱም ጋር ሂድ። ዐብረሃቸው ለመሄድ አትፍራ፤ ምክንያቱም የላክኋቸው እኔ ነኝ።” 21 ስለዚህም ጴጥሮስ ወደ ሰዎቹ ወርዶ፣ “የምትፈልጉት ሰው እኔ ነኝ። የመጣችሁት ለምንድን ነው?” አላቸው። 22 እነርሱም እንዲህ አሉት፤ "እግዚአብሔርን የሚያመልክ፣ በአይሁድ ሕዝብ ሁሉ ዘንድም የተመሰገነ ቆርኔሌዎስ የሚባል ጻድቅ ሰው፣ ወደ ቤቱ ሰው ልኮ እንዲያስመጣህ የእግዚአብሔር መልአክ ነገረው፤ እንዲህ ያደረገውም ከአንተ መልእክትን መስማት እንዲችል ነው።” 23 ጴጥሮስም እንዲገቡና ከእርሱና ዐብረውት ከነበሩ ሰዎች ጋር እንዲቈዩ በእንግድነት ተቀበላቸው። በማግስቱ ጧት ጴጥሮስ ተነሣና ከእነርሱ ጋር ሄደ፤ በኢዮጴ ከነበሩት ወንድሞችም አንዳንዶቹ ዐብረውት ሄዱ። 24 በሚቀጥለው ቀን ቂሣርያ ደረሱ። ቆርኔሌዎስ እየጠበቃቸው ነበር፤ ዘመዶቹንና የቅርብ ወዳጆቹንም ጠርቶ እንዲሰበሰቡ አደረገ። 25 ጴጥሮስ ሲገባ፣ ቆርኔሌዎስ አግኝቶት እግሩ ላይ ወድቆ ሰገደለት። 26 ነገር ግን ጴጥሮስ አነሣውና፣ “ተነሥ ቁም፤ እኔ ራሴም ሰው ነኝ” አለው። 27 ጴጥሮስ ከቆርኔሌዎስ ጋር እየተነጋገረ ወደ ውስጥ ሲገባ፣ የተሰበሰቡ ብዙ ሰዎችን አገኘ። 28 እንዲህም አላቸው፤ "አይሁዳዊ የሆነ ሰው ከሌላ ሕዝብ ከሆነ ጋር መገናኘት ወይም እርሱን መጎብኘት በሕግ እንደማይፈቀድለት እናንተ ራሳችሁ ታውቃላችሁ። ነገር ግን እግዚአብሔር ማንንም ሰው ርኩስ ወይም አስጸያፊ ብዬ መጥራት እንደማይገባኝ ለእኔ አሳይቶኛል። 29 ሲላክብኝ ሳልከራከር የመጣሁት ከዚህ የተነሣ ነው። ስለዚህ ለምን እንደ ላካችሁብኝ እጠይቃችኋለሁ።" 30 ቆርኔሌዎስም እንዲህ አለ፤ “ከአራት ቀን በፊት ልክ በዚህ ሰዓት በዘጠኝ ሰዓት በቤቴ ውስጥ እጸልይ ነበር፤ እነሆም ነጭ ልብስ ለብሶ ፊት ለፊቴ ቆመና፣ 31 ‘ቆርኔሌዎስ ሆይ፣ ጸሎትህ በእግዚአብሔር ዘንድ ተሰምቶአል፤ ምጽዋትህም መታሰቢያ ሆኖልሃል። 32 ስለዚህ ወደ ኢዮጴ ሰው ላክና ጴጥሮስም የሚባለውን ስምዖንን ወደ አንተ ጠርተህ አስመጣ። እርሱ በቆዳ ፋቂው በስምዖን ቤት በባሕር አጠገብ ተቀምጦአል’ አለኝ። 33 ስለዚህ ወዲያው ላክሁብህ። አሁን መምጣትህ መልካም አደረግህ። አሁን እንግዲህ እኛ ሁላችን እግዚአብሔር እንድትናገር ያዘዘህን ሁሉ ለመስማት በእግዚአብሔር ፊት እንገኛለን።" 34 ጴጥሮስም እንዲህ ብሎ ተናገረ፦ “እግዚአብሔር ለማንም እንደማያዳላ በእውነት ተገንዝቤአለሁ። 35 ይልቁን በማንኛውም ሕዝብ ውስጥ እግዚአብሔርን የሚፈራ፣ የጽድቅ ተግባራትንም የሚፈጽም ሁሉ በእርሱ ዘንድ ተቀባይነት አለው። 36 እግዚአብሔር በሁሉ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል የሰላምን የምሥራች ባወጀበት ጊዜ፣ ወደ እስራኤል ሕዝብ የላከውን መልእክት ታውቃላችሁ፦ 37 ዮሐንስ ካወጀው ጥምቀት በኋላ፣ በገሊላ በመጀመር በይሁዳ ሁሉ የታዩትን የተፈጸሙ ሁነቶችን እናንተ ራሳችሁ ታውቃላችሁ፤ 38 ሁነቶቹም እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስና በኀይል እንዴት እንደ ቀባው የናዝሬቱን ኢየሱስን የሚመለከቱ ናቸው። ኢየሱስ መልካም እያደረገና ለዲያብሎስ የተገዙትን እየፈወሰ ዞረ፤ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና። 39 በዕንጨት ላይ ሰቅለው የገደሉት ይህ ኢየሱስ ከአይሁድ አገርም በኢየሩሳሌምም ለፈጸማቸው ተግባራት ሁሉ እኛ ምስክሮች ነን። 40 ይህን ሰው እግዚአብሔር በሦስተኛው ቀን አስነሣው፤ እንዲገለጥም አደረገው፤ 41 ይኸውም እግዚአብሔር አስቀድሞ መርጦአቸው ለነበሩ ምስክሮች እንጂ፣ ለሕዝቡ ሁሉ አይደለም፦ ከሙታን ከተነሣ በኋላ ዐብረነው የበላንና የጠጣን እኛው ራሳችን ነን። 42 ለሕዝቡ እንድንሰብክና በሕያዋንና በሙታን ላይ እንዲፈርድ፣ እግዚአብሔር የመረጠው ይህ እንደ ሆነ እንድንመሰክር አዘዘን። 43 በእርሱ የሚያምን ሁሉ በስሙ የኀጢአትን ይቅርታ እንዲቀበል ነቢያት ሁሉ የሚመሰክሩት ስለ እርሱ ነው።” 44 ጴጥሮስ እነዚህን ነገሮች ገና እየተናገረ ሳለ፣ መልእክቱን በሚሰሙት ሁሉ ላይ መንፈስ ቅዱስ ወረደባቸው። 45 ከተገረዙት ወገን የሆኑ አማኞች፦ ከጴጥሮስ ጋር የመጡትም ሁሉ ተደነቁ፤ ምክንያቱም መንፈስ ቅዱስ በአሕዛብም ላይ ወርዶ ነበር። 46 እነዚህ አሕዛብ በሌሎች ቋንቋዎች ሲናገሩና እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑ ሰምተዋቸዋልና። ከዚያም በኋላ ጴጥሮስ መልሶ፣ 47 “እንደ እኛ መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉ እነዚህ ሰዎች እንዳይጠመቁ ማን ውሃ ሊከለክላቸው ይችላል?” አለ። 48 በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንዲጠመቁም አዘዛቸው። ከዚያ በኋላ ከእነርሱ ጋር ጥቂት ቀን እንዲቈይ ጴጥሮስን ለመኑት።
አጠቃላይ መረጃ: ይህ ስለቆርኖሊዮስ ቲክ ጅማሬ ነው፡፡ ይህ ስለእርሱ የኃላ ታሪክ መረጃ ይሰጠናል፡፡ የሆነ ሰው ነበር ይህ በታሪኩ ውስጥ አዲስን ሰው የማስዋወቂያ መንገድ ነው፡፡ ስሙም ቆርኖሊዮስ ይባላል፣ የመቶ አለቃ ነበር "ስሙ ቆርኔሊዮስ ይባላል፡፡ በእጣልያን ሀገር ውስጥ በሚገኘው የሮማዊያን ግዛት ውስጥ የመቶ ወታደሮችን አለቀ ነበር፡፡" እግዚአብሔርን የሚያመልክና የሚፈራ ሰው ነበር "በእግዚአብሔር የሚያምን እና በሕይወቱ እርሱን ለማክበር እና ለማምለክ የሚፈልግ ሰው ነበር" ከቤተሰቡ ሁሉ ጋር "ከእርሱ የቤተሰብ አባለላት ሁሉ ጋር"
ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ይህ ለአይሁዳዊን የተለመደ የጸሎት ሰዓት ነው፡፡ በግልጽ ተመለከተ "ቆርኔሊዮስ በግልጽ አየ" ቆዳ ሠሪ ከእንስሳት ቆዳ የቆዳ ውጤቶችን የሚያዘጋጅ ሰው፡፡
የተናገረው መለአክ ከሄደ በኋላ "ቆርኔሊዮስ የተመለከተው ራዕይ ካለቀ በኋላ" የሆነውን ነገር ሁሉ ነገራቸው ቆርኔሊዮስ ለሁለቱ ሎሌዎቹ እና ወታደሩ ነገራቸው፡፡ ወደ ጆባ ላካቸው "ሁለቱን ሎሌዎቹን እና አንዱን ወታደር ወደ ጆባ ላካቸው"
የሐዋርያት ሥራ 10፡ 9-12 አጠቃላይ መረጃ: ታሪኩ ከቆርኔሊዮስ ጴጥሮስ የሆነውን ነገር ወደ መዘገብ ተለወጠ፡፡ በጉዞ ላይ እያሉ "በቆርኔሊዎስ ትዕዛዝ መሠረት ሁለት ሎሌዎች እና ወታደሩ ወደ ጆባ እየተጓዙ ሳለ" ሰማይ ተከፍቶ ተመለከተ ይህ የጴጥሮ ራዕይ ጅማሬ ነበር፡፡ ትልቅ ጨርቅ የሚመስል ነገር እንስሶችን የያዘው ዕቃ ትልቅ ጨርቅ ይመስል ነበር፡፡
ድምፅ ሰማ የተናገረው ማን እንሆነ አልተገለጸም፡፡ ይሁን እንጂ የድምፁ ምንጭ እግዚአብሔር እንጂ ሴጣን አለመሆኑን ማወቅ ይቻላል፡፡ ጌታ ጴጥሮስ በዚህ ሥፍራ ላይ የተጠቀው ቃል የአክብሮት ቃል የሆነውን “ጌታ” የሚል ነው፡፡ እርኩስ የሆነ እና ንጹሕ ያለሆነ ነገር በልቼ አላውቅም፡፡ በዚህ ሥፍራ በተዘዋዋር መልኩ መረዳት የሚቻለው የቀረቡት እንስሳት በሙሴ ሕግ መሠረት እርኩስ የተባሌ እና ለመብልነት የማይሆኑ ናቸው፡፡
እነሆ “እነሆ” የሚለው ቃል በታሪኩ ውስጥ አዲስ አስገራሚ ነገር መኖሩን ያሳየናል፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሁለት ሰዎች በሩ ጋር መቆማቸው ነው፡፡ ከበሩ ፊት "ከቤቱ ፊት ለፉት ቆመዋል፡፡" በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ቤት ግድግዳ እና ትክክለኛ በር እንዳለው በተዘዋዋር መልኩ ተጠቅሷ፡፡ እንዲሁም ይጣራሉ በቆርኔሊዮስ የተላኩት ሰዎች ከቤቱ ውጭ ሆነው እነ ጴጥሮስ ዬት እንዳሉ ይጠይቃሉ፡፡
ጴጥሮስ ገና ስለተመለከተው ራዕይ እያሰላሰለ ሳለ "ጴጥሮስ ስላየው ራዕይ እያሰላሰለ ሳለ" መንፈስ "መንፈስ ቅዱስ" ተመልከት "ተጠንቀቅ" ወይም "ተነሥ"
እንዲህ አሉት "ከቆርኔሊዎስ ዘንድ ተልዕከው የመጡት ሦስቱ ሰዎች ለጴጥሮስ እንዲህ አሉት" ቆርኔሊዎስ በአይሁዊያን ሁሉ ዘንድ የታወቀ ሰው ነበር ብዙ የአይሁድ ሰዎች ስለ ቆርኖሌዎስ መልካም ነገር ይናገራሉ፡፡ የአይሁድ ሕዝብ ሁሉ ይህ በግነት መልኩ የቀረበው የቆርኖሌዊስ ባሕርይ በብዙ አይሁዳዊያን ዘንድ በጣም የሚታወቅ ነበር፡፡
የሐዋርያት ሥራ 10፡ 24-24 መጡ "ጴጥሮስ፣ ጴጥሮስን ከጆባ አጅበው የመጡት ሰዎች እና የቆርኖሊዎስ ሌሎዎች ሆነው" ዘመዶቹን እና ሁሉም ጓደኞቹን ጠራው፡፡ "እርሴ የሚለው ቃል የሚያመለክተው ቆርኖሊዎስን ነው፡፡
የሐዋርያት ሥራ 10፡ 25-26 በእግሩ ፊት ተደፉ ቆርኖሊዎስ በጴጥሮስ እግር ፊት ስወድቅ (ይህ የስግደት ተግባር ነው (UDB) እንጂ እንዲሁ የአክብሮት ተግባር አይደለም፡፡ ተነስ፤ እኔ እራሴ እንደ አንተው ሰው ነኝ ይህ ለቆርኖሊዎስ ጳውሎስን እንዳያመልክት የተነገረው መካከለኛ የሆነ ተግሳሳጽ ወይም ማስተካከያ ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስ በቆርኖሊዎስ ቤት ውስጥ ለተሰበሰቡት ሰዎች እንዲህ ሲል ንግግር አደረገ፡፡ ከእርሱ ጋር ተነጋገረ "ቆርኖሊዎስን አናገረው" ብዙ ሰዎች ተሰብስበው አገኘ "ብዙ አሕዛብ በዚያ ተሰብስቦ አገኘ፡፡" ከዚህ በተዘዋዋሪ መንገድ መረዳት የሚቻለው ቆርኖሊዎስ የጋበዛቸው ሰዎች አሕዛብ መሆናቸውን ነው፡፡ ለአይሁዳዊ ሰው ይህ በሕግ የተፈቀደ አይደለም "ይህ ለአይሁዳዊ ሰው በሕግ የተከለከለ ነው" ይህንን አንተ ራስህ ታውቃለህ ጴጥሮስ ለቆርኖሊዎስ እና እርሱ ለጋበዛቸው እንግዶች በመናገር ላይ ነው፡፡ “ስለዚህ ለምን እንደ አስጠራኸኝ ማወቅ እፈልጋለሁ፡፡” ምንም እንኳ ቆርኖሊዎስ ጥያቄውን ያቀረበው በቀጥታ ለቆርኖሊዎስ ቢሆንም “እናንተ” የሚለው ቃል በዚያ ሥፍራ ያሉትን አሕዛቦችን ሁሉ ያካትታል (ብዙ ቁጥር ነው)፡፡
የሐዋርያት ሥራ 10፡ 30-33 አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ቆርኖሊዎስ ለጴጥሮስ ጥያቄ እንዲህ ሲል ምላሽ ሰጠ፡፡ አጠቃላይ መረጃ: በቁጥር 31 እና 32 ላይ ቆርኖሊዎስ መልአኩ በዘጠኝ ሰዓት በተገለጠለት ጊዜ የተናገረውን ነገር ቃል በቃል በመጥቀስ ምላሽ ሰጠ፡፡ ከአራት ቀናት በፊት በመጽሐፍ ቅዱስ ባሕል መሠረት ይህ የነበሩበትን ቀንንም ያካትታል፡፡ በዘመናችን የምዕራባዊያን ባሕል መሰረት ይህ እንዲህ ሊሆን ይችላል “ከሦስት ቀናት በፊት” እየጸለይኩ ሳለ አንዳንድ ጥንታዊያን ቅጂዎች “ከእየጾምኩ” ይልቅ “እየጾምኩና እየጸለይኩ ሳለ”S ይላሉ፡፡ በዘጠን ሰዓት ላይ አይሁዊያን ወደ እግዚአብሔር የሚጸልዩበት የከሰዓቱ የተለመደው ሰዓት፡፡ እግዚብሔር አስቦሃል "እግዛብሔር ተመልክቶሃል" ስምኦን እንዲሁም በሌላ ስሙ ጴጥሮስ ተብሎ የሚጠራ ሰውን አስጠራ "ጴጥሮስ ተብሎ የሚታወቀውን ስምኦንን አስጠራ" እኔ ወደ አንተ እልከዋለሁ "እርሱን" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጴጥሮስን ብቻ ነው፡፤ እኛ ሁላችን በዚህ አለን "እኛ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጴጥሮስ ስናገር ይሰሙ ዘንድ ወደቆርኖሊዎስ ቤት የተጠሩትን ሰዎች ሁሉ ነው፡፡ “እኛ” የሚለው ቃል ጴጥሮስን አያካትትም፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስም በቆርኖሊዎስ ቤት ውስጥ ለሚገኙት ሰዎች ሁሉ መናገር ጀመረ፡፡ ከዚያም ጴጥሮስ አፉን ከፍቶ እንዲህ አለ "ጴጥሮስም ልናገራቸው ጀመር" ማንም እርሱን የሚያመልክ እና ትክክለኛውን ነገር የሚያደርግ ሰው በእርሱ ዘንድ ተቀባይነት አለው "እርሱ የሚያመልኩትን እና ትክክለኛውን ነገር የሚያደርጉ ሰዎችን ሁሉ ይቀበላል፡፡"
መልዕክቱን ታውቃላችሁ "ቃሉን ታውቃላችሁ እርሱ የሁሉ ጌታ ነውl "ሁሉም' የሚለው ቃል ሁሉን ሰው ይወክላል" እናንተ እረራሳችሁ ይህ ቆርኖሊዎስን እና የእርሱን እንግዶች ይወክላል፡፡
እኛ ምስክሮች ነን "ሐዋሪያቱ ምስክር ናቸው፡፡" ጴጥሮስ “እኛ” የሚለውን ቃል በመጠቀም አድማጮቹን ከዚህ ክልል ውጪ አድርጎዋቸዋል፡፡ ስለዚህ እርሱ "ስለዚህ ኢየሱስ እንዳደረገው" እነርሱ የገደሉት "የአይሁድ መሪዎች የገደሉት" ይህ ሰው "ይህ ሰው ኢየሱስ" እግዚአብሔር ከሞት አስነሳው "እግዚአብሔር እንደገና በሕይወት እንዲኖር አደረገው" እደገና እንዲታወቅ አደረገ "እንገና እንድገለጥ አድረገው"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስ በ ACT 10:34 ላይ በቆርኖሊዎስ ቤት ውስጥ ላሉ ሰዎች የጀመረውን ንግግር ጨርሷል፡፡ አዞናል "እግዚአብሔር ምስክር እንድንሆን ወይም ሐዋርያት እንሆን ዘንድ አዝዞናል፡፡ ይህ የጴጥሮስን አድማጮችን የማያካትት ነው፡፡ ይህ በእግዚአብሔር የተመረጠውን ነው “እግዚአብሔር ኢየሱስን መርጧል" ሕያዋን እና ሙታን ይህ አሁን በሕይወት ያሉ ሰዎችን እና የሞቱ ሰዎችን ያካትታል፡፡ ሰዎች ሁሉ ምስክር የሚሆኑ ለእርሱ ነው፡፡ "ነቢያት ሁሉ ለኢየሱስ ምስክር ይሆናሉ፡፡"
ያደምጡ በነበሩት ሰዎች ሁሉ ላይ ወረደ "ሁሉ" ጴጥሮስ የተናገረውን ነገር ያመኑትን በቤቱ ውስጥ የነበሩትን አይሁዊን ያልሆኑ ሰዎችን የሚያመለክት ሊሆን ይችላል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ወረደ አማራጭ ትርጉም፡ "እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን አፈሰሰ" ስጦታ "ነጻ ስጦታ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ይህ ስለቆርኖሊዎስ የተነገረው ታሪክ ፍጻሜ ነው፡፡ አሕዛብ በሌላ ቋንቋ ይናገሩ እና እግዚአብሔርን ያመልኩ ነበር እነዚህ አይሁዳዊን በእርግጥም አሕዛብ እግዚአብሔርን እያመለኩ እንደሆነ እንዲያውቁ ያደረጋቸው የሚታወቅ ቋንቋ ነበር፡፡ እነዚህ ሰዎች ማለትም . . . የተቀበሉ ሰዎች እንዳይጠመቁ የሚከለክል ሰው ይኖራንል? አማራጭ ትርጉም፡ "እነዚህ ሰዎች እንዳይጠመቁ የሚከለክል ማንም ሰው ሊኖር አይችልም፡፡ እነዚህ ሰዎች እኛ . . . እነርሱ ተቀብለዋልና ልጠመቁ ይገባቸዋል፡፡ ይጠመቁ ዘንድ አዘዘ አመራጭ ትርጉም፡ "ጴጥሮስ አሕዛብ አማኞችን ያጠምቁ ዘንድ አይሁዳዊያን አማኞችን አዘዘ፡፡" ጠየቁት "አሕዛብ ጴጥሮስን ጠየቁት"
1 ሐዋርያትና በይሁዳ የነበሩት ወንድሞች አሕዛብ ደግሞ የእግዚአብሔርን ቃል ተቀብለው እንደ ነበር ሰሙ። 2 ጴጥሮስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጥቶ በነበረ ጊዜ፣ ከመገረዝ ወገን የነበሩት ነቀፉት፤ 3 “ካልተገረዙ ወንዶች ጋር ተባብረሃል፣ አብረሃቸውም በልተሃል!” አሉት። 4 ጴጥሮስ ግን እንዲህ ብሎ ጉዳዩን በዝርዝር ያብራራላቸው ጀመር፤ 5 እኔ በኢዮጴ ከተማ እጸልይ ነበር፤ በተመስጦም አራት ማዕዘን ያለው ታላቅ ሸማ የመሰለ ዕቃ መያዣ ከሰማይ ሲወርድ ራእይ ዐየሁ፤ ወደ እኔ ወረደ፣ 6 ትኵር ብዬ ተመለክትሁትና ስለ እርሱ ዐሰብሁ። አራት እግር ያላቸው የምድር እንስሳትን፣ አራዊትን፣ የሚሳቡ ፍጥረታትን፣ የሰማይ አዕዋፍንም ዐየሁ። 7 በዚያን ጊዜ አንድ ድምፅ፣ “ጴጥሮስ ሆይ፣ ተነሣ፣ አርደህም ብላ!” ሲለኝ ሰማሁ። 8 “ጌታ ሆይ፣ አይሆንም፣ ምክንያቱም ጸያፍ ወይም ርኩስ የሆነ ምንም ነገር ከቶ ወደ አፌ ገብቶ አያውቅም” አልሁ። 9 ነገር ግን ድምፁ ዳግመኛ ከሰማይ፣ “እግዚአብሔር ንጹሕ ነው ያለውን አንተ ርኩስ ብለህ አትጥራው” ብሎ መለሰ። 10 ይህም ሦስት ጊዜ ሆነ፤ ከዚያም ሁሉም ነገር እንደ ገና ወደ ሰማይ ተወሰደ። 11 እነሆ፣ ወዲያውኑ እኛ በነበርንበት ቤት ፊት ለፊት ሦስት ሰዎች ቆመው ነበር፤ እነርሱም ከቂሣርያ ወደ እኔ የተላኩ ናቸው። 12 መንፈስም ከእነርሱ ጋር እንድሄድ፣ ስለ እነርሱም ልዩነት እንዳላደርግ አዘዘኝ። እነዚህ ስድስት ወንድሞች አብረውኝ ሄዱ፤ ወደ ሰውዬውም ቤት ገባን። 13 እርሱም መልአክ በቤቱ ቆሞ እንዳየና እንዲህ እንዳለውም ነገረን፤ “ወደ ኢዮጴ ሰዎችን ላክና ሌላው ስሙ ጴጥሮስ የሆነውን፣ ስምዖንን አስመጣ። 14 አንተና ቤተ ሰቦችህ ሁሉ የምትድኑበትን መልእክት ይነግርሃል።” 15 ለእነርሱ መናገር እንደ ጀመረና ልክ በመጀመሪያ በእኛ ላይ እንደ ሆነው፣ መንፈስ ቅዱስ በእነርሱ ላይ ወረደ። 16 “ዮሐንስ በእርግጥ በውሃ አጥምቆ ነበር፤ እናንተ ግን በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ” ብሎ እንደ ተናገረ፣ የጌታን ቃሎች አስታወስሁ። 17 እኛ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ባመንን ጊዜ እንደ ሰጠን ያለ ስጦታ እግዚአብሔር ለእነርሱ ከሰጣቸው እንግዲያ፣ እግዚአብሔርን እቃወም ዘንድ እኔ ማን ነበርሁ?” 18 እነርሱ እነዚህን ነገሮች በሰሙ ጊዜ፣ መልስ አልሰጡም፤ ነገር ግን እግዚአብሔርን አመስግነው፣ “እግዚአብሔር ለአሕዛብ ለሕይወት የሚሆን ንስሓን ደግሞ ሰጥቷቸዋል” አሉ። 19 ስለዚህ በእስጢፋኖስ መሞት የተጀመረው ሥቃይ ከኢየሩሳሌም የበተናቸው እነዚህ አማኞች እስከ ፊንቄ፣ ቆጵሮስና አንጾኪያ ድረስ ሄዱ። ስለ ኢየሱስ የሚናገረውን መልእክት ለአይሁድ ብቻ እንጂ ለሌላ ለማንም አልተናገሩም። 20 ነገር ግን ከቆጵሮስና ከቀሬና የነበሩ ሰዎች አንዳንዶቹ ወደ አንጾኪያ መጥተው ለግሪኮች ተናገሩ፤ ጌታ ኢየሱስንም ሰበኩላቸው። 21 የጌታም እጅ ከእነርሱ ጋር ነበረ፤ በቍጥ ብዛት ያላቸው ሰዎች አምነው ወደ ጌታ ዘወር አሉ። 22 ስለ እነርሱ ወሬ በኢየሩሳሌም ባለችው ጉባኤ ተሰማ፤ በርናባስንም እስከ አንጾኪያ ላኩት። 23 እርሱም መጥቶ የእግዚአብሔርን ስጦታ ባየ ጊዜ፣ ደስ አለው። ከሙሉ ልባቸው ከጌታ ጋር እንዲኖሩ ሁላቸውንም አበረታታቸው። 24 ምክንያቱም እርሱ መንፈስ ቅዱስና እምነት የሞላበት በጎ ሰው ነበር፤ ብዙ ሕዝብም ወደ ጌታ ተጨመሩ። 25 ከዚያም በርናባስ ሳውልን ሊፈልግ ወደ ጠርሴስ ወጣ። 26 ባገኘውም ጊዜ፣ ወደ አንጾኪያ አመጣው። እንዲህም ሆነ፣ አንድ ዓመት ሙሉ በቤተ ክርስቲያን አብረው ተሰበሰቡ፣ ብዙ ሕዝብንም አስተማሩ። ደቀ መዛሙርቱ በመጀመሪያ በአንጾኪያ ክርስቲያን ተባሉ። 27 በእነዚያ ቀናትም አንዳንድ ነቢያት ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ወረዱ። 28 ከእነርሱ አንዱ አጋቦስ የተባለው፣ ተነሥቶ ቆመና በመላው ዓለም ላይ ታላቅ ራብ እንደሚሆን በመንፈስ አመለከተ። ይህም በቀላውዴዎስ ዘመን ሆነ። 29 ስለ ሆነም፣ ደቀ መዛሙርቱ እያንዳንዳቸው እንደ ዐቅማቸው በይሁዳ ላሉት ወንድሞች እርዳታ ለመላክ ወሰኑ። 30 ይህንም አደረጉ፤ በበርናባስና በሳውል እጅ ለሽማግሌዎቹ ገንዘብ ላኩ።
አጠቃላይ መረጃ: ይህ በታሪክ ውስጥ አዲስ ታሪክ የሚጀመርበት ሥፍራ ነው፡፡ ጴጥሮስ ወደ እየሩሳሌም በመሄድ በዚያ ካሉ አይሁዳዊን ጋር ንግግር ይጀምራል፡፡ አሁን ይህ የአዲስ ነገር ጅማሬን ያሳያል፡፡ በይሁዳ የነበሩት "በይሁዳ ከተማ ይኖሩ የነበሩ" የእግዚአብሔርን ቃል ተቀበሉ ይህ አሕዛብ የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል መቀበላቸውን፣ መንፈስ ቅዱስ በእነርሱ ላይ መውረዱን እና አሕዛብ መጠመቃቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ ጴጥሮስ ወደ ኢየሩሳሌም በመጣ ጊዜ እየሩሳሌም የሚትገኘው በተራራማ ሥፍራ ነው፡፡ የተገረዙት ወገኖች እነዚህ ቡድኖች የክርስቶስ ተከታዮች የሆኑ ሰዎች ሁሉ መገረዝ እናየሙሴን ሕግ መጠበቅ አለባቸው የሚለው አይሁዊንን ናቸው፡፡ ገሰጹት "ከእርሱ ጋር ተነጋገሩ" ከእነርሱ ጋር በመብላቱ የተገረዙ ሰዎች ካልተገረዙ ሰዎች ጋር መብላታቸው ከሕግ ውጪ ስለሆነ ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስ ለዚህ ተቋቃውሞ ስለተመለከተው ራዕጥ እና በቆርኖሊዎስ ቤት ውስጥ የሆነውን ነገር መሠረት በማድረግ ምላሽ ሰጠ፡፡ ጴጥሮስ ማስረዳት ጀመረ ጴጥሮስ የአይሁድ አማኞችን አልተቻቸውም ልቁንም እንደጓደኛ በመሆን የሆነውን ነገር አብራራላቸው፡፡ በምድር ላይ ያሉ አራት እግራ ያላቸው እንስሳት በምድር ላይ ያሉ አራት እግር ያላቸው እንስሳት - ይህ ምንአልባት የሚያመለክተው ሰዎች ሊገሯቸው የሚችሉ እንስሳትን ነው፡፡
የዱር እንስሳት ይህ ሰዎች ልቆጣጠሯቸው ወይም ሊገሯቸው የማይችሉትን እንስሳትን ነው፡፡ ተሳቢ እንስሳትን እነዚህ በምድር ላይ የሚሳቡ እንስሳትን ያመለክታሉ፡፡
ያልተቀደሰ ወይም ንጹሕ ያለሆነ ነገር ወደ አፌ ገብቶ አያውቅም በቅርጫቱ ውስጥ የነበሩት እንስሳት አይሁዳዊን በብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ውስጥ በአይሁድ ሕግ መሠረት እንዳይበሏቸው የተከለከሉት እንስሳት ናቸው፡፡ አማራጭ ትርጉሞች፡ "እኔ ቅዱስ እና ንጹሕ የሆኑ ነገሮችን ብቻ ነው የሚበላው፡፡" እግዚአብሔር ንጹሕ ያደረገውን እርኩስ ብለህ አትጥራ ይህ “እግዚአብሔር ንጹሕ ብሎ የጠራውን ነገር ንጹሕ አትበል” ለማለት ነው፡፡” ንጹሕ ያልሆነ በብሉይ ኪዳን የአይሁድ ሕግ አንድ ሰው በሥርዓቱ “ንጹሕ አይደለም” የሚባለው በተለያዩ መንገዶች ነው፡፡ ከእነርሱ መካከል አንዱ የተከለከሉ እንስሳትን በመብላት ነው፡፡
እነሆ "ወዲያው" ወይም "በዚያው ወቅት" (UDB)፡፡ እነሆነ - ይህ ቃል በታኩ ውስጥ አዲስ ሰው መግባቱን ያመለክተናል፡፡ በቋንቋችሁ እንዲህ ዓይቱን ነገር ማድረግ የሚቻልበት መንገድ ይኖራል፡፡ ተልከዋል አማራጭ ትርጉም፡ “የሆነ ሰው ልኳቸዋል፡፡” በእነርሱ መካከል ምን ዓይነት ልዩነት እንዳላደረግ "አሕዛብ ወይም አይሁዳዊያን ናቸው ብዬ በመካከላቸው ልዩነት እንዳላደረግ" እነዚህ ስድስት ወንድሞች "እነዚህ ስድስት አይሁዳዊያን አማኞች" ጴጥሮስ ተብሎ የሚጠራውን ስሞኦንን ይዘውት መጡ "ጴጥሮስ ተብሎ የሚጠራውን ስምአፐን ይዘውት መጡ" ትድናላችሁ አማራጭ ትርጉም፡ "እግዚአብሔር ያድናችኋል"
በመጀመሪያ በእኛ ላይ እንደሆነው ሁሉ በእርሱ ላይም መንፈስ ቅዱስ ወረደባቸው "በጴንጤቆስጤ ቀን መንፈስ ቅዱስ በአይሁዳዊያን አማኞች ላይ እንደወረደ ሁሉ እንዲሁም በአሕዛብ አማኞች ላይም ወረደ" በመጀመሪያ በእኛ ላይ እንደወረደ "እኛ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጴጥሮስን እና ከመጀመሪያ ጊዜ ጀምሮ በዚያ የነበሩተን አይሁዳዊያን አማኞችን ሲሆን እነዚህ በክፍሉ ውስጥ ያሉት ሁሉ ከመጀመሪያው ጊዜ አንስቶ ነበሩ፡፡ በቋንቋችሁ ሌሎችን የሚለይ ቃል ካለ ተጠቀሙ፡፡ በመጀመሪያ በዚህ ሥፍራ ጴጥሮስ በዚህ ቃል አማካይነት ማመልከት የፈለገው ነገር የጴንጤቆስጤ ቀንን ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ አማራጭ ትርጉም፡ "እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ ያጠምቃችኋል"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጴጥሮስ በ ACT 11:4 ላይ የጀመረውን ስለተመለከተው ራዕይ እና በቆርኖሊዎስ ቤት ውስጥ ስለተከሰተው ነገር ለአይሁዳዊያን ማብራራቱን ጨርሷል፡፡ እግዚአብሔር ሰጥቶዋቸዋል "እነርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ቆርኖሊዎን እና እርሱ የጠራቸውን አሕዛብን ነው፡፡ ጴጥሮስ እነዚህ ሰዎች በእየሩሳሌም ባሉ አይሁዳዊያን አማኞች ፊት ባደረገው ንግግሩ ውስጥ አሕዛብ ብሎ አልጠራቸውም፡፡ ተመሳሳይ ስጦታ ጴጥሮስ የመንፍስ ቅዱስ ስጦታ በማለት ይጠራዋል. እግዚአብሔርን እቃወም ዘንድ እኔ ማን ነኝ? ግልጽ የሆነውን ነገር ለማብራራት ጴጥሮስ ይህንን ጥያቄ ይጠይቃል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እግዚአብሔርን መቃወም አልችልም፡፡" እነዚህ ነገሮች በሰሙ ጊዜ "እነርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጴጥሮስን በመቃወም ላይ የነበሩትን የተገረዙት ወገኖችን ነው፡፡ ለሕይወት የሚሆን ንሰሓን ሰጣቸው "ወደ ሕይወት የሚወስድ ንሰሓን ሰጣቸው"
አጠቃላይ መረጃ: ይህ የታሪኩ አዲስ ክፍል ነው፤ እስጥፋኖስ በድንጋይ ተወግሮ ከሞተ በኋላ አማኞች ላይ ምን እንደደረሰባቸው ይናገራል፡፡ ስለዚህ ይህ የታሪኩን አዲስ ክፍል መግቢያ ሆኖ ያገለግላል፡፡ ከእስጥፋኖስ ሞት በኋላ የጀመረው የአማኞች ሞት ከእየሩሳሌም እንዲበተኑ አደረገ "የአይሁድ መሪዎች እስጥፋኖስን ከገደሉት በኋላ ብዙ አማኞች መከራ ይገጥማቸው ጀመረ፡፡ እነዚህ አማኞች ከእየሩሳሌም ወጥተው ወደ ተለያዩ ሥፍራዎች ሄዱ፡፡" ለአይሁዳዊያን ብቻ እንጂ ለሌሎች አማኞች የእግዚአብሔር መልዕክት ለአይሁዳዊያን እንጂ ለአሕዛብም ጭምር ነው ብለው አያስቡም ነበር፡፡ የእግዚአብሔር እጅ የእግዚአብሔር እጅ የሚለው ሀረግ የሚያሳየው ኃይልን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እግዚአብሔር በኃይል እንዲቻል አደረገ"
አጠቃላይ መረጃ: በእነዚህ ቁጥሮች ውስጥ “እርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ባርናባስን ነው፡፡ ስለእነርሱ የተነገረው ዜና "እነርሱ" በአንጾኪያ ያለው አዳዲስ አማኞች፡፡ የቤተ ክርስቲያን ጆሮዎች "ጆሮዎች" የሚያመለክተው የተለያዩ ነገሮችን መስማትን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በእየሩሳሌም ያት አማኞች ስለእነርሱ ሰሙ፡፡" ላኩ "በእየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉት አማኞች ላኩ" የእግዚአብሔርን ስጦታ አዩ "የእግዚአብሔርን ጸጋ አዩ" ወይም "እግዚአብሔርን አማኞችን አስመልክቶ ቸርነቱን እንዳደረገ" (UDB) አበረታታቸው "ማበረታታቱን ቀጠለ" ከጌታ ጋር መሆኑን ቀጠለ "ለጌታ ታማኝ ሆኖ ቀጠለ፡፡" በልባቸው ሁሉ "ለጌታ የተሰጡ መሆን" ወይም "በጌታ ፈጽሞ መታመን" (UDB) በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ባርናባስ መንፈስ ቅዱስን መታዘዙን በቀጠለ ቁጥር መንፈስ ቅዱስ ባርናባስን ይቆጣጠረው ነበር፡፡ ብዙ ሰዎች ወደ ጌታ ተጨመሩ፡፡ "ተጨመሩ" ማለት አመኑ፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ብዙ ሰዎች በጌታ አመኑ፡፡"
ከጠርሴስ "ከጠርሴስ ከተማ ውጪ" ባገኘው ጊዜ ይዞት መጣ "ባርናባስ ሳኦልን ስያገኘው ይዞት መጣ" ከእነርሱ ጋር በአንድነት ተሰበሰቡ "ባርናባስ እና ሳኦል ከእነርሱ ጋር ተሰበሰቡ" ወይም "ባርናባስ እና ሳኦል ሁል ጊዜ ከእነርሱ ጋር ይሰበሰቡ ነበር" ደቀ መዛሙርቱ ክርስቲየን ተብለው ተጠሩ አማራጭ ትርጉም፡ "የአንጾኪያ ሰዎች ደቀ መዛሙርቱን ክርስቲያኖች ብለው ይጠሯቸው ነበር፡፡"
አሁን በዚህ ሥፍራ ጥቅም ላይ የዋለው ይህ ቃል በታሪኩ መሥመር ላይ ለውጥ መደረጉን ያሳያል፡፡ በዚህ ስፍራ ሉቃስ ስለ በአንጾኪያ ስለሆነውን ትንቢት የኃላ ታሪክ መረጃ ይሰጣል፡፡ ከእየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ወረዱ ከእየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ የከፍታ ለውጥ አለ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በእየሩሳሌም ያለው ቤተ መቅደስ ከፍተኛ ሚና እንዳውም ብዙ ሰዎች ይናገራሉ፡፡ ምንም አቀበታማ ቢሆንም ሰዎች ወደ እየሩሳሌም እና ቤተ መቅደሱ ይሄዳሉ እንዲሁም ከዚያም ይወርዳሉ፡፡ ታላቅ ረሃብም ሆነ "ከፍተኛ የምግብ እጥረት ተከሰተ" በዓለም ሁሉ ላይ ይህ የሮምን አገዛዝ ለማሳየት የዋለ ግነት የሞላበት ንግግር ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በአጠቃላይ ሮም አገዛዝ ውስጥ፡፡"
ስለዚህ ይህ የሆነው ነገር በመጀመሪያ ሌላ ነገር በመሆኑ ምክንያት እንደሆነ የሚያመለክት ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ገንዘብ የላኩ ከአጋቦስ ትንቢት የተነሣ ነው፡፡ ሁሉም ሰው የቻለውን ያኸል ሀብታሞች ብዙ ሲልኩ ድሆች ግን ጥቂት ሊከዋል፡፡ ይህንን አደረጉ፤ ገንዘብ ላኩ "በአንጾኪያ የሚገኙ አማኞች ገንዘብ አወጥተው ላኩ" በባርናባስ እና በሳኦል እጂ አድርገው "እጅ" ማለት በእነርሱ በኩል አድርገው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ባርናባስ እና ሳኦል ገንዘቡን ራሳቸው በኢየሩሳሌም በሚትገኛው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ወደአሉት ሽማግሌዎች ዘንድ ይዘው መጡ፡፡"
1 በዚያን ጊዜ ንጉሡ ሄሮድስ ሊያሠቃያቸው ከቤተ ክርስቲያን አንዳንዶቹን ያዛቸው። 2 የዮሐንስን ወንድም ያዕቆብን በሰይፍ ገደለው። 3 ይህ አይሁድን ደስ እንዳሰኛቸው ካየ በኋላ፣ ጴጥሮስንም ያዘው። ይህ የሆነው በቂጣ በዓል ጊዜ ነበር። 4 ከያዘውም በኋላ ወደ ወኅኒ አገባው፤ እንዲጠብቁትም እያንዳንዳቸው አራት ወታደሮች ያሏቸው ቡድኖችን መደበ፤ ከፋሲካ በኋላ ወደ ሕዝቡ ሊያቀርበው ዐስቦ ነበር። 5 ጴጥሮስም በወኅኒው ይጠበቅ ነበር፤ ነገር ግን ስለ እርሱ ጉባኤው ወደ እግዚአብሔር አጥብቆ ይጸልይ ነበር። 6 ሄሮድስ ሊያወጣው ባሰበበት በዚያ ሌሊት፣ ጴጥሮስ በሁለት ሰንሰለቶች ታስሮ በሩን በሚጠብቁ ሁለት ወታደሮች መካከል ተኝቶ ነበር። 7 እነሆም የጌታ መልአክ በድንገት በአጠገቡ ታየ፣ በክፍሉም ብርሃን በራ። መልአኩ የጴጥሮስን ጎን መትቶ ቀሰቀሰውና፣ “ፈጥነህ ተነሥ” አለው። በዚያን ጊዜ ሰንሰለቶቹ ከእጆቹ ወደቁ። 8 መልአኩ ጴጥሮስን፣ “ልብስህን ልበስ ጫማህንም አድርግ” አለው። ጴጥሮስም እንዲሁ አደረገ። መልአኩ፣ “መደረቢያህን ልበስና ተከተለኝ” አለው። 9 ጴጥሮስም መልአኩን ተከትሎ ወደ ውጭ ወጣ። መልአኩ ያደረገው ነገር በእውን እንደ ሆነ ጴጥሮስ አላወቀም። ራእይ ያየ መሰለው። 10 የመጀመሪያውንና ሁለተኛውን ዘብ እንዳለፉ፣ ወደ ከተማይቱ ወደሚያወጣው የብረት በር ደረሱ፤ እርሱም ዐውቆ ተከፈተላቸው። እነርሱም ወጥተው በአንድ መንገድ በኩል ወረዱ፤ መልአኩም ወዲያውኑ ተለየው። 11 ጴጥሮስም ራሱን ሲያውቅ፣ “ጌታ መልአኩን ልኮ ከሄሮድስ እጅ፣ የአይሁድ ሕዝብም ይጠብቁት ከነበረው ሁሉ እንዳዳነኝ አሁን ዐወቅሁ” አለ። 12 ጴጥሮስ ይህን ከተገነዘበ በኋላ፣ ማርቆስ ተብሎ ወደሚጠራው ወደ ዮሐንስ እናት ቤት መጣ፤ በዚያ ብዙ ምእመናን ተሰብስበው እየጸለዩ ነበር። 13 የደጁን በር ባንኳኳ ጊዜ፣ ሮዴ የሚሏት የቤት ሠራተኛ ልትከፍትለት መጣች። 14 የጴጥሮስን ድምፅ ባወቀች ጊዜ ከደስታዋ የተነሣ በሩን መክፈት አቃታት፤ ይልቁን ሮጣ ወደ ቤት ገባች፤ ጴጥሮስ ከበሩ ውጭ መቆሙን ተናገረች። 15 ምእመናኑም፣ “ዐብደሻል” አሏት። እርሷ ግን እንዲሁ ነው ብላ በዐሳብዋ ጸናች። እነርሱም፣ “የእርሱ መልአክ ነው” አሉ። 16 ጴጥሮስ ግን ማንኳኳቱን ቀጠለ፤ በሩን በከፈቱ ጊዜ፣ ዐይተውት ተደነቁ። 17 ጴጥሮስ ዝም እንዲሉ በእጁ ምልክት ሰጣቸው፤ ጌታ ከወኅኒ እንዴት እንዳወጣውም ነገራቸው። “እነዚህን ነገሮች ለያዕቆብና ለወንድሞች ንገሩ” አላቸው። ከዚያም ቤት ወጥቶ ወደ ሌላ ስፍራ ሄደ። 18 በማግስቱም፣ ጴጥሮስን በሚመለከት ስለ ተከሠተው ነገር በወታደሮች መካከል መደናገጥ ሆነ። 19 ሄሮድስ ጴጥሮስን ፈልጎ ሊያገኘው አልቻለም፤ ጠባቂዎችን መርምሮ እንዲገደሉ አዘዘ። ከዚያም ጴጥሮስ ከይሁዳ ወደ ቂሣርያ ወርዶ በዚያ ተቀመጠ። 20 ሄሮድስም በጢሮስና በሲዶና ሰዎች ላይ እጅግ ተቈጥሮ ነበር። የጢሮስና የሲዶና ሰዎች ተሰብስበው ወደ እርሱ ሄዱ። እንዲረዳቸው የንጉሡን ረዳት ብላስጦስን እሺ አሰኙት። ከዚያም ዕርቀ ሰላም እንዲወርድ ጠየቁ፤ ምክንያቱም አገራቸው ከንጉሡ አገር ምግብ ያገኝ ነበር። 21 በቀጠሮ ቀን ሄሮድስ ልብሰ መንግሥት ለብሶ በዙፋን ላይ ተቀመጠና ንግግር አደረገላቸው። 22 ሕዝቡም፣ “ይህ የአምላክ ድምፅ ነው እንጂ፣ የሰው አይደለም!” ብለው ጮኹ። 23 ሄሮድስ ለእግዚአብሔር ክብር ስላልሰጠ፣ ወዲያውኑ የጌታ መልአክ ቀሠፈው፤ በትል ተበልቶም ሞተ። 24 የእግዚአብሔር ቃል ግን እያደገና እየሰፋ ሄደ። 25 በርናባስና ሳውል ለኢየሩሳሌም የነበራቸውን ተልእኮ ከፈጸሙ በኋላ፣ ተመለሱ፤ ማርቆስ የተባለውንም ዮሐንስን ይዘው ሄዱ።
አጠቃላይ መረጃ: ይህ ስለጴጥሮስ መታሠር የሚያወራ አዲስ የታሪኩ ክፍል ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ ሄሮዶስ ያዕቆብን እንደገደለው መረጃ ይሰጠናል፡፡ አሁን ይህ በታሪኩ ውስጥ አዲስ ከፍል መጀመሩን ያበስራል፡፡ በዚያን ጊዜ ይህ በአንጾኪያ የነበሩት ደቀ መዛሙርት በይሁዳ ለነበሩት ወንድሞች ገንዘብ የላኩበትን ጊዜ ያመለክታል፡፡ እጆቻቸውን ጫኑባቸው ይህ ሄሮዶስ አማኞችን ይጨቁን እንደነበረ የሚያሳይ ነው፡፡ አማራጭር ትርጉም፡ “ለማሠር ወታደሮችን ላከ፡፡" ከተሰብሳቢዎቹ መካከል አንዳንዶቹ ከአውዱ የስብሰባው መሪዎች መሆናቸውን መረዳት ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "የስብሰባው መሪዎች፡፡" አሰቃዮዋቸው "አማኞች እንዲሰቃዩ አደረጉ" ያዕቆብ በስለት እንዲሞት አደረገ ይህ ሀረግ ያዕቆብ የተገደለበትን መንገድ በግልጽ ይናገራ፡፡ ገደለው "ንጉስ ሄሮዶስ ገደለው" ወይም "ንጉሥ ሄሮድ እንዲገደል ትዕዛዝ ሰጠ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ሉቃስ ስለ ጴጥሮስ መታሠር የኃላ ታሪክ መረጃን መስጠቱን ቀጥሏል፡፡ . ይህ አይሁዳዊያንን እንደሚያስደስት ካወቀ በኋላ "ሄሮዶስ የያዕቆብ መሞት የአይሁድ መሪዎችን እንዳስደሰተ ካወቀ በኋላ" አይሁዳዊያንን ማስደሰት "የአይሁድ መሪዎችን ማስደሰቱን" ጴጥሮስም ደግሞ እንዲታሠር አዘዘ "ሄሮዶስ ጴጥሮስም እንዲያዝ አዘዘ" ያም ሆነ "ይህም ሆነ" (UDB) ወይም "ሄሮዶስ ይህን አደረገ" ከያዘውም በኋላ በወህኒ ቤት አኖረው "ወታደሮች ጴጥሮስን ከያዙት በኋላ ሄሮዶስ ወታደሮቹን ጴጥሮስን በወህኒ ቤት እንዲያኖሩት አዘዛቸው" አራት ሰዎች ያሉት የወታደሮች ቡድን "አራት አራት ወታደሮች እየሆኑ፡፡" (UDB) ጴጥሮስን የሚጠብቁት የወታደሮች ቡድን እያንዳንዳቸው አራት አራት ወታደሮች ያሏቸው ሲሆን ሁሉም ቡድኖች በየተራ ይጠብቁ ነበር፡፡ ቡድኖቹም በቀኑ ውስጥ በተለያየ ሰዓት ይጠብቁት ነበር፡፡ ሁለት ወታደሮች በጎኑ ይሆኑ ነበር ሁለቱም ደግሞ መግቢያ በሩ ላይ ሆነው ይጠብቁት ነበር፡፡ እርሱን ለመጠበቅ "ጴጥሮስን ለመጠበቅ" እርሱን ወደ ሕዝቡ ዘንድ ለማቅረብ አብሰበው ነበር "ሄሮዶስ ጴጥሮስን ሕዝቡ ሁሉ በተገኘበት ፍርድ ለመስጠት አቅዶ ነበር" ወይም "ሄሮዶስ ጴጥሮስ ላይ የአይሁድ ሕዝብ ባለበት ለመፍረድ አቅዶ ነበር፡፡"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ሉቃስ ስለ ጴጥሮስ እስር የሰጠውን ዘገባ በዚህ ክፍል ውስጥ ያጠናቅቃል፡፡ . ስለዚህም ጴጥሮስ በወህኒ ቤት ታሠረ ይህ ዓረፍተ ነገር ጴጥሮስ በእስር ቤት ውስጥ ሁል ጊዜ በተዋደሮች እየጠጠበቀ እንደነበር በተዘዋዋር መንገድ ይገልጻል፡፡ በጽናት "ያለማቋረጥ" ወይም "ያለማቋረጥ በመሰጠት" በስብሰባቸው ላይ "በእየሩሳሌም የሚገኙ አማኞች ይጸልዩ ነበር" ወይም "በእየሩሳሌም የሚትገኘው ቤተ ክርስቲያን ትጸልይ ነበር" ስለእርሱ "ለጴጥሮስ" ሄሮዶስ እርሱን ከእስር ቤት ልያወጣው ፈለገ "ሄሮዶስ ጴጥሮስን ከእስር ቤት አውጥቶ ልገድለው ፈለገ" በሁለት ሠንሠለት ታሥሮ ነበር "በሁለት ሠንሠለት ታሥሮ ነበር" ወይም "በሁለት ሠንሠለት ታሥሯል" ይጠብቁት ነበር "ይጠብቁታል"
አጠቃላይ መረጃ: ይህ የታሪኩ ዋናው ክፍል ነው፤ የታኩ ዋና ዋና ተግባራት የሚገኙት በዚህ ክፍል ውስጥ ነው፡፡ እነሆ ይህ ቃል በቀጣይነት የሚሰጠው አስገራሚ መረጃን ላይ ትኩረት እንዲናደረግ ያደርገናል፡፡ በእርሱ "ከጵጥሮስ አጠገብ" ወይም "ከጴጥሮስ ጎን" በእስር ቤት ውስጥ "በታሠረበት ክፍል ነው" ጴጥሮስን መታው "መላአኩ ጴጥሮስን ነክቶ ቀሰቀሰው" ወይም "መልአኩ ጴጥሮስን አነቀው" እርሱን ይዞት ወጣ "ጴጥሮስን ይዞት ወጣ" የእጆቹ ዘንሰለለቶች ከእጆቹ ላይ ወደቁ መልአኩ በጴጥሮስ እጅ ላይ የነበሩት ሠንሰለቶች በእጅ ሳይነኩ እንዲወድቁ አደረገ፡፡ አማራጭ ትርጉሞች: "በጴጥሮስ እጆች ላይ የነበሩት ሠንሠለቶች ወደቁ፡፡" እንዲህም አለው "ለጴጥሮስ እንዲህ አለው" ጴጥሮስም ይህንኑ አደረገ "ጴጥሮስ መልአኩ አድርግ ያለውን ነገር አደረገ" ወይም "ጴጥሮስ ታዘዘ" መልአኩ ለእርሱ እንዲህ አለው "መልአኩ ለጴጥሮስ እንዲህ አለው" ተከተለኝ ይህ ማለት መልአኩ እና ጴጥሮስ በሚሄዱበት ጊዜ ጴጥሮስ ትኩረቱን ሁሉ በመልአኩ ላይ ማድረግ አለበት፡፡
አላወቀም ነበር "ጴጥሮስ አላወቀም ነበር" ወይም "ጴጥሮስ አላወቀም ነበር" በመልአኩ የተደረገው ነገር እውነት ነበር "መልአኩ ያደረገው ነገር እውን ነበር" ወይም "መልአኩ ያደረገው ነገር በእውነት የተካነወነ ነበር" . . . የሚያይ መስሎት ነበር "ጴጥሮስ . . . የሚያይ መስሎት ነበር" እነርሱ . . . በኋላ "ጴጥሮስ እና መልአኩ . . . በኋላ" በ. . . አልፎ ሄደ "አልፎ ሄደ" ሁለተኛው "ሁለተኛው ጠባቂ" ወደ . . . መጡ "መልአኩ እና ጴጥሮስ ወደ . . . ደረሱ" ወደ ከተማይቱ መሄጃ "ወደከተማዬቱ መግቢያ" በራሱ ተከፈተ "መግቢያው በር ተከፈተላቸው" ወይም "መግቢያው በር በራሱ ተከፈተላቸው" ወጡ "መልአኩ እና ጴጥሮስ በበሩ አልፈው ሄዱ" በመንገዱ ወደ ታች ወረዱ "በጎዳናዎቹ ላይ ተጓዙ" ወዲያው ትቶት ሄደ "ወዲያው ጴጥሮስን ትቶት ሄደ" ወይም "በድንገት ጠፋበት"
ጴጥሮስ ራሱን ባወቀ ጊዜ "ጴጥሮስ ከነበረበት ሁኔታ በነቃ ጊዜ" ወይም "ጴጥሮስ የሆነው ነገር ሁሉ እውን የተደረገ መሆኑን ባወቀ ጊዜ" ከሄሮዶስ እጅ አወጣኝ በዚህ ሥፍራ እጅ የሚለው ቃል የሚያመለክተው ዕቅድን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ሄሮዶስ በእኔ ላይ ልያደረግ ካቀደው ክፋት አዳነኝ፡፡" የአይሁድ ሕዝብ ከሚጠብቀው "የአይሁድ ሕዝብ በእኔ ላይ ይሆናል ብለው ከሚጠብቁ ነገር" ይህን አውቆ "ይህንን እውነት በማወቅ" ማርቆስ ተብሎ የሚታወቀው የዮሐንስ እናት "ማርቆስ ተብሎም የሚታወቀው"
አንኳኳ "ጴጥሮስ አንኳኳ፡፡" ወደ ሰዎች ቤት ሲኬድ በር ማንኳኳት በአይሁድ ባሕል ውስጥ የተለመደ ነው፡፡ በመግቢያ በሩ ላይ ቆሞ "በውጭ በር ላይ" ወይም "ከመንገዱ ወደ ቤቱ መግቢያ በር ለይ በውጪ ቆሞ" ምላሽ ለመስጠት መጣ "ወደ በሩ የሚያንኳኳው ማን እንደሆነ ለማየት መጣ" አወቀችው "ሬዴ አወቀችው" ከደስታዋ ብዛት "ደስተኛ ከመሆኗ የተነሣ" ወይም "በጣም ከመደሰቷ የተነሣ" በበሩ እንደቆመ "ከቤት ውጭ በበር ላይ እንደቆመ፡፡" ጴጥሮስ አሁንም በውጪ በር ላይ እንደቆመ ነው፡፡ እንዲህ አሏት "በቤቱ ውስጥ የነበሩት አማኞች ሮዴ ለተባለቸው ሎሌ እንዲህ አሏት" አንች አብደሻል ሰዎች እርሷን አለማመናቸው ብቻ ሳይሆን አብደሻል ብለው ገሰጸዋት፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "አብደሻል፡፡" እርሱ ግን እንደተመለከተች አጥብቃ ተናገረች "ሮዴ የተናገረችው ነገር እውነት መሆኑን አጥብቃ ተናገረች፡፡" እንዲህም አሏት "በቤቱ ውስጥ የነበሩት ሰዎች እንዲህ የሚል መልስጥ ሰጧት፡፡" የእርሱ መልአክ ነው "የተመለከትሽው የእርሱን መልአክ ነው፡፡" አንዳንድ አይሁዶች ጠበቂ መልአከት እንዳሉ ያምናሉ፡፡ ስለዚህም የጴጥሮስ መልአክ ወደ እነርሱ እንደመጡ አሰቡ፡፡
ነገር ግን ጴጥሮስ መዝጊያውን ማንኳኳቱን ቀጥሏል “ቀጥሏል” የሚለው ቃል ጴጥሮስ ይሄንን ሁሉ ጊዜ እነርሱ በቤቱ ውስጥ ሆነው ስነጋገሩ እርሱ መዝጊያ በሩን ያንኳኳ እንደነበር ያሳያል፡፡ መዝጊያ በሩን በከፈቱ ጊዜ እርሱ በዚያ ቆመ አዩና እጅግ በጣም ተገረሙ፡፡ "መዝግቢያ በሩን ከከፈቱ በኋላ በቤቱ ውስጥ የነበሩት ሰዎች ጴጥሮስን አዩት በዚህም በጣም ተገረሙ፡፡" ዘረዘረላቸው . . . ነገራቸው "በቤቱ ውስጥ ለነበሩት ሰዎች ዘረዘረላቸው . . . እንዲሁም ለሰዎቹ ነገራው" እነዚህን ነገሮች ነገራው "እነዚህ ነገሮች ነገራው" ከዚያ ወጥቶ ሄደ "ጴጥሮስ ከዚያ ሄደ"
የሐዋርያት ሥራ 12፡ 18-19 አሁን ይህ ቃል በታሪኩ ፍሰት ላይ መቃረጥ እንዳለ አመላካች ነው፡፡ ጊዜ አልፏል፤ አሁን ቀጣዩ ቀን ነው፡፡ ቀን በሆነ ጊዜ አማራጭ ትርጉም: "በነጋ ጊዜ" ትልቅ መገረም ሆነ ይህ ሀረግ ጥቅም ላይ የዋለው በእርግጥ የሆነውን ነገር አጽኖት ሰጥቶ ለማሳየት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ታላቅ አግራሞት" ወይም "ብዙ አግራሞት፡፡" አግራሞት ይህ እንደ ጭንቀት፣ ከፍተኛ ፍርሃት ወይም ግራ መጋባት ያሉትን አሉታዊ የሆነ መገረምን የሚያሳይ ነው፡፡ በተመለከተ "ስለ . . ." ወይም "በተመለከተ" ሄሮዶስ ቢፈልገውም ሊያገኘው ግን ከቶ አልቻለም "ምንም እንኳ ሄሮዶስ ጴጥሮስን ቢያስፈልገውም ሊያገኘው ግን አለቻለም፡፡ አማራጭ ትርጉምች፡ 1) "ሄሮዶስ ጴጥሮስ እንደ ጠፋ በሰማ ጊዜ ራሱ ሊፈልገው ወጣ" ወይም 2) "ሄሮዶስ ጴጥሮስ እንደ ጠፋ በሰማ ጊዜ ሌሎች ወታደሮች ይፈልጉት ዘንድ ላካቸው፡፡" ጠባቂዎችን ጠየቃቸው እንዲሁም በሞት እንዲቀጡ አዘዘ "ሄሮዶስ ጠባቂዎቹን ጠየቃቸው እንዲሁም ወታደሮቹ ጠባቂዎቹን እንዲገድሏቸው አዘዘ፡፡" ከዚያም ወደታች ወረደ "ከዚያ ሄሮዶስ ከዚያም ወደታች ወረደ፡፡" ከኢየሩሳሌም ከቅጣጫ ሁሉም ዝቅተኛ/ታች ተደርገው ይወሰዳሉ ምንያቱም ኢየሩሳሌም ተራራ ላይ በመሆኗ ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ: ይህ የታርኩ ሌላኛው ክፍል ሲሆን ስለሄሮዶስ ሕይወት ሌላ ታሪክ ነው፡፡ አሁን ይህ ቃል በታሪኩ ውስጥ የተፈጠረን አንድ ቀጣት ክስተት ያሳያል፡፡ ወደ እርሰስ አብረው ሄዱ "የጥሮስ እና የሴዶን ሰዎችን የሚወክሉት ሰዎች ከሄሮዶስ ጋር ለመወያየት ሄዱ" አሳመኑት "እነዚህ ሰዎች አሳመኑት" ብላስጦስ ብላስጦስ የንጉሥ ሄሮዶስ ረዳት ወይም ተወካይ ነበር፡፡ ሰላም እንዲሆን ጠየቁ "እነዚህ ሰዎች ሰላም ይሆንላቸው ዘንድ ጥያቄ አቀረቡ" በታቀደው ቀን "ለመሰብሰብ ባቀዱበት ቀን" እንዲህ በማለት ንግግር አደረገ "ሄሮዶስ ለሰዎቹ ንግግር አደረገ" ወይም "ሄሮዶስ ለሰዎቹ ተናገራቸው" በዙፋኑ ላይ ተቀመጠ ይህ ሄሮዶስ እርሱን ለማግኘት የመጡትን ሰዎችን በቀጥታ የተናገራቸው ነገር ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ፡ ይህ ስለሄሮዶስ የተነገረው ታሪክ የመጨረሻ ክፍል ነው፡፡ ወዲያውም "ሰዎቹ ሄሮዶስን እያመሰገኑ እያለ" ተመታ "ሄሮዶስ ታመመ" ወይም "ሄሮዶስ በጣም ታመመ" ለእግዚአብሔር ክብር አልሰጠም ነበር ሄሮዶስ ሰዎቹ እግዚአብሔርን እንዲያመልኩ ከማሳየት ፈንታ እርሱን እንዲያመልከት ፈቀደላቸው፡፡ በትል ተበልቶ ሞተ፡፡ "ትሎች ሄሮዶስ በሉት እርሱም ሞተ"
አጠቃላይ መረጃ: ይህ የእግዚአብሔር ቃል እንዴት እንደተስፋፋ እና ስለ ባርናባስ እና ሳኦል መረጃ የሚሰጠን ክፍል ነው፡፡ (ተመልከት: [[End of Story]]) የእግዚአብሔር ቃል እያደገ እና እየበዛ በዚህ ሥፍራ "ቃል' የሚለው ቃል የሚያመለክተው በኢየሱስ በኩል ስለሚገኝ ድነት የሚነገረውን የእግዚአብሔርን መልዕክት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "የእዚአብሔር መልዕክት በየቦታው ተስፋፋ የአማኞችም ቁጥር በጣም በዛ፡፡" ወደ ኢየሩሳሌም ሄደው እንዲፈጽሙ የሰተጣቸውን ተምልዕኮ አጠናቀቁ አማራጭ ትርጉም: "ገንዘቡን በኢየሩሳሌም ለነበረችው ቤተ ክርስቲያን አስረከቡ" ተመለሱ አማራጭ ትርጉም: "ባርናባስ እና ሳኦል ወደ አንጾኪያ ተመለሱ" ዮሐንስን ከእነርሱ ጋር ወሰዱት "ባርናባስ እና ሳኦል ዮሐንስን ከእነርሱ ጋር ወሰዱት" ሌላኛው ስሙ ማርቆስ ነው "ማርቆስ ተብሎ የሚጠራውን"
1 በአንጾኪያም ባለችው ጉባኤ አንዳንድ ነቢያትና መምህራን ነበሩ። እነርሱም በርናባስ፣ ኔጌር የተባለው ስምዖን፣ የቀሬናው ወንድሙ ምናሔ፣ ሳውልም ነበሩ። 2 ጌታን እያመለኩና እየጾሙ እያሉ፣ መንፈስ ቅዱስ፣ “ለጠራኋቸው ሥራ በርናባስንና ሳውልን ለዩልኝ” አለ። 3 ጉባኤው ከጾመ፣ ከጸለየና እጅ ከጫነም በኋላ አሰናበታቸው። 4 በርናባስና ሳውልም ለመንፈስ ቅዱስ ታዘዙና ወደ ሴሌውቅያ ወረዱ፤ ከዚያም በመርከብ ወደ ቆጵሮስ ደሴት ሄዱ። 5 በስልማና ከተማ በነበሩ ጊዜም፣ በአይሁድ ምኵራቦች የእግዚአብሔርን ቃል ሰበኩ። ማርቆስ የተባለው ዮሐንስ ሊረዳቸው አብሯቸው ነበር። 6 በደሴቲቱም ሁሉ እስከ ጳፉ በሄዱ ጊዜ፣ ስሙ በርያሱስ የተባለ፣ አንድ አይሁዳዊ የሐሰት ነቢይና አስማተኛ አገኙ። 7 ይህ አስማተኛ አስተዋይ ሰው ከነበረው ሰርግዮስ ጳውሎስ ከተባለው አገረ ገዥ ጋር ተባበረ። ይህ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል መስማት ስለ ፈለገ፣ በርናባስናን ሳውልን ጠራ። 8 ነገር ግን፣ “አስማተኛው” ኤልማስ ስሙ ሲተረጎም እንዲሁ ነውና ተቃወማቸው፤ አገረ ገዡን ከእምነቱ ለመመለስ ሞከረ። 9 ደግሞ ጳውሎስ የተባለው ሳውል ግን በመንፈስ ቅዱስ ተሞላ፤ ትኵር ብሎም ተመለከተውና 10 እንዲህ አለው፤ “አንተ የዲያብሎስ ልጅ፣ ክፋትና ተንኮል ሁሉ የሞላብህ ነህ። የጽድቅ ሁሉ ጠላት ነህ። የቀናችውን የጌታን መንገድ ማጣመምህን አታቆምምን? 11 አሁንም ተመልከት፤ የጌታ እጅ በአንተ ላይ ነችና ትታወራለህ። ለጥቂት ጊዜ ፀሐይን አታይም።” ወዲያውኑ በኤልማስ ጨለማና ጭጋግ ወደቀበት፤ እጁንም ይዘው እንዲመሩት ሰዎችን እየጠየቀ ይዘዋወር ጀመር። 12 አገረ ገዡ የሆነውን ካየ በኋላ፣ ስለ ኢየሱስ በቀረበው ትምህርት ስለ ተደነቀ፣ አመነ። 13 ጳውሎስና ጓደኞቹም በመርከብ ከጳፉ ተነሥተው በጵንፍልያ ወዳለችው ወደ ጴርጌን መጡ። ዮሐንስ ግን ትቶአቸው ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ። 14 ጳውሎስና ጓደኞቹ ከጴርጌን ተጕዘው የጲስድያ ወደ ሆነችው አንጾኪያ መጡ። በዚያ በሰንበት ቀን ወደ ምኵራብ ገብተው ተቀመጡ። 15 ሕግና ነቢያት ከተነበቡ በኋላ፣ የምኵራብ አለቆች፣ “ወንድሞች ሆይ፣ እዚህ ላሉት ሕዝብ የሚሆን የሚያበረታታ መልእክት ካላችሁ፣ ተናገሩ” በማለት መልእክት ላኩላቸው። 16 ጳውሎስም ቆመና በእጁ ምልክት ሰጥቶ እንዲህ አለ፤ “የእስራኤል ሰዎችና እናንተ እግዚአብሔርን የምታከብሩ፣ ስሙ። 17 የዚህ የእስራኤል ሕዝብ አምላክ አባቶቻችንን መርጦ በግብፅ ይኖሩ በነበሩበት ጊዜ፣ ሕዝቡን አበዛላቸው፤ በተዘረጋችም ክንድ መርቶ ከዚያ አወጣቸው። 18 ለአርባ ዓመታት ገደማ በምድረ በዳ ታገሣቸው። 19 በከነዓን ምድርም ሰባት ሕዝቦችን ካጠፋ በኋላ፣ ምድራቸውን ለሕዝባችን ርስት አድርጎ ሰጠ። 20 እነዚህ ሁነቶች ሁሉ በአራት መቶ ሃምሳ ዓመታት ውስጥ ተፈጸሙ። ከእነዚህ ነገሮች ሁሉ በኋላ፣ እግዚአብሔር እስከ ነቢዩ ሳሙኤል ድረስ መሳፍንትን ሰጣቸው። 21 ከዚህ በኋላ፣ ሕዝቡ ንጉሥ ይንገሥልን ብለው ጠየቁ፤ ስለሆነም፣ እግዚአብሔር ከብንያም ነገድ የሆነውን የቂስን ልጅ ሳኦልን ለአርባ ዓመታት ሰጣቸው። 22 ከዚያም እግዚአብሔር እርሱን ከንጉሥነት ከሻረው በኋላ፣ ንጉሣቸው እንዲሆን ዳዊትን አስነሣ። እግዚአብሔር፣ ‘እንደ ልቤ የሆነውን የእሴይን ልጅ ዳዊትን አገኘሁ፤ እርሱ እኔ የምፈልገውን ሁሉ ያደርጋል’ በማለት ስለ ዳዊት ተናግሮ ነበር። 23 ከዚህም ሰው ዘር እግዚአብሔር ተስፋ እንደ ሰጠ አዳኝ ኢየሱስን ለእስራኤል አመጣ። 24 ይህ መሆን የጀመረው ኢየሱስ ከመምጣቱ በፊት፣ ዮሐንስ መጀመሪያ ለእስራኤል ሕዝብ ሁሉ የንስሐን ጥምቀት ባወጀ ጊዜ ነው። 25 ዮሐንስ ሥራውን እንደ ጨረሰ እንዲህ አለ፤ ‘ማን እንደ ሆንሁ ታስባላችሁ? እኔ እርሱ አይደለሁም። ነገር ግን ስሙ፤ የጫማውን ማሰሪያ መፍታት ከማይገባኝ ከእኔ በኋላ እርሱ ይመጣል።’ 26 ወንድሞች፣ የአብርሃም ዘር ልጆች፣ እግዚአብሔርንም የምታመልኩ ሆይ፣ የዚህ ድነት መልእክት የተላከው ለእኛ ነው። 27 በኢየሩሳሌም የሚኖሩ፣ አለቆቻቸውም በእርግጥ ኢየሱስን አላወቁትም፤ በየሰንበቱ የሚነበበውን የነቢያትን ድምፅም በእውነት አልተረዱም፤ ስለ ሆነም በኢየሱስ ላይ ሞት በመፍረድ የነቢያትን ቃል ፈጸሙ። 28 ምንም እንኳ በእርሱ ላይ ለሞት የሚያበቃ ምክንያት ባያገኙም፣ እንዲገድለው ጲላጦስን ለመኑት። 29 ስለ እርሱ የተጻፈውን ሁሉ በፈጸሙ ጊዜም፣ ከዕንጨት ላይ አውርደው በመቃብር አኖሩት። 30 እግዚአብሔር ግን ከሙታን አስነሣው። 31 ከእርሱ ጋር ከገሊላ ወደ ኢየሩሳሌም የወጡት ብዙዎች ለአያሌ ቀናት ዐዩት። እነዚህ ሰዎች አሁን ለሕዝቡ የሚናገሩ የእርሱ ምስክሮች ናቸው። 32 ስለ ሆነም እኛ ለአባቶቻችን ስለ ተሰጠው ተስፋ የሚናገር የምሥራች እናመጣላችኋለን፤ 33 ኢየሱስን ከሙታን በማስነሣት እግዚአብሔር እነዚህን ተስፋዎች ለእኛ ለልጆቻቸው ጠብቆአል። ይህም ደግሞ በሁለተኛው መዝሙር፦ ‘አንተ ልጄ ነህ፣ እኔ ዛሬ ወለድሁህ’ ተብሎ የተጻፈ ነው።’ 34 ደግሞም ሥጋው እንዳይበሰብስ ከሙታን እንዳስነሣው፦ ‘የተቀደሰውንና እውነተኛውን የዳዊት በረከት እሰጥሃለሁ’ ብሎ ተናግሯል። 35 በሌላ መዝሙርም፣ ‘ቅዱስህ መበስበስን እንዲያይ አትፈቅድም’ የሚለው ስለዚህ ነው። 36 ዳዊትም በዘመኑ የእግዚአብሔርን ዐሳብ አገልግሎ አንቀላፋ፤ ከአባቶቹ ጋር ተቀበረ፤ መበስበስንም ዐየ። 37 እግዚአብሔር ያስነሣው ኢየሱስ ግን መበስበስን አላየም። 38 ስለ ሆነም ወንድሞች ሆይ፣ በዚህ ሰው በኩል የኃጢአት ይቅርታ እንደ ተሰበከላችሁ ይህ ለእናንተ የታወቀ ይሁን። 39 በሙሴም ሕግ እንድትጸድቁበት ከማይቻላችሁ ሁሉ፣ በእርሱ የሚያምን ሁሉ ጸድቆአል። 40 እንግዲያው ነቢያት እንዲህ ሲሉ የተናገሩለት ነገር እንዳይደርስባችሁ ተጠንቀቁ፦ 41 ‘እናንተ የምትንቁ፣ ተመልከቱ፤ ተደነቁ፣ ጥፉም፤ አንድ ስንኳ ቢነግራችሁ ከቶ የማታምኑትን ሥራ፣ በዘመናችሁ እሠራለሁና።’” 42 ጳውሎስና በርናባስ እንደ ወጡ፣ በሚቀጥለው ሰንበት ይህንኑ ቃል ደግመው እንዲናገሩ ሕዝቡ ለመኑአቸው። 43 የምኵራቡ ስብሰባ እንዳበቃም፣ ከአይሁድና ወደ ይሁዲነት ከገቡ ከሚያመልኩ ብዙዎቹ፣ በእግዚአብሔር ጸጋ እንዲጸኑ የመከሩአቸውን ጳውሎስና በርናባስን ተከተሉአቸው። 44 በሚቀጥለውም ሰንበት፣ ጥቂቶች ሲቀሩ፣ መላው ከተማ የጌታን ቃል ለመስማት አንድ ላይ ተሰበሰበ። 45 አይሁድ ሕዝቡን ባዩ ጊዜ፣ ቅንዓት ሞላባቸውና ጳውሎስ የተናገረውን ተቃወሙ፣ ሰደቡትም። 46 ጳውሎስና በርናባስ በድፍረት ተናገሩ፤ እንዲህም አሉ፤ “የእግዚአብሔር ቃል መጀመሪያ ለእናንተ መነገሩ አስፈላጊ ነበር። ቃሉን ከራሳችሁ ስትገፉትና ለዘላለም ሕይወት የተገባችሁ እንዳልሆናችሁ ራሳችሁን ስትቈጥሩ ዐይተናችሁ፣ ወደ አሕዛብ ዘወር የምንል መሆናችንን ተመልከቱ። 47 ጌታ፣ ‘እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ለድነት ትሆን ዘንድ፣ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌሃለሁ’” በማለት አዞናልና። 48 አሕዛብ ይህን እንደ ሰሙ ደስ አላቸው። የጌታንም ቃል አከበሩ። ለዘላለም ሕይወት የተመረጡትም አመኑ። 49 የጌታም ቃል በአገሩ ሁሉ ተስፋፋ። 50 አይሁድ ግን የሚያመልኩትን ታዋቂ ሴቶችን፣ የከተማይቱን ታላላቅ ወንዶችንም ቀሰቀሱ። በጳውሎስና በበርናባስ ላይም ስደት አስነሥተው ከከተማቸው ዳርቻ ወዲያ አውጥተው ጣሏቸው። 51 ጳውሎስና በርናባስ ግን የእግራቸውን ትቢያ አራገፉባቸው። ከዚያም ወደ ኢቆንዮን ከተማ ሄዱ። 52 ደቀ መዛሙርቱም ደስታና መንፈስ ቅዱስ ተሞልተው ነበር።
አጠቃላይ መረጃ በቁጥር አንድ ላይ የታሪክ መዘውሩ ወደ አንጾክያ ቤተክርስቲያን በመዞር ህዝቡ በአንጾክያ መሰብሰቡን እንመለከታለን፡፡ በአንፆኪያ በስብሰባ ላይ በዚያን ግዚ በዙ ህዝብ በአንፆክያ ተሰብስቦ ነበር ሲሞን ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ ( ) ይህ በእንዲህ እያለ ይህ ሃረግ በጥቅም ላይ የሚውለው አንድ ክስተት በተከሰተበት ወቅት በዚያው ተመሳሳይ ሰዓት ላይ ሌላ ክስተት ሲከሰት ነው፡፡ የሄሮድ የቅርብ ወዳጅ ምንኤን የሄሮድ አብሯ አደግ ወይም የቅርብ የሚባለ ሰው ነው፡፡ ስብሰባ በህብረት መቀመጥ አሊያም የአማኒያን ስብስብ እጃቸውንም በሰዎቹ ላይ ጫኑባቸው ለእግዚያብሄር ስራ መለየታቸውን ለማሳየት እጃቸውን ጫኑባቸው፡፡ እጅ የመጫን ስርዓት በአባቶች ልማድ መሰርት አንድን ለእግዚያብሄር ስራ የተለየን ሰው በመንፈስ ቅዱስ እንደተለዩ የሚረጋገጥባቸው ስርዓት አሊያም ወግ ነው፡፡ አሰናበቷቸው ሰዎቹን ወደ ስራቸው እንዲሄዱ አሰናበቷቸው ወይም በመንፈስ ቅዱስ የተለዩለትን ስራ እንዲሰሩ ሸኟቸው፡፡ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
ስለዚህ ይህ ቃል የሚያመለክተው አንድ ክስተት ከሱ በፊት በነበር ሌላ ክስተት ምክንያት መከሰቱ ነው፡፡ በዚህ ዓውድ መሰረትም የበርናባስና ጳውሎስ በመንፈስ ቅዱስ መለየታቸው ነው፡፡ ወረደ ይህ ደግሞ ስራውን ወደሌላ አቅጣጫ የሚቀይረው መዘውር ነው፡፡ ሴሊውቅያ ሴሊውቂያ በባህር አጠገብ ያለች ከተማ ናት እነሱ በየትኛውም አገባብ እነሱ የሚያመለክተው በርናባስና ጳውሎስን ነው፡፡ የሰላማነ ከተማ የሰላማነ ከተማ የምትገኘው በቆጵሮስ ነው፡፡ የአይሁድ ሙክራቦች ታሳቢ ወይም አማራጭ ፍቺዎች ሁለት ናቸው፡፡ 1ኛበርናባስና ሳኦል የሰበኩባቸው በሰላማነ የሚገኙ ሙክራቦች 2ኛ በርናባስና ሳኦል በሰላማና ከተማ ስብከት የጀመሩባቸውና በቆጵሮስ በተዘዋወሩበት ግዜ የተጠቀሙባቸው የአይሁድ ሙክራቦች፡፡ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
እነረሱም ሄዱ እነሱም የሚለው ተውላጠስ ስም የሚያመለክተው በርናባስ፣ጳውሎስ እና ዮሃንስ ማርቆስ ነው፡፡ መላው ደሴት ከአንድ ደሴት ወደ ሌላ ደሴት በመዘዋወር በሁሉም ቦታዎች የክርስቶስን ወነጌል ሰብከዋል፡፡ ጳፋ በቆጵሮስ ደሴት ከሚገኙ ከተሞች ዋናዋና ትልቋናት፡፡ አገኙ ተገኝቷል የሚለው ሃረግ እዚህ የያዘው ትርጓሜ አንድ ነገር በብዙ ጥረት ሳይፈልጉት ይዞ ማምጣት ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ እነርሱም መጡ አንድ ጠንቋይ ሰው የሆነ ጥንቆላን የሚያከናውን ውይም ከሰው አቅም በላይ የሆኑ ምትዓቶችን የሚተገብር ሰው፡፡ ይህ ምትዓተኛ ሰው ፈጣን የሆነ የማሰብ ችሎታ ነበረው ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ ( የተያያዙ ብዙውን ግዜ ከእርሱ ጋር አገረ ገዥ ለሮማዊያን አስተዳደር ተጠር የሆነ ክፍለ ሃገር አስተዳዳሪ ነው፡፡ ይህ ሰው ሰርግዮስ ጳውሎስ ኤልማስ ምትዓተኛው ሰው ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ ( ) የሰሙ ትርጓሜ ነው ይህ በፅርዕ ወይም በግሪክ የስሙ ትርጓሜ ና፡፡ እነሱን በመቃወም ለማዞር ሞከረ እነሱ ዘወር እንዲሉ ለማድረግ በፅኑ ተቃወማቸው ወይም ዘወር እንዲሉ ለማድረግ የእነሱ ተቃዋሚ ሆነ ቆመ ፈልጎ ነበር ሰርግዮ ጳውሎስ ሽቶ ነበር ሞከረ ኤልምያስ ሞከረ አገረ ገዢው ከእምነተ ዘውር እነዲል ለማድረግ ሞከረ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
ጳውሎስ ተብሎ የተጠራው ሳውል አማራጭ ትርጓሜ እራሱን ጳውሎስ ብሎ የጠራው ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ ( ትኩር ብሎ ተመለከተውና ጳውሎስ ምትአተኛውን በጥልቀት ተመለከተው አንተ የዲያቢሎስ ልጅ ጳውሎስ እያለ ያለው ሰውየው ሰይጣን ነው 1የዲያብሎስ ልጅ ወይም2 ልክ እንደ ዲያብሎስ 3 እነደ ዲያብሎስ የሚያደርግ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ ( አንተ ተንኮልና ክፋት የተሞላህ አንተ ሁልግዜ የሰው ልጆች በእውሸት እንዲያምኑ ውሸት የሆነውን የምታደርግ ክፋት በዚህ አውድ መሰረት የቃሉ ትርጓሜ ሰነፍ ሰው የእግዚያብሄርን ህግ መከተል እና በአገባቡ መኖር የማይፈልግ ማለት ነው፡፡ የጽድቅ ሁሉ ጠላት ጳውሎስ ኤማስን ከዲያቢሉስ ጎራ እየመደበው ሲሆን ልክ ዲያቢሎስ የእግዚያብሄርና የጽድቁ ተቃራኒ እንደሆነው ኤማስም እንዲሁ ነው እያለ ነው፡፡ የጌታን ቀና መንገድ ከማጣመም አታርፍምን? ጳውሎስ ኤማስን የዲያቢሎስን መንገድ መከተሉን እንዲያቆም እየገሰፀውና እየወቀሰው ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ፡ የእግዚያብሄርን እውነት ውሸት ነው ብለህ ማለትህን ማቆም አለብህ እያለው ነው፡፡ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ ( የእግዚያብሄር ቀና መንገድ ጳውሎስ ኤመሳን ስለ እግዚያብሄር ጽድቅና እውነት የሚናገረውን ውሸት እና ክህደት እየተቃወመው ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ፡ የእግዚያብሄር ቀና መንገድ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ (
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ጳውሎስ ኤማስን መናገሩን ጨርሷል፡፡ የእግዚያብሄር እጅ በአንተ ላይ ናት እጅ የሚለው ቃል እዚህ ጋር ያለው ትርጓሜ የእግዚያብሄር ኃይል በሚለው እና በአንተ ላይ የሚለው ደግሞ ቅጣትን ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ የእግዚያብሄር ቁጣ በአንተ ላይ ነው፡፡ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ ( አይነ ስውር ትሆናለህ እግዚያብሄር እውር ያደርግሃል፡፡ የጸሃይ ብርሃን አታይም ኤማስ ሙሉ በሙሉ እውር ይሆናል፡፡ በትንሽ ግዜ በትንሽ ግዜ ውስጥ የእግዚያብሄር እስኪመጣ ድረስ፡፡ ጭጋግ እና ጨለማ በኤልማስ ላይ ወደቀ ወይም ኤልማስ ሙሉ በሙሉ አለማት ሆነበት ወዲህ ወዲያ ማለት ጀመር ኤማስ የሚረዳውን ሰው ፍለጋ ዙሪያውን ያማትር ጀመር አገረ ገዥ ይህ ለሮማዊያን አስተዳደር ተጠሪ የሆነ ገዥ ነው፡፡ አመነ አገረ ገዥው አመነ ወይም አገረ ገዥው በኢየሱስ አመነ እርሱም በመገረም አገረ ገዥው በመገረም ወይም አገረ ገዥው በታላ መገርም ውስጥ ተሞልቶ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
አጠቃላይ መረጃ ቁጥር 13 እና 14 በጵሲዲያ አንጾኪያ የተጀመረውን አዲስ ታሪክ መነሻውን ይነግረናል፡፡ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ ( ) አሁን ይህ የአዲሱ ታሪክ ጅማሮ ማብሰሪያ ነው ጳውሎስና ጓደኞቹ ከጳፋ ተነሰተው ለመሄድ በጀለናቸው ተነሱ ጳውሎስና አብረውት ነበሩት በጀለባ ከጳፋ ተነስተው ሄዱ ዮሃንስ ማርቆስ ግን ተዋቸው ነገር ግን ዮሃንስ ማር ጳውሎስን በርናባስን ትቷቸው ሄደ በጵንፍሊያ ወደምትገኝ ጰርጊያ መጡ በጵንፍልያ በምትገኝ ጰርጊያ ከተማ ደረሱ፡፡ የነብያትንና ህግ መጽኃፍትን ካነበቡ በኋላ እኒህ መጸሃፍት የሚያመለክቱት በአይሁዳዊያን መጸሃፍ ቅዱስ ውስጥ በተለምዶ ንባብ የሚደረግባቸው ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ ( ) መልዕክት ላኩባቸው አንዳንድ ሰዎች ጳውሎስና ጓደኞቹ እንዲያናገርቻው ነገሩት ወንደሞች ይህ ቃል ክርስቲያን ሴት እና ወንዶችን የሚወክል ቃል ነው፡፡ የሚያጽናና ቃል ካለችሁ ከመካከላቸሁ ማንም ሊያጽናና እና ሊያበረታታ ሚችል ቃል ካለው፡፡ ተናገሩት እባካችሁ ተናገሩ
አጠቃላይ መረጃ: ጳውሎስ በአንጾኪያ ጲስድያ ውስጥ በሚገኘው ምኩራብ ውስጥ ለነበሩት ሰዎች መናገር ጀመረ፡፡ ንግግሩን የጀመረው በእስራኤል ታሪክ ውስጥ የተፈጸሙ ነገሮችን በማንሳት ነው፡፡ በእጆቹ እያሳየ ይህ ለመናገር ዝግጁ መሆኑን ለማሳየት እጆቹን ማንቀሳቀሱ ልሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ለመናገር እየተዘጋጀ መሆኑን ለማሳየት እጆችን ወደላይ ዘረጋቸው፡፡” እናንተ እግዚአብሔርን የሚትፈሩ ሰዎች ሆይ ይህ ወደ ክርስትና የተለወጡ አሕዛብን የሚያመለክት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “እናንተ ከእስራኤል ወገን ያልሆናችሁ ነገር ግን እግዚአብሔርን የሚታመልኩ ሰዎች ሆይ፡፡” አድምጡ "እኔን አድምጡ" ወይም "አሁን ልናገር ያለሁትን ነገር አድምጡ" የእነዚህ የእስራኤል ሕዝቦች አምላክ "የእስራኤል ሕዝብ የሚያመልከው እግዚአብሔር" አባቶቻችንን መረጠ በዚህ ሥፍራ ጥቅም ላይ የዋለው “እኛ” የሚለው ቃል ሁሉን የማያካትት ሆኖ ጳውሎስን እና የእርሱ ወገን የሆኑትን አይሁዳዊያንን የሚያካትት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ከብዙ ዘመናት በፊት የአይሁድ ሕዝብን መረጠ፡፡” እነርሱ በዚያ በቆዩ ጊዜ "እስራኤላዊያን በዚያ በቆዩ ጊዜ" ከዚያ እየመራ አወጣቸው "እግዚአብሔር እስራኤላዊያን ከግብጽ ምድር እየመራ አወጣቸው" ታገሳቸው "እግዚአብሔር እነርሱ ታገሰ" ወይም "እግዚአብሔር አለመታዘዛቸው ታገሰ"
አጠቃላይ መረጃ ጳውሎስም በጵሲዲያ አንጾክያ ሙክራብ ለሚገኙ ታዳሚዎቹ በእስራኤል የሆነውን ታሪክ ይነግራቸው ጀመረ፡፡ ካደረገም በኋላ እግዚያብሄርም ካደረገ በኋላ ሕዝቡም አንዳንድ ግዜ ይህቃ በአንድ ባልተወሰነ ቦታ ሚኖርን ማንኛውንም ህዝብ ለማመልከት ይገባል፡፡ ሕዝባችንን ሰጠን እግዚያብሄር እስራኤልን ሰጠን መሬታችሁ የእስራኤላዊያን ገዛ ቤታችሁ አራት መቶ አምሳ ዓመት ግዜ ውስጥየተከናወነ ለአራት መቶ አምሳ ዓመት የተከናወነ እስከ ነብዩ ሳሙኤል እስከ ዘመነ ነበዩ ሳሙኤል ድረስ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
ለአርባ ዓመታት ያህል ለአርባ ዓመታት ያህል የእነሱ ንጉስ እንዲሆን ዳዊትን አነገሰው እግዚያብሄር ዳዊትን መረጠው የእነሱ ንጉስ የእስራሄል ንጉስ፣ በእስራኤል ላይ ሚነገስ እግዚያብሄር ስለ ዳዊት የተናገረው እግዚያብሄር ይህን ስለዳዊት ተናገረ የእሰይን ልጅ ዳዊትን አገኘሁት የእሰይን ልጅ ዳዊትን ተመለከትኩት እንደ ልቤ የሆነ ይህ ማለት የምፈልገውን ነገር የሚፈልግ ማለት ነው፡፡ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
ከዚህ ሰው ዘር ከዳዊት ዘር በገባው ቃልኪዳን መሰረት እግዚያብሄር እንዳለው ያደርገዋል፡፡ የንስዓ ጥምቀት ንስዓ መግባትን የሚያሳይ ጥምቀት እኔ ማን መሰለኋቸሁ ዩሃንስ ህዝቡን ይህንን ጥያቄ የጠየቀው ህዝቡ ስለ እሱ ምን እንደሚያስብ ለማወቅ ነው፡፡አማራጭ ትርጓሜ፡ እኔ ማን እንደሆኩ አስቡ የእግሩን ጫማ እንኳ መፍታት የማይገባኝ የጫማውን ክር አእንኳ መፍታት የማይገባኝ ነኝ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
የሐዋርያት ሥራ .13፡26-27 እናንተ ከአብርሃም ዘር የሆናችሁ ውንደሞቼ… እግዚያብሄርን ምታመልኩ ጳውሎስ ለተደራሲያኑ ለእነሱ የሚጠቅማቸውን ነገር ሊነግራቸው መሆኑን ያመለክታል፡፡ ይህ ለእኛ ነው እኛ የሚለው ቃል ሁሉን አቀፍ ሲሆን ጳውሎስና በሙክራብ የተገኙ አድማጮቹን ይመለከታል፡፡ ይህ ስለ ደህንነታችን ነው፡፡ ይህ መልዕክት የተላከው ስለደህንነታችን ከእግዚያብሄር ነው፡፡ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ ( ) ኢየሱስን አላወቁትም ኢየሱስ መሆኑን አላወቁም የነብያቱ ቃል ቃል የሚለው የሚወክለው የነቢያቱን መልዕክት ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ የነበያቱትን ፅሁፍ አሊያም መጸሃፍ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ የሚነበበው የሚያነበው ሰው ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ ( ስለዚህ የነብያቱ ቃል እንዲፈፀም `ስለዚህ በኢየሩሳሌም ያሉ መሪዎች ያደረጉት በነበያቱ አፍ አስቀድሞ ተነገረውን ነው፡:
ለሞት የሚያበቃው አንድም ምክንያት አላገኙበትም የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን ለመግደል የሚያበቃ አንድም በቂ ምክንያት ላቸውም፡፡ እነሱ ይህ ተውላጠስ ስም በሚከሰተበት ቦታ ሁሉ የሚያመለክተው የአይሁድ መሪዎችን ነው፡፡ የእሱ በሁሉም ቦታዎች ላይ የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው፡፡ እነሱም ጲላጦስን ጠየቁት ጠየቁት የሚለው ቃል እዚህ ጋር ጠንከር ያለ ትርጓሜ ያለው ሲሆን እሱም መፈለግ፣መለመንና መማጠን ነው ስለ እሱ የተፃፈውን ሁሉ ከፈፀሙ በኋላ ልክ የአይሁድ መሪዎች ስለ ኢየሱስ በነብያት መፀሃፍ እንደ ሚሞት የተጻፈውን ከፈፀሙ በኋላ፡፡ ከተሰቀለበት እንጨት ላይ አውርደው፡፡ የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን ከተሰቀለበት አውርደው እንደሞተ አረጋገጡ
እግዚያብሄር ግን ከሞታን አስነሳው ነገር ግን ኢየሱስን እግዚያሔር ከሙታን አስነሳው እሱም ታያቸው ኢየሱስ ታይቷቸው ነበር እነሱም አሁን ለህዝቡ ምስክሮች ናቸው፡፡ ሰዎቹ አሁን ስለ ኢየሱስ ከሙታን መነሳት ምስክሮች ናቸው
ስለዚህ ይህ ቃል የሚያመለክተው አንድ ክስተት ከሱ ቀደሞ በነበረ ሌላ ክስተት ምክንያት መከሰቱን ያመለክታል በዚህ መሰረት እግዚያብሔር ኢየሱስን ከሞት ማስነሳቱ ቀዳሚው ክስተት ነው፡፡ እግዚያብሔር ለአባቶቻችን የገባውን ቃልኪዳን ለአባቶቻችን የገባውን ቃልኪዳን እግዚያብሔር ቃልኪዳኑን ጠበቀ እግዚያብሔር ቃል ኪዳኑን ፈፀመ ለእኛ፤ለእነሱ ልጆች ለእኛ ለቀደሞት አበቶቻችን ልጆች ኢየሱስን ከሙታን በማስነሳት ከሙታን መካከል ኢየሱስን በማስነሳት ይኽውም… እንዲህ ተብሎ ተፅፎ ነበር ልጅ… አባት እነኚህ ቃላት በጣም ወሳኝ ሲሆኑ በእግዚያብሔር አብና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት ያሳያል፡፡ እርሱ እንዳልበሰበሰና እግዚያብሔርም ከሙታን እንዳስነሳው እንዲህ ይላል፡፡ እግዚያብሔር ኢየሱስን ከሙታን እንዳስነሳው በሚናገርበት ቃል ኢየሱስ መበስበስን እንዳላየ ያረጋግጥልናል ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
የተቀደሰውና የታመነው የተቀደሰና በእርግጥ የታመነ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
ዳዊትም እንዲህ ይላል አንተ እዚህ ጋር ዳዊት ለእግዚያብሔር ይናገራል፡፡ መበስበስን እንዳያይ ስጋው ተቀብሮ እንዳይቀር በራሱ ዘመን በኖረበት ዘመን የእግዚያብሔርን ሃሳብ አገለገለ እግዚያብሔርን አገለገለ ወይም እግዚያብሔርን መስደሰት ፈልጎ አድርጓል፡፡ አንቀላፍቷል፡፡ ሞቷል ከአባቶቹ ጋር ተቀብሯል ከእሱ ቀደም አባቶቹ ጋር ወደ መቃብር ወርዷል፡፡ እርሱ ግን ኢየሱስ ግን መበስበስን አላየም የእሱ ስጋ ተቀብሮ አልቀረም ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
ይህ በእናነተ ዘንድ የታወቀ ይሁን ይህን እወቁ ወይም ህን ማወቅ ለእናነተ ልታውቁት የሚገባ ጠቃሚ ነገር ነው፡፡ ይህ የኃጢያት ይቅርታ የሚገኘው በኢየሱስ ነው እኛ የሰበክንላቹ የኃጢያታቸሁን ስርየት ያገኛችሁት በኢየሱስ ነው፡፡ በእርሱ በኢየሱስ በኩል ነገሮች ኃጢያት ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
የሐዋርያት ሥራ 13፡40-41 የማገናኛ ዓረፍተ ነገሮች ጳውሎስ በጵሲዲያን አንፆኪያ ሙክራብ የጀመረውን ንግግር እየጨረሰ ነው፡፡ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ ACT 13:16.
ስለዚህ ነብያት እንዲህ ብለው የተናገሩት ስለዚህ ነብያት የተናገሩለት እናንተ ፌዘኞች ተመልከቱ… ማንም ቢነግራችሁ እዚህ ጋር ጳውሎስ እየጠቀሰ ያለው የአንዱን ነብይ ሃሳብ ነው፡፡ ተመልከቱ እናንት ፌዘኞች እናት ብልጥ እንደሆናችሁ የሚሰማችሁ ንቁ ወይም እናንት በእኔ ላይ የምትሳለቁ ንቁ እናም ጥፉ እናም ሙቱ እኔ እኔ የሚለው ተውላጠስ ስም የሚያመለክተው እግዚያብሔርን ነው እሰራለሁ እኔ አንድ ነገር እሰራለሁ ወይም አንድ ተግባር አፈጽማለሁ በዘመናችሁ በእናነተ የህይወት ዘመን የምሰራው ሥራ እኔ የምሰራው ሥራ ምንም አንኳ ማንም ቢነግራችሁ ምንም እንኳ የሆነ ግለሰብ ስለጉዳዩ ቢነግራችሁ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
ጳውሎስና በርናባስ ሲወጡ ልክ ጳውሎስና በርናባስ ለቀው ሲሄዱ እንዲነገሯቸው ለመኗቸው ለመኗቸው ወደ ይሁዲ ኃይማኖት የገቡትን እነዚህ አይሁዳዊ ያይደሉ ወደ አይሁደነት የተቀየሩ ህዝቦች ናቸው እነሱንም ተናገሯቸው፤ መከሯቸው እና አሰጠነቀቋቸው በርናባስና ጳውሎስ ለህዝቡ ነገሯቸውና አሰጠነቀቋቸው በእግዚያብሄር ጸጋ ፀንተው እንዲኖሩ የእግዚያብሔርን ጸጋ በማመን ፀንተው እንዲኖሩ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
ከተማው በሙሉ ይህ ሃረግ የተቀመጠውበከተማው ከሚገኙ ትል ቁጥር ያለቸው ሰዎች ለእግዚያብሄር ቃል ምላሽ እንደሰጡ ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ በአብዛኛው የከተማው ክፍል( ) አይሁድም አይሁድ የሚለው ቃል እዚህ ጋር የሚወክለው የአይሁድ መሪዎችን ነው፡፡ አመራጭ ትርጓሜ የአይሁድ መሪዎች ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
በቅናት ተሞሉ የአይሁድ መሪዎች በቅናት ተሞልተው ነበር ይሰድቡት ነበር ጳውሎስን ሰደቡት
የእግዚያብሔር ቃል በመጀመሪያ ለእናንተ መነገር አለበት አማራጭ ትርጓሜ ለዚህ እኛ ደግሞ የእግዚያብሄርን ቃል ከሁሉ አስቀድመን ልንነግራቸሁ ወደድን
መጀመሪያ ለእነነተ መነገር አለበት መጀመሪያ ለእናነተ ለአይሁዳዊያን መነገር አለበት በተመለከቱት ግዜ ከእነርሱ ያርቁት ነበር አይሁዳዊያን የእግዚያብሔርን ቃል ሲያከፋፉት ተመለከትሁ እናንተ ግን ናቃችሁት የአይሁድ ህዝብ የጳውሎስን መልዕክት እሱም በኢየሱስ በኩል የሆነውን የዘላለም ሂወት ገፉት እኛም ወደ አህዛብ ዞርን እኛ የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስና በርናባስን ሲሆን ከእነሱ ጋር አብረው የነበሩትን አይመለከተም
ብርሃን አድርጌሃለሁ ይህ አባባል የተወሰደው ከብለክዩ ኪዳን እኔ የምለው እግዚያብሄር አብን… እሱ የሚለው ደግሞ መሲሁን ኢየሱስን ያመለክታል፡፡ እሱ የሚለው ተውላጠስ ስም ነጠላ ቁጥር ነው
ለዘላለም ህይወት የተዘጋጁትን ሁሉም እግዚያብሔር ዘላለማዊ ህይወትን እንዲወርሱ የመረጣቸው ሰዎች ፡፡ ለዘላለም ህይወት የተዘጋጁት እግዚያብሄር የዘላለም ህይወትን ለመስጠት የመረጣቸው የእግዚያብሄር ቃል በአከባቢው ባለው ሃገር ሁሉ ተስፋፋ በእረሱ የሚያምኑትም ካሉበት ቦታ በመውጣት ለሌሎች ስለ ኢየሱስ አዳኝነት መልዕክት ተናገሩ
አይሁድም የአይሁድ መሪዎች ቀስቅሰው አስተባብረው ወይም አነሳስተው ስደትን አስነሱባቸው እነዚህ ወንዶችና ሴቶች ስደትን አስመጡባቸው ከከተማም አውጥተው አባረሯቸው ጳውሎስና በርናባስን ከከተማ አስወጧቸው ወይም ከቀጠናቸው አባረሯቸው፡፡ የእግራቸውንም ትቢያ አራግፈው ይህ አይነቱ ትዕምርታዊ አገላለፅ ተግባር በጥንት ሲደረግ እግዚያብሄር ቅጣቱን ይስጣቸሁ ብሎ ማለት መሆኑን ይገልጻል፡፡ በመቃወማቸው ምክንያት እግዚያብሄርእንደሚቀጣቸው ማመላከቻ ነው ሄዱ ጳውሎስና በርናባስ ሄዱ
1 በኢቆንዮንም እንዲህ ሆነ ፤ ጳውሎስና በርናባስ ወደ አይሁድ ምኵራብ አብረው ገብተው፣ ከአይሁድና ከግሪክ ብዙ ሰዎች እስኪያምኑ ድረስ ተናገሩ። 2 ነገር ግን ማመን ያልፈለጉ አይሁድ የአሕዛብን ልብ በመቀስቀስ በወንድሞች ላይ በክፋት አነሣሡአቸው። 3 ጳውሎስና በርናባስም በጌታ ኀይል በድፍረት እየተናገሩ ረዘም ላለ ጊዜ በዚያ ተቀመጡ፤ ጌታም ስለ ጸጋው የሚነገረውን መልእክት በማስረጃ ለመደገፍ ጳውሎስና በርናባስ ምልክትና ድንቅ በእጃቸው እንዲደረግ ሰጠ። 4 የከተማዋ አብዛኛው ሕዝብ ግን፣ አንዳንዱ አይሁድን በመደገፍ፣ ሌላው ደግሞ ከሐዋርያት ጋር በመቆም ተከፋፈሉ። 5 አሕዛብና አይሁድ ጳውሎስንና በርናባስን እንዲያንገላቷቸውና በድንጋይም እንዲወግሯቸው አለቆቻቸውን በማሳመን ጥረት ማድረጋቸውን 6 በተረዱ ጊዜ፣ ወደ ሊቃኦንያ ከተሞች፣ ወደ ልስጥራና ወደ ደርቤ፣ እንዲሁም በአካባቢው ወዳለው ስፍራ ሸሹ፤ 7 በዚያም ወንጌልን ይሰብኩ ነበር። 8 በእግሩ መቆም የማይችልና ሽባ ከእናቱም ማሕፀን ጀምሮ አንካሳ የሆነ አንድ ሰው ተቀምጦ ነበር። 9 ይህ ሰው ጳውሎስ ሲናገር ሰማ። ጳውሎስም ዐይኑን ተከትሎ ይህን ሰው ሲመለከት ለመዳን የሚያስችል እምነት እንዳለው አየ። 10 ስለዚህ ድምፁን ከፍ አድርጎ፣ “ቀጥ ብለህ በእግርህ ቁም” አለው፤ ሰውየውም ብድግ ብሎ ተነሣና ወዲያ ወዲህ ይመላለስ ጀመር። 11 ሕዝቡም ጳውሎስ ያደረገውን ባዩ ጊዜ፣ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው፣ በሊቃኦንኛ ቋንቋ፣ «አማልክት በሰዎች መልክ ወደ እኛ ወርደዋል» አሉ። 12 ስለዚህም በርናባስን «ድያ» አሉት፤ ጳውሎስም ዋነኛ ተናጋሪ ስለ ነበር፣ «ሄርሜን» አሉት። 13 ቤተ ጣዖቱ ከከተማው ውጭ የነበረው የድያ ካህን በሬዎችንና የአበባ ጕንጕን ይዞ ወደ ከተማይቱ በር መጣ፤ እርሱና ሕዝቡም ለእነ ጳውሎስ መሥዋዕት ሊያቀርቡላቸው ፈለጉ። 14 ነገር ግን ሐዋርያቱ፣ ባርናባስና ጳውሎስ ይህን በሰሙ ጊዜ፣ ልብሳቸውን ቀደው በመጮኽ፣ ፈጥነው ወደ ሕዝቡ መካከል ገቡ፤ 15 እንዲህም አሉ፤ «እናንተ ሰዎች፣ ለምን እነዚህን ነገሮች ታደርጋላችሁ? እኛኮ እንደ እናንተው ዐይነት ስሜት ያለን ሰዎች ነን፤ ወደ እናንተም የመጣነው ከእነዚህ ከንቱ ነገሮች፦ ሰማያትን፣ ምድርንና ባሕርን፣ በውስጣቸውም የሚኖሩትን ሁሉ ወደ ፈጠረ፣ ወደ ሕያው እግዚአብሔር እንድትመለሱ የምሥራች ቃል ይዘን ነው። 16 እግዚአብሔር ባለፉት ዘመናት አሕዛብን ሁሉ በገዛ መንገዳቸው እንዲሄዱ ተዋቸው። 17 ይሁን እንጂ፣ ራሱን ያለ ምስክር አልተወም፤ ምክንያቱም መልካም ሥራ በመሥራት የሰማይን ዝናብና ፍሬያማ ወቅቶችን ሰጥቶአችኋል፤ ልባችሁንም በምግብና በርካታ ሞልቷል።" 18 ጳውሎስና በርናባስ እንደዚህ እየተናገሩም እንኳ፣ ሕዝቡ እንዳይሠዉላቸው መከልከሉ ቀላል አልነበረም። 19 ይልቁንም አንዳንድ አይሁድ ከአንጾኪያና ከኢቆንዮን መጥተው ሕዝቡን በማግባባት ጳውሎስን በድንጋይ ወገሩት፤ የሞተ ስለ መሰላቸውም በመሬት ላይ ጎትተው ከከተማው አወጡት። 20 ይሁን እንጂ፣ ደቀ መዛሙርቱ አብረውት ቆመው ሳሉ፣ ተነሥቶ ወደ ከተማው ገባ። በማግስቱም ከበርናባስ ጋር ወደ ደርቤ ሄደ። 21 በዚያም ከተማ ወንጌልን ሰብከው ብዙ ደቀ መዛሙርትን ካፈሩ በኋላ፣ ወደ ልስጥራ፣ ወደ ኢቆንዮንና ወደ አንጾኪያ ተመለሱ። 22 የደቀ መዛሙርቱንም ልብ እያበረቱ በእምነት እንዲጸኑ መከሯቸው። ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመግባት በብዙ መከራ ውስጥ ማለፍ እንዳለብንም ነገሯቸው። 23 ጳውሎስና በርናባስ በአማኞች ጉባኤ ሁሉ የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎችን ከሾሙ በኋላ፣ ላመኑበት ጌታ በጾምና በጸሎት ዐደራ ሰጡአቸው። 24 ከዚያም በጲስድያ አድርገው ወደ ጵንፍልያ መጡ። 25 ቃሉን በጴርጌን ከተናገሩ በኋላም ወደ አጣሊያ ወረዱ። 26 ለፈጸሙት ሥራ ከዚህ ቀደም ለእግዚአብሔር ጸጋ ወደ ተሰጡበት፣ወደ አንጾኪያ በመርከብ ሄዱ። 27 አንጾኪያ ደርሰው፣ ጉባኤውን በአንድነት ከሰበሰቡ በኋላም፣ እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ሆኖ የሠራውን ሁሉና ለአሕዛብም የእምነትን በር እንዴት እንደ ከፈተላቸው ተናገሩ። 28 በዚያም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ረጅም ጊዜ ቆዩ።
አጠቃላይ መረጃ የጳውሎስና የበርናባስ ታሪክ በኢቆንዮን ቀጥሏል ወደ ኢቆኚዮንም መጥተዋል አማራጭ ትርጓሜ በኢቆኒዮን ተመሳሳይ ነገር ሆኗል አይሁድ ግን አህዛብን አነሳስተው ወንድሞችን እንዲጠሉ አደረጓቸው ነገር ግን የመይታዘዙት አይሁዳዊያንም የአህዛብን ልቦና ወደራሳቸው በመመለስ አማኒያንን እንዲጠሉ አደረጓቸው
እዚያው ቆዩ ጳውሎስና በርናባስ በኢቆኒዮን ስለብዙ አማኒያን ሲሉ ቆዩ ስለዚህ የሚለው ቃል በምንባቡ ውስጥ ብዥታን የሚፈጥር ከሆነ ሊወጣይችላል፡፡ አረጋገጠላቸው እግዚያብሄርም ምልክትን አደረገላቸው ስለመልክቱም ማረጋጋጫ አደረገላቸው፡፡ መልዕክቱ እውነተኛ ስለመሆኑ የሚገልጽ ማስረጃ የጸጋውን ቃል ሰል እግዚያብሄር የጸጋ ቃል በጳውሎስና በበርናባስ እጅ እጅ የሚለው ቃል የሚሳየው የሁለቱን ሰዎች ጥረት በመንፈስ ቅዱስ በመታገዝ መሰራቱን ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ በጳውሎስና በርናባስ አገለ፤ግሎት
ከእነሱ ጋር በመደገፍ ወይም ለእነርሱ በማድላት ከሓዋሪያቱ ጋር ቅዱስ ሉቃስ እዚህ ጋር እያመላከተን ያለው ጳውሎስና በርናባስ ከ12 ሐዋሪያት እኩል መሆናቸውን ነው፡፡
መሪዎቻቸውን አሳምነው በኢቆኒዮንም ያሉ መሪዎችን አሳምነው ይህን እንዳወቁ እነሱ የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስና በርናባስን ነው፡፡ ሊቃኦኒያ በቱር የምትገኝ ግዛት ናት ልስጥራ በኢቆኒዮን በደቡብ በኩል ያለች የቱር ከተማ እና በሰሜን ደርቤ ያዋስናታል፡፡ ደርቤ በኢቆኒዮንና በልስጥራ በደቡብ በኩል የምትገኝ የቱርክ ከተማ በዚያም ወንጌልን ሰበኩ ጳውሎስና በርናባስ እንዲሁ ወንጌልን ይሰብኩ ነበር
አጠቃላይ መረጃ አሁን በርናባስና ጳውሎስ በልስጥራ ናቸው ይህ ደግሞ የታሪኩ አዲስ ምዕራፍ ነው እግሩ አንካሳ የሖነና ከተወለደ ጀምሮ ፈፅ በእግሩ ሄዶ የማያው ሽባ ሰው ከመወለዱ ጀምሮ ሽባ የነበረና መሄድ የማይችል ሰው ጳውሎስ ወደ እሱ ትኩር ብሎ ተመለከተ ጳውሎስም ወደ እሱ በቀጥታ ተመለከተ ባየ ጊዜ ሽባ እንደሆነ ባየ ግዜ ቀጥ ብሎ እንዲሄድ እንዲፈወስ እንዲህ አለው ጳውሎስም ለሽባው ሰው እንዲህ አለው፡፡
የሐዋርያት ሥራ 14፡11-13 አማልክት በሰው ተመስለው ወደ እኛ ወርደዋል ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ሰዎች ጳውሎስና በርናባስ ከሰማይ የወረዱ አመልክቶቻቸው አድርገው ቆጠሯቸው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ አማልክት ከሰማይ ወረዱልን
በሰው ተመስለው እነዚህ ሰዎች አመልክት ሙሉ በሙሉ ሰው እንደማይመስሉ ያምናሉ ቢኮዝ ሂወዝ ምክንያቱም ጳውሎስ ኮርማዎችና የአበባ ጉንጉን የእንስሳት መስዋህት እና የአበባ ጉንጉን ነበር ይህም ለጳውሎስና በበርናባስ እራስ ላይ ለማስቀመጥወይም በተሰዎ እንስሳት ላይ
ሐዋሪያቱ ቅዱስ ሉቀስ ጳውሎስና በርናባስን ከቀደምት 12 ሐዋሪያት እኩል ያደርጋቸዋል እናነተ ሰዎች ለምን ይህን ታደርጋላችሁ ጳውሎስና በርናባስ ህዝቡ ሊሰዋላቸውሰለተነሳ ተቃወሟቸው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ እናነተ ሰዎች ይህን ማድረግ አይገባችሁም፡፡
እኛም እንደ እናነተ ሰዎች ነን አማራጭ ትርጓሜ፡ ልክ እንደ እናነተ በሁሉ መልኩ እናነተ ደግሞ ከዚህ ከንቱነት እራቁ እነዚህን ዋጋ ቢስ አማልክትን ማምለክ አቁሙ ወይም እነዚህን ሃሰተኛ አማልክትን ማምለክ አቁሙ ህያው እግዚያብሄር በምትኩ ህያው እግዚያብሄርን አምልኩ እንድተመላለሱ እንደተጻፈው እንድትኖሩ
አያያዥ ዓረፍተ ነገሮች ጳውሎስና በርናባስ ለህዝቡ መናገራቸውን ቀጥለዋል እርሱ እራሱ አለተዋቸውም እግዚያብሔር እራሱ አልተዋቸውም በእዚህም ምክንያት አማራጭ ትርጓሜ በመረጃ እንደተረጋገጠ በመስጠቱ…ልባችሁን በመሙላት ጳውሎስ ሁሉንም አድማጮች እናነተ በማለት ይጠቀልላቸዋል በመግብና በድስታም ልባችሁን በመሙላት የምትበሉትን በመስጠትናየምትደሰቱበትን በማድረግ ጳውሎስና በርናባስ ህዝቡ እንዳይሰዋላቸው ያስተዎት በብዙ ችግር ነበር ህዝቡ በደፈናው ለጳውሎስና በርናባስ ይሰዋ ነበር፡፡
ህዝቡን አግባቡ ህዝቡንም በጳውሎስ ላይ አስነሱ ተነሳና ሄደ ይህ ጳውሎስን ነው የሚመለከተው ወደከተማ ገባ ጳውሎስ በድጋሜ ወደ ልስጥራን ከአማኞች ጋር ገባ ወደ ደርቤ ሄደ
የደቀመዛሙርቱን ልብ አበረታቱ ጳውሎስና በርናባስ አማኞች እንዲያምኑና በእምነታቸው እንዲያድጉ ምክንያት ሆኗቸው፡፡ በእምነታቸው ጸንተው እንዲቀጥሉ መከሯቸው፡፡ ጳውሎስና በርናባስ ሰዎችን በኢየሱስ ላይ ባላቸው እምነት እንዲቀጥሉ አበረታቷቸው ወደ እግዚያብሄር መንግስት ለመግባት በብዙ መከራ ማለፍ አለብን አሏቸው፡፡ ይህ ቀጥታ ያልሆነ ንግግር ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ እነሱም እንዲህ አሏቸው በብዙ መከራ ወደ እግዚያብሄር መንግሰት ልንገባ ይገባል፡፡
እነሱም አሏቸው ጳውሎስና በርናባስ በልስጥራ፣በኢቆኒዮን እነ በአንፆኪያ ላሉ ክርስቲያኖች ነገሯቸው ለመግባት ጳውሎስ ራሱን በርናባስንና አማኞችን ያካትታል
ከሾሙላቸውም በኋላ ጳውሎስና በርናባስ ለአዲስ አማኝ ቡድኖች መሪዎችን ሾሙላቸው አደራ ሰጧቸው ጳውሎስና በርናባስ የሾሟቸውን መሪዎች አደራ አሏቸው አልፈው… ተናግረው…ወረዱ…በጀልባ…ተሰጥተው ነበር አሁን ፈጽመውታል እነሱ የሚለው ተውላጠስ ስም የሚመለክተው ጳውሎስና በርናባስን ነው፡፡ በእግዚያብሄር ጸጋ በአደራ ወደተሰጡበት የአንጾኪያ ሰዎች ጳውሎስና በርናባስን እግዚያበሄር እንዲጠበቃቸውና እንዲከባከባቸው ጸለዩ፡፡
እዚያም በደረሱ ጊዜ ጳውሎስና በርናባስ ሲደርሱ እግዚያብሄር በእነሱ ያደረገውን እግዚያብሄር በጳውሎስና በበርናባስ ያደረገውን ለአህዛብ እንዴት የእምነት በር እንደከፈተላቸው እግዚያብሄር ለአህዛብ እንዴት አድርጎ በር እንደከፈተላቸው የሚሳይ አማራጭ ትርግም፡ እግዚያብሄር ለአህዛብ እንዲያምኑ አስችሏል፡፡ እንዴት እንዳደረገ ተቀመጡ ጳውሎስና በርናባስ ተቀመጡ
1 አንዳንድ ሰዎች ከአይሁድ ወደ አንጾኪያ ወርደው፣ «በሙሴ ሥርዓት መሠረት ካልተገረዛችሁ መዳን አትችሉም» በማለት ወንድሞችን አስተማሯቸው። 2 ጳውሎስና በርናባስም ከእነርሱ ጋር ጥልና ክርክር በገጠሙ ጊዜ፣ ጳውሎስና በርናባስ እንዲሁም ሌሎች ሰዎች ስለዚህ ጉዳይ በኢየሩሳሌም ወደ ነበሩ ሐዋርያትና ሽማግሌዎች እንዲወጡ ወንድሞች ወሰኑ። 3 ስለዚህ በቤተ ክርስቲያን ተልከው፣ በፊንቄና በሰማርያ በኩል አድርገው ሲሄዱ፣ የአሕዛብን መለወጥ እያወጁ ዐለፉ፤ ይህም ወንድሞችን ሁሉ እጅግ ደስ አሰኛቸው። 4 ወደ ኢየሩሳሌም በመጡ ጊዜም፣ ቤተ ክርስቲያን፣ ሐዋርያትና ሽማግሌዎች በደስታ ተቀበሏቸው፤ እነ ጳውሎስም እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ሆኖ የሠራውን ሁሉ ነገሯቸው። 5 ከፈሪሳውያን ወገን ያመኑ አንዳንድ ሰዎች ግን ተነሥተው፣ «እነርሱን መግረዝና የሙሴንም ሕግ እንዲጠብቁ ማዘዝ ያስፈልጋል» አሉ። 6 ስለዚህ ሐዋርያትና ሽማግሌዎች ይህን ጉዳይ ለማየት ተሰበሰቡ። 7 ከብዙ ጭቅጭቅ በኋላ ጴጥሮስ ተነሥቶ ቆመና እንዲህ አለ፦ «ወንድሞች ሆይ፣ አሕዛብ የወንጌልን ቃል ከአፌ እንዲሰሙና እንዲያምኑ፣ እግዚአብሔር ከጥቂት ጊዜያት በፊት ከእናንተ መካከል እኔን እንደ መረጠኝ ታውቃላችሁ።» 8 ልብን የሚያውቅ አምላክ፣ ለእኛ እንዳደረገው ሁሉ፣ ለእነርሱም መንፈስ ቅዱስን በመስጠት መሰከረላቸው፤ 9 በእኛና በእነርሱ መካከልም ልባቸውን በእምነት በማንጻት ልዩነት አላደረገም። 10 እንግዲህ አባቶቻችንና እኛ መሽከም ያልቻልነውን ቀንበር በደቀ መዛሙርት ጫንቃ ላይ በመጫን ለምን እግዚአብሔርን ትፈታተናላችሁ? 11 ነገር ግን እኛም በጌታ በኢየሱስ ጸጋ እንደ እነርሱ እንደምንድን እናምናለን።» 12 በርናባስና ጳውሎስ እግዚአብሔር በእነርሱ አማካይነት በአሕዛብ መካከል ስለ ሠራው ምልክትና ድንቅ ሲናገሩ፣ ሕዝቡ ሁሉ በጸጥታ አደመጡ። 13 ንግግራቸውንም በጨረሱ ጊዜ፣ ያዕቆብ እንዲህ ሲል መለሰ፤ «ወንድሞች ሆይ፣ አድምጡኝ። 14 እግዚአብሔር ለስሙ የሚሆንን ሕዝብ ከእነርሱ መካከል ይወስዱ ዘንድ፣ አሕዛብን በመጀመሪያ በጸጋ እንደ ረዳ ስምዖን ተናግሮአል። 15 የነቢያት ቃል ከዚህ ጋር ይስማማል እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፤ 16 ከእነዚህ ነገሮች በኋላ እመለሳለሁ፤ ፍርስራሹንም መልሼ እተክላለሁ፤ እንደገናም ዐድሳለሁ፤ 17 ይኸውም የተረፉት ሰዎችና በስሜ የተጠሩ አሕዛብ፣ እግዚአብሔርን እንዲፈልጉ ነው። 18 እነዚህ ጥንታዊ ነገሮች እንዲታወቁ የሚያደርግ ጌታ የሚለው ይህን ነው። 19 ስለዚህ የእኔ ዐሳብ ከአሕዛብ ወደ እግዚአብሔር የተመለሱትን እንዳናስጨንቃቸው ነው፤ 20 ነገር ግን በጣዖታት ከመርከስ፣ ከዝሙት፣ ከታነቀና ከደም እንዲርቁ እንጻፍላቸው። 21 ሙሴስ ከጥንት ዘመናት ጀምሮ በከተሞች ሁሉ በየሰንበታቱ በምኵራብ የሚሰብኩና የሚያነቡ ሰዎች አሉትና።» 22 ስለዚህ በርስያን የተባለው ይሁዳንና ሲላስን የቤተ ክርስቲያን መሪዎች አድርገው እንዲመርጡና፣ ከጳውሎስና ከበርናባስ ጋር ወደ አንጾኪያ እንዲልኳቸው ለሐዋርያትና ለሽማግሌዎች፣ ከቤተ ክርስቲያን ሁሉ ጋር መልካም መስሎ ታያቸው። 23 እንዲህም ብለው ጻፉ፤ «ለሐዋርያት፣ ለሽማግሌዎችና ወንድሞች፣ እንዲሁም በአንጾኪያ፣ በሶርያና በኪልቅያ ለሚገኙ ከአሕዛብ ወገን ለሆኑ ወንድሞች፣ ሰላም ለእናንተ ይሁን። 24 እኛ ያላዘዝናቸው አንዳንድ ሰዎች ከእኛ ዘንድ መጥተው ነፍሳችሁን በሚያስጨንቅ ትምህርት እንዳስቸገሩአችሁ ሰምተናል። 25 ስለዚህ በአንድ ልብ ሆነን ሰዎችን መርጠን ከወዳጆቻችን ከበርናባስና ከጳውሎስ ጋር ወደ እናንተ መላክ ለሁላችንም መልካም መስሎ ታየን፤ 26 እነዚህ ሰዎች ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሲሉ ለሕይወታቸው እንኳ ያልሣሡ ናቸው። 27 ይህንኑ እንዲነግሯችሁ ይሁዳንና ሲላስን ወደ እናንተ ልከናል፤ 28 ከእነዚህ አስፈላጊ ነገሮች በላይ ከባድ ሸክም እንዳንጭንባችሁ፣ ለመንፈስ ቅዱስና ለእኛ መልካም መስሎ ታይቶናልና፤ 29 ይኸውም ለጣዖት ከተሠዋ፣ ከደም፣ ከታነቀ፣ ከዝሙትም እንድትርቁ ነው። ራሳችሁን ከእነዚህ ብትጠብቁ መልካም ይሆንላችኋል፤ ደኅና ሁኑ።» 30 ከዚያም ተሰናብተው ወደ አንጾኪያ ወረዱ፤ ሕዝቡንም ሰብስበው ደብዳቤውን ሰጡአቸው። 31 ደብዳቤውንም አንብበው ስለ ተጽናኑ በጣም ደስ አላቸው። 32 ደግሞም ይሁዳና ሲላስ ነቢያት ስለ ነበሩ፣ወንድሞችን በብዙ ቃል በመምከር አበረታቱአቸው። 33 በዚያም ጥቂት ጊዜ ከተቀመጡ በኋላ፣ከወንድሞች በሰላም ተሰናብተው ወደ ላኳቸው ሄዱ። 34 ሲላስ ግን እዚያው መቆየት መልካም መስሎ ታየው። 35 ጳውሎስና በርናባስ ግን የጌታን ቃል ባስተማሩበትና በሰበኩበት በአንጾኪያ ከሌሎች ብዙ ሰዎች ጋር ተቀመጡ። 36 ከጥቂት ቀናት በኋላ፣ ጳውሎስ በርናባስን፣ «ተመልሰን የጌታን ቃል በሰበክንበት ከተማ ሁሉ ያሉትን ወንድሞች እንጐብኝ፤ በምን ሁኔታ እንዳሉም እንወቅ» አለ። 37 በርናባስም ማርቆስ የተባለውን ዮሐንስን ደግሞ ከእነሱ ጋር ይዞ ለመሄድ ፈለገ። 38 ጳውሎስ ግን ማርቆስን ይዞ መሄድ አልፈለገም፤ ምክንያቱም ማርቆስ ከዚህ ቀደም ከእነርሱ ጋር ለሥራ በመሄድ ፈንታ፣ በጵንፍልያ ተለይቶአቸው ቀርቶ ነበር። 39 በመካከላቸው ከፍተኛ አለምስማማት ስለ ተፈጠረም፣ ተለያዩ፤ በርናባስም ማርቆስን ይዞ ወደ ቆጵሮስ በመርከብ ሄደ። 40 ጳውሎስ ግን ሲላስን መረጠ፤ ወንድሞች ለጌታ ጸጋ አደራ ከሰጡት በኋላ፣ ተለይቶአቸው ሄደ። 41 ከዚያም አብያተ ክርስቲያናትን እያበረታታ በሶርያና በኪልቅያ ይዞር ነበር።
የሐዋርያት ሥራ 15፡1-2 አጠቃላይ መረጃ ይህ አዲስ የታሪክ ክስተት ሲሆን ጳውሎስና በርናባስ አሁንም በአንጾኪያ ሲሆኑ በአህዛብ መገረዝና አለመገረዝ ላይ ክርክሮች ነበሩ አንዳንድ ሰዎች የሆኑ ሰዎች አይሁድ ወረዱ አይሁዳዊያን ወደ ኢየሩሳሌም በመጀመሪያ ሲመጡ እየወጡ መሆኑና ሰመለሱ ደግሞ እየወረዱ መሆኑን ያስባሉ፡፡ ወንድሞችን ማስተማር ጀመሩ በአንጾኪያ ያሉ ወንድሞችን ማስተማር ቀጠሉ ወይም በአንጾኪያ ያሉ ክርሰቲያኖችን ማስተማር ጀመሩ በስርዓቱም መሰረት እንደ ስርዓታቸውም ከእነረሱ ጋር አይሁድ ከሆኑ ሰዎች ጋር ወደ ኢየሩሳሌም ወጡ ይህ ጥያቄ ይህ ጉዳይ
እነሱም በቤተ ክርስቲያን ተላኩ አማራጭ ትርጓሜ ስለዚህ ቤተክርስቲያን ጳውሎስና በርናባስን እንዲሁም ሌሎች አማኒያን ከአንጾኪያ ወደ ኢየሩሳሌም ላኳቸው፡፡
እንዲያልፉ…እንዲነገሩ ይህ የሚያመለክተው በሚሄዱበት ወቅት ጥቂት ግዜ እንደሚቆዩ ያሳያል፡፡ የአህዛብ መለወጥ ብዙ አህዛቦች የግሪክና የሮማዊያን አማልክትን ከማምለክ ወደ እግዚያብሄርን ማምለክ ተመልሰው ነበር ቤተክርስቲያነም ተቀብላቸው ነበር አማራጭ ትርጓሜ፡ እንደ ቤተክርስቲያን አባላ ተቀብለዋቸዋል፡፡ )
ከእነሱ ጋር በእነሱ በኩል
አሁን ጳውሎስና በርነባሳ ሐዋሪያትንና የቤተክርስቲያን ሽማግሌዎችን ለማግኘት በኢየሩስአሌም ተግኝተዋል፡፡ አነዳንድ ሰዎች ግን ቅዱስ ሉቃስ እያነጻጸረ ያለው ድህነት በኢየሱስ ብቻ የሚሉትንና ሌሎች ደግሞ በኢየሱስ ማመንና መገረዝን አብረው በሚይዙት መካከል ነው፡፡ አህዛብ እንዲገረዙና የሙሴን ህግ እንዲጠብቁ እነሱ የሚለው ቃል የሚያመለክተው ያልተገረዙ አህዛቦችን ነው፡፡ ህግን እንዲጠብቁ ህጉን እንዲታዘዙ ወይም እንዲከተሉ ጉዳዩን ለማጤን የቤተክርስቲያን መሪዎች በእነጳውሎስ መልዕክትና በፈሪሳዊያን መካከል ያለውን ጉዳይለመወያየት ያጤኑ ነበር፡፡ አማራጭ ትርጓሜ፡ በኃይማኖት ያለውን ልዩነት ለመወያት
አጠቃላይ መረጃ ጴጥሮስ ለሐዋሪያትና ለሽማግሌዎች መናገር ጀመረ እንዲህ አላቸው በጉባኤው ለተገኙ ሐዋሪያት ሸማገሌዎችና ሌሎች አማኞች ወንደሞች ጴጥሮስ ሁሉንም የተሰበሰቡትን ሰዎች እያመለከተ ነው፡፡ ከእኔ አንደበት አንደበት የሚለው ቃል የሚያመለክተው የጰጥሮስን ቃል ነው፡፡
አህዛብ የወንጌልን ቃል ሰምተው አህዛብ ወንጌልን ሰምተው ምስክር ሆነው ለአህዛብ ምስክር ሆነው ማድረጉን እግዚያብሔር ማድረጉን ምንም ልዩነት ሳያደርግ እግዚያብሄር በዳኑ አይሁዳዊያን እና በዳኑ አህዛብ መካከል ምንም ልዩነት ሳያደርግ በእኛ እና በእነሱ መካከል ጴጥሮስ እራሱን እኛ በማለት ሲያካትት የዳኑ አህዛብን ደግሞ እነሱ በማለት ይገልጻል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ጴጥሮስም ለሃዋሪያትና ለሽማግሌዎች መናገሩን ጨረሰ አባቶቻችንም እኛም ልንሸከመው የማንጨለውን ቀንበር ለምን በሌሎች ላይ እንጭናለን አሁንስ እግዚያብሄርን ትፈታተናላቸሁ ጴጥሮስ የአይሁዳዊያን ለመን በአህዛብ ላይ የመገረዝን ቀንበር እንዲሸከሙ ያዟቸዋል አባቶቻችንም እኛም ብንሆን ጴጥሮስ ታዳሚያኑን የዕኛ እና የእኛ በሚለው ቃል ሲያካትታቸው እንመለከታለን፡፡
ነገር ግን እኛ እኛም በክርስቶስ ኢየሱስ ጸጋ እንደዳንን እናምናለን ጴጥሮስ የዳኑ አይሁዳዊያንን ከራሱ ጋር ቀላቅሎ እየጠራ ነው፡፡ ልክ እንደ እነርሱ ልክ የዳኑ አይሁድ ያለሁኑት እንደዳኑበት
ሁሉም የተሰበሰቡት ሐዋሪያት፣ ሽማግሌዎችና ሌሎች ማንነታቸው ያልተገለጠ ተሰብሰቢዎች እግዚአብሔር ሥራውን ሰራው እግዚያብሔር ሰራው በእነሱ በእነሱ ሚለው የሚያመለክተው ጳውሎስና በርናባስን ነው፡፡ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
አጠቃላይ መረጃ ያዕቆብ ለሓዋሪያትና በዚያ ለተሰበሰቡት ሸማግሌዎች መናገር ጀመረ እነሱ መናገር ካቆሙ በኋላ በርናባስና ጳውሎስ መናገራቸውን ካቆሙ ወይም ከጨረሱ በኋላ ከእነሱ በመምረጥ ከመካከላቸው በመምረጥ ሰዎች በእንድ የተከማቹ ሰዎች ስለ ስሙ ስሙ የሚያመለክተው እግዚያብሔርን ነው፡፡ አማራጭ ትርጓሜ፡ ስለራሱ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ያዕቆብ ከነብያት መጽሃፍ ከሆነው ከአሞጽ መፅሃፍ ጠቀሰ በዚህ እንስማማለን ይህንን እውነት እናረጋግጣለን እመልሳችኋለሁ…እግነባችኋለሁ…እንደገና እሰራታለሁ እኔ የሚለው በነቢያቱ በኩል ይናገር ነበረውን እግዚያብሔርን ነው የሚያመለክተው የዳዊትን ድንኳን መልሼ አነሳታለሁ ድንኳን የሚለው ቃል እዚህ ጋር ሚያመለክተው ስረው መንግስትን ነው አማራጭ ትርጓሜ ከዳዊት ስርወ መንግስት ውስጥ ቀጠዩን መርጫለሁ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
የፈረሰችውን እንደገና እገነባታለሁ በዚያም ቅሪታዎች እግዚያብሄርን ይፈልጋሉ የዳዊትን ስርወ መንግስት እመሰርታለሁ በዚያም ህዝቦቿ እግዚያብሄርን የሚፈልጉ ይሆናሉ ፍርስራሹን አድሳለሁ ፍርስራሽ የሚያመለክተው በአንድ ከተማ መፈራረስ ምክንያት የምናገኘው የወዳደቁ እናየሚበሰበሱ ነገሮች ነው ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ያዕቆብ ለሓዋሪያትና ለሽማግሌዎች መናገሩን ጨረሰ አህዛብን ልናስጨንቃቸው አይገባም አህዛብ እንዲገረዙና የሙሴንም እግ እንዲጠብቁ ልናስገድዳቸው አይገባም (
እኛ ልናስጨንቃቸው አይገባም ያዕቆብ እኛ በማለት ሽማግሌዎችንና ሓዋሪቱንም ጭምር ነው ሚያካትተው፡፡ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ ( ) ጣዖት…..ብልግና…የታነቀ… ደም ብልግና፣የታነቁ ህንስሳት ደም መጠጣትና መሰል ተግባራት ጣዖትን በማምለክ ስርዓት ውስጥ ያሉ ስነ ስርዓቶች ናቸው ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
በሙሉ ቤተክርስቲያኗ በሙሉ የሚለው ግነታዊ አገላለጽ በቤተክርስቲያኒቱ ያሉትን መዕምናን የሚገልጽ ነው ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
ይሁዳ የሚሉት በርስያን በኢየሩሳሌም ባለች ቤተክርስቲያን መሪ የነበረ ሰው ሲላስ በኢየሩሳሌም ባለች ቤተክርስቲያን መሪ የነበረ ሰው ላኳቸው/ሰደዷቸው ይሁዳ እና ሲላስን ላኳቸው ይህን ፃፎላቸው ሓዋሪያትሽማግሌዎችና በኢየሩስ አሌም የነበሩ አማኒያን ቃላችውን ጽፈው ላኩ፡፡ ይህ የሃዋሪያት ደብዳቤ መጀመርን ያበስራል፡፡ ሲሊሲያ በቆጵሮስ በስተሰሜን በኩል የምትገኝ የቱርክ ባህር ዳርቻ ቦታ ናት ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
አያያዥ አረፍተ ነገር ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያዊቷ የአህዛብ ቤተክርስቲያን የተላከው ደብዳቤ ቀጥሏል፡፡ የተወሰኑ ሰዎች አንዳንድ ሰዎች ለማንም ይህን ትዕዛዝ መስጠት አንችልም ይህንን ወጥተው እንዲሰብኩ እኛ ልናዛቸው አንችልም ስለዚህ ሁላችንም መልካም ሆኖ ታየን ሁላችንም ተስማማን ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
የሐዋርያት ሥራ 15፡27-29 አያያዥ ዓረፈተ ነገር ይህ ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ደብዳቤ መላክን ያስቀረ የመጨረሻ ክስተት ነው፡፡ ለእናነተ ደግሞ በቃላቸው ያንን ይነግሯችኋል እነሱ እራሳቸው በገዛ ቃላቸው ይነግሯቸዋል፡፡ ደም ይህ የሚያመለክተው የታረዱና የሞቱ እንስሳተን ደም መጠጣት ይመለከታል፡፡ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ ( የታነቁ ነገሮች ደሙ ሳይፈስ ታንቆ የተገደለ እንስሳ ሰላምታና ስንብት የስንብትና የሰላምታ ደብዳቤ
ስለዚህ እነርሱ፣ እነርሱ ይህንን በማደረጉ ጊዜ . . . እነርሱ ይህንን ካደረጉ በኋላ . . . እነርሱ ነጻ ወጡ በዚህ ክፍል ውስጥ "እነርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ይሁዳን፣ ሲላስን፣ ጳውሎስን እና ባርናባስን ነው፡፡ ተለቀቁ "እንዲሄዱ ተፈቀደላቸው" ወይም "ተላኩ" ወደ አንጾኪያ እንዲወርዱ ይህ የከፍታ ለውጥን ያመለክታል፡፡ ይሁን እንጂ አይሁዳዊያን ወደ ኢየሩሳሌም የሚደረግ ጉዞ ወደ ከፍታ የሚደረግ ጉዞ አድርገው ይቆጥሩታል፡፡ በተመሳሳይ መልኩም ከኢየሩሳሌም የሚደረግ ጉዞን ወደታች የሚደረግ ጉዞ ያደርጉታል፡፡ ካነበቡት በኋላ ደስ አላቸው በዚህ ክፍል ውስጥ "እነርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው በአንጾኪያ ያሉት አሕዛብ አማኞችን ነው፡፡ እንዲሁም ነቢያት ነቢያት እርሱን ወኪለው መናገር ይችሉ ዘንድ በእርሱ ስልጣን የተሰጣቸው ናቸው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እነርሱ ነብያት ከመሆናቸው የተነሣ፡፡" ወንድሞችን አበረታቷቸው "በአንጾኪያ የሚገኙ ወንድሞችን አበረታቷቸው"
ከእነሱ በኋላ…እነሱ ተላኩ እነሱ የሚለው የሚያመለክተው ሲላስናይሁዳን ነው፡፡ ለጥቂት ግዜ ለተወሰኑ ግዚያት ወይም ለተወሰኑ ሳምንታት ከወንድሞች በሰላም ተለይተው ሄዱ እነሱም ሲሄዱ አማኒያኑ በሰላም አሰናበቷቸው ሰላምታ ከወንድሞች ልክ በአንጾኪያ እንዳሉ ጓደኞች ይሁዳና ሲላስን ወደላኳቸው ኢሩሳሌም ቤተክርስቲያን ነገርግን በርናባስና ጳውሎስ ቆዩ በርናባስና ጳውሎስ ግን እዛው ሆኑ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
እስኪ እንመልከት እኛ እንደምንለው ወንደሞችን ጎበኙ እንዴት እንደሆኑ ተመልከቱ ከወንድሞች እውነት የያዙበትን መንገድና ከሁኔታቸው ተማሩ ከእነሱ ጋር ማርቆስ የተባለውን ዩሃንስን ወሰዱት ከጳውሎስና ከበርናባስ ጋር ማርቆስ የተባለውን ዩሃንስን ወሰዱት ጳውሎስ ግን ማርቆስን መያዙን እንደ ጥሩ ነገር አለያውም በጥሩ አለማየት ማለት መቃወም ማለት ነው፡፡ ማስፈንጠሪያውን ይመልከቱ
በፍጹም አለመግባባት በርናባስና ጳውሎስ ወደ መስማማት ሊመጡ አልቻሉም ሰለዚህ ተለያዩ ስለዚህ በርናባስና ጳውሎስ ተለያዩ እናም በመርከብ ሄዱ በመርከብ ተጓዙ በወንድሞች በአንፆኪያ ባሉ አማኒያን በሲሪያና በሲሊሲያ በኩል ሄዱ ቤተክርስቲያንን አጠናከሩ ቤተክርስቲያንን በመንፈሳዊ ነገር እንድትተነክር አደረጉ፡፡
1 ጳውሎስ ወደ ደርቤና ወደ ልስጥራ መጣ፤ እነሆም፣ እናቱ አይሁዳዊት አማኝ የሆነች፣ አባቱ ግን ግሪክ የሆነ ጢሞቴዎስ የሚባል አንድ ደቀ መዝሙር አገኘ። 2 በልስጥራና በኢቆንዮን የነበሩ ወንድሞችም ስለ እርሱ ጥሩ ምስክርነት ነበራቸው። 3 ጳውሎስም እርሱን ይዞ መጓዝ ፈለገ፤ በዚያ አካባቢ ስለ ነበሩ አይሁድ ሲልም ጢሞቴዎስን ገረዘው፤ አባቱ የግሪክ ሰው እንደ ሆነ ሁሉም ያውቁ ነበርና። 4 በየከተሞቹ በሚዞሩበት ጊዜ፣ አብያተ ክርስቲያናት እንዲጠብቁት በኢየሩሳሌም የነበሩ ሐዋርያትና ሽማግሌዎች የጻፉትን መመሪያ ሰጡአቸው። 5 ስለዚህ አብያተ ክርስቲያናቱ በእምነት እየበረቱ፣ ቍጥራቸውም በየዕለቱ እየጨመረ ነበር። 6 በእስያ አውራጃ ቃሉን እንዳይሰብኩ መንፈስ ቅዱስ ስለ ከለከላቸው፣ ጳውሎስና ባልደረቦቹ በፍርግያና በገላትያ አውራጃዎች አድርገው ዐለፉ። 7 ወደ ሚስያ አካባቢ በደረሱ ጊዜ፣ ቢታንያ ለመግባት ሞከሩ፤ የኢየሱስ መንፈስ ግን ከለከላቸው። 8 ስለዚህ ሚስያን ዐልፈው ወደ ጢሮአዳ ወረዱ። 9 ጳውሎስም አንድ የመቄዶንያ ሰው ቆሞ፣ “ወደ መቄዶንያ ተሻግረህ ርዳን” እያለ ሲለምነው ሌሊት በራእይ ታየው። 10 ራእዩንም ካየ በኋላ፣ ወዲያው ወደ መቄዶንያ ለመሄድ ተነሣን፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ወንጌልን ለእነርሱ እንድንሰብክ እንደ ጠራን ዐሰብን። 11 ከጢሮአዳ ተነሥተንም ቀጥታ በመርከብ ወደ ሳሞትራቄ ሄድን፤ በማግስቱም ናጱሌ ደረስን፤ 12 ከዚያም የመቄዶንያ ከተማ ወደ ሆነችው ወደ ፊልጵስዩስ ሄድን፤ ከተማዋ የወረዳው ዋና ከተማና የሮም ቅኝ ግዛት ነበረች፤ በዚችም ከተማ ብዙ ቀን ተቀመጥን። 13 በሰንበት ቀንም፣ በወንዝ አጠገብ በነበረው በር በኩል ወደ ውጭ ወጣን፤ ይህም ስፍራ የጸሎት ቦታ እንደ ሆነ ዐሰብን። በዚያም ተቀምጠን ተሰብስበው ለነበሩ ሴቶች ተናገርን። 14 ከትያጥሮን ከተማ የመጣችና የሐምራዊ ሐር ሻጭ የነበረች፣ ልድያ የምትባል፣ እግዚአብሔርን የምታመልክ አንድ ሴት ትሰማን ነበር። ጳውሎስ እየተናገረ የነበረውን በሚገባ እንድታደምጥ፣ ጌታ ልብዋን ከፈተላት። 15 ከቤተ ሰብዋ ጋር በተጠመቀች ጊዜም፣ “በጌታ ማመኔን ከተረዳችሁልኝ ወደ ቤቴ ግቡና ተቀመጡ” ብላ ለመነችን፤ አስገደደችንም። 16 አንድ ቀን ጸሎት ቦታ ስንሄድ የጥንቈላ መንፈስ ያደረባት አንዲት ወጣት አገኘችን፤ በዚህ የጥንቈላ ሥራዋም ለአሳዳሪዎችዋ ከፍተኛ ገቢ ታስገኝ ነበር። 17 ይህችው ሴት ጳውሎስንና እኛን ከኋላ እየተከተለች፣ “እነዚህ ሰዎች የልዑል እግዚአብሔር አገልጋዮች ናቸው፤ የመዳንን መንገድ ይነግሯችኋል” እያለች ትጮኽ ነበር። 18 ይህንም ብዙ ቀን ደጋገመች። ጳውሎስ ግን በዚህ እጅግ ተበሳጨ፤ ዘወር ብሎም መንፈሱን፣ “ከእርስዋ እንድትወጣ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አዝሃለሁ” አለው፤ በዚያው ቅጽበትም መንፈሱ ወጣ። 19 አሳዳሪዎችዋም ተስፋ የሚያደርጉበት የገቢያቸው ምንጭ እንደ ጠፋ ባዩ ጊዜ፣ ጳውሎስንና ሲላስን ይዘው በምድር ላይ እየጎተቱ በገበያ ስፍራ ባለ ሥልጣኖቹ ፊት አቀረቡአቸው። 20 ወደ ገዢዎችም አምጥተዋቸው፣ “እነዚህ ሰዎች አይሁድ ሆነው ሳሉ በከተማችን ውስጥ ከፍተኛ ሁከት እየፈጠሩ ነው። 21 እኛ ሮማውያን ለመቀበል ያልተፈቀዱልንን ነገሮች ያስተምራሉ” አሉ። 22 በዚህ ጊዜ ሕዝቡ በጳውሎስና በሲላስ ላይ በአንድነት ተነሡ፤ ገዦቹም ልብሳቸውን አስወልቀው በዱላ እንዲደበድቡአቸው አዘዙ። 23 ብዙ ድብደባ ካደረሱባቸው በኋላ፣ ወደ ወኅኒ ጣሉአቸው፤ የወኅኒ ጠባቂውም በጥንቃቄ እንዲጠብቃቸው አዘዙት። 24 የወኅኒ ጠባቂውም ይህን ትእዛዝ ተቀብሎ፣ ወደ ውስጠኛው እስር ቤት ጣላቸው፤ እግራቸውንም ከግንድ ጋር አጣብቆ አሰራቸው። 25 እኩለ ሌሊት አካባቢም፣ ጳውሎስና ሲላስ እየጸለዩ በዝማሬ እግዚአብሔርን ያመሰግኑ ነበር፤ ሌሎች እስረኞችም አደመጡአቸው። 26 ድንገትም የወኅኒው መሠረት እስከሚናጋ ድረስ ታላቅ የምድር መናወጥ ተከሠተ፤ ወዲያውም የወኅኒው በሮች ሁሉ ተከፈቱ፤ የታሳሪዎችም ሁሉ ሰንሰለቶች ተፈቱ። 27 የወኅኒ ጠባቂውም ከእንቅልፉ ነቅቶ በሮቹ እንደ ተከፈቱ አየ፤ እስረኞቹ ያመለጡ ስለ መሰለውም፣ ሰይፉን መዞ ራሱን ሊገድል ቃጣ። 28 ጳውሎስ ግን በታላቅ ድምፅ፣ “ራስህን አትጉዳ! እኛ ሁላችን እዚሁ አለን” ብሎ ጮኸ። 29 የወኅኒ ጠባቂውም መብራት ለምኖ ሮጦ ወደ ውስጥ ገባ፤ በፍርሀት እየተንቀጠቀጠም በጳውሎስና በሲላስ ፊት ተደፋ፤ 30 ወደ ውጭም አስወጥቶአቸው፣ “ጌቶች ሆይ፣ ለመዳን ምን ማድረግ አለብኝ?” አላቸው። 31 እነርሱም፣ “በጌታ ኢየሱስ እመን፤ አንተም ቤተ ሰዎችህም ትድናላችሁ” አሉት። 32 ጳውሎስና ሲላስ ለእርሱና አብረውት በቤት ለነበሩ ሰዎች ሁሉ የጌታን ቃል ተናገሩ። 33 የወኅኒ ጠባቂውም ሌሊት፣ በዚያው ሰዓት ወስዶአቸው ቍስላቸውን አጠበላቸው። እርሱና ቤተ ሰዎቹም ሁሉ ወዲያው ተጠመቁ። 34 ጳውሎስንና ሲላስንም ወደ ቤቱ ይዞአቸው ወጣ፤ ምግብም አቀረበላቸው። ሁሉም በእግዚአብሔርም በማመናችው ከቤተ ሰዎቹ ጋር እጅግ ደስ አለው። 35 ሲነጋም ገዦቹ፣ “እነዚያን ሰዎች ልቀቋቸው” የሚል ትእዛዝ ለጠባቂዎቹ ላኩ። 36 የወኅኒ ጠባቂውም፣ “ገዦቹ እንድትፈቱ ትእዛዝ ለእኔ ልከዋል፤ ስለዚህ ውጡና በሰላም ሂዱ” ብሎ ለጳውሎስ ነገረው። 37 ጳውሎስ ግን እንዲህ አላቸው፤ “ሮማውያን የሆንነውን እኛን ያለ ፍርድ በሕዝብ ፊት ደብድበውናል፤ ወደ ወኅኒም አስገብተውናል፤ ታዲያ፣ አሁን በድብቅ ያስወጡናል? በፍጹም አይሆንም፤ እነርሱ ራሳቸው መጥተው ያስወጡን።” 38 ጠባቂዎቹም ይህንኑ አባባል ለገዦቹ ነገሯቸው፤ ገዦቹም ጳውሎስና ሲላስ ሮማውያን እንደ ሆኑ በሰሙ ጊዜ ፈሩ። 39 መጥተውም ተማጸኑአቸው፤ ከወኅኒም ካስወጡአቸው በኋላ፣ ከከተማው እንዲወጡ ጳውሎስንና ሲላስን ለመኑአቸው። 40 ጳውሎስና ሲላስም ከወኅኒው ወጥተው ወደ ልድያ ቤት ገቡ። ወንድሞችንም ባዩአቸው ጊዜ፣ አበረታቱአቸው፤ ከዚያም ከከተማዪቱ ወጥተው ሄዱ።
አጠቃላይ መረጃ: ይህ የታሪኩ ክፍል ጳውሎስ ከሲላስ ጋር ያደረገው ጉዞ የተዘገበበት ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ጢሞቴዎስ ከጳውሎስ እና ከሲላስ ጋር በመሆን ያደረጋቸውን ነገሮች መዘገብ ይጀምራል፡፡ ቁጥር 1 እና 2 ስለ ጢሞቴዎስ የኃላ ታሪክ መረጃ ይሰጠናል እነሆ “እነሆ” የሚለው ቃል ታሪኩ ስለአንድ አዲስ ሰው መዘገብ እንደጀመ ያሳየናል፡፡ በቋንቋችሁ እንዲህ ያለውን ነገር ማድረግ የሚቻበት መንገድ ይኖራል፡፡ የአንድ አይሁዳዊ አማኝ እናት "በክርስቶስ ያመነችው የአንዲት አይሁዳዊት ሴት እናት" ጥሩ ስም ያለው "ጢሞቴዎስ ጥሩ ስም አለው" ወይም "አማኞች ስለእርሱ መልካም መልካም ነገሮችን ይናገራሉ" ጳውሎስ ከእርሱ ጋር እንዲሄድ ይፈልጋል፤ ስለዚህም ከእርሱ ጋር ወሰደው "ጳውሎስ ጢሞቴዎስ ከእርሱ ጋር እንዲጓዝ ስለሚፈልግ ጢሞቴዎስን ከእርሱ ጋር ወሰደው፡፡" በዚህ ቁጥር ላይ በሦስተኛ መደበኛ ነጠላ ቁጥር የተገለጡት ሁሉ (እርሱ) የሚያለክቱት ጢሞቴዎስን ነው፡፡ አባቱ የግሪክ ሰው ነበር እንደ ግሪካዊ ሰው የጢሞቴዎስ አባት ጢሞቴዎስ እንዲገረዝ አላደረገውም ነበር፡፡ ስለዚህም ጳውሎስ ጢሞቴዎስ አስገርዞታል፡፡ ብዙ ጊዜ ግርዘት የሚፈጸመው እንደ ጳውሎስ ባሉ በአይሁድ መምህራን አማካኝነት ነው፡፡
አብረው ሄዱ በዚህ ክፍል ውስጥ “እነርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን፣ ሲላስን እና ጢሞቴዎስን ነው፡፡ እነርሱ ይታዘዙ ዘንድ "የቤተ ክርስቲያን አባላት ይታዘዙት ዘንድ" ወይም "አማኞች ይታዘዙት ዘንድ" በኢየሩሳሌም ባሉ ሐዋርያት እና ሽማግሌዎች አማካኝነት የተጻፉትን ነገሮች ይታዘዙ ዘንድ አማራጭ ትርጉሞች: "በኢየሩሳሌም ያሉት ሐዋርያት እና ሽማግሌዎች የጻፏቸው ነገሮች" ቤተ ክርስቲያን እየበረታች ሄደች አማራጭ ትርጉም: "ጳውሎስ፣ ሲላስ እና ጢሞቴዎስ ቤተ ክርስቲያን አበረቱ"
በፍርግያና በገላትያ እነዚህ አከባቢዎች በኢስያ ውስጥ የሚገኙ ናቸው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት እንዳይሄዱ ተከለከሉ አማራጭ ትርጉም፡ "መንፈስ ቅዱስ እንዳይሄዱ ከለከላቸው" ወይም "መንፈስ ቅዱስ እንዲሄዱ አልፈቀደላቸውም" በሚስያ . . . ቢታኒያ እነዚህ በሲስያ ውስጥ የሚገኙ ሁለት ተጨማሪ አከባቢዎች ናቸው፡፡ የኢየሱስ መንፈስ "መንፈስ ቅዱስ"
ጳውሎስ ራዕይ አየ ራዕይ ከሕልም ይለያል፡፡ ጠሩት "ጳውሎስን ለመኑት" ወይም "ጳውሎስ እንዲመጣላቸው ጠየቁት" እርዳን በዚህ ሥፍራ ላይ "እኛ" የሚለው ቃል ሌሎችን የሚያገል እና ጳውሎስን የማያካትት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እኔን እና በመቅዶኒያ ያሉትን ሰዎች እርዳ" ወጣን በዚህ ሥፍራ ላይ "እኛ" የሚለው ቃል ሁሉን የሚያቅፍ ሆኖ ጳውውሎስን እንዲሁም የሐዋርያት መጽሐፍ ጸሐፊ የሆነውን ሉቃስን የሚያካትት ነው፡፡ እግዚአብሔር ጠርቶናል በዚህ ሥፍራ ላይ "እኛ" የሚለው ቃል ሁሉን የሚያቅፍ ሆኖ ጳውውሎስን እንዲሁም የሐዋርያት መጽሐፍ ጸሐፊ የሆነውን ሉቃስን የሚያካትት ነው፡፡ ለእነርሱ ወንገል ለመስበክ "ለመቅዶኒያ ሰዎች ወንጌልን እንሰብክ ዘንድ"
አጠቃላይ መረጃ: ቁጥር 13 ሊዲያ የተባለችው ሴት ታሪክ የሚጀምርበት ነው፡፡ ይህ አጭር ታሪክ በጳውሎስ ጉዞ ውስጥ የተከናወነ ነው፡፡ አደረገን በዚህ ሥፍራ ላይ "እኛ" የሚለው ቃል ሁሉን የሚያቅፍ ሆኖ ጳውውሎስን እንዲሁም የሐዋርያት መጽሐፍ ጸሐፊ የሆነውን ሉቃስን የሚያካትት ነው፡፡ ሳሞትራቄ . . . ናጱሌ እነዚህ በፊልጵስዮስ አቅራቢያ የሚገኙ ከተሞች ናቸው፡፡ የሮም ግዛቶች ሮማዊያን በጦርነት አሸንፈው በዚያን ጊዜ የያዝዋቸው ሥፍራዎች ሲሆኑ በተለይም ወታደሮች የሠፈሩባቸው ቦታዎች ናቸው፡፡
አያያዥ ዓረፈተ ነገር: ይህ ስለ ሊዲያ የተነገረው ታሪክ ማጠቃለያ ነው፡፡ ሊዲያ የተባለች እንዲት ሴት ነበረች "ሊዲያ ተብላ የሚትጠራ አንዲት ሴት ነበረች" የድሪ ልብስ ትሸጥ ነበር "የድሪ ልብ ነጋዴ ናት" እግዚአብሔርን የሚያመልክ ሰው እግዚአብሔርን የሚያመልክ ተብሎ የሚጠራ ሰው አሕዛብ ሆኖ ለእግዚአብሔር ምስጋናን የሚያቀርብ እና እርሱን የሚከተል ሆኖ ሁሉንም አይሁድ ሕግጋትን የመማይከተል ሰው ማለት ነው፡፡ አድመጡን "የሚንናገረውን ነገር ታዳምጥ ነበር" በጳውሎስ የተናገራቸውን ነገሮች "ጳውሎስ የተናገራውን ነገሮች" እርሷ እና ቤተሰቧ በሙሉ በተጠመቁ ጊዜ "ሊዲያን እና የቤተሰቧን አባላት ባጠመቁ ጊዜ"
አጠቃላይ መረጃ: ይህ በጳውሎስ ጉዞ ውስጥ የተከናወነውን አጭር ታሪክ መጀመሪያ ነው፡፡ ይህ በታሪኩ ውስጥ የመጀመሪያው ድርጊት ነው፡፡ ታሪኩም ስለ አንድ ወጣት ጠንቋ ነው፡፡ አንድ ወጣት ሴት "አንድ ወጣት ሴት ነበረች" የጥንቆላ መንፈስ አንድ ክፉ መንፈስ ስለ ሰዎች የወደፊት ሁኔታ ብዙ ጊዜ ይነግራት ነበር፡፡ የወደፊቱን በመነናገር ለጌታዋ ብዙ ገንዘብ ታስገኝ ነበር ይህ ስለወጣቷ የኃላ ታሪክ መረጃ ነው፡፡ በእርሷ በጣም ከመበሳጨቱ የተነሳ "በእርሷ ከመበሰጫቱ የተነሣ" ወይም "እርሷ በሚታደርገው ነገር በጣም አስቸገራቸው" ወደ ኋላ ዞሮ "ጳውሎስ ፊቱን አዙሮ" ወይም "ከኋላዋ ወዳለችው ሴት ፊቱን አዙሮ" ወዲያ ከእርሷ ውስጥ ወጣ "መንፈሱም ወዲያው ከእርሷ ውስጥ ወጣ"
ጌታዋም የባሪያይቱ ጌታ የገንዘብ ማግኛ ምንጩ/ተስፋው ይህ ሴትቱ የነበራትን የመጠንቆል ችሎታ እና ሰዎች ስለትንቢቷ ይከፍሉ የነበረውን ነገር የሚያመለክት ነው፡፡ ጎተቷቸው ጌቶቹ “ጳውሎስን እና ሲላስን” ጎተቷቸው ይሁን እንጂ የቡድኑ አባላት የሆኑትን ሉቃስን እና ጢሞቴዎስን ግን አልነኳቸውም፡፡ በባለስልጣናት ፊት "በባለስልጣናት ፊት አቀረቧቸው" ወይም "በባለስልጣናት ይፈረድባቸው ዘንድ" ወደ ባለስልጣናቱ ፊት ባቀረቧቸው ጊዜ እንዲህ አሉ "ጌቶቹ ጳውሎስን እና ሲላስን ካቀረቧቸው በኋላ አለቃው እንዲህ አለ" ያስተምሩ ነበር "ጳውሎስ እና ሲላስ ያስተምሩ ነበር" በሕግ ያልተፈደልን ጌቶች እነርሱ ሮማዊያን እንደመሆናቸው መጠን ይህ ነገር ለእነርሱም አለመፈቀዱን ለማሳየት ተጠቅሞበታል፡፡
ፈራጆቹም ልብሳቸውን ቀደዱ "ፈራጆቹ የጳውሎስን እና የሲላስን ልብስ ቀደዱ" በዱላ ይቀጠቀጡ ዘንድ አዘዘ አማራጭ ትርጉም: "ወታደሮቹን ጳውሎስን እና ሲላስን በዱላ ይቀጠቅጧቸው ዘንድ አዘዙ" አውጥተው ወረወሯቸው "ፈራጆቹ ጳውሎስን እና ሲላስን አሰሯቸው" ወይም "ፈራጆሱ ወታደሮቹን ጳውሎስን እና ሲላስን ያስሯቸው ዘንድ አዘዙ" የወይህኒ ቤት ጠባቂዎቹን ጥንቃቄ ይጠብቋቸው ዘንድ አዘዙ የወህኒ ጠባቂዎች በእስር ወይም ወህኒ ቤት ውስጥ ያሉ ሰዎችን የሚጠብቁ ሰዎች ናቸው፡፡ “የወህኒ ቤት ጠባቂዎች እነዚህ ሰዎች አምልጠው እንዳይወጡ በጥንቃቄ ይጠብቋቸው ዘንድ አዘዙ፡፡ (UDB) አሠሯቸው "አሠሯቸው" ግንድ አንድ ሰው በተገቢው መንገድ እንቅስቃሴ እንዳያደረግ የሚያግድ ቀዳዳዎች የተበጁለት የግንድ ቁራጭ ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ: ይህ በታክ ውስጥ ሁለተኛው የተከናወነው ነገር ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ጳውሎስ እና ሲላስ እንዲሁም የወህኒ ጠባቂው ተካተዋል፡፡ አደመጣቸው በዚህ ክፍል ውስጥ “እነርሱ” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው ወደ እግዚአብሔር በመጸለይ እና ዝማሬን በማቅርብ የሚገኙትን ጳውሎስን እና ሲላስነን ነው፡፡ በዚህም ምክንያት የእስር ቤቱ መሠረት ተናወጠ "ይህም የእስር ቤቱን መሠረት አናወጠ" ሁሉም የታሠሩበት ሠንሠለት ተፈታ "የሁሉም ሠንሠለት ተፈታ"
ራሱን ሊያጠፋ ነበር የእስ ቤቱ ጠባቂ እስረኞች እንዲያመልጡ በማድረጉ ምክንያት የሚደርስበተን ቅጣት ከመቀበል ይልቅ ራሱን ለማጥፋት መረጠ፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ራሱን ለማጥፋት ዝግጁ ነበር፡፡" እኛ ሁላችብ በዚህ አለን በዚህ ክፍል ውስጥ “እኛ” የሚለው ቃል ሁሉም የሚያካትት ነው፡፡ ጳውሎስን፣ ሲላስን እና ሌሎች እሰረኞችን ያካትታል፡፡
በፍጥነት ወደ ውስጥ ሮጦ ገባ "ወደታሠሩበት በፍጥነት ገባ" በጳውሎስ እና በሲላስ ፊት በግንባሩ ተደፋ የወህኒ ጠባቂው በጳውሎስ እና ሲላስ ፊት በግንባሩ በመደፋት ራሱን ዝቅ አደረገ፡፡ ወደውጪ አወጣቸው "ከታሠሩበት ክፍል አወጣቸው"
አጠቃላይ መረጃ: በዚህ ሥፍራ “እነነርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን እና ሲላስን ነው፡፡ በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ የወህኒ ቤት ጠባቂው ጳውሎስን እና ሲላስን ወደ መኖሪያ ቤቱ ይዞዋቸው ሄደ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በእርሱ ቤት ውስጥ፡፡" እርሱ እና የእርሱ ቤተሰቦች ሁሉ ተጠመቁ አማራጭ ትርጉም፡ "ጳውሎስ እና ሲላስ የወህኒ ቤት ጠባቂውን እና የቤተሰቡን አባላት ሁሉ አጠመቋቸው" እርሱ . . . እርሱ . .. እርሱ ይህ ተውላጠ ስም የሚመለክተው የወህኒ ቤት ጠባቂውን ነው፡፡ ሁሉም በማመናቸው ምክንያት "የቤተሰቡ አባላት በሙሉ በማመናቸው ምክንያት"
አጠቃላይ መረጃ: አጠቃላይ መረጃ: ይህ በታሪኩ ውስጥ የመጨረሻው ክፍል ነው፡፡ ታሪኩም የጳውሎስ እና የሲላስ ከእስር ቤት መፈታትን የተመለከተ ነው፡፡ ቀን በሆነ ጊዜ ይህ አዲስ ታሪክ ጅማሬ መሆኑን ይነገርናል፡፡ መልእክት ላኩ "መልዕክት ላኩ" ወይም "ትዕዛዝ አስተላለፈ" እነዚያን ሰዎች ልቀቋቸው "እነዚያን ሰዎች ፍቷቸው" ወይም "እነዚያ ሰዎች እንዲሄዱ ፍቀዱላቸው" ውጡ "ከእስር ቤት ውጡ"
እንዲህም አላቸው "ለዘበኞቹ እንዲህ አላቸው" ገዥዎቹ በብዙዎች ዘንድ ይታወቃሉ "ገዥዎቹ በብዙዎች ዘንድ ይታወቁ ነበር" ደበደቡን እኛን በዚህ ሥፍራ “እኛ” የሚለው ቃለል ጳውሎስን እና ሲላስን ብቻ የሚያካትት ይሆናል፡፡ አይ በጭራሽ በዚህ ሥፍራ ጳውሎስ ለገዥዎቹ ወይም ለከተማይቱ አስተዳዳሪዎች መለስ ሰጠ፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ጳውሎስ ያናገረው ግን የእስር ቤት ኃላፊውን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "በጭራሽ አይሆንም!" ሮማዊያን ይህ የግዛቱ ሕጋዊ ዜግነት ያላቸውን ነው፡፡ ዜጋ መሆን ያለመገረፍ እና በሕግ ፍት በትክክል የመሰማት መብትን ያጎናጽፋል፡፡ የከተማይቱ መሪዎች ጳውሎስን እና ሲላስን እንዴት እንዳገላቷቸው የግዛቱ መሪዎች ይሰማሉ ብለው ፈርተው ነበር፡፡ እንዲመጡ ፍቀዱላቸው "የከተማይቱ መሪዎች ልመጡ ይገባል" ገዥዎቹም መጥተው ለመኗቸው "ገዥዎቹ መጥተው ጳውሎስን እና ሲላስን ለመኗቸው" ባመጧቸው ጊዜ "ገዥዎቹ ጳውሎስን እና ሰሲላስን ባመጧቸው ጊዜ"
አጠቃላይ መረጃ: ይህ ስለጳውሎስ እና ሲላስ መታሠር የመጨረሻ የታሪኩ ክፍል ነው፡፡ (ተመልከት: [[End of Story]]) የሊዲያ ቤት "የሊዲያ መኖሪያ ቤት" አበረታቷቸው "ጳውሎስ እና ሲላስ ወንዶሞችን አበረታቱ" ወይም "ጳውሎስ እና ሲላስ አማኞችን አበረታቱ"
1 አንፊጶልና አጶሎንያ በተባሉ ከተሞች በኩል ካለፉ በኋላም፣ ተሰሎንቄ ወደ ተባለች ከተማ መጡ፤ በዚያም ከተማ የአይሁድ ምኵራብ ነበረ። 2 ጳውሎስም እንደ ልማዱ፣ ወደ አይሁድ ሄዶ፣ ለሦስት ሰንበታት ያህል ከቅዱሳት መጻሕፍት እየጠቀሰ ከእነርሱ ጋር ይነጋገር ነበር። 3 ቅዱሳት መጻሕፍትንም እየገለጠ፣ ክርስቶስ መከራን መቀበልና ከሙታን መነሣት እንደ ነበረበት እያስረዳም፣ «ይህ እኔ የምሰብክላችሁ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ ነው» ይላቸው ነበር። 4 ከአይሁድም አንዳንዶቹ መልእክቱን ተቀብለው ከጳውሎስና ከሲላስ ጋር ተባበሩ፤ በተጨማሪም ለእግዚአብሔር ያደሩ ግሪኮች፣ የከበሩ ብዙ ሴቶችና ከፍተኛ ቍጥር ያላቸው ሰዎች ከእነርሱ ጋር ሆኑ። 5 ሌሎች ያላመኑ አይሁድ ግን፣ በቅንዓት በመነሣሣትና ክፉ ሰዎችን ከጎዳና ላይ በማሰባሰብ ሕዝብን አከማችተው ከተማዋን አወኩአት። የኢያሶንን ቤት በዐመፅ በመክበብም፣ ጳውሎስንና ሲላስን ይዘው ለሕዝቡ ለማስረከብ ፈለጉ። 6 ሊያገኙአቸው ባልቻሉ ጊዜም፣ ኢያሶንንና ሌሎች ወንድሞችን ይዘው መሬት ለመሬት እየጎተቱ ወደ ከተማዋ ባለ ሥልጣናት ፊት አወጡአቸው፤ እንዲህም እያሉ ይጮኹ ነበር፤ «እነዚህ ዓለምን የገለባበጡ ሰዎች ወደዚህ ደግሞ መጥተዋል፤ 7 ኢያሶን በቤቱ የተቀበላቸው እነዚህ ሰዎች የቄሣርን ሕግ የሚቃወሙ ናቸው፤ ኢየሱስ የሚባል ሌላ ንጉሥ አለ እያሉ ነው።» 8 ሕዝቡና የከተማው ሹሞች እነዚህን ነገሮች ሲሰሙ፣ ታወኩ። 9 ከኢያሶንና ከሌሎቹም የዋስትና ገንዘብ ተቀብለው ለቀቁአቸው። 10 ወንድሞች ጳውሎስንና ሲላስን በዚያው ሌሊት ወደ ቤርያ ሰደዱአቸው። እነርሱም እዚያ በደረሱ ጊዜ፣ ወደ አይሁድ ምኵራብ ገቡ። 11 እዚህ የሚኖሩ ሰዎች በተሰሎንቄ ከሚኖሩት ይልቅ ሰፊ አስተሳሰብ ስለ ነበራቸው፣ ነገሩ እንዲህ ይሆንን በማለት ቅዱሳት መጻሕፍትን በየዕለቱ እየመረመሩ፣ ልባቸው ቃሉን ለመቀበል ዝግጁ ነበር። 12 ስለዚህ ከእነርሱ ብዙዎች አመኑ፤ በተጨማሪ አንዳንድ ተደማጭነት ያላቸው የግሪክ ሴቶችና ሌሎች ወንዶችም አመኑ። 13 በተሰሎንቄ የነበሩ አይሁድም ጳውሎስ በቤርያም ደግሞ ቃሉን እንደ ሰበከ ባወቁ ጊዜ፣ ወደዚያ ሄደው ሕዝቡን በማነሣሣት አወኩ። 14 ወንድሞችም ወዲያው ጳውሎስን ወደ ባሕሩ አካባቢ እንዲሄድ አደረጉ ፤ ሲላስና ጢሞቴዎስ ግን እዚያው ቆዩ። 15 ጳውሎስን ይሸኙ የነበሩት ሰዎችም እስከ አቴና ድረስ ወሰዱት። ከዚያም ሲነሡ፣ ሲላስና ጢሞቴዎስ በተቻለው ፍጥነት ወደ እነሱ እንዲመጡ የሚል መልእክት ከጳውሎስ ተቀብለው ሄዱ። 16 ጳውሎስ አቴና ተቀምጦ እየጠበቃቸው ሳለ፣ ከተማዋ በጣዖት የተሞላች መሆንዋን ሲያይ፣ መንፈሱ በውስጡ ተበሳጨበት። 17 ስለዚህም ነገር በምኵራብ ከሚያገኛቸው አይሁድ፣ እግዚዘብሔርንም ከሚያመልኩ ሌሎች ሰዎችና ዘወትር በገበያ ቦታ ከሚያገኛቸው ሰዎች ጋር ይነጋገር ነበር። 18 ከኤፌቆስና ከኢስጦኢኮች ወገን የሆኑ አንዳንድ ፈላስፎችም ደግሞ ጳውሎስን አገኙት። ከእነርሱም አንዳንዶች፣ «ይህ ለፍላፊ ምን እያለ ነው?» አሉ። ሌሎቹም፣ ስለ ኢየሱስና ስለ ትንሣኤው ሲሰብክ ስለ ሰሙት፣ «ስለ እንግዳ አማልክት የሚሰብክ ይመስላል» አሉ። 19 ከዚያም፣ «አንተ የምትናገረውን ይህን ዐዲስ ትምህርት ማወቅ እንችላለን ወይ? 20 ምክንያቱም እየሰማናቸው ያሉ ነገሮች እንግዳ ናቸው። ስለዚህ፣ የእነዚህን ነገሮች ትርጕም ማወቅ እንሻለን» አሉት። 21 አቴናውያንና ሌሎች በዚያ የሚኖሩ እንግዶች ሁሉ ጊዜአቸውን የሚያሳልፉት በሌላ ጉዳይ ሳይሆን፣ ስለ ዐዳዲስ ነገሮች በማውራት ወይም በመስማት ነበር። 22 ስለዚህ ጳውሎስ በአርዮስፋጎስ መካከል ቆሞ እንዲህ አለ፤ «እናንተ የአቴና ሰዎች ሆይ፣ በየትኛውም መልክ እጅግ ሃይማኖተኞች እንደ ሆናችሁ እመለከታለሁ። 23 ምክንያቱም ወዲያ ወዲህ እየተመላለስሁ የምታመልኳቸውን ስመለከት፣ ላልታወቀ አምላክ የሚል ጽሑፍ የተጻፈበት አንድ መሠዊያ አይቻለሁ። እንግዲህ ይህን ሳታውቁ የምታመልኩትን አምላክ እኔ እነግራችኋለሁ። 24 ዓለምንና በውስጧ የሚገኙትን ሁሉ የፈጠረ አምላክ፣ የሰማይና የምድር ጌታ በመሆኑ፣ በእጅ በተሠራ መቅደስ ውስጥ አይኖርም። 25 ለሰዎች ሕይወት፣ እስትንፋስንና ሁሉንም ነገር የሚሰጠው እርሱ ራሱ ስለ ሆነ፣ እግዚአብሔር አንዳች እንደሚያስፈልገው በሰው እጅ አይገለገልም። 26 በምድር ገጽ ላይ የሚኖሩትንም ሕዝቦች ሁሉ ከአንድ ሰው ፈጠረ፤ የሚኖሩባቸውንም ስፍራዎች ወሰን፣ ወቅቶችንም የወሰነላቸው እርሱ ነው። 27 ስለዚህ እግዚአብሔርን ቢፈልጉ ሊያገኙት ይችላሉ፤ እንደ እውነቱ ከሆነ፣ እርሱ ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም። 28 ምክንያቱም የምንኖረው፣ የምንንቀሳቀሰውና በሕይወት የቆምነው በእርሱ ነው፤ ከእናንተ ባለ ቅኔዎች አንዱ እንዳለውም፣ 'እኛ ልጆቹ ነን።' 29 እንግዲህ የእግዚአብሔር ልጆች ከሆንን፣ መለኮትን በሰው ጥበብና እንደ ተቀረጸ ወርቅ ወይም ብር ወይም ድንጋይ አድርገን ማሰብ የለብንም። 30 ስለዚህ እግዚአብሔር የአለማወቅ ጊዜያትን አሳልፎ፣ አሁን ግን በየትኛውም ስፍራ ያሉ ሰዎች ሁሉ ንስሐ እንዲገቡ ያዛል። 31 ምክንያቱም በመረጠው ሰው አማካይነት በዓለም ላይ የሚፈርድበትን ቀን አዘጋጅቶአል። እግዚአብሔር ይህን ሰው ከሙታን በማስነሣቱ ለሁሉ ሰው ማረጋገጫ ሰጥቶአል።" 32 የአቴና ሰዎች ስለ ሙታን ትንሣኤ በሰሙ ጊዜ፣ አንዳንዶቹ በጳውሎስ ላይ አፌዙ፤ሌሎች ግን፣ «ስለዚህ ጉዳይ ዳግመኛ እንሰማሃለን» አሉት። 33 ከዚህ በኋላ፣ ጳውሎስ ተለይቶአቸው ሄደ፤ 34 አንዳንድ ወንዶች ግን ከእርሱ ጋር ተባብረው አመኑ፤ በእነዚህም ውስጥ የአርዮስፋጎስ አመራር አባል ዲዮናስዮስ፣ ደማሪስ የተባለች ሴትና ሌሎችም ይገኛሉ።
አጠቃላይ መረጃ: ለጳውሎስ እና ሲላስ ሲጓዙ የሚያሳየው ታሪክ ሌላኛው ክፍል ነው፡፡ አሁን በተሰሎንቄ ናቸው፡፡ ጢሞቴዎስ እና ሉቃስ ከእነርሱ ጋር የሉም፡፡ በዚያ አለፉ "በዚያ በኩል አልፈው ሄዱ" በአንፊጶልና በአጶሎንያም ከተሞች እነዚህ የመቅዶኒያ አከባቢ የሚገኙ ከተሞች ናቸው፡፡ እንደ ልማዱ ጳውሎስ ብዙ ጊዜ እሁድ እሁድ አይሁዳዊያን ወደሚሰበሰቡበት ወደ ምኩራብ አዘውትሮ ይሄዳል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “እንደ ልማዱ” ወይም “ብዙ ጊዜ እንደሚያደርገው፡፡" ወደ እነርሱም ሄዶ በዚህ ሥፍራ ላይ "እነርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ምኩራብን እና በዚያ የሚሰበሰቡትን አይሁዳዊያንን ነው፡፡ ከእነርሱ ጋር ይከራከር ነበር "በምኩራብ ውስጥ ካሉት አይሁዳዊያን ነገር ይከራከር ነበር" ወይም "በምኩራብ ውስጥ ካሉት አይዳዊያን ጋር ይወያይ ነበር"
ቅዱሳት መጻሕፍትን ከፍቶ አማራጭ ትርጉሞች 1) "ሰዎች እርሱ የሚያስተምረውን ትምህርት መረዳት ይችሉ ዘንድ ጳውሎስ በግልጽ ቅዱሳት መጽሐፍትን ያብራራላቸው ነበር" ወይም 2) "ጳውሎስ ቅዱሳት መጻሕፍት ወይም ጥቅል መጻሕፍትን ከፍት ነበር፡፡" እንዲህ መሆን ይባዋልና "ይህ የዕቅዱስ አካል ነው" ወይም "በዚህ መልኩ ሊሆን ይገባዋል" እንገና ተነሣ "እንደገና ሕያው ሆነ" አይሁዳዊያን የእርሱ ንግግር አሳመናቸው "አይሁዳዊያንን አመኑ" ወይም "አይሁዳዊያን አመኑ" ጳውሎስም ከእነርሱ ጋር ተቀላቀለ "ጳውሎስም ከእነርሱ ጋር ሕብረት ማድረግ ጀመረ" የተሰጡት ግሪኮች ምንም እንኳ በመገረዝ አይሁዳዊያን ሳይሆኑ እንዲሁ እግዚአብሔርን ያመልኩ የነበሩት አይሁዶች ታላቅ ሕዝብ "ትልቅ ሕዝብ"
ተነድቶ
"በ . . . ተነድቶ"
የሆኑ መጥፎ ሰዎች
በዚህ ስፍራ ላይ”ሰዎች” ተብለው የተጠቀሱት ወንዶችን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "መጥፎ ወንዶች፡፡"
ከገቢያ ቦታ
ይህ የተለያዩ ቢዝነሶች፣ የተለያዩ ነገሮች እንስሳት ግዥ እና ሽያጭ ወይም የተለያዩ ግልጋሎቶች የሚሰጡበት ሥፍራ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በመስቀል አደባባይ" (UDB).
ከተማይቱን
"ከተማይቱ . . . እንዲትሆን አደረገ"
ቤቶችን እያወከ
"መኖሪያ ቤቶችን በኃይል እያጠቃ"
ሊያመጡት ፈለጉ
ይህ ተውላጠ ስም የማያምኑ ሰዎችን እና በገቢያ ሥፍራ ያሉትን ክፉ ሰዎችን ይወክላል፡፡
ወደ ሰዎች ዘንድ አመጡት
"ወደ መንግስት ወይም በማህረሰቡ ላይ ስለተፈጠረው ተጽእኖ ውሳኔ ለመስጠጥ የተሰበሰቡት ሕጋዊ ዜግነት ያላቸው ሕጋዊ ወደሆኑት ቡድኖች"
በባለስልጣናቱ ፊት
"ባለስልጣናቱ ባሉበት"
እንዲህ ያደረጉት እነዚህ ሰዎች
የአይሁድ መሪዎች ስናገሩ “እነዚህ ሰዎች” በማለት የተናገሩት ስለ ጳውሎስ እና ሲላስ ነው፡፡
ዓለም ሁሉ ገለባብጠዋል
ይህ ሀረግ በሌላ አገላለጽ ጳውሎስ እና ሲላስ ከፍተኛ ኹከት አስነስተዋል ማለት ነው፡፡ የአይሁድ መሪዎች የጳውሎስን እና የሲላስን በትምህርታቸው ያላቸው የተጽእኖ አድማስ አጋነዋል፡፡ አማራጭ ትርጉሞች፡ “ከፍተኛ ኹከት አስነስተዋል፡፡”
ኢያሶንን ተቀበሉት
ይህ ኢያሶን ከጳውሎስ ኹከት ፈጣር መልዕክት ጋር የሚስማማ ሰው መሆኑን የሚያሳይ ሀረግ ነው፡፡
በጣም ተጨንቀው ነበር "ፈርተዋል" ወይም "አእምሮዋቸው ተጨንቋል" የገንዘብ ዋስ ጠርተው ይህ ገንዘብ መልካም ባሕርን እንዲሚያሳዩ ቃል መግባትን የሚሳይ ገንዘብ ነው፡፡ ሁሉ ነገር በተገቢው መንገድ ከሄደ ተመላሽ የሚደረግ ሲሆን ወይም መጥፎ ባሕርይ ቢከሰት ግን የጠፋውን ንብረት ለመተካት የሚውል ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ዋስትና የሚሆን ነገር አስዘው” (UDB)፡፡ ሌሎቹም "ከኢያሶን ውጪ ያሉት አማኞች" እንዲሄዱ ፈቀዱላቸው "ባለስልጣናቱ ኢያሶንን እና ሌሎች ያሠሯቸውን አማኞችን ለቀቁ"
አጠቃላይ መረጃ: ይህ ስለጳውሎስ እና ሲላስ ታሪክ ጉዞ ሌላኛው የታሪኩ ክፍል ነው፡፡ አሁን ያሉት በቡሪያ ነው፡፡ ወንድሞች በዚህ ሥፍራ “ወንድሞች” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ወንዶች እና ሴቶች አማኞች ነው፡፡ የተማሩት “ለማድመጥ ፈቃደኞች” የሆኑት በባለስልጣን እና ሀብታም ቤተሰቦች ውስጥ ለተወለዱት ሰዎች አዳዲስ ሀሳቦችን ማድመጥ ይኽንን ያህን የሚያስፈራ ነገር አልነበረውም፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ልባቸው የተከፈተ” ወይም “ለመስማት ይበልጥ ፈቃደኞች የሆኑ፡፡" ቃሉት ተቀበሉ "ትምህርቱን አደመጡ" በሙሉ የአእምሮ ዝግጁነት እነዚህ የቤሪያ ሰዎች ጳውሎስ ከቅዱሳት መጽሐፍት እየወሰደ የሚያስተምረውን ትምህርት ለመመር የተዘጋጁ ነበሩ፡፡ ቅዱሳት መጽሐፍትንም በየቀኑ ይመረምሩ ነበር "በጥንቃቄ በማንበብ ጠቃሚ የሆኑትን የቅዱሳት መጻሕፍት ክፍሎች በጥንቃቄ በየዕለቱ ይመረምሩ ነበር"
የተማሩትን "የተነገራቸውን" ወይም "ያወቁትን" ወይም "የሰሙትን" (UDB) ወደዚያ ሄደው ኹከት አስነሱ "ወደዚያ በመሄድ በጠበጡ" ወይም "ወደዚ በመሄድ አወኳቸው" ሕዝቡን አወኩት "በሰዎች መካከል ፍርሃትን ለቀቁ" ወንድሞች በዚህ ሥፍራ ላይ “ወንድሞች” የሚለው ቃል አማኝ ወንድሞችና እህቶችን የሚያመለክት ነው፡፡ ጳውሎስን ይመራ የነበረው "ከጳውሎስ ጋር አብሮ ይጓዝ የነበረው" ወይም "ከጳውሎስ ጋር አብሮ ይሄድ የነበረው"
አጠቃላይ መረጃ: ይህ ስለጳውሎስ እና ሲላስ ጉዞ ታሪክ ሌላኛው ክፍል ነው፡፡ ጳውሎስ አሁን የሚገኘው በአቴንስ ነው፡፡ በዚህም ሆኖ ሲላስና ጢሞቴዎስ ወደ እርሱ ዘንድ እንዲመጡ ይጠብቃል፡፡ መንፈሱ ታወከ "ተጨነቀ" ወይም "በጣም ታወከ" ወይም "በጣም ተጨነቀ" (UDB) ተከራከረ ይህ ግሥ ከሰባኪው አንጻር ሳይሆን ከአድማጮቹ ዘንድ ብዙ ክርክር እንደነበረ ያሳያል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ተከራከረ" ወይም "ተወያየ፡፡" በገቢያ ሥፍራ ይህ የተለያዩ ቢዝነሶች፣ የተለያዩ ነገሮች እንስሳት ግዥ እና ሽያጭ ወይም የተለያዩ ግልጋሎቶች የሚሰጡበት ሥፍራ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በመስቀል አደባባይ" (UDB).
ኤፊቆሮስ . . . ፈላስፎች እነዚህ ሰዎች ሁሉ ነገር በእድል የሆነ ነው በማለት ያምናሉ፡፡ አማልክት ራሳቸውን በማስደስት የተጠመዱ በመሆናቸው ምድርን ለማስተዳደር ግድ አይላቸውም፡፡ ትንሳኤ አካልን አይቀበሉም፡፡ እስቶይክ ፈላስፋዎች እነዚህ ሰዎች ነጻነት የሚገኘው ራሰን ከእድል በማላቀቅ ነው ብለው ያምናሉ፡፡ ሰዎችን የሚወድን አምላክ አይቀበሉም እንዲሁም በትንሳኤ ሙታን አያምኑም፡፡ ተሟገቱት "ከጳውሎስ ጋር ተከራከሩ" አንዳንዶቹም እንዲህ አሉ "አንዳዶቹ ፈላስፎች አንዲህ አሉ" ይህ ለፍላፊ ከዬት ነው የመጣው "ለፍላፊ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጥራጥሬ የሚለቃቅም ወፍን ነው፡፡ ይህ ቃል አሉታዊ በሆነ መልኩ ሀሜት የሚያወራን ሰው ለማመልከት ይውላል፡፡ ፈላስፎቹ ስለጳውሎስ ስናገሩ ለመስማት እንኳ ይህንን ያኸል ግድ የሚያሰኝ መረጃ የለውም ብለው ተናግረዋል፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ እንዲህ ብለዋል "ሌሎች ፈላስፎች እንዲህ ብለዋል" ሰባኪ ይመስላ "አዋጅ የሚነግር ሰው ይመስላል" ወይም "መልዕክቱን ለማሰራጨት የተላከ ሰው ይመስላል" ስለእንግዳ አማልክት ይናገራል ይህ “የማይገባ ማለት ሳይሆን” “አዲስ” ማለትም የግሪክ እና የሮማዊያን አማልክት ውጪ የሆነ አምላክ ማለት ነው፡፡ .
ጳውሎስን ወስደው "ኤፊቆሮስ እና የስቶይክ ፈላስፎች ጳውሎን ወስደው" ወደ አርዮስፋጎስ በአቴንስ ከተማ ውስጥ የሚገኝ ተራራማ ስፍራ ሲሆን የአቴን ከፍተኛው ፍድ ቤት ይገኝ የነበረው በዚያ ነበር እነዚህ ነገሮች ምን እንደሆነ ልናውቅ እንወዳለን አሉት በዚህ ሥፍራ "እኛ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ፈላስፎቹን ብቻ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እየተናገርካቸው ያሉትን ነገሮች ሰምተን የራሳችንን ቢያኔ ልንወስድ እንወዳለን፡፡" የአቴና ሰዎች ሁሉ ሆይ "የአቴና" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ከቴና ከተማ የመጡ ሰዎችን ነው፡፡ ይህች ከተማ ከመቂዶኒያ (ከአሁኗ ግሪክ) አቅራባ ያለች ከተማ ናት፡፡ እንዲሁም እንግዶች የሆናችሁ እንግዶች" ወይም “ለአቴና ማህበረሰብ አዲስ የሆኑትንም” ጊዜያቸውን ያሳለፉ "ጊዜያቸውን ይቀጠሙ " ወይም "ከእርሱ ጋር አሳለፉ" አዲስ ነገርን በመናገር ወይም በማድመጥ "አዳዲስ የፍልስፍና ሀሳቦችን" ወይም "ለእነርሱ አዲስ የሆነውን ነገር በመናገር" (UDB)
አጠቃላይ መረጃ: ጳውሎስ በአርዮስፋጎስ ለነበሩት ፈላስፎች ንግግሩን እንዲህ በማለት ነው የጀመረው፡፡ በሁሉም ነገር ሃይማኖተኞች ናችሁ ጳውሎስ ኤናዊያን በአደባባይ አማልክቶቻቸውን በጸሎት፣ መሰዊያዎችን በመሥራት እና መስዋእትን በመሰዋት እንደሚያከብሩ በመናገር፡፡ ስዘዋወር "ምክንያቱም ከቦታ ቦታ ስዘዋወር" ለማይታወቅ አምላክ አማራጭ ትርጉሞች 1) "የሆነ የማይታወቅ አምላክ" ወይም 2) "ለማያውቁት ማንኛውም አምላክ፡፡"
ዓለም በአጠቃላይ ትርጉሙ “ዓለም” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሰማይን እና ምድርን እንዲሁም በውጡ ያሉትን ነገሮች ሁሉ ነው፡፡ እርሱ ጌታ በመሆኑ ምክንያት በዚህ ሥፍራ ላይ "እርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስ እያብራራ ያለውን የማይታወቅ አምላክን ሲሆን ይህንን ጳውሎ ጌታ እግዚአብሔርን ነው ይላቸዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እርሱ ጌታ ስለሆነ፡፡" በእጆች የተሠራ "በሰዎች ጥረት የተሠራ" የሚገለገለው በዚህ ሥፍራ ላይ "የሚገለገለው" የሚለው ቃል የሚያመለክተው አንድ ዶክተር በሽተኛው ጤናማ እንዲሆን የሚያደርገውን ነገር ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ይጠነቀቅለታል፡፡" በሰዎች እጅ "በሰው ልጆች እጅ" ምክንያቱም እርሱ ራሱ "ምክንያቱም እርሱ ራሱ"
አንድ ሰው አማራጭ ትርጉሞች 1) "አንድ ሰው የሚለው የሚያመለክተው እግዚአብሔር የፈጠረውን አዳምን ነው" ወይም 2) "እግዚአብሔር የፈጠራቸቸውን አዳምን እና ሔዋንን ልያካትት ይችላል፡፡" እርሱ ሁሉንም ነገዶች ፈጥሯል "እግዚአብሔር ሁሉንም ነገዶች ፈጥሯል" እነርሱ . . . እነርሱ ይህ ተውላጠ ስም በምድር ላይ የሚኖሩ ነገዶችን ሁሉ የሚያመለክት ነው፡፡ ስለዚህ ይህ ቃል ከዚህ በፊት የተነገረብ አንዲ ዓረፍተ ነገር የሚያመለክት ሲሆን ከዚህ በፊት ከተነገረው ዓረፈተ ነገር የተነሣ፡፡ እግዚአብሔርን ይፈልጉታል "እግዚአብሔርን ይፈልጉታል" ወደ እርሱ ለመድረስ ይፈልጋሉ "እርሱን ለማግኘት ከፍተኛ ፍላጎት አላቸው" እርሱም ከእርሱ የራቀ አይደለም ጳውሎስ ያነሰውን ነጥብ ለማጎላት ሲል ማለት ከሚፈልገው ነገር ታቃራኒ የሆነ ነገር ተናግሯል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እርሱ ለእነርሱ በጣም ቅርብ ነው፡፡" ከእያንዳዳችን በዚህ ሥፍራ ላይ ጳውሎስ ራሱን፣ አድማጮቹን እና ሁሉንም ነገዶች በዚህ “እኛ” በሚለው ቃል ውስጥ አካቷል፡፡
ምክንያቱም በእርሱ "ምክንያቱም በእግዚአብሔር" እንኖራለን እንቀሳቀስማለን በዚህ ሥፍራ ላይ ጳውሎ አድማጮቹን ከራሱ ጋር ቀላቅሎ ይናገራል፡፡ እኛም የእርሱ ልጆች ነን በዚህ ሥፍራ ላይ “ልጆች” የሚለው ቃል የቅርብ ልጆች የሆኑትን የሚያመለክት አይደለም፡፡ ከቅድመ አያቶቻቸው ጋር የሚያመሳስላቸው ነገር አለ ማለት ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ “የእርሱ” የሚለው ቃል ማንን እንደሚያመለክት ግልጽ አይደለም፡፡ መለኮትነቱ በዚህ ሥፍራ ላይ “መለኮት” የሚለው ቃል የእግዚእሔር ባሕርይ የሚያመለክት ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ACT 17:22 ላይ የጀመረውን በአርዮስፋጎስ ለነበሩት ፈላስፎች ያደረገውን ንግግር ያጠናቅቃል፡፡ ስለዚህም ይህ ቃል ከዚህ በፊት በተነገረው ቃል ምክንያት የሚሆን ነገር የሚያሳይ ነው፡፡ ያለማወቅ አማራጭ ትርጉሞች 1) "ስለ አንድ ነገር እንዲሁ አለማወቅ" ወይም 2) "ሆን ብሎ አለመቀብል፡፡" ዓለም በዚህ ሥፍራ ላይ “ዓለም” የሚለው ቃል በዓለም ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን ያመለክታል፡፡ በሰው አማካኝነት መረጦአል "በሰው አማካኝነት እግዚአብሔር መርጦዋአል" እግዚአብሔር በዚህ ሰው አማካኝነት አረጋግጧል "እግዚአብሔር ይህንን ሰው እንደመረጠው አሳይቷል"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ይህ ጳውሎስ በአቴና ስለነበረው ቆይታ የሚተሪከው ክፍል ማብቂያ ነው፡፡ (ተመልከት: [[End of Story]]) የአቴና ሰዎች በአርዮስፋጎስ የነበሩትን እና ጳውሎስን እስከ አሁን ስሰሙት የቆዩት ሰዎች አንዳዶቹ ቀለዱበትl እነዚህ ሰዎች ሰው ከሞተ በኋላ ተመልሶ ወደ ሕይወት ይመጣል የሚለውን የማያምኑት ናቸው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “አንዳንዶቹ በጳውሎስ ላይ ተሳለቁበት” ወይም “አንዳንዶቹ በጳውሎስ ላይ ሳቁበት፡፡” እንሰማሃለን በዚህ ክፍል ውስጥ "እኛ" የሚለው ቃል ጳውሎስ የሚናገረውን ነገር ለመስማት ፍላጎት ያላቸውን የአቴና ሰዎችን ያመለክታል፡፡ እነዚህ ሰዎች በቀጥታ ለጳውሎስ ይናገሩት ነበር፡፡ ነገር ግን ጳውሎስን የእነርሱ ቡድን አድርገው አልተቀበሉትም ነበር፡፡ በአርዮስፋጎስ ያለው የፍርድ ቤት ፈራጅ ዲዮናስዮስ ደማሪስ የሚሉአትም አንዲት ሴት ዲያናስዮስ የአንድ ወንድ ስም ነው፡፡ Dionysius is a man's name. አርዮፓጌት የሚለው ቃል የሚያሳየው ዲዮናስዮስ በአርዮፋጎስ ፈራጅ የሆነውን ሰው ነው፡፡
1 ከዚህ በኋላ፣ ጳውሎስ ከአቴና ወደ ቆሮንቶስ ሄደ። 2 እዚያም ከጳንጦስ ወገን የሆነ አቂላ የሚባል አይሁዳዊ አገኘ። እርሱም አይሁድ ሁሉ ከሮም እንዲወጡ ቀላውዴዎብ ባዘዘው መሠረት፣ ከሚስቱ ከጵርቅላ ጋር በቅርብ ከኢጣሊያ የመጣ ሰው ነበር። ጳውሎስም ከእነርሱ ጋር ተቀራረበ። 3 ሥራቸው አንድ ዓይነት ስለ ሆነም፣ በእነርሱ ዘንድ እየኖረ ዐብሮአቸው ይሠራ ነበር። ሥራቸውም ድንኳን መስፋት ነበር። 4 በየሰንበቱም በምኵራብ ውስጥ በመገኘት እየተከራከረ፣ አይሁድንም ግሪኮችንም ያሳምን ነበር። 5 ሲላስና ጢሞቴዎስ ከመቄዶንያ እርሱ ወዳለበት በወረዱ ጊዜ ግን፣ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ እንደ ሆነ ለአይሁድ እንዲመሰክር መንፈስ ቅዱስ ጳውሎስን ገፋፋው። 6 አይሁድ በተቃወሙትና በተሳደቡ ጊዜ፣ ጳውሎስ ልብሱን እያራገፈባቸው፣ «ደማችሁ በራሳችሁ ላይ ይሁን፤ እኔ ንጹሕ ነኝ፤ ከአሁን ጀምሮ ወደ አሕዛብ እሄዳለሁ» አላቸው። 7 ከዚያም ወጥቶ ቲቶ ኢዮስጦስ ወደሚባል፣ እግዚአብሔርን ወደሚያመልክ ሰው ቤት ሄደ። ቤቱም በምኵራብ አጠገብ ነበር። 8 ቀርስጶስ የተባለም የምኵራብ አለቃ ከቤተ ሰዎቹ ሁሉ ጋር በጌታ አመነ። ጳውሎስ ሲናገር ከሰሙት ከቆሮንቶስ ሰዎች መካከልም ብዙዎቹ አምነው ተጠመቁ። 9 ጌታም ሌሊት በራእይ ጳውሎስን እንዲህ አለው፤ "አትፍራ ተናገር፣ ዝምም አትበል። 10 ምክንያቱም እኔ ከአንተ ጋር አለሁ፤ ሊጎዳህ የሚነሣብህ ማንም የለም፤ እንዲያውም በዚህ ከተማ ብዙ ሰዎች አሉኝ።" 11 ጳውሎስም በመካከላቸው የእግዚአብሔርን ቃል እያስተማረ አንድ ዓመት ከስድስት ወር እዚያ ተቀመጠ። 12 ነገር ግን ጋልዮስ የአካይያ አገረ ገዢ በሆነ ጊዜ፣ አይሁድ በጳውሎስ ላይ በአንድነት ተነሡ፤ ይዘውም ፍርድ ፊት አቀረቡት። 13 ከዚያም፣ “ሕዝቡ እግዚአብሔርን እንዲያመልክ ይህ ሰው ከሕግ ውጪ እየቀሰቀሰ ነው” አሉ። 14 ጳውሎስ ሊናገር ሲልም፣ ጋልዮስ አይሁድን፣ “አይሁድ ሆይ፣ ጉዳዩ በርግጥ የበደል ወይም የወንጀል ቢሆን ኖሮ፣ ልታገሣችሁ በተገባኝ ነበር። 15 ነገር ግን ክርክሩ ስለ ቃላትና ስለ ስሞች፣ ደግሞም ስለ ገዛ ሕጋችሁ ስለ ሆነ፣ እናንተው ራሳችሁ ተነጋገሩበት። እኔ ስለ እንደዚህ ዐይነት ጉዳይ ፈራጅ መሆን አልፈልግም” አለ። 16 ከዚያም ጋልዮስም ከችሎቱ አስወጣቸው። 17 እነርሱ ሁሉ ግን የምኵራቡን አለቃ ሶስቴንስን በጉልበት ይዘው በፍርድ ወንበሩ ፊት ደበደቡት። ይሁን እንጂ፣ ይህ ድርጊታቸው ለጋልዮስ ደንታም አልሰጠውም። 18 ጳውሎስም ብዙ ቀናት ከተቀመጠ በኋላ፣ ወንድሞችን ተሰናብቶ ከጵርስቅላና ከአቂላ ጋር በመርከብ ወደ ሶርያ ሄደ። ስእለት ስለ ነበረበትም፣ ከወደቡ ከክንክራኦስ ከመነሣቱ በፊት ራሱን ተላጨ። 19 ኤፌሶን በደረሱ ጊዜ፣ ጳውሎስ ጵርስቅላንና አቂላን ትቶአቸው ወደ ምኵራብ ሄዶ ከአይሁድ ጋር ይነጋገር ነበር። 20 እነርሱም ረዘም ላለ ጊዜ ዐብሮአቸው እንዲቆይ ሲለምኑት፣ ጳውሎስ እንቢ አለ። 21 ከዚያም፣ “እግዚአብሔር ቢፈቅድ እንደ ገና ተመልሼ እመጣለሁ” ብሎ ተሰናበታቸው። ከኤፌሶንም ተነሥቶ በመርከብ ሄደ። 22 ጳውሎስ ቂሣርያ በደረሰ ጊዜ፣ በኢየሩሳሌም ወደ ነበረችው ቤተ ክርስቲያን ወጥቶ ሰላምታ አቀረበላቸውና ወደ አንጾኪያ ወረደ። 23 በዚያም ጥቂት ጊዜ ከተቀመጠ በኋላ፣ ጳውሎስ ተለያቸው፤ በገላትያና በፍርግያ አካባቢ በማለፍም ደቀ መዛሙርቱን ሁሉ አበረታታ። 24 ትውልዱ እስክንድርያዊ የሆነ፣ አጵሎስ የሚባል አንድ አይሁዳዊ ወደ ኤፌሶን መጣ፤ እርሱም የንግግር ችሎታና በቂ የቅዱሳት መጻሕፍት ዕውቀት ያለው ሰው ነበር። 25 አጵሎስ የጌታን ትምህርት በሚገባ የተማረ በመሆኑ፣ በመንፈሱ ተነቃቅቶ ስለ ኢየሱስ በትክክል ይናገርና ያስተምር ነበር፤ የሚያውቀው ግን ስለ ዮሐንስ ጥምቀት ብቻ ነበር። 26 አጵሎስ ምኵራብ ውስጥ በድፍረት መናገር ጀመረ። ነገር ግን ጵርስቅላና አቂላ በሰሙት ጊዜ፣ ወደ እርሱ ቀርበው የእግዚአብሔር መንገድ ይበልጥ በትክክል አብራሩለት። 27 እርሱም ወደ አካይያ ማለፍ በፈለገ ጊዜ፣ ወንድሞች አበረታቱት፤ በአካይያ የነበሩ ደቀ መዛሙርት እንዲቀበሉትም ጻፉላቸው። እዚያ በደረሰ ጊዜም፣ በጸጋ ያመኑትን እጅግ ረዳቸው። 28 አጵሎስ ከቅዱሳት መጻሕፍት እያስደገፈ፣ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ እንደ ሆነ በማሳየት በኀይሉና በችሎታው አይሁድን ተከራክሮ ረታቸው።
አጠቃላይ መረጃ ይህ ከጳውሎስ የጉዞ ታሪኮች መካከል አንዱ ነው ፤በዚህ ጊዜ ጳውሎስ በቆሮንጦስ ከተማ ነው ያለው፡፡በዚህ ታሪክ ውስጥ አቂላ እና ጵርስቅላ የተካተቱ ሲሆን ቁጥር 2 እና 3 ላይ ስለ እነርሱ የጀርባ ታሪክ መረጃ ተካቷል፡፡ ከዚህ በኋላ በአቴና ከተከናወነው ድርጊት (ሁኔታ ) በኋላ በዚያ አገኘው ትርጉም ሊሆኑ የሚችሉ አማራጮች:-1)በዚያ ጳውሎስ በድንገት አገኘው 2)በዚያ ጳውሎስ ሆነ ብሎ ፈልጎ አገኘው የጳንጦስ ተወላጅ ጳንጦስ በጥቁር ባህር ደቡባዊ ዳርቻ የምትገኝ አውራጃ ናት በቅርብ ጊዜ የመጣ ይህ ምን አልባት ባለፈው አመት ውስጥ ሊሆን ይችላል ቀላውዲዮስ አዘዘ ቀላውዲዮስ የሮም ንጉሰ ነገስት ነበር አይሁድን ሁሉ አዘዘ ትዕዛዝ ሰጠ ወይም መመሪያ አስተላለፈ፡፡
አጠቃላይ መረጃ ሲላስና ጢሞቲዎስ ከጳውሎስ ጋር እንደገና ተገናኙ ጳውሎስ አስረዳ (መሰከረ) በዚህ ቦታ አስረዳ (መሰከረ) የሚለው ቃል ጳውሎስ ሁለት አይነት ንግግሮችን እንዳዳረገ ያሳያል:: አማራጭ ትርጉም ጳውሎስ ተከራከረ ወይም ጳውሎስ ተወያየ አሳመነ አማራጭ ትርጉም፡- ለማሳመን ጥረት አደረገ በመንፈስ ተገደደ አማራጭ ትርጉም፡- መንፈስ ግድ አለው፡፡ ልብሱን አራገፈ ይህ ድርጊት ጳውሎስ ከማያምኑ አይሁዳዊያን ጋር ያለውን ግንኙነት ያቋረጠበትን እና እነርሱን ለ እግዚያብሄር ፍርድ የተወበትን ሁኔታ የሚያሳይ ድርጊት ነው፡፡ ደማችሁ በራሳችሁ ላይ ይሁን በዚህ ቦታ ደም የሚለው በሃጢት ምክንያት ከሚመጣ ቅጣት ጋር ይነፃፀራል፡፡ ጳውሎስ አይሁዳዊያንን ንስሃ ካልገቡ በግትርነታቸው ምክንያት ለሚመጣባቸው የእግዚአብሄር ፍርድ ሃላፊነቱ የራሳቸው እንደሆነ ነገራቸው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- በሀጢያታችሁ ምክንያት የሚመጣውን ቅጣት የምትቀበሉት እናንተ ናችሁ፡፤
ከዚያም ሄደ ከዚያም ጳውሎስ ሄደ
ቲቶስ ኢዩስጦስ- - - ቀርስጦስ አይሁዳዊያን አማኞች የምኩራቡ አለቃ ይህ ሰው ምንም ያልተማረ ሲሆን ስራው የምኩራቡን ወጪዎች መሸፈንና ምኩራቡን ማስተዳደር እንጂ የግድ አስተማሪ አይደለም፡፡ ቤተሰቡ ሁሉ ዘመድ አዝማዱን ጨምሮ ከእርሱ ጋር የሚኖሩ ሁሉ ብዙ የቆሮንጦስ ሰዎች አይሁዳዊ ያልነበሩ የቆሮንጦስ ሰዎች
አትፍራ ተናገር ዝምም አትበል ጌታ ቃሎቹ የበለጠ ሀይል ያላቸው እንዲሆኑ አንድን ትዕዛዝ በተለያየ መንገድ ተናገር ዝምም አትበል ጌታ ጳውሎስን እንዲናገር በሃይል እያዘዘው ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- መናገር አለብህ፡፡ ዝም አትበል ስለ ወንጌል መናገር እንዳታቆም እኔ ነኝ እኔ የሚለው የሚወክለው (የሚያሳየው) ለጳውሎስ እየተናገረው ያለውን ጌታን ነው ከአንተ ጋር አንተ የሚለው የሚወክለው ጌታ በራዕይ እየተናገረው ያለውን ጳውሎስን ነው በዚህ ከተማ ብዙ ሰዎች አሉኝ በዚህ ከተማ እምነታቸውን በእኔ ላይ ያደረጉ ብዙ ሰዎች አሉኝ ጳውሎስ በዚያ ኖረ- - - የእግዚያብሄርን ቃ በመካከላቸው እያስተማረ (ተመልከት: [[End of Story]])
አጠቃላይ መረጃ ይህ በታሪኩ ውስጥ አዲስ ድርጊት ነው ፤ ጳውሎስን በጋልዮስ የፍርድ ወንበር ፊት አቀረቡት ጋልዩስ የአካይያ ገዥ ነበር አካይያ ቆሮንጦስን የምታካትት የሮምያውያን አውራጃ ስትሆን የአሁኑ ጊዜ ደቡባዊ ግሪክ ናት፡፡ በፍርድ ወንበር ፊት አቀረቡት አይሁዳዊያን ጳውሎስን በሃይል(ሃይልተጠቅመው) ፍርድ ቤት አቀረቡት፡፡አማራጭ ትርጉም፡- በአገረ ገዥው እንዲፈረድበት ወሰዱት ህጉ በማይፈቅደው መንገድ አይሁዳዊያን ሆነ ብለው የሚከሱት ያደረገው ነገር (የተናገረው ነገር) ከህጋቸው እና ከልምዳቸው የተፃረረ በመሆኑ ከሮም ህግ አንፃር ወንጀል ነው ብለው ነው፡፡
ጋልዮስ እንዲህ አለ ጋልዮስ በአውራጃው ላይ የተሾመ የሮም ገዢ ነው ህጋችሁ( የእናንተ ህግ) እነዚህ የሙሴን ህግና በጳውሎስ ዘመን የነበሩ የአይሁዳዊያን ልማዶችን ያካትታሉ እኔ በእንዲህ አይነት ነገር ፈራጅ መሆን አልሻም እኔ እንዲህ ባሉ ጉዳዩች ላይ መፍረድ አልፈልግም፡፡
ሁሉም ያዙት ይህ የግነት አገላለፅ የሕዝቡን ሃይለኛ ስሜት ለመግለፅ የገባ ነው፡፡አማራጭ ትርጉም:- ብዙ ሰዎች በጉጉት ያዙት ወይም አብዛኞቹ ያዙት፡፡ ሶስቴን የምኩራብ አለቃ ሶስቴን በቆሮንጦስ ያለው የአይሁድ ምኩራብ አለቃ ነበረ፡፡ መቱት (ደበደቡት) ሶስቴን አካላዊ ድብደባ ደርሶበታል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- መቱት ወይም በቡጢ መቱት፡፡
አጠቃላይ መረጃ ጳውሎስ ከጵርስቅላና አቂላ ጋር ቆሮንጦስን ለቆ በመውጠት ጉዞውን ቀጠለ ወንድሞች ወንድሞች የሚለው ቃል አማኝ የሆኑ ሴቶችን እና ወንዶችን የሚገልፅ ነው ከጵርስቅላ እና አቂላ ጋር ወደ ሶሪያ በመርከብ ሄዱ ጳውሎስ በመርከብ ወደ ሶሪያ ሄደ፡፡ጵርስቅላ እና አቂላም ከእርሱ ጋር ነበሩ ክንክራኦስ የባህር ወደብ ክንክራኦስ የታላቋ ቆሮንጦስ ከተማ አካል የሆነች የባህር ወደብ ናት፡፡ ስዕለት ይህ በሙሴ ህግ ላይ የተገለፀ እና ለእግዚያብሄር አንድ ነገር ለማድረግ ቃል መግባትን ወይም መሃላን የሚያሳይ ነው፡፡ይህም ከሌዊ ነገድ ውጪ የሆኑ ሰዎች እግዚያብሄርን እንዲያገለግሉ መንገድ ይከፍታል፡፡ ወደ ኤፌሶን ሲደርሱ ጳውሎስ፣ጵርስቅላ እና አቂላ ኤፌሶን ሲደርሱ፡፡ አስረዳ ተወያየ ወይም ተከራከረ
ጠየቁት አይሁዳዊያን ጠየቁት ሲለያቸው ሲሰናበታቸው
ቂሳሪያ በደረሰ ጊዜ ቂሳሪያ ደረሰ ወጥቶ ሄደ (ወደ ላይ ሄደ) ጳውሎስ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ ተጓዘ በኢየሩሳሌም ለምትገኘው ቤተክርስቲያን ሰላምታ አቀረበ በኢየሩሳሌም ባለችው ቤተክርስቲያን ላሉ ምዕመናን ሰላምታ አቀረበ ወደታች ወረደ አይሁዳዊያን ወደ እየሩሳሌም መሄድን ወደ ላይ እንደመሄድ ሲቆጥሩት ከእየሩሳሌም መራቅን ወደታች እንደመሄድ (እንደመውረድ) ይቆጥሩታል፡፡ ጳውሎስ ተለያቸው ጳውሎስ ወደ ሌላ ቦታ ሄደ ገላቲያ እና ፍርጊያ በእሲያ የሚገኙ አውራጃዎች የነበሩ ሲሆን በአሁኔ ጊዜ ቱርክ የምትባለው አገር ናት፡፡
የሐዋርያት ሥራ 15፡27-29 አጠቃላይ መረጃ አጵሎስ በታሪኩ ውስጥ የተካተተ ሲሆን ቁጥር 24 እና 25 ላይ ስለ እርሱ የጀርባ ታሪክ የእስክንድሪያ ተወላጅ የሆነ አማራጭ ከተሞች 1, በሰሜናዊ ዳርቻ በግብጽ የምትገኘው እስክንድርያ 2, በምዕራብ ዳርቻ በእሲያ የምትገኘው እስክንድሪያ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- በእስክንድሪያ ከተማ የተወለደ ሰው ነው፡፡ አንደበተ ርዕቱ ጎበዝ ተናጋሪ በመንፈስ የተቃጠለ በሙሉ ልቡ የሚቀናና የሚያስተምር ነበር የዮሐንስ ጥምቀት መጥምቁ ዮሐንስ የሚያጠምቀው ጥምቀት ይበልጥ በተስተካከለ ሁኔታ በተሟላ ሁኔታ
በፈለገ ጊዜ አጵሎስ በፈለገ ጊዜ አካይያ በደረሰ ጊዜ አካይያ የሮሜ አውራጃ ስትሆን በአሁኑ ጊዜ የደቡባዊ ግሪክ ክልል ናት፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- ወደ አካይያ ክልል በሄደ ጊዜ ወንድሞች እዚህ ቦታ ወንድሞች የሚለው ቃል አማኝ የሆኑ ወንዶችና ሴቶችን ነው ለደቀመዛሙርት ጻፉለት አካይያ ለሚገኙ ክርስትያኖች ደብዳቤ ጻፉለት በደረሰ ጊዜ አጵሎስ በደረሰ ጊዜ አጵሎስ በህዝብ ፊት ረታ አጵሎስ በሕዝብ ፊት አይሁዳዊያዊያንን በክርክሩ ረታቸው
1 አጵሎስ በቆሮንቶስ በነበረ ጊዜ፣ ጳውሎስ በላይኛው አገር አድርጎ ወደ ኤፌሶን ከተማ መጣ፤ በዚያም አንዳንድ ደቀ መዛሙርትን አገኘ። 2 ጳውሎስም፣ “ባመናችሁ ጊዜ መንፈስ ቅዱስን ተቀብላችኋል?” አላቸው። እነርሱም፣ “አልተቀበልንም፤ እንዲያውም መንፈስ ቅዱስ መኖሩን አልሰማንም” አሉት። 3 ጳውሎስም፣ “ታዲያ፣ በምን ተጠመቃችሁ?” አላቸው። እነርሱም፣ “የተጠመቅነው በዮሐንስ ጥምቀት ነው” አሉት። 4 ጳውሎስም መልሶ፣ “ዮሐንስ ያጠመቀው በንስሓ ጥምቀት ነው። ሰዎች ከእርሱ በኋላ በሚመጣው፣ በኢየሱስ ማመን እንደሚገባቸውም ነገራቸው” አለ። 5 ሕዝቡ ይህን ሲሰሙ፣ በጌታ ኢየሱስ ስም ተጠመቁ። 6 ጳውሎስም እጆቹን በሰዎቹ ላይ በጫነ ጊዜ፣ መንፈስ ቅዱስ ወረደባቸው፤ እነርሱም በልዩ ቋንቋ መናገርና መተንበይ ጀመሩ። 7 ቍጥራቸውም ዐሥራ ሁለት ያህል ነበረ። 8 ጳውሎስ ከዚህ በኋላ ወደ ምኵራብ እየገባ ሦስት ወር ያህል በድፍረት ይናገር ነበር፤ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት እየገለጠ ሰዎችን ያስረዳ ነበር። 9 አንዳንድ አይሁድ ግን ልባቸውን አደንድነው በመቃወም፣ በሕዝቡ ፊት የክርስቶስን መንገድ ተሳደቡ፤ ስለዚህ ጳውሎስ ትቶአቸው ሄደ፤ ያመኑትንም ከእነርሱ አራቀ። ጢራኖስ በሚባል የትምህርት አዳራሽም በየዕለቱ ንግግር ያደርግ ጀመር። 10 ይህም፣ በእስያ የሚኖሩ አይሁድና ግሪኮችም ሁሉ የጌታን ቃል እስኪሰሙ ድረስ፣ ሁለት ዓመት ቀጠለ። 11 እግዚአብሔር በጳውሎስ እጅ ታላላቅ ተአምራትን ያደርግ ነበር፤ 12 ስለዚህ የጳውሎስ አካል የነካው ጨርቅ ወይም መሐረብ ሲወሰድ፣ የታመሙት ይፈወሱ፣ አጋንንትም ከሰዎች ይወጡ ነበር። 13 አጋንንት እናስወጣለን እያሉ ከቦታ ቦታ የሚዞሩ አይሁድ ነበሩ፤ እነርሱም የኢየሱስን ስም ለገዛ ጥቅማቸው ለማዋል፣ በክፉ መናፍስት ላይ እየጠሩ፣ “እንድትወጡ ጳውሎስ በሚሰብከው በኢየሱስ እናዛችኋለን” ይሉ ነበር። 14 ይህን ያደረጉትም የአይሁድ የካህናት አለቃ የነበረው የአስቄዋ ሰባት ወንድ ልጆች ነበሩ። 15 ክፉው መንፈስም፣ “ኢየሱስን ዐውቀዋለሁ፤ ጳውሎስንም ዐውቃለሁ፤ ለመሆኑ እናንተ እነማን ናችሁ?” ብለው መለሱላቸው። 16 ክፉ መንፈስ ያለበትም ሰው ዘሎ ያዛቸው፤ አሸንፏቸውም ደበደባቸው። ከዚያም ቤት ቈስለው ዕራቁታቸውን ሸሹ። 17 ይህም በኤፌሶን ይኖሩ በነበሩ አይሁድና ግሪኮችም ዘንድ ሁሉ ታወቀ። እነርሱም ሁሉ በፍርሀት ተዋጡ፤ የጌታ ኢየሱስም ስም ተከበረ። 18 ደግሞም ካመኑት ብዙዎቹ መጥተው ቀደም ሲል ያደረጉትን ክፉ ነገር ሳይሸሽጉ ይናዘዙ ነበር። 19 አስማተኞችም የጥንቈላ መጻሕፍታቸውን ሰብስበው እያመጡ በሰው ሁሉ ፊት አቃጠሉ፤ ዋጋቸውም ሲተመን ሃምሳ ሺህ ብር ሆነ። 20 በዚህም መሠረት የጌታ ቃል በስፋትና በኀይል ተሠራጨ። 21 ጳውሎስ በኤፌሶን የነበረውን አገልግሎቱን ከፈጸመ በኋላ፣ በመቄዶንያና በአካይያ አድርጎ ወደ ኢየሩሳሌም ለመሄድ በመንፈስ ቅዱስ ሆኖ ወሰነ፤ ደግሞም፣ “እዚያ ከደረስሁ በኋላም፣ ሮሜን ማየት ይገባኛል” አለ። 22 ሲረዱት ከነበሩት ደቀ መዛሙርቱ ሁለቱን፣ ጢሞቴዎስንና ኤርስጦንን ወደ መቄዶንያ ላካቸው። እርሱ ራሱ ግን ጥቂት ጊዜ በእስያ ቆየ። 23 በዚህ ጊዜ የጌታን መንገድ በተመለከተ በኤፌሶን ትልቅ ሁከት ተነሣ። 24 ድሜጥሮስ የሚባል አንድ ብር ሠሪም የዲያናን ምስል ከብር እያበጀ ለአንጥረኞች ትልቅ ገቢ ያስገኝላቸው ነበር። 25 ስለዚህ በዚህ ሙያ ላይ የተሰማሩትን ብዙ ሠራተኞች አንድ ላይ ሰብስቦ፣ “ሰዎች ሆይ፤ በዚህ ሙያችን ብዙ ገንዘብ እንደምናገኝ ታውቃላችሁ። 26 ይህ ጳውሎስ በኤፌሶን ብቻ ሳይሆን፣ ከብዙ በጥቂቱ በእስያ ሁሉ አብዛኛውን ሕዝብ በቃላት እያባበለ ከእኛ ማራቁን እያያችሁና እየሰማችሁ ነው። በእጅ የሚሠሩ አማልክት የሉም እያላቸው ነው። 27 የእኛ ሞያዊ ጥበብ አላስፈላጊ መሆኑ ብቻ ሳይሆን፣ የታላቅዋ አምላክ የዲያና ቤተ መቅደስም እንደ ከንቱ ነገር የመቍጠር አደጋ ያሠጋል፤ እስያ ሁሉና ዓለሙ የሚያመልካት ይህች አምላክም ዝናዋን ታጣለች።” 28 ሕዝቡም ይህን በሰሙ ጊዜ፣ በቍጣ ተሞልተው፣ “የኤፌሶንዋ ዲያና ታላቅ ናት” እያሉ ጮኹ። 29 ከተማው ሁሉ ድብልቅልቁ ወጣ፤ ሕዝቡም በአንድ ላይ ገንፍለው ወደ ቲያትር ማሳያው ቦታ ገቡ። ከመቄዶንያ የመጡትንም የጳውሎስን የጕዞ ባልደረቦች፣ ጋይዮስንና አርስጥሮኮስን ያዙአቸው። 30 ጳውሎስ ወደ ሕዝቡ ሊደባለቅ ፈልጎ ነበር፤ ደቀ መዛሙርቱ ግን ከለከሉት። 31 ደግሞም፣ የጳውሎስ ወዳጆች የነበሩ አንዳንድ የአካባቢ ሹሞች ጳውሎስ ወደ ቲያትር ማሳያ ቦታ እንዳይገባ መልእክት ላኩበት። 32 ሕዝቡ ሁሉ ግራ ተጋብቶ ነበርና፣ አንዳንዶቹ ስለ አንድ ነገር ሲጮኹ፣ አንዳንዶቹ ደግሞ ስለ ሌላ ነገር ይጮኹ ነበር። አብዛኛዎቹ ደግሞ ለምን ተሰብስበው እንደ ወጡ እንኳ አያውቁም ነበር። 33 አይሁድም እስክንድሮስን ገፋፍተው ወደ ሕዝቡ ፊት አወጡት። እስክንድሮስ ለሕዝቡ በእጅ ምልክት እያሳየ ሊያስረዳቸው ሞከረ። 34 ሕዝቡም አይሁዳዊ መሆኑን በተረዱ ጊዜ ሁሉም በአንድ ድምፅ፣ “የኤፌሶንዋ ዲያና ታላቅ ናት” እያሉ ለሁለት ሰዓት ያህል ጮኹ። 35 የከተማዋ ጸሓፊ ሕዝቡን ዝም ካሰኘ በኋላ፣ እንዲህ አለ፤ “እናንተ የኤፌሶን ሰዎች ሆይ፣ የኤፌሶን ከተማ የታላቅዋ ዲያና ቤት መቅደስና ከሰማይ የወረደው ምስል ጠባቂ መሆንዋን የማያውቅ የትኛው ሰው ነው? 36 እንግዲህ ይህ የማይካድ ነገር መሆኑ ከታያችሁ፣ ጸጥ ልትሉ፣ አንዳች ነገርም በችኰላ ልታደርጉ አይገባም፤ 37 ምክንያቱም አብያተ መቅደስን ያልሰረቁ፣ አማልክታችንንም ያልሰደቡ እነዚህን ሰዎች ወደዚህ ፍርድ ቤት አምጥታችኋል። 38 ስለዚህ ድሜጥሮስና ከእርሱ ጋር ያሉ አንጥረኞች የሚከሱት ሰው ካለ፣ ፍርድ ቤቱ ክፍት ነው፤ ዳኞችም አሉ፤ እዚያ እርስ በርስ ይካሰሱ። 39 ስለ ሌላ ጉዳይ የምትፈልጉት ነገር ካለ ግን፣ ችግሩ በመደበኛው ጉባኤ ይፈታል፤ 40 ምክንያቱም በዛሬው ቀን የነበረው ዐመፅ ሳያስጠይቀን አይቀርም። የነበረው ግርግር መንሥኢ የለውም፤ እንዲህ ነው ብለን ልንገልጸውም አንችልም።” 41 ጸሓፊው ይህን ተናግሮ ጉባኤውን አሰናበተው።
አጠቃላይ መረጃ ይህ የጳውሎስ የጉዞ ታሪክ ሌላኛው ክፍል ነው፤ ጳውሎስ በዚህ ጉዜ ያለው በኤፌሶን ነው፡፡ እንዲህም ሆነ “ተከሰተ” በዚያ አለፈ በዚያ ተጓዘ የላኛው አገር ይህ የእስያ አካባቢና የአሁኑ ጊዜ ቱርክ ሲሆን የኤፌሶን እና የእስክንድርያ… መንፈስቅዱስን መቀበል መንፈስቅዱስን ማግኘት ስለ መንፈስቅዱስ ምንም አልሰማንም ስለ መንፈስቅዱስ የሰማነው ነገር የለም
አያያዥ ዓረፍ ነገር ጳውሎስ በኤፌሶን ከሚገኙ አዲስ አማኞች ጋር ውይይቱን(ንግግሩን) ቀጠለ ታዲያ በምን ተጠመቃችሁ? በማን ጥምቀት ተጠመቃችሁ? ወይም በማን ስም ተጠመቃችሁ? እንዲህ አሉ ደቀመዛሙርት እንዲህ አሉ በመጥምቁ ዮሐንስ ጥምቀት በመጥምቁ ዮሓንስ የውሃ ጥምቀት የንስሐ ጥምቀት ይህ ጥምቀት ሰዎች ከሃጢያታቸው መመለስ ሲፈልጉ የሚጠመቁት ጥምቀት ነው ከእርሱ በኋላ በሚመጣው ይህ ማለት ከጊዜ አንጻር ከመጥምቁ ዮሐንስ በኋላ የሚመጣ ነገር ግን በአካል እርሱን የማይከተል ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር) ይህ በኤፌሶን ስላሉት አዳዲስ አማኞች የነበረው ታሪክ መጨረሻ ነው ሰዎቹ ሰዎቹ የሚገልጸው ከጳውሎስ ጋር በመነጋገር ላይ የነበሩትን አማኞች ነው እጁን ጫነነባቸው እየጸለየላቸው እጆቹን በጭንቅላታቸው ላይ ጫነባቸው በሌሎች ቋንቋዎች ተናገሩ ፤ ትንቢትም ተናገሩ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ በ ACT 2:3-4 ላይ㙀ደጸገለጸው ሳይሆን በዚህ ሥፍራ ላይ የተናገሩትንም መልዕክት ትርጉም ማን እንደሰማ ( እንደተረዳ ) በግልጽ የተጻፈ የለም በአጠቃላይ ሰዎቹ 12 ያክሉ ነበር ይህ የተጠመቁ ሰዎች አጠቃላይ መረጃ ነው፡፡
ጳውሎስ ወደ ምኩራብ ገብቶ ለሶስት ወራት ያህል በግልጥ አስተማረ አማራጭ ትርጉም፡ ጳውሎስ ለሶስት ወራት በየቀኑ ( በየጊዜው ) በምኩራብ የሚደረጉ ጉባኤዎችን በመካፈል በዚያ ቦታ በድፍረት ይናገር ነበር ሰዎችን እያሳመነ እየተናገረ ስለነበርው እውነት ሰዎችን ለማሳመን ሞከረ ክፉ ነገርን መናገር መጥፎ ንግግሮችን ( ነገሮችን ) መናገር የክርስቶስ መንገድ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ያለ ደኀንነት በእሲያ የሚኖሩ ሁሉ ሰሙ ትርጉም ሊሆኑ የሚችሉ አማራጮች 1 ጳውሎስ በመላው እሲያ ለሚኖሩ ብዙ ሰዎች ወንጌልን መሰከረ ወይም 2 የጳውሎስ መልዕክት ከመላው እሲያ ወደ ኤፌሶን በሚመጡ ሰዎች አማካኝነት ወደ ሁሉም የእሲያ አካባቢዎች ተዳረሰ፡፡
በጳውሎስ እጅ በጳውሎስ በኩል ከጳውሎስ ልብስ ዘርፍና ከመጠምጠሚያው ጫፍ ሲወስዱ አማራጭ ትርጉም ፡ በጳውሎስ የተነኩ የልብስ ዘርፎችና የመጠምጠሚያ ጫፎች በድዊያን ወይም በታመሙ ሰዎች ላይ ሲደረጉ፡፡
አጠቃላይ መረጃ ይህ ክፍል ጳውሎስ በኤፌሶን ሳለ ርኩስ መንፈስን በሚያስወጡ አይሁዳዊያን ሰዎች ላይ የተከሰተ ሁኔታ ነው ርኩስ መንፈስ የሚያስወጡ ከሰዎች ወይም ከአካባቢያቸው ርኩስ መንፈስን የሚያባርሩ የኢየሱስን ስም ለግል ጥቅማቸው አዋሉት ወይም ተጠቀሙት ምንም እንኳን በኢየሱስ ባይምኑም የኢየሱስን ስም አስማት በመስራት ከሚጠቀሙባቸው ቃላት እንደ አንዱ ለመጠቀም ሞከሩ እርኩስ መንፈስ ያለባቸው በርኩስ መንፈስ ተጽዕኖ ሰር የነበሩ፡፡
ኢየሱስን አውቀዋለሁ፤ ጳውሎስን አውቀዋለሁ ኢየሱስንና ጳውሎስን አውቃቸዋለሁ ወይም ስለ ኢያሱስን ስለ ጳውሎስ ሰምቻለሁ
እነማን
ከመንፈሱ ይህንን ጥያቄ የጠየቀው አስማተኞቹ በርኩስ መንፈስ ላይ ስልጣን እንዳላቸው ለማረጋጋጥ ነው፡፡
አማራጭ ትርጉም፡ ምን ስልጣን አላቹ ወይም ምንም አይነት ስልጣን ያላቹም
አስማተኞች
በ ACT 19:13 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡
ራቁታቸውን ሸሹ
አስማተኞቹ በክፊል ወይም በአጠቃላይ ተራቁተው ሸሹ
እነርሱ በጣም ፈሩ
በኤፌሶን የሚኖሩ አይሁዳዊያንና ግሪካዊያን በጣም ፈሩ፡፡
አያያዥ ዓረፍ ነገር ይህ አይሁዳዊያኑ አስማተኞች ታሪክ የመጨረሻ ክፍል ነው፡፡ (ተመልከት: [[End of Story]]) መጽሐፍቶቻቸውን ሰበሰቡ መጽሐፍት አስማታዎ ድግምቶችና መመሪያዎች የተጻፈባቸው ጥቅልሎች ናቸው ሁሉም እያዩ በሰው ሁሉ ፊት የብር ሳንቲሞች አንድ የብር ሳንቲም ለአንድ የጉልበት ሰራተኛ ቀን ደሞዙ ነበር የጌታ ቃል በሐይልና በስፋት ተሰራጨ ስለ ጌታ የሚነገረው መልዕክት በጣም በተሳካ ሁኔታ መሰራጨትና ተጽዕኖ ማምጣት ጀመረ፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ጳውሎስ ወደ እየሩሳሌም ለመሄድ መወሰኑን ተናገረ ነገር ግን ከኤፌሶን ገና አልወጣም ጳውሎስ አገልግሎቱን ፈጸመ (ጨረሰ) ጳውሎስ እግዚአብሔር በኤፌሶን እንዲሰራ የሰጠውን ስራ ጨረሰ በመንፈስ ሆኖ ወሰነ ትርጉም ሊሆኑ የሚችሉ አማራጮች 1 ጳውሎስ በመንፈስ ቅዱስ እርዳታ ወሰነ ወይም 2 መንፈስ ጳውሎስን ወደ ውሳኔ መራው ሜቄዶኒያ እና አካያ እነዚህ አውራጃዎች የአሁኑ ጊዜ ግሪክ የሚባላው ቦታ ናቸው ሮሜን አይ ዘንድ ይገባኛል ወደ ሮሜ መሄድ አለብኝ ነገር ግን ራሱ ለጥቂት ጊዜ በእሲያ ቆየ በቀጣዮቹ ጥቂት ቁጥሮች ውስጥ ጳውሎስ በኤፌሶን እንደቆየ
አጠቃላይ መረጃ ይህ ታሪክ ጳውሎስ በኤፌሶን እያለ ስለተከሰተው የህዝብ አመጽ ጅማሬ ነው ፡፡ ድሜጥሮስ በዚህ ታሪክ ውስጥ ተካቷል ታላቅ ሁከት የህዝብ አመጽ ሊቀሰቀስ ያለበት ሁኔታ መንገዱ ይህ ቃል ክርስትናን ለመግለጽ ጥቅም ላይ ይውል ነበር አንጥረኛ አንጥረኛ የእጅ ሙያ ያለው ብርን በማቅለጥ የሀውልት ቅርጽና ጌጣጌጥ የሚሰራ ሰው ነው ድሜጥሮስ የሚባል ድሜጥሮስ በኤፌሶን የሚኖር አንጥረኛ ሲሆን ጳውሎስንና በኤፌሶን የምትገኘውን አጥቢያ ቤተክርስቲያንን ይቃወም ነበር፡፡ በብር ሀውልቶችን የሚሰራ…ለአንጥረኞችም ብዙ ትርፍ የሚያስገኝ ይህ ስለ ድሜጥሮስ የጀርባ ታሪክ ነው፡፡ አርጤምስ ምስል ትልቁ የአርጤምስ ቤተመቅደስ በኤፌሶን ይገኝ ነበር፡፡ ብዙ ትርፍ አስገኘ በአርጤምስ ምስል የተሰሩ ብዙ ሐውልቶችን ሸጠ፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር ድሜጥሮስ ለአንጥረኞች መናገሩን ቀጠለ አይታችኋል ሰምታችሁማል አውቃችኋል ተረድታችሁማል ብዙ ሰዎችን አስቷል ብዙ ሰዎችን ጣኦትን እንዳያመልኩ እና ወደ ክርስቶስ እንዲመለሱ አሳምኗቿል ታላቅነቷንም ልታጣ ትችላለች የአርጤምስ ታላቅነት ሰዎች ስለሷ ከሚያስቡት የሚመነጭ ነው መላው እሲያና አለሙም ሁሉ የሚያመልካት ይህ የአርጤምስን ታዋቂነት ለማሳየት ጥቅም ላይ የዋለ ግነት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- በእሲያና በመላ አለም ብዙ ህዝብ የሚያመልካት ናት፡፡
ሲሰሙ አንጥረኞቹ ሲሰሙ ቁጣ ሞላባቸው በጣም ተቆጡ ጮሁ በታላቅ ድምጽ እየጮሁ ተናገሩ ህዝቡም በአንድነት ተጣደፉ ይህ የህዝብ አመጽ የሚያሳይ ሁኔታ ነው ወደ ጫወታ ቦታ ( የቲያትር ቦታ ) የኤፌሶን የጫዎታ ቦታ ለህዝብ ስብሰባና ለመዝናኛ የሚሆኑ ድራማዎችንና ሙዚቃዎችን ለማቅረብ ጥቅም ላይ ይውላል እነርሱም የጳውሎስን ጓደኞች ያዙዋቸው ህዝቡም የጳውሎስን ጓደኖች ያዙዋቸው ጋይዮስ እና አርስጥሮኮስ እነዚህ የሰዎች ሰሞች ናቸው ከሜቄዶኒያ የመጡ ጋይዮስ እና አርስጥሮኮስ ከሜቄዶኒያ ቢመጡም በዚህ ሰዓት ከጻውሎስ ጋር በኤፌሶን እየሰሩ ነበር፡፡
የጫዎታ ቦታ በግማሽ ክብ ቅርጽ የተሰራና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን መያዝ ( ማስቀመጥ ) የሚችሉ መቀመጫዎች ያሉት ቦታ ነው፡፡
አይሁዳዊያን እስክንድሮስን አመጡት ጳውሎስ ጢሞቲዎስን የመዳብ ሰራተኛ ስለነበረው ስለ እስክንድሮስ አስጠንቅቆት ነበር (2 ጢሞቲዎስ 2TI 4:14) በእጁ ጠቀሰ ወይም ገለጸ ለህዝቡ ምልክት አሳየ ማብራሪያ ሰጠ ሊሟገትላቸው ፈልጎ ነበር ነገር ግን ምን ማለት እንደፈለገ ግልጽ አይደለም
አጠቃላይ መረጃ የከተማይቱ ጸሐፊ ህዝቡን ተናገረ እናንተ የኤፌሶን ሰዎች እናንተ የሚለው የሚያመለክተው በዚያ ቦታ የተገኙትን የኤፌሶን ሰዎችን ነው፡፡ የኤፌሶን ከተማ ለታላቂቷ አርጤምስ ከሰማይም ለወረደው ጣኦቷ የመቅደስ ጠባቂ መሆኗን የማያውቅ ሰው ማነው? ጸሃፊው ይህንን ጥያቄ የጠየቀው ህዝቡ ትክክል እንደሆኑ ለማረጋገጥና ሊያረጋጋቸው ፈልጎ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- የኤፌሶን ከተማ ለታላቂቷ አርጤምስ ከሰማይም ለወረደው ጣኦቷ የመቅደስ ጠባቂ እንደሆነች ሁሉም ሰው ያውቃል፡፡ መቅደስ ጠባቂ የኤፌሶን ሰዎች የአርጤምስን መቅደስ ጠብቀው አቆይተዋል ከሰማይ የወረደው ምስሏ በአርጤንስ ቤተመቅድስ ውስጥ በቀጥታ ከዛስ በጣ ተብሎ በሚታመን ድንጋይ የተሰራ የጣኦት ምስል ይገኛል;;
አያያዥ ጽሁፍ የከተማው ጸሃፊ ለህዝቡ ሚያደርገውን ንግግግር ጨረሰ ስለዚህ ይህ ቃል የሚያገለግለው ቀደሞ በተባለ ነገር ምክንያት የሚባልን ሌላ ነገር ለመግለፅ ነው;; በዚህ ጊዜ ይህ ቃል የሚያመለክተው ድሜጥሮስ ጋይዬስና አርስጥሮኮስ ሌቦችና ተሳዳቢዎች አይደሉም ብሎ የተናገረውን ACT 19:37 ነው፡፡ አገረ ገዢ ይህ በሮሜ አውራጃ ላይ የተሸመ አስተዳዳሪ ነው፡፡
1 ሁከቱ ካበቃ በኋላ፣ ጳውሎስ ደቀ መዛሙርቱን አስጠርቶ አበረታታቸው። ከዚያም ተሰናበታቸውና ወደ መቄዶንያ ለመሄድ ተነሣ። 2 በእነዚያም አካባቢዎች እያለፈ ያመኑትን እጅግ ካበረታታ በኋላ፣ ወደ ግሪክ ገባ። 3 በዚያም ሦስት ወር ከቈየ በኋላ፣ ወደ ሶርያ በመርከብ ለመሄድ እያሰበ ሳለ፣ አይሁድ አሤሩበት፤ ስለዚህ በመቄዶንያ አድርጎ ለመመለስ ወሰነ። 4 እስከ እስያ የሸኙትም የቤርያው ሱሲጳጥሮስ፣ ከተሰሎንቄ የመጡት አርስጥሮኮስና ሲኮንዱስ፣ የደርቤኑ ጋይዮስ፣ ጢሞቴዎስ፣ እንዲሁም ከእስያ የመጡት ቲኪቆስና ጥሮፊሞስ ነበሩ። 5 እነዚህ ሰዎች ግን ቀድመውን በጢሮአዳ ጠበቁን። 6 እኛም ከቂጣ በዓል ቀን በኋላ፣ ከፊልጵስዩስ በመርከብ ተነሥተን በዐምስት ቀን ውስጥ ጢሮአዳ ደረስንባቸው፤ እዚያም ሰባት ቀን ተቀመጥን። 7 በሳምንቱ መጀመሪያ ቀን እንጀራ ለመቊረስ በተሰበሰብን ጊዜ፣ ጳውሎስ ለምእመናኑ ንግግር አደረገ። በሚቀጥሉት ቀናት ለመሄድ ዐቅዶ ስለ ነበረ፣ እስከ እኩለ ሌሊት መናገሩን ቀጠለ። 8 በተሰበሰብንበትም ሰገነት ላይ ብዙ መብራቶች ነበሩ። 9 አውጤኪስ የሚባል ወጣትም በመስኮት ተቀምጦ ሳለ፣ እንቅልፍ ጭልጥ አድርጎ ወሰደው። ጳውሎስ ንግግሩን ባስረዘመ ጊዜ፣ ይህ ወጣት ገና ተኝቶ እንዳለ ከሦስተኛው ፎቅ ወደቀ፤ ሲያነሡትም ሞቶ ነበር። 10 ጳውሎስ ግን ወርዶ በላዩ ተዘረጋበት፣ ዐቀፈውም። ከዚያም፣ “በሕይወት ስላለ ከዚህ በኋላ አትታወኩ” አለ። 11 እንደ ገናም በደረጃ ወደ ላይ ወጣ፤ እንጀራ ቈርሶም በላ። እስኪነጋ ድረስም ለረዥም ጊዜ ከእነርሱ ጋር ከተነጋገረ በኋላ፣ ተለይቶአቸው ሄደ። 12 ወጣቱንም በሕይወት እያለ አመጡት፤ በዚህም እጅግ ተጽናኑ። 13 እኛም ራሳችን ጳውሎስን በመርከብ ለማሳፈር ወዳሰብንበት ወደ አሶን ቀድመን በመርከብ ሄድን። እርሱም ያሰበው ይህንኑ ነበር፤ በመርከብ ለመሄድ ዐቅዶ ነበርና። 14 በአሶን ሲያገኘንም፣ ወዳለንበት መርከብ አስገብተነው ወደ ሚሊጢን ጕዞአችንን ቀጠልን። 15 ከዚያም በመርከብ ተነሣንና በማግስቱ ኪዩ በምትባለዋ ደሴት ትይዩ ደረስን። በሚቀጥለውም ቀን ወደ ሳሞን ደሴት ጎራ ብለን፣ በማግስቱ ወደ ሚሊጢን ከተማ ገባን፤ 16 ጳውሎስም በእስያ ውስጥ ጊዜ ሳያባክን፣ ኤፌሶንን ዐልፎ በመርከብ ለመሄድ ወስኖ ነበርና፤ ምክንያቱም በተቻለው መጠን ሁሉ ለበዓለ ኀምሳ በኢየሩሳሌም ለመገኘት ቸኵሎ ነበር። 17 ሰዎችንም ከሚሊጢን ወደ ኤፌሶን ልኮ፣ የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎችን ወደ ራሱ አስጠራቸው። 18 ወደ እርሱ በመጡም ጊዜ፣ እንዲህ አላቸው፤ “ወደ እስያ ከገባሁበት ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ፣ ዘወትር እንዴት ከእናንተ ጋር እንደ ኖርሁ እናንተ ራሳችሁ ታውቃላችሁ። 19 ራሴን እጅግ ዝቅ በማድረግና በእንባ፣ ከአይሁድ ሤራ የተነሣ በገጠመኝ መከራም ውስጥ ጌታን ማገልገል አላቋረጥሁም። 20 ጠቃሚ የሆነውን ነገር ሁሉ ለእናንተ ከመግለጽና በአደባባይም ሆነ ቤት ለቤት በመዞር እናንተን ከማስተማር ወደ ኋላ እንዳላልሁ ታውቃላችሁ። 21 በንስሓ ወደ እግዚአብሔር ስለ መመለስና በጌታችን በኢየሱስ ስለ ማመን አይሁድንና ግሪኮችን እንዴት ሳስጠነቅቃቸው እንደ ነበር ታውቃላችሁ። 22 እንግዲህ ተመልከቱ፤ እዚያ ምን እንደሚጠብቀኝ ሳላውቅ፣ በመንፈስ ቅዱስ ታስሬ ወደ ኢየሩሳሌም እሄዳለሁ፤ 23 ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ እስራትና መከራ እንደሚቆየኝ በየከተማው ይመሰክርልኛል። 24 ነገር ግን ሩጫዬንና ከጌታ ኢየሱስ የተቀበልሁትን የእግዚአብሔርን ጸጋ ወንጌል የመመስከር አገልግሎት እስከምጨርስ ድረስ፣ እንደ ውድ ነገር በመቍጠር፣ ለሕይወቴ አልሳሳላትም። 25 እንግዲህ ተመልከቱ፤ የእግዚአብሔርን መንግሥት እየሰበክሁ በመካከላችሁ የዞርሁትን የእኔን ፊት ሁላችሁ ዳግመኛ እንደማታዩ ዐውቃለሁ። 26 ስለዚህ ከማንም ሰው ደም ንጹሕ እንደ ሆንሁ ዛሬ እመሰክርላችኋለሁ፤ 27 ምክንያቱም የእግዚአብሔርን ፈቃድ ሁሉ ለእናንተ ከመግለጽ ወደ ኋላ ብዬ አላውቅም። 28 ስለዚህ በገዛ ራሱ ደም የገዛትን የጌታን ጉባኤ ትጠብቁ ዘንድ፣ ስለ ራሳችሁና መንፈስ ቅዱስ ጠባቂ አድርጎ እናንተን ለሾመበት፣ ለመንጋው ሁሉ ተጠንቀቁ። 29 እኔ ከሄድሁ በኋላ፣ ለመንጋው ርኅራኄ የሌላቸው አጥፊ ተኵላዎች በመካከላችሁ እንደሚገቡ ዐውቃለሁ። 30 ከእናንተ መካከልም እንኳ ደቀ መዛሙርትን የራሳቸው ተከታዮች ለማድረግ አንዳንድ ሰዎች መጥተው ጠማማ ነገሮችን እንደሚናገሩ ዐውቃለሁ። 31 ስለዚህ ተጠንቀቁ። ሳላቋርጥ ቀንና ሌሊት፣ ሁላችሁንም ሦስት ዓመት በእንባ እንዳገለገልኋችሁም አስታውሱ። 32 አሁንም ለእግዚአብሔርና ሊያንጻችሁ፣ እንዲሁም በቅዱሳን ሁሉ መካከል ርስትን ሊሰጣችሁ ለሚችለው ለጸጋው ቃል ዐደራ እሰጣችኋለሁ። 33 የማንንም ብር፣ ወርቅ ወይም ልብስ አልተመኘሁም። 34 እነዚህ እጆቼ የእኔንም፣ ከእኔ ጋር የነበሩትንም ሰዎች ፍላጎት ሲያሟሉ እንደ ነበር እናንተ ራሳችሁ ታውቃላችሁ። 35 ደካሞችን በሥራ እንዴት እንደምትረዱ፣ “ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ የተባረከ ነው” የሚለውንም የጌታ ኢየሱስን ቃል እንዴት እንደምታስታውሱ በሁሉም ረገድ አርኣያ ሆንኋችሁ። 36 ጳውሎስ ይህን ሁሉ ካለ በኋላ፣ ተንበርክኮ ከሁሉም ጋር ጸለየ። 37 ሁሉም እጅግ በማልቀስ ዐንገቱ ላይ ተጠምጥመው ሳሙት። 38 ፊቱን ዳግመኛ እንደማያዩ መናገሩም ከሁሉ በላይ አሳዘናቸው። ከዚያም እስከ መርከቡ ድረስ ሸኙት።
አጠቃላይ መረጃ ጳውሎስ ጉዞውን ቀጠለ ከሁከቱ በኃላ ከረብሻው በኃላ ውይም ከህዘቡ ዘመጽ ቀጥሎ ተሰናበታቸው ሰዎች ብዙ ጊዜ ሲለያዩ ይሰነባበታሉ፡፡ አማረጭ ትረጉም፡- ደህና ሁኑ አላቸው፡፡ አማኞችን በጣም አበረታታተቸወ፡፡ አመኞችን ለማበረታታት ብዙ ነግረ ተናገረ በዚያም ሶስት ወር አሳለፈ በዚያም ሶስት ወር ተቀመጠ በጳውሎስ ላይ አይሁዳውያን አሴሩበት አማረጭ ትርጉም፡- አይሁዳውያን አሴሩበት፡፡ ሴራ ጠነሰሰ(ተሴረ) የድብቅ እቅድ ተዘጋጀ ወደሶሪያ በመርከብ ሊሄድ ነበር ወደ ሶሪያ በመርከብ ለመሄድ ዝግጁ ነበር፡፡
ያጅቡታል ከጰውሎስ ጋር ይጓዛሉ ሱሲጳጥሮስ ….ጥሮፊሞስ እነኚህ የሰዎች ስሞች ናቸው፡፡ ቤሪያ….. በርቤን…..ጢሮአዳ እነዚህ የቦታ ስሞች ናቸው፡፡ አርስጥሮኮስና . . . ጋይዮስ እነዚህ ስሞች በ ACT 19:29 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምህ ተመልክት፡፡ See how you translated these names in እነዚህም ሰዎቸ ቀድመውን ሄዱ የየሐዋርያት ሥራ ጸሀፊ የሆነው ሉቃስ እነዚህን ሰዎች እንደገና ተቀላቀላቸው፡፡ አማራጭ ትርጉም እነዚህ ሰዎች ከፊታችን ቀድመውን ተጓዙ፡፡
አጠቃላይ መረጃ ይህ ክፍል ስለ ጳውሎስ የጢሮአዳ ስብከትና ስለ አውጤኪስ የሚናገረው ታሪክ ጅማሬ ነው፡፡ በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን አሁድ እለት እንጀራ መቁረስ በጌታ እራት ጊዜ እንጀራ እየተቆረሰ ይበላል፡፡ ንግግሩን ቀጠለ ንግግሩን አላቋረጠም የላይኛው ክፍል ይህ ምንአልባት ሶስተኛ ፎቅ ላይ ሊሀን ይችላል፡፡
ጥልቅ የሆነ እንቅልፍ ወድቆ ነበር በጣም ከመተኛቱ የተነሳ ቢቀሰቅሱት እንኳ አይሰማም፡፡ ሦስተኛው ፎቅ "ከምድር ቤቱ በተጨማሪ ሁለት ፎቆች ያሉት ቤት" ከመሬት ስያነሱት ሞቶ ነበር ያለበትን ሁኔታ ለማጣራት ወደታች ሄደው ስመለከቱት ሞቶ አገኙት፡፡ ከዚያም እንዲህ አለ "ከዚያም ጳውሎስ እንዲህ አለ" አልሞተም በሕይወት አለ "አውጤኪስ በሕይወት አለ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ይህ ጳወልስ በተርሴት ያደረገው ስብከት እና አውጤኪስ በተመለከተ የተዘገበው ታሪክ ክፍል ማብቂያ ነው፡፡ ደረጃውን ይዞ ወደላይ ወጣ "ጳውሎስ ወደ ደረጃው ወጣ" ማዕድ ቆረሰ ይህ አንድን ዳቦ ለሁሉም ሰዎች እንዲከፋፈል ተደረጎ መከፋፈል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "በጋራ መብላት፡፡" ከዚያ ተነሥቶ ሄደ "ከዚያ ወጥቶ ሄደ" ወንዱ ልጅ አማራጭ ትርጉሞች 1) ከ14 ዓመት በላይ የሆነ ወጣት ወንድ ልጅ ወይም 2) አገልጋይ ወይንም ባሪያ ወይም 3) በ9 እና 14 ዓመት መካከል ያለ ወንድ ልጅ፡፡
አጠቃላይ መረጃ:
ጳውሎስ እና የአገልግሎት ባልደረቦቹ ጉዞዋቸውን ቀጥለዋል፡፡
እኛ ራሳችን ሄድን
በዚህ ሥፍራ ላይ “ራሳችን” የሚለው ቃ የገባው አጽኖት ለመስጠት ሲሆን ይህ ሉቃስን እና የጳውሎስ የአገልግሎት አጋሮች የሆኑትን እና ከእርሱ ጋር በመርከብ የተጓዙትን እና ያልተጓዙት የሚለይ ነው፡፡
ወደ አሶን በመርከብ ጉዞ ጀመረን
አሶን በአሁኗ ባህሬን፣ የቱርክ የወደብ ከተማ ከሆነች ከአጌን ሀይቅ አከባቢ የሚትገኝ ከተማ ናት፡፡
እርሱ ራሱ ይፈልግ ነበር
"ጳውሎስ ፍላጎት ነበረው"
እርሱ እኛ ወሰድነው
በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሉቃስን እና ከእርሱ ጋር የተጓዙትን እንጂ ጳውሎስን አይደለም፡፡
ወደ ሚጢሊኒ መጣን፤
ሚጢኒሊ በቱሪክ ሀገር ውስጥ በሚገኘው የኤአን ሐይቅ ዙሪያ የሚትገኝ የዘመኗ ሚጢሊኒ ናት፡፡
ከዚያ ተነሥተን ሄድን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል ጳውሎን፣ ሉቃስን እና ከእነርሱ ጋር በመጓዝ ላይ ያሉትን ሰዎች ያመለክታል፡፡ የኪዩ ደሴት ኪዩ በአሁኗ ቱሪክ ሀገር ውስጥ በሚገኘው የአጌን ሐይቅ ላይ የሚገኝ ደሴት ነው፡፡ ሳሞን የተባለው ደሴት ተሻግረን ሄድን ሳሞን በአጋን ሐይቅ ውስጥ በዘመኑ ትሪክ ከሚገኘው ከኪዮስ ደሴት በስተደቡብ ላይ ይገኛል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "የሳሞንን ደሴት ተሻግረን ሄድን፡፡" የሚሊጢን ከተማ ሚሊጢን በምዕራብ ኢስያ አከባቢ በሜንዴር ወንዝ ጫፍ ላይ የሚትገኝ የወደብ ከተማ ናት፡፡ ጳውሎስ በኤፌሶን በኩል ለመሄድ ወስኖ ነበር ጳውሎስ በመርከብ በደቡብ በኩል አድርጎ የኤፌሶንን ወደብ አልፎ ሄደ፡፡ ይህንንም ያደረገው ወደሚሊጢስ ምድር ለመድረስ ፈልጎ ነበር፡፡
ከሚሊጢስ ተነስቶ ይህንን በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ በ ACT 20:15 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ በኢስያ መረት ረገጡ "ወደ እስያ አከባቢ ገቡ" በትህትና "ራሴን ዝቅ አድርጌ" ወይም "በትህትና" በእንባ "አንዳንድ ጊዜ ጌታን እያገለገልኩ እንኳ አለቅሳለሁ" አንዳችን ነገር አላስቀረሁባችሁም "ምንም ነገር አልሸሸኳችሁም" ወይም "ከእናንተ የደበኩት ነገር የለም" ከቤት ነቤት ጉብኘንት አንስቶ ጳውሎስ በተለያዩ የግለሰቦች ቤት ውስጥ ያስተምር ነበር፡፡ በእግዚአብሔር ፊት የሚሆን ንሰሓ "ከኃጢአት ፍታቸውን መልሰው ወደ እግዚአብሔር ይዙሩ ዘንድ"
ከእየሩሳሌም ጋር በመንፈስ ቅዱስ አማካኘነት ይተሳሰሩ ዘንድ "ወደ እየሩሳሌም እሄድ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ ስላስገደደኝ" መንፈስ ቅዱስ ለእኔ መስክሯል "መንፈስ ቅዱስ ይህንን ነገር አስቀድሞ በማሳወቅ አስጠንቅቆኛል፡፡" እስራት እና መከራ ይጠብቀኛል "በሰንሰለት ገና እታሠራለሁ እንዲሁመም አካላዊ መከራም ገና ደርስበኛል፡፡ " ሩጫዬን ጨርሻለሁ "እግዚአብሔር እንድሠራው የላከኝ ሥራ አጠናቅቄያለሁ" ምስክር ይሆናሉ "ምስክርነት መስጠት" ወይም "መመስከር"
እናንተን ሁላችሁንም አወቃለሁl "እናንተ ሁላችሁ" የእግዚብሔርን መንግስት ለመስበክ አብሬያች የወጣሁት እናንተ "ስለ እግዚአብሔር መንግስት የሰበኩላችሁ እናንተ" ከእንግዲህ ፊቴን አታዩም በዚህ ሥፍራ ላይ “ፊት” የሚለው የፓውሎስ አካል የሚያሳይ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ከእንግዲህ በምድር ላይ እኔን በሥጋ አተታዩኘንም፡፡" እኔ የማንም ሰው ደም የለብኝም "ማንም ሰው በእግዚአብሔር በደለኛ ተደርጎ ቢፈረድበት በእኔ ምከክንያት ግን አይሆንም፡፡"
ስለዚህ በዚህ ሥፍራ ላይ “ስለዚህ” የሚለው ቃል ከዚህ በፊት በተነገረ አንድ ነገር ምክንያት ይህ እንደሆነ ያሳያል፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ጳውሎስ እስካሁን የተናገረውን ነገር የሚያመለክት ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ኤጴስ ቆጶስ አድርጎ በሾማችሁ መንጋዎች ላይ አማኞች የተመሰሉት በበግ መንጋ ነው፡፡ ልክ በጉችን የመጠበቅ ኃላፊነት የእረኞቹ እንነደሆነ ሁሉ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች የእግዚአብሔርን መንጋ ይጠብቁ ዘንድ አደራ ተሰጥቶዋቸዋል፡፡ ስለዚህም ከተኩላዎች የመጠበቅ ኃላፊነት አለባቸው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "መንፈስ ቅዱስ አደራ የሰጣችሁ የአማኞች ቡድን፡፡" በደሙ የገዛቸው የጌታ ጉባኤ የኢየሱስ ክርስቶስ “ደም” መፍሰስ ለእግዚአብሔር ስለኃጢአት የተከፈለ ዋጋ ሆኖ ቀርቧል፡፡ አመማራጭ ትርጉም፡ “ክርስቶስ ደሙን በመስቀል ላይ አፍስሶ የገዛቸው ሕዝቡ፡፡” ለራሳቸው ደቀ መዛሙርትን ያፈራሉ "የክርስቶስ ተከታይ የሆኑ ሰዎችን የእርሱ ተከታዩች ይሆኑ ዘንድ በራሳቸው፣ በተሳሳተ ትምህር ያሳምኗቸዋል፡፡"
ተጠንቀቁ፣ አስታውሱ አማራጭ ትርጉም: "ተጠንቀቁ እንዲሁም አስታውሱ" ወይም "እያስታወሳችሁ ተጠንቀቁ" ወይም "በማስታወስ ተጠንቀቁ" ተጠንቀቁ "ንቁና ጠብቁ" ወይም “ነቅታችሁ ጠብቁt" (UDB) ወይም "ንቁዎች ሁኑ" አስታውሱ "ማስታወሳችሁን ቀጥሉ" ወይም "እንዳትዘነጉ" ለሦስት ዓመታት ማስተማር አላቋረጥኩም ጳውሎስ ለሦስት ዓመታት ያኸል በተከታታይ አላስተማራቸው ይሁን እንጂ በእነዚህ ሦስት ዓመታት ውስጥ አልፎ አልፎ ያስተምራቸው ነበር፡፡ ማስተማር አላቋረጥኩም አማራጭ ትርጉሞች 1) "ማስጠንቀቅ አላቆምኩም" ወይም 2) "ማሰተካከያዎችን በመስጠጥ ማበረታታቴን አላቆምኩም ነበር፡፡"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: በ ACT 20:18 ላይ የጀመረውን ጳውሎስ በኤፌሶን ላሉ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ያደረገውን ንግግር በበዚህ ክፍል ውስጥ አጠናቋል፡፡ የማናችሁንም ብር አልቀማሁም "የማናችሁንም ሀብት አልተመኘሁም" ወይም "ለራሴ ምን ብር ከእናንተ አልፈለኩም" የሰውን ብር፣ ወርቅ ወይም ልብስ በዚያ ዘመን ልብስ እንደ ሀብት ይታይ ነበር፤ ብዙ ልብስ ባለህ ቁጥር ሀብታም ነህ ማለት ነው፡፡ እናንተ ራሳቸችሁ በዚህ ሥፍራ ላይ “ራሳችሁ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ በእነዚህ እጆቼ እየሠራሁ የሚያስፈልገኝ ነገር አድርግ ነበር በዚህ ሥፍራ ላይ “እጅ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የጳውሎስን አጠቃላይ መንፈስ እና አካልን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “በገዛ እጆቹ እየሠራሁ ገንዘብ አገኛለሁ እንደሁም ወጪዬን ሁሉ በዚህ እሸፍን ነበር፡፡" ደካሞችን ሥራ እየሠራችሁ አግዟቸው "ደካሞችን ማገዝ ያስችላችሁ ዘንድ ገንዘብ ለማግኘት ሥራ ሥሩ" ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብጹዕ ነው ሰው ከእግዚአብሔር ሞገዝን እና ሀሴት ማደረግን መቀበል የሚችለው ይበልጥ ሲሰጥ ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ይህ ጳውሎስ በኤፌሶን ካሉ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ጋር ያደረገውን ጸሎት የተዘገበበት ታሪክ ማብቂያ ነው፡፡ በጳውሎስ አንገት ላይ ተጠመጠመ "አጥብቆ አቀፈው" ወይም "እጆቻውን በእርሱ ዙሪያ አኖሩ" ሳሙት በመካከለኛው ምስራቅ አንድን ሰው ጉንጩን መሳም ወንድማማችነትን ወይም ጓደኝነት የሚያሳይ ነው፡፡ እንደገና ፊቱን አያዩትም በዚህ ሥፍራ “ፊት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የጳውሎስን ሙሉ አካልን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ በዚህ መድር ላጥ እንደገና በሥጋ አታዩኝም፡፡"
1 ከእነርሱም ተለይተን የባሕር ላይ ጕዞአችንን በቀጠልን ጊዜ፣ ቀጥታ ወደ ቆስ ከተማ አመራን፤ በማግስቱም ወደ ሩድ ከተማ፣ ከዚያም ወደ ጳጥራ ከተማ ሄድን። 2 ወደ ፊንቄ የሚሻገር መርከብ ባገኘን ጊዜም ተሳፍረን መጓዝ ጀመርን። 3 የቆጵሮስን ደሴት ከሩቅ ባየን ጊዜ፣ ወደ ግራ ትተናት በባሕር ወደ ሶርያ ተጓዝን፤ መርከብዋ ጭነቷን የምታራግፈው በዚያ ስለ ነበር፣ ጢሮስ ወደብ ላይ ደረስን። 4 ደቀ መዛሙርቱን ካገኘን በኋላም፣ በዚያ ሰባት ቀን ተቀመጥን። እነዚህም ደቀ መዛሙርት ጳውሎስ ወደ ኢየሩሳሌም እንዳይገባ በመንፈስ ቅዱስ ተናገሩት። 5 የምንቈይበት ጊዜ ሲገባደድ፣ ተነሥተን ጕዞአችንን ቀጠልን። ሁሉም፣ ከሚስቶቻቸውና ከልጆቻቸው ጋር ከከተማ እስክንወጣ ድረስ በመንገዳችን ሸኙን። ከዚያም እወደቡ ላይ ተንበርክከን ጸለይን፤ እርስ በርስም ተሰነባበትን። 6 እኛ በመርከቡ ተሳፈርን፤ እነርሱም ወደ ቤታቸው ተመልሰው ሄዱ። 7 ከጢሮስ የተነሣንበትን ጕዞ በጨረስን ጊዜ፣ አካ ደረስን። በዚያም ወንድሞችን አገኘንና አንድ ቀን ከእነርሱ ጋር ቈየን። 8 በሚቀጥለው ቀን ከዚያ ተነሥተን ወደ ቂሣርያ ሄድን። ከዚያም ከሰባቱ አንዱ ወደ ሆነው፣ ወደ ወንጌል ሰባኪው ወደ ፊልጶስ ቤት ገብተን ከእርሱ ጋር ሰነበትን። 9 ይህም ሰው ትንቢት የሚናገሩ አራት ደናግል ሴቶች ልጆች ነበሩት። 10 የተወሰኑ ቀናት እንደ ተቀመጥንም፣ አጋቦስ የሚሉት ነቢይ ከይሁዳ ወደ ነበርንበት ወረደ። 11 ወደ እኛም መጥቶ፣ የጳውሎስን መታጠቂያ ወሰደ፤ የገዛ ራሱን እጆችና እግሮችም አስሮ፣ “መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ይላል፤ ‘በኢየሩሳሌም ያሉ አይሁድ የዚህን መታጠቂያ ባለቤት እንደዚህ አድርገው ያስሩታል፤ አሳልፈውም ለአሕዛብ እጅ ይሰጡታል’” አለ። 12 እነዚህን ነገሮች በሰማን ጊዜ፣ እኛና በዚያ ስፍራ የሚኖሩ ሰዎችም ወደ ኢየሩሳሌም እንዳይወጣ ለመንነው። 13 ጳውሎስም፣ “እያለቀሳችሁ ልቤን የምትሰብሩት ምን ማድረጋችሁ ነው? እኔኮ መታሰር ብቻ ሳይሆን፣ ለጌታችን ለኢየሱስ ስም በኢየሩሳሌም ለመሞት ዝግጁ ነኝ” ብሎ መለሰ። 14 ጳውሎስ ምክር ለመቀበል እንዳልፈለገ በተረዳን ጊዜ፣ “የጌታ ፈቃድ ይሁን” ብለን መለመኑን አቆምን። 15 ከእነዚህ ቀናት በኋላ፣ እኛም የጕዞ ዕቃዎቻችንን ይዘን ወደ ኢየሩሳሌም ወጣን። 16 ደግሞም ከቂሣርያ የነበሩ አንዳንድ ደቀ መዛሙርት ከእኛ ጋራ መጡ። ምናሶን የሚባለውንም ሰው ይዘውት መጡ፤ እርሱም የቆጵሮስ ሰው፣ ወደ ፊት ከእርሱ ጋር እንድንቀመጥ የታሰበ የቀድሞ ደቀ መዝሙር ነበረ። 17 ኢየሩሳሌም በደረስን ጊዜ፣ ወንድሞች በደስታ ተቀበሉን። 18 በማግስቱም ጳውሎስ ከእኛ ጋር ወደ ያዕቆብ ሄደ፤ ሽማግሌዎችም ሁሉ በዚያ ነበሩ። 19 ሰላምታ ካቀረበላቸው በኋላ፣ እግዚአብሔር በእርሱ አገልግሎት አማካይነት በአሕዛብ መካከል የሠራቸውን ነገሮች አንድ በአንድ ዘርዝሮ ነገራቸው። 20 እነርሱም ስለ ሰሙት ነገር እግዚአብሔርን አመሰገኑ፤ እንዲህም አሉት፤ “ወንድም ሆይ፣ ከአይሁድ ያመኑት ስንትና ስንት ሺህ እንደ ሆኑ ታያለህ። ሁላቸውም ሕግን ለመጠበቅ የወሰኑ ናቸው። 21 በአሕዛብ መካከል የሚኖሩት አይሁድ ሁሉ ሙሴን እንዲተዉ እንደምታስተምራቸው፣ ልጆቻቸውንም እንዳይገርዙ እንደምትነግራቸውና በቀድሞው ልማድ እንዳይሄዱ እንደምታደርግ፣ ስለ አንተ ተነግሮአቸዋል። 22 እንግዲህ ምን እናድርግ? መምጣትህን እንደሚሰሙ ርግጠኞች ነን። 23 ስለዚህ አሁን እኛ የምንልህን አድርግ፤ ስለት ያለባቸው አራት ሰዎች እዚህ አሉን። 24 እነዚህን ሰዎች ይዘህ ከእነርሱ ጋር ራስህን አንጻ፤ ጠጕራቸውን ለመላጨት የሚያስፈልጋቸውንም ገንዘብ ክፈልላቸው። በዚህም ስለ አንተ የተነገራቸው ሁሉ ውሸት እንደ ሆነ ያውቃሉ፤ አንተም ልማዱን ጠብቀህ እንደምትኖር ይረዳሉ። 25 ስላመኑ አሕዛብ ግን ለጣዖት ከተሠዋ፣ ከደም፣ ከታነቀ፣ እንዲሁም ከዝሙት ራሳቸውን እንዲጠብቁ ጽፈን ትእዛዝ ሰጥተናል።” 26 ጳውሎስም ሰዎቹን ይዞ በሚቀጥለው ቀን ራሱን ከእነርሱ ጋር እያነጻ ወደ መቅደሱ ገባ፤ ይኸውም መሥዋዕቱ ስለ እያንዳንዳቸው እስከሚቀርብ ድረስ መንጻቱ የሚወስደውን ጊዜ በመንገር ነው። 27 ሰባቱ ቀናት ወደ መገባደዱ ሲቃረቡ፣ ከእስያ የመጡ አንዳንድ አይሁድ ጳውሎስን በቤተ መቅደስ ውስጥ አዩት፤ ሕዝቡንም ሁሉ በእርሱ ላይ አነሣሡ፤ ያዙትም። 28 እንዲህም እያሉ ይጮኹ ነበር፤ “የእስራኤል ሰዎች ሆይ፣ ርዱን። ሰዎችን ሁሉ ከሕዝቡ፣ ከሕጉና ከዚህ ስፍራ ጋር የማይስማሙ ነገሮችን የሚያስተምር ይህ ሰው ነው። ከዚህም በላይ የግሪክን ሰዎች ወደ ቤተ መቅደሱ በማስገባት፣ ይህን ቅዱስ ስፍራ የሚያረክሰውም እርሱ ነው።” 29 ምክንያቱም ቀደም ሲል የኤፌሶኑን ሰው ጥሮፊሞስን ከእርሱ ጋር በከተማ ስላዩት፣ ጳውሎስ ወደ ቤተ መቅደስ ያስገባው መሰላቸው። 30 ከተማውም ሁሉ ታወከ፤ ሕዝቡም በአንድነት ተሰባስበው ጳውሎስን ያዙት፤ ጐትተውም ከቤተ መቅደስ አስወጡት፤ በሮቹም ወዲያው ተዘጉ። 31 ሊገድሉት ሲሞክሩም፣ መላዋ ኢየሩሳሌም እጅግ ታውካለች የሚል ወሬ ወደ ጭፍሮቹ አለቃ ደረሰ። 32 እርሱም ወዲያው ወታደሮችንና የመቶ አለቆችን ይዞ ሕዝቡ ወዳሉበት በሩጫ ወረደ። ሰዎቹም ሻለቃውንና ወታደሮችን ሲያዩ፣ ጳውሎስን መደብደብ አቆሙ። 33 ከዚያም ሻለቃው ወደ ጳውሎስ ሄዶ ያዘው፤ በሁለት ሰንሰለቶች እንዲታሰርም አዘዘ። ስለ ማንነቱና ስለ ፈጸመው ድርጊትም ጠየቀው። 34 ከሕዝቡም ግማሾቹ ስለ አንድ ነገር ሲጮኹ፣ የቀሩት ደግሞ ስለ ሌላ ነገር ይንጫጩ ነበር። ሻለቃውም ከጫጫታው ሁሉ የተነሣ፣ ስለ ምን እንደሚጮኹ እንኳ መለየት አልቻለም፤ ስለዚህ ጳውሎስን ወደ ወታደሮች ምሽግ እንዲያገቡት አዘዘ። 35 ጳውሎስ ወደ መወጣጫው ደረጃ በደረሰ ጊዜ፣ ከሕዝቡ ረብሻ የተነሣ፣ ወታደሮቹ ተሸክመውት ሄዱ። 36 ሕዝቡ “አስወግደው!” እያሉና እየጮኹ ከኋላ ይከተሉ ነበር። 37 ጳውሎስም ወደ ምሽጉ ሊገባ ጥቂት ሲቀረው፣ ሻለቃውን፣ “አንድ ነገር እንድናገርህ ትፈቅድልኛለህ?” አለው። ሻለቃውም፣ “የግሪክ ቋንቋ መናገር ትችላለህ ወይ? 38 አንተ ከዚህ በፊት ዐመፅ አስነሥተህ፣ አራት ሺህ ሰዎችን በማስሸፈት፣ ወደ ምድረ በዳ የገባህ ግብፃዊ አይደለህምን?” አለው። 39 ጳውሎስም፣ “እኔስ በኪልቅያ ከምትገኘው ከጠርሴስ ከተማ የመጣሁ አይሁዳዊ ነኝ፤ የታዋቂዋ ከተማ ዜጋ ነኝ። አንድ ነገር እለምንሃለሁ፤ ለሰዎቹ እንድናገር ፍቀድልኝ” አለው። 40 ሻለቃው በፈቀደለት ጊዜም፣ ጳውሎስ መወጣጫ ደረጃው ላይ ቆሞ፣ በእጁ ወደ ሕዝቡ አመለከተ። ሕዝቡ ጸጥ እረጭ ሲልም፣ በዕብራይስጥ ቋንቋ እንዲህ ብሎ ተናገረ፦
አጠቃላይ መረጃ: ጳውሎስ እና ባልደረባዎቹ ጉዞዋቸውን ቀጥለዋል፡፡ ተከፋፈለን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሉቃስን፣ ጳውሎስን እና ከእነርሱ ጋር ይጓቹ የነበሩትን ሌሎችን ሰዎች ነው፡፡ ቆስ ተብላ ወደምትጠራዋ ከተማ የሚወስደውን መንገድ ይዘን መጓዝ ጀመርን "እኛ በቀጥታ ወደ ቆስ ከተማ የሚትሄደውን መንገድ ይዘን ተጓዝን" ወይም "እኛ በቀጥታ ወደ ቆስ ከተማ አመራን" ቆስ ከተማ ቆስ የግሪክ ደሴት ስትሆን በዘመኗ ቱሪክ በደቡብ ከአጌን ሐይቅ አከባቢ የሚትገኝ ከተማ ናት፡፡ የሩድ ከተማ ሩድ የግሪክ ደሴት ስትሆን በዘመኗ ቱሪክ በደቡብ ከአጌን ሐይቅ አከባቢከቆስ በደቡብ በኩል እና ከቄርጤስ በሰሜን ምስራቅ በኩል የሚትዋሰን ከተማ ናት፡፡ የጳጥራ ከተማ ጳጥራ በዘመናዊዋ ቱርክ ውስጥ ከሚገኘው ከአጌን ሐይቅ በደቡብ ምዕራብ በሜድትራኒያን ባህር አከባቢ የሚትግኝ ከተማ ናት፡፡
መጣን በዚህ ክፍል ውስጥ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሉቃስን፣ ጳውሎስን እና ከእነርሱ ጋር ይጓዙ የነበሩትን ሌሎች ሰዎችን ነው፡፡ ወደ ግራ ትተው ሄድን "ደሴቱን በግራ በኩል ትተን ሄድን" ደቀ መዛሙርቱ በመንፈስ አማካኝነት ለጳውሎስ እንዲህ አሉት "እነዚህ አማኞች ለጳውሎስ እግዚአብሔር የገለጠላቸውን ነገር ነገሩት"
ከእነርሱ ጋር ያሳለፈው ቃናት "ከእነርሱ ተለይቶ የሚሄድበት ጊዜ በደረሰ ጊዜ" እነርሱ ሁሉ በዚህ ሥፍራ “እነርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በጠርሴስ ውስጥ ያሉትን አማኞችን ነው፡፡ እርስ በእርሳቸው ተሰነባበቱ "እርስ በእርሳቸው ተሰነባበቱ"
በጀልባ መጓዛችን ስናጠናቅቅ በዚህ ክፍል ውስጥ “እኛ” የሚለው ቃል ሉቃስን፣ ጳውሎስን እና ከእነርሱ ጋር ይጓዙ የነበሩ ሌሎች ሰዎችን ያጠቃልላል፡፡ ወደ ፓቶሌሚያስ ደረሰን ፓቶሌሚያስ ከጥሮስ በስተደቡብ በሊባኖስ ውስጥ የሚትገኝ ከተማ ናት፡፡ ፓቶሌሚያስ በዘመኑ እስራኤል ውስጥ አካ አከባቢ የሚትገኝ ከተማ ናት፡፡ ከሰባቱ አንዱ በዚህ ሥፍራ ላይ “ሰባት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ምግብ ለማከፋፈል እና ለመበልቶች እገዛ ለማድረግ በ ACT 6:5 ላይ የተመረጡት ሰዎች ይህ ሰው "ፊልጶስ" ይህ ሰው ትንቢት የሚናገሩ አራት ደናግል ሴት ልጆች ነበሩት "አራቱ ደናግላን ሴት ልጆቹ ከእግዚአብሔር መልዕክት ተቀብለው በማስተላለፍ የታወቁ ነበሩ፡፡" ይህ ስለ ፊልጶስ የኃላ ታሪክ ማስረጃ ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ: ይህ በጳውሎስ ታሪክ ውስጥ ከተከናወኑት ነገሮች መካከል ሌላኛው ታሪክ መጀመሪያ ነው፤ ይህ አጋቦስ በተባለ ነቢይ አማካኝነት ስለ የተነገረ ትንቢት ነው፡፡ አንድ ነቢይ ይህ ሰው ብዙ ጊዜ ከእግዚአብሔት መልዕክ እየተቀበለ የሚያስተላልፍ ሰው ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ አጋቦስ ተብሎ የሚጠራ አጋቦስ ከይሁዳ የመጣ ሰው ነው፡፡ የጳውሎስን መታጠቂያ ወስዶ "የጳውሎስን መታጠቂያ ከወገቡ ላይ ፈትቶ" በዚያ አሠረው "የጳውሎስን ቀበቶ ወስዶ አሠረው" አሳልፈው ይሰጡታል "ያሣስሩታል" ወይም "ያስዙታል" ወደ . . . እጅ በዚህ ሥፍራ ላይ “እጅ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ቁጥጥር ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “በሕግ ቁጥጥር ሥር፡፡”
ምን እያደረጋችሁ ነው፣ እያለቀሳችሁ ስለምን ልቤን ትሰብሩታላችሁ? “ጳውሎስ ይህንን ጥያቄ የሚጠይቀው በዚያ የነበሩት አማኞች እርሱን መጎትጎታቸውን እንዲተው ለማድረግ ነው፡፡” የጌታ ፈቃድ ይሁን "አሁን በእየሩሳሌም እግዚአብሔር ለጳውሎስ ያለው ፈቃድ ይሁን ብለን ተቀበልን" ወይም "ጌታ ለጳውሎስ በኢየሩሳሌም ያለው እቅድን ለመቀበል አሁን የተዘጋጀን ሆንን"
=
ሻንጣዎቻችንን አንስተን በዚህ ሥፍራ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሉቃስን፣ ጳውሎስን እና ሌሎች ከእነርሱ ጋር እየተጓዙ ያሉ ሰዎችን ነው፡፡ ከእነርሱ ጋር ይዘው መጡ በዚህ ስፍራ ላይ “እነርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ከቄሳሪያ የመጡትን ደቀ መዛሙርት ነው፡፡ ምናሶን፣ የቆጵሮስ ሰው ነውson, a man from Cyprus ምናሶን ከቆጵሮስ ደሰት የመጣ ሰው ነው፡፡
አጠቃላይ መረጃ: ጳውሎስ እና ከእርሱ ጋር ይጓዙ የነበሩት ሰዎች ወደ እየሩሳሌም ደረሱ፡፡ ወንድሞች መልካም አቀባበል አደረጉላቸው ታላቁ ስደት ከተነሣ በኋላ በኢየሩሳሌም የቆዩ ወንዶች እና ሴቶች አይሁድ አማኞች ነበሩ፡፡ ሠላምታ ከተለዋወጠ በኋላ ሰለሆነው ነገር ይነግራቸው ጀመር "ጳውሎስ ሽማግሌዎቹን ሠላም ካለ በኋላ ስለሆነው ነገር ይነግራቸው ጀመር" ወይም "ሽማግሌዎቹን ሰሰላም ካለ በኋላ ስለሆነው ነገር ይነግራቸው ጀመር" እግዚአብሔር ስላደረገው ነገር አንድ በአንድ ነገራቸው አማራጭ ትርጉም፡ "ጳውሎስ እግዚአብሔር ስላደረጋቸው ነገሮች በጥልቀት ነገራቸው" አገልሎቱን "የጳውሎስን አገልግሎት"
አጠቃላይ መረጃ: በኢየሩሳለሉም ያሉ ሽማግሌዎች ለጳውሎስ ምላሽ መስጠት ጀመሩ፡፡ ይህንን በሰሙ ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገኑ እና እንዲህ አሉት "ሽማግሌዎቹ ከሰሙት በኋላ እግዚአብሔርን አመሰገኑ እንዲሁም ለጳውሎስ እንዲህ አሉት፣" ሁሉም እንዲህ ብለው ወሰኑ "አይሁድ አማኞች ሁሉ ወሰኑ" እንዲህ ተብሎ ተነግሯቸዋል አማራጭ ትርጉም: "ሰዎች ለአይሁዳዊያን አማኞች እንዲህ ብለው ነግረዋቸዋል" እንዲህ ብለህ ንገራቸው "ለአይሁዶች እንዲህ ብለህ ንገራቸው"
ምን ማድረግ አለብን? በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሽማግላቹን ና፡፡ የተማማሉ አራት ወንዶች ይህ ለተወሰነ ጊዜ ድረስ አልኮል መጠጥ ላለመጠጣት ወይም ጸጉራቸውን ለመላጨት የሚደረግ መሃላ ና፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ ለእግዚአብሔር የተሳሉ አራት ወንዶች፡፡" ለእነርሱ ወጪ አስፈላጊውን ነገር መክፍል ክፍያ የሚፈጸመው ወንድ እና ሴት ጠቦቶችን፣ ጥራጥሬዎችን እና የመጠጥ መስዋእት ለመግዛት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "የሚያስፈልጋቸውን ነገር ሁሉ ለመክፈል፡፡" ሕግን መከተል "ከሙሴን ሕግ እና ከሌሎች አይሁዳዊያን ሕግጋት ጋር የሚስማማ ሕይወትን መምራት"
አያያዥ ዓረፍ ነገር: በኢየሩሳሌም የነበሩት ሽማግሌዎች ለጳውሎስ ምላሽ መስጠትን ጨረሱ፡፡ እንዲህ ብለን ጻፍን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሽማግሌዎችን ነው፡፡ ታንቆ ከሞተ "ሳይታረደ የሞተን እንስሳ ለምግበት ከመጠመቀም" ራሱን ከእነርሱ ጋር ያንጻ ወደ ቤተ መቅዱስ አከባቢ አይሁዳዊያን የመነጻት ሥርዓትን ይፈጽማሉ፡፡ይህ የመንጻት ሥርዓት አይሁዳዊያን ከአሕዛብ ጋር ከመገናኘት ጋር የተገናኘ ነው፡፡ የመንጻት ቀን ይህ የመንጻት ሥርዓት ወደ መቅደሱ አከባቢ ከሚደረገው የመንጻር ሥርዓት የተለየ ነው፡፡ መስዋእት እስኪሰጥ ድረስ "እንስሳትን ለመስዋእትነት ከማቅረባቸው በፊት"
አጠቃላይ መረጃ: ይህ የጳውሎስን እስራት አስመልክቶ ያለው ታሪክ ጅማሬ ነው፡፡ በቁጥር 29 ከኢስያ ስለመጡት አይሁዳዊያን የኃላ ታሪክ መረጃ ይሰጠናል፡፡ ሕዝቡ ሁሉ ደስ ተሰኘ "ብዙ ሕዝብ እንዲያምጽ አደረገ" እጃቸውን ጫኑበት "ያዙት" ከዚህ በተጨማሪ ግሪኮችን ወደ ቤተ መቅዱስ አመጣቸው ወደ ኢየሩሳሌም ቤተ መቅዱስ የውስጠኛው ክፍል መግባት የሚችለው አይሁዳዊይ ወንዶች ብቻ ናቸው፡፡ ጥሮፊሞስ ይህ ጳውሎስ ለአይሁዳዊያን ብቻ ወደ ተከለከለው የመቅደሱ ውስጠኛው ክፍል ይዞት ገብቷል የተባለው የግሪክ ሰው ነው፡፡
ከተማይቱ በአጠቃላይ ታወከች በዚህ ሥፍራ ላይ “ሁሉ” የሚለው ቃል ግነት ሲሆን አለማውም አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ “ከተማ” የሚለው ቃል በከተማይ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “በከተማይቱ ውስጥ የነበሩ ብዙ ሰዎች በጳውሎስ ላይ ተቆጡ፡፡" የመዝጊያው በር ወዲያ ተዘጋ ሕዝቡ ጳውሎስን ጎትተው ካስወጡት በኋላ ጳውሎስን በእንግድነት የተቀበለው ሰው በሩን በፍጥነት ከኋላው ዘጋው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "አይሁዳዊያን የቤተ መቅደሱን በር በፍጥነት ዘጉት፡፡" ዋናው አለቃ የወታደሮች አለቃ ወይም የስድስት መቶ ወታደሮች አለቃ ኢየሩሳሌም በአጠቃላይ ታወከች በዚህ ሥፍራ ላይ “ኢየሩሳሌም” የሚለው ቃቃ በኢየሩሳሌም ውሰጥ የሚኖሩ ሰዎችን ያመለክታል፡፡ “ሁሉም” የሚለው ቃል ግነት የሞላበት ሲሆን ብዙ ሕዝብ በሁኔታውን እንደ ተበሳጨ ለማሳየት የዋለ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በኢየሩሳሌም ውስጥ ያሉት ብዙ ሰዎች ከተማይቱን አወኩ፡፡"
ወዲያው ወሰዱት "ወዲያው አለቃው ወሰደው" በፍጥነት በፍጥነት ወደ ችሎት ወሰዱት፡፡ ዋናው አለቃ የወታደሮች አለቃ ወይም የ600 ወታደሮች መሪ ጳውሎስን ይዞ "ጳውሎስን ይዞ" ወይም "ጳውሎስን አሠረው"
አለቃው የወታደሮች አለቃ ወይም የ600 ወታደሮች መሪ የወታደር ካምፕ ለወታደራዊ ግልጋሎት የሚውል እና በወታደሮች ከፍተኛ ጥበቃ የሚደረግለት ሕንጻ ነው፡፡ ወደ ደረጃው በደረሰ ጊዜ ተሸከሙት አማራጭ ትርጉም፡ "ጳውሎስ ወደ ደረጃዎቹ በደረሰ ጊዜ ወታደሮቹ ተሸከሙት" አስወግዱት ሕዝቡም በጩኸት እና ግልጽ ባልሆነ ቋንቋ ጳውሎስ እንዲገደል ይወተውቱ ነበር፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እንዲሞት፡፡"
ጳውሎስ ሊቀርብ ሲል አማራጭ ትርጉም: "ወታደሮቹ ጳውሎስን ለማቅረብ ዝግጅታቸው ስያጠናቅቁ" የወታደሮች ካምፕ ይህንን በ ACT 21:34 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ዋናው አለቃ የወታደሮች አለቃ ወይም የስድስት መቶ ወታደሮች አለቃ የግሪክ ቋንቋ ትናገራለህን? አንተ በእኛ ላይ አምጾ አራት ሺህ አሸባሪዎችን ይዞ ወደ በረሃው የገባው ግብጻዊው ሰው አይደለህምን? የወታደሮች አለቃ ይህንን ጥያቄ የጠየቀው ጳውሎስ ነው ብሎ ያሰበው ሰው አለመሆኑን በተረዳ ጊዜ መገረሙን ለመግለጽ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "የግሪክ ቋንቋ መናገር ትችላለህ እንዲያውም አራት ሺህ አሸባሪዎችን ይዞ ወደ በረሃ የገባው ሰው ነህ፡፡" አንተ ግብጻዊው ሰው አይደለህምን ጳውሎስ ወደዚያ አከባቢ ከመሄዱ ጥቂት ጊዜ በፊት ከግብጽ ምድር የመጣ አንድ ስሙ የማይታወቅ ሰው በኢየሩሰሌም ውስጥ በሮማዊያን ላይ ሰዎች እንዲያምጹ አድርጓል፡፡ ከዚያም “ወደ ምድረበዳ አምልጦ ሄዷል”፡፡ ስለዚህም ይህ የወታደሮች አለቃ ጳውሎስ ይህ ሰው ይሆን እንደሆነ አስቧል፡፡ አራት ሺህ አሸባሪዎችን "ከእነርሱ ጋር የማይስማሙ ሰዎችን ሁሉ የሚገድሉ አራት ሺህ ወንዶች"
እጠይቅሃለሁ "እለምንሃለሁ" ወይም "እኔ አንተን እጠይቃለሁ" ፍቀድልኝ "እባክህ ፍቀድልኝ" ወይም “እባክህ ፈቃድ ስጠኝ" አለቃ “የወታደሮች አለቃ ወይም የስድስት መቶ ወታደሮች አለቃ” ጳውሎስ በደረጃዎቹ ላይ ቆሞ በዚህ ሥፍራ ላይ “ደረጃ” የሚለው ቃል ወደ ወታደሮች ካንፕ መውጫ ደረጃዎችን የሚያመለክት ነው፡፡
1 “ወንድሞችና አባቶች ሆይ፣ አሁን ስለ ራሴ ለእናንተ የማቀርበውን መከላከያ አድምጡኝ።” 2 ሕዝቡም ጳውሎስ በዕብራይስጥ ቋንቋ ሲያናግራቸው በሰሙ ጊዜ፣ ጸጥ አሉ። ጳውሎስም ንግግሩን በመቀጠል እንዲህ አለ፤ 3 “እኔ በኪልቅያዋ ጠርሴስ የተወለድሁ አይሁዳዊ ነኝ፤ የተማርሁትም በዚሁ ከተማ በገማልያል እግር ሥር ተቀምጬ ነው። የአባቶቻችንንም ጥብቅ የሕግ መንገድ በሚገባ ተምሬአለሁ። ዛሬ እናንተ ሁላችሁ እንደ ሆናችሁት፣ እኔም ለእግዚአብሔር ቀናተኛ ነኝ። 4 ይህን መንገድ እስከ ሞት አሳድጄዋለሁ፤ ሴቶችንና ወንዶችን አስሬ ለወኅኒ አሳልፌ ሰጠኋቸው። 5 ደግሞም ከእነርሱ ደብዳቤ ተቀብዬ፣ በደማስቆ ስለሚገኙ ወንድሞች ወደዚያ ለመጓዝ እንደ ተነሣሁ፣ ሊቀ ካህናቱና ሽማግሌዎች ሁሉ መመስከር ይችላሉ። ከዚያ መንገድ የሆኑትን አስሬ ወደ ኢየሩሳሌም ለመምጣትና ለማስቀጣት ስንቀሳቀስም ነበር። 6 እየተጓዝሁ ወደ ደማስቆ ስቃረብ፣ ቀትር ላይ ድንገት ታላቅ ብርሃን ከሰማይ በዙሪያዬ በራ፤ 7 እኔም መሬት ላይ ወደቅሁ፤ ከዚያም፣ 'ሳውል፣ ሳውል፣ ለምን ታሳድደኛለህ?' የሚለኝን ድምፅ ሰማሁ። 8 እኔም፣ 'ጌታ ሆይ፣ አንተ ማን ነህ?' ብዬ መለስሁለት። እርሱም፣ 'አንተ የምታሳድደኝ፣ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ' አለኝ። 9 ከእኔ ጋር የነበሩትም ብርሃኑን አዩ፤ ነገር ግን የተናገረኝን ድምፅ አልሰሙም። 10 እኔም፣ ‘ጌታ ሆይ፣ ምን ላድረግ?’ አልሁ። ጌታም፣ ‘ተነሥና ወደ ደማስቆ ሂድ፤ ማድረግ የሚገባህን ሁሉ እዚያ ይነግሩሃል’ አለኝ። 11 ከዚያ ብርሃን ድምቀት የተነሣም አንዳች ማየት አልቻልሁም፤ ስለዚህ ከእኔ ጋር በነበሩት ሰዎች እጅ እየተመራሁ ወደ ደማስቆ ገባሁ። 12 ለሕጉ በትጋት የሚታዘዝና በዚያ የሚኖሩ አይሁድ ሁሉ መልካምነቱን የመሰከሩለት፣ ሐናንያ የሚባል አንድ ሰው አገኘሁ። 13 እርሱም ወደ እኔ መጥቶ አጠገቤ በመቆም፣ ‘ወንድሜ ሳውል፣ ዐይንህን ገልጠህ እይ’ አለኝ። እኔም በዚያው ቅጽበት አየሁት። 14 እርሱም እንዲህ አለኝ፤ ‘ቅዱሱን እንድታይና ከገዛ አፉ የሚወጣውን ድምፅ እንድትሰማ፣ የአባቶቻችን አምላክ ፈቃዱን እንድታውቅ መርጦሃል፤ 15 ምክንያቱም ስለ አየኸውና ስለ ሰማኸው ነገር ለሰዎች ሁሉ ምስክር ትሆንለታለህ። 16 ስለዚህ አሁን ለምን ታመነታለህ? ተነሥ፤ ስሙን እየጠራህ ተጠመቅና ከኃጢአትህ ታጠብ።’ 17 ወደ ኢየሩሳሌም ከተመለስሁ በኋላም፣ በቤተ መቅደስ እየጸለይሁ ሳለሁ፣ ሸለብ አድርጎኝ ሰመመን ውስጥ ገባሁ። 18 እርሱም፣ ‘ከኢየሩሳሌም ቶሎ ብለህ ውጣ፤ ምክንያቱም ስለ እኔ የምትናገረውን ምስክርነትህን አይቀበሉህም’ ሲለኝ አየሁ። 19 እኔም እንዲህ አልሁ፤ ‘ጌታ ሆይ፣ በምኵራብ ሁሉ በአንተ ያመኑትን ሳስርና ስደበድብ እንደ ነበርሁ እነርሱ ራሳቸው ያውቃሉ። 20 የሰማዕትህን የእስጢፋኖስንም ደም በሚያፈሱበት ጊዜ፣ በመስማማት እዚያው ቆሜ ነበር፤ የገዳዮቹንም ልብሶች እጠብቅ ነበር።’ 21 እርሱ ግን፣ ‘ተነሥተህ ሂድ፤ ምክንያቱም ወደ አሕዛብ እልክሃለሁ’ አለኝ።” 22 ሕዝቡም እስከዚህ ድረስ እንዲናገር ፈቀዱለት፤ ከዚህ በኋላ ግን፣ “እንደዚህ ያለ ሰው ከምድር ይወገድ፤ በሕይወትም ይኖር ዘንድ አይገባውም” እያሉ ይጮኹ ጀመር። 23 እየጮኹም ሳለ፣ ልብሳቸውን እያወለቁና አቧራም ወደ ላይ ይበትኑ ነበር፤ 24 ሻለቃውም ጳውሎስን ወደ ወታደራዊው ምሽግ እንዲወስዱት አዘዘ። እርሱ ራሱ ሕዝቡ ለምን እንደዚያ እንደ ጮኹበት ለማወቅ ስለ ፈለገ፣ እየገረፉ ጳውሎስን እንዲመረምሩት ትእዛዝ ሰጠ። 25 ሰዎቹ በጠፍር ወጥረው ባሰሩት ጊዜ፣ ጳውሎስ በአጠገቡ የቆመውን መቶ አለቃ፣ “ሮማዊ የሆነን ሰው፣ ገና ሳይፈረድበት እንዲህ መግረፍህ ሕጋዊ ነው ወይ?” አለው። 26 መቶ አለቃውም ይህን ሲሰማ፣ ወደ ሻለቃው ሄዶ፣ “ምን ማድረግህ ነው? ሰውየውኮ የሮማ ዜጋ ነው” በማለት ነገረው። 27 ሻለቃውም መጥቶ፣ “አንተ የሮማ ዜጋ ነህን? እስቲ ንገረኝ” አለው። ጳውሎስም፣ “አዎ፣ ነኝ” አለ። 28 ሻለቃውም፣ “እኔኮ ይህን ዜግነት ያገኘሁት በብዙ ገንዘብ ነው” ብሎ መለሰለት። ጳውሎስም፣ “እኔ ግን ከመወለዴ ጀምሮ ሮማዊ ነኝ” አለ። 29 ሊመረምሩት የመጡ ሰዎችም ወዲያው ትተውት ሄዱ። ሻለቃውም ጳውሎስ የሮም ዜጋ መሆኑን ባወቀ ጊዜ ፈራ፤ ምክንያቱም ጳውሎስን አሳስሮት ነበር። 30 በማግስቱም ሻለቃው፣ አይሁድ ጳውሎስን የከሰሱበትን ትክክለኛ ምክንያት ለማወቅ ፈለገ። ስለዚህ ጳውሎስን ከእስራት አስፈታውና የካህናት አለቆችና ሸንጎው በሙሉ እንዲሰበሰቡ አዘዘ። ከዚያም ጳውሎስን አስመጥቶ በመካከላቸው አቆመው።
አጠቃላይ መረጃ: ጳውሎስ በኢየሩሳሌም ውስጥ ለተሰበሰበው ሕዝብ መናገር ጀመረ፡፡ በቁጥር 2 ላይ ጳውሎስ እየጠናገረ ሳይሆን የኃላ ታሪክ መረጃ እየተሰጠ ነው፡፡ ወንድሞች እና አባቶች ይህ በጳውሎስ እድሜ ላይ ላሉ ሰዎች እንዲሁም ከእርሱ እድሜ በላይ የሆኑ ሰዎችን በትህትና መናገር ነው፡፡ የመከራከሪያ ሀሳቤን አድምጡኝ "እባካቸሁ የመከራከሪያ ሀሳቤን አድምጡ" ይህንንም አሁን አቀርብላችኋለሁ "አሁን እኔ ለእናንተ አቀረባለሁ" በዕብራይስጥ ቋንቋ "በእነርሱ የዕብራይስጥ ቋንቋ"
በዚህች ከተማ በገማሊያ እግር ሥር ሆኜ ተምሬያለሁ "በዚሁ በኢየሩሳሌም ውስጥ ገማሊያ በተባለው መምህር ተማሪ ነበርኩኝ" የቀደምት አባቶቻችን ሕግ በደንብ እከተል ዘንድ በደንብ ተምሬያለሁ አማራጭ ትርጉም: "እነርሱ የአባቶቻችን ሕግ መከተል እችል ዘንድ በሚገባ አስተምረውኛል" ወይም "የተማሪኩት ትምህርትም የአባቶቻችን ሕግጋት በትክክል መከተል እንዲችል ነው" ለእግዚአብሔር የቀናው ነኝ "የእግዚአብሔር ፈቃድ እንደሆነ የማምነውን ነገር የማደርገው ከልቤ ነው" ወይም "እኔ ለእግዚአብሔር የማደርገውን አገልግሎት የማደርገው በሙሉ ልቤ ነው" ዛሬ እናንተ ሁላችሁ እንደሚታደረጉት ጳውሎስ ራሱን ከሕዝቡ ጋር በማነጻጸር፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እናንተ ሁላችሁ ዛሬ እንደሚታደርጉት" ወይም "ዛሬ እንደሚታደረጉት ሁሉ፡፡" በዚህ መልኩ በዚህ ሥፍራ ላይ “መልኩ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በኢየሩሳሌው ውስጥ በአንድ ሥፍራ የተሰበሰቡትን አማኞችን ነው፡፡ ይህንን በ ACT 9:2 ምን ብለህ እንደተረጎምህ ተመልከት፡፡ ለመግደል ይህንን መንገድ የሚከተሉ ሰዎች ለመግደል ጳውሎስ ፈቃደኛ ነበር፡፡ ምስክር በመሆን "በመመስከር" ወይም "ምስክር በመሆን" ከእርሱ ደብዳቤ ተቀብዬ ነበር "ከሊቀ ካህናት እና ሽማግሌዎች ደብዳቤ ተቀብዬ ነበር" አሥሬ አመጣቸው ዘንድ ትዕዛዝን ተቀብዬለሁ አመራጭ ትርጉም: "በሠንሰለት አስሬ አመጣቸው ዘንድ ትዕዛዝ ሰጥተውኝ ነበር"
እንዲህ ሆነ ጳውሎስ ይህንን መንገድ መከተል ከመጀመሩ በፊት የሆነውን ነገር ነከመናገር በደማስቆስ መንገድ ላይ ጌታ እንዴት እንደጠራው ወደ መናገር ያደረገውን ሽግግር ያሳይለት ዘንድ ይህንን ሀረግ ተጠቅሟል፡፡
የእርሱ ድምፅ "የኢየሱስ ድምፅ" ከብርሃኑ ድምቀት የተነሳ ማየት እንኳ አልቻልኩም "ከብርሃኑ ድምቀት የተነሣ ከሌሎች ሁሉ ወደኋላ ቀረው"
እንደ ሕጉ ከሆነ እኔ ከሌሎች ሁሉ ይልቅ የተሰጠሁ ነበርኩ አናኒያስ የእግዚአብሔር ሕግ በመጠበቅ ረገድ በጣም ጥንቁቅ ነበር፡፡ የተመሠከረለት ነበር "በሌሎች ዘንድ ጥሩ ስም ነበረው" በተመሳሳይ ሰዓት ይህ ወዲያው የሆነን ነገር ለመግለጽ ጥቅም ላይ የሚለው የተለመደ መንገድ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በዚያው ወቅት" ወይም "ወዲያውም፡፡"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ የገዛ ታሪኩን እየተናገረ አናንያስ የተናረወን ነገር መናገሩን ቀጥሏል፡፡ ይህ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም ለነበሩተ ሰዎች ያደረገው ንግግር ነው፡፡ ከዚያም እንዲህ አለ "ከዚያም አናናስ እንዲህ አለ" የእርሱ ፈቃድ "እግዚአብሔር ያቀደው እና እንዲሆን ያደረገውን ነገር" ምን ትጠብቃለህ? ይህ ጥያቄ ጳውሎስ እንዲጠመቅ ለማበረታታት የቀረበ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ብዙ አትጠብቅ!" ወይም "ብዙ አትዘገይ!" ኃጢአትን ታጠብ ልክ ሰውነትን በመታጠብ በሰውነት ላይ ያለን ቆሻሻ እንደሚናስወግድ ሁሉ የኃጢአት ይቅርታን ለማግኘት የኢየሱስን ስም መጥራት የሰውን ውስጥ ከኃጢአት ያነጻል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "የኃጢአት ይቅርታን ለማግኘት መጠየቅ፡፡"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ለተሰበሰበው ሕዝብ ስለተመለከተው የኢየሱስ ራዕይ መናገር ጀመረ፡፡ ራዕይ ተሰጠኝ "ራዕይ ተገለጠልኝ" ወይም "እግዚአብሔር ለእኔ ራዕይ ሰጠኝ" እንዲህ ሲለኝ አየሁት "እንዲህ ስለኝ ኢየሱስን አየሁት" አልተቀበሉትም "በኢየሩሳሌም ያሉት አልተቀበሉትም"
አያያዥ ዓረፈተ ነገር: በዚህ ክፍል ውስጥ ጳውሎስ ኢየሱስን በራዕይ መመልከቱን መተረኩን ያበቃል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ይህ ንግግሩ በኢየሩሳሌም ለነበሩት የእርሱን ንግግር ተሰብስበው ያደምጡ ለነበሩት ሰዎች ያደረገው ንግግር ማብቂያም ነው፡፡ እነርሱ ራሳቸው ያውቁታል ይህ የሚያመለክተው በኢየሩሳሌም የነበሩትን የማያምኑ አይሁዳዊያንን ነው፡፡ "በግርፋት ቀጥተው ሊለቁት አሰቡ" በሁሉም ምኩራቦች ውስጥ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም ዙሪያ ባሉ ምኩራቦች ውስጥ የሚሳተፍ ማንኛውንም የአይሁድ አማኝ ይፈልግ ነበር፡፡ የእስጥፋኖስ ደም . . . በእርሱ ላይ ተረጭቶ ነበር ይህ የአነጋገር ዘይቤ ጥቅም ላይ የሚውለው አንድ ሰው ተገደለ ብሎ ለመግለጽ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እስጥፋኖስን ገደሉት፡፡"
እንደዚህ ያለውን ሰው ከምድር አስወግደው፥ "ግደለው" ይህንን ስያደርጉ ሳሉ "ይህንን ስያደርጉ ሳሉ" (UDB.) ይህ ቃል በተመሰሳይ ሰዓት የሆኑ ሁለት ነገሮችን የሚያሳይ ነው፡፡ ጳውሎስን ይዘው እንዲመጡ አዘዙ አማራጭ ትርጉም፡ "ጳውሎስን ይዘውት ይመጡ ዘንድ ወታደሮቹን አዘዘ" የወታደሮች ካምፕ ይህንን በ ACT 21:34 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ "አዛዡ እራሱ"
መግረፊያ አለንጋ፡፡ ሮማዊ እና በሕግ ቅጣት ያልተጣለበትን ሰው መግረፍ በሕግ ተፈቅዷልን? ይህ ጥያቄ ጥቅም ላይ የዋለው የመቶ አለቃው ጳውሎስን ለመግረፍ ምን ስልጣን እንዳለው ለመጠየቅ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ሮማዊ የሆነን እና ያልተፈረደበትን ሰው ለመግረፍ ምንም ስልጣን የለህም!" ምን ለማድረግ አስበሃል? አዛዡ ጳውሎስን ለመግረፍ የነበረውን እቅድ እደገና እንዲያስብበት የቀረበ ጥያቄ ነው፡፡ "ይህንን ማድረግ የለብህም!"
እንዲህ አለው "ለጳውሎስ ሂድ አለው" የተገኘ ዜግነት "ዜግነት ያገኘሁ" ወይም "ዜጋ የሆንኩ" የተወለድኩት ሮማዊ ሆኜ ነው "የተወለድኩት የሮም ዜግነት ካላቸው ቤተሰብ ነው፤ ስለዚህም የሮም ዜግነት ያገኘኹት በውልደት ነው፡፡" ይህንን ሊያደረግ የነበረው ሰው "ይህንን ለማድረግ ያቀደው ሰው" ወይም "ይህንን ለማድረግ እየተዘጋጀ ያለው ሰው"
ዋናው አዛዥ የስድስት መቶ ወታደሮች አለቃ ጳውሎስን ይዞት ወረደ ከወታደሮች ካምፕ ወደ ቤተ መቅደሱ የፍርድ አደባባይ ወደ ታች የሚወርድ ቀጥተኛ የሆነ መንገድ አለ፡፡
1 ጳውሎስም ትኵር አድርጎ ወደ ሸንጎው በመመልከት፣ “ወንድሞች ሆይ፣ እኔ እስካሁን ድረስ፣ በእግዚአብሔር ፊት በንጹሕ ኅሊና ሁሉ ኖሬአለሁ” አለ። 2 ሊቀ ካህናቱ ሐናንያም ጳውሎስ አጠገብ የነበሩትን ሰዎች አፉን እንዲመቱት አዘዛቸው። 3 በዚህ ጊዜ ጳውሎስ፣ “አንተ ነጭ ቀለም የተቀባህ ግድግዳ፣ እግዚአብሔር ይመታሃል። በሕጉ መሠረት ልትፈርድብኝ የተቀመጥህ፣ ሕጉን ጥሰህ እኔ እንድመታ ታዛለህን?” አለው። 4 በአጠገቡ ቆመው የነበሩትም፣ “የእግዚአብሔርን ሊቀ ካህናት እንዴት ትሰድባለህ?” አሉ። 5 ጳውሎስም፣ “ወንድሞች ሆይ፣ ሊቀ ካህናት መሆኑን አላወቅሁም፤ ምክንያቱም፣ በሕዝብህ አለቃ ላይ ክፉ ቃል ከአፍህ አይውጣ ተብሎ ተጽፎአል።” 6 ጳውሎስም ከሸንጎው አባላት ከፊሉ ሰዱቃውያን፣ ሌሎቹም ፈሪሳውያን መሆናቸውን ሲያይ፣ በሸንጎ መካከል ሆኖ በከፍተኛ ድምፅ፣ “ወንድሞች ሆይ፣ እኔ የፈሪሳዊ ልጅ የሆንሁ፣ ፈሪሳዊ ነኝ። ፍርድ ፊት የቀረብሁትም የሙታን ትንሣኤ እንዳለ ስለማምን ነው” አላቸው። 7 ይህን በተናገረ ጊዜ፣ በፈሪሳውያንና በሰዱቃውያን መካከል ክርክር ተነሣ፤ ጉባኤውም ተከፋፈለ። 8 ምክንያቱም ሰዱቃውያን ትንሣኤ ሙታን የለም፤ መላእክትም የሉም፤ መናፍስትም የሉም ስለሚሉና፣ ፈሪሳውያን ግን እነዚህ ሁሉ አሉ ስለሚሉ ነው። 9 በዚህ ጊዜ፣ ታላቅ ውካታ ሆነ፤ ከፈሪሳውያን ወገን የሆኑ አንዳንድ ጸሐፍትም ተነሥተው፣ “በዚህ ሰው ላይ አንድም ጥፋት አላገኘንም፤ መንፈስ ወይም መልአክ ተናግሮት እንደ ሆነስ ማን ያውቃል?” በማለት ተከራከሩ። 10 ክርክሩም እየጋለ ሲሄድ፣ ጳውሎስን ይዘው እንዳይቦጫጭቁት ሻለቃው ፈራ፤ ስለዚህ ወታደሮቹ ወርደው ጳውሎስን በኀይል ይዘው ከሸንጎ አባላት መካከል እንዲወስዱትና ወደ ምሽጉ አምጥተው እንዲያስገቡት አዘዘ። 11 በሚቀጥለውም ሌሊት ጌታ በጳውሎስ አጠገብ ቆሞ፣ “አትፍራ፤ በኢየሩሳሌም ስለ እኔ እንደ መሰከርኸው፣ በሮማም ደግሞ ልትመሰክር ይገባሃል” አለው። 12 በነጋም ጊዜ፣ አንዳንድ አይሁድ ጳውሎስን ሳንገድል እኽል ውሃ አንቀምስም በማለት በመሐላ ተስማሙ። 13 ይህን የዶለቱትም ሰዎች ቍጥር ከአርባ በላይ ነበር። 14 ወደ ካህናት አለቆችና ወደ ሽማግሌዎችም ሄደው እንዲህ አሉ፤ “ጳውሎስን እስከምንገድል ድረስ፣ እኽል እንዳንቀምስ በታላቅ ርግማን ተማምለናል። 15 ስለዚህ አሁን ሻለቃው ጳውሎስን ወደ እናንተ እንዲያወርደውና እናንተ የእርሱን ጉዳይ ይበልጥ በትክክል እንደምታዩለት አስመስላችሁ፣ ሸንጎው ለሻለቃው ያመልክት። በእኛ በኩል ግን እዚህ ከመምጣቱ በፊትም ቢሆን ልንገድለው ዝግጁ ነን።” 16 የጳውሎስ እኅት ወንድ ልጅም ጳውሎስን አድፍጠው እንደሚጠብቁት ዐወቀ፤ ሄዶም ወደ ምሽጉ ገብቶ ለጳውሎስ ነገረው። 17 ጳውሎስም አንዱን መቶ አለቃ ጠራና፣ “ይህን ወጣት ወደ ሻለቃው ውሰደው፤ የሚናገረው ነገር አለውና” አለ። 18 መቶ አለቃውም ወጣቱን ይዞ ወደ ሻለቃው አመጣውና እንዲህ አለ፤ “ጳውሎስ የተባለው እስረኛ ወደ ራሱ ጠርቶኝ፣ ይህን ወጣት ወደ አንተ እንዳቀርበው ለመነኝ፤ ወጣቱ ለአንተ የሚነግርህ ነገር አለው።” 19 ሻለቃውም እጁን ይዞ ወደ አንድ ገለልተኛ ስፍራ ወስዶት፣ “ልትነግረኝ የፈለግኸው ነገር ምንድን ነው?” ብሎ ጠየቀው። 20 ወጣቱም እንዲህ አለ፤ “አይሁድ ስለ ጉዳዩ ትክክለኛነት ይበልጥ ለመረዳት የፈለጉ አስመስለው፣ ነገ ጳውሎስን ወደ ሸንጎው እንድታወርደው አንተን ለመለመን ተስማምተዋል። 21 ነገር ግን እሺ አትበላቸው፤ ምክንያቱም ከአርባ በላይ የሚሆኑ ሰዎች አድፍጠው እየጠበቁት ነው። ጳውሎስን ካልገደሉም እኽል ውሃ እንደማይቀምሱ ተማምለዋል። አሁንም እንኳ የአንተን መስማማት እየጠበቁ ነው እንጂ ዝግጁ ናቸው።” 22 ስለዚህ ሻለቃው ወጣቱን ልጅ፣ “ስለ እነዚህ ነገሮች ለእኔ መግለጥህን ለማንም እንዳትናገር” ብሎ ካስጠነቀቀው በኋላ፣ አሰናበተው። 23 ከመቶ አለቆቹም ሁለቱን ወደ ራሱ ጠርቶ፣ “እስከ ቄሣርያ ለመሄድ የሚችሉ ሁለት መቶ ወታደሮችን፣ ሰባ ፈረሰኞችንና ሁለት መቶ ባለ ጦሮችን አዘጋጁ፤ ከሌሊቱም በሦስተኛው ሰዓት ትንቀሳቀሳላችሁ” አላቸው። 24 ጳውሎስ ወደ ሀገረ ገዡ፣ ወደ ፊልክስ የሚሄድበትንም ከብት እንዲያዘጋጁና በሰላም እንዲያደርሱት አዘዛቸው። 25 ከዚያም እንዲህ የሚል ደብዳቤ ጻፈ፤ 26 “ከቀላውዴዎስ ሉስዮስ፣ ወደ ተከበረው ሀገረ ገዢ ፊልክስ፤ ሰላም ለአንተ ይሁን። 27 ይህን ሰው አይሁድ ይዘው ሊገድሉት ሲሉ፣ ከወታደሮች ጋር ደርሼባቸው አዳንሁት፤ ይህን ያደረግሁትም ሮማዊ ዜጋ መሆኑን ስለ ተረዳሁ ነው። 28 ለምን እንደ ከሰሱት ለማወቅ ስለ ፈለግሁም፣ ወደ ሸንጎአቸው ይዤው ወረድሁ። 29 የገዛ ራሳቸውን ሕግ በሚመለከት በተነሣ ጥያቄ ምክንያት ተከሶ እንጂ፣ ሞት ወይም እስራት የሚገባው ክስ እንደሌለበት ዐውቄአለሁ። 30 በዚህ ሰው ላይ ሤራ እንደ ተካሄደበትም ደርሼበታለሁ፤ ስለዚህም ፈጥኜ ወደ አንተ ላክሁት፤ ከሳሾቹም በእርሱ ላይ ያላቸውን ክስ አንተ ባለህበት እንዲያቀርቡ መመሪያ ሰጥቻቸዋለሁ። በደኅና ሰንብት።” 31 ስለዚህ ወታደሮቹ በታዘዙት መሠረት፣ ጳውሎስን ይዘው በሌሊት ወደ አንቲጳጥሪስ ወሰዱት። 32 በሚቀጥለውም ቀን፣ አብዛኞቹ ወታደሮች ፈረሰኞቹን ከእርሱ ጋር እንዲሄዱ ትተው፣ ወደ ምሽግ ተመለሱ። 33 ፈረሰኞቹም ቂሣርያ በደረሱና ደብዳቤውን ለሀገር ገዡ ሲሰጡ፣ ጳውሎስንም ለእርሱ አስረከቡት። 34 ሀገረ ገዡም ደብዳቤውን ካነበበ በኋላ፣ ጳውሎስ ከየትኛው አውራጃ እንደ መጣ ጠየቀ፤ ከኪልቅያ እንደ መጣ ባወቀ ጊዜም፣ 35 “ከሳሾችህ ወደዚህ ሲመጡ፣ በሚገባ እሰማሃለሁ” አለው። ከዚያም በኋላ፣ በሄሮድስ ቅጥር ግቢ እንዲጠብቁት አዘዘ።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ከሸንጎው እና በሊቀ ካህኑ ፊት ይቆም ዘንድ ይዘውት መጡ፡፡ ACT 22:30. አናኒያስ ይህ የዚህ ሰው ስም ነው፡፡ ነጭ ቀለም የተቀባ ግድግዳ ይህ ግድግዳ ንጹሕ ይመስል ዘንድ ቀለም መቀባቱን ለማመልከት ነው፡፡ ጳውሎስ ለአናኒያስ እንዲህ ሲል ነገረው፡፡ ግድግዳ ንጹሕ ይመስል ዘንድ ቀለም እንደሚቀባው ሁሉ እንዲሁም አናኒያስም በውጪ መልካም ይመስላል ነገር ግን ውስጡ ግን በክፋት የተሞላ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ነጭ ቀለም የተቀባ ግድግዳ፡፡" እንድገረፍ አዘዘ "ሰዎች ይገርፉኝ ዘንድ አዘዘ" ወይም "እነዚህ ሰዎች ይደበድቡኝ ዘንድ አዘዘ"
የእግዚአብሔርን ሊቀ ካህን እንደዚህ እንዴት ትሰድባለህ? ሰዎቹ ይህንን ጥያቄ በመጠቀም ጳውሎስ የተናገረው ነገር አግባብነት እንዳሌለው ለማሳየት ጥረት አድረገዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "የእግዚአብሔር ሊቀ ካህን አትሳደብ!" ወንድም እኔ ይህ ሰው ሊቀ ካህን መሆኑን አላወኩም ነበር አማራጭ ትርጉሞች 1) "ጳውሎስ አላወቀም ነበር ምክንያቱ የዚህ ሰው ሁኔታው ሁሉ እንደ ሊቀ ካህን አይደለም" ወይም 2) "ጳውሎስ ከኢየሩሳሌ ለብዙ ጊዜያት ርቆ ስለነበር አዲስ ሊቀ ካህን መሾሙን አያውቅም ነበር፡፡"
ተፈርዶብኛል "አንተ በእኔ ላይ ፈርደሃል" ሸንጎው እርስ በእርሱ ተከፋፈለ "የሸነንጎው አባላት መስማማት አልቻሉም" ትንሰዔ የለም፣ መላእክት እና መናፈስት የሉም አማራጭ ትርጉሞች 1) በትንሳዔ፣ በመለአክት ወይም በመናፍስ አያምኑም ወይም 2) እግዚአብሔር ሰዎች እን መለአክት ወይም መናፍስት አድርጎ ሰዎችን ከሞት አያስነሳም፡፡
ከዚህም የተነሣ ከፍተኛ ኹከት ተነሣ “ስለዚህም” የሚለው ቃል አሁን የሆነው ነገር የሆነበት ምክንያት ከዚህ በፊት ከሆነው ነገር የተነሣ ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ከዚህ በፊት የተከናወወነው ነገር ጳውሎስ ስለ ትንሳዔ ያለውን እምነት መግለጹ ነበር፡፡ መናፍስት ወይን መለአክት ቢያናግሩትስ? ፈርሳዊያን መላእክት እና መናስፍት እንዳሉና ከሰዎች ጋር እንደሚነጋገሩ በመግለጽ ሳዱቃዊያንን ገሰጾዋቸው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "መላእክት ወይም መናፈስት ተናግረውት ይሆናል" ጳውሎስን እንደ ጨርቅ ልበጣጥሱ ፈለጉ "አካለዊ ጉዳት ባደረሱበት ነበር" በጉልበት ወሰዱት "ጳውሎስን በጉልበት ወሰዱት" ወደ ወታደሮች ካምፕ ወሰዱት ይህንን በ ACT 21:34 ላይ ምን ብለህ እንደ ተረጎምከው ተመልከት፡፡
መሰሰከረ አማራጭ ትርጉም 1) የግል ድነትን እንዴት እንደገኘ "መናገር" ወይም "መመሰከር" ወይም 2) የድነት መልዕክት መናገር፡፡
አጠቃላይ መረጃ: አጠቃላይ መረጃ: ይህ በጳውሎስ ታሪክ ውስጥ አዲስ ስለተፈጠረ ነገር ነው፡፡ አይሁዳዊያን ጳውሎስን ለመግደል ተማከሩ፡፡ ተማማሉ "አንድ ነገር ለማድረግ በመደበኛ ሁኔታ መስማማት" አርባ ወንዶች "40 ወንዶች"
ሄዱ "አርባ አይሁዶች ሄዱ" ስለዚህም ይህ ቃል ከዚህ በፊት በተነገረ አንድ ነገር ምክንያት ይህ እንደሆነ ያሳያል፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ አይሁዳዊያኑ ለሸንጎው የደረሱበትን ስምምነት በመናገራቸው ምክንያት ነው፡፡ ወደ እናንት እናመጣው ዘንድ "ጳውሎስን ከወታደሮች ካምፕ ይዘውት በቤተ መቅደሱ ውስጥ ወደሚገኙት ሸንጎዎች ዘንድ ለማምጣት"
ተኝተው ይጠባበቁ ነበር ጳውሎስን ለመግደል ቃል የተገባቡት ሰዎች በጳውሎስ በጉልበት ነጥቀው ለመውሰድ ተዘጋጅተው ነበር፡፡ የወታደሮች ካምፕ በ ACT 21:34 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ አንድ ነገር ሊነግረው ይፈልግ ነበር "ወጣቱ ለወታደሮች አለቃ የሆነ ነገር ሊነግረው ፈልጎ ነበር"
እስረኛው ጳውሎስ ወደ እርሱ ዘንድ አስጠራኝ "እስረኛው ጳውሎስ እንድመጣ እና ከእርሱ ጋር እንዳወራ ጠየቀኝ" ይህ ወጣት የወታደር አለቃው ወጣቱን በእጆቹ ይዞት ስለነበር ይህ የጳውሎስ የአጎት ልጅ እድሜው ከ12 እስከ 15 ይሆናል፡፡
አጠቃላይ መረጃ: የጳውሎስ የአጎቱ ልጅ ለወታደሮቹ አለቃ ጥያቄ መልስ ይሰጥ ነበር፡፡ አርባ ወንዶች "40 ወንዶች" ተኝተው ይጠብቁት ነበር "ጳውሎስን በጉልበት ለመንጠቅ ዝግጁዎች ነበሩ"
ሁለት መቶ አለቆች "2 መቶ አለቆች" ሰባ ፈረሰኞች "70 ፈረሰኞች" ሁለት መቶ ጦረኞች "200 ጦር የታጠቁ ወታደሮች" ከሌሊቱ ሦስተኛው ሰዓት ላይ ከሌልቱ ሰጠኝ ሰዓት ላይ፡፡ ፊሌክስ አገረገዥው የዚያ አከባቢ ገዥ የሆነው ፍልክስ በቄሳሪያ ይኖር ነበር፡፡
አጠቃላይ መረጃ: የወታደሮቹ አለቃ ለዘገረ ገዥው ፍልክስ የላከው ደብዳቤ የጀመረው እንዲህ ነው፡፡ ከቀላውዴዎስ ሉስዮስ ወደ ክቡር አገረ ገዡ ወደ ፊልክስ፤ ሰላም ለአንተ ይህ መደበኛ የደብዳቤ መግቢያ ነው፡፡ ቀላውዴዎስ ሉስዮስ የወታደሮቹ አለቃ ስም ነው፡፡ ፍልክስ አገረገዥው ፍሌክስ ለዚያ አከባቢ በአጠቃላይ በሮም የተሸመ አገረ ገዥ ነው፡፡ ልገድሉት ነበር አማራጭ ትርጉም: "አይሁዳዊያን ጳውሎስን ለመግደል ዝግጁዎች ነበሩ" መጡ "ደረሱ" ወይም "ወደፈለጉበት ቦታ ደረሱ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ይህ የወታደሮቹ አለቃ ለሀገረ ገዥው ፍልክስ የጻፈው ደብዳቤ ማብቂያ ነው፡፡ ማወቅ እፈልጋለሁ በዚህ ስፍራ ላይ “እኔ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ቀላውዴዎስ ሉስዮስ ነው፡፡ ከሰሱት "አይሁዳዊያን ጳውሎስን ከሰሱት" ከዚያ ነገሩ ምን እንደሆነ ተገነዘብኩ አማራጭ ትርጉም: "በኋላ ላይ ገባኝ"
ስለዚህም ወታደሮቹ የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ተግባራዊ አደረጉ በዚህ ሥፍራ ላይ “ስለዚህ” የሚለው ቃል ከዚህ በፊት በተነገረ አንድ ነገር ምክንያት ይህ እንደሆነ ያሳያል፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ የወታደሮቹ አለቃ ለወታደሮቹ የሰጣቸው ትዕዛዝ ጳውሎስን እንዲጠብቁት ነው፡፡ አንቲጳጥሪስ ይህች ሄሮዶስ ለአባቱ አንቶጳጥሪ ክብር ሲል የገነባት ከተማ ናት፡፡ በዘመናችን እስራኤል ውስጥ ትገኛለች፡፡
የኪልቅያ ሰው እንነደሆነ በተረዳ ጊዜ "አገረ ገዥው ጳውሎስ የኪልቅያ ሰው እንደሆነ ባወቀ ጊዜ" ይጠብቁት ዘንድ አዘዘ "ወታደሮቹ ጳውሎስን ይጠብቁት ዘንድ አዘዘ" ወይም "ወታደሮቹ ጳውሎስን ያስሩት ዘንድ አዘዘ"
1 ከዐምስት ቀናት በኋላ፣ ሊቀ ካህናቱ ሐናንያ፣ አንዳንድ ሽማግሌዎችና ጠርጠሉስ የተባለ አንድ የሕግ ባለ ሙያ ወደዚያ ሄዱ። እነዚህ ሰዎች ለገዡ አመልክተው ጳውሎስን ከሰሱት። 2 ጳውሎስ በገዡ ፊት በቆመ ጊዜ፣ ጠርጠሉስ ይከሰው ጀመር፤ ገዡንም እንዲህ አለው፤ «ክቡር ፊልክስ ሆይ፣ በአንተ ምክንያት ብዙ ሰላም አግኝተናል፤ የአንተ ማስተዋልም ለሕዝባችን ጥሩ መሻሻልን ያመጣለታል፤ 3 ስለ ሆነም አንተ የምታደርገውን ሁሉ በፍጹም ምስጋና እንቀበለዋለን። 4 ብዙ እንዳላቈይህ፣ በቸርነትህ በዐጭሩ እንድትሰማኝ እለምንሃለሁ። 5 ይህ ሰው ቅንቅን ሆነና በመላው ዓለም ላይ ያሉትን አይሁዶች ሲያሳምፅ አግኝተነዋልና። የናዝራውያን ወገን መሪ ነው። 6 ቤተ መቅደሱንም እንኳ ሊያረክስ ሞክሯል፤ ስለዚህ ያዝነው። 7 ነገር ግን ወታደራዊው መኰንን ሉስዮስ መጥቶ፣ ጳውሎስን በኀይል ከእጃችን ወሰደው። 8 አንተም ስለ እነዚህ ነገሮች ሁሉ ጳውሎስን በምትጠይቀው ጊዜ ለምን እንደምንከሰው ልታውቅ ትችላለህ።» 9 አይሁድም አንድ ላይ ሆነው ጳውሎስን ከሰሱት፤ ነገሮቹም ሁሉ እውነት መሆናቸውን ተናገሩ። 10 ገዡ ግን እንዲናገር ሲጠይቀው፣ ጳውሎስ እንዲህ ብሎ መልስ ሰጠ፤ «አንተ ለብዙ ዓመታት ለዚህ ሕዝብ ፈራጅ መሆንህን ዐውቃለሁ፤ ስለ ሆነም ደስ እያለኝ ስለ ራሴ እገልጽልሃለሁ። 11 ለማምለክ ወደ ኢየሩሳሌም ከወጣሁ ከዐሥራ ሁለት ቀን እንደማይበልጥ አንተ መርምረህ ልትደርስበት ትችላለህ፤ 12 እነርሱ በቤተ መቅደስ ባገኙኝ ጊዜም፣ ከማንም ጋር አልተከራከርሁም፤ በምኵራቦችም ሆነ በከተማው ሕዝብን አልቀሰቀስሁም፤ 13 አሁን በእኔ ላይ የሚያቀርቡት ክስ እውነተኛ ለመሆኑ ማስረጃ የላቸውም። 14 ነገር ግን ለአንተ ይህን እነግርሃለሁ፤ እነርሱ የእምነት ክፍል ብለው እንደሚጠሩት እኔም በዚያ ተመሳሳይ መንገድ የአባቶቻችንን አምላክ አገለግላለሁ። በሕግና በነቢያት ለተጻፈው ሁሉ የታመንሁ ነኝ። 15 ልክ እነዚህ ሰዎች ደግሞ እንደሚጠብቁት፣ ስለሚመጣው የሙታን ማለትም የጻድቃንና የኀጥአን ትንሣኤ በእግዚአብሔር ላይ እምነት አለኝ። 16 በዚህም በሁሉም ነገር በእግዚአብሕርና በሰዎች ፊት ነቀፋ የሌለበት ኅሊና እንዲኖረኝ እሠራለሁ። 17 ከብዙ ዓመታትም በኋላ ለሕዝቤ ርዳታና የገንዘብ ስጦታ ለመስጠት መጣሁ። 18 ይህንም ባደረግሁ ጊዜ ከእስያ የሆኑ አንዳንድ አይሁድ፣ ሕዝብም ጩኸትም ሳይኖር በቤተ መቅደስ የመንጻት ሥርዓት ላይ አገኙኝ። 19 እነዚህ ሰዎች በእኔ ላይ አንዳች ነገር ካላቸው፣ በፊትህ መጥተው ክሱን ሊያቀርቡብኝ ይገባቸዋል። 20 አለበለዚያም፣ እነዚሁ ሰዎች በአይሁድ ሸንጎ ፊት በቆምሁ ጊዜ፣ ምን እንዳጠፋሁ መናገር ነበረባቸው፤ 21 «ዛሬ አንተ የምትፈርድብኝ ስለ ሙታን ትንሣኤ ነው» ብዬ በመካከላቸው ቆሜ ድምፄን ከፍ በማድረግ ከተናገርሁት ከዚህ አንድ ነገር በቀር፣ ምንም የተናገርሁት የለም። 22 ፊልክስ ግን ስለ መንገዱ በሚገባ ያውቅ ነበር፤ ስለ ሆነም፣ «አዛዡ ሉስዮስ ከኢየሩሳሌም በሚወርድበት ጊዜ ለክሳችሁ ውሳኔ እሰጣለሁ» ብሎ አይሁድን እንዲጠብቁ አደረጋቸው። 23 ከዚያም ጳውሎስን እንዲጠብቀው፣ ነገር ግን እንዲያደላለት፣ እርሱንም ከመርዳት ወይም ከመጎብኘት ማንም ወዳጆቹን እንዳይከለክል የመቶ አለቃውን አዘዘው። 24 ከጥቂት ቀናት በኋላ፣ ፊልክስ ድሩሲላ ከምትባል አይሁዳዊት ሚስቱ ጋር ተመልሶ መጣ፤ ጳውሎስንም በማስጠራት በክርስቶስ ኢየሱስ ስላለው እምነት ከእርሱ ሰማ። 25 ነገር ግን ጳውሎስ ስለ ጽድቅ፣ ራስን ስለ መግዛት፣ ስለሚመጣውም ፍርድ ከእርሱ ጋር በተነጋገረ ጊዜ፣ ፊልክስ ፈራ፤ «ለአሁኑ ሂድ፤ እንደ ገና ጊዜ ሲኖረኝ ግን፣ አስጠራሃለሁ» አለው። 26 በዚሁ ጊዜ፣ ጳውሎስ ገንዘብ ይሰጠኛል ብሎ ፊልክስ ተስፋ ያደርግ ነበር፤ ስለዚህ ብዙ ጊዜ እያስጠራ ያነጋግረው ነበር። 27 ከሁለት ዓመት በኋላ ግን፣ ከፊልክስ ቀጥሎ ጶርቅዮስ ፊስጦስ ገዢ ሆነ፤ ፊልክስ ግን አይሁድን ለማስደሰት ፈልጎ ጳውሎስን በጥበቃ ሥር እንዲቆይ አደረገ።
አጠቃላይ መረጃ: ጳውሎስ በቄሳሪያ የፍርድ ሂደቱን በመከታተል ላይ ይገኛል፡፡ ጠርጡለስ የተባለ ሰው ለአገረ ገዥው ፍልክስ በጳውሎስ ላይ የቀረበው ክስ ምን እንደሆነ አቀረበ፡፡ ከአምስት ቀናት በኋላ "የሮም ወታደሮች ጳውሎስን ወደ ቄሳሪያ ከወሰዱት በኋላ ባሉት አምስት ቀናት ውስጥ" አናኒያስ በ ACT 23:1 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡ ተናጋር "ጠበቃ" ወይም "በፍርድ ቤት አንድን ሰው ከሶ የሚቆም ሰው” ወደዚያ ሄደ "went to Caesarea where Paul was" ጠርጢለሰስ ይህ የሰው ስም ነው፡፡ ጳውሎስ በአገረ ገዥው ፊት ሲቆም "ጳውሎስ በፍርድ ቤቱ ውስጥ ፈራጅ በሆነው በሀገረ ገዥው ፊት ሲቆም" እርሱን መክሰስ ጀመረ "እርሱን ተቃውሞ መናገር ጀመረ" ወይም "የሮምን ሕግ መተላለፉን በማሳየት ጳውሎስን መክሰስ ጀመረ" በአንተ ምክንያት በዚህ ሥፍራ ላይ “አንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሀገረ ገዥውን ነው፡፡ ሠላም አለን "አንተ የሚታስተዳድራቸው ሕዝቦች ሠላም አላቸው" ፍልክስ ይህንን በ ACT 23:25 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
ስለዚህም ብዙ ላቆይህ አልፈልግም አማራጭ ትርጉሞች 1) ስለዚህም ጊዜህን መሻማት አልፈልግም (UDB) ወይም 2) ስለዚህም ላደክምህ አልፈልግም፡፡ በአጭሩ የሚናገረውን አድምጠኝ "አጭር ንግግሬን አድምጥልኝ" ይህ ሰው እንዲህ ያለ ነገር ስያደርግ አግኝተነዋል “እኛ” የሚለው ቃል አናኒያስ፣ የተወሰኑ ሽማግሌዎች እና ጠርጠሊየስን ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ጳውሎስን ተመልክተነዋል” ወይም “ጳውሎስ ይህንን እንዳደረገ አውቀናል" በዓለም ያሉ አይሁዶች ሁሉ በዚህ ሥፍራ ላይ “ሁሉም” የሚለው ቃ በጳውሎስ ላይ የቀረበው ክስ ግነት ተሞልቶበት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በዓለም ያሉ አይሁዳዊያን ሁሉ”፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጠርጡለስ ለአገረ ገዥው ፍልክስ በጳውሎስ ላይ ያቀረበው ክስ አጠናቀቀ፡፡ ጳውሎስን በጠየቁት ጊዜ "ጳውሎስን ባወጣጡት ጊዜ" ወይም "በችሎት ፊት እንደሚደረገው ጥያቄ በተጠየቀ ጊዜ" እኛ የምከሰው ስለ … ነው "ጳውሎስ ይህንን በማድረጉ ነው የሚንከሰው" ወይም "ጳውሎስ ይህንን በማድረጉ ጥፋተኛ በመሆኑ ነው የሚንከሰው"
አጠቃላይ መረጃ: ጳውሎስ ለቀረበበት ክስ በሀገረ ገዥው ፍልክስ ፊት እንዲህ በማለት ምላሽ ሰጠ፡፡ አገረ ገዥው ተቁነጠነጠ "ሀገረ ገዥው ምልክት አሳየ" ሀሳቤን ላብራራ "ያለሁበትን ሁኔታ ላብራራ" አንተ ራስህ ልታረጋግጥ ትችላለህ "ማረጋገጥ ትችላለህ" እስካሁን ዐሥራ ሁለት ቀን ሆኖኛል "12 ቀናት ሆኖኛል" ኹከት አላስነሳሁም "አላወኩኝም" ወይም "ማንንም ለኹከት አልቀሰቀስኩም" የተከሰስኩበት ክስ "ጠፋተኛ ተደርጌ የተከሰስኩበት" ወይም 'ወንጀለኛ የተደረግኹት"
ይህን ለአንተ አምናለሁ "ይህንን በአንተ ፍት እቀበላሉ" ወይም "ይህንን ለአንተ እናገራለሁ" የስህተት ትምህርት ብለው ይጠሩታል "የስህተት ትምህርት ቡድኖች ብለው ይጠራሉ" የአባቶቻን አምላክ ይህ የሚያሳየው ጳውሎስ የሚከተለው የትንቱን ሃይማኖት መሆኑን ነው፡፡ ይህ ደግሞ አዲስ አይደለም. የስህተት ትምህርት ተብሎም መጠራት አይችልም፡፡" የተቀደሱት "ቅዱስ ሕዝብe" ይህንን ለማግኘት እሠራለሁ "ይህንን ለማግኘት እለማመዳለሁ" ወይም "ይህንን ለማግኘት እጥራለሁ" በእግዚአብሔር ፊት "በእግዚብሔር መገኘት ውስጥ"
ሀገሬን በመርዳት የገንዘብ ስጦታ፡፡ "ለመርዳት የሚሆን የገንዘብ ስጦታ" ከሕዝቡ ጋር አይደለም "ሕዝቡን የሰበሰብኩት ትክክለኛ ያልሆነ ነገር ለማድረግ አይደለም" እነዚህ ሰዎች "ከኢስያ የመጡ አይሁዳዊያን" የሚሉት ነገር አንዳች ካላቸው "የሚሉት ነገር ካላቸው"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ስለተከሰሰበት ነገር በሀገረ ገዥው ፍልክስ ፊት መለስ መስጠቱን አጠናቋል፡፡ እነዚሁ ተመሳሳይ ሰዎች በቄሳሪያ ጳውሎስ በችሎት በቀረበ ጊዜ የነበሩት እነዚሁ የሸንጎው አባላት የሆኑት ሰዎች፡፡
የወታደሮች አዛዡ ሉስዮስ በወረደ ጊዜ "የወታደሮች አለቃ የሆነው ሉስዮስ በወረደ ጊዜ" ወይም "የወታደሮች አለቃ የሆነው ሉስዮስ በወረደ ጊዜ" የአንተን ነገር ውሳኔ እሰጣለሁ "በአንተ ላይ የቀረበውን ክስ አስመልክቶ ውሳኔ እሰጣለሁ" ወይም "ጥፋተኛ መሆን አለመሆንን እወስናለሁ" በጥቂቱም ነጻነት ሰጠው "ለጳውሎስ በእስር ላይ እያለ በመጠኑም ቢሆን ነጻነት ሰጠው"
ከጥቂት ቀናት በኋላ "ከብዙ ቀናት በኋላ" ፍልክሽ ይህንን በ ACT 23:24 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ድሩሲላ የእርሱ ምስት ናት ድሩሲላ የሴት ስም ነው፡፡ ፍልክስ በፍራት ተሞላ ፍልክስ ስለኃጢአቱ ጸጸት ተሰምቶት ልሆን ይችላል፡፡ ለአሁኑ "ለአሁኑ" ወይም "እስከ በኋላ ድረስ"
ጳውሎስ ገንዘብ ልሰጠው ይችል ነበር ፍልክስ ጳውሎስ ነጻ ለመውጣት ጉቦ ልሰጥ ይችላል ብሎ አስቦ ነበር፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ጳውሎስ ለፍልክስ ገንዘብ መስጠት ይችል ነበር፡፡" ስለዚህም ብዙ ጊዜ ሰዎችን ልኮ ያስጠራው እንዲሁም ያወራው ነበር "ስለዚህም ፊስጦስክስ ብዙ ጊዜ ጳውሎስን አስጠርቶ ያወራው ነበር" ጶርቅዮስ ፊስጦስ ይህ ፍልክስን ተክቶ የሀገረ ገዥ የሆነው ሰው ስም ነው፡፡
1 ፊስጦስም ወደ ክፍለ ሀገሩ ገባ፤ ከሦስት ቀንም በኋላ ከቂሣርያ ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ። 2 የካህናት አለቃውና ታዋቂ የሆኑት አይሁድ ጳውሎስን ፊስጦስ ላይ ከሰሱት፤ ለፊስጦስም በኀይል ተናገሩ። 3 በመንገድም ላይ ሊገድሉት ጳውሎስን ወደ ኢየሩሳሌም እንዲያስጠራው ፊስጦስን ለመኑት። 4 ፊስጦስ ግን መልሶ ጳውሎስ በቂሣርያ እስረኛ እንደ ሆነ፣ እርሱ ራሱም ወደዚያ እንደሚመለስ ተናገረ። 5 “ስለዚህ፣ የሚችሉ ከእኛ ጋር ወደዚያ መሄድ አለባቸው። ሰውየው ያጠፋው ነገር ካለ፣ ክሰሱት” አለ። 6 ፊስጦስም ስምንት ወይም ዐሥር ቀን ከቆየ በኋላ፣ ወደ ቂሣርያ ወረደ። በማግስቱም በፍርድ ወንበር ተቀምጦ ጳውሎስን ወደ እርሱ እንዲያመጡት አዘዘ። 7 ጳውሎስም በደረሰ ጊዜ፣ ከኢየሩሳሌም የመጡት አይሁድ በአጠገቡ ቆሙ፤ በማስረጃ ማረጋገጥ ያልቻሉትን ብዙ ከባድ ክስም አቀረቡ። 8 ጳውሎስ፣ “በአይሁድ ስምም ላይ፣ በቤተ መቅደሱም ላይ፣ በቄሣርም ላይ በደል አልፈጸምሁም” ብሎ ራሱን ተከላከለ። 9 ፊስጦስ ግን አይሁድን ለማስደሰት ፈለገ፤ ስለሆነም፣ “እስከ ኢየሩሳሌም መውጣትና ስለ እነዚህ ነገሮች በዚያ ፍርድ እንድሰጥህ ትፈልጋለህን?” ብሎ ጳውሎስን ጠየቀው። 10 ጳውሎስም እንዲህ አለ፤ “ፍርድ ሊሰጠኝ በሚገባኝ በቄሣር የፍርድ ወንበር ፊት እቆማለሁ። አንተም ደግሞ በሚገባ እንደምታውቀው፣ አንድንም አይሁዳዊ አልበደልሁም። 11 ብበድልና ሞት የሚገባውን ነገር አድርጌ ቢሆን እንኳ፣ አልሞትም አልልም። እነርሱ በእኔ ላይ የሚያቀርቡት ክስ ከንቱ ከሆነ ግን፣ ማንም ለእነርሱ አሳልፎ ሊሰጠኝ አይችልም። ለቄሣር ይግባኝ ብያለሁ።” 12 ከዚያም ፊስጦስ ከሸንጎው ጋር ተነጋግሮ፣ “ለቄሣር ይግባኝ ብለሃልና ወደ ቄሣር ትሄዳለህ” ብሎ መለሰ። 13 ከጥቂት ቀናትም በኋላ ንጉሥ አግሪጳና በርኒቄ ፊስጦስን ለመጐብኘት ቂሣርያ ደረሱ። 14 ንጉሥ አግሪጳ በዚያ ብዙ ቀን ከተቀመጠ በኋላ፣ ፊስጦስ የጳውሎስን ጉዳይ ለንጉሡ አቀረበ፤ እንዲህም አለ፤ “ፊልክ አስሮ የተወው አንድ ሰው በዚህ አለ። 15 እኔ በኢየሩሳሌም በነበርሁ ጊዜ የካህናት አለቆችና የአይሁድ ሽማግሌዎች ክስ መሥርተውበት ለእኔ አመለከቱ፤ እንድፈርድበትም ለመኑኝ። 16 ለዚህም፣ የተከሰሰው ሰው በከሳሾቹ ፊት ቀርቦ ለተከሰሰበት ነገር እንዲከላከል ዕድል ሳይሰጠው አንድን ሰው አሳልፎ መስጠት የሮማውያን ልማድ አይደለም ብዬ መልስ ሰጠሁ።” 17 ስለዚህ፣ እነርሱ በአንድ ላይ ወደዚህ በመጡ ጊዜ፣ አልዘገየሁም፤ ነገር ግን በማግስቱ በፍርድ ወንበር ተቀምጬ ሰውዬውን እንዲያመጡት አዘዝሁ። 18 ከሳሾቹ ቆመው በከሰሱት ጊዜ፣ ካቀረቡበት ክሶች ማንኛቸውም ከባድ አይደሉም ብዬ ዐሰብሁ። 19 ይልቁንም ስለ ገዛ ራሳቸው ሃይማኖትና ጳውሎስ ሕያው ነው ስለሚለው ሞቶ ስለ ነበረው ኢየሱስ ከእርሱ ጋር ይከራከሩ ነበር። 20 ይህን ጉዳይ እንዴት እንደምመረምር ግራ ገብቶኝ ነበር፤ ስለ እነዚህ ነገሮችም በዚያ ለመፋረድ ወደ ኢየሩሳሌም ይሄድ እንደ ሆነ ጳውሎስን ጠየቅሁት። 21 ጳውሎስ ግን የንጉሠ ነገሥቱን ውሳኔ እስኪያገኝ፣ በዘብ እንዲጠበቅ ይግባኝ ባለ ጊዜ፣ ወደ ቄሣር እስክሰደው ድረስ በጥበቃ ሥር እንዲሆን አዘዝሁት።” 22 አግሪጳ፣ “እኔ ደግሞ ይህን ሰው ልሰማው እፈልጋለሁ” ብሎ ፊስጦስን አነጋገረው። ፊስጦስም፣ “ነገ ትሰማዋለህ” አለው። 23 ስለ ሆነም፣ በማግስቱ፣ አግሪጳና በርኒቄ በታላቅ ሥነ ሥርዓት ከወታደራዊ መኮንኖችና ከከተማዋ ታዋቂ ሰዎች ጋር ወደ አዳራሹ ገቡ። በፊስጦስ ትእዛዝም ጊዜ ጳውሎስን ወደ እነርሱ አመጡት። 24 ፊስጦስም እንዲህ አለ፤ “ንጉሥ አግሪጳ ሆይ፣ እዚህ ከእኛ ጋር ያላችሁትም ሰዎች ሁሉ፣ ይህን ሰው ተመልከቱት፤ በኢየሩሳሌምና እዚህም ያሉት የአይሁድ ሕዝብ ሁሉ ከእኔ ጋር ተማከሩ፤ ይህ ሰው ከእንግዲህ ወዲያ በሕይወት መኖር የለበትም ብለውም ጮኹብኝ። 25 እኔ ግን ለሞት የሚያበቃው ምንም በደል አለመፍጸሙን ዐወቅሁ፤ ነገር ግን ወደ ንጉሠ ነገሥቱ ይግባኝ በማለቱ ልሰደው ወሰንሁ። 26 ሆኖም ለንጉሠ ነገሥቱ ለመጻፍ አሳማኝ ነገር የለኝም። በዚህ ምክንያት ስለ ጉዳዩ የምጽፈው ነገር እንዲኖረኝ፣ በተለይ ንጉሥ አግሪጳ ሆይ፣ ወደ አንተ አምጥቼዋለሁ። 27 አንድን እስረኛ መስደድና የቀረበበትን ክስም አለመግለጽ ለእኔ ምክንያታዊ ያልሆነ ይመስለኛልና።”
አጠቃላይ መረጃ: አሁን ፊስጦስ የቄሳሪያ አገረ ገዥ ሆኗል፡፡ አሁን ይህ በታኩ ውስጥ የተከናወነው ቀጣዩ ነገር ምን እንደሆነ ምልክት ሆኖ ያሳየናል፡፡ ፊስጦስ ወደ መንደሩ ገባ አማራጭ ትርጉሞች 1) በቀላሉ ፊስጦስ ወደ አከባቢው መጣ ወይም 2) ፊስጦስ አከባቢውን ማስተዳደር ጀመረ፡፡ (UDB). ከቄሣሪያ አንስቶ እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ሄደ አማራጭ ትርጉሞች 1) ኢየሩሳሌም ወደ ላይ አድርጎ ማቀመጡ ኢየሩሳሌም ጠቃሚ መሆኗን የሚያሳይ ነው ወይም 2) ኢየሩሳሌም በተራራ ላይ ያለች ከተማ በመሆኗ ወደ ከፍታ መውጣቱን የሚያሳይ ነው፡፡ ጳውሎስ ላይ ክስ አቀረቡበት ይህ በፍርድቤት መደበኛ ክስ ማቅረባቸውን ያሳያል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ጳውሎስ ሕግጋትን መተላለፉን የሚያሳይ ክስ አቀረቡበት፡፡" በፊስጦስ ፊት አጥብቀው ከሰሱት "ፊስጦስን ለመኑት" ወይም "ፊስጦስን ጠየቁት" ይጠራው ዘንድ . . . እነርሱም እርሱን መግደል ይችሉ ዘንድ "ፊስጦስ ጳውሎስን ይጠራው ዘንድ . . . አይሁዳዊያንም ጳውሎስን መግደል ይችሉ ዘንድ" ይጠራው ዘንድ "ይልከው ዘንድ" በመንገድ ላይም እነርሱ መግደል ይችሉ ዘንድ ጳውሎስን በመንገድ ላይ ተደብቀው ልገድሉት ይፈልጉ ነበር፡፡
ጳውሎስ በቄሣሪያ እስረኛ ነበር አማራጭ ትርጉም፡ "ጳውሎስ በቄሣሪያ እስረኛ ከመሆኑ የተነሣ እኔ እራሴ ወደዚያ በፍጥነት እመለሳለሁ፡፡" ይህ ሰው ላይ አንዳች ነገር አድርጎ ከሆነ "ጳውሎስ ላይ ጥፋት የተገኘ እንደሆነ" ልትከሱት ትችላላችሁ "ክስ ልታቀርቡበት ትችላላችሁ" ወይም "የተላለፈውን ሕግ በማንሳት ልትከሱት ትችላላችሁ"
በዚያ ከቆየ በኋላ "ፊስጦስ በዚያ ቆየ" በፍርድ ወንበር ላይ ተቀመጠ "እንደ ዳኛ ሆኖ በሚፈርድበት ወንበር ላይ ተቀመጠ" ጳውሎስም በፊቱ እንዲቆም ተደረገ አማራጭ ትርጉም፡ "ጳውሎስንም በፊቱ አቀረቡ" በመጣ ጊዜም "ጳውሎስ በመጣና በፊስጦስ ፊት በቆመ ጊዜ" የአይሁዳዊያን ስም "የአይሁዳዊያን ሕግ" (UDB) የቤተ መቅደሱን ሐህግ አለመተላለፉን ጳውሎስ ወደ ቤተ መቅደሱ ማን መግባት ይችላል የሚለውን ሐህግ አለመተላለፉን ተናገረ፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ወደ ቤተ መቅደሱ መግባት የሚችሉሰዎች ሕግን አልመተላለፉን"
በአይሁዳዊያን ዘንድ ተቀባይነት ማግኘት ስለፈለገ "አይሁዳዊያንን ማስደሰት ስለፈለገ" እነዚህን ነገሮች ለመዳኘት እኔ አልችልም አማራጭ ትርጉም: "እነዚህን ነገሮች አስመልክቶ እኔ ምንም ቢያኔ መስጠት አልችልም" እነኔ ፍርድ መስጠት የሚችለው አማራጭ ትርጉም፡ "በእኔ ላይ ፍርድ መስጠት የሚችልበት ሥፍራ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጰውሎስ ከፊስጦስ ጋር መነጋገሩን ቀጥሏል፡፡ እኔ ያደረኩት ነገር ለሞት የሚያበቃ ከሆነ "ለሞት ቅጣት የሚያበቃ ጥፋት ፈጽሜ ከሆነ" ክሳቸው ትክክል ካልሆነ "የከሰሱኝ ክስ ትክክል ካልሆነ" ማንም ለእነርሱ አሳልፎ ልሰጠኝ አይችልም አማራጭ ትርጉሞች 1) ፊስጦስ ለእነዚህ በሐሰት ለከሰሱት ሰዎች አሳልፎ ልሰጠው የሚስችል ምን ሕጋዊ ሥልጣን የለውም ወይም 2) ጳውሎስ እያለ ያለው ያቀረቡት ክስ መሠረት ያሌለው ከሆነ ሀገረ ገዥው በአይሁዳዊያን ጥያቄ መሠረት ለእነርሱ አሳልፎ ልሰጠው አይገባም፡፡ ወደ ቄሣር ይግባኝ አለ "ቄሣር ይዳኘኝ ዘንድ በእርሱ ፊት መቅረብ እፈልጋለሁ" ፊስጦስ ከሸንጎዎቹ ጋር ተመካከረ በዚህ ሥፍራ ላይ “ሸንጎ” ተበሎ የተጠቀሰው በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ በአጠቃላይ የተጠቀሰው የአይሁድ ሸንጎ አይደለም፡፡ ይህ በሮም አገዛዝ ውስጥ ያለ ፖለቲካዊ ሸብጎ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ፊስጦስ ከራሱ የአስተዳደር አማካሪዎች ጋር ተነጋገረ፡፡"
አጠቃላይ መረጃ: ፊስጦስ የጳውሎስን ጉዳይ ለንጉሥ አግሬጳ ማስረዳት ጀመረ፡፡ አሁን ይህ ቃል በታሪኩ ውስጥ አዲስ ነገር መጀመሩን የሚያሳይ ነው፡፡ ንጉሥ አግሪጳ በርኒቄ አግሪጳ በዚያ ዘመን የነገሠ ንጉሥ ሲሆን በርኒቄ ደግሞ እህቱ ናት፡፡ ለፊስጢስ ኦፍሳሌያዊ ክፍያ ለመፈጸም "ፊስጢስን በኦፍሴላዊ ጉዳይ ለመጎብኘት" አንድ ሰው ፊስጦስእስረኛ ሆኖ ወደኋላ ቀርቶ ነበር አማራጭ ትርጉም: "ፊስጦስ ቢሮን ትቶ ሲሄድ ሰውዬውን በዚህ በእስር ትቶት ሄዶ ነበር፡፡"
ስለዚህ በዚህ ሥፍራ ላይ “ስለዚህ” የሚለው ቃል ከዚህ በፊት በተነገረ አንድ ነገር ምክንያት ይህ እንደሆነ ያሳያል፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥም ፊስጦስ የተከሰሰው ሰው ከከሳሾቹ ጋር መገናኘት እና መከላከያ ሀሳቡን ማቅረብ አለበት ብሏል፡፡ ሁሉም ስገናኙ "የአይሁድ መሪዎች በዚህ ከእኔ ጋር ለመገናኘት በመጡ ጊዜ" በፍርድ ወንበር ላይ እቀመጣለሁ "እንደ ዳኛ ሆኜ በምፈርድበት ወንበር ላይ እቀመጣለሁ" (ተመልከት: ACT 25:6) ሰውዬው እንዲመጣ አዝኩ አማራጭ ትርጉም፡ ወታደሮቹ ጳውሎስን ወደፊት ይዘውት ይመጡ ዘንድ አዘዝኩኝ" ስለራሳቸው ሃይማኖት “ሃይማኖት” የሚለው ቃል ሰዎች ስለ ሕይወት እና ልዕለ ተፈጥሮአዊ ኃይል ያላቸው እምነት ነው፡፡ ስለእነዚህ ነገሮች በዚያ ቤታ ፍርድ ይሰጣቸው ዘንድ አማራጭ ትርጉም፡ "የአይሁድ ሸንጎ በእነዚህ ጉዳዮች በተለከ ይህ ሰው ጥፋተኛ አድረገው ወሰኑበት"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ፊስጦስ ጉዳዩን ለንጉሥ አግሬጳ ማብራራቱን አጠናቀቀ፡፡ እንድጠብቁት አዘዝኳቸው አማራጭ ትርጉም፡ "ወታደሮች በእስር ቤት ውስጥ እንዲጠብቁት አዘዝኳቸሁ" "ነገ፣" ፊስጦስ እንዲህ አለ፣ "ትሰሙታላችሁ፡፡" "ፊስጦስ እንዲህ አለ፣ 'ነገ ጳውሎስ ስናገር መስማት ትችሉ ዘንድ አመቻቻለሁ፡፡'"
አግሪጳ እና በርኒቄ እነዚህ ስሞች በ ACT 25:13 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምካቸው ተመልከት፡፡ ጳውሎስ ወደ እነርሱ ዘንድ ቀረበ አማራጭ ትርጉም: "ጳውሎስን በእነርሱ ፊት ይቀር ዘንድ ይዘውት መጡ፡፡ ወደ እኔ ጮኹ "አይሁዳዊያን በእኔ ላይ ተቆጥተው ተናገሩ" ከእንግዲህ ወዲህ በሕይወት ልኖር ፈጽሞ አይገባውም ይህ ዓረፍተ ነገር አጽኖት ሰጥቶ የሚያስተላልፈው ከተባለው በተቃራኒ የሆነውን ነገር ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በአፋጣኝ መሞት ይኖርበታል፡፡"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ፊስጦስ ለንጉሥ አግሪጳ መናገሩን ቀጥሏል፡፡ እርሱን ወደ እናንተ ዘንድ ይዤው መጣሁ፣ በተለይም ወደ አንተ ወደ ንጉሥ አግሪጳ ዘንድ "ጳውሎስን ወደ እናንተ ሁሉ ዘንድ ይዤው መጣሁ ነገር ግን በተለይም አንተ ንጉሥ አግሪጳ ስለዚህ ተጨማሪ መጻሐፍ የሚችለው ነገር ይኖረኝ ዘንድ "ስለዚህ ሌላ መጻፍ እችል ዘንድ" ወይም "ስለዚህ ምን መጻፍ እንዳለብኝ አውቅ ዘንድ" አንድን እስረኛን የታሰረበት ምክንያት ምን እንደሆ በግልጽ ሳይጠቀስ ዝም ብሎ መላክ ምክንያታዊ አልመስል ብሎኛል "አንድን እስረኛ የታሠረበት ምክንያት ምን እንደሆነ በግልጽ ጽፎ መላክ ምክንያታዊ መስሎ ታይቶኛል" በእርሱ ላይ ያላቸው ክስ አማራጭ ትርጉሞች 1) የአይሁድ መሪዎች በእርሱ ላይ ያቀረቡት ክስ ወይም 2) በሮማዊያን ሕግ መሠረት ጳውሎስ ሊከሰስበት የሚችለው አንቀጽ፡፡
1 አግሪጳም ጳውሎስን፣ «አንተ ለራስህ ተናገር» አለው። ከዚያም በኋላ፣ ጳውሎስ እጁን ዘርግቶ መከላከያውን አቀረበ። 2 «ንጉሥ አግሪጳ ሆይ፣ ዛሬ በፊትህ አይሁድ ስለ ከፈቱብኝ ክስ ሁሉ መከላከያዬን ሳቀርብ ራሴን ደስተኛ አድርጌ እቈጥረዋለሁ፤ 3 ምክንያቱም በተለይ አንተ የአይሁድን ልማድና ጥያቄ ሁሉ ጠንቅቀህ ታውቃለህ። ስለዚህ በትግዕሥት እንድታደምጠኝ እለምንሃለሁ። 4 በእውነት ከልጅነቴ ጀምሮ በሕዝቤ መካከልና በኢየሩሳሌም እንዴት እንደ ኖርሁ አይሁድ ሁሉ ያውቃሉ። 5 ከመጀመሪያው አንሥቶ እኔን ያውቁኛል፤ የሃይማኖታችን በጣም ወግ አጥባቂ ክፍል ፈሪሳዊ ሆኜ እንደ ኖርሁም ሊያምኑ ይገባል። 6 አሁን እዚህ ለፍርድ የቆምሁት እግዚአብሔር ለአባቶቻችን የሰጠውን ተስፋ የምፈልግ በመሆኔ ነው። 7 በዚህ ምክንያት ዐሥራ ሁለቱ ነገዶቻችን ቀንና ሌሊት በቅንነት እግዚአብሔርን ያገለግላሉ፤ እኛም ወደ እርሱ ለመድረስ ተስፋ እናደርጋለን። ንጉሥ ሆይ፣ አይሁድ እኔን የሚከሱኝ ስለዚህ ተስፋ ነው! 8 እግዚአብሔር ሙታንን እንደሚያስነሣ አይታመንም ብላችሁ ለምን ታስባላችሁ? 9 አንድ ጊዜ እኔ የናዝሬቱ ኢየሱስን ስም በመቃወም ብዙ ነገር ማድረግ አለብኝ ብዬ ዐሰብሁ። 10 በኢየሩሳሌምም ይህንኑ አደረግሁ፤ ከምእመናን ብዙዎችን ወኅኒ እንዲገቡ አደረግሁ፤ ለዚህም ከካህናት አለቆች ሥልጣን ተቀብዬ ነበር፤ በሚገደሉበት ጊዜም፣ ተስማምቻለው። 11 ብዙ ጊዜም በምኵራቦች ሁሉ እንዲቀጡ አድርጌአለሁ፤ የስድብ ቃል እንዲናገሩም ጥረት አድርጌአለሁ። ምእመናኑን እጅግ እቈጣቸውና ሌሎች ከተሞች እንኳ አሳድዳቸው ነበር። 12 ይህን እያደረግሁ፣ ከካህናት አለቆች ሥልጣንና ትእዛዝ ተቀብዬ ወደ ደማስቆ ሄድሁ፤ 13 ወደዚያ በመጓዝ ላይ እያለሁም ንጉሥ ሆይ፣ እኩለ ቀን ላይ ከፀሐይ ይልቅ የሚያበራ ብርሃን ከሰማይ አየሁ፤ በእኔና አብረውኝ ይጓዙ በነበሩት ሰዎች ዙሪያም አበራ። 14 ሁላችንም በመሬት ላይ በወደቅን ጊዜ፣ በዕብራይስጥ ቋንቋ፣ «ሳውል፣ ሳውል፣ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? የመውጊያውን ብረት ብትረግጥ ለአንተ ይከፋብሃል» የሚል ድምፅ ሲናገረኝ ሰማሁ። 15 እኔም፣ 'ጌታ ሆይ፣ አንተ ማን ነህ?' አልሁ። ጌታም እንዲህ ብሎ መለሰልኝ፤ 'አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ። 16 ተነሣና በእግርህ ቁም፤ እኔ የተገለጥሁልህ አሁን ስለ እኔ ስለምታውቃቸውና ኋላ ላይ ስለማሳይህ ነገሮች አገልጋዬና ምስክር እንድትሆን ልሾምህ ነው፤ 17 ወደ እነርሱ ከምልክህ ሕዝብና ከአሕዛብም አድንሃለሁ ፤ 18 ዐይናቸውን እንድትከፍትላቸውና ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከሰይጣን ኃይልም ወደ እግዚአብሔር እንድትመልሳቸው አደርግሃለሁ፤ ይኸውም በእኔ በማመናቸው ለራሴ የለየኋቸው እነርሱ፣ ከእግዚአብሔር የኃጢአትን ይቅርታና ርስትን እንዲቀበሉ ነው።' 19 ስለዚህ፣ ንጉሥ አግሪጳ ሆይ፣ ለሰማያዊው ራእይ አልታዘዝም አላልሁም፤ 20 ነገር ግን መጀመሪያ በደማስቆ ላሉት፣ ከዚያም በኢየሩሳሌም፣ በመላው ይሁዳ፣ ደግሞም ለአሕዛብ ንስሓ እንዲገቡ፣ ወደ እግዚአብሔር ዘወር እንዲሉና ለንስሓ የሚገባ ሥራ እንዲሠሩ ሰበክሁ። 21 በዚህ ምክንያት አይሁድ በቤተ መቅደስ ያዙኝና ሊገድሉኝ ሞከሩ። 22 እስካሁን ድረስ እግዚአብሔር ረድቶኛል፤ ስለዚህ ለታናናሾችና ለታላላቆች ለመመስከር እዚህ ቆሜአለሁ፤ ምስክርነቴም ሙሴና ነቢያት ይሆናል ብለው ከተናገሩት የሚያልፍ አይደለም፤ 23 ይኸውም ክርስቶስ መከራ ይቀበላል፤ ከሙታን ለመነሣትና ለአይሁድ ሕዝብ፣ ለአሕዛብም ብርሃንን ለመስበክ የመጀመሪያው ይሆናል የሚል ነው። 24 ጳውሎስም መከላከያውን እንደ ጨረሰ ፊስጦስ፣ «ጳውሎስ፣ አንተ ዕብድ ነህ፤ ብዙ መማርህ አሳብዶሃል» ሲል ጮኾ ተናገረ። 25 ጳውሎስ ግን እንዲህ አለ፤ «እጅግ የተከበርህ ፊስጦስ ሆይ፣ እኔ ዕብድ አይደለሁም፤ ነገር ግን እውነተኛውንና ትክክለኛውን ቃል በድፍረት እናገራለሁ። 26 ንጉሡ ስለ እነዚህ ነገሮች ያውቃልና እንደ ልብ እነግረዋለሁ፤ በመሆኑም ከእነዚህ ነገሮች አንዱም ከእርሱ የተሰወረ እንዳልሆነ እርግጠኛ ነኝ። 27 ንጉሥ አግሪጳ ሆይ፣ በነቢያት ታምናለህን? እንደምታምን ዐውቃለሁ።» 28 አግሪጳም ጳውሎስን፣ «በአጭር ጊዜ ልታሳምነኝና ክርስቲያን ልታደርገኝ ትፈልጋለህን?» አለው። 29 ጳውሎስም፣ «በአጭር ይሁን ወይም በረዥም ጊዜ፣ አንተ ብቻ ሳትሆን፣ ዛሬ የሚሰሙኝ ሁሉ፣ ከእነዚህ የወኅኒ ሰንሰለቶች በቀር እንደ እኔ እንድትሆኑ ወደ እግዚአብሔር እጸልያለሁ» አለ። 30 ከዚያም ንጉሡ፣ ገዥውም፣ በርኒቄም ደግሞ፣ ከእነርሱ ጋር ተቀምጠው የነበሩትም ተነሡ፤ 31 ከአዳራሹም በወጡ ጊዜ፣ እርስ በርስ ተነጋግረው ፣«ይህ ሰው ለሞት ወይም ለእስራት የሚያበቃ ምንም አላደረገም» አሉ። 32 አግሪጳ ፊስጦስን፣ «ይህ ሰው ወደ ቄሣር ይግባኝ ባይል ኖሮ በነጻ ሊለቀቅ ይችል ነበር» አለው።
አያያዥ ዓረፈተ ነገር : ፊስጦስ ጳውሎስን በንግሥ አግሪጳ ፊት አቀረበው፡፡ በቁጥር 2 ላይ ለንግሥ አግሪጳ ለተከሰሰበት ክስ ምላሽ መስጠት ጀመረ፡፡ እጆቹን ዘርግቶ "የሕዝቡን ትኩረት ማግኘት ይችል ዘንድ ወደሕዝቡ እጆቹን ዘርግቶ" ለተከሰሰበት ክስ መልስ ሰጠ "ለተከሰሰበት ክስ መልስ መስጠት ጀመረ" ራሴን ደስተኛ ሰው አድርጌ እቆጥረዋለሁ ጳውሎስ ደስተኛ ነበር ምክንያቱም በንጉሥ አግሪጳ ፊት መቆሙ ወንጌልን ለመናገር እድል ስለምሰጠው ነው፡፡
አይሁዳዊያን ሁሉ አማራጭ ትርጉሞች 1) ከጳውሎስ ጋር ያደጉት እና ፈርሳዊ ሆኖ የሚያውቁት አይሁዳዊያን ወይም 2) "ጳውሎስ በፈሪሳዊነቱ ከነበረው ቅናት የተነሣ በአይሁዳዊያን ዘንድ የታወቀ ነበር እንዲሁመም በአማኝነቱም የታወቀ ነው፡፡" በራሴ ሀገር አማራጭ ትርጉም 1) በራሱ ሕዝብ መካከል፣ ይህ ማለት የግድ በእስራኤል መልከአምድር ውስጥ ማለት ላይሆን ይችላል ወይም 2) በእስራኤል ምድር ውስጥ፡፡
አሁን ጳውሎስ ይህንን ቃል የተጠቀመው ለተከሰሰበት ክስ መልስ በመስጠት ሂደት ውስጥ ወደሌላኛው መከራከሪያ ነጥቡ መሰጋገሩን ለማሳየት ነው፡፡ ዛሬ ፍርድ ለመቀበል በዚህ እገኛለሁ አማራጭ ትርጉም: "እነርሱ ከሰውኝ ዘሬ በዚህ አለሁ" እግዚብሔር ለአባቶቻችን የገባውን ቃል እጠባበቃለሁ ጳውሎስ የመስሑን መምጣት ይጠብቃል፡፡ ወደዚያ እንደሚንደርስ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ "እግዚአብሔር የገባውን ተስፋ እንደሚንቀበል ተስፋ እናደርጋለን" እግዚአብሔር የሞተ ሰውን ማስነሳቱ ይህንን ያኸል የማይታመን ነው ብላችሁ ስለምን አሰባችሁ? ጳውሎስ ይህንን ንግግር የተናገረው አግሪጳ ጳውሎስ የተናገረው ነገር አግሪጳ ከዚህ በፊት እግዚአብሔር ሰዎችን ከሞት ማስነሳት እንደሚችል በማመኑ ምክንያት ከዚያ ጋር ለማያያዝ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "አንተ ራሰህ እግዚአብሔር ሰውን ከሞት ልያስነሣ ይችላል ብለሃል!"
በአንድ ጊዜ ጳውሎስ ይህንን ሀረግ የተጠቀመው ለክሱ የመከራከሪያ ሀሳቡን በማቅረብ ሂደት ውስጥ ለውጥ መኖሩን ለማሳየት ነው፡፡ ዘሂን ደግሞ እንዴት ቅዱሳንን ያሳድድ አንደነበር መናገር ጀመረ፡፡ የኢየሱስን ስም በመቃወም በዚህ ሥፍራ ላይ “ስም” የሚለው ቃል የኢየሱስን መልዕክ የሚውክል ነው፡፡አማራጭ ትርጉም: "የኢየሱስን መልዕክት በመቃወም፡፡" እነርሱን በመቃወም ድምፄን ሰጥቻለሁ "እነርሱን ለመቅጣት ደምፅ ሰጥቻለሁ" ብዙ ጊዜ እቀጣቸው ነበር አማራጭ ትርጉሞች 1) ጳውሎስ የተወሰኑ አማኞችን ብዙ ጊዜ ቀጥቶዋቸዋል ወይም 2) ጳውሎስ ብዙና የተለያዩ አማኞችን ቀጥቶዋል፡፡
ይህንን በማድረግ ላይ ሳለሁ ጳውሎስ ይህንን ሀረግ የተጠቀመው በክርክር ሀሳኑ ላይ ሌላ ለውጥ መኖሩን ለማሳየት ነው፡፡ አሁን ኢዩስን ከማሳደድ እርሱን ወደ መከተል ኢየሱስ እንዴት እደለወጠው መናገር ጀመረ፡፡ እያለe ይህ ቃል በሆነ ጊዜ የተጀመሩ ሁለት ነገሮችን ያመለክታል፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ጳውሎስ ቅዱሳንን በማሳደድ ላይ ሳለ ወደ ደማስቆ ሄዶ ነበር፡፡ ስልጣን ተሰጥቶ እንዲሁም ማዘዣ ወረቀት ይዞ ጳውሎስ ከአይሁድ መሪዎች ዘንድ የተሰጠው አይሁዳዊያን አማኞች ለማሳደድ የሚያስችለው ስልጣን የተሰጠበት ደብዳቤ በእጁ ይዞ ነበር፡፡ . እግዚአብሔር መቃወም በጣም ከባድ ነው ጳውሎስ የእግዚአብሔርን ዕቅድ መቃወምን በሬ የአራሹን በተር ከመቃወም ጋር እግዚአብሔር እንዳነጻጸረ ተናገረ፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ለንጉሥ አግሪጳ የመከራከሪያ ሀሳቡን ማቅረቡን ቀጥሏል፡፡ በእነዚህ ቁጥሮ ከጌታ ጋር ያደረገውን ነግግር በቀጥታ እያጣቀሰ ይናገራል፡፡ ለእኔ ለራሴ ለይቼሃለሁ "የራሴ አድርጌሃለሁ" (UDB) ወይም "ለራሴ ለይቼሃለሁ" በእኔ ላይ ባለህ እምነት ይህ በእግዚአብሔር ማመን እግዚብሔር ለራሱ የለያቸው ሰዎች መሆኑን ያሳያል፡፡ በእኔ ላይ ካላቸው እምነት የተነሣ ለራሴ የለየኋቸው ጳውሎስ የጌታን ንግግር በቀጥታ መጥቀሱን ጨርሶዋል፡፡
ስለዚህ በዚህ ሥፍራ ላይ “ስለዚህ” የሚለው ቃል ከዚህ በፊት በተነገረ አንድ ነገር ምክንያት ይህ እንደሆነ ያሳያል፡፡ በዚህ ሁኔታ ውሰጥም ጳውሎስ ጌታ በራዕይ ምን እንዳሳየው ከዚህ በፊት አብራርቶ ጨርሷል፡፡ ሰማያዊውን ራዕይ ለመታዘዝ አሻፈረኝ አላልኩም "በዚህ ራዕይ ከሰማይ መጥቶ ለተሰጠኝን መልዕክት ታዝዤያለሁ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ለንጉሥ አግሪጳ ያቀረበውን የመከራከሪያ ሀሳብ አጠናቀቀ፡፡. ነቢያት ያሉት ነገር ጳውሎስ የብሉይ ኪዳን ነቢያት ጽሑፎች ስብስብን እያመለከተ ነው፡፡ ክርስስ መከራን እነንዲቀበል "ክርስቶስ መከራን ይቀበል ዘንድ እና እንዲሞት" ብርሃንን ያውጅ ዘንድ "የድነትን መልዕክት ይናገር ዘንድ"
አንተ አብደሃል "ትርጉም ያሌለው ነገር መናገር ጀምረሃል" ወይም "አብደሃል" አላበድኩም "ጤነኛ ነኝ" ወይም "የማስበውም በትክክል ነው" በጥንቃቄ ልታሰብበት የሚገባ ነገር ነው "ጥንቃቄ ያስፈልገዋል" ወይም "ጥንቃ የሚያስፈልገው ጉዳይ" ለእርሱ በግልጽ ነገርኩት "ለንጉስ አግሪጳ በግልጽ ነገርኩት" ይህ በድብቅ የተደረገ ነገር አይደለም "በምስጥር የተደረገ ነገር አይደለም"
ንጉሥ አግሪጳ ሆይ በነቢያት ታምናለህን? ጳውሎስ ይህንን ጥያቄ ለንጉሥ አግሪጳ የጠየቀው ንጉሥ አግሪጳ ነቢያት ስለ ኢየሱስ የተናገሩትን ነገር ያምን ስለነበረ ለማስታወስ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "የአይሁድ ነቢያት የተናገሩትን ነገር አንተ ታምናለህ!" በዚህ አጭር ጊዜ ልታሳምነኝ እና ክርስትያን ልታደረገኝ ትፈልጋለህን? አግሪጳ ይህንን ጥያቄ የጠየቀው ጳውሎስ ሌሎች ተጨማሪ መረጃዎችን ሳያቀርብ አግሪጳን እንዲሁ በቀላሉ ማሳመን እንደማይችል ለማሳየት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እኔን እንዲሁ በቀላሉ ማሳመን እችላለሁ ብለህ አስበሃል!"
ከዚያም ንጉሡ እና አገረ ገዥው ከመቀመጫቸው ተነሡ "ከዚያም ንጉሥ አግሪጳ እና አገረ ገዥው ፊስጦስ ከመቀመጫቸው ተነሡ"
1 ወደ ኢጣሊያ በመርከብ እንድንሄድ በተወሰነ ጊዜ፣ ጳውሎስንና ሌሎችን እስረኞች የአውግስጦስ ክፍለ ጦር አባል ለሆነ ዩልዮስ ለተባለ የመቶ አለቃ አስረከቡአቸው። 2 እኛም ከአድራሚጥዮን ተነሥተን በእስያ ጠረፍ ሊሄድ በተዘጋጀ መርከብ ላይ ተሳፍረን ወደ ባሕር ተጓዝን። በመቄዶንያ ካለችው ተሰሎንቄ የሆነው አርስጥሮኮስም ከእኛ ጋር ሄደ። 3 በማግስቱ ወደ ሲዶን ከተማ ደርሰን፣ ከመርከብ ወረድን፤ እዚያም ዩልዮስ ለጳውሎስ ቸርነት አደረገለት፤ ወደ ወዳጆቹ እንዲሄድና እንክብካቤ እንዲያደርጉለትም ፈቀደለት። 4 ከዚያም ተነሥተን ወደ ባሕር ሄድን፤ ነፋስ ይነፍስብን ስለ ነበር፣ በመርከብ ሆነን ነፋሱ በማያገኛት በቆጵሮስ ደሴት ዙሪያ ተጓዝን። 5 በኪልቅያና በጵንፍልያ አጠገብ ያለውን ባሕር ከተሻገርን በኋላም፣ የሉቅያ ከተማ ወደ ሆነው ወደ ሙራ ደረስን። 6 በዚያም፣ የመቶ አለቃው ከእስክንድርያ ወደ ኢጣሊያ የሚሄድ መርከብ አግኝቶ አሳፈረን። 7 ብዙ ቀንም በዝግታ ተጓዝንና በመጨረሻ በችግር ወደ ቀኒዶስ ደረስን፤ ነፋሱም በዚያ መንገድ እንዳንሄድ ስለከለከለን፣ በሰልሙና አንጻር ያለችውን ቀርጤስን ተገን አድርገን ተጓዝን። 8 በላሲያ ከተማ አጠገብ ወዳለው መልካም ወደብ ወደ ተባለው ስፍራ እስከምንደርስ ድረስ በችግር በጠረፉ በኩል ተጓዝን። 9 ብዙ ጊዜም አሳለፍን፤ የአይሁድ የጾም ወራት ደግሞ ዐልፎ ነበር፤ ጕዞውን መቀጠልም አደጋ የሚያስከትል ነበር። ስለዚህ ጳውሎስ አስጠነቀቃቸው፤ 10 እንዲህም አለ፤ “እናንተ ሰዎች፣ አሁን የምናደርገው ጕዞ አደጋና ብዙ ጉዳት እንደሚኖርበት ይታየኛል፤ አደጋውም በመርከቡና በጭነቱ ብቻ ሳይሆን፣ በእኛም ሕይወት ላይ የሚደርስ ነው።” 11 የመቶ አለቃው የሰማው ግን ጳውሎስ የተናገረውን ሳይሆን፣ በይበልጥ የመርከቡ አዛዥና ባለቤት ያሉትን ነው። 12 ክረምቱን ለማሳለፍ ወደቡ ተስማሚ ስላልነበረ፣ አብዛኛዎቹ ተጓዦች የሚቻል ከሆነ ከዚያ ተነሥተን ፊንቄ ወደ ተባለችው ከተማ እንድንሄድና ክረምቱን እዚያ እንድናሳልፍ ምክር ሰጡን። ፊንቄ በሰሜን ምሥራቅና በደቡብ ምሥራቅ አንጻር የምትገኝ የቀርጤስ ወደብ ነች። 13 የደቡቡ ነፋስ በቀስታ መንፈስ በጀመረ ጊዜ፣ መርከበኞቹ የፈለጉት እንደተከናወነላቸው ዐሰቡ። ስለዚህ ሸራውን አውርደው በባሕሩ ዳርቻ አቅራቢያ፣ በቀርጤስ በኩል አለፉ። 14 ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን፣ የሰሜን ምሥራቅ ዐውሎ ነፋስ የተባለ ኃይለኛ ነፋስ ደሴቲቱን አቋርጦ በመምጣት ይነፍስብን ጀመረ፤ 15 መርከቡም ወደ ፊት በተገፋና ነፋሱን መቋቋም ባልቻለ ጊዜ፣ ዝም ብለነው በነፋሱ እየተነዳን ሄድን። 16 ቄዳ የተባለችውን ትንሽ ደሴት ተተግነን ተጓዝን፤ በትልቅ ችግርም ሕይወት አድን ጀልባው ላይ መውጣት ቻልን። 17 መርከበኞቹ ጀልባውን ወደ መርከቡ ጎትተው አወጡት፤ ገመዱንም የመርከቡን ዙሪያ ለማሰር ተጠቀሙበት። ስርቲስ በምትባል አሸዋማ ስፍራ እንዳንወድቅ ፈርተው ነበር፤ ስለዚህ የባሕር ሸራውን አውርደው እየተነዱ ሄዱ። 18 ዐውሎ ነፋሱ በጣም ስላየለብን፣ በማግስቱ መርከበኞቹ የመርከቡን ጭነት ወደ ባሕር መጣል ጀመሩ። 19 በሦስተኛው ቀን መርከበኞቹ በመርከቡ የሚያገለግሉ ዕቃዎችን እያነሡ ጣሉ። 20 ለብዙ ቀንም ፀሐይና ከዋክብት ብርሃናቸውን ባልሰጡንና ትልቁ ማዕበልም በወረደብን ጊዜ፣ አንድንም ብለን ተስፋ ቈረጥን። 21 ተጓዦቹ ምግብ ሳይበሉ ብዙ ቀን ቈይተው ነበር፤ በዚያን ጊዜ ጳውሎስ በተጓዦቹ መካከል ቆሞ እንዲህ አለ፤ “እናንተ ሰዎች፣ ይህ አደጋና ጉዳት እንዳይደርስባችሁ፣ ከቀርጤስ አትነሡ ብዬ የነገርኋችሁን መስማት ነበረባችሁ፤ 22 አሁንም መርከቡ ብቻ ይጎዳል እንጂ ከመካከላችሁ የሚሞት አይኖርምና አይዞአችሁ ብዬ እመክራችኋለሁ። 23 ምክንያቱም ባለፈው ሌሊት የእርሱ የሆንሁትና ደግሞም የማመልከው የእግዚአብሔር መልአክ በአጠገቤ ቆሞ እንዲህ ብሏል፤ 24 “ጳውሎስ ሆይ፣ አትፍራ። በቄሣር ፊት ልትቆም ይገባሃል፤ ተመልከት፤ እግዚአብሔር በቸርነቱ ዐብረውህ የሚጓዙትን ሁሉ ሰጥቶሃል። 25 ስለዚህ እናንተ ሰዎች፣ አይዞአችሁ፤ ልክ እንደ ተናገረኝ እንደሚሆን እግዚአብሔርን አምነዋለሁ። 26 ነገር ግን ወደ አንዲት ደሴት ደርሰን ልናርፍ ይገባል።” 27 በዐሥራ አራተኛውም ሌሊት፣ በአድርያቲክ ባሕር ወዲያና ወዲህ እየተንገላታን እያለን፣ እኩለ ሌሊት ገደማ፣ መርከበኞቹ ወደ መሬት የቀረቡ መሰላቸው። 28 የባሕር ጥልቀት መለኪያ ገመድ ጣሉና ጥልቀቱን አርባ ሜትር ሆኖ አገኙት፤ ከጥቂት ጊዜ በኋላ፣ መለኪያውን ሲጥሉም ሠላሳ ሜትር ሆኖ አገኙት። 29 ከዐለቶቹ ጋር እንጋጫለን ብለውም ፈሩ፤ ስለዚህ ከኋላ አራት መልሕቆችን አውርደው ቶሎ እንዲነጋ ጸለዩ። 30 መርከበኞቹ መርከቡን ትተው ለመሄድ መንገድ ይፈልጉና ሕይወት አድን ጀልባውን ወደ ባሕሩ ውስጥ ያወርዱ ነበር፤ መልሕቆቹንም ከቀስቱ የሚወረውሩ መሰሉ። 31 ጳውሎስ ግን መቶ አለቃውንና ወታደሮቹን፣ “እነዚህ ሰዎች በመርከቡ ካልቆዩ በቀር፣ እናንተ መዳን አትችሉም” አላቸው። 32 ከዚያም ወታደሮቹ የጀልባውን ገመዶች ቈረጡት፤ እንዲንሳፈፍም አደረጉት። 33 ቀኑ ሊነጋ ሲልም፣ ምግብ እንዲበሉ ጳውሎስ ሁሉንም መከራቸው። እንዲህም አላቸው፤ “ምንም ሳትበሉ ከቈያችሁ ይህ ዐሥራ አራተኛ ቀናችሁ ነው። 34 ስለዚህ በሕይወት እንድትኖሩ፣ ጥቂት ምግብ እንድትበሉ እለምናችኋለሁ፤ ከራሳችሁ ላይ አንዲቱም ጠጕር አትጠፋም።” 35 ይህን ተናግሮ፣ እንጀራ አነሣና በሁሉም ፊት እግዚአብሔርን አመሰገነ። ከዚያም እንጀራውን ቈርሶ መብላት ጀመረ። 36 በዚያን ጊዜ ሁሉም ተጽናንተው ምግብ በሉ። 37 በመርከቡ ውስጥ 276 ሰዎች ነበርን። 38 በልተው በጠገቡ ጊዜም፣ ስንዴውን ወደ ባሕሩ በመጣል የመርከቡን ጭነት አቃለሉ። 39 በነጋታውም፣ የነበሩበትን ምድር አላወቁትም፤ ነገር ግን በዳርቻ ያለውን የባሕር ሰርጥ አዩ፤ መርከቡን ወደ ሰርጡ መግፋት ይችሉ እንደሆነም ተነጋገሩ። 40 ስለዚህ መልሕቆቹን ቈርጠው ባሕሩ ላይ ተዉአቸው። በዚሁ ጊዜም የመቅዘፊያዎቹን ገመዶች ፈትተው ሸራውን ወደ ነፋሱ ከፍ አደረጉና ወደ ባሕሩ ዳርቻ ለመውጣት ሄዱ። 41 ነገር ግን ሁለት ማዕበሎች ወደ ተገናኙበት ስፍራ መጡ፤ መርከቡም ወደ መሬት ገባ፤ የመርከቡ ቅስትም በዚያ ተተከለና የማይነቃነቅ ሆነ፤ የኋላ ክፍሉ ግን ከማዕበሉ ነውጥ የተነሣ ይሰባበር ጀመር። 42 የወታደሮቹ ዕቅድ ከመካከላቸው ማንም ዋኝቶ እንዳያመልጥ እስረኞቹን ለመግደል ነበር። 43 የመቶ አለቃው ግን ጳውሎስን ለማዳን ፈለገ፤ ስለዚህ ዕቅዳቸውን አልተቀበለም፤ መዋኘት የሚችሉትም በመጀመሪያ ከመርከቡ ላይ እየዘለሉ ወደ የብስ እንዲወጡ አዘዘ። 44 ከዚያም የቀሩት ሰዎች በሳንቃዎችና ከመርከቡ በተገኙ ስብርባሪዎች ላይ ሆነው ተከትለው እንዲወጡ አደረገ። በዚህ ዐይነት ሁላችንም በደኅና ወደ የብስ ወጣን።
አጠቃላይ መረጃ: ጳውሎስ ወደ ሮም ጉዞ ጀመረ፡፡ ይህ በተወሰነ ጊዜ አማራጭ ትርጉም፡ "ሀገረ ገዥው ይህንን በወሰነ ጊዜ" በመርከብ መሄድ ጀመርን በዚህ ክፍል ውስጥ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጸሐፊውን ሉቃስን እና ጳውሎስን ነው፡፡ እርሱ ጳውሎስ ወደ ሮም ስጓዝ አብሮት ተጉዞ ነበር፡፡ ወደ ጣሊያን በመርከብ ሄዱ ጣሊያን በሮም ውስጥ ያለች የአንድ አከባቢ ስም ነው፡፡ ዩልዩስ የተባለ መቶ አለቃ ዩልዩስ የወንድ ስም ነው፡፡ የአውጉስጦስ ጭፍራ ይህ የብዙ ሠራዊት መጠሪያ ስም ነው ወይም መቶ አለቃው ያለበት የወታደር ቡድን ስም ነው፡፡ በአድራሚጢስ መርከብ አማራጭ ትርጉም 1) ከአድራሚጢስ የሚመጣ መርከብ ወይም 2) በአድራሚጢስ ስም የተመዘገበ ወይም ፈቃድ ያወጣ መርከብ፡፡ ይህ ምናልባት በዘሟ ቱርክ በምዕራብ አከባቢ የሚገኝ ሥፍራ ሊሆን ይችላል፡፡ በመርከብ ለመጓዝ ጸዘጋጅታ ሻሉ "ለመገዋዝ ተዘጋጅተው" ወይም "ዝግጅታቸውን አጠናቀው" በባሕሩ ላይ መሄድ ጀመርን "በባሕሩ ላይ ጉዞዋችንንን ጀመርን" አርስጥሮኮስ ይህን በ ACT 19:29 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
ዩልዩስ ጳውሎስን በመልካም መንገድ አስተናገደው "ዩልዩስ ጳውሎስን በመልካም መንገድ አስተናገደው፡፡" “ዩልዩስ” የሚወለውን ስም በምን ዓይነት መንገድ አንተረጎምከው በ ACT 27:1 ተመልከት፡፡ እንክብካቤ ያደርጉለት ዘንድ ወደ ጓደኞቹ ዘንድ ሄደ "አስፈላጊውን እንክብካቤ ለማግኘት ወደ ጓደኞቹ ዘንድ ሄደ" ወይም "አስፈላጊውን እገዛ ለማግኘት ሲል ወደ ጓደኞቹ ዘንድ ሄደ" በቆጵሮስ ደሴት አድርገን አውሎ ንፋሱን ተከልለን ሄድን "ከአውሎ ንፋሱ ለመከለክ ስንል በቆጵሮስ ደስት ደሴት በኩል አድረገን ተጓዝን" (UDB) ጵንፍልያም ይህንን በ ACT 2:10 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ በሉቅያ ወዳለ ወደ ሙራ ደረስን። ሙራ በሉቅያ ውስጥ የሚትገኝ ከተማ ናት፡፡ ይህች ከተማ በዘመኗ ቱርክ ውስጥ በደቡብ ምዕራብ አከባቢ ተገኛለች፡፡ የሉቅያ ከተማ ሉቅያ የሮም ግዛት ስትሆን በዘመኗ ቱርክ ውስጥ በደቡብ ምዕራብ አከባቢ ትገኛለች፡፡ አሌክሳንደሪያa ይህ የአንድ ከተማ ስም ነው፡፡ ጣሊያን ይህንን በ ACT 27:1 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
ቀኒዶስ አቅራቢያ ይህ በዘመኗ ቱርክ ውስጥ የሚገኝ በጥንት ጊዜ ሰዎች ሠፍረውበት የነበረ ሥፍራ ነው፡፡ ሰልሙና ተቃራኒ ይህች የቀርጤስ ወደብ ከተማ ናት፡፡ መልካም ወደብ ይህ በልሳ አቅራቢያ የሚገኝ ከቀርጤስ ወደብ በስተደበቡ የሚገኝ ሥፍራ ነው፡፡ ለላሲያ ከተማ አቅራቢያ ይህች በቀርጤስ ውስጥ የሚትገኝ ወደብ ናት፡፡
አሁን ብዙ ጊዜ ወሰድን በንፋሱ አቅጣጫ ምክንያት ከቄሳሪያ ወደ መልካም ወደብ ያደረግነው ጉዞ ከታሰበው ቀን በላይ ፈጅቷል፡፡ የአይሁዳዊያን የጾምራጽም አልፏል ይህ ጾም ከመስከርም ወር ውስጥ ካለው የመስዋእት ዕለት አንስቶ እስከ ጥቅም ድረስ የሚቆይ በየዓቱ የሚደረግ ነው፡፡ ከዚህ ጊዜ በኋላ ከፍተኛ ማዕበል የመነሣት ዕድሉ ከፍተኛ ነው፡፡
መርከብቱ ይህንን ንፋስ የመቋቋም አቅም አይኖራትም "ይህንን ወጀብ ለመቋቋም የሚያስችል አቅም አይኖራትም" የፍንቄ ከተማ ፍንቄ በቀርጡስ ደሴት ውስጥ የሚትገኝ አንድ ወዳብ ናት፡፡ ከባድ መኀልቅ “ከባድ” የሚለው ቃል የሚመለክተው ከውሃ ውስጥ ለማውጣት ነው፡፡ መኀልቅ ከመርከብቱ ጋር በገመድ የሚታሠር መርከብቱ እንዳትቀሳቀስ የሚያደረግ ከባድ ዕቃ ነው፡፡ መኀልቁ በውሃ ውስጥ ከተጨመረ በኋላ ወደ ውሃው ውስጥ ይጣላልና መርከብቱ እንዳትሄድ ያደርጋል፡፡
ከባድ አውሎንፋሰስ "በጣም ጠንካራ እና አደገኛ የሆነ ንፋስ" ሸራ "ከንፋሹ ተከለሉ" ቄዳ ወደሚባል ትንሽ ደሴት ይህች ደሴት ከቀርጤስ ደሴት በስተደቡብ የሚትገኝ ናት፡፡
ወደላይ አወጧት "ተሸክመው አወጧት" ስርቲስም ወደ ተባለ አሸዋማ ሥፍራ ይህ ጥልቅ ያልሆነ አሸዋማ የሐይቁ ክፍል ሲሆን መርከቦችም በዚያ ተቀርቅረው ይቀራሉ፡፡ "ስርቲስ" በሰሜን አፍርካ ሊቢያ አከባቢ የሚገኝ ሥፍራ ነው፡፡ በንፋሱ እየተመራን ሄድን አማራጭ ትርጉም፡ "ንፋሱ በሚወስደን አቅጣጫ መጓዝ ግድ ሆነብን"
የመትረፈስ ተስፋችን ሁሉ ተሟጠጠ አማራጭ ትርጉም፡ "ሁሉም ሰው እንተርፋለን የሚለው ተስፋው ተሟጠጠ"
ከተጓዦቹ መካከል ከሰዎቹ መካከል" ጉዳት የሚደርስበት እና የሚጠፋ "በዚህ ምክንያት የሚጎዳ እና የሚጠፋ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ በመርከብቱ ለሚጓዙ ሰዎች መናገሩን ቀጠሏል፡፡ ከአንተ ጋር በመርከብቷ የሚጓዙ ሰዎችን ሁሉንም ሰጥቼሃለሁ "ከአንተ ጋር በመርከብቷ የሚጓዙ ሰዎች በሕይወት ይኖሩ ዘንድ ወስኛለሁ" አንድ ደሴት ፈልገን ወደዚያ መጠጋት ይኖርብናል "መርከቧ በአንድ ደሴት ላይ መቆም ይኖርባታል"
በአድርያ ባሕር ይህ በጣሊያን እና በግሪክ መካል ያለ ባሕር ነው፡፡ ለኩት የሐይቁን ውሃ መጠን ለኩት (UDB)፡፡ ሃያ የሰው ቁመት አገኙ "20 የሰው ቁመት አገኙ" ወይም "40 ሜትር አገኙ፡፡" ይህ የመለኪያ መንገድ ነው፡፡ ዐሥራ አምት የሰው ቁመት አገኙ "15 የሰው ቁመት አገኙ" ወይም "30 ሜትር" ከመርከብቱ በስተኋላ "በከመርከብቱ በስተዋኋላ"
ከጸጉርህ አንድ ዘለላ እንኳ አትጠፋም ይህ በአንተ ላይ ምንም ጉዳት አይደርስም ለማለት የተለመደ ንግግር ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ይህንን አስቸጋሪ ሁኔታ ያለምንም ጉዳ ሁላችሁም ታልፋላችሁ፡፡" መዕድ ቆረሰ "ዳቦ ሁለት ወይም ከዚያ በላ ቆርሶ" ወይም ዳቦውን ቆራርሶ"
በመርከብቱ ውስጥ የነበርነው ወደ 276 ሰዎች ነን "በመርከብቷ ውስጥ ወደሁለት መቶ ሰባ ስድተስ ሰዎች ነበርን፡፡" ይህ የኋላ ታርክ መረጃ ነው፡፡
ዬት ቦታ እንደሆነ አላወቁም "አንድ ሥፍራ ተመለከቱ ነገር ግን ይህ እነርሱ የሚያውቁት ሥፍራ አልነበረም" መኀልቁን ፈተው በውሃ ውስጥ ተውት "ገመዱን ቆርጠው መኀልቁን በዚያ ተውት" ወደባሕሩ ዳርቻ አመሩ "steered the ship toward the beach"
የወታደሮቹ እቅድ የነበረው "የወታደሮቹ እቅድ" ወደ ውሃ ውስጥ መዝለል "ከመርከብቱ ወደ ውሃው ውስጥ መዝለል"
1 ወደ መሬት በደኅና በደረስን ጊዜም፣ ደሴቲቱ ማልታ የምትባል መሆንዋን ዐወቅን። 2 የዚያች ደሴት ሰዎችም የተለመደውን ደግነት እንኳ አላሳዩንም፤ ሆኖም፣ በማያቋርጠው ዝናብና ብርድ ምክንያት እሳት አንድደው ሁላችንንም ተቀበሉን። 3 ነገር ግን ጳውሎስ ጭራሮ ሰብስቦ እሳቱ ላይ በጨመረው ጊዜ፣ ከሙቀቱ የተነሣ አንድ እፉኝት ወጣና በእጁ ላይ ተጣበቀ። 4 የደሴቲቱ ሰዎችም እፉኝቱ ከእጁ ላይ ተንጠልጥሎ ባዩ ጊዜ፣ እርስ በርሳቸው፣ “ይህ ሰው በእርግጥ ከባሕር ያመለጠ ነፍሰ ገዳይ ስለ ሆነ፣ ፍትሕ በሕይወት እንዲኖር አልፈቀደለትም” ተባባሉ። 5 ጳውሎስ ግን እፉኝቱን በእሳቱ ላይ አራገፈው፤ አልተጐዳምም። 6 ሰዎቹም ሰውነቱ በትኵሳት ያብጣል ወይም በድንገት ይሞታል ብለው ይጠባበቁ ነበር። ነገር ግን ረዘም ላለ ጊዜ ተጠባብቀውት ምንም እንዳልደረሰበት ካዩ በኋላ፣ ዐሳባቸውን ለውጠው አምላክ ነው አሉ። 7 በአቅራቢያው ባለ አንድ ስፍራም ፑብልዮስ የተባለ የደሴቲቱ ገዢ መሬት ነበር፤ እርሱም ተቀብሎን ሦስት ቀን በደግነት አስተናገደን። 8 የፑብልዮስ አባት ትኵሳትና ተቅማጥ ይዞት ታሞ ነበር። ጳውሎስ ወደ እርሱ ሄዶ ጸለየ፤ እጆቹን ጫነበት፤ ፈወሰውም። 9 ይህ ከሆነ በኋላ፣ በደሴቲቱ የሚኖሩ ታመው የነበሩ ሌሎች ደግሞ መጡና ተፈወሱ። 10 ሰዎቹም እጅግ አከበሩን። ለመሄድ በምንዘጋጅበት ጊዜም፣ የሚያስፈልገንን ሰጡን። 11 ከሦስት ወር በኋላ፣ አፍንጫው ላይ የመንታ ወንድማማች ዓርማ በነበረበት፣ ክረምቱን በደሴቲቱ ባሳለፈ የእስክንድርያ መርከብ ላይ ተሳፍረን ጕዞ ጀመርን። 12 ወደ ሲራኩስ ከተማ ከደረስን በኋላም፣ እዚያ ሦስት ቀን ቈየን። 13 ከዚያም ተጕዘን ወደ ሬጊዩም ከተማ ደረስን። ከአንድ ቀን በኋላ የደቡብ ነፋስ ተነሣ፤ በሁለት ቀንም ወደ ፑቲዮሉስ ከተማ መጣን። 14 እዚያም አንዳንድ ወንድሞችን አገኘንና ከእነርሱ ጋር ሰባት ቀን እንድንቈይ ተጋበዝን። በዚህ ዐይነት ወደ ሮም መጣን። 15 ከዚያም ወንድሞች ስለ እኛ ከሰሙ በኋላ፣ ሊቀበሉን አፍዩስ ገበያና ሦስቱ ማደሪያዎች ድረስ መጡ። ጳውሎስ ወንድሞችን ባየ ጊዜ፣ እግዚአብሔርን አመሰገነ፤ ተጽናናም። 16 ወደ ሮም በገባን ጊዜ፣ ጳውሎስ ከሚጠብቀው ወታደር ጋር ብቻውን እንዲኖር ተፈቀደለት። 17 ቀን በኋላ፣ ጳውሎስ በአይሁድ መካከል መሪዎች የነበሩትን ሰዎች አንድ ላይ ጠራ። በተሰበሰቡ ጊዜም፣ እንዲህ አላቸው፤ “ወንድሞች ሆይ፣ በሕዝቡ ወይም በአባቶች ሥርዓት ላይ የፈጸምሁት ስሕተት ባይኖርም እንኳ፣ ከኢየሩሳሌም በእስረኝነት ለሮማውያን እጅ ተላልፌ ተሰጠሁ። 18 እነርሱ ከመረመሩኝ በኋላ ለሞት የሚያበቃኝ ምክንያት ስላልነበረብኝ፣ በነጻ ሊለቁኝ ፈልገው ነበር። 19 ነገር ግን አይሁድ የሮማውያንን ፍላጎት ተቃውመው በተናገሩ ጊዜ፣ በሕዝቤ ላይ የማቀርበው ክስ ባይኖረኝም እንኳ፣ ወደ ቄሣር ይግባኝ ለማለት ተገደድሁ። 20 በዚህ ምክንያት፣ ላያችሁና ላነጋግራችሁ ልመና አቅርቤአለሁ፤ ምክንያቱም እኔ በዚህ ሰንሰለት የታሰርሁት ለእስራኤል ስለ ተሰጠው እምነት ነው።” 21 ከዚያም እነርሱ እንዲህ አሉት፤ “ከይሁዳ ስለ አንተ ደብዳቤ አልደረሰንም፤ ከወንድሞች መካከልም ስለ አንተ ያወራ ወይም ክፉ የተናገረ የለም። 22 ነገር ግን በሁሉም ስፍራ ተቃውሞ እየተወራበት መሆኑን እኛ ስለምናውቅ፣ ስለዚህ የሃይማኖት ወገን ምን እንደምታስብ ከአንተ መስማት እንፈልጋለን።” 23 ለጳውሎስ ቀን በቀጠሩለት ጊዜም፣ ብዙ ሰዎች ወደ መኖሪያ ቤቱ መጡ። እርሱም ጉዳዩን ገለጠላቸው፤ ስለ እግዚአብሔር መንግሥትም መሰከረላቸው። ከጠዋት እስከ ማታም ከሙሴ ሕግና ከነቢያት እየጠቀሰ፣ ስለ ኢየሱስ ሊያሳምናቸው ጥረት አደረገ። 24 አንዳንዶች የተናገረውን ቃል ሲያምኑ፣ ሌሎች ግን አላመኑም። 25 እርስ በርሳቸው ሳይስማሙ ሲቀሩ፣ ጳውሎስ ይህን አንድ ቃል ከተናገረ በኋላ ሄዱ፤ “መንፈስ ቅዱስ በነቢዩ ኢሳይያስ አማካይነት ለአባቶቻችሁ በትክክል ተናገረ። 26 እንዲህም አለ፤ ‘ወደዚህ ሕዝብ ሂድና እንደዚህ በላቸው፤ ‘መስማትስ ትሰማላችሁ፤ ነገር ግን አታስተውሉም፤ ማየትስ ታያላችሁ፤ ነገር ግን ልብ አታደርጉም። 27 በዐይናቸው እንዳያዩ፣ በጆሮአቸው እንዳይሰሙ፣ በልባቸው እንዳያስተውሉ፣ ተመልሰውም እንዳልፈውሳቸው፣ የዚህ ሕዝብ ልብ ደንድኖአል፤ ዐይናቸውም ተጨፍኖአል።’ 28-29 ስለዚህ፣ ይህ የእግዚአብሔር ድነት ወደ አሕዛብ እንደ ተላከ፣ እነርሱም እንደሚቀበሉት ዕወቁ። 30 ጳውሎስ በተከራየው በራሱ ቤት ሁለት ዓመት ሙሉ ኖረ፤ ወደ እርሱ የሚመጡትንም ሁሉ ይቀበል ነበር። 31 የእግዚአብሔርን መንግሥት ይሰብክ፣ ያስተምርም ነበር። ይህንም ሲያደርግ ማንም አልከለከለውም።
አወቅን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን እናበዘዚህ ጉዞ ላይ ከጳውሎስ ጋር አብሮ የተጓዘውን የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ጸሐፊ የሆነውን ሉቃስን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም "ከሰዎቹ አወቅን" ወይም "ከነዋሪዎቹ ጠይቀን ተረዳን፡፡" ደሴትቱ መላጥያ ትባላለች መላጥያ በአሁኗ ሲስል ደቡብ አከባቢ የሚትገኝ ደሴት ናት፡፡ የሀገሩ ሰዎች “የሀገሩ ሰዎች” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የግሪክ ቋንቋ መናገር የሚችሉ ሰዎች የግሪክ ባሕልን የተቀበሉ ሰዎች ናቸው፡፡ የሚያስገርም ቸርነት ይህ ሀረግ ከሚቀጠበው ተቃራኒ የሆነ ነገርን ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ታላቅ ቸርነት፡፡" እሳት አቀጣጥለው "እንጨት ሰብስበው እሳት አቀጣጠሉልን" ሁላችንንም በደስታ ተቀበሉን አማራጭ ትርጉሞች 1) "በመርከብቷ ውስጥ ያሉትን ሰዎች ሁሉ በደስታ ተቀበሉ" ወይም 2) "ጳውሎስን እና ከእርሱ ጋር የነበረሩትን ሁሉ በደስታ ተቀበሏቸው፡፡"
እፋኝት ወጣች "ከሚነደው እሳት ውስጥ መርዛማ የሆነች እባብ ወጣች" ከእጁ ጋር ተጣበቀች "የጳውሎስን እጅ ይዛ አለቀም አለች" ይህ ሰው በእርግጥም ነፍስ አጥፍ ነው አሉ "በእርግጠኝነት ይህ ሰው ነፍሰ ገዳይ ነው አሉ" ወይም "ይህ ሰው በእርግጥም ነፍሰ ገዳይ ነው" ይሁን እንጂ ፍትሕ በሕይወት እንዲቆይ አልፈቀደለትም "ፍትሕ ተብላ የሚትጠራ አምላክ ከሞት እንዲያመልጥ አልፈቀደችለተም"
እባቧን ወደ እሳት ውስጥ አራግፎ ጣላት "እባብቱን ከእጁ ላይ አራግፎ ወደ እሳቱ ውስጥ ጣላት" ተመርዞ ወዲያው ይወድቃል አማራጭ ትርጉሞች 1) ከፍተኛ ትኩሰሳት ይይዘዋል ወይም 2) ያብጣል፡፡ በእርሱ ላይ የታየ ለውጥ አልነበረም አማራጭ ትርጉም: "ሁሉን ነገር እንደቀድሞው ነበር" አምላክ ነው አሉ በመርዛማ እባብ ከተነደፈ በኋላ በሕይወት የሚኖር ሰው መለኮት ወይም አምላክ ነው የሚል እምነት አለ፡፡
በዚያም ስፍራ አጠገብ "በዚያ" የሚለው ቃል በታሪኩ ውስጥ አዲስ ሰው ወይም ነገር እንደተካተተ አመለካች ነው፡፡ የደሴትቱ አለቃ አማራጭ ትርጉሞች 1) የሕዝቡ ዋና መሪ ወይም 2) በደሴትቱ ለላይ ዋና ሰው ተደርጎ የሚወሰደው ምናልባትም በጣም ሀብታሙ ሰው ሊሆን ይችላል፡፡ ፑፕልዮስ ተብሎ የሚጠራ ሰው ፑፕልዮስ በደሴትቱ ላይ ዋና አለቃ ነው፡፡ መልካም አቀባበል አደረግልን "ጳውሎስን እና ከእርሱ ጋር የተጓዙትን ሰዎች" የሚያስፈልገንን ነገር ሁሉ በልግስና ሰጡን "ለእኛ እንግዶች ለሆነው ቸርነታቸውን አሳዩን" የፑፕልዮስም አባት በንዳድና በተቅማጥ ታሞ ተኝቶ ነበር፤ ይህ ስለ ፑፐፕልዮስ አባት አጠቃላይ የኃላ ታሪክ መረጃ የሚሰጥ ሆኖ አጠቃላይ ታኩን ለመረዳ ወሳኝ ነው፡፡ ታሞ ነበር "ታሟል" በንዳድና በተቅማጥ ታሞ ነበር ይህ የአንጀት በሽታ ነው፡፡ እኮቹን በእርሱ ላይ ጫነ "በእጆቹ ዳሰሰው" ተፈወሰ አማራጭ ትርጉም: "እነርሱንም ፈወሳቸው" (UDB)
አጠቃላይ መረጃ: ጳውሎስ ወደ ሮም የሚያደርገውን ጉዞ ቀጥሏል፡፡ በእስክንድሪያው መርከብ አማራጭ ትርጉሞች 1) "ከእስክንድሪያ በመጣው መርከብ አማካኝነት" ወይም 2) "በእስክንድሪያ የተመዘገበው ወይም ፈቃድ ያገኘው መርከብ፡፡" በ ACT 6:9 ላይ “እስክንድሪያ” የሚለውን ቃል ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ መንቲያ ወንድማማቾች ይህ ካስቶር እና ፖሉእክስ የተባሉትን ያመለክታል፤ እነዚህ የግሪክ አምላክ የሆነው ዙስ መንቲያ ወንድ ልጆች ናቸው፡፡ እነዚህ የመርከቦችን ደንነት የሚጠብቁ ናቸው ተብሎ ስለሚታሰብ ይፈራሉ፡፡ የሰራኩስ ከተማ ሰርኩስ በአሁን ዘመን ከጣሊያን ደቡብ ምዕራብ በኩል፣ ከሲስል ከተማ ደቡብ ምስራቅ በኩል የሚትገኝ የወደብ ከተማ ናት፡፡
የሬጊዩም ከተማ ይህ ከጣሊያን ጫፍ በደቡብ ምዕራብ በኩል የሚገኝ የወደብ ከተማ ነው፡፡ የደቡብ ንፋስ ተነስቶ "ከደቡብ የሚነሳ ንፋስ መንፈስ ጀመረ" የፑቲዮሉስ ከተማ "ፑቲዮሉስ" በዘመኗ ኔፓል ከጣሊያን በምዕራብ በኩል የሚትገኝ ከተማ ናት፡፡ ወንድሞች እነዚህ የኢየሱስ ተከታዮች ሲሆን ወንዶችን እና ሴቶችን ያካትታል፡፡ በዚህ መንገድ ወደ ሮም መጣን አንድ ጊዜ ጳውሎስ ወደ ፑቲዮሉስ ከደረሰ በኋላ የተቀረው ወደ ሮም የሚደረገው ጉዞ በየብስ ላይ የሚደረግ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ : "ከእነርሱ ጋር ለሰባት ቀናት ከቆየን በኋላ ወደ ሮም ሄድን፡፡" ሦስት ማደሪያ s ይህ በመንገድ ላይ ማረፊያ ቦታ ሲሆን ከሮም ከተማ 50 ኪሜ ርቀት ላይ የሚገኝ አፋን የተባለ ስፍራ ነው፡፡
ወደ ሮም በደረስን ጊዜ ጳውሎስ ተፈቀደለት አማራጭ ትርጉም: "ወደሮም ከደረስን በኋላ መንግስት ፈቃድ ሰጠው" በአይሁዳዊያን መካከል ያሉት መሪዎች አይሁዳዊያን ማህበረሰባዊ ወይም ሃይማኖታዊ መሪዎች በሮም ተገኝተው ነበር የሞት ቅጣት የሚያስቀጣ አንዳች ጥፋት አልተገኘብኝም "የሞት ቅጣት የሚያስቀጣ አንዳች ነገር አላደረኩም"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ በሮም ላሉት የአይሁድ መሪዎች መናገሩን ቀጥሏል፡፡ አይሁዳዊያን ተናገሩ "በኢየሩሳሌም ያሉት የአይሁድ መሪዎች ተናገሩ" ከእነርሱ ፍላጎት ውጪ "ከሮማዊያን መሪዎች መሻት ውጪ" እኔም ይግባኝ ለመጠየቅ ተገደድኩኝ አማራጭ ትርጉም: "ይግባኝ ከመጠየቅ ውጪ ሌላ አማራጭ አልነበረኝም" እስራኤል እርግጠኛ በሆነችበት ጉዳይ ላይ አማራጭ ትርጉም 1) "እግዚአብሔር መስሑን ወደ እስራኤል እንደሚልክ እስራኤል እርግጠኛ ናት" ወይም 2) የሞተውን ነገር ከሞት እግዚአብሔር እንደሚያስነሳ፡፡
አማራጭ ትርጉም: የአይሁድ መሪዎች ለጳውሎስ ምላሽ ሰጡ፡፡ ስለዚህ የስህተት ትምህርት ታስባለህን "ስለነዚህ ራሳቸውን ስለመረጡት ቡድኖች ታስባለህን" በሁሉም ሥፍራዎች በእነርሱ ላይ ተቃውሞ እየተነሣ ነው የወንጌል መልዕክትን ለመቀበል ፈቃደኛ ያልሆኑት በሮም አጠቃላይ ግዛት ውስጥ የሚኖሩት አይሁዊያን ስለ መንገዱ እና ይህንን መልዕክት አስመልክቶ መጥፎ ነገር መናገራውን በሮም የሚገኙ አይሁዳዊያን ሰምተዋል፡፡ .
አጠቃላይ መረጃ: በእነዚህ ቁጥሮች ውስጥ “እርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን ነው፡፡ በተቀመጡ ጊዜ በዚህ ሥፍራ ላይ “እርሱ” የሚለው ቃ የሚያመለክተው የኤሁድ መሪዎችን ነው፡፡ አንዳንዶቹን አሳመናቸው አማራጭ ትርጉም፡ "ጳውሎስ አንዳንዶቹን አሳመናቸው"
አጠቃላይ መረጃ: በእነዚህ ቁጥሮች ውስጥ “እነርሱ” የሚለው ቃል ጳውሎስ እየተናገራቸው ያሉትን ሰዎችን ነው፡፡ በቁጥር 26 ላይ ጳውሎስ ከነብዩ ኢሳያስ መጽሐፍ ወስዶ ተናግሯል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ከነቢይ ኢሳያስ መጽሐፍ ወስዶ መናገሩን አጠናቋል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ በሮም ላሉት የአይሁድ መሪዎች ያደረገውን ንግግር አጠናቀቀ፡፡ ያደምጡት ነበር "ከእነርሱ መካከል አንዳንዶቹ ያደምጡት ነበር"
No Note
1 የእግዚአብሔርን ወንጌል በሐዋርያነት እንዲያገለግል ተለይቶ ከተጠራው ከኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ከጳውሎስ። 2 ወንጌሉም በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በነቢያቱ አስቀድሞ ተስፋ የሰጠው ነው። 3 ይህም ወንጌል በስጋ ከዳዊት ዘር ስለተወለደው ስለ ልጁ ነው። 4 እርሱም በቅድስና መንፈስ ኃይል ከሙታን በመነሳት የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑ የተነገረለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነበር። 5 በስሙ ምክንያት ከእምነት የሚገኝ መታዘዝ በሕዝቦች ሁሉ መካከል እንዲሆን በእርሱ በኩል ጸጋንና ሐዋርያነትን ተቀበልን። 6 እናንተም በእነዚህ ሕዝቦች መካከል የኢየሱስ ክርስቶስ ለመሆን ተጠራችሁ። 7 ይህ መልዕክት የተጻፈው በእግዚአብሔር ለተወደዳችሁና ቅዱስ ሕዝብ ለመሆን ለተጠራችሁ በሮም ላላችሁት ሁሉ ነው። ከእግዚአብሔር ከአባታችንና ከጌታ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን። 8 ስለ እምነታችሁ በመላው ዓለም በመነገሩ ምክንያት አስቀድሜ ስለሁላችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል አምላኬን አመሰግናለሁ። 9 ባለማቋረጥ እንደማስባችሁ የልጁን ወንጌል በመንፈሴ የማገለግለው እግዚአብሔር ምስክሬ ነው። 10 አሁን በተቻለኝ መጠን በእግዚአብሔር ፈቃድ ተሳክቶልኝ ወደ እናንተ እንድመጣ ሁልጊዜ በጸሎቴ እለምናለሁ። 11 የሚያበረታችሁን ጥቂት መንፈሳዊ ስጦታ እንዳካፍላችሁ ላያችሁ እናፍቃለሁ፥ 12 ይኸውም የእኔና የእናንተ በሆነ የእርስ በርሳችን እምነት አማካይነት እንድንበረታታ ስለምጓጓ ነው። 13 ወንድሞች ሆይ፥ ብዙ ጊዜ ወደ እናንተ ለመምጣት እንደ ሞከርኩኝና እስካሁን እንደተስተጓጎልኩኝ ሳታውቁ እንድትቀሩ አልፈልግም። ወደ እናንተ መምጣት የፈለግሁበት ምክንያት ከተቀሩት አሕዛብ እንዳገኘሁት ሁሉ ከእናንተ ደግሞ ጥቂት ፍሬ እንዳገኝ ነው። 14 ለግሪኮችና ግሪኮች ላልሆኑት፥ ለጥበበኞችና ለማያስተውሉ ዕዳ አለብኝ። 15 ስለዚህ፥ በበኩሌ በሮም ለምትገኙት ለእናንተ ደግሞ ወንጌልን ለመስበክ ተዘጋጅቻለሁ። 16 በወንጌል አላፍርም! ምክንያቱም እርሱ አስቀድሞ ለአይሁድ ደግሞም ለግሪኮች የሚያምኑትን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ኃይል ስለሆነ ነው። 17 "ጻድቅ በእምነት ይኖራል" ተብሎ እንደተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ በወንጌል ከእምነት ወደ እምነት ተገልጧልና። 18 በአመጻቸው እውነትን በሚያፍኑ አመጸኞችና ክፉዎች ሰዎች ሁሉ ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ከሰማይ ተገልጧል። 19 ይኽውም እግዚአብሔር ስላስታወቃቸው ስለ እግዚአብሔር ሊታወቅ የሚገባው ነገር ለእነርሱ ግልጥ ነው። 20 የማይታዩት ገጽታዎቹ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ ግልጥ ሆነው ይታያሉ። እነዚህም በተፈጠሩት ነገሮች አማካይነት ይታወቃሉ። ገጽታዎቹም የዘላለም ኃይሉና የመለኮት ባህርዩ ናቸው። በመሆኑም እነዚህ ሰዎች የሚያመካኙት አይኖራቸውም። 21 ምክንያቱም ስለ እግዚአብሔር ቢያውቁም እንደ እግዚአብሔርነቱ ስላላከበሩትና ስላላመሰገኑት ነው። ይልቁንም በሀሳባቸው ሞኞች ሆኑ፥ የማያስተውለው ልባቸውም ጨለመ። 22 ጥበበኞች ነን ቢሉም የማያስተውሉ ሆኑ። 23 የማይጠፋውን የእግዚአብሔር ክብር በሚጠፋ ሰው አምሳል፥በወፎች፥ አራት እግር ባላቸው አራዊትና በደረታቸው በሚሳቡ ፍጥረታት መልክ ለወጡ። 24 ስለዚህ እርስ በርሳቸው ሰውነታቸውን እንዲያዋርዱ እግዚአብሔር ለልባቸው የክፋት ምኞት ለእርኩሰት አሳልፎ ሰጣቸው። 25 እነዚህ ሰዎች የእግዚአብሔርን እውነት በውሸት የለወጡና በፈጣሪ ፈንታ ፍጥረትን ያመለኩና ያገለገሉ ናቸው፤ እርሱ ግን ለዘላለም የተመሰገነ ነው።አሜን። 26 ከዚህም የተነሳ እግዚአብሔር ለአስነዋሪ ምኞት አሳልፎ ሰጣቸው፥ ሴቶቻቸውም ለተፈጥሮአቸው የሚገባውን ተግባር ተገቢ ባልሆነው ለወጡ። 27 እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ለተፈጥሮአቸው የሚገባውን ሴቶችን መገናኘት ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወተ-ሥጋ ምኞት ተቃጠሉ። እነዚህ ወንዶች የማይገባውን ነገር ከወንድ ጋር በማድረጋቸው ስለ ነውራቸው ቅጣትን የተቀበሉ ናቸው። 28 እግዚአብሔርን ለማወቅ ስላልፈቀዱ እነዚያን ተገቢ ያልሆኑ ነገሮች እንዲያደርጉ ለማይረባ አዕምሮ አሳልፎ ሰጣቸው። 29 እነርሱ በአመጻ ሁሉ፥ በጨካኝነት፥ በክፉ ምኞትና በምቀኝነት፥ በቅናት፥ በነፍስ መግደል፥ በጸብ፥ በማታለልና በክፉ ሃሳብ የተሞሉ ናቸው። 30 ሐሜተኞች፥ የሰው ስም አጥፊዎችና እግዚአብሔርን የሚጠሉ፥ ቁጡዎች፥ ዕብሪተኞችና ትዕቢተኞች ናቸው። ክፉ ነገሮችን የሚያመነጩና ለወላጆቻችው የማይታዘዙ፥ 31 ማስተዋል የሌላቸው፤ እምነት የማይጣልባቸው፥ ፍቅር የሌላቸውና የማይምሩ ናቸው። 32 እንደዚህ ያሉትን ነገሮች የሚያደርጉ ሞት እንደሚገባቸው የሚናገረውን የእግዚአብሔር ትዕዛዝ ያውቃሉ፥እነርሱ ግን እነዚህኑ ነገሮች ራሳቸው የሚያደርጉ ብቻ ሳይሆኑ የሚያደርጉትን ሌሎችን የሚያበረታቱ ናቸው።
ቋንቋህ የዚህን መልእክት ጸሓፊ የሚያስተዋውቅበት የተለየ መንገድ ሊኖረው ይችላል፡፡ በዚሁ ተመሳሳይ ጥቅስ ጳውሎስ ደብዳቤውን የጻፈላቸው ሰዎእ እነማን እንደሆኑ መናገር ያስፈልግህ ይሆናል (ሮሜ 1፡7) ፡፡ ‹‹እኔ ጳውሎስ ይህንን መልእክት ጽፌአለሁ (የተገመተ እውቀት እና ያልተገለጠ መረጃ የሚለውን ተመልከት)
ይህንን በአድራጊ ቅርጽ ልትተረጉመው ትችላለህ። “እግዚአብሔር ሐዋርያ እንድሆን ጠራኝ እንዲሁም ለሰዎች ስለ ወንጌል እናገር ዘንድ መረጠኝ።
ይህ ማለት እግዚአብሔር ሰዎችን የእርሱ ልጆች ይሆኑ ዘንድ፣ አገልጋዮቹም ይሆኑ ዘንድ እና በኢየሱስ በኩል ያዘጋጀውን የመዳን መልእክት እንዲነግሩ ይመርጣቸዋል ወይም ይወስናቸዋል ማለት ነው፡፡
እግዚአብሔር ለሕዝቡ መንግሥቱን እንደሚያቋቀቁምቃል ገብቷል፡፡ ለነቢያቱም ይህንን ቃል ኪዳን በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ እንዲጽፉ ነግሮአቸዋል፡፡
ይህ የሚያመለክተው ‹‹የእግዚአብሔርን ወንጌል››፣ እግዚአብሔር ልጁን ወደዚህ ዓለም እንደሚልከው የገባውን ቃል ኪዳን የሚገልጽ የምሥራች ነው፡፡
የእግዚአብሔር ልጅ፣ ይህ ለኢየሱስ አስፈላጊ ማዕረግ ነው፡፡ (ልጅ እና አባት እንዴት እንደተተረጎሙ ተመልከት)
እዚህ ላይ ‹‹ሥጋ›› የሚለው ቃል የሚያመለክተው ተጨባጭ የሆነውን አካል ነው፡፡ ‹‹ ተፈጥሮአዊ በሆነው አካል የዳዊት ዘር የሆነው ማን ነው›› ወይም ‹‹ከዳዊት ቤተ ሰብ የተወለደው ማን ነው›› (የተገመተ እውቀትና ያልተገለጠ መረጃ የሚለውን ተመልከት)
ጳውሎስ እዚህ ላይ የሚናገረው ለመስበክ ስላለበት ግዴታ ነው፡፡
ጳውሎስና የመልእክቱ አባቢዎች የሚያውቁትና የሚጓዙበት ዓለም የሮም ግዛት ነበር
ጳወሎሰ ከልቡ እንደሚጸልይላቸው እና ይህንንም ሲያደርግ እግዚአብሔር እንደሚያየው ትኩረት በመስጠት ይናገራል፡፡ ‹‹ስለ›› የሚለው ቃል ብዙ ጊዜ ሳይተረጎም ይቀራል፡፡
የሰው መንፈስ የሰውአንድ ክፍል ሲሆን እግዚአብሔርን የሚያውቅና የሚያምን ነው፡፡
የመጽሐፍ ቅዱስ የምሥራቹ ቃል (ወንጌሉ) የእግዚአብሔር ልጅ ዓለምን ለማዳን ራሱን አሳልፎ የሰጠበት ነው፡፡
ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ለሆነው ለኢየሱስ አስፈላጊ ማዕረግ ነው፡፡
‹‹ስለ እናንተ ለእግዚአብሔር ተናግሬአለሁ››
‹‹በምጸልይበት ጊዜ ሁሉ፣ ወደ እናንተ መጥቼ --- በመጨረሻ ውጤታማ እንድሆን --- እግዚአብሔርን እጠይቃለሁ፡፡
‹‹እግዚአብሔር በሚፈቅደው በየትኛውም መመንገድ››
‹‹ውሎ አድሮ›› ወይም ‹‹በመጨረሻ
‹‹እግዚአብሔር ስለፈለገው››
ጳውሎስ የመክፈቻ መግለጫውን በሮም ላሉ ሰዎች በመቀጠል ሊያያቸው እንደሚመኝ ይነግራቸዋል
‹‹ምክንያቱም በእርግጥ ላያችሁ ስለምፈልግ ነው››
ጳውሎስ የሮሜ ክርስቲያኖች በመንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዲጠነክሩ ይፈልጋል፡፡ ‹‹በምንፈሳዊ ሕይወታችሁ እንድታድጉ አንዳንድ ስጦታዎች ይረዱአችኋል››
ይህንን በአድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ፡፡ ‹‹በኢየሱስ ባለን እምነታችን እርስ በእርስ ልንዳችንን እንድንከፋፈል ማለቴ ነው››
ጳውሎስ ይህ መረጃ እንዲኖራቸው አጥብቆ ይፈልጋል፡፡ ይህንን በእጥፍ አሉታዊ በሆነ መንገድ የተገለጸውን በአዎንታዊ ቅርጹ ልትተረጉመው ትችላለህ፡፡ ‹‹እንድታውቁ እፈልጋለሁ››
ይህ ማለት ክርስቲያን ወገኖች ማለት ሲሆን፣ ሁቱንም ወንዶችንና ሴቶችን ያጠቃልላል፡፡
ይህንን በአድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ፡፡ ‹‹ሁልጊዜ የሆነ ነገር ይከለክለኛል››
ይህንን በአዎንታዊ ቅርጹ መተርጎም ትችላለህ፡፡ ‹‹በወንጌል ሙሉ ለሙሉ አምናለሁ››
እዚህ ላይ ‹‹ማመን›› ማለት እምነትን በክርሰቶስ ላይ ማድረግ ማለት ነው››
‹‹ለአይሁድ ሕዝቦች እና ለግሪክ ሰዎችም››
መጀመሪያ ማለት በጊዜ ውስጥ ከሁሉ ቀድሞ የሚመጣ ማለት ነው
‹‹በእርሱ›› የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስ ሙሉ ለሙሉ የሚታመንበትን ወንጌልን ነው፡፡
ጳውሎስ ስለ ወንጌል መልእክት እንደ አንድ ተጨባጭ ነገር ነገር
ይህንን በአድራጊ ቅርጹ ልትተረጉመው ትችላለህ፡፡ ‹‹አንድ ሰው በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ እንደ ጻፈው››
እዚህ ላይ ‹‹ጻድቅ›› የሚለው የሚያመለክተው በእግዚአብሔር የሚታመኑትን ነው፡፡ ‹‹በእግዚአብሔር የሚታመኑትን ሰዎች ከእርሱ ጋር የሆኑና ለዘላለም የሚኖሩ አድርጎ ይቆጥራቸዋል››
ጳውሎስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ያለመታየት ባሕርይውን መረዳታቸውን ሰዎች እነዚያን የእግዚአብሔር ባሕሪያት እንዳዩ ይናገራል፡፡ ይህ እንደ አድራጊ ቅርጽ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ‹‹ እግዚአብሔር ስለገለጠላቸው ስለ እግዚአብሔር ሊታወቅ የሚቻለው የዘላለም ኃይሉ ደግሞም አምላክነቱ በእነርሱ ዘንድ ግልጽ ነው፡፡››
‹‹የእግዚአብሔር ጠቅላላ ባሕርይ እና ችሎታው›› ወይም ‹‹እግዚአብሔርን አምላክ የሚያደርጉት ስለ እርሱ ያሉ ነገሮች››
ይህ የሚያመለክተው ሰማይንና ምድርን በውስጣቸው ያለውን ሁሉ ነው፡፡
x
‹‹ጥበበኛች እንደሆኑ ስለራሳቸው ሲናገሩ ነገር ግን ሞኞች ሆኑ››
በሮሜ 1፡18 የተጠቀሱት ሰዎች
‹‹ እግዚአብሔር ክቡር እና ፈጽሞ የማይሞት የመሆኑን እውነት ለወጡ›› ወይም ‹‹እግዚአብሔር ክቡር እና ፈጽሞ የማይሞት መሆኑን ማመናቸውን አቆሙ››
‹‹ጣዖታት የሚመስሉ ነገሮችን ማምለክ መረጡ››
‹‹የሚሞት ሰውን ››
‹‹ወይም ወሮችን የሚመስሉ አራት እግት ያላቸውን እንስሶች፣ ወይም የሚሳቡ ነገሮች››
‹‹ስለዚህ አሁን የተናገርኩት እውነት ነው››
‹‹እግዚአብሔር ለልባቸው ፍትወት እንዲሰጡ ፈቀደላቸው››
x
‹‹በምንዝርና እና በወሲብ ኃጢአት ምክንያት››
‹‹እግዚአብሔር ለርኩሰታቸው አሳልፎ ሰጣቸው››
‹‹የሚያሳፍር የወሲብ ፍላጎት››
‹‹በሴቶቻቸው ምክንያት››
‹‹ተፈጥሮአዊ ያልሆነ›› የግንኙነት አሳብ ለመጥራት እንኳ የማይገባ ጸያፍ የሆነ የወሲብ ግንኙነት ነው፡፡ ‹‹እግዚአብሔር ባልፈጠረው መንገድ ወሲብን መለማመድ ጀመሩ››
እዚህ ላይ ‹‹ተፈጥሮአዊ ግንኙነት›› የግብረ ሥጋ ግንኙነትን በማያሳፍር ሁኔታ የሚገለጽበት አባባል ነው፡፡ ‹‹ ብዙ ወንዶች ተፈጥሮአዊ በሆነ መንገድ ሴቶችን መገናኘት አቆሙ፡፡››
‹‹ወንዶች ለወንዶች ጠንካራ የፍትወት ፍላጎት አሳዩ››
‹‹ሊያፍሩበት የሚገባውን ተግባር፣ ያለምንም እፍረት አደረጉ››
“ወንዶች ባደረጉት ስህተት ምክንያት እግዚአብሔር በፍትሐዊነት ቀጣቸው”
የግብረገብ ስህተት፣ ስለ አንድ እውነት መሳት አይደለም
“እግዚአብሔርን ማወቅ አስፈላጊ እንደሆነ እንደነበር አላሰቡም
በሮሜ 1፡18 የተጠቀሱት እነዚህ ቃሎች የሚያመለክቱት ስለ “ሰው ልጆች” ነው።
እዚህ ላይ ‹‹የማይረባ አእምሮ›› ማለት ስለ አስጸያፊ ነገሮች ብቻ የሚያስብ ማለት ነው። “እግዚአብሔር ይህ የሚያስቡት የማይጠቅምና አስጸያፊ ሃሳብ አእምሮአቸውን ሙሉ ለሙሉ እንዲቆጣጠራቸው ፈቀደ።
ይህንን በአድራጊ ቅርጽ ልትተረጉመው ትችላለህ፡፡ ‹‹ በውስጣቸው እጅግ ጠንካራ ፍላጎት አላቸው›› ወይም ‹‹ ይህንን ለማድረግ በጣም ጠንካራ ፍላጎት አላቸው፡፡››
ይህንን በአድራጊ ቅርጽ ልትተረጉመው ትችላለህ፡፡ ‹‹ብዙዎች በሌሎች ሰዎች ላይ ዓመፃን ያደርጋሉ---ሰው ሰዎችን መግደልን በተከታታይ ይመኛል--- ክርክርና ፕልን በሰዎች መካከል ያነሳሳሉ--- ሌሎችን ያታልላሉ--- በሌሎች ላይ የጥላቻ ንግግርን የደርጋሉ››
ተሳዳቢዎች የተሳሳቱ ነገሮችን በሌላ ሰው ላይ በመናገር ሰውየውን ለአደጋ ያጋልጡታል፡፡
‹‹በሌሎች ላይ ክፉ ነገሮችን ለማድረግ አዳዲስ መንገዶችን ያስባሉ››
1 ስለዚህ አንተ ሰው፥ አንተው ፈራጁ እነዚያኑ ነገሮች ስለምታደርግ በሌላው በምትፈርድበት ራስህን ትኮንናለህና የምታመካኘው የለህም። 2 ነገር ግን እነዚያን ነገሮች በሚያደርጉት ላይ ቁጣው በሚወርድባቸው ጊዜ የእግዚአብሔር ፍርድ እውነተኛ እንደሆነ እናውቃለን። 3 ነገር ግን አንተው ራስህ ያንኑ እያደረግህ እንደነዚያ ያሉትን በሚያደርጉት ላይ የምትፈርድ አንተ ሰው፥ይህንን አስተውል። ከእግዚአብሔር ፍርድ ታመልጣለህን? 4 ወይስ የቸርነቱን ባለጠግነት፥የቅጣቱን መዘግየትና ትዕግስቱን ታቃልላለህን? ቸርነቱ ወደ ንስሐ ሊመራህ እንደሆነ አታውቅምን? 5 ነገር ግን በፍርድ ቀን ያም የእግዚአብሔር የጽድቅ ፍርድ በሚገለጥበት ጊዜ በድንዳኔህና ንስሐ በማይገባው ልብህ መጠን ለራስህ ቁጣን ታከማቻለህ። 6 እርሱ ለእያንዳንዱ ሰው እንደ ሥራው መጠን ዋጋውን ይከፍለዋል፤ 7 በበጎ ተግባር በመጽናት ምስጋናን፥ክብርንና የማይጠፋውን ሕይወት ለሚፈልጉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸዋል። 8 የራሳቸውን ጥቅም በሚፈልጉት፥ለአመጻ እንጂ ለእውነት በማይታዘዙት ላይ ግን መቅሰፍትና ብርቱ ቁጣ ይመጣባቸዋል። 9 አስቀድሞ በአይሁዳዊ ቀጥሎም በግሪክ ሰው፥ክፋትን ባደረገ ነፍስ ሁሉ ላይ እግዚአብሔር መከራና ጭንቀትን ያመጣባቸዋል። 10 አስቀድሞ ለአይሁድ ቀጥሎም ለግሪክ መልካም ላደርጉ ሁሉ ግን ምስጋና፥ክብርና ሰላም ይሆንላቸዋል። 11 እግዚአብሔር ስለማያዳላ 12 ሕግ እያላቸው ኃጢአት ያደረጉ ሁሉ በሕግ ይፈረድባቸዋል፥ሕግ ሳይኖራቸው ኃጢአት ያደረጉ ሁሉ ደግሞ ያለ ሕግ ይጠፋሉ። 13 በእግዚአብሔር ፊት የሚጸድቁት ሕጉን የሚሰሙት ሳይሆኑ ሕጉን የሚያደርጉት ናቸው። 14 ሕግ የሌላቸው አሕዛብ በተፈጥሮአቸው የሕጉን ነገሮች በሚፈጽሙበት ጊዜ ሕግ ባይኖራቸውም እንኳ ለእነርሱ ለራሳቸው ሕግ ናቸው። 15 በዚህም ሕጉ የሚጠይቃቸው ድርጊቶች በልቦናቸው መጻፋቸውን ያሳያሉ። ሃሳባቸው ሲከሳቸው ወይም ሲደግፋቸው ኅሊናቸው ደግሞ ለራሳቸውና 16 ለእግዚአብሔር ይመሰክራል። ይህም እኔ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደምሰብከው ወንጌል ሰዎች ሁሉ በስውር ስላደረጉት ነገር እግዚአብሔር በሚፈርድበት ቀን በዚያን ጊዜ ይሆናል። 17 በሕጉ በመመራትህ አይሁዳዊ ነኝ ትላለህ፥ በሕጉ ትደገፋለህ፥ በእግዚአብሔር በመመካት ደስ ትሰኛለህ፥ 18 ፈቃዱን ታውቃለህ፥ ከእርሱ ውጪ የሆኑትን ነገሮች መርምረህ ትረዳ ይሆናል። 19 አንተ ራስህ የዕውሩ መሪ፥ በጨለማ ላሉት ብርሃን፥ 20 የሰነፎች አስተማሪ፥ የሕጻናትም መምህር በመሆንህ በሕግ የእውቀትና የእውነት መልክ እንዳለህ ትታመን ይሆናል። 21 እንግዲህ አንተ ሌላውን የምታስተምር ራስህን አታስተምርምን? አትስረቅ ብለህ የምትሰብክ ትሰርቃለህን? 22 አታመንዝር የምትል አንተ ታመነዝራለህን? ጣዖታትን የምትጸየፍ ቤተመቅደሶችን ትዘርፋለህን? 23 አንተ በሕጉ በመመካት የምትደሰተው ሰው ሕጉን በመተላለፍ እግዚአብሔርን ትንቃለህን? ይህ ልክ "በእናንተ 24 ምክንያት በአሕዛብ መካከል የእግዚአብሔር ስም ይናቃል" ተብሎ እንደተጻፈው ነው። 25 ሕጉን ብትፈጽም በርግጥ መገረዝ ይጠቅማል፥ የሕጉ ተላላፊ ብትሆን ግን መገረዝህ እንደ አለመገረዝ ይሆናል። 26 እንግዲህ ያልተገረዘው ሰው የሕጉን ትዕዛዛት ቢጠብቅ አለመገረዙ እንደ መገረዝ አይቆጠርለትምን? 27 በፍጥረቱ ያልተገረዘው ሰው ሕጉን ቢፈጽም አይፈርድባችሁምን? ይህም እናንተ ቅዱሳት መጻሕፍትና መገረዝ እያላችሁ ሕጉን ተላለፊ ስለሆናችሁ ነው። 28 በውጫዊ ማንነቱ ብቻ አይሁዳዊ የሆነ እርሱ አይሁዳዊ አይደለም፥ የሥጋ ውጫዊ መገረዝ ብቻም መገረዝ አይደለም። 29 ነገር ግን በውስጣዊ ማንነቱ አይሁዳዊ የሆነ እርሱ አይሁዳዊ ነው፥ መገረዝም በፊደል ሳይሆን በመንፈስ በልብ የተደረገው ነው። እንዲህ ላለ ሰው ከሰዎች ሳይሆን ከእግዚአብሔር ምስጋና ይሆንለታል።
ጳውሎስ ሰዎች ሁሉ ኃጢአተኞች እንደሆኑና ክፉዎች ስለመሆናቸው ማሳሰቡን ያረጋግጣል፡፡
‹‹ስለዚህ›› የሚለው ቃል የጽሑፉ አዲስ መስመር መጀመሪያ ነው፡፡ እንዲሁም ጳውሎስ በሮሜ 1፡1-32 ለተናገረው መደምደሚያ ይሆናል። “እግዚአብሔር ኃጢአትን በተደጋጋሚ የሚያደርጉትን የሚቀጣ ከሆነ፣ በእርግጥ ለኃጢአታችሁ ይቅርታ አያደርግም።”
ጳውሎስ እዚህ ላይ ሲጽፍ ልክ ከእርሱ ጋር ለሚከራከር አንድ አይሁዳዊ እንደሚጽፍ አድርጎ ነው፡፡ ጳውሎስ ይህን የሚያደርገው እግዚአብሔር ኃጢአትን በማድረግ የሚጸኑትን እንደሚቀጣ የሚጽፍላቸውን አይሁዶች ቢሆኑ አሕዛብ+ ለማስገንዘብ ነው፡፡
ይህ ‹‹አንተ›› የሚለው ተውላጠ ስም የተናጠል ስም ነው፡፡
ጳውሎስ ‹‹አንተ›› የሚለውን ቃል የሚጠቀመው ማንኛውም ራሱን እንደ አምላክ የሚቆጥርና በሌሎች ላይ የሚፈርደውን ለመገሰጽ ነው፡፡ ‹‹አንተ ራስህ ሰብኤ ፍጥረት ሆነህ እያለ የእግዚአብሔር ቅጣት ይገባቸዋል በማለት በሌሎች ላይ ትፈርዳለህ››
‹‹እነርሱ እንደሚያደርጉት አንተም ታደርጋለህና በራስህ ላይ ትፈርዳለህ››
እዚህ ላይ ‹‹እኛ›› የሚለው ተውላጠ ስም ክርስቲያን አማኞችንና ክርስቲያን ያልሆኑ አይሁዶችን የሚያጠቃልል ነው፡፡
እዚህ ላይ ጳውሎስ ስለ ‹‹እግዚአብሔር ፍርድ›› ሲናገር ሕያው እንደሆነ በሰዎች ላይ ‹‹ሊወድቅ›› እንደሚችል አድርጎ ነው፡፡ ‹‹እግዚአብሔር እነዚያን ሰዎች በእውነትና በተገቢው ሁኔታ ይፈርድባቸዋል››
‹‹እነዚያን ክፉ ነገሮች የሚያደርጉ ሰዎች››
‹‹ስለዚህ ይህንን አስብ›› ወይም ‹‹ስለሆነም፣ ይህንን አስብ››
‹‹እኔ ልነግርህ ያለሁትን አስብ››
ለሰው ዘሮች ሁሉ የምትጠቀምበት አጠቃላይ ቃል ነው ‹‹አንተ ማንም ብትሆን›
‹‹አንድን ሰው የእግዚአብሔር ቅጣት ይገባዋል ብለህ የምትፈርድ አንተው ያንኑ ክፉ ነገር ታደርጋለህ››
ይህ ማስገንዘቢያ በጥያቄ መልክ የቀረበው አጽንዖት ለመስጠት ነው፡፡ ይህንን ጥያቄ እንደ አንድ ጠንካራ አሉታዊ መግለጫ አድርገህ ልትተረጉመው ትችላለህ፡፡ ‹‹አንተ በእርግጥ የእግዚአብሔርን ፍርድ አታመልጥም››
ይህ ማስገንዘቢያ ትኩረት እንዲያገኝ በጥያቄ መልክ ቀርቦአል፡፡ ይህንን እንደ ጠንካራ መግለጫ አድርገህ መተርጎም ትችላለህ፡፡ ‹‹እግዚአብሔር መልካም ስለሆነ ሰዎችን ለብዙ ጊዜ ይታገሳቸዋል ስለዚህ ይህ መልካመነቱ ንስሓ እንዲገቡ ያደርጋቸዋልና ምንም አይደለም የሚል ሁኔታ ሊኖርህ አይገባም››
‹‹ባለጠግነቱንና --- ትእግስቱን እንደማያስፈልግ›› ወይም ‹‹መልካም እንዳልሆነ --- ትቆጥራለህ››
ይህ ማስገንዘቢያ ትኩረት እንዲያገኝ በጥያቄ መልክ ቀርቦአል፡፡ ይህንን እንደ ጠንካራ መግለጫ አድርገህ መተርጎም ትችላለህ፡፡ ‹‹እግዚአብሔር መልካም እንደሆነ የሚያሳይህ አንተ ንስሓ እንድትገባ እንደሆነ ማወቅ አለብሕ››
ጳውሎስ ሕዝቡ ሁሉ ኃጢአተኛ መሆኑን ሕዝቡን ማስታወሱን ቀጥሎአል፡፡
ጳውሎስ እግዚአብሔርን ለመታዘዝ የማይፈልገውን ሰው ለመግለጽ ልቡን ከጠንካራ ድንጋይ ጋር በማነጻጸር ገልጾታል፡፡ እንዲሁም የግለሰቡን አእምሮ ወይም ውስጣዊ ማንነት ለመግለጽ “ልብ” የሚለውን ዘይቤ ይጠቀማል። “ለማዳመጥና ንስሐ ለመግባት አሻፈረኝ በማለቱ ምክንያት ነው”
ይህን “ንስሐ የማይገባ ልብ” በማለት ማጣመር ይቻላል።
“ማከማቸት” የሚለው ሐረግ የሚያመለክተው ብዙውን ጊዜ ሀብቱን የሚሰበስብ እና በአስተማማኝ ቦታ የሚያኖርን ሰው ነው፡፡ ጳውሎስ በሀብት ፋንታ ግለሰቡ የእግዚአብሔርን ቅጣት እየሰበሰበ ነው ብሏል፡፡ ንስሐ ሳይገቡ በቆዩበት መጠን ቅጣታቸውም ከባድ ይሆናል፡፡ “ቅጣታችሁን የከፋ ታደርጋላችሁ”
እነዚህ ሁለቱም ሐረጎች የሚያመለክቱት ያንኑ ቀን ነው፡፡ “እግዚአብሔር ቁጣውን ለሁሉም ሲያሳይ፣ ለሰው ሁሉ በትክክል ይፈርዳል”
“ትክክለኛ ዋጋ ወይም ቅጣት ይሰጣል”
“እያንዳንዱ ሰው በሠራው ሥራ መጠን”
x
ይህ ክፍል ምንም እንኳን ሃይማኖተኛ ስላልሆነ ኃጢአተኛ ሰው የሚናገር ቢሆንም፣ ጳውሎስ አይሁድ ያልሆኑትም ሆኑ አይሁዶች በእግዚአብሔር ፊት ኃጢአተኞች መሆናቸውን በመግለጽ ጠቅለል አድርጎ ገልጾታል፡፡
“ራስ ወዳድ” ወይም “ራሳቸው ስለሚደሰቱበት ብቻ ግድ የሚላቸው”
እነዚህ ሁለት ሐረጎች በመሠረቱ አንድ ዓይነት ናቸው፡፡ ሁለተኛው የመጀመሪያውን ያጠናክራል።
“ቁጣ” እና “የመረረ ንዴት” የሚሉት ቃላት በመሠረቱ አንድ ዓይነት ናቸው፤ የእግዚአብሔርን ቁጣ አፅንኦት ይሰጣሉ፡፡ “እግዚአብሔር እጅግ መቆጣቱን ያሳያል”
እዚህ ላይ “ቁጣ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔር በኃጢአተኛ ሰዎች ላይ የሚመጣውን ከባድ ቅጣት የሚገልጽ ነው።
“መከራ” እና “ጭንቀት” የሚሉት ቃላት በመሠረቱ አንድ አይነት ትርጉም ያላቸው ሲሆን፣ እዚህ ላይ አፅንኦት የሚሰጡት የእግዚአብሔር ቅጣት ምን ያህል መጥፎ እንደሆነ ነው፡፡ “አሰቃቂ ቅጣት ይሆናል”)
እዚህ ላይ፣ ጳውሎስ “ነፍስ” የሚለውን ቃል መላውን ሰው ለማመልከት እንደ መነጋገሪያ ዘዴ ይጠቀማል፡፡ “በእያንዳንዱ ሰው ላይ”
“ሁልጊዜም መጥፎ ነገሮችን የሚሠራ”
“እግዚአብሔር አስቀድሞ በአይሁድ ሕዝብ ላይ፣ ከዚያም አይሁድ ባልሆኑት ሕዝቦች ላይ ይፈርዳል”
ተቀባይነት ያላቸው ትርጉሞች 1) “መጀመሪያ ከጊዜ አንጻር” ወይም 2) “በእርግጠኝነት”
x
ጳውሎስ ለእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም መታዘዝ፣ ሕጉ የሌላቸውም ሰዎች ብቻ ሳይሆን ሕጉ ያላቸውንም እንደሚጨምር አንባቢው እንዲያውቅ መግለጹን ቀጠለ፡፡
ቁጥር 14 እና 15 ጳውሎስ ለአንባቢው የሚሰጠውን ተጨማሪ መረጃ ያቋርጣሉ፡፡ እንደዚህ ዓይነቱን ማቋረጥ በቋንቋህ ምልክት የምታደርግበት መንገድ ካለህ፣ እዚህ ላይ መጠቀም ትችላለህ፡፡
እዚህ ላይ “ሕጉ” የሙሴን ሕግ ያመለክታል። “የሙሴን ሕግ የሚሰሙ ብቻ አይደሉም”
“እግዚአብሔር እንደ ጻድቃን የሚቆጥራቸው”
“ነገር ግን እነርሱ የሙሴን ሕግ የሚታዘዙ ናቸው”
ይህንን በአድራጊ ቅርፅ መተርጎም ትችላለህ። “እግዚአብሔር የሚቀበለው እርሱ”
“ለራሳቸው ሕግ” የሚለው ሐረግ ማለት እነዚህ ሰዎች በተፈጥሮአቸው የእግዚአብሔርን ሕጎች ይታዘዛሉ ማለት ነው፡፡ “የእግዚአብሔር ሕጎች ቀድሞውኑ በውስጣቸው ነበራቸው”
እዚህ ላይ “ሕጉ” የሙሴን ሕግ ያመለክታል። “በመሠረቱ እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጣቸው ሕጎች የላቸውም”
“በተፈጥሮ ሕጉን በመታዘዛቸው ያሳያሉ”
እዚህ ላይ “ልቦች” የግለሰቡን ሀሳቦች ወይም ውስጣዊ ማንነትን የሚገልጽ ዘይቤያዊ አነጋገር ነው። “በልባቸው የተጻፈ” የሚለው ሐረግ በአዕምሯቸው ውስጥ የሆነ ነገር የማወቅ ምሳሌ ነው፡፡ ይህንን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “ሕጉ ምን እንዲያደርጉ የሚጠበቅባቸውን እግዚአብሔር በልባቸው ላይ ጽፎታል” ወይም “እግዚአብሔር በሕጉ መሠረት እንዲያደርጉ የሚፈልገውን ያውቃሉ።
እዚህ ላይ “ይመሰክራል” የሚያመለክተው እግዚአብሔር በልባቸው ውስጥ ከጻፈው ሕግ ያገኙትን እውቀት ነው፡፡ “የእግዚአብሔርን ሕግ የማይታዘዙ ወይም እየታዘዙ መሆናቸውን ይነግራቸዋል”
ይህ በሮሜ 2፡13 ላይ የተገለጸውን የጳውሎስን ኃሳብ ያጠቃልላል። “እግዚአብሔር በሚፈርድበት ጊዜ ይህ ይሆናል”
እዚህ ላይ ጳውሎስ ንግግሩን በመቀጠል አይሁድ ያላቸው ሕግ በመሠረቱ እነርሱ ስላልታዘዙት ይፈርድባቸዋል ይላል፡፡
“አንተ እራስህን አይሁዳዊ ብለህ ከጠራህ”
“በሕጉ ላይ እረፍ” የሚለው ሐረግ ሕጉን በመታዘዛቸው ጻድቃን መሆን እንደሚችሉ ማመንን ያመለክታል፡፡ “በሙሴ ሕግ መታመን”
“እና የእግዚአብሔርን ፈቃድ እወቅ”
ይህ በአድራጊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል፡፡ “ምክንያቱም ሰዎች ትክክለኛውን ነገር ከሕጉ ስላስተማሯችሁ” ወይም “ምክንያቱም ከሕጉ ስለ ተማራችሁ”
እዚህ ላይ “ዕውሮች” እና “በጨለማ የሚመላለሱ” ሕጉን ያልተረዱ ሰዎችን ይወክላሉ፡፡ “ሕግን ስለምታስተምር፣ አንተ ራስህ ለዕውሮች እንደ መሪ፣ በጨለማ ለሚመላለሱ ሰዎች እንደ ብርሃን ነህ”
“ስሕተት የሚያደርጉትን የምታርም”
እዚህ ላይ ጳውሎስ ስለ ሕጉ ምንም የማያውቁትን ከትናንሽ ሕፃናት ጋር ያነፃፅራቸዋል፡፡ “ሕግን የማያውቁትን ታስተምራለህ”
በሕጉ ውስጥ ያለው የእውነት እውቀት የሚመጣው ከእግዚአብሔር ነው፡፡ “ምክንያቱም እግዚአብሔር በሕጉ ውስጥ የሰጠውን እውነት መረዳትህን ታረጋግጣለህ”
ጳውሎስ አድማጮቹን ለመገሰጽ ጥያቄን ይጠቀማል። ይህንን እንደ ጠንካራ መግለጫ ልትተረጉመው ትችላለህ፡፡ “ሌሎችን ታስተምራለህ ግን ራስህን አታስተምርም!” ወይም “ሌሎችን ታስተምራለህ፣ ግን የምታስተምረውን አታደርግም!”
ጳውሎስ አድማጮቹን ለመገሰጽ ጥያቄን ይጠቀማል። ይህንን እንደ ጠንካራ መግለጫ ልትተረጉመው ትችላለህ፡፡ AT: “ሰዎች እንዳይሰርቁ ትነግራለህ፣ አንተ ግን ትሰርቃለህ!”
ጳውሎስ አድማጮቹን ለመገሰጽ ጥያቄን ይጠቀማል። ይህንን እንደ ጠንካራ መግለጫ ልትተረጉመው ትችላለህ፡፡ “ሰዎችን እንዳያመነዝሩ ትነግራለህ፣ አንተ ግን ታመነዝራለህ!”
ጳውሎስ አድማጮቹን ለመገሰጽ ጥያቄን ይጠቀማል። ይህንን እንደ ጠንካራ መግለጫ ልትተረጉመው ትችላለህ፡፡ “ጣኦትን እንደምትጠላ ትናገራለህ፣ ነገር ግን ቤተ መቅደሶችን ትዘርፋለህ!”
ተቀባይነት ያላቸው ትርጉሞች 1) “ከአሕዛብ የአጥቢያ ቤተ መዝቅደሶች ቁሳቁሶችን መስረቅ እና ትርፍ ለማግኘት መሸጥ” ወይም 2) “ለእግዚአብሔር የሆነውን ገንዘብ ሁሉ ወደ ኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ አለመላክ”፡፡
ጳውሎስ አድማጮቹን ለመገሰጽ ጥያቄን ይጠቀማል። ይህንን እንደ ጠንካራ መግለጫ ልትተረጉመው ትችላለህ፡፡: - “ሕግን ባለመታዘዝህ እግዚአብሔርን የምታዋርድ እየሆንክ፣ በሕግ እመካለሁ ማለታህ ኃጢአት ነው!”
ጳውሎስ እግዚአብሔር፣ በሕጉ፣ የእግዚአብሔር ሕግ ያላቸውን አይሁዶችንም ጨምሮ እንደሚኮንናቸው ማሳየቱን ቀጥሏል፡፡
“እነዚህን ሁሉ ያልኩት መገረዝ ስለሚጠቅማቸሁ ነው”
“በሕጉ ውስጥ ያሉትን ትእዛዛት የማትታዘዝ ከሆነ”
“ልክ ፈጽመህ እንዳልተገረዝክ ማለት ነው”
ያልተገረዘ ሰው ነው
“እግዚአብሔር በሕጉ ውስጥ ያዘዘውን ይታዘዛል”
ጳውሎስ መገረዝ በእግዚአብሔር ፊት ትክክል ለመሆን አስፈላጊ አለመሆኑን አጽንኦት ለመስጠት እነዚህን ሁለት ጥያቄዎች ይጠይቃል። እነዚህን ጥያቄዎች እንደ መግለጫ በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉማቸው ትቸላለህ፡፡ “እግዚአብሔር እንደተገረዘ አድርጎ ይቆጥረዋል። በአካል ያልተገረዘ ሰው በአንተ . . . በሕጉ ይፈርድብሃል፡፡
ይህ ሰዎች ሊመለከቱት የሚችሉትን እንደ መገረዝ ያለ የአይሁድን የአምልኮ ሥርዓቶች ይመለከታል፡፡
ይህ አንድ ሰው ሲገረዝ በአካሉ ላይ የሚታየውን አካላዊ ለውጥ ያመለክታል፡፡
ይህ ጠቅላላው የሰውን አካል የሚያመለክት መግለጫ ነው፡፡
1 እንግዲህ የአይሁዳዊ ብልጫው ምንድነው? የመገረዝስ ጥቅሙ ምንድነው? 2 በሁሉም አቅጣጫ ብልጫው ታላቅ ነው። አስቀድሞ ክእግዚአብሔር ዘንድ መገለጥ በአደራ የተሰጠው ለአይሁድ ነበር። 3 አንዳንድ አይሁድ ባያምኑስ? ያለማመናቸው የእግዚአብሔርን ታማኝነት ያስቀረዋልን? 4 በምንም ዓይነት አያስቀረውም፤ ይልቁንም ሰው ሁሉ ውሸተኛ ቢሆንም እንኳ እግዚአብሔር እውነተኛ ነው። "በቃልህ ጸድቅ ሆነህ ትገኝ ዘንድ፥ ወደ ፍርድ በመጣህ ጊዜም ትረታ ዘንድ" ተብሎ ተጽፏልና። 5 የእኛ አመጻ የእግዚአብሔርን ጽድቅ የሚያሳይ ከሆነ ግን ምን ማለት እንችላለን? እግዚአብሔር ቁጣውን በሚያመጣበት ጊዜ አመጸኛ አይደለም፥ ነወይ? ። ይህንን የምለው እንደ ሰው አስተሳሰብ ነው። 6 በፍጹም አይደለም። እንዲህ ከሆነማ እግዚአብሔር እንዴት በዓለም ላይ ይፈርዳል? 7 ነገር ግን የእግዚአብሔር እውነት በእኔ ውሸት አማካይነት ለእርሱ ብዙ ምስጋና ካመጣ ለምን አሁንም እንደ ኃጢአተኛ ይፈረድብኛል? 8 "መልካም እንዲመጣ ክፉን እናድርግ" ስለማለታችን በሐሰት እንዳስወሩብንና አንዳንዶችም እንዳመኑት ታዲያ ለምን አንልም? የሚደርስባቸው ፍርድ ትክክለኛ ነው። 9 እንግዲህ ምን ይሁን? በዚህ ጉዳይ ራሳችንን ነጻ እያደረግን ነውን? በጭራሽ። አይሁድና ግሪኮች ሁሉም ከኃጢአት በታች ስለመሆናቸው አስቀድመን ወንጅለናቸዋልና። 10 እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ "አንድም እንኳን ጻድቅ የለም። 11 አንድ እንኳን የሚያስተውል የለም። እግዚአብሔርን የሚፈልግ አንድም የለም። 12 ሁሉም ተሳስተዋል። በአንድ ላይ የማይጠቅሙ ሆነዋል። መልካም የሚያደርግ የለም፥አንድም እንኳን የለም። 13 ጉሮሮአቸው የተከፈተ መቃብር ነው። ምላሳቸው አታሏል። የእባብ መርዝ በከንፈሮቻቸው ሥር አለ። 14 አፋቸው እርግማንና መራራነትን ተሞልቷል። 15 እግሮቻቸው ደምን ለማፍሰስ ፈጣኖች ናቸው። 16 በመንገዶቻቸው ላይ ጥፋትና መከራ አለ። 17 እነዚህ ሰዎች የሰላምን መንገድ አላወቁትም። 18 በዓይኖቻቸው ፊት እግዚአብሔርን መፍራት የለም።" 19 ሕጉ የሚናገረው ሁሉ ከሕግ በታች ላሉት እንደሆነ እናውቃለን። ይህም አፍ ሁሉ እንዲዘጋና መላው ዓለም ለእግዚአብሔር መልስ እንዲሰጥ ነው። 20 ይህ የሆነበት ምክንያት ሥጋን የለበሰ ሁሉ ሕግን በመፈጸም በእግዚአብሔር ዓይን ስለማይጸድቅ ነው። ኃጢአት የሚታወቀው በሕግ አማካይነት ነውና። 21 አሁን ግን የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጧል። ልዩነት ሳይደረግ 22 በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የእግዚአብሔር ጽድቅ ለሚያምኑ ሁሉ ይሆንላቸው ዘንድ በሕግና በነቢያት የተመሰከረ ነው። 23 ሁሉም ኃጢአትን ሠርተዋል፥ከእግዚአብሔር ክብርም ጎድለዋል። 24 በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በተደረገው ቤዛነት በነጻ በጸጋው ይጸድቃሉ። 25 በደሙ በማመን የኃጢአት ማስተሰሪያ ይገኝ ዘንድ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስን ሰጥቷልና። በትዕግስቱ የቀደመውን ኃጢአት ስለመተዉ ለጽድቁ ማረጋገጫ እንዲሆን ክርስቶስን መስዋዕት አድርጎ 26 አቀረበው። በዚህ በአሁኑ ዘመን የእርሱ ጽድቅ እንዲታይ ይህ ሁሉ ሆነ። እንዲህም የሆነው እርሱ ጻድቅ መሆኑንና በኢየሱስ የሚያምነውን ሁሉ የሚያጸድቅ ራሱ መሆኑን ለማረጋገጥ ነው። 27 እንግዲህ ትምክህት ወዴት አለ? እርሱ ተወግዷል። ምን ላይ ተመሥርቶ? በሥራ ላይ ነውን? አይደለም፥በእምነት ላይ እንጂ። 28 ስለዚህ ማንኛውም ሰው ያለ ሕግ ሥራ በእምነት ይጸድቃል እንላለን። 29 ወይስ እግዚአብሔር የአይሁድ አምላክ ብቻ ነውን? የአሕዛብስ አምላክ አይደለምን? አዎን፥የአሕዛብም ደግሞ ነው። 30 እግዚአብሔር አንድ ከሆነ የተገረዙትንም ሆነ ያልተገረዙትን ስለ እምነታቸው ያጸድቃቸዋል። 31 እንግዲህ ሕግን በእምነት እንሽራለንን? እንዲህስ አይሁን። ይልቁንም ሕግን እናጸናለን።
እግዚአብሔር ሕጉን ስለ ሰጣቸው አይሁዶች ተጠቃሚዎች መሆናቸውን ጳውሎስ ያውጃል፡፡
ጳውሎስ በምዕራፍ 2 ላይ የጻፈውን ከሰሙ በኋላ ሰዎች ሊኖራቸው የሚችሏቸውን ሀሳቦች ያቀርባል። ይህንን ያደረገው በቁጥር 2 ላይ ለእነርሱ መልስ ለመስጠት ነው። “አንዳንድ ሰዎች ‘ታዲያ አይሁዳዊው ምን ጥቅም አለው? እና የመገረዝ ጥቅሙስ ምንድን ነው?ይሉ ይሆናል'” ወይም “አንዳንድ ሰዎች ምናልባት ደግሞ ‘ያ እውነት ከሆነ አይሁዶች ምንም ጥቅም የላቸውም፣ እንዲሁም መገረዝም ምንም ፋይዳ የለውም ይሉ ይሆናል፡፡'”
ጳውሎስ አሁን በቁጥር 1 ላይ ለተነሡት አሳቦች ምላሽ ይሰጣል። እዚህ ላይ “ይህ” የሚያመለክተው የአይሁድ ሕዝቦች አባል መሆንን ነው፡፡ “ግን አይሁዳዊ መሆን ትልቅ ጥቅም አለው”
ተቀባይነት ያላቸው ትርጉሞች 1) “በመጀመሪያ በጊዜ ቅደም ተከተል” ወይም 2) “በጣም በእርግጠኝነት” ወይም 3) “እጅግ በጣም በአስፈላጊነት” ናቸው፡፡
እዚህ ላይ “መገለጥ” የሚለው ቃል የእግዚአብሔርን ቃሎች እና ቃል ኪዳኖችን ያሳያል፡፡ ይህንን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “እግዚአብሔር ቃል ኪዳኖቹን የያዘውን ቃሎቹን ለአይሁድ ሰጥቷል”
ጳውሎስ ሰዎች እንዲያስቡ እነዚህን ጥያቄዎች ይጠቀማል። “አንዳንድ አይሁዶች ለእግዚአብሔር ታማኝ አልነበሩም። ከዚህ በመነሣት እግዚአብሔር የገባውን ቃል ኪዳን መፈጸም አይችልም ብለን መደምደም አለብንን?”
ይህ እንደማይሆን ይህ አገላለጽ አጥብቆ ይቃወማል፡፡ እዚህ ላይ ልትጠቀምበት የምትችለው በቋንቋህ ተመሳሳይ አገላለጽ ሊኖርህ ይችላል፡፡ “ፈጽሞ ሊሆን አይችልም!” ወይም “በጭራሽ አይሆንም!”
“ይልቁንስ ማለት አለብን”
እግዚአብሔር ሁል ጊዜ እውነተኛ ነው እናም ቃል ኪዳኑን ይጠብቃል፡፡ “እግዚአብሔር ሁል ጊዜ የገባውን ቃል ኪዳን ይፈጽማል”
“እያንዳንዱ” እና “ውሸተኛ” የሚሉት ቃላት እግዚአብሔር ለቃል ኪዳኑ ሁልጊዜ እውነተኛ መሆኑን አፅንኦት ለመስጠት የተጋነኑ ቃላት ናቸው፡፡ “ምንም እንኳ እያንዳንዱ ሰው ሐሰተኛ ቢሆን”
ይህንን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “ቅዱሳት መጻሕፍት ራሳቸው እኔ ከምናገረው ጋር ይስማማሉ”
እነዚህ ሁለት ሐረጎች በጣም ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው፡፡ ይህንን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “እያንዳንዱ ሰው የምትናገረው ነገር እውነት መሆኑን መቀበል አለበት፣ እናም ማንም ሰው ቢቃወምህ ሁል ጊዜ በጉዳይህ ላይ ታሸንፋለህ”
ጳውሎስ እነዚህን ጥያቄዎች የሚጠቀመው የአንዳንድ ሰዎችን መከራከሪያ ለማቅረብ እና አንባቢዎቹ እነዚህ መከራከሪያዎች እውነት መሆናቸውንና አለመሆናቸውን እንዲያስቡ ለማድረግ ነው፡፡ “አንዳንድ ሰዎች የእኛ አመጸኝነት የእግዚአብሔርን ጽድቅ ካሳየ፣ እግዚአብሔር እኛን በመቅጣቱ ጻድቅ አይደለም” ይላሉ።
እዚህ ላይ “ቁጣ” የቅጣት አባባል ነው። “ቅጣቱን በእኛ ላይ ለማምጣት” ወይም “እኛን ለመቅጣት”
“እዚህ ላይ የምናገረው አንዳንድ ሰዎች ያሉትን ነው” ወይም “አንዳንድ ሰዎች ያሉት ይህ ነው”
“እግዚአብሔር ዓመፀኛ ነው ማለት የለብንም”
አይሁዶች እግዚአብሔር በሰዎች ሁሉ ላይ እንደሚፈርድ ስለሚያምኑ ጳውሎስ በወንጌሉ ላይ የሚነሱት ክርክሮች ትክክለኛ ያልሆኑ መሆናቸውን ለማሳየት ይህንን ጥያቄ ይጠቀማል፡፡ “ሁላችንም በእውነት እግዚአብሔር በዓለም ላይ እንደሚፈርድ እናውቃለን!”
“ዓለም” በዓለም ውስጥ የሚኖሩትን ሰዎች ለመግለጽ የምንጠቀምበት ቃል ነው። “በዓለም ውስጥ ያለ ማንኛውም ሰው”
እዚህ ላይ ጳውሎስ አንድ ሰው የክርስቲያንን ወንጌል መቃወሙን እንደቀጠለ ይገምታል፡፡ ያ ተቃዋሚ ይሟገታል፣ ምክንያቱም ኃጢአቱ የእግዚአብሔርን ጽድቅ ያሳያል፣ ስለሆነም፣ ለምሳሌ፣ ውሸትን ቢናገር እግዚአብሔር በፍርድ ቀን ኃጢአተኛ መሆኑን መግለጽ የለበትም።
እዚህ ላይ ጳውሎስ በአሳብ ደረጃ ያለውን ተሟጋች ክርክር አቃልሎ ለማሳየት የእራሱን ጥያቄ ያነሣል። “እኔ እንዲሁ ለማለት እችላለሁ . . . ና!”
“አንዳንዶች እኛ ያልነው ይህ እንደሆነ አድርገው ለሌሎች በውሸት ይናገራሉ”
ጳውሎስ ባስተማረው ትምህርት ላይ ውሸት የሚናገሩትን የጳውሎስ ጠላቶች እግዚአብሔር ቢፈርድባቸው ፍርዱ ትክክለኛ ነው፡፡
ጳውሎስ በአጠቃላይ ሲናገር፣ ሁሉም ኃጢአተኛ ነው፣ ማንም ጻድቅ የለም፣ እግዚአብሔርንም የሚፈልግ የለም ይላል፡፡
ጳውሎስ አሳቡን ለማጉላት እነዚህን ጥያቄዎች ይጠይቃል፡፡ “እኛ አይሁዳውያን አይሁዳውያን በመሆናችን ብቻ ከእግዚአብሔር ፍርድ እናመልጣለን ብለን ለማሰብ መሞከር የለብንም!”
እነዚህ ቃላት በቀላሉ “አይደለም” ከምንለው ጠንካራ ናቸው፣ ነገር ግን እንደ “በፍጹም አይደለም!” እንደሚለው ጠንካራ አይደለም።
ይህንን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “ይህ ነቢያት በቅዱሳት መጻሕፍት እንደ ጻፉት ነው”
ትክክል የሆነውን ነገር የሚያስተውል የለም። “ትክክለኛ የሆነውን ነገር የሚያስተውል ማንም የለም”
እዚህ ላይ “እግዚአብሔርን መፈለግ” የሚለው ሐረግ ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት መፍጠርን የሚያመለክት ነው፡፡ “ማንም ከእግዚአብሔር ጋር እውነተኛ ኅብረት የውለም”
ይህ ሰዎቹ እግዚአብሔርን ማሰብ እንኳን እንደማይፈልጉ ለመግለጽ ጥቅም ላይ የዋለ ፈሊጣዊ አባባል ነው፡፡ እርሱን ለማስወገድ ይፈልጋሉ። “ሁሉም ከእግዚአብሔር ርቀዋል”
ማንም መልካም የሆነውን ስለማያደርግ ለእግዚአብሔር የማይጠቅሙ ናቸው። “እያንዳንዱ ለእግዚአብሔር የማይጠቅም ሆኗል”
“የእነርሱ” የሚለው ቃል በሮሜ 3፡9 ላይ የሚያመለክተው “አይሁዶችን እና ግሪኮችን” ነው፡፡
“ጉሮሮ” የሚለው ቃል ሰዎች ለሚናገሩት አመጽ እና አስጸያፊ ነገር ሁሉ በምሳሌነት የሚገልጽ ነው፡፡ እዚህ ላይ “የተከፈተ መቃብር” የሚለው ምሳሌ ሰዎች የሚናገሩትን ክፉ ቃላት የሚያመለክት ነው፡፡
“አንደበታቸው” የሚለው ቃል ሰዎች ለሚናገሩት ሐሰተኛ ቃላት ዘይቤያዊ አነጋገር ነው፡፡ “ሰዎች ውሸት ይናገራሉ”
እዚህ ላይ “የእባቦች መርዝ” የሚለው ቃል የሚወክለው ሰዎች የሚናገሩትን እጅግ ጎጂ የሆኑ ክፉ ቃላትን ነው፡፡ “ከንፈሮች” የሚለው ቃል የሰዎችን ቃላት ያመለክታል፡፡ “የእነርሱ ክፉ ቃላት ልክ እንደ አደገኛ እባብ መርዝ ሰዎችን ይጎዳል”
እዚህ ላይ “አንደበታቸው” የሰዎችን ክፉ ቃል የሚወክል ምሳሌአዊ አነጋገር ነው፡፡ “የተሞላ” የሚለው ቃል ሰዎቹ ምን ያህል መራርነትንና እርግማንን እንደሚናገሩ በማጋነን የሚያሳይ ነው፡፡ “ብዙውን ጊዜ እርግማን እና የጭካኔ ቃላትን ይናገራሉ”
እነዚህ ቃላቶች የሚያመለክቱት በሮሜ 3፡9 ውስጥ ያሉትን አይሁዶች እና ግሪኮችን ነው፡፡
እዚህ ላይ “እግሮች” የሚለው ሰዎቹን እራሳቸውን የሚያመለክት አባባል ነው፡፡ “ደም” የሚለው ቃል ሰዎችን መግደል የሚያመለክት ምሳሌ ነው፡፡ “ሰዎችን ለመጉዳት እና ለመግደል የፈጠኑ ናቸው”
እዚህ ላይ “ጥፋት እና መከራ” የሚሉት ቃላት የሚወክሉት ሰዎቹ በሌሎች ሰዎች ላይ የሚያስከትሉትን ጉዳትና መከራ ነው፡፡ “ሌሎችን ለማጥፋት እና መከራ ሊያደርሱባቸው ይጥራሉ”
“ከሌሎች ጋር በሰላም እንዴት መኖር እንደሚቻል።” “መንገድ” ጎዳና ወይም መተላለፊያ ነው፡፡
እዚህ ላይ “ፍርሃት” የሚለው ቃል እግዚአብሔርን ማክበር እና እርሱንም ለማክበር ፈቃደኝነትን የሚወክል ነው፡፡ “ሁሉም ሰው ለእግዚአብሔር የሚገባውን ክብር ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም”
ጳውሎስ እዚህ ላይ የሚናገረው ሕጉ ሕያው እንደሆነና ልክ የራሱ ድምፅ እንዳለው አድርጎ ነው፡፡ “ሕጉ የሚናገረው ሰዎች ማድረግ የሚገባቸው” ወይም “ሙሴ በሕጉ ውስጥ የጻፋቸው ትእዛዛት ሁሉ”
“ሕጉን መታዘዝ ያለባቸው”
እዚህ ላይ “ግን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስ መግቢያውን መጨረሱንና ዋንኛውን ነጥብ መጀመሩን ነው፡፡
“አሁን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስ ወደ ምድር ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡
ይህንን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “ሕጉን ሳትታዘዝ እግዚአብሔር በእርሱ ፊት ትክክል የምትሆንበትን መንገድ አሳውቆአል”
“ሕጉና ነቢያት” የሚሉት ቃላት የሚያመለክቱት በሙሴና በነቢያቱ በአይሁድ ቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የተጻፉትን ከፊል የእግዚአብሔር ቃል ነው። ጳውሎስ እዚህ ላይ የሚገልጻቸው በፍርድ ቤት ቆመው እንደሚመሰክሩ ሰዎች አድርጎ ነው፡፡ ይህንን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “ሙሴና ነቢያት የጻፉት ይህንን ያረጋግጣሉ”
እዚህ ላይ “ጽድቅ” ማለት ከእግዚአብሔር ጋር ትክክል መሆን ማለት ነው፡፡ “በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን በእግዚአብሔር ፊት ትክክል መሆን”
ጳውሎስ የሚያመለክተው እግዚአብሔር ሁሉንም ሰዎች በተመሳሳይ መንገድ እንደሚቀበል ነው፡፡ “በአይሁድና በአሕዛብ መካከል ፈጽሞ ልዩነት የለም”
እዚህ ላይ “የእግዚአብሔር ክብር” የሚለው ምሳሌያዊ አነጋገር ሲሆን፣ የሚያመለክተው የእግዚአብሔርን አምሳያ እና ባሕርይውን ነው። “እግዚአብሔርን ከመምሰል ጎደሉ”
እዚህ ላይ “መጽደቅ” የሚያመለክተው በእግዚአብሔር ፊት ትክክለኛ መሆንን ነው፡፡ ይህንን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “እግዚአብሔር በእርሱ ፊት ትክክለኛ ይሆኑ ዘንድ እንደ ነጻ ስጦታ ሰጥቷቸዋል፣ ምክንያቱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነጻ አውጥቶአቸዋልና።”
ይህ ማለት እነርሱ የጸደቁት የራሳቸው ሊያደርጉት ወይም የተገባቸው ሳይሆኑ ነው፡፡ እግዚአብሔር በነጻ ያጸድቃቸዋል፡፡ “በእግዚአብሔር ፊት ትክክል የሆኑት ሊያገኙት የሚገባቸው ሆኖ አይደለም”
ጳውሎስ ይህንን ጥያቄ የጠየቀው ሰዎች ሕጉን በመታዘዝ የሚኩራሩበት ምንም ምክንያት እንደሌለ ለማሳየት ነው፡፡ “እንግዲያው እነዚያን ሕጎች ስለታዘዝን በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ እንዳገኘን የምንኮራበት ምንም መንገድ የለም፡፡ ትምክህት ተወግዶአል”
ጳውሎስ የሚያነሣቸው እያንዳንዱ ነጥብ በእርግጠኝነት እውነት መሆኑን አፅንኦት ለመስጠት እነዚህን መልስ የማይሰጥባቸውን ጥያቄዎች ይጠይቃል ይመልሳልም፡፡ ይህንን ጳውሎስ ሊላቸው የፈለጋቸውን ቃላት አድራጊ ቅርፅን በመጠቀም ልትተረጉማቸው ትችላለህ። “ትምክህትን የምናስወግደው በምን መሠረት ነው? በመልካም ሥራችን ምክንያት ልናስወግደው ይገባልን? ፈጽሞ፣ ይልቁንም በእምነት ልናስወግደው ይገባናል”
ጳውሎስ እነዚህን ጥያቄዎች ለአጽንኦት ለመስጠት ይጠይቃል፡፡ “እናንተ አይሁዳውያን፣ በእርግጥ እግዚአብሔር የሚቀበለው እናንተን ብቻ እንደሆነ ማሰብ የለባችሁም!”
ጳውሎስ ነጥቡን ለማጉላት ይህንን ጥያቄ ይጠይቃል፡፡ “እርሱ ደግሞ አይሁድ ያልሆኑትን፣ አሕዛብንም ይቀበላል”
እዚህ ላይ “መገረዝ” አይሁድን የሚያመለክት ምሳሌአዊ አነጋገር ሲሆን “አለመገረዝ” ደግሞ አይሁድ ያልሆኑትን የሚያመለክት ምሳሌአዊ አነጋገር ነው፡፡ “እግዚአብሔር አይሁዶችንም ሆኑ አይሁድ ያልሆኑትን በክርስቶስ ላይ ባላቸው እምነት በኩል በፊቱ ያጸድቃቸዋል”
ጳውሎስ ሕጉን በእምነት ያጸናል፡፡
ጳውሎስ ከአንባቢዎቹ አንዱ ሊኖረው የሚችለውን ጥያቄ ይጠይቃል። “አንድ ሰው እምነት ስላለን ሕጉን ችላ ማለት እንችላለን ይል ይሆናል።”
ይህ አገላለጽ ቀደም ሲል ለተነሣው የአጻጻፍ ጥያቄ እጅግ ጠንካራ ምላሽ የሚሰጥ ነው፡፡ እዚህ ላይ ልትጠቀምበት የምትችል ተመሳሳይ አገላለጽ በቋንቋህ ሊኖርህ ይችላል፡፡ “ይህ በእርግጥ እውነት አይደለም” ወይም “ፈጽሞ አይደለም”
“ሕጉን እንታዘዛለን”
ይህ ተውላጠ ስም ጳውሎስን፣ ሌሎች አማኞችን እና አንባቢዎችን ይመለከታል።
1 እንግዲህ በስጋ አባታችን የሆነው አብርሃም ምን አገኘ እንበል? 2 አብርሃም በሥራ ጸድቆ ቢሆን ኖሮ ለመመካት ምክንያት በኖረው ነበር፥ትምክህቱ ግን በእግዚአብሔር ፊት አይደለም። 3 ቅዱሱ መጽሐፍ ምን ይላል? "አብርሃም እግዚአብሔርን አመነ፥ይህም ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት" ይላል። 4 ለሚሠራ ሰው ደሞዙ እንደ ተገቢ መብቱ እንጂ እንደ ነጻ ስጦታ አይቆጠርለትም። 5 ነገር ግን ለማይሠራ ይልቁንም ኃጢአተኛውን በሚያጸድቅ ለሚያምን ለእርሱ እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቆጠርለታል። 6 ዳዊት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ሥራ ጽድቅን በሚቆጥርለት ሰው ላይ በረከትን ይናገራል። 7 እርሱም፤ "መተላለፋቸው የተተወላቸው፥ ኃጢአታቸውም የተከደነላቸው እነርሱ የተባረኩ ናቸው። 8 ጌታ ኃጢአቱን የማይቆጥርበት ያ ሰው የተባረከ ነው።" ብሏል። 9 እንግዲህ ይህ በረከት የተነገረው በተገረዙት ላይ ብቻ ነው ወይስ ደግሞ ባልተገረዙትም ላይ? "ለአብርሃም እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት" እንላለን። 10 ታዲያ እንዴት ነበር የተቆጠረለት? አብርሃም ከመገረዙ በፊት ወይስ በኋላ? ከመገረዙ በፊት እንጂ ከተገረዘ በኋላ አልነበረም። 11 አብርሃም የመገረዝን ምልክት ተቀበለ። ይህም ከመገረዙ በፊት አስቀድሞ በእምነት ላገኘው ጽድቅ ማኅተም ነበር። የዚህ ምልክት ውጤት ምንም እንኳን ባይገረዙ ለሚያምኑ ሁሉ አባት መሆኑ ነው። ይኸውም ጽድቅ ይቆጠርላቸዋል ማለት ነው። 12 በተጨማሪም ይህ ማለት አብርሃም አባት የሆነው በመገረዝ በኩል ለሚመጡት ብቻ ሳይሆን ነገር ግን የአባታችን የአብርሃምን ምሳሌነት ለሚከተሉትም ነው። ይህም ሳይገረዝ በፊት በነበረው እምነት ነው። 13 ዓለምን የሚወርሱበት ለአብርሃምና ለዘሩ የተሰጠው ይህ ተስፋ በሕግ በኩል የተሰጠ አልነበረም። ይልቅ ይህ በእምነት በኩል የተገኘ ጽድቅ ነበር። 14 በሕግ በኩል የሆኑት ወራሾች ከሆኑ እምነት ከንቱ ሆኗል፥ተስፋም ባዶ ሆኗል ማለት ነው። 15 ሕግ ቁጣን ያመጣልና ሕግ ከሌለ አለመታዘዝም የለም። 16 በዚህ ምክንያት በጸጋ ይሆን ዘንድ ይህ የሚደረገው በእምነት ነው። በመሆኑም ተስፋው ለዘሩ ሁሉ የተረጋገጠ ነው። ይህ ዘር ሕጉን የሚያውቁትን ብቻ ሳይሆን ደግሞም እንደ አብርሃም የሚያምኑትን ያካትታል። 17 "ለሕዝቦች ሁሉ አባት አድርጌሃለሁ" ተብሎ ስለተጻፈ እርሱ የሁላችንም አባት ነው። አብርሃም ለሙታን ሕይወትን በሚሰጥና የሌሉትን ነገሮች ወደ መኖር በሚጠራ በታመነበት በእግዚአብሔር ፊት ነበረ። 18 ውጫዊ ሁኔታዎች ሁሉ ተስፋ ሰጪዎች ባይሆኑም አብርሃም ስለ ወደፊቱ ሳይጠራጠር በእግዚአብሔር ታመነ። እንዲሁም "ዘርህ እንዲህ ይበዛል" ተብሎ እንደተነገረለት የብዙ ሕዝብ አባት ሆነ። 19 በእምነት ደካማ አልነበረም። አብርሃም በመቶ አመቱ ገደማ የራሱን ሰውነትና የሣራም ማህጸን ምውት መሆኑን ተገነዘበ። 20 ነገር ግን አብርሃም ከእግዚአብሔር ተስፋ የተነሣ በእምነት ዕጦት አላመነታም። ከዚህ ይልቅ በእምነት በረታ፥ ለእግዚአብሔርም ምስጋናን ሰጠ። 21 እግዚአብሔር የሰጠውን ተስፋ ሊፈጽመው ደግሞ እንደሚችል በጥብቅ ተረዳ። 22 ስለዚህ ይህም ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት። 23 ተቆጠረለት የባለው ለእርሱ ጥቅም ብቻ የተጻፈ አይደለም። 24 ጌታችን ኢየሱስን ከሙታን ባስነሣው ለምናምን ለእኛም ደግሞ ይቆጠርልን ዘንድ ተጽፏል። 25 እርሱም ስለ መተላለፋችን ተላልፎ የተሰጠውና እኛን ለማጽደቅ ከሙታን የተነሣው ነው።
ጳውሎስ በቀድሞ ዘመን አማኞች በእግዚአብሔር ፊት የሚጸድቁት በእምነት እንጂ በሕግ እንዳልነበረ ያረጋግጣል፡፡
ጳውሎስ ጥያቄውን የሚጠቀመው የአንባቢውን ትኩረት ለመሳብ እና ስለ አዲስ ነገር ለመናገር ለመጀመር ነው። “በሥጋ አባታችን የሆነው አብርሃም ያገኘው ይህ ነው”
ጳውሎስ አጽንኦት ለመጨመር ይህንን ጥያቄ ይጠቀማል። ስለ እግዚአብሔር ቃሎች ሲናገር ልክ ሕያው እንደሆንኑ መናገር እንደሚችሉ አድርጎ ነው። “በእግዚአብሔር ቃል ልናነብ እንችላለን”
ይህንን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “እግዚአብሔር አብርሃምን እንደ ጻድቅ አድርጎ ቆጥሮታል”
ይህ በአድራጊ ቅርፅ ሊተረጎም ይችላል። “ማንም ሠራተኛ አሠሪው የሚሰጠውን ደሞዝ እንደ ስጦታ አድርጎ አይቆጥረውም”
ይህ በአድራጊ ቅርፅ ሊረተጎም ይችላል። አት: - “ነገር ግን አሠሪው ለሠራተኛው የሚከፍለው ዕዳ ነው”
“በእግዚአብሔር በሚያጸድቀው”
ይህ በአድራጊ ቅርፅ ሊተረጎም ይችላል። “እግዚአብሔር የግለሰቡን እምነት እንደ ጽድቅ ይቆጥርለታል” ወይም “እግዚአብሔር በእምነቱ ምክንያት ግለሰቡን ጻድቅ አድርጎ ይቆጥረዋል”
“ዳዊት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ሥራ ጽድቁን የሚቆጥርለትን ሰው እግዚአብሔር እንዴት እንደባረከው ጽፎአል”
ተመሳሳይ ፅንሰ-ሀሳብ በሦስት የተለያዩ መንገዶች ተገልጿል፡፡ ይህ በአድራጊ ቅርፅ ሊተረጎም ይችላል። “ጌታ ሕጉን የጣሱትን ይቅር ብሎአል . . . ኃጢአታቸውን ጌታ ከድኖላቸዋል . . . ጌታም ኃጢአታቸውን አልቆጠረባቸውም ”
ይህ አስተያየት በጥያቄ መልኩ መቅረቡ አፅንኦትን ለመጨመር ነው፡፡ “እግዚአብሔር የሚባረከው የተገረዙትን ብቻ ነው? ወይስ ያልተገረዙትን?”
እዚህ ላይ “የእምነት ጽድቅ” ማለት እግዚአብሔር እንደ ጻድቅ አድርጎ ይመለከተው ነበር፡፡ “ከመገረዙ በፊት በእግዚአብሔር በማመኑ ምክንያት እግዚአብሔር እንደ ጻድቅ አድርጎ የሚቆጥርበት ምልክት ነው”
ምንም እንኳ ባይገረዙም
ይህ በአድራጊ ቅርፅ ሊተረጎም ይችላል። “ይህ ማለት እግዚአብሔር እንደ ጻድቃን ይቆጥራቸዋል ማለት ነው”
እዚህ ላይ “መገረዝ” የሚያመለክተው በአይሁድም ሆነ በአሕዛብ በእግዚአብሔር እውነተኛ አማኞች የሆኑትን ነው፡፡
እዚህ ላይ “የእምነት እርምጃ ተከተሉ” ማለት የአንድን ሰው ምሳሌነት መከተል ማለት ነው። “የአባታችንን የአብርሃምን የእምነት ምሳሌ የሚከተሉ” ወይም “አባታችን አብርሃም እንዳደረገው እምነት ያላቸው”
እግዚአብሔር ቃል የገባላቸው ሕዝቦች ልክ ከቤተሰብ አባል ንብረትንና ሀብትን እንደሚወርሱ ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡
“ቃል ኪዳኑ መጣ” የሚሉትን ቃላት በመጀመሪያው ሐረግ እንረዳዋለን፡፡ በተዘዋዋሪ መንገድ የተጠቀሱትን ቃላት በመጨመር ይህንን ልትተረጉመው ትችላለህ፡፡ “ነገር ግን ቃል ኪዳኑ የመጣው እግዚአብሔር እንደ ጽድቅ አድርጎ በሚቆጥረው እምነት በኩል ነው”
እዚህ ላይ “በሕጉ የሚኖሩ” የሚያመለክተው ሕግን መታዘዝ ነው፡፡ “ሕጉን የሚታዘዙ እነርሱ ምድርን የሚወርሱት ከሆኑ”
“እምነት ዋጋ የለውም፣ ተስፋውም ትርጉም የለሽ ነው”
“መተላለፍ” የሚለውን ረቂቅ ስም ለማስወገድ እንደገና ሊጠቀስ ይችላል። “ማንም ሕጉን ሊጥስ የሚችል የለም” ወይም “ሕጉን አለመታዘዝ ፈጽሞ አይቻልም”
“ስለዚህ”
“ይህ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔር ቃል የገባውን መቀበል ነው፡፡ “ቃል ኪዳኑን የምንቀበለው በእምነት ነው” ወይም “ቃል ኪዳኑን በእምነት እንቀበላለን”
“ቃል ኪዳኑ በጸጋ ላይ ያርፋል” የሚለው የሚወክለው እግዚአብሔር ቃል የገባውን የሚሰጠው በጸጋ መሆኑን ነው። “ስለዚህ የገባው ቃል ኪዳን ነጻ ስጦታ ሊሆን ይችላል፣ ወይም “ስለዚህ ቃል ኪዳኑ በጸጋው ይሆናል ማለት ነው”
ይህ በአድራጊ ቅርፅ ሊገለጽ ይችላል። “ሁሉም የአብርሃም ዘሮች እግዚአብሔር እንደሚሰጥ ቃል የገባውን በእርግጥ ሊቀበሉ ይችላሉ”
ይህ የሙሴን ሕግ የመታዘዝ ግዴታ ያለባቸውን የአይሁድን ሕዝብ ይመለከታል፡፡
ይህም አብርሃም ከመገረዙ በፊት እንዳደረገው ሁሉ እምነት ያላቸውን ያመለክታል። “አብርሃም እንዳደረገው ያመኑ”
እዚህ ላይ “የእኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስንና አይሁድን በሙሉ እንዲሁም በክርስቶስ ያመኑ አይሁድ ያልሆኑትን ሁሉ ነው፡፡ አብርሃም የአይሁድ ሕዝብ በሥጋ አባታቸው ነው፣ ነገር ግን እርሱ ለሚያምኑ ሁሉ መንፈሳዊ አባት ነው፡፡
በተጻፈበት ቦታ ግልጽ ሊሆን ይችላል፡፡ እንዲሁም ይህን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “አንድ ሰው በቅዱሳት መጻሕፍት እንደ ጻፈው”
እዚህ ላይ “አንተን” የሚለው ቃል ነጠላ ሲሆን የሚያመለክተው አብርሃምን ነው፡፡
ይህ ዘይቤያዊ አነጋገር አብርሃም እግዚአብሔርን ያመነው ወንድ ልጅ እንደሚኖረው ተስፋ በማያደርግበት ጊዜ ነው፡፡ “ምንም እንኳን ለእርሱ ልጆች እንደሚኖሩት የማይቻል ቢመስልም እግዚአብሔርን አመነ”
ይህ በአድራጊ ቅርፅ ሊተረጎም ይችላል። “እግዚአብሔር ለአብርሃም እንደ ተናገረው”
እግዚአብሔር ለአብርሃም የሰጠው ሙሉ ተስፋ ግልፅ ሊሆን ይችላል፡፡ “ልትቆጥራቸው ከምትችላቸው በላይ ብዙ ዘሮች ይኖሩሃል”
ይህንን በአዎንታዊ መልኩ ልትተረጉመው ትችላለህ። “ምንም ቢሆን በእምነቱ ጠንካራ ነበር”
ይህንን ድርብ አሉታዊ በአዎንታዊ ቅርፅ መተርጎም ይቻላል። “በእምነት ማድረጉን ቀጠለ”)
ይህንን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “በእምነቱ ጠንካራ ሆነ”
“አብርሃም ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ ነበር”
“እግዚአብሔር ማድረግ ችሎ ነበር”
ይህን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “ስለዚህ እግዚአብሔር የአብርሃምን እምነት እንደ ጽድቅ ቆጠረለት” ወይም “ስለዚህ እግዚአብሔር የአብርሃምን ጽድቅ ቆጠረለት” ምክንያቱም አብርሃም በእርሱ አምኗልና፡፡
“አሁን” የሚለው ጥቅም ላይ የዋለው አብርሃም በእምነት በእግዚአብሔር ፊት መጽደቁን አሁን አማኞች በኢየሱስ ክርስቶስ ሞት እና ትንሣኤ በማመናቸው ከሚያገኙት ጽድቅ ጋር በማገናኘት ነው፡፡
“ለአብርሃም ብቻ”
ይህን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “እግዚአብሔር ጽድቅን ለእርሱ ቆጠረለት” ወይም “እግዚአብሔር እንደ ጻድቅ አድርጎ ቆጠረው”
“እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስንና በክርስቶስ የሚያምኑትን ሁሉ ነው፡፡
ይህን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “ለእኛም ጥቅም ነበር፣ ምክንያቱም የምናምን ከሆነ እግዚአብሔር እንደ ጻድቃን አድርጎ ይቆጥረናል”
“ከሙታን ያስነሣውን” እዚህ ላይ “እንደገና እንዲኖር ያደረገውን” የሚል ፈሊጣዊ አነጋገር ነው። “ጌታችን ኢየሱስን እንደገና ሕያው እንዲሆን ያደረገውን”
ይህን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “ስለ እኛ መተላለፍ እግዚአብሔር ለጠላቶች አሳልፎ የሰጠውን ደግሞም እግዚአብሔር ወደ ሕይወት ያመጣው ከእርሱ ጋር ጻድቃን እንሆን ዘንድ ነው።
1 በእምነት ስለ ጸደቅን በጌታችን በኢየሱስ በኩል ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም አለን። 2 እኛም ደግሞ በእርሱ በኩል አሁን ወደቆምንበት ወደዚህ ጸጋ በእምነት መቅረብ አለን። በእግዚአብሔር ክብር ውስጥ ተካፋዮች እንሆን ዘንድ እግዚአብሔር ስለወደፊቱ በሰጠን ተስፋ በመተማመን ደስ ይለናል። 3 ይህም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን በመከራዎቻችን ደግሞ ደስ ይለናል። መከራ መጽናትን እንደሚያደርግ እናውቃለን። 4 መጽናት ተቀባይነትን፥ ተቀባይነትም ስለ ወደፊቱ መተማመኛን ያስገኛል። 5 በተሰጠን በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት የእግዚአብሔር ፍቅር ወደ ልባችን ውስጥ ስለፈሰሰ ይህ ተስፋ ሐዘን የለበትም። 6 ክርስቶስ በትክክለኛው ጊዜ ለኃጢአተኞች የሞተው እኛ ገና ደካሞች እያለን ነበር። 7 ስለ ጻድቅ ሰው የሚሞት ከስንት አንዱ ነው። ይህም ማለት ስለ ደግ ሰው ለመሞት የሚደፍር ምናልባት ይገኝ ይሆናል። 8 ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች እያለን ክርስቶስ ስለ እኛ መሞቱ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያረጋግጣል። 9 እንግዲህ አሁን በደሙ ስለ ጸደቅን ይበልጡኑ በእርሱ ከእግዚአብሔር ቁጣ እንድናለን። 10 ጠላቶች እያለን በልጁ ሞት ከእግዚአብሔር ጋር ከታረቅን ይልቁንም ከታረቅን በኋላ በሕይወቱ እንድናለን። 11 ይህም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን አሁን ይህንን ዕርቅ ባገኘንበት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል እኛ ደግሞ በእግዚአብሔር ደስ ይለናል። 12 ስለዚህ በአንድ ሰው አማካይነት ኃጢአት ወደ ዓለም ገባ፥እንደዚሁም ሞት በኃጢአት አማካይነት ገባ። ሁሉ ኃጢአትን ስላደረጉ ሞት ወደ ሰው ሁሉ ደረሰ። 13 ሕግ እስኪመጣ ድረስ ኃጢአት በዓለም ነበረ፥ነገር ግን ሕግ በሌለበት ኃጢአት አይቆጠርም። 14 ይሁንና ሊመጣ ላለው ምሳሌ የሆነው የአዳምን አይነት ያለመታዘዝ ኃጢአት ባላደረጉት ላይ እንኳን ሳይቀር ከአዳም እስከ ሙሴ ድረስ ሞት ነገሠ። 15 ነጻ ስጦታው ግን እንደ መተላለፉ አይደለም። በአንዱ መተላለፍ ብዙዎች ከሞቱ የእግዚአብሔር ጸጋና በአንዱ ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ በኩል የሆነው ስጦታ ከዚያ ይልቅ ለብዙዎች በዛ። 16 ስጦታው እንደተሰራው ኃጢአት ውጤት አይደለም። በአንድ ወገን በአንዱ ሰው መተላለፍ ምክንያት የኩነኔ ፍርድ መጣ። በሌላ ወገን ግን ጽድቅን የሚያስገኘው ነጻ ስጦታው ከብዙ መተላለፍ በኋላ መጣ። 17 በአንዱ ሰው መተላለፍ ሞት በእርሱ በኩል ከነገሠ የጸጋን ብዛትና በአንዱ በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት በኩል የጽድቅን ስጦታ የተቀበሉት አብልጠው ይነግሳሉ። 18 እንግዲህ በአንዱ መተላለፍ በኩል ሰዎች ሁሉ ወደ ኩነኔ እንደመጡ እንዲሁ በአንዱ የጽድቅ ሥራ ለሰዎች ሁሉ የሕይወት መጽደቅ መጣ። 19 በአንድ ሰው አለመታዘዝ በኩል ብዙዎች ኃጢአተኞች እንደሆኑ እንዲሁ በአንዱ መታዘዝ ብዙዎች ጻድቃን ይሆናሉ። 20 ነገር ግን ሕግ ከጎን በመግባቱ መተላለፍ በዛ። ይሁን እንጂ ኃጢአት በበዛበት በዚያ ጸጋ ይበልጡኑ በዛ። 21 ኃጢአት በሞት እንደ ነገሠ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ለዘላለም ሕይወት ጸጋው በጽድቅ አብልጦ እንዲነግሥ ይህ ሆነ።
ጳውሎስ እግዚአብሔር አማኞችን ከእርሱ ጋር ሲያደርጋቸው የሚከሰቱ ብዙ የተለያዩ ነገሮችን መናገር ጀምሮአል፡፡
“ይህ” የሚለው ቃል በሮሜ 5፡1-2 የተገለጹትን ዐሳቦች ያመለክታል፡፡
“እኛ” “የእኛ” እና “እኛ” የሚሉት ቃላት በሚጠቀሱበት ቦታ ሁሉ የሚያመለክቱት ሁሉንም አማኞች ሲሆን ሁሉንም ያቀፈ መሆን አለበት።
እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ ለሚያምኑት የገባውን ቃል ኪዳን እንደሚፈጽም እርግጠኛ ነው፡፡
ጳውሎስ ስለ “መተማመን” ሲናገር ሕይወት እንዳለው አካል አድርጎ በመጠቀም ነው። “የምንጠብቃቸውን ነገሮች እንደምንቀበል በጣም እርግጠኞች ነን”
እዚህ ላይ “ልቦች” የአንድን ሰው ዐሳብ፣ ስሜት ወይም ውስጣዊ ማንነትን ያመለክታሉ፡፡ “የእግዚአብሔር ፍቅር በልቦቻችን ስለ ፈሰሰ” የሚለው ሐረግ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ፍቅሩን እንደሚያሳይ የሚገልጽ ምሳሌያዊ አነጋገር ነው፡፡ ይህ በአድራጊ ቅርፅ ሊገለጽ ይችላል፡፡ “እርሱ በጣም ስለ ወድዶናል” ወይም “እግዚአብሔር ምን ያህል እንደሚወደን ስላሳየን ነው”
“እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አማኞችን በሙሉ ሲሆን ሁሉንም የሚያቅፍ መሆን አለበት፡፡
“ለጻድቅ ሰውም እንኳ ለመሞት ፈቃደኛ የሆነን ሰው ማግኘት ከባድ ነው”
“ነገር ግን ለመልካም ሰው ለመሞት ፈቃደኛ የሚሆን ምንአልባት ይገኝ ይሆናል”
ይህንን ግስ አላፊ ጊዜን በመጠቀም “ገለጸ” ወይም “አሳየ” በማለት ልትተረጉመው ትችላለህ፡፡
x
“እኛ” የሚለው ቃል በተጠቀሰበት ቦታ ሁሉ የሚያመለክተው አማኞችን በሙሉ ሲሆን ሁሉን ያቀፈ መሆን አለበት፡፡
“የእግዚአብሔር ልጅ . . . የእግዚአብሔር ልጅ ሕይወት”
የእግዚአብሔር ልጅ ሞት በኢየሱስ ክርስቶስ ለምናምን ሁሉ የዘላለም ይቅርታን ሰጥቶናል፣ የእግዚአብሔርም ወዳጆች አድርጎናል፤ ይህን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ፡፡ “እግዚአብሔር ልጁ ለእኛ ሞቶአልና ከእርሱ ጋር ሰላማዊ ኅብረት እንዲኖረን ፈቀዶልናል”
ይህ የእግዚአብሔር ልጅ የሚለው ርእስ ለኢየሱስ ክርስቶስ በጣም አስፈላጊ ርእስ ነው፡፡
ይህንን በአድራጊ ቅርጽ ልትተረጉመው ትችላለህ። “አሁን እግዚአብሔር እንደገና ወዳጆቹ አድርጎናል”
ጳውሎስ እግዚአብሔር ሕጉን ለሙሴ ከመስጠቱ በፊት ሞት ለምን እንደ ተከሰተ ያብራራል፡፡
ጳውሎስ ኃጢአት “በአንድ ሰው” በአዳም በኩል ወደ ዓለም መግባቱን እጅግ አደገኛ ድርጊት እንደ ሆነ ይገልጻል፡፡ ይህ ኃጢአት ለሌላው አደገኛ ነገር ማለትም ለሞት በር ከፈተ፤ ይህም ሞት ወደ ዓለም መጣ፡፡
ይህ ማለት እግዚአብሔር ሕጉን ከመስጠቱ በፊት ሕዝቡ ኃጢአትን አድርጓል ማለት ነው፡፡ “እግዚአብሔር ሕጉን ለሙሴ ከመስጠቱ በፊት በዓለም የነበሩ ሰዎች ኃጢአትን አድርገዋል”
ይህ ማለት እግዚአብሔር ሕጉን ከመስጠቱ በፊት ሕዝቡን በኃጢአት አልከሰሳቸውም ማለት ነው፡፡ “ነገር ግን እግዚአብሔር ሕጉን ከመስጠቱ በፊት በሕጉ ላይ የተደረገን ኃጢአት አልቆጠረም”
“ምንም እንኳን የተናገርኩት እውነት ቢሆንም ሞት፣” ወይም “ከአዳም ዘመን ጀምሮ እስከ ሙሴ ጊዜ ድረስ፣ የተጻፈ ሕግ አልነበረም ነገር ግን ሞት፡፡” (ሮሜ 5፡13 ተመልከት)
ጳውሎስ ስለ ሞት ሲናገር ልክ እንደሚገዛ ንጉሥ አድርጎ ነው፡፡ “ሰዎች ከአዳም ዘመን ጀምሮ እስከ ሙሴ ድረስ በኃጢአታቸው ምክንያት መሞታቸውን ቀጥለዋል”
“ከአዳም ኃጢአት የተለየ ኃጢአት የነበራቸውም መሞታቸውን ቀጥለዋል”
አዳም ቆይቶ ለተገለጠው የክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡ ከእርሱ ጋር ብዙ የሚያመሳስላቸው ነገሮች ነበሩ፡፡
እዚህ ላይ “አንዱ” የሚለው የሚያመለክተው አዳምን ነው። “በአንዱ ሰው ኃጢአት ምክንያት ብዙዎች ሞቱ”
እዚህ ላይ “ጸጋ” የሚያመለክተው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ለሁሉም ሰው ያገኘውን የእግዚአብሔር ነጻ ስጦታ ነው፡፡ “ምንም እንኳ የሚገባን ባይሆንም ለሁላችንም በሞተው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል እግዚአብሔር በቸርነቱ የዘላለምን ሕይወት ሰጠን”
እዚህ ላይ “ስጦታው” የሚያመለክተው እግዚአብሔር የተመዘገበብንን ኃጢአት መዘረዙን ነው፡፡ “ስጦታው የአዳም ኃጢአት ውጤት አይደለም”
እዚህ ላይ ጳውሎስ “ስጦታው የአዳም ኃጢአት ውጤት አለመሆኑን” የሚያሳዩ ሁለት ምክንያቶችን ይሰጣል፡፡ “የበደለኝነት ፍርድ” የሚያመለክተው ሁላችንም ለኃጢአታችን የእግዚአብሔር ቅጣት የሚገባን መሆኑን ነው፡፡ “በአንድ በኩል እግዚአብሔር ሰዎች ሁሉ በአንድ ሰው ኃጢአት የተነሣ ሊቀጡ የሚገባቸው መሆኑን ያውጃል፣ በሌላ ወገን ግን”
ይህ የሚያመለክተው ምንም እንኳ የማይገባን ቢሆንም እግዚአብሔር በፊቱ ጻድቃን አደረገን፡፡ “የእግዚአብሔር ቸር ስጦታ እኛን በእርሱ ፊት ጻድቃን አድርጎናል”
“ከብዙዎች ኃጢአት በኋላ”
ይህ የአዳምን ኃጢአት ያመለክታል፡፡
እዚህ ላይ ጳውሎስ ስለ “ሞት” ሲናገር እንደሚገዛ ንጉሥ አድርጎ ነው፡፡ የሞት “ግዛት” እያንዳንዱ ሰው እንዲሞት ያደርጋል። “ሁሉም ሰው ሞተ”)
“አዳም በሠራው ኃጢአት የተነሣ” ወይም “በአዳም ኃጢአት ምክንያት”
እዚህ ላይ “ኩነኔ” የሚያመለክተው የእግዚአብሔርን ቅጣትን ነው፡፡ “ሰዎች ሁሉ በኃጢአት ምክንያት የእግዚአብሔር ቅጣት ይገባቸዋል”
የኢየሱስ ክርስቶስ መሥዋዕትነት
እዚህ ላይ “መጽደቅ” የሚያመለክተው እግዚአብሔር ሰዎችን በፊቱ ጻድቃን እንዲሆኑ ማድረግ መቻሉ ነው፡፡ “ሰዎች ሁሉ እንዲጸድቁ የእግዚአብሔር ስጦታ”
የአዳም አለመታዘዝ
ይህንን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “ብዙ ሰዎች ኃጢአትን አደረጉ”
የኢየሱስ መታዘዝ
ይህንን በአድራጊ ቅርፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። “እግዚአብሔር ብዙ ሰዎችን በፊቱ ያጸድቃቸዋል”
እዚህ ላይ ጳውሎስ ስለ ሕጉ ሲናገር ልክ እንደ ሰው አድርጎ ነው፡፡ “እግዚአብሔር ሕጉን ለሙሴ ሰጠው”
“ኃጢአት ጨመረ”
እዚህ ላይ “ጸጋ” የሚያመለክተው ለሰዎች የማይገባውን የእግዚአብሔርን በረከት ነው፡፡ “ምንም እንኳ የማይገባቸው ቢሆንም እግዚአብሔር በታላቅ ቸርነቱ ለእነርሱ የበለጠ ደግነትን አደረገ”
እዚህ ላይ ጳውሎስ ስለ “ኃጢአት” ሲናገር እንደሚገዛ ንጉሥ አድርጎ ነው፡፡ “ኃጢአት ሞትን እንደሚያስከትል”
ጳውሎስ እዚህ ላይ ስለ “ጸጋ” ሲናገር እንደሚገዛ ንጉሥ አድርጎ ነው፡፡ “ጸጋ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ አማካይነት የዘላለም ሕይወት ለሰው ልጆች ሰጣቸው”
ጳውሎስ እዚህ ላይ ስለ “ጸጋ” ሲናገር እንደሚገዛ ንጉሥ አድርጎ ነው፡፡ “ጽድቅ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔር ሰዎችን በፊቱ ማጽደቅ መቻሉን ነው፡፡ “ስለሆነም እግዚአብሔር የእርሱን ነጻ ስጦታ ሰጥቶ ሰዎችን በፊት ያጸድቃቸዋል”
ጳውሎስ እራሱን፣ አንባቢዎቹን እና ሁሉንም አማኞችን ያካትታል።
1-3 እንግዲህ ምን እንላለን? ጸጋ እንዲበዛ በኃጢአት ውስጥ መኖራችንን እንቀጥልን? እንዲህ አይሁን። ለኃጢአት የሞትን እኛ እንዴት በእርሱ ውስጥ መኖር እንቀጥላለን? ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የተጠመቁ ሁሉ ወደ ከሞቱ ጋር ለመተባበር እንደተጠመቁ አታውቁምን? 4 እንግዲህ ከሞቱ ጋር ለመተባበር በጥምቀት አማካይነት ከእርሱ ጋር ተቀብረናል። ይህም የሆነው ልክ ክርስቶስ በአብ ኃይል ከሙታን እንደ ተነሣ እኛ ደግሞ በታደሰ ሕይወት እንድንመላለስ ነው። 5 ሞቱን በሚመስለው ከእርሱ ጋር ከተባበርን ከትንሣኤው ጋር ደግሞ እንተባበራለን። 6 የኃጢአት ሰውነት ይጠፋ ዘንድ አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር እንደ ተሰቀለ ይህንን እናውቃለን። ይህም የሆነው ከዚህ በኋላ ለኃጢአት እንዳንገዛ ነው። 7 ከኃጢአት አኳያ ሲታይ የሞተ ሰው መጽደቁ ታውጆለታል። 8 ነገር ግን ከክርስቶስ ጋር ከሞትን ከእርሱ ጋር አብረን እንደምንኖር ደግሞ እናምናለን። 9 ክርስቶስ ከሙታን እንደ ተነሣና ሞቶ እንዳልቀረ እናውቃለን። ከዚህ በኋላ ሞት አይገዛውም። 10 ስለኃጢአት የሞተው ሞት ለዘላለም የሚሠራ የአንድ ጊዜ ሞት ነው። ይሁንና የሚኖረውን ሕይወት ለእግዚአብሔር ይኖራል። 11 ልክ እንደዚሁ እናንተ ደግሞ ለኃጢአት እንደሞታችሁ ነገር ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር እንደምትኖሩ መቁጠር ይገባችኋል። 12 ስለዚህ ለክፉ ምኞቱ እንድትታዘዙ በሚፈልግ የሚሞት ሥጋችሁ ላይ ኃጢአት እንዲነግሥ አትፍቀዱለት። 13 ከሙታን ሕያው እንደመሆናችሁ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር አቅርቡ እንጂ የሰውነት ክፍሎቻችሁን የአመጻ መሣሪያ አድርጋችሁ ለኃጢአት አታቅርቡ። የሰውነት ክፍሎቻችሁን ለእግዚአብሔር የጽድቅ መሣሪያ አድርጋችሁ አቅርቡ። 14 ኃጢአት እንዲገዛችሁ አትፍቀዱለት። ከጸጋ በታች እንጂ ከሕግ በታች አይደላችሁምና። 15 እንግዲህ ምን ይሁን? ከጸጋ በታች እንጂ ከሕግ በታች ባለመሆናችን ኃጢአት መሥራት አለብን? ከቶ እንዲህ አይሁን። 16 ትታዘዙት ዘንድ ራሳችሁን እንደ አገልጋይ ለምታቀርቡለት ለእርሱ አገልጋዮች እንደሆናችሁ አታውቁምን? ወደ ሞት የሚመራችሁ የኃጢአት አገልጋዮች ወይም ወደ ጽድቅ የሚመራችሁ የመታዘዝ አገልጋዮች ናችሁ። 17 ቀድሞ የኃጢአት አገልጋዮች ነበራችሁ፥ ነገር ግን ለተሰጣችሁ ትምህርት ከልባችሁ ስለ ታዘዛችሁ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን! 18 ከኃጢአት ነጻ ተደርጋችኋል፥የጽድቅም አገልጋዮች ሆናችኋል። 19 በሥጋችሁ ድካም ምክንያት እንደ ሰው ልማድ እናገራለሁ። ልክ የሰውነታችሁን ክፍሎች ለእርኩሰትና ለክፋት እንደ ባሪያ አድርጋችሁ እንዳቀረባችሁ እንደዚያው አሁን የሰውነት ክፍሎቻችሁ ሊቀደሱ የጽድቅ ባሪያዎች አድርጋችሁ አቅርቡ። 20 የኃጢአት ባሪያዎች በነበራችሁበት ጊዜ ከጽድቅ ውጪ ነበራችሁ። 21 አሁን በምታፍሩባቸው በእነዚያ ነገሮች ያን ጊዜ ምን ተጠቀማችሁባቸው? ምክንያቱም የእነዚያ ነገሮች ውጤት ሞት ነው። 22 አሁን ግን ከኃጢአት ነጻ ስለተደረጋችሁና ለእግዚአብሔር ባሪያዎች ስለሆናችሁ ለመቀደስ ፍሬ ታፈራላችሁ። ውጤቱም የዘላለም ሕይወት ነው። 23 የኃጢአት ደሞዝ ሞት ሲሆን የእግዚአብሔር ነጻ ስጦታ ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የዘላለም ሕይወት ነው።
ጳውሎስ የእግዚአብሔርን ቸርነት አስመልክቶ በክርስቶስ ያመኑ ሰዎች ኃጢአት ለመሥራት ያለቸው ስሜት እንደሞቴ ቆጥረው ለእግዚአብሔር በመኖር አዲስ አኗኗር እንዲከተሉ ይነግራቸዋል።
ጳውሎስ ይኸንን ማሳመኛ ጥያቄ የሚጠይቀው የአንባቢዎቹን ትኩረት ላማግኘት ነው። በሌላ አባባል፣ “እንግዲህ ስለዚህ ጉዳይ ሁሉ ምን እንላለን? በእርግጠኝነት የምንለው እግዚአብሔር ጨምሮ ጨማምሮ ቸርነቱን እንዲያበዛልን ብለን ኃጢአት መሥራት መቀጠል የለብንም”
"እኛ" የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው ጳውሎስን፣ አንባቢዎቹንና ሌሎች ሰዎችን ነው።
እዚህ ላይ "ለኃጢአት የሞትን" ማለት ኢየሱስን የሚከተሉ ሰዎች አሁን ኃጢአትን ለመሥራት ያላቸው ስሜት እንደሞቴ ቆጥረው በኃጢአት የማይሸነፉ ናቸው። ጳውሎስ ይኸንን ማሳመኛ ጥያቄ የተጠቀመው ለነገሩ አጽንኦት ለመስጠት ነው፤ በሌላ አባባል፣ "እኛ አሁን እንደሞቱ ሰዎች ነን ኃጢአት አያሸንፈንም! ስለዚህ በእርግጥ ኃጢአት መሥራትን መቀጠል የለብንም"
ጳውሎስ ይኸንን ጥያቄ የተጠቀመው አጽንኦት ለመስጠት ነው። በሌላ አባባል፣ "አስታውሱ፥ አንድ ሰው እኛ ከክርስቶስ ጋር ግንኙነት እንዳለን ለማሳየት ሲያጠምቀን ከክርስቶስ ጋር በመስቀል ላይ እንደሞትን ጭምር ለማሳየት ነው።
x
"አሮጌ ሰውነት" የሚለው ተለዋጭ ዘይቤ ሰው በክርስቶስ ከማመኑ በፊት የነበረውን ባሕርይ ያመለክታል። ጳውሎስ አሮጌውን ኃጢአተኛ ሰውነታችን በክርስቶስ ባመንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር በመስቀል ላይ እንደሚሞት ይናገራል። በሌላ አባባል፣ “ኃጢአተኛው ሰውነታችን ከኢየሱስ ጋር በመስቀል ላይ ሞቷል”
አሮጌው ሰውነት ማለት በአንድ ወቅት የነበረ አሁን ግን የሌለ ሰውነት ማለት ነው።
ኃጢአተኛው ሰውነት የሚለው ተምሳሌታዊ ቃል የሚያመለክተው በጥቅሉ ያለውን ኃጢአተኛ ሰውነት ነው። በሌላ አባባል፣ “ኃጢአተኛው ባሕርያችን”
በሌላ አተረጓጎም፣ “ሊሞት የሚችል”
በሌላ አተረጓጎም፣ “ኃጢአት ከእንግዲህ ወዲህ ሊገዛን አይገባም” ወይም “ከእንግዲህ ወዲህ ለኃጢአት ልንገዛ አይገባም”
ለኃጢአት ባሪያ መሆን የሚለው ተለዋጭ ዘይቤአዊ አነጋገር አንድ ሰው ኃጢአትን ለመሥራት ያለው ፍላጎት ራሱን መከልከል እስከማይችል ድረስ ጠንካራ ሲሆን ማለት ነው። ኃጢአት ሰውየውን የሚቆጣጠርበት ሁኔታ ውስጥ መግባት ነው። በሌላ አባባል፣ “ከእንግዲህ በኋላ በኃጢአት ቁጥጥር ሥር ልንሆን አይገባም”
"ሞተናል" የሚለው ቃል ሰው በክርስቶስ ካመነ በኋላ በኃጢአት ቁጥጥር ሥር አለመሆኑን ያመለክታል።
እዚህ ላይ ‘ከሞት እንዲነሣ እንደተደረገ’ የሚለው አባባል የሞተውን ሰው እንደገና ሕይወት እንዲኖረው ማድረግን ያመለክታል። በሌላ አባባል፣ "ክርስቶስ ከሞተ በኋላ እግዚአብሔር እሱን ከሞት እንዳስነሣው እናውቃለን"
ከሞቱት ሰዎች ሁሉ መካከል ማለት ነው። ይህ አባባል የሚገልጸው የሞቱ ሰዎች የሚቆዩበት ቦታ ያሉትን ሟቾች ሁሉ ነው። ከእነርሱ መካከል መነሣት እንደገና ወደ ሕይወት መመለስ ነው።
እዚህ ላይ "ሞት" ሥልጣን እንዳለው ንጉሥ ወይም ገዢ በሰዎች ላይ ኃይል እንዳለው ይገልጻል። በሌላ አባባል፣ “እንደገና ተመልሶ አይሞትም”
"አንድ ጊዜ" የሚለው ሐረግ አንድን ጉዳይ በአንድ ጊዜ ሙሉ በሙሉ መጨረስ ማለት ነው። በትርጉማችሁ ውስጥ ይኸንን ሐሳብ መግለጥ ትችላላችሁ። በሌላ አተረጓጎም፣ "እሱ በሞተ ጊዜ የሞትን ኃይል ሙሉ በሙሉ ሰብሮታል"
“"ስለዚህ እናንተም አስቡ"
"እናንተም ስለ ራሳችሁ እንደዚሁ አስቡ" ወይም "ራሳችሁን እንደዚሁ ተመልከቱ"
አንድ ሰው በድን የሆነውን አካል የሆነ ነገር እንዲሠራ ማስገደድ እንደማይችል ሁሉ ኃጢአት ክርስቲያን አማኞችን አስገድዶ እግዚአብሔርን ከማክበር ሊያግዳቸው አይችልም። በሌላ አባባል፣ “የኃጢአት ኃይል የማይሰማችሁ በሚመስል መልኩ የሞታችሁ”
"የኃጢአት ኃይል እንዳይሰማን የሞትን እግዚአብሔርን ለማክበር ግን የምንኖር"
"ክርስቶስ ኢየሱስ በሚሰጣችሁ ኃይል እግዚአብሔርን ለማክበር የምንኖር"
ጳውሎስ ሊያስታውሰን የፈለገው ሕግ ሳይሆን መልካምነቱ እንደሚገዛን ነው። እኛ የኃጢአት ተገዢዎች አይደለንም ግን ለእግዚአብሔር ተገዢዎች ነን።
ጳውሎስ ኃጢአት ለሚሠሩ ሰዎች ኃጢአት እንደ ንጉሥ ወይም እንደ ገዢ ሆኖ እንደሚቆጣጠራቸው ይናገራል። በሌላ አባባል፣ “ኃጢአተኛውን ምኞታችሁን እንዲቆጣጠራችሁ አትፍቀዱለት”
ይህ ሐረግ የሚያመለክተው የሚሞተውን የአንድ ሰው ውጫዊ አካሉን ነው።
ጳውሎስ ክፉ ምኞት ያለውን ሰው ኃጢአተኛው ለእርሱ ታዝዞ ክፉ ነገር እንዲያደርግ እንደሚፈልግ እንደ ገዢው "ኃጢአት " ይገልጸዋል።
እዚህ ክፍል ላይ ኃጢአተኛው የአካል ክፍሎቹን ለገዢው ወይም በእርሱ ላይ ለነገሠው እንደሚሰጥ አድርጎ ያሳያል። የአንድ ሰው የአካል ክፍሎች ለመላው ሰውነቱ ይሠራሉ። በሌላ አባባል፣ "እግዚአብሔርን የማያስከብር ነገር መሥራት እንዲትችሉ ራሳችውን ለኃጢአት አሳልፋችሁ አትስጡ”
እዚህ ላይ "ሕያዋን" የሚለው የክርስቲያኖችን አዲስ መንፈሳዊ ሕይወት ነው። "ነገር ግን ራሳችውን ለእግዚአብሔር መስዋዕት አድርጉ ምክንያቱም እሱ አዲስ መንፈሳዊ ሕይወት ሰጥቷችኋል" ወይም "ነገር ግን በፊት ሞተው አሁን ግን ሕያዋን እንደሆኑ ሰዎች ራሳችውን ለእግዚአብሔር መስዋዕት አድርጉ”
እዚህ ላይ "የአካል ክፍሎቻችሁ" የሚለው ለመላው ሰውነት የሚሠራ መሆኑን ያመለክታል። በሌላ አባባል፣ "እግዚአብሔር እርሱን ለሚያስደስት ሥራ እንዲጠቀሚባችው ፍቀዱለት"
ጳውሎስ "ኃጢአት" ሰዎችን የሚገዛ ንጉሥ ተምሳሌት አድርጎ ይገልፀዋል። በሌላ አባባል፣ "ክፉ ምኞታችሁ የሚታደርጉትን ነገር እንዲቆጣጠር አትፍቀዱ" ወይም "ልታደርጉ የሚትፈልጉትን ክፉ ነገር ለማድረግ ራሳችውን አትስጡ"
"ከሕግ በታች መኖር" ማለት በሕግ ውስንነት እና ጉድለት ውስጥ መመላለስ ማለት ነው። እናንተ ሲትተረጉሙ ሙሉ ትርጉም ለመስጠት ይህንን ግልጽ ማድረግ ትችላላችሁ። በሌላ አባባል፣ "እናንተ ከዚህ በኋላ ኃጢአትን ከመሥራት ሊገታችው በማይችለው በሙሴ ሕግ ተወስናችው የሚትኖሩ አይደላችውም"
"በእግዚአብሔር ምሕረት ሥር" ማለት የእግዚአብሔር ነፃ ስጦታ እናንተ ኃጢአትን ከመሥራት ራሳችሁን የሚትጠብቁበትን ኃይል ይሰጣችኋል ማለት ነው። እናንተ ስትተረጉሙ ሙሉ ትርጉም ለመስጠት ይህንን ግልጽ ማድረግ ትችላላችሁ። በሌላ አባባል፣"ኃጢአት መሥራትን የሚታቆሙበት ኃይል በሚሰጣችው በእግዚአብሔር ምሕረት ተይዛችዋል"
ጳውሎስ በእግዚአብሔር ቸርነትና ምህረት መኖርን እንደ ምክንያት ተጠቅመን ኃጢአት መሥራት አይገባም የሚለውን ሐሳብ አጽንኦት ለመስጠት በጥያቄ መልክ ተናገረ። በሌላ አባባል፣ "ይሁን እንጂ በሙሴ ሕግ ተይዘን ከመኖር ይልቅ በእግዚአብሔር ቸርነትና ምህረት ተይዘን የምንኖር ነን ሲባል በእርግጥ ኃጢአት ለመሥራት ተፈቅዶልናል ማለት አይደለም"
"ይህ እንዲሆን በፍፁም አንፈልግም" ወይም "ያን እንዳላደርግ እግዚአብሔር ይርዳኝ" ይህ አገላለጽ ነገሩ እንደዚህ እንዳይደረግ ያለውን ከፍተኛ ፍላጎት ያመለክታል። እዚህ ላይ በእናንተ ቋንቋ ተመሳሳይ አገላለጽ ሊኖር ስለሚችል መጠቀም ትችላላችሁ። በሮሜ 3፡31 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁ ተመልካቱ።
ጳውሎስ ኃጢአት እየሠሩ መኖርን ለመቀጠል በእግዚአብሔር ቸርነትና ምህረት መኖር የሚለው ምክንያት ሊሆን ይችላል ብሎ የሚያስብ ማንኛውንም ሰው ለመገሰጽ በጥያቄ መልክ ተናገረ። በሌላ እባባል፣ "ሊትታዘዙት ለመረጣችውት ጌታ ባርያ መሆናችውን ማወቅ አለባችው"
x
"ግን እኔ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ!"
ለኃጢአት ባሪያ መሆን የሚለው ተለዋጭ ዘይቤአዊ አነጋገር አንድ ሰው ኃጢአትን ለመሥራት ያለው ፍላጎት ራሱን መከልከል እስከማይችል ድረስ ጠንካራ ሲሆን ማለት ነው። ኃጢአት ሰውዬውን የሚቆጣጠርበት ሁኔታ ውስጥ መግባት ነው። በሌላ አባባል፣ “እናንተ ለኃጢአት እንደ ባርያ ነበራችሁ” ወይም “እናንተ በኃጢአት ቁጥጥር ሥር ነበራችሁ”
እዚህ ላይ "ልብ" የሚለው ቃል እዚህ ላይ የሚያመለክተው የምንሠራውን ሥራ በቅንነት ወይም በታማኝነት መሥራትን ነው። በሌላ አባባል፣ "ነገር ግን እናንተ በእውነት ታዛዦች ሆናችኋል”
"አኗኗር" የሚለው ቃል የሚያመለክተው እንደ እግዚአብሔር ሐሳብ ወደ መኖር የሚያመራ የኑሮ አካሄድን ነው። አማኝ ክርስቲያኖች አሮጌውን የኑሮ አካሄድ ቀይረው በክርስትና መሪዎች አስተምሮ መሠረት ከአዲሱ የኑሮ አካሄድ ጋር የሚሄድ ኑሮ ይኖራሉ። በሌላ አባባል፣ "የክርስትና መሪዎች ያስተማሯችውን ትምህርት"
በሌላ አባባል፣ "ክርስቶስ ከኃጢአት ኃይል ነፃ አውጥቶአችሁ ነበር"
እዚህ ላይ “ከኃጢአት ነፃ መውጣት” የሚለው ዘይቤአዊ አነጋገር አንድ ሰው ኃጢአትን ለመሥራት ያለውን ጠንካራ ፍላጎት መግታትና ራሱን መከልከል እስከመቻል መድረስን የሚያመለክት ነው። በሌላ አባባል፣ “ኃጢአትን ለመሥራት ያለችው ጠንካራ ፍላጎት ተወግዶአል” ወይም “በኃጢአት ቁጥጥር ሥር ከመሆን ነፃ ወጥታችኋል”
የእግዚአብሔርን ሐሳብ የማገልገል ባርነት የሚለው ዘይቤአዊ አነጋገር አንድ ሰው የእግዚአብሔርን ሐሳብ ለመፈጸም ያለውን ጠንካራ ፍላጎት የሚያመለክት ነው። የእግዚአብሔርን ሐሳብ ለመፈጸም ያለው ፍላጎት ሰውዬውን የሚቆጣጠርበት ሁኔታ እንደማለት ነው። በሌላ አባባል፣ “የእግዚአብሔርን ሐሳብ ለመፈጸም ላላችው ፍላጎት እንደ ባርያ ሆናችኋል” ወይም “አሁን እናንተ የእግዚአብሔርን ሐሳብ በመፈጸም ፍላጎት ቁጥጥር ሥር ናችሁ”
በሌላ አባባል፣ “ክርስቶስ የእግዚአብሔርን ሐሳብ የሚታገለግሉ ባሮች አድርጓችኋል” ወይም“ “አሁን እናንተ የእግዚአብሔርን ሐሳብ በመፈጸም ፍላጎት ቁጥጥር ሥር እንዲትሆኑ ክርስቶስ ለውጦአችኋል”
ጳውሎስ ለምን ስለ ባርያ እና ነፃነት ለምን እንደሚናገር አንባቢዎቹን ሳያስገርም እንደማይቀር ገምቶ ይሆናል። እዚህ ላይ እርሱ የሚናገረው ለአንባቢዎቹ እንዲገባቸው እነዚህን ሐሳቦች ከዕለት ዕለት የኑሮአቸው ተሞክሮ ወስዶ እየተጠቀመባቸው መሆኑን ይናገራል። ይኸውም ሰዎች ወይ በኃጢአት ቁጥጥር ሥር ወይ የእግዚአብሔርን ሐሳብ በመፈጸም ፍላጎት ቁጥጥር ሥር እንደሚሆኑ ነው። በሌላ አባባል፣ “እኔ ስለዚህ ነገር በሰውኛ አነጋገር እየተናገርኩ ነው” ወይም “እኔ ከዕለት ዕለት የኑሮአችሁ ተሞክሮ ምሳሌ እየወሰድኩ ነው”
ጳውሎስ ብዙ ጊዜ "ሥጋ (ለባሽ)" የሚለውን ቃል የሚጠቀመው የ "መንፈስ" ተቃራኒ ከመሆኑ አንፃር ነው። በሌላ አባባል፣ “ስለ መንፈሳዊ ነገሮች ሙሉ በሙሉ ስለማትረዱ”
እዚህ ላይ "የአካል ክፍሎቻችው" የሚለው መላ ሰውነትን ያመለክታል። በሌላ አባባል፣ "ራሳችሁን ክፉ ለሆነው እና እግዚአብሔርን ለማያስደስት ነገር አሳልፋችው ሰጣችው"
እዚህም ላይ "የአካል ክፍሎቻችው" የሚለው መላ ሰውነትን ያመለክታል። በሌላ አባባል፣ "እግዚአብሔር ለራሱ የተለያችው እንዲያደርጋችው እና እርሱን የሚታገለግሉበትን ኃይል እንዲሰጣችው በእግዚአብሔር ፊት ትክክል የሆነውን ነገር ለመሥራት ራሳችሁን ለዚህ ሥራ ተገዢ አድርጋችው አቅርቡ"
እዚህ ላይ “የእግዚአብሔርን ሐሳብ ከመፈጸም ነፃ መውጣት” የሚለው ዘይቤአዊ አነጋገር አንድ ሰው የእግዚአብሔርን ሐሳብ መፈጸም የማይጠበቅበት መሆኑን የሚያመለክት ነው።ሰዎቹ በእግዚአብሔር ፊት ትክክል የሆነውን ነገር መሥራት እንደማይጠበቅባቸው አድርገው በማሰብ ይኖሩ ነበር። በሌላ አባባል፣ “የእግዚአብሔርን ሐሳብ መፈጸም እንደማይጠበቅበት ተደርጎ ይወሰድ ነበር” ወይም “በእግዚአብሔር ፊት ትክክል የሆነውን ነገር መሥራት የማይጠበቅባችሁ የሚያስመስል ባሕርይ አሳይታችኋል”
“ፍሬ” የሚለው ዘይቤአዊ አነጋገር “ውጤት” ወይም “ጥቅም” ለማለት ነው። ጳውሎስ እዚህ ላይ በጥያቄ መልክ ያስቀመጠው ኃጢአትን መሥራት ለምንም እንደማይበጅ አጥብቆ ለማሳሰብ ነው። በሌላ አባባል፣ “አሁን እንዲታፍሩ ከሚያደርጓችሁ ነገሮች ምንም መልካም ነገር አላገኛችውም” ወይም "አሁን እንዲታፍሩ የሚያደርጓችው ነገሮችን በመሥራታችው ምንም አልተጠቀማችውም"
በሌላ አባባል፣ “ነገር ግን አሁን ከኃጢአት ነፃ ወጥታችው የእግዚአብሔር ባሪያ ሆናችኋል” ወይም “ነገር ግን አሁን እግዚአብሔር ከኃጢአት ነፃ አውጥቶአችሁ የራሱ ባርያ አድርጓችኋል”
“ከኃጢአት ነፃ መውጣት” የሚለው ዘይቤአዊ አነጋገር ኃጢአት መሥራት አለመቻልን የሚያመለክት ነው። በሌላ አባባል፣ “ነገር ግን አሁን እግዚአብሔር ኃጢአት ከመሥራት መቆጠብ እንዲትችሉ አደረጋችሁ”
ለእግዚአብሔር “ባርያ መሆን” የሚለው ዘይቤአዊ አነጋገር እግዚአብሔርን ማገልገልና ለእርሱ መታዘዝን የሚያመለክት ነው። በሌላ አባባል፣ “እግዚአብሔር እርሱን ማገልገል እንዲትችሉ አደረጋችሁ”
እዚህ ላይ “ፍሬ” የሚለው ዘይቤ “ውጤት” ወይም “ጥቅም” ለማለት ነው። በሌላ አባባል፣ “ጥቅሙ መቀደሳችው ነው” ወይም “ጥቅሙ እናንተ የተቀደሰ አኗኗር መምራታችሁ ነው”
“የዚህ ሁሉ ውጤት እናንተ ለዘላለም ከእግዚአብሔር ጋር ትኖራላችሁ”
1 ወንድሞች ሆይ፥ሰው በሕይወት እስካለ ድረስ ሕግ እንደሚገዛው አታውቁምን? ይህንን የምለው ስለ ሕግ ለሚያውቁት ነው። 2 ያገባች ሴት ባሏ በሕይወት እስካለ ድረስ ለእርሱ በሕግ የታሰረች ነች፥ባሏ ቢሞት ግን ከጋብቻ ሕግ ነጻ ትሆናለች። 3 እንግዲህ ባሏ በሕይወት እያለ ከሌላ ወንድ ጋር ብትኖር አመንዝራ ትባላለች። ባሏ ቢሞት ግን ከሕጉ ነጻ ስለሆነች ከሌላ ወንድ ጋር ብትኖርም አመንዝራ አትሆንም። 4 ስለዚህ ወንድሞቼ ሆይ፥እናንተም በክርስቶስ ሥጋ ለሕግ ምውት ተደርጋችኋል። ይኸውም ለእግዚአብሔር ፍሬ እናፈራ ዘንድ ከሌላው ማለትም ከሙታን ከተነሣው ጋር እንድትተባበሩ ነው። 5 በሥጋ በነበርንበት ጊዜ ኃጢአታዊ ምኞት በሕግ በኩል ሞትን ሊያፈራ በሰውነታችን ክፍሎች ይሠራ ነበር። 6 አሁን ግን ከሕግ ነጻ ተደርገናል። ተይዘን ለነበርንበት ለዚያ ሞተናል።ይኸውም በአሮጌው ፊደል ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ እንድናገለግል ነው። 7 እንግዲህ ምን እንላለን? ሕጉ ራሱ ኃጢአት ነውን? አይደለም። ይሁንና በሕግ በኩል ባይሆን ኖሮ ኃጢአትን አላውቅም ነበር። ሕጉ "አትጎምጅ" ባይል ኖሮ መጎምጀትን አላውቅም ነበር። 8 ነገር ግን ኃጢአት በትዕዛዛት አማካይነት ዕድል አገኘና መጎምጀትን ሁሉ በውስጤ አመጣ። ምክንያቱም ኃጢአት ያለ ሕግ ምውት ስለሆነ ነው። 9 በአንድ ወቅት ያለ ሕግ ሕያው ነበርኩ፥ትዕዛዝ በመጣ ጊዜ ግን እኔ ሞትኩኝና ኃጢአት ህያው ሆነ። 10 ሕይወትን እንዲያመጣ የተሰጠው ትዕዛዝ ለእኔ ሞት ሆነ። 11 ምክንያቱም ኃጢአት በሕግ አማካይነት ዕድል አግኝቶ አታሎኛል። በትዕዛዝ አማካይነትም ገደለኝ። 12 በመሆኑም ሕጉ ቅዱስ ነው፥ትዕዛዙም ቅዱስ፥ጻድቅና በጎ ነው። 13 ስለዚህ በጎ የሆነው እርሱ ለእኔ ሞት ሆነብኝን? አይደለም። ነገር ግን ኃጢአት በጎ በሆነው በእርሱ አማካይነት ኃጢአትነቱ ይታወቅ ዘንድ በእኔ ሞትን አመጣብኝ። ይህ የሆነው በሕግ አማካይነት ኃጢአት ያለ ልክ ኃጢአታዊ ይሆን ዘንድ ነው። 14 ሕጉ መንፈሳዊ መሆኑን እናውቃለንና እኔ ግን ሥጋዊ ነኝ። ለኃጢአት ባርነት ተሽጫለሁ። 15 በርግጥ የማደርገውን አላውቅም። ለማድረግ የምፈልገውን አላደርግም፥ለማድረግ የምጠላውን ግን ያንኑ አደርጋለሁ። 16 ለማድረግ የማልፈልገውን የማደርግ ከሆንሁ ሕጉ መልካም ስለመሆኑ እስማማበታለሁ። 17 አሁን ግን ያንን የሚያደርገው በእኔ የሚኖረው ኃጢአት ነው እንጂ እኔ አይደለሁም። 18 በእኔ ማለትም በሥጋዬ ውስጥ ምንም መልካም ነገር እንደሌለ አውቃለሁ። መልካም የማድረግ ፍላጎቱ አለኝ፥ነገር ግን ላደርገው አልችልም። 19 የምፈልገውን ያንን መልካሙን አላደርግም ክፉውን፥ያንን የማልፈልገውን ግን አደርጋለሁ። 20 ለማድረግ የማልፈልገውን የማደርግ ከሆነ እንግዲህ አሁን ያንን የሚያደርገው በእኔ ውስጥ የሚኖረው ኃጢአት እንጂ እኔ አይደለሁም። 21 እንግዲህ መልካም የሆነውን ለማድረግ የሚፈልግ ሕግ በውስጤ እንዳለ አያለሁ፥ነገር ግን በተግባር በውስጤ ያለው ክፋት ሆኖ አገኘዋለሁ። 22 በውስጡ ሰውነቴ በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለኛል። 23 ነገር ግን በሰውነቴ ክፍሎች ውስጥ ሌላ ሕግ አያለሁ። እርሱም በአዕምሮዬ ውስጥ ያለውን አዲሱን ሕግ በመቃወም ይዋጋል። በሰውነት ክፍሎቼ ውስጥ ባለ የኃጢአት ሕግ ይማርከኛል። 24 እኔ ምስኪን ሰው ነኝ! ለሞት ከሚዳርገኝ ከዚህ ሰውነት ማን ይታደገኛል? 25 እንግዲያውስ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን! እኔ ራሴ በአእምሮዬ የእግዚአብሔርን ሕግ አገለግላለሁ። ሆኖም በሥጋ የማገለግለው የኃጢአትን ሕግ ነው።
ጳውሎስ ከሕግ በታች መኖር የሚፈልጉትን ሰዎች ሕጉ እንዴት እንደሚቆጣጠር ይገልጻል።
ጳውሎስ ይህን ጥያቄ የሚጠይቀው ለነገሩ አጽንኦት ለመስጠት ነው። በሌላ አባባል፣ "ስለዚህ ሰዎች ለሕግ መታዘዝ ያለባቸው በሕይወት እስካሉ ብቻ መሆኑን በእርግጠኝነት ታውቃላችው"
ወንድሞች ማለት ክርስቲያን ወገኖች፣ ወንዶችንም ሴቶችንም አጠቃልሎ ማለት ነው።
ጳውሎስ የዚህን ምሳሌ በ7፡2-3 ላይ አስቀምጦአል።
እዚህ ላይ “በሕግ ከባሏ ጋር ተጣምራለች” የሚለው ዘይቤአዊ አነጋገር አንዲት ሴት ከባሏ ጋር በጋብቻ ሕግ መሠረት አንድነት መፍጠሯን የሚያመለክት ነው። በሌላ አባባል፣ በሕጉ መሠረት ያጋበች ሴት ከባሏ ጋር አንድነት ፈጥራለች”
ይህ ማንኛውንም ያገባች ሴት ለማመልከት ነው።
በሌላ አባባል፣ "እግዚአብሔር እሷን እንደ አመንዝራ ይወስዳታል" ወይም "ሰዎች እሷን አመዝራ ይሏታል"
እዚህ ላይ ከሕግ ነፃ መሆን ማለት ለሕጉ የግዴታ መታዘዝ አይጠበቅም ማለት ነው። ይህን ጉዳይ በተመለከተ ያገባች ሴት ሌላ ወንድ ማግባት አትችልም ለሚለው ሕግ የግዴታ መታዘዝ አይጠበቅባትም። በሌላ አባባል፣ “እርሷ የግዴታ ለሕጉ መታዘዝ አይጠበቅባትም”
ይህ ወደ ሮሜ 7፡1 ለማመልከት ነው።
ይህ ማለት ክርስቲያን ወገኖች ማለት ነው፤ወንዶችንም ሴቶችንም ያጠቃልላል።
በሌላ አተረጓጎም፣ "በክርስቶስ በኩል በመስቀል ላይ በሞታችው ጊዜ ለሕግም ደግሞ ሞታችኋል"
“ከሙታን እንዲነሣ ተደረገ” የሚለው አባባል እንደገና በሕይወት ወደ መኖር መመለስን ያመለክታል። በሌላ አባባል፣ “እግዚአብሔር እንደገና በሕይወት ወደ መኖር ለመለሰው ለእርሱ” ወይም “እግዚአብሔር ከሙታን መካከል ላስነሣው ለእርሱ”
እዚህ ላይ "ፍሬ" የሚለው ተለዋጭ ዘይቤአዊ አነጋገር እግዚአብሔርን የሚያስደስቱ ተግባራት መፈጸምን ያመለክታል። "እግዚአብሔርን የሚያስደስት ተግባር ልንፈጽም እንችላለን"
እዚህ ላይ "ፍሬ" የሚለው ተለዋጭ ዘይቤአዊ አነጋገር “የአንድ ሰው የድርጊቱ ውጤት” ወይም “በአንድ ሰው ድርጊት ምክንያት የመጣ” ማለት ነው። በሌላ አባባል፣ “ውጤቱ መንፈሳዊ ሞት ሆነ” ወይም “መንፈሳዊ ሞትን አመጣብን”
እግዚአብሔር ቅዱስ የሚያደርገን በሕግ እንዳልሆነ ጳውሎስ ያስታውሰናል።
በሌላ አባባል፣ "እግዚአብሔር ከሕግ እሥራት አላቅቆናል"
ይህ ተውላጠ ስም ጳውሎስንና አማኝ ክርስቲያኖችን ያመለክታል።
ይህ ሕግን ያመለክታል። በሌላ አባባል፣ "ይዞን ላለው ሕግ"
ይህ የሙሴ ሕግን ያመለክታል።በሌላ አባብል፣ "የሙሴ ሕግ"
ጳውሎስ አዲስ ርዕስ እያስተዋወቀ ነው።
“ታዲያ ይህማ እውነት አይደለም" ይህ አገላለጽ ለቀደመው ማሳመኛ ጥያቄ በጣም ጠንከር ያለ አሉታዊ መልስ ይሰጣል። በራሳችሁ ቋንቋም በዚህ ቦታ አስገብታችሁ የሚትጠቀሙት ተመሳሳይ አገላለጽ ሊኖራችሁ ይችላል። በሮሜ 9፡14 ላይ ምን ብላችሁ እንደተረጎማችሁ ተመልከቱ።
ጳውሎስ ኃጢአትን ሊንቀሳቀስና ሊሠራ ከሚችል ሰው ጋር ያነፃፅራል።
"ኃጢአት ለመሥራት ያለኝ ምኞት"
ይህ አባባል የሰው የሆነውን ነገር ለመውሰድ መፈለግንና ክፉ የሆነ የወስብ ምኞትን ያጠቃልላል።
"ሕግ ባይኖር ኖሮ ሕግን መተላለፍ አይኖርም ነበር፤ ይህ ማለት ደግሞ ኃጢአት የሚባል አይኖርም ነበር ማለት ነው።
x
በሮሜ 7፡7-8 ላይ እንደተጠቀሰው ጳውሎስ ኃጢአት 3 ነገሮች ማድረግ እንደሚችል ይገልጻል፣ ዕድልን መጠቀም፣ ማታለል እና መግደል። "ኃጢአትን መሥራት ስለፈለኩ በአንድ ጊዜ ኃጢአትንም እየሠራሁ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ መታዘዝ እችላለሁ ብዬ እያሰብኩኝ ራሴን አታለልኩ ነገር ግን ለእርሱ ባለመታዘዜ ምክንያት እግዚአብሔር እኔን ከራሱ በመለየት ቀጣኝ"
ኃጢአት ለመሥራት ያለኝ ምኞት
ጳውሎስ ኃጢአትን የሆነ ነገር ሊያደርግ ከሚችል አካል ጋር ያነፃፅራል። በሮሜ 7፡8 ላይ የሰጣችሁትን ትርጉም ተመልከቱ።
ጳውሎስ ኃጢአትን የሆነ ነገር ሊያደርግ ከሚችል አካል ጋር ያነፃፅራል። ጳውሎስ በኃጢአተኞች ላይ የሚመጣው የእግዚአብሔር ፍርድ አካላዊ ሞት እንደሚያስከትል አድርጎ ይናገራል። በሌላ አባባል፣ "እኔን ከእግዚአብሔር ለየኝ"
በሥነ ምግባር ፍጹም የሆነ፣ ኃጢአት የሌለበት
ጳውሎስ በውስጣዊው ሰውነቱ ባለው ኃጢአት እና የእግዚአብሔርን ሕግ በሚያውቀው አእምሮው መካከል (በኃጢአት እና በመልካም ሐሳቡ መካከል) በውስጡ ስለሚካሄደው ፍልሚያ ይናገራል።
ጳውሎስ አዲስ ርዕስ እያስተዋወቀ ነው።
ጳውሎስ ይህን ጥያቄ የተጠቀመው ለነገሩ አጽንኦት ለመስጠት ነው።
ይህ የሚያመለክተው የእግዚአብሔርን ሕግ ነው።
“እንዲሞት አደረገኝ”
ይህ አገላለጽ ለቀደመው ማሳመኛ ጥያቄ በጣም ጠንከር ያለ አሉታዊ መልስ ይሰጣል። በራሳችሁ ቋንቋም በዚህ ቦታ አስገብታችሁ የሚትጠቀሙት ተመሳሳይ አገላለጽ ሊኖራችሁ ይችላል።በሌላ አባባል፣ “ታዲያ ይህማ እውነት አይደለም"
ጳውሎስ ኃጢአትን በራሱ የሆነ ነገር ሊያደርግ እንደሚችል አካል አድርጎ ያየዋል።
"ከእግዚአብሔር ለየኝ"
"ምክንያቱም እኔ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ ስላልፈጸምኩ"
ጳውሎስ በሥጋዊ ምኞቱ እና በእግዚአብሔር ሕግ መካከል (በክፉ እና በመልካም መካከል) በውስጡ ስለሚካሄድ ፍልሚያ ይናገራል።
"እኔ አንዳንድ የማደርጋቸውን ነገሮች ለምን እንደማደርጋቸው እርግጠኛ አይደለውም”
ምክንያቱም እኔ የማደርገው
“አላደርግም” የሚለው ቃል ተጋንኖ የተነገረው ለነገሩ አጽንኦት ለመስጠት ሲባል ነው። ጳውሎስ ማድረግ የሚፈልገውን የሚደርገው በፈለገው ጊዜ ሁሉ አይደለም ወይም ደግሞ አንድ አንድ ጊዜ ማድረግ የማይፈገውን ነገር ያደርጋል። በሌላ አባባል፣ "እኔ ማድረግ የሚፈለገውን የማደርገው ሁል ጊዜ አይደለም"
“አደርጋለሁ” የሚለው ቃል በውስጡ የያዘው ሐሳብ ጳውሎስ ሁል ጊዜ ማድረግ የሚጠላውን ነገር ማድረጉን ነው። ይህም ተጋንኖ የተነገረው ለነገሩ አጽንኦት ለመስጠት ሲባል ነው። ጳውሎስ ማድረግ የማይፈልገውን ነገር ደጋግሞ ያደርጋል። በሌላ አባባል፣ "አንዳንድ ጊዜ የማደርጋቸው ነገሮች መልካም አለመሆናቸውን የማውቃቸው ነገሮች ናቸው"
"ይሁን እንጂ እንዲህ የማደርግ ከሆነ"
"የእግዚአብሔር ሕግ መልካም መሆኑን አውቃለሁ"
ጳውሎስ ኃጢአትን ራሱ ላይ ተጽዕኖ ማምጣት የሚችል ሕይወት ያለው ነገር አድርጎ ይገልጸዋል።
እዚህ ላይ "ሥጋ" ኃጢአተኛውን የሰው ተፈጥሮ የሚገልጽ ቃል ነው። በሌላ አባባል፣ “ኃጢአተኛው ተፈጥሮዬ”
"መልካሙ ሥራ" ወይም "መልካሙ ድርጊት"
"ክፉው ሥራ" ወይም "ክፉው ድርጊት"
ጳውሎስ "ኃጢአትን" በውስጡ የሚኖር ሕይወት ያለው ነገር አድርጎ በመሳል ይናገራል።
ጳውሎስ "ክፉ ሐሳብን" በውስጡ የሚኖር ሕይወት ያለው ነገር አድርጎ በመሳል ይናገራል።
ይህ በክርስቶስ የሚታመን የታደሰ መንፈስ ነው።
"እኔ ማድረግ የሚችለው አሮጌው ተፈጥሮአዊ ባሕርዬ የሚያዝዘኝን ብቻ ነው፤ መንፈስ ቅዱስ የሚያሳየኝን አዲስ አካሄድም እንዳልከተል ያደርገኛል"
ይህ በመንፈስዊ ሕይወት ሕያው የተደረገ አዲሱ ባሕርይ ነው።
ይህ አሮጌው ተፈጥሮአዊ ባሕርይ ነው፤ ሰዎች ይዘውት የሚወለዱት።
“ኃጢአተኛው ባሕርዬ”
ጳውሎስ ይህን ጥያቄ የተጠቀመው የተሰማውን ጥልቅ ስሜት ለመግለጽ ነው። በእናንተ ቋንቋ በመጮህ ወይም ጥያቄ በመሰንዘር ጥልቅ ስሜት የሚገለጽበት መንገድ ካለ እዚህ ጋ አስገቡ። በሌላ አባባል፣ "እኔ አካለ ከሚመኘው ምኞት ነፃ የሚያወጣኝን አንድ ሰው እፈልጋለሁ"
“ያድነኛል”
ይህ ተለዋጭ ዘይቤ አካላዊ ሞትን የሚሞተውን አካል የሚያመለክት ነው።
ይህ በ7፡24 ላይ ላለው ጥያቄ መልስ ነው።
እዚህ ቁጥር ላይ አእምሮ እና ሥጋዊ ምኞት የገቡት ምን ያህል ለእግዚአብሔር ሕግ ወይም ለኃጢአት ሥራ አካሄድ እንደሚገዙ በንፅፅር ለማሳየት ነው። በአእምሮ ወይም በዕውቀት አንድ ሰው እግዚአብሔርን ማስደሰትና መታዘዝን ሊመርጥ ይችላል፤ ወይ ደግሞ በሥጋዊ ምኞቱ ወይም በአካላዊ ባሕርይው ለኃጢአት ሊገዛ ይችላል። በሌላ አባባል፣ "አእምሮዬ እግዚአብሔርን ማስደሰት ይመርጣል፤ ሥጋዊ ምኞቴ ግን ለኃጢአት መገዛትን ይመርጣል"
1 ስለዚህ በኢየሱስ ክርስቶስ ውስጥ ላሉት አሁን ኩነኔ የለባቸውም። 2 ምክንያቱም በኢየሱስ ክርስቶስ ውስጥ ያለው የመንፈስ ቅዱስ ሕግ ከኃጢአትና ከሞት ሕግ ነጻ አውጥቶኛል። 3 በሥጋ ድካም ምክንያት ሕግ ሊፈጽመው ያልተቻለውን እግዚአብሔር ፈጽሞታል። እግዚአብሔር የገዛ ልጁን በኃጢአታዊ ሥጋ ምሳሌ ለኃጢአት መሥዋዕት ይሆን ዘንድ ልኮ ኃጢአትን በሥጋው ኮነነ። 4 ይህንንም ያደረገው እንደ መንፈስ ቅዱስ ፈቃድ እንጂ እንደ ሥጋ ፈቃድ በማንመላለስ በእኛ የሕጉ ትዕዛዛት ይፈጸሙ ዘንድ ነው። 5 እንደ ሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ ስለሥጋዊ ነገሮች ያስባሉ፥እንደ መንፈስ ቅዱስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን ስለመንፈስ ቅዱስ ነገሮች ያስባሉ። 6 የሥጋ አስተሳሰብ ሞት ሲሆን የመንፈስ ቅዱስ አስተሳሰብ ግን ሕይወትና ሰላም ነው። 7 ይህ የሆነበት ምክንያት የሥጋ አስተሳሰብ ለእግዚአብሔር ሕግ ስለማይገዛ፥መገዛትም ስለማይችል የእግዚአብሔር ጠላት በመሆኑ ነው። 8 በሥጋ ያሉትም እግዚአብሔርን ለማስደሰት አይችሉም። 9 ይሁን እንጂ የእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ውስጥ መኖሩ እውነት ከሆነ በመንፈስ እንጂ በሥጋ አይደላችሁም። ነገር ግን የክርስቶስ መንፈስ የሌለው ማንም ቢሆን ይህ የእርሱ ወገን አይደለም። 10 ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ ቢኖር ሥጋ በኃጢአት ምክንያት ምውት ነው፥ መንፈስ ግን በጽድቅ ምክንያት ህያው ነው። 11 ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው የእርሱ መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ውስጥ ቢኖር ክርስቶስን ከሙታን ያስነሣው እርሱ በውስጣችሁ በሚኖረው በቅዱስ መንፈሱ አማካይነት ለሚሞተው ሰውነታችሁ ደግሞ ሕይወትን ይሰጠዋል። 12 ስለዚህ ወንድሞች ሆይ ዕዳ አለብን፥ነገር ግን እንደ ሥጋ ፈቃድ ልንኖር ለሥጋ አይደለም። 13 እንደ ሥጋ ፈቃድ ብትኖሩ መሞታችሁ አይቀርም፥የሥጋን ሥራ በመንፈስ ቅዱስ ብትገድሉ ግን በሕይወት ትኖራላችሁ። 14 በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው። 15 ተመልሳችሁ እንድትፈሩ የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁም። ይልቅ የተቀበላችሁት "አባ፥አባት" ብለን የምንጮህበትን የልጅነትን መንፈስ ነው። 16 የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን መንፈስ ቅዱስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል። 17 ልጆች ከሆንን ወራሾችም ነን፥ማለትም የእግዚአብሔር ወራሾች ነን። ከእርሱ ጋር እንድንከብር በርግጥ አብረነው ደግሞ መከራን ብንቀበል ከክርስቶስ ጋር አብረን የምንወርስ ነን። 18 የአሁኑ ዘመን መከራ ሊገለጥልን ካለው ክብር ጋር ሊነጻጸር እንደማይገባው አስባለሁ። 19 ምክንያቱም ፍጥረት የእግዚአብሔርን ልጆች መገለጥ በናፍቆት ስለሚጠባበቅ ነው። 20 ፍጥረት ለከንቱነት ተገዝቷልና ይህም ባስገዛው ፈቃድ እንጂ በራሱ ፈቃድ አይደለም። አስተማማኙ ተስፋም 21 ፍጥረት ራሱ ከመበስበስ ባርነት ነጻ ወጥቶ ወደ እግዚአብሔር ልጆች የክብር ነጻነት ይደርስ ዘንድ ነው። 22 አሁን እንኳን መላው ፍጥረት አብሮ በመቃተትና በምጥ ጣር ላይ መሆኑን እናውቃለን። 23 ይህም ብቻ አይደለም፥ነገር ግን የመንፈስ ቅዱስ የመጀመሪያው ፍሬ ያለን እኛ፥የሰውነታችን ቤዛ የሚሆነውን ልጅነታችንን እየተጠባበቅን እኛ ራሳችን እንኳን በውስጣችን እንቃትታለን። 24 የዳንነው በዚህ ተስፋ ነው። ነገር ግን ተስፋ የምናደርገው የማይታየውን ነው፥የሚያየውንማ ማን በተስፋ ይጠባበቃል? 25 ገና ያላየነውን ተስፋ የምናደርግ ከሆነ ግን እንግዲያው በትዕግስት እንጠባበቀዋለን። 26 እንዲሁም መንፈስ ቅዱስ ደግሞ በድካማችን ውስጥ ያግዘናል። እንዴት መጸለይ እንደሚገባን ስለማናውቅ መንፈስ ቅዱስ ራሱ በቃላት ሊገለጥ በማይቻል መቃተት ስለ እኛ ይማልድልናል። 27 መንፈስ ቅዱስ ስለ አማኞች እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ስለሚማልድ ልብን የሚመረምረው እግዚአብሔር የመንፈስ ቅዱስን ሃሳብ ያውቃል። 28 እግዚአብሔርን ለሚወዱት፥ በዓላማው ለተጠሩት ለእነርሱ ሁሉን ነገር አጣጥሞ ለመልካም እንደሚሠራላቸው እናውቃለን። 29 ምክንያቱም አስቀድሞ ያወቃቸውን እነርሱን በብዙ ወንድሞች መካከል በኩር ይሆን ዘንድ የልጁን መልክ እንዲመስሉ አስቀድሞ ደግሞ ወሰነ። 30 አስቀድሞ የወሰናቸውን ደግሞ ጠራቸው። የጠራቸውን ደግሞ አጸደቃቸው። ያጸደቃቸውን ደግሞ አከበራቸው። 31 እንግዲህ ስለእነዚህ ነገሮች ምን እንላለን? እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ማን ይቃወመናል? 32 ለገዛ ልጁ ያልራራለት ነገር ግን ስለሁላችን አሳልፎ የሰጠው እርሱ እንዴት ሁሉን ነገር ደግሞ ከልጁ ጋር በነጻ አይሰጠንም? 33 እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን ይኮንናቸዋል? የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው። 34 የሚኮንንስ ማነው? ስለ እኛ የሞተው፥ ይልቁንም ደግሞ ከሞት የተነሣው ክርስቶስ ነው። እርሱ ከእግዚአብሔር ጋር በክብር ሥፍራ ይገዛል፥ስለ እኛም እየማለደልን ያለው እርሱ ነው። 35 ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ ወይስ ጭንቀት ወይስ ስደት ወይስ ራብ ወይስ ራቁትነት ወይስ አደጋ ወይስ ሰይፍ ይለየናልን? 36 "ቀኑን ሙሉ ስለአንተ ብለን እንገደላለን። እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን" ተብሎ እንደተጻፈው ነው። 37 በእነዚህ ነገሮች ሁሉ ውስጥ በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን። 38 ሞት ቢሆን ሕይወት፥ መላእክት ቢሆኑ መንግሥታት፥አሁን ያሉት ነገሮች ወይም ሊመጡ ያሉት ቢሆኑ፥ ኃይላት ቢሆኑ፥ 39 ከፍታም ቢሆን ዝቅታ፥ የትኛውም ሌላ ፍጥረት ቢሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ውስጥ ካለ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየኝ እንደማይችል ተረድቻለሁ።
ጳውሎስ ኃጢአት እና መልካም ነገርን በተመለከተ በሕይወቱ ስላለው ትግል መልስ ይሰጣል።
እዚህ ላይ "የጥፋተኝነት ወቀሣ" የሚለው በሕዝብ ላይ የሚመጣውን ቁጣ ያመለክታል። በሌላ አባባል፣ "እግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር ኅብረት ያላቸውን ጥፋተኛ ናችሁ ብሎ አይቀጣቸውም”
"በዚያ ምክንያት" ወይም "እኔ የነገርኳችው እውነት ስለሆነ"
ይህ የሚያመለክተው የእግዚአብሔር መንፈስን ነው። "በክርስቶስ ኢየሱስ የሚገኝ የእግዚአብሔር መንፈስ"
ከኃጢአትና ከሞት ሕግ ነፃ መውጣት የሚለው ዘይቤአዊ አነጋገር የኃጢአትና የሞት ሕግ ተገዢ አለመሆንን ያመለክታል። በሌላ አባባል፣ “የኃጢአትና የሞት ሕግ ከአሁን በኋላ እንዳይገዛችሁ አደረገ”
እነዚህን ትርጉሞች ሊያመለክት ይችላል፣ 1) ሰዎች ኃጢአት እንዲሠሩ የሚገፋፋ ሕግ፤ ኃጢአታቸው ደግሞ ሞት ያመጣባቸዋል። በሌላ አባባል፣ “ኃጢአትንና ሞትን የሚያመጣ ሕግ" ወይም 2) ሰዎች ኃጢአት ይሠሩና ይሞታሉ የሚል መርህ
እዚህ ላይ ሕጉ የኃጢአትን ኃይል ሊሰብር እንደማይችል እንደ አንድ አካል ተደርጎ ተገለጸ። በሌላ አባባል፣ "ሕጉ ኃጢአት ከመሥራት ሊያስቆመን የሚችል ጉልበት ስላልነበረው በኛ ውስጥ ያለው የኃጢአት ጉልበትም በጣም ጠንካራ ስለነበረ እግዚአብሔር ግን ኃጢአት ከመሥራት አስቆመን"
"በኃጢአተኛው የሰዎች ባሕርይ"
የእግዚአብሔር ልጅ የራሱን አካልና ሰዋዊ ሕይወት ስለኃጢአት የዘላለም መስዋዕት አድርጎ በማቅረብ በኃጢአታችን ምክንያት ሊመጣ ያለውን የእግዚአብሔርን ቁጣ ለዘላለም መልሶታል።
ይህ በጣም አስፈላጊ የእግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ማዕረግ ነው፤
"እንደ ማንኛውም ሰው የኃጢአተኛ ሰው መልክ የያዘ"
"ስለ እኛ ኃጢአት መስዋዕት ሊሆን እንዲሞት"
"እግዚአብሔር በልጁ አካል የኃጢአትን ኃይል ሰበረ"
በሌላ አተረጓጎም፣ "ሕጉ ከኛ የሚፈልገውን ነገር ማሟላት እንድንችል"
በመንገዱ መራመድ የሚለው ዘይቤአዊ አነጋገር አንድ ሰው ሕይወቱን እንዴት እንደሚመራ የሚገልጽ ነው። ሥጋ የሚለው ቃል ደግሞ ኃጢአተኛውን የሰው ባሕርይ የሚተካ ነው። በሌላ አባባል፣ “ኃጢአተኛ የሆነውን ፍላጎታችንን የማንታዘዝ እኛ”
"ነገር ግን ለመንፈስ ቅዱስ የምንታዘዝ"
ጳውሎስ ሥጋዊ ምኞትን አሁን በእኛ ካለው መንፈስ ጋር ማነፃፀሩን ቀጥሏል።
ጳውሎስ እዚህ ላይ ስለ "ሥጋዊ ምኞት" እና ስለ "መንፈስ" ሕይወት እንዳላቸው አካላት አድርጎ ያቀርባቸዋል። በሌላ አባባል፣ "ኃጢአተኞች ሰዎች እንዴት እንደሚያስቡ. . . መንፈስ ቅዱስን የሚያዳምጡ ሰዎች እንዴት እንደሚያስቡ"
ይህ ማለት የአንድ ሰው ከእግዚአብሔር መለየት ማለት ነው።
ይህ የሚያመለክተው ክፉ የሆነው ባሕርያቸው የሚነግራቸውን ነገር የሚሠሩትን ሰዎች ነው።
"በኃጢአተኛ ባሕርይ መመራት"፤ “ሥጋዊ ባሕርይ” በሮሜ 8፡5 ላይ እንዴት እንደተተረጎመ ተመልከቱ።.
"በመንፈስ ቅዱስ መመራት"
እነዚህ ሐረጎች ሁሉ መንፈስ ቅዱስን ያመለክታሉ
ይህ ማለት አንዳንዶቹ የእግዚአብሔር መንፈስ እንዳላቸው ጳውሎስ ይጠራጠራል ማለት አይደለም። ጳውሎስ ሁላቸውም የእግዚአብሔር መንፈስ እንዳላቸው እንዲገነዘቡ ፈልጎ ነው።
ክርስቶስ በአንድ ሰው ሕይወት ውስጥ እንዴት እንደሚኖር ግልጽ ተደርጎ መነገር አለበት። በሌላ አባባል፣ “ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት በእናንተ ውስጥ የሚኖር ከሆነ”
ይህ አባባል ሁለት ትርጉሞች ሊኖሩት ይችላል፣ 1) አንድ ሰው [የኃጢአት ኃይል ተጽዕኖ እንዳይሰማው] በመንፈስ የሞተ ነው 2) አንድ ሰው በኃጢአት ምክንያት አካላዊ ሞት ይሞታል።
ይህ አባባል ሁለት ትርጉሞች ሊኖሩት ይችላል፣ 1) አንድ ሰው በመንፈስ ሕያው ይሆናል ምክንያቱም ትክክል የሆነውን ነገር እንዲሠራ እግዚአብሔር ኃይል ይሰጣዋል 2) አንድ ከሞተ በኋላ እግዚአብሔር ያንን ሰው በሕይወት ወደ መኖር ይመልሰዋል ምክንያቱም እግዚአብሔር ጻድቅ በመሆኑ ለአማኝ ክርስቲያኖች የዘላለም ሕይወት ይሰጣቸዋል።
ጳውሎስ መንፈስ ቅዱስ በአንባቢዎቹ ውስጥ እንደሚኖር ያስባል። በሌላ አባባል፣ "ምክንያቱም መንፈሱ. . .በእናንተ ስለሚኖር".
"ከሞት ያስነሣው የእግዚአብሔር"
እዚህ ላይ ከሞት አስነሣ ማለት የሞተን ሰው እንደገና መልሶ ሕያው ማድረግ ማለት ነው። በሌላ አባባል፣ “ኢየሱስን መልሶ በሕይወት እንዲኖር አደረገ”
"ውጫዊ አካላት" ወይም "የሆነ ቀን ሊሞቱ ያሉ አካላት"
"የነገርኳችሁ ነገር እውነት ስለሆነ"
እዚህ ላይ ወንድሞች ሲል ክርስቲያን ወገኖች ለማለት ነው፣ ወንዶችንም ሴቶችንም ያጠቃልላል።
በሌላ አተረጓጎም፣"የእግዚአብሔር መንፈስ የሚመራቸው ሰዎች ሁሉ"
እዚህ ላይ 'በኢየሱስ ያመኑ አማኞች ሁሉ' ማለት ነው። ብዙ ጊዜም "የእግዚአብሔር ልጆች" ተብሎ ይተረጎማል።
“እንድንጮህ የሚያደርገን”
አብ የሚለው አባ ከሚለው የአረሜይክ ቋንቋ የመጣ ሲሆን አባት ማለት ነው።
x
ሰውነታችን በሚበዥበት ጊዜ እንደሚለወጥ ጳውሎስ እኛ አማኞችን እስከ 8፡25 ባለው በዚህ ክፍል ያስታውሰናል።
እዚህ ላይ 'አስባለሁ' የሚለውን ሐሳብ ለማጽናት ነው። 'ምክንያቱም' ለማለት አይደለም።
በሌላ አተረጓጎም፣ “የአሁኑን መከራ ከዚያ ጋር ማወዳደር አልችልም”.
በሌላ አተረጓጎም፣ "እግዚአብሔር ሊገልጠው ያለው" ወይም "እግዚአብሔር ሊያሳውቅ ያለው"
ጳውሎስ እዚህ ላይ እግዚአብሔር የፈጠራቸውን ነገሮች ሁሉ በጉጉት የሆነ ነገር የሚጠብቁ አካላት እንደሆኑ ይናገራል።
በሌላ አተረጓጎም፣ "እግዚአብሔር ልጆቹን የሚገልጥባቸውን ጊዜ"
ይህ ማለት በኢየሱስ ያመኑት ሁሉ፤ "የእግዚአብሔር ልጆች" ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።
ጳውሎስ የክርስቲያን አማኞችን መንፈስ ቅዱስ መቀበል ተተክሎና ወቅቱን ጠብቆ ከደረሰው የመጀመርያ ፍሬና አትክልት ጋር ያነጻጽራል። መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር ለክርስቲያን አማኞች ከሚሰጣቸው ነገሮች የመጀመርያ መሆኑን በአጽንኦት ለመናገር ነው። በሌላ አባባል፣ “እኛ የመጀመርያውን የእግዚአብሔር ስጦታ ያለን ነን፤ እሱም መንፈስ ቅዱስ ነው”
እዚህ ላይ "የእግዚአብሔር ልጅነታችን መሟላት" ማለት የእግዚአብሔር ቤተሰብ ሙሉ አባል ስንሆን ማለት ነው። "መበዥት" የሚለው ቃል እግዚአብሔር ሲያድነን ማለት ነው። በሌላ አባባል፣ "የእግዚአብሔር ቤተሰብ ሙሉ አባል መሆናችንን እየተጠባበቅን ይኸውም እሱ ኣካላችንን ከመበስበስና ከሞት ሲያድን"
በሌላ አተረጓጎም፣ “በእርሱ ተስፋ ስላደረግን እግዚአብሔር አዳነን”
ጳውሎስ የሚጽፍላቸውን ሰዎች "ተስፋ" የሚለው ቃል ምን ማለት እንደሆነ እንዲገነዘቡ በጥያቄ መልክ ተናገራቸው። በሌላ አባባል፣ "ነገር ግን በመታመን እየተጠባበቅን ከሆነ የምንፈልገው ነገር ገና አልሆነልንም ማለት ነው። የሚፈልገውን ካገኘማ ማንም በመታመን አይጠብቅም"
ምንም እንኳ ጳውሎስ በሥጋዊ ምኞት እና በመንፈሳዊ እውነታ መካከል በክርስቲያን አማኞች ሕይወት የሚካሄድ ትግል መኖሩን አጽንኦት ሰጥቶ የሚናገር ቢሆንም የእግዚአብሔር መንፈስ እንደሚያግዘን ደግሞ ያረጋግጥልናል።
x
ጳውሎስ ክርስቲያን አማኞችን ከእግዚአብሔር ፍቅር ማንም ሊለያቸው እንደማይችል ያስታውሳቸዋል።
በሌላ አተረጓጎም፣ "እግዚአብሔር ለመረጣቸው"
"ገና ሳይፈጥራቸው እንኳ ላወቃቸው”
"መዳረሻቸውን ደግሞ ወሰነ" ወይም "ደግሞም አስቀድሞ አቀደ"
እግዚአብሔር ከፍጥረት ጅማረ አስቀድሞ በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ የሚያምኑት ኢየሱስን ወደ መምሰል እንዲያድጉ አቀደ። በሌላ አባባል፣ "ልጁን እንዲመስሉ ልለውጣቸው"
ይህ ለኢየሱስ ለእግዚአብሔር ልጅ አስፈላጊ ማዕረግ ነው።
“ልጁ የመጀመርያ ልጅ እንዲሆን”
እዚህ ላይ "ወንድሞች" የሚለው ሁሉንም አማኞች ወንድንም ሆነ ሴት ያመለክታል። በሌላ አባባል፣ "የእግዚአብሔር ቤተሰብ ከሆኑት ከብዙ ወንድሞችና እህቶች መካከል"
"እግዚአብሔር አስቀድሞ ዕቅድ ላወጣላቸው"
እዚህ ላይ "ከጥፋተኝነት አወጣቸው" የሚለው ያለፈውን ጊዜ አመልካች መሆኑ ይህ በእርግጠኝነት እንደሚሆን አስረግጦ ለመግለጽ ነው። በሌላ አባባል፣ "እነዚህን ደግሞ በፊቱ ከጥፋተኝነት ነፃ አደረጋቸው"
x
ጳውሎስ ከላይ ለተናገረው ነገር አጽንኦት ለመስጠት ዐረፍተ ነገሩን በጥያቄ መልክ ያስቀምጣል። በሌላ አባባል፣ "ከዚህ ሁሉ መረዳት ያለብን ነገር ይህ ነው፣ እግዚአብሔር እየረዳን ከሆነ ማንም ሊያሸንፈን አይችልም"
ገደብ የለሽና ቅዱስ የሆነውን የእግዚአብሔርን ባሕርይ ኃጥአተኛ ከሆነው የሰው ባሕርይ ጋር ለማቀራረብ ቅዱስና ገደብ የለሽ መስዋዕት እንዲሆን እግዚአብሔር አብ የእግዚአብሔርን ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ መስቀል ላከ። እዚህ ላይ "ልጅ" የሚለው ለኢየሱስ ለእግዚአብሔር ልጅ አስፈላጊ ማዕረግ ነው።
"ነገር ግን በጠላቶቹ እጅ ኣሳልፎ ሰጠው"
ጳውሎስ ለተናገረው ነገር አጽንኦት ለመስጠት ዐረፍተ ነገሩን በጥያቄ መልክ ያስቀምጣል። በሌላ አባባል፣ "እርሱ በእርግጠኝነት ሁሉን ነገር በነፃ ይሰጠናል"
“በቸርነቱ ሁሉን ነገር ይሰጠናል"
ጳውሎስ ለተናገረው ነገር አጽንኦት ለመስጠት ዐረፍተ ነገሩን በጥያቄ መልክ ያስቀምጣል። በሌላ አባባል፣ "በእግዚአብሔር ፊት ማንም ልከሰን አይችልም ምክንያቱም በፊቱ ትክክለኛ ሕይወት እንዲኖረን ሊያደርገን የሚችል እርሱ ነው።
ጳውሎስ ለተናገረው ነገር አጽንኦት ለመስጠት ዐረፍተ ነገሩን በጥያቄ መልክ ያስቀምጣል። መልስ እንዲሰጥ ጠብቆ አይደለም። "ማንም ልወቅሰን አይችልም"
እዚህ ላይ ከሞት እንዲነሣ የተደረገ የሚለው አባባል የሞተን ሰው ተመልሶ በሕይወት እንዲኖር ማድረግ ለማለት ነው። በሌላ አተረጓጎም፣ "ክሁሉ ይልቅ እግዚአብሔር ከሙታን ያስነሣው እርሱ" ወይም "ከሁሉ ይልቅ እንዲያሁም ከሞት ወደ ሕይወት የተመለሰ እርሱ"
“በእግዚአብሔር ቀኝ” መሆን ከእግዚአብሔር ከፍ ያለ ክብር እና ሥልጣን የመቀበል ተግባር ምልክት ነው። በሌላ አባባል፣ “በእግዚአብሔር አጠገብ በክብር ቦታ ያለ”
ጳውሎስ ይህን ጥያቄ የተጠቀመው ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ሊለየን እንደማይችል ለማስተማር ነው። በሌላ አባባል፣ “መቼም ቢሆን ማንም ከክርስቶስ ፍቅር ሊለየን አይችልም”
“ከክርስቶስ ፍቅር ሊለየን” የሚሉትን ቃላት ከቀደመው ጥያቄ መረዳት ይቻላል። በሌላ አባባል፣ “መከራ ወይም ሥቃይ ወይም ስደት ወይም ረሃብ ወይም እርዛት ወይም አደጋ ወይም ሰይፍ ከክርስቶስ ፍቅር ሊለዩን ይችላሉ ወይ?
ጳውሎስ ይህን ጥያቄ የተጠቀመው እነዚህ ነገሮች እንኳ ከክርስቶስ ፍቅር ሊለዩን እንደማይችሉ በአጽንኦት ለመናገር ነው። በሌላ አባባል፣ “መከራ፣ ሥቃይ፣ ስደት፣ ረሃብ፣ እርዛት፣ አደጋ እናአሰይፍ ከክርስቶስ ፍቅር ሊለዩን አይችሉም”
በንድፈ ሐሳብ ደረጃ የተቀመጡ ስሞች በቃላት ሐረጎች ሊገለጹ ይችላሉ። እዚህ ላይ “ሰይፍ” የሚለው አነጋገር በጭካኔ መገደልን ይተካል። በሌላ አባባል፣ “ምንም እንኳ ሰዎች ቢያሰቃዩን፣ ቢጎዱን፣ ልብሳችንንና ምግባችንን ቢወስዱብን ወይም ቢገድሉን ከክርስቶስ ፍቅር ሊለዩን አይችሉም”
ሁለቱም ቃላት አንድ ትርጉም አላቸው።
እዚህ ላይ "ላንተ" የሚለው ቃል ነጠላ ሆኖ እግዚአብሔርን የሚያመለክት ነው
እዚህ ላይ "እኛ" የሚለው ቃል ይህን የቅዱሳት መጻሕፍት ክፍል የጻፈውን ሰው ሰው ሲያመለክት የመልዕክቱን ተቀባይ አያመለክትም፣ እሱም እግዚአብሔር ነበር። "ቀኑን ሙሉ" የሚለው ሐረግ ምን ያህል አደገኛ ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ በአጽንኦት አጋንኖ ለማሳየት ነው። ጳውሎስ ይህን የቅዱሳት መጻሕፍት ክፍል የተጠቀመው የእግዚአብሔር የሆኑ ሰዎች ሁሉ በሕይወታቸው ከባድ ጊዜ ሊገጥማቸው እንደሚችል መጠበቅ እንደሚገባቸው ለማሳየት ነው። በሌላ አተረጓጎም፣ “ጠላቶቻችን ሁሌም ሊገድሉን ይፈልጋሉ”
"እኛ ሙሉ የድል አድራጊነት ብቃት አለን"
ኢየሱስ እንዴት ያለ ፍቅር እንዳሳየ በግልጽ ማስቀመጥ እንችላለን። በሌላ አባባል፣ "በብዙ ፍቅር እኛን ከመውደዱ የተነሣ ኢየሱስ በእኛ ፈንታ ለመሞት ፍቃደኛ ነበር"
"አመንኩኝ" ወይም "እርግጠኛ ሆንኩኝ"
x
1 በክርስቶስ እውነትን እናገራለሁ እንጂ አልዋሽም፣ ህሊናዬ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ሆኖ ይመሰክርልኛል፣ 2 ከፍተኛ ሀዘንና የማያቋርጥ ህመም በልቤ ውስጥ አለ። 3 በሥጋ ዘሮቼ ስለሆኑት ወንድሞቼ ሲባል እኔ እራሴ በተረገምኩና ከክርስቶስ በተለየሁ ብዬ እመኛለሁ። 4 እነርሱ እስራኤላውያን ናቸው። የልጅነት መብት ፥ክብሩ፥ቃል ኪዳኑ፥የህግ ስጦታው፥የአምልኮ ሥርዓቱ፥ የተስፋው ቃል አላቸው። 5 ከሁሉ በላይና ለዘላለም የእግዚአብሔር ብሩክ የሆነው ክርስቶስ በሥጋ የመጣው ከአባቶቻቸው ነው። ለእርሱ ለዘላለም ምስጋና ይሁን። አሜን! 6 ነገር ግን የእግዚአብሔር የተስፋ ቃል ተሻረ ማለት አይደለም። ምክንያቱም በእስራኤል የሚኖር ሁሉ እስራኤላዊ አይደለም። 7 ወይም የአብርሀም ዘር ሁሉ የአብርሀም ልጆች አይደሉም። ነገር ግን «ዘርህ በይስሀቅ ይጠራልሀል» ተባለ። 8 ይህም ማለት የሥጋ ልጆች የሆኑ የእግዚአብሔር ልጆች አይደሉም። የተስፋው ቃል ልጆች ግን ዘሮቹ ሆነው ተቆጠሩ። 9 የተስፋው ቃል «በዚህ ጊዜ ተመልሼ እመጣለሁ ለሳራም ልጅ ይሰጣታል» የሚል ነው። 10 ይህ ብቻ አይደለም፣ ርብቃ ከአባታችን ከይስሀቅ 11 ከጸነሰች በኋላ በምርጫ የሆነው የእግዚአብሔር ዓላማ ከሥራ የተነሳ ሳይሆን ከእርሱ ጥሪ የተነሳ ይጸና ዘንድ ልጆቹ ገና ሳይወለዱና ክፉም ሆነ ደግ ሳያደርጉ 12 «ታላቁ ለታናሹ ይገዛል» ተብሎ ተነግሯት ነበር። 13 ልክ «ያዕቆብን ወደድኩ ኤሳውን ጠላሁ» ተብሎ እንደተጻፈው ማለት ነው። 14 እንግዲህ ምን እንላለን? በእግዚአብሔር ዘንድ የጽድቅ መጓደል አለ ማለት ነው? በጭራሽ አይደለም። 15 ምክንያቱም ለሙሴ «የምምረውን እምራለሁ ለምራራለትም እራራለሁ» ብሎታል። 16 ስለዚህም ምህረት ለፈለገ ወይም ለሮጠ ሳይሆን ምህረትን ከሚያሳይ ከእግዚአብሔር ነው። 17 ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ ስለፈርዖን ሲናገር «ኃይሌን በአንተ ላይ አሳይ ዘንድ ስሜም በምድር ሁሉ ይታወቅ ዘንድ ለዚህ ዋና ዓላማ አስነሳሁህ» ይላል። 18 ስለዚህም ከፈለገ ለአንዱ ምህረትን ይሰጠዋል ሌላውን ደግሞ ግትር ያደርገዋል። 19 «ታዲያ ሁልጊዜ ፈቃዱን የሚያደርግ ከሆነ ለምን ስህተትን ይፈልግብናል?» ትሉኝ ይሆናል። 20 በአንጻሩ ለእግዚአሔር መልስ የምትስጥ አንተ ማን ነህ? የሸክላ ጭቃ ቅርጽ ያወጣለትን ሰው ለምን እንደዚህ አድርገህ ሰራኽኝ ሊለው ይችላልን? ። 21 ሸክላ ሰሪው ከዚያው ጭቃ አንዱን ለየት ባለ ቀን አገልግሎት ላይ የሚውል ዕቃ ሌላውን ደግሞ በየቀኑ አገልግሎት የሚሰጥ ዕቃ አድርጎ ሊሰራው በሸክላ ጭቃው ላይ ሥልጣን የለውም እንዴ? 22 ቁጣውን ሊያሳይና ኃይሉ እንዲታወቅ የሚፈልገው እግዚአብሔር ለጥፋት የተዘጋጁትን የቁጣ ዕቃዎችአብዝቶ ሊታገሳቸው ቢፈልገስ? 23 ይህን ያደረገው አስቀድሞ ለክብር ባዘጋጃቸው የምህረት ዕቃዎቹ ላይ ክብሩን ሊያሳይ ቢሆንስ? 24 ይህንን ለአይሁድ ብቻ ሳይሆን ከአህዛብ ለተጠራን ለእኛም ቢያደርገውስ? 25 በትንቢት ሆሴዕም ላይ «ህዝቤ ያልሆነውን ህዝቤ ብዬ ያልተወደደችውንም የተወደደች ብዬ እጠራለሁ። 26 'ህዝቤ አይደላችሁም በተባሉበት በዚያው ቦታ 'የህያው እግዚአብሔር ልጆች' ይባላሉ» እንደሚለው ነው። 27 ኢሳያስ ስለእስራኤል «የእስራኤል ልጆች ብዛት እንደ ባህር አሸዋ ቢሆን እንኳ የሚድኑት ግን ትሩፋን ናቸው» ብሎ ይጮኸል። 28 ምክንያቱም እግዚአብሔር ቃሉን በምድር ላይ ሙሉ በሙሉ ፈጥኖ ይፈጽማል። 29 ይህም ኢሳያስ ቀደም ሲል «የሠራዊት ጌታ ዘር ባያስቀርልን ኖሮ እንድ ሰዶም በሆንን እንደ ገሞራም በሆነብን ነበር» እንዳለው ነው። 30 እንግዲህ ምን እንላለን? ለጽድቅ ያልሮጡት አህዛብ በእምነት የሆነውን ጽድቅ አገኙ። 31 ለጽድቅ ህግ የተጉት እስራኤል ግን ወደዚያ ሊደርሱ አልቻሉም። 32 ለምን አልደረሱም? ምክንያቱም ጽድቅን የፈለጉት በእምነት ሳይሆን በሥራ ስለሆነ ነው። በማሰናከያው ድንጋይ ተሰናከሉበት። 33 «በጽዮን የማሰናከያ ድንጋይና የዕንቅፋት ዐለት አስቀምጣለሁ በእርሱ የሚያምን አያፍርም» ተብሎ እንደተጻፈው ነው።
ጳውሎስ የእስራል ሕዝብ ይድናሉ ብሎ ምኞቱን ይገልፃል። ከዚያም እነሱ እንዲያምኑ እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ሲያዘጋጃቸው እንደነበር በአጽንኦት ይናገራል።
እነዚህ ሁለት አገላለጾች አንድ ዓይነት ትርጉም የሚሰጡ ናቸው። ጳውሎስ እነዚህን ተጠቅሞ እውነት እንደሚናገር በአጽንኦት ለማስገንዘብ ነው።
"መንፈስ ቅዱስ ሕልናዬን ይቆጣጠራል፤ እኔ የሚለውንም ነገር ያረጋግጣል"
እዚህ ላይ “የማያቋርጥ ሕመም በውስጤ” የሚለው አነጋገር ጳውሎስ የራሱን የጭንቀት ስሜት ለመግለጽ የተጠቀመበት ነው። በሌላ አባባል፥ “እኔ ከፍተኛና ጥልቅ የሐዘን ስሜት እንዳለኝ እነግራችኋለሁ”
እነዚህ ሁለቱ አገላለፆች ከመሠረታቸው አንድ ዓይነት ትርጉም አላቸው። ጳውሎስ የተጠቀመባቸው ስሜቱ ከፍተኛ መሆኑን በደንብ ለመግለጽ ነው።
በሌላ አባባል፥ “እኔ በግሌ ይህን ማድረጌ ከእኔ ቡድን የሆነውን ሕዝብ እስራኤላውያን ወገኖቼን በክርስቶስ ለማመን የሚረዳቸው ቢሆን ኖሮ በእግዚአብሔር ተረግሜ ከክርስቶስ ለዘላለም ለመለየት ፍቃደኛ ነበርኩ።
እንዲህ ማለት ክርስቲያን ወገኖች ለማለት ነው፤ይህም ወንዶችንም ሴቶችንም ይጨምራል።
እነርሱ እንደ እኔ እስራኤላውያን ናቸው። እነርሱ የያዕቆብ ዘር እንዲሆኑ እግዚአብሔር መርጦአቸዋል።
እዚህ ላይ ጳውሎስ “እንደ ልጆቹ” የሚለውን ዘይበኤአዊ አነጋገር የተጠቀመው እስራኤላውያን እንደ እግዚአብሔር ልጆች ይታያሉ የሚለውን ለማመልከት ነው። በሌላ አባባል “ለእነርሱ እግዚአብሔር አባታቸው ነው”
እዚህ ላይ “ክርስቶስ የመጣበት የዘር ግንድ” ሲባል ክርስቶስ ሰብአዊ የደም ዝምድናን በተመለከተ ከእስራኤላውያን ዘር ነው።በሌላ አባባል፥ “ክርስቶስ ሰብአዊ የዘር ግንዱን በተመለከተ የመጣው ከእነርሱ ዘር ነው”
ጳውሎስ በቤተ እስራኤል ውስጥ የተወለዱ ሰዎች ብቻ ከእምነት አንፃር እውነተኛ የእስራኤል ወገን ሊሆኑ ይችላሉ የሚለውን ሐሳብ ጠንከር አድርጎ ለማስረዳት ነው።
“ነገር ግን እግዚአብሔር የሰጠውን የተስፋ ቃል መጠበቅ አላቃተውም” ወይም “እግዚአብሔር የተስፋ ቃሉን ጠብቆአል”
እግዚአብሔር የተስፋ ቃሉን የሰጠው ከእስራኤል (ወይም ያዕቆብ) የዘር ግንድ ለተወለዱ ሁሉ አይደለም ነገር ግን በመንፈስ ከያዕቆብ ለተወለዱት ነው ማለትም በኢየሱስ የታመኑት ናቸው።
እዚህ ላይ “ሰብአዊ ልጆች” የሚለው ዘይበአዊ አነጋገር በሥጋ ከአብርሃም የተወለዱትን ያመለክታል። በሌላ አነጋገር “ከአብርሃም የዘር ግንድ የተወለዱ ሁሉ አይደሉም”
ይህ መንፈሳዊ ልጆቹ የሆኑ ሰዎችን የሚያመለክት ተለዋጭ ዘይቤአዊ አነጋገር ነው፥ በኢየሱስ ያመኑትን።
ይህ የሚያመለክተው እግዚአብሔር ለአብርሃም የሰጠውን የተስፋ ቃል የሚወርሱ ሰዎችን ነው።
“እነዚህ እግዚአብሔር የተስፋ ቃሉን ሲናገር የተጠቀመባቸው ቃላት ናቸው”
በሌላ አነጋገር ‘እግዚአብሔር ለሳራ ወንድ ልጅ ይሰጣል’ ማለት ይቻላል፝። “እኔ ለሳራ ወንድ ልጅ እሰጣለው”
ጳውሎስ ይኸንን በጥያቄ መልክ ሲያቀርብ የአንባቢዎቹን ትኩረት ለማግኘት ነው።
“ይህ ነገር አይቻልም” ወይም “ፈጽሞ አይሆንም” ይህ አገላለጽ ይህ ነገር እንደ ተባለው እንዳይሆን አጥብቆ ይከለክላል። በእናንተ ቋንቋ ሊትጠቀሙበት የሚትችሉት ተመሳሳይ አገላለጽ ይኖር ይሆናል።
ጳውሎስ እዚህ ላይ እግዚአብሔር ለሙሴ በአሁኑ ጊዜ እየሆነ እንዳለ ዓይነት አገላለጽ ተጠቅሞ መናገሩን ይገልጻል።
“ይህ የሚሆነው ሰው ከሚፈልገው ነገር የተነሣ ወይም ሰው ከሚያደርገው ጥረት የተነሣ አይደለም”
ጳውሎስ እዚህ ላይ የእግዚአብሔርን ቸርነት ለማግኘት መልካም ነገር ስለሚያደርግ ሰው ሲናገር ለውድድር የሚሮጥ ሰው ምሳሌን ተጠቅሞ ይገልጸዋል።
እዚህ ላይ ቅዱሳት መጻሕፍት ላይ የተነገረውን እግዚአብሔር ለፈረኦን እንደሚናገር ተደርጎ ተቀምጦአል። በሌላ አባባል፥ “ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚናገረው እግዚአብሔር እንዲህ ይላል”
እግዚአብሔር ራሱን ለማመልከት ነው።
ነጠላ ቁጥር አመልካች
x
ጳውሎስ ለትምህርቱ ተቃዋሚዎች ልክ ለአንድ ሰው እንደሚናገር ዓይነት አድርጎ ይናገራቸዋል።ብዙ ቁጥር አመልካችንም ልትጠቀሙ ትችላላችሁ።
እነዚህ የማሳመኛ ነጥቦች ጳውሎስ ለነገሩ አጽንኦት ለመስጠት የተጠቀመባቸው ናቸው።ሁሉንም ጠበቅ ያሉ ዐረፍተ ነገሮች አድርገን መተርጎም እንችላለን።
እነዚህ ቃላት እግዚአብሔርን የሚያመለክቱ ናቸው።
ጳውሎስ አንድ ሸክላ ሠሪ ከሸክላ የፈለገውን ዕቃ የመሥራት መብት አለው የሚለውን ዘይቤ ተጠቅሞ ፈጣሪ በፍጥረቱ የፈለገውን ነገር ለመሥራት መብት እንዳለው ይገልጻል። ጳውሎስ በጥያቄ መልክ ያቀረበው ነጥቡን ጠንከር አድርጎ ለማስቀመጥ ነው።
አንተ የሚለው ቃል እግዚአብሔርን ያመለክታል።በጥያቄ መልክ ሲናገር ደግሞ ለነገሩ አጽንኦት ለመስጠት ነው።ይኸንን እንደ አንድ ጥብቅ ዐረፍተ ነገር መተረጎምም ትችላላችሁ። በሌላ አባባል፥ “እግዚአብሔር ሆይ፥ እንደዚህ አድርገህ ሊታበጀኝ አይገባም ነበር!”
እነዚህ ቃላት እግዚአብሔርን የሚያመለክቱ ናቸው።
ጳውሎስ ሰዎችን እንደ ዕቃዎች በመውሰድ ይገልጻቸዋል። በሌላ አባባል፥ ቁጣ የሚገባቸው ሰዎች. . .ምህረት የሚገባቸው ሰዎች
ጳውሎስ የእግዚአብሔርን አስገራሚ ሥራዎች ከትልቅ ባለጠግነት ጋር ያነፃፅራል። በሌላ አባባል፥ “ትልቅ ዋጋ ያለው ክብሩ”
እዚህ ላይ “ክብር” የሚያመለክተው በሰማይ ከእግዚአብሔር ጋር የምንኖረው ሕይወት ነው።በሌላ አባባል፥ “ከእርሱ ጋር እንዲኖሩ ቀደም ብሎ ያዘጋጃቸውን”
ጳውሎስ በዚህ ክፍል የእስራኤል ሕዝብን አለማመን አስቀድሞ በነብዮ ሆሴዕ እንደተነገረ ይገልጻል።
እዚህ ላይ “እርሱ” የሚለው እግዚአብሔርን ያመለክታል። በሌላ አባባል፥ “ሆሴዕ በጻፈው መጽሐፍም ላይ እግዚአብሔር እንደተናገረው”
ሆሴዕ ነብይ ነበር።
እኔ በዚያን ጊዜ የእኔ ያልነበረውን ሕዝብ ሕዝቤ እንዲሆን እመርጠዋለሁ
እዚህ ላይ “እሷ” የሚለው የሚያመለክተው የእስራኤልን ሕዝብ የሚትወክለውን ጎመር የሚትባለውን የሆሴዕ ሚስት ነው። በሌላ አባባል፥ “በእኔ የማትወደድ የነበረችውን በእኔ የሚትወደድ እንዲትሆን እመርጣታለሁ” የሕያው እግዚአብሔር ልጆች
“ሕያው” የሚለው ቃል እግዚአብሔር ብቸኛው እውነተኛ አምላክ መሆኑን እንደ ሐሰተኛ ጣኦቶችም አለመሆኑን ያመለክታል።
“ይጣራል”
እዚህ ላይ ጳውሎስ የእስራኤል ሕዝብ ብዛትን ከባሕር አሸዋ ደቃቆች ብዛት ጋር ያነፃፅራል። በሌላ አባባል፣ “ከብዛቱ የተነሣ ለመቁጠር የሚከብድ”
ጳውሎስ “ይድናሉ” የሚለውን ቃል በመንፈሳዊ ትርጉሙ ይጠቀምበታል። እግዚአብሔር አንድን ሰው ካዳነ በኢየሱስ መስቀልና ሞት ባለው እምነት አማካይነት እግዚአብሔር ምህረት አድርጎለት በኃጢአቱ ምክንያት ከሚመጣበት ቅጣት ነፃ አደረገው።
እዚህ ላይ “ፍርድ” የሚለው ቃል ሰዎች ለመቅጣት የወሰነውን ውሳኔ ያመለክታል። በሌላ አባባል፣ “ጌታ በምድር ያለውን ሕዝብ በውሳኔው መሠረት ይቀጣዋል”
ይህ የሚያመለክተው ኢሳያስንና እርሱ ቃል የተናገራቸውን ሰዎች ነው።
x
ጳውሎስ ይህን ጥያቄ የተጠቀመው የአንባቢዎቹን ትኩረት ለማግኘት ሲል ነው። በሌላ አባባል፥ “ስለዚህ እንዲህ ማለት አለብን”
“እንዲህ እንላለን፣ አይሁድ ያልሆኑ ሕዝቦች”
“እግዚአብሔርን ለማስደሰት ጥረት ያላደረጉ”
እዚህ ላይ “በእምነት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በክርስቶስ መታመን ነው። ይህንን በትርጉማችን ገልጦ ማሳየትይቻላል፥ “እነርሱ በክርስቶስ በታመኑ ጊዜ እግዚአብሔር በፊቱ ትክክለኞች አድርጎ ተቀበላቸው”
ይህ ማለት እስራኤላውያን ሕግን ለመጠበቅ በመሞከር እግዚአብሔርን ሊያስደስቱ አልቻሉም። ይኸንን በትርጉማችን ገልጦ ማሳየትይቻላል፥ “ሕግን በመጠበቅ እግዚአብሔርን ማስደሰት አልቻሉም ምክንያቱም ሕግን መጠበቅ አልቻሉም”
ይህ በአጭሩ የተቀመጠ አባባል ነው። ለማለት የተፈለጉትን ቃላት ጨምረን መግለጽ እንችላለን። ጳውሎስ ይህን ጥያቄ የጠየቀው የአንባቢዎቹን ትኩረት ለማግኘት ነው። በሌላ አባባል ስናስቀምጠው፥ “እነርሱ በእግዝአብሔር ሐሳብ መሄድ ያልቻሉት ለምንድነው?”
ይህ የሚያመለክተው ሰዎች እግዚአብሔርን ለማስደሰት ሲሞክሩ የሚያደርጉትን ነገር ነው። ይህንን ሐሳብ በትርጉማችን ገልጦ ማሳየት ይቻላል፥ “እግዚአብሔርን የሚያስደስት ነገር ለመሥራት ጥረት ማድረግ” ወይም “ሕጉን በመጠበቅ”
ኢሳይያስ እንዲህ ብሎ ጽፎአል ማለት ይቻላል። በሌላ አባባል፣ “ነብዩ ኢሳይያስ እንደ ጻፈው”
1 ወንድሞች ሆይ፥ እኔ ስለእነርሱ ለእግዚአብሔር የማቀርበው ልመና እንዲድኑ ነው። 2 በእውቀት የሆነ ባይሆንም ለእግዚአብሔር እንደሚቀኑ እኔ ራሴ ስለእነርሱ እመሰክራለሁ። 3 የእግዚአብሔርን ጽድቅ አያውቁምና የራሳቸውን ጽድቅ ሊመሰርቱ ይጥራሉ፤ለእግዚአብሔርም ጽድቅ ራሳቸውን አያስገዙም። 4 ምክንያቱም ክርስቶስ ለሚያምን ሁሉ ለጽድቅ የሚሆን የህግ ፍጻሜ ነው። 5 ሙሴ ከህግ ስለሚመጣ ጽድቅ ሲናገር «ከህጉ የሆነውን ጽድቅ የሚያደርግ በዚያው ጽድቅ ይኖራል።» ይላልና። 6 በእምነት ስለሚሆን ጽድቅ ግን «በልብህ ማን ወደ ሰማይ ይወጣል አትበል (ይህ ክርስቶስን ማውረድ ነውና) 7 ወይም ወደ ሲዖል ማን ይወርዳል አትበል (ይህ ክርስቶስን ከሙታን መካከል ማውጣት ነውና)።» ይላል። 8 ነገር ግን ቃሉ ምን ይላል? «ቃሉ ለአፍህና ለልብህ ቅርብ ነው።» ይላል። የምንሰብከው የእምነት ቃል ይህ ነው። 9 ስለዚህም ኢየሱስ ጌታ እንደሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሳው በልብህ ብታምን ትድናለህ። 10 ምክንያቱም ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃል በአፉ መስክሮ ደግሞ ይድናል። 11 ምክንያቱም መጽሀፍ እንደሚል «በእርሱ የሚያምን አያፍርም» ። 12 በዚህ ጉዳይ በአይሁድና በግሪክ ልዩነት የለም። ያው አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና ለሚጠሩትም ሁሉ ባለጠጋ ነው። 13 የጌታን ስም የሚጠራም ሁሉ ይድናል። 14 ታዲያ ያላመኑበትን እንዴት ይጠሩታል? ስለእርሱ ሳይሰሙስ እንዴት ያምኑበታል? 15 ያለ ሰባኪስ ከየት ይሰማሉ? «በመልካም ነገር የተሞላ ደስታን የሚሰብኩ እግሮች እንዴት ያማሩ ናቸው» ተብሎ እንድተጻፈ፣ ሳይላኩስ እንዴት ይሰብካሉ? 16 ነገር ግን ኢሳያስ «ጌታ ሆይ መልዕክታችንን ማን አምኗል» እንዳለው ሁሉም ወንጌልን አልተቀበሉም። 17 ስለዚህ እምነት የሚመጣው ከመስማት ሲሆን መሰማት ያለበትም የክርስቶስ ቃል ነው። 18 ነገር ግን «አልሰሙ ይሆንን?» እላለሁ። በሙሉ እርግጠኝነት ሰምተዋል።«ድምጻቸው በምድር ሁሉ ላይ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ደርሷል።» 19 በተጨማሪም «እስራኤል አያውቁምን?» እላለሁ። ሙሴ አስቀድሞ «ህዝብ ባልሆነ በእሱ በቅናት አነሳሳችኋለሁ። በማያስተውልም ህዝብ በቁጣ አናውጣችኋለሁ» ይላል። 20 ደግሞም ኢሳያስ በድፍረት «ላልፈለጉኝ ተገኘሁ ላልጠየቁኝም ተገለጥኩ» ይላል። 21 ስለእስራኤል ግን «ለዚህ የማይታዘዝና ደንዳና ህዝብ ቀኑን ሙሉ እጄን ዘረጋሁ» ይላል።
ጳውሎስ እስራኤል በክርስቶስ እንዲያምን ምኞቱን እየገለጸ ግን ደግሞ አይሁድም ሆነ ሌሎች ሕዝቦች ሁሉም ሊድኑ የሚችሉት በኢየሱስ ባላቸው እምነት ብቻ መሆኑን አጥብቆ ያስገነዝባል።
እዚህ ላይ እንዲህ ማለት ወንዶችንም ሴቶችንም ጨምሮ ክርስቲያን ወገኞች ለማለት ነው።
እዚህ ላይ “ልብ” የሚለው ቃል የሰውን ውስጣዊ ስሜት ለማለት ነው። በሌላ አባባል፣ “ከሁሉም የሚበልጥ ፍላጎቴ”
“እግዚአብሔር አይሁዶችን ያድናቸዋል”
“እኔ ስለ እነርሱ እውነቱን እናገራለሁ”
እዚህ ላይ “የእግዚአብሔር መመዘኛ ሐሳብ” የሚለው እግዚአብሔር ሰዎችን በፊቱ ሐሳቡን የሚያሟሉ የሚያደርግበት መንገድን ያመለክታል።
“ክርስቶስ የእግዚአብሔርን ሕግ ሙሉ በሙሉ ፈጽሞአል።
እዚህ ላይ “የሚያምን” ማለት “የተማመነ” ማለት ነው። በሌላ አባባል፥ “በሱ የተማመኑትን በፊቱ ሐሳቡን የፈጸሙ አድርጎ እንዲቀበላቸው”
ጳውሎስ “የእግዚአብሔርን ሐሳብ መፈጸም” የሚለውን ሕይወት እንዳለውና እንደሚንቀሳቀስ አድርጎ ይናገራል። በሌላ አባባል፥ “ሕግ አንድን ሰው ከእግዚአብሔር ሐሳብ አንጻር እንዴት የተስተካከለ እንደሚያደርግ”
ሕግን በመፈጸም በእግዚአብሔር ፊት የእግዚአብሔርን ሐሳብ የፈጸመ ለመሆን ሕጉን ሙሉ በሙሉ መፈጸም አለበት፤ ይህ ደግሞ የሚቻል አይደለም። በሌላ አባባል፥ “ሕጉን ሙሉ በሙሉ የሚፈጽም ሰው በሕይወት ይኖራል ምክንያቱም ሕጉ የእግዚአብሔርን ሐሳብ የፈጸመ ያደርገዋል”
ይህ አባባል የሚያመለክተው 1) ዘላለማዊ ሕይወት 2) ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት ያለው የሚሞት ሕይወት
እዚህ ላይ “የእግዚአብሔርን ሐሳብ መፈጸም” የሚለው አባባል መናገር እንደሚችል ሰው ተደርጎ የቀረበ ነው።በሌላ አባባል፥ “ነገር ግን ሙሴ እምነት እንዴት አንድን ሰው በእግዚአብሔር ፊት ሐሳቡን የፈጸመ እንደሚያደርገው ሲጽፍ እንዲህ ብሏል።
ሙሴ ለሕዝቡ ሲናገር ለአንድ ሰው እንደሚናገር አድርጎ ያቀርበዋል።እዚህ ላይ “ልብ” የአንድን ሰው አእምሮ ወይም ውስጣዊ ስሜት የሚተካ ነው። በሌላ አባባል፥ “ራሳችሁን እንዲህ አትበሉ”
ሙሴ የሚናገራቸውን ሰዎች ለማስተማር በጥያቄ መልክ አቀረበ። ያለፈው ትምህርቱ ላይ “አትበሉ” ሲል ለዚህኛው ጥያቄ አሉታዊ መልስ እንደሚያስፈልገው ያሳያል። ይህን ጥያቄ በዐረፍተ ነገር መልክ ማስቀመጥ ይቻላል፥ “ወደ ሰማይ ሊወጣ የቻለ ማንም የለም”
“ክርስቶስ ወደ ምድር እንዲመጣ ለማድረግ”
ሙሴ የሚናገራቸውን ሰዎች ለማስተማር በጥያቄ መልክ አቀረበ።ያለፈው ትምህርቱ ላይ “አትበሉ” ሲል ለዚህኛው ጥያቄ አሉታዊ መልስ እንደሚያስፈልገው ያሳያል። ይህን ጥያቄ በዐረፍተ ነገር መልክ ማስቀመጥ ይቻላል፥ “ወደ ጥልቁ በመውረድ የሞቱ ሰዎች መናፍስት ያሉበት ቦታ ሊገባ የቻለ ማንም የለም”
ከሞቱት ሰዎች ሁሉ መካከል ማለት ነው።ይህ አባባል በታችኛው ዓለም የሚገኙትን የሞቱ ሰዎች በአንድ ላይ የሚገልጽ ነው።
ይህ ቃል ስለ አካላዊ ሞት ይናገራል።
ጳውሎስ ቅዱሳት መጻሕፍትን ሕይወትና ድምፅ እንዳለው አድርጎ ይናገራል። እዚህ ላይ ጳውሎስ የተጠቀመውን የቅዱሳት መጻሕፍት ቃል ጸሐፊውን በግልጽ መጥቀስ ትችላላችሁ። በሌላ አነጋገር፥ “ኢሳያስ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደጻፈው”
ይህ “የማያምን ሁሉ ያፍራል” ከማለት ጋር ተመጣጣኝ ትርጉም አለው። እዚህ ላይ በአሉታዊ መልኩ የተቀመጠው ለነገሩ አጽንኦት ለመስጠት ነው። በሌላ አባባል፥ “እግዚአብሔር በእርሱ የሚያምኑትን ሁሉ ያከብራል”
የጳውሎስ ሐሳብ እግዚአብሔር ለሁሉም ሕዝቦች እኩል ያስብላቸዋል።ይህንን ሐሳብ በትርጉማችን ገልጠን ማሳየት እንችላለን። በሌላ አባባል፥ “በዚህ መልኩ እግዚአብሔር ለአይሁድም አይሁድ ላልሆኑትም እኩል ያስብላቸዋል”
እዚህ ላይ “ሁሉን ነገር አለው” ተብሎ የተተረጎመው አባባል እግዚአብሔር በብዙ በረከት ይባርካል ለማለት ነው።ይህን ሐሳብ በትርጉማችን ገልጠን ማሳየት እንችላለን። በሌላ አባባል፥ “እርሱ በእርሱ የሚተማመኑትን በብዙ በረከት ይባርካቸዋል”
እዚህ ላይ “ስም” የሚለው ቃል ኢየሱስን የሚተካ ነው። በሌላ አባባል፥ “ጌታ በእርሱ የሚተማመኑትን ሁሉ ያድናል”
ጳውሎስ ይኸንን ጥያቄ የተጠቀመው የክርስቶስን የምሥራች ቃል ወዳልሰሙት ሰዎች የማድረስን አስፈላጊነት አጥብቆ ለማስገንዘብ ነው። “እነርሱ” የሚለው ቃል ገና የእግዚአብሔር ሕዝብ ያልሆኑትን ያመለክታል።በሌላ አባባል፥ “በእግዚአብሔር የማያምኑት የእርሱን ስም ሊጠሩ አይችሉም”
ጳውሎስ ለተመሳሳይ ምክንያት ሌላ ጥያቄ ይጠቀማል። በሌላ አባባል፥ “የእርሱን መልዕክት ያልሰሙ ከሆነ በእርሱ ሊያምኑ አይችሉም”
ይህ ማለት ያ ሰው ያለው እውነት መሆኑን መመስከር ማለት ነው።
ጳውሎስ ለተመሳሳይ ምክንያት ሌላ ጥያቄ ይጠቀማል።በሌላ አባባል፥ “ሰው ካልነገራቸው የእርሱን መልዕክት ሊሰሙ አይችሉም”
ጳውሎስ ለተመሳሳይ ምክንያት ሌላ ጥያቄ ይጠቀማል። “እነርሱ” የሚለው ቃል የእግዚአብሔር የሆኑትን ያመለክታል። በሌላ አባባል፥ “የሆነ ሰው ካልላካቸው መልዕክቱን ለሌሎች መንገር አይችሉም”
ጳውሎስ “እግር” የሚለውን አባባል የተጠቀመው መልዕክቱ ወዳልደረሳቸው ለማድረስ የሚጓዙትን ሰዎች ለማመልከት ነው። በሌላ አባባል። “መልዕክተኞች መጥተው የምሥራቹን ዜና ሲነግሩን በጣም አስገራሚ ነው”
እዚህ ላይ “እነርሱ” የሚለው ሐሳብ አይሁዶችን ያመለክታል። “ነገ ግን ያዳመጡት ሁሉም አይሁዶች አይደሉም”
ጳውሎስ ይህንን በጥያቄ መልክ ያቀረበው በቅዱሳት መጻሕፍት ኢሳያስ ስለ አይሁዶች በኢየሱስ አለማመን የተነበየውን አጽንኦት ሰጥቶ ለማስገንዘብ ነው።
እዚህ ላይ “እኛ” የሚያመለክተው እግዚአብሔር እና ኢሳይያስን ነው።
እዚህ ላይ “እምነት” የሚያመለክተው “በክርስቶስ ማመንን ነው።
መስማት ስለ ክርስቶስ የሚነገረውን መልዕክት በማዳመጥ ነው።
ጳውሎስ በጥያቄ መልክ ያቀረበው ለነገሩ አጽንኦት በመስጠት ነው።ጥያቄውን ወደ ዐረፍተ ነገር መልሳችሁ መተርጎም ትችላላችሁ። በሌላ አባባል፥ “ነገር ግን እኔ እላለሁኝ፥ አይሁዶች በእርግጥ ስለ ክርስቶስ የሚነገረውን መልዕክት ሰምተዋል።
ሁለቱም ዐረፍተ ነገሮች መሠረታዊ ትርጉማቸው አንድ ነው፤ ጳውሎስ ሁለቱን የተጠቀመው ነገሩን አጥብቆ ለመንገር ነው። “እነርሱ” የሚለው ሐሳብ የሚያመለክተው ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ እና ኮከቦችን ነው።እዚህ ላይ እነዚህ ስለ እግዚአብሔር ለሕዝቦች እንደሚናገሩ መልዕክተኞች ሰዎች ተደርገው ተገልጸዋል።ይህም የሚያመለክተው የነዚህ መኖር ራሱ ምን ያህል የእግዚአብሔርን ኃይልና ክብር የሚያሳይ እንደሆነ ነው።እዚህ ላይ ጳውሎስ ከቅዱሳት መጻሕፍት እየጠቀሰ መሆኑን ገልጣችሁ ማሳየት ትችላላችሁ። በሌላ አባባል፥ “ቅዱሳት መጻሕፍት ላይ እንደተጻፈው ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ እና ኮከቦች የእግዚአብሔር ኃይልና ክብር ማረጋገጫ ናቸው፤በዓለም ላይ ያሉት ሰዎች ሁሉ እነርሱን አይተው ስለ እግዚአብሔር እውነቱን ያውቃሉ”
ጳውሎስ በጥያቄ መልክ ያቀረበው ለነገሩ አጽንኦት ለመስጠት ነው፝። “እስራኤል” የሚለው ቃል በእስራል አገር የኖሩ ሕዝቦችን ለማመልከት ነው። በሌላ አባባል። “አሁንም እነግራቸዋለሁ፥ የእስራኤል ሕዝብ መልዕክቱን አውቀዋል”
ይህ ማለት ሙሴ እግዚአብሔር ያለውን ነው የተናገረው። “እኔ” የሚለው የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ነው፤ “እናንተ” የሚለው ሐሳብ ደግሞ እስራኤላውያንን ነው። በሌላ አባባል፥ “ሙሴ አስቀድሞ እንዲህ አለ፥ “እግዚአብሔር ያስቆጣችኋል. . .እግዚአብሔር እንዲትበሳጩ ያደርጋል”
“እናንተ እንደ ሕዝብ በማትቆጥሯቸው” ወይም “ከየትኛውም ሕዝብ በማይመደቡ ሰዎች”
እዚህ ላይ “ማስተዋል የሌለው” ማለት እግዚአብሔርን የማያውቅ ሕዝብ ማለት ነው። በሌላ አባባል፥ “እኔን ወይም ትዕዛዞቼን የማያውቁ ሰዎች በሚኖሩበት ሕዝብ”
“እንድትበሳጩ አደርጋለሁ” ወይም “እንዲትበሳጩ የሚያደርግ ነገር አደርጋለሁ”
ይህ የእስራኤልን ሕዝብ ያመለክታል።
እዚህ ላይ “እኔ” እና “የእኔ” የሚሉ ቃላት የሚያመለክቱት እግዚአብሔርን ነው።
ይህ ማለት ነብዩ ኢሳይያስ የጻፈው እግዚአብሔር የተናገረውን ነው።
ነቢያት ብዙውን ጊዜ ለወደ ፊት ሊከሰቱ ያሉትን ነገሮች እንደተፈጸመ አድርገው ይናገራሉ። ይህ አጥብቆ የሚያስረዳው ትንቢቱ በእርግጠኝነት እንደሚፈጸም ነው። በሌላ አባባል፥ “የእግዚአብሔር ያልሆኑ ሕዝቦች ምንም እንኳ ባይፈልጉኝ ያገኙኛል”
“ራሴን አሳወቅኩ”
“እርሱ” የሚለው የሚያመለክተው በኢሳይያስ በኩል የተናገረውን እግዚአብሔርን ነው።
ይህ ሐረግ አጥብቆ የሚገልጸው የእግዚአብሔርን ተከታታይ ጥረት ነው። “በተከታታይ”
“እናንተን ለመቀበልና ለመርዳት ሞከርኩ ነገር ግን እርዳታዬን እምቢ ብላችሁ በአለመታዘዝ ሕይወት ቀጠላችሁ።
1 ታዲያ እግዚአብሄር ህዝቡን ጣላቸውን? ፥በጭራሽ። ምክንያቱም እኔ ራሴ ከቢንያም ወገን የሆንኩ የአብርሀም ዘር እስራኤላዊ ነኝ። 2 እግዚአብሔር አስቀድሞ ያወቃቸውን ህዝቡን አልጣላቸውም። ኤልያስ እስራኤልን በመቃወም ከእግዚአብሔር ጋር እንዴት እንደተከራከረ መጽሀፍ የሚለውን አታውቁምን? 3 «ጌታ ሆይ ነቢያትህን ገድለዋል፣ መሰዊያዎችህንም አፍርሰዋል፣ እኔም ብቻዬን ቀርቻለሁ ሊገድሉኝም እየፈለጉኝ ነው።» 4 ነገር ግን እግዚአብሔር ምን ብሎ መለሰለት? «ለበዓል ያልሰገዱ ሰባት ሺ ሰዎችን ለራሴ ጠብቄ አቆይቻለሁ።» 5 በዚህም በአሁኑ ዘመንም ከጸጋ ምርጫ የተነሳ ትሩፋን አሉ። 6 ነገር ግን በጸጋ ከሆነ ከእንግዲህ በሥራ አይደለም።አለዚያ ጸጋ ከእንግዲህ ጸጋ መሆኑ ቀርቷል። 7 እንግዲህ ምን ይሁን፣ እስራኤል ይፈልገው የነበረውን ነገር አላገኘም ፥ የተመረጡት ግን አግኝተውታል፥ የቀሩት ግን ደንዳኖች ሆነዋል። 8 ይህም ልክ «እያዩ እንዳያዩ እየሰሙ እንዳይሰሙ እስከ አሁን እግዚአብሔር ያለማስተዋልን መንፈስ ሰጣቸው» ተብሎ እንደተጻፈው ነው። 9 ዳዊትም «ገበታቸው መረብ፥ወጥመድ፥የእንቅፋት ድንጋይና የበቀል ይሁንባቸው» ይላል። 10 እንዳያዩ አይናቸው ይጨልም፥ ሁልጊዜ ጀርባቸው እንደጎበጠ ይቅር።» ይላል። 11 «እስኪወድቁ ድረስ ተሰናከሉ» እላለሁን? ፈጽሞ አይሁን። በቅናት ሊያነሳሳቸው በእነርሱ ውድቀት ለአህዛብ ድነት ሆነ። 12 እንግዲህ ውድቀታቸው ለዓለም ሙላት ከሆነ ጉድለታችው ለአህዛብም ሙላት ከሆነ ሙላታቸው እንዴት ታላቅ ይሆን? 13 አሁን ለእናንተ ለአህዛብ እናገራለሁ። የአህዛብ ሀዋሪያ እንደመሆኔ በአገልግሎቴ እመካለሁ። 14 ምናልባት የገዛ ሥጋዬ የሆኑትን አስቀናና አንዳንዶቹን እናድን ይሆናል። 15 የእነኚያ መጣል ለዓለም የመታረቅ ምክንያት ከሆነ ተቀባይነት ማግኘታቸው ከሞት ወደ ህይወት ማምለጥ ካልሆን ምን ሊሆን ይችላል? 16 በኩሩ ቅዱስ ከሆነ ሊጡም ቅዱስ ነው። ሥሩ ቅዱስ ከሆነ ቅርንጫፉ ቅዱስ ነው። 17 ነገር ግን አንዳንዶቹ ቅርንጫፎች በመሰበራቸው ምክንያት አንተ የበረሀ ወይራ ዛፍ ቅርንጫፍ ባልወደቁት ቅርንጫፎች መካከል ብትጣበቅና የወይራ ዛፉን ሥር ብልጽግና ተካፋይ ብትሆን 18 በቅርንጫፎቹ ላይ አትኩራራ። ብትኩራራ ግን ሥሩ አንተን ተሸከምህ እንጂ አንተ ሥሩን አልተሸከመከውም። 19 «ቅርንጫፎቹ ስለተሰበሩ እኔ ተተካሁ» ትላለህ። 20 እውነት ነው ባለማመናቸው ምክንያት እነርሱ ተቆርጠው ወድቀዋል አንተ ደግሞ በእምነት ቆመሀል። ፍራ እንጂ ራስህ ከፍ አድርገህ አታስብ። 21 እግዚአብሔር ለመጀመሪያዎቹ ቅርንጫፎች ካልራራ ለአንተም አይራራልህም። 22 እንግዲህ የእግዚአብሔርን የምህረት ሥራና ጭካኔ አስተውል። በአንድ በኩል ጭካኔው በወደቁት በአይሁድ ላይ መጣ፥በሌላ በኩል ደግሞ ጸንታችሁ ከቆያችሁ ምህረቱ ወደ እናንተ መጥቷል። አለበለዚያ ግን እናንተም ተቆርጣችሁ ትጣላላችሁ። 23 ደግሞም እነርሱ ባለማመናቸው ካልጸኑ እንደገና በዛፉ ላይ ሊተከሉ ይችላሉ። እግዚአብሔር እንደገና በዛፉ ላይ ሊተክላቸው ይችላልና። 24 እናንተ መነሻችሁ የበረሀ የወይራ ዛፍ የሆነና ተቆርጣችሁ የነበራችሁ ቅርንጫፎች ከተፈጥሮ ህግ ውጪ በመልካሙ የወይራ ዛፍ ላይ እንደገና ከተተከላችሁ የመጀመሪያዎቹ ቅርንጫፎች እነኝህ አይሁድ ወደገዛ ዛፋቸው እንዴት እንደግና አይጣበቁም? 25 ወንድሞች ሆይ በራሳችሁ አስተሳሰብ ጥበበኞች የሆናችሁ እንዳይመስላችሁ ስለዚህ ምስጢር እንግዳ እንድትሆኑ አልፈልግም፡ የአህዛብ ሙላት እስኪፈጸም ድረስ ከፊል ድንዛዜ በእስራኤል ላይ ወድቋል። 26 ስለዚህም እስራኤል በሙሉ እንደተጻፈው ይድናሉ። «ከጽዮን ነጻ አውጪ ይነሳል ከያዕቆብም የማይገባ አካሄድን ያስወግዳል። 27 ኃጢአታቸውን በማስወግድላቸው ጊዜ ከእነርሱ ጋር የምገባው ኪዳን ይህ ነው።» 28 በአንድ በኩል ወንጌልን በተመለከተ ስለእናንተ የተጠሉ ናቸው፣ በሌላ በኩል ደግሞ በእግዚአብሔር ምርጫ ምክንያት ስለአባቶቻቸው የተወደዱ ናቸው። 29 ምክንያቱም የእግዚአብሔር ስጦታና ጥሪ አይለወጥም። 30 እናንተ ቀድሞ ለእግዚአብሔር የማትታዘዙ የነበራችሁ አሁን ግን በእነርሱ አለመታዘዝ ምክንያት ምህረትን አግኝታችኋል። 31 ልክ እንደዚያው ዘንድ እነዚህ አይሁድ አሁን የማይታዘዙ ሆነዋል። በውጤቱም ለእናንት በተሰጠው ምህረት እነርሱ ደግሞ እንዲቀበሉ ነበር። 32 ምህረቱን ለሁሉ ያሳይ ዘንድ እግዚአብሔር ሁሉን ባለመታዘዝ ዘግቶታልና። 33 ኦ የእግዚአብሔር ጥበብና እውቀት ባለጠግነት ምን ያህል ጥልቅ ነው! ፍርዱ እንዴት የማይመረመር መንገዱም እንዴት ከመታወቅ ያለፈ ነው! 34 «የጌታን ልብ የሚያውቅ ማነው? አማካሪውስ የሆነ ማነው? 35 ወይስ መልሶ ይከፍለው ዘንድ ለእግዚአብሔር ያበደረ ማነው?» 36 ሁሉም ነገር ከእርሱ በእርሱና ለእርሱ ነው። ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን። አሜን።
እስራኤል እንደ ሕዝብ እግዚአብሔርን ቢተዉትም ድነት ያለ ሥራ በጸጋ እንደሆነ ይረዱ ዘንድ እግዚአብሔር ይፈልግባቸዋል።
“እንግዲህ እኔ ጳውሎስ እላለሁ”
‘የአይሁድ ሕዝብ ልባቸው በመደንደኑ እግዚአብሔር አህዛብን በሕዝቡ ውስጥ አካተታቸው’ በማለት የሚበሳጩ የሌሎች አይሁዶችን ጥያቄ ለመመለስ እንዲያስችለው ጳውሎስ ይህንን ጥያቄ ይጠይቃል። (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
“ይህ ሊሆን የማይችል ነው!” ወይም “ያለጥርጥር አልጣላቸውም!” ይህ አገላለጽ ሊሆን እንደማይችል አጥብቆ ይቃወማል። በአንተ ቋንቋ እዚህ ጋ መጠቀም የምትችልበት ተመሳሳይ አገላለጽ ይኖርህ ይሆናል። ይህንን በሮሜ 9፡14 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት።
ይህ የሚያመለክተው እግዚአብሔር በ12 ጎሳ ከከፋፈላቸው ከእስራኤል ሕዝብ አንዱ ከሆነው ከብንያም ጎሳ የተገኙትን ነው።
“ከረጅም ጊዜ በፊት ያወቃቸውን”
ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “ኤልያስ እስራኤልን በእግዚአብሔር ፊት በከሰሳቸው ጊዜ ምን ተብሎ በመጽሐፍ እንደ ተጻፈ በእርግጥ ታውቃላችሁ” (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
ጳውሎስ አንባቢን ወደ ቀጣይ ማብራሪያው ለማምጣት ይህንን ጥያቄ ይጠይቃል። አ.ት፡ “እግዚአብሔር የመለሰለት እንዴት ነበር?” (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
ጳውሎስ የእግዚአብሔር ምህረት እንዴት እንደሚሠራ ማብራራቱን ይቀጣላል። አ.ት “የእግዚአብሔር ምህረት በጸጋ የሚሠራ ከሆነ ግን”
“ምን ብለን እንደምድም?” ጳውሎስ አንባቢውን ወደ ቀጣዩ ማብራሪያ ለመውሰድ ይህንን ጥያቄ ይጠይቃል። ይህንን እንደ መግለጫ አድርገህ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “ማስታወስ የሚኖርብን ይህንን ነው” (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
ይህ ሕዝቡ በመንፈስ የመደንዘዙን ሐቅ የሚያሳይ ዘይቤአዊ አነጋገር ነው። መንፈሳዊ እውነትን ለመስማት ወይም ለመቀበል አይችሉም። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ፣ ይህ ማለት እንደ “የጥበብ መንፈስ” ሁሉ “የአንዳች ዓይነት ጠባይ” ማለት ነው።
አንድ ሰው በዐይኑ የማየቱ አስተሳሰብ ዕውቀትን ከማግኘት ጋር እኩል እንደሆነ ተቆጥሯል።
በጆሮ የመስማት አስተሳሰብ ከመታዘዝ ጋር እኩል እንደሆነ ተቆጥሯል።
እዚህ ጋ “ማዕድ” ግብዣን የሚወክል ፈሊጣዊ አነጋገር ሲሆን “መረብ” እና “ወጥመድ” ቅጣትን የሚወክሉ ዘይቤአዊ አነጋገሮች ናቸው። ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “እግዚአብሔር ሆይ፣ እባክህን ግብዣዎቻቸውን እነርሱን እንደሚይዝ ወጥመድ አድርግ” (ፈሊጣዊ አነጋገር፣ ዘይቤአዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“እንቅፋት” አንድ ሰው ተደናቅፎ እንዲወድቅ የሚያስደርገው ማንኛውም ነገር ነው። እዚህ ጋ፣ አንድ ሰው ኃጢአትን እንዲያደርግ የሚፈታተነውን አንድ ነገር ይወክላል። አ.ት፡ “ኃጢአት እንዲሠሩ የሚፈታተናቸው ነገር” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“እንድትበቀላቸው የሚያስደርግህ ነገር”
እዚህ ጋ፣ “ወገባቸውን አጉብጥ” ባሮች በጀርባቸው ከባድ ሸክሞችን እንዲሸከሙ የሚገደዱበት ፈሊጣዊ አነጋገር ነው። እንዲሰቃዩ የማድረግ ዘይቤአዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “ከባድ ሸክም እንደሚሸከሙ ሰዎች አሰቃያቸው” (ፈሊጣዊ አነጋገር እና ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
እስራኤል እንደ ሕዝብ እግዚአብሔርን እንደተዉት ተመሳሳይ ስሕተት ከመፈጸም እንዲጠነቀቁ ጳውሎስ አሕዛብን ያሳስባቸዋል።
ጳውሎስ አጽንዖት ለመጨመር ሲል ይህንን ጥያቄ ይጠይቃል። አ.ት፡ “ኃጢአትን ስለ ሠሩ እግዚአብሔር ለዘላለም ትቷቸዋል? (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
“ይህ ሊሆን አይችልም!” ወይም “ያለጥርጥር አይደለም!” ይህ አገላለጽ ነገሩ እንዲህ እንደማይሆን አጥብቆ ይቃወማል። በአንተ ቋንቋ እዚህ ጋ ልትጠቀምበት የምትችለው ተመሳሳይ አገላለጽ ይኖርህ ይሆናል። ይህንን በሮሜ 9፡14 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት።
x
ይህንን ሐረግ በሮሜ 10፡19 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት።
ይህ የሚያመለክተው “እንደ እኔው አይሁዳዊ የሆኑ” የሚለውን ነው።
የሚያምኑትን እነዚያን እግዚአብሔር ያድናቸዋል። አ.ት፡ “ምናልባት አንዳንዶቹ ያምናሉ፣ እግዚአብሔርም ያድናቸዋል”
“እግዚአብሔር እነርሱን ትቷቸው ከሆነ የቀረውን ዓለም ከራሱ ጋር ያስታርቃል”
“የእነርሱ” የሚለው ተውላጸ ስም የማያምኑትን አይሁድ ያመለክታል።
እዚህ ጋ፣ “ዓለም” በዓለም የሚኖሩትን ሰዎች የሚያመለክት ፈሊጣዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “በዓለም ያሉ ሰዎች” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
እግዚአብሔር አይሁዶችን መቀበሉ አስደናቂ ነገር መሆኑን አጽንዖት ለመስጠት ጳውሎስ ይህንን ጥያቄ ይጠይቃል። አንተ በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “እግዚአብሔር ሲቀበላቸው ምን ይሆን ይሆን? ነገሩ ልክ ከሙታን መካከል የተነሡ ያህል ይሆናል!” ወይም “እግዚአብሔር እነርሱን በሚቀበልበት ጊዜ ከሞቱ በኋላ እንደገና በሕይወት የኖሩ ያህል ይሆናል!” (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ እና አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ይህ ቃል የሚናገረው በመቃብር ስላሉ፣ የሞቱ ሰዎች ሁሉ ነው።
ጳውሎስ የመጀመሪያው ሰብል ወይም “በኩራት” ሆነው እንደሚታጨዱ የሚናገረው የእስራኤላውያን አባቶች ስለሆኑት ስለ አብርሃም፣ ይስሐቅና ያዕቆብ ነው። ደግሞም ከእነዚያ ሰዎች ስለተወለዱት እስራኤላውያን ሲናገር ከሰብሉ እንደተዘጋጀ “ቡኮ” አድርጎ ይናገራል። አ.ት፡ “አብርሃም ለእግዚአብሔር ከቀረበው የመጀመሪያ ሆኖ ከተቆጠረ፣ የተከተሉት አባቶቻችን ሁሉ ደግሞ እንደ እግዚአብሔር ንብረት መቆጠር አለባቸው” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ተውላጸ ስም የሆነው “አንተ” እና “የበረሃ ወይራ ቅርንጫፍ” የሚለው ሐረግ የሚያመለክተው በኢየሱስ ድነትን የተቀበሉትን አሕዛብ ነው።
እዚህ ጋ፣ ጳውሎስ “የተሰበሩ ቅርንጫፎች” በማለት የሚያመለክተው ኢየሱስን የተቃወሙትን አይሁዶች ነው። ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “አንዱ ጥቂት ቅርንጫፎችን ቢሰብራቸው” (ዘይቤአዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ ጳውሎስ “እንደተጣበቁ ቅርንጫፎች” አድርጎ የሚናገረው ስለ አሕዛብ ክርስቲያኖች ነው። ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “በቀሩት ቅርንጫፎች መካከል እግዚአብሔር በዛፉ ላይ አጣብቆሃል” (ዘይቤአዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ፣ “የበለጸገው ሥር” የእግዚአብሔርን ተስፋ የሚያመለክት ዘይቤአዊ አነጋገር ነው። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ፣ “ቅርንጫፎቹ” የእስራኤልን ሕዝብ የሚወክል ዘይቤአዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “እግዚአብሔር ከጣላቸው የአይሁድ ሕዝብ አንተ እንደምትሻል አትናገር” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ጳውሎስ አሕዛብ አማኞች ቅርንጫፎች መሆናቸውን እንደገና ያመለክታል። እግዚአብሔር ለአይሁድ በገባው የኪዳን ተስፋ ምክንያት ብቻ ያድናቸዋል። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ፣ “ቅርንጫፎች” የሚያመለክተው ኢየሱስን የተቃወሙትንና አሁን እግዚአብሔር የተዋቸውን አይሁዶችን ነው። ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “እግዚአብሔር ቅርንጫፎቹን ሰበራቸው” (ዘይቤአዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ጳውሎስ ይህንን ሐረግ የሚጠቀመው እግዚአብሔር የተቀበላቸውን አሕዛብ አማኞች ለማመልከት ነው። ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “እኔን አስገብቶ ሊያጣብቀኝ” (ዘይቤአዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ተውላጸ ስም የሆኑት “የእነርሱ” እና “እነርሱ” የሚያመለክቱት ያላመኑትን አይሁዶች ነው።
ጳውሎስ የሚናገረው ማንም ሊያንቀሳቅሳቸው እስከማይቻለው ድረስ በታማኝነት ጸንተው ስለቆሙት አሕዛብ አማኞች ነው። አ.ት፡ “ነገር ግን በእምነታችሁ ምክንያት ቆማችኋል” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ፣ “በተፈጥሮአቸው ቅርንጫፍ የሆኑት” የሚያመለክተው ኢየሱስን የተቃወሙትን አይሁዶች ነው። አ.ት፡ “እግዚአብሔር ከሥር ጀምሮ ላደገው፣ የተፈጥሮ ዛፍ ቅርንጫፍ ለሆነው፣ ላላመኑት አይሁድ ካልራራላቸው፣ እንግዲህ ባታምን ለአንተም እንደማይራራልህ ዕወቅ። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ምንም እንኳን እግዚአብሔር በታላቅ ደግነት ቢያደርግላቸውም ሊፈርድባቸውና ሊቀጣቸው እንደማያመነታ ጳውሎስ አሕዛብ አማኞችን ያስታውሳቸዋል።
የነገር ስም የሆኑትን “ጭካኔ” እና “ደግነት” ለማስቀረት ይህንን እንደገና መጻፍ ይቻላል። አ.ት፡ “እግዚአብሔር በወደቁት አይሁድ ላይ ክፉን አድርጎባቸዋል … በአንተ ላይ ግን በደግነት ያደርጋል” (የነገር ስም የሚለውን ተመልከት)
የማይገባውን ማድረግ መውደቅ እንደሆነ ተነግሯል። አ.ት፡ “የማይገባውን ያደረጉ አይሁድ” ወይም “በክርስቶስ ለመታመን ፈቃደኛ ያልሆኑት አይሁድ” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
የነገር ስም የሆነውን “ደግነት” ለማስቀረት ይህ እንደገና ሊጻፍ ይችላል። አ.ት፡ “ትክክል የሆነውን ማድረግህን ብትቀጥል እርሱም ለአንተ ደግ መሆኑን ይቀጥላል” (የነገር ስም የሚለውን ተመልከት)
እግዚአብሔር ከፈለገ “ሊቆርጠው” ስለሚችለው ቅርንጫፍ ለመናገር ጳውሎስ እንደገና በዘይቤአዊ አነጋገር ይጠቀማል። እዚህ ጋ “መቆረጥ” አንድን ሰው የመጣል ዘይቤአዊ አነጋገር ነው። ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “ካልሆነ እግዚአብሔር አንተን ይቆርጥሃል” ወይም “ካልሆነ እግዚአብሔር አንተን ይጥልሃል” (ዘይቤአዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“ባለማመናቸው ካልቀጠሉ” የሚለው ሐረግ ድርብ አሉታ ነው። ይህንን በአዎንታ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “አይሁድ በክርስቶስ ማመን ከጀመሩ” (ድርብ አሉታ የሚለውን ተመልከት)
አይሁድ በኢየሱስ ማመን ከጀመሩ እንደ ቅርንጫፎች ተመልሰው በዛፉ ላይ ሊጣበቁ እንደሚችሉ ጳውሎስ ይናገራል። ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “እግዚአብሔር መልሶ አስገብቶ ያጣብቃቸዋል” (ዘይቤአዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ከአንድ ተክል ላይ ሕያው የሆነውን ቅርንጫፍ በሌላው ተክል ላይ በማስገባት አዲሱ ቅርንጫፍ በዚያ ተክል ላይ ማደጉን እንዲቀጥል ማድረግ የተለመደ ሂደት ነው።
ጳውሎስ የአሕዛብ አማኞችና አይሁድ የዛፍ ቅርንጫፎች እንደሆኑ አድርጎ መናገሩን ይቀጥላል። ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “እግዚአብሔር በተፈጥሮህ የበረሃ ወይራ ዛፍ የሆንከውን ቆርጦ ለተፈጥሮ ተቃራኒ በሆነው መልካም የወይራ ዛፍ ላይ ካጣበቀህ የተፈጥሮ ቅርንጫፎች የሆኑትን እነዚህን አይሁዶች በገዛ የወይራ ዛፋቸው ላይ እንዴት አብዝቶ አያጣብቃቸውም?” (ዘይቤአዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ጳውሎስ፣ አይሁድና አሕዛብ ቅርንጫፎች እንደሆኑ በመቁጠር ይናገራል። “የተፈጥሮ ቅርንጫፎች” የሚወክሉት አይሁዶችን ሲሆን “የተጣበቁት ቅርንጫፎች” የሚወክሉት ደግሞ አሕዛብ አማኞችን ነው። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“እነርሱ” ወይም “እነርሱን” የሚሉት አገባቦች በሙሉ የሚያመለክቱት አይሁዶችን ነው።
እዚህ ጋ ጳውሎስ ድርብ አሉታን ይጠቀማል። ይህንን በአዎንታ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “እንድትገነዘቡ በጣም እፈልጋለሁ” (ድርብ አሉታ የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ “ወንድሞች” ማለት ወንዶችንና ሴቶችን ጨምሮ እንደ እርሱ ክርስቲያን የሆኑትን ነው።
ተውላጸ ስም የሆነው “እኔ” የሚያመለክተው ጳውሎስን ነው።
ተውላጸ ስም የሆኑት “አንተ” እና “የአንተ” የሚያመለክቱት አሕዛብ አማኞችን ነው።
አሕዛብ አማኞች ካላመኑት አይሁዶች ይልቅ ጥበበኞች እንደሆኑ እንዲያስቡ ጳውሎስ አይፈልግም። አ.ት፡ “ከእነርሱ ይልቅ ጥበበኞች እንደሆናችሁ እንዳታስቡ”
ጳውሎስ ስለ “ድንዳኔ” ወይም እልኸኝነት በሰውነት ውስጥ እንዳለ ጠጣር ብልት አድርጎ ይናገራል። አንዳንድ አይሁዶች በኢየሱስ አማካይነት ድነትን ለመቀበል እምቢ ብለዋል። አ.ት፡ “ብዙ እስራኤላውያን እልኸኞች ሆነው ቀጥለዋል” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“እስኪመጣ ድረስ” የሚለው ቃል እግዚአብሔር አሕዛብን ወደ ቤተክርስቲያን ማምጣቱን ከጨረሰ በኋላ ጥቂት አይሁዶች እንደሚያምኑ ያመለክታል።
ጳውሎስ ለእግዚአብሔር ክብር ከእስራኤል ነጻ አውጪ እንደሚመጣ ይናገራል።
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊተረጎም ይችላል። አ.ት፡ “እንዲሁም እግዚአብሔር እስራኤልን ሁሉ ያድናል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “ልክ ቅዱሳት መጻሕፍት እንደ ዘገቡት” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ “ጽዮን” እግዚአብሔር ለሚኖርበት ስፍራ በፈሊጣዊ አነጋገር ጥቅም ላይ ውሏል። አ.ት፡ “እግዚአብሔር በአይሁዶች መካከል ከሚገኝበት” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“ሕዝቡን ወደ አስተማማኝ ስፍራ የሚያመጣቸው”
ጳውሎስ ኃጢአተኝነትን አንድ ሰው እንደሚያስወግደው ቁስ፣ ምናልባትም እንደሚገፈፍ ልብስ አድርጎ ይናገራል። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ “ያዕቆብ” በፈሊጣዊ አነጋገር እስራኤልን ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል። አ.ት፡ “ከእስራኤል ሕዝብ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ ጳውሎስ ኃጢአትን አንድ ሰው ሊያስወግደው እንደሚችለው ቁስ አድርጎ ይናገርለታል። አ.ት፡ “የኃጢአታቸውን ሸክም አስወግዳለሁ” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ጳውሎስ የምሥራቹን የሚጠቅስበትን ምክንያት ግልጽ ማድረግ ትችላለህ። አ.ት፡ “አይሁዶች የምሥራቹን ቃል ስለ ተቃወሙ”
የማን ጠላቶች እንደሆኑና ይህም እንዴት በአሕዛብ ምክንያት ሊሆን እንደቻለ ግልጽ ልታደርገው ትችላለህ። አ.ት፡ “ስለ እናንተ የእግዚአብሔር ጠላቶች ናቸው” ወይም “እናንተ ደግሞ የምሥራቹን እንድትሰሙ እግዚአብሔር እንደ ጠላት ቆጠራቸው”
ጳውሎስ ስለ ምርጫ የሚያነሣበትን ምክንያት ግልጽ ማድረግ ትችላለህ። አ.ት፡ “እግዚአብሔር አይሁዶችን መርጦአቸዋልና” ወይም “ምክንያቱም እግዚአብሔር አይሁዶችን ስለ መረጣቸው ነው”
አይሁዶችን ማን እንደሚወዳቸውና ጳውሎስ ለምን አባቶቻቸውን እንደሚጠቅስ ግልጽ ማድረግ ትችላለህ። ደግሞም ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “እግዚአብሔር ለአባቶቻቸው ሊያደርግላቸው ተስፋ በመስጠቱ ምክንያት አሁንም ይወዳቸዋል”
እግዚአብሔር ለሕዝቡ ሊሰጣቸው ቃል ስለገባላቸው መንፈሳዊና ቁሳዊ በረከቶች ጳውሎስ እንደ ስጦታዎች በመቁጠር ይናገራል። የእግዚአብሔር ጥሪ አይሁዶች የእርሱ ሕዝብ እንዲሆኑ እግዚአብሔር የመጥራቱን ሐቅ ያመለክታል። አ.ት፡ “ሊሰጣቸው ቃል ስለገባላቸው ነገርና የእርሱ ሕዝብ እንዲሆኑ እንዴት እንደጠራቸው እግዚአብሔር በፍጹም አሳቡን አልለወጠም”
“ባለፈው ጊዜ አልታዘዛችሁም ነበር”
እዚህ ጋ ምህረት ማለት የማይገቡ የእግዚአብሔር በረከቶች ማለት ነው። አ.ት፡ “አይሁዶች ኢየሱስን ስለ ተቃወሙት እናንተ የማይገባችሁን በረከቶች ተቀበላችሁ”
x
እዚህ ጋ የ “ጥበብ” እና “ዕውቀት” መሠረታዊ ትርጉማቸው አንድ ነው። አ.ት፡ “ከእግዚአብሔር ጥበብና ዕውቀት የሚገኙት ብዙ ጥቅሞች እንዴት የሚያስደንቁ ናቸው!”
“እርሱ የወሰናቸውን ነገሮችና በእኛ ላይ የሚፈጽምባቸውን መንገዶቹን ለመረዳት በፍጹም አንችልም”
እንደ ጌታ ጥበበኛ የሆነ ማንም እንደሌለ አጽንዖት ለመስጠት ጳውሎስ ይህንን ጥያቄ ይጠይቃል። ይህንን እንደ መግለጫ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “የጌታን አሳብ ያወቀ ማንም የለም፣ አማካሪው የሆነም ማንም የለም” (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ “አሳብ” ነገሮችን ማወቅ ወይም ስለ ነገሮች ማሰብ የሚለውን ገላጭ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “ጌታ የሚያውቀውን ሁሉ” ወይም “ጌታ ስለሚያስብለት ጉዳይ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ጳውሎስ ለማብራሪያው አጽንዖት ለመስጠት ይህንን ጥያቄ ይጠይቃል። አ.ት፡ “በመጀመሪያ ከእግዚአብሔር ሳይቀበል ለእግዚአብሔር አንዳች ነገር የሰጠ ማንም የለም” (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)* ከእርሱ … በእርሱ … ለእርሱ - እዚህ ጋ፣ “እርሱ” የሚሉት አገባቦች ሁሉ የሚያመለክቱት እግዚአብሔርን ነው።
ሰዎች ሁሉ እግዚአብሔርን እንዲያከብሩት ጳውሎስ ያለውን ምኞት ይህ ይገልጻል። በትርጉምህ ይህንን ግልጽ ልታደርገው ትችላለህ። አ.ት፡ “ሰዎች ሁሉ እርሱን ለዘላለም ያክብሩት”
1 ስለዚህም ወንድሞች ሆይ ሥጋችሁን ህያው መስዋዕት፥ቅዱስ፥ ለእግዚአብሔር የሚገባ አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ምህረት እለምናችኋለሁ፥ ያም ተገቢ የሆነ አገልግሎታችሁ ነው። 2 መልካም፥ተቀባይነት ያለውና ፍጹም የሆነውን የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንድታውቁ በታደስ አዕምሮ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትከትሉ። 3 ከእናንተ ማንም ስለራሱ ሊያስብ ከሚገባው በላይ እንዳያስብ በተሰጠኝ ጸጋ አሳስብለሁ። ይልቁኑም ለእያንዳንዱ ከእግዚአብሔር በተሰጠው እምነት ልክ በጥበብ ሊያስብ ይገባል። 4 ልክ እኛ በአንድ አካል ላይ ብዙ የአካል ክፍሎች ቢኖሩንም ተግባራቸው ግን ተመሳሳይ አይደለም። 5 እንዲሁ እኛም ብዙዎች ሳለን በክርስቶስ አንድ አካል ነን እያንዳንዳችንም አንዳችን የሌላችን የአካል ክፍል ነን። 6 በተሰጠን ጸጋ በኩል ልዩ ልዩ ስጦታዎች አሉን። የአንድ ሰው ስጦታ ትንቢት መናገር ከሆነ ባመነው መጠን ያድርገው። 7 የአንዱ ስጦታ ደግሞ ቸርነት ማድረግ ከሆነ ቸርነት ያድርግ። የማስተማር ስጦታ ያለው ያስተምር። 8 የማጽናናት ስጦታ ያለው ያጽናና፤ የመስጠት ስጦታ ያለው በልግስና ያድርገው፤ የመምራት ስጦታ ያለው በጥንቃቄ ይፈጽመው፤ምህረት የማድረግ ስጦታ ያለው በደስታ ያድርገው። 9 ፍቅራችሁ ያለግብዝነት ይሁን። ክፉ የሆነን ነገር ተጸየፉ፤መልካም የሆነውን ያዙ። 10 እውነተኛ የወንድማማች ፍቅር ይኑራችሁ፤ እርስ በእርሳችሁ ተከባበሩ። 11 ልግምተኞች አትሁኑ፤በመንፈሳችሁ ንቁ ሁኑ ፥ ጌታንም አገልግሉ። 12 ስላላችሁ የወደፊት ተስፋ ደስ ይበላችሁ፤ በመከራ ጊዜ ትዕግስተኞች ሁኑ፥ጸሎታችሁ የማያቋርጥ ይሁን፤ 13 ቅዱሳንን በችግራቸው እርዱ፤ መልካም ለማድረግ የሚያስችላቹሁን መንገዶች ፈልጉ። 14 የሚያሳድዷችሁን ባርኳቸው፥ባርኩ እንጂ አትርገሙ። 15 ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ። 16 አንድ ልብ ይኑራችሁ፥ትሁት ሰዎችን ተቀበሉዋቸው እንጂ በትዕቢት አታስቡ። በራሳችሁ አመለካከት ጥበበኞች እንደሆናችሁ አታስቡ። 17 ክፉ ላደረገባችሁ ለማንም ክፉ አትመልሱ። በሰዎች ሁሉ ፊት መልካምን ነገር አድርጉ። 18 በተቻላችሁ መጠን በእናንተ በኩል ከሰዎች ሁሉ ጋር በሠላም ኑሩ። 19 የተወደዳችሁ ሆይ ስለራሳችሁ አትበቀሉ ይልቁኑ ለእግዚአብሔር ቁጣ ዕድል ስጡ።ምክንያቱም እንዲህ ተብሎ ተጽፏል፦ «ጌታ 'በቀል የኔ ነው ብድራትን የምከፍለው እኔ ነኝ' ይላል»። 20 «ነገር ግን ጠላትህ ከተራበ መግበው። ከተጠማ ደግሞ የሚጠጣ ስጠው። ይህን ስታደርግ የእሳት ፍም በአናቱ ላይ ትከምራለህ። 21 ክፉን በመልካም አሸንፍ እንጂ በክፉ አትሸነፍ።»
ጳውሎስ የአማኝ ሕይወት ምን መሆን እንዳለበትና እንዴት ማገልገል እንዳለበት ይናገራል።
እዚህ ጋ፣ “ወንድሞች” የሚያመለክተው ወንዶችንና ሴቶች አማኞችን ነው። አ.ት፡ “አማኞች ሆይ፣ እግዚአብሔር በሰጣችሁ ታላቅ ምህረት ምክንያት አጥብቄ እለምናችኋለሁ”
ጳውሎስ እዚህ ጋ “ሰውነት” የሚለውን ቃል የሚጠቀመው ሙሉውን ሰው ለማመልከት ነው። ጳውሎስ በክርስቶስ ሆኖ እግዚአብሔርን በፍጹምነት የሚታዘዘውን አማኝ አይሁዶች አርደው ለእግዚአብሔር ከሚሰዉት እንስሳ ጋር እያነጻጸረ ነው። አ.ት፡ “በቤተ መቅደሱ መሰዊያ ላይ ታርዳችሁ በምትሰዉበት መልኩ ሕያው ሆናችሁ ሳላችሁ ራሳችሁን ሙሉ በሙሉ ለእግዚአብሔር እንድታቀርቡ”
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “ለእግዚአብሔር ብቻ የምታቀርቡትና እርሱን ደስ የሚያሰኘው መስዋዕት” ወይም 2) “ንጹህ ሥነ ምግባር ስለሆነ እግዚአብሔር የሚቀበለው” የሚሉት ናቸው።
“ይህ እግዚአብሔርን የማምለክ ትክክለኛው መንገድ ነው”
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “ዓለም እንደሚያደርገው አታድርጉ” ወይም 2) “ዓለም በሚያደርገው መልኩ አታስቡ” የሚሉት ናቸው። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ “ጸጋ” የሚያመለክተው ሐዋርያና የቤተ ክርስቲያን መሪ እንዲሆን እግዚአብሔር ጳውሎስን ስለመምረጡ ነው። ይህንን በትርጉምህ ግልጽ ልታደርገው ትችላለህ። ደግሞም ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “ምክንያቱም ሐዋርያ እንድሆን እግዚአብሔር በነጻ መርጦኛል”
“ከመካከላችሁ ማናቸውም ቢሆኑ ከሌሎች ሰዎች እንደሚሻሉ እንዳያስቡ”
“ነገር ግን ስለ ራሳችሁ በምታስቡት ጥበበኞች እንድትሆኑ”
እዚህ ጋ ጳውሎስ የሚያመለክተው፣ በእግዚአብሔር ላይ ካላቸው እምነት ጋር ተያይዞ አማኞች ስለሚኖራቸው የተለያዩ ችሎታዎች ነው። አ.ት፡ “በእርሱ ላይ ባላችሁ እምነት ምክንያት እግዚአብሔር ለእያንዳንዳችሁ የተለያዩ ችሎታዎችን ስለሰጣችሁ”
ጳውሎስ ይህንን ቃል የሚጠቀመው አንዳንድ ክርስቲያኖች ከሌላው እንደሚሻሉ ለምን ማሰብ እንደሌለባቸው የሚሰጠውን ማብራሪያ ለማሳየት ነው።
ጳውሎስ የሰው አካል ልዩ ልዩ ክፍሎች እንደሆኑ አድርጎ በክርስቶስ የሆኑትን አማኞች ሁሉ ያመለክታል። ይህንን የሚያደርገው አማኞች ክርስቶስን በተለያዩ መንገዶች የሚያገለግሉ ቢሆኑም እያንዳንዱ ሰው የክርስቶስ እንደሆነና ጠቃሚ በሆነ መንገድ እንደሚያገለግል ለማስረዳት ነው። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ጳውሎስ አማኞች ያሏቸው ልዩ ልዩ ችሎታዎች ከእግዚአብሔር በነጻ የተሰጡ ስጦታዎች መሆናቸውን ይናገራል። ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “እግዚአብሔር ልዩ ልዩ ነገሮችን ለእርሱ እንድናደርግለት ለእያንዳንዳችን ችሎታዎችን በነጻ ሰጥቶናል” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “እግዚአብሔር ከሰጠን የእምነት መጠን ያላለፈ ትንቢትን ይናገር” ወይም 2) “ከእምነታችን አስተምህሮ ጋር የሚስማማ ትንቢት ይናገር” የሚሉት ናቸው።
እዚህ ጋ “መስጠት” የሚያመለክተው ገንዘብንና ሌሎችንም ነገሮች ለሰዎች መስጠትን ነው። ይህንን ፍቺ በትርጉምህ ውስጥ ግልጽ ማድረግ ትችላለህ። አ.ት፡ “አንድ ሰው ገንዘብን ወይም ሌሎች መገልገያዎችን ለተቸገሩ ሰዎች የመስጠት ስጦታ ከተሰጠው”
ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “ሰዎችን በቅንነትና በእውነተኝነት መውደድ ይኖርባችኋል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ ጳውሎስ የሚጠቀምበት ቃል የሚያመለክተው ከእግዚአብሔር በሚመጣውና ራስን በማይጠቅምበት ጊዜም እንኳን ለሌሎች በሚደረግ መልካም ነገር ላይ የሚያተኩረውን የፍቅር ዓይነት ነው።
እዚህ ጋ ጳውሎስ አማኞች ምን ዓይነት ሰዎች መሆን እንዳለባቸው ለመንገር እያንዳንዳቸው “. . . ሁኑ” የሚል ቅርጽ ያላቸው ዘጠኝ ዓይነቶችን መዘርዘር ይጀምራል። አንዳንዶቹን ዝርዝሮች “. . . አድርጉ” ብለህ መተርጎም ይኖርብህ ይሆናል። ዝርዝሩ እስከ ሮሜ 12፡13 ይቀጥላል።
“እንደ እናንተው አማኞች የሆኑትን መውደድን አስመልክቶ”
ይህ የወንድማማች ፍቅር ወይም የጓደኛ ወይም የቤተሰብ ፍቅር የሚል ትርጉም ያለው ሌላ ቃል ነው። ይህ በጓደኛሞች ወይም በዘመዳሞች መካከል ያለ ተፈጥሮአዊና ሰብአዊ ፍቅር ነው።
ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “ፍቅርን አሳዩ” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“እርስ በእርሳችሁ ተከባበሩ፣ አክብሮትንም አሳዩ” ወይም “አማኝ ባልንጀሮቻችሁን በማክበር ክብርን ስጧቸው”
“በሥራችሁ ሰነፎች አትሁኑ፣ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን ለመከተልና ጌታን ለማገልገል የምትጓጉ ሁኑ”
“መከራ በሚደርስባችሁ ጊዜ ሁሉ በትዕግስት ቆዩ”
ይህ በሮሜ 12፡9 የጀመረው ዝርዝር የመጨረሻው ጉዳይ ነው። “እንደእናንተው ክርስቲያን የሆኑ በሚቸገሩበት ጊዜ በሚያስፈልጋቸው ነገር እርዷቸው”
“ማረፊያ በሚፈልጉበት ጊዜ ሁሉ በቤታችሁ ተቀበሏቸው”
ይህ በአንድነት መኖር የሚል ትርጉም ያለው የአነጋገር ዘይቤ ነው። አ.ት፡ “እርስ በእርሳችሁ ተስማሙ” ወይም “እርስ በእርሳችሁ በአንድነት ኑሩ” (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)
“ከሌሎች በበለጠ የምታስፈልጉ እንደሆናችሁ አታስቡ”
“የሚጠቅሙ የማይመስሉ ሰዎችን ተቀበሏቸው”
x
“ክፉ ባደረገባችሁ ሰው ላይ ክፉ አታድርጉ”
“ሁሉም መልካም እንደሆኑ የሚቆጥሯቸውን ነገሮች አድርጉ”
“ከሁሉ ጋር በሰላም ለመኖር የምትችለውን ሁሉ አድርግ”
ፈሊጣዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “እግዚአብሔር እንዲቀጣቸው ፍቀድለት” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “አንድ ሰው ጽፎታልና” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
እነዚህ ሁለቱም ሐረጎች መሠረታዊ ትርጉማቸው አንድ ሲሆን እግዚአብሔር ሕዝቡን እንደሚበቀል አጽንዖት ይሰጣሉ። አ.ት፡ “በርግጥ እኔ እበቀላችኋለሁ”
“አንተ” እና “የአንተ” የሚሉ አገባቦች ሁሉ ለአንድ ሰው እንደሚነገሩ ሆነው ቀርበዋል።
ጳውሎስ በ12፡20 ላይ ከሌላ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ይጠቅሳል። አ.ት፡ “ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ ደግሞ፣ ‘ጠላትህ ከተራበ … በራሱ ላይ …’ ይላል”
“ጥቂት ምግብ ስጠው”
ጳውሎስ አንድ ሰው በራሳቸው ላይ የእሳት ፍም የሚያፈስባቸው በሚመስልበት ሁኔታ ጠላቶች ስለሚቀበሏቸው በረከቶች ይናገራል። ሊሆኑ የሚችሉት ትርጉሞች፣ 1) “የጎዳችሁ ሰው የማይገባ ነገር እንዳደረገባችሁ እጅግ ተሰምቶት እንዲጸጸት አድርጉት” ወይም 2) “እግዚአብሔር በጠላትህ ላይ የከፋ ፍርድ የሚሰጥበትን ምክንያት እንዲያገኝ አድርገው” የሚሉት ናቸው። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ጳውሎስ “ክፉ”ን እንደ ሰው በመቁጠር ይገልጸዋል። ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉም ትችላለህ። አ.ት፡ “ክፉዎች እንዲያሸንፉህ አትፍቀድላቸው፣ ነገር ግን መልካም የሆነውን በማድረግ ክፉ የሆኑትን አሸንፋቸው” (ሰውኛ እና አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
1 ከእግዚአብሔር ካልተሰጠ በቀር ሥልጣን የለምና ሰው ሁሉ ለመንግስት ባለሥልጣናት ይገዛ። አሁን በሥልጣን ላይ ያለውም የተሾመው በእግዚአብሔር ነው። 2 ስለዚህም ይህን ሥልጣን የሚቃወም የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ ይቃወማል፥ የሚቃወሙትም ሁሉ በራሳችው ላይ ፍርድን ያመጣሉ። 3 ምክንያቱም ገዢዎች ክፉ ለሚያደርጉ እንጂ መልካም ለሚያደርጉ የሚያስፈሩ አይደሉም። ባለሥልጣንን አለመፍራት ትፈልጋለህ? መልካምን አድርግ ከእርሱ ሽልማትን ታገኛለህ። 4 ለመልካም ለአንተ የእግዚአብሔር አገልጋይ ነውና። ክፉ የምታደርግ ከሆነ ግን ያለምክንያት ሠይፍ አልታጠቀምና ልትፈራ ይገባሀል። ምክንያቱም ክፉ የሚያደርገውን በቁጣ የሚበቀል የእግዚአብሔር አገልጋይ ነው። 5 ስለዚህ ስለ ቁጣው ብለህ ብቻ ሳይሆን ስለህሊናህ ብለህ ልትገዛ ይገባሀል። 6 በዚህ ምክንያት ግብርም ትከፍላላችሁ። ምክንያቱም ባለሥልጣናት ይህንን ጉዳይ ያለመታከት የሚቆጣጠሩ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ናቸው። 7 ለእያንዳንዱ የሚገባውን ስጡ፥ ግብር ለሚገባው ግብርን፥ ቀረጥ ለሚገባው ቀረጥን፥ መፈራት ለሚገባው መፈራትን፣ አክብሮት ለሚገባው አክብሮትን ስጡ። 8 እርስ በእርስ ከመዋደድ በቀር የማንም ዕዳ አይኑርባችሁ። ምክንያቱም ባልንጀራውን የሚወድ ህግን ፈጽሟል። 9 ምክንያቱም «አታመንዝር፥ አትግደል፥ አትስረቅ፥ አትመኝ» የሚሉትና ሌሎቹም ትዕዛዛት «ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ» በሚለው ትዕዛዝ ተጠቃለዋል። 10 ፍቅር ያለው ባልንጀራውን አይጎዳም። ስለዚህ ፍቅር የህጉ ፍጻሜ ነው። 11 በዚህም ምክንያት ከእንቅልፍ የምትነቁበት እንደደረስ ታውቃላችሁ። መዳናችን መጀመሪያ ካመንበት ጊዜ ይልቅ ቅርብ ነው። 12 ሌሊቱ እያለፈ ቀኑም እየቀረበ ነው። ስለዚህ የጨለማን ሥራ ጥለን የብርሀንን የጦር ዕቃ እንልበስ። 13 ቅጥ ባጣ ፈንጠዝያና በስካር ሳይሆን በቀን እንደሚመላለስ ሰው በተገቢው ሁኔታ እንመላለስ። በዝሙት ወይም በማይገታ ክፉ ምኞት፥ በጭቅጭቅና በቅናት አንመላለስ ። 14 ይልቁኑ ኢየሱስ ክርስቶስን ልበሱት ለሥጋችሁና ለክፉ ምኞቱም ዕድል አትስጡ።
አማኞች በገዢዎቻቸው ሥር እንዴት መኖር እንዳለባቸው ጳውሎስ ይነግራቸዋል።
እዚህ ጋ “ነፍስ” ሙሉዉን ሰው በከፊል የሚገልጽ ነው። “ክርስቲያን ሁሉ መታዘዝ አለበት” ወይም “ሁሉም መታዘዝ አለበት”
“የመንግሥት ኃላፊዎች”
ምክንያቱም
“ሥልጣን ሁሉ የሚመጣው ከእግዚአብሔር ነው”
ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “በሥልጣን ላይ ያሉ ሰዎች በዚያ ያሉት እግዚአብሔር እዚያ ላይ ስላስቀመጣቸው ነው” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
“ያ የመንግሥት ሥልጣን” ወይም “እግዚአብሔር በኃላፊነት ላይ ያስቀመጠው ሰው ሥልጣን”
ይህንን በአድራጊ ድምፅ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “የመንግሥትን ሥልጣን በሚቃወሙት ላይ እግዚአብሔር ይፈርድባቸዋል” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
ጳውሎስ የሮሜ 13፡2 ማብራሪያውን ለመጀመርና መንግሥት በአንድ ሰው ላይ ቢፈርድበት ምን እንደሚከተለው ለመንገር ይህንን ቃል ይጠቀማል።
መልካም ሰዎችን ገዢዎች እንዲፈሩ አያደርጓቸውም።
ሰዎች በ”መልካም ሥራቸው” ወይም በ”ክፉ” ሥራቸው ተለይተዋል”።
ሰዎች ገዢዎችን ላለመፍራት ምን ማድረግ እንዳለባቸው እንዲያስቡ ለማድረግ ጳውሎስ ይህንን ጥያቄ ይጠይቃል። አ.ት፡ “ገዢዎችን እንዴት መፍራት እንደማይኖርባችሁ እንድነግራችሁ ፍቀዱልኝ”። (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)
መንግሥት መልካም የሆነውን ስለሚያደርጉ ሰዎች መልካም ነገር ይናገራል።
ይህንን በአዎንታ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “እርሱ ሰይፍ የሚታጠቀው በጣም ጥሩ በሆነ ምክንያት ነው” ወይም “እርሱ ሰዎችን የሚቀጣበት መብት አለው፣ ስለዚህ ሰዎችን ይቀጣቸዋል” (ምጸት የሚለውን ተመልከት)
ሮማውያን ገዢዎች የሥልጣናቸው ምልክት የሚሆን አጭር ሰይፍ ይታጠቁ ነበር። (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
እዚህ ጋ “ቁጣ” የሚወክለው ሰዎች ክፉ ነገር በሚያደርጉበት ጊዜ የሚቀበሉትን ቅጣት ነው። አ.ት፡ “በክፉ ላይ የመንግሥትን ቁጣ ለመግለጽ ሰዎችን የሚቀጣ ሰው” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
“መንግሥት እንዳይቀጣህ ብለህ ብቻ ሳይሆን በእግዚአብሔር ፊት ንጹህ ሕሊና እንዲኖርህ ደግሞ ነው”
“መንግሥት ክፉ አድራጊዎችን ስለሚቀጣ”
እዚህ ጋ ጳውሎስ የሚናገረው ለአማኞች ነው።
“ለባለሥልጣናት ግብር መክፈል የሚኖርባችሁ ለዚህ ነው”
“የሚያስተዳድሩ” ወይም “የሚሠሩ”
“ስጡ” የሚለውን ቃል ቀደም ሲል ከነበረው ዐረፍተ ነገር መገንዘብ ይቻላል። አ.ት፡ “ግብር ለሚገባው ግብርን፣ ቀረጥ ለሚገባውም ቀረጥን ስጡ። መፈራት ለሚገባው መፈራትን፣ ክብር ለሚገባውም ክብርን ስጡ”
እዚህ ጋ፣ መፈራትንና ክብርን መስጠት መፈራትና መከበር የሚገባቸውን እነርሱን የመፍራትና የማክበር ዘይቤአዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “መፈራት የሚገባቸውን እነርሱን ፍሩ፣ መከበር የሚገባቸውን እነርሱን ደግሞ አክብሩ” ወይም “ልታከብሯቸው የሚገባችሁን አክብሯቸው፣ አክብሮት ልታሳዩአቸው የሚገባችሁንም አክብሮትን አሳዩአቸው” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ይህ የቀረጥ ዓይነት ነው።
ባልንጀሮቻቸውን በሚመለከት ምን ማድረግ እንዳለባቸው ጳውሎስ ለአማኞች ይነግራቸዋል።
ይህ ድርብ አሉታ ነው። ይህንን በአዎንታ ልትተረጉመው ትችላለህ። አ.ት፡ “በእያንዳንዱ ላይ ያለባችሁን ዕዳ ክፈሉ፣ እርስ በእርሳችሁም ተዋደዱ” (ድርብ አሉታ የሚለውን ተመልከት)
ይህ ግሥ ብዙ ቁጥር ሲሆን በሮም የሚኖሩትን ክርስቲያኖች ሁሉ የሚመለከት ነው።
ከላይ በተጠቀሰው ማስታወሻ እንደተመለከተው ሊኖርባቸው የሚችለው ዕዳ ይህ ነው።
ይህ የሚያመለክተው ከእግዚአብሔር በሚመጣውና ራስን በማይጠቅምበት ጊዜም እንኳን ለሌሎች በሚደረግ መልካም ነገር ላይ የሚያተኩረውን የፍቅር ዓይነት ነው።
ለሌላው ሰው ያለው ነገር የራስ እንዲሆን ወይም እንዲኖር መፈለግ።
ይህ ሐረግ ፍቅርን ለሌሎች ሰዎች ደግ እንደሚሆን ሰው አድርጎ ይገልጸዋል። አ.ት፡ “ባልንጀሮቻቸውን የሚወዱ ሰዎች አይጎዷቸውም” (ሰውኛ የሚለውን ተመልከት)
ከእንቅልፍ መንቃት በሚያስፈልጋቸው መልኩ የሮም አማኞች የባህርይ ለውጥ ማድረግ እንደሚያስፈልጋቸው ጳውሎስ ይናገራል። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
ጳውሎስ አንባቢዎቹንና ሌሎች አማኞችን ከራሱ ጋር ያካትታል። (አካታች “እኛ” የሚለውን ተመልከት)
ጳውሎስ እንደ እውነተኞች አማኞች መኖርን ለማስረዳት አንድ ሰው በቀን እንደሚመላለስ አድርጎ ይናገራል። አ.ት፡ “ሁሉ ሊያየን እንደሚችል እያወቅን በግልጽነት እንመላለስ” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
እነዚህ አሳቦች መሠረታዊ ትርጉማቸው አንድ ነው። በትርጉምህ ውስጥ ልታጣምራቸው ትችላለህ። አ.ት፡ “አስጸያፊ የዝሙት ተግባር”
ይህ በሌሎች ላይ ማሴርንና ከሌሎች ሰዎች ጋር መከራከርን ያመለክታል።
ይህ በሌላው ሰው ስኬት ወይም ሌሎች በሚገጥሟቸው ዕድሎች የሚሰማውን አሉታዊ ስሜት ያመለክታል።
ጳውሎስ የክርስቶስን የሥነ ምግባር ባህርይ መቀበልን ሰዎች ሊያዩት እንደሚችሉት ውጫዊ ልብሳችን አድርጎ ይናገራል። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
የአንተ ቋንቋ ትዕዛዝን በብዙ ቁጥር የሚገልጽበት አግባብ ካለ እዚህ ጋ ተጠቀምበት።
እዚህ ጋ “ሥጋ” የሚያመለክተው እግዚአብሔርን የሚቃወመውን የሰዎችን ራስ - መር ተፈጥሮ ነው። ይህ የሰው ልጆች ኃጢአታዊ ተፈጥሮ ነው። አ.ት፡ “ክፉ ነገሮችን እንዲያደርግ ለአሮጌው ክፉ ልብ አንዳችም ዕድል ከቶ አትስጡት” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
1 በእምነት ደካማ የሆነውን በጥያቄዎቹ ላይ በመፍረድ ሳይሆን በፍቅር ተቀበሉት። 2 አንዳንዱ ማንኛውንም ነገር በእምነት ይበላል፥በእምነቱ ደካማ የሆነው ደግሞ አትክልት ብቻ ይበላል። 3 ስለዚህ ማንኛውንም ዓይነት ምግብ የሚበላው የማይበላውን አይናቀው። የማይበላውም በሚበላው ላይ አይፍረድ። ምክንያቱም እግዚአብሔር ተቀብሎታል። 4 በሌላው አገልጋይ ላይ የምትፈርድ አንተ ማን ነህ? በገዛ ጌታው ፊት ወይ ይቆማል አሊያም ይወድቃል። ነገር ግን ጌታ ሊያቆመው ይችላልና ይቆማል። 5 አንደኛው አንዱን ቀን ከሌላው ቀን የሚበልጥ አድርጎ ይቆጥራል። ሌላው ደግሞ ሁሉም ቀናት አንድ ናቸው ብሎ ያምናል። እያንዳንዱ ሰው የራሱ መረዳት ይኑረው። 6 ቀንን የሚያከብር ለእግዚአብሔር ብሎ ያከብራል፥ የሚበላውም እግዚአብሔርን ያመሰግናልና ለእግዚአብሔር ብሎ ይበላል። የማይበላውም ራሱን ከመብላት ያቅባል። እርሱም እግዚእብሔርን ያመሰግናል። 7 ምክንያቱም ከእኛ ማንም ለራሱ የሚኖር ወይም የሚሞት የለም። 8 ብንኖር ለጌታ እንኖራልንና ብንሞትም ለጌታ እንሞታለንና። እንግዲያውስ ብንኖርም ብንሞትም የጌታ ነን። 9 ምክንያቱም በሙታንና በህያዋን ላይ ጌታ ይሆን ዘንድ ለዚህ ዓላማ ክርስቶስ ሞቷል ደግሞም ህያው ሆኗል። 10 ግን አንተ በወንድምህ ላይ ለምን ትፈርዳለህ? አንተስ ወንድምህን ለምን ትንቃለህ? ሁላችንም በእግዚአብሔር የፍርድ ዙፋን ፊት እንቆማለን። 11 ምክንያቱም «እኔ ህያው ነኝና ጉልበት ሁሉ በፊቴ ይንበረከካል ምላስም ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናል» ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፏል። 12 ስለዚህም እያንዳንዳችን ስለ ስራችን በእግዚአብሔር ፊት መልስ እንሰጣለን። 13 ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲያ አንዳችን በሌላችን ላይ አንፍረድ በዚያ ፋንታ ማንም በወንድሙ ፊት መሰናክል ወይም ወጥመድ እንዳያስቀምጥ እንወስን። 14 ምንም ነገር በራሱ ርኩስ እንዳልሆነ በጌታ በኢየሱስ አውቃለሁ ተረድቻለሁም። ማንኛውም ነገር ርኩስ ነው ብሎ ለሚያስብ ለእርሱ ብቻ ያ ነገር እርኩስ ነው። 15 በምግብ ጉዳይ ወንድምህን የምታሰናክል ከሆነ አንተ በፍቅር እየተመላለስክ አይደለም። ስለምግብህ ብለህ ክርስቶስ የሞተለትን ሰው አታጥፋ። 16 ስለዚህ መልካም ስራዎቻችሁን ለሰዎች መቀለጃ አታድርጉ። 17 ምክንያቱም የእግዚአብሔር መንግሥት በመንፈስ ቅዱስ የሚሆን ጽድቅ፥ ሠላምና ደስታ እንጂ የመብልና የመጠጥ ጉዳይ አይደለም። 18 ክርስቶስ እንዲህ ባል ሁኔታ የሚያገለግለውን እግዚአብሔር ይቀበለዋል በሰዎችም ይመሰገናል። 19 ስለዚህ ሠላም የሚገኝበትንና እርስበእርሳችን የምንተናነጽባቸውን ነገሮች እንፈልግ። 20 በምግብ ምክንያት የእግዚአብሔርን ሥራ አታበላሹ። በእርግጥም ሁሉ ነገር ንጹህ ነው፥ ነገር ግን እየተጠራጠረ ለሚበላ ለዚያ ሰው ክፉ ነው፣ እንዲሰናከልም ያደርገዋል። 21 ወንድምህን የሚጎዳ ከሆነ ሥጋ ባትበላም ወይን ባትጠጣም ወይም ምንም ባታደርግ መልካም ነው። 22 አንተ በግልህ ያለህ መረዳት ባንተና በእግዚአብሔር መሀል ይቅር። አምኖ የተቀበለውን ነገር በማድረጉ ራሱን የማይወቅስ የተባረከ ነው። 23 እየተጠራጠረ የሚበላ ግን በእምነት ስላልሆነ ይፈረድበታል። ምክንያቱም ያለ እምነት የሆነ ነገር ሁሉ ኃጢአት ነው።
ጳውሎስ አማኞች በእግዚአብሔር ዘንድ ተጠያቂ አንደሆኑ እንዲያስታውሱ ያበረታታቸዋል።
ይህ የሚወክለው አንዳንድ ነገሮችን በመብላታቸው የወቀሳ ስሜት የሚሰማቸውን ሰዎች ነው።
“እናም በአስተሳሰባቸው ምክንያት አትክሰሷቸው”
እዚህ ላይ “እምነት” የሚለው ቃል አንድ ሰው እግዚአብሔር አድርግ ብሎኛል ብሎ የሚያምነውን ነገር ማድረግን ያመለክታል።
ይህ እርሱ ስጋን እንዲበላ እግዚአብሔር እንደማይፈልግ የሚያምንን ሰው ይገልጻል።
ጳውሎስ ይህን ጥያቄ በሌሎች ላይ የሚፈርዱ ሰዎችን ለመገሰጽ ይጠቀምበታል። ይህ በአረፍተ ሃሳብ መልክ ሊጻፍ ይችላል። አማራጭ ትርጉም፡- “እናንተ እግዚአብሔር አይደላችሁም፣ እናም የእርሱ አገልጋዮች ላይ ለመፍረድ አልተፈቀደላችሁም” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ “አንተ” የሚለው ቃል በነጠላ ቁጥር የተገለጸ ነው። (የሁለተኛ መደብ ቅርጾች የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ ጳውሎስ ስለ እግዚአብሔር ሲናገር አገልጋዮች እንዳሉት ጌታ አድርጎ ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “አገልጋዩን ለመቀበልም ሆነ ላለመቀበል መወሰን የሚችለው ጌታው ብቻ ነው” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
ጳውሎስ እዚህ ላይ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት ያገኘው አገልጋይ ከመውደቅ ይልቅ “እንዲቆም ይደረጋል” ሲል ይናገራል። ይህንን በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “ጌታ ግን ይቀበለዋል ምክንያቱም እርሱ አገልጋዮች ተቀባይነት እንዲኖራቸው ማድረግ ይችላል” (ተለዋጭ ዘይቤ እና ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“አንድ ሰው አንድ ቀን ከሌላው ቀን የበለጠ እንደሆነ ያስባል፣ ሌላው ግን ሁሉም ቀናት እኩል እንደሆኑ ያስባል።
የዚህን ትርጉም በግልጽ መናገር ይቻላል። ይህንን በገቢር/አድራጊ ቅርጽም መጻፍ ይቻላል። አማራጭ ትርጉም፡- “እያንዳንዱ ሰው የሚያደርገው ነገር ሁሉ እግዚአብሔርን ለማክበር እንደሆነ እርግጠኛ ይሁን” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ማክበር” የሚለው ማምለክን ያመለክታል። አማራጭ ትርጉም፡- “በአንድ በተወሰነ ቀን የሚያመልክ ሰው ይህን የሚያደርገው እግዚአብሔርን ለማክበር ነው” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“ሁሉንም” የሚለው ቃል ሮሜ 14:03 ላይ ባለው አገባብ መረዳት ይቻላል። እዚህ ላይ ተደግሞ ሊጻፍ ይችላል። አማራጭ ትርጉም፡- “ሁሉንም አይነት ምግብ የሚበላ ሰው” (አስጨምሬ የሚለውን ይመልከቱ)
“እግዚአብሔርን ለማክበር ይበላል” ወይም “በዚያ መንገድ የሚበላው እግዚአብሔርን ለማክበር ነው”
“ሁሉንም” የሚለው ቃል በሮሜ ሮሜ 14:03 ላይ ባለው አገባብ መሰረት መረዳት ይቻላል። እዚህ ላይ ተደግሞ ሊጻፍ ይችላል። አማራጭ ትርጉም፡- “ሁሉንም የማይበላ” ወይም “አንዳንድ የምግብ ዓይነቶችን የማይበላ ሰው” (አስጨምሬ የሚለውን ይመልከቱ)
“እነዚያን የምግብ ዓይነቶች ጌታን ለማክበር ሲል ከመብላት ይቆጠባል” ወይም “በዚያ መንገድ የሚበላው ጌታን ለማክበር ነው”
እዚህ ላይ “ለራሱ የሚኖር” ማለት ራሱን ለማስደሰት ብቻ የሚኖር ማለት ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “ማናችንም ራሳችንን ለማስደሰት ብቻ ብለን መኖር የለብንም” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ማለት የአንድ ሰው ሞት ሌሎች ሰዎችንም ይነካል ማለት ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “ማናችንም እኛ ብቻ ስንሞት እኛን ብቻ እንደሚጎዳ ማሰብ የለብንም። (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ጳውሎስ አንባቢዎቹንም በዚህ ንግግር ውስጥ እያካተተ ነው። (አካታች “እኛ” የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህን ጥያቄዎች በመጠቀም ጳውሎስ ከአንባቢዎቹ ውስጥ አንዳንድ ግለሰቦችን መገሰጽ እንደሚገባው ያሳያል። አማራጭ ትርጉም፡- “በወንድምህ ላይ መፍረድህ ትክክል አይደለም፣ ወንድምህንም መናቅ ትክክል አይደለም” ወይም “በወንድምህ ላይ መፍረድ፣ ወንድምህንም መናቅ አቁም!” (የሁለተኛ መደብ ቅርጾች የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ሌላ ክርስቲያን፣ ሴት ወይም ወንድ የሆነን ይወክላል።
“የፍርድ ዙፋን” የእግዚአብሔርን የመፍረድ ስልጣንን ያመለክታል። አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር በሁላችን ላይ ይፈርዳልና” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርጽ ሊጻፍ ይችላል። አማራጭ ትርጉም፡- “በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ አንድ ሰው እንዲህ ብሎ ጽፎ ነበርና’ … ” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ሐረግ አንድን መሃላ ወይም ቃልኪዳንን ለመጀመር ጥቅም ላይ ይውላል። አማራጭ ትርጉም፡- “ይህ እውነት እንደሆነ እርግጠኛ መሆን ትችላላችሁ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ጳውሎስ “ጉልበት” እና “ምላስ” የመሳሰሉትን ቃላት የሚጠቀመው የአንድን ሰው ሙሉ ማንነት ለመወከል ነው። በተጨማሪም ጌታ “እግዚአብሔር” የሚለውን ቃል ራሱን ለመወከል ይጠቀማል። አማራጭ ትርጉም፡- “ሁሉም ሰው ይሰግዳል፣ ምስጋናንም ለእኔ ይሰጣል” (ወካይ እና አንደኛ፣ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ መደብ የሚለውን ይመልከቱ)
“ለሰራናቸው ስራዎች ለእግዚአብሔር ማብራርያን እንሰጣለን”
እዚህ ላይ “የማሰናከያ እንቅፋት” ወይም “ወጥመድ” የሚሉት ቃላት ተመሳሳይ ነገርን ይወክላሉ። አማራጭ ትርጉም፡- “ነገር ግን ይልቁንም ሌላውን አማኝ ወደ ኃጢአት ሊወስድ የሚችል ነገርን አለማድረግንና አለመናገርን ግባችሁ አድርጉት” (ጥምር ቃል የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ሌላ ክርስቲያንን ይወክላል፣ ሴት ወይም ወንድ ሊሆን ይችላል።
እዚህ ላይ “አውቄያለሁ” እና “አምኛለሁ” የሚሉት ቃላት ተመሳሳይ ትርጉምን የያዙ ናቸው፡ ጳውሎስ እርግጠኛ መሆኑን አጽንኦት ለመስጠት ይጠቀምባቸዋል። አማራጭ ትርጉም፡- “ከጌታ ኢየሱስ ጋር ባለኝ ግንኙነት ምክንያት እርግጠኛ ነኝ” (ጥምር ቃል የሚለውን ይመልከቱ)
ይህን በአዎንታዊ መልኩ መተርጎም ይቻላል። አማራጭ ትርጉም፡- “ሁሉም ነገር በራሱ ንጹህ ነው” (መንትያ አሉታዎች የሚለውን ይመልከቱ)
“በተፈጥሮው” ወይም “በይዘቱ”
ጳውሎስ እዚህ ላይ ለመናገር የፈለገው አንድ ሰው ርኩስ ነው ብሎ ከሚያስበው ነገር መራቅ እንዳለበት ነው። ይህን በትርጉምህ ግልጽ አድርገህ ማስቀመጥ ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “ነገር ግን አንድ ሰው አንድን ነገር ርኩስ ነው ብሎ የሚያስብ ከሆነ፣ ለዚያ ሰው ያ ነገር ርኩስ ነውና ከእርሱ ሊርቅ ይገባዋል” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“የሌላውን ክርስቲያን እምነት በመብል ምክንያት የምትጎዳ ከሆነ” እዚህ ላይ “በመብልህ” ውስጥ ያለው የባለቤት አመልካች የሚያመለክተው በእምነቱ ጠንካራ የሆነን አማኝ ነው፣ “ወንድም” የሚለው ደግሞ በእምነታቸው ደካማ የሆኑትን ያመለክታል።
ይህ ሌሎች ክርስቲያኖችን ይወክላል፣ ወንዶችንም ሴቶችንም ይወክላል
ጳውሎስ የአማኞችን ባሕርይ ጉዞ እንደሆነ አድርጎ ይናገራል። አማራጭ ትርጉም፡- “ከእንግዲህ ፍቅርን እያሳየህ አይደለም” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“ሌላ ሰው አንድ ነገር ክፉ ነው ብሎ ካሰበ፣ ያንን ነገር አንተ አታድርገው፣ ምንም እንኳ አንተ መልካም ነው ብለህ የምታስብ ቢሆንም አታድርገው”
ጳውሎስ እግዚአብሔር መንግስቱን ያዘጋጀው ከራሱ ጋር ትክክለኛ የሆነ ግንኙነት እንዲኖረን ለማድረግ፣ እንዲሁም ሰላምንና ደስታን ሊሰጠን እንደሆነ በመናገር ይሞግታቸዋል። አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር መንግስቱን ያዘጋጀው የምንበላውንና የምንጠጣውን ለማስተዳደር አይደለም። መንግስቱን ያዘጋጀው ከእርሱ ጋር ትክክለኛ ግንኙነት እንዲኖረን፣ እንዲሁም ሰላምና ደስታን ሊሰጠን ነው። (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህን በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “ሰዎች እርሱን ይቀበሉታል” ወይም “ሰዎች እርሱን ያከብሩታል” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “የምንታነጽባቸውን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እርስ በርስ በእምነት የሚያሳድጉ ነገሮችን ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “አብረን በሰላም ለመኖርና በእምነታችን ለመበርታት እንፈልግ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
የዚህን አርፍተ ነገር ትርጉም ግልጽ አድርጎ መጻፍ ይቻላል። አማራጭ ትርጉም፡- “አንተ የሆነ የምግብ ዓይነት መብላት ስለፈለግህ ብቻ እግዚአብሔር ለአንድ አማኝ የሰራውን ስራ አታፍርሰው” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ሌላውን እንዲሰናከል የሚያደርግ” ማለት ደካማ የሆነው ወንድም ከሕሊናው ጋር የማይጣጣም ነገር እንዲያደርግ የሚገፋው ማለት ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “ነገር ግን አንድ ወንድም ሌላው ወንድም መብላት ትክክል አይደለም ብሎ የሚያስበውን ምግብ ቢበላ፣ ለዚያ ሰው ኃጢአት ይሆንበታል፣ እርሱ በመብላቱ ምክንያት ደካማውን ወንድም ከሕሊናው ጋር የማይጣጣም ነገር እንዲያደርግ ምክንያት ከሆነበት ኃጢአት ይሆንበታል” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“ስጋ መብላት፣ ወይን መጠጣት እንዲሁም ወንድምህ ኃጢአት እንዲያደርግ ምክንያት የሚሆን ነገርን አለማድረግ ይመረጣል”
ይህ ሌሎች አማኝ ክርስቲያኖችን ይወክላል፣ ወንድ ወይም ሴት ሊሆኑ ይችላሉ
“የአንተ” የሚለው በእምነቱ ጠንካራ የሆነውን ይወክላል፣ “ወንድም” የሚለው ደግሞ በእምነቱ ደካማ የሆነውን ይወክላል።
ይህ የሚያመለክተው ስለ መብልና መጠጥ ያላቸውን እምነት ነው።
ነጠላ ቁጥር ነው። ጳውሎስ መልዕክቱን የሚያስተላልፈው ለአማኞቹ ነው ስለዚህ ይህንን በብዙ ቁጥር መተርጎም ይቻላል። (የሁለተኛ መደብ ቅርጾች የሚለውን ይመልከቱ)
“ለማድረግ ወስነው በሚያደርጉት ነገር ወንጀለኝነት የማይሰማቸው ሰዎች የተባረኩ ናቸው”
ይህን በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “አንድ ሰው የሆነ ምግብ መብላት ትክክል መሆኑን እርግጠኛ ሳይሆን ያንን ምግብ ቢበላ እግዚአብሔር ያ ሰው ስህትተ ፈጽሟል ይለዋል” ወይም “አንድን ምግብ መብላት ትክክል ይሁን አይሁን እርግጠኛ ያልሆነ ሰው፣ ነገር ግን ምግቡን ቢበላው ያ ምግቡን የበላው ሰው መጥፎ ሕሊና ይኖረዋል” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“በእምነት ያልሆነ” ማንኛውም ነገር እግዚአብሔር እንድናደርገው የማይፈልገው ነገር ነው። ሙሉ ትርጉሙን በግልጽ ማስቀመጥ ይቻላል። አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር እንዲበላ የማይፈልገው ነገር መሆኑን አውቆ ያመነበትን ነገር በልቷልና እግዚአብሔር ስህተት ነህ ይለዋል” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“ከእምነት ያልሆነ” ነገር ሁሉ ማለት እግዚአብሔር እንድታደርጉት የማይፈልገው ነገር ማለት ነው። እዚህ ላይ ሙሉ ትርጉሙን በግልጽ ማስቀመጥ ይቻላል። አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር እንዳደርገው አይፈልግም ብላችሁ የምታምኑትን ነገር ብታደርጉ ኃጢአትን እየሰራችሁ ነው” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
1 እንግዲህ ብርቱዎች የሆንን እኛ የደካሞቹን ድካም ልንሸከም እንጂ ራሳችንን ብቻ ልናስደስት አይገባም። 2 መልካም ነውና እንድናንጸው እያንዳንዳችን ባልንጀራችንን ደስ እናሰኝ። 3 ምክንያቱም ክርስቶስ እንኳን እራሱን ደስ አላሰኘም። ይልቁንም «አንተን የሰደቡበት ስድብ በኔም ላይ ደረሰ» ተብሎ እንደተጻፈው ነው። 4 አስቀድሞ የተጸፈው ሁሉ በትዕግስትና በቅዱሳት መጽሀፍት እየተበረታታን ድፍረት እንድናገኝ ለትምህርታችን ተጽፎአል። 5 እንግዲህ የትዕግስትና የመጽናናት አምላክ ለእርስ በእርሳችሁ በክርስቶስ አንድ ልብ ይስጣችሁ። 6 በአንድ ልብና በአንድ አፍ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክና አባት እንድታመስግኑ ይህን ያድርግ። 7 ልክ ክርስቶስ እንደተቀበላችሁ ለእግዚአብሔር ክብር እርስ በእርሳችሁ ተቀባበሉ። 8 ስለ እግዚአብሔር እውነት ክርስቶስ የመገረዝ አገልጋይ ሆነ እላለሁ። ይህን ያደረገው ለአባቶች የተሰጠውን ተስፋ ሊያጸና 9 አህዛብ ደግሞ ስለምህረቱ እግዚአብሔርን እንዲያመሰግኑ ነው። ይህም «በአህዛብ መካከል አመሰግንሀለሁ፣ለስምህም እዘምራለሁ» ተብሎ በተጻፈው መሰረት ነው። 10 እንደገናም ደግሞ «እናንተ አህዛብ ከህዝቡ ጋር ደስ ይበላችሁ» ይላል። 11 ደግሞም እንደገና «አህዛብ ሁላችሁ እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ሰዎች ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግኑት» ይላል። 12 ኢሳያስ ደግሞ «አህዛብን ሊገዛ የሚነሳ የእሴይ ሥር ይወጣል፥ አህዛብም በእርሱ ይመካሉ።» ይላል። 13 በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በተስፋ ትሞሉ ዘንድ የተስፋ አምላክ በማመናችሁ ምክንያት በደስታና በሰላም ሁሉ ይሙላችሁ። 14 ወንድሞቼ ሆይ እናንተ ራሳችሁ በመልካምነትና በእውቀት እንደተሞላችሁ እርስ በእርሳችሁም ልትማማሩ እንደምትችሉ ስለእናንተ ተረድቻለሁ። 15 ነገር ግን ከእግዚአብሔር በተሰጠኝ ስጦታ ስለአንድ ጉዳይ ላሳስባችሁ በድፍረት ጽፌላችኋለሁ። 16 ይኸም ስጦታ የእግዚአብሔርን ወንጌልን እንደ ካህን እንዳቀርብላቸው ወደ አህዛብ የተላክሁ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ መሆኔ ነው። ይህን ማድረግ ያለብኝ የአህዛብ መስዋዕት ተቀባይነት እንዲያገኝና በመንፈስ ቅዱስ ለእግዚአብሔር እንዲቀርብ ነው። 17 እንግዲህ ደስታዬ በክርስቶስ ኢየሱስና ከእግዚአብሔር በሚሆኑ ነገሮች ነው። 18 አህዛብ ወደ መታዘዝ እንዲመጡ ክርስቶስ በእኔ ካከናወነው ነገር በቀር ስለምንም ነገር ለመናገር አልደፍርም። እነዚህም ነገሮች በቃልና በሥራ 19 በምልክትና በድንቆች ኃይል በመንፈስ ቅዱስም ኃይል የተከናወኑ ናቸው። ይህም በኢየሩሳሌምና በዙሪያዋ እስከ አልዋሪቆን ድርስ የክርስቶስን ወንጌል በሙላት እንዳደርስ ነበር። 20 በዚህ መንገድ ፍላጎቴ ወንጌልን መስበክ ነው፥ ነግር ግን የምሰብከው በሌላው ሰው መሠረት ላይ እንዳልገነባ የክርስቶስ ስም በሚታወቅበት አካባቢ አይደለም። 21 ይህም «ስለእርሱ ያልተነገራቸው ያዩታል፥ ያልሰሙም ያስተውላሉ» ተብሎ የተጻፈው እንዲፈጸም ነው። 22 ስለዚህም ወደ እናንተ እንዳልመጣ ብዙ ጊዜ እንቅፋት ገጠመኝ። 23 አሁን ግን በዚህ ባሉ ክልሎች እንብዛም የምሰራው ነገር የለኝም ወደ እናንተም ለመምጣት ለበርካታ ዓመታት ስናፍቅ ነበር። 24 ስለሆነም ወደ እስፔን በምሄድበት ጊዜ ከእናንተ ጋር ደስ የሚያሰኝ ጥቂት ጊዜ አሳልፌ በጉዞዬ እንድትረዱኝ ወደናንተ ጎራ ብዬ እንደማያችሁ ተስፋ አደርጋለሁ። 25 አሁን ግን በጌታ ያመኑትን ለማገልገል ወደ ኢየሩሳሌም እሄዳለሁ። 26 ምክንያቱም በመቄዶኒያና በአካይያ ያሉ አማኞች በኢየሩሳሌም ባሉ አማኞች መካከል ለሚገኙ ድሆች የተወሰነ ድጋፍ ለማድረግ በደስታ ፈቅደዋል። 27 አዎ በደስታ ሊያደርጉት መልካም ፈቃዳቸው ነበር፥ ለነገሩ የእነርሱ ባለዕዳዎች ናችው። አህዛብ ከእነርሱ መንፈሳዊ ነገርን ከተካፈሉ እነርሱ ደግሞ በቁሳዊ ነገር ሊያገለግሏቸው ይገባል። 28 ስለዚህም ይህን ስጦታውን የማድረስ ተግባሬን ከፈጸምኩ በኋላ በእናንተ በኩል ወደ እስፔን አልፋለሁ። 29 ወደ እናንተ ስመጣ በክርስቶስ በረከት ተሞልቼ እንደምመጣ አውቃለሁ። 30 እንግዲህ ወንድሞቼ ሆይ ስለኔ ወደ እግዚአብሔር በጸሎት አብራችሁኝ እንድትጋደሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ፣ በመንፈስ ቅዱስም ፍቅር እለምናችኋለሁ። 31 በይሁዳ ካሉ የማይታዘዙ ሰዎች እንድጠበቅ አገልግሎቴም በኢየሩሳሌም ባሉ አማኞች ተቀባይነት እንዲያገኝ ጸልዩ። 32 በእግዚአብሔር ፈቃድ ወደ እናንተ በደስታ መጥቼ አብሬያችሁ እንዳርፍ ጸልዩ። 33 የሠላም አምላክ ከሁላችሁም ጋር ይሁን። አሜን።
እዚህ ላይ ጳውሎስ ክርስቶስ እንዴት እንደኖረ በማስታወስ፣ አማኞች ለሌሎች ሊኖሩ እንደሚገባ የሚናገረውን ይህን ክፍል ይደመድመዋል።
ይህን ቃል በቋንቋችሁ ውስጥ በሙግት ውስጥ አዲስ ሃሳብን በሚያስተዋውቅ ቃል ተርጉሙት።
እዚህ ላይ “ብርቱ” የሚለው በእምነታቸው ብርቱ የሆኑ ሰዎችን ያመለክታል። እነርሱም እግዚአብሔር ምንም ዓይነት ምግብን እንዲበሉ እንደፈቀደ ያምናሉ። አማራጭ ትርጉም፡- “በእምነታችን ብርቱ የሆንን እኛ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ ጳውሎስ፣ ክርስቶስ (መሲሑ) ለእግዚአብሔር የሚናገርበትን አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ያነሳል። ይህን በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ መሲሑ ለእግዚአብሔር እንዲህ ሲል ተናግሯል …” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለጸ መረጃ እና ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
እግዚአብሔርን የሰደቡት ሰዎች ስድብ በክርስቶስ ላይ ወደቀ።
ይህን በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “ባለፉት ጊዜያት፣ ነቢያት በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የጻፉት ሁሉም ነገር እኛን ለማስተማር የተጻፈ ነውና” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ጳውሎስ አንባቢዎቹንና ሌሎች አማኞችን ያካትታል። (አካታች “እኛ” የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ተስፋ እንዲኖረን” የሚለው አማኞች እግዚአብሔር የገባውን ቃል እንደሚፈጽም ማወቃቸውን ያመለክታል። የዚህን ትርጉም በትርጉምህ ውስጥ በግልጽ ማስቀመጥ ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “በዚህ መንገድ መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር የገባውን ቃል በሙሉ እንደሚያደርግልን እያወቅን በተስፋ እንድንጠባበቅ ያበረታናል።” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ጳውሎስን ይወክላል (“እኔ” የሚለው አመልካች ጳውሎስን ይወክላል)
እዚህ ላይ “መገረዝ” የሚለው አይሁድን የሚወክል ምትክ ስም ነው። ይህን በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “ኢየሱስ ክርስቶስ የአይሁድ አገልጋይ ሆነ” (ምትክ ስም እና ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ ክርስቶስ የመገረዝ አገልጋይ የሆነበት ሁለት ዓላማዎች ወይም ምክንያቶች ናቸው። አማራጭ ትርጉም፡- “የተስፋ ቃሉን ያረጋግጥ ዘንድ … አሕዛብም ስለ ምሕረቱ እግዚአብሔርን እንዲያከብሩት”
እዚህ ላይ “አባቶች” የሚለው የአይሑድ ሕዝቦችን አባቶች ያመለክታል። ይህንን በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር ለአይሁድ ሕዝቦች አባቶች የሰጠውን የተስፋ ቃል” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለጸ መረጃ እና ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “አንድ ሰው በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ ብሎ እንደጻፈው” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ለስምህ” የሚለው እግዚአብሔርን የሚወክል ምትክ ስም ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “ለአንተ ምስጋናን እዘምራለሁ” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
“ደግሞም መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል”
ይህ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ያመለከታል። ይህን በትርጉሙ ውስጥ ግልጽ አድርጎ ማስቀመጥ ይቻላል። አማራጭ ትርጉም፡- “ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“ጌታን አመስግኑ”
እሴይ የንጉሥ ዳዊት የስጋ አባት ነበር። አማራጭ ትርጉም፡- “የእሴይ ዘር” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “እርሱ” የሚለው የእሴይን ልጅ የሆነውን መሲሑን ያመለክታል። አይሁድ ያልሆኑ ሰዎችም ቃሉን እንዲፈጽም እርሱን ያምኑታል። አማራጭ ትርጉም፡- “አይሁድ ያልሆኑትም ቃል የገባውን እንዲፈጽም እርሱን ያምኑታል” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ጳውሎስ እዚህ ላይ ለንግግሩ አጽንዖት ለመስጠት ግነትን ይጠቀማል። አማራጭ ትርጉም፡- “በታላቅ ደስታና ሰላም ይሙላችሁ” (ግነት እና ጅምላ ፍረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ጳውሎስ በሮም ያሉ አማኞች እግዚአብሔር እርሱን አሕዛብን ለመድረስ እንደመረጠው ያስታውሳቸዋል።
ጳውሎስ በሮም ያሉት አማኞች አንዱ ሌላውን በመልካም ባሕሪያቸው እያከበሩ እንደሆነ አርግጠኛ ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “እኔ ራሴ እናንተ በሌሎች ዘንድ በመልካም አካሄድ እንደሄዳችሁ እርግጠኛ ነኝ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ማለት ሌሎች አማኞችን ያመለክታል፣ ወንዶችና ሴቶችንም ያካትታል።
ጳውሎስ እዚህ ላይ ለንግግሩ አጽንዖት ለመስጠት ግነትን ይጠቀማል። አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔርን ለመከተል በሚበቃ እውቀት ተሞልታችሁ” (ግነት እና ጅምላ ፍረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ልትመካከሩ” የሚለው ማስተማርን ይወክላል። አማራጭ ትርጉም፡- “እርስ በርስ አንዱ ሌላውን ማስተማር መቻላችሁ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ጳውሎስ ጸጋን እግዚአብሔር በአካል እንደሰጠው የሚዳሰስ ስጦታ እንደሆነ አድርጎ ይናገራል። ጳውሎስ ኢየሱስን ለመከተል ከመወሰኑ በፊት ብዙ አማኞችን ያሰቃየ ቢሆንም እግዚአብሔር ሐዋርያ እንዲሆን ሹሞታል። ይህን በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ። (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ጳውሎስ ወንጌል የመስበክ ስራውን ልክ እርሱ ካህን እንደሆነና ለእግዚአብሔር መስዋዕትን እንደሚያቀርብ አድርጎ ይስለዋል። አማራጭ ትርጉም፡- “አሕዛብ እግዚአብሔርን ሲታዝዙ እርሱን እንዲያስደስቱት” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ ያለውን መንትያ አሉታዊ መግለጫ በአዎንታዊ መግለጫ መተርጎም ይቻላል። እዚህ ላይ “እነዚህ ነገሮች” የሚለው ክርስቶስ በጳውሎስ በኩል ያሳካቸውን ነገሮች ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “አሕዛብ እንዲታዝዙ፣ ክርስቶስ ብቻ በእኔ በኩል በቃሌና በስራዬ ፣ በምልክትና በድንቅ ነገር ኃይል በመንፈስ ቅዱስም ኃይል ያደረገውን ነገር እናገራለሁ” (መንትያ አሉታዎች እና ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ ሁለት ነገሮች ተመሳሳይ ትርጉምን የያዙ ሲሆን የተለያዩ ተዓምራትን ያመለክታሉ። (ጥምር ቃል የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ከኢየሩሳሌም ከተማ ከጣልያን ቅርብ ርቀት ላይ እስካለችው እስከ እልዋሪቆን ግዛት ድረስ ነው።
ጳውሎስ ወንጌልን መስበክ የሚፈልገው ስለ ክርስቶስ በጭራሽ ሰምተው ለማያውቁ ሰዎች ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “በዚህም ምክንያት ሰዎች ስለ ክርስቶስ ሰምተው በማያውቁበት ቦታ የምስራቹን መስበክ እፈልጋለሁ።” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ጳውሎስ አገልግሎቱ በመሰረት ላይ ቤትን የመገንባት ዓይነት እንደሆነ ይናገራል። አማራጭ ትርጉም፡- “ሌላ ሰው የጀመረውን ስራ መቀጠል እንዳይሆንብኝ። ሌላ ሰው በሰራው መሰረት ላይ ቤትን እንደሚገነባ ሰው መሆን አልፈልግም።” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ ጳውሎስ ኢሳይያስ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የጻፈውን ያነሳል። ይህን በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ፣ እንዲሁም ትርጉሙን በግልጽ ማስቀመጥ ይቻላል። አማራጭ ትርጉም፡- “እየተከሰተ ያለው ኢሳይያስ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንደጻፈው ነው” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ እና ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ ጳውሎስ “ዜናው” ወይም የክርስቶስ መልዕክት ሕያው እንደሆነና በራሱ እንደሚንቀሳቀስ አድርጎ ስሎታል። አማራጭ ትርጉም፡- “ማንም ሰው ስለ እርሱ ዜናውን ላልነገራቸው ሰዎች” (ሰውኛ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
ጳውሎስ በሮም ላሉ አማኞች እነርሱን ለመጎብኘት ስላለው የግል ሃሳብ ይነግራቸዋል፣ እንዲሁም አማኞቹን እንዲጸልዩ ይነግራቸዋል።
ይህን በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “ከለከሉኝ” ወይም “ሕዝቡ ከለከሉኝ” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
ጳውሎስ እዚህ ላይ ለማለት የፈለገው በነዚህ ስፍራዎች ሰዎች ስለ ክርስቶስ ያልሰሙበት ቦታ የለም ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “በእነዚህ ቦታዎች ሰዎች ስለ ክርስቶስ ያልሰሙበት ስፍራ የለም” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ጳውሎስ ሊጎበኘው የሚፈልግ ከሮም በስተሜን የሚገኝ የሮማ ግዛት ነው። (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል እና የማይታወቁትን መተርጎም የሚለውን ይመልከቱ)
“በሮም ሳልፍ” ወይም “በመንገድ ላይ ሳለሁ”
እዚህ ላይ ጳውሎስ ማለት የፈለገው በሮም ያሉት አማኞች እርሱ ወደ ስፔን በሚያደርገው ጉዞ የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉለት እንደሚፈልግ ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “በጉዞዬ እንድትረዱኝ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለጸ መረጃ እና ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“ከእናንተ ጋር ጊዜ በማሳለፌ ተደስቼ” ወይም “እናንተን በመጎብኘቴ ተደስቼ”
እዚህ ላይ “መቄዶንያ” እና “አካይያ” የሚሉት ቃላት በዚያ አካባቢ የሚኖሩትን ሕዝቦች የሚወክሉ ወካይ ስሞች ናቸው። አማራጭ ትርጉም፡- “በመቄዶንያና በአካይያ ግዛቶች የሚኖሩ አማኞች … ወድደዋልና” (ወካይ የሚለውን ይመልከቱ)
“በመቄዶንያና በአካይያ የሚገኙ አማኞች (በመርዳታቸው) ደስተኞች ነበሩ”
ጳውሎስ እዚህ ላይ ወደ ኢየሩሳሌም እየወሰደ ያለውን የተሰበሰበውን ገንዘብ ልክ ለእነርሱ እንደተሰበሰበ እንደ ፍራፍሬ አድርጎ ይስለዋል። አማራጭ ትርጉም፡- “ይህንን ስጦታ ለእነርሱ በአግባቡ አስረክቤ” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ሃረግ ክርስቶስ ጳውሎስንና የሮሜ አማኞችን ይባርካል ማለት ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “ስጎበኛችሁም፣ ክርስቶስ አትረፍርፎ እንደሚባርከን አውቃለሁ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ጳውሎስ ይተማመንባቸው ስለነበረው ስለ መልካም ነገሮች (ሮሜ 15:29) ማውራት አቁሞ ሊጋፈጣቸው ስላሉት ነገሮች ማውራት መጀመሩን የሚያሳይ ነው። ቋንቋችሁ ይሄንን የማሳያ መንገድ ካለው እዚህ ላይ ጥቅም ላይ አውሉት።
“አበረታታችኋለሁ”
ይህ ሌሎች ክርስቲያኖችን ያመለክታል፣ ሴቶችንና ወንዶችን ያካትታል
“በርትታችሁ እንድትሰሩ” ወይም “እንድትታገሉ”
ይህ በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መጻፍ ይችላል። አማራጭ ትርጉም፡- “ከማይታዘዙት እግዚአብሔር ያድነኝ ዘንድ” ወይም “የማይታዘዙት እንዳይጎዱኝ እግዚአብሔር ከእነርሱ ያድነኝ ዘንድ” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም ያሉ አማኞች ከመቄዶንያና ከአካይያ አማኞች ይዞ የመጣውን ገንዘብ በደስታ እንዲቀበሉት ያለውን ፍላጎት ያሳያል። አማራጭ ትርጉም፡- “የምወስድላቸውን ገንዘብ በኢየሩሳሌም ያሉ አማኞች በደስታ እንዲቀበሉኝ ጸልዩ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“የሰላም አምላክ” ማለት አማኞች ውስጣዊ ሰላምን እንዲኖራቸው የሚያደርግ አምላክ ማለት ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር ሁላችንም የውስጥ ሰላም እንዲኖረን እንዲያደርግ እጸልያለሁ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
1 በክንክራኦስ ያለችው ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆነችውን እህታችንን ፌበንን 2 በጌታ እንድትቀበሏት አደራ ሰጥቻችኋለሁ። ይህንንም ከአማኞች በሚጠበቅ መልኩ አድርጉት፣ የእናንተን እርዳታ በምትፈልግበት በማንኛውም ነገር ከጎኗ ቁሙ። ምክንያቱም እርሷ እራሷ እኔን ጨምሮ ብዙዎችን የምትርዳ ነች። 3 በክርስቶስ የአግልግሎቴ አጋሮች ለሆኑት ለአቂላና ለጵርስቅላ ሠላምታ አቅርቡልኝ፥ 4 እነርሱ ስለእኔ ህይወታቸውን ለአደጋ ያጋለጡ ናቸው። አመሰግናቸዋለሁ፥ እኔ ብቻ ሳልሆን የአህዛብ አብያተክርስቲያናትም ሁሉ ያመስግኗቸዋል። 5 በቤታቸው ላለች ቤተክርስቲያን ሠላምታ አቅርቡልኝ። በእስያ ለክርስቶስ የመጀምሪያው ፍሬዬ የሆነውን የምወደውን አጤኔጦንን ሠላም በሉልኝ። 6 ለእናንተ በሥራ ለደከመችው ለማሪያ ሠላምታ አቅርቡልኝ። 7 ዘመዶቼ ለሆኑትና አብረውኝ ታስረው ለነበሩት ለአንዲራኒቆንና ለዩልያን ሠላምታ አቅርቡልኝ። እነርሱ በክርስቶስ በመሆን የቀደሙኝና ከሐዋሪያት መካከል በመልካም የተመሰከረላቸው ናቸው። 8 በጌታ ለምወደው ለጵልያጦን ሠላምታ አቅርቡልኝ። 9 በክርስቶስ አብሮን የሚሠራውን ኢሩባኖንና የተወደደውን ስንጣክን ሠላም በሉልኝ። 10 በክርስቶስ መሆኑ ለተመሰከረለት ለኤጤሌን ሠላምታ አቅርቡልኝ። የአርስጣባሉን ቤተሰቦች ሠላም በሉልኝ። 11 ለዘመዴ ለሄሮድዮና ሠላምታ አቅርቡልኝ። ከንርቀሱ ቤተሰቦች መካከል በጌታ ላመኑት ሠላምታ አቅርቡልኝ። 12 በጌታ ሥራ ለሚደክሙት ለፕሮፊሞንና ለጢሮፊሞስ ሠላምታ አቅርቡልኝ። በጌታ ሥራ በብዙ የምትደክመውን የተወደደች ጠርሲዳን ሠላም በሉልኝ። 13 በጌታ ልተመረጠው ለሩፎን እና ለእርሱም ለእኔም እናት ለሆነችው ለእናቱ ሠላምታ አቅርቡልኝ። 14 አስቀራጦንን፥ አፍለሶንጳን፥ ሄሮሜንን፥ ጳጥሮባን፥ ሄርማንን እንዲሁም አብረዋቸው ያሉትን ወንድምች ሠላም በሉልኝ። 15 ለፍሌጎን፥ ለዩልያ፥ ለኔርያ ለእህቱም ለአልንጦን አብረዋቸውም ላሉት በጌታ ላመኑት ሁሉ ሠላምታ አቅርቡልኝ። 16 በተቀደሰ መሳሳም ሠላምታ ተለዋወጡ። የክርስቶስ አብያተክርስቲያናት ሁሉ ሠላምታ ያቀርቡላችኋል። 17 ወንድሞቼ ሆይ በመካከላችሁ የመለያየትንና የመሰናክል ምክንያት ስለሆኑት ሰዎች እንድታስቡ እለምናችኋለሁ። እነርሱ እናንተ ከተማራችሁት የወጣ ነገር ያስተምራሉና ከእነርሱ ተለዩ። 18 እንደነዚህ ያሉ ሰዎች የገዛ ሆዳቸውን እንጂ ክርስቶስን ጌታችንን አያገለግሉም። በለስላሳና በሚያባብል ቃላቸው የየዋሀንን ልብ ያታልላሉ። 19 የመታዘዛችሁ ምሳሌነታችሁ ለብዙዎች ደርሷል። ስለዚህም በእናንተ ደስ ይለኛል፥ ነገር ግን ለመልካም ነገር ጥበበኞች ለክፉ ነገር ደግሞ የዋሀን እንድትሆኑ እፈልጋለሁ። 20 የሠላም አምላክ ሠይጣንን በፍጥነት ከእግራችሁ በታች ይቀጠቅጠዋል። የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሠላም ከሁላችሁ ጋር ይሁን። 21 የሥራ አጋሬ ጢሞቴዎስና ዘመዶቼ ለቂዮስ፥ኢያሶንና ሱሲጴጥሮስ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። 22 ይህን ደብዳቤ በእጄ የጻፍኩ እኔ ጤርጥዮስ ሰላምታ አቀርብላችኋለሁ። 23 እኔና ቤተክርስቲያንን በሙሉ በቤቱ ያስተናገደን ጋይዮስ ሰላምታ ያቀርብላችኋል። የከተማው ገንዘብ ያዥ ኤርስጦስ ወንድማችንም ቁአስጥሮስ ሰላም ብለዋችኋል። 25 እንግዲህ በወንጌሌ በኢየሱስ ክርስቶስም ስብከት ከቀድሞ ዘመን ጀምሮ ተሰውሮ በነበረውና 26 አሁን ግን በዘላለማዊ አምላክ ትዕዛዝ በአህዛብ ሁሉ መካከል በተገለጠውና የእምነት መታዘዝ እንዲገኝ በትንቢታዊ መጽሀፍት አማካኝነት በታወቀው ሚስጥር መሠረት ሊያቆማችሁ ለሚችለው 27 ብቻውን ጥበበኛ አምላክ ለሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ለዘላለም ክብር ይሁን። አሜን።
ከዚህ በኋላ ጳውሎስ በሮሜ ያሉት አማኞችን ብዙዎቹን ስማቸውን እየጠራ ሰላምታን ያቀርባል።
“ፌበንን እንድታከብሯት እፈልጋለሁ”
ይህ የአንዲት ሴት ስም ነው። (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል እና የማይታወቁትን ተርጉም የሚለውን ይመልከቱ)
“እኅታችንን” የሚለው ቃል ውስጥ ያለው የባለቤት አመልካች “እኛ” ጳውሎስንና ሌሎች ሁሉንም አማኞች ይወክላል። አማራጭ ትርጉም፡- “በክርስቶስ እህታችን” (አካታች “እኛ” የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ በግሪክ የሚገኝ የወደብ ከተማ ነው። (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል እና የማይታወቁትን ተርጉም የሚለውን ይመልከቱ)
ጳውሎስ በሮሜ የሚገኙ አማኞች ፌበንን እንደ አጋር አማኝ እንዲቀበሏት ያበረታታቸዋል። አማራጭ ትርጉም፡- “ተቀበሏት፣ ምክንያቱም ሁላችንም የጌታ ነንና“ (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“አማኞች ሌሎች አማኞችን መቀበል ባለባቸው መንገድ”
ጳውሎስ የሮሜን አማኞች ለፌበን የሚያስፈልጋትን ነገር በሙሉ እንዲሰጧት ያበረታታቸዋል። አማራጭ ትርጉም፡- “የሚያስፈልጋትን ሁሉ በመስጠት እርዷት” (ለስላሴ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“ብዙ ሰዎችን ረድታለች፣ እንዲሁም እኔንም ረድታኛለች”
ጵርስቅላ የአቂላ ሚስት ነበረች። (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
ከጳውሎስ ጋር “አብረው የሚሰሩት” ለሰዎች ስለ ኢየሱስ የሚሰብኩ ሰዎች ናቸው። አማራጭ ትርጉም፡- “ስለ ክርስቶሰ ኢየሱስ ለሰዎች በመንገር አብረውኝ የሚሰሩ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የአንዲት ሴት ስም ነው። (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ የወንዶች ስሞች ናቸው። (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ሊሆን የሚችለው 1. ዩልያ፥ የሴት ስም ወይም 2. ዩልያን፥ የወንድ ስም (ይህ የወንድ ስም የመሆን ዕድሉ ዝቅተኛ ነው) (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
ይህን በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “ሐዋርያቱ በደንብ ያውቋቸው የነበሩ” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“የተወደደው ጓደኛዬ እንዲሁም አጋር አማኝ”
እነዚህ የወንዶች ስሞች ናቸው። (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
“የተረጋገጠለት” የሚለው ቃል ተፈትኖ ትክክለኛ መሆኑ የተረጋገጠን ሰው ያመለክታል። አማራጭ ትርጉም፡- “ክርስቶስ እምነቱን ላረጋገጠለት”
ይህ በኢየሱስ የሚታመኑን ያመለክታል። አማራጭ ትርጉም፡- “አማኞች የሆኑትን” ወይም “የጌታ የሆኑትን” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ የሴቶች ስሞች ናቸው። (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል እና የማይታወቁትን ተርጉም የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ የወንዶች ስሞች ናቸው። (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል እና የማይታወቁትን ተርጉም የሚለውን ይመልከቱ)
ይህን በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “ጌታ የመረጣቸው” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ የወንድ ስሞች ናቸው። (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል እና የማይታወቁትን ተርጉም የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ የአንዲት ሴት ስም ነው። ዩልያ የፍሌጎን ሚስት ልትሆን ትችላለች። (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል እና የማይታወቁትን ተርጉም የሚለውን ይመልከቱ)
ለሌሎች አማኞች ፍቅርን የመግለጫ መንገድ ነው
ጳውሎስ እዚህ ላይ በጠቅላላው ስለ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያናት ይናገራል። አማራጭ ትርጉም፡- “በዚህ አካባቢ ያሉ አብያተክርስቲያናት ውስጥ ያሉ አማኞች በሙሉ ሰላምታን ያቀርቡላችኋል” (ግነት እና ጅምላ ፍረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
ጳውሎስ ለአማኞች ስለ አንድነትና ለእግዚአብሔር ስለመኖር አንድ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ይሰጣል።
ይህ ሌሎች ክርስቲያኖችን ሲያመለክት፣ ወንዶችና ሴቶችን ያካትታል
“እንድትጠነቀቁ”
ይህ የሚያመለክተው ክርክርን የሚፈጥሩ ሰዎችንና፣ ሌሎችን በኢየሱስ እንዳያምኑ ምክንያት የሚሆኑትን ሰዎች ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “አማኞች እርስ በርስ እንዲከራከሩና በእግዚአብሔር እምነት እንዳይኖራቸው የሚያደርጉ” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
“እናንተ ከተማራችሁት እውነት ጋር የማይስማማ ትምህርት ያስተምራሉ”
“ራቁ” ማለት “አትስሟቸው” የሚለውን ትርጉም የያዘ ዘይቤ ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “አታዳምጧቸው” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“ያገለግላሉ” የሚለው ቃል ከላይ ካለ ሐረግ አገባብ ትርጉሙን መረዳት ይቻላል። ይህ በተለይ አረፍተ ሃሳብ መገለጽ ይችላል። አማራጭ ትርጉም፡- “ይልቁንም የራሳችውን ሆድ ነው የሚያገለግሉት” (አስጨምሬ የሚለውን ይመልከቱ)
“ሆድ” የሚለው ቃል የአካላዊ ፍላጎቶችን የሚያሳይ ምትክ ስም ነው። የገዛ ሆዳቸውን ማገልገል ማለት ፍላጎቶቻቸውን ማግኘት ማለት ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “ነገር ግን የራሳቸውን ራስ ወዳድ የሆኑ ፍላጎቶች ብቻ ማግኘት ነው የሚፈልጉት” (ምትክ ስም እና ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“ለስላሳ” እና “መልካም” የሚሉት ቃላት ተመሳሳይ ትርጉም አላችው። ጳውሎስ እነዚህ ሰዎች እንዴት አማኞችን እያታለሉ እንደሆነ አጽንዖት ይሰጣል። አማራጭ ትርጉም፡- “መልካምና እውነት የሚመስሉ ነገሮችን በመናገር” (ጥምር ቃል የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ልብ” የሚለው የአንድን ሰው አእምሮ ወይም ውስጣዊ ማንነት የሚወክል ምትክ ስም ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “ንጹሃን አማኞችን ያታልላሉ” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ገር፣ ብዙ የማያውቁና የዋህ አማኞችን ያመለክታል። አማራጭ ትርጉም፡- “በየዋህነት የሚያምኗቸውን” ወይም “እነዚህ አስተማሪዎች እያታለሏቸው እንደሆነ የማያውቁትን”
እዚህ ላይ ጳውሎ ስለ ሮሜ አማኞች ታዛዥነት ስናገር ታዛዠነታቸው ሰው እንደሆነና ወደ ሌሎች ሰዎች የሚሄድ እንደሆነ አድርጎ ገልጾታል። አማራጭ ትርጉም፡- “ኢየሱስን እንዴት እንደምትታዘዙ ሁሉም ሰው ሰምቷልና” (ሰውኛ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“ከእግራችሁ ስር ይቀጠቅጠዋል” የሚለው ሐረግ በጠላት ላይ ያለን ሙሉ ድል መንሳት ይወክላል። እዚህ ላይ ጳውሎስ በሰይጣን ላይ ያለውን ድል የሮሜ አማኞች ጠላቶቻቸውን በእግራቸው ስር እንደሚቀጠቅጡ አድርጎ ይስለዋል። አማራጭ ትርጉም፡- “ፈጥኖም እግዚአብሔር ሰላምና በጠላትም ላይ ፍጹም ድልን ይሰጣችኋል” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“ክፋትን ነገሮች የማትሰሩ እንድትሆኑ”
ጳውሎስ ከእርሱ ጋር ካሉት አማኞች ሰላምታን ያቀርባል።
እነዚህ የወንዶች ስሞች ናቸው። (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
ጤርጥዮስ ጳውሎስ የሚናገረውን በጽሑፍ ያሰፍር የነበረው ሰው ነው። (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
እነዚህ የወንዶች ስሞች ናቸው። (ስሞችን እንዴት መተርጎም ይቻላል የሚለውን ይመልከቱ)
ይህ ጳውሎስና ሌሎች አማኞች ለአምልኮ የሚሰበሰቡበት ቤት ባለቤት የሆነውን ሰው ጋይዮስን ያመለክታል።
ይህ ሰው የአንድ ቡድን ገንዘብ የሚይዝ ሰው ነው።
ጳውሎስ መልዕክቱን በበረከት ጸሎት ይዘጋል።
እዚህ ላይ “እንግዲህ” የሚለው ቃል የደብዳቤውን መጨረሻ ክፍል ያመለክታል። ይህን በራሳችሁ ቋንቋ መግለጽ የምትችሉ ከሆነ እሱን መጠቀም ይቻላል።
ጳውሎስ እዚህ ላይ ጠንካራ እምነት መኖርን ልክ ከመውደቅ ይልቅ እንደመቆም አድርጎ ይስለዋል። አማራጭ ትርጉም፡- “እምነታችሁን ለማበርታት” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
“ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሰበክሁት እንደ የምስራቹ ቃል”
ጳውሎስ እግዚአብሔር ቀድመው ተሰውረው የቆዩ ነገሮችን ለአማኞች እንደገለጠ ይናገራል። እነዚህ ነገሮች ሚስጥር እንደነበሩ አድርጎ ይናገራል። ይህን በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “ምክንያቱም እግዚአብሔር ለእኛ ለአማኞች ለረጅም ጊዜ ሚስጥር ሆኖ የጠበቀውን ነገር ስለገለጠልን” (ተለዋጭ ዘይቤ እና ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
“ተገልጧል” እና “እንዲታወቅ ሆኗል” የሚሉት ቃላት ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው። ጳውሎስ ሁለቱንም የሚጠቀመው አጽንዖት ለመስጠት ነው። እነዚህን ቃላት አንድ ላይ በማድረግ በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “አሁን ግን ዘላለማዊው እግዚአብሔር በነቢያቱ ጽሁፍ አማካይነት ለሕዝብ ሁሉ እንዲታወቅ አድርጓል” (ጥምር ቃል እና ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “መታዘዝ” እና “እምነት” የሚሉት ቃላት ረቂቅ ስሞች ናቸው። “ታዛዥነት” እና “መታመን” የሚሉትን በትርጉምህ ላይ መጠቀም ትችላለህ። አማራጭ ትርጉም፡- “ሕዝብ ሁሉ እግዚአብሔርን ስለሚታመኑት እንዲታዘዙት” (ረቂቅ ስሞች እና ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “በክርስቶስ ኢየሱስ” የሚለው ኢየሱስ የሰራውን ስራ ያመለክታል። “ክብር” ይሁን ማለት እግዚአብሔርን ማመስገን ማለት ነው። አማራጭ ትርጉም፡- “ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ በሰራው ስራ ምክንያት፣ ብቻውን አምላክና ብቻውን ጥበበኛ የሆነውን እግዚአብሔርን ለዘላለም እናመሰግናለን። (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለፀ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)
1 በእግዚአብሔር ፈቃድ ሐዋርያ ሊሆን በክርስቶስ ኢየሱስ የተጠራ ጳውሎስና ወንድማችን ሶስቴንስ በቆሮንቶስ ላለች ለእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን፤ በክርስቶስ ኢየሱስ ለተቀደሱት። 2 የእነርሱና የእኛ ጌታ የሆነውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በየስፍራው ከሚጠሩት ሁሉ ጋር ቅዱሳን ለመሆን ለተጠሩት ደግሞ እንጽፍላቸዋለን። 3 ከአባታችን ከእግዚአብሔር ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን። 4 ክርስቶስ ኢየሱስ ከሰጣችሁ ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሳ ሁልጊዜ ስለእናንተ አምላኬን አመሰግናለሁ። 5 በነገር ሁሉ፤በንግግርና በዕውቀት ሁሉ ባለጸጋ እንድትሆኑ አድርጎአችኋልና። 6 ስለክርስቶስ የተሰጠው ምስክርነት በመካከላችሁ እውነት ሆኖ እንደጸና ሁሉ ባለጸጎች አድርጎአችኋል። 7 ስለዚህ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መገለጥ በጉጉት ስትጠባበቁ አንድም መንፈሳዊ ስጦታ አይጎድልባችሁም። 8 እርሱ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ያለ ነቀፋ እንድትሆኑ እስከ ፍጻሜ ድረስ ያጸናችኋል። 9 ወደ ልጁ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችሁ እግዚአብሔር የታመነ ነው። 10 ስለዚህ ወንድሞችና እህቶች ሆይ፤ ሁላችሁም በአንድ አሳብ እንድትስማሙ እንጂ በመካከላችሁ መለያየት እንዳይሆን በጌታችን በኢየሱስ ድርስቶስ ስም አሳስባችኋለሁ። እንዲሁም በአንድ ልብና በአንድ ዓለማ የተባበራችሁ እንድትሆኑ አሳስባችኋለሁ። 11 በመካከላችሁ መከፋፈል እንደተፈጠረ የቀሎዔ ቤተ ሰዎች አስታውቀውኛል። 12 ይህን የምላችሁ፦ እያንዳንዳችሁ፦ "እኔ ከጳውሎስ ጋር ነኝ፥ ወይም ከአጵሎስ ጋር ነኝ፤ ወይም እኔ ከኬፋ ጋር ነኝ፤ ወይም እኔ ከክርቶስ ጋር ነኝ" ትላላችሁ። 13 ለመሆኑ ክርስቶስ ተከፍሎአልን? ጳውሎስስ ስለ እናንተ ተሰቅሎአልን? ወይም የተጠመቃችሁት በጳውሎስስ ስም ነውን? 14 ከቀርስጶስና ከጋይዮስ በቀር ማናችሁንም ስላላጠመቅሁ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ። 15 ስለዚህ ማናችሁም በእኔ ስም እንደተጠመቃችሁ ለመናገር አትችሉም። (የእስጢፋኖስን ቤተ ሰብ ደግሞ አጥምቄአለሁ። 16 ከዚህ ውጪ ሌላ ማንን አጥምቄ እንደሆነ አላውቅም።) 17 ክርስቶስ ወንጌልን እንድሰብክ እንጂ እንዳጥምቅ አላከኝም። በሰው ጥበብ እንድሰብክ አልላከኝም፤ እንዲሁም የክርስቶስ መስቀል ኃይሉ ከንቱ መሆን ስለሌለበት በሰው የንግግር ጥበብ አልሰብክም ። 18 ስለመስቀሉ ያለው መልእክት ለሚጠፉት ሞኝነት፤ ነገር ግን ለምንድን ለእኛ የእግዚአብሔር ኃይል ነው። 19 "የጥበበኖችን ጥበብ አጠፋለሁ፤ የአስተዋዮችንም ማስተዋል ከንቱ አደርጋለሁ" ተብሎ ተጽፎአልና። 20 ጥበበኛ ሰው የት አለ? ፈላስፋስ የት አለ? የዚህ ዓለም መርማሪስ የት አለ? እግዚአብሔር የዚህን ዓለም ጥበብ ሞኝነት እንዲሆን አላደረገምን? 21 ዓለም በጥበብዋ እግዚአብሔርን ስላላወቀች በስብከት ሞኝነት የሚያምኑትን ሊያድን የእግዚአብሔር ፈቃድ ሆኖአል። 22 አይሁድ ታዓምራትን ይፈልጋሉ፤ የግሪክ ሰዎችም ጥበብን ይሻሉ። 23 እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን። ይህም ለአይሁድ ማሰናከያ ለግሪክ ሰዎችም ሞኝነት ነው። 24 ነገር ግን እግዚአብሔር ለጠራቸው ለአይሁዶችም ሆነ ለግሪክ ሰዎች የእግዚአብሔር ኃይልና ጥበብ የሆነውን ክርስቶስን እንሰብካለን። 25 ምክንያቱም የእግዚአብሔር ሞኝነት የሚመስለው ነገር ከሰዎች ጥበብ ይበልጣል፤ እንዲሁም የእግዚአብሔር ድካም የሚመስለው ነገር ከሰዎች ብርታት ይበልጣል። 26 ወንድሞችና እህቶች ሆይ፤ በእናንተ ያለውን የእግዚአብሔርን ጥሪ ተመልከቱ። ብዙዎቻችሁ በሰው መስፈርት ጥበበኞች አልነበራችሁም። ብዙዎቻችሁ ኃያላን አልነበራችሁም፤ ብዙዎቻችሁም ከመሳፍንት አልነበራችሁም። 27 ነገር ግን እግዚአብሔር ጥበበኞችን ያሳፍር ዘንድ የዓለምን ሞኝ ነገር መረጠ። ብርቱንም ነገር ለማሳፈር የዓለምን ደካማ ነገር መረጠ። 28 ዓለም እንደ ከበረ ነገር የምትቆጥረውን ከንቱ ለማድረግ እግዚአብሔ የዓለምን ምናምንቴ ነገር መረጠ። የተናቀውንና ያልሆነውን ነገር መረጠ። 29 ይህን ያደረገው ማንም ሰው በእግዚአብሔር ፊት ለመመካት ምክንያት እንዳይኖረው ነው። 30 በክርስቶስ ኢየሱስ ለመሆን የበቃችሁት ከእግዚአብሔር ሥራ የተነሳ ነው፤ እርሱም ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበባችን፤ጽድቃችንና ቅድስናችን ቤዛችንም ሆኖአልና። 31 እንግዲህ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ ፦"የሚመካ በጌታ ይመካ" ነው።
ወንድማችን ሶስቴንስ ጳውሎስና የቆሮንቶስ ሰዎች ሶስቴንስን እንደሚያውቁ ይጠቁማል። ትኩረት፦ "ሶስቴንስ እናንተና እኔ የምናውቀው ወንድም።
ቅዱሳን ለመሆን የተጠሩት ሰዎች ትኩረት፦ «እግዚአብሔር ቅዱስ ሕዝብ እንዲሆኑ ጠርቶአቸዋል።»
የእነርሱና የእኛ ጌታ ኢየሱስ የጳውሎስና የቆሮንቶስ ሰዎች ጌታ ነው፤ እንዲሁም የሁሉም አብያተ ክርስቲያናት አንዱ ጌታ ነው። ለእናንተ «እናንተ» የሚለው ቃል በቆሮንቶስ ያሉትን ምእመናንን ያመለክታል።
ክርስቶስ ኢየሱስ የሰጣችሁ የእግዚአብሔር ጸጋ «በክርስቶስ ላላችሁ እግዚአብሔር የሰጣችሁ ጸጋ» ባለጸጋ አድርጎአችኋል ትርጉም ሊሆኑ የችሉ 1) «ክርስቶስ ባለጸጋ አድርጎአችኋል።» ወይም 2) «እግዚአብሔር ባለጸጋ አድርጎአችኋል።» በየስፍራው ባለጸጋ አድርጎአችኋል «በብዙ መንፈሳዊ በረከቶች ባለጸጋ አድርጎአችኋል» በንግግር ሁሉ እግዚአብሔር ለሌሎች ስለ እግዚአብሔር መልእክት በብዙ መንገድ እንድትናገሩ አስችሎአችኋል በዕውቀት ሁሉ እግዚአብሔር የእርሱን መልእክት በብዙ መንገድ እንድትረዱ አስችሎአችኋል። ስለ ክርስቶስ ምስክርነት «ስለ ክርስቶስ መልእክት» በመካከላችሁ እውነትን አረጋገጠ ትኩረት፦ « ሕይወታችሁን በግልጽ ለውጦአል።»
ስለዚህ «ከዚህ የተነሣ» ከመንፈሳዊ ስጦታ አልጎደለባችሁም «ማንኛውም መንፈሳዊ ስጦታ ይኑርባችሁ» የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መገለጥ አማራጭ ትርጉሞች 1) « እግዚአብሔር ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን የሚገልጥበት ጊዜ።» 2) «ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን በሚገልጥበት ጊዜ።» ነውር የሌለባችሁ ትሆናላችሁ እግዚአብሔር እናንተን የሚነቅፍበት ምክንያት ያለም ወደ ልጁ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችሁ እግዚአብሔር የታመነ ነው። እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አዲስ ሕይወት እንድትካፈሉ ጠርቶአችኋል።
ሁላችሁ የምትስማሙበት «እርስ በርሳችሁ በስምምነት ትኖራላችሁ» በመካከላችሁ መከፋፈል እንዳይኖር «በመካከላችሁ በተለያየ ቡድን መከፋፈል የለባችሁም።» በአንድ አሳብና በአንድ ዓላማ የተሳሰራችሁ ሁኑ « በኅብረት ኑሩ» የቀሎዔ ሰዎች ይህ ቀሎዓ የተባለች ሴት የምትመራው ቤተ ሰብ፥ የቤተ ሰብ አባላት፥ አገልጋዮችና ሌሎችንም የሚያመለክተው ነው። በመካከላችሁ ክፍፍሎች እየተፈጠሩ ናቸው። «እርስ በርሳችሁ የምትጣላሉ ቡድኖች ናችሁ።»
እያንዳንዳችሁ ትላላችሁ ጳውሎስ በአጠቃላይ ስለ ክፍፍል እየገለጸ ነው። ክርስቶስ ተከፍሎአልን? ጳውሎስ ከአንዱ በቀር ክርስቶስ ያልተከፋፈለ የመሆኑን እውነት ለማስረዳት ይፈልጋል። «እናንት በምትፈጉበት ሁኔታ ክርስቶስን መከፋፈል አይቻልም።» ጳውሎስ ተሰቅሎአልን? ጳውሎስ የተሰቀለው ጳውሎስ ወይም አጵሎስ ሳይሆን ክርስቶስ ብቻ እንደሆን ለማስረዳት ይፈልጋል። «በመስቀል ላይ ጳውሎስን ለእናንተ ድነት አልሰቀሉትም።»
በጳውሎስ ስም ተጠመቃችሁን? ጳውሎስ ለማስረዳት የፈለገው ሁላችን በክርስቶስ ስም እንደተመቅን ነው። «ሰዎች በጳውሎስ ስም አላጠቁም።» (ተመልከት፦
እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ ጳውሎስ በቆሮንቶስ ማንንም አለማጥመቁን ምን ያህል ትልቅ ሰው እንደሆን አጋኖ ይናገራል።
ቀርስጶስ የአይሁድ ምኩራብ አለቃ የነበረና ወደ ክርስትና የመጣ።
ጋይዮስ ከሐዋርያው ጳውሎስ ጋር አብሮ ተጉዞአል።
በስሜ ማናችሁም እንደተጠመቃችሁ የሚናገር ሰው እንዳይኖር ነበር «በኋላ ላይ ሰዎች እኔ እንዳጠመቅኋቸው አድርገው እንደይ ኩራሩብኝ ብዙ ሰዎችን በስሜ እንዳላጠምቅ ተከላክዬዋለሁ።»
የእስጢፋኖስ ቤተ ሰብ በእስጢፋኖስ ቤተ ሰብ ውስጥ ያሉ የቤተ ሰብ አባላትንና አገልጋዮችን የሚያሳይ ነው።
ክርስቶስ ለማጥመቅ አላከኝም ይህ ማለት ጥምቀት በጳውሎስ አገልግሎት ቅድሚያ የሚሰጠው አልነበረም። የክርስቶስ መስቀል ኃይል ከንቱ መሆን የለበትም ትኩረት፡- «የሰው ጥበብ የክርስቶስን መስቀል ኃይሉን ከንቱ ማድረግ ያለበትም።»
ስለ የመስቀል መልእክት «ስለ ስቅላት መስበክ» ወይም «ስለ ክርስቶስ በመስቀል ላይ መሞት መልእክት መስበክ ነው» (UDB) ሞኝነት ነው «ስሜት የማይሰጥ» ወይም «ከንቱ ነገር» ለሚሞቱ እዚህ ላይ «መሞት» ማለት የመንፈሳዊ ሞት ሂደትን የሚያሳይ ነው። ይህ የእግዚአብሔር ኃይል ነው «ይህ እግዚአብሔር በእኛ በኃይል የሚሠራውበት ነው።» የአስተዋዮችን ጥበብ ከንቱ አደርጋለሁ ትኩረት፦ «ዋቂ ሰዎችን ግራ እንዲጋቡ አደርጋለሁ» ወይም «የዐዋቂዎችን ዓላማ ሙሉ በሙሉ ከንቱ አደርጋለሁ።»
ጥበበኛ ሰው የት አለ? ፈላስፋስ የት አለ? የዚህ ዓለም መርማሪስ የት አለ? ጳውሎስ ሊገልጸው የፈለገው በእውነት ጥበበኛ የሆኑ ሰዎች የትም አይገኙም። ትኩረት፦ ከወንጌል ጥበብ ጋር ሲነጻጸር ጥበበኛ የሆኑ ሰዎች የሉም፤ ዐዋቂዎቹም የሉም። የዚህ ዓለም መርማሪዎቹም የሉም!" ዐዋቂ አንድ ሰው ከፍተኛ ዐውቀት እንዳለ የሚታወቅ የዚህ ዓለም መርማሪ አንድ ሰው ዐውቀት መኖሩን በክርክር ችሎታ የሚያሳምን እግዚአብሔር የዚህች ዓለም ጥበብን ሞኝነት አላደረገምን? እግዚአብሔር በዚህች ዓለም ጥበብ ላይ ያደረገውኔ ለምግለጽ የተጠቀመበት ጥያቄ ነው። ትኩረት፦ " እግዚአብሔር በርግጥ የዚህችን ዓለም ጥበብ ሞኝነት አድርጎአል" ወይም "እግዚአብሔር ያሰቡት የነበረው ሞኝነት እንደሆነ ለማሳየት ፈልጎአል። (UDB)
የሚያምኑ አማራጭ ትርጉሞች 1) «የሚያምኑ ሁሉ» (UDB) or 2) « እርሱን የሚያምኑ ሁሉ።»
እንሰብካለን «እኛ» የሚለው ቃል ጳውሎስንና ሌሎች ወንጌዋውያንን ይመለከታል። ክርስቶስ ተሰቅሎአል «ይህ በመስቀል ላይ ስለሞተው ክርስቶስ ነው።» የእንቅፋት ድንጋይ አንድ ሰው በመንገድ ላይ በድንጋይ እንቅፋት ሊሆን እንደሚሆንበት የክርስቶስ ስቅላት እንቅፋት ለአይሁድ እንቅፋት ሊሆን እንደቻለ ነው። «አይደለም» ትኩረት፦ «የሚቀበሉት አይደለም» ወይም «በጣም አስከፊ»
እግዚአብሔር ለመረጣቸው «እግዚአብሔር ለሚጠራቸው ሰዎች» ክርስቶስን እንሰብካለን «ስለክርስቶስ እናስተምራለን» ወይም «ስለ ክርስቶስ ለሰዎች ሁሉ እንናገራለን።» ክርስቶስ እንደ ኃይልና እንደ እግዚአብሔር ጥበብ ክርስቶስ እግዚአብሔር ኃይሉና ጥበቡን የሚገልጥለት ነው። የእግዚአብሔር ሞኝነት የእግዚአብሔር ድካም ይህ የእግዚአብሔርና የሰው ባሕርይ ንጽጽር ነው። የእግዚአብሔር ሞኝነት የሚመስል ወይም ድካም የሚመስል እንኳ ቢሆን ከሰው የመጨረሻ ከተሻለው ባሕርይ ጋር ሲነጻጸር የእግዚአብሔር ይበልጣል።
ለእናንተ የእግዚአብሔር ጥሪ «ቅዱሳን እንድትሆኑ እግዚአብሔር እንዴት እንደጠራችሁ» ከእናንተ ብዙዎች አልተመረጡም «ከእናንተ በጣም ጥቂቶች ብቻ»
የሰው ልማድ «የሰዎች ፍርድ" ወይም "ስለ መልካምነት የሰዎች አሳብ» ባለባት ሆኖ ስለ መወለድ «ቤተ ሰብህ አስፈላጊ ከመሆኑ የተነሣ የተለየ ነስ» ወይም «ንጉሳዊ» ጥበበኛን ለማሳፈር እግዚአብሔር የዚህ ዓለም ሞኝ ነገርን መረጠ የአይሁድ መሪዎች እነዚህ መሪዎች ከሌሎች ይልቅ ለእግዚአብሔር አስፈላጊ አይደለም ብለው የሚያምኑትን እግዚአብሔር ትሑታን ሰዎችን መረጠ።
ዝቅተኛና የተናቀ ምንድን ነው ዓለም የማትቀበላቸው ሰዎች ናቸው። ትኩረት፦ «ትሑታንና ተቀባይነት የሌላቸው ሰዎች ናቸው።» እንደ ምናምንቴ የሚቆጠሩ ሰዎች «ሁል ጊዜ ሰዎች ዋጋ እንደሌላቸው አድርገው የሚቆትሩአቸው» ዋጋ እንዳላቸው ተደርገው የሚያዙ ነገሮች «ሰዎች ዋጋ እንዳላቸው የሚቆጥሩአቸው ነገሮች» ወይም «ሰዎች ገንዘብ ወይም ክብር ይገባቸዋል ብለው ያስቡ»
እግዚአብሔር ካደረገው የተነሣ ይህ የሚያሳየው ክርስቶስ በመስቀል ላይ ያደረገውን ሥራ ነው። በእኛ የእኛ ጳውሎስ «በእኛ» በሚለው የቆሮንቶስ ሰዎችን ይጨምራል፡
እንግዲህ እናንት በክርስቶስ ኢየሱስ ናችሁ «አሁን እናንተ በክርስቶስ ኢየሱስ ድነትን ተቀብላችኋል» ክርስቶስ ኢየሱ ስለ እኛ የእግዚአብሔር ጥበብ የሆነው «ክርስቶስ አየሱስ እግዚአብሔር እንዴት ጥበበኛ እንደሆነ ግልጽ አደረገው»
የሚመካ በጌታ ይመካ «ሰው የሚመካ ከሆን ጌታ ምን ያህል ታላቅ በመሆኑ ይመካ»
1 ወንድሞችና እህቶች ሆይ፦ወደ እናንተ ስመጣ ስለ እግዚአብሔር የተሰወረውን የእውነት ምስጢር ሲሰብክላችሁ በሚያባብል የንግግር ችሎታ ወይም በላቅ ጥበብ አልመጣሁም። 2 በመካከላችሁ ሳለሁ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀርና፥ እርሱም እንደተሰቀለ ሌላ እንዳላውቅ ወስኜ ነበርና። 3 ወደ እናንተ የመጣሁት በድካምና በፍርሃት፤ እንዲሁም በብዙ መንቀጥቀጥ ነበር። 4 መልእክቴና ስብከቴም የመንፈስን ኃይል በመግለጥ እንጂ በሚያባብል የጥበብ ቃል አልነበረም፤ 5 ይህም እምነታችሁ በእግዚአብሔር ኃይል እንጂ በሰው ጥበብ ላይ እንዳይመሠረት ነው። 6 በእምነታቸው በሰሉት ሰዎች መካከል በጥበብ እንናገራለን፤ ነገር ግን የምንናገረው የዚህን ዓለም ጥበብ ወይም ከጊዜ በኋላ የሚሻሩትን የዚህን ዓለም ገዢዎች ጥበብ አይደለም። 7 ይልቁን እግዚአብሔር አስቀድሞ ከዘመናት በፊት ለክብራችን ያዘጃውን፥ ተሰውሮም የነበረውን የእግዚአብሔርን የጥበብ እውነት እንናገራለን። 8 የዚህም ዓልም ገዢዎች አንዳቸውም ይህን ጥበብ አላወቁትም፤ በዚያን ጊዜ ይህን አውቀውስ ቢሆን ኖሮ የክብርን ጌታ ባልሰቀሉትም ነበር። 9 ነገር ግን፦ "ዓይን ያላየውን፤ ጆሮም ያልሰማውን፤ በሰውም ልብ ያልታሰበውን፤ እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀውን ነገር" ተብሎ ተጽፎአልና። 10 እግዚአብሔር በመንፈሱ አማካይነት የተሰወሩትን ነገሮች ገልጦናን ። ምክንያቱም መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር ስንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራል። በሰው ውስጥ ካለው ከእርሱ መንፈስ በቀር የሰውን አሳብ የሚያውቅ ማን ነው? 11 እንዲሁም ከእግዚአብሔር መንፈስ በቀር የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር የሚያውቅ ማንም የለም። 12 እኛ ግን ክእግዚአብሔር በነፃ የተሰጠንን እንድናውቅ ከእግዚአብሔር የሆነውን መንፈስ እንጂ የዓለምን መንፈስ አልተቀበለንም። 13 የሰው ጥበብ ሊያስተምር የማይችለውን ነገር ግን የእግዚአብሔር መንፈስ የሚያስተምረውን ስለ እነዚህ ነገሮች በቃላት እንናገራለን። መንፈስ ቅዱስም መንፈሳዊውን ቃላት በመንፈሳዊ ጥበብ ይገልጥልናል። 14 የእግዚአብሔር መንፈስ የሌለው ሰው የእግዚአብሔር መንፈስ ነገር ሞኝነት ስለሚሆንበት አይቀበለውም ። በመንፈስም የሚመረመር ስለሆነ ሊያውቀው አይችልም። 15 የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት ሰው ሁሉን ይመረምራል፤ እርሱ ግን በማንም አይመረመርም። 16 "የጌታን አሳብ ማን አወቀው፤ ማንስ ሊያስተምረው ይችላል?" እኛ ግን የክርስቶስ ልብ አለን።
በሚያባብል የንግግር ችሎታ ማሳመን በሚችለውና በሚስብ ንግግር ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ምንም ላለማወቅ ወስኜ ነበር ጳውሎስ ከሰው አስተሳስብ ይልቅ በመስቀሉ ላይ አተኩሮአል። ትኩረት፦«ስለ ክርስቶስ ብቻ ለመናገር ወስኛ ነበር።»
ከእናንተ ጋር ነበርኩ «እኔ እናንተ ዘንድ ነበርኩ» በድካም አማጭ ትርጉሞች፦ 1) «የአካል ድካም» (UDB) or 2) «በሚገባ ሆኖ አለ መገኘት» አሳማኝ ማሳመን ወይም አንድ ነገር ሰዎች እንዲያደርጉ ተጽእኖ ማድረግ ወይም እንድን ነገር ማመን እነርሱ የጳውሎስ መልእክትና የወንጌል ስብከት
ጥበብን መናገር «የጥበብን ቃል ተናገር» የበሰለ ትኩረት፦ «የበሰሉ አማኞች» ለክብራችን «የወደፊት ክብራችንን ለማረጋገጥ»
የክብሩ ጌታ «ኢየሱስ የከበረ ጌታ» ዓይን ያላየው ነገሮች፥ጆሮም ያልሰማ ነገሮች፥ በልብም ያልታሰቡ ነገሮች ሦስቱም ነገሮች የሚያሳዩት ማንም ሰው በሁሉ አካሉ ክፍሎች እግዚአብሔር ያዘጋጃቸውን ነገሮች እንደማያውቅ ለመግለጽ ነው። እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጃቸው ነገሮች ጌታ ለሚወዱት አስደናቂ ነገሮችን በሰማይ አዘጋጅቶአል።
እነዚህ ነገሮች ናቸው ስለ ኢየሱስና ስለ መስቀል ያሉ እውነቶች በሰው ውስጥ ያለውን አሳብ ከሰው መንፈስ በቀር ማን ያውቃል? ጳውሎስ ይህን ጥያቄ የተጠቀመው ሰው የሚያስበውን ከራሱ ሰውየው በቀር ማንም አያውቅም። ትኩረት፦«ሰው የሚያስበውን ከሰው መንፈስ በቀር ማንም አያውቅም።»
እኛ ግን እዚህ «እ» ጳውሎስንና የእርሱን አድማጮችን ይጨምራል።
እግዚአብሔር በነጻ የሰጠን «እግዚአብሔር በነጻ ሰጠን» ወይም «እግዚአብሔር በነጻ ሰጥቶናል» መንፈስ ቅዱስ መንፈሳዊ ነገሮችን በመንፈሳዊ ጥበብ ይተረጉማል ቅዱስ መንፈስ የእግዚአብሔርን እውነት ለአማኞቹ በመንፈስ ቅዱስ በራሱ ቃላት ግንኙነት ያደርጋል እንዲሁም የራሱንም ጥበብ ይሰጣል።
መንፈሳዊ ያልሆነ ሰው ክርስቲያን ያልሆነ ሰው፥ መንፈስ ቅዱስን ያልተቀበለ ምክንያቱም በመንፈስ ስለሚመረመሩ «ምክንያቱም እነዚህን ነገሮች ለመረዳት የመንፈስ ቅዱስን ርዳታ ያስፈልጋል» መንፈሳዊ የሆነ ሰው ትኩረት፦ «መንፈስ ቅዱስን የተቀበለ አማኝ» የጌታን ልብ ማን አወቀው ማንስ ሊያስተምራው ይችላል? ጳውሎስ ይህን ጥያቄ የተጠቀመው የጌታን ልብ ማንም እንደማያውቀው ለማስረዳት ነው። ትኩረት፦ «የጌታን ልብ ማንም ሊያውቀው አይችልም። ስለዚህ ቀድሞኑ ስለማያውቀው ማንም ሊታስተምረው አይችልም።»
1 ወንድሞችና እህቶች ሆይ፤ እንደ ሥጋውያን፤ በክርስቶስም እንደ ሕፃናት እንጂ መንፈሳውያን እንደ ሆናችሁ ልናገራችሁ አልቻልሁም። 2 ገና ጠንካራ ምግብ ለመብላት ስላልቻላችሁ ጠንካራ ምግብ ሳይሆን ወተት ጋትኋችሁ። እስከ አሁን ስንኳ ጠንካራ ምግብ ለመብላት ገና አልበቃችሁም። 3 ምክንያቱም ገና ሥጋውያን ናችሁና። ቅናትና ክርክር ስለ ሚገኝባችሁ በሥጋ ፈቃድ እየኖራችሁ አይደላችሁምን? እንደ ሰውስ ልማድ እየተመላለሳችሁ አይደለምን? 4 አንዱ፦ "እኔ ጳውሎስን እከተላለሁ" እንዲሁም ሌላውም፦ "እኔ የአጵሎስ ተከታይ ነኝ" ሲል እንደ ሰዎች ልማድ መመላለሳችሁ አይደለምን? 5 ታዲያ አጵሎስ ማን ነው? ጳውሎስስ ማን ነው? በእነርሱ እጅ ያመናችሁ እንደ ተሰጣቸው አገልጋዮች ናቸው። 6 እኔ ተክልሁ አጽሎስም አጠጣ፤ ግን ያሳደገው እግዚአብሔር ነው። 7 እንግዲህ የሚተክል ወይም የሚያጠጣ ምንም አይደለም። ነገር ግን የሚያሳድግ እግዚአብሔር ነው። 8 የሚተክልና የሚያጠጣ አንድ ናቸው። እንዲሁም እያንዳንዱ እንደ ራሱ ድካም መሠረት የራሱን ደመወዝ ይቀበላል። 9 ምክንያቱም ከእግዚአብሔር ጋር አብረን የምንሠራ ነን። የእግዚአብሔር እርሻ፤ የእግዚአብሔርም ሕንፃ ናችሁ። ። 10 ከእግዚአብሔር በተሰጠኝ ጸጋ እንደ ዋና ሙያተኛ መሐንድስ መሠረትን ጠልሁ፤ ሌላውም ሰው በላዩ ያንጻል። እያንዳንዱ ሰው ግን በእርሱ ላይ እንዴት እንደሚያንጽ ይጠንቀቅ። 11 ከተመሠረተው በቀር ማንም ሌላ መሠረት ሊመሠርት አይችልም፤ እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። 12 ማንም ግን በዚህ መሠረት ላይ በወርቅ ቢሆን፤ በብር፤ በከበረ ድንጋይ፤ በእንጨት፤ በሣር ወይም በአገዳ ቢያንጽ፤ 13 የእያንዳንዱ ሥራ ይገለጣል፤ የቀን ብርሃንም ይገልጠዋልና። የእያንዳንዱም ሥራ ጥራት እንዴት መሆኑን እሳቱ ይፈትነዋል። 14 አንድ ሰው ማንኛውንም ነገር ያነጸው ሥራ ቢጸናለት ሽልማቱን ይቀበላል። ነገር ግን የማንም ሥራ የተቃጠለበት ከሆነ ይከስራል። 15 ነገር ግን እርሱ ራሱ ከእሳት እንደሚያመልጥ ሆኖ ይድናል ። 16 እናንተ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደሆናችሁ፤ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደሚኖርባችሁ አታውቁምን? 17 ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል። የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ እንደሆነ እናንተም እናንተም ቅዱሳን ናችሁ። 18 ማንም ራሱን አያታልል። ከእናንተ መካከል ማንም በዚህ ዘመን ጥበበኛ እንደሆነው ቢያስብ፤ ጥበበኛ ይሆን ዘንድ እንደ ሞኝ ራሱን ይቁጠር። 19 የዚህ ዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ፊት ሞኝነት ነውና። ምክንያቱም "እርሱ ጥበበኞችን በተንኮላቸው ይይዛል" ተብሎ ተጽፎአል። 20 ደግሞም፦ "ጌታ የጥበበኞችን አሳብ ከንቱ እንደ ሆን ያውቃል" ተብሎ ተጽፎአል። 21 ስለዚህ ማንም በሰው አይመካ። ነገር ሁሉ የእናንተ ነውና፤ 22 ጳውሎስ ቢሆን፥ ወይም አጵሎስ ቢሆን፥ ወይም ኬፋ ቢሆን፥ ወይም ዓለምም ቢሆን፥ወይም ሕይወት ቢሆን፥ ወይም ሞት ቢሆን፥ ወይም ያለውም ቢሆን፥ ወይም የሚመጣውም ቢሆን 23 ሁሉ የእናንተ ነው፤ እናንተም የክርስቶስ ናችሁ፤ ክርስቶስም የእግዚአብሔር ነው።
መንፈሳዊ ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የሚኖሩ ሰዎች ሥጋውያን ሰዎች የራሳቸውን ፍላጎት የሚከተሉ ሰዎች በክርስቶስ እንደ ሕፃናት የቅሮንቶስ ሰዎች በዕድሜአቸው ለመረዳት ገና እንደሆኑ ከሕፃናት ጋር ተነጻጽረዋል። ትኩረት፦ «በክርስቶስ በጣም ወጣት አማኞች» ተመልከት፦ ጠንካራ ምግብ ሳይሆን ወተት ጋትኩአችሁ የቆሮንቶስ ሰዎች ወተት እንደሚጠጡ ሕፃናት ሕፃናት ቀለል ያሉ ነገሮችን ብቻ መረዳት ይችላሉ። እንዳደጉና ጠንክር ያለ ምግብ ለመብላት እንደማይችሉ ሕፃናት ትላልቅ ነገሮችን ለመረዳት የበሰሉ አይችሉም። የበቃችሁ አይደላችሁም «ክርስቶስን ስለመከተል ከበድ ያሉ ትምህርቶችን ለመረዳት የበቃችሁ አይደላችሁም»
እስካሁን ሥጋውያን ናችሁ እንደ ኃጢአተኛ መሆን ወይም እንደ ዓለማዊ ፍላጎት መመላለስ በሥጋ መስፈርት የምትመላለሱ አይደለምን? ጳውሎስ የቆሮንቶስን ሰዎች ስለ ኃጢአተኛ ባሕርያቸው ይገስጻቸዋል። ትኩረት፦ «በሥጋዊ ፍላጎት መስፈርት ስለምትመላለሱ ልታፍሩ ይገባል!» በሰው መስፈርት የምትመላለሱ አይደለምን? ጳውሎስ የቆሮንቶስን ሰዎች በሰው መስፈርት ስለሚመላለሱ ይገስጻቸዋል። ትኩረት፦ «የሰውን መስፈርት ስለምትከተሉ ልታፍሩ ይገባል።» እንደ ሰው የምትኖሩ አይደለምን? ትኩረት፦ «መንፈስ ቅዱስ የሌላቸው ሰዎች እንደሚኖሩ ስለምትኖሩ ልታፍሩ ይገባል።» አጵሎስ ማን ነው? ጳውሎስስ ማን ነው? ጳውሎስ እርሱና አጵሎስ የወንጌል ዋና ምንጭ እንዳይደሉና ስለዚህም ተከታዮች ሊኖሩአቸው እንደማይገባ ለማስረዳት ነው። ትኩረት፦ «አጵሎስ ወይም ጳውሎስ በማለት ቡድን መመሠረት ስሕተት ነው።» በእነርሱ እጅ ያመናችሁ የጌታ አገልጋዮች ናቸው ጳውሎስ የራሱን ጥያቄ እርሱና አጵሎስ የእግዚአብሔር አገልጋዮች መሆናቸውን እንዲህ ሲል ይመልሳል። ትኩረት፦«ጳውሎስና አጵሎስ የክርስቶስ ባሪያዎችና ክርስቶስን የተቀላችሁት እኛ ስላገለገልን ነው።» እያንዳንዳቸውን ጌታ እንደሰጣቸው ተግባር ያመናችሁ ትኩረት፦ ፡ «ፃመነን፥ ጌታ ተግባር የተሰጠን ሰዎች ብቻ ነን።»
ተከለ የእግዚአብሔር ዕውቀት ለማደግ ዘር መተከል ስላለበት ንጽጽር ነው። ውኃ አጠጣ የተዘረ ዘር ውኃ እንደሚያስፈልጋው እምነትም ለማደግ ተጨማሪ ትምህርት ያስፈልጋል። ዕድገት እጽዋት እንደሚያድጉና ፍሬ እንደሚያፈሩ እምነትም በእግዚአብሔር ማደግና ሥር መስደድና ጠንካራ ይሆናል።
የሚተክል ምንም አይደለም፥ ነገር ግን እንዲያድግ የሚያደርገው እግዚአብሔር ነው ጳውሎስ እርሱ ወይም አጵሎስ ለአማኞች ዕድገት ኃላፊነት ያለባቸው ቢሆንም ይህን የሚያደርገው ግን እግዚአብሔር ነው።
የሚተክልና የሚያጠጣ አንድ ናቸው መትከልና ማጠጣት ጳውሎስ የቆሮንቶስን ቤተ ክርስቲያን ለማገልገል ራሱንና አጵሎስን የሚያነጻጽርበት እንደ አንድ ሥራ ቆጥሮአል። ደመወዝ በሠራው ሥራ መሠረት ለሠራተኛ የሚከፈል ገንዘብ መጠን ነው። እኛ ይህ የሚያመለክተው ጳውሎስንና አጵሎስን ሲሆን የቆሮንቶስን ቤተ ክርስቲያን አመለከትም።
ከእግዚአብሔር ጋር አብረው የሚሠሩ ጳውሎስ ራሱንና አጵሎስን ከእግዚአብሔር ጋር የሚሠሩ ሠራተኞች እንደሆኑ ይቆጥራል። የእግዚአብሔር እርሻ እግዚአብሔር አንድ ሰው እርሻው ፍሬ እንዲያፈራ እንደሚንከባከብ ለቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን ጥንቃቄ ያደርጋል። የእግዚአብሔር ሕንፃ እግዚአብሔር አንድ ሰው ሕንፃ እንደሚያንጽ የቆሮንቶስን ቤተ ክርስቲያን ቀርጾ ፈጥሮአታል።
ከእግዚአብሔር እንደተሰጠኝ ጸጋ «እግዚአብሔር እንድፈጽመው ሥራ በነፃ እንደሰጠኝ ጸጋ»
መሠረት ጠልኩ ጳውሎስ የእምነት ትምህርትና በክርስቶስ ያለውን ድነት ለሕንፃ መሠረት ከመጣል ጋር ተመሳሳይ ያደርገዋል።
ሌላው በላዩ ላይ የንጻል ሌላው ሠራተኛ እነዚህን አማኞች በመንፈሳዊ ርዳታ በቤተ ክርስቲያን ለማነጽ ይቀጥላል።
እያንዳንዱ ሰው ያድርግ ይህ የሚያመለክተው ባጠቃላይ የእግዚአብሔርን ሠራተኞችን ነው።ትኩረት፦ «እያንዳንዱ ሰው እግዚአብሔርን ያገልግል።» ከተመሠረተ በቀር ማንም ሌላ መሠረት ሊመሠርት አይችልም ትኩረት፦ «ማንም ሊመሠርት የማይችለውን አንድን መሠረት ብቻ መሥርቻለሁ ወይም እኔ ጳውሎስ መሠረትን መሠረትሁ»
እንግዲህ ማንም በመሠረቱ ላይ በወርቅ ቢሆን፥ በብር፥ በከበረ ድንጋይ፥በእንጨት፥በሣር ወይም በአገዳ ቢያንጽ፤ ሕንፃ ለማነጽ የምንጠቀምባቸው የሕንፃ መሣሪያዎች ሰው በመንፈሳዊ ባሕርይና ተግባሮችን በሕይወት ዘመኑ ለመንፈሳዊ ዋጋ ያለው እንዲሆን እንደምንገነባ ዓይነት ይነጻጸራል። ትኩረት፦ «አንድ ሰው በውድና በጠንካራ ዕቃዎች ወይም በሚቃጠል ርካሽ ዕቃዎች ይገነባል» የከበረ ድንጋይ «ውድ የሆኑ ድንጋዮች» የቀኑ ብርሃን ሲገለጠው ሥራው ይገለጣል የቀን ብርሃን የሕንፃ ሠራተኞችን ጥረት እንደሚገለጥ የሰውንም የሥራ ጥረትና እንቅስቃሴ ጥራት የእግዚአብሔር ብርሃን መገኘት ይገልጠዋል።»
በእሳት ሲፈተን የእያንዳንዱ ሥራ ጥራት በእሳት ይፈተናል እሳት በሚገለጥበት ጊዜ የሕንፃውን ጥንካሬ ወይም መውደቅ ይታወቃል፤ እንዲሁም የእግዚአብሔር እሳት የሰውን ጥረትና እንቅስቃሴ ይፈትናል። ትኩረት፦ እሳቱ የሥራውን ጥራት ያሳያል።"
ይጸናል «ይቆያል» ወይም «ይቋቋማል» (UDB) ማንም ሰው ሥራው የተቃጠለበት ትኩረት፦ «የማንንም ሥራ እሳቱ ቢያጠፋ» ወይም «እሳቱ የማንንም ሥራ ቢያፈርስ» የማንም እርሱ ራሱ እነዚህ ቃላት የሚያሳየው «ሰው» ነው። ትኩረት፦ «ሰው» ወይም «እርሱ» (UDB) ኪሳራ ያጋጥመዋል ነገር ግን ራሱ ይድናል «በእሳቱ ተፈትኖ ካላለፈ ማንኛውም ሥራውንና ሽልማቱን ያጣል እግዚአብሔር ግን ያድነዋል።»
የእግዚአብሔር መንፈስ የሚኖርባችሁ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደሆናችሁ አታውቁምን? ትኩረት፦ «የእግዚአብሔር መንፈስ የሚኖርባችሁ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደሆናችሁ እንደማያውቅ ሆናችሁ ታደርጋላችሁ»
ማፍረስ «ማፍረስ» ወይም «ማጥፋት» እግዚአብሔር ያንን ሰው ያፈርሰዋል ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነው፤ ያውም እናንተ ናችሁ። ትኩረት፦ «እግዚአብሔር ያንን ሰው ያፈርሰዋል ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነው፤ እናንተም ቅዱሳን ናችሁ።»
ማንም ራሱን አያታልል በዚህ ዓለም ጥበበኛ የሆነ ማንም በውሸት ማመን የለበትም። በዚህ ዘመን «አሁን» ጥበበኛ ለመሆን «ሞኝ» ይሁን «የእግዚአብሔርን እውነተኛ ጥበብ ለማግኘት ዓለም የሚያስበው ሞኝነት እንደሆን ሰው መቀበል አለበት»
ጥበበኞችን በተንኮላቸው ይይዛቸዋል እግዚአብሔር ጥበበኛ እንደሆኑ የሚያስቡትን በራሳቸው ተንኮል ይይዛቸዋል። ጌታ የጥበበኞችን አሳብ ያውቃል ትኩረት፦ «ጌታ ጥበበኛ እንደሆኑ የሚያስቡ ሰዎች የሚያቅዱትን ያውቃል» ወይም «ጌታ የጥበበኞችን እቅድ ሁሉ አስቀድሞ ያውቃል» (UDB)
ማንም ሰው በሰው ላይ መመካት የለበትም! ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ምእመናን ትእዛዝ ይሰጣል። ትኩረት፦ «አንዱ መሪ ከሌላው እንዴት የተሻለ እንደሆነ መመካትን ያቁም።» ትምክት «ከመጠን በላይ ትዕቢትን መግለጥ» የቆሮንቶስ ሰዎች ኢየሱስ ክርስቶስን ማምለክ ሲገባቸው ጳውሎስን ወይም አጵሎስን ከፍ ከፍ ያድርጉ ነበር። እናንተ የክርስቶስ ናችሁ፤ክርስቶስም የእግዚአብሔር ነው።
1 እንግዲህ ማንም ሰው እኛን የክርስቶስ አገልጋዮችና የእግዚአብሔር የተሰወረው ምሥጢር መጋቢዎች እንደሆነን ሊቆጥረን ይገባል። 2 በዚህ መሠረት መጋቢዎች ታማኝ ሆነው መገኘት ይገባቸዋል። 3 ነገር ግን በእናንተ ወይም በየትኛውም ፍርድ ቤት መፈረድ ካለብኝ ለእኔ በጣም ትንሽ ነገር ነው። 4 እኔ በራሴ እንኳ አልፈርድም። እኔ ምንም ክስ የለብኝም ግን ፍጹም ነኝ ማለቴ አይደለም። በእኔ የሚፈርድ ጌታ ነው። 5 ስለዚህ ጊዜ ሳይደርስ፥ ጌታ ከመምጣቱ በፊት ስለምንም ነገር አትፍረዱ።እርሱም በጨለማ የተሰወረውን ወደ ብርሃን ያወጣል፤ የልብንም አሳብ ይገልጣል። በዚያን ጊዜ እያንዳንዱ ሰው የሚገባውን ምስጋና ከእግዚአብሔር ዘንድ ይቀበላል። 6 እንግዲህ ወንድሞችና እህቶች ሆይ፦ "ከተጻፈው አትለፍ" የሚለውን ትርጉሙ ከእኛ መማር እንድትችሉ ስለ እናንተ ስል ለራሴና ለአጵሎስ እንደ ምሳሌ ተናገርሁ። ይህ ማናችሁም አንዳችሁ በሌላኛችሁ እንዳትታበዩ ነው። 7 በእናንተና በሌሎች መካከል ምን ልዩነት አለ? በነጻ ያልተቀበልከውስ ምን አለህ? በነጻ የተቀበልከው ከሆንህ እንዳልተቀበልህ የምትመካ ስለ ምንድን ነው? 8 አሁን የምትፈልጉት ሁሉ አላችሁ! አሁንስ ባለ ጠጎች ሆናችኋል! ከእኛ ተለይታችሁ መንገሥ ጀምራችኋል! በርግጥ እኛ ከእናንተ ጋር መንገሥ እንድንችል እናንተ ብትነግሡ በተመኘሁ ነበር። 9 እግዚአብሔር እኛን ሐዋርያቱን ሞት እንደ ተፈረደባቸው ሰዎች ከሁሉ ይልቅ የኋለኞች ያደረገን ይመስለኛል። ለዓለም፥ ለመላእክትና ለሰዎች መታያ ሆነናልና። 10 እኛ ስለ ክርስቶስ ሞኞች ነን፤ እናንተ ግን በክርስቶስ ጥበበኞች ናችሁ፤ እኛ ደካሞች ነን፤ እናንተ ግን ብርቱዎች ናችሁ እናንተ የከበራችሁ ናችሁ፤እኛ ግን የተዋረድን ነን። 11 እስከዚህ ሰዓት ድረስ እንራባለን፤ እንጥማለን፤ እንራቆታለን፤ ያለርኅራኄ እንደበደባለን፤ ራሳችንን የምናስጠጋበት ስለሌለን እንክራተታለን። 12 በገዛ እጃችን እየሠራን እንደክማለን፤ ሲሰድቡን እንመርቃለን፤ ሲያሳድዱን እንታገሣለን። 13 ክፉ ሲናገሩን እንማልዳለን፤ እስከ አሁን ድረስ የዓለም ጥራጊ የሁሉም ጉድፍ ሆነናል። 14 እነዚህን ነገሮች የጻፍኩላችሁ ላሳፍራችሁ ሳይሆን እንደ ተወደዱ ልጆቼ አድርጌ እንድትታርሙ ልገስጻችሁ ነው። 15 በክርስቶስ ብዙ እልፍ አዕላፋት አሳዳጊዎች ቢኖሩአችሁ እንኳ ብዙ አባቶች የሉአችሁም። እኔ ግን በኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል ልጆቼ ናችሁ። 16 እንግዲህ እኔን እንድትመስሉ እለምናችኋለሁ። 17 እንግዲህ የተወደደና ታማኝ የሆነውን በጌታ ልጄን ጢሞቲዎስን የላክሁላችሁ ለዚህ ነው ። እኔም በየስፍራውና በየአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እንደማስተምር፤ በክርስቶስ ያሉትን መንገዶቼ እርሱ ያሳስባችኋል። 18 አንዳንዶቻችሁ ግን ወደ እናንተ የማልመጣ መስሎአችሁ በትዕቢት የምትመላለሱ አላችሁ። 19 ነገር ግን ጌታ ቢፈቅድ ፈጥኜ ወደ እናንተ እመጣለሁ። እነዚህ በትዕቢት የሚመላለሱት የሚናገሩትን ብቻ ሳይሆን ኃይላቸውንም ለማወቅ እሞክራለሁ። 20 ምክንያቱም የእግዚአብሔር መንግሥት በኃይል ነው እንጂ በቃል ብቻ አይደለምና። ምን ትፈልጋላችሁ? 21 በበትር ወይስ በፍቅርና በትህትና መንፈስ እንድመጣባችሁ ትፈልጋላችሁ?
በዚህ መሠረት መጋቢዎች ትኩረት፦ «ከእነዚህ መጋቢዎች የተነሣ እኛ» መጋቢዎች ታማኝ ሆነው መገኘት ይገባቸዋል ትኩረት፦ « እንዲህ እንድንሆን ይገባል»
እኔ በእናንተ መፍረዴ ለኔ ትንሽ ነገር ነው ጳውሎስ በሰውና በእግዚአብሔር ፍርድ መካከል ያለውን ልዩነት ያመዛዝናል። ከእግዚአብሔር እውነተኛ ፍርድ ጋር ሲመዛዘን የሰው ፍርድ የማይጠቅም ነው። የሚመሠረትብኝ ክስ እንዳለ አላውቅም ትኩረት፦ «ማንኛውንም ክስ አልሰማሁም» ይህ ማለት ግን እኔ ንጹሕ ነኝ አይደለም። እኔ ንጹሕ መሆኔን ወይም አለመሆኔን ጌታዬ ያውቃል።»
ስለዚህ አትፍረዱ ጌታ ሲመጣ ሰለሚፈርድ እኛ እንፍረድ ጌታ ከመምጣቱ በፊት የጌታ ዳግም መምጣትን ያመለክታል በጨለማ የተሠወረውን ወደ ብርሃን ያመጣል እንዲሁም የልብንም አሳብ ይገልጣል እግዚአብሔር የሰውን አሳብና ዓለማ ይገልጣል። በእግዚአብሔር ፊት የተሰወረ ነገር የለም። የልብ «የሰው ልብ»
ስለ እናንተ «ስለ እናንተ በጎነት» ከተጻፈው በላይ አትለፍ «በቅዱሳት መጻሕፍት ከተጻፈው ውጪ አታድርግ» (TFT) በእናንተና በሌሎች መካከል ልዩነት ቢያዩ ጳውሎስ በጳውሎስ ወይም በአጵሎስ በማመናቸው የተሻሉ እንደሆኑ የሚያስቡትን የቆሮንቶስ ሰዎች ገሰጻቸው። ትኩረት፦«እናንተ በሌሎች ሰዎች ላይ የበላይ አይደላችሁም።» በነፃ ያልተቀበልካው ምን አለህ? ጳውሎስ እግዚአብሔር በነፃ እንደሰጣቸው ይገልጻል። ትኩረት፦ «ማንኛውንም ያላችሁ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር የሰጣችሁ ነው!»
የተቀበልከው ከሆንህ እንዳልተቀበልህ የምትመካ ስለ ምንድን ነው? ጳውሎስ በተቀበሉት ነገር በመመካታቸው ይገስጻል። ትኩረት፦ «ለመመካት መብት የላችሁም።» ወይም በምንም አትመኩ።»
እግዚአብሔር እኛን ሐዋርያትን መታያ እድርጎ አስቀመጠን ጳውሎስ ሐዋርያቱን እግዚአብሔር እንዴት ለዓለም እንዲታዩ መታያ እንዳለደረገ ሁለት መንገዶችን ይገልጻል። እኛን ሐዋርያትን መታያ አደረገን እግዚአብሔር ሐዋርያቱን እስረኛ በመጨረሻ ለስቅለት ራሳቸውን ትሑት አድርገው እንደሚቀርቡ እንደ ሮማ ወታደራዊ ሰልፍ ገልጣቸው።
ለሞት እንደተፈረደባቸው ሰዎች እግዚአብሔር ሐዋርያትን ለስቅለት እንደቀረቡ ሰዎች አጋልጦአቸዋል።
ለመላእክቱና ለሰዎች ለመንፈሳውያንና ለሰው
እኛ ስለ ክርስቶስ ሞኞች ነን እናንተ ግን በክርስቶስ ጥበበኞች ናችሁ ጳውሎስ የዓለምን አመለካከት ለማሳፈርና በክርስቶስ ለማመን የክርስትናን አመለካከት በተቃራኒ መንገድ ይጠቀማል። እኛ ደካሞች ነን እናንተ ግን ብርቱዎች ናችሁ ጳውሎስ የዓለምን አመለካከትንና በክርስቶስ ለማመን የክርስትና አመለካከትን በታቃራኒ መንገድ ይጠቀማል። እናንተ የከበራችሁ ናችሁ «የቆሮንቶስ ሰዎች በክብር ይዞአችኋል» እኛ የተዋረድን ነን «እኛን ሐዋርያቱን ሰዎች በውርደት ይዘውናል» እስከዚህ ሰዓት ትኩረት፦ «እስከዚህ ድረስ» ወይም «እስካሁን ድረስ» በጭካኔ/ ያለርኅራኄ ተደብድበዋል ትኩረት፦ «በአካላዊ ጉዳት ይቀጣል»
ሲሰድቡን እንመርቃለን «ሰዎች እኛን ሲሰድቡን እንመርቃቸዋለን»
ሲሳደቡ ትኩረት፦ «ሲሳደቡ» በሚቻለው፦ «ሲቃወሙ» ወይም «ሲረግሙን»(UDB) ሲያሳድዱን «ሰዎች እኛን ሲያሳድዱ» ክፉ ሲናገሩብን «ሰዎች ተገቢ ያልሆነውን ሲናገሩብ» በዚህ ዓለም የተጣልን ሆነናል « ሰዎች እኛን የዚህ ዓለም ጥራጊ አድርገው ቆጥረውናል»
እናንተን ለማሳፈር ሳይሆን እንድትታረሙ ነው «እናንተን ላሳፍራችሁ ሳይሆን እንድትሻሸሉ ነው» ወይም «እንድታፍሩ እያደረግሁ ሳይሆን እናንተን ለማረም ነው» (UDB) ለማስተካከል "እንድትሻሸሉ» ወይም «የተሻላችሁ እንድትሆኑ» እንልፍ አእላፋት የሚያስተምሩአችሁ ይህ የአንድ ሰው መንፈሳዊ አባት አስፈላጊነት እነርሱንም የሚመሩአቸው የሰዎች የተጋነነ ቁጥር አጉልቶ ለማሳየት ነው። ሕፃናት አባት ጳውሎስ እነርሱን ወደ ክርስቶስ ስለ መራቸው ለቆሮንቶስ ሰዎች እንደ አባት ነው። ማሳሰብ «በብርቱ ማበረታታት» ወይም «በብርቱ ማሳሰብ»
አሁን ይህ ዓለም የሚያሳየው ጳውሎስ እብሪተኛ የሆኑትን የቆሮንቶስ አማኞችን ባሕርይ ለመገሰጽ ርዕሱን መቀየሩ ነው።
ወደ እናንተ እመጣለሁ «እናንተን እጎበኛለሁ» በቃል አይደለም ትኩረት፦ «በቃል የሚደረግ አይደለም» ወይም «በቃላት የምትናገሩት አይደለም» ምን ትፈልጋላችሁ ጳውሎስ የቆሮንቶስን ሰዎች ስላደረጉት ስሕተት እየገሰጻቸው የመጨረሻ ልመና ያቀርብላቸዋል። ትኩረት፦ «አሁን ምን እንዲሆነላችሁ እንደምትፈልጉ ንገሩኝ» በበትር ወይም በፍቅርና በትህትና መንፈስ ልምጣባችሁን? ጳውሎስ የቆሮንቶስን ሰዎች በሁለት ተቃራኒ አስተሳሰቦችን ያቀርብላቸዋል። ትኩረት፦ «ወደ እናንተ በጭካኔ ትምህርት ልምጣን? ወይም «በትህትና መንፈስ ፍቅርን ላሳያችሁን?»
ትህትና ትኩረት፦ «በርኅራኄ» ወይም «በትህትና»
1 በእናንተ መካከል ዝሙት እንዳለ ሰምተናል፤የዚያም ዓይነት ዝሙት በአሕዛብ መካከል እንኳ ተሰምቶ የማይታወቅ ነው። እንደሰማነው ከእናንተ አንዱ ከእንጀራ እናቱ ጋር የሚተኛ አለ። 2 ስለዚህ በትዕቢት የምትመላለሱ አይደላችሁምን? በዚህም ልታዝኑ አይገባችሁምን? ይህን ያደረገ ሰው ከመካከላችሁ ሊወገድ ይገባል። 3 እኔ በአካል ከእናንተ ጋር ባልሆንም በመንፈስ ከእናንተ ጋር አለሁ፤ከእናንተም ጋር እንዳለሁ ሆኜ ይህን ባደረገው ሰው ላይ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሁን ፈርጄበታለሁ። 4 እናንተ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በምትሰበሰቡበት ጊዜ መንፈሴም ከጌታችን ኢየሱስ ኃይል ጋር እዚያው በመካከላችሁ አለ። 5 ይህ ሰው በጌታ በኢየሱስ ቀን ይድን ዘንድ፤ ለሥጋው ጥፋት ለሰይጣን እንዲሰጥ ፍርዴ ነው። 6 መመካታችሁ መልካም አይደለም። ጥቂት እርሾ ሊጡን ሁሉ እንደሚያቦካ አታውቁምን? 7 እንግዲህ እርሾ የሌለ እንጀራ ሆናችሁ አዲሱን ሊጥ ትሆኑ ዘንድ ከአሮጌው እርሾ ራሳችሁን አንጹ። ምክንያቱም የፋሲካችን በግ የሆነው ክርስቶስ ታርዶአል። 8 ስለዚህ በአሮጌ እርሾ በመጥፎ አስተሳሰብና በክፋት ሳይሆን በቅንነትና በእውነት በዓልን እርሾ በሌለ ቂጣ እናድርግ። 9 ዝሙትን ከሚያደርጉ ሰዎች ጋር ኅብረት እንዳታደርጉ በመልእክቴ ጽፌላችሁ ነበር። 10 በምንም ነገር የዚህን ዓለም ዝሙት ከሚያደርጉትን ወይም ገንዘብን ከሚመኙትን፥ ከነጣቂዎችንም፤ወይም ጣዖትን ከሚያመልኩትን ከማያምኑት አትተባበሩ። እንዲህ ቢሆን ኖሮ ከዓለም መውጣት በተገባችሁ ነበር። 11 አሁን ግን በክርስቶስ ወንድሞች ወይም እህቶች ተብለው ከሚጠሩት ከማናቸውም ዝሙትን ከሚያደርግ ወይም ገንዘብን ከሚመኝ ወይም ጣኦትን ከሚያመልክ ወይም ተሳዳቢ ወይም ሰካራም ወይም ነጣቂ ቢሆኑ ከእነርርሱ ጋር እንዳትተባበሩ እጽፍላችኋለሁ። እንደነዚህ ካሉት ጋር አብራችሁ እንኳን አትብሉ። 12 ከቤተ ክርስቲያን ውጭ ባሉ ሰዎች ላይ ለመፍረድ እንዴት እደፍራለሁ? በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ባሉ ሰዎች ላይ እናንተ አትፈርዱምን? 13 ከቤተ ክርስቲያን ውጭ ባሉቱ ግን እግዚአብሔር ይፈርድባቸዋል። "ክፉውን ከመካከላችሁ አውጡት።"
በአህዛብ ዘንድ እንኳን ተሰምቶ የማይታወቅ «አህዛብ እንኳን የማይፈቅዱት» የእንጀራ እናት የአባቱ ሚስት ግን የራሱ እናቱ አይደለችም። በዚህ ማፈር የለባችሁምን? ይህ ፈሊጣዊ አዘል ጥያቄ ክርስቲያኖችን ለማሳዘን ጥቅም ላይ ውለዋል። ) ይህን ያደረገ ሰው ከመካከላችሁ መወገድ አለበት «ይህን ያደረገውን ከመካከላችሁ ማስወገድ አለባችሁ»
በመንፈስ አብሮ መሆን ጳውሎስ በአሳቡ ከእነርሱ ጋር ነው። «በአሳቤ ከእናንተ ጋር ነኝ» በዚህ ሰው ላይ እኔ ፈጄበታለሁ «ይህ ሰው ጥፋተኛ ሆኖ አግኝቻለሁ» በአንድ ላይ መሆን «መገነኘት» በጌታችን በኢየሱስ ስም ኢየሱስ ክርስቶስን ለማምለክ አንድ ላይ ለመሰብሰብ ፈሊጣዊ አነጋገር ይህን ሰው ለሰይጣን አሳልፎ መስጠት ይህ የሚያመለክተው ሰውየውን ከእግዚአብሔር ሕዝብ ተለይቶ ከቤተ ክርስቲያን ውጪ በዓለም ውስጥ በሰይጣን ግዛት ይኖራል። ለሥጋው ጥፋት ሰውየው ስለ ኅጢአቱ በአካላዊ ሕመም እግዚአብሔር ይቀጠዋል።
መመካታችሁ መልካም አይደለም «መመካታችሁ መጥፎ ነው» ጥቂት እርሾ ሊጡን ሁሉ እንደሚያቦካ አታውቁምን? ጥቂት እርሾ እንጀራን ሁሉ እንደሚያደርስ ሁሉ ጥቂት ኀጢአት የአማኞችን ኅብረት ሁሉ ሊያበለሽ ይችላል። መስዋዕት ሆኖአል «ጌታ እግዚአብሔር ክርስቶስ ኢየሱስን መስዋዕት አደረገው።» ክርስቶስ የፋሲካችን በግ ታርዶአል የፋሲካ በግ የእስራኤልን ኀጢአት በእምነት እንደሚሸፍን የክርስቶስ ሞት በክርስቶስ ለሚያምኑት ኀጢአትን በክርስቶስ ለዘላለም ይሸፍናል።
ዝሙትን የሚያደርጉ ሰዎች በክርስቶስ እንደሚያምኑ የሚያስመስሉ ግን በዚህ ሁኔታ የሚመላለሱትን የሚያመለክት ዝሙትን የሚያደሩ የዚህ ዓለም ሰዎች በጌታ የማያምኑ በዝሙት ሕይወት ለመኖር ምርጫቸው ያደረጉ ስግብግብነት «ስግብግብ የሆኑ ሰዎች» ወይም «ማንኛውም ሰው ያለውን ሁሉን ነገር የሚፈልጉ ሰዎች» ነጣቂዎች ይህ ማለት የሚያታልሉ ሰዎች ወይም የሌሎችን ገንዘብ ወይም ንብረት የሚያጭበረብሩ። ከእነርሱ መለየት ቢሆን ከዓለም መውጣታችሁ ነበር በዓለም ከእንዲህ ዓይነት ተግባር ነፃ የሆነ ቦታ የለም። ትኩረት፦«ከእነርሱ መለየት ቢሆን ከሁሉንም ሰው ማስወገድ ያስፈልግ ነበር።»
ማንም የተጠራ ማንም ሰው ራሱን በክርስቶስ አማኝ ብሎ የሚጠራ ከቤተ ክርስቲያን ውጪ ባሉት ላይ እንዴት እፈርዳለሁ? ትኩረት፦ «የቤተ ክርስቲያን ባልሆኑ ሰዎች ላይ እኔ አልፈድም።» በቤተ ክርስቲያን ባሉ ሰዎች እናንተ አትፈርዱምን? «በቤተ ክርስቲያን ባሉት ላይ እናንተ መፍረድ አለባችሁ»
1 ከእናንተ አንድ ሰው ከሌላ ሰው ጋር ክርክር ቢኖረው፤ በቅዱሳን ፊት ስለጉዳዩ ከመነጋገር ይልቅ በማያምን ዳኛ ፊት ለመቆም ወደ ፍርድ ቤት ለመሄድ ይደፍራልን? 2 ቅዱሳን በዓለም ላይ እንደሚፈርዱ አታውቁምን? በዓለም ላይ የምትፈርዱ ከሆነ፤ በትናንሽ ጉዳዮችን መፍረድ እንዴት ይሳናችኋል? 3 በመላእክት ላይ እንኳ እንደምንፈርድ አታውቁምን? እንግዲህ በዚህ ዓለም ሕይወት ጉዳዮች ላይ የበለጠ ለመፍረድ እንዴት አንችልም? 4 ለዕለታዊ ጠቃሚ ጉዳዮች ላይ መፍረድ ካለባችሁ በቤተ ክርስቲያን መካከል ለሚነሱ ክርክሮች የማያምኑ ሰዎችን እንዲፈርዱ ታስቀምጣላችሁን? 5 አሳፍራችሁ ዘንድ ይህን እላለሁ። እንደዚህ ነውን? በወንድሞችና እህቶች መካከል ክርክሮችን ሊፈታ የሚችል አንድ አስተዋይ ሰው በእናንተ ዘንድ አይገኝምን? 6 ነገር ግን አንዱ አማኝ ሌላውን አማኝ ለመክሰስ በማያምን ዳኛ ፊት ለመቆም ይሄዳልን? 7 እንግዲህ በክርስቲያኖች መካከል የእርስ በርስ ማንኛውም ክርክር ቢኖርባችሁ ለእናንተ ሽንፈት ነው። ብትበደሉ አይሻልምን? ብትታለሉስ እይሻልምን? 8 ነገር ግን እናንተ ወድሞቻችሁንና እህቶቻችሁን ትበድላላችሁ ታታልሉማላችሁ። 9 ዓመጸኞች የእግዚአብሔርን መንግሥት እንደማይወርሱ አታውቁምን? በሐሰት አታምኑ። ዝሙት አድራጊዎች ቢሆኑ፣ወይም ጣዖትን የሚያመልኩ፥ ወይም አመዝሮች ወይም ግብረ ሶዶማውዎች ቢሆኑ፤ ወይም ሌቦች፥ ወይም ስግብግቦች፤ ወይም ሰካራሞች፣ ወይም ተዳዳቢዎች፥ 10 ወይም ነጣቂዎች፥ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። 11 ከእናንተም አንዳንዶቻችሁ እንዲሁ ነበራችሁ። ነገር ግን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአምላካችንም መንፈስ ታጥባችኋል፥ ተቀድሳችኋል፤ ጸድቃችሁማል። 12 ሁሉ ተፈቅዶልኛል፤ነገር ግን ሁሉም የሚጠቅም አይደለም። ሁሉ ተፈቅዶልኛል ነገር ግን በእኔ ላይ ምንም ነገር አይሠለጥንብኝም። 13 "መብል ለሆድ ነው፤ ሆድም ለመብል ነው።" እግዚአብሔር ግን ይህንም ያንም ያጠፋቸዋል። ሥጋ ግን ለጌታ ነው እንጂ ለዝሙት አይደለም። ይልቁን ሥጋችንም ለጌታ ነው፤እንዲሁም ጌታ ለሥጋ ያዘጋጃል። 14 እግዚአብሔርም ደግሞ ጌታን አስነሣ እኛንም በኃይሉ ያስነሣናል።ሥጋችሁ የክርስቶስ ብልቶች እንደሆነ አታውቁምን? 15 እንግዲህ የክርስቶስን ብልቶች ወስጄ የሴተኛ አዳሪ ሴት ብልቶች ላድርጋቸውን? ሊሆን አይችልም። 16 ከሴተኛ አዳሪ ጋር የሚተባበር ከእርስዋ ጋር አንድ ሥጋ እንዲሆን አታውቁምን? "ሁለቱ አንድ ሥጋ ይሆናሉ" በእግዚአብሔር ቃል ተጽፎአል። 17 ከጌታ ጋር የሚተባበር ግን ከእርሱ ጋር አንድ መንፈስ ነው። 18 ከዝሙት ሽሹ። ሰው የሚያደርገው ሌላ ኃጢአት ሁሉ ከሥጋ ውጭ ነው፤ ዝሙትን የሚያደርግ ሰው ግን በገዛ ሥጋው ላይ ኃጢአትን ያድርጋል። 19 ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁትና በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? 20 በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም። ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።
ክርክር ትኩረት፦ «አለመስማማት»ወይም «ሙጉት» ከአማኞች ይልቅ ወደ ማያምን ዳኛ ፊት ለመቆም ወደ መንግሥት ፍርድ ቤት ለመሄድ ይደፍራልን? ጳውሎስ ክርስቲያኖች በመካከላቸው አለመስማማት ቢኖር ራሳቸው መፍታት አለባቸው ይላል። ትኩረት፦«ክርስቲያን ባልንጀራችሁን በማያምን ዳኛ ፊት አትክሰስ። ክርስቲያን ባልንጀራዎች አለመስማማታቸውን ራሳቸው መካከል መፍታት አለባቸው።» መንግሥት ፍርድ ቤት መንግሥት በአካባቢ ባለው ጉዳዮችን የሚፈርድበትና ትክክል የሆነውን የሚወስንብት አማኞች በዓለም ላይ እንደሚፈርዱ አታውቁምን? ጳውሎስ ወደ ፊት በዓለም ላይ እንደሚፈረድ ያመለክታል። በዓለም ላይ የምትፈርዱ ከሆነ በትናንሽ ጉዳዮችን መፍረድ እንዴት ይሳናችኋል? ጳውሎስ ወደ ፊት በአጠቃላይ በዓለም ላይ የመፈረድ ኃላፊነትና ችሎታ እንደሚሰጥ ይናገራል፤ ስለዚህ በትናንሽ ጉዳዮች ላይ ራሳቸው መፍረድ አለባቸው። ትኩረት፦«ለወደ ፊት በዓለም ላይ ትፈርዳላችሁ ስለዚህ ይህን ጉዳይ መፍታት ትችላላችሁ።» . በመላእክት ላይ እንደምትፈርዱ አታውቁምን? «በመላእክት ላይ እንደምትፈዱ ታውቃላችሁ» እኛ ጳውሎስ ራሱንና የቆሮንቶስ ሰዎችን ይጨምራል። በዚህ ሕይወት ጉዳዮች ላይ የበለጠ መፍረድ እንደምንችል አታውቁምን? ትኩረት፦ «ምክንያቱም በመላእክት ላይ የመፍረድ ኃላፊነትና ችሎታ ስለተሰጠን በርግጠኝነት በሕይወት ጉዳዮች ላይ መፍረድ እንችላለን።»
ለዕለታዊ ኑሮ የሚያስፈልገው ጉዳይ ላይ መፍረድ ካለባችሁ ትኩረት፦ «ስለ ዕለታዊ ህይወት ለመወሰን የተጠራችሁ ከሆነ» ወይም «በዚህ አስፈላጊ ሕይወት ላይ መፍታት ካለባችሁ» (UDB) እንዲህ ያሉ ጉዳዮችን ለምን ታስቀምጣላችሁ «እንዲህ ያሉ ጉዳዮችን መስጠት የለባችሁም» በቤተ ክርስቲያን የማያምኑ ሰዎች ጳውሎስ እነዚህን ነገሮች እንዴት እንደሚይዙ የቆሮንቶስ ሰዎችን ይገስጻቸዋል። አማራጭ ትርጉሞች 1)«እንዲያ ያሉትን ነገሮች ለመወሰን ተገቢ ያልሆኑትን አባላትን እንዲህ ያሉትን ጉዳዮች መስጠት አቁሙ» ወይም 2) «እንዲህ ያሉትን ጉዳዮች ከቤተ ክርስቲያን ውጪ ላሉ ሰዎች መስጠት አቁሙ» ወይም 3) «በሌሎች አማኞች መልካም ሆኖ ላልተቆጠሩ አባላት እንኳን እንዲህ ያሉትን ጉዳዮችን መስጠት የለባችሁም።» ላሳፍራችሁ ትኩረት፦ «ለእናንተ ውርደት» ወይም «በዚህ ጉዳይ ላይ እንዴት እንደ ወደቃችህ ለማሳየት» (UDB) በወንድሞችና እህቶች መካከል ያለ ክርክር ለመፍታት በመካከላችሁ አስተዋይ ሰው የለምን? ትኩረት፦ «በአማኞች መካከል ያለውን ክርክር የሚፈታ አንድ አስተዋይ ሰው ማግኘት ትችላላሁ።» ክርክር/ሙግት «ክርክር» ወይም «አለመስማማት» ነገር ግን እንዳለ ትኩረት፦ «ነገር ግን አሁን ባለው ሁኔታ» ወይም «ነገር ግን በዚህ ፈንታ» (UDB) አንዱ አማኝ ሌላውን ለመክሰስ በማያምን ዳኛ ፊት ለመቆም ወደ ፍርድ ቤት ይሄዳል ትኩረት፦ «እርስ በርሳቸው ክርክር ያለባቸው አማኞች የማያምን ዳኛ ስለ ጉዳያቸው እንዲፈርድላቸው ይጠትቃሉ» ይህ ጉዳይ ይቀርባል «ይህን ጉዳይ አማኝ ያቀርባል»
ሽንፈት ትኩረት፦ «ውድቀት» ወይም «ኪሳራ» መበደል አይሻልምን? መታለል አይሻልምን? ትኩረት፦«ሌሎች ቢበድሉና ወደ ፍርድ ቤት ቢወሰዱና ቢያታልሉ ይሻላል» ማታለል ትኩረት፦ «ማሳሰት» ወይም «ማሳት» የራሳችሁ ወንድሞችና እህቶች ሁሉም በክርስቶስ የሆኑ አማኞች እርስ በርሳቸው ወንድሞችና እህቶች ናቸው። ትኩረት፦ «የራሳችሁ በእምነት ባልንጀሮች ናችሁ።»
ይህን አታውቁምን? ጳውሎስ ይህን እውነት አስቀድሞ እንደሚያውቁ ያብራራል። ትኩረት፦«ይህን አስቅድማችሁ ታውቃላችሁ» አመፀኞች አይወርሱም «ጸድቃን ብቻ ይወርሳሉ» የእግዚአብሔርን መንግሥት ይወርሳሉ እግዚአብሔር እንደ ጸድቃን አይፈርድባቸውም፥ ወደ ዘላለም ሕይወት አይገቡም። ግብረ ሰዶማውያን ወንድ ከወንድ ጋር የሚተኙ ዝሙተኞች የግብረ ሰዶማዊ ልምምድ የሚያደርጉ ወንድ ሆኖ ከሌላ ወንድ ጋር የሚተኙ ሌቦች «ከሌሎች የሚሰርቁ ሰዎች» ወይም «ነጣቂዎች» ስግብግቦች ትኩረት፦ «ከሌሎቹ ይልቅ ተስገብግቦ ብዙ የሚወስዱ ሰዎች» አጨበርባሪዎች ትኩረት፦ «አታላዮች» ወይም «በእንርሱ ላይ እምነት ከጣሉባቸው ሰዎች የሚሰርቁ»(UDB) ታጥባችኋል እግዚአብሔር ንፁሕ አድርጎአችኋል ለእግዚአብሔር ተለይታችኋል/ተቀድሳችኋል ትኩረት፦ «እግዚአብሔር ለራሱ ቀድሶአችኋል» ወይም «እግዚአብሔር ቅዱሳን አድርጎአችኋል» ከእግዚአብሔር ጋር ጸድቃችኋል እግዚአብሔር ከራሱ ጋር ጻድቃን አድርጎአችኋል
«ሁሉም ተፈቅዶልኛል» ትኩረት፦ «አንዳንዶች እንዲህ ይላሉ፥'ማንኛውንም ነገር ማድረግ እችላለሁ' ወይም «ማንኛውንም ነገር ለማድረግ ተፈቅዶልኛል» ነገር ግን ሁሉም አይጠቅመኝም «ነገር ግን ሁሉ ለእኔ መልካም አይደለም.» በማናቸውም አይግዛም/ማናቸውም አይሠለጥኑብኝም ትኩረት፦ «እነዚህ ነገሮች አንዳቸውም በእኔ ላይ ጌታ ሆነው አይሠለጥኑብኝም» «ምግብ ለሆድ ነው፥ሆድም ለምግብ ነው፤» ነገር ግን እግዚአብሔር ሁለቱንም ያጠፋቸዋል ትኩረት፦ «አንዳንዶች እንዲህ ይላሉ፥ 'ምግብ ለሆድ ነው፤ሆድም ለምግብ ነው' ነገር ግን እግዚአብሔር ምግብንም ሆድንም ያጠፋቸዋል» ሆድ የሚታይ አካል ያጠፋል «ማጥፋት»
ጌታን አስነሣ
ኢየሱስን አስነሥቶ ሕያው አደርገ
የአካል ብልቶቻችሁ የክርስቶስ እንደሆኑ አታውቁምን?
እጃችንና እግራችን የአካላችን ክፍሎች እንደ ሆኑ አካላችንም የክርስቶስ አካላት፥የቤተ ክርስቲያን ናቸው። ትኩረት፦ «አካላችሁ የክርስቶስ ነው»
የክርስቶስን አካል ወስጄ ከሴተኛ አዳሪ ጋር አንድ ላድርጋውን?
ትኩረት፦«እናንተ የክርስቶስ አካል ናችሁ። የሴተኛ አዳሪ ጋር አንድ አላደርጋችሁም።»
ሊሆን አይችልም ትኩረት፡- «ይህ ሊሆን የሚገባ አይደለም!»
ይህን አታውቁምን? «ይህን አስቀድማችሁ ታውቃላችሁ።» ጳውሎስ አስቀድሞ የሚያውቁትን እውነትየገልጥላቸዋል።
ነገር ግን ከጌታጋር አንድ ሆነ ከእርሱ ጋር አንድ መንፈስ ይሆናል ትኩራት፡- «አንድ ሰው ከጌታ ጋር አንድ የሆነ ከጌታ ጋር አንድ መንፈስ ይሆናል።»
መሸሽ የአንድ ሰው በአካላዊ ሁኔታ መሸሽ ከመንፈሳዊ ሁኔታ ኀጢአትን ከመቃወም ጋር ሲነጻጸር ነው። ትኩረት፦ «ሽሽ» መተላልፍ «ማድረግ» ወይም «ማከናወን» «ሌላ ኀጢአት ከአካል ውጭ ይደረጋል» ነገር ግን ዝሙትን የሚያደርግ ግን በገዛ ሥጋው ነው የዝሙት ኀጢአት በሰው በራሱ አካል በሽታ መያዝ የሚችልበት ሲሆን፥ ነግር ግን ሌላ ኀጢአት በዚያው መንገድ አካልን አይጎደም።
አታውቁምን? «አስቀድማችሁ ታውቃላችሁ» ጳውሎስ ይህን እውነት አስቀድሞ እንድሚያቁ ያስረዳቸዋል። ሰውነታችሁ የእያንዳንዱ ክርስቲያን አካል የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ ነው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ ቤተ መቅደስ ለመለኮት የተለየ ነው እንዲሁም የመለኮትም ማደሪያ ነው። በተመሳሳይ ሁኔታ የአንድ ክርስቲያን አማኝ አካል እንደ ቤተ መቅደስ የመንፈስ ቅዱስ የሚገኝበት ነው። በዋጋ ተገዝታችኋል እግዚአብሔር ለቆሮንቶስ ሰዎች ከባርነት ነፃ እንዲወጡ ዋጋ ከፍሎላቸዋል። ትኩረት፦«እግዚአብሔር ለእናንተ ነፃነት ዋጋ ከፍሎላችኋል።» ስለዚህ ትኩረት፦ «እንግዲህ» ወይም «ይህ እውነት ስለሆን» ወይም «ከዚህ እውነት የተነሣ»
1 እንግዲህ ስለጻፋችሁኝ ነገር ሰው ከሴት ጋር አለመገናኘት መልካም ነው። 2 ነገር ግን ስለ ዝሙት ፈተና ምክንያት እንዳይሆን እያንዳንዱ ሰው የራሱ ሚስት ይኑረው፤ እንዲሁም ለእያንዳንዱ ሴት የራስዋ ባል ይኑራት። 3 ባል ለሚስቱ የሚገባትን ያድርግላት፤ እንደዚሁም ደግሞ ሚስቲቱ ለባልዋ የሚገባትን ታድርግ። 4 ሚስት በገዛ ሰውነትዋ ላይ ሥልጣን ያላትም፤ ሥልጣን ለባልዋ ነው እንጂ፤ እንዲሁም ባል በገዛ ሰውነቱ ላይ ሥልጣን የላውም ሥልጣን ለሚስቱ ነው እንጂ። 5 በጸሎት ለመትጋት ተስማምታችሁ ለጊዜው ካልሆነ በቀር እርስ በርሳችሁ አትከላከሉ። ራሳችሁን ስለ አለመግዛት ሰይጣን እንዳይፈታተናችሁ ደግሞ አብራችሁ መሆን ትችላላችሁ። 6 ዳሩ ግን ይህን እንደ ፈቃድ እላለሁ እንጂ እንደ ትእዛዝ አይደለም። 7 ሰው ሁሉ እንደ እኔ ቢሆን እወዳለሁ። ነገር ግን እያንዳንዱ ሰው ለራሱ ከእግዚአብሔር የተቀበለ አንዱ አንድ ዓይነት ሌላው ሌላ ዓይነት ስጦታ አለው። 8 ላላገቡትና ባሎቻቸው ለሞተባቸው ሴቶች ግን እላለሁ፦ እንደ እኔ ሳያገቡ ቢኖሩ ለእነርሱ መልካም ነው። 9 ነገር ግን ራሳቸውን መግዛት የማይችሉ ከሆነ መጋባት ይሻላል። በምኞት ከመቃጠል ይልቅ መጋባት ይሻላቸዋልና። 10 ደግሞ የተጋቡትን እንዲ ብዬ አዛቸዋለሁ ይህንም እኔ ሳልሆን ጌታ ነው፦ "ሚስት ከባልዋ አትለይ፥ 11 ብትለይ ግን ሳታገባ ትኑር" ወይም "ከባልዋ ጋር ትታረቅ፥እንዲሁም" ባልም ሚስቱን አይፍታት።" 12 ነገር ግን ሌሎችንም ጌታ ሳይሆን እኔ እላለሁ፦ ማንም ያላመነች ሚስት ያለው ወንድም፥ ከእርሱ ጋር ለመኖር ብትስማማ አይፍታት፤ 13 እንዲሁም ያላመነ ባል ያላት ሚስትም ብትኖር፥ ከእርስዋ ጋር ለመኖር ቢስማማ አትፍታው። ያላመነች ሚስት በአማኙ ባልዋ ተቀድሳለችል፤ 14 እንዲሁም ያላመነ ባል በአማኝ ሚስቱ ተቀድሶአል። አለዚያ ልጆቻቸውሁ ርኩሳን ይሆኑ ነበር፤ አሁን ግን የተቀደሱ ናቸው። 15 የማያምን የትዳር ጓደኛ ግን የሚለይ ከሆነ ይለይ። እንዲህ በሚመስል ነገር ወንድም ወይም እህት በቃል ኪዳን መታሰር የለባቸውም። እግዚአብሔር ግን በሰላም እንድንኖር ጠርቶናል። 16 አንቺ ሴት ባልሽን ታድኚ እንደ ሆንሽ ምን ታውቂአሽ? ወይስ አንተ ሰው ሚስትህን ታድናት እንደ ሆንህ ምን ታውቃለህ? 17 እያንዳንዱ ሰው እንደተጠራው ዓለማና ጌታ በሰጠው ሕይወት ብቻ ይመላለስ። ይህ ለአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ የእኔ ድንጋጌ ነው። 18 ማንም ተገርዞ ወደ እምነት ተጠርቶአልን? ወደ አለመገረዝ መመለስ የለበትም። እንዲሁም ማንም ሳይገርዝ ወደ እምነት ተጠርቶአልን? መገረዝ የለበትም። 19 የእግአብሔርን ትእዛዛት መጠበቅ ነው እንጂ መገረዝ ወይም አለመገረዝ የሚያመጠው ችግር የለም። 20 እያንዳንዱ ሰው እግዚአብሔር ለእምነት በጠራበት ጊዜ እንደነበረ ይመላለስ። 21 እግዚአብሔር ሲጠራህ ባሪያ ነበርን? ይህ ሊገድህ አይገባም። ነፃ የምትወጣ ከሆንህ ተቀበለው። 22 አንድ ሰው በጌታ ባሪያ ሆኖ የተጠራ የጌታ ነፃ ሰው ነው፤ እንደዚሁም ነፃ ሆኖ ለእምነት የተጠራ የክርስቶስ ባሪያ ነው። 23 በዋጋ ተገዝታችልኋልና የሰው ባሪያ አትሁኑ። 24 ወድሞችና እህቶች ሆይ፤ እያንዳንዳችን በተጠራንበት እንደዚሁ ሆነን በእግዚአብሔር ዘንድ እንኑር። 25 ላላገቡት የጌታ ትእዛዝ የለኝም። ነገር ግን በጌታ ምሕረት እንደ ታመነ ሰው ሆኜ የራሴን ምክር እሰጣለሁ። 26 ስለዚህ ለችግር ጊዜ መፍትሔ እንዲሆን ሰው ሳያገባ መኖር ከቻለ መልካም ይመስለኛል። 27 በጋብቻ ቃል ኪዳን በሚስት ታስረሃልን? እንዲህ ከሆነ ከዚህ ነፃ ለመሆን አትሻ። በበጋብቻ በሚስት አልታሰርህ ወይም ያላገባህ ነህ? ሚስትን አትሻ። 28 ነገር ግን ካገባህ ኃጢአት አይሆንብህም። እንዲሁም ያላገባች ሴት ብታገባ ኃጢአት አይሆንባትም። ሆኖም ግን የሚያገቡ በኑሮአቸው ብዙ ችግር ይሆንባቸዋል፤ ከእንዲ ዓይነት ሕይወት እንድትርቁ እመኛለሁ። 29 ዳሩ ግን ወንድሞ ሆይ፤ ይህን እላለሁ፤ ዘመኑ አጭር ነው። ከእንግዲህ ወዲህ ሚስቶች ያሉአቸ እንደሌላቸው ይኑሩ። 30 የሚያላቅሱም እንደማያለቅሱ ይሁኑ፤ እንዲሁም የሚደሰቱ ደስታ እንደሌላቸው ይሁኑ፤ 31 ደግሞ ማንኛውንም ነገር የሚገዙ ምንም እንደሌላቸ ይሁኑ፤ በዚህች ዓለም የሚጠቀሙ በሙሉ እንደ ማይጠቀሙ ይሁኑ ምክንያቱም የዚች ዓለም አሠራር ሁሉ አላፊ ነውና። 32 ነገር ግን ያለ ጭንቀት እንድትኖሩ እወዳለሁ። ያላገባው ጌታን እንዴት ደስ እንደሚያሰኘው የጌታን ነገር ያስባል። 33 ያገባው ግን ሚስቱን እንዴት ደስ እንዲያሰኛት የዓለምን ነገር ያስባል፥ ልቡም ተከፍሎአልና። 34 ያላገባች ሴት ወይም ድንግል በሥጋና በመንፈስ እንዴትምትቀደስ የጌታን ነገር ታስባለች። ያገባች ሴት ግን ባልዋን እንዴት ደስ እንደምታሰኘው የዓለምን ነገር ታስባለች። 35 ሌላ ሸክም ሊጭንባችሁ ሳይሆን ለራሳችሁ ጥቅም ይህን እላለሁ። ያለ ምንም ጉዳት በጌታ እንድትጸኑ ስለእውነት ይህን እላለሁ። 36 ዳሩ ግን ማንም ሰው ያጫትን ድንግል በአግባቡ ካልያዘ የእርስዋም ዕድሜ እየገፋ ከሄደ ሊያገባት ካሰበ ያግባት። ይህ ኃጢአት የለበትም። 37 ነገር ግን አንድ ሰው ላለማግባት ቢወስንና ስሜቱንም ለመቆጣጠር ከቻለ እርስዋን ባለማግባቱ መልካም ያደርጋል። 38 የእርሱንም እጮኛ የሚያገባት መልካም ያደርጋል፤እርስዋንም ለማግባት የማይመርጥ የበለጠ መልካም ያድርጋል። 39 አንዲት ሴት ባልዋ በሕይወት እስካለ ድረስ ከባልዋ ጋር የታሰረች ናት። ነገር ግን ባልዋ ቢሞት በጌታ የሆነውን ብቻ ለማግባት ነጻነት አላት። 40 እንደ እኔ ውሳኔ ግን ሳታገባ ብትኖር ደስተኛ ትሆናለች። እኔም የእግዚአብሔር መንፈስ ያለኝ ይመስለኛል።
እንግዲህ ጳውሎስ በትምህርቱ አዲስ ርዕስ ያስተዋውቃል። ስለ ጻፋችሁልን ነገሮች የቆሮንቶስ ሰዎች ለጳውሎስ ለአንዳንድ ጥያቄዎች መልስ ፈልገው ደብዳቤ ጽፈውለት ነበር። ለሰው እዚህ ላይ ወንድ ወይም ሴት የትዳር ጓደኛ ይህ መልካም ነው ትኩረት፡- «ይህ ትክክልና ተቀባይነት ያለው ነው» ነገር ግን ስለ ዝሙት ምክንያት ፈተና ትኩረት፦ «ነገር ግን ሰዎች በዝሙት ፈተና ላይ እንዳይውድቁ» እያንዳንዱ ሰው የራሱ ሚስት ይኑራው እንዲሁም እያንዳንዷ ሴት ለራሷ ባል ይኑራት ብዙ ሚስት በሚያገቡ ማህበር ሰብ ግልጽ ለማድረግ፦«እያንዳንዱ ሰው አንድ ሚስት ሊኖረው ይገባል እንዲሁም እያንዳንዷ ሴት የራሷ ባል ሊኖራት ይገባል»
ስለ ገብረ ሥጋ ግንኙነት መብት ሁለቱም ባልና ሚስት ከትዳር ጓደኛቸው ጋር ሁል ጊዜ አብሮ መተኛት ይገባል።
አብራችሁ ለመተኛት እርስ በርሳችሁ አትከላከሉ ትኩረት፦ «ከትዳር ጓደኛ ጋር አብራችሁ ለመተኛት እምቢ አትበሉ» ለጸሎት ራሳችሁ ለመትጋት ተስማምታችሁ በተለይም ለጸሎት ጊዜ ለመውሰድ ለተወሰኑ ቀናት አብሮ ሳይተኙ ለማሳለፍ ይወስናሉ። በአይሁድ እምነት አንድ ለሁለት ሳምንታት ይሆናል። ራሳችሁን ማትጋት «ራሳችሁን መስጠት» እንደ ገና አንድ ሁኑ ትኩረት፦ «እንደገና አንድ ላይ ተኙ» ራሳችሁን ለመግዛት ካለ መቻል የተነሣ መቆጣጠር* ትኩረት፦ «ምክንያቱም ከጥቂት ቀናት በኋላ የግብረ ሥጋ ፍላጎታችሁን ለመቆጠጠር ከባድ ይሆናል»
ይህን እንደ ፈቃድ እንጂ እንደ ትእዛዝ አይደለም ጳውሎስ የቆሮንቶስን ሰዎችን ለአጭር ጊዜ አብሮ ከመተኛት ለጸሎት መታቀብ ይችላሉ፤ነገር ግን ይህ የተለየ ጉዳይ ነው እንጂ የሚቀጥል መስፈርት አይደለም። እንደ እኔ ቢሆን ያላገቡ (አስቀድሞ ያገቡ ወይም ያላገቡ) እንደ ጳውሎስ ያሉ ነገር ግን እያንዳንዱ ከእግዚአብሔር የራሱ ስጦታ ይኑረው እንዲሁም ሌላውም እንደዚው ይሁን ትኩረት፦ «እግዚአብሔር ለአንድ ሰው ችሎታ ይሰጣል እንዲሁም ለሌላኛው ሰው ሌላ ችሎታ ይሰጣል»
ያላገባ «አሁን ያላገባ» ይህ ያላገቡትንና ቀደም ብሎ ያገቡትን ይጨምራል። መበለት ባል የሞተባት ሴት ይህ መልካም ነው «መልካም» የሚለው ቃል እዚህ ላይ ትክክልና ተቀባይነት ያለው የሚለውን ያመለክታል። ትኩረት፦«ይህ ትክክልና ተቀባይነት ያለው ነው።» መጋባት ባልና ሚስት መሆን
ያገባ የትዳር ጓደኛ ያለው(ባልና ሚስት) መለየት የለባቸውም አብዘኛው የግሪክ ሰዎች ሕጋዊ ፍቺና እንዲሁ መለየትን አይለይም ነበር። «መለየት» ለአብዘኛው ባለ ትዳሮች ጋብቻ የማይቆይ እንደ ሆነ ማለት ነው። ከርሱ ጋር ታረቁ «ከባልዋ ጋር ያለውን ጉዳይ መፍታት አለባቸው እንዲሁም ወደ እርሱም ትመለስ» መፋታት የለባቸውም ይህ «መለየት የለባቸውም» ከሚለው ጋር ተመሳሳይ። (ከላይ ያለውን ማስታወሻ።) ሕጋዊ ፍቺ ወይም እንዲያው መለየት።
ይዘት «ፈቃድ» ወይም«መርካት» የማያምን ባል የተለየ ነው «እግዚአብሔር ያላመነውን ባል» ያላመነት ሴት የተለች ናት «እግዚአብሔር ያላመነችን ሴት ለይቶአል»
እነርሱ የተለዩ ናቸው «እግዚአብሔር »እንርሱን ለይቶአቸዋል»
በዚህ ዓይነት ጉዳይ ወንድሞች ወይም እህት ለቃል ኪዳናቸው የታሰሩ አይደለም «በዚህ ዓይነት ጉዳይ የአማኝ ባለትዳሮች ጋብቻ አስገዳጅነት የላቸውም።»
አንቺ ሴት ባልሽን ታድኚው እንደ ሆነ ምን ታውቂያለሽ? «የማያምን ባልሽን ታድኚው እንደ ሆነ ምን ታውቂያለሽ።»
አንተ ሰው ሚስትህን ታድናት እንደ ሆነ ምን ታውቃለህ «የማታምን ሚስትህን ታድናት እንደ ሆነ ምን ታውቃለህ።»
እያንዳንዱ ሰው «እያንዳንዱ አማኝ» ይህ ለአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ትእዛዜ ነው ጳውሎስ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ በዚህ ሁኔታ እንዲያደርጉ አማኞችን ያስተምራል። አንድ ሰው ሲጠራ ተገርዞአልን ጳውሎስ የተገረዙትን አንድ ሰው ወደ እምነት ሲጠራ ያልተገረዘ ነውን ጳውሎስ ያልተገረዙትን ይጠቅሳል። ትኩረት፦«ላልተገረዙት፤ እግዚአብሔር ለእምነት ሲጠራችሁ ያልተገረዛችሁ ነበርን።»
በጥሪ እዚህ ላይ «ጥሪ» ወደ ሥራ ወይም የምትሳተፉበት ማኅበራዊ ደረጃን ያመለክታል። ትኩረት፦«እንደምታደርጉ ኑሩና ሥሩ።» (UDB) እግዚአብሔር ሲጠራችሁ ባርያ ነበራችሁን? ትኩረት፦ «እግዚአብሔር ለእምነት ሲጠራችሁ ባርያ ለነበራችሁ።» የጌታ ነፃ ሰዎች ይህን ነፃነት በእግዚአብሔር ይቅር ተብላችኋል ስለዚህ ከሰይጣንና ከኀጢአት ነፃ ሁኑ። በዋጋ ተገዝታችኋል ትኩረት፦ «ክርስቶስ ስለ እናንተ በመሞት ገዝቶአችኋል» ለእምነት በምንጠራበት ጊዜ «እግዚአብሔር እኛን ለእምነት በክርስቶስ ሲጠራን» እኛን --- እኛ ሁሉንም ክርስቲያኖችን ይመለከታል
እንግዲህ ያላገቡትን በሚመለከት ከጌታ ትእዛዝ የለኝም ጳውሎስ ስለዚህ ሁኔታ የሚናገር የኢየሱስ ትምህርት እንደ ሌለ ይናገራል። ትኩረት፦ «ስላላገቡ ሰዎች ከጌታ ትእዛዝ የለኝም።» የእኔ አሳብ ጳውሎስ ስለ ጋብቻ እነዚህ አሳቦች የእርሱ እንደ ሆነ እንጂ በቀጥታ ከጌታ አለመሆኑን ያሳስባል። ስለዚህ ትኩረት፦ «እንግዲህ/ስለዚህ» ወይም «በዚህ ምክንያት» ለችግር ጊዜ መፍትሔ እንዲሆን ትኩረት፦ «የሚመጣ መከራ»
ከአንዲት ሴት ጋር በጋብቻ ታስራችኋል ጳውሎስ ላገቡት ወንዶች ይናገራል። ትኩረት፦ «ያገባችሁ ከሆነ» ከዚህ ነፃ ለመሆን አትሻ ትኩረት፦ «ከጋብቻ ቃል ኪዳን ነፃ ለመሆን አትሞክሩ» ከሚስትህ ጋር በቃል ኪዳን ነፃ ወይም ያላገባህ ነህ? ጳውሎስ አሁን ላላገቡት ይናገራል። ትኩረት፦ «አሁን ያላገባህ ከሆንህ» ሚስት አትሻ ትኩረት፦ «ለማግባት አትፈልግ» መሰጠት «ተከናወነ» ወይም «ተሳትፎአል» ከእነርሱ ለመለየት እወዳለሁ ትኩረት፦ «ከእነርሱ ጋር እንድትሆን አልወድም»
ጊዜው አጭር ነው ትኩረት፦ «ጥቂት ጊዜ አለ» ወይም «ጊዜው ተጋባዶአል» ማልቀስ «መጮህ» ወይም «በእንባ ማዘን» ከዓለም ጋር የሚተባበሩ ትኩረት፦ «በየቀኑ ከማያምኑ ጋር የሚተባበሩ» ከዚህ ጋር ምንም እንደ ሌለ ትኩረት፦ «ከማያምኑ ጋር ምንም ግንኙነት እንደ ሌለ» የዚህ ዓለም አሠራር መጨረሻ ደርሷል ይህ ዓለም በሰይጣን ሥር ከመሆኑ የተነሣ ይህ ዓለም በአጭር ጊዜ ያልፋል።
ከጭንቀት ነፃ መሆን ትኩረት፡- «ጸጥ ማለት» ወይም ያለ ጭንቀት» ስለ አንድ ነገር ትኩረት መስጠት «በአንድ ነገር ማተኮር» እርሱ ተከፍሏል ትኩረት፦ «እግዚአብሔርን ለማስደሰት እንዲሁም ሚስቱን ለማስደሰት ይፈልጋል»
እጥረት «ሸክም» ወይም «ገደብ» ለዚህ ተሰጥቶ ሊሆን ይችላል «ትኩረት መስጠት ይችላል»
አጠቃላይ መረጃ አንዳንድ ሰዎች ጳውሎስ ያላገቡ ሰዎች ለማግባት ስለሚፈልጉ ሴቶች እንደ ሚናገር ያስባሉ (see ULB and UDB። ሌሎች ደግሞ ጳውሎስ የሚናገረው ስላላገቡ ሴቶች አባቶች እንደ ሆነ ያስባሉ (በዚህ ማስታወሻ ያሉትን አማራጭ ትርጉሞችን ተመልከት)። በአክብሮት አለመያዝ «ቸር አለመሆን» ወይም «አለማክበር» እጮኛውን አማራጭ ትርጉሞች 1)«ሊያገባት ተስፋ የሰጣት ሴት» ወይም 2)«ድንግል የሆነች ልጃ ገረድ።» እጮኛ አንድ ሴት እና አንድ ወንድ ለጋብቻ የተስማሙበት ፍላጎቱ በጣም ከፍተኛ አማራጭ ትርጉሞች 1) ስለ ወስባዊ ፍላጎቱ (UDB) ወይም 2) «ምክንያቱም ሴቷ ለማግባት የዕድሜ ብቁነት» ያግባት አማራጭ ትርጉሞች 1)«እጮኛውን ያግባት»(UDB) ወይም 2) «ሴት ልጁ ለጋብቻ ይፍቀድ» ላለማግባት ከወሰነ አማራጭ ትርጉሞች 1)«ለማግባት ፍላጎት እንደ ሌለ ከወሰነ» (UDB) ወይም 2) «እንድታገባ ሴት ልጁን የማይፈቅ ከሆነ» እርስዋን በለማግባቱ መልካም አደረገ አማራጭ ትርጉሞች 1) «እርስዋን ላለማግባት የሚያደርገው ውሳኔ መልካም ነው» (UDB) ወይም 2)«ያላገባችውን እንዳታገባ ቢያቆያት መልካም ነው።» እጮኛውን ያገባል አማራጭ ትርጉም፦ «ሴት ልጁ ለጋብቻ ይሰጣታል» ለማግባት አይመርጥም አማራጭ ትርጉም፦ «ሴት ልጁን ለጋብቻ አይሰጥም»
በሕይወት ካለ «እስከ ሞት ድረስ» የፈለገችውን ትኩረት፦ «ማንንም የፈለገችውን» በጌታ ትኩረት፦ «አዲሱ ባል አማኝ ከሆነ» ፍርዴ «የእግዚአብሔርን ቃል መረዳቴ» ደስተኛ የበለጠ ተስማምቶአል፤ የበለጠ ደስተኛ እንዳለ ይኖራል ትኩረት፦ «ሳያገባ ይኖራል»
1 ለጣዖት ስለተሰዋ ሥጋ፦ "ሁላችንም ዕውቀት እንዳለን" እናውቃለን።ዕውቀት ያስታብያል፤ ፍቅር ግን ያንጻል። 2 አንድ ሰው አንድ ነገር እንደሚያውቅ ቢያስብ፥ ያ ሰው ፥እንደሚገባ እንደሚያውቅ ገና አለወቀም። 3 ነገር ግን ማንም ሰው እግዚአብሔርን ቢወድ እርሱም በእግዚአብሔር ዘንድ ይታወቃል። 4 እንግዲህ ለጣዖት የተሠዋውን ሥጋ ስለ መብላት በተመለከተ፦ "የዚህ ዓለም ጣዖት ከንቱ ነው፤" እና "ከአንዱም ከእግዚአብሔር በቀር ሌላ አምላክ የለም" ይህንን እናውቃለን። 5 ብዙ "አማልክትና ጌቶች" እንዳሉ ሁሉ፥ ምንም እንኳ በሰማይና በምድር አማልክት የተባሉ ቢኖሩ ለእኛስ ነገር ሁሉ ከእርሱ የሆነ 6 እኛም ለእርሱ የሆንን አንድ አምላክ አብ ብቻ አለን፤ እንዲሁም ነገር ሁሉም በእርሱ በኩል የሆነ እኛም በእርሱ በኩል የሆንን አንድ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ አለን። 7 ይሁን እንጂ ይህ ዕውቀት በሁሉም አይገኝም። በዚህ ፈንታ፥ አንዳንዶች ግን እስካሁን ድረስ ጣዖትን ማምለክ ስለ ለመዱ፦ ለጣዖት እንደ ተሠዋ አድርገው ይበላሉ። ሕሊናቸው ደካማ ስለ ሆነ ይረክሳሉ። 8 መብል ግን ወደ እግዚአብሔር አያደርሰንም። ስላልበላምንም አንረክስም፤ ወይም ስለበላንም የተሻለን አንሆንም። 9 ነገር ግን ይህ ነጻነታችሁ በእምነት ደካማ ለሆኑት ምክንያት ሆኖ መሰናከያ እንዳይሆን ተጠንቃቁ። 10 አንተ ዕውቀት ያለህ በጣዖት ቤት በማዕድ ተቀምጠህ ስትበላ አንድ ሰው ቢያይህ፤ በእምነቱ ያልጠነከረ ሰው ለጣዖት የተሠዋውን ለመብላት አይደፋፈርምን? 11 ስለ ጣዖት ባሕርይ በአንተ ዕውቀት የተነሣ ክርስቶስ የሞተላቸው ደካማ ወንድም ወይም እህት ይጠፋሉ። 12 ስለዚህም ወንድሞችንና እህቶችን ስትበድሉና ደካማ ሕሊናቸውንም ስታቆሽሹ ክርስቶስን ትበድላላችሁ። 13 ስለዚህም መብል ወንድሜንና እህቴን የሚያሰናክል ከሆን ወንድሜንና እህት እንዳላሰናክል ለዘላለ ከቶ ሥጋን አልበለም።
እንግዲህ ስለ ጳውሎስ የቆሮንቶስ ሰዎች ወደ ጠየቁበት ጥያቄ መሸጋገሪያ እንዲሆን ይህን ሐረግ ይጠቀማል። ለጣዖት የተሠዋ አህዛብ ለአምልኮአቸው እህል፥ዓሣ፥ ወፍ፥ ወይም ሥጋ ለአማልክት ይሠዋሉ። ካህናቱም የመሥዋዕቱን ከፊል በመሠዊያ ላይ እንዲቃጠል ያደርጋሉ። ጳውሎስ የሚናገረው ለሚያመልኩት ወይም በገበያ ስለሚሸጠው ቀሪው ክፍል ነው። «ሁላችንም ዕውቀት እንዳለን» እናውቃለን ጳውሎስ አንዳንድ የቆሮንቶስ ሰዎች ካሉት ይህን ሐረግ ይጠቅሳል። ትኩረት፡- 'ሁላችን ዕውቀት አለን' ራሳችሁ እንደምትሉ «ሁላችን እናውቃለን።» ትዕቢት «አንድ ሰው ይታበያል» ወይም «አንድ ሰው ራሱን ከሌላ የተሻለ እንደሆን ያስባል» አንድ ነገር እንደሚያውቅ ያስባል «ማንኛውንም ነገር እንደሚያውቅ ያምናል» ይህ ሰው በእርሱ ዘንድ ይታወቃል «እግዚአብሔር ይህን ሰው ያውቃል» (ተመልከት፦ )
እናውቃለን «እኛ» ማለት ጳውሎስና የቆሮንቶስ ሰዎች የዚህ ዓለም «ጣዖት ምንም እንደ ሆን እናውቃለን» ጳውሎስ አንዳንድ የቆሮንቶስ ሰዎች ከተጠቀሙት ይህን ሐረግ ይጠቅሳል። ትኩረት፦ «ራሳችሁ እንደምትሉ፥'ጣዖት ኀይል እንደሌለ ወይም ለእኛ ትርጉም የለም' እንደምትሉ እናውቃለን» ጣዖታትና ጌቶች ጳውሎስ በብዙ ጣዖቶች አያምንም ነገር ግን አይዛብ በጣዖታት እንደሚያምኑ ያውቃል። እኛን ይህ «እኛን» የሚለው ጳውሎስና የቆሮንቶስ ሰዎችን ነው። ለእኛ አለን «እናምናለን»
እያንዳንዱ ሰው አንዳንዶች «ሁሉም ሰዎች» ከሁሉም ሰዎች የተወሰኑ ክፍሎች የተበላሹ «የጠፉ» ወይም «የተጎዱ»
ምግብ ወደ እግዚአብሔር አያደርስም «ምግብ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነትን አያስገኝም» ወይም «የምንበላው ምግብ እግዚአብሔርን ደስ አያሰኝም ደካማ የሆነ ሰው በእምነታቸው ብርቱ ያልሆኑ ለመብላት የሚደፍሩ «ለመብላት የበረታቱ»
ደካማ ወንድም ወይም እህት ይጠፋሉ ወንድም ወይም እህት በእምነታቸው ያልበረቱ እምነታቸው ይፈተናል ወይም እምነታቸውን ያጣሉ። ስለዚህ «ከዚህ መጨረሻ መመሪያ የተነሣ» ምግብ ምክንያት ከሆነ «ምግብ ይህን የሚያስከትል» ወይም «ምግብ የሚያደፋፍር ከሆነ»
1 እኔ ነፃ አይደለሁም? እኔ ሐዋርያስ አይደለሁም? ጌታችን ኢየሱስን አላየሁትም? እናንተስ በጌታ የሥዬ ፍሬዎች አይደላችሁም? 2 ለሌሎች ሐዋርያ ባልሆን እንኳ ቢያንስ ለእናንተ ሐዋርያ ነኝ። በጌታ ሐዋርያ ለመሆኔ እናንተ ማረጋገጫ ናችሁና። 3 ለሚጠይቁኝ መልሴ ይህ ነው። 4 እኛስ ለመብላትና ለመጠጣት መብት የለንም? 5 እንደ ሌሎቹ ሐዋርያት፣ እንደ ጌታ ወንድሞች፣ እና እንደ ኬፋ፣ አማኝ የሆነች ሚስት ይዞ ለመሄድ መብት የለንም? 6 ወይስ የመሥራት ግዴታ ያለብን እኔና በርናባስ ብቻ ነን? 7 በራሱ ወጪ በውትድርና የሚያገለግል ማን ነው? የወይን ተክል ተክሎ ከፍሬው የማይበላ ማን ነው? ወይስ ከሚጠብቀው መንጋ ወተት የማይጠጣ ማን ነው? 8 እነዚህን ነገሮች የምናገረው በሰው ሥልጣን መሠረት ነው? ሕጉስ ይህን አይልም? 9 በሙሴ ሕግ፦ "የሚያበራየውን በሬ፣አፉን አትሰር" ተብሎ ተጽፎአል። በእርግጥ እግዚአብሔር ስለ በሬዎች አስቦ ነው? 10 እየተናገረ ያለው ስለ እኛ አይደለም? የተጸፈው ስለ እኛ ነው፣ምክንያቱም የሚያርስ በተስፋ ሊያርስ፣የሚያበራይም ከመከሩ ለመካፈል ተስፋ በማድረግ ሊያበራይ ይገባዋል። 11 በመካከላችሁ መንፈሳዊ ነገር ዘርተን ከሆነ፣ከእናንተ ቁሳዊ ነገሮችን ብናጭድ ይበዛብናል? 12 ሌሎች ይህን መብት ከእናንተ የሚያገኙ ከሆነ፣እኛስ የበለጠ መብት የለንም? ሆኖም ግን ይህን መብት ይገባናል አላልንም፣ይልቁንም ለክርስቶስ ወንጌል እንቅፋት እንዳንሆን ሁሉን ታገስን። 13 በመቅደስ የሚያገለግሉ ምግባቸውን ከመቅደስ እንደሚያገኙ አታውቁም፣በመሠዊያው ላይ የሚያገልግሉስ መሠዊያው ላይ ከሚሠዋው እንደሚካፈሉ አታውቁም? 14 እንዲሁም ደግሞ ወንጌልን የሚያውጁ ከወንጌል በሚገኝ እንዲኖሩ ጌታ አዟል። 15 እኔ ግን ከእነዚህ መብቶች አንዱንም ይገባኛል አላልሁም። ይህንንም የጻፍሁት አንዳች እንዲደረግልኝ አይደለም። ይህን ትምክህቴን ማንም ከሚወስድብኝ ሞትን እመርጣለሁ። 16 ይህ ግዴታዬ ስለሆነ ወንጌል ብሰብክ የምታበይበት ምክንያት የለኝም፣ ወንጌልን ባልሰብክ ግን ወዮልኝ! 17 ይህን በፈቃደኝነት ባደርገው ግን ሽልማት አለኝ። በፈቃደኝነት ባላደርገው ግን በአደራ የተሰጠኝ ኃላፊነት አለብኝ። 18 ታዲያ ሽልማቴ ምንድነው? በወንጌል ውስጥ ያለ ሙሉ መብቴን ትቼ ያለምንም ክፍያ ወንጌልን ስሰብክ ነው። 19 ምንም እንኳ ከሁሉም ነፃ ብሆንም፣ ብዙዎችን ለመማረክ እንድችል፣የሁሉ አገልጋይ ሆንሁ። 20 አይሁድን ለመማረክ እንድችል፣ እንደ አይሁዳዊ ሆንሁ። ምንም እንኳ በሕግ ስር ባልሆንም፣ በሕግ ስር ያሉትን መማረክ እንድችል፣ ከሕግ ስር እንዳለ ሰው ሆንሁ። 21 ከሕግ ውጭ ያሉትን መማረክ እንድችል፣እኔ ራሴ ከእግዚአብሔር ሕግ ውጭ ሳልሆን፣ ነገር ግን ከክርስቶስ ሕግ ስር እያለሁ፣ ከሕግ ውጭ እንዳለ ሰው ሆንሁ። 22 ደካማውን መማረክ እንድችል፣እንደ ደካማ ሆንሁ። አንዳንዶችን ማዳን እንድችል፣ ለሰዎች ሁሉ ብዬ ሁሉን ሆንሁ። 23 ይህን ሁሉ ያደረግሁት ከወንጌል በረከት መካፈል እንድችል፣ ስለ ወንጌል ብዬ ነው። 24 በሩጫ ውድድር የሚሳተፉ ሯጮች ሁሉ እንደሚሮጡ፣ ነገር ግን ሽልማት የሚቀበል አንዱ ብቻ እንደሆነ አታውቁም? ስለዚህ ሽልማት ለማግኘት ሩጡ። 25 ለውድድር የሚዘጋጅ ሰው ሥልጠና ጊዜ ሁሉ ራሱን መቆጣጠር ይለማመዳል። እነርሱ የሚጠፋውን ሽልማት ለማግኘት ይሮጣሉ፣ እኛ ግን የማይጠፋውን ሽልማት ለማግኘት እንሮጣለን። 26 ስለዚህም ያለ ዓላማ አልሮጥም፣ወይም ንፋስ በቦክስ አልመታም። 27 ነገር ግን ለሌሎች ከሰበክሁ በኋላ ከውድድሩ ውጭ እንዳልሆን ሥጋዬን በመቆጣጠር አስገዛዋለሁ።
1 ወንድሞች እና እህቶች፣ይህን እንድታውቁ እወዳለሁ፣አባቶቻችን ከዳመና በታች እና በባሕር ውስጥ አለፉ። 2 ሁሉም በዳመና እና በባሕር ውስጥ በሙሴ ተጠመቁ፣ 3 መንፈሳዊ ምግብ ተመገቡ፣ 4 ሁሉም አንድ ዓይነት መንፈሳዊ መጠጥ ጠጡ። እነርሱም ይከተላቸው ከነበረው መንፈሳዊ ዓለት ጠጡ፣ያም ዓለት ክርስቶስ ነበር። 5 ነገር ግን እግዚአብሔር በብዙዎች አልተደሰተምና ሬሳቸው ምድረ በዳ ውስጥ ወድቆ ቀረ። 6 እኛም እነርሱ እንዳደረጉት ክፉ ነገር እንዳንመኝ እነዚህ ነገሮች ምሳሌ እንዲሆኑልን ተጽፈውልናል። 7 "ሕዝቡ ሊበሉና ሊጠጡ ተቀመጡ፣በዝሙት ፍላጎት በመነሳሳት ሊጨፍሩ ተነሡ።" ተብሎ እንደተጻፈ፣ከእነርሱ አንዳንዶች እንዳደረጉት ጣዖት አምላኪዎች አትሁኑ። 8 ከእነርሱ ብዙዎች ዝሙት በመፈጸማቸው ምክንያት ሃያ ሦስት ሺ ሰዎች በአንድ ቀን እንደሞቱ፣እኛም ዝሙት አንፈጽም። 9 ከእነርሱም ብዙዎች ክርስቶስን እንደፈተኑት እና በእባብ እንደጠፉ፣እኛም ጌታን እንፈታተን። 10 በማጉረምረማቸው ምክንያት የሞት መልአክ እንዳጠፋቸው፣እኛም አናጉረምርም። 11 በእነርሱ ላይ የሆኑት እነኚህ ነገሮች ምሳሌ እንዲሆኑልን የተጻፈው፣ የዘመን ፍጻሜ ለደረሰብን ለእኛ ትምህርት እንዲሆንልን ነው። 12 ስለዚህ ማንም ቆሜአለሁ ብሎ የሚያስብ፣ እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ። 13 በሰው ሁሉ ላይ ከሚደርሰው በላይ የሆነ ፈተና አልደረሰባችሁም። ነገር ግን እግዚአብሔር ታማኝ ነውና ከምትችሉት በላይ እንድትፈተኑ አያደርግም። ይልቁን ፈተናውን መወጣት እንድትችሉ ከፈተናው ጋር ማምለጫ መንገዱንም ያዘጋጅላችኋል። 14 ስለዚህ ወዳጆቼ ሆይ፣ከጣዖት አምልኮ ሽሹ። 15 ይህን የምናገራችሁ አስተዋዮች በመሆናችሁ ነው፤የምለውን አመዛዝኑ። 16 የምንባርከው የበረከት ጽዋ፣የክርስቶስን ደም መካፈል አይደለም? የምንቆርሰው እንጀራ የክርስቶስን ሥጋ መካፈል አይደለም? 17 እንጀራው አንድ እንደሆነ፣ብዙዎች ሆነን ሳለ አንዱን እንጀራ በመካፈል አንድ አካል ነን። 18 የእስራኤልን ሕዝብ ተመልከቱ፦ ከመሥዋዕቱ የሚበሉ ከመሠዊያው ተካፋዮች አይደሉም? 19 ስለዚህ ምን እያልሁ ነው? ጣዖት ምንም አይደለም እያልሁ ነው? ወይስ ለጣዖት የተሠዋ ምግብ ምንም አይደለም ማለቴ ነው? 20 እያልሁ ያለሁት፣አሕዛብ የሚሠዋቸው ነገሮች፣ለአጋንንት እንጂ ለእግዚአብሔር አይደለም። ከአጋንንት ጋር ተካፋዮች እንድትሆኑ አልፈልግም! የጌታንም ጽዋ፣ የአጋንንትንም ጽዋ ልትጠጡ አትችሉም። 21 በጌታም ማዕድ፣ በአጋንንትም ማዕድ ኅብረት ልታደርጉ አትችሉም። 22 ይህን ብማድረግ ጌታን ለቅናት እናነሳሳዋለን? ከእርሱ የምንበረታ ነን? 23 "ሁሉም ነገር ተፈቅዷል፣" ነገር ግን ሁሉም ነገር የሚጠቅም አይደልም። "ሁሉም ነገር ተፈቅዷል፣" ነገር ግን ሁሉም ነገር ሰዎችን የሚያንጽ አይደለም። 24 ማንም ለራሱ መልካም የሆንውን ብቻ አያስብ። ይልቁን፣እያንዳንዱ ለሌሎች ሰዎች ሁሉ መልካም የሆነውን ይፈልግ። 25 በገበያ ቦታ የሚሸጥ ማንኛውንም ነገር፣የኅሊና ጥያቄ ሳታነሱ መብላት ትችላላችሁ። 26 "ምድርና በውስጧ ያለው ሁሉ የጌታ ነውና።" 27 አንድ አማኝ ያልሆነ ሰው ምግብ ቢጋብዛችሁና ግብዣውን ተቀብላችሁ መሄድ ብትፈልጉ፣ በፊታችሁ የቀረበላችሁን ማንኛውንም ነገር የኅሊና ጥያቄ ሳታነሱ ብሉ። 28 ነገር ግን እንድ ሰው፣"ይህ ምግብ ለጣዖት የተሠዋ ነው።" ብሎ ቢነግራችሁ አትብሉ። ይህን ማድረግ የሚገባችሁ፣ ለነገራችሁ ሰው እና ለኅሊና ስትሉ ነው። 29 ይህን ስል ስለ እናንተ ኅሊና ሳይሆን ስለ ሌላው ሰው ኅሊና ነው። ስለ ሌላው ኅሊና ሲባል ለምን በነፃነቴ ላይ ይፈረዳል? 30 ምግቡን በአክብሮት ከተቀበልሁ፣አመስግኜ ለበላሁት ነገር ለምን እሰደባልሁ? 31 ስለዚህ፣ስትበሉ እና ስትጠጡ፣ወይም በምታደርጉት ሁሉ፣ሁሉን ለጌታ ክብር አድርጉት። 32 ለአይሁዶች ወይም ለግሪኮች፣ እንዲሁም ለእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን መሰናከያ አታድርጉ። 33 እኔ ሰዎችን ሁሉ በሁሉ ነገር ደስ ለማሰኘት እንደምፈልግ ሁሉ እናንተም እንዲሁ አድርጉ። የራሴን ጥቅም ሳይሆን፣ለብዙዎች ጥቅም የሚሆነውን እፈልጋለሁ። ይህን የማደርገው ወደ ድነት እንዲመጡ ብዬ ነው።
1 እኔ ክርስቶስን እንደምመስል፣እናንተም እኔን ምሰሉ። 2 አሁን የማመሰግናችሁ በሁሉ ነገር ስለምታስቡኝ ነው። ለእናንተ ያስተላለፍኳቸውን ልምዶች ልክ እንደዚያው እንዳሉ አጥብቃችሁ በመያዛችሁ አመሰግናችኋለሁ። 3 ክርስቶስ የወንድ ሁሉ ራስ ፣ወንድ ደግሞ የሴት ራስ ፣ እግዚአብሔር የክርስቶስ ራስ እንደሆነ እንድትረዱ እፈልጋለሁ። 4 ራሱን ሸፍኖ የሚጸልይ ወይም ትንቢት የሚናገር ወንድ የእርሱ ራስ የሆነውን ክብር ያሳጣል። 5 ነገር ግን ራሷን ሳትሸፍን የምትጸልይ ወይም ትንቢት የምትናገር ሴት ራሷን ክብር ታሳጣለች። ይህን ማድረግ ልክ ጠጉሯን እንደመላጨት ነው። 6 ሴት ራሷን ካልሸፈነች፣ጠጕሯን አሳጥራ መቆረጥ ይኖርባታል። ሴት ጠጕሯን አሳጥራ መቆረጧ ወይም መላጭቷ አሳፋሪ ከሆነ፣ ራሷን ትሸፍን። 7 ወንድ ራሱን መሸፈን የለበትም፣ ምክንያቱም እርሱ የእግዚአብሔር መልክ እና ክብር ነውና። 8 ሴት ግን የወንድ ክብር ነች። ወንድ ከሴት አልተገኘምና። ይልቁንስ፣ሴት ከወንድ ተገኝታለች። 9 ወንድ ለሴት አልተፈጠረም፣ሴት ግን ለወንድ ተፈጥራለች። 10 ለዚህ ነው፣ ከመላእክቱ የተነሳ፣ ሴት በራሷ ላይ የሥልጣን ምልክት ሊኖራት የሚገባው። 11 የሆነ ሆኖ፣በጌታ ሴት ከወንድ፣ ወንድም ከሴት የተነጣጠሉ አይደሉም። 12 ሴት የተገኘችው ከወንድ እንደሆነ ሁሉ፣ወንድም የተገኘው ከሴት ነው። ሁሉም ነገር ደግሞ የተነኘው ከእግዚአብሔር ነው። 13 ራሳችሁ ፍረዱ፦ሴት ራሷን ሳትሸፈን ወደ እግዚአብሔር ብትጸልይ ተገቢ ነው? 14 ወንድስ ረጅም ጠጕር ቢኖረው አሳፋሪ እንደሆነ ተፈጥሮ ራሱ አያስተምራችሁም? 15 ሴት ግን ረጅም ጠጕር ቢኖራት ክብሯ እንደሆነ ተፈጥሮ ራሱ አያስተምራችሁም? ለእርሷ ጠጕር የተሰጣት እንደ መሸፈኛ ነውና። 16 ነገር ግን በዚህ ማንም ክርክር ሊያስነሳ ቢፈልግ፣እኛም ሆንን የእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት ከዚህ የተለየ ልምምድ የላቸውም። 17 በሚከተሉት መመሪያዎቼ ግን፣አላመሰግናችሁም። ምክንያቱም በምትሰበሰቡበት ጊዜ፣ ለተሻለ ነገር ሳይሆን እጅግ ለከፋ ነገር ትሰበሰባላችሁ። 18 በመጀመሪያ፣ በቤተክርስቲያን ስትሰበሰቡ በመካከላችሁ መከፋፈል እንዳለ ሰምቼአለሁ፣ ደግሞም ይህ እንደሚሆን በመጠኑም ቢሆን አምኜበታልሁ። 19 ምክንያቱም በእናንተ መካከል ተቀባይነትያላቸው እንዲለዩ የተለያዩ ቡድኖች መኖራቸው ግድ ነው። 20 በአንድነት በምትሰብሰቡበት ጊዜ፣የምትበሉት የጌታን ማዕድ አይደለምና። 21 በምትበሉበት ጊዜ፣ሌሎች ምግብ ከማግኘታቸው በፊት እያንዳንዱ ቀድሞ የየራሱን ምግብ ይበላል። አንዱ ተርቦ ሳለ ሌላው ይሰክራል። 22 የምትበሉበትና የምትጠጡበት ቤት የላችሁም? የእግዚአብሔርን ቤተክርስቲያን በመናቅ ምንም የሌላቸውን ታዋርዳላችሁ? ምን ልበላችሁ? ታዲያ ላመስግናችሁ? ለዚህ አላምሰግናችሁም! 23 ከጌታ የተቀበልሁትን ለእናንተ አሳልፌ ሰጥቼአለሁ፣ ጌታ ኢየሱስ ታልፎ በተሰጠበት ምሽት፣እንጀራ አንሳ። 24 ካመሰገነ በኋላ ቆረሰውና፣"ለእናንተ የሆነ ሥጋዬ ይህ ነው፣ይህን እኔን ለማስታወስ አድርጉት፣" አለ። 25 እንዲሁም ከእራት በኋላ ጽዋን አንስቶ፣"ይህ በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው።ይህን በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ እኔን ለማስታወስ አድርጉት።" 26 ይህን እንጀራ በበላችሁ እና ይህን ጽዋ በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ፣ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ታውጃላችሁ። 27 ስለዚህ ማንም፣ተገቢ ባልሆነ ሁኔታ የጌታን እንጀራ ቢበላ ወይም የጌታን ጽዋ ቢጠጣ፣ለጌታ ሥጋ እና ለጌታ ደም ተጠያቂ ይሆናል። 28 አንድ ሰው ራሱን ከመረመረ በኋላ እንጀራውን ይብላ ጽዋዉንም ይጠጣ። 29 የጌታ ሥጋ መሆኑን ሳይረዳ የሚበላ እና የሚጠጣ፣በራሱ ላይ ፍርድን ይበላል ይጠጣልም። 30 በመካከላችሁ ብዙዎች የታመሙ እና በሽተኞች የሆኑት ስለዚህ ነው፣ አንዳንዶችም ደግሞ ሞተዋል። 31 ነገር ግን ራሳችንን ብንመረምር አይፈረድብንም። 32 በጌታ ስንፈረድ ግን፣ከዓለም ጋር እንዳንኮነን እንገሠጻለን። 33 ስለዚህ፣ወንድሞቼ እና እህቶቼ፣ለመብላት ስትሰበሰቡ፣እርስ በርሳችሁ ተጠባበቁ። 34 ማንም የተራበ ቢኖር፣እቤቱ ይብላ፣እንዲያ ሲሆን ስትሰበሰቡ ለፍርድ አይሆንባችሁም። ስለ ጻፋችሁልኝ ሌሎች ነገሮች፣ስመጣ መመሪያዎችን እሰጣለሁ።
1 ወንድሞች እና እህቶች መንፈሳዊ ስጦታዎችን በተመለከተ፣የማታውቁት ነገር እንዲኖር አልፈልግም። 2 አረማውያን በነበራችሁበት ወቅት፣መናገር እንኳ በማይችሉ ጣዖታት ወደማታውቁት መንገድ ተመርታችሁ እንደነበር ታውቃላችሁ። 3 ስለዚህ ማንም በእግዚአብሔር መንፈስ፣"ኢየሱስ የተረገመ ነው፣" የሚል እንደሌለ ሁሉ፤ እንዲሁም በእግዚአብሔር መንፈስ ካልሆነ በቀር፣"ኢየሱስ ጌታ ነው፣" ሊል የሚችል እንደሌለ እወቁ። 4 ልዩ ልዩ ስጦታዎች አሉ፣መንፈስ ቅዱስ ግን አንድ ነው። 5 አገልግሎቶች ልዩ ልዩ ናቸው፣ጌታ ግን አንድ ነው። 6 ልዩ ልዩ ሥራዎች አሉ፣ነገር ግን ለእያንዳንዱ ሰው ችሎታን የሚሰጥ አንዱ እግዚአብሔር ነው። 7 ደግሞም ለእያንዳንዱ መንፍስ ቅዱስን መግለጥ የተሰጠው ለሁሉም ጥቅም ሲባል ነው። 8 ለአንዱ የጥበብ ቃል በመንፈስ ቅዱስ ይሰጣል፣ለሌላው ደግሞ የእውቀት ቃል በዚያው መንፈስ ይሰጣል። 9 ለሌላው በዚያው መንፈስ እምነት ይሰጠዋል፣ለሌላው ደግሞ በዚያው መንፈስ የፈውስ ስጦታ ይሰጠዋል። 10 ለሌላው ደግሞ የኃይል ሥራዎች፣ለሌላው ትንቢት መናገር። ለሌላው ደግሞ መናፍስትን መለየት፣ለሌላው በልዩ ልዩ ልሳኖች መናገር፣እና ለሌላው ልሳኖችን የመተርጎም ስጦታ ይሰጠዋል። 11 ነገር ግን፣ለእያንዳንዳቸው እንደወደደ ልዩ ልዩ ስጦታዎችን በመስጠት በእነዚህ ሁሉ የሚሠራው ያው አንዱ መንፈስ ቅዱስ ነው። 12 አካል አንድ ሆኖ ሳለ ብዙ ብልቶች እንዳሉት ሁሉ፣ ሁሉም ብልቶች የእንዱ አካል ክፍል እንደሆኑ፣በክርስቶስም እንዲሁ ነው። 13 በአንድ መንፈስ በአንድ አካል እንደተጠመቅን፣አይሁድ ይሁኑ ግሪኮች፣ባሪያ ይሁን ነጻ፣ሁሉ ከአንዱ መንፈስ ጠጥተዋል። 14 አካል አንድ ብልት ብቻ ሳይሆን ብዙ ብልቶች አሉት። 15 እግር፣"እኔ እጅ አይደለሁም፣ስለዚህ የአካሉ ክፍል አይደለሁም፣" ቢል የአካሉ ክፍል መሆኑ አይቀርም። 16 ጆሮም ተነስቶ፣"ዓይን ስላይደለሁ፣የአካሉ ክፍል አይደለሁም፣" ቢል የአካሉ ክፍል ከመሆን አይቀነስም። አካል ሁሉ ዓይን ቢሆን፣ መስማት ወዴት ይሆናል? 17 አካል ሁሉ ጆሮ ቢሆን፣ማሽተት ወዴት ይሆናል? 18 እግዚአብሔር ግን እያንዳንዱን የአካል ክፍል እንደወደደ ሠርቶታል። 19 ሁሉም አንድ ብልት ቢሆኑ ኑሮ፣አካል ወዴት በሆነ ነበር? 20 አሁን ግን ብዙ ብልቶች ያሉት፣ አንድ አካል ነው። 21 ዓይን እጅን፣"አንተ አታስፈልገኝም፣" ሊል አይችልም። ራስም እግርን፣"አታስፈልገኝም፣" ሊል አይችልም። 22 ነገር ግን ዝቅተኛ ግምት የሚሰጣቸው ብልቶች አስፈላጊ ናቸው፣ 23 ዝቅተኛ ግምት የምንሰጣቸውን የሰውነት ክፍሎች ትልቅ ክብር እንሰጣቸዋለን፣እምናፍርባቸውን ብልቶች ደግሞ በአክብሮት እንይዛለን። 24 የማናፍርባቸውን ብልቶች ደግሞ በአክብሮት መያዝ አያስፈልገንም ምክንያቱም ቀድሞዉኑ ክብር አግኝተዋል። እግዚአብሔር ግን ብልቶችን ሁሉ በአንድነት በማያያዝ ክብር ላልተሰጣቸው የበለጠ ክብርን ሰጥቷል። 25 እግዚአብሔር እንዲህ ያደረገው በአካል ውስጥ መከፋፈል እንዳይኖርና ይልቁን ብልቶች በበለጠ ፍቅር እርስ በርሳቸው አንዳቸው ሌላቸውን እንዲከባከቡ ነው። 26 እናም አንዱ ብልት ሲሰቃይ ሁሉም ብልቶች አብረው ይሰቃያሉ። አንዱ ብልት ሲከብር፣ሁሉም ብልቶች አብረው ሐሴት ያደርጋሉ። 27 እንግዲህ እናንተ የክርስቶስ አካል ስትሆኑ እያንዳንዳችሁ የአካሉ ብልቶች ናችሁ። 28 እግዚአብሔርም በቤተክርስቲያን በመጀመሪያ ሐዋርያትን፣ሁለተኛ ነቢያትን፣ሦስተኛ አስተማሪዎችን፣ከዚያም ተአምራት ማድረግን፣በመቀጠል የፈውስ ስጦታዎችን፣እርዳታ የሚያደርጉትን፣ የአስተዳደር ሥራ የሚሠሩትን፣ እና ልዩ ልዩ ዓይነት ልሳኖችን የሚናገሩትን ሰጥቷል። 29 ታዲያ ሁላችን ሐዋርያት ነን? ሁላችንስ ነቢያት ነን? ወይስ ሁላችን አስተማሪዎች ነን? ሁላችን ተአምራቶችን እናደርጋለን? 30 ሁላችን የፈውስ ስጦታዎች አሉን? ሁላችን በልሳኖች እንናገራለን? ሁላችን ልሳኖችን እንተረጉማለን? 31 የሚበልጡትን ስጦታዎች በከፍተኛ ጉጉት ፈልጉ። እጅግ የሚበልጠውንም መንገድ አሳያችኋልሁ።
1 በሰዎች እና በመላእክት ልሳኖች ብናገር፣ግን ፍቅር ከሌለኝ፣የሚንጫጫ ቃጭል ወይም የሚጮህ ታንቡር ነኝ። 2 የትንቢት ስጦታ ቢኖረኝ፣ የተሰወሩ እውነቶችን እና እውቀት ሁሉ ቢኖረኝ፣ተራሮችን ከስፍራቸው የሚያስወግድ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ፣ ፍቅር ከሌለኝ ግን ምንም የማይጠቅም ነኝ። 3 ድሆችን ለመመገብ ያለኝን ሁሉ ብሰጥ፣ ሰውነቴንም እንዲቃጠል ብሰጥ፣ፍቅር ከሌለኝ ግን ምንም አይጠቅመኝም። 4 ፍቅር ታጋሽና ደግ ነው። ፍቅር አይመቀኝም ደግሞም አይመካም። አይታበይም 5 ወይም ትህትና የጎደለው አይደለም። ራስ ወዳድ አይደለም። በቀላሉ አይበሳጭም፤ወይም በደልን አይቆጥርም። 6 ፍቅር በአመጽ ደስ አይሰኝም፣በእውነት ግን ደስ ይለዋል። 7 ፍቅር ሁሉን ይታገሳል፤ሁሉን ያምናል፤በሁሉም ድፍረት አለው በሁሉ ይጸናል። 8 ፍቅር ፍጻሜ የለውም። ትንቢቶች ያልፋሉ፤ልሳኖችም ቢሆኑ ያበቃሉ፤ዕውቀትም ቢሆን ጊዜ ያልፍበታል። 9 ከዕውቀት የተወሰነውን እናውቃልን፣ትንቢትም በከፊል እንተነቢያለን። 10 ነገር ግን ፍጹም የሆነው ሲመጣ፣ፍጹም ያልሆነው ወደ ፍጻሜ ይደርሳል። 11 ልጅ በነበርሁበት ጊዜ፣እንደ ልጅ እናገር ነበር፣እንደ ልጅም አስብ ነበር፣የመረዳት ችሎታዬም እንደ ልጅ ነበር። ጎልማሳ ስሆን ግን የልጅነት ነገሮችን አስወገድሁ። 12 አሁን በጨለማ ውስጥ ያለን ምስል በመስታዋት እንደሚያይ እንመለከታለን፣የዚያን ጊዜ ግን ፊት ለፊት እናያለን። አሁን ዕውቀትን በከፊል አውቃለሁ፣የዚያን ጊዜ ግን ልክ እኔ ሙሉ በሙሉ እንደምታወቀው ሙሉ በሙሉ አውቃለሁ። 13 ነገር ግን እምነት፣ ተስፋ፣ፍቅር እነዚህ ሦስቱ ግን ጸንተው ይኖራሉ። ከእነዚህ የሚበልጠው ፍቅር ነው።
1 ፍቅርን ተከታተሉ ለመንፈሳዊ ስጦታዎችም ከፍተኛ ጉጉት ይኑራችሁ፣ 2 በተለይም ደግሞ ትንቢት የመናገር ስጦታን በብርቱ ፈልጉ። በልሳን የሚናገር ለሰው ሳይሆን ለእግዚአብሔር ይናገራል፣በመንፈስ የተሰወሩ ነገሮችን ይናገራልና ማንም አይረዳውም። 3 ትንቢት የሚናገር ግን ሰዎችን ለማነጽ፣ለማበረታታትና፣ ለማጽናናት፣ ይናገራል። 4 በልሳን የሚናገር ራሱን ያንጻል፣ትንቢት የሚናገር ግን ቤተክርስቲያንን ያንጻል። 5 እንግዲህ ሁላችሁም በልሳኖች ብትናገሩ ምኞቴ ነበር። ከዚያ ይበልጥ ትንቢት ብትናገሩ እወዳለሁ። በልሳን የተነገረውን የሚተረጉም ከሌለ፣ ቤተክርስቲያን እንድትታነጽ ልሳን ከሚናገር ይልቅ ትንቢት የሚናገር ይበልጣል። 6 ወንድሞች እና እህቶች፣ልሳን እየተናገርሁ ወደ እናንተ ብመጣ ምን እጠቅማችኋለሁ? በመገለጥ፣ወይም በእውቀት፣ወይም በትንቢት፣ወይም በማስተማር ካልሆነ ልጠቅማችሁ አልችልም። 7 ሕይወት የሌላቸው እንደ ዋሽንት ወይም ክራር ያሉ የሙዚቃ መሣሪያዎች መለየት የሚቻሉ ድምፆችን ካላወጡ፣አንድ ሰው የትኛው የሙዚቃ መሣሪያ እንደተጫወተ እንዴት ማወቅ ይችላል? 8 መለከት ሊለይ በማይቻል ድምፅ ቢነፋ፣አንድ ሰው ለጦርነት ለመዘጋጀት ጊዜው እንደሆነ እንዴት ሊያውቅ ይችላል? 9 እናንተንም በተመለከተ እንዲሁ ነው። ሊታወቅ የማይችል ንግግር ብትናገሩ አንድ ሰው ምን እንደተናገራችሁ እንዴት ሊያውቅ ይችላል? እናንተ ትናገራላችሁ ነገር ግን ማንም አይረዳችሁም። 10 በዓለም ውስጥ ብዙ ልዩ ልዩ ቋንቋዎች እንዳሉ ጥርጥር የለውም፣ 11 አንዳቸውም ግን ትርጉም የሌላቸው አይደሉም። የአንድን ቋንቋ ትርጉም የማላውቅ ከሆን ለሚናገረው ሰው እንግዳ እሆንበታለሁ፣ተናጋሪውም እንግዳ ይሆንብኛል። 12 ለእናንተም እንዲሁ ነው። ለመንፈስ ቅዱስ መገለጦች ከፍተኛ ፍላጎት ስላላችሁ፣ቤተክርስቲያንን ለማነጽ ጉጉት ይኑራችሁ። 13 ስለዚህ በልሳን የሚናገር መተርጎም እንዲችል ይጸልይ። 14 በልሳን በምጸልይበት ጊዜ መንፈሴ ይጸልያል፣አእምሮዬ ግን ያለ ፍሬ ነው። 15 ታዲያ ምን ላድርግ? በመንፈሴም እጸልያልሁ፣በአእምሮዬም እጸልያለሁ። በመንፈሴ እዘምራለሁ፣በአእምሮዬም እዘምራለሁ። 16 እንደዚያ ካልሆነ ግን እግዚአብሔርን በመንፈሳችሁ ብታመሰግኑና ሌላው ሰው በምታመሰግኑበት ሰዓት ምን እያላችሁ እንደሆነ ካላወቀ እንዴት "አሜን" ይላል? 17 በእርግጠኝነት በሚገባ እያመሰገናችሁ ነው፣ሌላው ሰው ግን እየታነጸበት አይደለም። 18 ከሁላችሁም የበለጠ በልሳን ስለምናገር እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ። 19 በቤተክርስቲያን ውስጥ ግን ሰዎችን ማስተማር እንድችል፥ በልሳን አሥር ሺ ቃላትን ከምናገር፣ በአእምሮዬ አምስት ቃላትን መናገር እመርጣለሁ። 20 ወንድሞች እና እህቶች፣በአስተሳሰባችሁ ልጆች አትሁኑ። ይልቁን ክፋትን በተመለከተ እንደ ሕፃናት ሁኑ። ነገር ግን በአስተሳሰባችሁ ይበልጥ የበሰላችሁ ሁኑ። 21 በሕጉ እንደተጻፈው፣"የማያውቁት ቋንቋ ባላቸው ሰዎችና እንግዳ በሆነ ንግግር ለዚህ ሕዝብ እናገራለሁ። እንደዚያም ሆኖ አይሰሙኝም፣" ይላል እግዚአብሔር። 22 ስለዚህ ልሳኖች ለአማኞች ሳይሆን አማኝ ላልሆኑ ሰዎች ምልክት ናቸው። ትንቢት መናገር ግን ለማያምኑ ሰዎች ሳይሆን ለአማኞች ምልክት ነው። 23 ስለዚህ፣ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለ ሰው ሁሉ ቢሰበሰብ እና በልሳኖች በመናገር ላይ እያሉ ከውጭ ያሉና የማያምኑ ሰዎች ቢገቡ አብደዋል አይሉምን? 24 ነገር ግን ሁላችሁም ትንቢት እየተናገራችሁ ባለበት ሰዓት አማኝ ያልሆነ ወይም የውጭ ሰው ቢገባ በሚሰማው ነገር ሁሉ ኃጢአተኝነቱ ይሰማዋል። በሚነገረው ነገር ሁሉ ይፈረድበታል። 25 የልቡም ምስጢር ሁሉ ይገልጣል። ከዚህም የተነሳ፣ በግንባሩ ተደፍቶ እግዚአብሔርን ያመልካል። እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ነው! ብሎ ያውጃል። 26 ታዲያ ምን ይሁን፣ወንድሞች እና እህቶች? በአንድነት በምትሰበሰቡበት ጊዜ፣እያንዳንዳችሁ መዝሙር፣ትምህርት፣መገለጥ፣ልሳን፣ወይም ልሳን መተርጎም አላችሁ። የምታደርጉትን ሁሉ ቤተክርስቲያንን ለማንጽ አድርጉት። 27 ማንም በልሳን ቢናገር ሁለትም ሦስትም ብትሆኑ ተራ በተራ አድርጉት። ሌላው ሰው ደግሞ በልሳን የተነገረውን ይተርጉም። 28 የሚተረጉም ከሌለ ግን፣ሁሉም ሰው ድምፁን ሳያሰማ ለራሱ እና ለእግዚአብሔር ብቻ ይናገር። 29 ሁለት ወይም ሦስት ነቢያቶች በሚናገሩበት ጊዜ ሌሎች የሚነገረውን በመመርመር ያዳምጡ። 30 ነገር ግን በስብሰባው ውስጥ አንድ ሰው መረዳት ከመጣለት በመናገር ላይ ያለው ዝም ይበል። 31 ትንቢት ስትናገሩ ሁሉም ሰው እንዲበረታታ እያንዳንዳችሁ ተራ በተራ መናገር ትችላላችሁ። 32 የነቢያቶች መንፈስ ለነቢያት ይገዛል። 33 እግዚአብሔር የሰላም አምላክ እንጂ ግራ የመጋባት አምላክ አይደለም። በሁሉም የአማኞች አብያተክርስቲያናት ውስጥ፦ 34 ሴቶች በቤተክርስቲያን ውስጥ ዝም ይበሉ። እንዲናገሩ አይፈቀድላቸውም። ሕጉ ይህን ይላልና ይልቁንስ ይገዙ ። 35 ሊያውቁ የሚፈልጉት ነገር ቢኖር፣ባሎቻቸውን በቤት ውስጥ ይጠይቁ። ሴት በቤተክርስቲያን ውስጥ መናገሯ አሳፋሪ ነውና። 36 የእግዚአብሔር ቃል የመጣው ከእናንተ ነውን? ወይስ ወደ እናንተ ብቻ ደርሷልን? 37 ማንም ሰው ራሱን ነቢይ እንደሆነ ወይም መንፈሳዊ እንደሆነ ቢያስብ፣የጻፍሁላችሁ ነገሮች የጌታ ትዕዛዛት እንደሆኑ ሊያውቅ ይገባዋል። 38 ነገር ግን ማንም ይህን ባያውቅ እርሱም ዕውቅና አያግኝ። 39 እንግዲህ ወንድሞች እና እህቶች፣ትንቢትን መናገር በቅንነት ፈልጉ፣ ማንንም ልሳኖችን እንዳይናገር አትከልክሉ። 40 ነገር ግን ማንኛውም ነገር በመልካም ምግባር እና በሥርዓት ይደረግ።
1 ወንድሞች እና እህቶች፣ ስላወጅሁላችሁ እና እናንተም ጸንታችሁ ስለቆማችሁበት ወንጌል አሳስብባችኋለሁ። 2 የሰበክሁላችሁን ቃል አጥብቃችሁ ብትይዙ፣በዚህ ወንጌል መዳን ይሆንላችኋል፣አለዚያ ግን ማመናችሁ ምንም ጥቅም የለውም። 3 ለእናንተ ያስተላለፉሁት በቀዳሚነት አስፈላጊ የሆነውን እና እኔም የተቀበልሁትን ነው፤ መጽሐፍት እንደሚሉት ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፣ 4 ተቀበረ፣ በሦስተኛውም ቀን ተነሳ፣መጽሐፍትም ይህን ያረጋግጣሉ። 5 ለኬፋ ታየ፣ከዚያም ለእሥራ ሁለቱ። 6 እንደገና ከአምስት መቶ ለሚበልጡ ወንድሞች እና እህቶች በእንድ ጊዜ ታየ። አብዛኛዎቹ እስካሁን ድረስ በሕይወት አሉ፣የተወሰኑት ደግሞ አንቀላፍተዋል። 7 ከዚያም ለያዕቆብ፣ደግሞም ለሐዋርያቱ ሁሉ ታየ። 8 ከሁሉም በኋላ፣ያለ ጊዜው እንደተወለደ ልጅ ለሆንሁት ለእኔ ታየ። 9 ከሐዋርያት ሁሉ የማንስ ነኝና። የእግዚአብሔርን ቤተክርስቲያን አሳድጃለሁና ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ አይገባኝም። 10 ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁትን ሆኜአለሁ፣በእኔ ውስጥ የነበረው ጸጋም በከንቱ አልነበረም። ይልቁን ከሁሉም በላይ ጠንክሬ ሠራሁ። ሆኖም ይህ የሆነው ከእኔ ሳይሆን ከእኔ ጋር ካለው የእግዚአብሔር ጸጋ የተነሳ ነው። 11 ስለዚህ እኔም ሆንሁ እነርሱ ስንሰብክላችሁ አመናችሁ። 12 አሁን ክርስቶስ ከሞት እንደተነሳ ከተሰበከ፣ከእናንተ አንዳንዶች ታዲያ እንዴት የሙታን ትንሣኤ የለም ይላሉ? 13 ሙታን ትንሣኤ ከሌለ እንግዲያው ክርስቶስም ከሙታን አልተነሳማ። 14 ክርስቶስም ካልተነሳ ስብከታችንም፣የእናንተም እምነት ዋጋ የሌለው ሆኗላ። 15 እንግዲህ እኛም ስለ እግዚአብሔር የሐሰት ምስክሮች ሆነን ተገኝተናል፣ ምክንያቱም እርሱ ክርስቶስን ሳያስነሳ እኛ አስነስቶታል በማለታችን በእግዚአብሔር ላይ በሐሰት መስክረንበታል። 16 ሙታን ካልተነሱ፣ክርስቶስም አልተነሳም ማለት ነው። 17 ክርስቶስ ካልተነሳ ደግሞ፣ እምነታችሁ ምንም ዋጋ የለውምናም አሁንም በኃጢአታችሁ አላችሁ። 18 ስለዚህ በክርስቶስ ሆነው የሞቱ ደግሞ ጠፍተዋል ማለት ነው። 19 ክርስቶስ ተስፋ ያደረግነው ለዚህ ሕይወት ብቻ ከሆነ፣ከሰዎች ሁሉ ይልቅ የምናሳዝን ነን። 20 አሁን ግን ክርስቶስ ከሙታን ሁሉ በኩር ሆኖ ተነስቷል። 21 ሞት በአንድ ሰው በኩል እንደመጣ፣ የሙታን ትንሣኤም በአንድ ሰው በኩል መጥቷል። 22 በአዳም ሁሉም እንደሞቱ፣ሁሉም ደግሞ በክርስቶስ ሕያው ይሆናሉ። 23 ግን እያንዳንዱ በቅደም ተከተሉ መሠረት፦ ክርስቶስ በኩር፣ ቀጥሎ የክርስቶስ የሆኑት እርሱ ተመልሶ ሲመጣ ሕያዋን ይሆናሉ። 24 ከዚያም ክርስቶስ መንግሥቱን ለእግዚአብሔር አብ ሲያስረክብ ፍጻሜ ይሆናል። ይህም የሚሆነው ግዛትን ሁሉ፣ ሥልጣንን ሁሉ፣ እና ኃይልን ሁሉ ሲደመስስ ነው። 25 ጠላቶቹን ሁሉ ከእግሮቹ ስር እስኪያደርግ ድረስ ሊነግሥ ይገባዋል። 26 ሊደመሰስ የሚገባው የመጨረሻው ጠላት ሞት ነው። 27 "ሁሉን ከእግሮቹ በታች አደረገ።" ነገር ግን፣"ሁሉን አደረገ፣" ሲል፣ሁሉን እንዲገዛለት ያደረገውን እንደማይጨምር ግልጽ ነው። 28 ሁሉም ሲገዛለት፣ ልጁ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ለእርሱ ይገዛል። ይህ የሚሆነው እግዚአብሔር አብ ሁሉ በሁሉ እንዲሆን ነው። 29 አለበዚያ ግን ፤ ስለ ሙታን የሚጠመቁ ሰዎች ለምን ያደርጉታል? ሙታን ፈጽሞ የማይነሱ ከሆነ፣ስለምን ያጠምቁላቸዋል? 30 ስለምንስ በየሰዓቱ አደጋ ውስጥ እንወድቃለን? 31 ወንድሞች እና እህቶች፣ ስለ እናንተ በክርስቶስ ባለኝ ትምክህት ይህን እናገራለሁ፦ በየቀኑ እሞታለሁ ። 32 በሰው ዓይን ሲታይ፣ በኤፌሶን ከአውሬዎች ጋር መጋደሌ፣ ሙታን የማይነሱ ከሆነ ምን ይጠቅመኛል? "ነገ መሞታችን ስለማይቀር፣እንብላ፣ እንጠጣ።" 33 አትታለሁ፦ "መልካም ያልሆነ ግንኙነት መልካሙን ጠባይ ያበላሻል።" 34 ራሳችሁን ተቆጣጠሩ! የጽድቅ ሕይወት ኑሩ! ኃጢአት ማድረግን አትቅጠጥሉ። አንዳንዶቻችሁ ስለ እግዚአብሔር ዕውቀት የላችሁም። ይህን የምላችሁ ላሳፍራችሁ ነው። 35 አንዳንዶች ግን እንዲህ ይላሉ፣"ሙታን የሚነሱት እንዴት ነው? በምን ዓይነት አካል ይመጣሉ?" 36 ዕውቀት የጎደላችሁ ናችሁ! የዘራችሁት ዘር ካልሞተ አይበቅልም። 37 የዘራችሁት አካል ተምልሶ አይበቅልም፣ይልቁን ዘር ነው እንጂ። ስንዴ ወይም የተዘራውን ሌላ ዓይነት ዘር ሆኖ ይበቅላል። 38 እግዚአብሔር እንደወደደ አካልን ይሰጠዋል፣ለእያንዳንዱም ዘር የራሱን አካል ይሰጠዋል። 39 ሥጋ ሁሉ አንድ ዓይነት አይደለም። ይልቁን፣ የሰው ሥጋ አለ፣ እንዲሁም የእንሰሳት ሥጋ አለ፣ የአእዋፍት ሥጋም እንዲሁ፣ ዓሣም ደግሞ ሌላ ዓይነት ሥጋ አለው። 40 እንዲሁም ደግሞ ሰማያዊ አካልና ምድራዊ አካል አለ። ነገር ግን የሰማያዊ አካል ክብር አለ የምድራዊ አካል ክብር ደግሞ ሌላ ነው። 41 የፀሐይ ክብር አለ፣ የጨረቃ ክብር ደግሞ ሌላ ነው፣ ከዋክብት ደግሞ ሌላ ክብር አላቸው። የአንዱ ኮከብ ክብር ከሌላው ኮከብ ይለያል። 42 የሙታን ትንሣኤም ልክ እንደዚሁ ነው። የተዘራው የሚጠፋ ነው፣ የሚነሳው ደግሞ የማይጠፋ ነው። 43 ሲዘራ በውርደት ሲነሳ ግን በክብር ነው። ሲዘራ በድካም፣ሲነሳ ግን በኃይል ነው። 44 የተዘራው ፍጥረታዊ አካል፣የሚነሳው ግን መንፈሳዊ አካል ነው። ፍጥረታዊ አካል እንዳለ ሁሉ መንፈሳዊ አካልም አለ። 45 እንዲህም ተብሎ ተጽፎአል፣ "የመጀመሪያው አዳም ሕያው ነፍስ ሆነ።" የመጨረሻው አዳም ግን ሕይወት ሰጭ መንፈስ ሆነ። 46 መጀመሪያ የመጣው መንፈሳዊው ሳይሆን ፍጥረታዊው ነው፣ከዚያም መንፈሳዊው ተከተለ። 47 የመጀመሪያው ሰው ከምድር ሲሆን የተሠራውም ከአፈር ነው። ሁለተኛው ሰው ከሰማይ ነው። 48 አንዱ ከአፈር እንደተሠራ፣ከአፈር የተሠሩ ሁሉ እንዲሁ ናችው። እንዲሁም ከሰማይ እንደሆነው ሰው፣ ከሰማይ የሆኑትም እንዲሁ ናቸው። 49 ልክ እኛ ከአፈር የተሠራውን ሰው እንደምንመስል፣ እንዲሁ ደግሞ የሰማዩን ሰው መልክ እንይዛለን። 50 ወንድሞች እና እህቶች፣ አሁን እንዲህ እላለሁ፣ሥጋ እና ደም የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊወርስ አይችልም። እንዲሁም የሚጠፋው የማይጠፋውን ሊወርስ አይችልም። 51 ምስጢር የሆነ እውነት እነግራችኋለሁ፦ ሁላችን አንሞትም፣ግን ሁላችን እንለወጣለን። 52 የመጨረሻው መለከት ሲነፋ፣ዐይን ተጨፍኖ እስኪገለጥ ባለ ፍጥነት ድንገት እንለወጣለን። መለከቱ ሲነፋ፣ ሙታን የማይጠፋውን አካል ለብሰው ይነሳሉ፣ እኛም እንለወጣለን። 53 ይህ የሚጠፋው የማይጠፋውን ይለብሳል፣ ሟቹ ደግሞ የማይሞተውን ይለብሳል። 54 የሚጠፋው የማይጠፋውን ሲለብስ፣እና ይህ ሟች የሆነው የማይሞተውን ሲለብስ፣ እንዲህ ተብሎ የተጻፈው ይፈጸማል፣"ሞት በድል ተዋጠ።" 55 ሞት ሆይ ድል ማድረግህ የት አለ? ሞት ሆይ መንደፊያህ የት አለ?" 56 የሞት መንደፊያ ኃጢአት ነው፣ የኃጢአት ኃይል ደግሞ ሕጉ ነው። 57 ነገር ግን በጌታ በክርስቶስ ኢየሱስ ድል የሚሰጠን እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን! 58 ስለዚህ ውድ ወንድሞቼ እና እህቶቼ፣ የጸናችሁ እና የማትነቃነቁ ሁኑ። ሁልጊዜም የእግዚአብሔር ሥራ ይብዛላችሁ፣ምክንያቱም በጌታ የምትደክሙት ድካም በከንቱ አይደለም።
1 አሁን ደግሞ ለአማኞች የሚሰበሰበውን ገንዘብ በተመለከተ፣የገላትያ አብያተክርስቲያናትን እንዳዘዝሁት ሁሉ፣እናንተም እንደዚሁ አድርጉ። 2 እኔ ስመጣ ገንዘብ ከመሰብሰብ፣ በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን፣እያንዳንዳችሁ እንደቻላችሁት መጠን የተወሰነ ገንዘብ አጠራቅሙ። 3 ወደ እናንተ በደረስሁ ጊዜ በመረጣችሁት ሰው በኩል ከደብዳቤ ጋር መባችሁን ወደ እየሩሳሌም እልከዋለሁ። 4 የእኔም መሄድ አስፈላጊ ከሆነ ከእኔ ጋር ይሄዳሉ። 5 ነገር ግን ወደ መቄዶንያ መሄዴ ስለማይቀር፣ በመቄዶንያ በኩል ሳልፍ ወደ እናንተ እመጣለሁ። በምሄድበት ሁሉ ለጉዞዬ እንድትረዱኝ፣ 6 ምናልባትም ከእናንተ ጋር ልቆይና ክረምቱንም ከእናንተ ጋር ላሳልፍ እችላልሁ። 7 አሁን ግን ጊዜው ስለሚያጥር ላያችሁ አላስብም። ጌታ ቢፈቅድና ብመጣ ግን ከእናንተ ጋር ረዘም ላለ ጊዜ ለመቆየት ተስፋ አደርጋልሁ። 8 ግን በኤፌሶን እስከ በዓለ ኅምሳ ቀን ድረስ እቆያልሁ፣ 9 ሰፊ በር የተከፈተልኝ ቢሆንም ብዙ ተቃዋሚዎች አሉብኝ። 10 ጢሞቴዎስ ልክ እንደ እኔ የጌታን ሥራ የሚሠራ ነውና ወደ እናንተ ሲመጣ፣ያለ አንዳች ስጋት ከእናንተ ጋር እንዲቀመጥ አድርጉ። 11 ማንም አይናቀው። ወደ አኔ ሲመጣ በሰላም እንዲሄድም እርዱት። ምክንያቱም ከሌሎች ወንድሞች ጋር እንዲመጣ እጠብቃለሁ። 12 አጵሎስን በተመለከተ፣ከወንድሞች ጋር በመሆን እንዲጎበኛችሁ አበረታትቼው ነበር። አሁን ለመምጣት አልወሰነም፣ይሁን እንጂ ዕድሉን ሲያገኝ ይመጣል። 13 ተጠንቀቁ፣በእምነትም ጸንታችሁ ቁሙ፣ቆራጦች ሁኑ፣በርቱ። 14 የምታደርጉት ሁሉ በፍቅር ይሁን። 15 የእስጢፋኖስን ቤተሰቦች ታውቃላችሁ። እነርሱ በአካይያ የመጀመሪያ አማኞች እንደሆኑና አማኞችን ለማገልገል ራሳችውን እንደሰጡ ታውቃላችሁ። ወንድሞች እና እህቶች 16 እንደዚህ ላሉ ሰዎች፣ በሥራ እየረዱንና አብረውን እየደከሙ ላሉ ሰዎች ሁሉ እንድትገዙ አሳስባችኋለሁ። 17 በእስጢፋኖስ፣በፈርዶናጥስ፣ እና በአካይቆስ መምጣት ተደስቼአልሁ። የእናንተን በዚህ ያለመኖር ጉድለት ሞልተውልኛል። 18 የእኔን እና የእናንተን መንፈስ አድሰዋል። እንዲህ ላሉ ሰዎችን እውቅና ስጧቸው። 19 በእስያ ያሉ አብያተ ክርስቲያናት ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። አቂላና ጵርስቅላ፣ እንዲሁም በቤታቸው ያለችው ቤተክርስቲያን በጌታ ስም ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። 20 ወንድሞች እና እህቶች ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። በተቀደሰ አሳሳም እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተለዋወጡ። 21 እኔ ጳውሎስ፣ ይህን በእጄ ጽፌአለሁ። 22 ማንም ጌታን የማይወድ ቢኖር፣ የተረገመ ይሁን። ጌታ ሆይ ና! 23 የጌታ የኢየሱስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን። 24 በክርስቶስ ኢየሱስ ፍቅሬ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።
1 በእግዚአብሔር ፈቃድ የክርስቶስ ኢየሱስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ እና ወንድማችን ከሆነው ጢሞቲዎስ፥ በቆሮንቶስ ለምትገኝ የእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን እንዲሁም በመላው አካይያ ላሉ አማኞች ሁሉ፡ 2 ከእግዚአብሔር ከአባታችን እንዲሁም ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋና ሰላም ለናንተ ይሁን። 3 የምህረት አባት፥ የመፅናናት አምላክ እና በመከራችን ሁሉ የሚያፅናናን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ። 4 እግዚአብሔር በመከራችን ሁሉ ያፅናናል፥እኛም ራሳችን በእርሱ በእግዚአብሔር በተፅናናንበት መፅናናት ልክ ሌሎችን ማፅናናት እንችላለን። 5 ምክንያቱም የክርስቶስ መከራ በእኛ ላይ እንደበዛ፥ መፅናናታችንም በክርስቶስ በኩል እንዲሁ ይበዛልናል። 6 ነገር ግን መከራን ብንቀበል፥ስለናንተ መፅናናት እና ድነት ነው። ወይንም ደግሞ የእኛ መፅናናት የእናንተም መፅናናት ማለት ነው፤ይህም እኛ በምንቀበለው መከራ እናንተም በተመሳሳይ መልኩ በትእግስት አብራችሁን ስለምትካፈሉ ነው። 7 በናንተም ያለን መታመን ፅኑ ነው፥በመከራችን እንደምትካፈሉ ሁሉ በመፅናናታችንን ደግሞ እንደምትካፈሉ እናውቃለን። 8 ወንድሞች ሆይ፥በእስያ ስለደረሰብን መከራ እንድታውቁ እንወዳለን፤ በህይወት ለመኖር ተስፋ እስክንቆርጥ ድረስ ከአቅማችን በላይ ከብዶን ነበር። 9 በርግጥም ሞት ተፈርዶብን ነበር። ሆኖም ግን ያ የደረሰብን መከራ ሙታንን በሚያስነሳ በእግዚአብሔር እንጂ በራሳችን እንዳንታመን አደረገን። 10 ከብርቱ ጥፋት አዳነን እንዲሁም ያድነናል። መታመናችንን በእርሱ ላይ አድርገናል፤እርሱም ይታደገናል። 11 በእናንተም የፀሎት ድጋፍ አምላካችን ስራውን ይሰራል። በመቀጠልም በብዙዎች ፀሎት አማካኝነት ለእኛ ስለተሰጠው ሞገስ በርካቶች ምስጋናን ያቀርባሉ። 12 የምንመካው በህሊናችን ምስክርነት ላይ ነው። ምክንያቱም በዚህ ዓለም ስንመላለስ የነበረው በንፁህ ህሊና እና ከእግዚአብሔር በሚሰጥ ቅንነት ነበር። በተለይም ከናንተ ጋር የነበረን ግንኙነት የተመሰረተው በእግዚአብሔር ፀጋ ላይ እንጂ በምድራዊ ጥበብ ላይ አልነበረም። 13 ልታነቡትና ልትረዱት የማትችሉትን አንዳችም ነገር አንዳልፃፍንላችሁ ተስፋ አደርጋለሁ፤ 14 እናንተም በከፊል እንደተረዳችሁን በጌታችን በኢየሱስ ቀን እናንተ በእኛ እንደምትመኩ እኛም እንዲሁ በእናንተ እንመካለን። 15 ስለዚህ ርግጠኛ ስለነበርሁ፥ በመጀመሪያ ወደናንተ መምጣት ፈለግሁ፤ ይህ ደግሞ በሁለቱም ጉብኝቶቼ ተጠቃሚዎች እንድትሆኑ ነው። 16 ወደ መቄዶንያ ስሄድ ልጎበኛችሁ ፤ከዚያ ደግሞ ክመቄዶንያ ስመለስ ላያችሁ፤በኋላ ግን እናንተው ወደ ይሁዳ እንደምትልኩኝ አቅጄ ነበር። 17 ይህንን ሳስብ ታዲያ የወላወልኩ ይመስላችኋልን? ወይስ በአንድ ጊዜ እንደ ሰው መስፈርት "አዎን፥ አዎን" እና "አይደለም፥አይደለም" በማለት አቀድኩን? 18 ነገር ግን እግዚአብሔር የታመነ እንደሆነ፣ እኛም በሁለት ቃል "አዎን" እና "አይደለም" ብለን አንናገርም። 19 ምክንያቱም በእናንተ መካከል በእኔ፥ በስልዋኖስ እና በጢሞቲዎስ የተሰበከው የእግዚአብሔር ልጅ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን በአንድ ጊዜ "አዎን" እና "አይደለም" አልነበረም፥ይልቅስ ሁልጊዜም በእርሱ "አዎን" ነው። 20 በእርሱ የእግዚአብሔር ተስፋዎች ሁሉ "አዎን" ናቸው። ስለዚህ እኛም በእርሱ በኩል ለእግዚአብሔር ክብር "አሜን" እንላለን። 21 እንግዲህ እኛንም ከእናንተ ጋር በክርስቶስ የሚያፀናን እንዲሁም የሾመን እግዚአብሔር ነው። 22 ለዚህም ወደፊት ለሚሰጠን ዋስትና እንዲሆነን መንፈሱን በልባችን የሰጠን ማህተሙንም ያደረገብን እርሱ ነው። 23 ሆኖም ግን ወደ ቆሮንቶስ ያልመጣሁት እንዳላሳዝናችሁ አስቤ እንደሆነ እግዚአብሔር ምስክሬ ነው። 24 እኛም እምነታችሁ ምን መምሰል እንዳለበት በናንተ ላይ ልናዝዝ ሳይሆን በእምነታችሁ ፀንታችሁ እንድትቆሙ ለደስታችሁ የምንሰራ ነን።
ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ በቋንቋችሁ የዚህን ደብዳቤ ፀሐፊ ለማስተዋወቅ ምናልባት የተለየ መንገድ መንገድ መጠቀም ያስፈልጋችሁ ይሆናል። AT: "እኔ ጳውሎስ፥ ይህንን ደብዳቤ ፅፌያለሁ።" ወንድማችን በአዲስ ኪዳን፥ሐዋርያት ብዙውን ጊዜ ለክርስቲያን ወዳጆች "ወንድም" የሚል ቃል ይጠቀማሉ፥ምክንያቱም አማኞች ሁሉ በክርስቶስ እግዚአብሔር የሰማይ አባት በሆነበት የአንድ መንፈሳዊ ቤተሰብ አባላት ስለሆኑ ነው። አካይያ ይህ የሮም አውራጃ መጠሪያ ሲሆን በአሁኑ ዘመን ግሪክ ተብሎ የሚጠራው ደቡባዊ ክፍል ነው። ፀጋና ሰላም ለናንተ ይሁን "ለናንተ" የሚለው ቃል የሚያሳየው የቆሮንቶስ ቤተክርስትያንን ህዝብ እና በዚያ የሚገኙትን ክርስቲያኖች ነው። ይህ ጳውሎስ በደብዳቤዎቹ የሚጠቀመው የተለመደ ሰላምታ ነው።
አምላክና አባት "አምላክ የሆነው አባት" የምህረት አባት፥የመፅናናት ሁሉ አምላክ እነዚህ ሃረጎች አንድን ነገር በተመሳሳይ መንገዶች ይናገራሉ። "አባት" እና "አምላክ" የሚሉት ቃላት እግዚአብሔር "የሚሰጥ" ወይም "ምንጭ" መሆኑን የሚገልፁ ሲሆን ምክንያቱም እግዚአብሔር የነገሮች ሁሉ ምንጭ ስለሆነ ነው። AT: "የምህረት እና የመፅናናት ሁሉ ምንጭ" በመከራችን ሁሉ ያፅናናል እዚህ ላይ "እኛ" እና "የእኛ" የሚሉት ቆሮንቶሶችን ያጠቃልላል።
የክርስቶስ መከራ በእኛ ላይ እንደበዛ "ክርስቶስ ስለእኛ በብዙ መከራ እንደተቀበለ" ነገር ግን መከራን ብንቀበል ጳውሎስ ከቆሮንቶስ ሰዎች ውጪ እነርሱም የተቀበሉትን መከራ ይገልፃል። የእናንተ መፅናናት "መፅናናት ትለማመዳላችሁ"
እንድታውቁ እንወዳልን "እንድታውቁ እንፈልጋለን" ለመኖር ተስፋ እስክንቆርጥ "ተስፋ እስክንቆርጥ" የሚለው ቃል የሚያሳየው የሃዘን ስሜትን ነው። "በሃዘን መዋጥ" ከአቅማችን በላይ ከብዶን ጳውሎስ እና ጢሞቲዎስ የተሰማቸውን የሃዘን ስሜት የሚያነፃፅሩት ልክ መሸከም እንደሚገባቸው ከባድ ሸክም ነው። (See:
ሞት ተፈርዶብን ነበር
ሞት ከተፈረደበት ሰው ጋር ነው። AT: "ሞት እንደተፈረደበት አይነት ሰው በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ነበርን"
በእግዚአብሔር እንጂ
"እምነታችንን ልናደርግ" የሚሉት ቃላት ከዚህ ሃረግ ውስጥ ወጥተዋል። AT: "ነገር ግን እምነታችንን በእግዚአብሔር እንድናደርግ"
ሙታንን በሚያስነሳ
"የሞተውን ወደ ህይወት እንደሚመልስ"
ብርቱ ጥፋት
ጳውሎስ እና ጢሞቲዎስ የተሰማቸውን የሃዘን ስሜት የሚያነፃፅሩት ከብርቱ ጥፋት እና ከከፋ አደጋ ጋር ነው። (UDB) AT: "ተስፋ መቁረጥ።"
በእናንተም ድጋፍ እርሱ ስራውን ይሰራል "እናንተ የቆርንቶስ ሰዎች ሆይ፥እናንተ ለእኛ ስትፀልዩ እግዚአብሔር ደግሞ ከአደጋ ያድነናል።
በህሊናችን ምስክርነት ጳውሎስ እና ጢሞቲዎስ ለራሳችው ሃሳቦች እና ድርጊቶች የተሰጠው ማረጋገጫ። ምድራዊ ጥበብ "ሰዋዊ ጥበብ" ልታነቡትና ልትረዱት የማትችሉትን አንዳችም ነገር አንፅፍላችሁም AT: "የፃፍንላችሁን ሁሉ ልታነቡትም ሆነ ልትረዱት የምትችሉትን ነው። እንዲሁ በናንተ እንመካለን፡ ትኩረት፡ "እናንተ የመመካታችን ምክንያቶች ናችሁ"
ስለዚህ ርግጠኛ ስለነበርሁ ይህ ጳውሎስ ለቆሮንቶሶች አስቀድሞ የሰጠውን አስተያየት ያሳያል። ወደ ይሁዳ እንደምትልኩኝ "ወደ ይሁዳ በማደርገው ጉዞ እንደምታግዙኝ"
ይህንን ሳስብ የወላወልኩ ይመስላችኋልን? ጳውሎስና ጢሞቲዎስ ይህንን ጥያቄ የሚጠቀሙት ውሳኔያቸው ትክክል እንደሆን ለማሳየት ነው። ትኩረት፡"በዚህ መንገድ ሳስብ፥በውሳኔዬ እተማመናለሁ"
የወላወልኩ ይመስላችኋልን? "ርግጠኛ አልነበርሁምን?" ወይስ በአንድ ጊዜ እንደ ሰው መስፈርት "አዎን፥ አዎን" እና "አይደለም፥አይደለም" በማለት አቀድኩን? ጳውሎስ ለታማኝነቱ መከላከያ ያቀርባል። ትኩርት፡ "ነገሮችን የማቅደው እግዚአብሔር እንዳቅደው እንደሚፈልገው ነው። መልሴ እውነት እስከሆነ ድረስ ምላሼ አዎን ወይም አይደለም እላለሁ።"
የእግዚአብሔር ልጅ ይህ የኢየሱስ አስፈላጊ መጠሪያ ሲሆን ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት የሚገልፅ ነው። (ተመልከት፡
"አዎን" እና "አይደለም" አልነበረም ይህ ኢየሱስ እንዴት ጥያቄዎችን ይመልስ እንደነበር ነው። ትኩረት፡"እዎን" እና "አይደለም" በማለት ሁለት መልስ አይመልስም ነበር። በእርሱ "አዎን" ናቸው "በእርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስ ክርስቶስን ነው።
ማህተሙን ያደረገብን "ማህተሙን" የሚለው ቃል የእግዚአብሔርን ማረጋግጫ ያመለክታል። ትኩረት፡ "ማረጋገጫ የሰጠን"
እግዚአብሔር ምስክሬ ነው "ምስክሬ ነው" የሚለው ሃረግ የሚያመለክተው አንድ ሰው ሙግቱን ለመርታት ሲል ያየውን ወይም የሰማውን ሲናገር ነው። ትኩረት፡ "የምናገረው ነገር እውነት መሆኑን እንዲያሳይ እግዚአብሔርን እጠይቃለሁ" በእምነታችሁ ፀንታችሁ እንድትቆሙ "እንድትቆሙ" የሚለው ቃል አንድ የማይለወጥ ነገርን ያሳያል። ትኩረት፡"በእምነታችሁ ፀንታችሁ ኑሩ"
1 ስለዚህም በበኩሌ እንደገና ላስከፋችሁ ተመልሼ መምጣት አልፈለግሁም። 2 ባስከፋችሁ እንኳ ሊያስደስተኝ የሚችለው ያው ያስከፋሁት ሰው አይደለምን? 3 እንደፃፍኩላችሁ ወደ እናንተ በመጣሁ ጊዜ ደስ ሊያሰኙኝ የሚገባችው ሰዎች እንዳያሳዝኑኝ ነው። ስለሁላችሁም እርግጠኛ የምሆንበት በእኔ ያለ ደስታ በተመሳሳይ መልኩ በእናንተም ዘንድ ያለ መሆኑ ነው። 4 የፃፍኩላችሁም በታላቅ ጭንቀት፥ በልብ መናወጥ እንዲሁም በብዙ እንባ ነበር፥ ምክንያቱ ደግሞ ለናንተ ያለኝን ጥልቅ ፍቅር እንድታውቁ እንጂ እንዳላሳዝናችሁ ነው። 5 ማንም ያሳዘነ ሰው ቢኖር እኔን ብቻ ያሳዘነ ሳይሆን በተወሰነ መልኩ ሁላችሁንም ነው። 6 ለዚያም ሰው በብዙዎች የደረሰበት ቅጣት ይበቃዋል። 7 ግን ይህን ሰው በብዙ ሐዘን እንዳይዋጥ ከመቅጣት ይልቅ ይቅር ልትሉትና ልታፅናኑት ይገባል። 8 ስለዚህም ለዚህ ሰው ፍቅራችሁን በይፋ እንድታረጋግጡለት አደፋፍራችኋለሁ። 9 የፃፍኩላችሁ በሁሉ ነገር ታዛዦች መሆናችሁን እንድፈትንና እንዳውቅ ነው። 10 አንድን ሰው ይቅር ብትሉት፣ እኔም ያንን ሰው ይቅር እለዋለሁ። እኔ ይቅር የምለው አንዳች ነገር ቢኖር ይቅርታ የማደርግለት በክርስቶስ ፊት ስለ እናንተ ስል ነው። 11 ይህን የማደርገውም ሰይጣን እንዳያታልለን ነው። ምክንያቱም የርሱን እቅድ አንስተውምና። 12 ምንም እንኳ ወደ ጥሮአዳ ስመጣ የክርስቶስን ወንጌል ለመስበክ በጌታ በር ተከፍቶልኝ ነበር። ሆኖም ወንድሜን ቲቶን በዚያ ስላላገኘሁት በአዕምሮዬ አላረፍኩም ነበር። 13 ስለሆነም እነርሱን ትቼ ወደ መቄዶንያ ተመለስኩ። 14 ነገር ግን ሁልጊዜ በክርስቶስ በድል ለሚመራን፥ ጣፋጭ የእውቀት ሽታ በየስፍራውም ለሚናኘው ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን። 15 ምክንያቱም በሚድኑትና በሚጠፉት መካከል ለእግዚአብሔር የክርስቶስ ጣፋጭ ሽታ ነን። 16 ለሚጠፉት ሰዎች፥ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ ስንሆን ለሚድኑት ደግሞ ለህይወት የሚሆን የህይወት ሽታ ነን። ለነዚህ ነገሮች የበቃ ማነው? 17 የእግዚአብሔርን ቃል ለትርፋቸው እንድሚነግዱበት እንደ ብዙዎች አይደለንም። በዚያ ፈንታ በክርስቶስ ሆነን በእግዚአብሔር ፊት፥ ከእግዚአብሔር እንደተላክን በቅን ልቦና እንናገራለን።
በበኩሌ "የወሰንኩት ራሴ ነኝ" ላስከፋችሁ ትኩረት፡ "የምታደርጉትን በብርቱ ተቃውሜያለሁ" ባስከፋችሁ እንኳ ሊያስደስተኝ የሚችለው ያው ያስከፋሁት ሰው አይደለምን? ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች ደስ እንዳሰኙት ከነገራቸው በኋላ ቢጎዳቸው ግን ሁለቱንም የሚያስከፋ ያስታውቃቸዋል። ትኩረት፡ "ባስከፋችሁ ደስ ስለማትሰኙ እኔም አልደሰትም"
እንዳያሳዝኑኝ ነው ጳውሎስ እዚህ ጋር የስሜት ጉዳት ስላደረሱበት የተወሰኑ የቆሮንቶስ አማኞች ይናገራል። ትኩረት፡"በእነርሱ ድርጊት እንዳልጎዳ" በታላቅ ጭንቀት፥ በልብ መናወጥ እንዲሁም በብዙ እንባ እነዚህ ሃረጋት የጳውሎስን ታላቅ ሃዘን ያሳያሉ፤ ይህንንም የፃፈው ለቆሮንቶስ ሰዎች ባለው ፍቅር በትልቅ ችግር ሆኖ ነው። ትኩረት፡ "ትልቅ ችግር ሊገጥመኝ የቻለው ታላቅ ሃዘን ስለገባኝ ሲሆን የዚህም መነሾ ለናንተ ካለኝ ሃላፊነት የተነሳ ነው።"
በተወሰነ መልኩ "በጥቂቱ" የደረሰበት ቅጣት "ያለበቂ ርህራሄ" ወይም "በበዛ ጭካኔ" በብዙ ሐዘን እንዳይዋጥ ይህ ማለት ለበዛ ሃዘን የበረታ የስሜት ምላሽ ያስፈልጋል ማለት ነው።
ፍቅራችሁን በይፋ እንድታረጋግጡለት ይህ ማለት ወደ አማኞች ህብረት ተመልሶ ሲመጣ አቀባበል ማድረግ ማለት ነው። ትኩረት፡"በጋራ በምትሰበሰቡብት ጊዜ ቤተሰብ እንደምትወዱት ያህል አሁንም እንደምትወዱት አስታውቁ" በሁሉ ነገር ታዛዦች ይህ የሚያመለክተው ሁለቱንም ነገሮች ማለትም አንድን ሰው ለበደሉ መቅጣትና ከዚያም ይቅር ማለትን ነው። ትኩረት፡"እንድታደርጉት እንዳስተማርኳችሁ በሁሉ ነገር ታዛዦች ናችሁ"
ይቅርታ የማደርግለት * ስለ እናንተ ስል ነው
ስሜት ሊስጡ የሚችሉት ትርጉሞች 1) "ከእኔ ውስጥ ከሚውጣው ፍቅር የተነሳ ይቅር ብዬዋለሁ" (UDB) ወይንም 2) "ለናንተ ጥቅም ይቅር ተብሏል።" ምክንያቱም የርሱን እቅድ አንስተውምና ትኩረት፡ "እቅዱን ስለምናውቅ ነው" (ተመልከት፡
በር ተከፍቶልኝ ነበር የተከፈተ በር አንድን ሰው አልፎ እንዲራመድ እንደሚያደርገው ሁሉ ጳውሎስም በጥሮአዳ የወንጌልን መልዕክት እንዲያካፍል እድል አግኝቶ ነበር። ትኩረት፡ "እድልን ተስጥቶኝ ነበር" ወንድሜን ቲቶን ብዙውን ጊዜ ጳውሎስ በአገልግሎቱ ውስጥ የሚካፈሉትን ሌሎች ሰዎች በክርስቶስ ወንድም በማለት ይጠራል። እነርሱን ትቼ "ስለዚህም የጥሮአዳ ሰዎችን ትቼያቸው ሄድኩ"
በድል ለሚመራን ጳውሎስ ክርስቶስን ድልን እንደሚያቀዳጅ የጦር መሪ ይገልፀዋል። ትኩረት፡ "ድልን ይሰጠናል።" (ተመልከት፡ ጣፋጭ የእውቀት ሽታ "መልካም የእውቀት ሽታ።" ጳውሎስ "ጣፋጭ ሽታ" ሲል ደስ የሚያሰኝ እውቀትን ያመላክታል። ትኩረት፡"አስደሳች እውቀት" የክርስቶስ ጣፋጭ ሽታ "መልካም የክርስቶስ ሽታ" ጳውሎስ "ጣፋጭ ሽታ" የሚለውን ሃርግ ሲጠቀም አስደሳች እውቀት የሚለውን እንዲያመለክት ነው። ትኩረት "የክርስቶስ አስደሳች እውቀት" (ተመልከት፡
ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ
ለህይወት የሚሆን የህይወት ሽታ
"ሽታ" የሚለው ቃል የሚያሳየው ክርስቶስን ስለማወቅ ነው። በመንፈስ ህያው የሆኑ ሰዎች፥ የክርስቶስ እውቀት ልክ እንደ ጣፋጭ የመዓዛ ሽታ ነው። ትኩረት፡"የህይወት እውቀት ሽታ ለህያዋን ሰዎች ነው"
ለነዚህ ነገሮች የበቃ ማነው?
ጳውሎስ ይህንን ጥያቄ የሚጠይቀው ክርስቶስን ማወቅ ከእግዚአብሔር የሚሰጥ እንጂ ማንም የሚገባው ሆኖ እንዳልሆነ ለማሳየት ነው። ትኩረት፡"እነዚህ ነገሮች የሚገባው እንድም ሰው የለም።"
በቅን ልቦና
"እውነተኛ ፍላጎቶች"
በክርስቶስ* እንናገራለን
"የምንናገረው በክርስቶስ ባለን እምነት ነው"
1 ራሳችንን እንደገና ልናወድስ እንጀምራለንን? አንዳንድ ሰዎች እንደሚያደርጉት ለናንተም ሆነ ከእናንተ የድጋፍ ደብዳቤ ያስፈልገን ይሆን? አያስፈልገንም። 2 እናንተ ራሳችሁ በልባችን ላይ የተፃፋችሁ፥በሁሉም ሰዎች የምትታውቁ እና የምትነበቡ የድጋፍ ደብዳቤያችን ናችሁ። 3 በእኛ የቀረባችሁ የክርስቶስ መልዕክት ከመሆናችሁም በላይ በህያው የእግዚአብሔር መንፈስ እንጂ በቀለም ያልተፃፋችሁ፤በሰዎች የልብ ፅላት ላይ እንጂ በድንጋይ ፅላት ላይ ያልተቀረፃችሁ ናችሁ። 4 እንግዲህ በክርስቶስ በኩል በእግዚአብሔር ላይ ይህ መታመን አለን። 5 ከእኛ የሆነ ብለን ልናስበው የምንችል አንዳች ችሎታ የለንም፤ነገር ግን ብቃታችን ከእግዚአብሔር ነው። 6 እርሱም የአዲስ ኪዳን አገልጋዮች አደረገን። ይህ ኪዳን የፊደል ሳይሆን የመንፈስ ነው። ምክንያቱም ፊደል ይገድላል፣ መንፈስ ግን ህይወትን ይሰጣል። 7 የእስራኤል ህዝብ ከፊቱ ክብር የተነሳ እያደር የሚደበዝዘውን የሙሴን ፊት መመልከት እስኪያቅታቸው ድረስ በፊደላት በድንጋይ ላይ የተቀረፀው የሞት አገልግሎት በክብር ከሆነ፤ 8 የመንፈስ አገልግሎት እጅግ በክብር አይልቅምን? 9 የኩነኔ አገልግሎት ክብር ከነበረው፥የፅድቅ አገልግሎት እንደምን በክብር ይብዛ! 10 በርግጥም ቀድሞ በክብር የነበረው ከሱ በሚበልጥ ክብር ተሽሯል። 11 አላፊው በክብር ከሆነ ፀንቶ የሚኖረው በክብር እንዴት ይበልጥ! 12 እንግዲያውስ እንዲህ ያለ ትምክህት ስላለን እጅግ በድፍረት እንናገራለን። 13 እኛ የእስራኤል ህዝቦች የሚያልፈውን ክብር ትኩር ብለው መመልከት እንዳልቻሉት፤ ፊቱን በመሸፈኛ እንደ ከለለው እንደ ሙሴ አይደለንም። 14 ሆኖም ግን አእምሮዋቸው ተሸፈነባቸው። እስከዛሬም አሮጌው ኪዳን ሲነበብ ያው መሸፈኛ ይኖራል፤ሊገለጥም አይችልም፤ ምክንያቱም ሊወገድ የሚችለው በክርስቶስ ነው። 15 ሆኖም ግን እስከዛሬ ድረስ የሙሴ ህግ ሲነበብ በልባቸው ላይ መሸፈኛው ይኖራል። 16 ሰው ግን ወደ ጌታ መለስ ሲል ፥መሸፈኛው ይነሳል። 17 ጌታም መንፈስ ነው፤የጌታም መንፈስ ባለበት ነፃነት አለ። 18 እኛም ሁላችን ባልተሸፈነ ፊት የጌታን ክብር እያየን እርሱን ወደሚመስል ከአንድ ክብር ደረጃ ወደ ሌላ ክብር ደረጃ እንለወጣለን፤ይህም የሚሆነው መንፈስ ከሆነው ጌታ ነው።
ራሳችንን እንደገና ልናወድስ እንጀምራለንን? ጳውሎስ ይህን ሲናገር ራሳቸውን ከሌሎቹ የተሻሉ አድርገው እንደማይመለከቱ ለማስታውቅ ነው። ለናንተም ሆነ ከእናንተ የድጋፍ ደብዳቤ ያስፈልገን ይሆን? ጳውሎስ የሚለው ቆሮንቶሶች ስለ ጳውሎስም ሆነ ስለጢሞቲዎስ መልካም ስም አስቀድመው አውቀዋል። የድጋፍ ደብዳቤያችን ጳውሎስ እና ጢሞቲዎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች ያላቸው ፍቅር ቤተ ክርስቲያን ጳውሎስ እና ጢሞቲዎስ የታመኑ መሆናቸውን ከሚያሳየው የድጋፍ ደብዳቤ ጋር ይንፃፀራል። በእኛ የቀረባችሁ የክርስቶስ መልዕክት ከመሆናችሁም በላይ በህያው የእግዚአብሔር መንፈስ እንጂ*፤በሰዎች የልብ ፅላት ላይ እንጂ ጳውሎስ እዚህ ጋር የሚናገረው በቆሮንቶስ ያሉ ሰዎች ልክ እንደ ደብዳቤ ስለ ምሳሌነታቸው የሚነገር ጳውሎስ እና ጢሞቲዎስም ያካፈሉት የክርስቶስ መልዕክትም በመንፈስ ቅዱስ ሃይል ለውጧቸው አሁን ምን አይነት ሰዎች እንደሆኑ ነው። በሰዎች የልብ ፅላት ላይ እንጂ በድንጋይ ፅላት ላይ ያልተቀረፃችሁ ናችሁ "ድንጋይ" የሚለው ቃል ለማይለወጥ ነገር ስዕላዊ መግለጫ ነው። "በሰዎች የልብ" የሚለው ሃረግ ጥቅም ላይ የዋለው ለስላሳ እና የሚለወጥ በመሆኑ ነው። ፅላት እነዚህ ጠፍጣፋ ለፅህፈት ስራ የሚያገለግሉ ከድንጋይ ወይም ከሸክ ላ የሚሰሩ ነገሮች ናቸው።
2ኛ ቆሮንቶስ 3፡4-6
ይህ መታመን "ይህ" የሚለው ቃል ጳውሎስ እና ጢሞቲዎስ ክርስቶስን ማወቅ በቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን ህዝብ ውስጥ ያመጣውን ለውጥ እንዴት እንደተገነዘቡት ያመለክታል። አንዳች ችሎታ፡ "በራሳችን ብቃት ያለን" ብቃታችን "የእኛ መስፈርት" የፊደል ሳይሆን የመንፈስ ጳውሎስ "ፊደል" የሚለውን ቃል ሲጠቀም የብሉይ ኪዳንን ህግጋት ለማመላከት ሲሆን በዚያም ፊደላት ቃልን የሚመሰርቱበት ነው። "የፊደል ኪዳን" የሚለው ሃረግ የብሉይ ኪዳን እያንዳንዱ ህግ ማለት ነው። ትኩረት፡ "ህግን በመታዘዝ ሳይሆን የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ በመቀበል ነው።" ፊደል ይገድላል ይህ ሃረግ የሚለው የብሉይ ኪዳንን ህግጋት በፍፁምነት ለመታዘዝ መሞከር ወደ መንፈሳዊ ሞት የሚመራ ውድቀት ያድርሳል።
የመንፈስ አገልግሎት እጅግ በክብር አይልቅምን? በመንፈስ ቅዱስ ውስጥ ያለው ክብር በሙሴ ህግ ውስጥ ካለው ክብር እጅግ ይበልጣል። ትኩረት፡"ምክንያቱም* የመንፈስ ቅዱስ ስራ የበለጠ ነውና።"
በፊደላት * የተቀረፀው
"በፊደላት የተቀረፀው" የሞት አገልግሎት * የመንፈስ አገልግሎት
ጳውሎስ "የ አገልግሎት" የሚለውን ሃረግ የሚጠቀመው እግዚአብሔር በህግ አማካኝነት የሰጠውን ሞት ወይም በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት የሰጠውን ህይወት አመላካች ነው። ትኩረት፡ "ሞት የሚያስከትለው መንገድ * መንፈስ ቅዱስ መንገድ የሚመጣው።"
የኩነኔ አገልግሎት ይህ ሀረግ የሚያመለክተው እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠውን ህግ ነው። የሚያነጣጥረውም የሰውን ለእግዚአብሔር አለመታዘዝ ሲሆን፥ውጤቱም የሰውን ልጅ ለሞት ፍርድ መዳረግ ነው። የፅድቅ አገልግሎት ይህ ሀረግ የሚያመለክተው በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት የተሰጠውን የይቅርታ መልዕክት ነው። የሞትን ፍርድ እንደሚያመጣው ህግ ሳይሆን ይቅርታን እና አዲስ ህይወትን ያስገኛል። በክብር ይብዛ የክርስቶስ የፅድቅ አገልግሎት ከህግ ክብር ይልቅ እጅጉን የከበረ ነው። በርግጥም ቀድሞ * የነበረው
"የነበረው" የሚለው ቃል የሙሴን ህግ አመላካች ነው። ይበልጥ "ያ የተሻለ ነው" አላፊው "ዓላማውን ፈፅሟል"
የሚያልፈውን ክብር፡ የእግዚአብሔር ክብር ብርሃን በሙሴ ፊት ላይ ነበርና ሙሴ እስራኤላውያን በፊቱ ላይ የሚደበዝዘውን ክብር እንሳያዩ ብሎ መሸፈኛ ፊቱ ላይ ያደርግ ነበር። ትኩረት፡ "ከሙሴ ፊት ላይ እየደበዘዘ የሚሄደው የእግዚአብሔር የክብሩ ብርሃን"
የእነርሱ "እስራኤላዌያን" ያው መሸፈኛ አይነርግብ ፊትን እንደሚሸፍን፥ጳውሎስም እዚህ ጋ መንፈሳዊ አይነርግብ አይሁድን የእግዚአብሔርን መልዕክት እንዳይረዱ እንደሚከለክላቸው ይናገራል። የሙሴ ህግ ሲነበብ ይህ በሙሴ አማካኝነት የተፃፉትን መፃህፍት ያመላክታል። ትኩረት፡ "የሙሴ ፅሁፎች በተነበቡ ጊዜ ሁሉ" (ተመልከት፡ ወደ ጌታ መለስ ሲል "መለስ" የሚለው ቃል የአስተሳሰብ ለውጥን የሚያመለክት ነው። ትኩረት፡ "ራሳቸውን ከማመን ጌታ ወደ ማመን መለወጥ" መሸፈኛው ይነሳል "መሸፈኛ" የሚለው ቃል የእግዚአብሔርን መልዕክት መረዳት አለመቻልን ያሳያል። "ይነሳል" ሲልም በዚህ ጊዜ ደግሞ የመረዳት ችሎታ ይሰጣቸዋል ማለት ነው።
ባልተሸፈነ ፊት የጌታን ክብር እያየን የእንድ ሰው ፊት መሸፈኛ ሲነሳለት በግልፅ ማየት የሚችል ሲሆን መረዳት መቻልን ያመላክታል። "እያየን" የሚለው ቃል አንድን ነገር መረዳትን ያመለክታል። እርሱን ወደሚመስል ከጌታ ክብር ጋር የሚመሳሰል ክብር ወይንም የእግዚአብሔርን ክብር የሚያሳይ ነገር ከአንድ ክብር ደረጃ ወደ ሌላ ክብር ደረጃ "ከእንድ የክብር መጠን ወደ ሌላ የክብር መጠን"
1 እንግዲህ፥ይህ አገልግሎት ስላለን እንዲሁም ምህረት እንደተቀበልን መጠን፥ ተስፋ አንቆርጥም። 2 በዚያ ፈንታ ግን አሳፋሪ እና ድብቅ የሆኑ መንገዶችን ክደናል። የተንኮል ህይወት አንኖርም፥የእግዚአብሔርንም ቃል ያለ አግባብ አንጠቀምበትም። እውነትንም እየተናገርን ራሳችንን ለሰው ሁሉ ህሊና በእግዚአብሔር ፊት እናቀርባለን። 3 ሆኖም ግን ወንጌላችን የተሸፈነ ቢሆን፥የተሸፈነው ለሚጠፉት ሰዎች ብቻ ነው። 4 በእነርሱ ሁኔታ ታዲያ የዚህ ዓለም አምላክ የማያምን አዕምሮዋቸውን አሳውሮታል። በዚህም የእግዚአብሔር መልክ የሆነውን የክርስቶስን የክብር ወንጌል ብርሃን እንዳያዩ አደረጋቸው። 5 ክርስቶስ ኢየሱስ ጌታ እንደሆነ እንጂ ራሳችንን አንሰብክም፥እንዲሁም ስለ ኢየሱስ ስንል የእናንተ አገልጋዮች ነን። 6 ውስጥ ብርሃን ይብራ" ያለው ራሱ እግዚአብሔር ነው፤እናም በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት የእግዚአብሔር ክብር የእውቀት ብርሃን እንዲሰጠን በልባችን ውስጥ አበራልን። 7 ነገር ግን እጅግ ታላቅ የሆነው ሃይሉ ከእግዚአብሔር እንጂ ከእኛ እንዳልሆነ ለማሳየት ይህ ሃብት በሸክላ ዕቃ ውስጥ አለን። 8 በሁሉ መንገድ መከራን እንቀበላለን፥ሆኖም በዚያ አንዋጥም። እናመነታለን ነገር ግን ተስፋ በማጣት አንረበሽም። 9 ቢሆንም ግን ተረስተን አንቀርም። 10 የኢየሱስ ህይወት በሰውነታችን እንዲገለጥ የእርሱን ሞት ሁልጊዜ በሰውነታችን እንሸከማለን። 11 ይህም የኢየሱስ ህይወት በሰብዓዊ ሰውነቶቻችን እንዲገለጥ እኛ ህያዋን የሆንን በየዕለቱ ስለ ኢየሱስ ምክንያት ለሞት ታልፈን እንሰጣለን። 12 በዚህም ምክንያት ሞቱ በእኛ፥ ህይወቱም በእናንተ ይሰራል። 13 ነገር ግን "አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ"ተብሎ እንደተፃፈ፡ ሁላችንም አንድ አይነት የእምነት መንፈስ አለን። ስለምናምንም እንናገራለን። 14 ጌታ ኢየሱስን ከሞት ያስነሳው እኛንም ከእርሱ ጋር ያስነሳናል። ከእናንተም ጋር ወደ ፊቱ እንዲያመጣን እናውቃለን። 15 የሚሆነው ለእናንተ ጥቅም ሲሆን ፀጋ ለብዙዎች ሲበዛ ለእግዚአብሔር ክብር የሚሆን ምስጋናም ይጨምራል። 16 ስለዚህም ተስፋ አንቆርጥም። ምንም እንኳ ውጫዊው ማንነታችን እየደከም ቢመጣም ውስጣዊው ማንነታችን ዕለት በየዕለት ይታደሳል። 17 ይህ ጊዜያዊ፣ ቀላል መከራችን መለኪያ ለሌለው፥ ለላቀው ዘላለማዊ ክብር የሚያዘጋጀን ነው። 18 የሚታዩትን ነገሮች ሳይሆን የማይታዩትን ነገሮች እንመለከታለን። የምናያቸው ነገሮች ጊዜያዊ ሲሆኑ የማይታዩት ነገሮች ግን ዘላለማዊ ናቸው።
እኛ፡ "እኛ" ለሚለው ለዚህ ትርጉም ሊሆኑ የሚችሉ 1) ጳውሎስ እና የአገልግሎት ቡድኑ ወይም 2) ጳውሎስ እና ሌሎች ሐዋርያቶች ወይም 3) ጳውሎስ እና የቆሮንቶስ አማኞች ይህ አገልግሎት ስላለን እንዲሁም ምህረት እንደተቀበልን፡ እነዚህ ሁለቱም ሃረጎች የሚያመላክቱት እግዚአብሔር እርሱን እንድንመስል በመለወጥ ምህረቱን በማሳየት እንዴት እንዳገለገለን ነው። አሳፋሪ እና ድብቅ እነዚህ ሁለት ቃላት አንድ አሳብን ይገልፃሉ። ትኩረት፡ "ድብቅ አሳፋሪ" የተንኮል ህይወት፡ "በማታለል መኖር" የእግዚአብሔርንም ቃል ያለ አግባብ አንጠቀምበትም፡ ይህ ሃረግ አንድ አዎንታዊ ሃሳብ ለመግለፅ ሁለት አሉታዊ ሃሳቦችን ያነሳል። ትኩረት፡"የእግዚአብሔርን ቃል በትክክል እንጠቀማለን። በእግዚአብሔር ፊት፡ እግዚአብሔር የፀሐፊውን እውነተኛነት የሚረዳበት ሁኔታ እግዚአብሔር እነርሱን ከሚያይበት ጋር ተመላክቷል።
ወንጌላችን የተሸፈነ ቢሆን፥የተሸፈነው * ብቻ ነው፡
"የተሸፈነው የሚለው ቃል ለመረዳት የማይቻል ማለት ነው። አንድ ነገር ከተሸፈነ ሊታይ የማይችል ነው ማለት ነው። የማይታይ ነገር መረዳት ከማይቻል ነገር ጋር እኩል ነው። የዚህ ዓለም አምላክ፡ ይህ ሃረግ የሚያመለክተው ሰይጣንን ነው። የእንግሊዝኛ ትርጉሞች ሃሰተኛ አማልክትን ለማመልከት ትንሹን "ጂ" ይጠቀማሉ። ኣሳውሮታል፡ ትኩረት፡"ከመረዳት ከለከላቸው" ብርሃን፡ "ብርሃን" የሚለው ቃል እውነትን ያመለክታል።
ክርስቶስ ኢየሱስ ጌታ እንደሆነ እንጂ * የእናንተ አገልጋዮች ነን፡
ይህ የዕብራዊያን ፀሐፊ እንዲህ በማለት የፃፈውን ያሳያል። ትኩረት፡"ክርስቶስ ጌታ እንደሆነ እና ለጥቅማችሁ እንደምንሰራ እናውጃለን።" ስለ ኢየሱስ ስንል፡ ትኩረት፡ ለኢየሱስ ክብር ለማምጣት በጨለማ ውስጥ ብርሃን ይብራ፡ ብርሃን መረዳትን ያመላክታል። ትኩረት፡ "ሰዎች ከዚህ ቀደም ያላስተዋሉትን ሲያስተውሉ" አበራልን፡ "አበራልን" የሚለው ቃል የእግዚአብሔርን የብሬሃን ፈጣሪነት እና መረዳትን ሰጪነት አመላካች ነው።" በልባችን ውስጥ፡ "ልብ የሚለው ቃል ሰው በራሱ እውነት ነው ብሎ የሚረዳውን ስፍራ አመላካች ነው። ትኩረት "ለእኛ"
ይህ ሃብት፡ ፀሐፊው በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት ያለውን "የእግዚአብሔር እውቀት ክብር" ያመለክተናል።" በሸክላ ዕቃ፡ ፀሐፊው ይህንን ሃረግ የሚጠቀመው ለሰው ልጅ ሰውነት ነው። በሁሉ መንገድ መከራን እንቀበላለን፥ሆኖም በዚያ አንዋጥም። እናመነታለን ነገር ግን ተስፋ በማጣት አንረበሽም። ቢሆንም ግን ተረስተን አንቀርም፡ እነዚህ ሃረጋት የሚያመላክቱት በተግዳሮት ውስጥ ያለ ነገር ግን ያልተሸነፈ ሰውን ነው። የእርሱን ሞት ሁልጊዜ በሰውነታችን እንሸከማለን፡ "የኢየሱስ ሞት" የሚለው ሃረግ የሚያመለክተው ኢየሱስ ለሰው ልጆች ሃጢያት ማስተሰረያ የመሞቱን መረዳት ነው። ትኩረት፡ "ሁልጊዜ የኢየሱስን ሞት እውቀት በሰውነታችን እንሸከማለን።" የኢየሱስ ህይወት በሰውነታችን እንዲገለጥ፡ "በሰውነታችን" የሚለው ቃል አማኞች በኢየሱስ የሚኖሩትን አኗኗር የሚያሳይ ነው። (ተመልከት፡
2ኛ ቆሮንቶስ 4፡11-12 እኛ ህያዋን የሆንን፡ ጳውሎስ በዚህ የሚያመለክተው በክርስቶስ አምኖ ጌታን የሚሰብክ ፥በሞት ያልተለየን ማንኛውንም ሰው ነው። ታልፈን እንሰጣለን፡ "አደጋ ውስጥ" የኢየሱስ ህይወት * እንዲገለጥ፤፡
ይህ ሃረግ ቀጣይ የሆነውን የኢየሱስ ህይወት የሚያመላክት እና ለዕብራውያን ፀሐፊም ምን ማለት እንደሆነ የሚያሳይ ሲሆን በተጨማሪም እምነታቸውን በክርስቶስ ጌታ ላይ በማድረጋቸው ምክንያት እስከ ሞት ድረስ አደጋ ውስጥ የከተቱትን አማኞች ያጠቃልላል። ትኩረት፡ "እምነታችን ኢየሱስ ከሞት እንደተነሳ እና የዘላለም ህይወት እንደሚሰጠን ይረጋገጥ ዘንድ ነው።" በሰብዓዊ ሰውነቶቻችን፡ በዚህ ማብራሪያ እንደሚታየው [2CO 4:10] ሞቱ በእኛ ይሰራል፡ ጳውሎስ ሞት ስራ እንደሚሰራ አድርጎ ያሳያል። ይህም ሞት የሚያስፈራቸው ሰዎች በሌሎች ላይ ግን አዎንታዊ ውጤት እንደሚኖራቸው ነው። ህይወቱም በእናንተ ይሰራል፡ ጳውሎስ ህይወት ስራ እንደሚሰራ አድርጎ ያሳያል። ይህም የዘላለም ህይወት እውቀት ሰዎች በአይሁድ እማኞች ኑሮ ላይ አዎንታዊ ውጤት እንደሚኖረው ነው። (ተመልከት፡
ሁላችንም አንድ አይነት፡ "ሁላችንም" የሚለው ቃል ጳውሎስን ፥ጢሞቲዎስን እና የቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያንን ያመለክታል። አንድ አይነት የእምነት መንፈስ፡ "ተመሳሳይ የእምነት እሳቤ" "መንፈስ" የሚለው ቃል አንድ ሰው የሚያስብበትንና የሚወስንበትን መንገድ ያሳያል። ጳውሎስ እና ጢሞቲዎስ እያሉ ያሉት እግዚአብሔርን የመታመናቸው ዝንባሌ ከቆሮንቶሶች ጋር ተመሳሳይ ነው ማለት ነው። አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ፡ ይህ ቃል ከንጉስ ዳዊት የተጠቀሰ ነው። ከናንተም ጋር እንዲያመጣን፡ "እንዲያምጣን" የሚለው ቃል ውስጥ ቆሮንቶሶችን አይጨምርም። ምስጋና፡ መልካሙ አምላክ ያደረገውን ማሰብና ማመስገን
ስለዚህም ተስፋ አንቆርጥም፡ ትኩረት፡ "ስለዚህ እንበረታታለን" (ተመልከት፡
ውጫዊው ማንነታችን እየደከም ቢመጣም፡ ይህ ሃረግ የጳውሎስን እና የጢሞቲዎስ ውጫዊ ገፅታን ያሳያል። '"እየደከመ" የሚለው ቃል የሚያሳየው ጤናማ ገፅታ እያጣ የመጣን የአንድን ሰው ሁኔታ ነው። ውስጣዊው ማንነታችን ዕለት በየዕለት ይታደሳል፡ "ውስጣዊ" የሚለው ቃል የሰውን ማሰቢያ ውስጣዊ ማንነት አመላካች ነው። "ይታደሳል" የሚለውም ቃል እሳቤዎች እንደገና አዎንታዊ መልክ እንደሚይዙ ያሳያል። መለኪያ ለሌለው፥ ለላቀው ዘላለማዊ ክብር፡ ጳውሎስ እና ጢሞቲዎስ የሚጥብቃቸው ክብር ከእቅም በላይ ከሆነ ክብደት ጋር ተነፃፅሯል። ይህ በሌላ አባባል በስራቸው እጅግ ታላቅ ክብር እንደሚያግኙ ያሳያል። ትኩረት፡ "በሰማይ ለዘላለም በታላቅ ሁኔታ መክበር" (ተመልከት፡
የሚያዘጋጀን፡ ይህ ቃል የሚያመለክተው እንድ ሰው እንዲሆን የሚጠብቀውን ነው። ትኩረት፡ "መፈለግ" የምናያቸው ነገሮች፡ ይህ በህይውት ሳለን የሚገኙ ንብረቶች ናቸው። ትኩረት፡ "ንብረቶች" የማይታዩት ነገሮች፡ ይህ የሚያመለክተው በሰማይ ያለውን ሽልማት ነው። ትኩረት፡ "በሰማይ ያለ ታላቅ ብድራት" ቀደም ብሎ ከሚገኘው ሃረግ መገንዘብ እንደሚቻለው ጳውሎስና ጢሞቲዎስ የሚጠብቁት ይህንን ነው።
1 ምድራዊው መኖሪያችን ቢፈርስ እንኳ በሰማይ በሰው እጅ ያልተሰራ ዘላለማዊ ቤት በእግዚአብሔር እንደተሰራልን እናውቃለን። 2 ድንኳን ውስጥ ሆነን እንቃትታለን፥ሰማያዊ መኖሪያችንንም ልንለብስ እንናፍቃለን። 3 ምክንያቱም ያን ለብሰን ስንገኝ ራቁታችንን ሆነን አንገኝም ። 4 በርግጥ በዚህ ድንኳን ውስጥ ሆነን ከብዶን እንቃትታለን፤ምክንያቱ ደግሞ ሟች የሆነው ሰውነት በህይወት መዋጥ ስላለበት እኛም ለብሰን እንጂ ራቁታችንን መሆን አንፈልግም። 5 ወደ ፊት ሊመጣ ላለው የመንፈሱን ዋስትና የሰጠን ለዚህም ያዘጋጀን እግዚአብሔር ነው። 6 እንግዲህ በሰውነታችን በዚህ ምድር በምንኖርበት ጊዜ በሰማይ ካለው ጌታ ርቀን እንዳለን ይህን እርግጠኛ ሁኑ 7 ምክንያቱም በእምነት እንጂ በማየት አንመላለስምና። 8 ስለዚህ ይህ ድፍረት አለን፤ከሰውነታችን ተለይተን ከጌታ ጋር በሰማይ ቤት መሆንን እንመርጣለን። 9 ስለሆነም በምድርም ብንሆን ወይም ከምድር ብንለይ ግባችን እርሱን ማስደሰት ነው። 10 እያንዳንዳችን በሰውነታችን በዚህ ምድር ላይ የሰራነውን መልካምም ሆነ ክፉ እንቀበል ዘንድ ሁላችን በክርስቶስ የፍርድ ወንበር ፊት መቅረባችን ግድ ነው። 11 እንግዲህ ጌታን መፍራት ምን ማለት እንደሆን ስለምናውቅ ሰዎችን ግድ እንላለን። ማንነታችን በእግዚአብሔር ፊት የተገለጠ ስለሆነ ለናንተም ህሊና ግልፅ እንደሚሆን ተስፋ አለኝ። 12 ራሳችንን ደግመን እንድታወድሱን አናቀርብላችሁም፥ ሆኖም በልብ ሳይሆን በውጫዊው መልክ ለሚመኩ መልስ መስጠት እንዲቻላችሁ እኛን ምክንያት አድርጋችሁ እንድትመኩ እናስታውቃችኋለን። 13 እንደ እብድ ቢያረገን፥ ለእግዚአብሔር ነው፤እንደ ባለአዕምሮ ብንሆን ደግሞ ለእናንተ ስንል ነው። 14 የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናል፥ በዚህ ነገር እርግጠኞች ነን፡አንዱ ሰው ስለሁሉ ሞተ፥ ስለሆነም ሁሉም ሞቱ ማለት ነው። 15 በህይወት ያሉትም ስለእነርሱ ለሞተውና ለተነሳው እንጂ ለራሳቸው እንዳይኖሩ ክርስቶስ ስለሁሉ ሞተ። 16 ስለዚህም ምክንያት ክርስቶስን ከዚህ ቀደም በሰዋዊ መንገድ አይተነው ቢሆን፥ካሁን ጀምሮ ማንንም በሰዋዊ መስፈርት አንፈርድም። በማንም ላይ ከዚህ በኋል በዚህ መንገድ አንፈርድም። 17 ስለሆነም ማንም በክርስቶስ ውስጥ ቢሆን እርሱ አዲስ ፍጥረት ነው። አሮጌ ነገሮች አልፈዋል። ተመልከቱ፥ ሁሉ አዲስ ሆኗል። 18 እነዚህ ነገሮች ሁሉ የሆኑት እኛን በክርስቶስ ከራሱ ጋር ባስታረቀንና የዕርቅ አገልግሎት በሰጠን በእግዚአብሔር ነው። 19 እግዚአብሔርም በደላቸውን ሳይቆጥርባቸው ዓለሙን በክርስቶስ ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበር። እኛንም ለዚህ የዕርቅ መልዕክት ታማኝ አድርጎ ሾመን። 20 ስለዚህም እግዚአብሔር በእኛ ሆኖ ልመናውን እንደሚያቀርብ፥ የክርስቶስ ተወካዮች ሆነን ተሹመናል። ከእናንተም ጋር በመሆን ስለ ክርስቶስ "ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ!" ብለን ልመና እናቀርባለን። 21 እኛም በእርሱ የእግዚአብሔር ፅድቅ እንድንሆን ሃጢያት ሰርቶ የማያውቀውን ክርስቶስን እግዚአብሔር የሃጢያት መስዋዕት አደረገው።
ምድራዊ መኖሪያችን፡ ሰብዓዊ ሰውነታችን መኖሪያችን ቢፈርስ፡ ሰብዓዊ ሰውነታችን ሲጠፋ በሰማይ በሰው እጅ ያልተሰራ ዘላለማዊ ቤት በእግዚአብሔር እንደተሰራልን እናውቃለን፡ እግዚአብሔር የምንኖርበትን አዲስ ዘላለማዊ አካል ይሰጠናል። ድንኳን ውስጥ ሆነን እንቃትታለን፡ ትኩረት፡"በዚህ ምድራዊ አካል ውስጥ ሆነን እንታገላለን"
ምክንያቱም ያን ለብሰን ስንገኝ ራቁታችንን ሆነን አንገኝም፡ ትርጉም ሊሆኑ የሚችሉ፡ 1) በእግዚአብሔር ፅድቅ እንሸፈናለን ወይም 2) እግዚአብሔር አዲስ አካልን ሰጥቶ ያለብሰናል።
በዚህ ድንኳን ውስጥ ሆነን፡ "በዚህ ምድራዊ አካል ውስጥ ሆነን" ከብዶን እንቃትታለን፡ ትኩረት፡ "ከሐጢያት ጋር እየታገልን" ራቁታችንን፡ ትኩረት፡ "ስንሞት" ለብሰን፡ ትኩረት፡ "በዘላለማዊ አካላችን ውስጥ ስንኖር" ሟች የሆነው ሰውነት በህይወት መዋጥ ስላለበት፡ ትኩረት፡"ምድራዊ የሆነው አካላችን ወደ አዲስ ሰማያዊ አካል ይለወጣል"
በሰውነታችን በዚህ ምድር በምንኖርበት ጊዜ፡ ትኩረት፡"በዚህ ምድራዊ ሰውነት በምንኖርበት ጊዜ" በሰማይ ካለው ጌታ ርቀን፡ ትኩረት፡ "ከጌታ ጋር በቤት አይደለንም" ወይም "በሰማይ ከጌታ ጋር አይደለንም" ከጌታ ጋር በሰማይ ቤት፡ ትኩረት፡"ከጌታ ጋር በሰማይ መኖር"
በምድርም ብንሆን ወይም ከምድር ብንለይ፡ ትኩረት፡"በምድራዊ እካል በምድር ወይም በሰማይ" በክርስቶስ የፍርድ ወንበር ፊት፡ "ለፍርድ በክርስቶስ ፊት መሆን" እንቀበል ዘንድ፡ ትኩረት፡"ሽልማትም ሆን ቅጣት ለመቀበል" በዚህ ምድር የሰራነውን፡ ትኩረት፡ "በዚህ ምድራዊ አካል የተሰራውን" መልካምም ሆነ ክፉ፡ "መልካምም ሆን ክፉ ቢሆኑ"
ጌታን መፍራት ምን ማለት እንደሆን ስለምናውቅ፡ ትኩረት፡ "እግዚአብሔር ሐጢያትን እንደሚጠላ እንደሚፈርድም አውቀን" ለናንተም ህሊና ግልፅ እንደሚሆን፡ ትኩረት፡ "እናንተም እንደዚሁ እንደምታውቁ" አናቀርብላችሁም፡ ጳውሎስ እዚህ ጋር ከቆሮንቶስ አማኞች ውጪ ያሉትን ሲያመላክት ነው።
የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናል፡ "እኛን የሚያነሳሳን የክርስቶስ ፍቅር ነው" ስለሆነም ሁሉም ሞቱ፡ እኛ ሁላችን እንደሞትን ተቆጠርን። ለራሳቸው፡ ትኩረት፡"በሃጢያት ለሚገኝ ደስታ" ለተነሳው፡ "ደግሞም ለተነሳው"
ማንም በክርስቶስ ውስጥ ቢሆን፡ ትኩረት፡ "ማንም ክርስቶስን ቢያምን" አዲስ ፍጥረት ነው፡ ትኩረት፡ "አዲስ ባህሪ መያዝ" አሮጌ ነገሮች አልፈዋል፡ ትኩረት፡ "አሮጌው የአኗኗር መንገድ እና እስተሳሰብ ይጠፋል" ሁሉ አዲስ ሆኗል፡ ትኩረት፡ "አኗኗራችንና አስተሳሰባችን ክርስቶስን ከማወቃችን በፊት የነበረውን የማይመስል የተለየ ነው"
ባስታረቀንና፡ "በመለሰንና" "ባደሰን" የዕርቅ አገልግሎት፡ ሰዎችን ከክርስቶስ ጋር መልሶ የሚያገናኝ እና የሚያድስ አገልግሎት እግዚአብሔርም * ዓለሙን በክርስቶስ ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበር፡
እግዚአብሔር በክርስቶስ መስቀል ሞት ሰዎችን ወደ ራሱ ይመልስ ነበር። እኛንም ለዚህ የዕርቅ መልዕክት ታማኝ አድርጎ ሾመን፡ እግዚአብሔር ለጳውሎስ መልዕክቱን እንዲያሰራጭ ብሎም ከእግዚአብሔር ጋር እንዲያድሱ ይፈልጋል።
ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ፡ ትኩረት፡"ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ" ክርስቶስን *የሃጢያት መስዋዕት፡ "እግዚአብሔር የክርስቶስን የመስቀል ሞት ተቀባይነት ያለው መስዋዕት አደረገው" እኛም በእርሱ የእግዚአብሔር ፅድቅ እንድንሆን፡ ትኩረት፡ "በእኛ ውስጥም የክርስቶስ ፅድቅ እንድንሆን"
1 እንደዚሁም፥ አብሮ እንደሚሰራ የእግዚአብሔርን ፀጋ እንዲሁ እንዳትቀበሉ እለምናችኋለሁ። 2 ምክንያቱም እግዚአብሔር እንዲህ ብሏልና "በምቹ ጊዜ ሰማሁህ በድነትም ቀን ረዳሁህ።" ልብ በሉ፥ ምቹ ጊዜም ሆነ የድነት ቀን አሁን ነው። 3 አገልግሎታችን እንዳይነቀፍ በማንም ፊት ማሰናከያ አናኖርም። 4 ከዚያ ይልቅ፥ በድርጊቶቻችን ሁሉ የእግዚአብሔር አገልጋዮች መሆናችንን እናረጋግጣለን። ይህም በመፅናት፥በመከራ፥ በስቃይ፥በችግር 5 በመገረፍ፥ በእስራት፥ጥላቻ በተሞላ አመፅ፥ ፥በከባድ ስራ ፥እንቅልፍ በማጣት፥በርሃብ፥ 6 በንፅህና፥በእውቀት፥በትዕግስት፥በርህራሄ፥በመንፈስ ቅዱስ፥በእውነተኛ ፍቅር፥ 7 በእውነት ቃል፥ በእግዚአብሔር ሃይል ማለትም ለቀኝ እና ለግራ ለሚሆን ለፅድቅ የጦር ዕቃ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ነን። 8 በክብርም ሆነ በውርደት፥ በሃሜትም ሆነ በሙገሳ ውስጥ እንሰራለን። በሃሰት ብንከሰስም እውነተኞች ሆነን ተገኝተናል። 9 ያልታወቅን ሆነን ስንሰራ፥እንታወቃለን፤ የምንሞት ስንመስል ህያዋን ነን። በጥፋታችን እንደሚቅጣ ሰው ብንሆንም፥ሞት አልተፈረደብንም። 10 እንደ ሃዘንተኞች ስንሰራ ሁልጊዜም ግን ደስተኞች ነን፤ ድሆች ስንሆን ብዙዎችን ባለፀጎች እናደርጋለን፥ ምንም የሌለን ስንሆን፥ ሁሉም አለን። 11 የቆሮንቶስ ሰዎች ሆይ፥ ሁሉን ነገር በግልፅ ነግረናችኋል፥ልባችንንም ለእናንተ ከፍተንላችኋል። 12 ልባችሁ በራሳችሁ መሻት እንጂ በእኛ ምክንያት አልተዘጋም። 13 ተገቢ በሆነ ሁኔታ እኔም እንደ ልጆች እናገራችኋለሁ፤ልባችሁን ክፈቱልን። 14 ከማያምኑ ጋር በማይሆን መንገድ በአንድ ላይ አትተሳሰሩ። ፅድቅ ከአመፀኝነት ጋር ምን መዛመድ አለው? ብርሃንስ ከጨለማ ጋር ምን ህብረት አለው? 15 ክርስቶስስ ከቤልዖር ጋር ምን ስምምነት አለው? የሚያምንስ ከማያምን ጋር ምን ድርሻ አለው? 16 የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስስ ከጣዖታት ጋር ምን ስምምነት አለው? እግዚአብሔር "ከእነርሱም ጋር አድራለሁ፥በመካከላቸውም እመላለሳለሁ፤ አምላካቸው እሆናለሁ፥ እነርሱም ህዝብ ይሆኑኛል" ብሎ ስለተናገረ እኛ የህያው እግዚአብሔር መቅደሶች ነን። 17 ስለዚህም "ከመካከላቸው ውጡ፤የተለያችሁም ሁኑ" ይላል ጌታ፥ "እርኩሱን አትንኩ፥እኔም እቀበላችኋለሁ። 18 አባት እሆናችኋለሁ እናንተም ወንዶችና ሴቶች ልጆች ትሆኑኛላችሁ።" ብሏል ሁሉን የሚችል ጌታ።
አብሮ እንደሚሰራ፡ ትኩረት፡ "ከእግዚአብሔር ጋር አብሮ የሚሰራ" ጳውሎስ በተዘዋዋሪ መንገድ እርሱ እና ጢሞቲዎስ ከእግዚአብሔር ጋር እንደሚሰሩ ያሳያል። የእግዚአብሔርን ፀጋ እንዲሁ እንዳትቀበሉ እለምናችኋለሁ፡ ጳውሎስ ቆሮንቶሶችን የእግዚአብሔር ፀጋ በኑሯቸው እንዲገለጥ ያበረታታቸዋል። ትኩረት፡ "እግዚአብሔር ፀጋውን እንዳሳያችሁ ሰዎች መኖራችሁን እርግጠኞች እንድትሆኑ አሳስባችኋለሁ።" በምቹ ጊዜ ሰማሁህ፡ ትኩረት፡"በትክክለኛው ጊዜ ሰማሁህ" ምቹ ጊዜም ሆነ የድነት ቀን አሁን ነው፡ ትኩረት፡"በርግጥም፥ትክክለኛው ጊዜ አሁን ነው፤የድነትም ቀን አሁን ነው" አገልግሎታችን እንዳይነቀፍ በማንም ፊት ማሰናከያ አናኖርም፡ ትኩረት፡ ማንንም ሊያሳስት በሚችል አይነት መንገድ አንኖርም ወይም በአገልግሎታችንም የሚያስት ነገር አናደርግም።"
በድርጊቶቻችን፡ ጳውሎስ እዚህ ጋ የሚያመለክተው ወደራሱ እና ጢሞቲዎስ ነው። በድርጊቶቻችን ሁሉ የእግዚአብሔር አገልጋዮች መሆናችንን እናረጋግጣለን፡ ትኩረት፡"የእግዚአብሔር አገልጋዮች መሆናችንን በአኗኗሯችን እና በንግግራችን እናረጋግጣለን" በእውነት ቃል፡ "እውነትን በታማኝነት በመስበክ" ለቀኝ እና ለግራ ለሚሆን ለፅድቅ የጦር ዕቃ ፡ ጳውሎስ ለሁሉም አይነት ሁኔታ በሚያስፈልግ መልኩ በመንፈሳዊ ሃይል በእግዚአብሔር እንደታጠቀ ያመለክታል።
እንሰራለን፡ "እንሰራለን" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን እና ጢሞቲዎስን ነው። በክብርም ሆነ በውርደት፡ እነዚህ ሰዎች የጳውሎስን አገልግሎት የሚመለከቱበትን ፅንፎች ያሳያል። በሃሜትም ሆነ በሙገሳ፡ እነዚህ ሰዎች ስልጳውሎስ አገልግሎት የሚናገሩትን ፅንፎች ያሳያል። የምንሞት ስንመስል ህያዋን ነን፡ ትኩረት፡"እንደምትመለከቱት፥የምንሞት ስንመስል ህያዋን ነን" ሁልጊዜም ግን ደስተኞች ነን፡ ትኩረት፡"መልካም ዜና በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ምክንያት ሁልጊዜ ደስ ይለናል" ምንም የሌለን ስንሆን፥ ሁሉም አለን፡ ትኩረት፡"ምንም ባይኖረንም የእግዚአብሔር ሃብት ግን አለን"
ሁሉን ነገር በግልፅ ነግረናችኋል፡ "በታማኝነት ነግረናችኋል" ልባችንንም ለእናንተ ከፍተንላችኋል፡ ትኩረት፡"በነፃ ፍቅራችንን አሳይተናችኋል" ልባችሁ * በእኛ ምክንያት አልተዘጋም፡
ትኩረት፡"በእኛ ዘንድ የፍቅር ጉድለት አላሳየንም" ልባችሁ በራሳችሁ መሻት እንጂ፡ ትኩረት፡ "ፍቅራችሁን በሆነ ምክንያት ዘግታችሁብናል" ተገቢ በሆነ ሁኔታ እኔም እንደ ልጆች እናገራችኋለሁ፤ልባችሁን ክፈቱልን፡ ትኩረት፡ "በቀላሉ በልጅ ቋንቋ ስንናግራችሁ፥ተገቢ የሚሆነው እናንተም ፍቅራችሁን ስታሳዩን ነው"
ከማያምኑ ጋር * በአንድ ላይ አትተሳሰሩ፡
ትኩረት፡"ከአማኞች ጋር ብቻ የምትተሳስሩ ሁኑ"
በአንድ ላይ፡ "በጋራ መቧደን" ወይም "የቅርብ ህብረት መፍጠር"
ብርሃንስ ከጨለማ ጋር ምን ህብረት አለው፡ ብርሃን ከጨለማ ጋር አብረው በጋራ መኖር አይችሉም። ብርሃን ሲኖር ፥ጨለማ ይሸሻል። (ተመልከት፡
ቤልዖር፡ "ቤልዖር" የዲያብሎስ ሌላ ስሙ ነው። የሚያምንስ ከማያምን ጋር ምን ድርሻ አለው፡ አማኞች ከማያምኑ ጋር ተመሳሳይ የሆነ እሴት የላቸውም። ትኩረት፡"አማኝ ከማያምን ጋር ምን አይነት እሴት ይኖረዋል"
የህያው እግዚአብሔር መቅደሶች ነን፡ ጳውሎስ ክርስቲያኖች ሁሉ የእግዚአብሔር መቅደስ ማደሪያዎች እንደሆኑ ያመለክታል። ትኩረት፡"በውስጣችን የሚኖር የእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ አለን" (ተመልከት፡
እርኩሱን አትንኩ፡ የሙሴ ህግ አንድን ሰው ሊያረክሰው የሚችለው መንገድ መንካት እንደሆን ይደነግጋል። "ንፁህ የሆነውን ነገር ብቻ ንኩ" (ተመልከት፡
አባት እሆናችኋለሁ፡ ትኩረት፡"የተወደደ አባት ለልጆቹ እንክብካቤ እንደሚያደርግ እናንተንም እንከባከባችኋለሁ" እናንተም ወንዶችና ሴቶች ልጆች ትሆኑኛላችሁ፡ "እናንተም ልጆቼ ትሆናላችሁ" (ተመልከት፡
1 የተወደዳችሁ ሆይ፥ እነዚህ ተስፋዎች ስላሉን በእግዚአብሔር ፍርሃት ቅድስናን እየተከተልን ስጋችንን እና መንፈሳችንን ከሚያረክስ ከማናቸውም ነገር ራሳችንን እናንፃ። 2 ለእኛ በልባችሁ ስፍራ ስጡን! ማንንም አልበደልንም፥ማንንም አልጎዳንም፥ ማንንም ለራሳችን ጥቅም አልበዘብዝንም። 3 ይህንን የምላችሁ ልኮንናችሁ ብዬ አይደለም፤ምክንያቱም አብረን ለመሞትም ሆነ ለመኖር በልባችን ውስጥ አላችሁና ነው። 4 በእናንተም ታላቅ መታመን አለኝ፣ትምክህቴም ናችሁ። በመከራዎቻችን እንኳ መፅናናት እና የተትረፈርፈ ደስታ ሞልቶኛል። 5 ወደ መቄዶንያ በመጣን ጊዜ ሰውነታችን እረፍት አልነበረውም። ይልቁንስ በውጭ ግጭት እና በውስጥ ፍርሃት ስለነበረብን በሁሉ አቅጣጫ ተጨነቅን ። 6 ነገር ግን ተስፋ የቆረጡትን የሚያፅናና አምላክ በቲቶ መምጣት አፅናናን። 7 የእርሱ መምጣት ብቻ ሳይሆን እናንተም እርሱን ያፅናናችሁት ማፅናናት እኛን አፅናናን። ለእኔም ያላችሁን ታላቅ ፍቅር፥ርህራሄ እና ጥልቅ ሃሳብ ሲነግረን በይበልጥ ተደሰትሁ። 8 ምንም እንኳ በመልዕክቴ ባሳዝናችሁም ለምን ፃፍኩ ብዬ አልፀፀትም። ነገር ግን፥የምፀፀተው መልዕክቴ ለጥቂት ጊዜም እንዳሳዘናችሁ ስለማውቅ ነው። 9 አሁን የምደሰትበት ምክንያት ስላዘናችሁ ሳይሆን ሃዘናችሁ ወደ ንስሃ ስለመራችሁ ነው። እግዚአብሔር የሚወደው አይነት ሃዘን እየተለማመዳችሁ ስለሆነ በእኛ ምክንያት ያጣችሁት ነገር የለም። 10 እግዚአብሔር የሚወደው ሃዘን ፀፀት የሌለበት፥ ወደ ድነት የሚመራ ንስሃን ያመጣል። ዓለማዊ ሃዘን ግን ሞትን ያመጣል። 11 እግዚአብሔር የሚወደው ሃዘን ምን አይነት ታላቅ ቁርጠኝነት እንዳመጣላችሁ እዩ። ይህም ታላቅ ቁርጠኝነት ምን ያህል ንፁህ መሆናችሁን፥ ምን ያህል በሃጢያት ላይ እንድትቆጡ እንዳደረጋችሁ፥ ምን አይነት ናፍቆት እንዳሳደረባችሁ፥ ምን አይነት በጎ ቅንዓት እንደፈጠረባችሁ ፥ፍትህ እንድታደርጉም ምን አይነት ጥልቅ መሻት እንዳደረገላችሁ ተመልከቱ! በዚህ በኩል በሁሉም ንፁህ መሆናችሁን አስመስክራችኋል። 12 ምንም እንኳ ብፅፍላችሁም የፃፍኩት ለክፉ አድራጊ ወይም በክፉ አድራጎቱ መከራ ለሚቀበል ሳይሆን ለእኛ ምን ያህል እንደምታስቡ በእግዚአብሔር ፊት እንዲታወቅ ነው። 13 በዚህ እንበረታታለን። እኛ ከመፅናናታችን በተጨማሪ በቲቶ ደስታ ሃሴት አድርገናል፤ መንፈሱ በሁላችሁ ምክንያት አርፏልና ነው። 14 ስለናንተ በመመካት ለእርሱ ተናግሬ ነበር፣እናንተም አላሳፈራችሁኝም። በሌላ አንፃር ስለናንተ የተናገርነው ሁሉ እውነት ነበር፥ለቲቶም ስለናንተ የተናገርነው ሁሉ ትክክል መሆኑ ተረጋግጧል። 15 እርሱም በፍርሃት እና በመንቀጥቀጥ ያደረጋችሁለትን አቀባበል እንዲሁም የሁላችሁንም መታዘዝ በሚያስብበት ጊዜ ለእናንተ ያለው ፍቅር ታላቅ ነው። 16 በናንተ ሙሉ መታመን ስላለኝ፥ሃሴት አደርጋለሁ።
የተወደዳችሁ ሆይ፡ ጳውሎስ የሚያመለክተው የቆሮንቶስ ሰዎችን ነው። ራሳችንን እናንፃ፡ እዚህ ጋር ጳውሎስ ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ግንኙነት ከሚጎዳ ከየትኛውም አይነት ሃጢያት እንድንርቅ ይናገራል። በእግዚአብሔር ፍርሃት፡ በእግዚአብሔር ፊት ትሁታን መሆን።
በልባችሁ ስፍራ ስጡን፡ "በኑሮአችሁ ለእኛ ስፍራ ይኑራችሁ"
ይህንን የምላችሁ ልኮንናችሁ ብዬ አይደለም፡ ትኩረት፡ "አላሳጣችሁም" ምክንያቱም አብረን ለመሞትም ሆነ ለመኖር በልባችን ውስጥ አላችሁና፡ ትኩረት፡"ከናንተጋር ለመኖርም ሆነ ለመሞት የሚያስችል ፍቅር አለን" በመከራዎቻችን እንኳ፡ ትኩረት፡ "ከገጠሙን ተግዳሮቶች በላይ"
ሰውነታችን እረፍት አልነበረውም፡ ትኩረት፡"በጣም ደክሞን ነበር" ወይም "ዝለን ነበር" በቲቶ መምጣት አፅናናን፡ ትኩረት፡"ከእናንተ ከቆሮንቶሶች ይዞ የመጣው የሚያበረታታ ዜና" ለእኔም ያላችሁን ታላቅ ፍቅር፥ርህራሄ እና ጥልቅ ሃሳብ ሲነግረን፡ ትኩረት፡"በእኔ በሆነብኝ ምክንያት ለእኔ ያላችሁን ፍቅር፥ርህራሄ እና ለደህንነቴ ያላችሁን ጥልቅ ሃላፊነት ነገረን።" በይበልጥ ተደሰትሁ፡ ትኩረት፡"በደስታ ተሞላሁ"
ምንም እንኳ በመልዕክቴ፡ ትኩረት፡"ከመልዕክቴ እንደተረዳሁት" ነገር ግን፥* ለጥቂት ጊዜም እንዳሳዘናችሁ፡
"ነገር ግን ያዘናችሁት ለጥቂት ጊዜ ነው" እግዚአብሔር የሚወደው አይነት ሃዘን እየተለማመዳችሁ፡ ትኩረት፡ ወደ ንስሃ የሚመራ እግዚአብሔር የሚወደው ሃዘን እግዚአብሔር የሚወደው ሃዘን ፀፀት የሌለበት፥ ወደ ድነት የሚመራ ንስሃን ያመጣል፡ "ከሃጢያት እንድንርቅ የሚያደርግ እግዚእብሔር የሚወደው ሃዘን" ዓለማዊ ሃዘን ግን ሞትን ያመጣል፡ ትኩረት፡"ዓለማዊ ሃዘን ግን ወደ መንፈሳዊ ሞት የሚመራ በመሆኑ ንስሃ የለውም።
ምን አይነት ታላቅ ቁርጠኝነት፡ "ታላቅ ቁርጠኝነትን መረዳት" እንዳመጣላችሁ እዩ። ይህም ታላቅ ቁርጠኝነት ምን ያህል ንፁህ መሆናችሁን፡ ትኩረት፡"ንፁህ መሆናችሁን ለማረጋግጥ፥ውስጣችሁ የማጣ ነገር አለ" ምን ያህል በሃጢያት ላይ እንድትቆጡ እንዳደረጋችሁ፡ "ቁጣችሁ በሃጢያት ላይ ታላቅ ነበር" እንድትቆጡ፡ "የእናንት ቁጣ" ናፍቆት፡ ትኩረት፡ ልታዩኝ በእጅግ ትፈልጉ ነበር" ቅንዓት፡ ትኩረት፡"ትክክለኛ የሆነውን ለማድረግ እጅግ ትጓጉ ነበር" ለእኛ ምን ያህል እንደምታስቡ በእግዚአብሔር ፊት እንዲታወቅ ነው፡ ትኩረት፡"እግዚአብሔርም ሆነ እኛ እንድምንገነዘበው ለእኛ ያላችሁ ስሜት መልካም ነበር"
በዚህ እንበረታታለን፡ ትኩረት፡ "እውነተኛ በሆነው ለእኛ ባላችሁ ታማኝነት እንበረታታለን" ስለናንተ በመመካት ለእርሱ ተናግሬ ነበር፡ "በእናንተ መመካቴን ለእርሱ አሳይቼዋለሁ" አላሳፈራችሁኝም፡ ትኩረት፡"አላሳዘናችሁኝም" ትክክል መሆኑ ተረጋግጧል፡ "እውነት መሆኑ ታይቷል"
ለእናንተ ያለው ፍቅር ታላቅ ነው፡ ትኩረት፡"ባሁኑ ጊዜ ቲቶ ከፊት ይልቅ ያስብላችኋል" በፍርሃት እና በመንቀጥቀጥ ያደረጋችሁለትን አቀባበል፡ ትኩረት፡"በፍርሃት እና በመንቀጥቀጥ አቀባበል አደረጋችሁለት እናም ታዘዛችሁት" ወይም "በታላቅ ክብር ተቀብላችሁ ታዘዛችሁት"
1 ወንድሞችና እህቶች ሆይ ለመቄዶንያ ለአብያተ ክርስቲያናት ስለ ተሰጠው የእግዚአብሔር ጸጋ እንድታውቁ እንፈልጋለን 2 እጅግ የሚፈትናቸው መከራ በደረሰባቸው ጊዜ የደስታቸው መብዛትና የደህንነታቸው አስከፊነት የልግስናቸውን መትረፍረፍ አብዝቷል። 3 የሚቻላቸውን ያህል ከሚቻላቸውም እንደ ሰጡ እኔ እመሰክርላቸዋለው። በፈቃዳቸውም ለቅዱሳን በሚሰጠው በዚህ አገልግሎት የመሳተፍ ዕድል ይኖራቸው ዘንድ 4 እኛን በብዙ ልመና ለመኑን። 5 ይህም የሆነው እኛ እንደጠበቅነው አይደለም ነገር ግን በመጀመሪያ ራሳቸውን በጌታ ከዚያም በእግዘአብሔር ፈቃድ ለእኛ ሰጡ። 6 ስለዚህ አስቀድሞ ከእናንተ ጋር የጀመረውን ተግባር በእናንተ ዘንድ ያለውን ይህን የልግስና ስራ ከፍጻሜ እንዲደርስ ቲቶን ግድ ብለነው ነበር። 7 ነገር ግን እናንተ በሁሉም ነገር በእምነት፥ በንግግር ፣በዕውቀት በትጋት ሁሉ እንዲሁም ለእኛ ባላችሁ ፍቅር እንደሚልቁ በዚህ በበጎ ስራ ደግሞ የምትልቁ ሁኑ። 8 ከሌሎች ሰዎች ትጋት ጋር በማወዳደር የፍቅራችሁን ቅንነት ለማረጋገጥ እንጂ ይህንን እንደ ትዕዛዝ አልልም እናንተ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ጸጋ ታውቃላችሁና። 9 በእርሱ ድኽነት እናንተ ባለጠጎች ትሆኑ ዘንድ ፥ እርሱ ባለ ጠጋ ቢሆንም እንኳ ስለ እናንተ ደኸየ። 10 በዚህ ጉዳይ እናንተን ስለሚጠቅማችሁ ነገር ምክር እለግሳችኋለው። ከአንድ ዓመት በፊት አንድን ነገር ለማድረግ መጀመር ብቻ ሳይሆን ነገር ግን ልታደርጉት መሻት በውስጣችሁ ነበር። 11 አሁን ያንኑ ማድረጋችሁን ፈጽሙ። እንግዲህ ልክ በዚያን ጊዜ ልታደርጉት ጉጉትና ጠንካራ ፍላጎት እንደ ነበራችሁ፣ወደ ፍጻሜ ልታመጡት ደግሞ ትችላላችሁ። 12 ይህን ስራ ለመስራት ጉጉት ካለ፣ አንድ ሰው በሌለው ሳይሆን ባለው ነገር ላይ ተመስርቶ ሲሰራ መልካምና ተቀባይነት ያለው ነው። 13 ይህ ተግባር ሚዛናዊነት እንዲኖር ነው እንጂ ሌሎች እንዲቀልላቸው እናንተም ሸክም እንዲበዛላችሁ አይደለም። 14 አሁን ያለው የእናንተ መትረፍ ለእነርሱ የሚያስፈልጋቸውን ይሞላል። ይህም ደግሞ ሚዛናዊነት ይኖር ዘንድ የእነርሱ መትረፍረፍ የእናንተ ፍላጎት ደግሞ እንዲሞላ ነው። 15 እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ ፦ «ብዙ ያለው ምንም አልተረፈውም ፣ጥቂት ያለው ግን ምንም አልጎደለውም።» 16 ነገር ግን እኔ ለእናንተ ያለኝን ቅን ሃሳብ በቲቶ ልብ ያኖረው እግዚአብሔር ይመስገን። 17 እርሱ ልመናችንን መቀበል ብቻ ሳይሆን ፣ ትጋትን በማሳየት በራሱ ፈቃድ ወደ እናንተ መጥቷልና። 18 ከእርሱ ጋርም ወንጌልን በማወጅ ስራው በአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ የተመሰገነውን ወንድም ልከናል። 19 ይህ ብቻ አይደለም ነገር ግን ለራሱ ለጌታ ክብርና እኛ ለመረዳት ያለንን ጉጉት ለመግለጥ ይህን የጸጋ ስራ እንዲያከናውን አብሮን ይጓዝ ዘንድ አብያተ ክርስቲያናት ደግሞ መርጠውት ነበር። 20 ስለምንሰበስበው ስለዚህ የልግስና ስጦታ ማንም ትችት ለማቅረብ ምክንያት እንዳያገኝ እንጠነቀቃለን። 21 በጌታ ፊት ብቻ ሳይሆን ነገር ግን በሰዎች ፊት ደግሞ የከበረውን ነገር ለማድረግ እንተጋለን። 22 ብዙ ጊዜ ፈትነን በበርካታ ተግባራት ተነሳሽነት ያለው ሆኖ ያገኘውን ፣አሁን ግን በእናንተ ላይ ትልቅ መታመን ምክንያት የበለጠ ትጋት የሚያሳየው ሌላ ወንድም ከእነርሱ ጋር እንልካለን። 23 ቲቶን በሚመለከት ግን ስለ እናንተ ከእኔ ጋር የሚሰራ አጋሬ ነው። ወንድሞቻችንን በሚመለከት አብያተ ክርስቲያናት የላኳቸው የክርስቶስ ክብር ናቸው። 24 ስለዚህ ፍቅራችንን ፣ በሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ዘንድም ስለ እናንተ ለምን እንደ ተመካን ግለጡላቸው።
1 ለቅዱሳን ስለ ሚሆነው አግልግሎት ለእናንተ ልጽፍላችሁ አያስፈልገኝም ። 2 ለመቄዶንያ ሰዎች ስለተመካሁት በውስጣችሁ ስላለው መሻት አውቃለው። በአካዶያ የሚነግሩት ካለፈው ዓመት ጀምሮ መዘጋጀትቱን ነገርኋቸው። የእናንተ ቅንዓት ብዙዎቻቸውን ለስራ አነሳስቷል። 3 እንግዲህ የተዘጋጃችሁ ትሆናላችሁ እንዳልኩት የተዘጋጃችሁ ትሆኑ ዘንድ፣ ስለ እናንተ መመካታችን ከንቱ እንዳይሆን ወድሞችን ልኬአለው። 4 ምናልባት አንዳቸው ከ እኔ ጋር ከሜቄዶንያ በመጡ፣ሳትዘጋጁ ቢያገኟችሁ ሁላችንም ሀፍረት ይሰማናል ነገር ግን በእናንተ ስለምተማመን ፣ ስለ እናንተ የምለው ምንም የለኝም። 5 ስለዚህ ወደ እናንተ እንዲመጡና እናንተ ተስፋ ለሰጣችሁት ስጦታ በቅድሚያ ዝግጅት እንዲያደርጉ ወንድሞችን መለመን አስፈላጊ እንደሆነ አሰብሁ። ይህም እንድትሰጡ ስለ ተገደዳችሁ ሳይሆን በነጻ እንደተሰጠ ስጦታ ዝግጁ ይሆን ዘንድ ነው። 6 ፍሬ ነገሩ ይህ ነው ፦ በጥቂት የሚዘራ በጥቂቱ ያጭዳል ፣ አትረፍርፎ የሚዘራ አትረፍርፎ ያጭዳል። 7 እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ ስትሰጡ በሐዘን ወይም በግድ አይደለም። 8 እግኢአብሔር ሁልጎዜ በነገር ሁሉ የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ አግኝቷችሁ በብጎ ስራ ሁሉ ትበዙ ዘንድ ጸጋን ሁሉ ሊያበዛላችሁ ይችላል። 9 እንዲህ ተብሎ እንደተፃፈ «ሀብቱን በተነ ፣ለድሆችም አከፋፈለ።» 10 ለዘሪን ዘርን ለምግብ እንጀራን የሚሰጥ ፣የሚዘራ ዘርን ደግሞ ይሰጣል ያበዛውማል፣ ምርት ይጨምራል። 11 ለጋሶች እንድትሆኑ በሁሉም ረገድ መበልጸግ ትላላችሁ፣ ይህም በእኛ በኩል ለእግኢአብሔር ምስጋና ምክንያት ይሆናል። 12 ይህ የመስጠት አገልግሎት ለቅዱሳን ይሚያስፈልጋቸውን ሁሉ የሚሰጥ ብቻ አይደለምና፣ ነገር ግን ለእግዚአብሔር የሚቀርብ ብዙ ምስጋና ደግሞ ይበዛል። 13 በዚህ አገልግሎት ተፈትናችሁ አልፋችኋል ደግሞም በክርስቶስ ወንጌል ምስክርነት በመታዘዛችሁ ፣እንዲሁም ለእነርሱና ለሁሉ ባደረጋችሁት የስጦታችሁ ልግስና እግዚአብሔርን ታከብራላችሁ። 14 በእናንተ ላይ ካለው እጅግ ታላቅ የእግዚአብሔር ጸጋ የተነሳ ስለ እናንተ ሲጸልዩ ይናፍቁአችኋል። 15 ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን!
1 እኔ ራሴ ጳውሎስ ፣ በፊታችሁ ትሁት የሆንሁ በክርስቶስ ገርነትና የዋህነት እለምናችኃለሁ። 2 እንደ ስጋ ፈቃድ እንደምንኖር የሚያስቡትን በምቃወምበት ጊዜ ፣ ከእናንተ ጋር ሳለሁ መሆን እንደሚገባኝ በራስ በመተማመን የምደፍር መሆን የለብኝም ብዬ እለምናችኃለው ። 3 ምንም እንኳ በስጋ የምንመላለስ ብንሆን፣ እንደ ስጋ አንዋጋም። 4 የምንዋጋባቸው የጦር መሳሪያዎች ሥጋዊ አይደሉምና ይልቁንም ምሽጎችን ለመስበር መለኮታዊ ኃይል አለቸው ፥ አሳሳች የሆኑ ክርክሮችንም ያፈርሳሉ። 5 ደግሞም በእግዚአብሔር ዕውቀት ላይ የሚነሳውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን ፥ እንዲሁም ለክርስቶስ ለመታዘዝ ሀሳብን ሁሉ እንማርካለን። 6 መታዘዛችሁም በተፈጸመ ጊዜ ፣ ይለመታዘዝን ተግባር ሁሉ ለመቅጣት እንዘጋጃለን። 7 በግልጽ ከፊታችን ያለውን ተመልከቱ ፥ ማንም የክርስቶስ እንደሆነ ቢያምን ልክ እርሱ የክርስቶስ እንደሆነ እኛ ደግሞ እንዲሁ መሆናችንን ራሱ ያሰበው። 8 ሊያንጻችሁ እንጂ ሊያጠፋችሁ የይደለ ጌት ኣስለ ሰለ ሰጠው ስልጣናችን ጥቂት አብዝቼ ብመካም እንኳ፥ አላፍርም። 9 በመልዕክቶቼም ላስደነግጣችሁ አልፈልግም። 10 አንዳንድ ሰዎች ፥«መልእቶቹ ጠንከር ያሉና ኃይለኛ ናቸው፥ ነገር ግን በአካል ደካማ ነው፥ ንግግሩም ሊሰማ የሚገባ አይደለም»ይሉናል። 11 እንደነዚህ ያሉ ሰዎችን ስንርቅ በመልዕክት የምንለው፥እዚያ ስንሆን ከምናደርገው ጋር አንድ መሆኑን ይረዱ። 12 ራሳቸውን ከሚያመሰግኑ ጋር ራሳችንን እስከ ማስተያየት ወይም እስከ ማወዳደር ድረስ አንሔድም። ነገር ግን እነርሱ ራሳቸውን ከሌላ ጋር ሲመዝኑና ራሳቸውን እርስ በእርስ ሲያወዳድሩ ፥ ማስተዋል ተላቸውም። 13 ይሁን እንጂ እኛ ከልክ በላይ አንመካም፥ ነገር ግን ወደ እናንተ እንኳ እስክንደርስ እግዚአብሔር በወሰነልን ስራ እንሆናለን። 14 ወድ እናንተ ስንደርስ ከመጠን አላለፍንምንና በክርስቶስ ወንጌል ወደእናንተ ለመድረስ የመጀመሪያዎች ነበርን። 15 በሌሎች ድካም ከልክ ያለፈ አንመካም ፥ ነገር ግን ከእናንተ አካባቢ አልፎ እንኳ 16 ወንጌልን እንሰብክ ዘንድ እምነታችሁ ሲያድግ ስራችን እጅግ እንደሚስፋፋ ተስፋ እናደርጋለን ። በሌላ ስፍራ እየተሰራ ስላለው ሥራ አንመካም። 17 «ነገር ግን የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ።» 18 ጌታ የሚያመሰግነው እንጂ፣ ራሱን የሚያመሰግን ተፈትኖ የሚወጣ አይደለምና።
1 በጥቂት ሞኝነቴ ልትታገሱኝ ብትችሉ እመኝ ነበር፣ እናንተ ግን በእርግጥ ታግሳችሁኛል! 2 እኔ ስለ እናንተ እቀናለሁና እንደ አንዲት ንጽሕት ድንግል ለክርስቶስ ላቀችርባችሁ ለአንድ ባል ስላጨዋችሁ በእግዚአብሔር ቅንአት እቀናላችኃለው ። 3 ነገር ግን እባብ በተንኮሉ ሔዋንን እንዳታለላት ፣ ሐሳባችሁ ለክርስቶስ ካልችሁ ቅንና ንጹህ ታማኝነት መረን እንዳትወጡ ብዬ እፈራለው። 4 አንድሰው መጥቶ እኛ ከሰበክበው የተለየ ሌላ ኢየሱስ ቢያውጅላችሁ፣ ወይም ቀድሞ ከተቀበላችሁት የተለየ መንፈስ ብትቀበሉ ወይም እናንተ ከተቀበላችሁት የተለየ ወንጌል ቢደርሳችሁ ደህና ትታገሱታላችሁና። 5 ከነዚያ «ገናና ሐዋርያት» በጥቂቱ እንኳ የማንስ አይደለሁም ብዬ አስባለውና። 6 ነገር ግን በአነጋገር ያልሰለጠንሁ አይደለሁም። በሁሉም መንገድና በሁሉም ነገር ይህን አሳውቀናችኋል። 7 የእግዚአብሔርን ወንጌል በነፃ ስለሰበኩለችሁ፥ እናንተ ከፍ እንድትሉ እኔ ራሴን በማዋረዴ ኋጢያት ሰራሁን? 8 እናንተን ማገልገል እችል ዘንድ ከእነርሱ እርዳታ በመቀበል ሌሎችን አብያተ ክርስቲያናት«ጎዳሁ»። 9 አብሬአችሁ በሆንኩና በተቸገርሁ ጊዜም በማንም ላይ ሸክም አልሆንሁም። ከመቄዶንያ የመጡት ወንድሞች የሚያስፈልገኝን ሰጥተዋልና። በሁሉም ረገድ ለእናንተ ሸክም ከመሆን ተጠንቅቄአለሁ፣ይህን ማድረጌንም እቀጥላለው ። 10 የክርስቶስ እውነት በእኔ ውስጥ ያለ እንደ መሆኑ፣ ይህ የእኔ ትምህርት? 11 ለምንስ እንዲህ ይሆናል? ለማልወደችሁ ነውን? እንደምወዳችሁ እግዚአብሔር ያውቃል። እንደነዚህ ያሉ ሰዎችን ራሳቸውን እንደ ክርስቶስ ሐዋርያት በማስመሰል ሐሰተኞች ሐዋርያት፣ አታላይ ሰራተኞች ናቸውና ። 12 እኔን የሚነቅፉትንና እኛ የምናደርገውን እነርሱም እያደረጉ እንደ ሆነ እየተናገሩ የሚመኩበትን ምክንያት ለማሳጣት አሁን የሚደረገውን ወደ ፊትም አደርጋለሁ። 13 እንደ እነዚህ ያሉ ሰዎች ሐሰተኛ ሐዋርያትና አታላይ ሸራተኞች ናቸው። 14 ይህም የሚያስደንቅ አይደለም፣ ሰይጣን እንኳ ራሱን የብርሓን መልአክ በማስመሰሉ ርሱን ይለውጣልና። 15 የእርሱ አግልጋዮች ደግሞ የጽድቅ አገልጋዮች በማስመሰል ራሳቸውን ቢለውጡ እጅግ የሚያስደንቅ አይደለም። ዕጣ ፈንታቸውም እንደ ሥራቸው ይሆናል። 16 ደግሜ እላለሁ፦ እኔ ሞኝ እንደሆንሁ ማንም አያስብ ። ሞኝ እንደሆንሁ ብታስቡ ግን በጥቂቱ እመካ ዘንድ እንደ ሞኝ ተቀበሉኝ። 17 እንደዚህ ታምኜ በመመካት የምናገረው፣ ጌታ የፈቀደው አይደለም፣ እኔ ግን እንደ ሞኝ እናገራለው። 18 ብዙ ሰዎች በሥጋ ሰለሚመኩ፣ እኔም ደግሞ እመካለው። 19 እናንተ ብልሆች ሆናችሁ ሞኞችን በደስታ ትታገሣላችሁና! 20 ማንም ባሪያዎች ቢያደርጋችሁ፣ ማንም በመካከላችሁ መለያየትን ቢፈጥር፣ ማንም መጠቀሚያ ቢያደርጋችሁ፣ ማንም ቢቀማችሁ ፣ወይም ፊታችሁን በጥፊ ቢመታችሁ ትታገሱታላችሁና. 21 ይህንን ስናደርግ በጣም ደካሞች እንደ ነበርን እያፈርሁ እናገራለ። ሆኖም ማንም በሚመካበት ጊዜ ሁሉ እንደ ሞኝ እላለው፣ እኔ ደግሞ እመካለሁ። 22 እነርሱ ዕብራውያን ናቸውን? እኔ ደግሞ ነኝ እስራኤላውያን ናቸውን እኔ ደግሞ ነኝ። የአብርሃም ዘር ናቸውን? እኔ ደግሞ ነኝ። 23 የክርስቶስ አግልጋዮች ናቸውን? እኔ ደግሞ ነኝ (እንደ እብድ እናገራለው) እኔ እበልጣለሁ፣ በከባድ ሥራ አብዝቼ በመታሰር አብዝቼ፣ በመደብደብ ከልክ በላይ፣ ብዙ የሞት አደጋዎችን በመጋፈጥ ብዙ ጊዜ ሆንሁ። 24 አይሁድ «አንድ ሲጎድል አርባ ጅራፍ»አምስት ግዜ ገረፉኝ። 25 ሦስት ጊዜ በበትር ተመታሁ። አንድ ግዜ በድንጋይ ተወገርሁ። ሦስት ጊዜ የተሳፈርኩበት መርከብ ተሰበረ። አንድ ሌሊትና አንድ ቀን በባህር ላይ አሳለፍሁሁሁ፣ 26 በተደጋጋሚ በመንገድ ተጓዝሁ። በወንዞች አደጋ፣ በወንበዴዎች አደጋ በወገኖቼ በኩል አደጋ፣ በአሕዛብ በኩል አደጋ፣ በከተማ አደጋ በምድረ በዳ አደጋ፣ በባሕር አደጋ፣ በሐሰተኞች በኩል አደጋ ነበረብኝ። 27 በከባድ ስራና በችግር፣ እንቅልፍ ባጣሁባቸው ብዙ ሌሊቶች፣ በረሃብና በጥም ፣ እንዲሁም የሚበላ በማጣት፣በብርድባ በራቁትነት ነበርሁ። 28 ከሌላውም ሁሉ በተለይ ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ ለአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ያለኝ ጭንቀት ነው። 29 ደካማ ምን ነው እኔስ አልደክምምን? ኃጢአት እንዲሠራ ሌላውን ያሰናከለ ማን ነው፣ እኔስ በውስጤ አልናደድምን?። 30 መመካት ካለብኝ፣ ድካሜን ስለሚያሳየው ነገር እመካለው። 31 እንደማልዋሽ፣ ለዘላለም የተመሰገነው የጌታ ኢየሱስ አምላክና አባት ያውቃል። 32 በደማስቆ ከንጉስ አርስጦስዮስ በታች የሆነ ገዢ እኔን ይዞ ለማሰር ከተማዋን እየጠበቀ ነበር፣ 33 ነገር ግን በቅጥሩ ባለ መስኮት በቅርጫት አወረዱኝ፣ ከእጆቹም አመለጥሁ።
1 መመካት አለብኝ፤ ነገር ግን በመመካት ጥቅም አይገኝም። ከጌታ ወዳሉት ራዕዮችና መገለጦች ግን እሄዳለው። 2 በሥጋ ይሁን ወይም ከሥጋ ውጭ አላውቅም፤ እግዚአብሔር ግን ያውቃል። ከዐሥራ አራት ዓመታት በፊት በክርስቶስ የሆነ አንድ ሰው ወደ ሦስተኛ ሰማይ ተነጠቀ። እንደዚህ ያለውን ሰው ዐውቃለው። 3 በሥጋ ይሁን ወይም ከሥጋ ውጭ እኔ አላውቅም፣ እግዚአብሔ ግን ያውቃል፣ 4 ይህ ሰው ወደ ገነት ተነጠቀ፤ ማንኛውም ሰው የማይናገራቸው እጅግ የተቀደሰ ነገሮችን ሰማ። 5 እንደዚህ ስላለው ሰው እመካለው ስለራሴ ግን ከድካሜ በቀር አልመካም። 6 ልመካ ከፈለግሁ፣ ሞኝ አይደለሁም፣ እውነትን እናገራለሁና፤ ነገር ግን ማንም በእኔ ከታየው ወይም ከእኔ ከተሰማው ፣ 7 ወይም በመገልጦቹ ልዩ ባሕርይ ምክንያት የምበልጥ አድርጎ እንዳያስብ አልመካም።ስለዚህ እንዳልታበይ፣ እጅግ እንዳልኩራራ የሥጋ መውጊያ፣የሚነዘንዘኝ የሰይጣን መልዕክተኛ ተሰጠኝ። 8 መውጊያውን ከእኔ እንዲያነሣው ሦስት ጊዜ ጌታን ለመንሁ። 9 እርሱም፣ «ጸጋዬ ይበቃሃል ኃይል በድካም ይፈጸማልና» አለኝ። ስለሆነም የክርስቶስ ኃይል ያርፍብኝ ዘንድ አብዝቼ ስለ ድካሜ እመካለው። 10 ስለዚህ ስለ ክርስቶስ በድካም፣ በስድብ፣ በችግር፣ በስደት ፣ በጭንቀትም እርካታ ይሰማኛል በምደክምበት ጊዜ ሁሉ ብርቱ ነኝና። 11 ሞኝ ሆኜአለሁ! እንዲህ እንድሆን ያስገደዳችሁኝ እናንተ ናችሁ፣እናንተ እኔን ልታመሰግኑኝ ይገባችሁ ነበር፥ምክንያቱም እኔ ምንም ባልሆን እንኳ ከ«ገናና ሐዋርያት» የማንስ አልነበርሁም። 12 የአንድ ሐዋርያ እውነተኛ ምልክቶች በሁሉ ትዕግሥት፦ በምልክቶችና በድንቆች በብርቱ ተግባራትም በእናንተ መካከል ተደረጉ። 13 እኔ ሸክም ካልሆንሁባችሁ በቀር ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት የምታንሱት እንዴት ነበር? ይህን ስሕትቴን ይቅር በሉኝ! 14 አስተውሉ! ለሦስተኛ ጊዜ ወደ እናንተ ለመምጣት ተዘጋጅቻለው፤ ሸክም አልሆንባችሁም፤ እናንተን እንጂ፣ የእናንተ የሆነውን አልፈልግም። ወላጆች ለልጆች እንጂ ልጆች ለወላጆች ገንዘብ አያስቀምጡምና። 15 እኔ እጅግ በጣምታልቅ በሆነ ደስታ ስለ ነፍሳችሁ እከፍላለው። እናንተን የበለጠ ብወዳችሁ፣ እኔ ከዚህ ያነሰ መወደድ አለብኝን? 16 ልክ እንደዚህ፣ እኔ አልከበድሁባችሁም፤ነገር ግን በጣም በተንኮልና በጥበብ ያታለልኃችሁ መሰላችሁ። 17 ወደ እናንተ በላክሁት በማንም ተጠቀምሁባችሁን? 18 ወደ እናንተ እንዲመጣ ቲቶን የግድ አልኩት ፤ ከእርሱ ጋርም ሌላውን ወንድም ላክሁት። ቲቶስ ተጠቀመባችሁን? በአንድ መንገድ አልተጓዝንምን? በአንድ ፈለግስ አልተራመድንምን? 19 በዚህ ጊዜ ሁሉ ለእናንተ ራሳችንን የምንከላከል ይመስላችኃልን? በእግዚአብሔር ፊት ስለእናንተ ድፍረት በክርስቶስ ብዙ ነገር እየተናገርን ነበር። 20 ስመጣ እንደምፈልገው ሆናችሁ አላገኛችሁምብዬ እፈራለው። እናንተም እንደምትፈልጉት ሆኜ አታግኙኝም ብዬ እፈራለው ምናልባት ክርክር፣ ቅንዓት፣ የቁጣ መግንፈል፣ራስ ወዳድነት ያለበት ምⶉት፣ ሐሜት፣ ኩራትና ሁከት ይሆናሉ። 21 ተመልሼ ስመጣ፣ አምላኬ በፊታችሁ ዝቅ እንዳያደርገኝ ብዬ እፈራለው ፣ከዚህ በፊትም ኃጢያ ስለሠሩት፣ እንዲሁም ስለ ፈጸሙት ርኩሰትና ዝሙት መዳራትም ስለ ብዙዎቻቸው አዝናለው ብዬ እፈራለው።
1 ወደ እናንተ ስመጣ ይህ ሦስተኛዬ ነው። «ክስ ሁሉ በሁለት ወይም በሦስት ምስክሮች መጽናት አለበት።» 2 ሁለተኛ ስመጣ በፊት ኃጢያት ለሰሩትና ለሌሎች ሁሉ ተናግሬአለው፥ አሁንም ደግሞ እላለው ተመልሼ ስመጣ እንዲሁ አላልፋቸውም። 3 ክርስቶስ በእኔ በኩል እየተናገረ ስለ መሆኑ ማስረጃ ስለምትሹ ይህን እነግራችሏለው። ክርስቶስ ስለ እናንተ አይደክምም፥ ይልቁንም እርሱ በእናንተ ኃይለኛ ነው። 4 እርሱ በድካም ተሰቅሏልና፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር ኃይል ሕያው ነው። እኛ ደግሞ በእርሱ ደካሞች ነንና፤ ነገር ግን በመካከላችሁ ብለው የእግዚአብሔር ኀይል ሕያዋን ነን። 5 በእምነት መሆናችሁን ለማየት ራሳችሁን መርምሩ። ራሳችሁን ፈትኑ። ኢየሱስ ክርስቶስ በእናንተ እንደሚኖር አትገነዘቡምን? ተፈትናችሁ ካላለፋችሁ በቀር፣ እርሱ በእናንተ ይኖራል። 6 እኛ ግን ተፈትነን ያለፍን መሆናችንን እንደምታውቁ እተማመናለው። 7 እንግዲህ እናንተ ክፉ እንዳታደርጉ ወደ እግዚአብሔር እንጸልያለን፥ ይህንም የምናደርገው ፈተናውን ያለፍን መሰለን ለመታየት አይደለም፥ ነገር ግን ፈተናውን ያላለፍን ብንመስልም እንኳ፣ እናንተ ትክክል የሆነውን ታደርጉ ዘንድ እጸልያለው። 8 ስለ እውነት እንጂ የእውነት ተቃራኒ የሆነ ነገር መሥራት አንችልምና። 9 እኛ ደካሞች ሆነን እናንተ ብርቱዎች ስትሆኑ ደስ ይለናልና። እናንተ ፍጹማን እንድትሆኑ እንኛ ደግሞ እንጸልያለን። 10 ከእናንተ ርቄ እያለው እነዚህን ነገሮች ጻፍሁላችሁ፤ ከእናንተ ጋር ሳለው እናንተ ለማነጽ እንጂ ለማፍረስ ያይደለ ጌታ የሰጠኝ ሥልጣንን በመጠቀም እንዳላመናጭቃችሁ ንችው። 11 በመጨረሻ፣ ወንድሞችና እኅቶች፣ ደስ ይበላችሁ! ለተሐድሶ ሥሩ፤ተበረታቱ፤እርስ በርሳችሁ ተስማሙ፤በሰላም ኑሩ፤ የፍቅርና የሰላም አምልክም ከእናንተ ጋር ይሆናል። 12 በተቀደሰ አሳሳም ሰላም ተባባሉ። 13 ቅዱሳን ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። 14 የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፣ፍቅር፣የመንፈስ ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን።
1 በሰው በኩል ወይም ከሰው ሳይሆን በክርስቶስ ኢየሱስ ደግሞም እርሱን ከሞት ባስነሳው በእግዚአብሔር አብ ሐዋርያ የሆንኩት ጳውሎስ 2 አብረውኝ ካሉ ወንድሞች ጋር በገላትያ ለምትገኙ አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ 3 ከአባታችን ከእግዚአብሔር አብ ከጌታም ከኢየሱስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ 4 ይሁን፣እርሱ እንደ አምላካችን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ከአሁኑ ክፉ ዘመን ያድነን ዘንድ እራሱን ስለ ኃጢአታችን ሰጥቶአልና 5 ለእርሱ ከዘላለም እስከዘላለም ክብር ይሁን። አሜን! 6 ወደሌላ ወንጌል በዚህ ፍጥነት በመዞራችሁ እጅግ ተገርሜአለሁ። በክርስቶስ ጸጋ ከተጠራችሁ ከእርሱ ፊታችሁን ማዞራችሁ አስገርሞኛል። 7 ሌላ ወንጌል የለም፣ ነገር ግን የሚያውኩዋችሁና የክርስቶስን ወንጌል ሊያጣምሙ የሚፈልጉ አንዳንድ ሰዎች አሉ። 8 ነገር ግን እኛም ሆንን የሰማይ መልአክ አስቀድመን ከሰበክንላችሁ ሌላ ወንጌል ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን። 9 አስቀድመን እንዳልን እንደገና እላለሁ «ማንም ከተቀበላችሁት ወንጌል የተለየ ወንጌል ቢሰብክላችሁ የተረገም ይሁን» 10 ለመሆኑ እኔ የምጥረው ከሰው ወይስ ከእግዚአብሔር ይሁንታን ለማግኘት ነው? ጥረቴ ሰውን ለማስደሰት ነው? እስከአሁን ድረስ ሰውን ለማስደሰት እየጣርኩ ከሆነ እውነት እኔ የክርስቶስ አገልጋይ አይደለሁም። 11 ወንድሞች ሆይ የሰብኩላችሁ ወንጌል ከሰው እንዳልሆን እንድታውቁ እፈልጋለሁ። 12 ከጌታ ከኢየሱስ ከተሰጠኝ መገለጥ እንጂ ከሰው አልተቀበልኩትም ከሰውም አልተማርኩትም። 13 የይሁዲ እምነት ተከታይ በነበርኩበት በቀድሞው ህይወቴ ወቅት እንዴት ቤተክርስቲያንን በአመፅ አሳድድና አጠፋ እንደነበረ ስለእኔ ሰምታችኋል። 14 በይሁዲነት ከአብዛኛዎቹ አብረውኝ ከነበሩ አይሁዶች እየላቅሁ ነበር። ለአባቶቼም ወግ ከመጠን ያለፈ ቀናኢ ነበርኩ። 15 ነገር ግን እግዚአብሔር ገና በማህጸን ሳለሁ ሊመርጥኝ ወደደ፣ 16 በአረማውያን መካከል አውጀው ዘንድ ልጁን በእኔ ለመግለፅ በጸጋው ጠራኝ። በጠራኝ ጊዜ ወዲያውኑ ከስጋና ከደም ጋር አልተማከርኩም 17 ፣ከእኔ አስቀድመው ሃዋሪያት የሆኑት ወደሚገኙበት ወደ ኢየሩሳሌምም አልሄድኩም። ነገር ግን ወደ አረቢያ በኋላም ደግሞ ወደ መቄዶኒያ ተመለስኩ። 18 ከዚያም ከሶስት አመት በኋላ ኬፋን ለመጠየቅ ወደኢየሩሳሌም ሄጄ ከእርሱ ጋር አስራአምስት ቀናት ቆየሁ። 19 ነገር ግን ከጌታ ወንድም ከያዕቆብ በስተቀር ሌሎች ሃዋሪያትን አላገኘሁም። 20 በምፅፍላችሁ በእነዚህ ነገሮች በእግዚአብሔር ፊት እንዳልዋሸሁ እወቁ። 21 ቀጥሎም ወደ ሶሪያና ኪልቂያ አውራጃዎች ሄድኩኝ። 22 እስከዚያን ጊዜ ድረስ በይሁዳ ላሉት አብያተክርስቲያናት በአካል አልታወቅም ነበር፣ 23 ነገር ግን «ያ ቀድሞ ያሳድደን የነበረው ሰው አሁን ሊያጠፋው ሲጥር የነበረውን እምነት እየሰበከ ነው» የሚል ወሬ ብቻ ይሰሙ ነበር፣ 24 ስለ እኔም እግዚአብሔርንም ያከብሩ ነበር።
ሐዋርያው ጳውሎስ ይህንን ደብዳቤ በገላትያ አካባቢ ላሉት አብያተ ክርስቲያናት ጻፈ ፡፡
በሌላ መንገድ ካልተገለጸ በቀር በዚህ ደብዳቤ ውስጥ “እርስዎ” እና “የእርስዎ” የሚሉት ሁሉም ምሳሌዎች የገላትያ እና ብዙ ናቸው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ዮዎ)
"ኢየሱስ ክርስቶስን ያስነሳው"
እዚህ ላይ ይህ ማለት የሞተ ሰው እንደገና ሕያው ይሆናል ማለት ነው ፡፡
በክርስቶስ የሚያምኑ ሁሉ የአንድ ሰማያዊ ቤተሰብ አባላት ስለሆኑ ይህ ማለት ወንዶችም ሆኑ ሴቶችን ጨምሮ እዚህ ያሉ ክርስቲያኖችን ማለት ነው ፡፡ አት: “ወንድሞች እና እህቶች” (የበለስ_ቁጥር መግለጫዎችን ይመልከቱ)
ኃጢአቶች ቅጣትን ይወክላሉ ፡፡ አት: - “በኃጢአታችን ምክንያት የተገባንን ቅጣትን ለመውሰድ” (ይመልከቱ።
እዚህ “ይህ… ዘመን” በስራ ላይ ያሉ ሀይሎችን ይወክላል። በዚህ ወቅት “በዓለም ላይ ከሚሠራው ከክፉ ኃይሎች ነፃ ያወጣናል” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ይህ የሚያመለክተው “እግዚአብሔር አባታችንን” ነው ፡፡ እርሱ አምላካችን እና አባታችን ነው ፡፡
ጳውሎስ ይህንን ደብዳቤ የጻፈበትን ምክንያት ሲገልፅ ወንጌልን መረዳታቸውን እንዲቀጥሉ አሳስቧቸዋል ፡፡
"ይገርመኛል" ወይንም "ደንግጫለሁ"። ይህንን እያደረጉ ስለሆነ ጳውሎስ አዝኗል።
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “በፍጥነት በእርሱ ላይ መታመን አቆምክዋል” ወይም 2) “ለእሱ ታማኝ መሆንን በፍጥነት አቆሙ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
"እግዚአብሔር፥ የጠራችሁ"
እዚህ ማለት ይህ ማለት እግዚአብሔር ሰዎችን የእሱ ልጆች እንዲሆኑ ፣ እንዲያገለግሉት እና በኢየሱስ በኩል የመዳንን መልእክት እንዲሰብኩ ሾሞላቸዋል ወይም መረጣቸው ማለት ነው ፡፡
“በክርስቶስ ጸጋ ምክንያት” ወይም “በክርስቶስ ደግነት መስዋትነት”
"የተለየ ወንጌል እያመናችሁ ነው"
ሰዎች
ይህ ያልተፈጠረ እና የማይከሰት አንድ ነገርን እየገለጸ ነው። አት: - “ያውጃል” ወይም “ማወጅ አለበት” (ይመልከቱ: የበለስ_አፖፖ)
“ከወንጌል የተለየ” ወይም “ከመልእክቱ የተለየ”
እግዚአብሔር ያንን ሰው ለዘላለም ይቀጣል ፡፡ ቋንቋዎ በሌላ ሰው ላይ የመርገም የተለመደ መንገድ ካለው ያንን መጠቀም አለብዎት።
እነዚህ አጸያፊ ጥያቄዎች “አይሆንም” የሚል መልስ ይጠብቃሉ ፡፡ እኔ: - “የሰዎችን ሞገስ አልፈልግም ፣ ይልቁንም የእግዚአብሔርን ሞገስ እጠይቃለሁ ፡፡ ሰዎችን ለማስደሰት አልፈልግም ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ሁለቱም “ከሆነ” ሐረግ እና “ታዲያ” ሐረግ ከእውነት ተቃራኒ ናቸው ፡፡ እኔ አሁንም ሰዎችን ለማስደሰት አልሞከርኩም ፣ እኔ የክርስቶስ አገልጋይ ነኝ ወይም ደግሞ “አሁንም ሰዎችን ለማስደሰት እየሞከርኩ ከሆነ የክርስቶስ አገልጋይ ባልሆንኩ”
ጳውሎስ ወንጌልን ከሌሎች እንዳልተማረ ገል explainsል ፡፡ እሱ የተማረው ከኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
በ1፡1 ላይ እንዳለው ይተርጉሙት
ይህንን ሐረግ በመጠቀም ጳውሎስ ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ሰው አይደለም ለማለት እየሞከረ አልነበረም ፡፡ ክርስቶስ ሰውም ሆነ እግዚአብሔር ስለሆነ ፣ እሱ ኃጢያተኛ ሰው አይደለም ፡፡ ጳውሎስ ወንጌሉ ከየት እንደመጣ እየጻፈ ነው ፡፡ እርሱ የመጣነው ከሌሎች ኃጢአተኛ የሰው ልጆች ነው ፣ ግን የመጣው ከኢየሱስ ክርስቶስ ነው ፡፡
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ወንጌልን ገለጠኝ” ወይም 2) “ኢየሱስ ክርስቶስ ማን እንደ ሆነ አሳየኝ ፡፡
"በአንድ ጊዜ ባህሪ" ወይም "የቀደመው ህይወት" ወይም "የቀድሞው ኑሮ"
ይህ ዘይቤ ጳውሎስ ፍጹም አይሁዳውያን ለመሆን ባላቸው ግብ ውስጥ በዕድሜው ከሌሎች አይሁዳውያን እንደሚቀድም ያሳያል ፡፡
እኔ እንደ እኔ ተመሳሳይ ዕድሜ ያሉ የአይሁድ ሰዎች ነበሩ ”
ቀደምት አባቶች
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “እግዚአብሔር ቸር ነው ፣ እንዳገለግለው ጠራኝ” ወይም 2) “እርሱ በጸጋው በኩል ጠራኝ” ፡፡
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “ልጁን እንዳውቅ ይፈቅድልኛል” ወይም 2) “ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን በእኔ በኩል ዓለምን ለማሳየት” ነው ፡፡
ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
“የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አውጅ” ወይም “ስለ እግዚአብሔር ልጅ የሚገልጸውን ምሥራች ስበኩ”
ይህ ከሌሎች ሰዎች ጋር መነጋገር ማለት አገላለፅ ነው ፡፡ አት: - “መልዕክቱን ለመረዳት ሰዎች እንዲረዱኝ ሰዎችን ጠይቅ” (የበለስ_ ቪዲዮም ተመልከት)
ወደ ኢየሩሳሌም ሂጂ ” ኢየሩሳሌም ለመድረስ ብዙ ኮረብታዎችን መውጣት አስፈላጊ ስለነበረች ከፍታ ኮረብታዎች አካባቢ ነች ፣ እናም ወደ ኢየሩሳሌም መጓዙ “ወደ ኢየሩሳሌም እንደሚወጣ” መግለጹ የተለመደ ነበር ፡፡
ይህ ድርብ አሉታዊ አፅን emphasiት የሰጠው ጳውሎስ ያየው ሐዋርያው ያዕቆብ ብቻ መሆኑን ነው ፡፡ አት: - “እኔ ያየሁት ሌላ ሐዋርያ ያዕቆብ ብቻ ነበር” (የበለስ_ቁጥር አተያይ)
ጳውሎስ የገላትያ ሰዎች ጳውሎስ ሙሉ በሙሉ ከባድ መሆኑን እና እግዚአብሔር የሚናገረውን እንደሚሰማ እና እውነቱን ካልተናገር እንደሚፈርድበት እንዲገነዘቡ ይፈልጋል።
ጳውሎስ እውነቱን እየተናገረ መሆኑን ለማጉላት ድምጾችን ይጠቀማል ፡፡ አት: - “በጻፍኳቸው መልእክቶች ውስጥ አልዋሽም” ወይም “በጻፍኩላችሁ ነገር ውስጥ እውነቱን እነግራችኋለሁ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
“የአለም ክፍል”
ግን እነሱ ሌሎች ስለ እኔ ሲናገሩ የሰሙትን ብቻ ያውቁ ነበር ”
በይሁዳ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ በክርስቶስ ውስጥ ካሉ ሰዎች ውስጥ ማንም አላገኘኝም ”
1 ከአስራ አራት ዓመት በኋላ ቲቶን ይዤ ከበርናባስ ጋር እንደገና ወደ ኢየሩሳሌም ሄድኩ። 2 የሄድኩበትም ምክንያት መሄድ እንዳለብኝ እግዚአብሔር ስላመለከተኝ ነበር። ሄጄም በአህዛብ መካከል እየሰበኩት ስላለው ወንጌል ነገርኳቸው፣ ነገር ግን በከንቱ እንዳልሮጥኩ ወይም እየሮጥኩ እንዳልሆን እርግጠኛ ለመሆን ይህን የተናገርኩት በሌሎቹ ዘንድ እንደ ዋና ለሚታሰቡት ብቻ ነበር። 3 ግሪካዊ የሆነው ሲላስ እንኳ እንዲገረዝ አልተገደደም። 4 ይህ ጉዳይ የተንሳው በክርስቶስ ያገኘነውን ነፃነት ለመሰለል ሾልከው በገቡ ውሸተኞች ወንድሞች ምክንያት ነበር። 5 የህግ ባሪያዎች ሊያደርጉን ይመኙ ነበር። ነገር ግን ለእናንተ ወንጌሉ ሳይለወጥ ይቆይላችሁ ዘንድ ለአንድ ሰዓት እንኳ ለሀሳባቸው አልተገዛንም። 6 ነገር ግን ሌሎች መሪዎች ናቸው ያልዋቸው ምንም አስተዋፅኦ አላደርጉልኝም። ማንም ይሁኑ ለእኔ ትርጉም አልነበረውም። ሆኖም ግን ልክ ጴጥሮስ ለተገረዙት ወንጌልን ለማድረስ አደራ እንደተሰጠው ሁሉ 7 እኔም ላልተገረዙት ወንጌልን ለማድረስ አደራ እንደተቀበልኩ አዩ፥ 8 ምክንያቱም ለተገረዙት ሃዋሪያ ይሆን ዘንድ በጴጥሮስ የሰራ እግዚአብሔር ላልተገረዙት ሃዋሪያ እሆን ዘንድ በእኔም ስለሚስራ ነው። 9 እንደመሪዎች የሚታወቁት ያዕቆብ፥ኬፋና ዮሀንስ በእኔ ላይ ያለውን ፀጋ ባዩ ጊዜ እኛ ወደ አህዛብ እነርሱ ደግሞ ወደተገረዙት ይሄዱ ዘንድ የማህበራቸውም ተካፋዮች እንድንሆን ሙሉ መብት ሰጡን። 10 እኔ ለማድረግ የምናፍቀውን ድሆችን እንድናስብም አሳሰቡን። 11 ከዚያም ኬፋ ወደ አንፆኪያ በመጣ ጊዜ ሥራው ትክክል ስላልነበረ ፊት ለፊት ተቃወምኩት። 12 ምክንያቱም ከያዕቆብ ዘንድ ሰዎች ከመምጣታቸው በፊት ኬፋ ከአህዛብ ጋር ይበላ ነበር። ሰዎቹ በመጡ ጊዜ ግን እነኚህን የተገረዙ ሰዎች ፈርቶ ከአህዛብ ጋር መብላቱን አቆመ እንዲያውም ተለያቸው። 13 በርናባስ እንኳ በግብዝነታቸው እስኪሳብ ድረስ ሌሎቹም አይሁድ በኬፋ ግብዝነት ተካፋዮች ነበሩ። 14 ወንጌልን በሚፃረር መንገድ መሄዳቸውን ባየሁ ጊዜ ኬፋን በሁሉም ፊት «አንተ አይሁዳዊ ሆንህ በአህዛብ ስርአት የምትኖር ከሆነ አህዛብ በአይሁድ ስርአት እንዲኖሩ ለምን ታስገድዳቸዋልህ?» አልኩት። 15 እኛ«አህዛብ ኃጢአተኞች» ያልሆንን ነገር ግን በትውልድ አይሁዳዊ የሆንን በክርስቶስ ኢየሱስ ላይ ባለ እምነት እንጂ ማንም ህግን በመፈፀም እንደምይፀድቅ እናውቃለን። 16 በህግ ሥራ ማንም ሊፀድቅ ስለማይችል በህግ ሥራ ሳይሆን በክርስቶስ ኢየሱስ ባለ እምነት እንፀድቅ ዘንድ ወደ ክርስቶስ ኢየሱስ እምነት ተጠርተናል። 17 ነገር ግን እግዚአብሔር በክርስቶስ እንዲያፀድቀን እየፈለግን ሳለ ራሳችንን ኃጢአተኞች ሆነን እናገኛለን፥ 18 ታዲያ ክርስቶስ የኃጢአት አገልጋይ ሆነ ማለት ነው? በፍፁም አይደለም። 19 ምክንያቱም አውልቄ የጣልኩትን ህግን የመፈፀም ትምክህት እንደገና ብገነባ ራሴን ህግ ተላላፊ ሆኜ አገኘዋለሁ። በህግ በኩል ለህግ ሞቼአለሁ። 20 ከክርስቶስ ጋር ተሰቅያለሁ። ከእንግዲህ የምኖረው እኔ አይደለሁም፥ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል። አሁን በሥጋ የምኖረው ኑሮ በወደደኝና እራሱን ስለ እኔ በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው። 21 የእግዚአብሔርን ፀጋ አላቃልልም፥ ህግን በመጠበቅ ፅድቅ የሚገኝ ቢሆን ኖሮ ክርስቶስ መሞቱ ከንቱ በሆነ ነበር።
ጳውሎስ ሐዋርያትን ሳይሆን ፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ወንጌልን እንዴት እንደ ተማረ ታሪክ ማቅረቡን ቀጠለ ፡፡
"ተጓዘ" ኢየሩሳላ በተራራማ አገር ውስጥ ትገኛለች ፡፡ በተጨማሪም አይሁዶች ኢየሩሳሌምን ወደ ሰማይ ቅርብ የሆነ ቦታ እንደሆነ አድርገው ይመለከቱት ነበር ፣ ስለዚህ ጳውሎስ በምሳሌያዊ ሁኔታ እየተናገረ ሊሆን ይችላል ፣ ወይም ወደ ኢየሩሳሌም ለመድረስ አስቸጋሪ የሆነውን ፣ ከፍ ያለ ፣ ጉዞውን የሚያንፀባርቅ ሊሆን ይችላል።
"በምእመናን መካከል በጣም አስፈላጊ መሪዎች"
ጳውሎስ ለስራ እንደ ዘይቤ ሩጫ ይጠቀማል ፣ እናም እሱ የሠራው ሥራ ትርፋማ መሆኑን ለማጉላት ድርብ አሉታዊን ይጠቀማል። አት: - “ትርፋማ ሥራ ነበርኩ ፣ ወይም ሠራሁ ፣” (የበለስ_ቁጥር አሃዶች እና በለስ
“ለትርፍ” ወይም “በከንቱ”
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “አንድ ሰው እንዲገረዘው ያድርጉት (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
“ክርስቲያን ነን የሚሉ ሰዎች ወደ ቤተ ክርስቲያን መጡ ፣” ወይም “ክርስቲያን ነን የሚሉ ሰዎች በመካከላችን መጡ”
ሰዎች በነፃነት እንዴት እንደሚኖሩ በድብቅ ይመልከቱ
ነፃነት
“እነዚህ ሰላዮች ይፈልጉ ነበር” ወይም “እነዚህ የሐሰት ወንድሞች ፈልገዋል”
የሕግ ባሪያዎች እንድንሆን ያደርገናል ፡፡ ጳውሎስ እየተናገረ ያለው ህጉ ያዘዘውን የአይሁድን የአምልኮ ሥርዓት ለመከተል ስለ መገደድ ነው ፡፡ ይህን እየተናገረ ያለው ስለ ባርነት ነው ፡፡ በጣም አስፈላጊው የአምልኮ ሥርዓት ግርዘት ነበር ፡፡ አት: - “ህጉን እንድንታዘዝ ለማስገደድ” (የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
“አስገባ” ወይም “አዳምጥ”
እዚህ “እኔ” የሚለው ቃል ጳውሎስ የሚያስተምረውን ይወክላል ፡፡ አት: - "እኔ በም አስተምርበት ምንም ነገር አልጨምሩም" ወይም "በም አስተምርበት ምንም ነገር እንዳክል አልነገረኝም"
“ይልቁን” ወይም “ይልቁን”
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር አመነኝ” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ሰዎች ስለ ኢየሱስ የሚያስተምሩት እና ሰዎች በኢየሱስ እንዲያምኑ ያመኑ ሰዎች ነበሩ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነልኝ አየሁ (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
“ተቀባይነት ያለው… እንደ ባልደረባችን” ወይም “በክብር የተቀበሉት… በክብር” (ይመልከቱ ፡፡
"ቀኝ እጆቻቸው"
“ለችግረኞች ፍላጎቶች ይንከባከቡ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ ቪዲዮም)
“በፊቱ” የሚሉት ቃላት “ሊያይ እና ሊሰማኝ የሚችልበት ስፍራ” የሚል አገላለጽ ነው ፡፡ አት: - “በአካል ፊት ለፊት አጋጥቼዋለሁ” ወይም “በግለሰቡ በግለሰቡ ላይ ተከራክሬያለሁ”
ከጊዜ ጋር በተያያዘ
ከእነሱ ጋር መብላት አቆመ ”
እነዚህ መገረዝ የጠየቁት እነዚህ ሰዎች የሆነ ጥፋት እየፈጸመ እንደሆነ ይፈርዳል ብለው ፈራ ”ወይም“ እነዚህ ግርዛት የጠየቁት እነዚህ ሰዎች የሆነ ጥፋት በመፈጸማቸው ተጠያቂ እንደሚያደርጋቸው ፈርቶ ነበር ”(የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
ክርስትናን የተቀበሉ አይሁዶች ግን በክርስቶስ የሚያምኑ በአይሁድ ወጎች መሠረት እንዲኖሩ የጠየቁ አይሁዶች
ከ “ራቁ” ወይም “ተቆጥበዋል”
“እነሱ ወንጌልን እንደሚያምኑ ሰዎች አልነበሩም” ወይም “እነሱ ወንጌልን እንደማያምኑ ሆነው ይኖሩ ነበር”
ይህ የአጻጻፍ ጥያቄ ተግሣጽ ነው እናም እንደ መግለጫ ሊተረጎም ይችላል። AT: - “አሕዛብ ልክ እንደ አይሁዶች እንዲኖሩ ማስገደድ ስህተት ነዎት” ፡፡ “እርስዎ” የሚለው ቃል ጴጥሮስን የሚያመለክት ሲሆን ነጠላ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ እና በለስ_ዮዎ)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ቃላትን በመጠቀም ሀይል ወይም 2) ማሳመን (ዩ.አር.ቢ.) ናቸው።
ህጉን ለሚያውቁ አይሁዶች እንዲሁም ህጉን የማያውቁ አሕዛብ እንደሚድኑ ጳውሎስ ለአማኞች ይነግራቸዋል ህጉን ባለመጠበቅ ብቻ ፡፡
“አይሁዶች የአህዛብ ወገን ብለው የሚጠሩት አይደለም”
“በክርስቶስ ኢየሱስ አምነናል”
ይህ ምናልባት የሚያመለክተው ጳውሎስንና ሌሎችን እንጂ ገላትያዎችን አይደለም። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
“ሥጋ” የሚለው ቃል ለሰውየው አጠቃላይ መግለጫ ነው ፡፡ አት: - “ማንም ሰው” (ይመልከቱ: የበለስ_ስኔክዶቼ)
“በክርስቶስ መጽደቅ” የሚለው ሐረግ ትክክለኛ ነው ምክንያቱም ከክርስቶስ ጋር አንድ ስለሆንን እና በክርስቶስ አማካይነት ጸድቀዋል ፡፡
“ተገኝተዋል” የሚሉት ቃላት “እኛ በእርግጥ ኃጢአተኞች ነን” የሚል አፅን idት የሚሰጥ ዘይቤያዊ አነጋገር ነው ፡፡ አት: - “እኛ ደግሞ በእርግጥ ኃጢአተኞች መሆናችንን እናውቃለን” (የበለስ_ ቪዲዮን ተመልከት)
"በእርግጥ ይህ ያ እውነት አይደለም!" ይህ አገላለጽ ቀደም ባለው የአጻጻፍ ጥያቄ ላይ ጠንካራ ምላሽ የሚሰጥ አሉታዊ መልስ ይሰጣል “ክርስቶስ የኃጢአት አገልጋይ ሆኗል?” እዚህ ሊጠቀሙባቸው በሚችሉት ቋንቋዎ ተመሳሳይ መግለጫ ሊኖርዎት ይችላል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
ፖል አዎንታዊውን ለማጉላት አሉታዊ ተናግሯል ፡፡ አት: - የ “ዋጋን አረጋግጣለሁ” የበለስ_ቁጥርቆች)
ጳውሎስ ከዚህ በፊት ያልነበረን ሁኔታ እየገለጸ ነው ፡፡ አት: - “ጽድቅ ግን አልተገኘም… ስለዚህ ክርስቶስ አልሞተም” (የበለስ_አፖን ተመልከት)
"አንድ ሰው ህጉን በመጠበቅ ጻድቅ ሊሆን ይችላል"
በመሞቴ ምንም አላከናወንም ”
1 እናንተ ማስተዋል የጎደላችሁ የገላቲያ ሰዎች ማነው በክፉ ዓይኑ ያያችሁ፥ ክርስቶስ እንደተሰቀል ሆኖ በፊታችሁ ተስሎ አልነበረምን? 2 ይህን ብቻ ከእናንተ ማወቅ እፈልጋለሁ። መንፈስ ቅዱስን የተቀበላችሁት በህግ ሥራ ነው ወይስ የሰማችሁትን በማመናችሁ? 3 ይህን ያህል ሞኞች ናችሁ እንዴ፥ በመንፈስ ጀምራችሁ በሥጋ ትጨርሳላችሁ? 4 በእርግጥ ይህ ከንቱ ከተባለ ያን ሁሉ መከራ የተቀብላችሁት በከንቱ ነውን? 5 መንፈስ ቅዱስን የሰጣችሁና በመካከላችሁ ኃይለኛ ነገርን ያደረገው እርሱ ይህን ያደረገው በህግ ሥራ ነው ወይስ ከእምነት በሆነ እምነታችሁ ነው? 6 ልክ አብርሀም «እንዳመነና እምነቱ እንደ ፅድቅ እንደተቆጠረለት» 7 የሚያምኑ ሁሉ የአብርሀም ልጆች እንደሆኑ አስተውሉ። 8 ቅዱሳት መፅሀፍት እግዚአብሔር አህዛብን እንደሚያፀድቅ አስቀድመው አመልክተዋል። ወንጌል «አህዛብ ሁሉ በአንተ ይባረካሉ» ተብሎ በመጀመሪያ ለአብርሀም ተሰብኳል። 9 ስለዚህም የሚያምኑ እምነት ከነበረው ከአብርሀም ጋር የተባረኩ ናቸው። 10 «ህግን ሁሉ ይፈፅም ዘንድ ለህግ የማይታዘዝ ሁሉ የተረገመ ነው» ተብሎ ተፅፎአልና በህግ ስራ የሚታመን ሁሉ በእርግማን ስር ነው። 11 «ጻድቅ በእምነት ይኖራልና» እግዚአብሔር ማንንም በህግ እንደማያጸድቅ ግልጽ ነው። 12 ህግ ከእምነት የመነጨ አይደለም፥ ይልቁኑም «በህግ ውስጥ ያሉትን እነዚያን ነገሮች የሚያደርግ በህግ ይኖራል» 13 «በእንጨት ላይ የሚሰቀል የተረገመ ነው» ተብሎ በተጻፈው መሰረት እርሱ ስለኛ እርግማን በመሆን ከህግ እርግማን ዋጀን። 14 የዚህ ተግባር ዓላማ የመንፈስ ቅዱስን ተስፋ በእምነት እንቀበል ዘንድ በአብርሀም ላይ የነበረው በረከት በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል በአህዛብም ላይ እንዲሆን ነው። 15 የምናገረው በሰው ቋንቋ ነው። ልክ በሰዎች መካከል እንደተደረገ ውል ማንም ከዚህ ሊቀንስ ወይም ሊጨምር አይችልም። 16 እንግዲህ ተስፋዎቹ የተነገሩት ለአብርሀምና ለዘሩ ነው። ብዙ ሰዎችን እንደሚያመለክት «ለዘሮቹ» አላለም። ነገር ግን አንድ መሆኑን በሚገልጽ መልኩ«ለዘሩ» ብሎ ይናገራል። ያም ለዘሩ የተባለለት ክርስቶስ ነው። 17 እንግዲህ እንዲህ ልበል። አስቀድሞ በእግዚአብሔር የተረጋገጠው ቃል ኪዳን ተስፋ ከ430 ዓመት በኋላ በተሰጠ ህግ አልተሻረም። 18 ምክንያቱም ውርሱ በህግ የመጣ ቢሆን ኖሮ በተስፋ በኩል ባልመጣ ነበር፥ ነገር ግን እግዚአብሔር ለአብርሃም በተስፋ አማካኝነት ርስትን እንዲያው ሰጠው። 19 ታዲያ ህግ ለምን አስፈለገ? የአብርሃም ዘር ተስፋ ወደተሰጣቸው እስኪመጣ ድረስ በመተላለፍ ምክንያት ህግ ተሰጠ፤ ህጉ በመካከለኛ አማካኝነት በመላዕክት አማካኝነት ተግባራዊ ሆኗል። 20 መካከለኛ ሲል ከአንድ ሰው በላይ እንደሆነ ያመለክታል፥ እግዚአብሔር ግን አንድ ነው። 21 ታዲያ ህግ የእግዚአብሔርን ተስፋ ይቃረናል ማለት ነው? በፍጹም አይደለም። ህይወትን ሊሰጥ የሚችል ህግ ተሰጥቶ ቢሆን ኖሮ በእርግጠኝነት ጽድቅ በህግ በኩል ይመጣ ነበር። 22 ነገር ግን ይልቁኑ መጽሀፍ ሁሉን ነገር ከኃጢአት በታች እስርኛ አድርጓል። ስለዚህም እኛን በክርስቶስ ኢየሱስ ለማዳን እግዚአብሔር የሰጠው ተስፋ ለሚያምኑ ተሰጠ። 23 ነገር ግን በክርስቶስ ማመን ከመምጣቱ በፊት እምነት እስከተገለጠበት ጊዜ ድረስ በህግ ታስረንና ታግደን ነበር። 24 ስለዚህ በእምነት እንድንጸድቅ ህግ ወደ ክርስቶስ ዘመን የሚያደርሰን ሞግዚት ሆነ። 25 አሁን እምነት ስለመጣ ከዚህ በኋላ በሞግዚት ሥር አይደለንም። 26 ምክንያቱም ሁላችሁም በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁ። 27 በክርስቶስ ስም የተጠምቃችሁ ሁላችሁ ክርስቶስን ለብሳችሁታል። 28 ሁላችሁ በክርስቶስ አንድ ስለሆናችሁ በዚህ ጉዳይ በአይሁድና በግሪክ ሰዎች፥ በባሪያና ነጻ በሆነ፥በሴትና በወንድ መካከል ልዩነት የለም። 29 እንግዲህ የክርስቶስ ከሆናችሁ የአብርሀም ዘሮች እንደተስፋ ቃሉም ወራሾች ናችሁ።
ጳውሎስ በገላትያ የነበሩትን አማኞች የእግዚአብሔርን ህግ ባለመፈፀም ሳይሆን እግዚአብሔርን በእምነት መንፈስ ቅዱስ እንደሰጣቸው አስታውሷቸዋል ፡፡
ጳውሎስ ገለልተኛ ጥያቄዎችን በመጠየቅ ገላትያዎችን ገሥጻቸው ነበር ፡፡
ጳውሎስ የገላትያ ሰዎች አንድ ሰው ፊደል እንዳስመሰላቸው የገለጹትን አስጨናቂ እና አፀያፊ ጥያቄን እየተጠቀመ ነው ፡፡ አንድ ሰው በእጃቸው ላይ አስማተኛ እንዳደረገ በእውነት አያምንም ፡፡ አት: - "አንድ ሰው አስማተኛ እንዳሳደረብዎት ታሳያላችሁ!" (ይመልከቱ: የበለስ እና የበለስ_ቁጥር)
ይህ ከቁጥር 1 ድረስ አጠራጣሪ ሆኖ ይቀጥላል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_አሮን)
ይህንን የአጻጻፍ ጥያቄ ከቻሉ እንደ ጥያቄ ይተረጉሙ ፣ ምክንያቱም አንባቢው እዚህ ጥያቄ ይጠብቃል ፡፡ ደግሞም ፣ ለጥያቄው መልስ “የሰማችሁትን በማመን” ሳይሆን “ህጉ የሚናገረውን በማድረግ” መሆኑን አንባቢው ማወቋን ያረጋግጡ። AT: "መንፈስ ቅዱስን የተቀበለው ህጉ ያለውን ነገር በማድረግ ሳይሆን የሰማችሁትን በማመን ነው ፡፡" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ የተዛባ ጥያቄ ጳውሎስ የገላትያ ሰዎች ሞኞች መሆናቸው እንደተገረመ አልፎ ተርፎም እንደተናደደ ያሳያል ፡፡ አት: - "በጣም ሞኞች ናችሁ!" (UDB) (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
“ሥጋ” የሚለው ቃል ጥረትን ለመግለጽ ዘይቤያዊ አነጋገር ነው። አት: - “በእራስዎ ጥረት” ወይም “በገዛ ሥራዎ”
ጳውሎስ የገላትያ ሰዎች በሚሰቃዩበት ወቅት የተወሰነ ጥቅም እንደሚያገኙ ያምን ዘንድ ይህን ጥያቄ ይጠቀም ነበር ፡፡ አት: - "በእርግጥ ብዙ ነገሮችን በከንቱ እየሠቃዩ እንደነበረ አላሰብኩም ...!" ወይም “በርግጥ ብዙ ነገሮችን ለመሠቃየት አንድ ጥሩ ዓላማ እንደነበረ አውቀዋል…!” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
በክርስቶስ ላይ ባላቸው እምነት ምክንያት በሚቃወሟቸው ሰዎች ምክንያት እነዚህን ሁሉ መከራዎች እንደደረሱ በግልፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ AT: "በክርስቶስ ያለዎት እምነት በእምነት ሲቃወሙህ ብዙ ብዙ መከራዎች ደርሶብሃል" ወይም "በክርስቶስ አምነሃል ፣ ክርስቶስን በሚቃወሙትም ብዙ መከራዎች ደርሶብሃል ፡፡ እምነትህ እና መከራ በከንቱ ነበር" (ተመልከት : የበለስ_ቁጥር)
“ጥቅም የሌለው” ወይም “ጥሩ ነገር የማግኘት ተስፋ ሳይኖር”
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ጳውሎስ ይህንን የተዛባ ጥያቄ ተጠቅሞ ልምዶቻቸው በከንቱ እንዳይሆኑ ለማስጠንቀቅ ነው ፡፡ አትቲ: - “በከንቱ ይሁን! ወይም “በኢየሱስ ክርስቶስ ማመንን ማቆም እና ሥቃያችሁ በከንቱ አይሁን” ወይም 2) ጳውሎስ ይህንን ጥያቄ የተጠቀመው መከራቸው በከንቱ እንዳልሆነ ያረጋግጥልናል ፡፡ አት: - በእርግጥ ይህ በከንቱ አልነበረም! (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ጳውሎስ የገላትያ ሰዎች ሰዎች መንፈስ ቅዱስን የሚቀበሉበትን መንገድ ለማስታወስ ሌላ የአጻጻፍ ጥያቄ ይጠይቃል ፡፡ አት: - እሱ ... የሕጉን ሥራ የሚሠራው በእምነት አይደለም ፤ ይህን የሚያደርገው በእምነት በመስማት ነው። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ ህጉ የሚፈልገውን ሥራ የሚሠሩ ሰዎችን ይወክላል ፡፡ አት: - "ህጉን እንድናደርግ ያዘዘንን ታደርጋላችሁና"
ቋንቋዎ ሰዎች የሰሙትና ያመኑበት ነገር በግልፅ እንዲገለጽ ሊፈልግ ይችላል። አት: - “መልእክቱን ስለሰማችሁ እና በኢየሱስ ስለምታምኑ” ወይም “መልእክቱን ስላዳመጥክ እና በኢየሱስ ስለ ታምነሃል” (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
ጳውሎስ ፣ አብርሃም እንኳ በሕግ ሳይሆን በእምነት በእምነት ጽድቅን እንደተቀበለ የገላትያ አማኞችን ያስታውሳል ፡፡
እግዚአብሔር የአብርሃምን በእግዚአብሔር ላይ እምነት እንዳለው አየ ፣ ስለሆነም እግዚአብሔር አብርሃምን እንደ ጻድቁ ተቆጥሯል ፡፡
“እምነት ያላቸው” “እምነት” የሚለው ስም “ማመን” ከሚለው ግስ ጋር ሊገለጽ ይችላል ፡፡ አት: “የሚያምኑ” (የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎችን ይመልከቱ)
ይህ እግዚአብሔር ለአብርሃምን የሚመለከታቸው ሰዎችን ይወክላል ፡፡ አት: - “እንደ አብርሃም በተመሳሳይ ጻድቅ” (የበለስ_ማወቅን ይመልከቱ)
እግዚአብሔር ለአብርሃም የገባውን ቃል የገባላቸው እና ተስፋው በክርስቶስ በኩል ከመሆኑ በፊት የጻፉት ስለሆነ ፣ መጽሐፉ ከመፈጸሙ በፊት የወደፊቱን እንደሚያውቅ ሰው ነው ፡፡ አት: - “አስቀድሞ የተተነበየ” ወይም “ይህ ከመከሰቱ በፊት አየ” (ይመልከቱ።
“ባደረጋችሁት ነገር” (ዩ.አር.ቢ.) ወይም “ባረካችሁ” ፡፡ “እርስዎ” የሚለው ቃል አብርሃምን የሚያመለክት ሲሆን ነጠላ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ዮዎ)
“በዓለም ውስጥ ያሉ ሁሉም ሰዎች-ቡድኖች” (UDB)። እግዚአብሔር ትኩረት እየሰጠ ያለው እርሱ የተመረጠውን ቡድን የአይሁድን ሕዝብ ብቻ አለመሆኑን ነው ፡፡ የመዳን እቅዱ ለአይሁድም እና አይሁድ ላልሆኑ ነበሩ ፡፡
በእርግማን ሥር መሆን መርገምን ያመለክታል ፡፡ እዚህ የሚያመለክተው ዘላለማዊ ቅጣት መቀጣትን ነው ፡፡ “የሚተማመኑትን… ሕጉ የተረገመ ነው” ወይም “በሕግ ላይ የሚመኩትን ግን ለዘላለም ይቀጣቸዋል” (ይመልከቱ ፡፡
ግልጽ የሆነው ነገር በግልጽ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ በ “ቅዱሳት መጻሕፍት ግልጽ ናቸው” ወይም “ቅዱሳት መጻሕፍት በግልፅ ያስተምራሉ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ይህ ከነቃ ግስ ጋር ሊገለጽ ይችላል። አት: - “እግዚአብሔር ማንም በሕግ ጻድቅትን አያጸድቅም”
ጳውሎስ ሕጉን ቢታዘዙ እግዚአብሔር እንደሚያጸድቃቸው ያላቸውን እምነት እያስተካከለ ነው ፡፡ አት: - “ሕጉን በመታዘዝ ማንም በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ አይደለንም” ወይም “እግዚአብሔር ሕጉን ስለታዘዙ ማንንም አያጸድቅም” (የበለስ_ቁጥር 3 ን ይመልከቱ)
ይህ ጻድቃንን ያመለክታል ፡፡ አት: - “ጻድቃንም ሰዎች” ወይም “እግዚአብሔር ጻድቃን አድርጎ የሚቆጥራቸው ሰዎች”
"ህጉ ምን ማድረግ እንዳለበት"
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “ሁሉንም መታዘዝ አለባቸው” (ዩ.አር.ቢ.) ወይም 2) “ሕጉ የሚፈልገውን ለማድረግ ባለው ችሎታ ይፈረድበታል” ፡፡
ህጉን መጠበቅ አንድን ሰው ሊያድን እንደማይችል እና ህጉ ለአብርሃም በተሰጠ እምነት አዲስ ሁኔታ እንደማይጨምር ጳውሎስ በድጋሚ እነዚህን አማኞች ያስታውሳል ፡፡
“እርግማን” የሚለው ስም “እርግማን” ከሚለው ግስ ጋር ሊገለጽ ይችላል። አት: - “በሕጉ ምክንያት እንዳይረገም” ወይም “ህጉን ባለመታዘዙ የተረገመ”
“እርግማን” የሚለው ስም “እርግማን” ከሚለው ግስ ጋር ሊገለጽ ይችላል። አት: - “ለእኛ በመረገምን” ወይም “በእኛ ፋንታ እግዚአብሔር ሲረገም” (የበለስ_ቁጥር መግለጫዎችን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ የተረገመ እርግማን የተወገዘ መሆኑን ያሳያል ፡፡ አት: - “በሕግ ከመኮነን… በእኛ ፋንታ የተወገዘ… ሁሉም የተወገዘ ነው” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ጳውሎስ አድማጮቹ ኢየሱስ በመስቀል ላይ ስለ ተሰቀለው እየተናገረ መሆኑን ይገነዘባሉ ፡፡
ይሆናል
“እኛ” የሚለው ቃል ደብዳቤውን የሚያነቡ ሰዎችን ያካትታል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህንን በ 1 1 ውስጥ ተርጉም ፡፡
“እንደ ሰው” ወይም “ብዙ ሰዎች ከሚረዱት”
ይህ ቃል ጳውሎስ አጠቃላይ መርህ እንደገለጠ እና አሁን አንድ የተወሰነ ጉዳይ ለማስተዋወቅ መጀመሩን ያሳያል ፡፡
"ብዙ ዘሮችን መጥቀስ"
“የአንተ” የሚለው ቃል ነጠላ ሲሆን የሚያመለክተው የተወሰነ የአብርሃም ዘር የሆነውን (እና ያ ዘር ደግሞ “ክርስቶስ” ተብሏል) ፡፡ ይመልከቱ: የበለስ_አዎ)
ጳውሎስ እየተናገረ ያለው ውርስ የሚገኘው በተስፋ ቃል በኩል ብቻ መሆኑን ለማጉላት ስላልነበረ ሁኔታ ነው ፡፡ የ “የእግዚአብሔር ሕግን ማክበር ባለመቻላችን ርስታችን በተስፋው ቃል በኩል ሆኗል” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ሂፖ)
እግዚአብሔር ለአማኞች የገባውን ቃል መቀበል ከቤተሰብ አባል የርስት እና ሀብት ውርስ እና ዘላለማዊ በረከቶች እና ቤዛ እንደሆነ ተደርጎ ይገለጻል። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ጳውሎስ በገላትያ ላሉት አማኞች እግዚአብሔር ህጉን ለምን እንደ ሰጣቸው ነግሯቸዋል ፡፡
ጳውሎስ ሊወያይበት የሚፈልገውን ቀጣዩን ርዕስ ለማስተዋወቅ አነጋገራዊ ጥያቄን ይጠቀማል ፡፡ እንደ መግለጫም ሊተረጎም ይችላል ፡፡ አት: - የሕጉ ዓላማ ምን እንደሆነ እነግርዎታለሁ ወይም “እግዚአብሔር ህጉን ለምን እንደሰጠ ልንገርዎ” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር አክሎታል” ወይም “እግዚአብሔር ህጉን ጨምሯል” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ሕጉን በመላእክት እገዛ አወጣ ፣ አስታራቂም ሥራ ላይ አደረገው” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
"የሚወክል"
እግዚአብሔር ያለ አስታራቂ እግዚአብሔር ለአብርሃም ተስፋውን ሰጠው ፣ ግን ሕጉን ለሙሴ ግን አስታራቂ ሰጠ ፡፡ በዚህ ምክንያት ፣ የጳውሎስ አንባቢዎች ሕጉ በሆነ መንገድ ቃል ኪዳኑን እንደማይፈጽም ያስቡ ይሆናል ፡፡ ጳውሎስ አንባቢዎቹ እዚህ ምን ሊያስቡበት እንደነበር እየገለጸ ነው ፣ በሚቀጥሉት ጥቅሶችም ይመልሳል ፡፡
በዚህ ክፍል ውስጥ “እኛ” የሚለው ቃል ሁሉንም ክርስቲያኖችን ያመለክታል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
“መቃወም” ወይም “በግጭት ውስጥ”
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፣ እና ቀልብ ስሙ “ሕይወት” የሚለው “የቀጥታ” ከሚለው ግስ ሊተረጎም ይችላል። አት: - “እግዚአብሔር የሚጠብቁት በሕይወት እንዲኖሩ የሚያደርግ ሕግ ከሰጠ” (የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያ)
ያንን ሕግ በመታዘዝ ጻድቅ ልንሆን ይችል ነበር ”
ሌሎች ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “ሁላችንም ኃጢአትን ስለምንሠራ ፣ በክርስቶስ ሁሉንም ለሚያምኑ የገባውን ቃል ለእምነት ለሚያምኑ ይሰጣቸዋል ፣ ሁላችንም ኃጢአት ስለሠራን እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር በሕግ ቁጥጥር ስር አደረገ ፡፡ ኃጢአት ስለሠራን እግዚአብሔር እስር ቤት እንዳስገባ ሁሉ ሁሉንም ነገር ከሕግ የበላይነት በታች አስቀመጠ ፡፡ ይህንን ያደረገው በክርስቶስ ኢየሱስ ለሚያምኑ የገባውን ቃል ለሚያምኑ ሁሉ ለመስጠት ይፈልጋል ፡፡ . "
ጳውሎስ ጥቅስ እንደ ሰው አድርጎ የሚናገር ሲሆን ጥቅስ የጻፈውን እግዚአብሔርን ይናገራል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር” (ይመልከቱ: የበለስ_ኔሽን)
ጳውሎስ አማኞች በሕጉ ሥር ባሪያዎች ሳይሆኑ በአምላክ ቤተሰብ ውስጥ ነፃ መሆናቸውን ጳውሎስ በገላትያ ላሉት ሰዎች አሳስቧቸዋል።
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - ህጉ እስረኞችን ይይዘናል እናም እስር ቤት ነበርን አሊያም "ህጉ በእስር ቤት ውስጥ ያዙን" (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ሕጉ በቁጥጥር ስር የዋለን የእስረኞች ጠባቂ አካል ሕጉ የሚገዛንበት መንገድ ተገልጻል ፡፡ አት: - “ህጉ እንደ እስር ቤት ጠባቂ ሆኖ ይቆጣጠርን ነበር” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለጽ ይችላል ፣ እና ይህ እምነት ያለበት ማን በግልጽ ሊገለፅ ይችላል። በዚህ: - “እግዚአብሔር በክርስቶስ የሚያምኑትን እንደሚያጸድቅ እስከገለጠ ድረስ” ወይም “በክርስቶስ የሚያምኑትን እንደሚያጸድቅ እስኪያሳይ ድረስ” (የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር ግልፅ) ይመልከቱ
“ለልጅ የበላይነት” ከሚለው በላይ ይህ ብዙውን ጊዜ በወላጅ የተሰጡትን ህጎች እና ባህሪዎች የማስፈፀም ሃላፊነት የተሰጠው እና በልጁ ድርጊቶች ላይ ለወላጅ ሪፖርት የሚያደርግ አገልጋይ ነው ፡፡
ክርስቶስ እስከመጣበት ጊዜ ድረስ
ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት ፣ እግዚአብሔር እኛን ለማፅደቅ አቅዶ ነበር ፡፡ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ፣ እኛን ለማፅደቅ ያለውን ዕቅዱን ፈፅሟል ፡፡ ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - "እኛ እግዚአብሔር ጻድቃችንን ያሳውቀን ነበር" (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “እርስዎ… ልክ እንደ ክርስቶስ አንድ ዓይነት ሰው ሆነዋል” (UDB) ወይም 2) “እርስዎ… ልክ እንደ እግዚአብሔር ከእግዚአብሔር ጋር አንድ ዓይነት ግንኙነት አለዎት” ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እግዚአብሔር በአይሁድና በግሪክ ፣ በባሪያና በነጻ ፣ ወንድና ሴት መካከል ምንም ልዩነት የለውም ፡፡
እግዚአብሔር ቃል የገባላቸው ሰዎች ንብረትንና ሀብትን ከቤተሰብ አባል እንደሚወርሱ ተደርገው ይወሰዳሉ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
1 ያን የምለው ህጻን ሳለ ምንም እንኳ ሁሉም የእርሱ ቢሆንም ወራሹ ከባሪያ አይለይም። 2 ነገር ግን አባቱ የወሰነልት ቀን እስኪደርስለት ድረስ በተንከባካቢዎቹና በሞግዚቶቹ ስር ይቆያል። 3 እኛም ልጆች ሳለን በዚህ ዓለም ዋና ትምህርቶች እስራት ሥር ነበርን። 4 ነገር ግን በትክክለኛው ጊዜ እግዚአብሔር በህግ ሥር ያሉትን 5 ነጻ እንዲያወጣና የልጅነትን መብት እንዲኖረን ከሴት የተወለደውንና በህግ ሥር የተወለደውን ልጁን ላከ። 6 ልጆች ስለሆናችሁ «አባ አባት» እያለ የሚጣራውን የልጁን መንፈስ ወደ ልባችን ላከ። 7 በዚህም ምክንያት ከእንግዲህ ልጆች እንጂ ባሮች አይደላችሁም፥ ልጆች ከሆናችሁ ደግሞ የእግዚአብሔር ወራሾች ናችሁ። 8 ነገር ግን እግዘአብሔርን በማታውቁበት በቀድሞው ዘመን በባህሪያቸው ፈጽሞ አማልክት ላልሆኑት ተገዝታችሁ ኖራችሁ። 9 አሁን ግን እግዚአብሔርን አውቃችኋል ይልቁኑም በእግዚአብሔር ታውቃችኋል፥ ታዲያ እንዴት ወደ ደካማና ዋጋ ወደሌለው የዚህ ዓለም ዋና ትምህርት ተመለሳችሁ።እንደገና ባሮች መሆን ትፈልጋላችሁ? 10 ልዩ ቀናትን፥አዳዲስ ጨረቃዎችን፥ ወራትና ዓመታትን ታመልካላችሁ። 11 ስለ እናንተ የደከምኩት ድካም ከንቱ ሆኖብኝ እንዳይሆን ብዬ እፈራለሁ። 12 ወንድሞች ሆይ ልክ እኔ ለእናንተ እንደምሆነው እናንተም ለእኔ እንደዚያው እንድትሆኑ እለምናችኋለሁ። 13 ምንም ክፉ አላደርጋችሁብኝም ነገር ግን ወንጌልን በመጀመሪያ በሰብኩላችሁ ጊዜ የሥጋ ህመም አሞኝ እንደነበረ ታውቃላችሁ። 14 በሥጋዬ ላይ የነበረው ለእናንተ ከባድ ፈተና ቢሆንም አልተጸየፋችሁኝም አልጣላችሁኝምም፥ ይልቁኑ እንደ እግዚአብሔር መልአክ ወይም ክርስቶስን በተቀበላችሁብት አቀባበል ተቀበላችሁኝ። 15 አሁን ደስታችሁ በምንድነው? ዓይናችሁን እንኳ አውጥታችሁ ልትሰጡኝ ፈቃደኛ እንደነበራችሁ እኔ ራሴ ምስክር ነኝ። 16 ታዲያ እውነትን ስለነገርኳችሁ የእናንተ ጠላት ሆንኩ ማለት ነው? 17 አጥበቀው ይፈልጓችኋል ነገር ግን ለመልካም አይደለም። እነርሱን እንድትከተሉ ከእኔ ሊለዩዋችሁ ይፈልጋሉ። 18 እኔ ከእናንተ ጋር ስሆን ብቻ ሳይሆን ሁልጊዜ ለመልካም ነገር መትጋት ተገቢ ነው። 19 ጨቅላ ልጆቼ ሆይ ክርስቶስ በውስጣችሁ እስኪቀረጽ ድረስ ስለእናንተ ምጥ ይዞኛል! 20 የእናንተ ነገር ግራ ስለገባኝ በመካከላችሁ ተገኝቼ በቁጣ ልናገራችሁ እመኛለሁ። 21 እስኪ እናንተ በህግ ሥር ለመሆን የምትፈልጉ ንገሩኝ ህጉ ምን እንደሚል አልሰማችሁምን? 22 አብርሃም አንድ ባሪያ ከነበረች ሴት አንድ ደግሞ ነጻ ከነበረች ሴት የተወለዱ ሁለት ልጆች እንደነበሩት ተጽፏል። 23 ነገር ግን ከባሪያይቱ የተወለደው በሥጋ ብቻ የተወለደ ነው፥ ከነጻይቱ የተወለደው ግን በተስፋ የተወለደ ነው። 24 እነዚህ ነገሮች እንደ ምሳሌ ሊገለጹ ይችላሉ።እነኚህ ሴቶች እንደ ሁለቱ ቃል ኪዳኖች ናቸው፥ አንደኛዋ በሲና ተራራ የተሰጠውንና ባርነትን የወለደውን ታመለክታለች፥ እርሷም አጋር ናት። 25 እንግዲህ አጋር በአረቢያ ምድር የሚገኘው የሲና ተራራ ስትሆን ከልጆቿ ጋር በባርነት የምትኖረውን የአሁኗን ኢየሩሳሌምን ትወክላለች። 26 ነገር ግን እናታችን የሆነችው ላይኛይቱ ጽዮን ነጻ ነች። 27 ምክንያቱም እንዲህ ተብሎ ተጽፏል «አንቺ ያልወለድሽና መካን የሆንሽ ሴት ሀሴት አድርጊ፥አንቺ መውለድን ያልተለማምድሽ ውጪና በደስታ ጩኺ፤ ባል ካላቱ ይልቅ የመካኗ ልጆች በዝተዋልና»። 28 እንግዲህ እናንተ ወንድሞቼ እንደ ይስሀቅ የተስፋ ልጆች ናችሁ። 29 ነገር ግን እንደ ሥጋ ፈቃድ የተወለደው እንደ መንፈስ ፈቃድ የተወለደውን እንዳሳደደው አሁንም እየሆነ ያለው እንደዚያው ነው። 30 መጽሀፍ ስለዚህ ነገር ምን ይላል«የባሪያይቱ ልጅ ከነጻይቱ ልጅ ጋር አይወርስምና ባሪያይቱንና ልጇን አስወጣ»። 31 ስለዚህ ወንድሞች ሆይ እኛ የነጻይቱ እንጂ የባሪያይቱ ልጆች አይደለንም።
ጳውሎስ በሕጉ ሥር ያሉትን ለማዳን ክርስቶስ እንደመጣ ፣ እና ከእንግዲህ ልጆች ባሪያዎች እንዳልሆኑ አድርጎ ለገላትያ አማኞች ማሳሰብ ቀጥሏል ፡፡
"ተመሳሳይ"
ለህፃናት ህጋዊ ኃላፊነት ያላቸው ሰዎች
ዋጋ ያላቸው እቃዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ሌሎች ሰዎች የሚያምኗቸው ሰዎች
እዚህ እኛ “እኛ” የሚለው ቃል የጳውሎስን አንባቢዎችንም ጨምሮ ሁሉንም ክርስቲያኖች ያመለክታል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ይህ የአለም ህጎችን ወይም የሞራል መርሆዎችን ይመለከታል ፣ ወይም 2) ይህ የሚያመለክተው አንዳንድ ሰዎች በምድር ላይ የሚሆነውን የሚቆጣጠሩትን መንፈሳዊ ሀይል ነው።
ጳውሎስ የጠፋውን ንብረት በመግዛት ወይም የባሪያን ነፃ በመግዛት ምሳሌያዊ ምሳሌ ተጠቅሞ በመስቀል ላይ በመሞት ኢየሱስ ለህዝቡ ኃጢአት የከፈለውን ምስል ያሳያል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
እዚህ ላይ ጳውሎስ ቃሉን የተጠቀመበት ለወንድ ልጅ ነው ምክንያቱም ርዕሰ ጉዳዩ ውርስ ነው። በባህሉ እና በአንባቢዎቹ ዘንድ ፣ ውርስ በተለምዶ ፣ ግን ሁልጊዜ ለወንዶች ልጆች ያልፋል ፡፡ እሱ እዚህ የሴቶች ሕፃናትን አልገለጸም ወይም አልገለጸም ፡፡
እግዚአብሔር አብ የእግዚአብሄርን ልጅ መንፈስ ወደ አማኞች ልብ ልኮታል ፡፡ እግዚአብሔር ሁል ጊዜ እንደሚወዳቸው ያውቃሉ ልክ እንደዚህ ደግ አባት ልጆቹን ይወዳል ፡፡
ልብ ለሚያሰበው እና ለሚሰማው ሰው ልብ ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - "እንዴት ማሰብ እና እርምጃ መውሰድ እንዳለብን እንዲያሳይን የልጁን መንፈስ ልኮ ነበር" (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
የሚጠራው መንፈስ ነው ፡፡
አንድ ትንሽ ልጅ አባቱን በጳውሎስ ቤት ቋንቋ ለአባቱ የሚናገርበት መንገድ ይህ ነው ፣ በገላትያ አንባቢዎች ቋንቋ ግን አይደለም ፡፡ የውጪ ቋንቋን ስሜት ለመጠበቅ ይህንን ቋንቋዎ “አባ” ከሚለው ጋር የሚመሳሰል ድምጽን ይተርጉሙ ፡፡
ጳውሎስ አንባቢዎቹን አንድ ሰው እንደሆኑ አድርጎ እያነጋገራቸው ነው ፣ ስለዚህ “እርስዎ” እዚህ ነጠላ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ዮዎ)
እግዚአብሔር ቃል የገባላቸው ሰዎች ንብረትንና ሀብትን ከቤተሰብ አባል እንደሚወርሱ ተደርገው ይወሰዳሉ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ጳውሎስ የገላትያ አማኞችን በእምነት በእምነት ከመኖር ይልቅ እንደገና በእግዚአብሔር ሕጎች ስር እንደገና እንደሚሞክሩ አሳስቧቸዋል ፡፡
ገለልተኛ ጥያቄዎችን በመጠየቅ ገላትያዎችን መገሰሱን ቀጥሏል ፡፡
“እነዚያ እነዚያ” ወይም “እነዚያ መናፍስት”
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ያውቅሃል” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ይህ ከሁለቱም የአጻጻፍ ጥያቄዎች የመጀመሪያው ነው ፡፡ አት: - “ወደ… መርሆዎች” መመለስ የለብዎትም ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህንን ሐረግ በ 4፡3 ውስጥ እንደተረጉሙት በተመሳሳይ መንገድ ይተርጉሙ ፡፡
ይህ ጥያቄ እንደ መግለጫ ሊተረጎም ይችላል ፡፡ አት: - "እንደገና ባሪያዎች መሆን የለብዎትም!" ወይም እንደገና ባሪያዎች መሆን የሚፈልጉ ይመስላል። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ጳውሎስ እየተናገረ ያለው የተወሰኑ ጊዜዎችን ለማክበር ጥንቃቄ እንዳላቸው በማሰብ ነው ፣ ይህም ያንን ማድረጉ በእግዚአብሔር ፊት ትክክለኛ ያደርገዋል ፡፡ አት: - “ቀኖችን ፣ አዲስ ጨረቃዎችን ፣ ወቅቶችን እና ዓመቶችን በጥንቃቄ ታከብራላችሁ”
«ምንም ላይጠቅሙ ይችሉ ነበር» ወይም «ምንም ዓይነት ተፅእኖ አልደረሰም»
ጳውሎስ የገላትያ አማኞችን አብሯቸው በነበረበት ጊዜ እንዴት በደግነት እንዴት እንደያዙቸው የሚያስታውስ ሲሆን አብሯቸው በማይኖርበት ጊዜ በእሱ መታመናቸውን እንዲቀጥሉ አበረታቷቸዋል ፡፡
እዚህ ማለት በጥብቅ መጠየቅ ወይም መሻር ማለት ነው ፡፡ ይህ ገንዘብን ወይም ምግብን ወይም ቁሳዊ ቁሳቁሶችን ለመጠየቅ የሚያገለግል ቃል አይደለም ፡፡
በ1፡1 ላይ እንዳለው ተርጉሙት
ይህ በአዎንታዊ መልኩ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “መልካም አደረግከኝ” ወይም “እንደቻልሽ አደረግከኝ”
“በአካላዊ ህመም ብታየኝ ለእኔ ከባድ ቢሆንም”
እጅግ መጥላት
እነሱን እንዲቀላቀሉ ለማሳመን "
"እኛን እንዳያሳየን" ወይም "ለእኛ ታማኝ አለመሆንን እንዲያቆም"
“የምታደርጉትን ሁሉ ለማድረግ በቅናት”
ፀጋ እና ህግ አብረው ሊሠሩ እንደማይችሉ ጳውሎስ ለአማኞች ይነግራቸዋል ፡፡
ይህ ለደቀመዛምርቶች ወይም ለተከታዮች ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - “በእኔ ምክንያት እናንተ ደቀመዛሙርቶች ናችሁ” (የበለስ_ማይታፎርን ይመልከቱ)
ጳውሎስ ልጅ መውለድን ለገላትያ ሰዎች አሳቢነት ለማሳየት እንደ ዘይቤ ነው ፡፡ AT: - “አንቺን መውለድ የምችል ሴት እንደሆንኩ ያህል ህመም ይሰማኛል እናም ክርስቶስ በእውነት እስከሚቆጣጠርዎ ድረስ በሥቃዬ እቀጥላለሁ” (የበለስ_አሜን)
"አንድ ጥያቄ መጠየቅ እፈልጋለሁ" ወይም "የሆነ ነገር ልነግርዎት እፈልጋለሁ"
ጳውሎስ ቀጥሎ ምን እንደሚል እያስተዋወቅ ነው። አት: - "ህጉ በትክክል ምን እንደሚል መማር ያስፈልግዎታል" ወይም "ህጉ በትክክል ምን እንደሚል ልንገራችሁ" (የበለስ_ቁስለትን ይመልከቱ)
ጳውሎስ አንድን እውነት ለመግለጽ ታሪክ ይጀምራል-ያ ሕግ እና ጸጋ አብረው ሊኖሩ አይችሉም ፡፡
ይህ የሁለቱ ልጆች ታሪክ እኔ አሁን የምነግራችሁን ስዕል ነው ”
“አመላካች” ማለት ሰዎች እና በውስጡ ያሉ ሌሎች ነገሮች የሚወክሉበት ታሪክ ነው ፡፡ በጳውሎስ ዘገባ ፣ በ 4 21 ውስጥ የተጠቀሱት ሁለቱ ሴቶች ሁለት ቃል ኪዳኖችን ይወክላሉ።
‹በሲና ተራራ› ሙሴ እዚያ ለነበሩ እስራኤላውያን የሰጠው ሕግ የሕግ ማሳያ ነው ፡፡ አት: - "ሙሴ ለእስራኤል ሕግን የሰጠበት በሲና ተራራ ላይ" (የበለስ_ስኔክዶቼን ይመልከቱ)
ጳውሎስ ህጉን እንደ ሰው አድርጎ ይመለከታል። አት: - “በዚህ ቃል ኪዳን ስር ያሉ ሰዎች ሕጉን እንደሚታዘዙ ባሪያዎች ናቸው” (የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር) ተመልከት
"ስዕል ነው"
አጋር አጋርና ልጆችዋ ከእሷ ጋር ባሪያዎች ናቸው ፡፡ አት: - እንደ ኢየሩሳሌም እንደ ገዛ ባሪያ ናት ፣ ልጆችዋም ከእሷ ጋር ባሪያዎች ናቸው (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ለታ)
እዚህ “ነፃ” ማለት የታሰረ እንጂ ባርያ አይደለም።
"ደስተኛ ሁኑ"
እዚህ “እርስዎ” መካን ሴትን ያመለክታል እና ነጠላ ነው። (ይመልከቱ: የበለስ_ዮዎ)
በ1፡1 ላይ እንዳለው ተርጉሙት
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች ገላትያኖች የእግዚአብሔር ልጆች ሆነዋል 1) በእግዚአብሔር ቃል በማመን (UDB) ወይም 2) እግዚአብሔር ለአብርሃም የገባውን ቃል ለመፈፀም ተዓምራትን ስለ ሠራ በመጀመሪያ በመጀመሪያ ለአብርሃም ወንድ ልጅን ከዚያም ገላትያንም የአብርሃምን ልጆች በመፍጠር እና ስለሆነም የእግዚአብሔር ልጆች ፡፡
ይህ የሚያመለክተው አጋርን ሚስት አድርጎ በመውሰድ አብርሃም የእስማኤል አባት መሆንን ነው ፡፡ አት: - “በሰው ድርጊት” ወይም “ሰዎች በሠሩት ነገር ምክንያት” (ይመልከቱ።
“መንፈስ ቅዱስ በሆነ ነገር”
በ1፡1 ላይ እንዳለው ይተርጉሙ
የቀሩትን ቃላት እዚህ ውስጥ መሞላት ይቻላል ፡፡ ግን ይልቁን እኛ የነፃይቱ ሴት ልጆች ነን ”(ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ሊሲስ)
1 ክርስቶስ ነጻ ያወጣን በነጻነት እንድንኖር ነው ። ስለዚህ ጸንታችሁ ቁሙ፥ እንደገና በባርነት ቀንበር አትጠመዱ። 2 እኔ ጳውሎስ የምለውን ተመልከቱ ብትገረዙ ክርስቶስ በምንም ዓይነት መልኩ አይጠቅማችሁም። 3 የተገረዘ ሁሉ ህግን ሁሉ የመፈጸም ግዴታ አለበት ብዬ እንደገና እመሰክራለሁ። 4 በህግ ልትጸድቁ የምትደክሙ ሁላችሁ የእግዚአብሔር ጠላቶች ሆናችኋል፤ከጸጋም ርቃችኋል። 5 ምክንያቱም እኛ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት የጽድቅን ዋስትና ስለምንጠብቅ ነው። 6 በክርስቶስ ኢየሱስ ከፍቅር የሆነ እምነት እንጂ መገረዝም ሆነ አለመገረዝ ምንም ትርጉም የለውም። 7 በጥሩ ሁኔታ ትሮጡ ነበር። ታዲያ ለእውነት ከመታዘዝ ያስቆማችሁ ማነው? 8 ይህን እንድታደርጉ የሚያደርግ ጉትጎታ ከጠራችሁ የመጣ አይደለም። 9 ትንሽ እርሾ ሊጡን በሙሉ እንዲቦካ ያደርጋል። 10 በሌላ መልኩ እንደማታስቡ በጌታ እተማመንባችኋለሁ። ግራ የሚያጋባችሁ ማንም ይሁን ማን ፍርዱን ይቀበላል። 11 ወንድሞች ሆይ እስከአሁን ተገረዙ እያልኩ የምሰብክ ቢሆን ለምን እሰደድ ነበር? እንግዲያውስ የመስቀሉ እንቅፋት ይደመሰሳል። 12 የሚያስቷችሁ እራሳቸው ሄደው በተሰለቡ ብዬ እመኛለሁ። 13 ወንድሞች ሆይ እግዚአብሔር የጠራችሁ ለነጻነት ነው። ብቻ ነጻነታችሁን ለሥጋ ፈቃድ አትጠቀሙበት፥ በዚያ ፈንታ እርስ በእርሳችሁ በፍቅር አንዳችሁ አንዳችሁን አገልግሉ። 14 ምክንያቱም ህግ ሁሉ «ባልንጀራህን እንደራስህ ልትወድ ይገባል» 15 በሚለው ትዕዛዝ የተጠቀለለ ነው። 16 በመንፈስ ተመላለሱ የሥጋን ክፉ ምኞት አትፈጽሙ እላችኋለሁ። 17 ምክንያቱም ሥጋ ከመንፈስ ተቃራኒ መንፈስም ከሥጋ ተቃራኒ ነገር ይመኛሉና ነው። 18 እነዚህ እርስ በእርሳቸው ስለሚቀዋወሙ በውጤቱ እናንተ የምትፈልጉትን ለማድረግ አትችሉም። 19 እንግዲህ የሥጋ ስራዎች የተገለጡ ናቸው። እነዚህም አስቀድሜ እንዳስጠነቀኩዋችሁ 20 ዝሙት፣እርኩሰት፣ክፉ ምኞት፣ጣዖትን ማምለክ፣ምዋርት፣ጥል፣ክርክር፣ቅናት፣ በቁጣ መገንፈል፣አድመኛነት፣መለያየት፣ 21 መናፍቅነት፥ ምቀኝነት፥ መግደል፥ስካር፥ ዘፋኝነትና የመሳሰሉት ናቸው፥ ፥አስቀድሜ እንደነገርኳችሁ እነዚህን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። 22 የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፣ ሠላም፣ ትዕግሥ፣ ቸርነት፥ መልካምነት፥ እምነት፥ 23 የውሃት፥ ራስን መግዛት ናቸው። ህግ እነዚህን አይቃወም። 24 የክርስቶስ ኢየሱስ የሆኑት ሥጋን ከክፉ ስሜቱና መሻቱ ጋር ሰቅለውታል። 25 በመንፈስ የምንኖር ከሆነ በመንፈስ እንመላለስ። 26 አንታበይ፣ እርስ በእርሳችን ለክፉ አንነሳሳ፣ አንቀናና።
ሁሉም ሕጎች እንደ እኛ ጎረቤቶቻችንን በመውደድ የተሟላ በመሆኑ ክርስቶስ አማኞች በክርስቶስ ነፃነታቸውን እንዲጠቀሙ በማስታወስ ይህንን ምሳሌ ተጠቅሟል ፡፡
በቀደሙት ቁጥሮች ላይ ከተገለፀው ባርነት በተቃራኒ ትርጉሙ “ነፃነት” ን ማጉላት አለበት ፡፡
ክርስቶስ ነፃ ያወጣን ነፃ እንድንሆን ነው ፡፡
እዚህ ላይ ቆመ ማለት ላለመቀጠል መወሰንን ያሳያል ፡፡ እንዴት እንደማይቀየሩ በግልፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ሌላ ነገር ለሚያስተምሩ ሰዎች ክርክር አይስጡ” ወይም “ነፃ ለመሆን ቁርጥ ውሳኔ ያድርጉ” (የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር ግልፅ) ይመልከቱ
ጳውሎስ ግርዘትን ለአይሁድ እምነት ምሳሌ አድርጎ ይጠቀማል። አት: - "ወደ የአይሁድ ሃይማኖት ብትመለሱ" (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
“አውጁ” ወይም “ምስክርነት”
ጳውሎስ መገረዝ አይሁዳዊ ለመሆን እንደ ተመሳሳዩን ቃል ይጠቀማል። አት: - “አይሁዳዊ ለሆነ ሰው ሁሉ” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
“የታሰረ” ወይም “የታገደ” ወይም “የባርነት”
“ከክርስቶስ ጋር የነበረሽን ግንኙነት ጨርሰሻል”
እዚህ ላይ ጳውሎስ እዚህ ላይ እየተናገረ ነው ፡፡ በሕግ የተጠየቀውን ነገር ለማድረግ በመሞከር ማንም አይሁዳዊ ጻድቅ ሊሆን እንደማይችል በእውነት አስተምሯል ፡፡ አት: - “በሕግ የተጠየቀውን በማከናወን እናንተ ጻድቅ ትሆናላችሁ የምትሉ ሁሉ” ወይም “በሕግ ልትጸድቁ የምትፈልጉ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ.
ያ ጸጋ ከየት እንደመጣ በግልፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር አይራራዎትም” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
እዚህ ላይ እኛ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስንና የክርስቲያኖችን ግርዘት የሚቃወሙትን ነው ፡፡ እሱ ምናልባት ገላትያዎችን ጨምሮ ሊሆን ይችላል። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህም የሆነው ምክንያቱ
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “እኛ ስለ እምነት የጽድቅ ተስፋ በእምነት እንጠብቃለን” ወይም 2) “በእምነት የሚመጣውን ትክክለኛውን የጽድቅ ተስፋ እንጠብቃለን” ፡፡
"እግዚአብሔር ሁልጊዜ ከራሱ ጋር እንዲያጸናን በትዕግሥት እና በትዕግሥት እየጠበቅን ነው ፣ እናም እርሱ እንደሚያደርገው እንጠብቃለን"
እነዚህ አይሁዶች ወይም አይሁዳዊ ያልሆኑ መሆናቸው መገለጫዎች ናቸው ፡፡ አት: - “አይሁዳዊም ሆነም አይሁዳዊ አለመሆን” (ይመልከቱ ፡፡
"ይልቁንም ሌሎችን በመውደድ የምናሳየው እግዚአብሔር በእርሱ ላይ ያለን እምነት ያሳስበዋል"
የሚጠቅም ነው
“ኢየሱስ ያስተማረውን ተግባራዊ እያደረጉ ነው”
“ይህን እንድታደርግ ያሳመነሽ እግዚአብሔር አይደለም ፣ እርሱም የሚጠራው”
የጠራቸው ምን እንደሆነ በግልጽ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እናንተ የእሱ ሕዝብ እንድትሆኑ የሚጠራችሁ” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
አንድን ሰው ማሳመን ማለት ያመነውን እንዲለውጥ እና በተለየ መንገድ እርምጃ እንዲወስድ ማድረግ ነው ፡፡
እኔ የምነግራችሁን ከነገርዎት የተለየ ነገር አያምኑም ”
የሚያስጨንቅህን እግዚአብሔር ይቀጣል "
“እውነቱን እንድታውቁ ያደርጋችኋል” ወይም “በመካከላችሁ ችግር ያስነሳል”
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች የሙሴን ሕግ መታዘዝ እንዳለባቸው የሚናገሩትን ሰዎች ስም አያውቅም ወይም 2) ጳውሎስ የገላትያ ሰዎች “ግራ የሚያጋቡ” ሀብታሞች መሆን አለመሆናቸውን እንዲገነዘቡ አልፈለገም ፡፡ ድሃ ወይም ትልቅ ወይም ትንሽ ወይም ሀይማኖት ወይም ሃይማኖተኛ ያልሆነ
ጳውሎስ ሰዎች እየሰደዱበት መሆኑን አፅን emphasizeት ለመስጠት የሌለበትን ሁኔታ እየገለጸ ነው ምክንያቱም ሰዎች አይሁድ መሆን አለባቸው ብለው እየሰበከ አይደለም ፡፡ ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ AT: - “ወንድሞች ፣ እኔ ገና አይሁዳውያን ስደት እያደረሱብኝ ስለ መገረዝ እንዳልናገር ታውቃላችሁ ፡፡” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር እና በለስ_ማቶ)
በ1፡1 ላይ እንዳለው ተርጉሙት
ጳውሎስ ሰዎች በመስቀል ላይ ባከናወኑት ሥራ እግዚአብሔር ይቅር እንደሚል ስለሚሰብክ ሰዎች ስደት እንደሚያደርሱበት ለማጉላት በሌለበት ሁኔታ እየገለጸ ይገኛል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ኪፖ)
“ሰዎች አሁንም አይሁዳውያን መሆን አለባቸው” እያልኩ ከሆነ
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ስለ መስቀሉ ማስተማር እንቅፋት የለውም” ወይም “የመስቀል ትምህርት ምንም ነገር የሚያሰናክል ነገር የለም” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ማሰናከል ኃጢያትን ይወክላል ፣ እና እንቅፋት ሰዎችን ወደ ኃጢአት የሚወስድ አንድ ነገርን ይወክላል። በዚህ ሁኔታ ኃጢያቱ በእግዚአብሔር ፊት ትክክል እንዲሆን ለማድረግ ፣ ሰዎች ለእኛ ኢየሱስ በመስቀል ላይ እንደሞተ ማመን ብቻ ያስፈልጋቸዋል የሚለውን አስተምህሮ እውነታውን አለመቀበል ነው ፡፡ አት: - “ሰዎች ስለ እውነት እንዲናገሩ የሚያደርጋቸው የመስቀል ትምህርት ተወግ "ል” ወይም “ኢየሱስ በመስቀል ላይ መሞቱን አስመልክቶ ሰዎች ትምህርቱን እንዲተዉ የሚያደርጋቸው ምንም ነገር የለም” (የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር ግልፅ)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ቃል በቃል ፣ የወንዶች አካሎቻቸውን ለመቁረጥ ጃንደረቦች ወይም 2) ዘይቤያዊነት ፣ ከክርስቲያን ማኅበረሰብ ሙሉ በሙሉ ይርቃሉ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ጳውሎስ በ 5፡11 ውስጥ ለቃሉ የተናገረውን ምክንያት እየሰጠ ነው ፡፡
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል። አት: - “እግዚአብሔር ወደ ነፃነት ጠራህ” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “ነፃ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ህዝቡ መረጠህ” ወይም 2) “ነፃ እንድትሆን እግዚአብሔር አዝዞሃል”
በ1፡1 ላይ እንዳለው ተርጉሙት
በእድሉ እና በኃጢያት ተፈጥሮ መካከል ያለው ግንኙነት ይበልጥ በግልፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እንደ ኃጢያተኛ ተፈጥሮዎት ለመምሰል እድል ይሰጡዎታል” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “መላውን ሕግ በአንድ ትእዛዝ ብቻ መግለጽ ይችላሉ ፣ ይህ ነው” ወይም 2) “አንድን ትእዛዝ በመታዘዝ ፣ ሁሉንም ትእዛዛት ታደርጋላችሁ ፣ እና አንደኛው ትእዛዝ ይህ ነው።”
“እርስዎ” ፣ “የእርስዎ” እና “ራስዎ” የሚሉት ቃላት ሁሉም ነጠላ ናቸው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ዮዎ)
ጳውሎስ ኃጢአት በኃጢያት ላይ ቁጥጥርን እንደሚሰጥ ጳውሎስ አብራርቷል ፡፡
በእግር መሄድ የሕይወት ዘይቤ ነው ፡፡ አት-“ሕይወትዎን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ይኑሩ” ወይም “ሕይወትዎን በመንፈስ ላይ በመመካት ኑሩ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
“የአንድን ሰው ምኞቶች ማከናወን” የሚለው ሐረግ “አንድ ሰው የሚፈልገውን አድርግ” የሚል ዘይቤያዊ አነጋገር ነው። አት: - “ኃጢአተኛ ተፈጥሮህ የሚፈልገውን አትፈጽምም” (የበለስ_ ቪዲዮን ተመልከት)
የኃጢያተኛው ተፈጥሮ ሰው ሆኖ ኃጢአት መሥራት እንደፈለገ ተደርጎ ተገልጻል። አት: - “በኃጢአተኛ ተፈጥሮህ ምን ማድረግ ትፈልጋለህ” ወይም “sinfulጢአት ስለሆንክ ምን ልታደርጋቸው ትፈልጋለህ?”
'የሙሴን ሕግ የመታዘዝ ግዴታ አልነበረውም'
“ሥራ” የሚለው የግሪክኛ ስም “እሱ” ከሚለው ግስ ጋር ሊተረጎም ይችላል። አት: - "የኃጢያት ተፈጥሮ ምን ያደርጋል"
የኃጢያተኛው ተፈጥሮ ነገሮችን የሚያደርግ የሚያደርግ ሰው ነው ተብሎ ተገልጻል። አት: - “ሰዎች በኃጢአታቸው ምክንያት የሚያደርጉት” ወይም “ሰዎች ኃጢአተኞች በመሆናቸው ምክንያት የሚያደርጉት” (ይመልከቱ። የበለስ_ከዋክብት)
ለአማኞች እግዚአብሔር ቃል የገባውን ቃል መቀበል ከቤተሰብ አባል ንብረትንና ሀብትን እንደሚወርስ ይገለጻል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ቁጥጥር - ጳውሎስ ሰዎች በሌሎች ሰዎች ሊያዩት ለሚችሉት ዘይቤ እንደ ዘይቤ ይጠቀማል ፡፡ አት-መንፈስ ቅዱስ የሚቆጣጠራቸው ሰዎች ፍቅርን ይገልጣሉ ... እንደ ዛፍ ራስን መግዛትን ያፈራል "(ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር) ፡፡
"መንፈስ ምን ያፈራል"
ጳውሎስ እንደ ሰው ስብዕና በኃጢያት ተፈጥሮአቸው ለመኖር ፈቃደኛ ያልሆኑ ክርስቲያኖችን ይናገራል ፣ እነሱ በመስቀል ላይ ስለገደሉት ፡፡ አት-“በመስቀል ላይ እንደገደሉት አድርገው ከኃጢያት ተፈጥሮው እና ፍላጎቱ ጋር ላለመመኘት እምቢ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቀፎ እና የበለስ_ቁጥር)
የኃጢያት ተፈጥሮው ምኞት እና ምኞት ያለው ሰው እንደሆነ ተደርጎ ተገልጻል። አት: - “የኃጢአታቸው ተፈጥሮ ፣ እና በእሱ ምክንያት ለማድረግ በጣም የፈለጉት ነገር” (ይመልከቱ።
"የእግዚአብሔር መንፈስ በሕይወት እንድንኖር አድርጎናል"
በየቀኑ "መራመድ" ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - "እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውን እና የምናከብርውን ነገር እናደርጋለን ፣ ስለሆነም መንፈስ ቅዱስ እንዲመራን ፍቀድልን" (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
“አለብን”
1 ወንድሞች ሆይ አንድ ሰው ስቶ ቢገኝ መንፈሳዊያን የሆናችሁ እናንት በጨዋነት መንፈስ ልታቀኑት ይገባል።ወደ ፈተና እንዳትገቡ ለራሳችሁም ተጠንቀቁ። 2 የእርስ በእርሳችሁን ሸክም በመሸካከም የክርስቶስን ህግ ፈጽሙ። 3 ምክንያቱም ማንም ምንም ሳይሆን ምንም እንደሆነ ቢያስብ ራሱን ያታልላል። 4 እያንዳንዱ ከሌላው ጋር ሳያነጻጽር የራሱን ሥራ ሊመዝን ይገባል፥ያን ጊዜ የሚመካበት ሊያገኝ ይችላል። 5 እያንዳንዱ የየራሱን ሸክም ይሸከማልና። 6 ቃሉን የሚማር ከመምህሩ ጋር ሁሉን ነገር ይካፈል ዘንድ ይገባዋል። 7 አትታለሉ እግዚአብሔር አይቀለድበትም።ሰው ምንም ነገር ቢዘራ ያንኑ ደግሞ ያጭዳል። 8 በሥጋው የሚዘራ ከሥጋው ውድቀትን ያጭዳል፤በመንፈስ የሚዘራ ግን ከመንፈስ የዘላለምን ህይወት ያጭዳል። 9 በተገቢው ጊዜ ፍሬውን እናጭዳለንና መልካምን ከመስራት አንቦዝን። 10 ስለዚህም ባገኘነው አጋጣሚ ሁሉ ለሰው ሁሉ በተለይም ለእምነት ቤተሰቦች መልካምን እናድርግ። 11 በገዛ እጅ ጽህፈቴ ምን ዓይነት ትልልቅ ቃላት እንደጻፍኩላችሁ ተመልከቱ። 12 እነዚያ በሥጋ መልካም መስለው የሚታዩ ስለክርስቶስ መስቀል መከራ ላለመቀበል ብለው እንድትገረዙ ያስገድዱዋችኋል።የተገረዙት እራሳቸው ህጉን አይጠብቁ፣ 13 ነገር ግን እናንተን እንድትገረዙ በማድረጋቸው ጉራ ለመንዛት እንድትገረዙ ይፈልጋሉ። 14 ዓለም ለእኔ ከተሰቀለበት እኔም ለዓለም ከተሰቀልኩበት ከክርስቶስ መስቀል በስተቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ። 15 አዲስ ፍጥረት መሆን እንጂ መገረዝም ሆነ አለመገረዝ ምንም አይጠቅምም። 16 በዚህ ሥርዓት ለሚሄዱ ሁሉ እንዲሁም የእግዚአብሔር ለሆነችው ለእስራኤል ሠላምና ምህረት ይሁን። 17 የክርስቶስን ምልክት በሥጋዬ ተሸክሜአለሁና ከእንግዲህ ማንም አይረብሸኝ። 18 ወንድሞች ሆይ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከመንፈሳችሁጋር ይሁን። አሜን!
ጳውሎስ አማኞችን ሌሎች አማኞችን እንዴት መያዝና እግዚአብሔር እንዴት ወሮታ እንደሚሰጥ አስተምሯቸዋል።
በ1፡1 ላይ እንዳለው ተርጉሙት
“አንድ ሰው” ወይም “ከመካከላችሁ ማንም”
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) አንድ ሰው በድርጊቱ ውስጥ የተገኘ ሰው ፣ “በኃጢያት ተገኝቷል ፣” ወይም 2) ያ ሰው ክፋትን ለማድረግ ሳይያስብ ኃጢአት ሠርቶ “እጅ ሰጠው ኃጢአት ሠርቷል” ፡፡
“ከእናንተ በመንፈስ የሚመሩ” ወይም “በመንፈስ መሪነት የምትኖሩ”
"የበደለውን ሰው እርማት" ወይም "የበደለውን ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ወደ ትክክለኛው ዝምድና እንዲመለስ አጥብቀው ይመክሩ"
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) መንፈስ እርማትን የሚሰጥ ወይም 2) “በገርነት” ወይም “በደግነት” የሚመራው መንፈስ ነው ፡፡
እነዚህ ቃላት ገላትያንን እያንዳንዳቸውን እንደሚናገር ለማጉላት ሁሉም አንድ ሰው እንደሆኑ አድርገው ይመለከቷቸዋል ፡፡ AT: - “ስለራሳችሁ አስቡ” ወይም “እያንዳንዳችሁን ፣ ስለ ራሳችሁ ጉዳይ ይጨነቁ” እላለሁ ፡፡
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ስለሆነም ምንም ኃጢአት እንዳትሠሩ እንዳትፈታተኑ” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
"ምክንያቱም።" ይህ የሚያሳየው የሚከተለው ቃል የገላትያ ሰዎች 1) “አንዱ የሌላውን ሸክም መሸከም” (6 1) ወይም 2) እነሱ ራሳቸው እንዳልተፈተኑ ተጠንቀቁ (6 1) ወይም 3) “እንዳይታለሉ” ( 5 1) ፡፡
“እሱ በጣም አስፈላጊ የሆነ ሰው ነው” ወይም “እሱ ከሌላው ይበልጣል”
እሱ እሱ አስፈላጊ አይደለም ወይም “እሱ ከሌሎቹ አይሻልም”
እያንዳንዱ ሰው የግድ መሆን አለበት
እያንዳንዱ ሰው የሚፈርደው በገዛ ሥራው ብቻ ነው ወይም “እያንዳንዱ ሰው ለገዛ ሥራው ብቻ ነው ተጠያቂው”
እያንዳንዱ ሰው ያደርጋል
"ሰውየው"
እዚህ ላይ ይህ ማለት እግዚአብሔር “በእግዚአብሔር ቃል” ወይም “በእውነት ቃል” ማለት እግዚአብሔር የተናገረው ወይም ያዘዘውን ሁሉ ማለት ነው ፡፡
መትከል በአንድ ዓይነት ውጤት የሚጠናቀቁ ነገሮችን ማድረጉን ይወክላል ፣ እናም መሰብሰብ አንድ ሰው ያደረገውን ውጤት ያሳያል ማለት ነው። አት: - “አንድ ገበሬ ማንኛውንም የተተከለውን ዘር ፍሬ እንደሚሰበስብ ሁሉ ፣ እያንዳንዱ ሰው የሚያደርገውን ማንኛውንም ነገር ያገኛል” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
እዚህ እዚህ ላይ ጳውሎስ ወንዶችን አልገለጸም ፡፡ "ሰው ... ያ ሰው"
እንደ ኃጢአተኛው ተፈጥሮው ዘር ይተክላሉ። በኃጢያት ተፈጥሮው ምክንያት ይህ ማድረግ የሚፈልገውን ማድረጉን ይወክላል። አት: - “በኃጢያት ተፈጥሮው እንደፈለገው እንደ ዘር ይተክላል” ወይም “በኃጢያቱ ተፈጥሮው ለማድረግ የሚፈልገውን ነገር ያደርጋል” (የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
“ላደረገው ነገር ቅጣትን ይቀበላል” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
የእግዚአብሔር መንፈስ የወደደውን ያደርጋል “(የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
ከእግዚአብሔር መንፈስ እንደ ሽልማት የዘላለም ሕይወት ይቀበላሉ ”
“መልካም ማድረጋችንን መቀጠል አለብን”
ለሌሎች ደህንነት ሲባል መልካም ማድረግ
“በጊዜው” ወይም “እግዚአብሔር በመረጠው ጊዜ”
"በዚህ ምክንያት" ወይም "በዚህ ምክንያት"
“ከሁሉም በላይ ... ለእነዚያ” ወይም “በተለይም ... ለእነዚያ”
"በእምነት በእምነት የእግዚአብሔር ቤተሰብ አባላት የሆኑት"
ጳውሎስ ይህንን ደብዳቤ ሲዘጋ ፣ ሕጉ የማያድን እና የክርስቶስን መስቀል ማስታወስ እንዳለበት አንድ ተጨማሪ ማሳሰቢያ ሰጣቸው ፡፡
ይህ ማለት ጳውሎስ አፅን wantsት ለመስጠት ይፈልጋል 1) የሚቀጥለውን መግለጫ ወይም 2) ይህ ደብዳቤ የመጣው ከእርሱ ነው ፡፡
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ምናልባት ጳውሎስ ምን እንደሚጽፍ የነገረውን ይህን ደብዳቤ አብዛኛው ሰው የፃፈው ረዳት ሳይኖረው አይቀርም ፣ ግን ጳውሎስ ራሱ የፃፋውን ይህን የመጨረሻውን ክፍል ጻፈ ወይም 2) ጳውሎስ መላውን ደብዳቤ ራሱ ጻፈ።
"ሌሎች ስለእነሱ እንዲያስቡ" ወይም “ሌሎች ጥሩ ሰዎች ናቸው ብለው እንዲያስቡ አድርጓቸዋል”
“በሚታይ ማስረጃ” ወይም “በእራሳቸው ጥረት”
"በኃይል" ወይም "በከፍተኛ ተጽዕኖ"
አይሁዶች እንዳያሳድዱት "ክርስቶስ መስቀል ብቻውን ሰዎችን ያድናል"
እዚህ ላይ መስቀል በመስቀል ላይ በሞተ ጊዜ ክርስቶስ ለእኛ ያደረገውን ያሳያል ፡፡ አት: - “ኢየሱስ በመስቀል ላይ ያከናወነው ሥራ” ወይም “የኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ” (ይመልከቱ። የበለስ.
እንድትገረዙ የሚጠይቁአችሁ ሰዎች
"ህግን ለመጠበቅ በሚሞክሩ ሰዎች ላይ ስለጨምሩህ ይኮሩ ዘንድ"
“ከመስቀል ውጭ በሌላ በየትኛውም ነገር መመካት አልፈልግም” ወይም “በመስቀል ብቻ ልኮራ”
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ዓለምን እንደ ቀድሞው አስባለሁ” ወይም “ዓለምን በመስቀል ላይ እንደገደለው ወንጀለኛ አደርገዋለሁ” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ከዚህ በፊት ካለው ሐረግ ውስጥ “ተሰቅለዋል” የሚሉት ቃላት ተረድተዋል ፡፡ አት: - "እኔ ለዓለም ተሰቅዬአለሁ" (የበለስ_ሊሲስስ ይመልከቱ)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “ዓለም እንደ ቀድሞው እንደቆየችኝ” ወይም 2) “እግዚአብሔር በመስቀል ላይ እንደገደለው ወንጀለኛ ቆጠረችኝ”
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) የዓለም ሰዎች ፣ ለእግዚአብሄር ምንም ደንታ የሌላቸውም ወይም 2) ለእግዚአብሄር ምንም ግድየለሾች የሚያሳስባቸው ነገር አስፈላጊ ናቸው ፡፡
“ለእግዚአብሔር አስፈላጊ ነው”
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) አዲስ ክርስቶስ አማኝ ወይም 2) የአማኝ አዲስ ሕይወት።
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) አማኞች በአጠቃላይ የእግዚአብሔር እስራኤል ናቸው ወይም 2) “ሰላምና ምሕረት በአህዛብ አማኞችና በእግዚአብሔር እስራኤል ላይ ይሁን” 3) “ህጉን ለሚከተሉ እና ምህረት ሊሆኑ ይችላሉ ፡፡ በእግዚአብሔር እስራኤል ላይ ይሁን።
ይህ ደግሞ “በመጨረሻም” ወይም “ይህን ደብዳቤ እንደጨረስኩ” ማለት ይችላል ፡፡
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች እንዳያስቸግሩት ፣ “ይህን እያዘዝኩህ ነው ፣ አትጨነቅ” ወይም 2) ጳውሎስ ሁሉንም ሰዎች እንዳያሳዝኑት ለገላትያኖች እየነገራቸው ነው ፣ “እኔ ነኝ ይህን ሁሉ ለሁሉም በማዘዝ “አታስጨንቁኝ ፣” ወይም 3) ጳውሎስ ምኞቱን እየገለጸ ነው ፣ “ማንም እንዲያስቸገረኝ አልፈልግም ፡፡
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “ስለእነዚህ ጉዳዮች ለእኔ ንገሩኝ” (ዩ.አር.ቢ.) ወይም 2) “ችግር ያመጣብኛል” ወይም “ጠንክሮ ስጠኝ” ፡፡
እኔ የኢየሱስን አገልግሎት በማግኘቴ በሰውነቴ ውስጥ የተፈወሱ ቁስሎች አሉኝ ”ወይም“ እኔ የኢየሱስ በመሆኔ አሁንም እኔ በሰውነቴ ውስጥ የተፈወሰው የቁስል ምልክት አለኝ ፡፡
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) በጦር ወታደር በወታደር ወይም በአገልጋይ በአደገኛ ሥራ ላይ ከደረሰባቸው ቁስል ቁስሎች ወይም 2) የባሪያ መለያ ምልክት የሆኑ ምልክቶች ፡፡
"ጌታ ኢየሱስ ለመንፈሳችሁ ደግ እንዲሆን እጸልያለሁ"
በ1፡1 ላይ እንዳለው ተርጉሙ
1 በእግዚአብሔር ፈቃድ የክርስቶስ ኢየሱስ ሐዋርያ ከሆነው ከጳውሎስ፥ ለእግዚአብሔር ለተለዩት በክርስቶስ ኢየሱስ ለሚያምኑ በኤፌሶን ለሚኖሩ ቅዱሳን፤ 2 ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን። 3 በክርስቶስ ኢየሱስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባትና አምላክ ይባረክ። 4 እግዚአብሔር በክርስቶስ የምናምነውን እኛን ዓለም ከመፈጠሩ በፊት መርጦናል። ይህም በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን እንሆን ዘንድ ነው 5 እግዚአብሔር በፍቅር በኢየሱስ ክርስቶስ የራሱ ልጆች አድርጎ ሊቀበለን አስቀድሞ ወሰነን። ይህንንም የፈጸመው ሊያደርግ የፈለገውን ነገር ለማድረግ ደስ ስለተሰኘ ነበር። 6 ይህ ሁሉ የተፈጸመው በሚወደው ልጁ እንዲያው በነጻ ስለ ተሰጠን ክቡር ጸጋው እግዚአብሔር ይመሰገን ዘንድ ነው። 7 እንደ ጸጋው ባለጠግነት መጠን በሚወደው ልጁ ደም ቤዛነትን ይኸውም የሐጢአት ይቅርታን አገኘን። 8 ይህም ጸጋ በጥበብና በማስተዋል ሁሉ ተትረፍርፎ ተሰጠን። 9 በክርስቶስ በተገለጠው ፈቃዱ መሠረት እግዚአብሔር በዕቅዱ ውስጥ ያለውን የተሰወረውን እውነት እንድናውቅ አድርጎናል፤ 10 ዕቅዱን የሚፈጽምበት ጊዜ ሲድርስ በሰማይና በምድር ያሉትን ነገሮች ሁሉ በአንድ ላይ በክርስቶስ ስር ይጠቀልላል። 11 ሁሉንም ነገር እንደ ገዛ ፈቃዱ በሚያደርገው ዕቅድ መሠረት በክርስቶስ ተመረጥን፤ አስቀድሞም ተወሰንን 12 ይህም የሆነው በክርስቶስ በማመን ቀዳሚ የሆንነው እኛ ለክብሩ ምስጋና ይሆን ዘንድ እንድንኖር ነው። 13 ባመናችሁበትና እንደ ተሰጠው ተስፋ በመንፈስ ቅዱስ በታተማችሁበት በክርስቶስ አማካይነት የመዳናችሁ ወንጌል የሆነውን የእውነት ቃል የሰማችሁት በክርስቶስ ነው 14 ለክብሩ ምስጋና እንዲሆን ተስፋ የተደረገው ሀብት በእጅ እስገሚገባ ድረስ መንፈስ ቅዱስ የርስታችን ዋስትና የሚሆን መያዣ ነው። 15 ስለዚህ በጌታ ኢየሱስ ስላላችሁ እምነትና ለእርሱም ቅዱሳን ሁሉ ስላላችሁ ፍቅር ከሰማሁበት ጊዜ አንስቶ 16 ስለ እናንተ እግዚአብሔርን ማመስገንና እናንተንም በጸሎቴ ማስታወስ አላቋረጥሁም ። 17 የክብር አባት፥የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን ለማወቅ የሚያስችላችሁን የጥበብ እና የመገለጥ መንፈስ እንዲሰጣችሁ እጸልያለሁ፤ 18 የምጸልየውም የመጠራታችን አስተማማኝነት እና በእርሱ ቅዱሳን መካከል የርስቱ ክብር ባለጠግነት ምን እንደሆነ ታውቁ ዘንድ የልባችሁ ዐይኖች እንዲበሩ 19 እንዲሁም እንደ ኀይሉ ብርታት አሠራር በእኛ በምናምነው ውስጥ የሚሠራው የኀይሉ ታላቅነት ምን እንደሆነ እንድትረዱ ነው። 20 ይህም እግዚአብሔር ከሙታን ባስነሳውና በሰማያዊ ስፍራ በቀኙ እንዲቀመጥ ባደረገው ጊዜ በክርስቶስ ውስጥ የታየው ኀይል ነው። 21 ክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በአብ ቀኝ የተቀመጠውም ከማንኛውም ግዛት፥ ሥልጣን፥ኀይልና ጌትነት እንዲሁም በዚህ ዘመን ብቻ ሳይሆን በሚመጣውም ዘመን ቢሆን ሊሰየም ከሚችለው ስም ሁሉ በላይ ነው። 22 እግዚአብሔር ሁሉም ነገር በክርስቶስ እግር ሥር እንዲገዛ አድርጓል፤ እርሱንም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሁሉም ነገር ላይ ራስ አድርጎ ሾሞታል 23 ቤተ ክርስቲያንም ሁሉንም ነገር በሁሉም መንገድ የሚሞላው የእርሱ ሙላት የሆነች አካሉ ናት።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ ይህን ደብዳቤ የሚከፍተው በእግዚአብሔር ፊት ያላቸውን የአማኞችን ደረጃ እና ደህንነት በመናገር ነው። በእግዚአብሔር ፈቃድ፡ "በእግዚአብሔር ፈቃድ" ወይም "በእግዚአብሔር ምርጫ" ለእግዚአብሔር ለተለዩት ትኩረት፡ "በግብረ ገብ ያለ ነቀፋ መሆን" ወይም "ቅዱሳን" በክርስቶስ ኢየሱስ ለሚያምኑ፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባትና አምላክ ይባረክ፡ ትኩረት፡ "የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክና አባት እንባርከው" የባረከን፡ ትኩረት፡"እግዚአብሔር ባርኮናልና" "ባረከን" የሚለው ቃል ጳውሎስን እና በኤፌሶን ያሉትን አማኞች ያጠቃልላል። በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ፡ ትኩረት፡"ከእግዚአብሔር መንፈስ የሚመጣ በረከት ሁሉ" በክርስቶስ፡ "በክርስቶስ" እና ተመሳሳይ አገላለጦች ዘይቤያዊ አባባሎች ሲሆኑ በተደጋጋሚ በአዲስ ኪዳን ደብዳቤዎች ውስጥ የምናገኛቸው ናቸው። እንዚህ አባባሎችም በክርስቶስና እና በእርሱ በሚያምኑት መካከል ጠንካራ ግንኙነት የሚያሳዩ ናቸው። (ተመልከት፡ [[rc://*/tw/bible/kt/inchrist]]) ቅዱሳንና ነውር የሌለን እንሆን ዘንድ፡ ጳውሎስ በእግዚአብሔር ልንሆን የምንችላቸውን ሁለት ባህሪያት ያሳየናል።
እግዚአብሔር * የራሱ ልጆች አድርጎ ሊቀበለን አስቀድሞ ወሰነን፡
"ሊቀበለን" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን፥የኤፌሶንን ቤተክርስቲያን እና በክርስቶስ ውስጥ ያሉትን አማኞች ነው። ትኩረት፡"እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ ልጆች አድርጎ ሊቀበለን ወሰነ" ልጆች አድርጎ ሊቀበለን፡ እዚህ ጋር"ልጆች አድርጎ ሊቀበለን" የሚለው ሃሳብ ወደ እግዚአብሔር ቤተሰብነት መቀላቀልን አመልካች ነው። በኢየሱስ ክርስቶስ፡ እግዚአብሔር አማኞችን ወደ ራሱ ቤተሰብ የሚያመጣው በኢየሱስ ክርስቶስ ስራ አማካኝነት ነው። ይህንንም የፈጸመው ሊያደርግ የፈለገውን ነገር ለማድረግ ደስ ስለተሰኘ ነበር፡ "የፈፀመው" እና "ሊያደርግ" የሚሉት ቃላት እግዚአብሔርን አመላካች ናቸው። በሚወደው በልጁ፡ "የእግዚአብሔር ውድ" ወይንም "ኢየሱስ ክርስቶስ"
በሚወደው ልጁ፡ "በእግዚአብሔር ውድ፥በኢየሱስ ክርስቶስ" ቤዛነትን*አገኘን "አገኘን" የሚለው ቃል ሁሉንም አማኞች ነው።
ፀጋ*ተትረፍርፎ፡ "የእግዚአብሔር ፀጋ ታላቅነት" ወይም "የእግዚአብሔር ፀጋ መትረፍረፍ" በጥበብና በማስተዋል ሁሉ፡ እግዚአብሔር ለአማኞች ታላቅ ጥበብ እና ማስተዋል ሰጥቷል። ትኩረት፡"የበዛ ጥበብ እና ማስተዋል።"
በፈቃዱ መሰረት፡ "እንደ እርሱ ደስታ" በክርስቶስ፡ "በክርስቶስ" እና ተመሳሳይ አገላለጦች ዘይቤያዊ አባባሎች ሲሆኑ በተደጋጋሚ በአዲስ ኪዳን ደብዳቤዎች ውስጥ የምናገኛቸው ናቸው። እንዚህ አባባሎችም በክርስቶስና እና በእርሱ በሚያምኑት መካከል ጠንካራ ግንኙነት የሚያሳዩ ናቸው። (ተመልከት፡ [[rc://*/tw/bible/kt/inchrist]]) በእቅዱ ውስጥ ያለውን፡ ትኩረት፡"ትክክለኛው ጊዜ ሲደርስ" ዕቅዱን የሚፈፅምበት ጊዜ ሲደርስ፡ ትኩረት፡"እርሱ እቅዱን ይፈፅማል"
ተመረጥን፡ "እግዚአብሔር የእርሱ ርስት እንሆን ዘንድ መረጠን" ወይም እግዚአብሔር የእርሱን ርስት እንቀበል ዘንድ መረጠን።" አስቀድሞም ተወሰንን፡ "ተወሰንን" የሚለው ቃል ጳውሎስን እና የአይሁድን በክርስቶስ አማኝ ህዝብ እንጂ አህዛብን በሚያደርገው ዕቅድ፡ "የእግዚአብሔር እቅድ" እንደ ገዛ ፈቃዱ በሚያደርገው ዕቅድ መሠረት፡ "የእግዚአብሔር ፈቃድ"
የእውነት ቃል የሰማችሁት በክርስቶስ ነው፡ ትኩረት፡"በክርስቶስ በማመናችሁ በእርሱ እንደዳናችሁ ሰማችሁ" በክርስቶስ አማካይነት የመዳናችሁ ወንጌል የሆነውን፡ ትኩረት፡"ክርስቶስ የመዳናችሁ ወንጌል ነው" ባመናችሁበትና፡ ትኩረት፡ "እናንተም በክርስቶስ አመናችሁ" በመንፈስ ቅዱስ በታተማችሁበት፡ ደብዳብ በሰም እንድሚታሸግ እና ማን እንድላከው ምልክት እንድሚደረግበት፥እግዚአብሔርም እንዲሁ በመንፈስ ቅዱስ አትሞ ባለቤትነቱን ያሳያል። ትኩረት፡ "እግዚአብሔር በተስፋው ቅዱስ መንፈስ አትሟችኋል" (ተመልከት፡ እንዲሁም
መንፈስ ቅዱስ የርስታችን ዋስትና የሚሆን መያዣ፡ እግዚአብሔር በትክክለኛው ጊዜ መንፈስ ቅዱስን የዘላለም ህይወት ተስፋ ስጦታ አድርጎ ሰጠን። ትኩረት፡"መንፈስ ቅዱስ ዋስትና ነው።" ተስፋ የተደረገው ሀብት በእጅ እስገሚገባ ድረስ፡ ትኩረት፡ "የርስታችንን ሃብት እስክናገኝ ድረስ" ወይንም "ርስታችንን እስክንቀበል ድረስ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ ለኤፌሶን አማኞች ከመፀለዩም በላይ አማኞች በክርስቶስ ውስጥ ስላላቸው ሃይል ያመሰግናል። ስለዚህ፡ "በዚህ ምክንያት" ለእርሱም ቅዱሳን ሁሉ ስላላችሁ፡ "ለክርስቶስ ቅዱሳን ላላችሁ ፍቅር" ወይም "ለአማኞች ሁሉ ላላችሁ ፍቅር" እግዚአብሔርን ማመስገን*አላቋረጥሁም፡ ትኩረት፡"ማመስገኔን እቀጥላለሁ"
እርሱን ለማወቅ * የጥበብ እና የመገለጥ መንፈስ:
ትኩረት፡"የእርሱን መገለጥ መረዳት የሚያስችል መንፈሳዊ ጥበብ" የልባችሁ ዐይኖች እንዲበሩ፡ "የልባችሁ አይኖች እንዲበሩ" የሚለው ሃረግ የአንድን ሰው የማስተዋል ሁኔታ ይገልፃል። ትኩረት፡"ማስተዋልን አግኝታችሁ እንዲበራላችሁ"
የመጠራታችን ተስፋ፡ "የጥሪያችን ተስፋ" የርስቱ ክብር ባለጠግነት፡ "የርሱ የከበረ ርስት ባልጠግነት" ወይም "የከበረው ርስቱ ብዛት" በእርሱ ቅዱሳን፡ ይህ ሃሳብ ያለ ነቀፋ መሆንን፥መለየትን እና መቀደስን ያጠቃልላል።
የኀይሉ ታላቅነት ምን እንደሆነ፡ የእግዚአብሔር ሃይል ከሌሎች ሃይል ሁሉ ይበልጣል። እንደ ኀይሉ ብርታት አሠራር፡ ትኩረት፡"ለእኛ የሚሰራልን ታላቅ ሃይል" በቀኙ እንዲቀመጥ፡ "ክርስቶስን በእግዚአብሔር ቀኝ አስቀመጠው" ወይም "ክርስቶስ በክብር ስፍራ ተቀመጠ" ከማንኛውም ግዛት፥ ሥልጣን፥ኀይልና ጌትነት *በላይ፡ እነዚህ የተለያዩ የልዕለ ተፈጥሮ አካላትን ማለትም ሁለቱም የመላዕክትም ሆነ የዲያብሎስን ደረጃዎች ያሳያሉ። በዚህ ዘመን፡ "በዚህ ጊዜ" በሚመጣውም ዘመን፡ "ወደፊት"
እግዚአብሔር * እንዲገዛ አድርጓል፡
"እግዚአብሔር አስቀመጠለት" "እግዚአብሔር አደረገለት" (UDB) በክርስቶስ እግር ሥር፡ እዚህ ጋር "እግር" የክርስቶስን ጌትነት፥ስልጣን እና ሃይል ይወክላል።" በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሁሉም ነገር ላይ ራስ አድርጎ ሾሞታል፡ "ራስ" የሚያመለክተው መሪነትን ወይም ሃላፊነትን ነው። ትኩረት፡"በቤተክርስቲያን ውስጥ ባሉ ነገሮች ላይ ሁሉ ይገዛል" የእርሱ * አካሉ፡
ብዙውን ጊዜ የክርስቶስ አካል የሚለው ቤተክርስቲያንን ነው። በሁሉም መንገድ የሚሞላው የእርሱ ሙላት፡ ትኩረት፡"ክርስቶስ ለነገሮች ሁሉ ህይወት እንደሚሰጥ ቤተክርስቲያኑን በህይወት እና በሃይል ይሞላታል"
1 እንግዲህ እናንተ ከበደላችሁና ከሓጢአታችሁ የተነሳ የሞታችሁ ነበራችሁ። 2 በዚያን ጊዜ የዚህን ዓለም ክፉ መንገድ በመከተል፥ በአየር ላይ ባሉት ኀይላት ላይ ገዥ ለሆነው እንዲሁም በማይታዘዙት ልጆች ላይ ለሚሠራው መንፈስ እየታዘዛችሁ ትኖሩ ነበር። 3 በአንድ ወቅት እኛ ሁላችን ለሥጋችን ክፉ ምኞት እየታዘዝንና ፈቃዱን እየፈጸምን፥ የአእምሮአችንንም ሐሳብ እየተከተልን በእነዚህ በማያምኑት ሰዎች መካከል እንኖር ነበር፤ በተፈጥሮአችንም እንደሌሎቹ የቁጣ ልጆች ነበርን። 4 ነገር ግን እግዚአብሔር ምሕረት በማድረግ ባለጠጋ ስለሆነ፥ ከወደደን ከታላቅ ፍቅሩ የተነሳ 5 በበደላችን ሙታን በነበርንበት ጊዜ እንኳ ከክርስቶስ ጋር አዲስ ሕይወት ሰጠን፤የዳናችሁትም በጸጋ ነው፤ 6 ከእርሱም ጋር አስነሳን፤በሰማያዊ ስፍራም ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር እንድንቀመጥ አደረገን። 7 ይህንንም ያደረገው፥በክርስቶስ ኢየሱስ በቸርነቱ የገለጠውን የጸጋው ባለጠግነት ምን ያህል ታላቅ እንደሆነ በሚመጣው ዘመን ለእኛ ያሳይ ዘንድ ነው። 8 የዳናችሁት በእምነት አማካይነት በጸጋ ነውና ፤ ይህ ከእግዚአብሔር ያገኛችሁት ስጦታ እንጂ ከእናንተ የሆነ ነገር አይደለም። 9 ማንም ሰው እንዳይመካ በሥራ የተገኘ ነገር አይደለም 10 ምክንያቱም እግዚአብሔር ከዘመናት በፊት እንድንፈጽመው ያዘጋጀውን መልካም ሥራ ለመሥራት በክርስቶስ ኢየሱስ የተፈጠርን የእግዚአብሔር እጅ ሥራዎች ነን። 11 ስለዚህ በአንድ ወቅት በአካል ላይ በሰው እጅ የሚከናወነውን መገረዝ ስላገኙ «የተገረዙ» በሚባሉት ዘንድ «ያልተገረዙ» ተብላችሁ የምትጠሩ በትውልድ አሕዛብ የነበራችሁ እንደሆነ አስታውሱ። 12 በዚያን ጊዜ ከክርስቶስ ተለይታችሁ፥ የእስራኤል ወገን ከመሆን ርቃችሁ፥ለተስፋውም ኪዳን ባዕድ ሆናችሁ ያለ ተስፋ እና ያለ እግዚአብሔር በዓለም ላይ ትኖሩ እንደነበር ልብ በሉ። 13 ነገር ግን አሁን ከእግዚአብሔር ርቃችሁ የነበራችሁት በክርስቶስ ኢየሱስ በመሆን በክርስቶስ ደም አማካይነት ወደ እግዚአብሔር እንድትቀርቡ ተደርጋችኋል። 14 አይሁድንና አሕዛብን ሁለቱን አንድ ሕዝብ ያደረገ እርሱ ሰላማችን ነውና ፤ በሥጋውም እርስ በርስ የለያየንን የጥል ግድግዳ አፈረሰ። 15 ይኸውም ከሁለቱ ሕዝቦች አንድ አዲስ ሕዝብ በመፍጠር ሰላምን ያደርግ ዘንድ የትእዛዛትንና የሕግ ደንቦችን በሥጋው ሻረ። 16 ይህንንም ያደረገው በመስቀሉ አማካይነት በመካከላቸው የነበረውን ጠላትነት ገድሎ ሁለቱን ሕዝቦች አንድ አካል በማድረግ ከእግዚአብሔር ጋር ለማስታረቅ ነው። 17 ኢየሱስ መጥቶ ርቀው ለነበሩት እና ቀርበው ለነበሩት ለእነዚያ የምሥራቹን ወንጌል ሰበከ፤ ሰላሙንም አወጀ። 18 በኢየሱስ አማካይነት እኛ ሁለታችንም በአንድ መንፈስ ወደ አብ መቅረብ እንችላለንና። 19 ስለዚህ እናንተ አሕዛብ ከቅዱሳንና ከእግዚአብሔር ቤተ ሰብ አባላት ጋር የአንድ አገር ዜጎች ናችሁ እንጂ ከእንግዲህ መጻተኞችና እንግዶች አይደላችሁም። 20 እነዚህ በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ የተመሠረቱ ናቸው፤ የማዕዘኑም ራስ ድንጋይ ክርስቶስ ኢየሱስ ራሱ ነው። 21 ቤተ ሰቡ የሆነው ሕንጻ ሁሉ በኢየሱስ ኀይል አንድ ላይ ተገጣጥሞ ለጌታ ቅዱስ ቤተ መቅደስ ለመሆን ያድጋል። 22 እናንተም እግዚአብሔር በመንፈሱ የሚኖርበት ሕንጻ እንድትሆኑ አብራችሁ በክርስቶስ እየታነጻችሁ ነው።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ አማኞችን ስላለፈው ጊዜ ካስታወሳቸው በኋላ አሁን ደግሞ በእግዚአብሔር ፊት ያላቸውን ሁኔታ ይነግራቸዋል። ከበደላችሁና ከሓጢአታችሁ የተነሳ የሞታችሁ ነበራችሁ፡ የሞተ ሰው በአካሉ ምላሽ መስጠት ሃጢያተኛ ሰዎች እንዴት እግዚአብሔርን መታዘዝ እንደማይችሉ ያሳያል። ከበደላችሁና ከሓጢአታችሁ የተነሳ፡ ሁለቱም "በደል" እና "ሐጢያት" የሚሉት ቃላት የሚያሳዩት አንድ አይነት ነገር ነው። ጳውሎስ እነዚህን ቃላት የሚጠቀመው የሰዎችን ሃጢያት ታላቅነት ነው። እንኖር ነበር፤ ይህ ሰዎች ይኖሩ የነበሩበትን ባህሪ ያሳያል። ትኩረት፡"ቀድሞ ትኖሩ ነበር።" በዚያን ጊዜ የዚህን ዓለም ክፉ መንገድ በመከተል፡ ሐዋርያት "ዓለም" የሚለውን ቃል የሚጠቀሙት ስግብግብነት የሞላበትን ብልሹ የዚህ ዓለም ሰዎችን ባህሪያት ለማሳየት ነው። ትኩረት፡"በዚህ ዓለም ውስጥ እንደሚኖሩት አይነት ስዎች እሴት" ወይም የዚህን ጊዜያዊ ዓለም መርሆች በመከትል" በአየር ላይ ባሉት ኀይላት ላይ ገዥ ለሆነው፡ ይህ ዲያብሎስን ወይም ሰይጣንን ያመለክታል። ለሚሠራው መንፈስ፡ "ለሚሰራው መንፈስ" የሚለው ሃረግ ዲያብሎስ ወይም ሰይጣንን ያመለክታል። ለሥጋችን ክፉ ምኞት እየታዘዝንና ፈቃዱን እየፈጸምን፥ የአእምሮአችንንም ሐሳብ እየተከተልን፡ "ስጋ" እና "አዕምሮ" የሚሉት ቃላቶች መላው ሰውነትን ይወክላል። የቁጣ ልጆች፡ እግዚአብሔር የተቆጣቸው ሰዎች (ተመልከት፡
እግዚአብሔር ምሕረት በማድረግ ባለጠጋ ስለሆነ፡ "እግዚአብሔር በምህረት የተትረፈረፈ ነው" ወይም "እግዚአብሔር ለእኛ እጅግ ሩህሩህ ነው" ከወደደን ከታላቅ ፍቅሩ የተነሳ፡ "ለእኛ ካለው ታላቅ ፍቅር የተነሳ" ወይም "እጅግ በጣም ስለሚወደን" በበደላችን ሙታን በነበርንበት ጊዜ እንኳ ከክርስቶስ ጋር አዲስ ሕይወት ሰጠን፡ ይህ የሚያሳየው የሞተ ሰው ከሞት ካልተነሳ በቀር ምላሽ መስጠት እንደማይችል፤ሃጢያተኛ ሰውም አዲስ መንፈሳዊ ህይወት ካልተቀበለ እግዚአብሔርን መታዘዝ አይችልም። በክርስቶስ ኢየሱስ፡ "በክርስቶስ ኢየሱስ" " እና ተመሳሳይ አገላለጦች ዘይቤያዊ አባባሎች ሲሆኑ በተደጋጋሚ በአዲስ ኪዳን ደብዳቤዎች ውስጥ የምናገኛቸው ናቸው። እነዚህ አባባሎችም በክርስቶስና እና በእርሱ በሚያምኑት መካከል ጠንካራ ግንኙነት የሚያሳዩ ናቸው። (ተመልከት፡ [[rc://*/tw/bible/kt/inchrist]]) በሚመጣው ዘመን፡ "ወደፊት"
የዳናችሁት በእምነት አማካይነት በጸጋ ነውና፡ የእግዚአብሔር ርህራሄ በኢየሱስ በማመን ብቻ ከፍርድ ልንድን የቻልንበት ሁኔታ ነው። ትኩረት፡"በእርሱ በማመናችሁ ምክንያት እግዚአብሔር በፀጋው አዳነን።" የሆነ ነገር አይደለም፡ "የሆነ ነገር" የሚለው ሃረግ ወደ ኋላ "የዳናችሁት በእምነት አማካይነት በጸጋ ነውና" የሚለውን አመላካች ነው። በስራ የተገኘ አይደለም፡ ትኩረት፡"ይህ መዳን በስራ አማካኝነት የተገኝ አይደለም" የእግዚአብሔር እጅ ሥራዎች ነን፡ "ነን" የሚለው ቃል ጳውሎስን እና በኤፌሶን ያሉትን አማኞች ሁሉ ነው። በክርስቶስ ኢየሱስ፡ "በክርስቶስ ኢየሱስ" " እና ተመሳሳይ አገላለጦች ዘይቤያዊ አባባሎች ሲሆኑ በተደጋጋሚ በአዲስ ኪዳን ደብዳቤዎች ውስጥ የምናገኛቸው ናቸው። እነዚህ አባባሎችም በክርስቶስና እና በእርሱ በሚያምኑት መካከል ጠንካራ ግንኙነት የሚያሳዩ ናቸው። (ተመልከት፡ [[rc://*/tw/bible/kt/inchrist]]) ለመስራት፡ ትኩረት፡ "መከተል" ወይም "ማድረግ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ እነዚህን አማኞች ሊያሳስባቸው የሚፈልገው ነገር አህዛብ እና አይሁድ በክርስቶስ እና በመስቀሉ አማካኝነት አንድ እንደሆኑ ነው። በትውልድ አሕዛብ፡ ከአይሁድ ህዝብ ውጪ የሆነውን ያመለክታል። ያልተገረዙ፡ ከአይሁድ ህዝብ ውጪ የሆኑት በህፃንነታቸው የማይገረዙ ስለነበር በአይሁዶች እግዚአብሔርን እንደማይከተሉ ይቆጠሩ ነበር። መገረዝ ፡ ይህ ቃል የአይሁድ ህዝብ 8 ቀን ከሆነው ወንድ ልጅ ጀምሮ የሚያደርጉትን ግዝረት ያመላክታል። ከክርስቶስ ተለይታችሁ፡ ትኩረት፡ "የማያምኑ" በሰው እጅ የሚከናወነውን መገረዝ፡ ግዝረቱ የሚከናወነው በወንድ ህፃናት አካል ላይ ነው። የእስራኤል ወገን ፡ "የእስራኤል ማህበረሰብ" ለተስፋውም ኪዳን ባዕድ ሆናችሁ፡ ትኩረት፡ "የእግዚአብሔርን የተስፋ ኪዳን አታውቁም ነበር"
አሁን * በክርስቶስ ኢየሱስ በመሆን፡
ጳውሎስ የኤፌሶንን አማኞች በክርስቶስ ከማመናቸውና ካመኑ በኋላ ያለውን ልዩነት ያሳያቸዋል። (ተመልከት፡ [[rc://*/tw/bible/kt/inchrist]]) ከእግዚአብሔር ርቃችሁ የነበራችሁት * ወደ እግዚአብሔር እንድትቀርቡ ተደርጋችኋል፡
አማኞቹ ቀደም ብሎ በሐጢያታቸው ምክንያት ከእግዚአብሔር ተለይተው ነበር። አሁን ግን ኢየሱስ በደሙ አማካኝነት ወደ እግዚአብሔር አቅርቧቸዋል። እርሱ ሰላማችን ነውና፡ ትኩረት፡"ኢየሱስ ሰላሙን ሰጥቶናል" በሥጋውም፡ ትኩረት፡ "በመስቀል ሞት በመሞት" የጥል ግድግዳ፡ ትኩረት፡"የጥላቻ ግድግዳ" ወይም "ጤናማ ያልሆን እሳቤ" የለያየንን፡ ይሄ የሚያሳየው ጳውሎስንና የኤፌሶን ሰዎችን እንዲሁም አይሁድ አማኞችንና አህዛቦችን ነው። የትእዛዛትንና የሕግ ደንቦችን በሥጋው ሻረ፡ የኢየሱስ ደም አይሁድ እና አህዛብ በሰላም በእግዚአብሔር ፊት ይኖሩ ዘንድ የሙሴን ህግ ማሟላት ችሏል። አንድ አዲስ ሕዝብ፡ አንድ አዲስ ህዝብ፥የተዋጀ የሰው ዘር ሁለቱን ሕዝቦች* ለማስታረቅ፡
ትኩረት፡"አይሁድንም ሆነ አህዛብን በአንድ ላይ ለማምጣት" በመስቀሉ አማካይነት፡ ይህ በክርስቶስ በመስቀል ሞት አማካይነት ማለት ነው። (ተመልከት፡ በመስቀሉ አማካይነት* የነበረውን ጠላትነት ገድሎ፡
ኢየሱስ አይሁድ እና አህዛብ እርስ በእርሳቸው የሚኖራቸውን ጠላትነት አስወግዷል። እንደሙሴ ህግ እንደገና መኖር አያስፈልጋቸውም።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ ለኤፌሶን አማኞች እያላቸው ያለው በአሁኑ ጊዜ ያሉት አማኞች ከሐዋርያት እና ከነቢያት ጋር አንድ በመሆናቸውም የእግዚአብሔር መንፈስ ቤተ መቅደስ ሆነዋል። ሰላሙንም አወጀ፡ ትኩረት፡ "የሰላም ወንጌል አስታወቀ" ወይም "የሰላም ወንጌል አወጀ" ርቀው ለነበሩት፡ ይህ አህዛብን ወይም አይሁድ ያልሆኑትን አመልካች ነው። ቀርበው ለነበሩት፡ ይህ አይሁድን ያሳያል። በኢየሱስ አማካይነት እኛ ሁለታችንም * መቅረብ እንችላለንና፡
እዚህ ጋር "ሁለታችንም" የሚለው ጳውሎስን አማኝ አይሁድን እና አማኝ የሆኑትን አህዛብ ነው። በአንድ መንፈስ፡ ሁሉም አማኞች፥ አይሁድ እና አህዛብ ወደ እግዚአብሔር አብ መገኘት በዚያው አንድ መንፈስ መግባት ይችላሉ።
እናንተ አሕዛብ ከቅዱሳንና ከእግዚአብሔር ቤተ ሰብ አባላት ጋር የአንድ አገር ዜጎች ናችሁ እንጂ ከእንግዲህ መጻተኞችና እንግዶች አይደላችሁም፡ ልክ ዜጋ ያልነበር ዜጋ እንድሚሆነው ሁሉ ይህ የአህዛብን መንፈሳዊ ሁኔታ ከማመናቸው በፊት እና በኋላ ያለውን ሁኔታ ያሳያል። እንግዶች አይደላችሁም፡ "የውጭ አገር ሰዎች አይደላችሁም" መፃተኞች፡ "ዜጋ ያልሆናችሁ" መሠረት ላይ የተመሠረቱ ናቸው፡ ጳውሎስ የእግዚአብሔርን ቤተሰብ ከህንፃ ጋር ያስተያየዋል። ክርስቶስንም እንደ ማዕዘን ራስ ድንጋይ፥ሐዋርያትን እንደ መስረት እንዲሁም አማኞችን እንደ ውቅር። ቤተሰቡ የሆነው ሕንጻ ሁሉ በኢየሱስ ኀይል አንድ ላይ ተገጣጥሞ ለጌታ ቅዱስ ቤተ መቅደስ ለመሆን ያድጋል፡ ልክ ግንበኛ ድንጋዮቹን በቦታቸው እንደሚገጣጥማቸው፥ጳውሎስ የክርስቶስን ቤተሰብ አሁንም በህንፃ መመሰሉን ይቀጥላል። በእርሱ * በክርስቶስ
"በክርስቶስ ኢየሱስ" " እና ተመሳሳይ አገላለጦች ዘይቤያዊ አባባሎች ሲሆኑ በተደጋጋሚ በአዲስ ኪዳን ደብዳቤዎች ውስጥ የምናገኛቸው ናቸው። እነዚህ አባባሎችም በክርስቶስና እና በእርሱ በሚያምኑት መካከል ጠንካራ ግንኙነት የሚያሳዩ ናቸው። (ተመልከት፡ [[rc://*/tw/bible/kt/inchrist]]) እናንተም እግዚአብሔር በመንፈሱ የሚኖርበት ሕንጻ እንድትሆኑ፡ ይህ አማኞች እርስ በእርስ በመገጣጠም በመደበኛነት እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ ሃይል እንዴት በመካከላቸው እንድሚኖር ይገልፃል።
1 በዚህ ምክንያት አሕዛብ ስለሆናችሁት ስለ እናንተ እኔ ጳውሎስ የክርስቶስ ኢየሱስ እስረኛ ሆኛለሁ። 2 ለእናንተ ጥቅም ሲባል ስለ ተሰጠኝ የእግዚእብሔር ጸጋ መጋቢነት ሰምታችኋል ብዬ አስባለሁ። 3 ቀደም ሲል እንደጻፍሁላችሁ እግዚአብሔር የተሰወረውን ምስጢር በመገለጥ እንዳውቅ አድርጓል። 4 ይህን በምታነቡበት ጊዜ ስለ ክርስቶስ ምስጢር እኔ ያለኝን መረዳት መገንዘብ ትችላላችሁ። 5 ምስጢሩም አሁን በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ለሓዋርያቱ እና ለነቢያቱ የተገለጠው ያህል ባለፉት ዘመናት ለነበሩ ሰዎች አልተገለጠም ነበር። 6 ይህም ምስጢር አሕዛብ በወንጌል አማካይነት አብረው ወራሾች፥ አብረው የካሉ ብልቶች እንዲሁም በክርስቶስ በተገኘው ተስፋ አብረው ተካፋዮች መሆናቸው ነው። 7 እንደ እርሱ ኀይል አሠራር በተሰጠኝ በእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ አገልጋይ ሆኛለሁ። 8 ምንም እንኳ ከቅዱሳን ሁሉ ያነስሁ ብሆንም፥ የማይመረመረውን የክርስቶስ የባለጠግነት ወንጌል ለአሕዛብ እሰብክ ዘንድ ይህ ጸጋ ለእኔ ተሰጠኝ። 9 እንዲሁም የሁሉን ነገር ፈጣሪ በሆነው በእግዚአብሔር ላለፉት ዘመናት ተሰውሮ ስለነበረው ምስጢር የእግዚአብሔር ዕቅድ ምን እንደሆነ ለሁሉም እገልጥ ዘንድ ተሰጠኝ። 10 በዚህም ምክንያት በቤተ ክርስቲያን አማካይነት ብዙ ገጽታ ያለው የእግዚአብሔር ጥበብ በሰማያዊ ስፍራ ላሉት አለቆችና ባለ ሥልጣናት እንዲታወቅ ነው። 11 ይህም የሆነው በጌታችን በክርስቶስ ኢየሱስ በፈጸመው ዘላለማዊ ዕቅዱ መሠረት ነው። 12 በክርስቶስ በማመናችን በእርሱ ሆነን በድፍረትና በልበ ሙሉነት ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እንችላለንና። 13 ስለዚህ ክብራችሁ በሆነው ለእናንተ ስል በምቀበለው መከራ ተስፋ እንዳትቆርጡ እለምናችኋለሁ። 14 በዚህም ምክንያት በአብ ፊት እንበረከካለሁ፤ 15 እርሱም በሰማይና በምድር ላለ ቤተ ሰብ ሁሉ ስያሜ የሰጠ እና እነርሱንም የፈጠረ ነው። 16 የምጸልየውም ትጠነክሩ ዘንድ በውስጣችሁ በሚኖረው በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት እንደ ክብሩ ባለጠግነት መጠን ኀይል እንዲሰጣችሁ ነው። 17 ይህም በእምነት ክርስቶስ በልባችሁ እንዲኖር፥ በፍቅሩ ሥር እንድትሰዱና እንድትታነጹ ነው፤ 18 ደግሞም የክርስቶስ ፍቅር ስፋቱ፥ርዝመቱ፥ከፍታውና ጥልቀቱ ምን ያህል እንደ ሆነ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር መረዳት ትችሉ ዘንድ ነው። 19 እንዲሁም በእግዚአብሔር ፍጹም ሙላት ሁሉ ትሞሉ ዘንድ ፥ ከሰው ዕውቀት ሁሉ በላይ የሆነውን የክርስቶስን ታላቅ ፍቅር እንድታውቁ ነው። 20 እንግዲህ በእኛ ውስጥ እንደሚሠራው ሀይሉ መጠን ሁሉንም ነገር እኛ ከምንለምነው ወይም ከምናስበው በላይ እጅግ አብልጦ ማድረግ ለሚቻለው 21 በቤተ ክርስቲያንና በክርስቶስ ኢየሱስ በትውልዶች ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም ለእርሱ ክብር ይሁን፤አሜን።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ ውድ ኋላ መለስ ብሎ የአይሁድንና የአህዛብን አንድ መሆን ካመላከት በኋላ አሁን ደግሞ አማኞች ቤተ መቅደስ የሆኑበትን የተሰወረ እውነት ያስታውቃል። በዚህ ምክንያት፡ "ለናንተ በተሰጠው ፀጋ ምክንያት" ለእናንተ ጥቅም ሲባል ስለ ተሰጠኝ የእግዚእብሔር ጸጋ መጋቢነት፡ "እግዚአብሔር ለናንተ የሰጠኝን የፀጋ ማስተዳደር ሃላፊነት"
በመገለጥ እንዳውቅ አድርጓል፡ ትኩረት፡"እግዚአብሔር ገልጦልኛል" (ተመልከት፡
ቀደም ሲል እንደጻፍሁላችሁ፡ ጳውሎስ ለነዚህ ሰዎች ቀደም ብሎ አጠር ያለ ደብዳቤ የፃፈ ሲሆን፥የሚያመለክተውም እርሱን ነው። ስለ ክርስቶስ ምስጢር እኔ ያለኝን መረዳት፡ ትኩረት፡"ለዚህ ስውር እውነት ያለኝ መረዳት" ባለፉት ዘመናት ለነበሩ ሰዎች አልተገለጠም ነበር፡ ትኩረት፡"እግዚአብሔር ባለፉት ዘመናት ለነበሩት ሰዎች አላሳወቃቸውም ነበር።" ምስጢሩም አሁን በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት* የተገለጠው፡
ትኩረት፡ "አሁን መንፈስ ቅዱስ ገልጦታል" ወይም "መንፈስ ቅዱስ አሁን እንዲታወቅ አድርጎታል"
አሕዛብ በወንጌል አማካይነት አብረው ወራሾች፥ ይህ ጳውሎስ ቀደም ባሉት ቁጥሮች ሊገልፃቸው የጀመረው ተሰውሮ የነበር እውነት ነው። ክርስቶስን የተቀበሉ አህዛብ ልክ እንድ አይሁድ አማኞች አንድ አይነት ርስት ይቀበላሉ። አብረው የአካሉ ብልቶች፡ ብዙውን ጊዜ ቤተክርስቲያን የክርስቶስ አካል ትባላለች። አገልጋይ ሆኛለሁ፡ "አሁን የእግዚአብሔር አገልጋይ የሆንሁት ወንጌልን ለማዳረስ ነው"
ምንም እንኳ ከቅዱሳን ሁሉ ያነስሁ ብሆንም፥*ይህ ጸጋ ለእኔ ተሰጠኝ፡ ትኩረት፡ "ምንም እንኳ ከእግዚአብሔር ህዝብ በሙሉ የማይገባኝ ታናሽ ብሆንም፥እግዚአብሔር የፀጋውን ስጦታ ቸረኝ" ተሰውሮ ስለነበረው ምስጢር የእግዚአብሔር ዕቅድ ምን እንደሆነ ለሁሉም እገልጥ ዘንድ፡ "የእግዚአብሔርን ህዝብ በሙሉ ስለ እግዚአብሔር እቅድ አስታውቅ ዘንድ" የሁሉ ነገር ፈጣሪ በሆነው በእግዚአብሔር ላለፉት ዘመናት ተሰውሮ ስለነበረው ምስጢር የእግዚአብሔር ዕቅድ ምን እንደሆነ ለሁሉም እገልጥ ዘንድ፡ ትኩረት፡"እግዚአብሔር ሁሉን ከፈጠረ ጀምሮ ለረጅም ዘመን ጠብቆ ያቆየው"
ብዙ ገፅታ ያለው የእግዚአብሔር ጥበብ በሰማያዊ ስፍራ ላሉት አለቆችና ባለ ሥልጣናት እንዲታወቅ ነው፡ ገፅታ ያለው የእግዚአብሔር ጥበብ ትኩረት፡ "እግዚአብሔር ታላቅ የሆነ ጥበቡን በሰማይ ስፍራ ላሉ አለቆችና ስልጣናት የሚያስታውቀው በቤተ ክርስቲያን በኩል ነው" ብዙ ገፅታ ያለው የእግዚአብሔር ጥበብ፡ ገፅታ ያለው የእግዚአብሔር ጥበብ- የእግዚአብሔር ውስብስብ ጥበብ አለቆችና ባለ ሥልጣናት፡ እነዚህ ቃላት ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው። ጳውሎስ ይህንን የተጠቀመው ማንኛውም መንፈሳዊ ፍጥረት የእግዚአብሔርን ጥበብ እንደሚያውቅ ነው። ዘላለማዊ ዕቅዱ፡ "በዘላለማዊ እቅዱ እየጠበቀ" ወይም "ከዘላለማዊ ዕቅዱ ጋር በሚስማማ" በጌታችን በክርስቶስ ኢየሱስ፡ በክርስቶስ አማካኝነት
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ ስለ መከራው እግዚአብሔርን ከማመስገኑም በላይ ስለኤፌሶን አማኞች ይፀልያል። በልበ ሙሉነት * መቅረብ፡
ትኩረት፡"ወደ እግዚአብሔር ፊት ለመቅረብ ድፍረት ማግኘት" በክርስቶስ በማመናችን፡ በክርስቶስ በማመናችን ምክንያት
በዚህም ምክንያት፡ "እግዚአብሔር ይህንን ሁሉ የስራው ለናንተ ስለሆነ" በአብ ፊት እንበረከካለሁ፡ "በአብ ፊት ለፀሎት እንበረከካለሁ" ወይም "በአብ ፊት በትህትና እፀልያለሁ" በሰማይና በምድር ላለ ቤተ ሰብ ሁሉ ስያሜ የሰጠ፡ ስያሜ መስጠት ምናልባት የመፍጠርን ድርጊት ያመለክት ይሆናል። ትኩረት፡"በሰማይና በምድር ሁሉንም ቤተሰብ ስያሜ የሰጠ እና የፈጠረ" እንዲሰጣችሁ: እርሱ በፈቃዱ እንዲሰጣችሁ
በእምነት * በልባችሁ፡
"ልባችሁ" የሚለው የሰውን ነፍስ የሚያመላክት ሲሆን "በ" ደግሞ ማስተላለፊያውን መንገድ ያሳያል፤ይህም ክርስቶስ በአማኞች ልብ ውስጥ በእግዚአብሔር የእምነት ስጦታ አማካኝነት እንደሚኖር አመላካች ነው። በፍቅሩ ሥር እንድትሰዱና፡ ጳውሎስ እምነታቸውን ላይ ስሩን ዘርግቶ እንደተተከለ ዛፍ ወይንም በጥልቅ መሰረት ላይ እንደተገነባ ህንፃ ጋር ያመሳስለዋል። ትኩረት፡ "እንደ ዛፍ ስር ሰዳችሁ እንድትተከሉና እንደ ህንፃ በአለቱ ላይ እንድትገነቡ።"
ከቅዱሳን ሁሉ ጋር፡ "በክርስቶስ የሆኑት አማኞች ሁሉ" ወይም "ቅዱሳን ሁሉ" ከሰው ዕውቀት ሁሉ በላይ የሆነውን የክርስቶስን ታላቅ ፍቅር፡"በልምድ ልናውቀው ከምንችለው በላይ የሆነውን የክርስቶስ ፍቅር ልታውቁ ትችላችሁ"
ለእርሱ፡ "ለእግዚአብሔር" እጅግ አብልጦ፡ እኛ ከምንጠይቀው ወይም ከምንገምተው በላይ እግዚአብሔር ሊያደርግ ይችላል። እኛ ከምንለምነው ወይም ከምናስበው፡ "እኛ" የሚለው ቃል አማኞችን ሁሉ የሚያመለክት ነው።
1 ስለዚህ የጌታ እስረኛ እንደመሆኔ በእግዚአብሔር ለተጠራችሁለት መጠራት የሚገባውን ሕይወት ትኖሩ ዘንድ እለምናችኋለሁ። 2 ይኽውም እርስ በርስ በፍቅር ተቻችላችሁ በፍጹም ትሕትና፥በገርነትና በትዕግሥት እንድትኖሩ ነው። 3 በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ አስፈላጊውን ጥረት ሁሉ አድርጉ። 4 በተጠራችሁ ጊዜ በአንድ ተስፋ እንደተጠራችሁ ሁሉ፥ አንድ አካል እና አንድ መንፈስ አለ፤ 5 አንድ ጌታ፥አንድ እምነት፥አንድ ጥምቀት አለ ፤ 6 ደግሞም ከሁሉ በላይ የሆነ፥በሁሉ የሚሠራ፥ በሁሉ የሚኖር ፥የሁሉም አባት የሆነ አንድ አምላክ አለ። 7 ክርስቶስ ስጦታ መጠን ለእያንዳንዳችን ጸጋ ተሰጥቶናል 8 ይህም የእግዚአብሔር ቃል «ወደ ላይ በወጣ ጊዜ ምርኮኞችን ማረከ፤ለሰዎችም ስጦታ ሰጠ» በማለት እንደሚናገረው ነው። 9 «ወደ ላይ ወጣ» ሲል ደግሞም «ወደ ምድር ጥልቅ ወረደ» ማለት ካልሆነ በቀር ሌላ ምን ሊያመለክት ይችላል? 10 ታች የወረደው ሁሉንም ይሞላ ዘንድ ከሰማያት ሁሉ በላይ የወጣው ያው እርሱ ራሱ ነው። 11 ወንጌል ሰባኪዎችን፥እረኞችን እና አስተማሪዎችን ስጦታ አድርጎ የሰጠ ክርስቶስ ራሱ ነው። 12 ያደረገው የክርስቶስን አካል ለማነጽና ለአገልግሎት ሥራ ቅዱሳንን ለማስታጠቅ ነው። 13 የሚሆነው ሁላችንም የእግዚአብሔርን ልጅ በማመን እና በማወቅ ወደ ሚገኘው አንድነት እንዲሁም ወደ ክርስቶስ ሙላት ልክ እንዳደጉት ሰዎች ሙሉ ሰው ወደ መሆን ደረጃ እስከምንደርስ ድረስ ነው። 14 በሰዎች ረቂቅ ተንኮል እና ማታለል በተዘጋጀ የትምህርት ነፋስ ወዲያና ወዲህ የምንነዳ ሕጻናት መሆን አይገባንም 15 ይልቁንም እውነትን በፍቅር የምንናገር እና ራስ ወደ ሆነው ወደ ክርስቶስ በሁሉም መንገድ የምናድግ ሰዎች መሆን ይጠበቅብናል። 16 የአማኞችን አካል ሁሉ በሚያገናኘው ጅማት እየተያያዘና እየተጋጠመ፥እያንዳንዱም ክፍል የራሱን ተግባር እያከናወነ በፍቅር ያድጋል። 17 እየለመንኋችሁ ይህን የምናገረው፥ ከእንግዲህ በአእምሮአቸው ከንቱነት እንደሚመላለሱት እንደ አሕዛብ እንዳትኖሩ ነው። 18 እነርሱም አእምሮአቸው ጨልሞአል፤ካለማወቃቸውና ከልባቸው ደንዳናነት የተነሳ ከእግዚአብሔር ሕይወት ርቀዋል፤ 19 ስግብግብነት ሁሉ ለሞላበት ቅጥ ላጣ ብልግና ራሳቸውን አሳልፈው ሰጥተዋል። 20 ግን ስለ ክርስቶስ የተማራችሁት እንደዚህ አይደለም። 21 እርሱ የሰማችሁ እና የተማራችሁ ከሆነም በርግጥ የተማራችሁት ስለ ኢየሱስ የሚናገረውን እውነት ነው። 22 ክፉ ምኞት የጎደፈውን አስቀድሞ ትኖሩበት የነበረውን አሮጌውን ሰው ልታስወግዱ ይገባል። 23 በአእምሮአችሁ መንፈስ እንድትታደሱ 24 እውነተኛ በሆነው ጽድቅና ቅድስና በእግዚአብሔር የተፈጠረውን አዲሱን ሰው እንድትለብሱ ነው። 25 ውሸትን አስወግዱ፤ ሁላችንም የአንድ አካል ብልቶች ስለሆንን «እያንዳንዱ ከባልንጀራው ጋር እውነትን ይነጋገር»። 26 «ተቆጡ፤ ነገር ግን ኀጢአት አትሥሩ» በቁጣችሁ ጸሓይ እስከሚገባ ድረስ አትቆዩ፤ 27 ዕድል አትስጡት። 28 የነበረ ከእንግዲህ አይስረቅ፤ይልቁንም ለተቸገሩ ሰዎች ማካፈል ይችል ዘንድ በራሱ እጅ በተገቢው ሁኔታ እየሠራ ለማግኘት ጥረት ማድረግ ይገባዋል። 29 ለማነጽ የሚያስፈልግ፥ ለሚሰሙትም ጸጋን የሚሰጥ ጠቃሚ ቃል እንጂ የማይረባ ቃል ከቶ ከአፋችሁ አይውጣ። 30 ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔር መንፈስ አታሳዝኑ። 31 ሁሉ፥ቁጣንና ንዴትን፥ጭቅጭቅንና ስድብን ከማንኛውም ዓይነት ክፋት ጋር ከእናንተ ዘንድ አስወግዱ። 32 በርሳችሁ ቸሮች፥ ርኅሩሆች ሁኑ፤ ደግሞም እግዚአብሔር በክርስቶስ እንዲሁ ይቅር እንዳላችሁ እርስ በርሳችሁ ይቅር ተባባሉ።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ በፅሁፉ ለኤፌሶኖች በፃፈላችው፥የአማኞችን አንድነት በማጉላት እንደ አንደ አማኝ እንዴት መኖር እንዳለባቸው ያበረታታቸዋል። የጌታ እስረኛ፡ ትኩረት፡ "ጌታን ለማገልገል ባደረገው ምርጫ እንደ እንድ እስረኛ" ለተጠራችሁለት መጠራት የሚገባውን ሕይወት ትኖሩ ዘንድ፡ "ትኖሩ" የሚለው ቃል የኤፌሶን አማኞችን ያመላክታል። ትኩረት፡ "ለተጠራችሁለት ጥሪ የሚመጥን የሚገባ ማንነት እንዲኖችሁ አበረታታችኋለሁ" ይኽውም እርስ በርስ በፍቅር ተቻችላችሁ በፍጹም ትሕትና፥በገርነትና በትዕግሥት፡ ትኩረት፡"ትሁት፥ገር እና እርስ በእርሳችሁም የምትቀባበሉ መሆንን ተማሩ" በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ፡ "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ በሰላም ለመኖር ጥረት አድርጉ"
አንድ አካል፡ ብዙውን ጊዜ ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ እካል በመባል ትታወቃለች። አንድ መንፈስ፡ "አንድ ቅዱስ መንፈስ ብቻ" (UDB) በተጠራችሁ ጊዜ በአንድ ተስፋ እንደተጠራችሁ፡ "እግዚአብሔር የጠራችሁ በተረጋገጥ ተስፋ ነው" (ተመለከት፡
የሁሉም አባት የሆነ፡ "የሁሉ ነገር አባት የሆነ በሁሉ ነገር ላይ በሁሉ ነገር በኩል በሁሉ ነገር ውስጥ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ ክርስቶስ ለአማኞች የሰጠው ስጦታዎች በቤተክርስቲያን ማለትም ለመላው የአማኞች እካል ጥቅም ነው። ለእያንዳንዳችን፡ ይህ ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን እና መላው የኤፌሶን አማኞችን ነው። ለእያንዳንዳችን ጸጋ ተሰጥቶናል፡ ትኩረት፡"እግዚአብሔር ለእያንዳንዳችን ስጦታን ሰጥቶናል" ወይም "እግዚአብሔር ለአማኝ ሁሉ ስጦታን ስጥቶታል"
ወደ ላይ በወጣ ጊዜ፡ "ክርስቶስ ወደ መንግስተ ሰማይ"
ወደ ላይ ወጣ፡ "ክርስቶስ ወደ ላይ ሄደ" ወረደ፡ ወደታች ወረደ" ወይም "ክርስቶስም ወደ ታች መጣ" ወደ ምድር ጥልቅ ወረደ፡ ትርጉሞች ሊሆኑ የሚችሉ 1) "ወደ ታች የምድር አካባቢዎች" 2) ወደ ታች የምድር ክፍሎች ሁሉንም ይሞላ ዘንድ፡ "ሁሉንም ነገር ሙሉ በሙሉ እንዲሞላ" ወይም "ሁሉም በእርሱ ይሞላ ዘንድ"
ስጦታ አድርጎ የሰጠ ክርስቶስ፡ "ክርስቶስ ለቤተክርስቲያን ስጦታዎችን እንደዚህ አድርጎ ሰጠ"
ለአገልግሎት ሥራ፡ ትኩረት፡ "ሌሎችን ማገልገል" የክርስቶስን አካል ለማነጽና፡ ይህ በመንፈሳዊ ህይወት ማደግ፥ የሰውነት እንቅስቃሴ እያደረጉ ሰውነትን ከማበርታት ጋር ይነፃፀራል። ይህም የሚሆነው ሁላችንም የእግዚአብሔርን ልጅ በማመን እና በማወቅ ወደ ሚገኘው አንድነት፡ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆን ማወቅ በእምነት ወደሚገኘው አንድነት ወይም ወደ አማኞች ብስለት ለመድረስ አስፈላጊ ነው። በማመን * ወደ ሚገኘው አንድነት፡
"በአንድነት በእምነት መጠንከር" የእግዚአብሔርን ልጅ፡ ይህ ለኢየሱስ አስፈላጊ መጠሪያ ነቅ። ሙሉ ሰው ወደ መሆን ደረጃ፡ "የበሰሉ አማኞች መሆን"
ከእንግዲህ፡ "ከዚህ በኋላ እንዲህ እናደርጋለን" የምንነዳ ሕጻናት፡ ይህ በመንፈሳዊ ህይወት ያላደጉትን አማኞች በህይወት ጥቂት ልምድ ካላቸው ህፃናት ጋር ተነፃፅሯል። የትምህርት ነፋስ ወዲያና ወዲህ የምንነዳ፡ ይህ ደግሞ አቅጣጫዋን በቅጡ የማታውቅ ጀልባ በነፋስ በምትገፋበት ጊዜ ያለውን ሁኔታ ከአንድ የስተትን ትምህርት ሰምቶ ከሚንቀሳቀስ ካልበሰለ አማኝ ጋር ያነፃፅረዋል። በሰዎች ረቂቅ ተንኮል እና ማታለል፡ "አማኞችን በሰላ ውሸት የሚያታልሉ ተንኮለኛ ሰዎች" ይልቁንም * የምንናገር፡
"ይሌቁንስ እንናገራለን" ራስ ወደ ሆነው አካል ሁሉ እየተያያዘና እየተጋጠመ ያድጋል፡
"ስለዚህም አማኞች እርስ በእርስ በፍቅር ለማደግ መደጋገፍ ይችላሉ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ እየነገራቸው ያለው በእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ እንደታተሙ አማኞች ማድረግ የሌለባቸውን ነው። በጌታ እየለመንኋችሁ ይህን የምናገረው፡ ትኩረት፡ "ስለዚህም በጌታ ሆኜ በእጅጉን አደፋፍራችኋለሁ። በአእምሮአቸው ከንቱነት እንደሚመላለሱት እንደ አሕዛብ እንዳትኖሩ ነው፡ ትኩረት፡"የማይረባ ሃሳብ እንደያዙ አህዛብ መኖርን አቁሙ" አእምሮአቸው ጨልሞአል፤ካለማወቃቸውና ከልባቸው ደንዳናነት የተነሳ ከእግዚአብሔር ሕይወት ርቀዋል፡ ትኩረት፡"ስለታወሩ እና ልባቸው ደንዳና ስለሆነ የእግዚአብሔርን ህይወት ሊለማመዱ አይችሉም" አእምሮአቸው ጨልሞአል፡ ጥርት ባለ መልኩ ማሰብም ሆን ማመዛዘን አይችሉም። ካለማወቃቸውና ከልባቸው ደንዳናነት የተነሳ ከእግዚአብሔር ሕይወት ርቀዋል፡ ትኩረት፡ "አለማወቃቸው ከእግዚአብሔር ህይወት ለይቷቸዋል" ወይም "እግዚአብሔርን ስለማያውቁ የእግዚአብሔርን ህይወት ሊለማመዱ አይችሉም" ከልባቸው ደንዳናነት፡ እግዚአብሔርን መስማትና ትምህርቱን መከተል እንቢ አሉ። ርኩሰትና ስግብግብነት ሁሉ ለሞላበት ቅጥ ላጣ ብልግና ራሳቸውን አሳልፈው ሰጥተዋል፡ ትኩረት፡"ቅጥ ላጣ ፍላጎታቸውና ለራሳቸው ደስታ በክፉ ባህሪያቸው ኑሯቸውን አሳልፈው ሰጡ"
እናንተ ግን ስለ ክርስቶስ የተማራችሁት እንደዚህ አይደለም፡ ትኩረት፡ "ነገር ግን ክርስቶስን በዚህ መከተል አልተማራችሁም" ስለ እርሱ የሰማችሁ እና የተማራችሁ ከሆነም በርግጥ የተማራችሁት ስለ ኢየሱስ የሚናገረውን እውነት ነው፡ ትኩረት፡"ስለ ኢየሱስ ስለ ሰማችሁና ስለእርሱም እውነተኛውን ነገር ሰምታችኋልና" በሚያታልል ክፉ ምኞት የጎደፈውን አስቀድሞ ትኖሩበት የነበረውን አሮጌውን ሰው ልታስወግዱ ይገባል፡ ትኩረት፡"በክፉ ምኞት ተታልላችሁ ስትኖሩበት የነበረውን የድሮውን የተለመደ አኗኗር ዘዬ ማስወገድ ይገባችኋል" አሮጌውን ሰው ልታስወግዱ ይገባል፡ ልብስ አውልቃችሁ ወደዚያ እንደምታስወግዱት ሃጢያተኛ ባህሪያችሁን ልታስወግዱ ይገባል። ትኩረት፡"ባህሪያችሁን ልትለውጡ ይገባል" (ተመልከት፡
አስቀድሞ ትኖሩበት የነበረውን፡ ትኩረት፡"ከአሮጌው ባህሪ ጋር የሚስማማ ማንነት" ወይም "ከድሮው ማንነት ጋር የሚሄድ አይነት ፀባይ" በሚያታልል ክፉ ምኞት የጎደፈውን፡ ትኩረት፡"በውሸት የስጋ ምኞት እየባሰበት የሚሄድ"
እንድትታደሱ፡ ትኩረት፡"እንድትለወጡ" ወይም "እንድትታደሱ" አዲሱን ሰው እንድትለብሱ፡ አንድ ሰው አዲስን ልብስ ሲለብስ ፈፅሞ የተለየ እንደሚሆነው ሁሉ ያላመነ በክርስቶስ በማመን አዲስ ሰው ይሆናል።
ውሸትን አስወግዱ፡ ትኩረት፡"ሀሰት መናገርን ማቆም ይገባችኋል" እያንዳንዱ ከባልንጀራው ጋር እውነትን ይነጋገር፡ ትኩረት፡ "አማኞች ከጎረቤቶቻቸው ጋር እውነትን ሊነጋገሩ ይገባል" ሁላችንም የአንድ አካል ብልቶች ስለሆንን፡ "ሁላችንም የእግዚአብሔር ቤተሰብ አባላት ነን"
ተቆጡ፤ነገር ግን ኀጢአት አትሥሩ፡ "ልትቆጡ ትችላላችሁ፥ሆኖም ሃጢያትን አትስሩ" በቁጣችሁ ጸሓይ እስከሚገባ ድረስ አትቆዩ፡ ትኩረት፡ "ምሽት ከመምጣቱ በፊት ሃጢያታችሁ ይብረድ" ወይም "ቀኑ ከመጠናቀቁ በፊት ቁጣችሁ ይቁም"
የማይረባ ቃል ከቶ ከአፋችሁ አይውጣ፡ "ከአፋችሁ መጥፎ ቋንቋ አይውጣ" ወይም "ክፉ ንግግር ከአፋችሁ አይውጣ" ሌሎችን ለማነጽ የሚያስፈልግ፡ "ይልቁንም ለአማኞች ብርታትን መስጠት የሚችል ጠቃሚ ቃላትን ተናገሩ" ለሚሰሙትም ጸጋን የሚሰጥ ጠቃሚ ቃል እንጂ፡ "በዚህ መንገድ ለሚያዳምጧችሁ ፀጋን መስጠት ይቻላችኋል" ቅዱሱን የእግዚአብሔር መንፈስ አታሳዝኑ፡ ትኩረት፡"የእግዚአብሔርን ቅዱስ መንፈስ በመጥፎ ንግግራችሁ እንዲያዝን አታድርጉት" የታተማችሁበትን፡ ትኩረት፡ "ምክንያቱም እርሱ ስላተማችሁ"
መራራነት * ቁጣንና፡
"መራራነት" እና "ቁጣ" የሚሉት ቃላት ታላቅ መጠን ያለውን ቁጣ ያሳያሉ" ትኩረት፡"ከቁጥጥር ውጭ የሆነ ቁጣ"
ጭቅጭቅንና ስድብን፡ "ጭቅጭቅ" የሚለው ቃል "የስደብ" ፀያፍ ደረጃ ነው። ትኩረት፡ "ፀያፍ የቃላት ናዳ" እርስ በርሳችሁ ቸሮች፥ ርኅሩሆች ሁኑ፡ ትኩረት፡"ይልቁንስ እርስ በእርሳችሁ ደጎችና ቸሮች መሆን ይገባችኋል" ወይም "በርህራሄ የተሞላችሁ ደጋጎች መሆን ይገባችኋል"
1 እንግዲህ እንደ ተወደዱ የእርሱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትመስሉ ሁኑ፤ 2 እንደ ወደደን፥ ራሱንም ስለ እኛ መልካም መዓዛ ያለው መባና መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር እንዳቀረበ ሁሉ እናንተም በፍቅር ኑሩ። 3 የሚገባ ባለመሆኑ ዝሙት፥ማንኛውም ርኩሰትና ስስት በእናንተ ዘንድ ሊኖር አይገባም፤ 4 ጸያፍ ንግግር፥ዋዛ ወይም ውርደትን የሚያስከትል ቀልድ ለእናንተ ስለማይገባ ከመካከላችሁ አስወግዱ፤ከዚህ ይልቅ የምታመሰግኑ ሁኑ። 5 አመንዝራ፥ርኩስ፥ ስግብግብ የሆነ ይኽውም ጣዖት አምላኪ ሰው በክርስቶስና በእግዚአብሔር መንግሥት ርስት እንደማይኖረው ርግጠኛ ልትሆኑ ይገባል። 6 ከንቱ በሆነ ንግግር ማንም አያታላችሁ፤በእነዚህ ነገሮች ምክንያት የእግዚአብሔር ቁጣ በማይታዘዙት ልጆች ላይ ይመጣል 7 ስለዚህ የእነርሱ ተባባሪዎች አትሁኑ። 8 ወቅት ጨለማ ነበራችሁና፤ አሁን ግን በክርስቶስ ብርሃን ናችሁ። ስለዚህ እንደ ብርሃን ልጆች ኑሩ። 9 ምክንያቱም ከብርሃኑ የሚገኘው ፍሬ መልካም ነገር ሁሉ፥ ጽድቅና እውነት ነው 10 እንዲሁም ጌታን ደስ የሚያሰኝ ነገር ለማድረግ አስቡ፤ 11 ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፤ይልቁን ልትገልጡት ይገባል። 12 በስውር ያደረጉትን ነገር ለመግለጽ እንኳ አሳፋሪ ነውና። 13 በሚኖርበት ጊዜ ማንኛውም ነገር በግልጽ ይታያል። 14 ብርሃኑ በላዩ ላይ ስለሚያበራ ነው። ስለዚህ፥ «አንተ የምትተኛ ንቃ፤ከሙታን ተነሳ፤ክርስቶስም ያበራልሃል» ተብሎ ተነግሯል። 15 ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን፥እንደ ጥበብኞች እንዴት እንደምትኖሩ ተጠንቀቁ። 16 ክፉዎች ስለሆኑ ዘመኑን ዋጁ። 17 ፈቃድ ምን እንደሆነ አስተውሉ እንጂ ሞኞች አትሁኑ። 18 ሕይወታችሁን ለጥፋት ስለሚዳርግ፥በወይን ጠጅ አትስከሩ፤ይልቁንስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ። 19 እርስ በርሳችሁ በመዝሙር፥በቅኔና በመንፈሳዊ ዝማሬ ተነጋገሩ፤ ጌታንም በልባችሁ አመስግኑ፤ለእርሱም ተቀኙ። 20 በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ስለ ሁሉም ነገር ሁልጊዜ እግዚአብሔር አብን አመስግኑ 21 ክርስቶስን ለማክበር ስትሉ አንዳችሁ ለሌላችሁ ተገዙ። 22 ሚስቶች ሆይ! ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ። 23 ክርስቶስ አካሉ ለሆነችውና አዳኟ ለሆናት ቤተ ክርስቲያን ራስ እንደ ሆነ ሁሉ ባልም የሚስቱ ራስ ነውና። 24 ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ ሁሉ ሚስቶችም በማንኛውም ነገር ለባሎቻቸው ሊገዙ ይገባል። 25 ባሎች ሆይ፤ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳት ስለ እርስዋም ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ፥ እናንተም ሚስቶቻችሁን ውደዱ። 26 ይህንንም ያደረገው በቃሉ አማካይነት በውሃ አጥቦ በማንጻት እንድትቀደስ፥ 27 ጉድፍ ወይም የፊት መጨማደድ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ ነገር ሳይታይባት ቅድስት የሆነችና ነውር የሌለባት ክብርት ቤተ ክርስቲያን አድርጎ ለራሱ ሊያቀርባት ነው። 28 ባሎች የገዛ ሥጋቸውን እንደሚወዱ ሚስቶቻቸውን መውደድ ይገባቸዋል። ሚስቱን የሚወድ ራሱን ይወዳል። 29 የራሱን ሥጋ የሚጠላ ማንም የለም፤ ይልቁን ይመግበዋል፤ ይንከባከበዋልም። ይህም ክርስቶስ ልክ ቤተ ክርስቲያንን እንደሚወድ ነው። 30 እኛ የእርሱ ብልቶች ነን። 31 ምክንያት ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፤ከሚስቱም ጋር አንድ ይሆናል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ። 32 ታላቅ ምስጢር ነው፤ እኔም ይህን የምናገረው ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ ክርስቲያኑ ነው። 33 ግን ከእናንተ እያንዳንዱ ደግሞ ሚስቱን እንደ ራሱ አድርጎ መውደድ ይገባዋል፤ ሚስትም ባልዋን ታክብር።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ እንግዲህ*እግዚአብሔርን የምትመስሉ ሁኑ፡ እንደ ተወደዱ የእርሱ ልጆች፡ በፍቅር ኑሩ፡ መልካም መዓዛ ያለው መባና መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር እንዳቀረበ፡
ለቅዱሳን የሚገባ ባለመሆኑ ዝሙት፥ማንኛውም ርኩሰትና ስስት በእናንተ ዘንድ ሊኖር አይገባም፡ ማንኛውም ርኩሰትና፡ ስስት፡ በእናንተ ዘንድ ሊኖር አይገባም፡ ለቅዱሳን የሚገባ ባለመሆኑ ወይም ጸያፍ ንግግር፥ዋዛ ወይም ውርደትን የሚያስከትል ቀልድ ለእናንተ ስለማይገባ ከመካከላችሁ አስወግዱ፤ከዚህ ይልቅ የምታመሰግኑ ሁኑ፡
ከንቱ በሆነ ንግግር ማንም አያታላችሁ፡ በእነዚህ ነገሮች ምክንያት የእግዚአብሔር ቁጣ በማይታዘዙት ልጆች ላይ ይመጣል፡ ስለዚህ የእነርሱ ተባባሪዎች አትሁኑ፡
ባንድ ወቅት ጨለማ ነበራችሁና፡ አሁን ግን በክርስቶስ ብርሃን ናችሁ፡ ምክንያቱም ከብርሃኑ የሚገኘው ፍሬ መልካም ነገር ሁሉ፥ ጽድቅና እውነት ነው፡ ፍሬ ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፡ ፍሬ ከሌለው ከጨለማ ሥራ፡ ይልቁን ልትገልጡት ይገባል፡
ብርሃን በሚኖርበት ጊዜ ማንኛውም ነገር በግልጽ ይታያል፡ አንተ የምትተኛ ንቃ፤ከሙታን ተነሳ፡ ክርስቶስም ያበራልሃል፡
እንግዲህ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን፥እንደ ጥበብኞች እንዴት እንደምትኖሩ ተጠንቀቁ፡ ዘመኑን ዋጁ፡ ቀኖቹ ክፉዎች ስለሆኑ፡
በወይን ጠጅ አትስከሩ፡ ይልቁንስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ፡ በመዝሙር፥በቅኔና በመንፈሳዊ ዝማሬ፡ ሁልጊዜ* አመስግኑ፡
ተገዙ፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ አካሉ ለሆነችውና አዳኟ ለሆናት፡ ሚስቶችም በማንኛውም ነገር ለባሎቻቸው ሊገዙ ይገባል፡
ሚስቶቻችሁን ውደዱ፡ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ * በውሃ አጥቦ በማንጻት እንድትቀደስ፡
ስለ እርስዋም ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ፡ በቃሉ አማካይነት በውሃ አጥቦ በማንጻት፡ ቤተ ክርስቲያን አድርጎ ለራሱ ሊያቀርባት ነው፡
የገዛ ሥጋቸውን እንደሚወዱ፡ ይልቁን ይመግበዋል፡ ምክንያቱም እኛ የእርሱ ብልቶች ነን።
በዚህም ምክንያት፡ ሚስቱን እንደ ራሱ አድርጎ መውደድ ይገባዋል፡ ሚስትም ባልዋን ታክብር፡
1 ልጆች ሆይ፤ በጌታ ለወላጆቻችሁ ታዘዙ፤ ይህ ተገቢ ነውና። 2 «አባትህንና እናትህን አክብር» በሚለው የመጀመሪያ ትእዛዝ ውስጥ ያለው ተስፋ 3 እንዲሆንልህ፥ ዕድሜህም በምድር ላይ እንዲረዝም» የሚል ነው። 4 እናንተም አባቶች ሆይ፤ ልጆቻችሁን አታስቆጡአቸው፤ ይልቁንስ በጌታ ሥርዓትና ምክር አሳድጓቸው። 5 ባሮች ሆይ፤ ለክርስቶስ እንደምትታዘዙት ለምድራዊ ጌቶቻችሁም በታላቅ አክብሮት፥ በመንቀጥቀጥና በልባችሁ ቅንነት ታዘዙ፤ 6 ለታይታ እነርሱን ደስ ለማሰኘት ብላችሁ ሳይሆን፥ እንደ ክርስቶስ አገልጋዮች የእግዚአብሔርን ፈቃድ ከልብ በመፈጸም ታዘዙአቸው። 7 ሰውን ሳይሆን ጌታን እንደምታገለግሉ እያሰባችሁ በደስታ አገልግሉ። 8 ባሪያም ይሁን ነጻ ሰው እያንዳንዱ ሰው ለሚያደርገው መልካም ነገር ከጌታ ሽልማት እንደሚቀበል ልብ በሉ። 9 እናንተም ጌቶች ሆይ፤ ለባሮቻችሁ እንዲሁ አድርጉላቸው፤ የእነርሱና የእናንተም ጌታ የሆነው እርሱ በሰማይ እንዳለና ለሰው ፊትም እንደማያዳላ ተረድታችሁ አታስፈራሯቸው። 10 በጌታና ብርቱ በሆነው ኀይሉ የበረታችሁ ሁኑ። 11 የዲያብሎስን ተንኮል አዘል ዕቅድ መቋቋም ትችሉ ዘንድ የእግዚአብሔርን የጦር ዕቃ ሁሉ ልበሱ። 12 ውጊያችን ከሥጋና ከደም ጋር ሳይሆን ከአለቆች፥ ከሥልጣናት፥ ከዚህ ከጨለማ ዓለም ገዦችና በሰማያዊ ስፍራ ካሉ ርኩሳን መናፍስት ጋር ነው። 13 በክፉ ቀን ክፉውን በመቃወም ጸንታችሁ ትቆሙ ዘንድ የእግዚአብሔርን የጦር ዕቃ ሁሉ ልበሱ፤ ጸንታችሁ ለመቆምም ማድረግ የምትችሉትን ሁሉ አድርጉ። 14 ወገባችሁን በእውነት ቀበቶ ታጥቃችሁ፥የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ ጸንታችሁ ቁሙ፤ 15 የሰላምን ወንጌል ለማወጅ እግሮቻችሁ በዚያ ተጫምተው ዝግጁ ይሁኑ 16 የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ማጥፋት ትችሉ ዘንድ ሁል ጊዜ የእምነትን ጋሻ አንሱ። 17 የመዳንን ራስ ቁር አድርጉ፤የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ፤ይህም የእግዚአብሔር ቃል ነው። 18 ዓይነት ጸሎትና ልመና ሁልጊዜ በመንፈስ በመጸለይና መልሱን ከእርሱ በመጠበቅ፥ ለቅዱሳንም ልመና በማቅረብ ትጉ። 19 ምስጢር በድፍረት ለመናገር አፌን በምከፍትበት ጊዜ ሁሉ ቃል ይሰጠኝ ዘንድ ለእኔም ጸልዩልኝ። 20 መናገር እንደሚገባኝ በድፍረት እናገር ዘንድ በሰንሰለት የታሰረ መልእክተኛ የሆንሁት ለዚሁ ነውና። 21 ሁኔታ እንዳለሁና ምን እያደረግሁ እንደምገኝ፥ የተወደደ ወንድምና በጌታ ታማኝ አገልጋይ የሆነው ቲኪቆስ ሁሉንም ነገር ይነግራችኋል። 22 ያለንበትን ሁኔታ እንድታውቁና እናንተንም እንዲያበረታታ በማለት ወደ እናንተ ልኬዋለሁ። 23 ከአብ፥ ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ሰላምና ፍቅር ከእምነት ጋር ለወንድሞች ይሁን። 24 ኢየሱስ ክርስቶስን በማይጠፋ ፍቅር ከሚወዱ ጋር ሁሉ ጸጋ ይሁን።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ልጆች ሆይ፤በጌታ ለወላጆቻችሁ ታዘዙ፡ መልካም እንዲሆንልህ፥ዕድሜህም በምድር ላይ እንዲረዝም፡
እናንተም አባቶች ሆይ፤ልጆቻችሁን አታስቆጡአቸው፡ ይልቁንስ በጌታ ሥርዓትና ምክር አሳድጓቸው፡
ባሪያዎች ሆይ *ታዘዙ፡ በታላቅ አክብሮት፥ በመንቀጥቀጥና፡ በመንቀጥቀጥና በልባችሁ ቅንነት ታዘዙ * እንደ ክርስቶስ አገልጋዮች፡
እነርሱን ደስ ለማሰኘት ብላችሁ ሳይሆን፥ እንደ ክርስቶስ አገልጋዮች፡ እንደ ክርስቶስ አገልጋዮች የእግዚአብሔርን ፈቃድ ከልብ በመፈጸም ታዘዙአቸው፡
እናንተም ጌቶች ሆይ፤ለባሮቻችሁ እንዲሁ አድርጉላቸው * አታስፈራሯቸው፡
የእነርሱና የእናንተም ጌታ የሆነው እርሱ በሰማይ እንዳለና፡ ለሰው ፊትም እንደማያዳላ
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ በጌታና ብርቱ በሆነው ኀይሉ የበረታችሁ ሁኑ፡ የዲያብሎስን ተንኮል አዘል ዕቅድ መቋቋም ትችሉ ዘንድ የእግዚአብሔርን የጦር ዕቃ ሁሉ ልበሱ፡
ከሥጋና ከደም፡ የእግዚአብሔርን የጦር ዕቃ ሁሉ ልበሱ፤
በእውነት ቀበቶ፡ ቀበቶ ለአንድ ወታደር በሚገባ እንደሚይዝለት እውነትም ለአማኝ ነገሮችን አጥብቆ ይይዝለታል። የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ፡ ጥሩር የወታደርን ደረት እንደሚሸፍንለት የፅድቅ ስጦታም የአማኝን ልብ ይከልልለታል።
የሰላምን ወንጌል ለማወጅ እግሮቻችሁ በዚያ ተጫምተው ዝግጁ ይሁኑ፡ ወታደር ለእግሩ ጥሩ ጫማ መጫማት እንዳለበት ሁሉ አማኝም ጠንካራ የሆን የሰላም ወንጌል እውቀት ሊኖረው ይገባል። የእምነትን ጋሻ አንሱ፡ ወታደር ጠላትን ለመከላከል ጋሻውን እንደሚጠቀምበት ሁሉ እግዚአብሔር ለአማኝ የሚሰጠውም እምነት ከዲያብሎስ ጥቃት መከላከያ ነው። (ተመልከት፡ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች፡
እንዲሁም የመዳንን ራስ ቁር፡ በእግዚአብሔር የሚሰጥ ድነት የአማኝን አዕምሮ እንደ ራስ ቁር ሆኖ ይከላከላል። የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ፤ይህም የእግዚአብሔር ቃል ነው፡ ወታደር ሰይፍ መዝዞ ጠላትን ለማጥቃትና ለመከላከል እንደ ሚጠቀምበት ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ የሆነ የእግዚአብሔር ቃልም ለአማኝ ዲያብሎስን ማጥቂያ መሳሪያ ነው። በማንኛውም ዓይነት ጸሎትና ልመና ሁልጊዜ በመንፈስ በመጸለይና፡ ትኩረት፡ ስትፀልዩ እና የተወሰኑ ልመናዎችን ስታቀርቡ በመንፈስ ቅዱስ ሁልጊዜ የምትፀልዩ ሁኑ። ከእርሱ በመጠበቅ፥ ለቅዱሳንም ልመና በማቅረብ ትጉ፡ "ለአማኞች ሁሉ መደበኛ የሆነ ንቃት እና ፀሎት"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ በእስር ሆኖ ወንጌል በድፍረት እንዲናገር እንዲፀልዩለት ይለምናል፥ለዚህም ደግሞ ቲኪቆስን ያደፋፍራቸው ዘንድ ይልከዋል። ከዚያም ክርስቶስን ለሚወዱ አማኞች ሁሉ በሰላምና በፀጋ ይባርካቸዋል። ቃል ይሰጠኝ ዘንድ፡ ትኩረት፡ "እግዚአብሔር ቃሉን እንዲሰጠኝ" ወይም "እግዚአብሔር መልዕክትን እንዲሰጠኝ" መናገር እንደሚገባኝ በድፍረት እናገር ዘንድ፡ ትኩረት፡ "በድፍረት ገለፃ እንዳደርግ" በሰንሰለት የታሰረ መልእክተኛ የሆንሁት ለዚሁ ነውና፡ ትኩረት፡ "የወንጌል ተወካይ በመሆኔ አሁን በእስር እገኛለሁ" በእስራቴም መናገር እንደሚገባኝ በድፍረት እናገር ዘንድ፡ ትኩረት፡ "የእግዚአብሔርን መልዕክት በድፍረት እንድናገር"
ምን እያደረግሁ እንደምገኝ፡ "የኔ ሁኔታ" ወይም "እኔ ያለሁበት ድባብ" ቲኪቆስ፡ ቲኪቆስ ከጳውሎስ ጋር ካሉት በርካታ ሰዎች መካከል አንዱ ነው። ያለንበትን ሁኔታ እንድታውቁና፡ ትኩረት፡ "ሁሉንም ነገሮች እንነግራችኋለን"
ማስታወሻ የለውም።
1 የክርስቶስ ኢየሱስ አገልጋዮች ከሆኑት ከጳውሎስና ከጢሞቲዎስ፤ በክርስቶስ ኢየሱስ ቅዱሳን ለሆኑ በፊልጵስዩስ ከተማ ከእረኞችና ከዲያቆናት ጋር ለሚኖሩ ሁሉ። 2 ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ስላም ለአናንተ ይሁን። 3 ስለእናንተ በማስብበት ሁሉ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ። 4 ስለ ሁላችሁም በምጸልይበት ጊዜ ሁሉ በደስታ እጸልያለሁ። 5 ከመጀመሪያ ጀምሮ እስካሁን ወንጌል በሚሰበክበት ሥራ ስላሳያችሁት ትብብራችሁ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ። 6 ይህን መልካም ሥራ በእናንተ ውስጥ የጀመረው ኢየሱስ ክርስቶስ እስከሚመለስ ቀን ድረስ እንደሚፈጽም እርግጠኛ ነኝ። 7 እናንተ በልቤ ስላላችሁ ስለ ሁላችሁ እንዲህ ማሰብ ይኖርብኛል። በእስራቴና ስለ ወንጌል በመቆሜ ስለእርሱም በመመስከሬ ሁላችሁም በጸጋ ተባባሪዎች ሆናችኋል። 8 በኢየሱስ ክርስቶስ ባለኝ ጥልቅ ፍቅር ሁላችሁንም እንድምናፍቃችሁ እግዚአብሔር ምስክሬ ነው። 9 ፍቅራችሁ በዕውቀትና በሙሉ መረዳት የበለጠ እንዲበዘላችሁ እጸልያለሁ። 10 ይህን የምጸልይበት ምክንያት የተሻለውን ነገሮችን መርምራችሁ እንድታውቁ እንዲሁም ክርስቶስ ተመልሶ በሚመጣበት ቀን ንጹኃንና ነውር የሌለባችሁ ሆናችሁ እንድትገኙ ነው። 11 ይህ ደግሞ ከኢየሱስ ክርስቶስ በሚገኘው የጽድቅ ፍሬ ተሞልታችሁ ለእግዚአብሔር ክብርና ምስጋና እንዲሆን ነው። 12 ወንድሞች ሆይ፥በእኔ ላይ የደረሰው ሁሉ ወንጌል በጣም እንዲስፋፋ እንዳደረገ እንድታውቁ እወዳለሁ። 13 እኔም የታሰሁት በክርስቶስ ምክንያት መሆኑን የቤተ መንግሥት ጠበቂዎችና ሌሎችም እዚያ ያሉት ሰዎች ሁሉ እንዲያውቁ ሆኖአል። 14 በእኔ መታሰር ምክንያት በጌታ ወንድሞች ከሆኑት ብዙዎቹ የበለጠ ከቀድሞ ይልቅ የእግዚአብሔርን ቃል ያለ ፍርሃት ለመናገር ድፍረት አግኝተዋል። 15 በርግጥ አንዳንዶቹ የክርስቶስን ወንጌል የሚሰብኩት በቅናትና በፉክክር መንፈስ ነው፤ሌሎቹ ግን ክርስቶስን የሚሰብኩት በቅን ልቡና ነው። 16 እነዚህ የእግዚአብሔርን ቃል በቅን ልቡና የሚሰብኩት ከፍቅር የተነሳ ነው፤እነርሱም እኔ ስለወንጌል ቆሜ በመከራከርይ መታሰሬን ያውቃሉ። 17 እነዚያ ግን ስለ ክርስቶስ የሚሰብኩት በራስ ወዳድነትና ቅንነት በሌለበት አስተሳሰብ ነው። በእስራቴም ላይ ተጨማሪ መከራ ሊያመጡብኝ አስበው ነው። 18 ታዲያ ምን ይደረግ? በርግጥ በዚህ ደስ ይለኛል፤በማስመሰል ወይም በእውነት በሁሉም መንገድ ክርስቶስ ይሰበካል። 19 ምክንያቱም በእናንተ ጸሎትና በኢየሱስ ክርስቶስ መንፈስ ርዳታ ነጻ እንደምወጣ አውቃለሁ። 20 እንደማላፍርበት በሙሉ መተማመ እጠባበቃለሁ። ነገር ግን ዘወትር እንደማደርገውና በተለይም ዛሬም በሕይወት ብኖር ወይም ብሞት ክርስቶስ በሰውነቴ ይከብራል ብዬ በድፍረት እናገራለሁ። 21 ስለዚህ ለእኔ ሕይወት ማለት በክርስቶስ መኖር ነው፤ ሞትም ማለት ማትፍረፍ ነው። 22 ነገር ግን በሥጋ መኖር ለእኔ የሥራ ፍሬ ቢሆን የትኛውን እንደምመርጥ አላውቅም። 23 ምክንያቱም በእነዚህ በሁለቱ አሳቦች መካከል ተወጥሬአለሁ። በአንድ በኩል ከክርስቶስ ጋር መሆን ከሁሉ የሚበልጥ ነገር ስለሆነ ከዚህ ሕይወት ተለይቼ ከክርስቶስ ጋር መሆንን እፈልጋለሁ። 24 ሆኖም በሥጋ መኖሬ ለእናንተ የበለጠ አስፈላጊ ነው። 25 እምነታችሁ እንዲያድግና ደስታን እንድታገኙ እንደምቆይና ከሁላችሁም ጋር እንደምቀጥል ስለዚህ ነገር እተማመናሉ። 26 በዚህ ምክንያት እኔም እንደገና ወደ እናንተ ስመጣት ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ በእኔ ትመካላችሁ። 27 እንግዲህ ከሁሉም በላይ ሕይወታችሁ ለክርስቶስ ወንጌል እንደሚገባ ይሁን፤ ይህም እኔ መጥቼ ባያችሁ ወይም ከእናንተ ብርቅ በአንድ መንፈስ ጸንታችሁ መቆማችሁንና ለወንጌልም እምነት በኅብረት መጋደላችሁን እሰማ ዘንድ ነው። 28 ተቃዋሚዎቻችሁንም በምንም ነገር አትፍሩአቸው፤ ይህም ለእነርሱ የመጥፋታቸው ምልክት ሲሆን፤ ለእናንተ ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ የሆነ የመዳናችሁ ምልክት ነው። 29 ምክንያቱም ከክርስቶስ የተነሳ ይህ የተሰጣችሁ አገልግሎት በእርሱ እንድታምኑ ብቻ ሳይሆን በእርሱ ምክንያት መከራ እንድትቅበሉም ጭምር ነው። 30 ስለዚህ አሁን ከእኔ ጋር የመከራ ተካፋዮች ሆናችኋል፤ ይህም መከራ ከዚህ በፊት ደርሶብኝ ያያችሁትና አሁንም እየደረሰብኝ መሆኑን የሰማችሁት ነው።
የክርስቶስ ኢየሱስ አገልጋዮች ''እኛየክርስቶስ ኢየሱስ አገልጋዮች ነን'' ) በክርስቶስ ኢየሱስ ቅዱሳን ሆነው ለተለዩት ሁሉ ''በክርስቶስ ኢየሱስ አማኝ ለሆኑ ሁሉ'' ለእረኞችና ዲያቆናት ትኩረት፡''የቤተ ክርስቲያን መሪዎች'' ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን ይህ ለሌሎች በረከት እንዲሆንላቸሁ መመኘት የሚገለጽበት መንገድ ነው። ለእናንተ እዚህ ላይ ''እናንተ'' የሚያመለክተው በፊልጵስዩስ ቤተ ክርስቲያን የሚገኙ አማኞችን ነው።
እግዚአብሔር አባታችን እዚህ ላይ''የእኛ'' የሚያመለክተው ምናልባት ጳውሎስንና ጢሞቲዎስን ጨምሮ በክርስቶስ አማኞችን ሁሉ እና የፊልጵስዩስ አማኞችን ነው።
''እኔ'' ጳውሎስን ያመለክታል እናንተ እዚህ ላይ ''እናንተ'' የፊልጵስዩስ አማኞችን ያመለክታል። በወንጌል ስላላችሁ ኅብረት አመሰግናኋለሁ ጳውሎስ የፊልጵስዩስ ሰዎች ወንጌል በመስበካቸው እግዚአብሔርን ያመሰግናል። ትኩረት፡''ወንጌል በመስበካችሁ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ'' ትምክህት አለኝ ''እርግጠኛ ነኝ'' በእናንተ የጀመረው ''የጀመረው እግዚአብሔር'' ይፈጽመዋል ''ይህን ለመፈጸም ይቀጥላል''
እናንተ በልቤ አላችሁ ትኩረት፡ ''በጣም እወዳችኋለሁ''
በጸጋው ተባባሪዎች ናችሁ ትኩረት፡''ከእኔ ጋር የጸጋ ተካፋዮች ሆናችኋል'' ወይም '' ከእኔ ጋር የጸጋው ተካፋዮች'' እግዚአብሔር ምስክሬ ነው ትኩረት፡ ''እግዚአብሔር ያውቃል'' ወይም '' እግዚአብሔር ይገበዋል'' በክርስቶስ ኢየሱስ ጥልቅ ፍቅር ይህ ሐረግ ''በጥልቅ ፍቅር'' የሚያመለክተው በውስጣችን ከስሜት ክፍል የሚወጣበት ቦታ ነው።''
እንዲበዘላችሁ ''ይተረፍላችኋል'' በዕውቀትና በሙሉ መረዳት ትኩረት፡''እግዚአብሔርን የሚያስደስተውን ባወቃችሁና በተርዳችሁ መጠን''
ይህን አደርጋለሁ ''ይህን እጸልያለሁ'' የተሻሉ ነገሮች ትኩረት፡'' በጣምእ ግዚአብሔርን የሚያስደስት ነገር'' ንጹኃንና ነውር የሌለባችሁ ''ንጹኃን" እና "ነውር የሌለባችሁ" የሚሉ ቃላት መሠረታዊ ነገሩ ተመሳሳይ ነው። ጳውሎስ የሞራል ንጽሕናን ለመግለጽ አንድ አድርጎ ያገናኘዋል''
በክርስቶስ ቀን ''በጌታ ቀን'' ወይም '' በፍርድ ቀን'' ትሞላላችሁ ትኩረት፡ '' ኢየሱስ ክርስቶስ የበለጠ እግዚአብሔርን እንድትታዘዙ ያደርጋችኋል''
በጽድቅ ፍሬዎች ትሞላላችሁ ይህ አማኞች እግዚአብሔርን ለመታዘዝ በዛፍ ላይ የሚያፈሩትን ፍሬ ያስተያያል።
ለእግዝዚአብሔር ክብርና ውዳሴ ይህ በተለየ ሁኔታ ሊተረጎም ይችላል። ትኩረት፡ ''እናንተ መልካም ያደረጋችሁትን ሰዎች አይተው እግዚአብሔርን እንዲያመሰግናሉ እንዲሁም ለእግዚአብሔር ክብር ይሰጣሉ።
እዚህ ላይ ''እንግዲህ''የሚለው የደብዳቤውን አዲስ ክፍል ለማድረግ ጥቅም ላይ ውሎአል። ወንድሞች እዚህ ላይ ይህ ማለት ከሰማያዊው እግዚአብሔር ጋር በክርስቶስ ያመኑ ሁሉ አንድ መንፈሳዊ ቤተ ሰብ ስለሆኑ ወዶችንና ሴቶችን ጨምሮ ክርስቲያን ወዳጆችን ነው። በእኔ የሆኑ ነገሮች ጳውሎስ የሚናገረው በእስር ቤት የነበረበትን ጊዜ ነው። ትኩረት፡ "ይህን ሁሉ መከራ የተቀበልኩት የኢየሱስን ወንጌል እንድሰብክ በእስር ቤት የተጣልኩበት'' የቤተ መንግሥት ጠባቂዎች እንግዲህ በጌታ ወንድሞች የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራሉ ትኩረት፡ '' እኔ በመታሰሬ ምክንያት ብዙ በጌታ የሆኑ ወንድሞች የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራሉ'' በበለጠ ድፍረትና ያለ ፍርሃት ጳውሎስ የሚገልጸው በአዎንታዊና አሉታዊ ተመሳሳይ አሳብን በአደገኛ ሁኔታ ላይ ሆነው ወንጌልን በታላቅ ድፍረት መስበካቸውን ለመግለጽ ነው። ትኩረት፡ '' በታላቅ ድፍረትና ያለ ፍርሃት''
''አንዳንድ ሰዎችስለ ክርስቶስ የምሥራች ይሰብካሉ በቅናትና በፉክክር ትኩረት፡ '' ሰዎች እኔን ለመስማት ባለመፈለጋቸው ችግር ለመፍጠር ይፈልጋሉ'' እንዲሁም ሌሎች ከቅን ልቦና ትኩረት፡ ''ነገር ግን ሌሎች ቸሮችና ለመርዳት በመፈለጋቸው አድርገውታል'' አንዳንዶች ''ሰዎቹ ለዚህ ተመድቤአለሁ ትኩረት፡ '' እግዚአብሔር መርጦኛል" ወንጌልን ለመደገፍ ትኩረት፡ "የኢየሱስ መልእክት እውነት መሆኑን ሁሉንም ለማስተማር'' "ነገር ሌሎች ክርስቶስን ይሰብካሉ" በቅናትና በቅን ልቦና። በእስራቴ በምቀበለው መከራ እየጨመሩብኝ ያስባሉ"
እንግዲህ ምን ይደረግ ጳውሎስ አንዳንድ ሰዎች ስለ ክርስቶስ የሚሰብኩት አስፈላጊ አይደለም። ትኩረት፡ ''አይመለከተኝም'' በየትኛውም መንገድ በማስመሰል ወይም በእውነት ክርስቶስ ይሰበካል ትኩረት፡ ''ሰዎች ስለ ክርስቶስ እስከሰበኩ ድረስ በመልካም ወይም በመጥፎ ምክንያት ቢያደርጉትም ምንም አይደለም" በዚህ ሁሉ ደስ ይለኛል ትኩረት፡ ሰዎች ስለ ክርስቶስ በመስበካቸው ደስ ይለኛል" እደሰታለሁ "በዓል አደርጋለሁ'' ወይም ''እደሰታለሁ'' ይህ ለእኔ ነፃ መውጣትን ያመራልታል ትኩረት፡ '' እግዚአብሔር ከእስራቴ ነፃ ያወጣኛል" በእናንተ ጸሎትና በኢየሱስ ክርስቶስ መንፈስ ርዳታ ትኩረት፡ "እናንተ ስለምትጸልዩና የኢሱስ ክርስቶስ መንፈስ እየረዳኝ ነው።" የኢየሱስ ክርስቶስ መንፈስ ትኩረት፡ "መንፈስ ቅዱስ"
ይህ ትምክቴና በእርግጠኝነት የምጠብቀው ነው እዚህ ላይ"በትምክት የምጠብቀው" እና "በርግጠኝነት" የሚሉ ቃላት የሚናገሩት በመሠረቱ ተመሳሳይ ነው። ጳውሎስ የሚጠቀመው በተያያዘው የእርሱ አጠባበቅ ምን ያህል ጠንካራ እንደሆነ ለመግለጽ ነው። ትኩረት፡" እኔ ሙሉ ለሙሉ አምናለሁ"
ነገር ግን በሙሉ ድፍረት ሁልጊዜ እንደሚደረግና በተለይም በአሁኑ ጊዜ ትኩረት፡ "ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ ሁልጊዜ እንዳለኝ ሁሉ ሙሉ ድፍረት አለኝ።'' በሥጋዬ ለክርስቶስ ክብርን አመጣለሁ ጳውሎስ የራሱን ሕይወት ለማቅረብ አካላዊ "ሥጋ" ይጠቀማል። ትኩረት፡ "በማደርገው ሁሉ ክርስቶስን አከብራለሁ።
በሕይወቴ ወይም በሞቴ ትኩረት፡ "በሕይወት ብኖር ወይም ብሞት"
''ፍሬ'' የሚለው ቃል የጳውሎስ መልካም ውጤትን ያመለክታል። ትኩረት፡ '' ነገር ግን በሥጋ መኖሬ ሰዎች በክርስቶስ እንዲያምኑ ለማገዝ የበለጠ ዕድል ይሰጠኛል።'' በሥጋ መቆየቴ ለእናንተ የበለጠ አስፈላጊ ነው ትኩረት፡ ''በሥጋ መኖሬ ለእናንተ የበለጠ የሚረዳ ነው''
ስለዚህ ነገር እርግጠኛ ከሆንሁ
''እርግጠኛ ከሆንሁ''
እንደምቆይ አውቃለሁ
''በሕይወት ለመኖር እንደምቀጥል አውቃለሁ'' ወይም ''መኖሬን እንደምቀጥል አውቃለሁ''
ከሁላችሁ ጋር መኖሬን እቀጥላለሁ
''ሁላችሁንም ማገልገሌን እቀጥላለሁ''
በዚህ ምክንያት እኔም እንደገና ወደ እናንተ ስመጣ ስለ ክርስቶስ በእኔ ትመካላችሁ
ትኩረት፡ ''እንግዲህ እንደገና ወደ እናንት ስመጣ እኔ ስለ ክርስቶስ ስላደረግሁት በእኔ ትመካላችሁ ምክንያቱም''
ሕይወታችሁ እንደሚገባ ብቻ ይሁን
''ሕይወታችሁ እንደሚገባ ብቻ ኑሩ''
በአንድ መንፈስ በአንድ ነፍስ ጸንታችሁ ቁሙ፤
እነዚህ ሁለት ሐረጎች ተመሳሳይ ትርጉሞችንና የህብረትን አስፈላጊነት ይገልጻሉ። ''ምንፈስ'' እና ''ነፍስ'' የሚሉ ቃላት አእምሮንና ስሜትን ይገልጻሉ። ትኩረት፡ '' ሁሉም የቅቆረጠ ተመሳሳይ ዓላማና አብሮ መሥራት ፍላጎት አላቸው''
ስለ ወንጌል እምነት
ትኩረት፡ ''በወንጌል ላይ የተመሠረተ እምነትን ለማሠረጫት'' ወይም '' የምሥራቹ ቃል እንደሚያስተምረን ለመኖር ማመን'' (UDB)
በአንዳች አትፍሩ ይህ ለፊጵስዩስ አማኞችትእዛዝ ነው።
ከሚቃወሙአችሁ ''በሚታደርጉት ነገር ላይ ከሚቃወሙአችሁ'' ለእነርሱ የመጥፋታችው ምልክት ለእኛ ግን ከእግዚአብሔር የሚሆን የመዳናችን ምልክት ነው ትኩረት፡''ምክንያቱም ድፍረታችሁ የሚያሳያቸው እግዚአብሔር እነርሱን እንደሚያጠፋቸው ነገር ግን እናንተን እንደሚያድናችሁ ነው''
በእኔ ያያችሁት መከራ ስለ ተቀበላችሁ አሁንም በእኔ እየተፈጸመ እንዳለ ሰምታችኋል ትኩረት፡ ''ይህም መከራ ከዚህ በፊት ደርሶንኝ ያያችሁትና አሁንም እየደረሰብኝ መሆኑን የሰማችሁት ነው።
1 በክርስቶስ መበረታታት ካላችሁ፤ከፍቅሩም መጽናናት ካላችሁ፤የመንፈስም ኅብረት ካላችሁ፤እርስ በእርሳችሁም ደግነትና ርኅራኄ ካላችሁ። 2 ስለዚህ በአንድ አሳብ፤ በፍቅር፤ በመንፈስ አንድነት፤በአንድ ዓላማ እየተስማማችሁ ደስታዬ እንዲፈጸም አድርጉት። 3 በራስ ወዳድነት ወይም በከንቱ ትምክህት ምንም አታድርጉ፤ነገር ግን በዚህ ፈንታ ሌሎች ሰዎች ከእናንተ እንደሚሻሉ በትህትና ቁጠሩ። 4 እንዲሁም እያንዳንዳእሁ የራሳችሁን ጥቅም ብቻ ሳይሆን የሌላውንም ሰው ጥቅም አስቡ። 5 በኢየሱስ ክርስቶስ የነበረ አሳብ በእናንተም ደግሞ ይኑር፤ 6 እርሱም የመለኮት ባሕር ነበረው፥ ነገር ግን ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር እኩል የሚያደርጋውን የመለኮት ባሕይ እንደ ያዘ አልቆጠረም። ክብሩን ትቶ ራሱን ባዶ አደረገ። 7 የባሪያንም መልክ ያዘ፤ በሰው አምሳል ተገለጠ፤ እንደ ሰውም ሆኖ በትህትና ራሱን ዝቅ አደረገ። 8 እንዲሁም እስከ ሞት፤ያውም እስከ መስቀል ሞት ድረስ ታዛዥ ሆነ። 9 ስለዚህም እግዚአብሔር ከሁሉ በላይ ከፍ ከፍ አደረገው፤ ከስም ሁሉ በላይ የሆነ ስም ሰጠው። 10 በዚህም ምክንያት ጉልበት ሁሉ በሰማይና በምድር፤ ከምድርም በታች ሁሉ በኢየሱስ እግሮች በታች እንዲንበረከኩ ነው። 11 አንደበትም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር እንዲሆን፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ ነው ብሎ እንዲመሰክር ነው። 12 ስለዚህ ወዳጆቼ ሆይ፤ እኔ ከእናንተ ጋር በነበርኩበት ጊዜ ሁሉ እንደምትታዘዙ፥ይልቁንም አሁን ከእናንተ በራቅሁበት ጊዜ ይበልጥ ታዛዦች እንድትሆኑ ነው። 13 በፍርሃትና በመንቀጥቅቀጥም መዳናችሁን ሥሩ። ምክንያቱም ለመልካምነቱ መፍቃዱንና ማድረግን በእናንተ የሚሠራ እግዚአብሔር ነው። 14 ማናቸውንም ነገር ሳታጉረምግሙና ሳትከራከሩ አድርጉ። 15 ይህን በማድረግ ነውርና ነቀፋ የሌለባችሁ ታማኝ የአግዚአብሔር ልጆች ትሆናላችሁ። በዚህ በጠማናና በመጥፎ ትውልድ መካከል በዚህ ዓለም እንደ ደማቅ ብርሃን ታበራላችሁ። 16 ሕይወት የሚገኝበትን ቃል አጥብቃችሁ በምትይዙበት ጊዜ በከንቱ እንዳልሮጥሁና በከንቱም እንዳልደከምሁ ክርስቶስ በሚመለስበት ቀን ለማክበር ምክንያት ሊኖረኝ ይችላል። 17 ነገር ግን ለእግዚአብሔር በእምነት በምታቀርቡት መሥዋዕትና አገልግሎት ላይ የእኔም ሕይወት እንደ መሥዋዕት ሆኖ ቢቀርብ እንኳ ደስ ይለኛል። ከሁላችሁ ጋር ታላቅ ደስታ እደሰታለሁ። 18 እንዲሁም በተመሳሳይ ሁኔታ እናንተም ከእኔ ጋር ደስተኞች ትሆናላችሁ። 19 ነገር ግን እናንተ እንዴት እየሠራችሁ እንዳላችሁ ሰምቼ እንድጽናና ጢሞቲዎስን ወደ እናንተ ፈጥኜ እንደምልክ በጌታ በኢየሱስ ተስፋ አደርጋለሁ። 20 ስለ እናንተ ሁኔታ ከልብ የሚያስብ ከጢሞቲዎስ በስተቀር ሌላ ሰው የለኝም። 21 ሌሎቹ ግን የራሳቸውን ጥቅም ብቻ ስለሚፈልጉ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ግድ የላቸውም። 22 ነገር ግን ጢሞቲዎስ ልጅ አባቱን እንደሚያገለግል ከእኔ ጋር ወንጌልን በማሠራጨት እንዳገለገለና ስለታማኝነቱም የተመሰከረለት መሆኑን እናንተም ታውቃላችሁ። 23 ስለዚህ የእኔን ሁኔታ እንዳወቅሁ በፍጥነት ጢሞቲዎስን ወደ እናንተ እንደምልክላችሁ ተስፋ አደርጋለሁ። 24 እንዲያውም እኔ ራሴ በቶሎ ወደ እናንተ እንደምመምጣት በጌታ እተማመናለሁ። 25 ነገር ግን ኤጳፍሮዲቱስን መልሼ ወደ እናንተ መላክ አስፈላጊ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። እርሱ እኔን በሚያስፈልገኝ ሁሉ እንዲረዳኝ ልካችሁት የነበረውን ወንድሜና ከእኔ ጋር የተሰለፈ ወታደርና የሥራ ባልደረባዬ ነው። 26 እርሱን ወደ እናንተ የምልከውም ሁላችሁንም ለማየት በመናፈቁና እናንተም መታመሙን በመስማታችሁ ስለ ተጨነቀ ነው። በእርግጥ በጠና ታሞ ለሞት ተቃርቦ ነበር፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ምሕረት አደረገለት። 27 ከሕመሙ መዳኑ ለእርሱ ብቻ ሳይሆን ሐዘን በሐዘን ላይ እንዳይደረርብኝ ለእኔም ጭምር ነው። 28 ስለዚህ እናንተ እርሱን በማየት እንድትደሰቱና የእኔም ሐዘን እንዲቃለል እርሱን ወደ እናንተ ለመላክ ከፍተኛ ፍላጎት አድሮብኛል። 29 እንግዲህ ኤጳፍሮዲቱስን በሙሉ ደስታ በጌታ ተቀበሉት። እንደ እርሱ ያሉትን ሰዎች አክብሩአቸው ። 30 በቅርብ ተገኝታችሁ ልታደርጉልኝ ያልቻላችሁትን በእናንተ ቦታ ሆኖ ሲያገለግለኝና የሚያስፈልገኝን ለማሟላት ስለ ክርስቶስ ሥራ በማለት ለሕይወቱ ሳይሳሳ በማድረግ ለሞት ተቃርቦ ነበር።
x
በራስ ወዳድነት ወይም በከንቱ ምኞት አንዳች አታድርጉ ትኩረት፡ ''ራሳችሁን ብቻ የሚያስደስት ወይም ከሌሎች ይልቅ የበለጠ አስፈላጊ እንደሆናችሁ የሚያደርጋችሁን ከቶ አታድርጉ።'' ለራሳችሁ ብቻ የሚያስፈልጋችሁን አትፈልጉ ትኩረት፡ '' ለራሳችሁ ብቻ የሚያስፈልጋችሁን አትመልከቱ።''
በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረ አሳብ በእናንተ ይሁን እዚህ ላይ ''አሳብ'' የአንድ ሰው ዝንባሌ ወይም እንዴት እንደሚያስቡ እንደሆነ ያመልክታል። ትኩረት፡ ''በክርስቶስ ኢየሱስ ያለ አሳብ በእናንተ ይኑራችሁ'' ወይም '' ነገሮችን ክርስቶስ ኢየሱስ በሚያስብበት መንገድ አስቡ''
እግዚአብሔር ከሁሉ በላይ ከፍ አደረገው
'' እግዚአብሔር ኢየሱስን ከሁሉ በላይ ከፍ አደረገው''
ከስሞች ሁሉ በላይ
እዚህ ላይ ''ስም'' ማዕረግ ወይም ያመለክታል። ትኩረት፡ "ከማዕረግ ሁሉ በላይ" ወይም "ከክብርም ሁሉ በላይ"
ጉልበት ሁሉ
እዚህ ላይ "ጉልበት" የሰው ሁለንተና ነው። ትኩረት፡ "እያንዳንዱ ሰው" ወይም "ማንኛውም ፍጥረት"
ከምድር በታች ይህ የሚያመለክተው ሰዎች ከሞቱ በኋላ የሚሄዱበት ቦታ፤ "ገሀነም" የሚጠራ፤እንዲሁም አጋንንት የሚኖሩበት ጨለማ/ጥልቅ ገደል ተብሎ የሚጠራ።" እዚህ ላይ "ምላስ" የሰው ሁለንተናን ያመለክታል። ትኩረት፡ "እያንዳንዱ ሰው" ወይም "እያንዳንዱ ፍጥረት"
የሚያገናኝ ዐረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ በሌሎች ፊት የክርስትና ሕይወት እንዴት እንደሚኖሩ የፊልጵስዩስ አማኞችን የበረታታል፤ የእርሱንም ምሳሌ ያስታውሳቸዋል። የተወደዳችሁ ትኩረት፡"በእምነት ውድ ወዳጆቼ" እኔ ባለሁበት ትኩረት፡"እኔ ከእናንተ ጋር በምሆንበት" እኔ በራቅሁበት ትኩረት፡ "ከእናንተ ዘንድ በሌለሁበት ጊዜ" መዳናችሁን ፈጽሙ ትኩረት፡ "እግዚአብሔርን መታዘዝ ቀጥሉ" በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ "ፍርሃትና መንቀጥቀጥ" የሚሉ ቃላት የሚናገሩት መሠረታዊ ነገሩ ተመሳሳይ ነው። ጳውሎስ በእግዚአብሔር ክብር እንዲኖር ለመግለጽ ይጠቀማል። ትኩረት፡ "ጥልቅ ክብር" ፍቃዱንና ማድረግን እግዚአብሔር የእርሱን ሥራ እንድንሠራ ያበረታተናል ያስችለንማል።
ነውርና ነቀፋ የሌላችሁ ጳውሎስ ተመሳሳይ አሳብን በአዎንታዊና አሉታዊ ቃላትን በመጠቀም ይገልጻል። ትኩረት፡"ፍጽም ንፁሐን" ያለ ነቀፋ ትኩረት፡"ያለ ነውር" ወይም "ፍጹም" ብርሃን ታበራላችሁ ይህ እግዚአብሔርን በማያከብሩ ሰዎች መካከል እግዚአብሔርን እያከበሩ በጨለማ ብርሃን እያበሩ የሚኖሩ አማኞችን ያወዳድራል ።ትኩረት፡ "እግዚአብሔርን በሚያስከብር መንገድ ኑሩ" በዓለም ላይ እዚህ ላይ "ዓለም" እግዚአብሔርን የማያከብር እሴትና አስተሳሰብን ያሳያል። በጠማማና በመጥፎ እነዚህ ሁለት ቃላት ማለት በመሠረቱ ተመሳሳይ ነው። ጳውሎስ እነዚህን ቃላት የሚጠቀመው ትውልዱ ምን ያህል ክፉ እንደሆነ ለመግለጽ ነው።ትኩረት፡"ፍጹም ክፉ" ለክብር "ሐሴት ለማድረግ" ወይም "ለመደሰት" በክርስቶስ ቀን ይህ ኢየሱስ መንግሥትን ለማጽናትና ምድርን ለመግዛት በሚመጣበት ጊዜ መሆኑን ያመለክታል። ትኩረት፡ "ክርስቶስ በሚመለስበት ጊዜ" በከንቱ አልሮጥም ወይም በከንቱ አልደክምም "በከንቱ መሮጥ" እና "በከንቱ መድከም" የሚሉ ሐረጎች እዚህ ላይ የሚሉት ተመሳሳይ ነገር ነው። ጳውሎስ ሰዎች በክርስቶስ እንዲያምኑ ያደረገው ምን ያህል ከባድ እንደሆን ለመግለጽ ነው። ትኩረት፡ "እንግዲህ የደከምሁት በከንቱ አይደለም"
ነገር ግን የእኔ ሕይወት እንደ መሥዋዕት ሆኖ ቢቀረ እንኳ ደስ ይለኛል፤ ከሁላችሁ ጋር ታላቅ ደስ ይለኛል ጳውሎስ የራሱ ሞት ከብሉይ ኪዳን ወይን ወይም የወይራ ዘይት በእንስሳት መሥዋዕት ላይ ወይም አጠገብ መሥዋዕት አቅራቢ ለእግዚአብሔር እንደሚያፈስ ዓይነት ያወዳድራል። ጳውሎስ እያለ ያለው እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ከሆነ ለፊልጵስዩስ ሰዎች በደስታ ልሞት እንደሚገባ ነው። ትኩረት፡ "ነገር ግን ሮማውያን ሊሰቅሉኝ ቢወስኑ እንኳ የእኔ ሞት ለእናንተ እምነትና ደስታ የሚያደርግ ከሆነ የበለጠ እግዚአብሔርን የሚያስደስት ከሆነ እጅግ ደስ ይለኛል" በተመሳሳይ ሁኔታ ትኩረት፡ "በተመሳሳይ ሁኔታ" በታላቅ ደስታ ጋር መደሰት አለባችሁ "ከታላቅ ደስታ ጋር መደሰት" የሚለው ሐረግ ለመግለጽ ይጠቀማል። ትኩረት፡ "ከእኔ ጋር በታላቅ ደስታ እንድትደሰቱ እፈልጋለሁ"
የሚያገናኝ ዐረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ ጢሞቲዎስን እንደሚልክላቸው አሳብ እንዳለና ኤጳፍሮድጡን በልዩ ሁኔታ እንዲያስተናግዱ ይነግራል። ነገር ግን በጌታ ኢየሱስ እጠብቃለሁ ትኩረት፡ "ነገር ግን ጌታ ኢየሱስ ፈቃዱ ከሆነ እጠብቃለሁ" ስለ እነርሱ ሁሉ እዚህ ላይ "እነርሱ" የሚለው ቃል ጳውሎስ ወደ ፊልጵስዩስ ለመላክ መተማመን የማይችላቸው የሰዎች ቡድን ናቸው። ጳውሎስ ደግሞ መሄድ የነበረባቸው ነገር ግን ጳውሎስ መልእክታቸውን ለመፈጸም ያልታመነ፤ ከቡድኑ ጋር ደስተኛ አለመሆኑን እየገለጸ ነው።
ጢሞቲዎስ ራሱን አረጋገጠ ትኩረት፡ "ጢሞቲዎስ ለኢየሱስ ነገሮች ጥንቃቄ መውሰድ አሳይቶአል"
ልጅ አባቱን እንደሚያገለግል እኔን አገለገለኝ ጳውሎስ የጢሞቲዎስን አገልግሎት ከእርሱ ጋር ልጅ አባቱን እንደሚያግልግል ያወዳድራል።
በወንጌል ሥርጭት ትኩረት፡" ለሰዎች ስለ ወንጌል መንገር" በጌታ እታመናለሁ እኔ ራሴ ቶሎ እመጣለሁ ትኩረት፡ "የጌታ ፈቃድ ከሆነ ቶሎ እንደምመጣ እርግጠኛ ነኝ"
ኤጳፍሮዲቱስን ይህ ሰው ጳውሎስን በእስር ቤት እንዲያገለግል የተላክ ነው። አብሮኝ የሚሠራና ወታደር እዚህ "ወታደር" ጦርነትን ከሚዋጋ ሰው መንፈሳዊ ጦርነት ከሚዋጋ አማኝ ጋር የሚነፃፀር ነው። ጳውሎስ አማኙ ወንጌልን ለማሰራጨት ከክፉ ጋር የሚያደርገው ትግል ለመግለጽ ነው። ትኩረት፡"በእምነት ከእኛ ጋር አብሮ የሚሠራና የሚታገል" መልእክተኛና በሚያስፈልገኝ አገልጋይ ትኩረት፡ "መልእክቶቻችሁን ወደ እኔ የሚያመጣና በሚያስፈልገኝ የሚረዳኝ" በጥልቀት አዝኖአል፤ ከሁላችሁ ጋር ለመሆን ፈልጎአል ሐዘን ላይ ሐዘን ትኩረት፡በእስር ላይ እያለሁ ሐዘን ላይ ሐዘንን ልጨምርብኝ ነበር"
ኤጳፍሮዲቱስን ተቀበሉት "ኤጳፍሮዲቱስን ተቀበሉት" በጌታ ከሁሉ ደስታ ጋር ትኩረት፡ "በጌታ በእምነት አብሮ የሚሠራ" ወይም "ጌታ ኢሱስ ስለሚወደን ታላቅ ደስታ አለን"(UDB) የክርስቶስን ሥራ የሚሠራ ትኩረት፡ለክርስቶስ መሥራት"(UDB) የሚያስፈልገኝን አዘጋጀ ትኩረት፡"የሚያስፈልገኝን ያዘጋጃል"
1 በጨረሻም ወንድሞቼ ሆይ፥ በጌታ ደስ ይበላችሁ። ከዚህ በፊት የጻፍኩላችሁን ተመሳሳይ ነግሮች አሁንም ደግሜ ብጽፍላችሁ አይታክተኝም። እነዚህ ነገሮች እናንተን ከስሕተት ይጠብቃችኋል። 2 ከውሾች ተጠንቀቁ። ከክፉ ሠራተኞች ተጠንቀቁ፤ከሐሰተኞች መገረዝም ተጠንቀቁ። 3 እኛ በእግዚአብሔር መንፈስ የምናመልክ፤ በሥጋም የማንታመን፤ በክርስቶስ ኢየሱስ የምንታመን የተገረዝን ነን። 4 በሥጋ ትምክሕት የሚያስፈልግ ቢሆን እኔ በብዙ ነገር ልመካ እችል ነበረ። ማንም በሥጋ የሚመካበት አለኝ ብሎ የሚያስብ ሰው ቢኖር እኔ ከእርሱ የበለጠ የምመካበት ብዙ አለኝ። 5 እኔ በተወለድኩ በስምንተኛው ቀን ተገርዤአለሁ፤ በትውልዴም ከብንያም ነገድ የሆንኩ እስራኤላዊ ነኝ፤ ከዚህም የተነሳ ጥርት ያልኩ ዕብራዊ ነኝ። የአይሁድን ሕግ ስለ መጠበቅም ቢሆን ፈሪሳዊ ነበርኩ። 6 በቅንዓት ቤተ ክርስቲያን አሳድድ ነበር። ሕግን በመጠበቅ ስለ መጽደቅም ቢሆን ያለ ነቀፋ እኖር ነበር። 7 ነገር ግን ከዚህ በፊት ጠቃሚዎች ናቸው ብዬ አምንባቸው የነበሩትን ነገሮች ሁሉ ስለ ክርስቶስ ብዬ ዋጋ እንደሌላቸው እንደ ከንቱ ነገሮች አድርጌ ቆጥሬአቸዋለሁ። 8 በርግጥ፥ ከሁሉ ይልቅ ስለሚበልጥ ስለ ክርስቶስ ጌታዬ ዕውቀት ነገር ሁሉ ጉዳት እንዲሆን እቆጥራለሁ። ስለ እርሱም ሁሉን ነገር አጥቻለሁ። ክርስቶስንም ለማግኝትና በእርሱም ለመገኝት ስል ሁሉን ነገር እንደ ቤት ጥራጊ እቆጥራለሁ። 9 እንግዲህ በሕግ ላይ የተመሠረተው የራሴ ጽድቅ የለኝም። በዚህ ፈንታ በክርስቶስ በኩል በሚገኝ እምነት የእግዚአብሔር ጽድቅ አለኝ። 10 ይኸውም እርሱን የማወቅ ጽድቅ፤ የእርሱ የትንሣኤ ኃይልና የመከራው ተካፋይ የመሆንና በሞቱም ክርስቶስን ለመምሰል ነው። 11 ደግሞም ከሙታን ትንሣኤን አገኝ ዘንድ ነው። 12 እነዚህን ነገሮች ገና አልጨበጥኩአቸውም ፤ ፍጹም ሆኜአለሁ ማለትም አልችልም። ነገር ግን በክርስቶስ ኢየሱስ ያገኘሁትን አገኝ ዘንድ ወደ ፊት ጥረቴን እቀጥላለሁ። 13 ወንድሞች ሆይ፤እኔ ራሴ ገና እንደጨበጥኩ አልቆጥርም። ነገር ግን አንድ ነገር አደርጋለሁ፤ ይኸውም በስተኋላዬ የነበረውን እየረሰሁ በፊቴ ያለውን ለመያዝ እተጋለሉ። 14 እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት ጠርቶ ሽልማቴን ለማግኘት በፊት ወዳለው ግብ እሮጣለሁ። 15 ስለዚህ እኛ ብዙዎቻችን በመንፈሳዊ ሕይወት እንዳደጉ ሰዎች ነገሮችን ሁሉ ማሳብ ይኖርብናል። ደግሞ በማንኛውም ነገር የተለያየ አስተሳሰብ ቢኖራችሁ እግዚአብሔር ሁሉንም ግልጥ ያደርግላችኋል። 16 ይሁን እንጂ በደረሰንበት በዚያው ሁኔታ እንመላለስ። 17 ወንድሞች ሆይ፥ የእኔን ምሳሌነት ተከተሉ፤ በእኛም ምሳሌነት የሚመላለሱትን ሁሉ ልብ ብላችሁ ተመልከቱ። 18 ከአሁን በፊት ብዙ ጊዜ እንደ ነገርኳችሁና አሁንም እንባዬን እያፈሰስኩ እንደምነግራችሁ ሁሉ ብዙዎቹ በአካሄዳቸው የክርስቶስ መስቀል ጠላቶች ሆነዋል። 19 የእነርሱ አምላክ ሆዳቸው ነው፤ አሳፋሪ የሆነ ነገርም ለእነርሱ ክብራቸው ነው፤ አሳባቸውም የሚያተኩረው በምድራዊ ነገር ላይ ነው ስለዚህ የእነርሱም መጨረሻ ጥፋት ነው፤ 20 ነገር ግን የሚመጣውን አዳኝ ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የምንጠብቅ የሰማይ መንግሥት ዜጎች ነን። 21 እርሱ ይህን የተዋረደውን ሰውነታችንን በመለወጥ የእርሱን ክቡር ሰውነት እንዲመስል ያደርገዋል። ይህንንም የሚያደርገው ሁሉን በሥልጣኑ ሥር ለማድረግ በሚያስችለው ኃይል ነው።
የሚያገናኝ ዐረፍተ ነገር፡ አብሮ የሚሠሩ አሮጌውን የአይሁድ ሕግ ለመከተል የሚሞክሩትን የእምነት ወዳጆችን ለማስጠንቀቅ፤ ጳውሎስ የአማኞችን ስደት ስለ ራሱ ምስክርነት ይሰጣል። በመጨራሻም፤ ወንድሞቼ ትኩረት፡ "ወንድሞቼ ሆይ፤ወደ ፊት ስለሚሆን፤ ወይም "ወድሞቼ ሆይ፤ስለሌሎች ጉዳዮች" በጌታ ደስ ይበላችሁ ትኩረት፡ጌታ ስላደረጋቸው ሁሉ ደስ ይበላችሁ" ከዚህ በፊት የጻፍኩላችሁን ተመሳሳይ ነገሮች አሁንም ደግሜ ብጽፍላችሁ አይታክተኝም ትኩረት፡"አሁንም እነዚህን ተመሳሳይ ትምህርቶችን ብጽፍ ደስ ይለኛል" እናንተን በሰላም ይጠብቁአችኋል እዚህ ላይ "እነርሱ" የሚለው የጳውሎስን አስተምህርሆዎች ያሳያል። ትኩረት፡"እነዚህ ትምህርቶች ከስሕተት ስለሚጠብቁአችሁ"
ተጠበቁ "ጥንቃቄ አድርጉ" ወይም "ተጠንቀቁ" ውሾች፤ክፉ አድራጊዎች፤ ከሐሰተኞች መገረዝ እነዚህ የሐሰት አስተማሪዎች ተመሳሳይ ቡድን የሆኑ የተለያዩ ሦስት መንገዶችን የሚገልጹ ናቸው። ውሾች "ውሾች" የሚለው ቃል ከአይሁድ ውጪ የሆኑትን ሰዎችን ለመግልጽ አይሁዶች የተጠቀሙበት ነው። ጳውሎስ የሐሰት አስተማሪዎችን እንደ ስድብ ከውሾች ጋር ያነጻጽራል። በባሕላችሁ የረከሰ የተለየ እንስሳ ካለ ወይም እንደ ስድብ የሚቆጠር ካለ በውሻ ፈንታ ይህን እንስሳ ልትጠቀሙ ትችላላችሁ። ሐሰተኛ መገረዝ "መግረዝ" ማለት በአሰቃቂ ሁኔታ ማረድ ወይም መቁረጥ ማለት ነው። ጳውሎስ የሐሰት አስተማሪዎችን ለመኮነን የግሪዛትን ድርጊት በተጋነነ ሁኔታ ይገልጻል። የሐሰት አስተማሪዎች የሚሉት አንድ ሰው የተገዘ እንደሆነ ነው። ስለዚህ እኛ እውነተኛ መገረዝ ጳውሎስ በአካል ያልተገረዙትን ነገር ግን በመንፈሳዊ የተገረዙትን ማለትም በእምነት መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉትን በክርስቶስ አማኝ የሆኑትን ለማሳየት ይህን ሐረግ ይጠቀማል። ትኩረት፡ "በእውነት የእግዚአብሔር ሕዝብ" በሥጋ መመካት የለም ትኩረት፡ "እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ሥጋችንን በመቁረጥ አትመኩ"
እኔ ራሴ ትምክህት ልኖረኝ እችል ነበር። ፥ማንም ሰው በሥጋ ትምክህት አለኝ ብሎ ቢያስብ እኔ እበልጠዋለሁ ይህ ለጳውሎስ ለማመን የማይቻል መላምት ሁኔታ ነው። ጳውሎስ የሚለው እግዚአብሔር ሰዎችን በሠሩ ሥራ የሚያድን ከሆነ እግዚአብሔር እርሱን ያድን ነበር። ትኩረት፡ "ማንም ሰው እግዚአብሔርን ለማስደሰት በቂ ነገሮችን መሥራት የሚችል ቢሆን ኖሮ እኔ ነበርኩ" እኔ ራሴ ጳውሎስ "እኔ ራሴ" የሚለውን የሚጠቀመው ትኩረት ለመስጠት ነው። ትኩረት፡" በእርግጥ እኔ ነበርሁ" ተገርዤ ነበር ትኩረት፡ "ካህኑ ገርዞኝ ነበር"
ስምንተኛው ቀን "ከተወለድኩ ሰባት ቀኖች በኋላ" (UDB) ከዕብራዊ ዕብራዊ "ዕብራዊው ልጅ ከዕብራዊ ወላጆች" ከሕግ አንፃር ፈሪሳዊ ትኩረት፡"እንደ ፈሪሳዊ ሕግን በጠበቅ ፍጹም ነበርኩ"
ቤተ ክርስቲያንን አሳድድ ነበርሁ ትኩረት፡"ክርስቲያኖችን ለመጉዳት በጣም ቁርጠኛ ነበርኩ" ሕግን በመጠበቅ ያለ ነቀፋ ነበርኩ ትኩረት፡ " ሕግን በመጠበቅ ፍጹም ነበርኩ" እንደ ከንቱቆ ጥሬዋለሁ ጳውሎስ የእርሱ የጽድቅ ሥራዎች ሁሉ በክርስቶስ ፊት ከንቱ እንደሆነ ይደመድማል።
በርግጥ "በርግጥም" ወይም "በእውነት" አሁን እቆጥራለሁ "አሁን" የሚለው ቃል ጳውሎስ ፈሪሳዊ መሆኑን የተዋበትና በክርስቶስ አማኝ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ መለወጡን ለማጉላት ነው" ትኩረት፡ "አሁን በክርስቶስ አምኛለሁ" ሁሉን ነገር እንደ ጉዳት እቆጥራለህ ጳውሎስ ከክርስቶስ ሌላ በማንኛውም ነገር መታመን ከንቱ እንደሆነ ይገልጻል። ትኩረት፡ "ማንኛውንም ነገር እንደ ከንቱ እቆጥራለሁ" ከሁሉ ይልቅ ስለሚበልጠው ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ ጌታዬ ዕውቀት ትኩረት፡"የክርስቶስ ኢየሱስ ጌታዬ ዕውቀት ከሁሉ ይበልጣል" ስለ እርሱ ሁሉ ነገር እንደ ጥራጊ እቆጥራለሁ ትኩረት፡ከእርሱ የተነሣ ማንኛውንም ነገር በፈቃዴ ክጃለሁ" እንደ ቤት ጥራጊ እቆጥራለሁ ጳውሎስ አንድ ሰው የሚመካበት ነገር የሚጣል መሆኑን ያነጻጽራል። ምን ያህል ከንቱ እንደሆን ትኩረት ይሰጣራል። ትኩረት፡ "እንደ ጉድፍ አስባለሁ" ወይም "ፍጽም ከንቱ እንደሆኑ አስባለሁ" ስለዚህም ክርስቶስን አገኝ ዘንድ "ስለዚህ ክርስቶስ እንዲኖረኝ ብቻ" አሁን በእርሱ ተገኝቻለሁ "በእርሱ ተገኝቻለሁ" የሚለው ሐረግ ማለት ከእርሱ ጋር የቅርብ ግንኙነት ወይም ከክርስቶስ ጋር ህብረት መኖር ማለት ነው" ከሕግ የራሴ የሆነ ጽድቅ የለኝም ትኩረት፡"በራሴ ሕግን በመታዘዝ እግዚአብሔርን ለማስደስት አልሞክርም" በዚህ ፈንታ አለኝ "ይልቁን ይህ አለኝ" ወይም "በቀጥታ ተቃራኒውአለኝ" ከእግዚአብሔር ያለኝ ጽድቅ በእምነት በክርስቶስ ያለኝ ነው ትኩረት፡ "እግዚአብሔር በክርስቶስ ባለኝ እምነት የተነሣ እግዚአብሔር ተቀብሎኛል" የትንሣኤው ኃይል ትኩረት፡የእርሱ ኃይል ሕይወት እንደሚሰጥ አውቃለሁ" የእርሱ የመከራው ተካፋዮች "የመከራው ተካፋዮች" ሞቱን በሚመስል በክርስቶስ ተለውጫለሁ "መለወጥ" የሚለው ቃል ማለት አንድን ነገር በአንድ ነገር መለወጥ ማለት ነው።ኢየሱስ የሞተበት መንገድ የዘላለም ሕይወት አስገኘ። እንግዲህ ጳውሎስ የዘላለ ሕይወት ለማግኘ ሞቱ የኢየሱስን ሞት እንዲመስል ይፈልጋል። ትኩረት፡ "ክርስቶስ ሞቱን እንዲመስል ለውጦኛል" እንግዲህ እንደምንም ከሞት መነሳትን ለማመድ እንድችል ነው "እንደምንም" የሚለው ቃል ማለት ጳውሎስ በዚህ ዓለም ምን እንደሚሆን አያውቅም፤ ነገር ግን ምንም ቢሆን የዘላለ ሕይወት መሆኑ አይቀርም። ትኩረት፡ "እንግዲህ አሁን ምን ቢሆን ግድ የለም፤ ከሞትኩ በኋላ ወደ ሕይወት እመጣለሁ"
የሚያገናኘው ዐረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ ለአማኞች ለሚጠብቃቸው መንግሥተ ሰማያትና አዲስ ሕይወት የተነሣ የአሁኑን ሕይወት ምሳሌ እንዲከተሉ ያስጠነቀቃቸዋል። እነዚህን ነገሮች አግኝቻለሁ እነዚህ ክርስቶስን ማወቅ፤የትንሳኤውን ኃይል ማ ወቅ፤ መከራ ተካፋይ መሆንና ከክርስቶስ ጋር በሞቱና በትንሳኤው ሕብረት ማድረግን ይጨምራል። እንግዲህ አሁን ፍጹም አይደለሁም "እንግዲህ ገና ፍጹም አይደለሁም" ወይም "እንግዲህ ገና ብስለት የለኝም" ነገር ግን ወደ ፊት ጥረቴ እቀጥላለሁ "ነገር ግን ሙከራዬን እቀጥላለሁ"(UDB) እጨብጣለሁ "እነዚህን ነገሮች እቀበላለሁ" በክርስቶስ ኢየሱስ አግኝቻለሁ ትኩረት፡ "በዚህ ምክንያት ክርስቶስ የእርሱ የራስይ እንደሆንኩ ቆጥሮአል" ወንድሞች ሆይ፤ ጳውሎስ የፊልጵስዩስ አማኞችን ያመለክታል። ትኩረት፡ "የእምነት ወዳጆች" እኔ ራሴ ገና አልጨበጥኩትም ትኩረት፡ "እነዚህ ነገሮች ሁሉ ገና የእኔ መሆናቸው አልታወቀም" ከኋላዬ ያለውን እየረሰው ወደ ፊት ያለውን ለመያዝ እዘረጋለሁ በእሽቅድድም እንደሚሮጥ ሰው ከኋላ ያለውን ሳይሆን ወደ ፊት በቀራው ላይ ትኩረት እንደሚደረግ ጳውሎስ የሚናገረው የእርሱ የሃይማኖታዊ ጽድቅ ሥራ ወደ ኋላ ትቶ በክርስቶስ በተዘጋጀው እንዲጨርሰው በፊቱ ባለው ሩጫ ትኩረት ማድረግ ነው። ትኩረት፡"ቀድሞ ስለሥራሁት ግድ የለኝም" ግቡን ለመድረስ በክርስቶስ የእግዚአብሔርን ጥሪ ለማሸነፍ ወደ ፊት ጥረቴን እቀጥላለሁ ጳውሎስ እሽቅድድምን ለማሸነፍ እንደሚሮጥ ንጽጽሩን ይቀጥላል፤ ጳውሎስ ለማገልገልና ለክርስቶስ በመታዘዝ መመላለስን ትኩረት ያደርጋል። ትኩረት፡" የእርሱ ለመሆንና ከሞትኩ በኋላ እግዚአብሔር ሲጠረኝ ወደ ራሱ ለመሄድ በክርስቶስ ማመኔን እቀጥላለሁ"
ስለዚህ እንደ ባለአእምሮ እናስብ ጳውሎስ የእምነት ወዳጆችን እርሱ እንደ ጠቀሳቸው ፍላጎት እንዲኖሩ ይፈልጋል PHP 3:8-11። ትኩረት፡ "በእምነት እንደ ጠነከሩ ሆነው አንድ አሳብ እንዲያስቡ ሁላችንንም አማኞች አደፋፍራለሁ" እንደምታስቡ እዚህ ላይ "እናንት" የሚለው ቃል የሚያሳየው በተለየ ሁኔታ የሚያስቡ አማኞች ወይም ከጳውሎስ ጋር የማይስማሙትን ነው። እግዚአብሔር ደግሞ ለእናንተ ይገልጻል "እግዚአብሔር ደግሞ ግልጥ ያደርግላችኋል" በየትኛውም ደርጃ የደረስን ቢሆን በዚያው በደረስንበት ሁኔታ እንመላለስ ትኩረት፡"ሁላችንም በተቀበልነው እውነት መሠረት በመታዘዝ እንቀጥል"
ወንድሞች ሆይ፤ ተባበሩኝ ጳውሎስ የፊልጵስዩስ አማኞችን እንደ ራሱ ወንድሞቹ በቁጥር ይገልጻል። እኔን ምሰሉ "እኔ የማደርገውን አድርጉ" ወይም "እኔ እንደምኖር ኑሩ" በጥንቃቄ ጠብቁ "በጥንቃቄ ተመልከቱ" በምሳሌአችን ለሚመላለሱ "ቀድሞኑ እኔ እንደምኖር የሚኖሩ" ወይም "ቀድሞኑ እኔ እንደማደርገው የሚያደርጉ" ሁልጊዜ እንደ ነገርኩአችሁ "ብዙውን ጊዜ ነግሬአችኋለሁ" በእንባ እነግራችኋለሁ "በታላቅ ሐዘን እነግራችኋለሁ" ብዙዎች የክርስቶስ ጠላቶች ሆነው ይኖራሉ እዚህ ላይ "የክርስቶስ መስቀል" የክርስቶስን መከራና ሞትን ያመለክታሉ። ጠላቶቹ በክርስቶስ እናምናለን የሚሉና ነገር ግን የክርስቶስን መከራውን ለመቀበል ወይም ፤ለመሞት ፍቃደኛ የማይሆኑ። ትኩረት፡ብዙ ሰዎች በኢየሱስ እንደሚያምኑ የሚናገሩ ነገር ግን ሥራቸው መከራ ሊቀበልና በመስቀል ላይ ለመሞት ፍቃደኛ የሆነው የክርስቶስ ጠላቶች ናቸው።" መጨራሻቸው ጥፋት ትኩረት፡ "እግዚአብሔር አንድ ቀን ያጠፈቸዋል" ሆዳቸው አምላካቸው እዚህ ላይ "ሆድ" የአንድ ሰው ለአካላዊ ምቾች ፍላጎቶችን ያመለክታል። ትኩረት፡ "እግዚአብሔርን ከመታዘዝ ይልቅ ምግብና ሌሎች ለአካል የሚያስፈልጉ ምቾችን ይፈልጋሉ" ክብራቸው በነውራቸው ትኩረት፡ "ውርደት በሚሆኑ ነገሮች ላይ የሚመኩ ናቸው" ስለ ምድራዊ ነገሮች ያስባሉ እዚህ ላይ "ምድራዊ" የሚያሳየው ማንኛውም ነገሮች ለአካል ምቾት የሚሰጡና ለእግዚአብሔር ክብር የማይሰጡ ነገሮችን ያመለክታል። ትኩረት፡ "የሚያስቡት ሁሉ እግዚአብሔርን ከሚያስደስተው ይልቅ ራሳቸውን የሚያስደስቱ ነገሮችን ነው"
የእኛ፤እኛ ጳውሎስ "የእኛ" እና "እኛ" በማለት አድማጮችን ያካትታል። መኖሪያችን በሰማይ ነው "መኖሪያችን በሰማይ ነው" ወይም "እውነተኛ ቤታችን በሰማይ ነው" አዳኙን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ከምንጠባበቅበት "እኛ ከሰማይ ወደ ምድር የሚመለሰውን አዳኙን ጌታ አየሱስ ክርስቶስን እንጠባባቃለን" የተዋረደውን ሰውነታችንን ይለውጣል "የእኛን ደካማና ምድራዊ አካላችንን ይለውጣል" ክብሩን በሚመስል በተሠራው አካላት "አካሉን በሚመስል አካላት" ሁሉን ለመቆጣጠር በእርሱ ኃይል በተሠራው ትኩረት፡ "ሁሉን ነገር ለመቆጣጠር በሚጠቀምበት በተመሳሳይ ኃይል አካላችንን ይለውጣል"
1 ስለዚህ ውድ ወንድሞቼ፤ ወዳጆቼም ሆይ፤ የምናፍቃችሁ፤ ደስታዬና አክሊሎቼ የሆናችሁ በዚህ መንገድ በጌታ ጸንታችሁ ቁሙ። 2 ኤዎድያና ሲንጢኪ እርስ በርሳቸው በጌታ ተስማምተው እንዲኖሩ እለምናቸዋለሁ። 3 በርግጥ አንተም እዚያ ያለኸው የሥራ ባልደርባዬ እነዚህን ሴቶች እንድትረዳቸው እለምንሃለሁ። እነርሱም ወንጌልን በማሰራጨት ከእኔና ከቅሌምንጦስ ጋር እንዲሁም ስማቸው በሕይወት መጽሐፍ ከተጻፉት ከሌሎች የሥራ ባልደረቦቼ ጋር ብዙ ተጋድለዋል። 4 ሁል ጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ ደግሜም እላለሁ ደስ ይበላችሁ። 5 ደግነታችሁ በሰዎች ሁሉ ዘንድ ይታወቅ። 6 ስለ ሁሉም ነገር በጸሎት፤ በልመናና በምስጋና ለእግዚአብሔር አስታውቁ እንጂ ስለምንም ነገር አትጨነቁ። ጌታ ቅርብ ነውና። 7 ከማስተዋል በላይ የሆነው የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል። 8 በመጨረሻም ወንድሞችሆይ፥ እውነት የሆነውን ሁሉ፤ ክቡር የሆነውን ሁሉ፤ ትክክል የሆነውን ሁሉ፤ንጹሕ የሆነውን ሁሉ፤ ፍቅር የሆነውን ሁሉ፤ መልካም የሆነውን ሁሉ፤ በጎነት ቢሆን፤ ምስጋናም ቢሆን፤ እንደ እነዚህ ያሉትን ነገሮች ሁሉ አስቡ። 9 ከእኔ የተማራችሁትንና የተቀበላችሁትን፤ የሰማችሁትንና ያያችሁትን ማናቸውንም ነገር አድርጉ። የሰላምም አምላክ ከእናንተ ጋር ይሆናል። 10 እንደገና በመጨረሻ ጊዜ ለእኔ ማሰብ ስለ ጀመራችሁ በጌታ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል። በርግጥ ከዚህ በፊት ስለ እኔ ያሰባችሁ ቢሆንም እኔን ለመርዳት ዕድሉን አላገኝችሁም ነበር። 11 ይህን የምለው ለራሴ ጥቅም አይደለም። ምክንያቱም በሁሉም ሁኔታ ባለኝ ነገር መርካትን ተምሬአለሁ። 12 በማጣትም ሆነ በማግኘት እንዴት መኖር እንዳለብኝ ዐውቃለሁ። በማንኛውም መንገድ የመጥገብንና የመራብን፤ የማግኝትንና የማጣትን ምሥጢር ተምሬአለሁ። 13 ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን ነገር ማድረግ እችላለሁ። 14 ይሁን እንጂ፤ እናንተ የችግሬ ተካፋዮች በመሆናችሁ መልካም አድርጋችኋል። 15 እናንተ የፊልጵስዩስ ሰዎች የወንጌልን ተልዕኮ በጀመርኩበት ጊዜ ከመቄዶንያ ስወጣ ከእናንተ በቀር በመስጠትም ሆን በመቀበል ከእኔ ጋር የተባበረ ሌላ ቤተ ክርስቲያን እንዳልነበረ ታውቃላችሁ። 16 በተሰሎንቄ በነበርኩበት ጊዜም ቢሆን ከአንድ ጊዜ በላይ ለሚያስፈልገኝ ርዳታ ልካችሁልኛል። 17 ይህንንም ስል የእናንተን ስጦታ ለማግኝት በመፈለግ ሳይሆን የልግሥናችሁ ፍሬ እንዲበዛላችሁ በመመኘት ነው። 18 ሁሉንም ነገር ተቀብያለሁ፤በዝቶልኛል፤ ሞልቶልኛልም። የላካችሁልኝን ስጦታ ከኤጳፍሮዲቱስ እጅ ተቀብዬአለሁ። ይህም ስጦታ በመልካም መዓዛ እንደ ተሞላ መሥዋዕት እግዚአንሔር የሚቀበለውና ደስ የሚሰኝበት ነው። 19 ደግሞም አምላኬ እንደ ክብሩ ባለጠግነቱ በክርስቶስ ኢየሱስ አማካይነት የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ ይሰጣችኋል። 20 እንግዲህ ለአባታችንና ለአምላካችን ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ክብር ይሁን፤ አሜን። 21 በክርስቶስ ኢየሱስ ለሆኑት ሁሉ ሰላምታ አቅርቡልኝ። ከእኔም ጋር ያሉት ወንድሞች ሰላምታ ያቀርቡላችሁኋል። 22 እዚህ ያሉት አማኞች ሁሉ በተለይም የሮማ ቤተ መንግሥት ያሉ ሠራተኞች ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። 23 የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከመንፈሳችሁ ጋር ይሁን።
የሚያገነኝ ዐረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ በፊልጵስዩስ ለሚኖሩ አማኞች በህብረት ጉዳዮች ላይና አማኞች ከአንዳንድ ተጨባጭ መመሪዎች ጋር ለጌታ እንዴት እንደሚኖሩ መመሪያ መስጠቱን ይቀጥላል። ስለዚህ የምናፍቃችሁ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ትኩረት፡ "የእምነት ወዳጆቼ እወዳችኋለሁ እንዲሁም መጥቼ እናንተን ለጠየቅ ከፍተኛ ፍላጎት አለኝ" ደስታዬና አክሊሎቼ ጳውሎስ"ደስታ" የሚለውን ቃል የደስታው ምክንያት የፊልጵስዩስ ቤተ ክርስቲያን እንደሆነች ለመግልጽ ይጠቀማል። "አክሊል" ከቅጠል የሚሠራና አንድ ሰው አንድ ጨወታ ሲያሸንፍ ለክብር ምልክት እንዲሆን በጭንቅላት ላይ የሚደፋ ነው። እዚህ ላይ "አክሊል" የሚለው ቃል የፊልጵስዩስ ቤተ ክርስቲያን ለጳውሎስ በእግዚአብሔር ፊት ክብርን አምጥቶአል። ትኩረት፡ "በኢየሱስ በማመናችሁ ምክንያት ደስታ ሆናችኋል እንዲሁም ለሥራዬ ሽልማቴና ክብሬ ናችሁ" የተወደዳችሁ ወዳጆቼ ሆይ፤በዚህ መንገድ ጸንታችሁ ትኩረት፡ "እንግዲህ ውድ ወዳጆቼ እኔ ባስተመኩአችሁ መንገድ ለጌታ መኖራችሁን ቀጥሉ" ከኤዎድያና ከሲንጢኪ ጋር አብሬ እያዘንኩ ነው በፊልጵስዩስ ቤተ ክርስቲያን ጳውሎስን የረዱ አማኝ የነብሩ ሴቶች ናቸው።ትኩረት፡ " ኤዎዲያንና ሲንጢኪን እለምናቸዋለሁ" በጌታ በአንድ ልብ ሁኑ "በአንድ ልብ ሁኑ" የሚለው ሐረግ ተመሳሳይ አስተሳሰብ ወይም አመለካከት ማለት ነው። ትኩረት፡ "በአንድ ጌታ ስለምታምኑ እርስ በርሳችሁ ተስማሙ" በርግጥ እውነተኛ የሥራ ባልደረባዬ ደግሞ እያስተናገድኩ ነው እዚህ ላይ "እናንተ" የሚለው ቃል አስፈላጊ ነው። ጳውሎስ የሰው ስም አልጠቀሰም። ወንጌልን ለማሰራጨት ከጳውሎስ ጋር የሠራ አንድ ሰው የሚጠቅሰው "እውነተኛ የሥራ ባልደረባዬ" ብሎ ብቻ ይጠራል። ትኩረት፡ "አዎን፤ እውነተኛ የሥራ ባልደረባዬ ደግሞ እጠይቃለሁ" ከቄሌመጦስ ጋር ቄሌመንጦስ አማኝ የነበረውና በፊልጵስዩስ ቤተ ክርስቲያን የሚሠራ ነበር። ስማቸው በሕይወት መጽሐፍ ላይ ያላቸው ትኩረት፡ "ስማቸውን በሕይወት መጽሐፍ እግዚአብሔር የጻፋቸው"
ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችህ ደግሜ እላለሁ በጌታ ደስ ይበላችሁ ጳውሎስ የሚናገረው ለሁሉም ፊልጵስዩስ አማኞች ነው።ደስ የበለጠ ትኩረት ለመስጠት እንዴት አስፈላጊ እንደሆነ ይበላችሁ የሚለውን ትእዛዝ ይደግማል ። ትኩረት፡ "ጌታ ስላደረገላችሁ ነገር ደስ ይበላችሁ! እንደገና እነግራችኋለሁ ደስ ይበላችሁ!" ጌታ ቅርብ ነው አማራጭ ትርጉሞች 1)ጌታ ኢየሱስ ለአማኞቹ ቅርብ ነው ወይም2) ጌታ ኢየሱስ ወደ ምድር የሚመለስበት ቀን ቅርብ ነው። በሁሉ ነገር በጸሎት የሚያስፈልጋችሁን ጠይቁ አመስግኑም "የሚያስፈልጋችሁን እግዚአብሔርን በጸሎትና በምስጋና ጠይቁ" ከመረዳት የሚያልፈውን "ልንረዳው ከምንችለው በላይ" ልባችሁንና አሳባችሁን ይጠብቃል ይህ የእግዚአብሔር ሰላም እንደ ወታደር ስሜቶቻችንና አሳቦቻችንን ከጭንቀት የሚጠብቀውን ያቀርባል። ትኩረት፡ "እንደ ወታደር ስሜታችንና አሳባችንን ስለዚህ ዓለም መጨነቅ ይጠብቃችኋል"
በመጨረሻ ይህ የደብዳቤውን ይህ ክፍል ያጠቃልላል። ጳውሎስ አማኞች ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም እንዲኖር እንዴት እንደሚኖሩ ማጠቃለያ እየሰጠ ነው። ወንዲሞች ሆይ እዚህ ላይ ይህ ማለት ክርስቲያን ወዳጆች፤ ወንዶችንና ሴቶችን ጨምሮ ከእግዚአብሔር ጋር እንደ ሰማያዊ አባታቸው ሁሉም አማኞች በክርስቶስ አንድ መንፈሳዊ ቤተ ሰብ አባላት ስለሆኑ ነው። ማንኛውም ነገሮች በፍቅር ነው "ማንኛውም ነገሮች የሚያስደስቱ ናቸው" ማንኛውም ነገሮች ከመልካም የሚነገር "ማንኛውም ነገሮች ሰዎች የሚያደንቁ" ወይም "ማንኛውም ነገሮች ሰዎች የሚያከብሩ" ትክክል ይሆነውን ሁሉ "በሞራል መልካም ከሆኑ" ማንኛውም ምስጋና ካላቸው "ለምስጋና ምክንያት ከሆኑ" እነዚህን ነገሮች አስቡ "ስለእነዚህ ነገሮች አስቡ" ከእኔ የተማራችሁትንና የተቀበላችሁትን የሰማችሁንና ያያችሁትን "እኔ ያስተማርኩአችሁንና ያሳየኋችሁትን"
የሚያገነኘው ዐረፍተ ነገር፡ ጳውሎስ የሚናገረው በገንዘብ ስለ ደገፉት ሲሆን፤ እንድዲሁም በሰላምታና ምስጋና ይደመድማል። ከዚህ በፊት ስለ እኔ ያሰባችሁ ቢሆንም እኔን ለመርዳት ዕድሉን አላገኛችሁም ነበር። "ካሁን በፊት ስለ እኔ ታስቡ እንደነበረ አውቃለሁ፤ ነገር ግን ድጋፋችሁን ለመላክ ምክንያት አልነበራችሁም" የረካ መሆን "መርካት" ወይም " ደስተኛ መሆን" በሁሉም ሁኔታ "በየትኛውም ሁኔታ ቢሆን ግድ የለኝም" እንዴት እንደምኖር አውቃለሁ ትኩረት፡ "ትክክለኛ አስተሳሰብ እንዴት እንደሚኖረኝ አውቃለሁ" በአስፈላጊ ጊዜ "የሚያስፈልገኝ ሁሉ በማይኖረኝ ጊዜ" በሚበዛበት ጊዜ "ከሚያስፈልገኝ በላይ ሲሆረኝ" በመጥገብና በመራብ፤ በመብዛትና በሚያስፈልገኝ ጊዜ እነዚህ ሁለት ሐረጎች በመሠረቱ ተመሳሳይ ነገር ነው። ጳውሎስ በማንኛውም ሁኔታ መርካትን እንዴት እንደተማረ ትኩረት ለመስጠት እነዚህን ሐረጎች ይጠቀማል። ኃይልን በሚሰጠኝ ሁሉ ማድረግ እችላለሁ "ሁሉን ማድረግ እችላለሁ ምክንያቱም ክርስቶስ ኃይልን ይሰጠኛል"
በችግሬ ጊዜ "ነገሮች አስቸጋሪ በሚሆኑበት ጊዜ" የወንጌል ተልእኮ ይህ የሚያመለክተው ጳውሎስ ስለ ኢየሱስ ለመንገር ወደ ተለያዩ ከተሞች መጓዙን ነው። በመስጠትና በመቀበል ጉዳይ ላይ ከእናንተ በስተቀር የረዳኝ ቤተ ክርስቲያን የለም ትኩረት፡ "የእናንተ ቤተ ክርስቲያን ብቻ ናችሁ ገንዘብ ወይም ርዳታ የሰጣችሁኝ" ፍሬአችሁ እንዲበዛላችሁ እፈልጋለሁ ጳውሎስ የቤተ ክርስቲያን ስጦታ ለአንድ ሰው የበለጠ የሚጨምረው ብልጽግና እያነጻጸረ ነው።ጳውሎስ የፊልጵስዩስ ሰዎች መንፈሳዊ በረከት ለመቀበል ስለሚችሉ እንዲሰጡ ይፈልጋል"
ሁሉም ነገር በብዛት አለኝል። ሞልቶልኛል ትኩረት፡ "ማንኛውም የሚያስፈልገኝና የሚተርፍ አለኝ" እነርሱም ጠፋጭ መዓዛ ያለው፤ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት ያለው መሥዋዕትና እግዚአብሔርን የሚያስደስት ነው። መልካም መዓዛ፤ ተቀባይነት ያለው እግዚአብሔርን የሚያደስት መሥዋዕት፤ጳውሎስ የፊልጵስዩስ ቤተ ክርስቲያን ስጦታን ከብሉይ ኪዳን መሥዋዕት ጋር እያነጻጸር ነው። ካህናት እግዚአብሔርን ደስ የሚያስኘውን መሥዋዕት ያቃጥላሉ። ጳውሎስ የቤተ ክርስቲያን ስጦታ ታላቅ ዋጋ ያለ መሆኑን ትኩረት እየሰጠ ነው። ትኩረት፡ "እነዚህ ስጦታዎች እግዚአብሔርን የሚያስደስት እንደሆነ አረጋግጣለሁ" የሚያስፈልገውን ሁሉን ያዘጋጃል "የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ ያዘጋጃል" በክርስቶስ ኢየሱስ እንደ ክብሩ ባለ ጠግነት ትኩረት፡ "በክርስቶስ ከክብሩ ባለጠግነት ይሰጣል" አሁን ለአላካችን "አሁን" የሚለው ቃል የመዝጊያ ጸሎትና የዚህ ደብዳቤ ክፍል መደምደሚያ ነው።
1 በእግዚአብሔር ፈቃድ የክርስቶስ ኢየሱስ ሐዋርያ ከሆነው ከጳውሎስና ከወንድማችን ከጢሞቲዎስ፤ 2 በቆላስይስ ለሚኖሩ ለእግዚአብሔር ለተለዩና በክርስቶስ ታማኝ ለሆኑ አማኞች፤ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ጸጋና ሰላም ይሁንላችሁ። 3 ለእናንተ በምንጸልይበት ጊዜ ሁሉ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባት እግዚአብሔርን እናመሰግናለንን። 4 በክርስቶስ ኢየሱስ ስላላችሁ እምነትና ለእግዚአብሔር ለተለዩት ሁሉ ስላላችሁ ፍቅር ሰምተናል። 5 በሰማይ ከተጠበቀላችሁ ከመታመነ ተስፋ የተነሣ ይህ እምነትና ፍቅር አላችሁ። ስለዚህም ተስፋ በወንጌል የእውነት ቃል አስቀድማችሁ ሰማችሁ፤ ይህም ወደ እናንት ደርሶአል። 6 ይህንም ወንጌል ከሰማችሁበትና የእግዚአብሔርን ጸጋ በእውነት ከተረዳችሁበት ቀን ጀምሮ በእናንተም ዘንድ እየሠራ እንዳለ ሁሉ በዓለም ዙሪያ ሁሉ ፍሬ እያፈራና እያደገ ነው። 7 በእኛ ምትክ ለእናንተ የክርስቶስ ታማኝ አገልጋይ የሆነውና ከእኛም ጋር አብሮን ከሚያገለግል ከተወዳጁ ከኤጳፍራ ይህን ተምራችኋል። 8 ደግሞም በእግዚአብሔር መንፈስ ያላችሁን ፍቅር ነግሮናል። 9 ከዚህም ፍቅር የተነሣ ስለ እናንተ ከሰማንበት ቀን ጀምሮ ለእናንተ ከመጸለይ አላቋረጥንም። በፈቃዱ ዕውቀት፣ በጥበብ ሁሉና በመንፈሳዊ ማስተዋል እንድትሞሉ እንጸልይላችኋለን። 10 ጌታን ደስ በሚያሰኝ መንገድ በሁሉም እንደሚገባ እንድትመላለሱ፤ በማናቸውንም መልካም ሥራ ፍሬ እንድታፈሩና በእግዚአብሔርም ዕውቀት እንድታድጉ እንጸልያለን። 11 በሁሉም ነገር እንድትጽኑና ትእግሥት እንዲኖራችሁ ፣ከኅይሉ ክብር የተነሣም በሁሉ ብርታትና ጥንካሬ እንዲኖራችሁ እንጸልያለን። 12 በብርሃን ከሚኖሩት አማኞች ጋር የርስቱ ተካፋይ እንድንሆን ላበቃን ለእግዚአብሔር በደስታ ምስጋና ማቅረብ እንድትችሉ እንጸልያለን። 13 ከጨለማ ኅይል አዳነን፤ ወደ ተወደደውም ወደ ልጁ መንግሥት አሸጋገረን። 14 በልጁም የኅጢአታችንን ይቅርታ፣ ድነትን አገኘን። 15 ልጁ የማይታየው አምላክ ምሳሌ ነው። እርሱ የፍጥረት ሁሉ በኩር ነው። 16 ምክንያቱም በሰማያትና በምድር፤ የሚታዩትና የማይታዩት ነገሮች ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋል። ዙፋናትም ሆኑ ኅይላት ወይም ግዛቶችች ወይም ሥልጣናት፤ሁሉም ነገር በእርሱና ለእርሱ ተፈጥረዋል። 17 እርሱ ከሁሉ በፊት ነበረ፤ሁሉም ነገር የተያያዘው በእርሱ ነው። 18 እርሱ አካሉ ለሆነችው ቤተ ክርስቲያን ራስ ነው። እርሱ የሁሉም መገኛና የሁሉም የመጀመሪያ፣ከሙታንም በኩር ነው። 19 በመሆኑም በሁሉም ነገሮች መካከል የመጀመሪያ ነው። በእርሱ የእግዚአብሔር ሙላቱ ሁሉ እንዲኖርና እግዚአብሔር በልጁ በኩል ሁሉን ነገር 20 ከራሱ ጋር ያስታርቅ ዘንድ ስለ ወደደ ነው። እግዚአብሔር ልጁ በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደም በሰማያትም ሆነ በምድር ያሉትን ነገሮች ሁሉ አስታረቀ። 21 እናንተም ቀድሞ ከእግዚአብሔር ርቃችሁ ነበር፤ በአሳባችሁና በክፉ ሥራችሁም ምክንያት ጠላቶች ነበራችሁ። 22 አሁን ግን ቅዱሳንና ንጹሓን፤ ነቀፋም የሌለባችሁ አድርጎ በፊቱ ሊያቀርባችሁ በልጁ ሞት እግዚአብሔር ከራሱ ጋር አስታረቃችሁ። ይህም በእርሱ ተመሥርታችሁና ተደላድላችሁ በወንጌሉ ከተገኘው ተስፋ ሳትናወጡ 23 በእምነት ጸንታችሁ እንድትኖሩ ነው። ይህም ወንጌል እናንተ የሰማችሁትና ከሰማይ በታች ላለ ፍጥረት ሁሉ ተሰብኮአል። እኔም ጳውሎስ አገልጋይ የሆንኩት ለዚህ ወንጌል ነው። 24 አሁን ስለ እናንተ በምቀበለው መከራ ደስ ይለኛል። አካሉ ስለ ሆነችው ስለ ቤተ ክርስቲያንም ከክርስቶስ መከራ ከመካፈል የጎደለውን በሥጋዬ አሟላለሁ። 25 የእግዚአብሔርን ቃል በሙሉ ለእናንተ እንድገልጥ ከእግዚአብሔር በተሰጠኝ ኅላፊነት ቃሉን ለመፈጸም የማገለግለው ይህችን ቤተ ክርስቲያን ነው። 26 ይህም ባለፉት ዘመናትና ትውልዶች ከሰው ልጆች ተሰውሮ የቆየውና አሁን ግን እግዚአብሔር ለሚያምኑት ሁሉ የገለጠው ምስጢር ነው። 27 እግዚአብሔርም በእናንተ መካከል ለአሕዛብ ሊገልጥላቸው የፈለገው የዚህ ምስጢር የክብር ብልጽግና ምን ያህል ታላቅ እንደሆነ ነው። ይህም ምሥጢር በተስፋ የምንጠባበቀው ክብር የሚገኝበት ክርስቶስ በእናንተ መካከል መሆኑ ነው። 28 የምንሰብከው እርሱን ነው። እያንዳንዱን ሰው በክርስቶስ ፍጹም አድርገን ለማቅረብ ጥበብን ሁሉ በማስተማርና በመምክር ሰውን ሁሉ እንገስጻለን። 29 በውስጤ በኅይል በሚሠራው መሠረት በብርቱ እየታገልኩ እደክማለሁ።
አጠቃላይ መረጃ: ይህ ወደ በቆላስያስ ለሚኖሩ አማኞች በጳውሎስ እና በጢሞቴዎስ አመካኝነት የተጻፈ ደብዳቤ ነው፡፡ በእግዚአብሔር ፈቃድ የክርስቶስ ኢየሱስ ሐዋርያ የሆነ "የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ለመሆን በእግዚአብሔር የተመረጠ" ወንድሞቻችን “እኛ” በሚለው ቃል ውስጥ ጳውሎስ ተደራሲያኑንም አካቷል፡፡" ጸጋ ለእናንተ ይሁን ለሌላ ሰው ባርኮትን መስጠት ወይም ለሌላ ሰው መመኘት እናንተ በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በቆላስያስ የሚገኙ ቅዱሳንን እና ታማኝ የሆኑ ወንድሞችን ነው፡፡ ስለእናነት ዘወትር እንጸልያለን አማራጭ ትርጉም፡ "ስለ እናንተ ሁል ጊዜ ከልባችን ሆነን እንጸልያለን፡፡"
አጠቃላይ መረጃ: በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥር አመልካች ሲሆን የሚመለክተው በቆላስያስ የሚገኙ አማኞችን ነው፡፡ ስለ እናንተ ሰምተናል በዚህ ሥፍራ ጳውሎስ “እኛ” የሚለው ቃል በመጠቀም አንባቢያኑን በውስጡ አላካተተም፡፡ በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ያላችሁን እምነት "በኢየሱስ ክርስቶስ ያላችሁ እምነት" ለቅዱሳንም ሁሉ ስላላችሁ ፍቅር ሰምተን፥ "ለቅዱሳን ሁሉ ያላችሁን ፍቅር" (UDB) በሰማይ ከተዘጋጀላችሁ ተስፋን እንደሚታገኙ ካላችሁ ሙሉ እምነት የተነሣ "እግዚአብሔር በሰማይ ያስቀመጠላችሁን ተስፋ ላይ ካላችሁ እርግጠኝነት የተነሣ" እርግጠኛ ተስፋ "አጥብቃችሁ የያዛችሁት ተስፋ" ፍሬ ያፈራል እንዲሁም ያድጋል ይህ የተለያዩ ለምግብነት የሚሆኑ ነገሮችን ከሚያፈራ ዘፍ ወይም እጽዋጽ ጋር ተነጻጽሮ የቀረበ ሲሆን ሰዎችን የሚለውጠው ወንጌልም አድጎ ብዙ ሰዎች ባመኑት ቁጥር በዓለም ሁሉ ይሰራጫል፡፡ በዓለም ዙሪያ ሁሉ ወንጌል በሚታወቀው ዓለም ዙሪያ ሁሉ ይሰራጫል እንዲሁም ያድጋል፡፡ የእግዚአብሔር ጸጋ በእውነት "እውነተኛው የእግዚአብሔር ጸጋ" ወይም "እውነተኛው የእግዚአብሔር ሞገስ"
ልክ ከኤጳፍራ እንደተማራችሁት ሁሉ "ልክ ኤጳፍራ እንዳስተማራችሁ ሁሉ" ወይም "ኤጳፍራ ያስተማራችሁን ሁሉ ሙሉ ለሙሉ በሚገባ እንደተረዳችሁት ሁሉ" ልክ እደዛው “እርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የወንጌል መልዕክት በቆላስያ ከተማ ውስጥ በሚገኙ አማኞች የዕለት ተዕለት ሕይወት ላይ ያመጣውን ውጤት የሚያመለክት ነው፡፡ እናንተ ተምራችኋል በቆላስያ ከተማ ይኖሩ የነበሩት አማኞች ይህንን ተምረዋል ኤጳፍራ ኤጳፍራ Epaphras በቆላስያ ከተማ ውስጥ ከነበሩ አማኞች ወንጌል የሰበከላቸው ሰው ነው፡፡ ከተወደደ ከእኛም ጋር አብሮ ባሪያ ከሆነው ከኤጳፍራ እንዲህ ተማራችሁ፥ እርሱም ስለ እናንተ ታማኝ የክርስቶስ አገልጋይ ነው። ይህ ማለት ኤጳፍራ ጳውሎስ በእስር ቤት ባይሆን ኖሮ ልፈጽመው የሚችለው ነገር በማድረግ የክርስቶስን ሥራ የሠራ ሰው ነው ማለት ነው፡፡ አርሱ ለእኛ ገልጦልናል "ኤጳፍራ ለእኛ አስታውቆናል" በመንፈስ ስላልችሁ ፍቅር "ለአማኞች ፍቅር እንዲኖራችሁ መንፈስ ቅዱስ አቅም ሰጥቶአችዋለህ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ በክርስቶስ ስላላቸው እምነት እና በመንፈስ ስላላቸው ፍቅር ይጸልይላቸዋል፡፡ በዚህ ፍቅራችሁ ምክንያት "መንፈስ ቅዱስ ሌሎች አማኞችን መውደድ እንዲትችሉ ስላደረጋችሁ" ስለእናንተ ከሰማንበት ጊዜ አንስቶ "ኤጳፍራ ስለ እናንተ ለእኛ ከነገረበት ጊዜ አንስቶ" ሰምተናል ይህ የሚያመለክተው ጳውሎስ እና ጢሞቴዎስን እንጂ በቆላስያስ ከተማ የሚገኙ አማኞችን አይደለም፡፡ መጸለይ አላቋረጥንም "ብዙ ጊዜ እና ከልባችን ወደ እግዚብሔር እንጸልያለን" የእርሱ ፈቃድ ምን እንደሆነ ታውቁና በዚህ ትሞሉ ዘንድ እንጠይቃለን "የእርሱን ፈቃድ ታደርጉ ዘንድ በእውቀት ሞላችሁ ዘንድ እግዚአብሔርን እንጠይቀዋለን" በጥበብ እነና መንፈሳዊ መረዳት ሁሉ "በመንፈስ ቅዱስ የሚሰጥ ጥበብ እና መረዳት" በሁሉም ነገር ለጌታ እንደሚገባ ትኖሩ ዘንድ "ጌታ በሚፈቅደው መንገድ መኖር ትችሉ ዘንድ ፍሬ እንዲታፈሩ ይህ ሀረግ ፍሬጣማ እጽዋትነን ከአማኝ መልካም ሥራ ጋር የሚያነጻጽር ነው፡፡ ልክ እጽዋት አድገው ፍሬ እደሚያፈሩ ሁሉ አማኞችም በእግዚአብሔር እውት ልያድጉ እና መልካም ሥራን ልሠሩ ይገባል፡፡
ስለ እናንተ እንጸልያለን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል ጳውሎስን እና ጢሞቴዎስን የሚወክል እንጂ በቆላስያስ የሚገኙ አማኞችን የሚወክል አይደለም፡፡
እንደ ክብሩ ጉልበት መጠን በኃይል ሁሉ እየበረታችሁ፥ "በታላቅ ክብሩ አማካኝነት በኃይሉ የበረታችሁ ሁኑ" በነገር ሁሉ ጽኑ እንዲሁም ትእግስት ኑራችሁ "ፈጽማችሁ ማመናችሁን አቁሙ እንዲሁም ትእግስት ይኑራችሁ" ለአብን በደስታ ምስጋናን እያቀረባችሁ "ለአብ በደስታ ምስጋናን እያቀረባችሁ" በቅዱሳንም ርስት በብርሃን እንድንካፈል ያበቃንን አማራጭ ትርጉም: "እንዲንካፈል ያበቃንን" እንድትበቁ ያደረጋችሁን በዚህ ሥፍራ ላይ ጳውሎስ ተደራሲያኑ የእግዚአብሔር ጸጋ ተካፋዮች መሆናቸው ላይ ትኩረት ያደርጋል፡፡ ይህ ማለት ግን እርሱ ይህንን ባርኮት በመውረስ ውስጥ ምንም ድርሻ የለኝም እያለ ግን አይደለም፡፡ ርስቱን ለመካፈል "ርስቱን ለመካፈል" በብርሃን "በክብሩ መገኘት ውስጥ" for the believers አማራጭ ትርጉም: "ቅዱሳን ለሆኑት" ወይም "ለልዩ ጥቅም የተመረጡት" ለእርሱ "ለአባት"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ክርስቶስ በምን መንገድ ልቆ እንደሚገኝ ይናራል፡፡ እርሱ አዳነን "እግዚአብሔር አባት አዳነን" አፈለሰን "አሸጋገረን፡፡" በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል ጳውሎስን እና በቆላስያስ ከተማ የሚገኙ አማኞችን በውስጡ ያካትታል፡፡ በእርሱ ውድ ልጁ "የእግዚአብሔር አብ ተወዳጅ ልጁ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ" በገዛ ልጁ ቤዛነትን አገኘን "ልጁ ቤዛነትን ሰጠን" የኃጢአታችን ይቀርታን "ልጁ ኃጢአታችንን ይቅር አለን" ወይም "አብ በልጁ በኩል ኃጢአታችን ይቅር አለን"
ልጁ የማይታየው አምላክ መልክ ነው ልጁ ኢየሱስ ምን እንደሚመስል በማወቅ እግዚአብሔር አብ ምን እንደሚመስል ማወቅ እንችላለን፡፡ ልጅ ይህ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው የኢየሱስ ወሳኝ ስም ነው፡፡ እርሱ በኩር ነው "ልጁ በኩር ነው፡፡" ኢየሱስ በጣም ወሳኝ እና ልዩ የሆነ የእግዚአብሔር “ልጅ” ነው፡፡ “ልጅ” የሚለው ቃል ኢየሱስ ከአብ ጋር ያለውን ልዩ የሆነ ግንኙነት ያሳያል፡፡ ይህ በአብ እና በልጁ መካከል ያለው ግንኙነት በቋንቋችሁ ውስጥ “በልጅ” እና “አባት” የሚለውን ቃል ካልተጠቀማችሁ በስተቀር መረዳት አይቻል፡፡ ምክንያቱም ሁሉም ነገሮች የተፈጠሩት በእርሱ አማካኝነት ነው "ምክንያቱም ልጁ የተፈጠሩት ነገሮች ሁሉ ፈጥሯልና" ዙፋን ቢሆን ወይም ግዛት ወይም መንግስታት ወይም ሥልጣናት ሁሉም ነገሮች በእርሱ እና ለእርሱ ተፈጥረዋል ልጁ ሁሉን ነገር ለራሱ ፈጥረዋል ይህ ዙፋንን፣ ስልጣንን፣ ገዥዎችን እና ስልታናትን ያካትታል፡፡ እርሱ ከነገሮች ሁሉ በፊት ነው "እርሱ ከሁሉም ነገር በፊት ነበር" በእርሱ ሁሉም ነገር እርስ በእርሱ ተያይዟል "እርሱ ሁሉን ነገር አያይዟል" (UDB)
እርሱ ራስ ነው "የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ራስ ነው" እርሱ አካሉ የሆነችው የቤተ ክርስቲያን ራስ ነው፡፡ ይህ ዓረፍተ ነገር ኢየሱስ በቤተ ክርስቲያን ላይ ያለውን ሥልጣን ራስ በሰው አካል ጋር ካለው ጋር ያነጻጽራል፡፡ ልክ ራስ አካልን እንደሚገዛ እንዲሁም ዚየሱስ ቤተ ክርስቲያንን ይገዛል፡፡ የሥልጣን ሁሉ ምንጭ እርሱ ዋነኛ አለቃ ወይም መሥራች ነው፡፡ ኢየሱስ የቤተ ክርስቲያን ጀማሪ ነው፡፡ ከሙታን መከካከል በኩር ነው ኢየሱስ ሞተው ከሞት ወደ ሕይወት ከተመለሱት ሰዎች በኩር ነው፣ ከእንግዲህም ፈጽሞ እንደገና አይሞትም፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያት እግዚአብሔር የእርሱ ሙላት በእርሱ ውስጥ አንዲኖር ስለፈቀደ ነው "እግዚአብሔር አብ እርሱ ያለው ነገር ሁሉ በክርስቶስ እንዲሆን ስለፈቀደ ነውt" በመስቀል ላይ በፈሰሰው የልጁ ደም በኩል “በኩል” ተብሎ የተተረጎመው ዋናው ቃል መሥመር ወይም መንገድ የሚል ሀሳብን በውስጡ ያዘለ ሲሆን እግዚአብሔር በመስቀል ላይ ሞቶ በፈሰሰው የኢየሱስ ደም በኩል ሰላምን እና እርቅን ማምጣቱን የሚያሳይ ነው፡፡ ልጅ ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ለሆነው ለኢየሱስ ወሳኝ ስም ነው፡፡
እንዲሁም እናንተም ደግሞ "እንዲሁም በቆላስያስ ከተማ የሚትኖሩ አማኞችም ጭምር" ለእግዚአብሔት እንግዶች ነበራችሁ were strangers to God አማራጭ ትርጉም: "ከእግዚአብሔር የተለያችሁ ነበራችሁ" ወይም "እግዚአብሔር የተዋችሁ ነበራችሁ" በአእምሮዋችሁ እና በክፉ ተግባራችሁ የእግዚብሔር ጠላቶች ነበራችሁ "ጠላቶቹ ነበራችሁ ምክንያቱም ክፉ ሀሳብን ስለምታስቡ እና ምክንያቱም ክፉ ተግባርን ስለምትፈጽሙ ነው፡፡." (UDB) በክርስቶስ ሥጋ በሞቱ እግዚአብሔር እናንተን አስታረቀ እግዚአብሔር እናንተ ከኢየሱስ ጋር ስያስታርቃችሁ በመስቀል ላይ የተመለከተው ክርስቶስን ሳይሆን እናንተን ነው ይሁን እንጂ እናንተ ክርስቶስ ሲሞት እናንተም በመስቀል ላይ መሞታችሁን ተመልክቷል፡፡ እንከን የለሽ "ምንም እንከን ያሌለበት" ከነቀፋ ውጪ "ምንም ነቀፋ ያሌለበት" በራሱ ፊት "በእግዚአብሔር በራሱ ፊት" ጸንታችሁ ቆማችሁ "በቀጣይነት ጸንታችሁ ተተክላችሁ" ወይም "በቀጣይነት ቆማችሁ" በእምነት ጽንታችሁ "አለመናወጥ" ወይም "መጽናት" በወንጌል መተማመን "በወንጌል ተማምናችሁ" እኔ ጳውሎስ ባሪያ የሆንኩለት ከሰማይ በታች ለፍጥረታት ሁሉ የሰበኩትን ወንጌል "ሰዎች ወንጌልን ከሰማይ በታች ላሉ ፍጥረታት ሁሉ ሰብከዋል፡፡ እኔ ጳውሎስ የሚሰብከው እና እግዚአብሔር እንዳገለግል የተራሁት ይህ ተመሳሳይ ወንጌል ነው፡፡"
አሁን እኔ ደስ ይለኛል "እኔ ጳውሎስ አሁን ደስ ይለኛል" ለእናንተ ሲል የሚቀበለው መከራ "ስለ እናንተ ጥቅም ስለል መከራን እቀበላለሁ" (UDB) ስለ እናንተ "ለእናንተ የቆላስያስ አማኞች ሲባል" ስለ አካሉም ማለት ስለ ቤተ ክርስቲያን በሥጋዬ በክርስቶስ መከራ ውስጥ የጐደለውን እፈጽማለሁ። ጳውሎስ እየተናገረ ያለው ለቤተ ክርስቲያን ጥቅም ሲል እየደረሰበት ያለውን ተቃውሞ እነና ስደት ነው፡፡ ጳውሎስ ገና አማኝ ሲሆን ይህ ከባድ የሆነ መከራ እንደሚደርስበት አስቀድሞ አሳይቶት ነበር፡፡ ቤተ ክርስቲያንን አገለግላለሁ "እኔ ጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን የሚስፈልጋትን ነገር ለመሙላት እፈልጋለሁ" የእውነት ምስጢር "ሚስጥሩ" ለዘመናት ተሸሽጎ ነበር ይህ ከፍጥረት ጊዜ እንስቶ ጳውሎስ ለአሕዛብ ወንጌልን እስከ ሰበከበት ጊዜ ያለውን ዘመን ያመለክታል፡፡ ለአማኞች ተገልጧል አማራጭ ትርጉም: "ለእርሱ ተከታዮች ግልጽ ተደርጎላቸዋል፡፡" ይህ አይሁድንና አሕዛብ ያካትታል፡፡ ለእነርሱም እግዚአብሔር በአሕዛብ ዘንድ ያለው የዚህ ምሥጢር ክብር ባለ ጠግነት ምን እንደ ሆነ ሊያስታውቅ ወደደ፥ እግዚአብሔር ለአሕዛብ ያለው ዕቅድ ምን ያኸል ግሩም እንደሆነ ማሳወቅ ፈለገ፡፡ ምሥጢሩም የክብር ተስፋ ያለው ክርስቶስ በእናንተ ዘንድ መሆኑ ነው። "ምሥጢሩም የእግዚብሔርነን ክብር ለወደፊት የመካፈላችሁ ርግጠኝነት ነው" (UDB)
እና የሚነስበከው እርሱን ነው "ጳውሎስ እና ጢሞቴዎስ የሚሰብኩት ክርስቶስ ይህ ነው፡፡" ሁሉንም ሰው እናስተጠነቅቃለን "ሰዎችን ሁሉ እናስጠነቅቃለን" ሰዎችን ሁሉ ማቅረብ እንችል ዘንድ "ሰዎችን ሁሉ ለእግዚአብሔር ማቅረብ እንችል ዘንድ" መፈጸም "መንፈሳዊ ብስለት" ስለዚህ እደክማለሁ "እኔ ጳውሎስ ስለዚህ ነገር እደክማለሁ" በእኔ በኃይል እንደሚሠራ እንደ አሠራሩ "በእኔ እንደሚሠራው የክርስቶስ ዓላማ"
1 ስለ እናንተና በሎዶቅያ ስላሉት ሰዎች እንዲሁም ፊቴን በሥጋ አይተውት ስለማያውቁ ስለ ብዙዎች ምን ያህል ብርቱ ትግል እንዳደረግሁ እንድታውቁ እወዳለሁ። 2 ልባቸው ተጽናንቶና በፍቅር ተሳሰረው ፍጹም የሆነ የመረዳት ብልጽግና እንዲኖራቸውና የእግዚአብሔርን ምስጢር የሆነውን እውነት ክርስቶስን እንዲያውቁ እታገላለሁ። 3 የጥበብና የዕውቀት ሀብት ሁሉ የተሰወረው በእርሱ ነው። 4 ይህን የምላችሁ ማንም በሚያታልል ንግግር እንዳያስታችሁ ነው። 5 በሥጋ ከእናንተ ጋር ባልሆን እንኳ በመንፈስ ከእናንተ ጋር ነኝ። የእናንተን መልካም ሥርዐትና በክርስቶስ ያላችሁን ጽኑ እምነት እያየሁ ደስ ይለኛል። 6 ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ተቀበላችሁት በእርሱ ተመላለሱ። 7 በእርሱም ተመሥርታችሁና ታንጻችሁ፤ እንደ ተማራችሁትም በእምነት ተደላድላችሁ ኑሩ፤ ምስጋናም ይብዛላችሁ። 8 በክርስቶስ ላይ ባልተመሠረተ በሰው ሠራሽ ልማድና በዓለማዊ ነገሮች፥ በፍልስፍናና በከንቱ ሽንገላ ማንም እንዳይማርካችሁ ተጠንቀቁ። 9 የእግዚአብሔር ፍጹም ሙላት በእርሱ ይኖራልና። 10 በእርሱም ተሞልታችኋል። እርሱ የአለቅነትና የሥልጣን ሁሉ ራስ ነው። 11 በእርሱም ተገርዛችኋል፤ ይህም መገረዛችሁ የሥጋዊ አካል በማስወገድ በሰው እጅ የተደረገ ሳይሆን በክርስቶስ የተደረገ ነው። 12 በተጠመቃችሁ ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ተቀበራችሁ፤በእርሱም ክርስቶስን ከሞት ባስነሣው በእግዚአብሔር ኅይል በእምነት ተነሥታችኋል። 13 እናንተም በበደላችሁና በሥጋችሁ ባለመገረዝ ሙታን ሳላችሁ፤ እግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር ሕያዋን አድርጎ መተላለፋችንንም ሁሉ ይቅር ብሎአል። 14 እርሱ ይከሰን የነበረውን የዕዳ ጽሑፍ ደመሰሰው። ሁሉንም በመስቀል ላይ ቸንክሮ ከእኛ አስወገደው። 15 ኅይላትንና ባለሥልጣናትን በመስቀሉ ድል አድርጎ በይፋ እንዲጋለጡ አደረጋቸው። 16 እንግዲህ በመብል ወይም በመጠጥ ወይም የበዓላትን ቀናት ወይም የወር መባቻን፤ ወይም ሰንበትን በማክበር ምክንያት ማንም አይፍረድባችሁ። 17 እነዚሁ ሁሉ ወደ ፊት ሊመጡ ላሉት ነገሮች እንደ ጥላ ናቸው፤ እውነተኛው አካል ግን በክርስቶስ ነው። 18 አስመሳይ በሆነ ትሕትና የመላእክትን አምልኮ በመፈለግ ማንም ዋጋ እንዳያሳጣችሁ። እንዲህ ያለው ሰው ስለሚያየው ነገር በሥጋዊ አስተሳሰቡ ይታበያል። 19 እርሱም ራስ ከሆነ ከክርስቶስ ጋር አልተያያዘም። በእግዚአብሔር በተሰጠው እድገት በመገጣጠሚያና በጅማት አካልን በሙሉ አያይዞ የሚመግበውና ለአካል ሙሉ ዕድገት የሚሰጠው ራስ ነው። 20 ከክርስቶስ ጋር ከሞታችሁ፣ ለዓለማዊ ነገሮች እየታዘዛችሁ ስለ ምን ትኖራላችሁ? ትእዛዞቹም፦ 21 «አትያዝ፤አትቅመስ፤ አትንካ!» የሚሉ ናቸው። 22 እነዚህ ሁሉ የሰው ትእዛዛትና ትምህርቶች ሥራ ላይ ከዋሉ በኋላ የሚጠፉ ናቸው። 23 እነዚህ ትእዛዞች ሰው ሰራሽ «ጥበብ» አምልኮና የሐሰት ትሕትና ሰውነትንም በማጎሳቆል ላይ የሚያተኩሩ፤ ነገር ግን ሥጋዊ ስሜትን በመቆጣጠር ረገድ ዋጋ ቢሶች ናቸው።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ በቆላስያስ እና በሎዶቂያ የሚገኙ አማኞች ክርስቶስ አምላክ እንደሆነ እና በአማኞች ውስጥ እንደሚኖር ተገንዝበው እርሱን በተቀበሉበት መቀበል መኖር እንዳለባቸው ማበረታታቱን ቀጥሏል፡፡ ስለዚህ ይህንን ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ "እኔ ጳውሎስ በቆላስያስ የሚትኖሩ አማኞች ይህንን ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ" እንዴት ያለ ትልቅ መጋደል እንዳለኝ ልታውቁ እወዳለሁና፤ የእርሱን ንጽሕና ለማሳደግ እና የወንጌል መረዳታቸቸውን ለመጨመር ጳውሎስ ከፍተኛ ጥረት አድርጓል፡፡ በሎዶቅያ ላሉት ይህች ከተማ የቆላስያስ ከተማ ቅርብ የሆነች ከተማ ሲትሆን በዚህች ከተማ ውስጥመም ቤተ ክርስቲያን ነበረች፣ ጳውሎስም ለዚህች ከተማ ይጸልይላታል፡፡ ብዙዎች በሥጋ ፊቴን የማየት እድል አላገኙም "ብዙዎቹን በአካል አላገኘኋቸውም" ወይም "ብዙዎችነን ፈጽሞ ፊት ለፊት አግኝቼአቸው አላውቅም" ልባቸውም "ጳውሎስን በአካል አይተውት የማያውቁት ሁሉም አማኞች ልብ" ወደ አንድነት እንዲሰበሰብ በእውነተኛ ግንኙነት እንድቀራረቡ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እርስ በእርሳቸው እንዲተባበበሩ" ወይም "እርስ በእርሳቸው እንዲቀራረቡ" ከመረዳት የሚመጣ መተማመን ይህ እነዚህ ነገሮች በማወቅ የሚገኝ መተማመን ማለት ነው፡፡ የእግዚአብሔር ምስጢር ይህ በእግዚአብሔር ስገለጥ ብቻ የሚታወቅ ነገር ነው፡፡ ይኼውም ክርስቶስ ነው ኢየሱስ ክርስቶስ በእግዚአብሔር የተገለጠ ምስጢር ነው፡፡ የጥበብ እና እውቀት የተደበቀ መዝገብ ታላቅ የጥበብ እና የእውቀት ሀብት ወይም ባለጠግነት ጥበብ እ እውቀት እነዚህ ቃላት በመሠረታዊ ሀሳባቸው ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ጳውሎስ እነዚህ ቃላት በአንድነት የተጠቀመው ሁሉም መንፈሳዊ መረዳቶች ከክርስቶስ ዘንድ አንደሚመጡ አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ በእርሱ ናቸው “እርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ክርስቶስን ነው፡፡
ይህንን እላለሁ "እኔ ጳውሎስ ይህንን እላለሁ" እንዳያስታችሁ "እናንተ የቆላስያስ አማኞችን ወደ ተሳሳተ ሥፍራ ወይም ድምዳሜ እንዳይመራችሁ" በሚያሳምን ንግግር የሆነ ነገርንን እንዲታምኑ የሚያደርግ ንግግር ወይም አንድን ሀሳብ የሚታመን የሚያድረግ ንግግር ምንም እንኳ በሥጋ ከእናንተ ጋር ባልሆንም "በአካል ከእናንተ ጋር ባልሆንም" በመንፈስ ግን ከእናንተ ጋር ነኝ "ሁል ጊዜ ስለ እናንተ አስባለሁ" መልካም ሥርዓታችሁን ጳውሎስ ስለ አንድነታቸው እና ስለ እምነታቸው ጥንካሬ እንዲሁም በክርስቶስ ላይ ስላላቸው እምነት አመስግኖዋቸዋል፡፡
በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ተመላለሱ ይህ በተወሰነ የአኗኗር ዘይቤ ወይም መነንገድ መኖርን ለማመልከት ጥቅም ላይ የዋለ አገላለጽ ነው፡፡ እንደተቀበላችት "በቆላስያስ ከተማ ውስጥ ያሉ አማኞች ክርስቶስን እንደተቀበሉት" በእርሱ ጸንታችሁ ቁሙ፣ በእርሱ እደጉ በዚህ ሥፍራ ጳውሎስ ክርስትያኖች መኖር ያለባቸውን ሕይወት ለመግለጽ እና ስለ መንፈሳዊ ብስከለት ለመግለጽ ሁለት ምሳሌያዊ ነግግሮችን ይጠቀማል በእምነታችሁ ጽኑ "ሕይወታችሁን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ባላችሁ እምነት መሥርታችሁ ኑሩ" ምስጋና ይብዛላችሁ "እግዚአብሔርን በጣም አመስግኑት"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ አማኞች ወደ ቃላት እና ሌሎች ሕግጋት እንዳይመለሱ ያስጠነቅቃል ምክንያቱም አማኞች አሁን በክርስቶስ ካላቸው የእግዚአብሔር ሙላት ላይ ምንም የሚጨምሩት ነገር የላቸውምና፡፡ ይህንን ተመልከቱ "ጥንቃቄ አድርጉ" ወይም "ተጠንቀቁ" ፍልስፍና ስለ እግዚአብሔር እና ሕይውት ከእግዚአብሔር ቃል ያልወጣ ሃይማታዉ አስተምህሮዎች እና እምነቶች ባዶ ማታለል ይህ በክርስቶስ ወደ ሆነ ሕይወት የማይመሩ አሻች ሀሳቦችን ያመለክታል፡፡ ምንም ነገር አያፈሩም ባዶ ወይም ዋጋ ያሌላቸው ነገሮች ናቸው፡፡ እንደ ሰው ወግና እንደ ኃጢአት የሞላበት የዓም ሥርዓት የአይሁድ እና የአረማዊያን (አሕዛብ) የእምነት ሥርዓቶች፣ ሁለቱም ምንም ዋጋ የላቸውም፡፡ እንደ ክርስቶስ ትምህርት አይደሉም "እንደ ክርስቶስ ትምህርት አይደሉም" ወይም "በክርስቶስ ትምህርት ላይ የተመሠረቱ አይደሉም" ምክንያቱም የመለኮት ሙላት ሁሉ በአካሉ ውስጥ ይኖራል "ምክያቱም የእግዚአብሔር ሙሉ ባሕርይ በክርስቶስ አካል ውስጥ ይኖራል"
በእርሱ "በኢየሱስ ክርስቶስ" እናንተ ናችሁ "እናንተ በቆላስያስ የሚትኖሩ አማኞች ናችሁ ፈጽሞ ሙሉ ሆናችኋል "ሙሉ ሆናችኋል" እግዚአብሔር ገርዞዋችኋል ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ልክ በግርዛት ወቅት ሥጋ በቢላዋ ተቆርጦ እንደሚጣል ሁሉ እግዚአብሔር የአማኖችን ኃጢት ፈጽሞ አስወግዷል፡፡ ከእርሱ ጋር ተቀብራችኋል ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ልክ አንድ ሰው ሲሞት አካሉ በምድር ውስጥ እንደሚቀበር ሁሉ እንዲሁም ድነትን ባገኛችሁበት ወቅት የድሮው ባሕርያችሁ በመቅጽበት እንዴት እንደሚወገድ የሚብራራ ነው፡፡ ከእርሱ ጋር ተነሥታችኋል ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ልክ አንድ ሰው ከሞት ስነሳ አዲስ ህይወት እንደገና እንደሚኖረው ሁሉ አንድ አማኝ እንዴት አዲስ ባሕርይ እንደሚሰጠው ያመለክታል፡፡
ሙታን በሆናች ጊዜ "የቆላስያስ አማኞች በመንፈሳዊ ሞት ውስጥ በነበሩበት ጊዜ" በመተላለፋችሁ ሙታን ነበራችሁ እንዲሁም በሥጋችሁም ያልተገረዛችሁ ነበራችሁ በሁለት ነገሮቸ ሙታን ነበሩ: 1) በመንፈሳዊ ሕይወት ሙታን፣ ክርስቶስ የሚበድል ኃጢአት የሞላበትን ሕይወት ትኖሩ ነበር እና 2) እንደ ሙሴ ሕግ የተገረዛችሁ አልነበራችሁም፡፡ እርሱ እናንተን እንዲህ አደረጋችሁ "ኢየሱስ እናንተን የቆላስያስ አማኞችን እንዲህ እንዲትሆኑ አደረገ" መተላለፋችንን ሁሉ ይቅር አለን "ኢየሱስ ክርስቶስ አይዳዊያንን እና አሕዛብን ሁለቱን መተላለፋችንን ሁሉ ይቅር አለልን፡፡" እናንተ ሙታን ነበራችሁ . . . ሕያዋን እንዲትሆኑ አደረገ ይህ ምሳሌዊ ንግግር ልክ የሞተ ሰው ወደ ሕይወት በአካል እንደሚመጣ ሁሉ እኛም እንዴት ኃጢአተኛ ከሆነ ሕይወት ወደ አዲስ መንፈሳዊ ሕይወት እንደመጣን ያሳያል፡፡ በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው፤
ይህ ምሳሌያዊ ንግግር እግዚአብሔር የእኛን ኃጢአት (እዳ) እና የእግዚአብሔርን ሕግ መተላለፋችን መሰረዙን በወረቀት ላይ የተጸፉ ዝርዝሮችን ከመሰረዝ ጋር እያነጻጸረ ያቀርባል፡፡ ድል በመንሣት በእርሱ እያዞራቸው በግልጥ አሳያቸው። በሮማዊያን ዘመን የሮም ወታደሮች ከጦርነት ሲመለሱ “የድል ጉዞ” ማድረግ የተለመደ ነገር ነው፡፡ በዚህ ወቅት በምርኮ የያዝዋቸውን ምርኮኞች እና የነጠቁትን ሀበት ያሳያሉ፡፡
ማንም አይፍረድባችሁ ጳውሎስ አማኞችን አሕዛቦች የሙሴን ሕግ መጠበቅ አለባቸው ከሚሉ አይዳዊያን ይጠበቁ ዘንድ ያስጠነቅቃቸዋል፡፡ በሚበላ ወይም በሚጠጣ ነገር የሙሴ ሕግ ምን መበላት እና መጠጣት እዳለበት የሚያሳይ ሕግ አለው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ AT: "በምትበሉት ወይም በምትጠጡት ነገር" የጾም ቀን ወይም አዲስ ጨረቃ ወይም ስለ ሰንበት የሙሴ ሕግ መከበር ያለባቸው፣ የአምልኮ ቀናት እና መስዋእት የሚቀርብበት ቀን መቼ እንደሆነ ይደነግጋል፡፡ እነዚህ ለሚመጣው ነገር ጥላ ናቸው “ጥላ” የአንድን ነገር ቅርጽ እና አጠቃላይ ሁኔታን ድብዝብዝ ባለ መንገድ የሚያሳይ ነው፡፡ በተማሳሳይ መልኩም እንደ ሙሴ ሕግ ያሉ ሃይማኖታዊ ትውፊቶች በኢየሱስ ክርስቶስ የተገለጠውን እውነተኛውን ነገር በከፍል ብቻ የሚያሳዩ ናቸው፡፡
ዋጋችን ማንም ሰው እንዳይወስድባችሁ "ማንም ከሚያገኘው ዋጋ የተነሣ እንዳያታልላችሁ፡፡" ይህ ምሳሌያዊ ንግግር የውሸት ትህትናን እና የመላእክት አምልኮን በቆላስያስ ከተማ ውስጥ የአማኞችን ድነት ለመስረቅ ከሚሞክር ሌባ ጋር ያነጻጽራል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ማንም የሌላ ሰውን ሽልማት እንዲሰርቅ አትፍቀዱለት፡፡" የውሸት ትህትና "ትሁት ለመመስል የሚደረግ ጥረት፡፡" ይህ ማለት በሌሎስ ሰዎች ፊት ትሁት ለመምሰል የተለያዩ ነገሮችን ማድረግ ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ራስን የካዱ መምሰል” በተለያዩ ነገሮች ከሚገባ በላይ መያዝ ይህ ማለት አእምሮን ሁል ጊዜ የሚዝ ወይም በሆነ ነገር በጣም መያዝን ያሳያል፡፡ አዲስ አስተሳሰብ ይህ ማለት እንደ መንፈሳዊ ሰው ሳይሆን ተፈጥሮአዊ ወይም ኃጢአተኛ ሰው ማሰብ ማለት ነው፡፡ አጥብቆ አይዝም "አጥብቆ አይዝም" ወይም "አይጠጋም፣" ልክ ልጅ ወደ ወላጆቹ እንደሚጠጋው ማለት ነው፡፡
እንደዚህ ያለ ሰው ራስ ወደሚሆነው አይጠጋም፥ ከእርሱም አካል ሁሉ በጅማትና በማሰሪያ ምግብን እየተቀበለ እየተጋጠመም፥ እግዚአብሔር በሚሰጠው ማደግ ያድጋል።
ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ክርስቶስ በቤተ ክርስቲያን ላይ ያለው ስልጣንን የሰው ልጅ ጭንቅለላት አካሉን ከሚቆጣጠርበት እና ከሚገዛበት መንገድ ጋር ያነጻጽራል፡፡
ከክርስቶስ ጋር ለዚህ ዓለም ኃጢአተኛ ሥርዓት ከሞትን ይህ ምሳሌያዊ ንግግር የሚያሳየው ልክ የሞተ ሰው የዚህ ዓለም አካላዊ ፍላጎቶች ታዲያ ለዚህ ዓለም እምነት ተገዝታችሁ ስለምን ትኖራላችሁ ጳውሎስ ይህን ጥያቄ የተጠቀመው የቆላስያስ አማኞች የዚህ ዓለምን የሐሰት የእምነት ሥርዓት መከተላቸውን ለመገሰጽ ነው፡፡) ተገዝቶ መኖር "መገዛት" ወይም "መሰጠት" ወይም "መታዘዝ" መጥፋት "መበስበስ" እነዚህ ደንቦች በሰው የተዘጋጁ ሃይማኖታዊ “ጥበቦች” አሏቸው እንዲሁም ትሁታን ይመስላሉ አካላቸውንም ሃይማኖተኛ ለመምሰል ያጎሳቁላሉ፡፡ ሃይማኖትን በመፍጠር እና የሐሰት ትህትና እና አካላቸውም በሃይማኖት ስም በማጎሳቆል - "እነዚህ ህግጋት ከሰው ልጅ የእይታ አንጻር ጥበብ የሞላባቸው ይመስላሉ እንዲሁም አካላቸውን ያጎሳቁላሉ"
ማጎሳቆል "በከፍተኛ ሁኔታ መጉዳት" ወይም "ማሰቃየት" ነገር ግን ሥጋ ያለ ልክ እንዳይጠግብ ለመከልከል ምንም አይጠቅምም። "የሥጋን ፍላጎት መከተልን ለማስቆም ግን ምንም እገዛ አያደርጉም"
1 እግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር ከሞት ካስነሣችሁ፤ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ ያሉትን ነገሮች እሹ። 2 በላይ ስላሉት ነገሮች እንጂ በምድር ስላሉት ነገሮች አታስቡ። 3 ምክንያቱም ሞታችኋል፤ ሕይወታችሁንም እግዚአብሔር በክርስቶስ ውስጥ ሰውሮታልና። 4 ሕይወታችሁ የሆነ ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ እናንተም ከእርሱ ጋር በክብር ትገለጣላችሁ። 5 ስለዚህ ምድራዊ ምኞቶቻችሁን ግደሉ፦ እነርሱም፦ ዝሙት፣ ርኩሰት፣ ፍትወት፣ ክፉ ምኞት፣ ስግብግብነትና ጣዖትን ማምለክ ናቸው። 6 በእነዚህም ነገሮች ምክንያት በማይታዘዙ ልጆች ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ይመጣባቸዋል። 7 እናንተም ራሳችሁ ከዚህ በፊት በማይታዘዙ ሰዎች መካከል ሳላችሁ እነዚህን ነገሮች እያደረጋችሁ ትመላለሱ ነበር። 8 አሁን ግን ቁጣን፤ ንዴትን፤ ተንኮልን፤ ስም ማጥፋትን ከእናንተ አስወግዱ፤ የሚያሳፍር ንግግርም ከአፋችሁ አይውጣ። 9 አሮጌውን ሰው ከሥራው ጋር አውልቃችሁ ስለ ጣላችሁ፣ አንዳችሁ በሌላው ላይ አትዋሹ። 10 የፈጠረውንም ምሳሌ እንዲመስል ዕውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል። 11 በዚህ ዕውቀት በግሪካዊና በአይሁዳዊ፣ በተገረዘና ባልተገረዘ፣ በሠለጠነና ባልሠለጠነ፣ በባሪያና በነጻ ሰው መካከል ልዩነት የለም፤ ክርስቶስ ግን ሁሉ ነው፤ በሁሉም ነው። 12 ስለዚህ እንደ እግዚአብሔር ምርጦች ቅዱሳንና የተወደዳችሁ ሆናችሁ ርኅራኄን፣ ቸርነትን፣ ትሕትናን፣ ገርነትን፣ ትዕግሥትን ልበሱ። 13 እርስ በርሳችሁ ታገሱ፤ እርስ በርሳችሁም ቸሮች ሆኑ። ከእናንተ አንዱ በሌላው ላይ ቅርታ ቢኖረው፣ ክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ ይቅር ተባባሉ። 14 በዚህ ሁሉ ላይ የፍጻሜ ማሰሪያ የሆነው ፍቅር ይኑራችሁ። 15 የአንድ አካል ክፍሎች ሆናችሁ የተጠራችሁት ለዚህ ሰላም ስለ ሆነ የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይንገሥ፤ የምታመሰግኑም ሁኑ። 16 የክርስቶስ ቃል በሙላት ይኑርባችሁ። በጥበብ ሁሉ እርስ በርሳችሁ ተማማሩ፤ ተመካከሩ፤በመዝሙርና በውዳሴ፤ በመንፈሳዊ ዜማም እግዚአብሔርን ከልብ እያመሰገናችሁ ዘምሩ። 17 በእርሱ እግዚአብሔር አብን እያመሰገናችሁ በቃልም ሆነ በሥራ የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም አድርጉት። 18 ሚስቶች ሆይ፥ ለጌታ እንደሚገባ ለባሎቻችሁ ታዘዙ። 19 ባሎች ሆይ፥ ሚስቶቻችሁን ውደዱ መራራም አትሁኑባቸው። 20 ልጆች ሆይ፥ ይህ ጌታን ደስ የሚያሰኝ በመሆኑ ለወላጆቻችሁ በሁሉ ነገር ታዘዙ። 21 አባቶች ሆይ፥ልጆቻችሁ ተስፋ እንዳይቆርጡ አታስመርሩአቸው። 22 አገልጋዮች ሆይ፥ ሰውን ለማስደሰትና ለታይታ ሳይሆን በቅን ልብ ጌታን በመፍራት ለምድራዊ ጌቶቻችሁ በሁሉ ነገር ታዘዙ። 23 የምታደርጉትን ሁሉ ለሰው እንደምታደርጉ ሳይሆን ለጌታ እንደምታደርጉ በሙሉ ልባችሁ አድርጉት። 24 ከጌታ ዘንድ እንደ ዋጋ የምትቀበሉት ርስት እንዳለ ታውቃላችሁና። 25 በዚህም የምታገለግሉት ጌታ ክርስቶስን ነው። በእግዚአብሔር ዘንድ አድልዎ ስለሌለ ክፉ የሚሠራ ማንም ስለ ክፉ ሥራው ቅጣቱን ይቀበላል።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ከክርስቶስ ጋር አንድ በመሆናችሁ ምክንያት አማኞች ማድረግ የሌለባቸው ነገሮች አሉ በማለት ጳውሎስ አማኞች ያስጠነቅቃቸዋል፡፡ እግዚአብሔር እናንተን ከክርስቶስ ጋር ከሞት አስነስቷችኋል ልክ እግዚአብሔር ክርስቶስን ከሞት እንዳነሣው ሁሉ እግዚአብሔር በቆላስያስ ከተማ የሚገኙ አማኞችም ከሞት እንደተነሱ ይቆጥራል፡፡ አንስቶዋችኋል “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በቆላስያስ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ አማኞችን ነው፡፡ የላይኛውን ነገር "ሰማያዊውን ነገር" ወይም "መለኮታዊውን ነገር" በምድር ላይ ያለውን "ምድራዊውን ነገር" ወይም "የምድርን ነገር" እናንተ ሞታችኋልና ክርስቶስ በእርግጥ እንደሞተ እግዚአብሔር በቆላስያስ ከተማ ውስጥ የሚኖሩት አማኞችንም ከክርስቶስ ጋር እንደሞቱ አድርጎ ይቆጥራቸዋል፡፡ እግዚአብሔር ሸሽጎታል "እግዚአብሔር ሰውሮታል" ከእርሱ ጋር በክብሩ ውስጥ በዚህ ሥፍራ “እርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ክርስቶስን ነው፡፡
ስለዚህ ኃጢአተኛ መሻታችሁን ግደሉት፡፡ ይህ ልክ ክፉ ሰው እንዲሞት እንደሚደረግ ሁሉ ኃጢአተኛ መሻታችሁ ፈጽም እና ለመጨረሻ ጊዜ ማስወገድ ይኖርባችኋል፡፡ ንጹሕ ያልሆነ ነገር "ንጹሕ ያልሆነ ባሕርይ" መሻት "ጠንካራ የዝሙት ምኞት" እና ጣኦትን ለማምለክ መመኘት "እና ስግብግብነት፣ ይህ ልክ እንደ ጣኦትን ማምለክ ነው" ወይም "እና ስግብግብ አትሁኑ ምክንያቱም ይህ ጣኦትን ከማምለክ ጋር ተመሳሳይ ነውና" (UDB) ስለዚህም በእነዚህ ነገሮች ምክንያት በማይታዘዙ ልጆች ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ይመጣል፡፡ "እነዚህ ነገሮች በሚያደርጉ በማያምኑ ሰዎች ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ይመጣባቸዋል፡፡" እናንተም ደግሞ ትኖሩባቸው በነበራችሁ ጊዜ፥ በፊት በእነዚህ ተመላለሳችሁ። "እነዚህ ነገሮች ትፈጽሙ በነበረበት ወቅት ትመላለሱ የነበረው እንዲህ ነበር፡፡ ቁጣ "ቅጣት" ንዴተ "ቁጣ" ክፉ ምኞቶች አማራጭ ትርጉም: "የልብ ክፋት፣ ሕይወት እና ባሕርይ" ስድቦች "እግዚአብሔርን መሳደብ" ወይም "እርኩሰት የሞላበት ቃል መናገር፡፡" ይህ ሌሎች ሰዎችን ለመጉደት ሲባል የሚነገር ንግግርን ያመለክታል፡፡ አሳፋሪ፣ ሰዎችን የሚያሰናክል ንግግር አማራጭ ትርጉም: "ቆሻሻ ንግግር"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ በአሕዛብ እና በአይሁድ፣ በባሮች እና በነጻ ሰዎች መካከል የነረው ግድግዳ ክርስቶስ እንዳፈረሰው በማስታወስ አማኞች እንዴት መኖር እንዳለባቸው ማስታወሱን ቀጥሏል፡፡ እናንተ ገፋችሁታል በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በቆላስያስ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ አማኞችን ነው፡፡ አሮጌውን ሰው ከሥራው ጋር ገፋችሁታልና፥ የፈጠረውንም ምሳሌ እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል፤ ይህ ምሳሌዊ ንግግር እግዚአብሔር የማይከብርበትን ባሕርይ አስወግድ እግዚአብሔር የሚከብርበትን ተግባር መፈጸም የጀመሩ ክርስትያኖች ቆሻሻ ልብስን አውልቆ አዲስ እና ንጹሕ ልብስከለበሰ ሰው ጋር ያነጻጽረዋለረ፡፡ የእርሱ መልክ ይህ ኢየሱስ ክርስቶስን የሚወክል ነው፡፡ የእርሱ መልክ እውቀት ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ እና መረዳት በዚያም የግሪክ ሰው አይሁዳዊም የተገረዘም ያልተገረዘም አረማዊም እስኩቴስም ባሪያም ጨዋ ሰውም መሆን አልተቻለም፥ ይህ ማለት እግዚአብሔር ሁሉንም ሰዎች ያለልዩነት ይመለከታቸዋል፣ በዘር፣ በሀገር ወይም በማህበረሰቡ ውስጥ ባላቸው ደረጃ ሳይሆን ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ዘር፣ ሃይማኖት፣ ባሕል እና በማህበረሰቡ ውስጥ ያለው ደረጃ የሚያመጣው ነገር የለም፡፡” ክርስቶስ ሁሉ በሁሉ ነው ከክርስቶስ ሕልውና ውጪ የሚሆን ምንም ነገር የለም፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ክርስቶስ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡”
ልበሱት . . . የርህራሄን ልብ ሰው ልብስ እንደሚለብስ ሁሉ አማኞችም ለእያንዳንዳቸው በሚያሳዩት ባሕርይ ርህራሄን፣ ትህትናን ወዘተን መልበስ ይገባቸዋል፡፡ ስለዚህ ልበሱት በዚህ ሥፍራ ላይ "ስለዚህ" የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው ከዚህ በፊት በነበረው ውይይት ወይም በተሰጠው ትምህርት መሠረት መደረግ ያለበትን መተግባር ወይም ባሕርይ ለይቶ ለመናገር ነው፡፡ (ተመልከት: [[rc://*/ta/workbench/discourse/home]]) የእግዚአብሔር ምርጦች እንደመሆናችሁ - ቅዱስ እና የተወደደ "የእግዚአብሔር ቅዱሳን እና በእርሱ የተወደዳችሁ ምርጦቹ እንደመሆናችሁ፡፡ የርህራሄ ልብ፣ መልካምነት፣ ትህትና፣ ገርመት እና ትዕግስት "ርህራሄ. መልካምነት፣ ትህትና፣ ቅንነት እና ትዕግስት የውስት ማንነት ናቸው" ርሁሩ ልብ "የሚራራ ልብ" ወይም "ለሌሎች የሚያስብ ልብ" መልካምነት "መልካምነት" ወይም "ገርነት" ትህትና "የአእምሮ ትህትና" ወይም "የአእምሮ ገርነት" ቅንነት "ቅንነት፡፡" ነፈስ ስሜትን ከመከተል ይልቅ ወደ እግዚአብሔር የሚጋድል ከሆነ ትዕግስት "መቻል" ወይም "መከራን መቀበል መቻል" እርስ በእርስ መቻቻል በመስማማት እና በፍቅር በአንድነት መሥራትለ፡፡ “እርስ በእርስ መስማማት” ወይም “እርስ በእርስ መቻቻል፡፡” አንዱን ሌላኛውም መውቀስ "ሌላኛውን መውቀስ" ፍቅር ይኑራችሁ "ፍቅርን ደርቡ ይህ የፍጹምነት ማሠሪያ ነው "ይህ አንድ ልይ በትክክል የሚያያዝ ነው" ወይም "ይህ በአንድ ላይ ፍጹም በሆነ መልኩ በስምምነት የሚያሳስር ነው፡፡"
በልባችሁ ይግዛ "በልባችሁ ላይ ይንገሥ" በልባችሁ ውስጥ በዚህ ሥፍራ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚየመለክተው የቆላስያስ አማኞች ነው፡፡ በእናንተ ይኖራል "በእናንተ ውስጥ ያድራል" ወይም "በእናንተ ውስጥ ይኖራል" እርስ በእርሳችሁ ተጠባበቁ "አንዳችሁ ለሌኛችሁ ተጠንቀቁ" በመዝሙር እና በምስጋና እንዲሁም በመንፈሳዊ መዝሙር "በሁሉም ዓይነት መዝሙሮች እግዚአብሔርን አመስግኑት" በልባችሁ አመስግኑ "የሚያመሰግን ልብ ይኑራችሁ" በእርሱ በኩል "በጌታ ኢየሱስ በኩል"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ከዚያም ጳውሎስ አንዳንድ መመሪያዎችን ለሚስቶች፣ ለባሎች፣ ለሕጻናት፣ ለአባቶች፣ ለባሮች እና ለጌቶች ተገቢ የሆነ "ተገቢ ነው" ወይም "ትክክለኛ የሆነ" አታበሳጯቸው "ክፉ አትሁኑባቸው" ወይም "አትቆጦዋቸው" ይህ ጌታን የሚያስደስት ነገር ነው "ቤተሰቦቻችሁን የሚትታዘዙ ከሆነ ጌታ በዚህ ደስ ይለዋል" ልጆቻችሁን አታበሳጩ "ልጆቻችሁን አታስቆጡ" ወይም "ልጆቻችሁ እንዲበሳጩ አታድርጓቸው"
ጌቶቻችሁን ታዘዙ በዚህ ሥፍራ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በቆላስያስ የሚገኙ አማኝ የሆኑ ባሮች የሚያመለክት ነው፡፡ ለታይታ አይሁን ጌቶቻችሁ ስመለከቷችሁ ብቻ አትታዘዙ፡፡ ሰዎችን የሚታስደስቱ ከጌታ ይልቅ በሌሎች ሰዎች ዘንድ ተቀባይነትን ለማግኘት ሲሉ የተለያዩ ነገሮችን የሚያደርጉ አንዳንድ ሰዎች አሉ፡፡ (UDB) የሚታደርጉትን ነገር ሁሉ በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ባሮችን ቢሆንም እናንተ ግን በቆላስያስ ከተማ ውስጥ የሚገኙትን ሁሉንም ክርስቲያኖች የሚያመለክት አድርጋችሁ ልትተረጉምት ትችላላችሁ፡፡ ከነፍስ "በሙሉ ልባችሁ" (UDB) ለጌታ ብላችሁ "ለጌታ ብላችሁ" (UDB) የርስት ብድራት "ጌታ ቃል የገባውን ነገር እንደሚወርስ ነው" (UDB) ጽድቅ ያልሆነ ነገር የሚያደርግ ይህ ማንኛውንም ትክክለኛ ያልሆነ ነገር (ሥነ-ምግባር፣ ማህበረሰባዎ ወይም አካላዊ) የሚያመለክት ነው፡፡ “ትክክል የማያደርግ ሰው” ወይም “ክፋትን የሚያደረግ ሰው”፡፡ ቅጣትን ይቀበላል አማራጭ ትርጉም: "ይቀጣል" ያለልዩነት "ያለምንም ማዳላት" ወይም "ምንም አድሎ አይደረግለትም"
1 ጌቶች ሆይ፥ እናንተም በሰማይ ጌታ እንዳላችሁ ዐውቃችሁ ለአገልጋዮቻችሁ በትክክልና የሚገባቸውን ስጡአቸው። 2 በንቃት እግዚአብሔርን እያመሰገናችሁ ሳታቋርጡ ጸልዩ። 3 የክርስቶስ ምሥጢር የሆነውን የቃሉን እውነት መናገር እንድንችል እግዚአብሔር በር እንዲከፍትልን ለእኛም ደግሞ በአንድ ልብ ጸልዩልን፤ ምክንያቱም እስር የሆንኩት ስለእርሱ ነውና። 4 እኔም እንደሚገባ ቃሉን መግለጥና መናገር እንድችል ጸልዩልኝ። 5 በውጪ ካሉት ጋር በጥበብ ተመላለሱ፤ ዘመኑንም ዋጁ። 6 ለእያንዳንዱ ሰው እንዴት መመለስ እንዳለባችሁ እንድታውቁ ንግግራችሁ ሁልጊዜ በጨው እንደ ተቀመመ በጸጋ ይሁን። 7 ቲኪቆስ መጥቶ እኔ ስላለሁበት ሁኔታ ሁሉንም ነገር ይነግራችኋል። እርሱም ተወዳጅ ወንድም፤ ታማኝ አገልጋይና በጌታ ሥራም የአገልግሎት ባልደረባዬ ነው። 8 እርሱንም ወደ እናንተ የላክሁበት ምክንያት ስለ እኛ ሁኔታ ትክክል የሆነውን እንዲነግራችሁና ልባችሁንም እንዲያጽናና ነው። 9 ከእርሱም ጋር የእናንተ ወገን የሆነውን የታመነውንና የተወደደውን ወንድም አናሲሞስን ወደ እናንተ ልኬዋለሁ። እነርሱ በዚህ ስፍራ የተደረገውን ነገር ሁሉ ይነግሩአችኋል። 10 ከእኔም ጋር የታሰረው አርስጥሮኮስም ሰላምታ ያቀርብላችኋል፤ አንድ ጊዜ፥ «ወደ እናንተ በሚመጣበት ጊዜ ተቀበሉት» ብዬ አሳስቤአችሁ የነበረው የበርናባስ የአጎት ልጅ ማርቆስም ሰላምታ ያቀርብላችኋል። 11 ኢዮስጦስ ተብሎ የሚጠራው ኢያሱም ሰላምታ ያቀርብላችኋል። ከተገረዙ ወገኖች መካከል ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ከእኔ ጋር አብረው የሚሠሩት ሰዎች እነዚህ ብቻ ናቸው፤ ለእኔም መጽናናት ሆነውኛል። 12 የእናንተ ወገን የሆነው የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ኤጳፍራም ሰላምታ ያቀርብላችኋል። እርሱም ፍጹም ጠንክራችሁና ሙሉ በሙሉ ተማምናችሁ በእግዚአብሔር ፈቃድ በሁሉ ጸንታችሁ እንድትቆሙ ዘወትር ስለ እናንተ በጸሎት እየተጋ ነው። 13 ስለ እናንተ በሎዶቅያና በሂራፖሊስ ስላሉትም ሰዎች ተግቶ እንደሚሠራ እኔ ራሴ እመሰክርለታለሁ። 14 የተወደደው ሐኪም ሉቃስና ዴማስም ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። 15 በሎዶቅያ ላሉት ወንድሞች ለንምፉና በቤትዋም ላለች ቤተ ክርስቲያን ሰላምታ አቅርቡልኝ ። 16 ይህን መልእክት እናንተ ካነበባችሁ በኋላ በሎዶቅያ ሰዎች ዘንድ ባለችው ቤተ ክርስቲያን እንዲነበብ አድርጉ፤እናንተም ከሎዶቅያ የሚላክላችሁን መልእክት አንብቡ። 17 ለአርኪጳስም፥ «በጌታ አገልግሎት የተሰጠህን ሥራ በጥንቃቄ ፈጽም» ብላችሁ ንገሩልኝ። 18 ይህን ሰላምታ በገዛ እጄ የጻፍኩት እኔ ጳውሎስ ነኝ፤ በሰንሰለት ታስሬ እንዳለሁ አስታውሱና ጸልዩልኝ። የእግዚአብሔር ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ለግለሰቦች የሰጠውን መመሪያ ያጠናቀቀው ለጌቶች በመናገር ነው፡፡ ለአገልጋዮቻችሁ ስጡ በዚህ ክፍል ውስጥ “እናነተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በቆላስያስ የሚገኙ የባሪያ ባለቤት የሆነ አማኞችን ነው፡፡ በጽድቅ እና ቅንነት ይህ ባለቤቶቹ በጽድቅ እና ቅንነት በሞለበት መንገድ ለባሮቻቸው ያሳዩ ዘንድ የታዘዙት ነገርን የሚገልጽ ነው፡፤ በሰማይ ያለው ጌታ እግዚአብሔር ጌታ መሆኑ የሚያሳየው 1) እግዚአብሔር የባሪያ ባለቤቶችች በምድር ላይ ያሉትን ባሮቻቸውን በያየዙበት መንገድ ነው ወይም 2) ምድራዊ ባሪዎቻችሁን በሚትንከባከቡበት መንገድ እግዚአብሔር፣ ጌታችሁ በተመሳሳይ መንገድ ይመልስላችኋል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ አማኞች እንዴት መኖር እና መናገር እንደሚገባቸው መመሪያ መስጠቱን ቀጥሏል፡፡ በጸሎት ጸንታችሁ ቀጥሉ "በታማኝነት መጸለያችሁን ቀጥሉ" ወይም "በቀጣይነት መጸለያቸሁን ቀጥሉ" በተጨማሪ ለእኛ በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን እና ጢሞቴዎስን ነው ነገር ግን የቆላስያስ አማኞች የሚያካትት አይደለም፡፡ እግዚአብሔር በር ይከፍታል አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር እድል ያዘጋጃል" የክርስቶስ ምስጢር ይህ ከክርስቶስ መምጣት በፊት ሰዎች በደንብ ያልተረዱትን የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌልን የሚያመለክት ነው፡፡ በዚያ ቃል ምክንያት እኔ እስረኛ ነኝ "አሁን በእስር ቤት ያለሁት የኢየሱስ ክርስቶስን መልዕክት በመናገሬ ምክንያት ነው" ግልጽ አድርግ ዘንድ እና ልናገር እንደሚገባኝ ያህል መናር እችል ዘንድ ጸልዩልኝ። "የኢየሱስ ክርስቶስን መልዕክት ግልጽ በሆነ መልኩ መናር እችል ዘንድ ጸልዩልኝ፡፡"
በጥበብ ተመላለሱ። "ባሉት ዘንድ ጠቢባን ሁኑ" በውጭ ባሉቱ ዘንድ "አማኞች ባልሆኑት ዘንድ" ዘመኑን ዋጁ "በሚታደርጉት ነገር ጠቢባን ሁኑ" ቃላችሁ ሁል ጊዜ በጸጋ ይሆኑ፡፡ በጨው የተቀመመ ይሁን፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ንግግራችሁ በጸጋ እና ሰዎችን የሚስብ ይሁን፡፡" ለእነዚህ ነገሮች እንዴት ምላሽ መስጠት እንዳለብህ እወቅ "ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ከማንም ለሚመጣው ጥያቄ እንዴት መልስ መስጠት እንዳለብህ ማወቅ ይገባሃል"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ለተወሰኑ ሰዎች ይሰጥ የነበረውን መመሪያ እንዲሁም ለግለሰቦች እና አማኞች ሰላምታ መስተላለፉን የሚበቃበት ክፍል ነው፡፡ ስለ እኔ ማወቅ የሚገባቸውን ነገር ለእናንተ ታውቋል "እኔ ላይ የሆነውን ነገር ሁሉ እነርሱ ይነግሯችኋል" (UDB) ለእናንተ ይገለጻል በዚህ ሥፍራ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የቆላስያስ አማኞችን ነው፡፡ አብሮን ባሪያ የሆነው "አብሮን የሚያገለግለው፡፡" ምንም እንኳ ጳውሎስ ነጻ ሰው ቢሆንም ራሱን የክርስቶስ ባሪ አድርጎ ይመለከት ነበር እንዲሁም ቲኪቆስ አብሮን የሚያገለግል ነው፡፡ ስለእኛ ታውቁ ይሆናል በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስ እና ከእርስ ጋር የሚሠሩትን ሰዎችን ነው ነገር ግን ይህ በቆላስያስ የሚገኙ አማኞችን አያመለክትም፡፡ ልባችሁም እንዲጸና "እናንተን ለማበረታታት" አናሲሞስ አናሲሞስ በቆላስስ ከተማ ውስጥ የፊልሞን ባሪያ ነበር፡፡ ይህ ባሪያ ከፊልሞን ገንዘብ በመስረቅ ወደ ሮም ጠፍቶ የነበረ ሲሆን በዚያም በጳውሎስ አገልግሎት አማካኝነት ክርስቲያን ሆኗል፡፡ አሁን ከጳውሎስ ዘንድ የተጻፈውን ደብዳቤ ወደ ቆላስያስ ቤተ ክርስቲያን ይዘው የመጡት ቲኪቆስ እና አናሲሞስ ናቸው፡፡ ታማኝና ተወዳጅ ወንድም ጳውሎስ አናሲሞስን ክርስቲያን ወንድም እና የክርስቶስ ባሪያ ብሎ ይጠራዋል፡፡ ያስታውቃችኋልe " ቲኪቆስ እና አናሲሞስ ይነግሯችኋል" በዚህ የነበራቸውን ነገር ፈጽመዋል በቆላስያስ ከተማ ለሚገኙ አማኞች አሁን ጳውሎስ በሚኖርበት ሥፍራ እየተከናወነ ያለውን ነገር ይነግሯችኋል፡፡ በትውፊት ደረጃ ጳውሎስ በሮም በቤት እስር ወይም እስር ቤት እንደነበር ይነገራል፡፡
አርስጥሮኮስ ጳውሎስ ይህንን ደብዳቤ ለቆላስያስ ሰዎች ሲጽፍ በኤፌሶን ከጳውሎስ ጋር በእስር ነበረ፡፡ እርሱ ከመጣ "ማርቆስ ከመጣ" ኢየሱስ ተብሎ የሚጠራው ኢዮስጦስም ይህ ሰውም ከጳውሎስ ጋር አብሮ ይሠራ የነበረ ሰው ነው፡፡ ከተገረዙት መካከል አብረውኝ በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ የሚሠሩት እነዚህ ብቻ ናቸው፡፡ "እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ንጉሥ እንደሆነ ከእኔ ጋር ይሰብኩ የነበሩት ከአይዳዊያን አማኞች መካል እነዚህ ሦስት ሰዎች ብቻ ነበሩ" (UDB) ከተገረዙት መካከል እነነዚህ ብቻ ናቸው "ከተገረዙት ሰዎች መካከል እነዚህ ሰዎች ኢዮስጦስም፣ ማርቆስ እና ኢየሱስ ብቻ ናቸው"
ኤጳፍራ ኤጳፍራ በቆላስያስ ከተማ ውስጥ ላሉ ሰዎች ወንጌልን የሰበከ ሰው ነው፡፡ (ተመልከት COL 1:7) ከእናንተ የሆነው "ከእናንተ ከተማ የሆነው" ወይም "የከተማችሁ ሰው የሆነው" (UDB) የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ "የክርስቶስ ኢየሱስ የተሰጠ ደቀ መዝሙር" በጸሎት ሁል ጊዜ ስለ እናንተ ይጋደላል "በትጋት ስለ እናንተ ይጸልያል" ፈጽማችሁ በእርግጠኝነት በሙላት መቆም ትችሉ ዘንድ "በብስለት እና በመተማመን መቆም ትችሉ ዘንድ" ስለ እናንተ በትጋት እንደሚሠራ እኔ እመሰክራለሁ "ስለ እናንተ በትጋት እንደሚሠራ እኔ ራሴ ተመልክቻለሁ" (UDB) በሎዶቅያ ስላሉት በሎዶቅያ ከተማ ውስጥ ያለችው ቤተ ክርስቲያን፡፡ ሎዶቅያ በቆላስያስ አቅራቢያ የሚትገኝ ከተማ ናት፡፡ በኢያራ ስላሉት በኢያራ ከተማ ውስጥ ያለችው ቤተ ክርስቲያን፡፡ ዴማስ እርሱም ከጳውሎስ ጋር አብሮ ይሠራ የነበረ ሌላ ሰው ነው፡፡ ሰላም ብለዋችኋል "ሰላምታ አቅርበውላችኋል"
ወንድሞችን ሰላም በሉልን "ለወንድሞች ሰሰላምታችንን አቅርቡልንል" በሎዶቅያ ላሉ በቆላስያስ ከተማ አቅራቢያ የሚትገኝ ከተማ ሲትሆን በዚህች ከተማ ውስይ ቤተ ክርስቲያን ነበር ንምፉ የተባለች ሴት ሲትሆን በቤቷ ውስጥ ቤተ ክርስቲያንነበር በሎዶቅያ ከተማ ውስጥ የሚገኘው ቤተ ክርስቲያን ንምፉ ተብላ በሚትጠራ ሴት ቤት ውስጥ ይካሄድ ነበር፡፡አማራጭ ትርጉም: "ንምፉ እና በእርሷ ቤት ውስጥ የሚገናኙት የአማኝ ቡድኖች" (UDB) በእናንተ መካከል ይነበብ በዚህ ሥፍራ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በቆላስያስ ከተማ ውስጥ የሚገኙ አማኞች ነው፡፡ “ለአክሪጳም፦ በጌታ የተቀበልኸውን አገልግሎት እንድትፈጽሙው ተጠንቀቅ በሉልኝ።" ጳውሎስ አክሪጳን እግዚአብሔር የሰጠውን የሥራ ኃላፊነት በማስታወስ አክሪጳ ይህንን ኃላፊነት ለመወጣት በጌታ የተሰጠው አደራ እንዳለ ያስታውሰዋል፡፡
ኖት የለውም።
1 ከጳውሎስ፣ ስልዋኖስና ጢሞቴዎስ በእግዚአብሔር አብና በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ላሉ ለተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን፤ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን! 2 በጸሎታቻን እያሳሰብን እግዚአብሔርን ሁልጊዜ ስለ ሁላችሁም እናመሰግናለን። 3 በእምነት ስለምትሠሩት ሥራ፣ በፍቅር ስለምትደክሙት ድካምና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ባላችሁ ተስፋ በመታመን ስለመጽናታችሁ በእግዚአብሔር በአባታችን ፊት ሳናቋርጥ እናስታውሳችኋለን። 4 በእግዚአብሔር የተወደዳችሁ ወንድሞች ሆይ! መመረጣችሁን እናውቃለን፣ 5 ወንጌላችን በቃል ብቻ ወደ እናንተ አልመጣምና፥ ነገር ግን በኃይል፣ በመንፈስ ቅዱስና በብዙ መረዳትም እንጂ፥ ስለእናንተ ስንል በመካከላችሁ ደግሞ እንዴት እንደነበርን ታውቃላችሁ። 6 በብዙ መከራ ውስጥ ቃሉን ከመንፈስ ቅዱስ ደስታ ጋር ስትቀበሉት እኛንና ጌታን የምትመስሉ ሆናችሁ፣ 7 በመቄዶንያ ሁሉና በአካይያ ላሉ ለሚያምኑት ምሳሌ ሆናችሁላቸዋል። 8 የጌታ ቃል ከእናንተ ተነሥቶ በመቄዶንያና አካይያ ብቻ ሳይሆን ምንም መናገር እስከማያስፈልገን ድረስ በእግዚአብሔር ላይ ያላችሁ እምነት በሁሉ ሥፍራ ተወርቷል። 9 እኛን በሚመለከት እንዴት ያለ አቀባበል እንዳደረጋችሁልን፣ ሕያውና እውነተኛ የሆነውን አምላክ ታገለግሉ ዘንድ ከጣዖታት እንዴት ወደ እግዚአብሔር ዘወር 10 እንዳላችሁ፣ደግሞም ከሰማይ የሚመጣውን ልጁን፣ ያም ከሙታን ያስነሳውን፣ ሊመጣ ካለው ቁጣ የሚያድነንን ኢየሱስን እንደምትጠባበቁ እነርሱ ራሳቸው ይመሰክራሉ።
ጳውሎስ፣ ስልዋኖስ ጢሞቴዎስም ለቤተ ክርስቲያን UDB በግልጽ ይህንን ደብዳቤ የጻፈው ጳውሎስ መሆኑን ይናገራል፡፡ ሠላም ለእናንተ ይሁን በዚህ ሥፍራ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የተሰሎንቄ አማኞችን ነው፡፡
እኛም ሁል ጊዜ ለእግዚአብሔር ምስጋናችንን እናቀርባለን አማራጭ ትርጉም: "አዘውትረን ለእግዚአብሔር ምስጋናን እናቀርባለን" ሁል ጊዜ እኛ በዚህ ሥፍራ “እኛ” የሚለው ቃል ጳውሎስን ስልዋኖስን እና ጢሞቴዎስን የሚወክል እንጂ በተሰሎንቄ ያሉ አማኞችን የሚወክል አይደለም፡፡ በጸሎታችን ስለ እናንተ እናሳስባለን "ስለ እናንተ እንጸልያለን" ያለማቋረጥ እናስባለን "ያለማቋረጥ እናስባለን" የእምነት ሥራ "የእምነት ሥራ" ወይም "በእግዚአብሔር የሚታምኑ ስለሆነ ለእርሱ ትሠራላችሁ" (UDB) የጠስፋችሁን መጽናት "በመተማመን መጽናታችሁን"
ወንድሞች "ወንድሞች" መጠራታችሁን እናውቃለን "በልዩ ሁኔታ ታገለግሉት ዘንድ እግዚአብሔር እንደመረጣችሁ እናውቃን" ወይም "የእርሱ ሕዝቦች እንሆን ዘንድ እግዚአብሔር እንደመረጣችሁ እናውቃለን" (UDB) እናውቃለን በዚህ ሥፍራ “እኛ” የሚለው ቃል ጳውሎስ፣ ስልዋኖስ እና ጢሞቴዎስን የሚያመለክት እንጂ በተሰሎንቄ ያሉትን አማኞችን የሚያመለክት አይደለም፡፡ ነገር ግን በኃይል፣ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት አማራጭ ትርጉሞች 1) "ጳውሎስ እና የእርሱ የሥራ አጋሮች በመንፈስ ቅዱስ ኃይል አማካኝነት ወንጌልን በኃይል ይሰብካሉ፡፡" ወይም 2) "ወንጌል በመንፈስ ቅዱስ ወቃሽ ኃይል አማካኝነት በአማኞች ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ የሚያመጣ ነው፡፡" በላቀ ማረጋገጫ "በተመሳሳይ መልኩ" (UDB) ምን ዓይነት ሰዎች "እንዲህ ሲሆን እንዴት ባለ ሁኔታ መኖር እንዳለብን" (UDB)
እኛን መሳዮች ሆናችኋል መመስል ማለት መኮረጅ ወይም መከተል ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “እኛ መስላችኋል”፡፡ በታላቅ መከራ "በታላቅ መከራ ወቅት" ወይም "በታላቅ ስደት ውስጥ" አካይ ይህች ከተማ በዘመኗ ግሪክ ውስጥ የነበረች ከተማ ናት፡፡
ወጥተዋል "ወጥቶ ሄዷል" አካይ ይህች ከተማ በዘመኗ ግሪክ ውስጥ የነበረች ከተማ ናት፡፡ ) በእያንዳንዱ ሥፍራ "በአከባቢው ሁሉ ባሉ የተለያዩ ቦታዎች" እነርሱ ራሳቸው ስለሆኑ ጳውሎስ በዚህ ሥፍራ ላይ እያመለከተ ያለው ስለ ተሰሎንቄ አማኞች የሰሙትን በዚያ አከባቢ የሚገኙ ቤተ ክርስቲያናትን ነው፡፡ እነርሱ ራሳቸው በዚህ ሥፍራ ላይ “እነርሱ ራሳቸው” ስለ ተሰሎንቄ አማኞች የሰሙትን ሰዎች አጽኖት ሰጥቶ ያመለክታል፡፡ ወደ እናንተ መግባታችን እንዴት እንደነበረ ስለ እኛ ይናገራሉና፤ "እንዴት ባለ መልኩ እኛን እንደተቀበላችሁ ታውቃላችሁ" (UDB) ልጆቹ ይህ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያሳይ ወሳኝ የሆነ ስም ነው፡፡ እርሱ ያስነሳው "እግዚአብሔር ከሞት ያስነሳው" እኛንም ያዳነን በዚህ ሥፍራ ላይ ጳውሎስ “እኛ” በሚለው ቃል ውስጥ የሚጽፍላቸውን ዓማኞች አካቷል፡፡
1 ወንድሞች ሆይ! ወደ እናንተ መምጣታችን ፍሬቢስ እንዳልነበረ እናንተው እራሳችሁ ታውቃላችሁ፣ 2 ነገር ግን እንደምታውቁት ቀደም ሲል በፊልጵስዩስ መከራና እንግልት ደረሰብን። በብዙ ተቃውሞ መካከል የእግዚአብሔርን ወንጌል ለእናንተ ለመንገር አምላካችን ድፍረት ሰጥቶናል። 3 የምንመክራችሁ ምክር ከስሕተት ወይም ከእርኩሰት ወይም ከማታለል የመነጨ አይደለም፣ 4 ነገር ግን ወንጌልን በአደራ ይሰጠን ዘንድ እግዚአብሔር ታማኞች አድርጎ እንደቆጠረን እንዲሁ ሰውን ሳይሆን ልባችንን የሚመረምረውን እርሱን ደስ ለማሰኘት እንናገራለን። 5 እናንተው እንደምታውቁት መቼም ቢሆን የሽንገላን ቃል አልተጠቀምንም፣ ገንዘባችሁን በመመኘት እንዳልሆነም እግዚአብሔር ምስክር ነው፣ 6 የክርስቶስ ሐዋርያት እንደመሆናችን ልንጠቀምባችሁ መብት ቢኖረንም እንኳን ከእናንተ ወይም ከሌሎች ክብርን ከማንም ሰው አልፈለግንም። 7 ይልቁንም እናት የራስዋን ልጆች እንደምትንከባከብ በመካከላችሁ የዋሆች ሆንን። 8 ለእናንተ ካለን ፍቅር የተነሳ የእግዚአብሔርን ወንጌል ብቻ ሳይሆን የራሳችንን ሕይወት እንኳን ጨምረን ብንካፈላችሁ ደስ ይለን ነበር፣ ምክንያቱም ለእኛ እጅግ የተወደዳችሁ ሆናችኋልና። 9 ወንድሞች ሆይ! የእግዚአብሔርን ወንጌል በሰበክንላችሁ ጊዜ በማናችሁም ላይ ሸክም ላለመሆን ቀንና ሌሊት እንደሠራን ድካማችንንና ጥረታችንን ታስታውሳላችሁ። 10 በእናንተ በምታምኑት መካከል እንዴት በቅድስና፣ በጽድቅና ነቀፋ በሌለበት ኑሮ ራሳችንን እንዳቀረብንላችሁ እግዚአብሔርና እናንተም ጭምር ምስክሮች ናችሁ፣ 11 እናንተው እንደምታውቁት አባት ለራሱ ልጆች እንደሚያደርገው እያንዳንዳችሁን መከርናችሁ፣ አበረታታናችሁና 12 መሰከርንላችሁ፣ይኸውም ወደ ራሱ መንግሥትና ክብር ለጠራችሁ ለእግዚአብሔር እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ ነው። 13 በዚህ ምክንያት እኛ ደግሞ ሳናቋርጥ እግዚአብሔርን እናመሰግናለን፣ የመልዕክቱን ቃል፣ የእግዚአብሔርን ቃል ከእኛ በሰማችሁ ጊዜ እንደ ሰው ቃል ሳይሆን፣ ነገር ግን እውነት እንደሆነ፣ በእናንተ በምታምኑት ደግሞ እንደሚሠራ እንደ እግዚአብሔር ቃል ተቀበላችሁት። 14 እናንተም ወንድሞች ሆይ፣ በይሁዳ የሚኖሩ በክርስቶስ ኢየሱስ የሚያምኑትን የእግዚአብሔር አብያተክርስቲያናት የምትመስሉ ሆናችኋል፣ እነርሱ ከአይሁድ መከራ እንደደረሰባቸው እናንተ ደግሞ ከገዛ ራሳችሁ ሕዝብ ያንኑ መከራ ተቀብላችኋልና፣ 15 አይሁድ ጌታ ኢየሱስንና ነቢያትን ገደሉ፣ እኛንም አሳደዱን፣ እነርሱ እግዚአብሔርን ደስ አያሰኙትም፥ ሰውን ሁሉ ይቃወማሉ። 16 ዘወትር ኀጢአታቸውን ለማብዛትም ይድኑ ዘንድ ለአሕዛብ እንዳንናገር ይከለክሉናል። ቁጣው በላያቸው ላይ መጥቶባቸዋል። 17 ወንድሞች ሆይ፣ እኛ ለጥቂት ጊዜ በልባችን ሳይሆን በአካል ተለይተናችሁ ነበር፣ በመሆኑም በነበረን ታላቅ ናፍቆት ፊታችሁን ለማየት የተቻለንን ያህል ጥረት አድርገናል፣ 18 ወደ እናንተ ለመምጣት ፈልገን ነበር፣ እኔ ጳውሎስም ከአንድም ሁለት ጊዜ ሞከርኩኝ፣ ነገር ግን ሰይጣን አዘገየን። 19 ጌታችን ኢየሱስ በሚመጣበት ጊዜ በፊቱ ተስፋችን ወይም ደስታችን ወይም የመክበራችን አክሊል እንደሌሎቹ ሁሉ እናንተ አይደላችሁምን? 20 ምክንያቱም እናንተ ክብራችንና ደስታችን ናችሁ።
እናንተ ራሳችሁ
በዚህ ሥፍራ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በተሰሎንቄ የሚገኙ አማኞችን ነው፡፡
ወንድሞች
በዚህ ሥፍራ ላይ ቃሉ ያለው ትርጉም ክርስቲያኖች ማለት ሲሆን ወንዶችን እና ሴቶችን ያካትታል፡፡ በክርስቶስ የሚያምኑ ሰዎች ሁሉ እግዚአብሔር መንፈሳዊ አባታቸው የሆነ የአንድ መንፈሳዊ ቤተሰብ አባላት በመሆናቸው ምክንያት ነው፡፡
መምጣታችን
በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል ጳውሎስ፣ ስልዋኖስ እና ጢሞቴዎስን የሚያመለክት ነው፡፡ ይሁን እንጂ በተሰሎንቄ የነበሩትን አማኞች ግን አያመለክትም፡፡
ከንቱ አልነበረም
"በጣም ጠቃሚ ነበር"
መከራን ተቀበልን እንዲሁም ተዋረድን
ጳውሎስ በፊልጵስዮስ እያለ ተደብድቧል እንዲሁም ታሥሯል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ተንገላታን እንዲሁም ተሰደብን፡፡"
ከብዙ ግጭቶች መካከል
"ታላቅ ተቃውሞ ከደረሰብን በኋላ"
ለእኛ ብርታት ይሆነን ዘንድ በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል ጳውሎስ፣ ስልዋኖስ እና ጢሞቴዎስን የሚያመለክት ነው፡፡ ከስሕተት ወይም ከርኵሰት ወይም ከተንኰል አልነበረምና፤ "እውነተኛ፣ ንጹሕ እና ታማኝ" ልባችንን የሚመረምረው እግዚአብሔር "አእምሮዋችንን እና ሥራችንን የሚመረምረው እግዚአብሔር"
እኛ ስለሆንን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል ጳውሎስ፣ ስልዋኖስ እና ጢሞቴዎስን የሚያመለክት ነው፡፡ ይሁን እንጂ በተሰሎንቄ የነበሩትን አማኞች ግን አያመለክትም፡፡ በሚያማልል መልኩ ከቶ አልተናገርንም "የውሸት ሙገሳን ከቶ አልተናገርንም" ያመካኘን በመጐምጀት አልሠራንም፤ "ወይም በስስት እናንተ የተለያዩ ነገሮችን ትሰጡን ዘንድ የተለያዩ ቃላትን አልተጠቀምንም" የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች ይገባናል ማለት እንችል ነበር "የተለያዩ ነገሮችን እንዲትሰጡን ልንጠይቅ እንችል ነበር"
ልክ እናት ልጆቿን እንደሚታጽናና ልክ እናት በእርጋታ ልጇችን እንደምታጽናና እንዲሁም ጳውሎስ፣ ስልዋኖስ እና ጢሞቴዎስን ለተሰሎንቄ አማኞች ረጋ ባለ ሁኔታ አስረድተዋቸዋል፡፡ እንወዳችኋለን "ወደናችኋል" ለእኛ በጣም የተወደዳችሁ ሆናችኋል "ለእናነት ከልባችን እንጠነቀቃለን" ወንድሞች በዚህ ሥፍራ ላይ ቃሉ ያለው ትርጉም ክርስቲያኖች ማለት ሲሆን ወንዶችን እና ሴቶችን ያካትታል፡፡ በክርስቶስ የሚያምኑ ሰዎች ሁሉ እግዚአብሔር መንፈሳዊ አባታቸው የሆነ የአንድ መንፈሳዊ ቤተሰብ አባላት በመሆናቸው ምክንያት ነው፡፡ ልፋታችን እና ድካማችን “ድካማችን” እና “ልፋታችን” የሚሉት ቃላት በመሠረታዊነ ትርጉማቸው ተመሣሣይ ናቸው፡፡ ጳውሎስ እነዚህ ቃላት የተጠቀመው በእነርሱ መካከል ሳለ ጳውሎስ ምን ያኸል እንደደከመ ለማሳየት መው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ምን ያኸል በትጋት እንደሠራን፡፡" በማናችሁም ላይ ሸክም እንዳንሆን ብለን ቀን ከሌት ሠራን "ከእናንተ ዘንድ እርዳታ እንዳንሻ በማለት ለራሳችን የሚያስፈልገንን ነገር ሠረተን አገኘን፡፡"
ቅዱስ፣ ጻድቅ እና እንከን ያሌለበት ጳውሎስ እነዚህ በመሠረታዊ ትርጉማቸው ተመሳሳይ ቃላትን በዚህ ሥፍራ የተጠቀመበት ምክንያት በመካከላቸው ሳለ ጥሩ ባሕርይ እንደነበረው አጽኖት ሰጥቶ ለማሳየት ነው፡፡ አባት ከልጆቹ ጋር ጳውሎስ አባት ልጆቹ ምን ዓይነት ባሕርይ እንዲኖራቸው ከሚያስተምርበት መንገድ ጋር እያነጻጸረ አማኞች ለእግዚአብሔር እንደሚገባ ይኖሩ ዘንድ አማኞችን ያበረታታል፡፡ እየመከርንን እናጽናናችኋለን “መምከር” እና “ማጽናናት” የሚሉት ቃላት በመሠረታዊ ሀሳባቸው ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው ቃላት ነው፡፡ ጳውሎስ እነዚህ ቃላት በዚህ ሥፍራ ላይ የተጠቀመው በተሰሎንቄ የሚኖሩ ክርስቲያኖችን ለማበረታታት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “እኛ አጥብቀን እናበረታታችኋለን”፡፡ ለራሱ መንግስት እና ክብር በዚህ ሥፍራ ላይ “ክብር” የሚለው ቃል “መንግስት” ለሚለው ቃል ምንነትን የሚገልጥ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ለእርሱ ለራሱ በክብር የተሞላ መንግስት፡፡"
በዚህም ምክንያት እኛም እግዚአብሔርን ሁል ጊዜ እናመሰግናለን "እግዚአብሔርን ሁል ጊዜ እናመሰግናን ምክንያቱም" እናንተ በተቀበላችሁ ጊዜ በተሰሰሎንቄ ይኖሩ የነበሩ አማኞች ጳውሎስ ያመታውን መልዕክት ከእግዚአብሔር ዘንድ የመጣ መልዕክት አድርገው ተቀበሉት እንጂ ከራሱ በጳውሎስ ኃይል የመጣ አድርገው አላዩትም፡፡
ወንድሞች በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ቃል ክርስትያኖች የሚል ትርጉም አለው፡፡ ቤተ ክርስቲያናትን የሚትመስሉ ሁኑ የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች በአይሁድ መሪዎች ስደት የደረሰባቸው ሲሆን ልክ እንደዚሁም በተሰሎንቄ ያሉት አማኞች በተሰሎንቄ ከተማ በሚኖሩ ሰዎች ስደት ደርሶባቸዋ፡፡ "ቤተ ክርስቲያናትን መስላችኋል" ከገዛ ሀገራችን ሰዎች "ከሌሎች በተሰሎንቄ ከተማ ከሚኖሩ ሰዎች" እንዳንናገር ከለከሉን "እንዳንናገር ሊያስቆሙን ጥረት አደረጉ" ኃጢአታቸውን ይሞላ ዘንድ ሁል ጊዜ "በቀጣይነት ኃጢአት ያደርጉ ዘንድ" ቁጣ በእነርሱ ላይ መጥቶባቸዋል "የእግዚአብሔር ቅጣት በእነርሱ ላይ መጥቷል" ወይም "የእግዚአብሔር ቁጣ በእነርሱ ላይ መጥቷል"
ወንድሞች በዚህ ሥፍራ ቃሉ የሚያመለክተው ክርስትያኖችን ነው፡፡ በአካል፣ በልብ ሳይሆን "በአካል ነገር ግን ሁል ጊዜ ስለ እናንተ መጸለያችንን ቀጥለናል" ፍታችሁን ለማየት "እናንተን ለማየት" ወይም "ከእናንተ ጋር ለመሆን" እኔ ጳውሎስ እንደገና "እኔ ጳውሎስ ሁለት ጊዜ ያኸል ሞክሬያለሁ" እርሱ ሲመጣ ትምክታችን የሚሆነው ምንድ ነው? "ጌታችን ኢየሱስ ዳግም ሲመጣ ለወደፊት ትምክታችን፣ ሐሴት የሚናደርግበት እና የክብር አክልል የሚትሆኑን እናነት እና ሌሎች ናችሁ፡፡"
1 ስለዚህ ከዚያ በላይ ልንታገስ ባልተቻለን ጊዜ በአቴና ለብቻችን መቅረታችን መልካም እንደሆነ አሰብን። 2 በእምነታችሁ ያጸናችሁና ያበረታችሁ ዘንድ ወንድማችንንና በክርስቶስ ወንጌል የእግዚአብሔር አገልጋይ የሆነውን ጢሞቴዎስን ላክንላችሁ፣ 3 ይህንን ያደረግነውም በእነዚህ መከራዎቻችሁ ማንም እንዳይናወጥ ነው፣ ለዚህ እንደተመረጥን ራሳችሁ ታውቃላችሁና። 4 በእርግጥ ከእናንተ ጋር በነበርንበት ወቅት መከራ ልንቀበል እንዳለን አስቀድመን ነግረናችሁ ነበር፣ እንደምታውቁት የሆነውም ይኸው ነው። 5 በዚህ ምክንያት ወደፊት ልታገስ ባቃተኝ ጊዜ ምናልባት ፈታኙ ፈትኗችሁ ልፋታችንም ከንቱ ሆኖ እንዳይቀር ስለ እምነታችሁ አውቅ ዘንድ ላክሁት። 6 ጢሞቴዎስ ከእናንተ ዘንድ ተመልሶ ስለ እምነታችሁና ፍቅራችሁ የምሥራች ባመጣልን ጊዜ ሁልጊዜ በመልካም እንደምታስታውሱንና እኛ ደግሞ ልናያችሁ እንደምንናፍቅ ሁሉ ልታዩን እንደምትናፍቁ ሲነግረን 7 በዚህ ምክንያት ወንድሞች ሆይ፣ በችግራችንና በመከራችን ሁሉ በእናንተ እምነት ተጽናንተናል። 8 በጌታ ጸንታችሁ ብትቆሙ እኛ ደግሞ አሁን በሕይወት እንኖራለን። 9 በእናንተ ምክንያት በአምላካችን ፊት ስላገኘነው ደስታ ሁሉ ስለ እናንተ ለእግዚአብሔር እንዴት ያለ ምስጋና ማቅረብ እንችል ይሆን? 10 ፊታችሁን ለማየትና በእምነታችሁ የሚጎድላችሁን ለመሙላት ሌሊትና ቀን እጅግ አጥብቀን እንጸልያለን። 11 ራሱ አምላካችንና አባታችን፣ ጌታችንም ኢየሱስ ወደ እናንተ እንድንመጣ መንገዳችንን ያቅና፣ 12 እኛ ደግሞ እንደምናፈቅራችሁ ጌታ ለእርስ በርሳችሁና ለሰው ሁሉ የሚሆን ፍቅራችሁን ያብዛ ያትረፍርፍም። 13 ጌታችን ኢየሱስ ከቅዱሳኑ ሁሉ ጋር ሲመጣ በአምላካችንና በአባታችን ፊት ልባችሁን ነቀፋ በሌለበት ቅድስና ያጸና ዘንድ ይህንን ያድርግላችሁ።
ከእንግዲህ ልንሸከመው አንችልም በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል ጳውሎስ፣ ስልዋኖስ እና ጢሞቴዎስን የሚያመለክት ነው፡፡ ይሁን እንጂ በተሰሎንቄ የነበሩትን አማኞች ግን አያመለክትም፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ከእንግዲህ ወዲህ ስለ እናንተ አንጨነቅም፡፡" በአቴና ብቻችንን ልንቀር በጎ ፈቃዳችን ሆነ። "ስልዋኖስ እና አኔ በአቴና ወደ ኋላ ለመቅረት በጎፈቃዳችን ሆነ፡፡" በጎ "ትክክለኛ" ወይም "ምክንያታዊ" አቴና ይህች በአሁና ግሪክ ውስጥ በአካያ ግዛት ውስጥ የሚትገኝ ከተማ ናት፡፡ ወንድማችንr "ክርስትያን ወንድማችን" ማንም ሰው እንዳይናወጥ "ማንም ሰው እንዳይረበሽ" ወይም "ማንም እንዳይደናገጥ" እኛ እንደተመረጥን "እኛ እንደተወሰንን"
እውነት አማራጭ ትርጉም: "በእርግጠኝነት" ወይም "ርግጡን" እኛ ከእናንተ ጋር ነን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል ጳውሎስ፣ ስልዋኖስ እና ጢሞቴዎስን የሚያመለክት ነው፡፡ ይሁን እንጂ በተሰሎንቄ የነበሩትን አማኞች ግን አያመለክትም፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ከእንግዲህ ወዲህ ስለ እናንተ አንጨነቅም፡፡" መካራን መቀበል "በሌሎች ሰዎች መሰቃየት" እታገሥ ዘንድ ባልተቻለኝ ጊዜ በዚህ ሥፍራ ላይ “እኔ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “በአስቸኳይ ለማወቅ እፈልጋለሁ”፡፡ ላኩኝ "ጢሞቴዎስን ላኩኝ" በከንቱ "ጥቅም ላሌለው ነገር"
ወደ እኛ መጣ በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን ስልዋኖስ እና ጢሞቴዎስን እንደጂ በተሰሎንቄ የነበሩ አማኞችን አይደለም፡፡ ስለ እምነታችሁ መልካም ዜናን "ስለ እምነታችሁ መልካም ወሬ ይዞ መጥቷል" እናንተ ሁል ጊዜ መልካም ትዝታ አላችሁ "እናንተ ሁል ገዚ መልካም ትዝታ አላችሁ" ከእንግዲህ ወዲህ አታዩንም "ለታዩን ትፈልጋላችሁ" ወንድሞች በዚህ ሥፍራ “ወንድሞች” የሚለው ቃል ክርስትያኖች ማለት ነው፡፡ በእምነታችሁ በኩል "በክርስቶስ ባላችሁ እምነት በኩል" ወይም "በክርስቶስ ላይ ባላችሁ ቀጣይነት ያለው እምነት፡፡ በመከራችን እና በችግሮቻችን ሁሉ ውስጥ በዚህ ሥፍራ “መከራ” የሚለው ቃል በ”ችግር” ውስጥ ለመግባት ምክንያቱ ምንድ እንደሆነ ያብራራል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ሰዎች መከራን በእኛ ላይ በማምጣታቸው ምክንያት በተፈጠዉት ችግሮቻችን ውስጥ፡፡"
አሁን በሕይወት እንኖራለን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን ስልዋኖስ እና ጢሞቴዎስን እንደጂ በተሰሎንቄ የነበሩ አማኞችን አይደለም፡፡ አማራጭ ትርጉም: "በጣም ተበረታተናል፡፡" እናንተ ጸንታችሁ ቁሙ አማራጭ ትርጉም፡ "እናንተ አብዝታችሁ ታመኑ" ከእናንተ የተነሣ ስለምንደሰተው ደስታ ሁሉ፥ ለእግዚአብሔር በእናንተ ምክንያት ምን ያህል ምስጋና እናስረክብ ዘንድ እንችላለን? ይህ ጥያቄ ምስጋንን የሚያሳይ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እግዚብሔር ስለእናንተ ስላደረገው ነገር እግዚአብሔር አመስግነን አንጠግብም! ወደ እግዚአብሔር ስንጸልይ ስለ እናነት በጣም ደስ ይለናል!" ሌሊት እና ቀን "Frequently" በጣም ከባድ "ከመጠን ይልቅ" ፊታችሁን ላይ "እናንተን ለመጎብኘት"
እግዚአብሔር አምላካችን ያድርግ "አምላካችን ይህንን ያድረግ ዘንድ እንጸልያለን" አምላካችን . . . ጌታችን ኢየሱስ ይህንን ያድረግ በዚህ ሥፍራ ላይ “የእኛ” የሚለው ቃል ሁሉንም አማኞችን የሚያመለክት ቃል ነው፡፡ አብ እራሱ በዚህ ሥፍራ ላይ “እራሱ” የሚለው ቃል ወደ ኃላ ኄዶ “አብ”ን የሚያመለክት ሲሆን ጠቀሜታውም አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ መንገዳችንን ያቅና በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን ስልዋኖስ እና ጢሞቴዎስን እንደጂ በተሰሎንቄ የነበሩ አማኞችን አይደለም፡፡ እኛም ይህንን እናደረጋለን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን ስልዋኖስ እና ጢሞቴዎስን እንደጂ በተሰሎንቄ የነበሩ አማኞችን አይደለም፡፡ እርሱም ይህንን ያድረግ "እግዚአብሔር ይህንን እንዲያደረግ እንጸልያለን" በጌታችን በኢየሱስ መምጫ ጊዜ "ኢየሱስ ወደ ምድር ተመልሶ በሚመጣበት ጊዜ" ከእርሱ ቅዱሳን ሁሉ ጋር "የእርሱ ከሆኑት ሁሉ ጋር" (UDB)
1 በመጨረሻም ወንድሞች ሆይ፣ እንዴት መመላለስና እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት እንዳለባችሁ ከእኛ በተቀበላችሁት ትምህርት መሠረት አሁን እንደምትኖሩት ሁሉ ከዚህም አብልጣችሁ እንድታደርጉ በጌታ በኢየሱስ እንመክራችኋለን እናደፋፍራችሁማለን። 2 በጌታ በኢየሱስ በኩል እንዴት ያለውን ትዕዛዝ እንደሰጠናችሁ ታውቃላችሁና፤ 3 በቅድስና መኖራችሁ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው፣ 4 ከእናንተ እያንዳንዱ ከዝሙት በመራቅ የራሱን አካል በቅድስናና በክብር ማግኘት እንዳለበት ታውቃላችሁ፣ 5 እግዚአብሔርን እንደማያውቁ እንደ አሕዛብ የፍትወት ምኞት አይሁን፣ 6 በዚህ ጉዳይ ማንም አይተላለፍ ወንድሙንም አያታልል፣ ምክንያቱም አስቀድመን እንደነገርናችሁና እንዳስጠነቀቅናችሁ ጌታ ስለነዚህ ነገሮች ሁሉ የሚበቀል ነውና። 7 እግዚአብሔር ለቅድስና እንጂ ለእርኩሰት አልጠራንም። 8 ስለዚህ ይህንን የማይቀበል ሰውን ሳይሆን የማይቀበለው ቅዱስ መንፈሱን የሰጣችሁን እግዚአብሔርን ነው። 9 የወንድማማች መዋደድን በተመለከተ ማንም ሊጽፍላችሁ አያስፈልጋችሁም፣ እርስ በርስ ስለመዋደድ እናንተው ራሳችሁ ከእግዚአብሔር ተምራችኋልና። 10 በመቄዶንያ ላሉ ወንድሞች ሁሉ ይህንን ታደርጋላችሁ፣ ይሁን እንጂ ወንድሞች ሆይ፣ ከዚህም አብልጣችሁ እንድታደርጉት ደግሞ እንመክራችኋለን። 11 ደግሞም ልክ እንዳዘዝናችሁ በጸጥታ እንድትኖሩ፣ በራሳችሁ ጉዳይ ላይ እንድታተኩሩና በገዛ እጆቻችሁ እንድትሠሩ እንመክራችኋለን። 12 በማያምኑት ዘንድ በአግባብ እንድትመላለሱና በኑሮአችሁ ምንም የሚጎድላችሁ እንዳይኖር ይህንን አድርጉ። 13 ወንድሞች ሆይ፣አንቀላፍተው ስላሉት ባለማወቃችሁ ስለወደፊቱ ተስፋ እንደሌላቸው እንደ ሌሎች ሀዘናችሁ መሪር እንዲሆን አንፈልግም። 14 ኢየሱስ እንደሞተና እንደተነሳ ካመንን በእርሱ አምነው ያንቀላፉትን እግዚአብሔር ከኢየሱስ ጋር ያመጣቸዋል። 15 በጌታ ቃል የምንነግራችሁ ይህንን ነው፣ ጌታ በሚመጣበት ጊዜ እኛ ሕያዋን ሆነን የቀረነው አስቀድመው ያንቀላፉትን በርግጥ አንቀድምም። 16 ጌታ ራሱ በታላቅ ድምፅ፣ በመላዕክት አለቃ ድምፅና በእግዚአብሔር መለከት ከሰማይ ይወርዳል፣ በክርስቶስ የሞቱትም አስቀድመው ይነሳሉ። 17 ከዚያም እኛ ሕያዋን ሆነን የምንገኘው ጌታን በአየር ላይ ለመገናኘት ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፣ ሁልጊዜም ከጌታ ጋር እንሆናለን። 18 ስለዚህ እርስ በርሳችሁ በእነዚህ ቃላት ተጽናኑ።
ወንድሞች በዚህ ሥፍራ “ወንድሞች” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ክርስትያኖችን ነው፡፡ እንመክራችኋለን እንዲሁም እንለምናችኋለን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን ስልዋኖስ እና ጢሞቴዎስን እንደጂ በተሰሎንቄ የነበሩ አማኞችን አይደለም፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ “መምከር” እና “መለመን” የሚሉ ቃላት በመሠረታዊ ትርጉማቸው ተመሣሣይ ናቸው፡ ጳውሎስ በበዚህ ሥፍራ ላይ እነዚህ ቃት የተጠቀመው አጽኖት ለመስጠት እና ምን ያኸለወ አማኞችን ለማበረታታት እንደፈለገ ለማሳየት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "አብዝተን እናንተን እናበረተታችኋለን፡፡" ከ . . . ዘንድ መመሪያ ወስዳችኋል "እናንተ በ . . . ተምራችኋል" ልትመላለሱ ይገባል በዚህ ሥፍራ “መመላለስ” የሚለው ቃል የአንድ ሰው አኗኗር መንገድን የሚያሳይ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "እናት መኖር ይገባችኋል፡፡"
ከዝሙት እንዲትርቁ "ከዝሙት ተግባር ራቁ" እንዴት ማግኘት እንዳለባችሁ ታውቁ ዘንድ "እንዴት አብራችሁ መኖር እንደሚትችሉ እንዲታውቁ" በፍተወት ምኞት "ትክክለኛ ያልሆነ የዝሙት ጥማት" ማንም "አንድም ሰው" ወይም "ዬትኛውም ሰው" መተላለፍ እና መበደል ይህ አንድን ሀሳብ በሁለት የተለያዩ መንገዶች መግለጽ ነው፡፤ አማራጭ ትርጉም፡ “መበደል”፡፡ ጌታ የሚበቀል ነው "ጌታ የሚተላለፉትን ይቀጣል እንዲሁም ለተበደሉት ይሟገትላቸዋል" እናንተን አስቀድሞ አስጠንቅቋችኋልና ተመስክሮላችኋል "አስቀድሞ ለእናነት ተነግሯችኋል እንዲሁም ከዚህ ነገር እንዲትቆጠቡ አበክሮ አስጠንቅቆዋችኋል"
እግዚአብሔር ቅድስና እንጂ ለርኩሰት አልጠራንም "እግዚብሔር ፍጹም ንጹሐን እና ቅዱሳን እንዲንሆን ጠርቶናል" እግዚአብሔር አልጠራንም በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሁሉንም አማኞች ነው፡፡ ይህንን የማይቀበል ሰው "ይህንን ትምህርት የማይቀበል ማንኛውም ሰው" ወይም "ይንን ትምህርት ቸል የሚል ማንኛውም ሰው"
የወንድማማች መዋደድ "ለአማኞች ያለ ፍቅር" እንዲሁ በመቄዶንያ ሁሉ ላሉት ወንድሞች ሁሉ ታደርጋላችሁና። "በመቅዶንያ ውስጥ ላሉት አማኞች ፍቅር ታሳያላችሁና፡፡" ወንድሞች በዚህ ሥፍራ “ወንድሞች” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ክርስቲያኖችን ነው፡፡ መነሳሳት "መከታተል" ወይም "ከልብ መጣር" የራሳችሁን ሥራ ሥሩ ይህ ማለት የሌላ ሰው ጉዳይ ውስጥ ጣልቃ አትግቡ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “የራሳችሁን ጉዳይ ብቻ ሥሩ”፡፡ በእጆቻችሁ ሥሩ "ለመኖር የሚያስፈልጋችሁን ለማግኘት የራሳችሁን ሥራ ሥሩ" በአግባቡ ተመላለሱ "በአክብሮት እና አግባብ ባለው መንገድ ነገሮች አከናውኑ" ተመልከት: ከእምነት ውጪ ያሉ ሰዎች "በክርስቶስ የማያምኑ ሰዎች" የሚያስፈልጋችሁ ነገር እንዳይኖር "አንዳች እንዳያስፈልጋችሁ"
በተሳሳተ መንገድ እንዳትረዱት እንሻለን "በተገቢው መንገድ እንዲትገነዘቡን ዘንድ መሻታችን ነው" አንልግም በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን ስልዋኖስ እና ጢሞቴዎስን እንደጂ በተሰሎንቄ የነበሩ አማኞችን አይደለም፡፡ ወነወድሞች በዚህ ሥፍራ “ወንድሞች” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ክርስትያኖችን ነው፡፡ ማንቀላፋት ይህ ቃል በዚህ ሥፍራ ያለው ትርጉም “መሞት” ማለት ነው፡፡ ማዘን የለባችሁም "ማልቀስ የለባችሁም" ተስፋ እንደሌላቸው እንደ ሌሎች ደግሞ እንዳታዝኑ፥ "እንደማያምኑ ሰዎች" የምናምን ከሆነ በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን እና የእርሱ ተደራሲያንን ነው፡፡ ከሞት እንደገና ተነሣ "ወደ ሕይወት እንደገና ተነሣ" እንዲሁም በኢየሱስ ያንቀላፉቱን እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ያመጣቸዋልና። "እርሱ ተመልሶ ስመጣ በኢየሱስ አምነው የሞቱትን መልሶ ከሞት ያስነሳቸዋል፡፡" ማቀላፋት ምሳሌያዊ ነግግር ሲሆን የሚያመለክተውም መሞትን ነው፡፡ ስለዚህም እንዲህ እንላለን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን ስልዋኖስ እና ጢሞቴዎስን እንደጂ በተሰሎንቄ የነበሩ አማኞችን አይደለም፡፡ ጌታ ዳግም ሲመጣ "በክርስቶስ መምጫ ቀን" በእርግጥ አንቀድምም "ከእርሱ ፈጽሞ አንቀድምም"
ጌታ ራሱ ይወርዳል "ጌታ ራሱ ወደታች ይወርዳል" የመላእክት አለቃ "የመላእክት አለቃ" በክርስቶስ ሆነው የሞቱት በመጀመሪያ ይነሣሉ በዚህ ሥፍራ ይህ ቃል ያለው ትርጉም አካላዊ ሞትን የሚያመለክት ነው፡፡ "በኢየሱስ ክርስቶስ ያመኑት ነገር ግን የሞቱት ሰዎች በመጀመሪያ ከሞት ይነሣሉ" እኛ በሕይወት ያለን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሁሉንም አማኞችን ነው፡፡ ከእነርሱ ጋር በዚህ ሥፍ “እነርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የሞቱትን አማኞችን ነው፡፡ ጌታን በአየር ላይ ለመገናኘት በዳመና እነንነጠቃለን "ጌታን በሰማይ ለመገናኘት"
1 ወንድሞች ሆይ፣ አሁን ስለ ጊዜያትና ዘመናት ሊጻፍላችሁ አያስፈልጋችሁም። 2 ሌባ በሌሊት እንደሚመጣ የጌታ ቀንም እንደዚያው እንደሆነ እናንተ ራሳችሁ በሚገባ ታውቃላችሁና። 3 እርጉዝን ሴት የምጥ ህመም እንደሚሆንባት ሁሉ “ሁሉ ሰላምና ደህና ነው” በሚሉበት በዚያን ጊዜ ድንገተኛ ጥፋት ይመጣባቸዋል፣ እነርሱም በምንም መንገድ አያመልጡም። 4 ወንድሞች ሆይ፣ እናንተ ግን ያ ቀን እንደ ሌባ ይመጣባችሁ ዘንድ በጨለማ አይደላችሁም። 5 ሁላችሁም የብርሃን ልጆች የቀንም ልጆች ናችሁና። እኛ የሌሊት ወይም የጨለማ ልጆች አይደለንም። 6 እንግዲያውስ ሌሎች እንደሚያደርጉት አናንቀላፋ፣ ነገር ግን እንንቃ በመጠንም እንኑር። 7 የሚያንቀላፉ በሌሊት ያንቀላፋሉ፣ የሚሰክሩትም በሌሊት ይሰክራሉና። 8 የብርሃን ልጆች እንደመሆናችን በመጠን እንኑር፣ የእምነትንና የፍቅርን ጥሩር፣ የድነታችንን ተስፋ እርግጠኝነትም እንደ ራስ ቁር እንልበስ። 9 በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት ድነትን ልንቀበል እንጂ እግዚአብሔር ለቁጣ አልመደበንም፣ 10 የነቃን ወይም ያንቀላፋን ብንሆን ከእርሱ ጋር እንድንኖር ስለ እኛ ሞቶአልና። 11 ስለዚህ አሁን እንደምታደርጉት ሁሉ እርስ በርሳችሁ ተጽናኑ፣ አንዱም ሌላውን ያንጸው። 12 ወንድሞች ሆይ፣በመካከላችሁ በማገልገል የሚለፉትንና በጌታ የሚያስተዳድሯችሁን፣ የሚመክሯችሁንም እንድታከብሯቸው እንጠይቃችኋለን። 13 ደግሞም በሥራቸው ምክንያት ከፍ ያለ የፍቅር አክብሮት እንድታሳዩአቸው እንጠይቃችኋለን። እርስ በርሳችሁ በሰላም ኑሩ። 14 ወንድሞች ሆይ እንመክራችኋለን፣ ያለ ሥርዓት የሚመላለሱትን ገስጹአቸው፣ ድፍረት ያጡትን አበረታቱአቸው፣ ደካሞችን ደግፉአቸው፣ሰውን ሁሉ ታገሱ። 15 ማንም ስለተደረገበት ክፉ ነገር ለሌላው በክፉ እንዳይመልስ ተጠንቀቁ፣ ነገር ግን ለእርስ በርሳችሁና ለሰው ሁሉ መልካም የሆነውን ለማድረግ ሁልጊዜ ትጉ። 16 ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፣ 17 ባለማቋረጥ ጸልዩ፣ 18 ስለ ሁሉም ነገር አመስግኑ፣ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ለእናንተ ነውና። 19 የመንፈስ ቅዱስን ሥራ አታዳፍኑ። 20 ትንቢትን አትናቁ። 21 ሁሉን መርምሩ፣ መልካም የሆነውን ያዙ፣ 22 ማንኛውንም ዓይነት ክፋት አስወግዱ። 23 የሰላም አምላክ ራሱ ፈጽሞ ይቀድሳችሁ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚመጣበት ጊዜ መላው መንፈሳችሁ፣ ነፍሳችሁና ሥጋችሁ ያለ ነቀፋ ይጠበቅ። 24 የጠራችሁ ታማኝ ነው፣ እርሱም ደግሞ ያደርገዋል። 25 ወንድሞች ሆይ፣ ስለ እኛ ደግሞ ጸልዩ። 26 ወንድሞችን ሁሉ በተቀደሰ አሳሳም ሰላም በሏቸው። 27 ይህ መልዕክት ለወንድሞች ሁሉ እንዲነበብ በጌታ አደራ እላችኋለሁ። 28 የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።
ጌዜውን እና ዘመኑን "ጌታ ኢየሱስ ተመልሶ የሚመጣበት ጊዜ" (UDB) ወንድሞች በዚህ ሥፍራ ላይ “ወንድሞች” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ክርስቲያኖችን ነው፡፡ በግልጽ "በደንብ" ወይም "በእርግጥ" (UDB) እንደ ሌባ በምሽት ሌባ በምሽት ለመስረቅ በስትን ሰዓት እንደሚመጣ ማንም እንደማያውቅ ሁሉ ጌታም መቼ እንደሚመጣ አናውቅም፡፡ አማራጭ ትርጉም: "በድንገት፡፡" እነርሱ እንዲህ ሲሉ "ሰዎች እንዲህ ባሏችሁ ጊዜ" ከዚያ ድንገተኛ ጥፋት ይሆናል "ከዚያም ያልተጠበቀ ጥፋት ይሆናል" ምጥ እርጕዝን እንደሚይዛት ልክ እርጉዝ ሴት በድንነት ምጥ እንደሚጀምራት እና እስክትወልድ ድረስ እንደማያቋርጥ እንደዚሁ ጥፋት ይመጣና ከዚህ ጥፋት ሰዎች አያመልጡም፡፡ (ተመልከት:
እናንተ ወንድሞች ሆህ በጨለማ ውስጥ አይደላችሁም በዚህ ሥፍራ “ወንድሞች” የሚለው ቃል ክርስትያኖችን የሚያመለክት ነው፡፡ “የዚህ ክፋት የሞላበት ምድር፣ በጨለማ ውሰጥ አይደላችሁም፡፡" ቀኑ እንደ ሌባ ይደርስባችሁ ዘንድ የጌታ መምጫ ቀን ሌባ ለመዝረፍ መምጣቱ እንደሚያስገርም አያስገርምም፡፡ "ሳትዘጋጁ እንዳይደርስባችሁ፡፡" እናነት ሁላችሁ የብርሃን ልጆች ናችሁ...የጨለማ ልጆች አይደላችም በዚህ ሥፍራ ላይ “የብርሃን ልጆች” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የክርስቶስን ተከታዮችን ነው፡፡ “የጨለማ ልጆች” የሚለው ቃል ደግሞ ዓምን የሚከተሉትን ሁሉ ነው፡፡ ሌሎች እንዳንቀላፉት አናንቀላፋ ጳውሎስ እንቅልፍን ኢየሱስ በዓለም ላይ ለመፍረድ ተመልሶ እንደሚመጣ ከማያውቁ ሰዎች ጋር ያነጻጽረዋል፡፡ "ኢየሱስ ዳግም እንደሚመጣ እንደማያቁ ሌሎች ሰዎች አንሁን፡፡" መሆን በዚህ ክፍል ውስጥ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሁሉንም አማኞችን ነቅተን እንጠብቅ እንዲሁም በመጠን እንኑር በክርስቶስ አማኞች ስለ እርሱ ዳግም ምጻት ማወቅ እና ራሳቸውን በመግዛት መኖር ይገባቸዋል፡፡ የሚያንቀላፉት ሰዎች በምሽት ያንቀላፉ ሰዎች የሚተኙት በምሸት እንደሆነ ሁሉ እንዲሁም ምን እንደተፈጠረ እንደማያወቁ ሁሉ ዓለምም እንዲሁ ናት ክርስቶስ መቼ ተመልሶ እንደሚመጣ አታውቅም፡፡ የሚጠጡ ሰዎች ይህንን በምሽት ያደርጋሉ ጳውሎስ መጠጥ የሚጠጡ ሰዎች በምሽት ይህንን እንደሚድርጉ በምግለጽ እንዲሁም ሰዎች ክርስቶስ ዳግም እንደሚመጣ አለማወቃቸው ራሳቸውን ገዝተው እንዳይሩ ያደርጋል፡፡
የብርሃን ልጆች ይህ በክርስቶስ የሚምኑ ሰዎች መገለጫ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በክርስቶስ የሚያምኑ" ወይም "የብርሃን ልጆች፡፡" ራሳችንን እንግዛ "ራሳችንን በመግዛት እንኑር" ጥሩር ልበሱ ወታደር አካሉን ለመጠበቅ ጥሩር ይለብሳል፡፡ እንዲሁም በእመነት እና በፍቅር የሚኖር አማኝም መከላከያ ያገኛል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ራሳችንን እንጠብቅ፡፡” የራስ ቁር ልክ የራስ ቁር የወታደሮችን ራስ ቅል ከአደጋ እንደሚጠብቅ ሁሉ የድነት ዋስትናም አማኞችነን ይጠብቃል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ይህንን እወቁ” ነቅተንም ይሁን አልቀላፈተን ቢሆን "በሕይወት ቢንኖር ወይም ቢንሞት" እርስ በእርሳችሁ ተናነጹ "እርስ በእርሳችሁ ተበረታቱ"
ወንድሞች በዚህ ሥፍራ ላይ “ወንድሞች” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አማኞችን ነው፡፡
በመካከላችሁ የሚደክሙትን በጌታም የሚገዙአችሁን የሚገሥጹአችሁንም ታውቁ ዘንድ ስለ ሥራቸውም በፍቅር ከመጠን ይልቅ ታከብሩአቸው ዘንድ እንለምናችኋለን። "በመሪነት ላይ ያሉ ሰዎችን አበረታቷቸው"
በጌታም የሚገዙአችሁን ይህ በአንድ አከባቢ ያሉ የአማኞች ቡድኖችን ለማገልገል በእግዚብሔር የተሾሙትን ሰዎችን ያመለክል፡፡ ስለ ሥራቸውም በፍቅር ከመጠን ይልቅ ታከብሩአቸው ዘንድ እንለምናችኋለን። አማራጭ ትርጉም: "ስለ ሥራቸው አክብሯቸው ምክንያቱም ትወዷቸዋላችሁና"
ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤ ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ጳውሎስ አማኞች በነገር ሁሉ የሚያመሰግኑ አመለካከት እንዲኖራቸው፣ በትጋት እንዲጸልዩ እና በሁሉም ነገር አመስጋኞች ይሆኑ ዘንድ ያበረታታል፡፡
ትንቢትን አትናቁ፤ "ትንቢት ይበቃል አትበሉ" ወይም "መንፈስ ቅዱስ ለአንድ ሰው የተናገረውን ነገር አትጥሉ" ሁሉን ነገር ፈትኑ "ሁሉም ትንቢቶች እውነት እና ከእግዚአብሔር መሆናቸውን እርግጠኞች ሁኑ"
ለራሱ ሁሉን ነገር ሙሉ ለሙሉ ሰጥቶዋ አማራጭ ትርጉም: "እናንተን ለይቷል" ወይም "ኃጢአት እንዳታድርጉ ለማድረግ እናንተን ከነቀፋ ውጪ ለማድረግ" (UDB) አጠቃላይ መንፈሳችሁን፣ ነፍሳችሁን እና አካላችሁን እነዚህ በንጽጽር የቀረቡት “መንፈስ፣ ነፍስ እና ሥጋ” የሚሉት ቃላት በመሠረቱ ተመሳሳይ ትርጉም ሲኖራቸው የቀረቡበት ምክንያትም አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ ያለ ነቀፋ ፈጽመው ይጠበቁ። "ኃጢአት ከማደረግ ተቆጠቡ" የጠራችሁ እርሱ የታመነ ነው አማራጭ ትርጉም: "የጠራችሁ እርሱ የታመነ ነው" እርሱ ደግሞ ያደርገዋል "እርሱ ይረዳቿኋል"
ኖት የለውም ።
1 ከጳውሎስ፣ ስልዋኖስና ጢሞቴዎስ በእግዚአብሔር በአባታችን በጌታችንም በኢየሱስ ክርስቶስ ላሉ ለተሰሎንቄ ሰዎች ቤተክርስቲያን። 2 ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችንም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን። 3 ወንድሞች ሆይ፣ ስለ እናንተ ሁልጊዜ ለእግዚአብሔር ምስጋና ማቅረብ አለብን፣ ይህ ተገቢ ነውና፣ ምክንያቱም እምነታችሁ እጅግ እያደገ ነውና፣ የእያንዳንዳችሁ ፍቅርም ለሌሎች የሚተርፍ ሆኗል። 4 በመሆኑም በስደቶቻችሁና በመከራዎቻችሁ ሁሉ ስለ መጽናታችሁ ስለ ትዕግስታችሁና እምነታችሁ እኛ ራሳችን በእግዚአብሔር አብያተክርስቲያናት መካከል በልበ ሙሉነት እንመሰክራለን። 5 እናንተ ደግሞ መከራን ለምትቀበሉለት ለእግዚአብሔር መንግሥት ብቁ ሆናችሁ ትቆጠሩ ዘንድ ይህ የእግዚአብሔር ፍርድ ጻድቅ የመሆኑ ግልጽ ምልክት ነው። 6 መከራን ለሚያመጡባችሁ መከራን ይመልስላቸው ዘንድ ይህ በእግዚብሔር ፊት ቅን ፍርድ ነው፣ 7 ጌታችን ኢየሱስ ከኀይሉ መላዕክት ጋር ከሰማይ በሚገለጥበት ጊዜ ከእኛ ጋር መከራን ለተቀበላችሁት ደግሞ እረፍትን ይሰጣችኋል። 8 እግዚአብሔርን የማያውቁትንና ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል የማይታዘዙትን ግን በሚነድ እሳት ይበቀላቸዋል። 9 ከጌታ ሀልዎትና ከኀይሉ ክብር ርቀው በዘላለም ጥፋት እየተቀጡ ይሰቃያሉ፣ 10 እርሱ በቅዱሳኑ ሊከበር በሚመጣበት በዚያን ቀን፣ ምስክርነታችንን አምናችኋልና በሚያምኑት ሁሉ ይገረምባቸዋል። 11 በዚህ ምክንያት እኛ ደግሞ አምላካችን ለጥሪአችሁ የተገባችሁ አድርጎ ይቆጥራችሁና መልካሙን ምኞታችሁንና ማናቸውንም የእምነት ሥራ በኀይል ይፈጽምላችሁ ዘንድ ባለማቋረጥ እንጸልይላችኋለን። 12 ይህም በአምላካችንና በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ምክንያት የጌታችን የኢየሱስ ስም በእናንተ እንዲከበርና እናንተም በእርሱ ትከብሩ ዘንድ ነው።
ስልዋኖስ "ስልዋኖስ " በላቲን ሲላስ ማለት ነው፡፡ " ይህ ሰው በሐዋሪያትሰ ሥራ መጽሐፍ ላይ ከጳውሎስ ጋር ጉዞ ያደረገው ሰው ነው፡፡ እናነተ በዚህ ቁጥር ላይ “እናንተ” የሚለው ቃለ በተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን ያሉ አማኞችን የሚያሳይ
ግድ አለብን፤
ግድ አለብን
“አለብን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን፣ ስልዋኖስንና ጢሞቲዮስን እንጂ የተሰሎንቄ አማኞችን አይደለም፡፡
ሁልጊዜ እግዚአብሔርን ልናመሰግን
እግዚአብሔርን በተደጋጋሚ እናመሰግናለን ማለት ነው፡፡
ስለእናነተ
እዚህ ላይ “ስለእናንተ” የሚያመላክተው በተሰሎንቄ የሚገኙ አማኞችን ነው፡፡
ወንድሞች ሆይ “ወንድሞች” ማለት ሌሎች አማኞችን ማለት ነው፡፡ እንደሚገባ ተገቢን ነገር ማድረግ በተገቢው ሁኔታ ማድረግ ወይም መልካምን ነገር ማድረግ ማለት ነው፡፡ እኛ ራሳችንን በዚህ ስፍራ “ራሳችንን” የሚለው ቃል ጳውሎስ ያለውን መመካት የሚያመለክት ነው፡፡ እርስ በርሳችሁ "ከሌሎች አማኞች ጋር ማለት ነው፡፡" በስደታችሁና በመከራችሁ በመሰረቱ እነዚህ ሁለት ቃላት ተመሳሳይ ናቸው፡፡ እነዚህ ሁለት ቃላት ጳውሎስ አጣምሮ የተጠቀመበት ምክንያት የሚያልፉበት መከራ ምን ያዕል የጸና እንደነበር ለማሳት ነው፡፡ ለእግዚአብሔር መንግሥት የምትበቁ ሆናችሁ ትቈጠሩ ዘንድ፥ አት AT: "በእግዚአብሔር መንግስት ዋጋ እንዳለው ተደርጋችሁ ትታሰቡ ዘንድ “(ተመልከት:
በእግዚአብሔር ፊት በእርግጥ ጽድቅ ነውና "እግዚአብሔር ልክ ነው" ወይም "እግዚአብሔር ጻድቅ ነው " ዕረፍትን አት : "እግዚአብሔር እረፍትን ይመልስላችኃል፡፡"
ከሥልጣኑ መላእክት "የእግዚአብሔር ኃያላን መልዕክተኞች "
በእሳት ነበልባል ሲገለጥ ይበቀላል "ጌታኢየሱስ በእሳት ነበልባል ይቀጣቸዋል " ወይም "በእሳት ነበልባል እረሱ ይቀጣቸዋል፡፡" (UDB)
ይቀጣሉ "ለወንጌል ያልታዘዙ ሰዎች ይቀጣሉ " በዚያም ቀን ሲመጣ "ኢየሱስ በጌታ ቀን ሲመጣ” በቅዱሳኑ ሊከብር፥ አትAT: "አማኞች ያከብሩታል " በሚያምኑት ሁሉ ዘንድ ሊገረም to be marveled at by all those who believed አትAT: "የሚያምኑት ሁሉ ይደነቃሉ” ወይም "በእርሱ የሚያምኑት ሁሉ በመገረም አብረውት ይቆማሉ፡፡” /ተመልከት: አምናችኋልና በዚህ ቃል ውስጥ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የተሰሎንቄ አማኞችን ነው፡፡ (ተመልከት:
ስለ እንናነተ ሁል ጊዜ እንጸልያለን "ስለእናንተ ባለማቋረጥ እንጸልያለን” የሚጸልዩት ጳውሎስን፣ ስልዋኖስንና ጢሞቲዮስ ናቸው፡፡
እናንተ “እናንተ” የሚለው ቃል በተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን ያሉ አማኞችን ያመለክታል፡፡ ለመጥራቱ እግዚአብሔር ሰዎች ልጆቹ፤ አገልጋዮቹና በኢየሱስ በኩል የተገለጠውን የድኅነት ወንጌል አብሳሪዎች እንዲሆኑ መምረጡ ወይም መሾሙን የሚያመለክት ነው፡፡ የበጎነትንም ፈቃድ ሁሉ "በምትፈልጉበት መንገድ ሁሉ በጎ ማድረግ እንድትችሉ” (UDB) የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስም በእናንተ ዘንድ ሊከብር አትAT: "የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስምን እንድታከብሩ" እናንተም በእርሱ ዘንድ ልትከብሩ፥ አት AT: "ኢየሱስ እንዲያከብራችሁ " እንደ አምላካችን ጸጋ፥ "በአምላካችን ጸጋ ምክንያት"
ኖት የለውም።
1 ወንድሞች ሆይ፣ አሁን የምንለምናችሁ ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መምጣትና ወደ እርሱ ስለመሰብሰባችን ነው፣ 2 ከእኛ የሆነ በሚመስል በመንፈስ፣ በቃል ወይም በደብዳቤ እነሆ የጌታ ቀን ሆኗል ብላችሁ በማመን በቀላሉ በአዕምሮአችሁ እንዳትናወጡ ወይም እንዳትደነግጡ እንለምናችኋለን። 3 በየትኛውም መንገድ ማንም አያስታችሁ። የመጨረሻው ክህደት ሳይመጣና የአመጽ ሰው እርሱም የጥፋት ልጅ ሳይገለጥ ያ ቀን አይመጣምና። 4 የሚቃወመውና አምላክ ከተባለው ወይም ከሚመለከው ሁሉ በላይ ራሱን ከፍ የሚያደርገው እርሱ ነው፣ በእግዚአብሔር ቤተመቅደስ እስኪቀመጥም ድረስ ራሱን እንደ አምላክ ያስተዋውቃል። 5 ከእናንተ ጋር በነበርኩበት ጊዜ ስለእነዚህ ነገሮች እንደነገርኳችሁ ትዝ አይላችሁምን? 6 በትክክለኛው ጊዜ ብቻ ይገለጥ ዘንድ አሁን የሚከለክለው ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ። 7 የአመጽ ምስጢር በሥራ ላይ ነው፣ ከመንገድ እስኪወገድ ድረስ አሁን የሚከለክለው አንድ ብቻ አለ። 8 ከዚያም ጌታ ኢየሱስ በአፉ እስትንፋስ የሚገድለውና በመምጣቱ መገለጥ የሚያጠፋው የአመጽ ሰው ይገለጣል። 9 የአመጽ ሰው አመጣጥ እንደ ሰይጣን አሰራር በኀይል ሁሉ፣ በምልክቶችና በሐሰተኛ ድንቆች፣ 10 ይድኑ ዘንድ የእውነትን ፍቅር ስላልተቀበሉ ለሚጠፉት በአመጽ ማታለል ሁሉ ነው። 11 በዚህ ምክንያት ሐሰትን ያምኑ ዘንድ እግዚአብሔር የስሕተትን አሠራር ይልክባቸዋል፣ 12 ይኸውም እነዚያ እውነትን ያላመኑ ነገር ግን በአመጻ የተደሰቱ ሁሉ ይፈረድባቸው ዘንድ ነው። 13 ነገር ግን ስለ እናንተ በጌታ ስለተወደዳችሁት ወንድሞች ለእግዚአብሔር ሁልጊዜ ምስጋና ልናቀርብ ይገባናል፣ ምክንያቱም እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ መቀደስና እውነትን በማመን ለድነት እንደ በኩራት መርጧችኋልና፣ 14 የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር እንድትካፈሉ በወንጌላችን ጠራችሁ። 15 እንግዲያውስ ወንድሞች ሆይ፣ ጸንታችሁ ቁሙ፣ በቃልም ሆነ ወይም በደብዳቤአችን የተማራችኋቸውን ልማዶች አጥብቃችሁ ያዙ። 16 አሁን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱና የወደደን፣ የዘላለምን መጽናናትና በጸጋው ተስፋ የምናደርግበትን መልካሙን መታመን የሰጠን እግዚአብሔር አባታችን፣ 17 በቃልና በመልካም ሥራ ሁሉ ልባችሁን ያጽናኑት፣ ያበርቷችሁም።
ነገር ግን፥
ጳውሎስ ይህን ቃል የተጠቀመው የጀመረውን ርዕሰ ጉዳን ለመቀየር ነው፡፡
እንለምናችኋለን
በዚህ ቃል ውስጥ “እኛ” የሚለው የሚያመለክተው፤ ጳውሎስን፣ ስልዋኖስንና ጢሞቲዮስን ነው፡፡አትAT: " እማጸናችኋለው"
እናንተ
“እናንተ” የሚለው ቃል በተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን ያሉ አማኞችን ያመለክታል፡፡
ወንድሞች ሆይ
“ወንድሞች” ማለት ሌሎች አማኞችን ማለት ነው፡፡
.
ከአእምሮአችሁ ቶሎ እንዳትናወጡ እንዳትደነግጡም
AT: "እንዚህ ነገሮች በቀላሉ እንዳያውኳችሁ"
በመንፈስ ወይም በቃል ወይም በመልእክት።
"ከእኛ ዘንድ በወጣ ደብዳቤ ወይም በተነገረ ቃል"
ከእኛ እንደሚመጣ
ሌላ ሰው እንዳደርገው እንደተናገረኝ እንደማለት ነው፡፡
የጌታ ቀን
ይህ ቀን ማለት በእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ላይ ያመጹና መሲሁን ባልተቀበሉ ላይ የመጨረሻው ፍርድ የሚሰጥበት ቀን ማለት ነው፡፡
አያስታችሁ፤ “እናንተ” የሚለው ቃል በተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን ያሉ አማኞችን ያመለክታል፡፡ አይደርስምና "የጌታ ቀን አይመጣምና” የዓመፅ ሰው አትAT: " እና እግዚአብሔር የዓመጽ ሰውን ሳይገልጥ " የጥፋት ልጅ "የሚችለውን ነገር ሁሉ የሚያጠፋ” ወይም “አጥፊ” አምላክ ከተባለው ሁሉ፥ ሰዎችም ከሚያመልኩት ሁሉ አ/ት: "ሰዎች ነው እንደ አምላክ የሚያውቁትና የሚያመልከትን ነገር ሁሉ”(UDB) (ተመልከትSee:
ትዝ አይላችሁምን “እናንተ” የሚለው ቃል በተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን ያሉ አማኞችን ያመለክታል፡፡ አት : "እንደምታሳውሱ እርግጠኛ ነኝ፡፡" ይህን እንዳልኋችሁ ከኢየሱስ ተመልሶ መምጣት ጋር፤ ከጌታ ቀን ጋር፤ እንዲሁም ከዓመጽ ሰው ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ነገሮች የሚያመለክት ነው፡፡ በገዛ ራሱ ጊዜም ይገለጥ ዘንድ፥ አትAT: " እግዚአብሔር የዓመጽን ሰው ጊዜው ሲደርስ ይገልጠዋል፡፡" የዓመፅ ምሥጢር በእግዚአብሔር ብቻ ሊገለጥ የሚችልን የተሰወረን የእምነት ምስጢር ያመለክታል፡፡
ዓመፀኛ ይገለጣል፤ አትAT: "እግዚአብሔ አመጸኛውን ይገልጠዋል" ወይም "እግዚአብሔ ሐሰተኛውን ክርስቶስን ይገልጠዋል" በአፉ መንፈስ የሚያጠፋው፥ "በሚናገረው ቃል ኃይል " ሲመጣም በመገለጡ የሚሽረው ኢየሱስ ተመልሶ በመምጣቱ የዓመጽን ሰው ያጠፋዋል፡፡ የእርሱ መምጣት እንደ ሰይጣን አሠራር ነው። እርሱ የተባለው የዓመጽ ሰው ሲሆን ሲመጣ ሰይጣን የዓመጽን ሰው ስልጣን እንዲኖረው፣ ምልክቶችንና ሐሰተኛ ድንቆች ማድረግ እንዲችል ያደርገዋል፡፡
ስለዚህም ምክንያት፥
"ሰዎች እውነትን ባለመቅደዳቸው ምክንያት”
ሐሰትን ያምኑ ዘንድ እግዚአብሔር የስሕተትን አሠራር ይልክባቸዋል
"እግዚአብሔር የዓመፅን ሰው እንዲያሳስታቸው ላከው
ፍርድን እንዲቀበሉ፥
አትAT: "እግዚአብሔር ይፈርድባቸዋል፡፡”
በእውነት ያላመኑ ነገር ግን በዓመፅ ደስ ይላቸው የነበሩ ሁሉ those who did not believe the truth but took pleasure in unrighteousness
"እውነቱን ባለማመናቸው ምክንያት ዓመፁ ደስ አሰኛቸው፡፡"
ነገር ግን፥ግን ጳውሎስ ይህን ቃል የተጠቀመው የጀመረውን ርዕሰ ጉዳን ለመቀየር ነው፡፡
እግዚአብሔርን ልናመሰግን ግድ አለብን፥ " በተደጋጋሚ ልናመሰግን ይገባል " እኛ በዚህ ቃል ውስጥ “እኛ” የሚለው የሚያመለክተው፤ ጳውሎስን፣ ስልዋኖስንና ጢሞቲዮስን ነው፡፡ እናንተ “እናንተ” የሚለው ቃል በተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን ያሉ አማኞችን ያመለክታል፡፡ በጌታ የተወደዳችሁ ወንድሞች ሆይ፥ AT: "for the Lord loves you, brothers" ወንድሞች ሆይ “ወንድሞች” ማለት ሌሎች አማኞችን ማለት ነው፡፡ ለመዳን እንደ በኵራት መርጦአችኋልና፤ "ከመጀመሪያዎቹ አማኞች መካከል እንድትሆኑ " (UDB) በመንፈስ መቀደስ "እግዚአብሔ የሚያድነንና የሚቀድሰን በመንፈሱ አማካኝነት ነው" (UDB)
እውነትንም በማመን "በእውነት መታመን" ወይም "በአውነት መተማመን " ወግ ያዙ ወግ ወይም ተውፊት የሚያመለክተው ጳውሎስ እና ሌሎች ሐዋሪያት ስለኢየሱስ ክርስቶስ ትክክለኛውን አውነት ያስተማሩትን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "አውነታውን አስታውሱ" የተማራችሁትንyou were taught አት AT: "ያስተማርናችሁን" (UDB) በቃላችንም ቢሆን ወይም በመልእክታችን whether by word or by our letter "በአካል ከእናንተ ጋር ሆነን እንደነገርናችሁ ወይም በደብዳቤያችን እንደጻፍንላችኁ ቃል "
ግን ጳውሎስ ይህን ቃል የተጠቀመው የጀመረውን ርዕሰ ጉዳን ለመቀየር ነው፡፡ የወደደን.. የሰጠን የወደደን እና የሰጠን የሚለው ቃል አማኞችን ሁሉ የሚያመለክት ነው”. ራሱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስና በዚህ ስፍራ “ራሱ” የሚለው ቃል “ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚለው ተጨማሪ መግለጫ ነው፡፡ " ልባችሁን ያጽናኑት “እናንተ” የሚለው ቃል በተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን ያሉ አማኞችን ያመለክታል፡፡. "ያጽናናችሁ እና ያበርታችሁ”
1 በቀረውስ ወንድሞች ሆይ፣ በእናንተ ዘንድ ደግሞ እንደሚሆነው የጌታ ቃል በፍጥነት እንዲዳረስና እንዲከበር ስለ እኛ ጸልዩ፣ 2 ሁሉ እምነት ያላቸው አይደሉምና ከአመጸኞችና ከክፉዎች ሰዎች እንድንድን ጸልዩልን። 3 ነገር ግን የሚያጸናችሁና ከክፉው የሚጠብቃችሁ ጌታ የታመነ ነው። 4 ያዘዝናችሁን ነገሮች እንደጠበቃችሁና ወደፊትም እንደምትጠብቁ ስለ እናንተ በጌታ ታምነናል። 5 ጌታ ልባችሁን ወደ እግዚአብሔር ፍቅርና ወደ ክርስቶስ ጽናት ይምራው። 6 ወንድሞች ሆይ፣ ከእኛ እንደተቀበላችሁት ልማድ ሳይሆን ሥራ በመፍታት ከሚኖር ወንድም ሁሉ ትለዩ ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዛችኋለን። 7 እንዴት ምሳሌነታችንን መከተል እንደሚኖርባችሁ እናንተው ታውቃላችሁ። በመካከላችሁ በስንፍና አልተመላለስንም፣ 8 ወይም ገንዘብ ሳንከፍል የማንንም ምግብ አልበላንም። ከዚያ ይልቅ ከእናንተ በማንም ላይ ሸክም ላለመሆን በድካምና በጥረት ሌሊትና ቀን ሠራን። 9 ይህንን ያደረግነው እኛን ትመስሉ ዘንድ ምሳሌ ልንሆንላችሁ ብለን እንጂ ሥልጣን ስላልነበረን አይደለም። 10 ከእናንተ ጋር በነበርንበት ጊዜ “ሊሠራ የማይወድ ማንም ቢኖር እርሱ መብላት የለበትም” ብለን አዝዘናችሁ ነበር። 11 በመካከላችሁ ሥራ ፈት ሆነው የሚመላለሱ አንዳንዶች መኖራቸውን ሰምተናልና፤ ሥራ አይሠሩም ነገር ግን በሰው ጉዳይ ጣልቃ ይገባሉ። 12 እንደነዚህ ያሉትን በጸጥታ እንዲሠሩና የራሳቸውን ምግብ እንዲበሉ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እናዛቸዋለን እንመክራቸዋለንም። 13 እናንተ ግን ወንድሞች ሆይ፣ ትክክል የሆነውን ከማድረግ አትታክቱ፡፡ 14 በዚህ ደብዳቤ ውስጥ ያለውን ቃላችንን የማይታዘዝ ማንም ቢኖር ይህንን ሰው ልብ በሉት፣ ያፍርም ዘንድ ከእርሱ ጋር ኅብረት አታድርጉ፡፡ 15 እንደ ወንድም ገስጹት እንጂ እንደ ጠላት አትቁጠሩት፡፡ 16 የሰላም ጌታ ራሱ ሁልጊዜ በሁሉ መንገድ ሰላምን ይስጣችሁ። ጌታ ከሁላችሁም ጋር ይሁን። 17 እኔ ጳውሎስ፣ ሰላምታዬ እንዲህ ነው፣ በራሴ እጅ በምጽፋቸው ደብዳቤዎች ሁሉ ላይ ምልክቴ ይህ ነው። 18 የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።
በቀረውስ ጳውሎስ ይህን ቃል የተጠቀመው የጀመረውን ርዕሰ ጉዳን ለመቀየር ነው፡፡ ወንድሞች ሆይ “ወንድሞች” ማለት ሌሎች አማኞችን ማለት ነው፡፡ ስለ እኛ ጸልዩ በዚህ ቃል ውስጥ “እኛ” የሚለው የሚያመለክተው፤ ጳውሎስን፣ ስልዋኖስንና ጢሞቲዮስን ነው እንጂ የተሰሎንቄ አማኞችን አያመላክትም፡፡ የጌታ ቃል እንዲሮጥ "እጅግ በጣም ብዙ ሰዎች ስለጌታ ኢየሱን የሚነገረውን የምስራች መልዕክት እንዲሰሙ" እንዲከበር "ስለጌታ ኢየሱን የሚነገረውን የምስራች መልዕክትን ሰዎች እንዲያከብሩት”
በእናንተም ዘንድ ደግሞ እንደሚሆን… የሚያጸናችሁ “እናንተ” የሚለው ቃል በተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን ያሉ አማኞችን ያመለክታል፡፡. እንድንድን "እግዚአብሔር እንዲያድነን” ወይም “ እግዚአብሔር እንዲታደገን “ እምነትም ለሁሉ ስለማይሆን "ብዙ ሰዎች አማኞች አይደሉም" የሚያጸናችሁ "የሚያበረታችሁ " የሚያጸናችሁ "ያጠነክራችሁ"
ታምነናል በዚህ ቃል ውስጥ “እኛ” የሚለው የሚያመለክተው፤ ጳውሎስን፣ ስልዋኖስንና ጢሞቲዮስን ነው እንጂ የተሰሎንቄ አማኞችን አያመላክትም፡፡ በጌታ "ከጌታ ጋር ተባብረን " (UDB) ስለ "እንደ" እናንተ “እናንተ” የሚለው ቃል በተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን ያሉ አማኞችን ያመለክታል፡፡. ልባችንን ያቅናው "አቅጣጫ ያሳያችሁ “ይምራችሁ”
በቀረውስ ጳውሎስ ይህን ቃል የተጠቀመው የጀመረውን ርዕሰ ጉዳን ለመቀየር ነው፡፡ . በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ። ጳውሎስ በጌታ ስም ማዘዙ ጌታ እንዲያደርግ የፈለገውን ነገር ማድረጉን ያመላክታል . እናዛችኋለን በዚህ ቃል ውስጥ “እኛ” የሚለው የሚያመለክተው፤ ጳውሎስን፣ ስልዋኖስንና ጢሞቲዮስን ነው እንጂ የተሰሎንቄ አማኞችን አያመላክትም፡፡ እናዛችኋለን “እናንተ” የሚለው ቃል በተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን ያሉ አማኞችን ያመለክታል፡፡ ወንድሞች ሆይ “ወንድሞች” ማለት ሌሎች አማኞችን ማለት ነው፡፡ ጌታችን `የኛ” የሚለው ቃል አማኞችን ሁሉ የሚያመለክት ነው”.. ያለ ሥርዓት ከሚሄድ "ሰነፍ እና ለመስራት ፈቃደኛ ያልሆነ " (UDB) እኛን ልትመስሉ "እኛ እንደምናደርገው የምታደርጉ " በድካምና በጥረት እየሠራን ድካም አስቸጋሪ ስራን በብዙ ልፋት መስራትን የሚያመላክት ሲሆን ጥረት ባልተመቻቸ ሁኔታ ውስጥ የሚሰራን ስራ AT: "በብዙ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ስራን ሰርተናል" ሌሊትና ቀን "በሌሊትን በቀን ግዜ” ሁል ግዜ ያለ ሥልጣን ስለ ሆንን አይደለም "በእርግጥ ስልጣን አለን፡፡ "
ጋር ሳለን በዚህ ቃል ውስጥ “እኛ” የሚለው የሚያመለክተው፤ ጳውሎስን፣ ስልዋኖስንና ጢሞቲዮስን ነው እንጂ የተሰሎንቄ አማኞችን አያመላክትም፡፡ ) ከእናንተ “እናንተ” የሚለው ቃል በተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን ያሉ አማኞችን ያመለክታል፡፡. ሊሠራ የማይወድ "መስራት የማይፈልግ ወይም “አንዳንድ ሰነፍ ሰዎች” በጸጥታ እየሠሩ "በእርጋት፤ ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ፤ ሁከት በሌለበት መንገድ”
ግን፥ ጳውሎስ በትጉህ ሰራተኛ አማኞችና በሰንፍ ወይም ሊሰሩ በማይወዱ አማኞች መካከል ንጽጽር ለማድረግ የተጠቀመበት ቃል ነው፡፡ . እናንተ፣ ወንድሞች ሆይ፥ “እናንተ” የሚለው ቃል በተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን ያሉ አማኞችን ያመለክታል፡፡. አትታክቱ። "ተስፋ አትቁረጡ ወይም “የጀመራችሁትን ነገር አታቁሙ”" or "do not stop" ከእርሱ ጋር አትተባበሩ።take note of him "በአደባባይ ለዩት፤ በግልጽ ተለዩት"
ኖት የለውም።
1 መታመኛችን በሆነው በክርስቶስ ኢየሱስ እና በአዳኛችን በእግዚአብሔር ትእዛዝ የክርስቶስ ኢየሱስ ሐዋርያ ጳውሎስ፣ 2 በእምነት እውነታኛ ልጄ ለሆነው፣ ለጢሞቴዎስ፡፡ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችንም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፣ ምሕረትና ሰላም ለአንተ ይሁን፡፡ 3 ወደ መቄዶንያን በሄደኩ ጊዜ አንዳንድ ሰዎች ልዩ ትምህርትን እናዳያስተምሩ፣ 4 በእምነት የሆነውን የእግዚአብሔርን እቅድ ለማያግዙ ለታሪኮችና መጨረሻ የሌላቸውን የትውልዶችን ሐረግ ለመቁጠር ትኩረት ወደ መስጠት እንዳያዘነብሉ ታስጠነቅቃቸው ዘንድ በኤፌሶን እንድትቀመጥ አዘዝኩህ፡፡ 5 ነገር ግን የትእዛዙ ግብ ከንጹህ ልብ፣ ከመልካም ኅሊና እና ከእውነተኛ እምነት የሚወጣ ፍቅር ነ|ው፡፡ 6 አንዳንድ ሰዎች ከእነዚህ ነገሮች ርቀው ወደ ባዶ ወሬ ዞረዋል፡፡ 7 የሕግ አስተማሪዎች ለመሆን ተመኝተዋል፤ ነገር ግን የሚናገሩትንና መሆን አለበት የሚሉትን ነገር አያውቁትም፡፡ 8 ሆኖም ሕግ በትክክል ቢጠቀምበት መልካም እንደሆነ እናወቃለን፡፡ 9 እንዲሁም ሕግ ለጻድቅ ሰው እንዳልተሠራ እናውቃለን፤ ነገር ግን ሕግ የተሰጠው፣ ሕገወጥ ለሆኑና ለአመጸኞች ሰዎች ፣ እግዚአብሔርን ለማይፈሩና ለኃጢአተኞች ፣ 10 ለአመንዝሮችና ለግብረ ሰዶማውያን፣ ሰዎችን ባርያ አድርገው ለሚሸጡ፣ ለውሸተኞች፣ ለሐሰት ምስክሮች፣ ከእውነተኛው ትምህርት ርቀው ለሚገኙ ሰዎች ነው፡፡ 11 ይህ እውነተኛ ትምህርት በተባረከው አምላካችን ለእኔ በአደራ የተሰጠው ወንጌል ነው፡፡ 12 ለዚህ አገልገሎት ታማኝ እንድሆን ያበቃኝንና የሾመኝን፣ ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን አመሰግናለሁ፡፡ 13 ምንም እንኳ አስቀድሞ ተሳዳቢና አሳዳጅ ብሆንም፣ ባለማወቅና ባለማመን ስላደረግሁት ከጌታ ዘንድ ምሕረትን አግኝቼአለሁ፡፡ 14 ነገር ግን የጌታችንም ጸጋ በክርስቶስ ኢየሱስ ከእምነትና ከፍቅር ጋር ይበልጥ በዛ፡፡ 15 ‹‹ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደዚህ ዓለም መጣ›› የሚለው መልዕክት ሁሉም ሊቀበሉት የተገባና አስተማማኝ ነው፡፡ እኔም ከእነዚህ ሁሉ የባስኩ ኃጢአተኛ ነኝ፡፡ 16 በዚህም ምክንያት ከኃጢአተኞች ዋነኛ በምሆን በእኔ ክርስቶስ ኢየሱስ ትእግስቱን ሁሉ ሊያሳይ ምሕረትን አገኘሁ፤ ይህም የሆነው በእርሱ ለሚያምኑና የዘላለም ሕይወት ለሚያገኙ ምሳሌ እሆን ዘንድ ነው፡፡ 17 ስለዚህ ለዘላለም ንጉሥ ፣ ለማይሞተው እና ለማይታየው፣ ብቻውን አምላክ ለሆነው፣ ክብርና ግርማ ለዘላለም ይሁን፡፡ አሜን፡፡ 18 ልጄ ጢሞቴዎስ ሆይ፣ ስለ አንተ አስቀድሞ በተነገረው ትንቢት ተስማምቼ ይህን አዝሃለሁ፤ መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል፤ 19 ስለዚህም እምነትና መልካም ኅሊና ይኑርህ፡፡ አንዳንድ ሰዎች እነዚህን ክደው መርከብ አለመሪ እንደሚጠፋ በእምነት ነገር ጠፍተዋል፡፡ 20 ከእነዚህም መካከል በእግዚአብሔር ላይ የስድብን ቃል እንዳይናገሩ፣ ለሰይጣን አሳልፌ የሰጠኋቸው፣ ሄሜኔዎስ እና እስክንድሮስ ይገኙባቸዋል፡፡
ጳውሎስ "ከጳውሎስ" ወይም "እኔ ጳውሎስl" በትዕዛዙ መሠረት "አንዳዘዘው ትዕዛዝ" ወይም "በልጣኑ መሠረት" እኛ . . . እኛ . . . እኛ በዚህ ሥፍራ ላይ ጳውሎስ ስለ ራሱ፣ ስለ ጢሞቴዎስ እና ምናልባት ሌሎች ሰዎችን ጨምሮ እየተናገረ ይሆናል፡፡ መድኀኒታችን እግዚአብሔር "ያዳነን እግዚአብሔር" ተስፋችን የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ "ተስፋችን የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ" ወይም "የሚንተማመንበት ኢየሱስ ክርስቶስ" ለጢሞቴዎስ "ይህ ደብዳቤ የተጻፈው ለጢሞቴዎስ ነው" እውነተኛ ልጅ ይህ ሀረግ በጳውሎስ እና በጢሞቴዎስ መካከል ያለውን ግንኙነት በአባት እና በልጅ መካከል ካለው ግንኙነት ጋር ያነጻጽራል፡፡ ጢሞቴዎስ የጳውሎስ እውነተኛ የጳውሎስ ልጅ ልጁ ባይሆንም ጢሞቴዎስ ለአባቱ የሚሰጠውን ተመሳሳይ አክብሮትን፣ ትዕዛዝን እና አገልግሎትን ይሰጣል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "እርሱ እንደ እውነተኛ ልጅ ነው" ጸጋ፣ ምሕረት እና ሠላም ከ . . . "ከ . . . ጸጋ፣ ምሕረት እና ሰላም በእናነተ ዘንድ ይሁን" ወይም "መልካምነት፣ ምሕረት እና ሠላም ከ . . . ይሁንላችሁ" እግዚአብሔር አባት "አባታችን የሆነው እግዚአብሔር" ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "ጌታችን የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ጢሞቴዎስ ሕግን በተሳሳተ መንገድ መጠቀመን እነንዲቃወም እና ከእግዚአብሔር መልካም ትምህርት እንዲጠቀም ያበረታታዋል፡፡ እኔ አንተን እንደለመንኩህ "እንተ እንደለመንኩህ" ወይም "በስልጣን እንደተየኩህ" ወይም "እንደነገርኩህ" አንተ ነጠላ ቁጥር በኤፌሶን ቆየህ "በኤፌሶን ከተማ ውስጥ ቆየኸኝ" መጨረሻም ወደሌለው ወደ ትውልዶች ታሪክ እንዳያደምጡ "ወይም ከፍተኛ ትኩረት እንዳይሰጡ" ወይም "እንዳያደምጡ ልታዛቸው" ትውልዶች ታሪክ የትውልድ ሀረግ በአፍ የሚነገር ወይም የተጻፈ ወላጆች እና ዘሮች ዝርዝር ነው፡፡ ይህ በአይዳዊያን ባሕል ውስጥ በጣም ወሳኝ የሆነ ነገር ነው፡፡ ይህ አንድ ሰው በእስራኤል ሕዝብ ውስጥ በዬትኛው ነገድ ውስጥ እንደሆኑ ለማወቅ የሚረዳ በመሆኑ በአይሁድ ባሕል ውስጥ በጣም አስፈላጊ የሆነ ነገር ነው፡፡ ማቴዎስ 1 እና ሉቃስ 3 በጣም ጥሩ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ክርክርን የሚያመጡ "ሰዎች በንዴት ተሞልተው እንዳይስማሙ የሚያደረግ" ሰዎች በእርግጠኝነት ማንም ልያውቃቸው የማይችለውን የተለያዩ ታሪኮችን እና ትውልዶችን ማዕከለ አድርገው ይከራከራሉ፡፡ የእዚአብሔርን ዕቅድ ከመርዳት ይልቅ "የእግዚአብሔርን ዕቅድ እንዲስፋፋ ከማድረግ ይልቅ" ወይም "ከእግዚአብሔር ዘንድ የመጣውን ነገር በአግባቡ ከማስተዳደር ይልቅ" በእምነት "በእመነት በመቀበል" ወይም "በእምነት የተሠራውን ነገር"
የትዕዛዘቱ ግብ "የመመሪያው ግብ" ወይም "እኛ ሐዋርያት እንዲታደርጉት የነገርናችሁ ነገር" ትዕዛዝ ስርዓት፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ቃል ያለው ትርጉም ብሉይ ኪዳን ወይም ዐሥርቱ ትዕዛዛትን አይደሉም ይልቁንም በ1፡3 ላይ ፓውሎስ የሰጠውን ትዕዛዝ የሚያመለክት ነው፡፡ ፍቅር አማራጭ ትርጉም 1) የእግዚአብሔር ፍቅር (UDB) ወይም 2) ከባልንጀራ ያለህ ፍቅር፡፡ ከንጹሕ ፍቅር የተነሣ "ኃጢአት ላለማድረግ ካለ መሻት" መልካም ሕልና "ትክክለኛ ወይም የተሳሳተ ምርጫ የሚያደረግ ሕልና" በእውነት "ታማኝ" ወይም "እውነት" ወይም "ያለምንም ትምክት፡፡" ሕግ በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ቃል የሚያመለክተው የሙሴን ሕግ ነው፡፡ ይሁን እንጂ አልተረዱትም "ምንም አንኳ ባይረዱትም" ወይም "ያልተረዱት ቢሆንም እንኳ" አስረግጠው የሚናገሩት ነገር "በጠንካራ ቃላት የሚናገሩት" ወይም "በእርግጠኝነት የሚናገሩት ነገር" ይሁን እንጂ "አሁን" ሕግ መልካም እንደሆነ እናውቃለን ሕግ ጠቃም እንደሆነ እንረዳለን" ወይም "ሕግ የሚጠቅም ነገር መሆኑን እንገነዘባለን" አንድ ሰው በሕግ ጥቅም ላይ ካዋለው "ምንም በአግባቢ የሚጠቀመው ከሆነ" ወይም "ለተቀመጠለት ዓላማ ማንም የሚጠቀመው ከሆነ"
እናም ይህንን እናውቃለን "ይህንን እንረዳለን" ወይም "ይህንን ስለምንገነዘብ" ወይም "ይህንንም ስለምናውቅ" ለጻድቃን አልተሠራም "ለጻድቅ ሰው አልተሰጠም" ወይም "ለሚታዘዙት ሰዎች አልተሰጠም" ወይም "በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ለሆነ ሰው አልተሰጠም" እናቶቻቸውን እና አባቶቻቸውን ለገደሉት ሰዎች "አባቶቻቸውን እና እናቶቻቸውን ለገደሉ ሰዎች" ወይም "አባታቶቻቸው እና እናቶቻቸው ላይ አካላዊ ጉዳት ያደረሱ ሰዎች ግብረስጋዊ ግንኙነት ግብረገብ የጊደላቸው ሰዎች ይህ በተባአት ጾታ የተገለጸ በሴቶች የሚካሄድ የሴተኛ አደርነትን የሚያሳይ ነው፡፡ በሌለ ሥፍራ ለእግዚአብሔር ታማኝ ያልሆኑ ሰዎችን ለመወከል በምሳሌነት ጥቅም ላይ ውሎ እናገኛለን ነገር ግን በዚህ ክፍል ውስጥ ያለው ትርጉም ከጋብቻ ውጪ ማንም ከሌላ ሰው ጋር ግብረስጋ ግንኙነት የፈጸመን ይወክላል፡፡ ከወንድ ጋርም ለሚተኙ፥ "ከሌላ ወንድ ጋር የሚተኙ ወንዶች፡፡" ባሪያ አድራጊዎች "ሰዎችን እየሠረቁ ባሪያ አድርገው የሚሸጡ" ወይም "ሰዎችን ባሪያ አድርገው የሚሸጡ ሰዎች" የተባረከው የእግዚአብሔር ብሩክ ወንጌል "የተባረከው የእግዚአብሔር የሆነው ስለ ክብር የሆነው ወንጌል" ወይም "ስለ ክብር የሆነው ወንጌል እና የተባረከው አምላክ" ለእኔ አደራ እንደ ተሰጠኝ "እግዚአብሔር የሰጠኝ እና ተጠያቂ ያደረገኝ"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ባለፉት ጊዜያት እንዴት እንደሠራ በመናገር ጢሞቴዎስ ለእግዚአብሔር ታማኝ ይሆን ዘንድ ያበረታታዋል፡፡ እኔ አመሰግናለሁ "አመሰግናለሁ" ወይም "እኔ አመሰግናለሁ" ተማኝ አድርጎ ቆጥሮኛልና "ታማኝ አድርጎ ቆጥሮኝ" ወይም "ታማን እንደሆንኩ ቆጥሮ" በአገለግሎቱ ላይ ሾመኝ "እንዳገለግል ሾመኝ" ወይም "በአገልግሎት ላይ ሾመኝ" እኔን ከዚህ በፊት አሳዳጅ የነበርኩትን "በክርስቶስ ላይ ክፉ ክፉ ነገሮችን የተናገርኩትን ሰው" ወይም "እኔን ባለፉት ዘመናት ተሳዳቢ የነበርኩትን ሰው" አደገኛ ሰው "ሌሎች ሰዎችን የሚጎዳ ሰው፡፡" ይህ ሌሎች ሰዎን የመጉዳት መብት አለኝ ብሎ የሚያምን ሰው ነው፡፡ ነገር ግን ሳላውቅ ባለማመን ስላደረግሁት ምህረትን አገኘሁ፥ አማራጭ ትርጉም: "በኢየሱስ የማላምን በመሆኔ ምክንያት እና የማደርገውን ነገር የማላውቅ በመሆነ ከኢየሱስ ዘንድ ምሕረትን አገኘሁ፡፡" ምሕረትን አገኘሁ አማራጭ ትርጉም: "ኢየሱስ ምሕረት አሳየኝ" ወይም "ኢየሱስ ማረኝ" ነገር ግን ጸጋ "እና ጸጋ" ከእምነትና ከፍቅር ጋር አብልጦ በዛ። "በጣም በዛ" ወይም "ከበቂ በላይ ሆነ"
ይህ መልእክት የታመነ ነው "ይህ ዓረፍተ ነገር እውነት ነው" ሁሉም ሰው ሊቀበለው የተገባ ነው "ያለምንም ጥርጥር መቀበል ይቻላል" ወይም "በሙሉ መተማመን ልቀበሉት የተገባ ነው" በመጀመሪያ ምሕረት ተሰጠኝ "በመጀመሪ እግዚአብሔር ምሕረቱን አሳየኝ" ወይም "በመጀመሪያ ከእግዚብሔር ዘንድ ምሕረትን አገኘሁ" ለዘመናት ንጉሥ የሆነ "ዘላለማዊ ንጉሥ" ወይም 'ለዘላለም ዋና ገዥ የሆነ" ክብር እና ምስጋና "እርሱ ልመሰገን እና ልከበር ይገባዋል" ወይም "ሰዎች ያክብሩት እነንዲሁም ምስጋነናን ያቅርቡለት"
በእናንተ ፊት ይህንን ትዕዛዝ አስምጫለሁ "ይህ እኔ የሰጠኋችሁ ትዕዛዝ" ወይም "ይህ ለእናንተ የሰጠሁት ትዕዛዝ" ልጅ ይህ “ወንድ ልጅ” ወይም “ሴት ልጅ” ከሚለው ቃል ይበልጥ ጠቅለል ያለ ሀሳብን በውስጡ ያዘለ ቃል ነው፡፡ ይሁን እንጂ በዚህኛውም መልኩ ከአባት ጋር ያለን ዝምድና የሚያሳይ ነው፡፡ ጳውሎስ ይህንን ለጢሞቴዎስ ያለውን ፍቅር ለማሳየት በምሳሌነት ተጥቅሞበታል፡፡ መልካም ጦርነት ተዋጋ "የአንተን ጥረት በሚጠይቅ ዋጋ ያለው ጦርነት ውስጥ ተሳትፎ አድርግ" ወይም "ጠላቶችህን ለማሸነፍ ጠንክረህ ሥራ፡፡" ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ያለው ትርጉም “ለጌታ ጠንክረህ ሥራ” (UDB)፡፡
መርከብ አለ መሪ እንደሚጠፋ፥ በእምነት ነገር ጠፍተዋልና፤
ጳውሎስ የእመነት ሁኔታን ከድንጋይ ጋር እንደሚትላተም መረከብ በመመሠል ጽፏል፡፡ የዚህ ምሳሌያዊ ንግግር ትርጉሙ “በእምነታቸው ላይ የሆነ ነገር በጣም መጥፎ ነው” (UDB)፡፡ በእናንተ ቋንቋ ግልጽ ከሆነ ተመሳሳይ ምሳሌን መጠቀም ትችላለህ፡፡ መማር ይችላሉ "እግዚአብሔር ሊያስተምራቸው ይችላል"
1 ስለዚህ ከሁሉ በፊት፣ ጸሎት፣ ምልጃና ምሥጋና ስለ ሰዎቸ ሁሉ እንዲደረግ እመክራለሁ፤ እግዚአብሔርን በመፍራትና በማክበር፣ 2 በጸጥታ ሕይወት ሰላማዊ ኑሮ እንድንኖር፣ ለነገሥታትና በሥልጣን ላይ ላሉ ሁሉ ጸልዩ፡፡ 3 ይህም በአዳኛችን በእግዚአብሔር ፊት መልካምና ተቀባይነት ያለው ነገር ነው፡፡ 4 እርሱ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑና እውነትን ሁሉ ወደ ማውቅ እንዲደርሱ ይፈልጋልና፡፡ 5 አንድ እግዚአብሔር አለና፣ እንዲሁም በሰዎችና በእግዚአብሔር መካከል፣ ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ አንድ መካከለኛ አለ፤ 6 እርሱም ለሁሉ ራሱን ቤዛ አድርጎ የሰጠ፣ በትክክለኛው ጊዜ የተገለጠ ምስክር ነው፡፡ 7 ለዚህም ዓላማ እኔ ራሴ፣ አወጅ ነጋሪና ሐዋርያ ሆኜአለሁ፡፡ እውነትን እናገራለሁ አልዋሽም፤ እኔ ለአሕዛብ የእምነትና የእውነት አስተማሪ ነኝ፡፡ 8 ስለዚህ፣ ወንዶች ሁሉ በየሥፍራው ያለ ጥርጥርና ያለ ቁጣ የተቀደሱ እጆቻቸውን እያነሱ እንዲጸልዩ እፈልጋለሁ፡፡ 9 እንደዚሁም፣ ሴቶች አግባብ ያለው አለባበስ ይኑራቸው፣ ራሳቸውን በመግዛት ረጋ እንዲሉ እንጂ ጸጉራቸውን በወርቅ ወይም በዕንቁ በመሥራት ወይም ውድ የሆኑ ልብሶችን በመልበስ ሊያጌጡ አይገባም፡፡ 10 ነገር ግን እግዚአብሔርን ለሚፈሩ ሴቶች አግባብ እንደሆነው፣ በመልካም ሥራ ተውበው ይታዩ፡፡ 11 ሴት በጸጥታና በመታዘዝ ትማር፡፡ 12 ሴት በጸጥታ እንድትኖር እንጂ፣ እንድታስተምርና በወንድ ላይ ሥልጣን እንዲኖራት አልፈቅድም፡፡ 13 አስቀድሞ አዳም ተፈጥሮአልና፣ ከዚያም ሔዋን፡፡ 14 አዳም አልተታለለም፣ ነገር ግን ሴቲቱ ሙሉ ለሙሉ በመተላለፍ ተታልላለች፡፡ 15 ሆኖም፣ በእምነትና በፍቅር፣ በቅድስናም በመልካም አዕምሮ ጸንታ ብትኖር፣ ልጆችን በመውለድ ትድናለች፡፡
አያየዥ ዓረፍተ ነገር: ጢሞቴዎስ ለሰዎች ሁሉ ይጸልይ ዘንድ ያበረታታዋል፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ "ከሁሉ በበለጠ" ወይም "ከምንም ነገር በፊት" እለምንሃለሁ "እለምንሃለሁ" ወይም "እጠይቅሃለሁ" አክብሮት ሰዎች እኛን የሚያከብሩበት መንገድ፡፡ ይህ ቃል “መለኮትን ከመምሰል” ጋር ተያይዞ ሲመጣ ሰዎች እግዚአብሔርን የሚያከብሩበት እና የሚያመሰግኑበት መንገድ ነው፡፡
በእግዚአብሔር እና በሰው መካከል አንድ መካከለኛ አለ መካከለኛ በሁለት ባልተስማሙ አካላት መካከል የሠላም ድርድር እንዲኖር የሚያደርግ ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ኃጢአተኞች ከእግዚአብሔር ጋር ሠላም እንዲሆኑ ያግዛል፡፡ ራሱን ሰጠ "በፈቃደኝነት ሞተ" ቤዛነት "የነጻነት ዋጋ" ወይም "ነጻነትን ለማግኘት የሚከፍል ዋጋ" ምስክርነት በትክክለኛ ጊዜ "በትክክለኛ ሠዓት የእርሱ ምስክርነት" ወይም "በዚህ ሰዓት የምስክርነት ጊዜ" ለዚህ ዓላማ ሲባል "ለዚህ ሲባል" ወይም "በዚህ ምክንያት ሲባል" ወይም "ለዚህ ምስክርነት ሲባል አዋጅ ነጋሪ ሆንኩ "ሰባኪ ሆኜ ተሾምኩ" ወይም "ሰባኪ ለመሆን በክርስቶስ ተሾምኩ" እውነትን መናገር "እውነትን እናገራለሁ" ወይም "እኔ እውነትን እናገራለሁ" አልዋሽም "እኔ አልዋሽም" በእምነት እና በእውነት "ስለ እምነት እና እውነት" ወይም "ከእምነት እና እውነት ጋር"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ስለ ሴቶች ልዩ የሆነ መመሪያዎችን ሰጥቷል፡፡ በሁሉም ሥፍራ ያሌ ሰዎች "በሁሉም ሥፍራ ያሉ ወንዶች" ወይም "በሁሉም ቦታ ያሉ ወንዶች" ማንሣት "መዘርጋት" ቅዱሳን እጆች "ለእግዚአብሔር የተለዩ እጆች፡፡" ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ኃጢአትን ያስወገደ ሰውን ያመለክታል፡፡ ከቁጣ እና ከመጠራጠር ውጪ "ቁጣን ከመግለጽ ውጪ እና ከሌሎች ጋር ከመጣላት ውጪ" ወይም "በሌሎች ላይ ከመቆጣት እና እግዚአብሔር ከመጠራጠር ውጪ" በትህትና "ለእነርሱ የተሳሳተ ትኩረት የሚሰጥ ምልክት በማያሳይ መልኩ" ወይም "ለሰዎች እና ለእግዚአብሔር ተገቢ ክብር በሚያሳይ መልኩ" በሽሩባ ሳይሆን "ጸጉራቸው ለማስዋብ ከፍተኛ ጥረት ከማድረግ ይልቅ፡፡” working overly hard to make their hair look good." ሽሩባ መሠረት ሴት ልጅ ለጸጉሯ ትኩረት መስጠቷ የሚታይበት አንዱ መንገድ ብቻ ነው፡፡ በመልካም ሥራችን መልካምነቱን መግለጥ "መልካም ነገሮችን በማድረግ የእግዚአብሔር መሆናቸውን ማሳየት"
አንድት ሴት ይህንን ልትማር ይገባታል "ሴት ልጅ ይህንን ትማር" ወይም "ሴት ልጅ ይህንን መማር ይኖርባታል" በዝምታ "በጸጥታ" ወይም "ጸጥ ባለ ባሕርይ" በነገር ሁሉ እየተገዛች "እግዚአብሔር ያዘዘውን ነገር ሁሉ ለመታዘዝ ዝግጁ እየሆነች" አንድት ሴት ይህንን እንድታደረግ አልፈቅደም "ሴት ልጅ ይህንን እንድታደረግ አልፈቅደም"
በመጀመሪያ የተፈጠረው አዳም ነውt "እግዚአብሔር በመጀመሪያ የፈጠረው አዳምን ነው" ወይም "በእግዚአበብሔር በመጀመሪያ የተፈጠረው አዳም ነው" ከዚያ ሔዋን "ከዚያ ሔዋን ተፈጠረች" እንዲሁም የታለለው አዳም አልነበረም "በእባቡ የተታለለው አዳም አልነበረም" በመተላለፍ ፈጽመው ተሳሳቱ "ፈጽሞ በመተለሏ ምክንያት የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ ተላለፉ፡፡" የዚህ ንዑስ ዓረፍተ ነገር ዋና ነጥብ የእግዚአብሔር ሕግ የተላለፈችው ሔዋን እንጂ አዳም አይደለም፡፡ ልጅ በመውለድ ትድናለች "በተለመደው የሕይወት መንገድ ውስጥ እግዚአብሔር ደንነቷን ይጠብቃል፡፡ በዚህ መንገድ የቀጠለ እንደሆነ "በዚያው ከጸኑ" ወይም "በዚያ መንገድ መኖሩ ከቀጠሉ" በእምነትና በፍቅር በቅድስና "በኢየሱስ በማመን እና እርስ በእርስ በመዋደድ እና የቅድስና ሕይወትን በመኖር" ራሳቸውን እየገዙ "ራስን በመግዛት" ወይም "መልካም የሆነውን ነገር በማወቅ"
1 አንድ ሰው መሪነትን ቢፈልግ፣ መልካምን ሥራ ተመኝቶአል፣ የሚለው አባባል የታመነ ነው፡፡ 2 ስለዚህ መሪው ነቀፋ የሌለበት፣ የአንዲት ሚስት ባል፣ በመጠን የሚኖር፣ አስተዋይ፣ ሥርዓት ያለው፣ እንግዳ ተቀባይ፣ ለማስተማር የሚበቃ፣ 3 የማይሰክር፣ የማይጨቃጨቅ፣ ነገር ግን፣ ለሌሎች የሚጠነቀቅ፣ ሰላማዊ፣ ገንዘብን የማያፈቅር መሆን አለበት፡፡ 4 ቤቱን በመልካም የሚያስተዳድርና ልጆቹም በሁሉም ረገድ የሚታዘዙለት ለሆን ይገባል፤ 5 ሰው የራሱን ቤት በመልካም ማስተዳደር የማያውቅ ከሆነ ለእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን እንዴት ሊጠነቀቅ ይችላል? 6 ዲያብሎስ በትእቢት እንደወደቀ እንዳይወድቅ አዲስ አማኝ የቤተ ክርስቲያን መሪ አይሁን፤ 7 በውጭ ባሉት ዘንድ መልካም ምስክርነት ያለው ሊሆን ይገባል፣ በመሆኑም በነቀፋ እና በዲያብሎስ ወጥመድ አይወድቅም፡፡ 8 ዲያቆናትም እንዲሁ፣ የተከበሩ፣ ቃላቸው አንድ የሆነ፣ ብዙ የወይን ጠጅ የማይጠጡ፣ የማይስገበገቡ መሆን አለባቸው፡፡ 9 በንጹህ ኅሊና የተገለጠውን የእምነት እውነት ሊጠብቁ ይገባቸዋል፡፡ 10 አስቀድመው ይገምገሙ፣ ከዚያም ያለነቀፋ ሆነው ከተገኙ በዲቁና አገልግሎት ይሾሙ፡፡ 11 እንዲሁም ሴቶች የተከበሩ፣ የማያሙ፣ ልከኞችና በሁሉ ነገር የታመኑ ሊሆኑ ይገባቸዋል፡፡ 12 ዲያቆናት እያንዳንዳቸው የአንዲት ሚስት ባል መሆን አለባቸው፤ ቤታቸውንና ልጆቻቸውንም በመልካም የሚያስተዳሩ ሊሆኑ ይገባል፡፡ 13 መልካም አገልግሎት የሚያበረክቱ እነርሱ በክርስቶስ ኢየሱስ ባላቸው እምነት ለራሳቸውእውነተኛ መሠረትና ድፍረትን ያገኛሉ፡፡ 14 እነዚህን ነገሮች ስጽፍልህ ወደ አንተ በቅርቡ እንደምመጣ ተስፋ በማድረግ ነው፡፡ 15 ነገር ግን ብዘገይ፣ በእግዚአብሔር ቤት፣ ማለትም የእውነት ዓምድና መሠረት በሆነው፣ በሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን እንዴት መኖር እንደሚገባህ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ፡፡ 16 እኛ ሁላችን በዚህ እንስማማለን፡- ‹‹የተገለጠው እግዚአብሔርን የመምሰል ምስጢር ታላቅ ነው፣›› ይህም በሥጋ የተገለጠው፣ በመንፈስ የጸደቀው፣ በመላእክት የታየው፣ በሕዝቦች መካከል የታወጀው፣ በዓለም የታመነው፣ በክብር ወደ ሰማይ ያረገ ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍ ነገር: ኤጲስ ቆጶስ ቤተ ክርስቲያን እንዴት መጠበቅ እንዳለባቸው እና እንዴት ነገሮችን ማከናወን እንዳለባት ጳውሎስ ልዩ የሆነ መመሪያ ይሰጣል፡፡ መልካም ሥራ "የተከበረ ሥራ" የአንድት ምስት ባል የኤጲስ ቆጶስ አንድ ምስት ብቻ ልኖረው ይገባል፡፡ ይህ ከዚህ ምስቶቻቸው የሞቱባቸው ወይም አግብተው የፈቱ ወይም ፈጽመው አግብተው የማያውቁ ሰዎችን ያካተት ወይም አያካትት የሚታወቅ ነገር የለም፡፡ ልከኛ "በልኩ ነገሮችን የሚያከናውን ሰው" ተቀባይነት ያለው ሰው "ጠበብ ያለውን ነገር የሚያስብ" ወይም "ጥሩ ፍርድ የሚያደርግ ሰው" ወይም "አመክኒዮዊ" ወይም "አመክኒዮ" ሥርዓት ያለው "ጥሩ ባሕርይ ያለው" እንግዳ ተቀባይ "መጻተኞች የሚቀበል" የመጠጥ ሱስ ያሌለበት "ሰካራም ያልሆነ" ወይም "ብዙ ወይን የማይጠጣ ሰው" የማይጨቃጨቅ "መደባደብ እና መከራከር የማይወድ ሰው" ገንዘብ የማይወድ የማይሰርቅ ወይም በቀጥተኛ መንገድ ወይም በማጭበርበር ወይም በትክክለኛ መንገድ ሠርቶ ገንዘብ የሚያገኝ ሰው ነገር ግን ለሰዎች ግድ የማይለው ሰው፡፡
ቤቱን በተገቢው መንገድ ማስተዳደር የሚችል እና ልጆቹም ተገቢውን ክብር የሚሰጧው ሰዎች፡፡ አማራጭ ትርጉሞች 1) ኤጴስ ቆጶስ ልጆቹ የሚታዘዙለት ሊሆን ይገባል እንዲሁም ሌሎች ሰዎችን የሚያከብሩ ልሆኖኑ ያገባል (UDB) ወይም 2) ኤጴስ ቆጶስ በአክብሮት የሚያስተዳድር ልሆን ይገባዋል፡፡ የራሱን ቤት የሚያስተዳድር "ቤተሰቡን የሚንከባከብ" ወይም "በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ ያሉ ሰዎችን በአግባቡ መምራት የሚችል" ከአክብሮት ሁሉ ጋር በዚህ ሥፍራ ላይ “ሁሉ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው “ሁሉንም ሰዎችን” ወይም “በሁሉም ጊዜ” ወይም “በሁሉም ሁኔታዎች ውስጥ”፡፡ አንድ ሰው እንዴት ነገሮችን ማከናወን እንዳለበት የማያውቅ ከሆነ "ምክንያቱም አንድ ሰው እንዴት ማከናውን እንዳለበት የማያውቅ ከሆነ" ወይም "አንድ ሰው ካልቻለ" ወይም "ነገር ግን አንድ ሰው የማችል መሆኑን ከታሰበ" እንዴት ለእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን መጠበቅ ይችላል አማራጭ ትርጉም: "የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን እንዴት መጠበቅ ይችላል" ወይም "የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን መምራት አይችልም"
አዲስ አማኝ ይሁን "አዲስ አማኝ ሊሆን አይገባም" ወይም "አማኝ ከሆነ ብዙ ጊዜ ያልሆነ ሰው መሆን የለበትም" ወይም "የበሰለ አማኝ ልሆን ይባዋል" በትዕቢት ተነፍቶ በዲያብሎስ ፍርድ እንዳይወድቅ፥ "እንደ ዳቢሎስ በትዕቢት ተሞልቶ እና እንደ ዳቢሎስ እንዳይፈረድበት" በውጪ ባሉት ዘንድ በጥሩ ምግባሩ የሚታወቅ ሊሆን ይገባዋል "በኢየሱስ የማያምኑ ሰዎች በጎነቱን የሚመሰክሩለት ሰው" ወይም "ከኢየሱስ የማያምኑ ሰዎች በጎነቱን የሚናገሩለት ሰው" (UDB) ከጸጋ እንዳይወድቅ "በራሱ ላይ ውርደትን እንዳያመጣ" ወይም "በእርሱ ላይ እንከን የሚፈልጉ ሰዎች ምንም ምክንያት ማግኘት እንዳይችሉ" እንዳይወድቅ ...በዳብሎሽ ወጥመድ ተጠልፎ "ዳብሎስ ጠልፎ እንዲጥላቸው እንዳይፈቅድላቸው፡፡" ሴጣን ወጥመድን አዘጋጅቷል ወይም መጥመድ ሴጣን አማኞችን ሳያውቁ ኃጢአት እንዲያደርጉ የማታለያ መንገዱን ለማሳየት ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: የቤተ ክርስቲያን ዲያቆናት እና ምስቶቻቸው ምን ማድረግ እንዳለባቸው ጳውሎስ ልዩ የሆነ መመሪያዎቹን መስጠቱን ቀጠሏል፡፡ በተመሳሳይ መልኩም ዲያቆናት "ልክ እንደ ኤጵስ ቆጶሳት ሁሉ ዲያቆናትም" የተከበሩ ሊሆኑ ይገባል "በሰዎች ዘንድ የተከበሩ ሊሆኑ ይገባል" ሁለት አፍ ያላቸው መሆን የለባቸውም ሁለት አፍ የመሚናገሩ - "አንድ ነገር እየተናገሩ በሌላ በኩል ደግሞ ሌላ የሚሉ" ወይም "ለአንዱ ሰው አንድ ነገር ሌላ ሰው ደግሞ ሌላ የሚናገሩ"
ብዙ ወይን ጠጅ የማጠጡ "ወይን የመጠጣት ሱስ ያሌለባቸው" ወይም "ብዙ የወይን ጠጅ የማይጠጡ" ስስታሞች ያልሆኑ "ታማኝነትን በማጉደል ትርፍን የማይፈልጉ" የተገለጠውን የእምነት እውነት ልጠብቁ ይገባል "እግዚአብሔርን ለእኛ የገለጠውን እና እኛም የምናምነውም እውነተኛውን መልዕክት በማመን የሚቀጥሉ ሊሆን ይገባል፡፡" ይህ ለተወሰነ ጊዜ ያለ እውነት ሲሆን ይህንን እውነት እግዚእሔት ለእርሱ አሳይቶዋቸዋል፡፡ በንጹሕ ሕልና "ስህተት አለማድረጋቸው በሚያውቅ ሕልና" ይህንን ማድረግ አለባቸው ...በመጀመሪያ የተፈቀደላቸው "ለአገልግሎቱ ብቁ መሆናቸውን ለማረጋገጥ መገምገም ይኖርባቸዋል" ወይም "በመጀመሪያ ብቁ መሆኑን ማሳየት ነው፡፡" ያለነቀፋ ያልሆነ "ሰዎች ምንም ስህተት የማያገኙባው በመሆናቸው ምክንያት" ወይ "ያለነቀፋ በመሆናቸው ምክንት" ወይም "ምንም ስህተት ባለመስራታቸው ምክንያት"
ሴቶችም በተመሳሳይ መልኩ በዚህ ሥፍራ ላይ “ሴቶች” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አጠቃላይ ሴቶችን ቢሆንም በተለይ ግን የዲያቆናት ምስተፐች ወይም ሴት ዲያቆናትን የሚያመለክት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "በተመሳሳይ መልኩም ምስቶችም መሥፈረት አላቸው" ወይም "ሴት ዲያቆናትም እንደ ወንድ ዲያቆናት መሥረት አላቸው፡፡" ትክክለኛ ባሕርይ "በትክክል መፈጸም" የማይሳደቡ "ስለ ሌሎች ሰዎች ክፉ የሆነ ነገር የማይናገሩ" ልከኞች "ከመጠን በላይ የሆነ ነገርን የማደርጉ" የአንድ ምስት ባል የአንድ ምስ ባል፡፡ ይህ ምስት የሞተባቸውን፣ የተፋቱ ወይም ፈጽሞ ያለገቡ ወንዶችን ያመልክት አያመልክት ምንም የሚታወቅ ነገር የለም፡፡ ልጆቻቸውን እና ቤታቸውን በአግባቡ ማስተዳደር የሚችል "ልጆቻቸውን እና በቤታቸው ውስጥ ያሉትን ሌሎች ሰዎችን መንካከብ እና መመራት የሚችሉ፡፡" እንዲህ ያሉ ሰዎች "እንዲህ ያሉ ሰዎች" ወይም "ኤጴስ ቆጶሶች፣ ዲያቆናት እና ሴት ዲቆናት” ወይም "የቤተ ክርስቲያን መሪ የሆኑ ሰዎች" ለራሳቸው የያገኛሉ "ለራሳቸው ይቀበላሉ" ወይም "ለራሳቸው ያተርፋሉ"
እነዚህን ነገሮች ጽፌልሃለሁ "እነዚህም መመሪያዎችን ጽፌልሃለሁ" ወደ እናንት በቶሎ እመጣ ዘንድ ተስፋ አደርጋለሁ "ምንም እንኳ ወደ እናንተ በቶሎ እንድመጣ ተስፋ ባደርግም" ነገር ግን ከዘገየሁ "ይሁን እንጂ በቶሎ መምጣት ካልቻልኩኝ" ወይም "ይሁን እንጂ ወደ እናንተ ዘንድ በቶሎ እንዳልመጣ የተከለከልኩ እንደሆነ" . . . ዘንድ እጽፍልሃለሁ፡፡ "ለዚህ ዓላማ እጽፍልሃለሁ፡፡" የእግዚአብሔር ቤት...በዚህ ልመራ ይገባዋል "የእግዚአብሔርን ቤተሰብ በዚህ መሠረት ልትመራው ይገባል" በእውነት ዓምድና መሠረት ይህ ምሳሌያዊ ንግግር እግዚአብሔር እውነቱን የገለጸበት ትልቅ፣ ጠንከራ መሠረትን ያሳያል፡፡ ይህ መሠረት የተለያዩ ክፍሎች፣ መሠረት እና ዓምድ አለው፡፡
በሥጋ "እንደ እውነተኛ የሰው ልጅ" እግዚአብሔርን የመምሰል ምስጥር ያለጥርጥር ታልቅ ነው "ስለ እምነታችን እግዚአብሔር የገለጠልን እውነት ትልቅ ነው" በመንፈስ የጸደቀ "ኢየሱስ ስለ ራሱ ማንነት የተናገረውን ነገር መንፈስ ቅዱስ አረጋግጧል" በአሕዛብ ሁሉ ዘንድ የተሰበከ "በተለያዩ ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ሰዎች ለሌሎች ሰዎች ስለ ኢየሱስ ተናግረዋል" በዓለም ሁሉ የታመነ "በዓለማችን የተለያዩ ክፍሎች ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች በኢየሱስ አምነዋል"
1 አሁን ግን መንፈስ በመጨረሻ ዘመን አንዳንድ ሰዎች የራሳቸውን ኅሊና በውሸት በተሞላ ግብዝነት በማደንዘዝ፤ 2 ለሚያስቱ መናፍስትና ለአጋንንት ትምህርት ትኩረት በመስጠት እምነትን ይክዳሉ በማለት በግልፅ ይናገራል፡፡ 3 እውነትን ለማወቅ የመጡትን አማኞች ከምሥጋና ጋር ከሚቀበሉትና እርስበርሳቸው ከሚካፈሉት እግዚአብሔር ከፈጠረው ምግብ እንዲርቁ፣ ጋብቻንም እንዳያደርጉ ይከለክላሉ፡፡ 4 በእግዚአብሔር የተፈጠረው ሁሉ መልካም ነውና፤ በምሥጋና የሚቀበሉት እንጂ የሚጣል የለውም፡፡ 5 በእግዚአብሔር ቃልና በጸሎት የተቀደሰ ነው። 6 እነዚህን ነገሮች ለወንድሞች ብታስረዳ፣ በእምነት ቃሎች እና በተከተልከውም መልካም ትምህርት የምትመገብ የኢየሱስ ክርስቶስ መልካም አገልጋይ ትሆናለህ፡፡ 7 ራስህን እግዚአብሔርን ለመምሰል አሰልጥን እንጂ፣ አሮጊቶች የሚወዱአቸውን አለማዊ ተረቶችን አትቀበል፡፡ 8 የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለጥቂት ነገር ይጠቅማል፣ ነገር ግን እግዚአብሔርን መምሰል ለአሁኑና ለሚመጣውም ሕይወት ተስፋ ስላለው ለሁሉ ነገር ይጠቅማል፡፡ 9 ይህ መልእክት የታመነና ሁሉም ሊቀበሉት የተገባው ነው፡፡ 10 ለዚህም እንታገላለን ጠንክረንም እንሠራለን፣ ይህም የሚሆነው ሰዎችን ሁሉ በተለይም የሚያምኑትን በሚያድን በሕያው እግዚአብሔር ስለምንታመን ነው፡፡ 11 እነዚህን ነገሮች አውጅ አስተምርም፡፡ 12 ማንም ወጣትነትህን አይናቀው፣ ነገር ግን በዚህ ፈንታ፣ በቃልና በሥራ፣ በፍቅር፣ በእምነትና በንጽሕና የእምነት ምሳሌ ሁን፡፡ 13 እስክመጣ ድረስ፣ ማንበብህን፣ መምከርህን እና ማስተማርህን ቀጥል፡፡ 14 በትንቢት ከሽማግሌዎች የእጅ መጫን ጋር ለአንተ የተሰጠህን የጸጋ ስጦታ ቸል አትበል፡፡ 15 ለእነዚሀ ነገሮች ተጠንቀቅ፣ በእነርሱም ጽና፣ ይህን በማድረግህ ማደግህ በሁሉም ዘንድ ይገለጻል፡፡ 16 ለራስህ እና ለትምህርቱ ተጠንቀቅ፣ በእነዚህም ጽና ይህን ብታደርግ ራስህንም የሚሰሙህንም ታድናለህ፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ መንፈስ እንደሚሆን የነገረውን ነገር እያስታወቀው ምን ምን ነገሮችን ማስተማር እንዳለበት በመናገር ያበረታታዋል፡፡ በኋላኛው ዘመን አማራጭ ትርጉሞች 1) ከጳውሎስ ዘመን በኋላ፣ "ለወደፊት" ወይም "በቀጣዩ ዘመን" ወይም 2) በጳውሎስ ዘመን "ከመጨረሻው በፊት ባለው ጊዜ ውስጥ" እምነት መተው "በኢየሱስ ማመን መተው" ወይም "አስቀድመው ከሚያምኑት ነገር መራቅ" እና ትኩረት መስጠት "እና ትኩረት መስጠት" ወይም "ትኩረት በመስጠታቸው ምክንያት" ወይም "ስያደምጡ ሳለ" አሳሳች መንፈስ እና የዳቢሎስ ትምህርቶች "ሰዎችን የሚያሳሰስት ትምህርት እና ዳቢሎስ የሚያስተምረው ትምህርት" በግብዝነት ውሸት "በግብዞች አማካኝነት በሚነገር ውሸት" በገዛ ሕሊናቸው እንደሚቃጠሉ ደንዝዘው፥ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር የሚያሳየው አንድ ጌታ በባሪያዎቹ ወይም እንስሳቶቹ ቆዳ ላይ የእርሱ ባለቤትነት የሚያሳይ ምልክት በጋለ ብረት የሚየስቀምጥበት መንገድ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉሞች 1) ማቃጠል የመለያ ምልክት ነው፣ "ግብዞች እንደሆኑ እያወቁ እንኳ ይህንን ያደርጋሉ፣" ወይም 2) ሕልናቸው ደንዝዟ፣ "ሕልናቸው እንድደነዝዝ በጋለ ብረት የተሰጠበሰ ይመስል፡፡"
ይህንን ያደርጋሉ "እነዚህ ሰዎች ይህንን ያደርጋሉ" መጋባትን ይከለክላሉ "አማኞች እንዳገቡ ይከለክላሉ" ወይም "አማኞች እንዳያገቡ ይከለክላሉ" ይከለክላሉ . . . ምግብ መቀበልን "ሰዎች ከምግብ ይርቁ ዘንድ ግድ ይላሉ" ወይም "ሰዎች ምግብ እንዳይበሉ ግድ ይላሉ" ወይም "ሰዎች የተወሰነ ዓይነት ምግብ እንዳይበሉ ይከለክላሊ፡፡" በዚህ ሥፍራ ላይ "ሰዎች" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ምናልባት አማኞችን ነው (UDB)፡፡ እውነት ለማወቅ የሚመጡ አማኞች "እውነት የሚያውቁ አማኞች" ወይም "እውነትን ያወቁ አማኞች" ከምስጋና ጋር ይቀበሉ ዘንድ እግዚአብሔር ከፈጠረው መብል እንዲርቁ ያዝዛሉ። "እግዚአብሔርን ያመሰገንበትን ነገር አውጥተን አንጥልም" ወይም "በማመስገን የሚንበላው ማንኛውም ነገር የተመሰገነ ነው" በእግዚአብሔር ቃል እና ጸሎት ለእግዚአብሔር የተሰጠ ነው አማራጭ ትርጉም: "ለእግዚአብሔር ቃል በመታዘዝ እና ወደ እርሱ በመጸለይ ለእግዚአብሔር የተሰጠ ነው" ወይም "በተገለጠው የእግዚአብሔር እውነት ጋር የሚስማማ ከሆነ በጸሎት ለእግዚአብሔር የተሰጠ ይሆናል፡፡
ይህንን ነገር በ. . . ፊት አኑሩት "ይህንን ሀሳብ በአማኞች አእምሮ ውስጥ አስቀምጡት" ወይም "አማኞች እነዚህ ቃላት ያስታውሱ ዘንድ አግዟቸው፡፡" ሁሉም “የማስተማር” ሁደት እና “ቃል” በ 1TI 3:16 እስከ 1TI 4:5. ላይ የተጠቀሰውን ትምህርት የሚያመለክቱ ናቸው፡፡ ተገቢውን ምግብ ማግኘት "መሰልጠን" (UDB)፡፡ እግዚአብሔር ጢሞቴዎስ ይበልጥ ጠንካራ እንዲሆን አድርጎታል እንዲሁም እግዚአብሔርን የሚያስደስት ነገር እንዲያደርግ አስተምሮታል፡፡ የእምነት ቃላት "ሰዎች እንዲያምኑ የሚያደርጉ ቃላት" በአሮጊት ሴቶች የሚወደዱ ተራ ታሪኮች "ተራ የሆነ እና የአሮጊት ሴቶች ተረት ተረተ፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ “ታሪኮች” የሚለው ቃል በ [1TI 1:4] እግዚአብሔርን ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ። "ይበልጥ እግዚአብሔርን ለመምሰል ራሳችሁን አስለምዱ" ወይም "እግዚአብሔር በሚያስደስት መልኩ ነገሮችን ለማከናወን ራስህን አስለምድ" ወይም "እግዚአብሔርን መምሰልን ይበልጥ ራስግን አስለምድ" አካላዊ ለምምድ "አካላዊ ልምምድ" ለዚህ ሕይወት የሆነው ተስፋ ያዝ "ለዚህ ሕይወት ጠቃሚ ነው" ወይም "ይህንን ሕይወት የተሻለ ለማድረግ አጋዥ ነው"
worth full acceptance "worthy of your complete belief" or "worthy of your full trust" ስለዚህ ምክንያት "ምክንያቱ ይህ ነው" እንታገላለን እንዲሁም ተግተን እንሠራለን በዚህ ሥፍራ ጥቅም ላይ የዋሉት “መታገል” እና “ተግቶ መሥራት” የሚሉት ቃላት በመሠረታዊ ትርጉማቸው ተመሳሳይ ናቸው፡፡ እነዚህ ቃላት ጳውሎስ በአንድነት የተጠቀማቸው ምን ያህል ተግተው በመስሥራት ላይ እንዳሉ ለማሳየት ነው፡፡ ሕያው በሆነ አምላክ ተስፋ ስለምናደረግ "ተስፋችንን በሕያው እግዚአብሔር ላይ እናደርጋለን" ወይም "ተስፋችንን በሕያው አምላክ ላይ እናደርጋለን" ነገር ግን በተለይም ለአማኞች "በተለይ ደግሞ አማኞች ለሆኑ ሰዎች እርሱ አዳኛቸው ነው"
እነዚህ ነገሮች ስበከት እንዲሁም አስተምር "እነዚህን ነገሮች እዘዝ እንዲሁም አስተምር" ወይም "አሁን የነገርኩን ነገሮች እዘዝነ እንዲሁም አስተምር" ወጣት በመሆንን ምክንያት ማንም ሰው እንዳይንቅህ "ወጣት በመሆን ምክንያት ማንም ይህንን ያኸል ጠቃሚ አይደለም ብሎ እንዳያስብህ" ተግተህ አንብብ "ቅዱሳት መጻሕፍትን አንብብ" ወይም "በአደባባይ የእግዚአብሔር ቃል ማንበብህን ቀጥልበት" ሌሎችን አበረታታ "ሌሎች ሰዎች አበረታታ" ወይም "ሌሎች ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል በሕይወታቸው ተግባራዊ ያደርጉት ዘንድ አበረታታ"
በአንተ ውስጥ ያለውን ስጦታ ቸል አትበለው "እግዚአብሔር የሰጠህን ስጦታ ተጠቀምበት" በትንቢት "የቤተ ክርስቲን መሪዎች የእግዚአብሔር ቃል በመናገር" ሽማግሌዎች እጃቸውን በመጫን ይህ የቤተ ክርስቲን መሪዎች እጆቻቸውን በጢሞቴዎስ ላይ በማድረግ እግዚአብሔር እንድሠራው ያዘዘውን ሥራ ማከናውን ይችል ዘንድ የጸለዩበት ሃይማኖታዊ ሥርዓት ነው፡፡ ስለእነዚህ ነገሮች አስብ፣ ኑራቸውም "እነዚህን ነገሮች ሁሉ አድርግ እንዲሁም በእነዚህም መሠረት ኑር" እድገተህ በሰዎች ሁሉ ዘንድ የተገለጠ ይሆን ዘንድ "ሌሎች ሰዎች እድገትህን መመልከት ይችሉ ዘንድ" ወይም "እነዚህ ነገሮች በማድረግ ያሳየኸውን እምርታ ሌሎች ሰዎች መመልከት ይችሉ ዘንድ" ስለራሰህ ከፍተኛ ትኩረት ስጥ "በጥንቃቄ ነገሮችን አከናውን" ወይም "ባሕርይህን ተቆጣጠር" በእነዚህ ነገሮች ቀጥል "እነዚህ ነገሮችን ማድረግህን ቀጥልበት" ራስህን እና የሚያደምጡህን ታድናለህ "ራስህን እና የሚያደምጡህን ሰዎች የሐሰት መልዕክት ከመስማት እና የተሳሳተ ተግባር ከማድረግ ታድናለህ፡፡" የሐሰት መልዕክት የሚያምኑ ሰዎች እና የተሳሳተ ተግባር የሚፈጽሙ ሳች በዚህ ምክንያት መከራ ይደርስባቸዋል፡፡ ጳውሎስ ጢሞቴዎስ እና የእርሱ ወዳጆች የስህተት ትምህርት በማመን እና የተሳሳተ ነገር በማድረግ መከራ እንዲያገኛቸው አይፈልግም፡፡
1 ሽማግሌ የሆነውን አትገስጸው፣ ነገር ግን እንደ አባት ለምነው፣ ወጣቶችን እንደ ወንድሞች፣ 2 አሮጊቶችን እንደ እናቶች፣ ቆነጃጅቶችን እንደ እኅቶች በሙሉ ንጽሕና ለምናቸው፡፡ 3 በትክክል መበለት የሆኑትን አክብር፤ 4 ነገር ግን ባሏ የሞተባት ልጆችና የልጅ ልጆች ከሏት፣ እነርሱ ራሳቸው በቤታቸው አክብሮትን፣ ለወላጆቻቸው ብድራት መክፈልን ይማሩ፣ ይህ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ነገር ነው፡፡ 5 ነገር ግን እውነተኛ መበለት ሁሉን ነገር ትታ በእግዚአብሔር ታምና ትኖራለች፣ ልመናዋን ሁል ጊዜ በእርሱ ፊት በማቅረብ ሌትና ቀን ትጠባበቃለች፡፡ 6 የሆነ ሆኖ፣ መቀማጠልን የምትወድ ሴት በሕይወትም ብትኖር የሞተች ነች፡፡ 7 ከወቀሳ የራቁ እንዲሆኑ እነዚህን ነገሮች ስበክ፡፡ 8 ነገር ግን ማንም ለዘመዶቹ የሚያስፈልጋቸውን የማይሰጥ፣ ይልቁንም ለገዛ ቤተሰቡ የማያስብ እምነትን የካደ ከማያምን ሰው ይልቅ የከፋ ነው፡፡ 9 ባሏ የሞተባት ሴት በመዝገብ ለመጻፍ እድሜዋ ከስድሳ ማነስ የለበትም፣ የአንድ ባል ሚስትም መሆን አለባት፡፡ 10 ልጆቿን በሥርዓት የምታሳድግ፣ እንግዶችን የምትቀበል፣ ወይም የቅዱሳንን እግር በማጠብ፣ የተጨነቁትንም በማጽናናት፣ በመልካም ሥራ ሁሉ የተመሰከረላት መሆን አለባት፡፡ 11 ወጣት መበለቶችን ግን እንደ መበለት አትመዝግባቸው፣ ምክንያቱም የክርስቶስ ተቃራኒ የሆነው ሥጋዊ ፍላጎታቸው ሲያይልባቸው ለማግባት ይፈልጋሉና፡፡ 12 በዚህ ሁኔታ የቀድሞ እምነታቸውን ስለተዉ በደለኞች ናቸው፡፡ 13 ለሥራ ፈትነትም ስለሚጋለጡ ከቤት ወደ በት የሚዞሩ ይሆናሉ፡፡ ሥራ ፈቶች መሆናቸው ብቻ ሳይሆን ሐሜተኞችና በሰው ጉዳይ ጣልቃ እየገቡ የማይገባውን የሚናገሩ ይሆናሉ፡፡ 14 ስለዚህ ወጣት ሴቶች እንዲያገቡ እና ልጆችን እንዲወልዱ ቤታቸውንም በመልካም እንዲያስተዳድሩ፣ ተቃዋሚውም ክፉ እንደምናደርግ የሚከስበትን ምክንያት እንዲያሳጡት እመክራለሁ፡፡ 15 አንዳንዶች ሰይጣንን ለመከተል ዞር ብለዋል፡፡ 16 መበለቶች ያሏት አንዲት የምታምን ሴት ብትኖር፣ ትርዳቸው፣ ስለሆነም የቤተ ክርስቲያን ሸክም ይቀልላታል እውነተኞቹን መበለቶች ለመርዳት ትችላለች፡፡ 17 በመልካም የሚያስተዳድሩ መሪዎች በተለይም በቃሉ ስብከትና በማስተማር የሚተጉ እጥፍ ክብር ይገባቸዋል፡፡ 18 የእግዚአብሔር ቃል ‹‹የሚያበራየውን በሬ አፉን አትሰር›› እንዲሁም ‹‹ለሠራተኛ ደመወዙ ይገባዋል›› ይላል፡፡ 19 ሁለት ወይም ሦስት ምስክሮች ሳታገኝ በሽማግሌ ላይ ክስ አትቀበል፡፡ 20 ሁሉም ይማሩ ዘንድ አጥፊዎችን በሁሉ ፊት ገስጻሳቸው፡፡ 21 በእግዚአብሔር ፊት፣ በክርስቶስ ኢየሱስ ፊት፣ በተመረጡትም መላእክት ፊት አዝዝሃለሁ፣ አንዳች አድልኦ ሳታደርግ እነዚህን ደንቦች ጠብቅ፡፡ 22 በማንም ላይ ቸኩለህ እጅህን አትጫን፣ ከማንም ኃጢአት ጋር አትተባበር፣ ርስህን በንጽሕና መጠበቅ አለብህ፡፡ 23 በተደጋጋሚ ሆድህን ስለሚያምህ ጥቂት የወይን ጠጅ ጠጣ እንጂ ለወደፊቱ ውኃ ብቻ አትጠጣ፡፡ 24 የአንዳንድ ሰዎች ኃጢአት በግልጽ የታወቀ ነው፣ ፍርድን ያስከትልባቸዋል፣ አንዳንዶች ግን ኋላ ይከተሉታል፡፡ 25 ልክ እንደዚሁ አንዳንድ መልካም ሥራዎች የተገለጡ ናቸው፣ ነገር ግን ሌሎቹ በጊዜው የተገለጡ ባይሆንም እንኳ የተሰወሩ አይደሉም፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉ ወንዶችን፣ ሴቶችን፣ መበልቶች እና ወጣት ሴቶችን በምን ዓይነት መንገድ ማስተናገድ እንዳለባት መናገሩን ቀጥሏል፡፡ አጠቃላይ መረጃ: ጳውሎስ እነዚህ ትዕዛዛት የሰጠው ጢሞቴዎስ ለተባለ አንድ ሰው ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ “አንተ” የሚለው ቃል የተገለጸው በነጠላ ቁጥር ነው፡፤ ሽማግሌውን አትገስጸው "በሽማግሌ ላይ ጠንከር ያለ ቃል አትናገር" ይሁን እንጂ አባት እንደሚሆን ቆጥረህ አበረታታ "ነገር ግን አባትህ ሊሆን እንደሚችል በማሰብ አበረታታው" ከአክብሮት ጋር ወጣት ወንዶችንም ወንድሞችህ እንደሚሆኑ በማሰብ አበረታታቸው "ወጣት ወንዶችንም ወንድሞችህ ሊሆኑ እንደሚችሉ በማሰብ አበረታታቸው" ወይም "ወጣት ወንዶችን ልክ ወንድምህን በሚትንከባከብበት መንገድ ተንከባከባቸው፣" በሰላማዊ መንገድ፡፡ አሮጊት ሴቶችን እንደ እናት አበረታቷቸው "አሮጊት ሴቶችን ልክ እንደ እንናታችሁ ተንከቧከቧቸው" ወይም "አሮጊት ሴቶችን ልጅ እንደ እናራችሁ ተንከቧከቧቸው" ወጣት ሴቶችን ልጅ እንደ እህታችሁ "ወጣት ሴቶችን ልክ እህቶቻችሁን በምትቀርቡበት መንገድ ቅረቧቸው" ወይም "ለወጣት ሴቶችን ልክ ለእህቶቻችሁን የሚታደርጉትን እንክብካቤ አድርጉላቸው" በንጽሕና ሁሉ "በንጹህ ሀሳቦች እና ተግባራት" ወይም "በቅዱስ መንገድ"
ክብር "አክብሯቸው እንዲሁም አስፈላጊውን ነገር ስጧቸው" ባልቴቶች፣ እውነተኛ ባልቴቶች "ባልቴቶች፣ በእርግጥም ባልቴት ለሆኑ" ወይም "ባልቴቶች፣ ማንም የሚያስፈልጋቸው የማያቀርብላቸው ባልቴቶች" ነገር ግን አንድት ባልቴት "ይሁን እንጂ ባልቴቷ" ልጆች "የእርሷ ልጆችን የሚሆኑ ካሏት" ወይም "እናቴ ብለው የሚጠሯት ልጆች ካሏት" የልጅ ልጆች "የእርሷ የልጅ ልጅ ናቸው የሚትላቸው ካሏት" ወይም "እናቴ ወይም አያቴ ብለው የሚጠሯት ካላት" በመጀመሪያ ለእነርሱ ፍቀዱላቸው በመጀመሪያ ደረጃ እነርሱ . . . ማድረግ ይኖርባቸዋል" ወይም "እነርሱ . . . ለማደረግ ቅድሚያ መስጠት ይኖርባቸዋል" አክብሮትን መስጠትን ተማር "ሃይማኖተኛ መሆናቸው ይታይ" ወይም "እግዚአብሔር መምሰላቸው ያሳዩ" ወይም "ሃይማኖታቸውን ያሳዩ" ወይም "ኃላፊነታቸውን መወጣትን ይለማመዱ" በገዛ ቤታቸው ውስጥ "ለራሳቸው ቤተሰብ" ወይም "በቤታቸው ውስጥ ለሚኖሩት ሰዎች" እንዲሁም ለወላጆቻቸው ብድራታቸውን ይክፈሉ "ለወላጆቻቸው መልሰው መክፈል ይችሉ ዘንድ" ወይም "ወላጆቻቸው በሰጧቸው መልካም ነገሮች ፈንታ እነርሱ ለወላጆቻቸው መልካም ነገርን ማድረግ ይችሉ ዘንድ" ምክንያቱ ይህ እግዚአብሔርን የሚያስደስት ነው "እነዚህ ነገሮች ስያደርጉ እግዚአብሔር በዚህ ደስ ይለዋል" ወይም "ይህ የማክበር ተግባር እግዚአብሔርን የሚስደስት ነው"
ይሁን እንጂ እውነተኛዋ በልታቴ ማንም የላትም
"ይሁን እንጂ እውነተኛ ባልቴት የሆነች ሴት የሚያግዛት ቤተሰብ የላትም"
ሁል ጊዜ በጥያቄ እና በጸሎት በእርሱ ፊት ትቀርባለች
"በእግዚአብሔር ፊት ጥያቄዎቿን እና ጸሎቶቿን ይዛ ዘወትር ትቀርባለች"
ጥያቄዎቿን እና ጸሎቷን
እነዚህ ሁለት ቃላት ትርጉማቸው በመሠረቱ ተመሳሳይ ነው፡፡ እነዚህ ቃላት ጳውሎስ በዚህ ሥፍራ ላይ የተጠቀማቸው ባልቴቷ ምን ያህል እንደሚትጸልይ አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡
ቀን እና ሌሊት
አማራጭ ትርጉም፡ “ሁል ጊዜ”፡፡
ይሁን እንጂ
"ነገር ግን"
ሞተ
የዚህ ምሳሌያዊ ንግግር ትርጉሙ ለእግዚአብሔር መልስ ለመስጠት አትችልም የሚል ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ልክ እንደ ሞተ ሰው ለእግዚአብሔር መልስ አትሰጥም፡፡
ሕያው
ይህ ሥጋዊ ሕይወትን ያመለክታል፡፡
እንዲሁም እነዚህን ነገሮች ስበክ "በተጨማሪም እነዚህን ነገሮች ስበክ" ወይም "በተጨማሪም እነዚህን ነገሮች በሥልጣን አስተምር፡፡" ጡሞቴዎስ ራሱ የጳውሎስን ቃላት መታዘዝ ነበረበት—እንደሁም ሌሎችም የጳውሎስን ቃላት እንዲታዘዙ ማዘዝ አለበት፡፡ ያለነቀፋ መሆን ይችሉ ዘንድ "ማንም በእነርሱ ላይ ስህተት ማግኘት እዳይችል፡፡" አማራጭ ትርጉሞች "እርሱ" 1) "እነዚህ ባልቴቶች እና ቤተሰቦቻቸው" (UDB) ወይም 2) "ቤተ ክርስቲያን፡፡" በዚህ ሥፍራ ላይ የዐረፍተ ነገሩን ባለቤት “እነርሱ” በሚለው መተው መልካም ሳሆን አይቀርም፡፡ ለራሱ ዘመዶች አስፈላጊውን ነገር የማያቀርብ ሰው "ዘመዶቹ የሚያስፈልጋቸውን ነገር የማይሰጣቸው ሰው" ወይም "የገዛ ዘመዱን የማይረዳ ሰው" ለሀዛ ቤተሰቦቹ "ለቤተሰቡ ሁሉ" ወይም "በቤቱ ውስጥ ላሉት ሰዎች" የራሱ የሆኑት በተሰቦች "ለቤተሰቦቹ" ወይም "በቤቱ ውስጥ የሚኖሩት ቤተሰቦቹ ለሆኑት ሰዎች" እምነትን ክዷል "የሚያደርገው ነገር ሃይማቱን የካደ ያስመስለዋል" ወይም "የሚያደርጋቸው ነገሮች እኛ ከምናምናቸው ነገሮች ተቃራኒ የሆኑትን ነው" ወይም "ቀድሞ ከሚያምናቸው ነገሮች ወደ ኋላ ተመልሷል" ከማያምኑትም የከፋ ነው "ይህ ሰው በኢየሱስ ከማያምኑት ሰዎች ይልቅ የከፋ ነው፡፡" በኢየሱስ የማያምኑት ሰዎች እንኳ የገዛ ቤተሰቦቻቸውን ይንከባከባሉ፤ ስለዚህም ከአማኞች ደግም ከእነዚህ ይልቅ ምን ያኸል ማድረግ ይጠበቃል!
ባልቴቶች ተብሎ የተመዘገቡት ይህ የሚያየው በጽሑፍም ይሁን ወይም አይሁን የባልቴቶች ስም ዝርዝርዝ ታውቋል ማለት ነው፡፡ ቤተክርስያንም ለእነዚህ ሴቶች የሚያስፈልገውን እንደ መጠለያ፣ ልብስ እና ምግብ ማቅረብ ይኖርባታል እንዲሁም እነዚህ ሴቶች ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል ራሳቸውን መስጠት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ከስልዳ አመት በታች ያልሆነች ከስልሳ ዓመት በታች የሆነች ባልቴት ሴት እንደገና ማግባት ትችላለች ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን አስፈላጊውን ሁሉ እንክብካቤ ማድረግ ያለባት ከስልሳ ዓመት በላይ ለሆኑ ባልቴት ሴቶች ነው፡፡ የአንዲት ምስት ባል "ለባሏ ታማኝ የሆነች ሴት" በመልካም ተግባሮቿ የሚትታወቅ ልትሆን ይገባል ይህንንተከትሎ የሚመጡት ሀረጋት ሴትቱ ልትታወቅባቸው የሚገቡ መልካም ተግባራት ምን ምን ልመስሉ እንደሚችሉ ምሳሌ ይሆናል፡፡ እግር ማጠብ "ይህ እገዛ ለማደረግ የተለመደ ሥራ ነው፡፡" በጭቃ እና አቧራ ውስጥ ስራመዱ የቆዩ ሰዎችን እግር ማጠብ ሌሎች ሰዎች የሚያስፈልጋቸውን ነገር የማድረግ እና ሕይወት ይበልጥ ተወዳጅ እንዲሆን የማድረግ ምሳሌ ነው፡፡ አማኞች "የእግዚአብሔር ቅዱስ ሕዝብ" መልካም ስራን ሁሉ የሚከታተሉ "is known for doing good works"
ይሁን እንጂ ወጣት ባልቴቶችን በዚህ ውስጥ ማካተት የለባችሁም "በዚህ የባልቴቶች ዝርዝር ውስጥ ወጣት ሴቶችን ማካተት የለባችሁም፡፡" ዝርዝሩ በውስጡ መያዝ ያለበት ቤተ ክርስቲያን ልታግዛቸው የሚገቡ ዕድሜያቸው ስልሳ እና ከስልሳ በላይ የሆኑ ባልቴቶችን ብቻ ነው፡፡ ክርስቶስን በሚቃወም አካላዊ ፍላጎች ይሸነፋሉ፡፡ "በፍተወት መሻት ምክንያት ከክርስቶስ ይርቃሉ" ወይም "መንፈሳዊ መሰጠታቸውን ከስሜታዊ መሻታቸው የተነሣ ይተውታል" የመጀመሪያውን መሰጠታቸውን ይተውታል "የመጀመሪያ መሰጣቸውን አይጠብቁም" ወይም "አስቀድመው እንደሚያደርጉ ቃል የገቡትን ነገር አይፈጽሚም" ቃል መግባት የባልቴቶቹ ስምምነት ቤተ ክርስቲያን የሚያስፈልጋቸውን ነገሮች የሚታሟላ ከሆነ ቤተ ክርስቲያንን ለማገልግል ነው፡፡ ሐሜተኞች እነዚህ ስለ ሰዎች የግል ሕይወት ለሌሎች ሰዎች የሚወሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ጣልቃ በመግባት እነዚህ በሌሎች ሰዎች ሕይወት ውስጥ ጣልቃ የሚገቡ ሰዎች ናቸው፡፡ መናገር የማይገባቸው ነገር "ለማንሳት እንኳ ተገቢ ያልሆኑ ነገሮችን"
እኛን ለመክሰስ “እኛ” ለሚለው ቃል አማራጭ ትርጉሞች 1) ወጣት ሴቶች ወይም 2) ሐዋሪያው ጳውሎስን እና ወጣት ሴቶችን በበላይነት የሚያስተዳድሩ ሽማግሌዎች ወይም 3) ከወጣት ሴቶቹ ጋር አብረው የተቆጠሩት ሁሉም ክርስትያን አማኞች፡፡ አንዳንዶች ሰይጣንን እንዲከተሉ ፈቀቅ ብለዋልና። "ሴጣንን ለመከተል ከክርስቶስ መንገድ ፈቀቅ ብለዋልና፡፡ ዬትኛዋም አማኝ ሴት "ዬትኛዋም ክርስትያን ሴት" ወይም "በክርስቶስ የሚታምን ዬትኛዋም ሴት" ባልቴቶች ያሏቸው "በዘመዶቿ መካከል ባልቴት ያላት" እውተኛ ባልቴቶች "የሚያግዛቸው ማንም ሰው ያሌላቸው ሴቶች"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: እንደገና ጳውሎስ ሽማግሌዎች (ኤጵስ ቆጳሳት)ን እንዴት መንከባከብ እንደሚገባ ይናራል፡፡ . . . እንደሚገባቸው ቁጠሩ አማራጭ ትርጉም: "አማኝ የሆናችሁ ሁላችሁ . . . ቁጠሩ፡፡" እጥፍ ክብር አማራጭ ትርጉሞች 1) "ሁለቱንም ዓይነት ክብርለ አክብሮት እና ደሞዝ" ወይም 2) "ከሌሎች ሰዎች ይልቅ አክብሮት፡፡" በመስበክና በማስተማር የሚደክሙት፥ "የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰብኩ እና የሚያስተምሩት" የሚያበራየውን በሬ አፉን አትሰር ማሰሪያ በበሬ አፍ ላይ የሚታሰር ሲሆን በሬው ሥራውን በሚሠራበት ወቅት እንዳይበላ ያደርገዋል፡፡ በሬ እንደ ላም ያለ ትልቅ እንስሳ ነው፡፡ ሰብል ማበራየት እህሉን ከገለባው ለመለየጥ በታጨደ ሰብል ላይ መራመድ ወይም ከባድ ዕቃ ማንከባለል ነው፡፡ በሬዎች በሚያበራዩበት ወቅት ከገለባው እንዲበሉ ይፈቀድላቸዋል፡፡ ይገባዋል "ይገባዋል
መቀበል "ማድመጥ" ወይም "መቀበል" ሁለት ወይም ሦስት "ቢያንስ ሁለት" ወይም "ሁለት ወይም ከዚያ በላይ" መገሠጽ "ገሰጸ" ወይም "አስተካከለ" ኃጢአተኞች ይህ ማንም እግዚአብሔር የማይታዘዝ ወይም የማያስደስትን ሥራን የሚሠራ ሰውን ያመለክታል፡፡ ይህ ምናልባት ያደረገውን ነገር ማንም ሰው ላያውቀው ይችላል፡፡ በሁሉም ፊት "ማንም ሰው በሚመለከተው ሥፍራ" ሌሎች ሰዎች ይፈሩ ዘንድ "ሌሎች ሰዎች ኃጢአትን ይፈሩ ዘንድ"
አንተ ጳውሎስ ለአንድ ሰው፣ ለጢሞቴዎስ በመነናገር ላይ ሲሆን በዚህ ሥፍራ ላይ “አንተ” የሚለው ቃል የተገለጸው በነጠላ ቁጥር ነው፡፡ አስቀድሞ የተሰጠ ፍርድ "አስቀድሞ የተሰጠ ፍርድ" ወይም "ሁሉም ሰው በራሱ በኩል ስለተፈጠረው ነገር የሚናረውን ነገር ሳታደምጥ ውሳኔ መስጠት፡፡" ጢሞቴዎስ እውነታው ምን እንደሆነ ማድመጥ ከዚያም የራሱን ፍርድ መስጠት ይጠበቅበታል፡፡ ከአድሎ ውጪ "ለሚትወደው ሰው ማዘንበል" ወይም "በወዳጅነት መሠረት፡፡" ጢሞቴዎስ ፍርድን መስጠት ያለበት በሁኔታው ውስጥ የተሳተፉት እነማን ናቸው በሚል መሥፈረት ሳይሆን በእውነት መሠረት ላይ በመሆን ነው፡፡ እጅ በመጫን ይህ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች በሰዎች ላይ እጃቸውን ጭነው ወደ እግዚአብሔር በመጸለይ ይሀህ ሰው እግዚብሔርን በሚያስደስት መንገድ ማገልገል እንዲችለል እግዚአብሔር ያስችለው ዘንድ የሚጸልዩበት ሥርዓት ነው፡፡ የሌላ ሰው ኃጢትን መካፈል "በሌላ ሰው ኃጢአት ውስጥ መካፈል፡፡" የዚህ አማራጭ ትርጉሞች እነዚህ ናቸው 1) ጢሞቴዎስ አንድ ኃጢአት እንደሠራ የሚታወቅ ሰውን የቤተ ክርስቲያን ሠራተኛ እንዲሆን ከመረጠ እግዚብሔር በዚህ ሰው ኃጢአት ጢሞቴዎስን ተጠያቁ ያደርገዋል፡፡ ወይም 2) ሌሎች ሰዎች ስያደርጉ የተመለከተውን ኃጢአት ጢሞቴዎስ እርሱ ማድረግ የለበትም፡፡
አጠቃላይ መረጃ: በቁጥር 23 ላይ ለጢሞቴዎስ የተሰጠ የግል ማሳሰቢያ የገባ ይመስላል፡፡ ከዚያም በቁጥር 24 ላይ ጳውሎስ በቁጥር 22 ላይ መናገር የጀመረውን ነገር ይቀጥላል፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ ውሃ መጠጣት የለብህም ወይም "ውሃ መጠጣት መቆም ይርብሃል፣" ውሃ ብቻ የሚጠጣ ሰው (UDB)፡፡ ጳውሎስ ውሃ መጠጣትን ሙሉ ለሙሉ ፈጽሞ አልከለከለም፡፡ ይሁን እንጂ ጳውሎስ ለጡሞቴዎስ የሰጠው አስተያየት ወይንን እንደ የሕክምና መዲሃኒት ይጠቀመው ዘንድ ነው፡፡ በዚያ አከባቢ የሚገኘው ውሃ ብዙ ጊዜ በሽታን ያስከትል ነበርና፡፡ ወደ ፍድ ከእነርሱ በፊት ይሄዳል "ኃጢአታቸው ከእርሱ ፊት ለፍርድ ይሄዳል፡፡" እነዚህ አማራጭ ትርጉሞች ናቸው 1) ኃጢአታቸው የሚያሳየው ይህ ሰው እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ እንደሆነ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያን ይህ ሰው ምንም እንኳ የቤተ ክርስቲያን መሪ ቢሆንም ልትፈርድበት እንደሚገባ ነው፡፡ወይም ወይም 2) ኃጢአታቸው እንደሚያሳየው ሰውዬው እንደ ከዚህ ቀደሙ በመሆኑ ምንያት ሰውዬው ጥፋተኝነቱ ይረጋገጥም አይረጋገጥም ቤተ ክርስቲያን ግን ውሳኔ ማስተላለፍ ይኖርባቸዋል፡፡ ወይም 3) ኃጢአታቸው የተረጋገጠ በመሆኑ እግዚአብሔር አሁን ይፈርድባቸዋል፡፡ ኋላ ላይ ሌሎች ይከተሏቸዋል "ይሁን እንጂ አንዳንድ ኃጢአቶች እነዚህን ሰዎች ይከተሏቸዋል፡፡" አማራጭ ትርጉሞች 1) እስከ በኋላ ድረስ አንዳንድ ኃጢአቶችን ጢሞቴዎስ አያውቃቸውም ወይም 2) አንዳንድ ኃጢአቶችን ቤተ ክርስቲያን እስከ በኋላ ድረስ አታውቃቸውም፣ ወይም 3) አንዳንድ ኃጢአቶች እግዚአብሔር እስከ መጨረሻው ፍርድ ድረስ አይፈርድባቸዋም፡፡ መልካም በዚህ ሥፍራ ላይ “መልካም” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ከእግዚብሔር ባሕርይ፣ ዓላማዎች እና ፈቃድ ጋር የሚስማማውን ነው፡፡ ሌሎቹም ቢሆኑ መሸሸግ አይችሉም አማራጭ ትርጉሞች፡ "ሌሎች መልካም ሥራዎችም ቢሆኑ ለወደፊት ይታወቃሉ"
1 የእግዚአብሔር ስምና ትምህርቱ እንዳይሰደብ ከቀንበር በታች ያሉ ባሪያዎች ለገዢዎቻቸው የሚገባቸውን ክብር ይስጡ፡፡ 2 አማኞች የሆኑ ገዢዎች ያሉአቸው ባሪያዎች፣ በእምነት ወንድሞቻቸው ስለሆኑ ገዢዎቻቸውን መናቅ የለባቸውም፡፡ ይልቁንም በመልካም ሥራቸው የሚጠቅሙ የተወደዱ ወንድሞች በመሆናቸው አብልጠው ያገልግሉአቸው፡፡ እነዚህን ነገሮች አስተምር ግለጽም፡፡ 3 ማንም ልዩ ትምህርትን ቢያስተምር፣ እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚረዳውን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶሰን ቃል እና የእኛንም ጤናማ ቃል ባይቀበል፣ 4 በትእቢት ተነፍቶአል አንዳችም አያውቅም፡፡ ነገር ግን በክርክርና በቃል በመዋጋት የተለከፈ ነው፣ ከዚህም ምቀኝነት፣ ክርክር፣ መሳደብ፣ ክፉ አሳብና፣ እርስ በርስ መናደድም ይወጣሉ፡፡ 5 እነርሱም አእምሮአቸው የተበላሸባቸው ከእውነትም የራቁ እግዚአብሔርን መምሰል ጥቅም ማግኛ የሚመስላቸው ናቸው፡፡ 6 ባለው ለሚረካ ግን እግዚአብሔርን መምሰል እጅግ ማትረፊያ ነው፡፡ 7 ወደ ዓለም ምንም አላመጣንምና፣ አንዳችም ይዘን መሄድ አይቻለንም፡፡ 8 ምግብ እና ልብስ ካለን ያ ይበቃናል፡፡ 9 ባለጠጋ ለመሆን የሚመኙ በፈተና ውስጥ ይወድቃሉ፣ በወጥመድ፣ ሞኝነት በመሰሉ አያሌ ጎጂ ምኞቶች፣ እንዲሁም ሰዎችን በሚያሰጥሙና በሚያጠፉ በሌሎች ነገሮች ላይ ይወድቃሉ፡፡ 10 የገንዘብ ፍቅር የክፋት ሁሉ ሥር ነውና፡፡ አንዳንድ ሰዎች ይህን ሲመኙ ከእምነት ስተው ራሳቸውን በብዙ ሐዘን ጎዱ፡፡ 11 አንተ ግን፣ የእግዚአብሔር ሰው፣ ከእነዚሀ ነገሮች ሽሽ፡፡ ጽድቅን፣ እግዚአብሔርን መምሰል፣ ታማኝነትን፣ ፍቅርን፣ ጽናትን እና ለሰዎች መጠንቀቅን ተከታተል፡፡ 12 መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል፡፡ የተጠራህለትን በብዙ ምሥክሮች ፊት ስለመልካምነቱ የመሰከርክለትን የዘላለምን ሕይወት ያዝ፡፡ 13 ሁሉን ነገር በፈጠረ፣ በእግዚአብሔር ፊት፣ በጴንጤናዊው በጲላጦስ ፊት እውነትን በመሰከረው፣ በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት አዝዝሃለሁ፣ 14 ኢየሱስ ክርስቶስ እስኪገለጥ ድረስ ያለነቀፋ ሆነህ ትእዛዛቱን በፍጹምነት ጠብቅ፡፡ 15 እርሱም መገለጡን የተባረከውና፣ ብቻውን ኃያል የሆነው፣ የነገሥታት ንጉሥ፣ የጌቶችም ጌታ በወሰነው በትክክለኛው ጊዜ ያሳያል፡፡ 16 እርሱ ብቻ የማይሞት ነው፤ ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን ውስጥ ይኖራል፡፡ ማንም ሰው አላየውም ሊያየውም አይችልም፡፡ ለእርሱ ክብር የዘላለምም ኃይል ይሁን፡፡ አሜን፡፡ 17 በአሁኑ ዘመን ሀብታሞች ለሆኑት እንዳይታበዩ ንገራቸው፡፡ ደስ እንዲለን እግዚአብሔር በሚሰጠን እውነተኛ ብልጥግና እንጂ እርግጠኛ ባልሆነው በዚህ ምድራዊ ባለጠግነት ተስፋ እንዳያደርጉ እዘዛቸው፡፡ 18 በመልካም ሥራ ባለጠጎች እንዲሆኑ፣ መልካም የሆነውን እንዲያደርጉ ለማካፈልም ፈቃደኞች እንዲሆኑ ንገራቸው፡፡ 19 በዚህ ሁኔታ በሚመጣው ዓለም ለራሳቸው መልካም መሠረትን ይጥላሉ፣ እውነተኛውንም ሕይወት ይይዛሉ፡፡ 20 ጢሞቴዎስ ሆይ፣ ለአንተ የተሰጠህን አደራ ጠብቅ፡፡ የማይረባውን ወሬ አስወግድ፣ በሐሰት እውቀት ከተባለ እርስ በርሱ ከሚጋጭ ነገር ጋር ከመከራከር ራቅ፡፡ 21 አንዳንድ ሰዎች ይህ እውቀት አለን በማለት ከእምነት ርቀዋል፡፡ ጸጋ ከአንተ ጋር ይሁን፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ለባሮቸ እና ለጌቶቻቸው አንዳንድ ልዩ መመሪያዎችን መስጠቱትን ቀጥኮ እንዴት እግዚብሔር በመመስል መኖር እንደሚቻል መመሪያን ይሰጣል፡፡ ከቀንበር በታች ያሉቱ ባሪያዎች ይህ ባሪያን እንደ በሬ የሚመስል በመሆኑ በዚህ መልኩ ልተረጎም ይችላል፡፡ ይህንን ምሳሌያዊ ንግግር ለመተርጎም አስቸጋሪ ሊሆን ከቻለ ሳይተረጎም ሊያልፍ ይችላል፡፡ ይህ ክርስቲያን መሆንን በሚያለክት ምሳሌያዊ ንግግር ሊተረጎም ይችላል፡፡ የእግዚአብሔር ስም እና ነትምህርቱ ይሰደባል "ከቤተ ክርስቲያን ውጪ ያሉ ሰዎች ስለ እግዚአብሔር ስም እና ትምህርቱ አክብሮት ይናገሩ ዘንድ"
አንድ ሰው ካስተማረ "ይህንን የሚያስተምር ማንኛውም ሰው" ወይም "ይህንን የሚያስተምሩ ሰዎች፡፡" “የተለያዩ” ነገሮቸን የሚያስተምሩ ሰዎች እንዳሉ ጳውሎስ ታሳቢ ያደርጋል፡፡ የሆነ ሰው . . . እርሱ . . . እርሱ UDB ብዙ ቁጥር አመላካች ይጠቀማል "እንዳንድ ሰዎች . . . እንዲህ ያሉ ሰዎች . . . እነርሱ"፤ “የሚያስተምረው” “ማንኛውም ሰው” ወንድ ወይም ሴት፣ አንድ ሰው ወይም ብዙ ሰዎች፡፡ እነዚህ አማራጭ ትርጉሞች ሊያሳይ የሚችልን ቃል በቋንቋችሁ ካለ ተጠቀሙበት፡፡ በጭቅጭቅ ታሟል "ማድረግ የሚፈልገው ነገር ሁሉ መከራከር ነው" ወይም "ክርክረን ይፈልጋሉ፡፡" እንዲህ ያሉ ሰዎች ክርክር ራሱን ይፈልጉታል እና መስማመማት የማይችሉበትን መንገድ ይፈልጋሉ፡፡ ቅንአት "ሌሎች ሰዎች ያላቸውን ነገር ለማግኘት ይፈልጋሉ" ክርክር "በአማኞች መካከል ያለ ክርክር" ስድብ "ሰዎች በሐሰት ስለ ሌሎች ሰዎች መጥፎ ነገርን ይናገራሉ" ክፉ ጥርጣረተ ከእነርሱ ጋር የማይስማማ ማንኛውም ሰው በእነርሱ ላይ ክፉ ነገር ለማድረግ እየሞከረ እንደሆነ መናገር፡፡ ከሰዎች ጋር ሁል ጊዜ መጣላት "ከሁሉም ሰዎች ጋር መጣላት" የበሰበሰ አእምሮ "በመጥፎ ሀሳቦች ፈጽሞ የተበላሸ አእምሮ"
ትልቅ ትርፍ ነው "ትልቅ ትርፍን ያስገኛል" ወይም "ለእኛ ብዙ መልካም ነገርን ያደርጋል" ወደ ዓለም ምንም ነገር አላመጣም "ስወለድ ወደ ዓለም ምንም ነገር ይዞ አልመጣም" እንዲሁም ምንም ወስደነው የሚንሄደው ነገር የለም "እንዲሁም ስንሞት ከዓለም ይዘነው የሚንሄደው ነገር የለም" ይህን እናድረግ "ይህንን ማድረግ አለብን"
እንዳንወድቅ ይህ አንድ ሰው ሕይወቱን ወይም በአእምሮው የማሰብ ሂደቱን ማጣቱን የሚያመለክት ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ በፈተና እንዳይወድቅ "መቋቋም ከሚችለው በላይ ወደ ሆነ ፈተና እንዳይገባ" በወጥመድ ተይዞ . . . እንዳይወድቅ "በመጥመድ እንዳይያዝ፡፡" ለራስ ጥቅም መሥራት አለመቻልን እና ጉዳት የሚያደርሱ ሰዎችን በመቃወም መሥራት አለመቻልን የሚያመለክት ምሳሌ ነው፡፡ በብዙ ሙኝነት በሞላባቸው እና ጉዳት በሚያደርሱ መሻት ውስጥ መውደቅ "ሞኝነት በሞላባቸው እና ጉዳት በሚያደርሱ ፍለጎቶች ቁጥጥር ሥር መሆን" ሰዎችን እንዲሰምጡ ማድረግ "ሰዎችን እንዲሠርጉ ወደ ታች መጎተት" ገንዘብን መውደድ የክፋት ሁሉ ሥር ስለሆነ "ገንዘብን መውደድ የክፋት ሁሉ ሥር በመሆኑ ምክንያት" ለሚሹት ሰዎች "ገንዘብን ለሚሹ ሰዎች" ከእምነት ፈቀቅ ብለዋል "የእውነትን መንገድ ትተው ሄደዋል" ወይም "በእውነት ማመን ትተዋል" በብዙ ሥቃይ ራሳቸውን ወጉ። ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ኃዘንን ከብላዋ ወየም ከጦር ጋር በማነጻጸር ያስቀምጣል፡፡
የእግዚአብሔር ሰው "የእግዚብሔር አገልጋይ" ወይም "የእግዚአብሔር የሆነ ሰው" ከእነዚህ ነገሮቸ ራቅ "እነዚህ ነገሮች አንተን ለመጉዳት እንደሚችሉ ነገሮች በማድረግ ከእነርሱ ራቅ፡፡" የዚህ ነገር አማራጭ ተትርጉሞቹ 1) “ገንዘብን መውደድ" ፈልግ "ተከተ" ወይም "ተከታተል" ወይም "ይህን ለማድረግ የሚትችለውን አድርግ" መልካምን ገድል ተጋደል...አጥብቀህ ያዝ...ሕይወት አንዳንዶች ይህንን ከክፍል የእስፖርታዊ ውድድር ጋር ተነጻጽሮ የቀረበ ምሳሌያዊ ንግግር አድርገው ይመለከቱታል፡፡ በዚህ ውድድር ውስጥም አሸናፊው ሽልማቱን “ለመያዝ” “ይጋደላል”፡፡ መያዝ . . . ሕይወት አንዳንዶች ይህንን ምሳሌያዊ ንግግር “መለካም ገድልን ተጋደል” ለሚለው ሌላ አማራጭ ንግግር እንደሆነ ይረዱታል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ሕይወትን ለማግኘት የሚታደርገውን ነገር ሁሉ አድርግ" ምስክርነት ስጥ "ምስክርነት ስጥ" ወይም "መስክር" በፊት "በመገኘቱ ውስጥ" መልካም የሆነውን ነገር "የሚታምነውን ነገር"
በእግዚአብሔር ፊት "በእግዚብሔር መገኘት ውስጥ" ወይም "እግዚብሔር ምስክርህ ሆኖ" በክርስቶስ ፊት "በክርስቶስ መገኘት ፊት" ወይም "ክርስቶስ ምስክርህ ሆኖ" በጴንጤናዊው ጵላጦስ ፊት "በጴንጤናዊው ጵላጦስ ፊት" ከነቀፋ ውጪ የዚህ አማራጭ ትርጉሞች የሆኑት 1) እግዚአብሔር በጢሞቴዎስ ላይ ምንም ስሕተት አያገኝበትም (UDB) ወይም 2) ሌሎች ሰዎች በጢሞቴዎስ ላይ ምንም ስሕተት አያገኙበትም፡፡ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ "ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እስከሚገለጥበት ቀን ድረስ"
በትክክለኛው ሰዓት "በትክክለኛው ጊዜ" (UDB) በተዘጋጀ "በተወሰነ" ወይም "በተመረጠ" የተባረከው "ሁሉንም በረከቶች በራሱ የያዘው" ወይም "ሁሉንም በረከቶች የሚሰጠው እግዚአብሔር፡፡" ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስን እንዲገለጥ የሚያደርገው እግዚአብሔር አባትን ነው፡፡
እርግጠኞች ያልሆኑ ባለጠጎች "ባለ ጠጎች የሆኑት የትዕቢትን ነገር እንዳያስቡ፡፡" በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ የሚያመለከተው ቁሳዊ የሆነ ነገር ነው፡፡ እውነተኛ ባለጠግነት "በእውነተኛ መንገድ ደስተኞች እንድንሆን የሚያደርገው፡፡" በዚህ ስፍራ ላይ ይህ የሚያመለክተው ቁሳዊ ነገር የሚያለክት ነው ይሁን እንጂ ሰዎች በቁሳዊ ነገሮች አማካኝነት ለማግኘት የሚጥሯቸውን ፍቅርን ሐሴትን እና ሰላምን የሚወክል ነው፡፡ በመልካም ሥራ ባለጠጎች ሁኔ "ሌሎችን በተለያዩ መንገዶች በማገዝ አገልግሉ፡፡" ቤተ ክርስቲያንንም መገንባት መሠረት ቤት በመሥራት ሂደት ውስጥ ልሠራ የሚገባው የመጀመሪያው ክፍል፡፡ ይህ የመጀመሪያው “እውነተኛ ባለጠግነት” መገለጫ ምሳሌ ነው እንዲሁም እግዚአብሔር ለለእርሱ ሕዝብ ለዘላለም የሚሰጠው “የእውነተኛ ሕይወት” ጅማሬ ነው፡፡ እውነተኛውን ሕይወት ያዝ ይህ በ 1TI 6:12 ላይ የተገለጸውን የእስፖርት ውድድር አሸናፊ የሚይዘውን ሽልማት የሚያሳይ ምሳሌያዊ ንግግርን የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ “ሽልማት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሕይወትን ነው፡፡
ኖት የለውም።
1 በእግዚአብሔር ፈቃድ፣ በኢየሱስ ክርስቶስ ለሆነው የሕይወት ተስፋ፣ የክርስቶስ ኢየሱስ ሐዋርያ የሆነው፣ጳውሎስ 2 ለተወደደው ልጄ፣ ለጢሞቴዎስ፣ ጸጋና ምሕረት ሰላምም በእግዚአብሔር አባታችን፣ ቤታችንም በኢየሱስ ክርስቶስ ለአንተ ይሁን፡፡ 3 ሌትና ቀን በጸሎቴ ስለማስብህ፣ እንደ አባቶቼ አድርጌ በንጹህ ኅሊና የማገለግለወን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፣ 4 እምባህን እያሰብኩ በደስታ እሞላ ዘንድ ላይህ እናፍቃለሁ፤ 5 ያለህንም እውነተኛ እምነት አስባለሁ፣ ይህም እምነት አስቀድሞ በአያትህ በሎይድ በእናትህም በኤውንቄ ነበረባቸው፣ በአንተም እንዳለ ተረድቼአለሁ፡፡ 6 እግዚአብሔር የሰጠህን በአንተ ያለውን ስጦታ እንድታነሣሣ ስእጆቼን በመጫኔ አሳስብሃለሁ፡፡ 7 እግዚአብሔር የኃይል እና የፍቅር ራስንም የመግዛት እንጂ፣ የፍርሃት መንፈስ አልሰጠንም፡፡ 8 በጌታ እና የእርሱ እስረኛ በሆንኩት በእኔም ምሥክርነት አትፈር፣ እንደ እግዚአብሔር ኃይል መጠን ስለ ወንጌል መከራን ተቀበል፡፡ 9 ከዘላለም ዘመናት በፊት በክርስቶስ ኢየሱስ ያዳነን፣ በቅዱስም አጠራር የጠራን እግዚአብሔር ነው፤ ይህም የሆነው በራሱ እቅድና በጸጋወ ነው እጂ በእኛ ሥራ አይደለም፡፡ 10 አሁን ግን የእግዚአብሔር ማዳን፣ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ እና፣ ሞትን በማጥፋቱ እና የዘላለምን ሕይወት ወደ ብርሃን በማውጣቱ በወንጌሉ ተገልጦአል፣ 11 ይህንንም ወንጌል ለማብሰር እኔ ሐዋርያ እና አስተማሪ ሆኜ ተሹሜአለሁ፡፡ 12 ስለዚህ ምክንያት እኔ መከራ እቀበላለሁ፣ ነገር ግን አላፍርበትም፣ ያመንኩትን አውቃለሁና፤ የሰጠሁትን አደራ እስከዚያች ቀን ድረስ እንደሚጠብቅ ተረድቼአለሁ፡፡ 13 ከእኔ የሰማኸውን ጤናማ ቃል፣ በክርስቶስ ኢየሱስ ባለ እምነትና ፍቅር በምሳሌነት ጠብቅ፡፡ 14 በእኛ በሚኖረው በመንፈስ ቅዱስ አድርገህ በእግዚአበሔር የተሰጠህንም አደራ ጠብቅ፡፡ 15 በእስያ ያሉት ሁሉ ከእኔ ፈቀቅ እንዳሉ ታውቃለህ፣ ከእነዚህም ጊሊጎስ እና ሄርዋጌኔስ ይገኙባቸዋል፡፡ 16 ጌታ ለሄኔሲፎሩ ቤተ ሰብ ምሕረትን ይስጣቸው፣ ብዙ ጊዜ አሳርፎኛልና፣ በሰንሰለቴም አላፈረበትም፡፡ 17 ነገር ግን በሮም በነበረ ጊዜ፣ በብርቱ ፈልጎ አገኘኝ፣ 18 ጌታ በዚያች ቀን ምሕረትን እንዲያገኝ ይስጠው፣ በኤፌሶን ምንያህል እንደረዳኝ አንተ በደኅና ታውቃለህ፡፡
ጳውሎስ "ከጳውስ" ወይም "እኔ ጳውሎስ ይህንን ደብዳቤ ጻፍኩላችሁ" በእግዚአብሔር ፈቃድ አማካኝነት "ከእግዚብሔር ፈቃድ የተነሣ" ወይም "እግዚአብሔር ይህንን ነገር በመፈለጉ ምክንያት፡፡" ጳውሎስ ሐዋርያ የሆነው እግዚአብሔር ጳውሎስ ሐዋርያ እንዲሆን በመፈለጉ እንጂ ሰዎች ሐዋርያ እንዲሆ ስለመረጡት አይደለም፡፡ እንደ አማራጭ ትርጉሞች፡ 1) "ከ ጋር በመስማማት" ትርጉሙም እግዚአብሐየር ለኢየሱስ በገባው ቃለል መሠረት ኢየሱስ ሕይወትን ይሰጣል እንዲሁም ጳውሎስን ሐዋርያ አድርጓል ወይም 2) "ለዚህ ዓላማ ሲባል፣" ትርጉሙም እግዚአብሔር ጳውሎስን የሾመበጽ ምክንያት ጳውሎስ በኢየሱስ በኩል የሚገኘውን ሕይወት ለሌሎች ሰዎች ይናገር ዘንድ ነው፡፡ በኢየሱስ ክርስቶስ ውስጥ የሚገኘውን የሕይወት ተስፋ "በክርስቶስ ኢየሱስ የሆኑ ሰዎች ሕያዋን እንደሚሆኑ እግዚአብሔር የተስፋ ቃልን ሰጥቷል፡፡" የተወድህ ልጄ ሆይ "ውድ ልጄ ሆይ" ወይም "የተወደድከው ልጄ ሆይ" ወይም "የሚወድህ ልጄ ሆይ፡፡" ጢሞቴዎስ ወደ ክርስቶስ የመጣው በጳውሎስ አማካኝነት ነው ስለዚህም ጳውሎስ ጢሞቴዎስን ልክ እንደ ገዛ ልጁ አድርጎ ይመለከተው ነበር፡፡ ጸጋ፣ ምህረት እና ሰላም ከ . . . "ጸጋ፣ ምህረት እና ሰላም ለእናነት ከ . . . ዘንድ ይሁንላችሁ" ወይም "ከውስጥ መልካምነትን፣ ምህረትን እና ሰላምን ከ . . . ዘንድ ይሁንላችሁ" እግዚአብሔር አባት "አባታችን የሆነው እግዚአብሔር" እናም ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ "እንዲሁም ጌታችን ከሆነው ከክርስቶስ ኢየሱስ ዘንድ"
ቀደምት አባቶቻችን እንዳገለገሉ እኔም አገለግላለሁ ጳውሎስ የሚያገለግለው ቀደምት አባቶቹ ያገለገሉትን እግዚአብሔርን ነው፡፡ “. . . እንደ ክርስትያን ኃላፊነትን የሚወጣው ከዚህ በፊት የኖሩት ቀደምት አባቶ ባደረጉት መልኩ ነው፡፡" በንጹሕ ሕልና "በንጹሕ ሕልና፡፡" በመጥፎ ሀሳብ የሚወዛገብ ሳይሆን ሁል ጊዜ ትክክለኛ ነገርን ለማድረግ ጥረት ያደርጋል፡፡ እኔ ሁል ጊዜ ስለ አንተ ሳስታውስ "ሁል ጊዜ ስለአንተ ሳስታውስ" ወይም 'ሁል ጊዜ ስለአንተ በማስታውስበት ወቅት" ምሽት እና አማራጭ ትርጉሞች 1) "በምሽት እና በቀን ስጸልይ" ወይም 2) "በቀን እና በሌልት አንተን ሳስታውስ ወይም 3) "በምሽት እና በዘን አንተን ለማየት ስጓጓ፡፡" አንተን ለማየት ስጓጓ "አንተን ለማየት ከፍተኛ ፍላጎት ስለላለኝ" እንባህን እያስታወስኩ "ያሳለፍከውን መከራ ሁሉ እያስታወስኩ" በደስታ እሞላለሁ "ከፍኛ ደስታም ይሰማኛል" ወይም "በጣም ደስ ይለኛል" ይህንን እያስታወስኩ "ይህንን ስላምስታውስ" ወይም "ይህንን ባስታወስኩ ቁጥር" ወይም "ይህን በማስታወሴ ምክንያት" እውነተኛውን እምነትህ "እውነተኛ የሆነውን እምነትህን" ወይም "ማስመሰል ያሌለበትን እምነትህን፡፡" ይህ እውነተኛ ወይም ምንም ውሸት ያሌለበትን እምነቱን የሚያመለክት ነው፡፡ እውነት...በመጀመሪያ በአያትህ ዘንድ የነበረውን . . . በአንተም ውስጥ ያለውን የጢሞቴዎስ ቅድመ አያት ለእግዚአብሔር የተሰጡ ነበሩ እናም ጳውሎስ የጢሞቴዎስን እምነት ከኤቱ እምነት ጋር ያነጻትራል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ጢሞቴዎስ በኃይል፣ በፍቅር እና በደቀ መዝሙርነት እንዲኖር ያበረታታዋል፡፡ በተጨማሪም በጳውሎስ መታሠር እንዳያፍር ምክንያቱም የጳውሎስ መከራ በክርስቶስ በማመኑ ምክንያት ነው፡፡ ይህ ምክንያት ነው "በዚህ ምክንያት" ወይም "በኢየሱስ ላይ ባለህ እውነተና እምነት የተነሣ" ወይም "በኢየሱስ ላይ እውነተኛ እምነት ስላለህ" አስታውስሃለሁ "እኔ አስታውስሃለሁ" ወይም "እንደገና እነግርሃለሁ" እጅ በመጫን በአንተ ውስጥ ያለውን የእግዚብሔር ስጦታ አነሳሳለሁ ጳውሎስ በጢሞቴዎስ ላይ እጆቹን በመጫን በእርሱ ላይ ያለውን መንፈስ ቅዱስ እና የመንፈስ ቅዱስ ስጦታን አረጋግጧል፡፡ ጳውሎስ እየነገረው ያለው ነገር ለክርስቶስ በሚሠራበት ወቅት እነዚህን የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች “እንደገና እንቀሰቅስ” ወይም “እንዲያነቃቃ” ነው፡፡ የከሰል እሳትን ማራገብ ወይም ማቀጣጠል የሚለው ምስላዊ ገለጻ በጢሞቴዎስ የተዘነጉ ወይም በጢሞቴዎስ ጥቅም ላይ እየዋሉ ያልሆኑ መንፈሳዊ ስጦታዎቸን መቀስቀስን ያመለክታሉ፡፡ ለእግዚአብሔር "በእግዚአብሔር ምክንያት" እግዚአብሔር የፍርሃትን መንፈስ አልሰጠንም ጳውሎስ ከእግዚአብሔር ዘንድ መንፈስን ተቀብሏል፡፡ በጢሞቴዎስ ላይ እጆቹን በሚጭንበት ጊዜ በጢሞቴዎስ ላይ ተመሳሳይ መንፈስ ያርፍበታል፡፡ ይህ መንፈስ ደግሞ እግዚአብሔር ወይም ሌሎች ሰዎችን እንዲፈራ አያደርገውም፡፡ ራስን የመግዛት መንፈስ አማራጭ ተትርጉሞች “የእግዚአብሔር መንፈስ ራሳችን የመግዛት መንፈስን ይሰጠናል" (UDB) ወይም 2) "የእግዚአብሔር መንፈስ በተሳሳተ መንገድ የሚሄዱ ሰዎችን እንድናስተካክል ያደርገናል፡፡"
ስለዚህ በዚህ አትፈር "ስለዚህ አትፍራ" ወይም "ስለዚህ በፍርሃት አትሞላ" ለወንጌል መከራን ተቀበል ጳውሎስ ትክክል ባልሆነ መልኩ መከራን እየተቀበለ ያለው በወንጌል ምክንያት ነው፡፡ ስለዚህም ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ በተመሳሳይ መልኩ ለወንጌል መከራን ለመቀበል አትፍራ በማለት ይመክረዋል፡፡ እንደ እግዚአብሔር ኃይል "እግዚአብሔር እንዲያጠነክርህ ፍቀድለት" እንደ ሥራችን ሳይሆን "የምንድነው መልካም ራዎችን በሰራንበት መጠን አይደለም፡፡" ወይም "እግዚአብሔር ያዳነን በሠራነው መልካም ሥራ መሠረት አይደለም" ወይም "ምንም እንኳ መጥፎ ስራዎችን የሠራን ቢንሆንም እንኳ እግዚአብሔር አድኖናል" እኛን ያዳነን ማን ነው . . . በእቅዱ መሰረት "እግዚአብሔር እኛን ለማዳን አቅዶ ዘሁን አዳነን" ወይም "እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ወስኗል እነንዲሁም እንዲሁም እንዴት እንደሚያድነን ወስኖ አሁን እኛን አዳነን" ወይም "እኛን ማን አዳነን...በዕቅዱ መሠረት" ጊዜ ከመጀመሩ በፊት "ምድር ከመፈጠሯ በፊት" ወይም "ጊዜ ከመፈጠሩ በፊትn" ጊዜ ይህ ዓለማትን የሚያመለክት ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ የእግዚብሔር ድነት በአዳኛችን ኢየሱስ ክርስቶስ መገለጠ ምክንያት ተገልጧል፡፡ "እግዚአብሔር እኛን እንዴት እንዳዳነን አዳናችን መስሑን በመግለጥ አሳይቶናል፡፡" ሞትን ያጠፋ "ሞት በእኛ ላይ የነረውን ኃይል የሰበረው" በወንጌል አማካኝነት ማብቂያ ያሌለውን ሕይወት ያመጣ "በወንጌል ስብከት አማካኝነት ማብቂ ስላሌለው ሕይወት ያስተማረ" እኔ ሰባኪ ሆኜ ተሾሙክ "መልዕከቱን እሰብክ ዘንድ እግዚአብሔር መረጠኝ"
በዚህ ምክንያት አማራጭ ትርጉም: "ሐዋሪያ በመሆኔ ምንክንያት" እኔም እራሴ በእነዚህ ነገሮች መከራ ይደርስብኛል ጳውሎስ በዚህ ሥፍራ እያመለከተ ያለው የሚደርስበት እስራት ነው፡፡ አምኛለሁ "አምኛለሁ" በዚያ ቀን አማራጭ ትርጉም 1) ጌታ ዳግም በሚመጣበት ቀን ወይም 2) እግዚአብሔር በሕዝቡ ላይ በምፈርድበት ቀን፡፡ ከእኔ የሰማኸውን የእምነት መመሪያ ጠብቅ "ያስተማርኩህን ትክክለኛ ትምህርት ጠብቅ" ወይም "ምን እና እንዴት ማተማር እንዳለብህ ለማወቅ የእኔን ቃላት እና የማስተማሪያ ዘዴ ተጠቀም" እነዚያ መልካም ነገሮችን ይህ ወንጌልን በትክክለኛ መልኩ የመስበክ ሥራን ያመለክታል፡፡ ጠብቀው ሰዎችን ሥራውን ሊቃወሙ ስለሚችሉ ጢሞቴዎ ነቅቶ መጠበቅ ይኖርበታል፣ እንዲሁም ይህን ተግራቸውን እንዲያቆሙ ለማድረግ መጣር ይኖርበታል እንዲሁም የሚናገረውን ነገር እንዳጠፉበት መጠበቅ አለበት፡፡ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት "መንፈስ ቅዱስ እንዲታደረግ የሚነግርህን ነገር ሁሉ እና እርሱን ብቻ አድርግ"
ከእኔ ተለይተው ሄደዋል ስለታሠረ እና በወህኒ ቤት ስለተጣለ ትተውታል፡፡ በሰንሰለቴ አለፈረም ለሄኔሲፎሩ በጳውሎስ መታሠር አላፈረም ብዙ ጊዜም ወደ ወህኒ ቤት እየመጣ ይጠይቀው ነበረወ፡፡ “ሠንሠለት” የመታሠር ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ ምህረትን ያገኝ ዘንድ ሰጠው . . . በዚያ ቀን ጳውሎስ ለሄኔሲፎሩ ፍርድ ሳይሆን ምህረትን እንዲቀበል ይመኛል፡፡ 1) ጌታ ዳግመኛ በሚመጣበት ቀን ወይም 2) እግዚብሔር ሰዎችን ላይ በምፈርድት ቀን፡፡
1 እንግዲህ ልጄ ሆይ በኢየሱስ ክርስቶስ በሆነው ጽጋ በርታ፡፡ 2 ከብዙ ምስክሮች ጋር ከእኔ የሰማኸውን፣ ሌሎችን ሊያስተምሩ ለሚችሉ ለታመኑ ሰዎች አደራ ስጥ፡፡ 3 እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ መልካም ወታደር ሆነህ አብረኸኝ መከራ ተቀበል፡፡ 4 አለቃውን ማስደሰት የሚፈልግ ወታደር በምድራዊው ነገር ራሱን አያጠላልፍም፡፡ 5 ማንም በስፖርታዊ ውድድር የሚሳተፍ፣ በደንቡ መሠረት ካልተወዳደረ የድሉን አክሊል ሊያገኝ አይችልም፡፡ 6 በርትቶ የሚሠራው ገበሬ ምርቱን ከሚበሉት የመጀመሪያው ሊሆን ይገባል፡፡ 7 የምለወን ተመልከት ጌታም በነገር ሁሉ ማስተዋልን ይስጥህ፡፡ 8 በወንጌል መልእክቴ የገለጽኩትን፣ ከሙታን የተነሣውንና ከዳዊት ዘር የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን አስብ፡፡ 9 በዚህም ምክንያት እንደ ወንጀለኛ በመታሰር መከራ እቀበላለሁ፣ ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል አይታሰርም፡፡ 10 ስለዚህ ስለተመረጡት ስል በሁሉ እጸናለሁ፣ እነርሱ በክርስቶስ ኢየሱስ የሆነውን መዳን ከዘላለማዊ ክብር ጋር ያገኙ ዘንድ፡፡ 11 እንዲህ የሚለው ቃል የታመነ ነው ‹‹ከእርሱ ጋር ከሞትን፣ ከእርሱ ጋር እንኖራለን፡፡ 12 ብንጸና ከእርሱ ጋር እንነግሣለን፡፡ ብንከዳው እርሱ ደግሞ ይክደናል፡፡ 13 ባናምነው እርሱ የታመነ ሆኖ ይኖራል፣ ራሱን ሊክድ አይችልምና፡፡ 14 እነዚህን ነገሮች አስታውሳቸው፡፡ በቃል እንዳይጣሉ በእግዚአብሔርም ዘንድ አስጠንቅቃቸው፣ይህ ምንም ጥቅም የሌለው የሚሰሙትንም የሚጎዳ ነው፡፡ 15 የእውነትን ቃል በትክክል የሚይዝ፣ የማያሳፍርም ሠራተኛ ሆነሀ ራስህን በእግዚአብሔር ፊት ለማቅረብ ትጋ፡፡ 16 እግዚአብሔርን ከመምሰል የሚያርቅህን አለማዊ ተረቶቸን አስወግድ፡፡ 17 ቃላቸው እንደ ቆላ ቁስል ነው፣ ከእነርሱም ሄሜኔዎስና ፊሊጦስ ይገኙባቸዋል፣ 18 እነዚህም ሰዎች ከእውነት ርቀው ትንሣኤ ሙታነ ካሁን ቀደም ሆናል ይላሉ፣ በዚህም የአንዳንዶችን እምነት ይገለብጣሉ፡፡ 19 ሆኖም፣ ‹‹ጌታ ለእርሱ የሆኑትን ያውቃል›› ደግሞም ‹‹የጌታን ስም የሚጠራ ከዓመፃ ይራቅ›› የሚለው ማኅተም ያለበት የእግዚአብሔር መሠረት ቆሞአል፡፡ 20 በሀብታም ቤት ውስጥ የሚገኙት የወርቅ እና የብር ዕቃዎች ብቻ አይደሉም ነገር ግን የእንጨት እና የሸክላ ዕቃዎችም ይገኛሉ፣ አንዳንዶቹ ለክብር ሌሎቹም ክብር ለማይሰጣቸው ሥራዎች ይውላሉ፡፡ 21 ማንም ከማያስከብር ሥራ ራሱን ቢያነጻ፣ የተከበረ ዕቃ፣ የተቀደሰ፣ ለጌታውም የሚጠቅም፣ ለማንኛውም መልካም ሥራ የተዘጋጀ ይሆናል፡፡ 22 ከወጣትነት ምኞት ራቅ፣ በንጹህ ልብ ጌታን ከሚጠሩ ጋር ጽድቅን፣ እምነትን፣ ፍቅርን፣ ሰላምን ተከታተል፡፡ 23 ነገር ግን ጠብን እንደሚያመጣ አውቀህ ከሰነፎችና ካልተማሩ ምርመራ ራቅ፡፡ 24 የጌታ አገልጋይ ሊጣላ አይገባውም፣ ከዚሀ ይልቅ ለሁሉ የሚጠነቀቅ፣ ለማስተማርም የሚበቃ በትእግስትም የሚጸና፣ 25 በትህትናም ለሚቃወሙት ትምህርት የሚሰጥ ሊሆን ይገባዋል፡፡ እውነትን በማወቃቸው እግዚአብሔር ምናልባት ንስሐን ይሰጣቸው ይሆናልና፣ 26 እንዲሁም ለዲያብሎስ እና ለፈቃዱ ከተያዙበት ወጥመድ ተላቀው ወደ ኅሊናቸው ሊመለሱ ይችሉ ይሆናል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ የጢሞቴዎስን የክርስትና ሕይወት ከወታደር፣ ከገበሬ ሕይወት እና ከእስፖርተኛ ሕይወት ጋር በማነጻጸር ይጽፋል፡፡ በክርስቶስ ኢየሱስ ባለ ጸጋ በርታ አማራጭ ትርጉሞች 1) "እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት በሰጣችሁ ጸጋ አማካኝነት ያበርታችሁ" (UDB) ወይም 2) " በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት ብቻ የሚገኘው ጸጋን በማወቅ ራሳችሁን አበርቱ፣" ከብዙ ምስክሮች መካከል "የእኔ ቃላት እውነት ስለመሆናቸው ብዙ ሰዎች ምስክር ናቸው" ታማኝ "ታማኝ"
ከእኔ ጋር መከራን ተቀበል አማራጭ ትርጉም 1) "እኔ መከራን እንደሚቀበል መከራን ታገስ" (UDB) ወይም 2) "በእኔ ከራ ውስጥ ተካፈሉ" በራሱ ሕይወት ውስጥ የተዋጠ ወታደር ተገቢውን አገልግሎት መስጠት አይችልም "በሕይወቱ የእለት ተዕለት ተግባራት ውስጥ ብቁ ተሳታፊ የሆነ ወታደር ተገቢውን አገልግሎት መስጠት አይችልም" ወይም "ወታደሮች በግዳጅ ላይ ሲሆኑ ሰዎች በእለት ተዕለት ኑሮዋቸው በሚያደርት ነገር ሀሳባቸው አይሰረቅም፡፡" የክርስቶስ አገልጋዮች የሕይወት የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ለክርስቶስ እንዳይሠሩ ሀሳባቸውን ሊሰርቅ አይገባውም፡፡ እንዳይታነቅ ሌሎች ነገሮችን በመሥራታቸው ምክንያት ከማገልገል የሚከለክል ነገር በመረብ እንደመያዝ ነው፡፤ ከፍተኛ ባለስልጣን "ወታደር እንዲሆን የመለመለው ሰው" አንድ እስፖርተኛ . . . በሕጉ መሠረት ውድድሩን ካላካሄደ ሽልማትን አያገኝም የክርስቶስ አገልጋይ ክርስቶስ አድርጉ ያለውን ነገር ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡ በሕጉ መሠረት ነገሮችን ማከናወን ካልቻለ ሽልማትን ማግኘት አይችልም አማራጭ ትርጉም: "አሸናፊ ሆኖ ሽልማትን ማግኘት የሚችለው በሕጉ መሠረት ውድድሩን ከፈጸመ ብቻ ነው" አይሸለምም "ሽልማቱን አያገኝም" በሕጉ መሠረት ካተወዳደረ "በሕጉ መሠረት ውድድሩን ካላጠናቀቀ" ወይም "ሕጉን በትክክል ካልተከተለ"
ጠንካራ ሠራተኛ የሆነው ገበሬም የሰብሉን ከሚበሉት የመጀመሪ ሊሆን ይገባዋል ይህ ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ የነገረው ሦስተናው ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ አንባቢያን አንድ መገንዘብ ያለባቸው ነገር የክርስቶስ አገልጋዮች ታታሪ ሠራተኞች መሆን አለባቸው፡፡ አሁን ስለሚናገረው ነገር አስቡ ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ ስእላዊ ምሳሌዎችን በመጠቀም ይነግረዋል ነገር ግን የእነዚህ ምስሎች ትርጉም ምን እንደሆነ ግን አይነግረውም፡፡ ስለ ክርስቶስ አገልጋየች አንዚህም ምሳሌዎች በመጠቀም ጳውሎስ እየተናገረ ያለው ምን እንደሆነ ጢሞቴዎስ ራሱ ፈልጎ እንዲያገኝ ይተወዋል፡፡ ለጌታ "በጌታ ምክንያት"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ ለክርስቶስ እንዴት መኖር እንደሚቻል፣ ለክርስቶስ እንዴት መከራን መቀበል እንደሚቻል እና ሌሎች ለክርስቶስ እንዴት መኖር እንዳለባቸው መመሪያዎችን ይሰጠዋል፡፡ በእኔ ወንጌል መልዕክት መሠረት "የእኔ ወንዴል መልዕክ እንደሚለው" እኔ መከራን የሚቀበልበት ምክንያት "እኔ መከራን የሚቀበልለት" በሠልሰለት የታሰርኩት "መታሠር" የእግዚአብሔር ቃል አይታሠርም "አይወሰንም" ወይም "አይታሠረም፡፡" አማራጭ ትርጉም: "ሙሉ ነጻነት አለው" ለተመረጡት ሰዎች "እግዚአብሔር ለመረጣቸው ሰዎች" ድነትን ያገኙ ዘንድ "ድነትን እንዲያገኙ" ከዘላለም ክብር ጋር "እግዚብሔርን ለዘላለም እያመሰገኑ" ወይም "ሰዎችን ወደ እግዚአብሔር ለዘላለም እያመለከቱ"
ይህ አባባል "እነዚህ ቃላት" ሞቷል በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ቃል ያለው ትርጉም አንድ ለራሱ የሞተን ሰው ያመለክታል፡፡ ለራሱ መሻት ያልተገዛን ሰው ያመለክታል፡፡ እኛ ታማኞችን ካልሆንን "እኛ ብንወድቅ እንኳ" ወይም "እግዚአብሔር እንድናድረግ የሚፈልገው ነገር የሚናምነው ነገር ባናደርግ እንኳ" ራሱን ሊክድ ፈጽሞ አይቻለውም "እርሱ እንደ ባሕርይው ልፈጽም የግድ ነው" ወይም "ከእርሱ ባሕርይ ተቃራኒ የሆነ ነገርን ለማድረግ አይችልም"
እነርሱ አማራጭ ትርጉሞች: 1) "መምህራን" (UDB) ወይም 2) "የቤተ ክርስቲያን ሕዝቦች" በእግዚአብሔር ፊት "በእግዚአብሔር መገኘት ውስጥ" ወይም "እግዚአብሔር ይመለከትሃል እንዲሁም ይመለከታቸዋ፡፡" በቃላት አትጣሉ "በቃላት ትርጉም ላይ አትከራከሩ" ወይም "በቃላት ላይ አትጣሉ" ወይም "በቃላት ትርጉምልዩበት ለሌሎች ሰዎችን አትጉዱ" ምንም ትርፍ የለውም "ለማንም ምንም ጥቅም የለውም" ወይም "ጥቅም የለውም" ማበላሸት የሕንጻ ማፍረስ ምሳሌ ነው፡፡ ጥሉን የተመለከቱ ሰዎች የክርስትያኖችን መልዕክት ማክበር ያቆማሉ፡፡ የሚያደምጡ ሰዎች "የሚያደምጡ ሰዎች" ራስህን በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት ያላው ለማድረግ ትጋ "የማያሳፍርም ሠራተኛ ሆነህ፥ የተፈተነውን ራስህን ለእግዚአብሔር ልታቀርብ ትጋ።" እንደ ሠራተኛ "ልክ እንደ ሠራተኛ" ወይም "እንደ ሠራተኛ" በትክክለኛ መንገድ "በትክክል በማብራራት"
ቃሉ ልክ እንደ ጋንግሪን ይሠራጫል "የሚናገሩት ነገር ልክ እንደ በሽታ ይሰራጫል፡፡" ጋንግሪን በሰው ሰውነት ውስጥ በፍጥነት እንደሚሰራጭ እና አካሉን እንደሚያጠፋ ሁሉ እነዚህ ሰዎች የሚናገሩት ነገር ከሰው ወደ ሰው በቀላሉ በመሰራጨት የሰሙትን ሰዎች እምነት ላይ ጉዳት ያደርሳል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ቃላቸው በፍጥነት ይሰራጫል እንዲሁም ልክ እንደ ጋንግሪን ከፍተኛ ጉዳት ያሳድራል" ወይም "የሚሉትን ነገር ሰዎች በፍጥነት ይሰሙታል እንዲሁም በዚህ ንግግር ይጎዳሉ፡፡ ጋንግሪን የሞተ፣ የበሰበበሰ ሥጋ፡፡ ጋንግሪን በሰውነት ውስጥ እንዳይሰራጭ እና ሰውዬውን እዳይገድለው ማድረጊያ ብቸኛው መንገድ የተበከለውን የሰውነት ክፍል ቆርጦ መጣል ነው፡፡ ከእውነት ርቀዋል ይህ እነዚህን ትርጉሞች ሊኖሩት ይችላል 1) "ስለ እውነት ተሳስተዋል" ወይም "ስለ እውነት በስህተት ውስጥ ናቸው፣" ዒላዋን እንደ ሳተ ቀስት ወይም 2) "በእውነት ማመን አቁመዋል፡፡" ትንሳዔ ...ሆኗልd "እግዚአብሔር የሞቱ አማኞችን ወደ ዘላለማዊ ሕይወተ አስነስቷቸዋል" የአንዳንዶችን እምነት ይገለብጣሉ "የአንዳንድ አማኞቸን እምነት ጥርጣሬ ውስጥ ይጥላሉ" ወይም "አንዳንድ አማኞች ማመናቸውን እንዲያቆሙ በማሳመን"
የእግዚአብሔር መሠረት አማራጭ ትርጉሞች 1) "እግዚአብሔር ከመጀመሪያው አንስቶ የመሠረታት ቤተ ክርስቲያን" ወይም 2) "ስለ እግዚአብሔር ያለ እውነት" (UDB) ወይም 3) "የእግዚአብሔር ታማኝነት፡፡" የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ "በክርስቶስ እንደሚያምኑ የሚነገሩ ሰዎች" ከእምነት ተለይተው የወጡ አማራጭ ትርጉም 1) "ክፉ መሆንን ማቆም" ወይም 2) "ትክክለኛ ያልሆነ ነገር ማድረግን ማቆም፡፡" መሣሪያዎች ይህ ሰዎች ምግብ ዌም መጠጥ በውስጡ የሚያስቀምጡባቸውን ጎድጓዳ ሳህኖች፣ ሳህኖች እና ድስቶች መጠሪያነት የሚውል አጠቃላይ ቃል ነው፡፡ በቋንቋችሁ ከዚህ ጋር ተመሳሰይ የሆኑ አጠቃላይ ቃል ካሌለ ያለውን ተጠቀሙ፡፡ ይህ ለሰዎች በዚህ ሥፍራ ላይ ጥቅም ላይ የዋለ ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ ለክብር . . . ውርደት አማራጭ ትርጉሞች 1) "ልዩ ሁኔታዎች ...በተለመዱት ጊዜያት" (UDB) ወይም 2) "መልካም የሆኑ ሰዎች የሚያከናውኗቸው የተለያዩ ተግባራት...መልካም የሆኑ ሰዎች በድብቅ የሚያከናውነዋቻ ተግባራት፡፡" ራሱን ለውርደት ጥቅም ለላይ ከመዋል ያነጻል አማራጭ ትርጉሞች 1) "ራሱን ከወራዳ ሰዎች ይለያል" ወይም 2) "ራሱን ንጹሕ ያደርጋል፡፡" የተከበተ ዕቃ "በልዩ ሁኔታዎች ጠቃሚ የሆኑ" ወይም "መልካም ሰዎች በአደባባይ ለሚያደርጓቸው ነገሮች የሚጠቅሙ"
ሽሽ . . . ተከተል እነዚህ ምሳሌያዎ ንግግሮች የሚያመለክቱት በተቻለው ፍጥነት መሮጥን ነው፡፡ መሸሽ የሚያመለክተው ከሚጎዳ ነገር ማምለጥን ነው፤ መከታተለ ደግሞ መልካም የሆነ ነገር ለማግኘት የሚደረግ ጥረትን ያመለክታል፡፡ (ተመልከት:.) ከወጣትን መሻቶች ሽሽ ልክ ሰዎች ጥቃት ሊያደርስባቸው ከሚችል እንስሳት እንደሚሸሽ ሁሉ “ወጣቶችን ከሚፈታቱ ነገሮች ሽሽ"፡፡ በቋንቋችሁ “መሻት” የሚለው ቃል በስም ማስቀመጥ የማይቸል ከሆነ “ወጣቶች አዘውትረው ለማድረግ ከሚፈልጓቸው ነገሮች መሸሽ” በማለት መተርጎም ትችላላችሁ፡፡ ጽድቅን ተከታተሉ "ጽድቅን መፈለግ" ጋር አማራጭ ትርጉሞች 1) "ከ . . . ጋር" ትርጉሙ “ጽድቅን በመፈለግ ሂደት ውስጥ ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር በመተባበር" ወይም 2) "ከ . . . ጋር ሆናችሁ" ትርጉሙ “ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር ሰላም ለመሆን የሚትችሉትን ሁሉ አድርጉ፡፡" እነርሱ ወወደ ጌታ የሚጠሩት "ክርስትያኖች" ወይም "የጌታ ሰዎች ብለው ራሳቸውን የሚጠሩት ሰዎች" ከንጹሕ ልብ "በንጹሕ መነሻ ሀሳብ" ወይም "ለመልካም ምክንያቶች" የሞኝ እና ያላዋቂ ጥያቄዎችን የሞኝ እና የማያውቁ ሰዎችን ጥያቄዎችን መልስ አትስጥ" ሞኞች … ጥያቄዎች "ለእግዚአብሔር ምንም ክብር ያሌላቸው ዎች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎች" የማያውቁ ሰዎች ጥያቄዎች "እውነትን ማወቅ የማይፈልጉ ሰዎች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎች"
ትዕግስት "ታጋሽ" ወይም "ትሁት" ማስተማር "ማስተማሪ" ወይም "ትምህርት መስጠት" ወይም "ማስተካከል" ንሰሓ እንዲሰጣቸው "ከኃጢአታቸው እንዲመለሱ" ለእውነት እውቀት ሲባል "እውነትን ያውቁ ዘንድ" ወደ አእምሮዋቸው ይመለሱ ዘንድ "ከእንግዲህ ወዲህ ትክክለኛ ያልሆነ ነገርን እንዳያስቡ" ወይም "እንደገና ስለ እግዚአብሔር ማሰብ ይጀምሩ ዘንድ" የዳቢሎስ ወጥመድ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር የሚያመለክተው በትክክለኛው መንገድ ሴጣንን እየተከተሉ ሳለ እግዚብሔትን የሚከተሉ ለሚመስላቸው ሰዎች ነው፡፡ ለእርሱ ፈቃድ ሲባል በእርሱ የተያዙ ሰዎች "የያዛቸው ሰዎች እና አሁን እርሱ የሚፈልገውን ነገር ሁሉ እንዲሠሩ የሚያደርጋቸው"
1 ነገር ግን ይህን እወቅ፣ በመጨረሻዎቹ ቀናት አደገኛ ዘመን ይመጣል፡፡ 2 ሰዎች ራሳቸውን የሚወዱ ይሆናሉ፣ ገንዘብን የሚወዱ፣ ትእቢተኞች፣ ትምክህተኞቸ፣ በእግዚአብሔር ላይ የስድብን ቃል የሚናገሩ፣ ለወላጆቻቸው የማይታዘዙ፣ የማያመሰግኑ፣ ቅድስና የሌላቸው፣ 3 ተፈጥሮአዊ ፍቅር የሌላቸው፣ ሰላምን የማይፈጥሩ፣ ሐሜተኞች፣ ራሳቸውን የማይገዙ፣ አመጸኞች፣ መልካም የሆነውን የማይወዱ፣ 4 ከዳተኞች፣ ምክርን የማይሰሙ፣ በትእቢት የተነፉ፣ ከእግዚአብሔር ይልቅ ተድላን የሚወዱ ይሆናሉ፡፡ 5 እግዚአብሔርን የመምሰል መልክ አላቸው ነገር ግን ኃይሉን ይክዳሉ፣ ከእነዚህ ሰዎች ራቅ፡፡ 6 ከእነዚህም አንዳንዶች በቤተ ሰብ ውስጥ ሾልከው እየገቡ በኃጢአት የሚገረሙትንና በልዩ ልዩ ምኞትም የሚነዱትን ሞኞችን ሴቶች ይማርካሉ፡፡ 7 እነዚህ ሴቶች ሁል ጊዜ አዳዲስ ነገሮችን ለመማር ይሞክራሉ፣ ነገር ግን ፈጽሞ ወደ እውነት እውቀት ሊደርሱ አይችሉም፡፡ 8 ኢያኔስ እና ኢያንበሬስ ሙሴን እንደተቃወሙት፣ እነዚህ የስህተት አስተማሪዎች እውነትን ይቃወማሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች አዕምሮአቸው የተበላሸባቸው፣ የእምነታቸውም እውነተኝነት ያልተረጋገጠ ነው፡፡ 9 ዳሩ ግን የእነዚያ የሁለቱ ሰዎች ሞኝነት እንደተጋለጠ፣ እነዚህም ሞኝነታቸው ይገለጣልና አይሳካላቸውም፡፡ 10 አንተ ግን ትምህርቴን፣ አካሄዴን፣ ዓላማዬን፣ እምነቴን፣ መጽናቴን፣ ፍቅሬን፣ ትእግስቴን፣ 11 ስደቴን፣ መከራዬን፣ በአንጾኪያ፣ በኢቆንዮን እና በልስጥራን የደረሰብኝን ሁሉ ተከትለሃል፡፡ ይህን ሁሉ ስደት በጽናት አልፌዋለሁ፣ ጌታም ከሁሉ አዳነኝ፡፡ 12 በክርስቶስ ኢየሱስ እግዚአብሔር እንደሚወደው ሊኖሩ የሚፈልጉ ሁሉ ይሰደዳሉ፡፡ 13 ከፉ ሰዎች እና አታላዮች በክፋት እየባሱ ሌሎችንም እያሳቱና ራሳቸውም ችየሳቱ ይሄዳሉ፡፡ 14 አንተ ግን በተማርህበትና በምታምንበት ነገር ጸንተህ ኑር፣ ከማን እንደተማርከው ታውቃለህና፡፡ 15 ከሕፃንነትህ ጀምሮ በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን ስለሚገኘው መዳን ጥበብ ሊሰጡህ ስለሚችሉት ቅዱሳት መጻሕፍት አውቀሃል፡፡ 16 በእግዚአብሔር የተገለጡ ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ ለመሠረተ እምነት፣ በእምነትም ለመጽናት፣ በጽድቅም ላለው ምክር ይጠቅማሉ፣ 17 በመሆኑም የእግዚአብሔር ሰው ለመልካም ሥራ የተዘጋጀ እና የታጠቀ እንዲሆን ያደርጉታል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ በመጨረሻው ዘመን ሰዎች በእውነት ላይ ፊታቸውን እንደሚያዞሩ ጢሞቴዎስ እንዲያውቅ ፈልጓል እንዲሁም ስደት እንደሚመጣም እንዲያውቅ ፈልጓል ይሁን እንጂ በዚህ ሁሉ ውስጥ በእግዚአብሔር ቃል ላይ መደገፍ ይችላል፡፡ በአደገኛ ጊዜያት ይህ ክርስትያኖች አደገኛ ሁኔታ ውስጥ የሚሆኑባቸውን ቀናትን፣ ወራትን ወይም እንዲያውም ዓመታትን ሊያመለክት ይችላል፡፡ የእነርሱ ወዳጆች በዚህ ሥፍራ ላይ “ወዳጆች” የሚለው ቃል ትርጉሞ ወንድማዊ ፍቅር ወይም የጓደኛ ፍቅር ወይም የቤተሰብ አባላት ፍቅር ሊሆነ ይችላል፡ በተፈጥሮአዊ ሰው መካከል ያለ የጓደኛማቾች ወይም የዘመዳማቾች ፍቅርም ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ ከእግዚአበብሔር ዘንድ የሚመታውን ዓይነት ፍቅር አይደለም፡፡ መመካት ስለ ራሱ በኩራት የሚናገር ሰው፡፡ ከተፈጥሮአዊ ፍቅር ውጪ "ቤተሰባቸውን የማይወዱ" የማይስማሙ "ከማንም ጋር የማይስማሙ" ወይም "ከመማንም ጋር በሰላም የማይኖሩ" ተሳዳበቢዎች "በሐሰት የሚከሱ" ተደባዳቢዎች "ግልፍተኞች" ወይም "ሌሎች ሰዎችን የሚጎዳ ነገር ብዙ ጊዜ የሚያደርጉ" መልካም ነገር የማይወዱ "መልካ ነገር የሚጠሉ"
ከዳተኞች "የማይታመኑ" ችኩሎች "ከሌሎች ሰዎች እነርሱ የተሻሉ እንደሆኑ የሚያስቡ"
የአምልኮ መልክ ያላቸው "ሃይማኖተኛ የሚመስሉ" ወይም "ቅዱሳን የሚመስሉ " ወይም "መልካም የሚመስሉ" ኃይሉን ግን ክደዋል አማራጭ ትርጉሞች 1) "እግዚአብሔር በእውነት ሊሰጣቸው የሚፈልገውን ኃይል ለመቀበል ፈቃደኞች አይደሉም" (UDB) ወይም 2) "አለን ብለው የሚናገሩትን መልካምነት በሕይወታቸው ውስጥ አይታይም፡፡" ከእነዚህ ራቅ "ራቅ" ሾልከው ከገቡት "ሾልከው ወደ . . . ከገቡት" ወደ ቤት አማራጭ ትርጉም 1) "ቤተሰብ" ወይም "በቤት ውስጥ የሚኖሩ ቤተሰብ" ወይም 2) “ቤት” ቁሳዊ (UDB). መማረክ "ተጽእኖ ለማድረግ ኃይል ያላቸው" ሞኝ ሴቶችን "በመንፈሳዊ ነገር ደካሞች የሆኑ ሴቶችን፡፡" ይህ የሆነበት ምክንያት እግዚአብሔርን ለመምሰል ባለመስራታቸው ወይም ሥራ ፈቶች በመሆናቸው ምክንያት ወይም “በኃጢአት በመዋጣቸው” ምክንያት ሊሆን ይችለል፡፡ በኃጢአት የተዋጡት አማራጭ ትርጉሞች 1) "በብዙ ኃጢአት የተዋጡት" ወይም 2) "ብዙ ጊዜ ኃጢአት የሚያደርት ሰዎች፡፡" ሀሳቢ ኃጢአት ለማድረግ ለማቆም አልቻሉም፡፡ በተለያዩ መሻቶች ተመርተው የተወሰዱት አማራጭ ትርጉም: "እነዚህ ሴቶች ሌሎች ብዙ መሻቶች አሏቸው ስለዚህም ክርስቶስን መታዝ አቁመዋል፡፡ ወይም "እነዚህ ሴቶች ክርስቶስን መታዘዝነአቁመዋል ይልቁንም ብዙ መሻታቸውን መከተል ጀምረዋል፡፡" እውቀት የዚህ ቃል ትርጉሚ ስለ አንድ ሰው የሚታውቀው ያንን ሰው ለብዙ ጊዜ በጥንቃቄ ስትከታተለው ነው፡፡
ኢያኔስና ኢያንበሬስም እነዚህ ሁለት ስሞች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙት በዚህ ሥፍራ ላይ ብቻ ነው፡፡ አንድ ትውፊት እነዚህ ሰዎች በዘጸአት 7-8 ውስጥ የተጠቀሱት ሙሴን የተቃወሙት ግብጻዊያን ምትሃተኞች እንደሆኑ ይናገራል፡፡ (ተመልከት:.) ተቃወሙት "ተቃወሙት" ስለዚህም "በተመሳሳይ መልኩም" እውነት "የኢየሱስ ወንጌል" በአእምሮ የተበከሉ "ከእንግዲህ በትክክል ማሰብ የማይችሉ" ከፊት ይልቅ "በተሻለ" ሞኝነት "የመረዳት ችግር" ወይም "ሞኝ" የታወቀ "በቀላሉ የሚታይ" ወይም "በቀላሉ የሚታወቅ"
ነገር ግን አንተ ተከታተላቸው "ይሁን እንጂ አንተ በጥንቃቄ ተመልከት" ትምህርት "መመሪያ" ተግባር "የሕይወት መንገድ" ዓላማ "መፍትሔ" ወይም "ውሳኔ" መከራን መቋቋም "ከሰዎች ጋር መታገስ" ትዕግስት አማራጭ ትርጉሞች 1) "ከባድ በሆነበት ጊዜ እንኳ ሳይቀር እግዚአብሔርን አገለግላለሁ" (UDB) ወይም 2) "በከባድ ሁኔታዎች ውስጥ እንኳ ትክክለኛ አመለካከትን እጠብቃለሁ፡፡" መታደግ "መዳን" ፈለገ "መሻት" አታላዮች "ስለራሳቸው ሌሎች ሰዎችን የሚያሳስቱ ሰዎች" ወይም "ከሆኑት ውጪ ሌላ እንደሆኑ የሚያስመስሉ ሰዎች"
በተማሪከው ነገር ቀጥል "የተማርከውን ነገር አትርሳ፡፡" ጠቢብ እንዲትሆን የሚያደርጉህ ቅዱሳት መጻሕፍት "የእግዚአብሔር ቃል የሚያስፈልግህን ሁሉ ጥበብ ይሰጡሃል" በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት የሚገኘውን ድነት "እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ያለህን እምነት አንተን ለማዳን እንዲጠቀምበት፡፡” ድነት አማራጭ ትርጉም 1) "እግዚአብሔር ዘላለማዊ ሕይወትን ይሰጥሃል" ወይም 2) "እግዚአብሔር በዚህች ሕይወት ውስጥ ካለ ሞኝነት ያድንሃል፡፡"
ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ በእግዚአብሔር እስትንፋስ የተጻፉ ናቸው "እግዚአብሔር ቅዱሳት መጽሐፍትን ሁሉ በመንፈሱ አማካኝነት ተናግሯቸዋል፡፡" (UDB) ወይም "ቅዱሳት መጽሐፍት ሁሉ የእግዚአብሔር እስትንፋስ አለባቸው፡፡ ሰዎች ምን መጻፍ እንዳለባቸው እግዚአብሔር ነግሯቸዋል፡፡ ጠቃሚዎች ናቸው "ይጠቅማሉ" ወይም "ጠቃሚዎች ናቸው" ለተግሳጽ "ሰስህተትን ለማቅናት" ለማስተካከል "ስህተትን ለማስተካከል" ለማሰልጠን "ለማለማመድ" ወይም "ለማሳደግ" ሙሉ ሰው ለማድረግ "ለመሙላት"
1 በእግዚአብሔር ፊት፣ በሕያዋንና በሙታን ሊፈርድ ባለው በክርስቶስ ኢየሱስ ፊት፣ በመገለጡና በመንግስቱ፣ አዝዝሃለሁ፣ 2 ቃሉን ስበክ ሲመችህም ሳይመችህም የተዘጋጀህ ሁን፡፡ እየታገስክና እያስተማርክ ዝለፍ፣ ገስጽ፣ ምከርም፡፡ 3 ሰዎች እውነተኛውን ትምህርት የማይታገሱበት ዘመን ይመጣል፣ ይልቁን፣ ለፍላጎታቸው የሚስማማቸውን የሚሰብኩአቸውን አስተማሪዎችን በዙሪያቸው ይሰበስባሉ፡፡ ይህም ጆሮቻቸውን የሚያሳክክላቸው ይሆናል፡፡ 4 ጆሮቻቸውን እውነትን ከመስማት ይመልሳሉ፣ ወደ ስህተትም ያዘነብላሉ፡፡ 5 አንተ ግን፣ በነገር ሁሉ የነቃህ ሁን፣ መከራን ተቀበል፣ የወንጌላዊነትን ሥራ አድርግ፣ አገልግሎትህንም ፈጽም፡፡ 6 እኔ እንደ መስዋዕት ልሰዋ ነው፡፡ የምሄድበትም ጊዜ ደርሶአል፡፡ 7 መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ፣ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፣ እምነቱንም ጠብቄአለሁ፡፡ 8 የጽድቅም አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፣ ይህንንም ጻድቅ ፈራጅ፣ የሆነው ጌታ፣ በዚያን ቀን ለእኔ ያስረክባል፣ ለእኔ ብቻ አይደለም፣ ነገር ግን መገለጡን ለሚወዱ ሁሉ ነው፡፡ 9 ወደ እኔ በቶሎ ልትመጣ ትጋ፣ 10 ዴማስ ትቶኛልና፣ ይህንንም ዓለም ወድዶ ወደ ተሰሎንቄ ሄዶአል፡፡ ቄርቂስ ወደ ገላትያ፣ ቲቶም ወደ ድልማጥያ ሄደዋል፡፡ 11 ሉቃስ ብቻ ከእኔ ጋር አለ፡፡ ማርቆስን ይዘኸው ና እርሱ በሥራው እጅግ ይጠቅመኛል፡፡ 12 ቲኪቆስን ወደ ኤፌሶን ልኬዋለሁ፡፡ 13 ስትመጣ በጢሮአዳ የተውኩትን ልብሴን፣ ይልቁንም በብራና የተጻፉትን መጻሕፍት ይዘህልኝ ና፡፡ 14 መዳብ አንጥረኛው አሌክሳንደር እጅግ ከፋብኝ፡፡ ጌታ ስለ ክፉ ሥራው ዋጋውን ይከፍለዋል፡፡ 15 አንተም ደግሞ ከእርሱ ተጠበቅ፣ ቃላችንን እጅግ ተቃውሞአልና፡፡ 16 በፊተኛው የፍርድ ቤት ክርክሬ ከአኔ ጋር ማንም አልቆመም፣ ነገር ግን ሁሉም ተዉኝ፡፡ ይህንንም አይቁጠርባቸው፡፡ 17 ነገር ግን፣ አሕዛብ ሁሉ እንዲሰሙት፣ የወንጌሉ ስብከት በእኔ እንዲፈጸም፣ ጌታ በአጠገቤ ቆሞ አበረታኝ፣ ከአንበሳም አፍ ዳንኩኝ፡፡ 18 ጌታ ከክፉ ሥራዎች ሁሉ አውጥቶኛል፣ ለሰማያዊውም መንግሥቱ ይጠብቀኛል፡፡ ለእርሱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ይሁን፡፡ አሜን፡፡ 19 ለጵርስቅላና ለአቂላ ለሄኔሲፎሩ በተ ሰብ ሰላምታ አቅርብልኝ፡፡ 20 ኤርስጦስ በቆሮንቶስ ቀረ፣ ነገር ግን ጥሮፊሞስ ስለታመመ በሚሊጢን ተውኩት፡፡ 21 ከክረምት በፊት ልትመጣ ትጋ፡፡ ኤውግሎስና ጱዴስ፣ ሊኖስና ቅላውዲያም ወንድሞች ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡልሃል፡፡ 22 ጌታ ከመንፈስህ ጋር ይሁን፡፡ ጸጋ ከአንተ ጋር ይሁን፡፡ አሜን፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ጢሞቴዎስ ታማኝ ሆነ እንዲቀጥል ያሳስበዋ እንዲሁም ጳውሎስ ለመሞት ዝግጁ እንደሆነ ያስረዳዋል፡፡ በእግዚአብሔር እና በክርስቶስ ኢየሱስ ፊት "በእግዚአብሔር እና በክርስቶስ ኢየሱስ መገኘት ውስጥ፡፡ እንዴት UDB ይህንን ዓረፍተ ነገር ጥቅም ላይ እንዳዋለው እና እንዳስተካከለው ተመልከት፡፡ ልፈረድ ያለው "በቅርቡ ለመፍረድ የሚመጣው" አጥብቀህ "ጠንከር አድርገህ" ወይም "ጫን ብለህ" ወይም "በእያንዳንዱ ቃል ትርጉም" ይህ ሳይሆን ሲቀር "ይህ ተስማሚ ሳይን ሲቀር" ዝለፍ "ሰዎች በደለኞች ሲሆኑ ንገራቸው" ወይም "ሰዎች የሰሩት ስህተት ምን እንደሆነ አስታውቃቸው" ገስጽ "አስጠንቅቅ" በጽናት አስተምር አማራጭ ትርጉሞች 1) ይህ ጢሞቴዎስ እንዴት ሰዎችን ያበረታታ እንደነበር ያሳያለል ወይም 2) ይህ ጢሞቴዎስ እንዴት ማስተማር እንዳለበት ያሳያል ወይ 3) ይህ ጢሞቴዎስ በመጨረሻው ዓረፍተ ነገር ውስጥ ሁሉን ነገር እንዴት ማድረግ እንዳለበት ያሳል፡፡ በጽናት "በትዕግስት" በጽናት ሁሉ "በታላቅ ጽናት" ወይም "በጣም በመታገስ"
ጊዜ ይመጣልና "ለወደፊት . . . ጊዜ ይመጣልና" ሰዎች አውዱ እንደሚያሳየው እነዚህ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉ ሰዎች ናቸው (UDB)፡፡ ትክክለኛ ትምህርት ይህ አጠቃላይ ቤተ ክርስቲያን እውነተኛ እና ትክክለኛ ብላ የሚትቀበለው ማለት ነው፡፡ ከእነርሱ ፍላጎት ጋር ተስማሚ የሆነ ትምህርትን ከሚያስተምህሩ መምህራን ጋር ይሆናሉ፡፡ በዚህ መልኩ ጆራቸውን ያኩላቸዋል፡፡ አማራጭ ትርጉሞች 1) ከግል ፍላጎታቸው የተነሣ ለመስማት የሚፈልጉትን ነገር በሚነግሯቸው መምህራን ዙሪያ ይሰበሰባሉ፡፡ ወይም 2) ከእነርሱ የግል ፍላጎት ጋር ከሚስማሙ መምህራን ዙሪያ ይሰበሰባሉ እነርሱም የሚፈልጉትን በጆሮዋቸው ይነግሯቸዋል፡፡ ለራሳቸው መሻት "የግል ፍላጎታው" ጆሮዋቸውን ያኩላቸዋል "እነዚህ መምህራን ጆሮዋቸውን ያኩላቸዋል፡፡" "ጆሮዋቸውን ማከክ" ምሳሌያዊ አነጋገር ሲሆን የሚያሳየው መስማት የሚያስደስታቸውን ፣ ደስተኞች እንደሆኑ የሚያደርጋቸውን ነገር መናገር ማለት ነው፡፡ የወንጌላዊነት ሥራ ይህ ማለት ኢየሱስ ማን እንደሆነ፣ ለእነርሱ ምን እንዳደረግ እና ለእርሱ እንዴት መኖር እንዳለባቸው ለሰዎች መናገር ማለት ነው፡፡ አገልግሎት ስለ እግዚአብሔር እነርሱን በማስተማር እነርሱን በመንሳዊ ነገር ማገልገል ማለት ነው፡፡
ከአንተ የሚለይበት ጊዜ ተቃርቧል "በቅርቡ እሞታለሁ፣ ይህችንም ምድር ትቼ እሄዳለሁ" (UDB)፡፡ ጳውሎስ ከእንግዲህ በኋላ ለረጅም ጊዜ እንደማይኖረ አውቆዋል፡፡ ሩጫዬን በተገቢው ሁኔታ አጠናቅያለሁ ይህ የድብድብ፣ የትግል ወይም የቡጥ እስፖርታዊ ምሳሌ ነው፡፡ ጳውሎስ የሚችለውን ሁሉ አድርጓል፡፡ ይህ “የሚችለውን ሁሉ ጥረት አድርጌያለሁ” ወይም “ያቅሜን ያህለ አድርጌያለሁ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ሩጫዬን ጨርሻለሁ ይህ ምሳሌያዊ ንግግር የሚያሳየው በሩጫ ውድድር ላይ የመጨረሻ መስመር ላይ መድረስን ከሕይወት ፍጻሜ ጋር በማነጻጸር ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ማድረግ የሚገባኝነት ነገር ጨርሼያለሁ፡፡ እምነትን ጠብቄያለሁ አማራጭ ትርጉሞች 1) "የሚናምነውን ነገር ከስህተት ጠብቄያለሁ" ወይም 2) "አገልግሎቴን በታማኝነት ጨርሼያለሁ" (UDB). የጽድቅ አክልል ለእኔ ተቀምጦልኛል አማራጭ ትርጉም: "የትድቅ አክልል ይሰጣኛል" የጽድቅ አክሊል አማራጭ ትርጉሞች 1) አክሊል እግዚአብሔር በትክክለኛ መንገድ ለኖሩ ሰዎች የሚሰጠው ሽልማት ነው፡፡ (UDB) ወይም 2) አክሊል ለጽድቅ ምሳሌ ነው፡፡ የውድድር ዳኛው ለአሸናፊው አክሊል እንደሚሰጠው ሁሉ ጳውሎስ ሕይወቱን አጠናቆ ሲሄድ እግዚአብሔር ጳውሎስን ጸድቅ ብሎ ይጠራዋል፡፡ አክሊል የሩጫ ውድድርን አሸንፈው ለሚገቡ ሮሯጮች የሚሰጥ ከወይራ ቅጠል የሚሠራ አክሊል ነው፡፡ በዚያ ቀን "ጌታ ዳግም በሚመጣት ቀን" ወይም "እግዚአብሔር ሕዝቡ ላይ በሚፈርድበት ቀን"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: በመዝጊያውም ጳውሎስ ጢሞቴዎስ ወደ እርሱ ዘንድ እንዲመጣ ያበረታታዋል፡፡ እንዲሁም ሉቃስንም ከእርሱ ጋር ይዞት እንዲመጣ፣ ከጌታ ፊታቸውን ያዞሩ ሰዎችን ስም ዝርዝር ይነግራል በመጨረሻም ከጢሞቴዎስ ጋር ላሉት ሰዎች ሰላምታውን እንዲያቀርብለት ይጠይቀዋል፡፡ በፍጥነት "በተቻለ ፍጥነት" ምክንዬት ስለዚህ አሁን ያለችው ዓለም አማራጭ ትርጉሞች 1) የዚህ ዓለም ጊዜያዊ ነገር፣ "የዚህች ዓለም ምቾት እና ደስታ፣" ወይም 2) አሁን ያለው ሕይወት እና መሞት የሚሻለው፡፡ ዴማስ ከጳውሎስ ጋር ከቆየሁ ይገሉኛል ብሎ ፈርቶ ሊሆነ ይችላል፡፡
ቄርቂስም ወደ ገላትያ ቲቶም ወደ ድልማጥያ ሄደዋል፤ እነዚህ ሁለት ሰዎች ጳውሎስን ትተውት ደዋል ነገር ግን ጳውሎስ እነዲህም ልክ እንደ ዴማስ “ይህንን ዓለም ወደዋል” እያለ አይደለም፡፡
እርሱ በሥራ ለእኔ አጋዤ ነው አማራጭ ትርጉሞች 1) "በአገልግሎት ሊያግዘኝ ይችላል" ወይም 2) "እኔን በመርዳት ሊያገለግለኝ ይችላል፡፡"
በእኔ ላይ መጥፎ ነገር አድርጓል "ክፉ ነገር አድርጎብኛል" ወይም "ጎድቶኛል" አንተም ተጠንቀቀው "አንተም ቢትሆን እርሱን ልትጠነቀቅ ይገባሃል" ወይም "ከእርሱ ራስህን ጠብቅ" ወይም "ከእርሱ ራስህን ጠብቅ" እርሱ . . . እርሱ . . . እርሱ . . . እርሱ ሁሉም የሚያመለክቱት እስክንድሮስ ነው፡፡ የምንናገረውን እጅግ ተቃውሞአልና። "መልዕክታችንን ለመቃወም በከፍተኛ ሁኔታ ተነሥቷል" ወይም "መልዕክታችንን ይቃወማል" ከእኔ ጋር የቆመ አንዳችም ሰው የለም ሁሉም ትተውኝ ሄደዋል "ከእኔ ጋር የቆ ማንም ሰው የለም ይልቁንም ሁሉም ትተውኝ ሄደዋል፡፡" ይህንም አይቍጠርባቸው፤ "እነዚህ አማኞች እኔን ለብቻዬ ትተውኝ በመሄዳቸው እግዚአብሔር እንዲቀጣቸው አልፈልግም"
ከእኔ ጋር ቁም "እኔን ለማገዝ ከእኔ ጋር ቁም" የስብከቱ ሥራ በእኔ እንዲፈጸም አሕዛብም ሁሉ እንዲሰሙት አማራጭ ትርጉሞች 1) ይህ እየሆነ ያለ ነገር ነው (UDB) ወይም 2)ይህ ለጳውሎስም ቢሆን ለወደፊት የሚሆን ነገር ነው፣ "ቃሉን ሙሉ ለሙሉ መናገር እችል ዘንድ እና አሕዛብ ሁሉ ይሰሙ ዘንድ፡፡" ከአንበሳ አፍም ዳንሁ። ይህ አደጋ አካላዊ፣ መንፈሳዊ ወይም ሁለቱም ልሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ከታላቅ አደጋ ተረፍኩኝ፡፡"
ኖት የለውም።
1 የእግዚአብሔር ባሪያና፣የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነው ጳውሎስ፣ በእግዚአብሔር የተመረጡት ሰዎች እምነት እንዲጸና፣ እግዚአብሔርን ከመምሰል ጋር የሚስማማውን የእውነት እውቀት ለማፅናት፣ 2 የማይዋሽ እግዚአብሔር፣ በተረጋገጠ ዘላለማዊ ሕይወት ከዘመናት በፊት ተስፋን ሰጠ፣ 3 እንደ መድሃኒታችን እግዚአብሔር ትዕዛዝ፣ በትክክለኛው ጊዜ፣ ቃሉን ለእኔ አደራ በሰጠኝ መልዕክት ገለጠ፡፡ 4 የጋራችን በሆነ እምነት እውነተኛ ልጄ ለሆነ ለቲቶ። ከእግዚአብሔር አብ፣ከመድሃኒታችን ክርስቶስ ኢየሱስ ፀጋ፣ምህረትና ሰላም ለአንተ ይሁን። 5 አንተን በቀርጤስ የተውኩበት ምክንያት፣ ያልተጠናቀቁትን ነገሮች እንድታስተካክልና፣ በነገርኩህ መሠረት በየከተማው ሁሉ ሽማግሌዎችን እንድትሾም ነው፡፡ 6 የቤተክርስቲያን ሽማግሌ፣ ነቀፋ የሌለበት፣የአንዲት ሚስት ባል፣ ከክፍዎችና ካልታረሙ ጋር ስማቸው የማይነሳ ታማኝ ልጆች ያሉት ሊሆኑ ይገባዋል። 7 የቤተክርስቲያን ሽማግሌ የእግዚአብሔርን ቤት የሚያስተዳድር መሪ ስለሆነ ነቀፋ የሌለበት፣ የማይጮህ፣ራሱን የሚገዛ ፣የማይቆጣ ፣ለወይን ጠጅ የማይገዛ፣ የማይጣላና ስስታም ያልሆነ ሊሆን ይገባል። 8 ነገር ግን እንግዳ ተቀባይ፣ መልካምን የሚወድ፣ ጠንቃቃ፣ ጻድቅ፣ መንፈሳዊና ራሱን የሚገዛ መሆን አለበት። 9 በጤናማ ትምህርት ሌሎችን ለማበረታታት፣ የሚቃወሙትን ለመገሠጽ እንዲችል እውነተኛውን ትምህር አጥብቆ መያዝ ይኖርበታል። 10 ሥርዓት የሌላቸው በተለይም ከተገረዙት ወገን የሆኑ ብዙዎች አሉ። ቃላቸው ከንቱ ነው። ሰዎችን ያስታሉ፣ በተሳሳተ መንገድም ይመራሉ። 11 እነዚህን ዝም ማሰኘት ይገባል። ለነውረኛ ትርፍ ብለው ማስተማር የማይገባቸውን እያስተማሩ፣ መላ ቤተሰብን ያፈርሳሉ። 12 ከነሱ ከራሳቸው ነብያት መካከል አንዱ፣ "የቀርጤስ ሰዎች ዘወትር ውሸተኞች፣ ክፉና አደገኛ አውሬዎች፣ ሰነፍ ሆዳሞች ናቸው" ብሏል፡፡ 13 ይህም አባባል ትክክል ነው፣ ስለዚህ ጤነኛ እምነት እንዲኖራቸው አጥብቀህ ገሥጻቸው ። 14 ጊዜያቸውን በአይሁድ ተረትና፣ ከእውነት በራቁ ሰዎች ትዕዛዛት ላይ አያባክኑ። 15 ንጹሆች ለሆኑት፣ ሁሉም ንጹህ ነው፣ ለርኩሶችና ለማያምኑ ግን ንጹህ የሆነ ምንም የለም። ይልቁን፣ አዕምሯቸውና ሃሳባቸው እንኳ የረከሰ ነው፡፡ 16 እግዚአብሔር እንደሚውያቁ ይናገራሉ፣ በሥራቸው ግን ይክዱታል። የሚያስጸይፉ የማይታዘዙና፣ ለመልካም ስራም የማይበቁ ናቸው፡፡
ጳውሎስ በአማርኛ ቋንቋ ጳውሎስ የሚለው ስም የሰፈረበት ምክንያት ጳውሎስ የመጽሐፉ ጸሐፊ መሆኑን ለማስተዋወቅ ነው፡፡ አት : "ይህን ደብዳቤ የጻፍኩት፣እኔ፣ ጳውሎስ " የእግዚአብሔር ባሪያና የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆንሁ በዚህ መስመር ውስጥ “የሆንሁ” የሚለው ሐረግ “እኔ ነኝ” ብሎ ብሎ ለማመላከት ነው፡፡ አት AT: "እኔ የእግዚአብሔር አገልጋይና እና የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋሪያ ነኝ” . እምነት እንዲሆንላቸው አትAT: "እንዲታነጹ ለማድረግ " በእግዚአብሔር ለተመረጡት "እግዚአብሔር የመረጣቸው ሰዎች " እንደ አምልኮት ያለውን እውነት "ከእግዚአብሔር ህግ ጋር የሚስማማ እውነት"ወይም "ለቅዱሳን ምልካም የሆነ እውነት " የማይዋሽ "በፍጹም ሐሰትን የማይናገር" ከዘላለም ዘመናት በፊት "ጊዜ ከመጀመሩ በፊት" በዘመኑም ጊዜ፥ "በተገቢው ጊዜA" ለእኔ አደራ በተሰጠኝ ስብከት አት “ቃሉን እንዳውጅ ለእኔ አደራ ተሰጥቶኝ ነበር" ወይም " እንድሰብክ ሀላፊነት ተሰጠኝ " መድኃኒታችን እግዚአብሔር "ያዳነን እግዚአብሔር " (UDB)
እውነተኛ ልጄ ቲቶ የጳውሎስ የስጋ ልጁነው ማለት አይደለም፡፡ አት : "አንተ ለእኔ ልክ እንደ ልጄ ነህ " (UDB) በሃይማኖት ኅብረት our common faith አት " ሁለታችንንም በምንጋራው በክርስቶስ ላይ ባለን ተመሳሳይ እምነት "ወይም " ሁለታችንም በምናምነው ተመሳሳይ ትምህርት " ጸጋና ፤ምሕረት፤ ሰላምም ይሁን ይህ በጣም የተለመደ የሰላምታ አሰጣጥ ነው፡፡ አት: "ጸጋ፤ ምሕረት እና ሰላም ለእናንተ ይሁን" ወይም "መልካምነትን፤ ምሕረትን እና ሰላም በውስጣችሁ ሁኖ ተለማመዱት " ከመድኃኒታችንም ከጌታ ከኢየሱስ ክርስቶስ Christ Jesus our Savior "ያዳነን ክርስቶስ ኢየሱስ " ስለዚህ ምክንያት አት : "ምክንያቱ ይህ ነው " በቀርጤስ ተውሁህ፤ አት "በቀርጤስ እንድትቆይ ነገርኩህ " የቀረውን እንድታደራጅ "መስተካከል የሚገባቸው ነገሮች አስተካክለህ እንድትጨርስ " ሽማግሌዎችን እንድትሾም ordain elders "ለሽማግሌዎች ሐላፊነትን እንድትሰጥ " (UDB) ወይም "ሽማግሌዎችን እንድትሰይም " ሽማግሌዎች በጥንቷ ቤተክርስቲያን ለአማኞች ጉባኤ መንፈሳዊ አመረር ይሰጡ የነበሩት ክርስቲያን ሽማግሌዎች ነበሩ፡፡
የሽግግር ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ ለቲቶ በቀርጤስ ደሴት ላይ በሚገኙ በሁሉም ከተሞች ውስጥ ሽማግሌዎችን እንዲሾም አዞታል አሁን ጳውሎስ ስለሚሾሙት ሽማግሌዎች መስፈርትን ይሰጣል የማይነቀፍ ሽማግሌ አትAT: "መልካም ስም ያለው” የአንዲት ሚስት ባል የሚሆን፥ የተለያዩ አብያተክርስቲያናት ከዚህ በፊት ሚስቱ ስለሞተችበት ሰው፤ ሚስቱን ስለፈታ እና በጭራሽ ያላገቡ ሰዎች ወደ አመራር ስለሚመጡበት ሁኔታ የተለያየ አቋም አላቸው፡፡ የሚያምኑም ልጆች ያሉት፥ አማራጭ ትርጉም ሊሆኑ የሚችሉት 1) በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ልጆች ወይም 2) ታማኝ የሆኑ ልጆች የማይነቀፍ ሊሆን ይገባዋልና "የማይታወቅ " ወይም "ስሙ በዚህ መልክ የማይነሳ " ስለ አለመታዘዝ undisciplined "አመጸኛነት” ወይም "የእግዚአብሔርን ህግ የማይከተል" ሊሆን ይገባዋልና፤ አት: "ኤጲስ ቆጶስ በግድ መሆን ያለበትAn overseer must" እንደ እግዚአብሔር መጋቢ፥ "የእግዚአብሔር ባለአደራ" ወይም "ለእግዚአብሔር ቤት ላይ ሓላፊነት ያለበት" የማይሰክር "የመጠጥ ሱሰኛ ያልሆነ " ወይም "ሰካራም ያልሆነ " ወይም "ብዙ የወይን ጠጅ የማይጠጣ " የማይጨቃጨቅ፥ "ረብሸኛ ያልሆነ " ወይም " ጠብን የማይወድ " (UDB)
በጎ የሆነውን ነገር የሚወድ፥ "መልካም የሆኑ ነገሮችን የሚወድ " (UDB) ጠንቃቃ " የተሰጠ" ወይም "የተረዳ "ወይም "ጠንካራ ግንዛቤ ያለው " ሕይወት በሚገኝበት ትምህርት good teaching "እውነት የሆነ ትምህርት" ወይም "ትክክለኛ የሆነውን የሚያስተምር "
የሽግግር ዓረፍተ ነገር: ትክክለኛውን አስተምህሮ የሚቃወ ሙ በመኖራቸው ምክንያት ጳውሎስ ቲቶ የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰብክበትን እና ከሐሰት አስተማሪዎች የሚጠነቀቅበትን ምክንያት ይነግረዋል፡፡ ከተገረዙት ወገን የሚሆኑ those of the circumcision "የተገረዙ ሰዎች "ወይም " መገረዝን የሚፈጽሙ ሰዎች " ይህ አባባ፤ የተገረዙ አይዳዊያንን ያመላክታል፡፡ Their words are worthless "Their words do not benefit anyone" አፋቸውን መዝጋት ይገባል። "የሐሰት ትምህርታቸውን እንዳያስፋፉ ሊከለከሉ ይገባል፡፡" ወይም or "በንግግራች በሌሎች ላይ ተጽዕኖ እንዳይፈጥሩ በግድ ልናቆማቸው ይገባል፡፡” የማይገባውን እያስተማሩ "መማር የማይገባን ነገሮችን እያስተማሩ” ስለ ነውረኛ ረብ "ሰዎች ገንዘብ እንዲሰጦአቸው፡፡ ይህ አሳፋሪ ድሪጊት ነው" (UDB). ይህ የሚያመለክተው ሰዎች ተገቢ ያልሆነን ነገር በማድረግ ጥቅም ለማግኘት ሚፈልጉበት ሁኔታን ነው፡፡ ቤቶችን በሞላው ስለ ሚገለብጡ፥ "የቤተሰብን ሁኔታ የሚያበላሹ” አት : "የቤተሱቡን እምነት የሚያጠፉ"
ከእነርሱ አንዱ። One of them "ከቀርጤስ ሰዎች መካከል አንዱ የሆነ" ወይም "የቀርጤሳዊ የሆነ አንድ ሰው " የገዛ ራሳቸው ነቢይ የሆነ አት: "ሌሎች ሰዎች እንደ ነብይ የሚቆጥሩት ሰው " (UDB) የቀርጤስ ሰዎች ዘወትር ውሸተኞች፥ "ቀርጤሳዊያን ሁል ጊዜ ይዋሻሉ" ወይም "መዋሸት በፍጹም አያቆሙም " በአርግጥ ይህ ምን ያዕል ውሸተኞች መሆናቸውን ለማመላከት በማጋነን ሲቀርብ ነው፡፡ ክፉዎች አራዊት፥ ክዎች እና አውሬዎች የሚለው አገላለጥ ተምሳሌታዊ ሲሆን የቀርጤስ ሰዎችን ከአራት ጋር በማነጻጸር ያቀረበ ነው፡፡ በላተኞች፥ ሥራ ፈቶች lazy bellies "ሰነፍ በላተኞች" ወይም "ምንም የማይሰሩ ነገር ግን ብዙ የሚበሉ ናቸው " ሰው ስለሆዱ ያለው ግንዛቤ ማንነቱን እንደሚያሳይ የሚያስረዳ ምሳሌያዊ አባባል ነው፡፡ በብርቱ ውቀሳቸው። ልክ እንዳልሆኑ አበክረህ ንገራቸው፡፡ በሃይማኖት ጤናሞች እንዲሆኑh "ጤናማ እምነት እንዲኖራቸው" ወይም "እውነትን እንዲያምኑ " ወይም "እምነታቸው እውነት እንዲሆን "
ሳያዳምጡ፥ "ለመስማትጊዜሳያጠፉ" የአይሁድንተረትና ይህየአይሁዳዊያንየሐሰትትምህርትንያመለክታል፡፡ ፈቀቅየሚሉትን "አማኝነታቸውንያቆሙትን"
ሁሉለንጹሖችንጹሕነው፤ አት: "ንጹህለሆነሰውሁሉምነገርንጹህነው" ወይም "አንድሰውበውስጡንጹህከሆነየሚሰራውስራሁሉንጹህይሆናልIf someone is pure inside, everything they do will be pure." ለንጹሖች "ንጹህለሆኑሰዎች " ወይም "በእግዚአብሔርዘንድተቀባይነትላላቸው" ለርኵሳንናለማያምኑግንንጹሕየሆነምንምየለም፥ to those who are polluted and unbelieving, nothing is pure አትAT: "የተበላሸስንምግባርያላቸውእናመንጻትእንደሚችሉማያምኑማለትነው፡፡" ረክሶአል "ተበላሽቶችል" ወይም "መገንዘብአይችልም" በሥራቸውይክዱታል "ተግባራቸውየሚገልጠውእርሱንእንደማያውቁትተግባራቸውይገልጠዋል፡፡" የሚያስጸይፉናdetestable "አሳፋሪዎች" ለበጎሥራምሁሉየማይበቁ "ለየትኛውምመልካምተግባርየማይመጥኑመሆናቸውንያሳያሉ” ወይም"የትኛውንምመልካምተግባራመስራትእንደማይችሉያሳያሉ"
ሁሉ ለንጹሖች ንጹሕ ነው፤ አት: " ንጹህ ለሆነ ሰው ሁሉም ነገር ንጹህ ነው" ወይም "አንድ ሰው በውስጡ ንጹህ ከሆነ የሚሰራው ስራ ሁሉ ንጹህ ይሆናል " ለንጹሖች "ንጹህ ለሆኑ ሰዎች " ወይም "በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት ላላቸው" ለርኵሳንና ለማያምኑ ግን ንጹሕ የሆነ ምንም የለም፥ አማራጭ ትርጉም (አት): "በስነምግበራቸው ችግር ያላቸውና ንጹ መሆን እንደሚችሉ የማምኑ"
ረክሶአል "ተበላሽቶአል"ወይም "መገንዘብ የማይችል" በሥራቸው ይክዱታል። "ተግባራቸው እርሱን እንደማያውቁት ያሳያል" የሚያስጸይፉdetestable "ማስጠሎ ምንም የማያምር " ለበጎ ሥራም ሁሉ የማይበቁ ስለ ሆኑ፥ prove to be unfit for any good work "ለበጎ ስራ የማይመጥኑ እንደሆነ አሳያቸው " ወይም "የትኛውንም መልካም ስራ መስራት ማይችሉ እንደሆነ አሳይ"
1 አንተ ግን፣ ከጤናማው ትምህርት ጋር የሚስማማውን ተናገር። 2 በእድሜ የገፋ ሰዎች ልከኞች፣ ጨዋዎች፣ ጠንቃቆች ጤናማ እምነት፣ ፍቅርና ጽናት ያላቸው ሊሆኑ ይገባችዋል፡፡ 3 በእድሜ የገፉ ሴቶችም እንዲሁ ጨዋዎችና፣ ከሃሜት የራቁ መሆን አለባቸው፡፡ ወይን ጠጅ ጠጪዎች መሆን አይገባቸውም። መልካም የሆነውን ማስተማር ይገባችዋል 4 ወጣት ሴቶችን በአስተሳሰባቸው ሚዛናዊ እንዲሆኑ እንዲያሳስቧቸው፣ የገዛ ባሎቻቸውና ልጆቻቸውን የሚወዱ፣ ጠንቃቃ እንዲሆኑ እንዲያበርቷቷቸው፣ 5 የእግዚአብሔር ቃል እንዳይሰደብ ንፁህ፣ መልካም የቤት አስተዳዳሪና፣ ለባሎቻቸውም የሚታዘዙ ይሁኑ። 6 በተመሳሳይ መንገድ፣ ወጣት ወንዶች ጠንቃቆች እንዲሆኑ አሳስባቸው። 7 በነገር ሁሉ ራስህን የመልካም ሥራ ምሳሌ አድርገህ ተገኝ፤ በትምህርትም ንጽህናን፣ ጨዋነት፣ የማይነቀፍ ጤናማ ቃላት ይኑርህ። 8 ስለ እኛ የሚናገረው ምንም ክፉ ነገር እንዳይኖር። የማይነቀፍ ስህተት የሌለበትን፣ ነገር ግን ሊቃወም የሚሞክረውን የሚያሳፍር ቃላትን ተናገር። 9 ባሪያዎች በሁሉም ነገር ለጌቶቻቸው ይታዘዙ። ጌቶቻቸውን ደስ ሊያሰኟቸው ይሞክሩ እንጂ፣ አይከራከሯቸው። 10 ስለ መድሃኒታችን እግዚአብሔር የምናስተምረው፣ በሁሉ መንገድ የሚማርክ እንዲሆን፣ ታማኝነትን ያሳዩ እንጂ አይስረቁ። 11 ሰዎችን ሁሉ ሊያድን የሚችለው የእግዚአብሔር ፀጋ ተገልጧል፡፡ 12 ይህም ፀጋ ሃጢዓተኝነትና ዓለማዊ ምኞትን እንድንክድና፣ በአሁኑ ዘመን በጥንቃቄ፣ በጽድቅና፣ እግዚአብሔርን በመምሰል እንድንኖር ያስለምደናል 13 ይህም የተባረከውን ተስፋችንን፣ የታላቁን አምላካችንና አዳኛችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ፣ ለመቀበል በደስታ እንድንጠባበቅ ነው። 14 ኢየሱስ ራሱን ለእኛ የሰጠው፣ ከዓመፅ ነፃ ሊያወጣንና ሊያነፃን፣ ገንዘቡና መልካምን ለማድረግ የሚናፍቅ ሕዝብ፣ ለራሱ ሊያደርገን፣ ዋጋ ለመክፈል ነው። 15 እነዚህን ነገሮች ተናገር፣ አበረታታ፣ በሙሉ ስልጣን ገስጽ፣ ማንም አይናቅህ።
የሽግግር ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ በዚህ ክፍል ላይ ቲቶ በእርሱ መጋቢነት ስር ያሉትን ኣዛውንቶች፤ አሮጊቶች፤ ወጣት ሴቶችና ባርያዎች ወይም ሰራተኞች እንደአማኝ እንዴት መኖር እንዳለባቸው የሚሰብክበትን ምክንያት ያስረዳዋለወ፡፡ ነገር ግን አንተ አት አማራጭ ትርጉም "ነገር ግን አንተ,ቲቶ፣ ከሌሎች የሐሰት መምህራን አንጻር " ሕይወት ለሚገኝበት ትምህርት "ትክክለኛ አስተምህሮ " ወይም "ርቱዕ አስተምሮ " ራሳቸውን የሚገዙ፥ "ያልተሳከረ አህምሮ " ወይም "ራሳቸውን የሚቆጣጠሩ " ጭምቶችsensible "ራሱን የሚቆጣጠር" ወይም "ፍላጎቱን የሚገዛ " ጤናሞች "ትክክለኛ " በእምነት ጤናሞች "ጤናማ እምነት ያለው " ወይም "ትክክለኛ እምነት ያለው" ጤናሞች በፍቅር "በጤናማ ፍቅር " ጤናሞች በመጽናትም "ጽንአን " ወይም "ማይናወጡ" ወይም "የማይደክም"
እንዲሁም "በተመሳሳይ መንገድ " አማራጭ ትርጉም አት: "አዛውንቶቹን እንደመከርክ እንዲሁ አሮጊቶችን እዘዛቸው " አካሄዳቸው "ሁኔታቸው "ወይም "አኗኗራቸው " የማያሙ በዚህ ቁጥር ላይ ጥቅም ላይ የዋለው ቃል “ሰይጣን” ወይም “ሐሜተኛ” ወይም “ጠላት” ማለት ነው፡፡ ሌሎች ሰዎችን ለመጉዳት ክፋት የሚናገሩ ሰዎችን ያመለክታል፡፡ . ይምከሩአቸው "ማስተማር" ወይም "ሰነሰርዓት “ ወይም "ማበረታታት" በጎ የሆነውን ነገር "ጠቢባን " ንጹሖች አማራጭ ትርጉም "መልካምን የሚያስብ እና መልካምን የሚያደርግ" ወይም "ንጹሁ የሆነን ነገር የሚያስብ እና መልካምን የሚያደርግ" የእግዚአብሔር ቃል እንዳይሰደብ፥ "በዚህ ምክንያት የእግዚአብሔር መልዕክት ተቀባይነት እንዳያጣ " አማራጭ ትርጉም "በሴቶቹ ድርጊት ምክንያት ሌሎች ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዳይተቹና እንዳይቃወሙ”
እንዲሁ ይህ በቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ ሴቶችን ስለማሰልጠን አስፈላጊነት የተነገረውን የበፊቱን ቃል የሚያስተሰውስ ሲሆን በተመሳሳይ መንገድ ወንዶችን ማሰልጠን አስፈላጊ እንደሆነ ለማሳት ነው፡፡ ምከራቸው "ማስተማር" ወይም "ሰነሰርዓት “ ወይም "ማበረታታት" ራስህን አሳይ፤ present yourself አማራጭ ትርጉም "እንዲህ ልትሆን ይገባል" ወይም "ራስህን እንዲህ ልተሳይ ይገባል " መልካምን በማድረግህ ምሳሌ የሚሆን "ትክክለኛ ነገርን በማድረግ ምሳሌ መሆne መቻል " የሚቃወም ሰው ስለ እኛ የሚናገረውን መጥፎ ነገር ሲያጣ እንዲያፍር፥ ይህ ሐሳብ እንደ ጳውሎስ ግምት አንድ ሰው ቲቶን ቢቃወመው ውጤቱ ሐፍረት እንደሆነ ለማሳየት የተጠቀሰ ሲሆን ይህ ግን ገና ይሆናል ተብሎ የተገመተ እንጂ የተፈጸመ አይደለም፡፡
ለገዛ ጌቶቻቸው "ግዢዎቻቸው " በሁሉምin everything "በሁሉም ሁኔታ ውስጥ ወይም "ዘወትር " ደስ እንዲያሰኙ፥ አማራጭ ትርጉም : "ገዢዎቻቸውን ደስ እንዲያሰኙ "ወይም "ገዢዎቸቸውን ማርካት እንዲችሉ " በጎ ታማኝነትን ሁሉ አማራጭ ትርጉም "በሁሉም ነገር ለገዢዎቻችሁ ተማኝ ሁኑ" ወይም "በገዢዎቻቸውን ለመታመን እንደበቁ የሚገልጡ " ስለ መድኃኒታችን ስለ እግዚአብሔር God our Savior "ያዳነን እግዚአብሔር " ያስመሰግኑ ዘንድ፥ ሰዎችን ወደ ነገሩ መሳብን ያመለክታል ሌሎችን ሰዎች ለመሳብ እንደተዋበ ስጦታ በሁሉ ነገር "በምታደርጉት ሁሉ "
11
12-13 ይህም ጸጋ፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል እንድንኖር ያስተምረናል፤
የሽግግር ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ በዚህ ክፍል ላይ ቲቶን የጌታን ተመልሶ መምጣት እና ለእርሱ በክርስቶስ የተሰጠው ስልጣን እንዲያስተውስ ያበረታታዋል፡፡ ነገር ግን አንተ አት አማራጭ ትርጉም "ነገር ግን አንተ,ቲቶ፣ " ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤ አማራጭ ትርጉም "የሚያድነው የእግዚአብሔር ሁሉ ሰው እንዲያየው በግልጥ መጥቶአል፡፡ " ተገልጦአልና "ወደ ብርሃን መምጣት "ወይም "መታየት ቻለ " ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ "ትክክለኛው ነገር ሚያስተምረን " አማራጭ ትርጉም "ፈተናዎችን ተቋሙአል መልካምን እንድናደር የሚያርገን" ዓለማዊን ምኞት "ስለዚህ ዓለም በሆነው ነገር” ወይም "ስለ ምድራዊ ነገር ያለ ጠንካራ ፍላጎት አይቻልም፡፡" በአሁኑ ዘመን "በዚህ ምድር በምንኖርበት ግዜ " ወይም or "በዚህ ምድር ጊዜ " እየጠበቅን፥ "ለመቀበል እየጠብቅን " ክብር መገለጥ ይህ ቃል “መከሰትን” እና “ክብርን” አብሮ የያዘ ሲሆን “በክብር የሆነ መገለጥ” ማለት ነው፡፡
ስለ እኛ ነፍሱን ሰጥቶአል። "ስለ እኛ ለመሞት ራሱን አሳልፎ ሰጠ " ከዓመፅ ሁሉ እንዲቤዠን ፥ ይህ አገላለጥ ልክ ባሪያ አስፈላጊውን ክፍያ ከፍሎ ወይም ዓመታቱን ቆጥሮ ከጌታው ቁጥጥር ስር በህግ ተጠያቂ እንዳይሆን ነጻ እንደሚወጣ ሁሉ ከኃጢያ ነጻ መውጣታቸቸንን ያሳያል፡፡ ለራሱ እንዲያነጻ፥ "እንዲያነጻን" ገንዘቡም የሚሆነውን ሕዝብ አማራጭ ትርጉም "እንደ ውድ ሀብት የሚቆጠር መልካም ህዝብ " የሚቀናውን "በጣም ከፍተኛ ፍላጎት ያለው "
ይህን በሙሉ ሥልጣን ተናገርና ምከር አማራጭ ትርጉም "ሰሚዎችህ እንዚህ ነገሮች ማድረግ እንዲችሉ አስተምራቸው አበረታታቸው" በሙሉ ሥልጣን ገሥጽም፤ give correction with all authority "ይህን ነገር የማያድርጉትን በሙሉ ስልጣን አርማቸው " ማንም "ለማንም አትፍቀድ" አይናቅህ አማራጭ ትርጉም (አት)፡ "ቃልን ለመስማት እምቢ አይበል" ወይም "ማንም አላከብርህም አይበል"
1 ለገዢዎችና ለባለሥልጣኖች እንዲገዙ፣ እንደታዘዟቸው፣ ለበጐ ሥራ ሁሉ የተዘጋጁ እንዲሆኑ፣ 2 ማንንም እንዳይሳደቡ፣ የሌሎችንም ፈቃድ እንዲያከብሩ እንጂ እንዳይከራከሩ፣ ለሁሉም ሰው ትህትን እንዲያሳዩ አሳስባቸው። 3 እኛም ቀድሞ የማናስተውልና የማንታዘዝ ነበርን። የሳትንና የተለያዩ ምኞቶቻችንና ፍላጐቶቻችን ባሪያዎች ነበርን። በክፋትና በምቀኝነት እንኖር ነበር። የተጠላንና እርስበርስ የምንጠላላ ነበርን። 4 ነገር ግን፣ የመድሃኒታችን የእግዚአብሔር ርህራሔና ለሰው ልጅ ያለው ፍቅር በተገለጠ ጊዜ፣ 5 ከምህረቱ የተነሳ፣ በአዲስ ልደት መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ መታድስ አዳነን እንጂ፣ በሠራነው የጽድቅ ሥራ ምክንያት አይደለም። 6 እግዚአብሔር በመድሃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል፣ አብዝቶ መንፈስ ቅዱስን አፈሰሰልን። 7 ይህም በፀጋው ፀደቅን፣ የዘላለም ህይወት ተስፋ ወራሾች እንድንሆን ነው። 8 እነዚህ ቃሎች የታመኑ ናቸው። በእግዚአብሔር የሚያምኑ እርሱ በፊታቸው ላኖረው መልካም ሥራ እንዲተጉ፣ እነዚህን ነገሮች በድፍረትት እንድትናገር እፈልጋለሁ። እነዚህ ነገሮች መልካምና ለሰዎች ሁሉ የሚጥቅሙ ናቸው። 9 ነገር ግን ከከንቱ ክርክር፣ ከዘር ቆጠራና በህግ ጉዳይ ከሚሆን ጸብና ግጭት ራቅ። እነዚህ ነገሮች፣ የማይገቡና የማይጠቅሙ ናቸው፡፡ 10 አንዴ ወይም ሁለቴ ካስጠነቀቅከው በኋላ፥ በመካከሃላችሁ መከፋፈል የሚፈጥረውን ሰው አስወግደው፡፡ 11 እንዲህ ዓይነቱ ሰው፣ ከእውነተኛው መንገድ የወጣ፣ ሃጢያት የሚያደርግና በራሱ የፈረደ እንደሆነ እወቅ። 12 አርጢሞንን ወይም ቲኪቆስን ወደ አንተ ስልክ፣ ክረምቱን ለማሳለፍ ወደ ወሰንኩበት ወደ ኒቆሊዎን ፈጥነህ ና። 13 የህግ ባለሞያውን፣ ዜማስንና አጵሎስን የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ ሰጥተህ ቶሎ ላካቸው። 14 ወገኖቻችንም እለታዊ ፍላጎታቸውን ማግኛት እንዲችሉ ፍሬ ቢስም ሆነው እንዳይገኙ፣ መልካም ሥራ ማድረግን መማር አለባቸው። 15 ከኔ ጋር ያሉት ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡልሃል ። የሚወዱንን አማኞችን ሁሉ ሰላም በልልን። ፀጋ ከሁላችሁ ጋር ይሁን፡፡አሜን።
የሽግግር ዓረፍተ ነገር: ጳውሎስ በዚህ ክፍል ላይ ቲቶ በእርሱ መጋቢነት ስር ያሉትን ሽማግሌዎች እና ሕዝብ እንዴት ማስተማር እናዳለበት ተከታታይ መመሪያ ይሰጠዋል፡፡ ኣሳስባቸው "በቤተክርስቲያን ላሉ ሰዎች በአጠቃላይ ከዚህ በፊት የሚያውቁትን ነገሮች ንገራቸው” ወይም "ሳታሰልስ አስታውሳቸው " የሚገዙና የሚታዘዙ፥እንዲሆኑ አት : "የፖለቲካ መሪዎች እና የመንግስት ባለስልጣናት የሚሉትን በማድረግ ታዘዙላቸው” ለገዦችና ለባለ ሥልጣኖች እንዚህ ቃላት ተመሳሳይ ትርጉም ሲኖራቸው የመንግሰትን ስልጣን የያዘን ሰው ሁሉ የሚያላክቱ ናቸው፡፡ ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጁ፥ "በየትኛውም አጋጣሚ የሚገኘውን ዕድል መልካምን ስራ ለመስራት የተዘጋጀ” ማንንም የማይሰድቡ፥ "ክፍ የማይናገር" ለሰው ሁሉ የዋህነትን ሁሉ የሚያሳዩ አት : "የዋህ "
የ "ምክንያቱም" አስቀድመን "ከዚህ ቀድሞ" ወይም "የሆነ ጊዜ “ ወይም "ከዚህ በፊት " የማናስተውል "ሞኞች" ወይ፣or "ማስተዋል የጎደለን" ለምኞትና ለልዩ ልዩ ተድላ እንደ ባሪያዎች የምንገዛ፥ ይህ ተምሳሌታዊ ንጽጽር ኃጢያታዊ ምኞታችን እንዴት እንደ ባሪያ ሊቆጣጠረን እንደሚችል የሚያሳ ነው፡፡ አት: "የኃጢያት መሻታችን ለተድላ ፍላጎታችን ባሪያ አድርጎናል" የምንስት አት: "የታለልን " ምኞት "ከፍተኛ ጉጉት" ወይም "መሻት " በክፋትና በምቀኝነት የምንኖር፥ አት: "ዘወትር ክፋትን የምንሰራና የሌላውን ሰው ምንመኝ ነበርን" የምንጣላ፥ እርስ በርሳችን የምንጠላላ ነበርን። "ለመጠላት የተገባን ነበርን" አት: "ሌሎች ሰዎችን እንዲጠሉን የምናደርግ ነበርን"
ነገር ግን የመድኃኒታችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ፥ አት : መድኃኒታችን እግዚአብሔር ፍቅሩንና መልምነቱን ለሰዎች ባሳየ ጊዜ" ወደ ሰዎች "ለሰዎች " እንደ ምሕረቱ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም፤ "አዳነን፡፡ ያዳነን እንደ እርሱ ምሕረት ነው እንጂ ስለመካም ስራችን አይደለም፡፡” በ…አዳንን saved us through "ያዳነን….ዘዴ" ወይም "በ…አዳነን " ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና አት: " መንፈሳዊ በሆነ አዲስ ልደት ውስጣችንን ንጹህ አደረገልን" በመታደስ "አዲስ መሆን " አማራጭ ትርጉም "መንፈስ ቅዱስ አዲስ አደረገን "ወይም "መንፈስ ቅዱስ አዲስ ሰዎች አደረገን" እንደምሕረቱ "በምህረቱ መጠን ልክ " ወይም "ምሕረቱን በእኛ ላይ ስላበዛ"
አትርፎ "አትረፍርፎ " ወይም "ያለመሰሰት" ያን መንፈስም፥ በእኛ ላይ አፈሰሰው። ይህ ዘይቤያዊ አገላለጥ በካህናት ላይ ሲፈስ ከነበረው ዘይት ጋር ተቀራራቢነት አለው፡፡ አማራጭ ትርጉም: መንፈሱን ያለመሰሰት ሰጠንን" በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ "ኢየሱስ ባዳነን ጊዜ " በጸጋው ጸድቀን አማራጭ ትርጉም(አት): "በእግዚአብሔር ጻድቃን ተደርገናል" ወራሾች እንድንሆን፥ አማራጭ ትርጉም (አት): "እግዚአብሔር የመውረስ መብት ያላቸው ልጆች አደረገን” በዘላለም ሕይወት ተስፋ "አሁን የዘላለም ሕይወት እንዳለን በእርግጠኛነት እናውቃለን "
እግዚአብሔርንም የሚያምኑት እነዚህን አስረግጠህ እንድትናገር እፈቅዳለሁ። ይህ መልካምና ለሰዎች የሚጠቅም ነው፤ ቃሉ የታመነ ነው። ይህ የሚያመከለክተው በቀዳሚው ቁጥር ላይ እግዚአብሔር በኢየሱስ በኩል መንፈሱን እንደሰጠን የሚናገረውን ቁጥር ነው፡፡ በጥንቃቄ እንዲጸኑ፥ "ትኩረት እንዲያደርጉ"ወይም "በተደጋጋሚ እንዲያስቡበት " በመልካም ሥራ AT: "እግዚአብሔር እንዲሰጠሩ በሰጣቸው "
የሽግግር ዓረፍተ ነገር : ጳውሎስ በአማኞች መካከል ጠብ የሚፈጥሩነት ወይም የተለየ አስተያየት ያላቸውን ሰዎች እንዴት መያዝ እንዳለበት ወይም ማስወገድ እንዳለበት ለቲቶ ገለጻ ያደርግለታል፡፡ ነገር ግን But "ነገር ግን አንተ ቲቶ " ሞኝነት ካለው ምርመራ "አላስፈላጊ ሙግት " ጠብ "ጭቅጭቅ ሁከት " ስለ ሕግም "ስለሕግም " ራቅ አማራጭ ትርጉም : "አትነጋገር "ወይም "አብርሃቸው ጊዜን አታሳልፍ " ወይም "አስወግዳቸው" አንድ ጊዜ ሁለት ጊዜም ከገሠጽኸው በኋላ "ሰውየውን አንዴ ወይም ሁለቴ ካስጠየነቀቅከው በኃላ " እንዲህ ከሚመስል ሰው "ይህን የመስል ሰው " እንዲህ ከሚመስል ሰው ""ይህን የመስል ሰው "
የሽግግር ዓረፍተ ነገር : ጳውሎስ በአማኞች መካከል ጠብ የሚፈጥሩነት ወይም የተለየ አስተያየት ያላቸውን ሰዎች እንዴት መያዝ እንዳለበት ወይም ማስወገድ እንዳለበት ለቲቶ ገለጻ ያደርግለታል፡፡ ወደ አንተ ስልክ፥ "ከላኩልህ በኃላ " አርጢሞንን ወይም ቲኪቆስን ዜማስን
በዚያ ልከርም ቈርጬአለሁና። "ክረምቱን እቆያለው" ወደ እኔ እንድትመጣ ትጋ፤ "ፍጠንና ና” ወይም "ፈጥነህ ና" በጉዞአቸው ተግተህ እርዳ ። "ፍጠን" ወይም "ለመላክ አትዘግይ " ና አጵሎስን "እና አንዲሁም አጵሎስ ላከው"
በመልካም ሥራ እንዲጸኑ ይማሩ። "ባተሌ እና በመልም ስራ የተጠመዱ " ፍሬ ቢሶች ሆነው እንዳይቀሩ፥ አማራጭ ትርጉም
ኖት የለውም።
1 ስለክርስቶስ ኢየሱስ እስረኛ የሆነው ጳውሎስ ከወንድማችን ከጢሞቴዎስ ጋር ለተወደደው ወንድማችንና የሥራ አጋራችን ለሆነው ለፊሊሞና፣ 2 ለእህታችን ለአፒፊያ፣አብሮን ወታደር ለሆነው ለአክሪፋ እንዲሁም በቤትህ ላለችው ቤተክርስቲያን፡ 3 ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሠላም ለእናንተ ይሁን። 4 በጸሎቴ ሁሉ ስላንተ እያነሳሁ ሁልጊዜ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ። 5 ምክንያቱም በጌታ በኢየሱስ ስላለህ እምነት ለቅዱሳንም ሁሉ ስላለህ ፍቅር ሰምቻለሁ። 6 በክርስቶስ በኩል የመልካም ነገር ሁሉ እውቀት በእኛ ውስጥ ስላለ በእምነት ያለህ ተካፋይነት ውጤታማ እንዲሆን እጸልያለሁ። 7 ወንድሜ ሆይ፣ ለዚህም ምክንያቱ የቅዱሳን ሁሉ ልብ በአንተ በማረፉ ምክንያት በፍቅርህ በጣም ደስ ስላለኝና ስለተጽናናሁ ነው። 8 ስለዚህም ምንም እንኳ ምን ማድረግ እንዳለብህ በክርስቶስ ለማዘዝ ድፍረት ቢኖረኝም 9 በዚህ ፈንታ እንደ ሽማግሌው አሁን ደግሞ ስለ ክርስቶስ እስረኛ እንደሆነው ጳውሎስ በፍቅር እለምንሀለሁ። 10 ልመናዬ በእስርቤት አባት ስለሆንኩት ስለ ልጄ ኦኖሲሞስ ነው። 11 ምክንያቱም ቀድሞ ለአንተ የማይጠቅም አሁን ግን ለአንተም ለእኔም ጠቃሚ በመሆኑ ነው። 12 የልቤ የሆነውን እርሱን ወደ አንተ ልኬዋለሁ። 13 በእኔ በኩልስ አንተን ወክሎ ስለ ወንጌል በእስር ቤት ያለሁትን ያገለግለኝ ዘንድ እኔ ጋ ቢቀር እወድ ነበር። 14 ነገር ግን መልካም ሥራህ በግድ ሳይሆን በፈቃድህ ይሆን ዘንድ ያለ አንተ ፈቃድ ምንም ማድረግ አልፈለግሁም። 15 ለጥቂት ጊዜ ከአንተ ተለይቶ የነበረው ምናልባት ለዘላለም የአንተ ይሆን ዘንድ ነው ። 16 ነገር ግን ከዚህ በኋላ ከባሪያ የተሻለ እንደተወደደ ወንድም እንጂ እንደባሪያ አይደለም፥ በተለይ ለእኔ የተወደደ ከሆነ ለአንተማ በሥጋም በጌታም የበለጠ ይሆናል። 17 እንግዲህ እንደ አጋርህ ከቆጠርከኝ እንደኔ አድርገህ ተቀበለው። 18 ነገር ግን በምንም መልኩ አሳዝኖህ ቢሆን ወይም ዕዳ ቢኖርበት በእኔ ላይ ቁጠረው። 19 እኔ ጳውሎስ እኔ እከፍላለሁ ብዬ በገዛ እጄ ጽፌአለሁ።የገዛ ህይወትህ እንኳ የኔ ነው ብዬህ አላውቅም። 20 አዎ ወንድሜ ሆይ እስኪ በጌታ ደስ ይበለኝ፥ ልቤም በክርስቶስ ይጽናና። 21 እንደምትታዘዘኝ በመተማመን ካልኩህም በላይ እንደምታደርግ ስለማውቅ ጽፌልሀለሁ። 22 በነገራችን ላይ ከጸሎታችሁ የተነሳ ወደ እናንተ እንደምመጣ ተስፋ ስለማደርግ አንድ የእንግዳ ክፍል አዘጋጅልኝ። 23 ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ አብሮኝ የታሰረው ኤጳፍራ 24 እንዲሁም የሥራ አጋሮቼ ማርቆስ፣አርስጥሮኮስ፣ዴማስና ሉቃስ ሠላምታ ያቀርቡልሀል። 25 የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከመንፈሳችሁ ጋር ይሁን። አሜን!
የክርስቶስ ኢየሱስ እስረኛ እና ጢሞቴዎስ ለፊልሞና በቋንቋችሁ የደብዳቤ ጸሐፊን ማስተዋወቂያ መንገድ ሊኖር ይችላል፡፡ አመራጭ ትርጉም፡ "በክርስቶስ ኢየሱስ እስረኛ የሆንኩት ጳውሎስ እና ወንድማችን ጢሞቴዎስ እና ይህንን ደብዳቤ ለፊልሞና ጽፈናል፡፡" የክርስቶስ ኢየሱስ እስረኛ "ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ በማስተማሩ ምክንያት እስረኛ የሆነው፡፡" ኢየሱስን የማይወዱት ሰዎች ጳውሎስብ በእስር ቤት ውስጥ በማኖር ቀጥተውታለል፡፡ ወንድም በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ቃል ያለው ትርጉም ክርስትያን ማለት ነው፡፡ የተወደደው ወዳጃችን "ተወዳጁ ከእኛ ጋር አማኝ የሆነው" ወይም "የሚንወደው መንፈሳዊ ወንድማችን" የሥራአ አጋር "ልክ እንደ እኛ ወነንጌልን በማሠራጨት ሥራ የተጠመደው" እህታችን አፊያ ይህ ማለት "እንደ እና አማኝ የሆነችው አፊያ" ወይም "መንፈሳዊ እህታችን የሆነችው አፊያ" ለአርክጳ ይህ አንድ ሰው ስም ነው፡፡ ከእኛ ጋር የሚሠራ ሰው በዚህ ሥፍራ ላይ “ወታደር” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ወንጌልን በተለያዩ ሥፍራዎ ለማሠራጨት የሚጥርን ሰው ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ከእኛ ጋር መንፈሳዊ ውጊያን የሚዋጋ" ወይም "ከእኛ ጋር መንፈሳዊ ውጊያን የሚዋጋ ሰው፡፡" በመኖሪያ ቤታችሁ ውስጥ የሚትሰበሰበው ቤተ ክርስቲያን "በአንተ ቤት ውስጥ የሚሰበሰቡት የአማኞች ቡድን" (UDB) ቤትህ ውስጥ በዚህ ሥፍራ ላይ “አንተ” የሚለው ቃል የተገለጸው በነጠላ ቁጥር ሲሆን የሚያመለክተው ፊልሞናን ነው፡፡ ጸጋ እና ሰላም ከአባታችን ከእግዚአብሔር እና ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ለእናነተ ይሁን "እግዚአብሔር አባታችን እና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋንና ሰላምን ለእናንተ ይስጣችሁ፡፡” ይህ ባርኮት ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የተገለጸው በብዙ ቁጥር ሲሆን ጳውሎስ በዚህ ደብዳቤ በመጀመሪያዎቹ ሁለት ቁጥሮች ላይ ሰላምታ የሰጣቸውን ሰዎችን ያመለክታልis is a blessing. The word "you" is plural and refers to all the people Paul greeted in verses 1 and 2.
እኔ ይህንን ደብዳቤ የጻፈው ጳውሎስ ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ “እኔ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጳውሎስን ነው፡፤ አንተ በዚህ ሥፍራ ላይ እና በዚህ ደብዳቤ ውስጥ በብዙ ሥፍራዎች ላይ “አንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ፊልሞንን ነው፡፡ በክርስቶስ የእኛ የሆነው የዚህ ትርጉም ሊሆን የሚችለው ከክርስቶስ የተነሣ እኛ አለን የሚል ይሆናል፡፡" ልቦች በዚህ ሥፍራ ላይ “ልቦች” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የአማኞችን ጽናት ነው፡፡ ወንድም ጳውሎስ ፊልሞንን “ወንድም” ብሎ ይጠራዋል ምክንያቱም ሁለቱም አማኞች በመሆናቸው ምክንያት ነው፡፡ ከዚህ በተጨመማሪም ምናልባት በሁለቱ መካከል ያለው ወዳጅነት አጽኖት መስጠት ፈልጎም ሊሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "የተወደድከው ወንድም" ወይም "ውድ ወንድሜ፡፡"
በክርስቶስ ያለን ድፍረት ሁሉ አማራጭ ትርጉሞች "ከክርስስ የተነሣ ያለን ሥልጣን" ወይም "ከክርስቶስ የተነሣ ያለን ብርታት፡፡" አማራጭ ትርጉም: "የክርስቶስ ሐዋርያ በመሆነ ያለኝ ሥልጣን፡፡" ይሁን እንጂ ከፍቅር የተነሣ አማራጭ ትርጉም 1) "የእግዚአብሔርን ሕዝብ እንደሚትወድ ስለማውቅ" 2) "እኔን ስለምትወደኝ" ወይም 3) "አንተን ስለሚወድህ፡፡"
ልጄ አናሲሞስ የእኔ ልጅ ስለሆነው አናሲሞስ ፡፡ ጳውሎስ ከአናሲሞስ ጋር የነበረውን ቅርብ ግንኙነት በአባት እና በለልጅ መካከል ካለው ግንኙነት ጋር ያነጻጽረዋል፡፡ አናሲሞስ የጳውሎስ ልጅ አይደለም፡፡ ይሁን እንጂ አናሲሞስ ሕይወትን ያገኘው ጳውሎስ ስለ ኢየሱስ ካስመተማረው በኋላ ነው፤ ጳውሎስም ወደደው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ተወዳጁ ልጁ አናሲሞስ" ወይም "መንፈሳዊ ልጄ አናሲሞስ፡፡" አናሲሞስ ይህ የአንድ ሰው ስም ነው፡፡ እኔ አባት የሆኑኩት አናሲሞስ የጳውሎስ ልጅ የሆነበት መንገድ ግልጽ ነው፡ "ስለ ክርስቶስ ሳስተምረው መንፈሳዊ ልጄ የሆነው እና አዲስ ሕይወትን የተቀበለው፡፡" አማራጭ ትርጉም: "ለእኔ ልጅ የሆነው" ወይም "ለእኔ እንደ ልጅ የሆነው፡፡" በእስራቴ በእስራቴ፡፡" በዚያ ዘመን እስረኞች ብዙ ጊዜ በበሰንሰለት ይታሠሩ ነበር፡፡ ጳውሎስ አናሲሞስን ባስተመረበት ወቅት በእስር ቤት ነበር እንዲሁም ይህንንም ደብዳቤ በሚጽፍበት ወቅትም በእስር ላይ ነበር፡፡ በፊት የሚጠቅም አልነበረም ይህ እንደ አዲስ ዓረፈተ ነገር ተደርጎ ልተረጎም ይችላል፡፡ “ከዚህ በበፊት እርሱ ምንም የምጠቀም አልነበረም፡፡” አሁን ግን የሚጠቅም ሆኗል "አሁን ግን ጠቃሚ ሆኗል፡፡" ተርጓሚዎች በግሪጌ ማስታወሻ ላይ “ኦናሲሞስ የሚለው ቃል ትርጉም ጠቃሚ ማለት ነው” የሚለውን ማስቀመጥ ይችላሉ፡፡" የእኔ ልብ የሆነውን ወደ አንተ መልሼ ልኬዋለሁ ጳውሎስ ይህንን ደብዳቤ የጻፈው ኦናሲሞስን ከመላኩ ጥቂት ቀደም ብሎ ሊሆን ይችላል፡፡ የልቤ የሆነውን በዚህ ሥፍራ ላይ “ልብ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ተወዳጅ የሆነ ሰውን ነው፡፡ ጳውሎስ እየተናገረ ያለው ስለ ኦናሲሞስ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ከልቤ የሚወደውን፡፡" በእናንተ ፈንታ ሆኖ ያገለግለኝ ዘንድ "እናንተ በዚህ መሆን ስለማትችሉ እርሱ ለረዳኝ ይችላል፡፡" አዲስ ዓረፈተ ነገር ተደርጎ ልተረጎም ይችላል፡፡ በእናንተ ፈንታ ልረዳኝ ይችላል፡፡" እኔ በበሠንሰለት ታሥሬያለሁ አማራጭ ትርጉም: "በእስር እያለሁ" ወይም "በእስር ቤት ውስጥ ስላለሁ" ለወንጌል ሲባል አማራጭ ትርጉም: "ወንጌልም መስበክ ስላለብኝ፡፡"
ይሁን እንጂ እናንተን ሳላማክር አንዳች ነገር ማድረግ አልፈልግም "ይሁን እንጂ እናንተ ሳትፈቅዱ እዚህ ላስቀረው አልፈለኩም" ወይም "ይሁን እንጂ እናንተ ከፈቀዳቹልኝ ብቻ በእኔ ዘንድ እንዲቆይ አደርገዋለሁ፡፡" የአንተ . . . አንተ በዚህ ሥፍራ ላይ የተጠቀሱት ተውላጠ ስሞች በነጠላ ቁጥር ሲሆን የሚመለክቱት ፊልሞንን ነው፡፡ ስለዚህ የሚታደርገውን መልካም ነገር ሁሉ የሚታደርገው እኔ ስላሰገደድኩህ መሆን የለበትም አማራጭ ትርጉም: "ትክክለኛ የሆነውን ነገር አድርግ፣ እኔ ስላስገደድኩህ ኤደለም፡፡" ነገር ግን አንተ ስለፈለከው እንጂ "ትክክለኛውን ነገር ለማድረግ አንተ ራሰህ ስለመረጥክ እንጂ" ምናልባት ከአንተ የተለየበት ምክንያት “እግዚአብሔር ኦናሲሞስ ከአንተ እንዲለይ ያደረገበት ምክንያት፡፡" ምናልባት "ምንአልባት" ለተወሰነ ጊዜ "በእነዚህ ጊዜያት" ከባሪያ የተሻለ "ከባሪያ የተሻለ ጠቃሚ እንዲሆን" ተወዳጅ ወንድም "ውድ ወንድም" ወይም "በክርስቶስ ውድ የሆነ ወንድም" ለአንተ ድግሞ ከዚህ እንዴት አይበልጥ "ለአንተ ከዚህም በላይ ነው" በሰው እይታ ይህ በሰዎች መካከል የሚደረግ ግንኙነት በግልጽ ይቀመጣል፡ “እርሱ የአንተ ባርያ በመሆኑ ምክያት፡፡" አማራጭ ትርጉም: "እንደ ሰው" ወይም "በሰውና ግንኙነትህ፡፡" እንዲሁም በጌታ አማራጭ ትርጉም፡ "በጌታ ወንድምህ እንደመሆኑ መጠን" ወይም "የጌታ በመሆኑ ምክንያት፡፡"
እኔን እንደ አጋርህ ከቆጠርከኝ "እኔን ለክርስቶስ አጋር ሠራተኛህ አድርገህ የሚታስበኝ ከሆነ" እዳውን በእኔ ላይ አድርገው አማራጭ ትርጉም: "የእርሱ እዳ በእኔ ላይ አድርገው" ወይም "ባለእዳው እኔ እንደሆንኩ ቁጠረው፡፡" ይህን በገዛ አጆቼ የሚጽፍልህ እኔ ጳውሎስ ነኝ ጳውሎስ ይህንን ለፊልሞና የጻፈው የተጻፉት ነገሮቸ እውነት መሆናቸውን ለማረጋገጥ ነው፡፡ ጳውሎስ በእርግጥ ያለበትን እዳ ሁሉ ይከፍለዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “እኔ ጳውሎስ ይህንን በገዛ እጆቼ ጻፍኩልህ፡፡” ይህንን ለአንተ ማስታወስ የለብኝም "ይህንን ለአንተ ማስታወስ አይኖርብኝም" አማራጭ ትርጉም: "አንተ ታውቃለህ" ለእኔ የራስህ ደግሞ ብድር አለብህ "የገዛ ሕይውትን ብርድ ለእኔ አለብህ፡፡" ፊልሞን የጳውሎስ ብድር እንዳለበት የሚያሳየው ኣረፍ ነገር እንዲህ በግለጽ ሊቀመጥ ይችላል፡ “ይህ እዳ አለበህም ምክንቱም ሕይወትህ ያደንኩህ እኔ ነኝ፡” ወይም የራሰህ ሕይወት እንኳ የእኔ ነው ምክንቱም የዳንከው እኔ በነገርኩህ ነገር ነው፡፡" ጳውሎስ በተዘዋዋሪ መንገድ እያለ ያለው ኦናሲሞስ ወይም ጳውሎስ እዳለ አለባቸው ማለት የለበትም ምክንቱም ኦናሲሞስ የጳውሎስ ብዙ እዳ አለበት፡፡ ልቤን አዲስልኝ ኦናሶሞስ ለጳውሎስ ያደረገው ነገር እንዲህ በግልጽ ሊቀመጥ ይችላል: "ኦናሲሞስን በመቀበል ልቤን አዲስልኝ፡፡" አማራጭ ትርጉም: "ልቤ እንዲበሰት አድርግ" ወይም "ደስተኛ እንዲሆን አድርግ" ወይም "አጽናናኝ፡፡"
ስለመታዘዝህ ከፍተኛ መተማመን አለኝ "ምክንያቱም ያዘዝኩን እነነደሚታደረግ እርግጠኛ ነኝ" የአንተ መታዘዝ...እጽፍልሃለሁ . . . ታደርገዋለህ ጳውሎስ ይህንን የጻፈው ለፊልሞና ነው፡፡ እያወቅሁ "አውቃለሁ" በተመሳሳይ መልኩ "እንዲሁም" ለእኔ ማረፊያ ሥፍራ አዘጋጅልኝ "በቤትህ ለእኔ ማረፊያ የሚሆን ሥፍራን አዘጋጅልን፡፡" ጳውሎስ ፊልሞን ይህንን እንዲያደረግ ይጠይቀዋል፡፡ በእናንተ ጸሎት . . . ልጎበኛችሁ በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ፊልሞንን እና በእርሱ ቤት ውስጥ የሚሰበሰቡ አማኞችን ነው፡፡ በጸሎታችሁ አማራጭ ትርጉም: "በጸሎታችሁ ምክንያት" ወይም "እናንተ ሁላችሁ ስለ እኔ በመጸለያችሁ ምክንያት፡፡" በቶሎ ልጎበኛችሁ እችላለሁ "በእስር ያቆኙ ሰዎች ቶሎ በነጻ እንዲለቁኝ እግዚአብሔር ያደርጋል ከዚያም ወደ እናንተ መምጣት እችላለሁ፡፡"
ኖት የለውም።
1 ከረጅም ጊዜ በፊት በተለያዩ ዘመናትና በተለያዩ መንገዶች እግዚአብሔር በነቢያት በኩል ለአባቶቻችን ተናግሮ ነበር። 2 አሁን ግን የሁሉም ነገር ወራሽ ባደረገው፣ ዓለምንም በፈጠረበት በልጁ ተናገረን። 3 ልጁ የክብሩ ነጸብራቅ ነው፤ እርሱ በባሕርዩ ከእግዚአብሔር ጋር ፍጹም አንድ ነው፤ በሥልጣን ቃል ሁሉን ደግፎ ይዞአል። የሰዎችንም ኃጢአት ካነዳ በኃላ በሰማይ በግርማው ቀኝ ተቀምጧል። 4 እርሱ የወረሰው ስም ከሰማቸው እጅግ የላቀ በመሆኑ፣ ከመላእክትም የበለጠ ሆኖአል። 5 ለመሆኑ፣ ከመላክት መካከል፣ “አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወልጄሃለሁ” ደግሞስ፣ “እኔ አባት እሆነዋለሁ፤ እርሱም ልጄ ይሆናል” ያለው ለማን ነው? 6 የበኩር ልጁን ወደ ዓለም ሲያስገባ እግዚአብሔር፣ “የእግዚአብሔር መላእክት ሁሉ ይስገዱለት” ብሏል። 7 ስለ መላእክቱ ግን፣"መላዕክቱን ነፋሳት፥ አገልጋዮቹንም የእሳት ነበልባል ያደርጋል" ይላል። 8 ስለ ልጁ ግን፣ “አምላክ ሆይ፣ዙፋንህ ከዘላለም እስከ ዘላለም ነው፤ የመንግሥትህም በትር የጽድቅ በትር ነው። 9 ጽድቅን ወደድህ፤ ዐመፅንም ጠላህ ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክህ፣ ከጓደኞችህ ይልቅ በደስታ ዘይት ቀባህ” ብሏል። 10 እንዲሁም፣ “ጌታ ሆይ፣ በመጀመሪያ ምድርን ፈጠርህ፤ ሰማያትም የእጅህ ሥራ ናቸው። 11 እነርሱ ይጠፋሉ፤ አንተ ግን ትኖራለህ። ሁሉም እንደ ልብስ ያረጃሉ። 12 እንደ መጎናጸፊያ ትጠቀልላቸዋለህ፤እንደ ልብስም ይለወጣሉ። 13 በየትኛውም ጊዜ ነበር እግዚአብሔር ከመላእክቱ ለአንዱ፣ “ጠላቶችህን ከእግርህ በታች እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ” ያለው? 14 ታድያ፣ መላእክት ሁሉ እኔን እንዲያመልኩና ድነት የሚወርሱትን ለመርዳት ተተላኩ መንፈሶች አይደሉምን?
ነጸብራቅ "ብርሃን" የእርሱ ባሕርያ ትክክለኛ መገለጫ አንድ ሰው ወደ ልጁ በመመልከት እግዚአብሔር ምን እንደሚመስል ያያል፡፡ ቃሉ የእርሱ ኃይል "ኃይለኛ በሆነው ቃሉ" የኃጢአታንን መንጻት አስገኘ "ከኃጢአት እኛ ማንጻት ፈጸመ" እግዚአብሔር በልጁ አማካኝነት ለእኛ ተናገረን . . . ዓለማትን ሁሉ ፈጠረ የእግዚአብሔር ልጅ አምላክ ነው፣ አምላክ የሆነ ልጅ ነው፡፡ ልጁ ዓለማትን ፈጥሯል፡፡ ልጅ የእግዚአብሔር ልጅ የሚለው ስም ለኢየሱስ እጅግ ወሳኝ የሆነ የማዕረግ ስም ነው፣ የእርሱ ልጅ የእርሱ ክብር ማንጸባረቂያ፣ የእርሱ ባሕርይ መገለጫ . . . ሁሉን ነገር በእጁ ደግፎ የያዘ ልጁ የእግዚአብሔርን ክብር ያንጸባርቃል፣ የእግዚአብሐየርን ባሕርይ እና መገለጫ ያሳያል እንዲሁም የፈጠረውን ፍጥረታት ሁሉ በእጆቹ ደግፎ ይይዛል ምክንያቱም እርሱ አምላክ ስለሆነ ነው፡፡
እርሱ . . . ሆነ "ኢየሱስ . . . ሆነ" ከመላእክት መካከል እንዲህ ያለው ለማን ነው . . . አባት"? "እግዚአብሔር ከመላእክት መካከል ለአንዳቸውን እንዲህ አላለም . . . አባት፡፡" ፈጽሞ እንዲህ ብሎ ያውቃልን "አባት የሆነው እግዚአብሔር ፈጽሞ እንዲህ ብሎ ያውቃልን" እንደገናም . . . ለእኔ "እንደገናም ከመላእክት መካከል ለአንዳቸውም ፈጽሞ እንዲህ አላለም . . . ለእኔ?" አንተ ልጄ ነህ ...እኔ አባት ሆኜሃለሁ . . . እኔ አባት እሆነዋለሁ . . . እርሱም ለእኔ ልጅ ይሆናል እግዚአብሔር አባት ከእግዚአብሔር ወልድ ጋር ያለው የተለየ ግንኙነት በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥ ኢየሱስ ከመወለዱ ብዙ መቶ ዓመታት በፊት ተገልጾ እናገኘዋለን፡፡
በኹር በዚህ ሥፍራ ይህ ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስን ነው፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ የእግዚአብሔር በኹ ተብሎ ተጠርቷል፡፡ ምክንያቱም ከሌሎቹ ሁሉ በላይ አስፈላጊ ስለሆነ እና በሁሉም ላይ ሥልጣን ስላለው ነው፡፡ የእርሱ አገልጋዮች መላእክት መናፈስት . . . የእሳት ነበልባዮች አማራጭ ትርጉሞች፡ 1) እርሱን ልክ የሚያገለግሉትን መላእክት መናስፍስታትን እንደ እሳት መበልባል አድርጎ ፈጥሮዋቸዋል (UDB)፣ 2) ንፋስን እና የእሳት ነበልባን የእርሱ መልዕክተኞች አድርጎዋቸዋል፡፡
ስለ ለልጁ እንዲህ ብሏል፣ "ዙፋንህ ከዘላለም እስከ ዘላለም ነው . . . ስለዚህም አምላክ፣ የአንተ አምላክ የእግዚብሔር ልጅ ለዘላለም ይገዛል፡፡ ስለልጁ እንዲህ አለ "ስለልጁ እግዚአብሔር እንዲህ ብሏል" ልጅ ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ለሆነው ለኢየሱ በጣም ወሳኝ የማዕረግ ስም ነው፡፡ በትር መንግስት በንጉሥ ወይም ንግሥት ያላቸውን ስልጣን ለማሳየት በእጅ የሚያዝ ልዩ ዓይነት በተር ናት፡፡ ይበልጥ አንተን በደስታ ቅባት ቀባህ "ይበልጥ ደስታን ሰጠህ" የደስታ ቅባት አማራጭ ትርጉሞች 1) ሰዎች ደስታቸውን ለመግለጽ የሚቀቡት ልዩ መዓዛ ያለው ቅባት ወይም 2) ነገሥታ በሚነግሱበት ወቅት የሚቀቡት ቅባት ነው፡፡ በዚህም ሁኔታ ውስይ “ደስታ” የሚለው ቃል የሚመጣው እግዚአብሔር ከሚሰጠው ክብር ነው፡፡
ያረጃሉ እያረጁ ይሄዳሉ ልብስ ልብስ ትጠቀልላቸዋለህ ያረጁ ልብሶችን መጠቀም ስታቆም የሚታደርጋቸውን ለመግለጽ ጥቅም ላይ የሚውል ግሥን ተጠቀም፡፡ መጎናጸፊያ መጎናጸፊያ ወይም ከላይ የሚደረብ ልብስ
መርገጫ በሚትቀመጥበት ወቅት እግሮችህ የሚያርፉበት ሥፍራ ስለእነርሱ ለእነርሱ ሲባል ሁሉም መላእክት መናፈስት አይደሉምን አማራጭ ትርጉም: "ሁሉም መላእክት መናስፍት ናቸው"
1 ስለዚህ ከሰማነው ነገር እንዳንወሰድ፣ ስለ ሰማነው ነገር ይበልጥ መጠንቀቅ አለብን። 2 በመላእክት አማካይነት የመጣው መልእክት ጽኑ ከሆነና፣ ማንኛውም መተላለፍና ዐመፅ ተገቢውን ቅጣት የሚቀበል ከሆነ። 3 ታዲያ፣ይህንን ታላቅ መዳን ቸል ካልን እንዴት ማምለጥ እንችላለን? 4 እግዚአብሔርም ምልክቶችን፣ ድንቆችንና የተለያዩ ተአምራትን በማድረግ፣እንደ ፈቃዱ በታደሉት በመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች አማካይነት ምስክርነታቱን አጽንቶአል። 5 ይህ እየተናገርንለት ያለውን ወደ ፊት የሚመጣውን ዓለም እግዚአብሔር ለመላእክት አላስገዛም። 6 እንዲያውም በቅዱሳት መጻህፍት አንድ ሰው አንድ ስፍራ ሲናገር፣ 7 ሰውን ከመላእክት በጥቂት አሳነስኸው የክብርና የምስጋና ዘውድ ጫንህለት። [1]8 ማንኛውንም ነገር ከእግሮቹ በታች አስገዛህለት” ብሏል። እግዚአብሔር ከእግሩ በታች ሲያስገዛለት ምንም ያላስገዛለት ነገር የለም። ነገር ግን በእሁኑ ጊዜ ሁሉም ነገር ተገዝቶለት ገና አናይም። 9 ይሁን እንጂ፣ ከመከራውና ከሞቱ የተነሣ ከመላእክቱ በጥቂቱ አንሶ የነበረውን ኢየሱስ፣ የክብርና የምስጋና ዘውድ ተጭኖለት እናያለን። በእግዚአብሔር ጸጋ እርሱ ለሰው ሁሉ ሞትን ቀምሷል። 10 ሁሉም በእርሱና ለእርሱ የሚኖር ብዙ ልጆችን ወደ ክብር ለማምጣት የድነታቸውን መሥራች በመከራው አማካይነት እግዚአብሔር ፍጹም ሊያደርገው ተገቢ ሆነ። 11 የሚቀድሰውም ሆነ የሚቀደሱት ሁለቱም ከአንዱ ምንጭ፣ ከእግዚአብሔር ናቸው። በዚህም ምክንያት የሚቀድሳቸው እርሱን ወንድሞቼ ብሎ ሊጠራቸው አላፈረም። 12 እንዲያውም፣ 13 እንዲሁም፣ “እኔ በእርሱ እታመናለሁ” ይላል። በተጨማሪ፣ “እነሆ እኔንና እግዚአብሔር የሰጠኝን ልጆች ተመልከቱ” ብሏል። 14 ስለዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ሁሉ በሥጋና ደም ስለሆኑ፣ በሞቱ አማካይነት ሞት ላይ ሥልጣን ያለውን ማለትም ዲያብሎስን ለመሻር ኢየሱስም እንደ እነርሱ ሥጋ ለብሶ። 15 ይህም የሆነው ዕድሜ ልካቸውን በሞት ፍርሃት ምክንያት ዕድሜ ልካቸውን ባርነት ውስጥ የነበሩትን ሁሉ ነጻ ለማውጣት ነው። 16 እርግጥም እየረዳቸው ያለው መላእክትን ሳይሆን፣ የአብርሃም ዘሮችን ነው። 17 ስለሆነም የእግዚአብሔር በሆነ ነገር ሁሉ መሓሪና ታማኝ ሊቀ ካህን ለመሆንና ለሰዎችም ሁሉ የኃጢአት ይቅርታን ለማስግገኘት በሁሉም ረገድ ወንድሞችን መምሰሉ አስፈላጊ ሆነ። 18 ኢየሱስ ራሱ መከራ የተቀበለና የተፈተነ በመሆኑ፣ የሚፈተኑትን ሁሉ ሊረዳቸው ይችላል።
ምናልባት እንዳንወሰድ "ስለዚህም እንዳንጠፋ"
ትክከለኝነቱ የተረጋገጠ እውነት መሆኑ የተረጋገጠ ማንኛውም መተላለፍ እና አለመታዘዝ የሚገባውን ቅጣት ይቀበላል አማራጭ ትርጉም: "ኃጢአት ያደረገ ማንኛውም ሰው እና የማይታዘዝ ሰው ሁሉ የሚገባውን ቅጣት ይቀበላል፡፡" መተላለፍ እና አለመታዘዝ እነዚህ ሁለት ቃላት በመሠረቱ ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው ሲሆን ማንኛውም አለለመታዘዝ ቅጣት እንደሚያስከትል አጽኖት ይሰጣል፡፡ መተው "ትኩረት አለመስጠት" ወይም "አለመቀበል" አከፋፈለ ሰጠ፣ መሰከረ እንደ እርሱ ፈቃድ "ፈጸም በሚፈልገው መልኩ"
የሰው ልጆች ሰዎች ለእርሱ አንዳች ነገር ሳያስገዛ አልተወም አማራጭ ትርጉም፡ "ሁሉን ነገር ለእርሱ አስገዛለት"
ከመለአክት አንሶ ሳለ . . . ክብር እና ምስጋና ይህንን በ HEB 2:7 ላይ በተረጎምከው መሠረት ተርጉመው፡፡ ልጆች በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ቃል የሚያመለክተው በክርስቶስ ያመኑ ሰዎችን ነው፡፡
ወንድሞች ልላቸው ከተውንም አላፈረም "ወንድሞቹ ልላቸው ወዷል" ወንድሞች በዚህ ሥፍራ ይህ ቃል የሚያመለክተው ክርስትያን ወንድሞችን ነው፡፡ ይህም በክርስቶስ ያመኑት ሁሉ እግዚአብሔር ሰማያዊ አባታቸው የሆነ፤ የአንድ መንፈሳዊ ቤተሰብ አባላት ከመሆናቸው የተነሣ ነው፡፡
እነንደገናም እንዲህ አለ አማራጭ ትርጉም: "እንደገናም ነቢይ በሌላ ቅዱስ መጽሐፍ ላይ ክርስቶስ ስለ እግዚአብሔር ያለውን እንዲህ ጽፎታል፡" (UDB) የእግዚአብሔር ልጆች በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ቃል የሚያመለክተው መንፈሳዊ ልጆቹ የሆኑትን ሰወዎችን ነው፡፡ ለምሳሌ ያኸል፣ "የእግዚአብሔር ልጆች" የሚለው ቃል በኢየሱስ በማመን የእግዚአብሔር የሆኑትን ሰዎችን ነው፡፡ ሁሉም ሥጋንና ደምን ተካፍለዋል አማራጭ ትርጉም: "ሁሉም የሰው ልጆች ናቸውን" ሕይወታቸውን ሁሉ በባርነት ኖረዋል ይህ ሀረግ ምሳሌያዊ ነው፡፡ የሚያመለክተውም ሞትን በመፍራት ባርነት ውስጥ መኖራቸውን ነው፡፡
አገኘ አማራጭ ትርጉም: "አገኘ"
1 ስለዚህ የሰማያዊ ጥሪ ተከፋዮች የሆናችሁ ቅዱሳን ወንድሞች የእምነታችንን ሐዋርያና ሊቀ ካህናት የሆነውን ኢየሱስን አስቡ። 2 ሙሴ በእግዚአብሔር ቤት ሁሉ ላይ ታማኝ እንደ ነበር ሁሉ፣ እርሱም ለሾመው ለእግዚአብሔር ታማኝ ነበር። 3 ቤቱን የሚሠራው ከራሱ ከቤቱ የበለጠ ክብር እንዳለው ሁሉ፣ ኢየሱስም ከሙሴ ይልቅ የበለጠ ክብር እንደሚገባው ተቆጥሯል። 4 ማንኛውም ቤት ሠሪ አለው፤ ሁሉም ነገር የሠራ ግን እግዚአብሔር ነው። 5 ወደ ፊት መነገር ለሚገባው ነገር ምስክር እንዲሆን፣ ሙሴም በእግዚአብሔር ቤት ሁሉ እንደ አገልጋይ ታማኝ ነበር። 6 ክርስቶስ ግን በእግዚአብሔር ቤት ሥልጣን ያለው ልጅ ነው። የምንተማመንበትንና የመተማመናችንን ድፍረት አጥብቀን ብንይዝ ቤቱ ነን። 7 ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ፣ዛሬ ድምጹን ብትሰሙ 8 በምድረበዳ በፈተና ቀን በአመጽ እንዳደረጋችሁት ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ። 9 ይህ የሆነው አባቶቻችሁ እኔን በመፈታተን ሲያምፁብኝና ዐርባ ዓመት ሙሉ ሥራዎቼን ባዩበት ጊዜ ነበር። 10 ስለዚህ በዚያ ትውልድ ደስ አልተሰኘሁም። እንዲህም አልኩ፤ ልባቸው ሁል ጊዜ ይስታል መንገዴንም አላወቁም። 11 ስለዚህ በቁጣዬ፥ "ወደ እረፍቴ አይገቡም" ብዬ ማልሁ። 12 ወንድሞች ሆይ ከእናንተ ማንም የማያምን ክፉና ከሕያው እግዚአብሔር ዘወር የሚል ልብ እንዳይኖረው ተጠንቀቁ። 13 ይልቁንስ ከእናንተ ማንም በኃጢአት መታለል እልኸኛ እንዳይሆን ከዛሬ ጀምሮ በየዕለቱ እርስ በርሳችሁ ተበረታቱ። 14 ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ድረስ በእርሱ ያለንን ድፍረት አጥብቀን ከያዝን ከክርስቶስ ጋር ተባባሪዎች እንሆናለን። 15 ስለዚህም፣ "ዛሬ ድምጹን ብትሰሙ በአመጽ ጊዜ እንደሆነው ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ" ተብሏል። 16 ለመሆኑ፣እነዚያ ድምፁን ሰምተው ያመፁት እነማን ነበሩ? ሙሴ እየመራ ከግብፅ ያወጣቸው ሁሉ አይደሉምን? 17 ለአርባ ዓመት እግዚአብሔር የተቆጣባቸውስ እነማን ነበሩ? ኃጢአት ያደረጉና ሬሳቸው በበረሃ ወድቆ የቀረው አይደሉምን? 18 ደግሞስ እነዚያ ያልታዘዙት ካልሆኑ በቀር ወደ ዕረፍቱ እንደማይገቡ እግዚአብሔር የማለባቸው እነማን ሊሆኑ ነው? 19 ባለማመናቸው ምክንያት ወደ ዕረፍቱ ሊገቡ እንዳልቻሉ እናያለን።
ወንድሞች በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ቃል የሚያመለክተው ወንዶች እና ሴቶችን ያካተተ ክርስቲያኖችን ነው፡፡ ምክንያቱም በክርስቶስ የሆኑት እግዚአብሔር ሰማያዊ አባታቸው የሆኑ የአንድ መንፈሳዊ ቤተሰብ አባላት ናቸውና፡፡ የሃይማኖታችን አማራጭ ትርጉም፡ "እኛ የተቀበልነው" ወይም "እኛ ያመንበት"
የእግዚአብሔር ቤት በእግዚአብሔር ቤተሰብ ውስጥ ያሉ ሰዎች ልጅ ይህ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው የኢየሱስ ወሳኝ ስም ነው፡፡ የምንደፍርበት የምንመካበት አማራጭ ትርጉም፡ "እኛ የምንመካበት ተስፋ አለን"
አለመደሰት "ደስተኛ አለመሆን" በልባቸው ሁሉ ጊዜ ይኮበልላሉ አማራጭ ትርጉም: "ሁል ጊዜ እኔን ለመከተል አይፈልጉም" ወደ እረፍቴ አይገቡም "እኔ በሚገኝበት ሆነው እንዲያርፉ አልፈቅድላቸውም"
ኖት የለውም።
ወንድሞች በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ቃል የሚያመለክተው ወንዶች እና ሴቶችን ያካተተ ክርስቲያኖችን ነው፡፡ ምክንያቱም በክርስቶስ የሆኑት እግዚአብሔር ሰማያዊ አባታቸው የሆኑ የአንድ መንፈሳዊ ቤተሰብ አባላት ናቸውና፡፡ ከእናንተ በማንኛችሁም ውስጥ የማያምን ክፉ ልብ "ክፉ የሆነ፣ የማያምን ልብ በማናችሁም ውስጥ" ወይም "ማንኛችሁም ክፋትን እንዲታደርጉ የሚያደረግ የማያምን ልብ" ኮብላይ ልብ "እንድትኮበልሉ የሚያደርግ ልብ፡፡" ሕያው አምላክ አማረጭ ትርጉም: 1) "በእርግጥ ሕያው የሆነ እውነተኛ አምላክ" ወይም 2) "ሕይወትን የሚሰጥ አምላክ፡፡" ዛሬ ተብሎ ስጠራ ሳለ ዕድሉ እስካለ ድረስ ከእናንተ መካከል ማንም በኃጠአት ተታሎ ልቡን እንዳያደነድን አማራጭ ትርጉም፡ "እልከኛ እንዳይሆን፣ ሌሎች እንዲያስቱት እንዳይፈቅና ኃጢአት እንዳያደርግ" ወይም "ኃጢአትን አታድረግ፣ ራስህን አታታል እንዲሁም እለከኛ አትሁን"
እኛም ሆነናልና ጸሐፊውና አንባቢያኑ ሁለቱም መተማመን ፍጹም የሆነ እምነት እስከ መጨረሻው ሞት ድምፁን "እግዚአብሔር" ወይም "እግዚአብሔር የተናገረውን" ልባችሁን አታደንድኑ፣እስራኤላዊያነ በአመፅ እንዳደረጉት ይህንን በ HEB 3:8 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከት፡፡
የእርሱ እረፍት የእግዚአብሔር ሕዝብ እግዚአብሔር የሰጣቸውን የተስፋ ቃላት ሁሉ ፍጻሜን አግኝቶ በመመልከት ሐሴት የሚያደርግበት እና መከራ ያሌለበት ሥፍራ ነው፡፡ እኛ ጸሐፊው እና አንባቢያኑ
1 ከእናንተ ማንም የእግዚአብሔር ዕረፍት ከሆነው ዘላቂ ተስፋ የሚጎድል እንዳይመስለው በጣም መጠንቀቅ አለብን። 2 ምክኒያቱም ለእስራኤላውያን እንደ ተነገረ ሁሉ ለእኛም ስለ እግዚአብሔር ዕረፍት መልካም ዜና ተነግሮናል፤ ሆኖም፣ የሰሙትን መልእክት ሰሞዎቹ በእምነት ስላልተቀበሉት አልጠቀማቸውም። 3 “ወደ ዕረፍቴ አይገቡም፣ ብዬ በቁጣዬ ማልሁ” እንዳለው ሳይሆን እኛ ያመንን ግን ወደ ዕረፍቱ እንገባለን። የእርሱ ፍጥረት ሥራ ከዓለም መፈጠር ጀምሮ የተጠናቀቀ ቢሆንም፣ 4 ስለ ሰባተኛ ቀን በማመልከት አንድ ቦታ “በሰባተኛው ቀን እግዚአብሔር ከሥራው ሁሉ ዐረፈ” ይላል። 5 ደግሞም፣ “ወደ ዕረፍቴ አይገቡም” ይላል። 6 ወደ እግዚአብሔር ዕረፍት ለመግባት ለአንዳንዶች አሁንም የተጠበቀባቸው በመሆኑና ፣ መልካሙን ዜና ከሰሙት እስራኤላውያን ብዙዎቹ ባለ መታዘዛቸው ምክንያት ወደ ዕረፍቱ ባለ መግባታቸው እግዚአብሔር በድጋሚ፣ 7 “ዛሬ” የተባለ ቀን ወስኖአል። 8 ኢያሱ አሳርፎአቸው ቢሆን ኖሮ፣ እግዚአብሔር ስለ ሌላ ቀን አይናገርም ነበር። 9 ስለዚህ ለእግዚአብሔር ሕዝብ አሁንም ቢሆን የሰንበት ዕረፍት ተጠብቆላቸዋል። 10 ምክንያቱም ወደ እግዚአብሔር ዕረፍት የገባ ሰው እግዚአብሔር ከሥራው እንዳረፈ ሁሉ፣ እርሱም ከሥራው ያርፋል። 11 ስለዚህ ማንም የእነዚያን ሰዎች ዐመፅ ተከትሎ እንዳይወድቅ ወደዚያ ዕረፍት ለመግባት እንናፍቅ። 12 የእግዚአብሔር ቃል ሕያው፣ የሚሠራና፣ ሁለት አፍ ካለው ሰይፍ ይልቅ፣ ስለታም ነው። ነፍስንና መንፈስን፣ ጅማትንና ቅልጥምን እስኪለያይ ድረስ ይወጋል። የልብን ሐሳብና ውስጥን ይመረምራል። 13 ከእግዚአብሔር ፊት የሚሰወር ምንም ፍጥረት የለም። እኛ ተጠያቂዎች በሆንንበት በእርሱ ዓይኖች ፊት ማንኛውም ነገር የተገለጠና የተራቆተ ነው። 14 እንግዲህ በሰማያት ያለፈ ታላቅ ሊቀ ካህናት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ስላለን፣ እምነታችንን አጥብቀን እንያዝ። 15 ነገር ግን እርሱ ከኃጢአት በቀር በማንኛውም ነገር እንደ እኛ የተፈተነ ነው እንጂ በድካማችን ሊራራልን የማይችል ሊቀ ካህናት የለንምና። 16 ስለዚህ በሚያስፈልገን ጊዜ ምሕረትንና የሚረዳንን ጸጋ እንድንቀበል ወደ ጸጋው ዙፋን በድፍረት እንቅረብ።
ስለዚህ ምክንያም እግዚአብሔር በእርግጠኝነት የማይታዘዙትን ሰዎች ይቀጣልና (HEB 3:19) ከእናንተ መካከል ማንኛችሁም እግዚአብሔር ተስፋ ወደ ገባው የእግዚአብሔር እረፈት ሳይገባ እንዳይቀር አማራጭ ትርጉም፡ "ከእናንተ መካከል ማንንም እግዚአብሔር ወደ እርሱ አይገቡም ብሎ እንዳይናገር" ወይም "እግዚአብሔር ለሁላችሁም እርሱ ባለበት ያርፉ ዘንድ ተንግሯቸዋል" እንዲህ ማድረግ ይጠበቅብናል ጸሐፊው እና አንባቢያኑ ይህንን ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ለእኛ ለጸሐፊዎቹ እና ለአንባቢያኑ በእምነት ከራሳቸው ጋር ሳያዋህዱ የሰሙት ሰዎች አማራጭ ትርጉም፡ "የኢየሱስን መልዕክት የሰሙት ነገር ግን ያላመኑት ሰዎች"
የፍጥረት ሥራው ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ተፈጽሟል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ዓለም ከመፈጠሩ በፊት እንኳ ዕቅዱ ሙሉ ለሙሉ ታውቋል፡፡" ወደ እረፍቴ ፈጽሞ አይገቡም "እኔ ባለሁበት በዚያ አያርፉም"
አንዳንዶች ይገቡበት ዘንድ የእግዚአብሔር እረፍት ተጠብቆላቸዋል፡፡ "እግዚአብሔር አንዳንድ ሰዎች ከእርሱ ጋር ያርፉ ዘንድ ፈቅደቃል፡፡" ድምፁ "እግዚአብሔር" ወይም "እግዚአብሔር እያለ ያለው" ልባችሁን አታደንድኑ ይህንን በ HEB 3:8 ላይ ምንም ብላችሁ እንደተረጎማችሁ ተመልከቱ፡፡
ወደ እግዚአብሔር እረፍት የሚገቡት "እግዚአብሔር ባለበት ከእርሱ ጋር የሚያርፉት ሰዎች" ወደዚያ እረፍት ለመግባት እንትጋ "በተጨማሪ እግዚአብሔር በሚገኝበት ከእርሱ ጋር ለማረፍ ማድረግ የሚገባንን ነገር ሁሉ እናድረግ" እንትጋ "ፈቃደኞች እንሁን" ልክ አንደእነርሱ ባለመታዘዝ እንዳንወድቅ አማራጭ ትርጉም: "በተመሳሳይ መልኩ አለመታዘዝ" እነርሱ ያንን አደረጉ በበረሃ እስራኤላዊያን በእግዚአብሔር ላይ በማመጽ ያንንን አደረጉ
የእግዚአብሔር ቃል የእግዚአብሐየር ቃል ወይም እግዚአብሔር የተናገረው መልዕክት ሕያው እና የሚሠራ እግዚአብሔር ቃል ሕያው እንደሆነ፤ እንዲሁም ኃይል አለው፡፡ ከባለ ሁለት አፍ ሰይፍ ይልቅ አፍ ሰይፍ - የእግዚአብሔር ቃል ወደ ሰው ውስጥ ዘልቀው ይገባል፡፡
የልብን ሀሳብ እና መነሻ ሀሰብ ያውቃል የእግዚአብሔር ቃል ድብቅ ሀሳባችንን እንኳ ሳይቀር ይገልጣል፡፡ and ሁሉ ነገር የተገለጸ ነው እንዲሁም በመጨረሻ ተጠያቂ በሚንሆንበት በእርሱ ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተ ነው፡፡ "በአኗኗራችን መሠረት የሚፈርድብን እንዲሁም ሁሉንም ነገራችንን የሚመለከት እግዚአብሔር ነው፡፡" የተራቆተ እና የተገለጠ ነው እነዚህ ሁለት ቃላት በመሠረቱ ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው ሲሆኑ አጽኖት የሚሰጡትን ከእግዚአብሔር ፊት ምንም የተሠወረ ነገር አለመኖሩን ነው፡፡
ኢየሱስ የእግዚብሔር ልጅ፣ እምነታችንን አጥብቀን እንያዝ አማኞች “የእግዚአብሔር ልጅ” የሆነውን ኢየሱስን “አጥብቀው መያዝ” ይኖርባቸዋ፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ ይህ የኢየሱስ እጅግ ወሳኝ የሆነ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ለእኛ የማይራራ ሊቀ ካህን የለንም፡፡ "ያለን ሊቀ ካህን ለእኛ የሚራራ ነው፡፡" እርሱ ኃጢአት የለበትም አማራጭ ትርጉም፡ "እርሱ ኃጢአት አላደረገም" የጸጋው ዙፋን አማራጭ ትርጉም: "ጸጋ የሚገኝበት የእግዚአብሔር ጸጋ" ወይም "ለጋስ የሆነው እግዚአብሔር በዙፋኑ ላይ ተቀምጧል፡፡"
1 እያንዳንዱ ሊቀ ካህን ከሰዎች መካከል ይመረጣል፤ ለኃጢአት መሥዋዕትንና መባን ለማቅረብ እግዚአብሔርን በሚመለከት ጉዳይ እነርሱን በመወከል ይሾማል። 2 እርሱ ራሱም በድካም ውስጥ ያለ በመሆኑ ዐላዋቂዎችንና ከመንገድ የሳቱትን ሊራራላቸው ሊቀበላቸው ይችላል። 3 ከዚህም የተነሣ ለሕዝቡ ኃጢአት እንደሚያድርገው ሁሉ እርሱም ለገዛ ራሱ ኃጥአት መሥዋዕት ማቅረብ ይኖርበታል። 4 እንደ አሮን በእግዚአብሔር የተጠራ ካልሆነ በቀር ማንም ይህን ክብር በራሱ አያገኘውም። 5 ክርስቶስ ራሱም ቢሆን ሊቀ ካህናት የመሆንን መብት በገዛ ራሱ አልወሰደም። ይልቁንም እግዚአብሔር ለእርሱ፣ 6 ይህም በሌላ ቦታ፣ እግዚአብሔር፣እንደመልከጼዴቅ ሹመት አንተ ለዘላለም ካህን ነህ" ይላል። 7 ኢየሱስ ሰው ሆኖ በዚህ ምድር በነበረ ዘመን ፣ ከሞት ሊያድነው ወደሚችለው አምላክ በታላቅ ጩኸትና በብዙ እንባ ጸሎትንና ልመናን አቀረበ። እግዚአብሔርን በመፍራቱም ጸሎቱ ተሰማለት። 8 ምንም እንኳ እርሱ ልጅ ቢሆንም፣ ከደረሰበት መከራ የተነሣ መታዘዝን ተማረ። 9 በዚህ ሁኔታ ሁሉ የዘላለም ድነት ምክንያት ሆነላቸው፤ 10 እግዚአብሔርም እንደ መልከጼዴቅ ሹመት ሊቀ ካህናት አድርጎ ሾመው። 11 ስለ ኢየሱስ ብዙ የምንናገረው አለን፤ ሆኖም፣ ለመቀበል ዳተኞች ስለሆናችሁ፣ ለእናንተ ማስረዳት አዳጋች ነው። 12 እስከ አሁን ድረስ መምህራን መሆን ሲገባችሁ፣ የእግዚአብሔርን ቃል መሠረታዊ መርሖዎች የሚያስተምራችሁ ሰው ገና ትፈልጋላችሁ። እናንተ የምትፈልጉት ወተት እንጂ፣ ጠንካራ ምግብ አይደለም። 13 ወተት ብቻ ሊጋት ማንኛውም ሰው ገና ሕፃን ስለሆነ የጽድቅ ትምህርት ልምምድ የለውም። 14 በሌላ በኩል ደግሞ ጠንካራ ምግብ ግን መልካምንና ክፉውን መለየት ለተማሩና ትክክል የሆነውን ካልሆነው የመለየት ልምድ ላላቸው ትልልቅ ሰዎች ነው።
በእነርሱ ፈንታ ይፈጽማል አማራጭ ትርጉም: "እነርሱን ይወክላል" ይገባቃል አማራጭ ትርጉም: "ይጠበቅበታል"
ልጅ . . . አባት ይህ በኢየሱስ እና በእግዚአብሔር አባት መካል ያለውን ግንኙነት የሚያሳይ በጣም ወሳኝ የሆነ የማዕረግ ስም ነው፡፡
እንደገናም እንዲህ አለ እግዚአብሔርም እንዲህ አለ (HEB 5:5)
በሥጋው ወራት አማራጭ ትርጉም: "በምድር ላይ ሲኖር ሳለ" ልጅ፣ በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ቃል የሚያመለክተው የሰው ልጅ ሆኖ ወደ ምድር የመጣውን የእግዚአብሔር ልጅ የሆነውን ኢየሱስን ነው፡፡
ፈጸመ በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ቃል የሚያመለክተው "ማጠናቀቅን" ወይም "ሙሉ መሆንን" ነው፡፡ እናንተ ለማድመጥ የዘገያችሁ ናችሁ "እናንተ ለመረዳት የዘገያችሁ ናችሁ" ወይም "እናንተ ለማድመጥ ምንም ፍላጉት የላችሁም"
መርሆዎች በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ቃል ያለው ትርጉም መመረያ ወይም ውሳኔ ለመወሰን የሚረዳ መርህ ነው፡፡ ወተት መሠረታዊ የሆነ መንፈሳዊ እውነቶች ጠንካራ ምግብ "ጠንካራ መንፈሳዊ እውነቶች"
1 ስለዚህ ስለ ክርስቶስ መልእክት በመጀመሪያ የተረዳነውን ተወት በማድረግ ወደ ብስለት ልንሻገር ይገባናል እንጂ ከሞተ ሥራ ንስሐ መግባትንና በእግዚአብሔር ማመንን፣ 2 ወይም ጥምቀቶችን፣እጆች መጫንን፣ የሙታን ትንሳኤን እንዲሁም የዘላለም ፍርድን ወደ ሚመለከት መሠረትን የመጣል ትምህርት መመለስ አይገባንም። 3 እግዚአብሔር ከፈቀደ እነዚህንም እናደርጋለን 4 ይህንን የምናደርገው አንድ ጊዜ ብርሃን በርቶላቸው ሰማያዊውን ስጦታ የተቀበሉትን፣ከመንፈስ ቅዱስ ተሳታፊዎች የነበሩትን፣ 5 መልካሙን የእግዚአብሔር ቃልና በመጪው ዘመን ሊመጣ ያለውን ኃይል ከቀመሱ በኃላ 6 የካዱትን በንስሐ እንዲታደሱ ማድረግ የማይቻል በመሆኑ ነው። እነዚህ ለሕዝብ መሳለቂያ ይሆን ዘንድ ራሱን የእግዚአብሔርን ልጅ ራሳቸው እንደገና ይሰቅሉታል። 7 በእርሷ ላይ ብዙ ጊዜ የሚዘንበውን ዝናብ ተቀብላ ለደከሙባት የሚጠቅም ፍሬን የምታፈራ መሬት ከእግዚአብሔር በረከትን ትቀበላለች። 8 እሾህና አሜኬላ የምታበቅል ከሆነች ግን ዋጋ ቢስና እርግማን የሚጠብቃት ትሆናለች፣ ፍጻሜዋም መቃጠል ይሆናል። 9 እንደዚህ የምንናገር ብንሆንም፣ ወዳጆች ሆይ፣ እናንተንና ድነታችሁን በሚመለከት ግን የተሻለ ነገር ስለ መኖሩ እርግጠኞች ነን። 10 ምክንያቱም ቅዱሳንን በማገልገላችሁና አሁንም እያገለገላችኋቸው በመሆኑ ለስሙ ያላችሁን ፍቅር በማሳየት የሠራችሁትን ሥራ ይረሳ ዘንድ እግዚአብሔር ዓመፀኛ አይደለም። 11 በፍጹም የመተማመን ዋስትና እያንዳንዳችሁ ይህንኑ ትጋት እስከመጨረሻ እንድታሳዩ በእጅጉ እንናፍቃለን። 12 ከእምነትና ከትዕግሥት የተነሣ የተስፋ ቃሉን የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ቸልተኞች እንድትሆኑ አንፈልግም። 13 ምክንያቱም እግዚአብሔር ለአብርሃም የተስፋ ቃል በገባለት ጊዜ ከራሱ በሚበልጥ በማንም ሊምል ስላልቻለ 14 “በእርግጥ እባርክሃለሁ፣ ዝርያዎችህንም እጅጉን አበዛለሁ” በማለት በራሱ ምሎአልና። 15 በዚህ መንገድ በትዕግሥት ከጠበቀ በኃላ ተስፋ የተገባለትን ተቀበለ። 16 ሰዎች ከእነርሱ በሚበልጠው ይምላሉና፣ በመካከላቸው ለሚፈጠርውም ለማንኛውም ሙግት መሐላ የመጨረሻው ማጽኛ ነው። 17 የዓለማውን የማይለወጥ ባሕርይ ለተስፋው ወራሾች ይበልጥ ግልጽ አድርጎ ለማሳየት እግዚአብሔር በወሰነ ጊዜ በመሃላ አጸናው። 18 ይህንን ያደረገው እግዚአብሔር ሊዋሽ በማይችልባቸው ሁለት የማይለወጡ ነገሮች በፊታችን ያለውን መተማመኛ አጥብቀን ይዘን አምባ ፍለጋ ለሸሸን ለእኛ ብርቱ ድፍረት ይሆንልን ዘንድ ነው። 19 ከመጋረጃው በስተጀርባ ወዳለው ቅድስት የሚገባውና እኛ የያዝነው ይህ መተማመኛ፣ ሥጋት የሌለበትና አስተማማኝ የነፍሶቻችን መልሕቅ ነው። 20 በመልከ ጼዴቅ ሥርዓት ለዘላለም ሊቀ ካህናት በመሆን ኢየሱስ ወደዚህ ስፍራ ለእኛ ቀዳሚ በመሆን ገብቷል።
ወደፊት መግፋት ይኖርብናል አማራጭ ትርጉም: "ወደፊት መገስገስ ይኖርብናል" እጆቻችንን በመጫን ይህ ዓይነቱ ልምምድ የሚደረገው አንድ ነው ለልዩ አገልፍሎት ወይም ሥልጣን ለመለየት ነው፡፡
ሰማያዊ ስጦታን የቀመሱ ይህ የሚያመለክተ እግዚአብሔር ያዳናቸውን አማኞችን ነው፡፡ የእግዚአብሔር መልካም ቃል የቀመሱትን ይህ የእግዚአብሔርን ቃል ራሳቸው አማኞችን የሚያመለክት ነው፡፡ የእግዚአብሔርን ልጅ ይሰቅሉታል ሰዎች ከእግዚአብሔር ፊታቸውን ሲያዞሩበት ልክ ኢየሱስን እንደሚሰቅሉት ነው፡፡ ወደቁ አማራጭ ትርጉም: "ከእግዚአብሔር ፊታቸውን አዙሩ"
እግዚአብሔር ይረሳ ዘንድ አመጸኛ አይደለም አማራጭ ትርጉም፡ "እግዚአብሔር ፍትሐዊ ነው እንዲሁም አይዘነጋም" HEB << | HEB >>
ታታርነት ጥንቃቄ የተሞላበት በትጋት መሥራት ዳተኛ ሰነፍ መመስል የሌላውን ሰው ባሕርይ ለመምሰል የሚደረግ ጥረት
እንዲህ ይላል እግዚአብሔር እንዲህ ይላል
እርግጥ እና ጽኑ መልሕቅ በዚህ ሥፍራ ላይ “እርግጥ” እና “ጽኑ” ተብለው የተተረጎሙት ቃላት በመሠረታዊ ትርጉማቸው ተመሳሳይ ሲሆኑ አጽኖት ሰጥተው የሚያሳዩት መልሕቁ ላይ ሙሉ ለሙሉ አስተማማኝ መሆኑን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ፈጹም አስተማማኝ መሕልቅ" የነፍሳችን መሕልቅ መሕልቅ ጀልባ በውሃ ተንድታ እንዳትወሰድ እንደሚያደረግ ሁሉ ኢየሱስ በእግዚአብሔር መገኘት ውስጥ እንድንሆን ያደርገናል፡፡ ስለእኛ ቀዳሚ ነው "ስለ እኛ ሲል ቀድሞ የሄደ"
1 የሳሌም ንጉሥና የልዑል እግዚአብሔር ካህን የነበረው ይህ መልኬ ጼዴቅ የባረከው አብርሃምን ነገሥታቱን ድል አድርጎ ሲመለስ ነበር። 2 አብርሃምም ከማረጀው ከማንኛውም ነገር አንድ አሥረኛውን ለእርሱ ሰጠው። ‘መልኬ ጼዴቅ’ የሚለውም የስሙ ትርጉም ‘የጽድቅ ንጉሥ’ ደግሞም ‘የሳሌም ንጉ’ ማለትም ‘የሰላም ንጉሥ’ ማለት ነው። 3 እርሱ አባትም ሆነ እናት፣ የትውልድ ሐረግም ሆነ የጅማሬ ወይም የፍጻሜ አመን የሌለው ነው። ይልቁንም እንደ እግዚአብሔር ልጅ ሁሉ እርሱም ካህን ሆኖ ለዘላለም ይኖራል። 4 ይህ ሰው እንግዲህ ምን ያህል ታላቅ እንደነበረ አስቡ። አባታችን አብርሃም በጦርነት ካገኛቸው ምርጥ ነገሮች አንድ አሥረኛ የሚሆነውን ሰጥቶታል። 5 በእርግጥ የክህነቱን አገልግሎት የተቀበሉትም የሌዊ ዝርያዎች ከአብርሃም ዝርያ የተገኙ ቢሆኑም ከሕዝቡ ማለትም ከእስራኤላውያን ወገኖቻቸው አሥራትን ይሰበስቡ ዘንድ በሕጉ ታዘዋል። 6 ይሁን እንጂ የሌዊ ዝርያ ያልነበረው መልኬ ጼዴቅ የተስፋ ቃሎች ከነበሩት ከአብርሃም አሥራትን ተቀበለ፣ ባረከውም። 7 ታናሹ በታላቁ እንደሚባረክ የሚካድ ነገር አይደለም። 8 በአንድ በኩል ስናየው አሥራትን የሚቀበሉ ሰዎች አንድ ቀን ይሞታሉ በሌላ በኩል ስንመለከተው ግን ከአብርሃም አሥራትን የተቀበለው ሕያው ሆኖ እንደሚኖር ተገልጿል። 9 በሌላ አነጋገር አሥራትን ይቀበል የነበረው ሌዊ እንኳን በአብርሃም በኩል አሥራትን ሰጥቷል። 10 ምክንያቱም መልኬ ጼዴቅ አብርሃምን ባገኘው ጊዜ ሌዊ በቀደምት አባቱ በአብርሃም አብራክ ውስጥ ነበረና። 11 ሕዝቡ ሕጉን የተቀበሉት በዚህ ሥርዓት በነበሩ ጊዜ ነበርና ፍፁምና በሌዊ ክህነት ማግኘት የሚቻል ቢሆን ኖሮ በአሮን ሥርዓት ሳይሆን በመልከ ጼዴቅ ሥርዓት የሚሾም ሌላ ካህን ወደፊት ይነሳ ዘንድ ምን ያስፈልግ ነበር? 12 ክህነቱ የሚለውጥ ከሆነ ደግሞ ሕጉም መለወጥ ይገባዋል። 13 እነዚህ ነገሮች እየተነገሩለት ያለው ከወገኖቹ ከቶ ማንም በመሠዊያው ላይ አገልግሎ የማያውቅ የሌላ ነገድ ወገን ነውና። 14 እንግዲያውስ ጌታችን ካህናትን በሚመለከት ሙሴ ከቶውንም ምንም ካልተናገረለት ከይሁዳ ነገድ የመጣ መሆኑ ግልጽ ነው። 15 መልከ ጼዴቅን የመሰለ ሌላ ካህን ቢነሳ የምንለው ይበልጥ ግልጽ ይሆናል። 16 ይሄኛው ካህን ደግሞ ሰብዓዊ ዝርያን መሠረት በሚያደርገው ሕግ ሳይሆን የማይጠፋ የሕይወት ያይልን መሠረት ባደረገ ሕግ ካህን የሆነ ነው። 17 ቅዱሳት መጻሕርትም ስለ እርሱ እንዲህ ሲሉ ይመሰክራሉ፦ “በመልከ ጼዴቅ ሥርዓት አንተ ለዘላለም ካህን ነህ” 18 የቀደመው ትዕዛዝ ገለል የተደረገው ደካማና የማይጠቅም በመሆኑ ነውና። 19 ሕጉ ፍጹም ያደረገው ምንም ነገር አልነበረምና። ይሁን እንጂ ከዚህ በኃላ ወደ እግዚአብሔር የምንቀርብበት የተሻለ መተማመኛ አለ። 20 ይሄኛው የተሻለው መተማመኛ ግን ያለ መሃላ እውን አልሆነም፣ ምክንያቱም እነዚህ ሌሎቹ ካህናት ምንም መሃላ አልፈጸሙም። 21 “ጌታ ምሎአል ሃሳቡንም አይቀይርም፤ ‘አንተ ለዘላለም ካህን ነህ’” ተብሎ እንደተጻፈ። 22 በዚህም ደግሞ ኢየሱ ለሚሻል ኪዳን ዋስ ሆኖአል። 23 በእርግጥም ሞት ካህናቱን ለዘላለም ከማገልገል ያግዳቸዋል። እብንዱ ሌላውን እየተካ፣ ካህናት የሆኑት የበዙት ከዚህ የተነሣ ነው። 24 ኢየሱስ ግን ለዘላለም ስለሚኖር የእርሱ ክህነት የማይለወጥ ነው። 25 ስለዚይ ስለ እነርሱ ሊማልድ ምን ጊዜም በሕይወት ስለሚኖር በእርሱ በኩል ወደ እግዚአብሔር የሚቀርቡትን ሙሉ በሙሉ ሊያድናቸው ይችላል። 26 እንደዚህ ያለው ማለትም ኃጢአትና ነቀፋ የሌለበት፣ ንጡሕ፣ ከኃጢአተኞች የተለየ ከሰማያትም በላይ ከፍ ያለ ሊቀ ካህን ሊኖረን ይገባል። 27 እርሱ ሊቀ ካህናቱ ሲያደርጉት እንደነበረው በመጀመሪያ ራሱ ለሠራቸው ኃጢአቶች ከዚያም ሕዝቡ ሁሉ ለፈፀሟቸው ኃጢአቶች በየቀኑ መሥዋዕቶችን ማቅረብ አያስፈልገውም። ራሱ አሳልፎ በሰጠ ጊዜ ይህንን ለአብዴና ለመጨረሻ ጊዜ አድርጎታል። 28 ሕጉ ድካም ያለባቸውን ሰዎች ሊቀ ካህናት አድርጎ ይሾማልና፣ ከሕጉ በኃላ የመጣው የመሐላው ቃል ግን ለዘላለም ፍጹም የተደረገውን ልጁን ሾሟልና።
እርሱ አባት የለው መልከጼደቅ አባት የለውም የዘመን ጅማሬ ወይም የሕይወት ፍጻሜም የለውም መልከጼደቅ የተወለደበትን ወይም የሞተበትን ዘመን የሚያሳይ ምንም መረጃ የለም፡፡
የክህነት አገልግሎት የተሰጣቸው ከሌዊ ወገን አማራጭ ትርጉም: "ካህናት የሚሆኑት ከሌዊ ወገን የሆኑት ናቸው፡፡" የሌዊ ወገን የሆኑት ሁሉ ግን ካህናት አይሆኑም፡፡
was in the private parts of his ancestor Abraham AT: "had not yet been born"
what further need was there for another priest to arise after the order of Melchizedek, and not be named after the order of Aaron? "no one would have needed another priest, one who was like Melchizedek and not like Aaron, to arise."
ከሰው ዘር ጋር ግንኙነት ያላቸው ሕጎች ክርስቶስ የሌዊ ወገን ሳይሆን ካህን መሆን ይችል ነበር፡፡ እንደ መልከ ጼደቅ ሹመት አማራጭ ትርጉም: "እንደ መልከ ጼደቅ"
ሕጉ ምንም ነገርን ፍጹም ማድረግ አይችልም ይህ የሚያሳየው ሕግ “ደካማ እና ጥቅም ያሌለው” መሆኑን ያሳያል፤ ስለዚህም “ልሻር” ይገባዋል፡፡ መቅረብ "ቅረቡ"
ይህ የተሻለው ማስተማመኛ በመሓላ ባይረጋገጥ ኖሮ ባልሆነም ነበር "የተሻለ መተማመን ይኖረን ዘንድ ዘንድ ሰው በመሓላ ማረጋገጥ ይኖርበታል” ወይም “. . . ክርስቶስ ካህን ሆኖ ለመሾም” አንተ ለዘላለም ካህን "አንተ ሁል ጊዜም ካህን ነህ እንዲሁም ካህን ትሆናለህ" (UDB)፡፡
ማረጋገጫ "ማረጋገጫ" ወይም "ተስፋ" his priesthood is unchangeable "he will remain a high priest forever"
ሰማይ. ሰማይ፣ ሰማያዊ ስለዚህ "ክርስቶስ ለዘላለም ሊቀ ካህናችን ስለሆነ" በእርሱ በኩል "እርሱ ካደረገልን ነገር የተነሣ"
ምንም አያስፈልገውም "ክርስቶስ አያስፈልገውም" ሕጉ ይፈቅዳል "እግዚአብሔር በሕጉ በኩል በፈቀደው መሰረት" ከሕጉ በኋላ የመጣው የመሓላ ቃል ልጁን ሾመው፡፡ "ሕጉን ከሰጠ በኋላ እግዚአብሔር ማለ እንዲሁም ልጁን ሾመው" ፍጹም የሆነውን "እግዚአብሔርን ፈጽሞ የታዘዘውን እና ፍጹም የሆነውን" ራሱን መስዋእት አድርጎ ሰጠ . . . ለዘላለም ራሱን ፍጹም ያደረገውን ልጁን የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ኢየሱስ ራሱን ለዓለም ሁሉ ኃጢአት ብቸኛ ፍጹም መስዋእት አድርጎ ሰጠ፡፡ እግዚአብሔር ስለዓለም ሁሉ ኃጢአት ሌላ መስዋእትን አይቀበልም ነበር ምክንያቱም ፍጹም፣ ለሁሉም የሚሆን እና ቅዱስ የሆነ ሌላ መስዋእት ልኖር ስላማይችል ነው፡፡ እግዚአብሔር እራሱ መስዋእት መሆን ይገባው ነበር ስለዚህም የእግዚአብሔር ልጅ ዘላለማዊ የኃጢአት ይቅርታን ለማስገኘት ሲል ሕይወቱን አሳልፎ ሰጠ፡፡ ልጅ ይህ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው የኢየሱስ ወሳኝ የማዕረግ ስሙ ነው፡፡
1 እንግዲህ ልንናገር የፈለግነው ጉዳይ ዋና ነጥቡ ይሄ ነው፦ በሰማያት በልዑል እግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ ሊቀ ካህን አለን። 2 እርሱ እግዚአብሔር በተከላት እውነተኛይቱ የማደሪያ ድንኳን፣ በተቀደሰው መቅደስ አገልጋይ የሆነ ነው እንጂ ማንኛውም ሟች ሰው አይደለም። 3 ማንኛውም ሊቅቀ ካህናት የሚሾመው ስጦታዎችንና መሥዋዕቶችን ለማቅረብ በመሆኑ፣ የሚቀርብ ነገር ይዞ መገኘት አስፈላጊ ነው። 4 ታዲያ ክርስቶስ አሁን በምድር ላይ የሚኖር ቢሆን በሕጉ መሠረት ስጦታዎችን የሚያቀርቡ ስላሉ እርሱ በፍጹም ካህን መሆን ባልቻለም ነበር። 5 የማደሪያ ድንኳኑን ለመሥራት በተነሣ ጊዜ እግዚአብሔር ሙሴን”አስተውል፣ በተራራው ላይ ባየኸው ምሳሌ መሰረት ማንኛውንም ነገር እንድትሠራ” በማለት እንዳስጠነቀቀው ሁሉ እነርሱ የሰማያዊ ነገሮች ጥላና ግልባጭ የሆኑ ነገሮችን የሚያገለግሉ ናቸው። 6 ነገር ግን በተሻለ ተስፋ ላይ የተመሠረተ የተሻለ ኪዳን መካከለኛው በመሆኑ ክርስቶስ አሁን የላቀ አገልግሎት ተቀብሏል። 7 ያ የመጀመሪያው ኪዳን ነቀፋ ካልነበረው ሁለተኛ ኪዳን የሚፈለግበት ምንም ምክንያት አይኖርም ነበር። 8 እግዚአብሔር በሕዝቡ ላይ ነቀፋ ባገኘ ጊዜ እንደዚህ ብሎ ነበርና”አስተውሉ፣ ከእስራኤል ቤትና ከይሁዳ ቤት ጋር አዲስ ቃል ኪዳን የምገባበት ዘመን ይመጣል” ይላል እግዚአብሔር። 9 “ከግብፅ ምድር በእጆቼ መርቼ ባወጣኋቸው በዚያን ዘመን ከአባቶቻቸው ጋር እንደገባሁት እንደዚያ ቃል ኪዳን አይሆንም። በዚያ ኪዳኔ አልጸኑምና እኔም ችላ አልኳቸው” ይላል እግዚአብሔር። 10 “ከእነዚያ ዘመናት በኃላ ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው ይህንን ኪዳን ነው፥ ‘ሕጌን በልቦናቸው አኖራለሁ፣ በልቦቻቸውም ላይ እጽፈዋለሁ። አምላካቸው እሆናለሁ እነርሱም ሕዝቤ ይሆናሉ። 11 እያንዳንዱ ጎረቤቱን እያንዳንዱም ወንድሙን፥ ‘እግዚአብሔርን እወቅ እያለ አያስተምርም፣ እጅግ ታናሽ ከሆነው ጀምሮ እጅግ ታላቅ እስከሆነው ድረስ ሁሉም ያውቁኛልና። 12 በዓመፅ ለፈጸሟቸው ድርጊቶች ሁሉ ምሕረት አደርጋለሁና ኃጢአቶቻቸውንም ከእንግዲህ አላስብምና” 13 ‘አዲስ’ በማለቱም የመጀመሪያው ኪዳን አስረጅቷል። አሮጌ ነው ብሎ የገለጸውም ሊወገድ ተቃርቧል።
ቅጂ እና ጥላ እነዚህ ቃላት በመሠረታዊ ትርጓመማቸው ተመሳሳይ ናቸው፡፡ አጽኖት ሰጥተው የሚያስተላልፉትም መልዕክት የመገናኛ ድንኳኑ በሰማይ ያለው የመገናኛ ድንኳን ምሳሌ መሆኑን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ግልጽ ያልሆነ ምስል" ምሳሌ "ዲዛይን"
ክርስቶስ ተቀብሏል "እግዚአብሔር ለክርስቶስ ሰጥቶታል" ነቀፋ ያሌለበት ፍጹም
ተመልከት አማራጭ ትርጉም፡ "ተመልከት" ወይም "አድምጥ" ወይም "አሁን ልነግራችሁ ያለሁትን ነገር በጥንቃቄ አድምጡ፡፡"
1 የመጀመሪያው ኪዳን ቢሆን በዚህ ምድር ለሚከናወነው አምልኮም ሆነ ለአምልኮ ደንቦች ስፍራ ነበረው። 2 በመገናኛው ድንኳን የተዘጋጀ ቅድስት የተባለ ውጨኛ ክፍል ነበር። በዚህ ስፍራ መቅረዙ፣ ጠረጴዛውና የመንግስቱ መገለጫ ኅብስት ነበሩበት። 3 ከሁለተኛው መጋረጃም በስተጀርባ ቅድስተ ቅዱሳን የተባለ ሌላ ክፍል ነበረ። 4 ዕጣን ለማጠን የሚሆን የወርቅ መሠዊያ ነበረው። ሙሉ በሙሉ በወርቅ የተለበጠ የኪዳን ታቦትም ነበረበት። በእርሱም ውስጥ መና ያለበት የወርቅ መሶብ፣ ያቆጠቆጠች የአሮን በትርና የኪዳኑ የድንጋይ ጽላቶች ነበሩት። 5 በኪዳኑም ታቦት ላይ በስርየት መክደኛው ላ ያሰፈፉ የከበሩ የኩሩቤል ምስሎች ነበሩ። ይሁን እንጂ ስለ እነዚህ ሁሉ አሁን በዝርዝር መግለጽ አንችልም። 6 እነዚህ ሁሉ ነገሮች ከተዘጋጁ በኃላ፣ ካህናቱ አገልግሎቶቻቸውን ለመፈጸም በመደበኛነት በማደሪያው ድንኳን ውጫዊው ክፍል በኩል ይገባሉ። 7 ሊቀ ካህናቱ ግን በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ሁለተኛው ክፍል ይገባል፣ በሚገባበትም ጊዜ ለራሱና ሕዝቡም ባለማወቅ ለፈጸሟቸው በደሎች የደም መሥዋዕት ይዞ እንጂ እንደዚሁ አይደለም። 8 የመጀመሪያይቱ የመገናኛ ድንኳን በስፍራዋ ቆማ እስካለች ድረስ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን የሚያመራው መንገድ ገና እንዳልተገለጠ መንፈስ ቅዱስ በምሳሌ እያሳየ ነው። 9 ይህም ለአሁኑ ጊዜ ተምሳሌት ነው። አሁን እየቀረአቡ ያሉት ስጦታዎችም ይሁኑ መሥዋዕቶች የአምላኪውን ሕሊና ፍጹም ማድረግ የሚችሉ አይደሉም። 10 ከተለያዩ የመንፃት ሥርዓቶች ጋር የተያያዙ ምግቦችና መጠጦች ብቻ ናቸው። እነዚህ ሁሉ አዲሱ ሥርዓት በሥራ ላይ እስኪውል ድረስ በሥጋዊ ደረጃ እንዲከበሩ የተሰጡ ሥርዓቶች ናቸው። 11 ክርስቶስ በሰው እጆች በተሠራችው ሳይሆን ላቅ ባለችውና ይበልጥ ፍጹምና ቅድስት በመሆነችው፣ ከዚህም ከፍጥረታዊው ዓለም ባልሆነችው ድንኳን በኩል ለመጡት መልካም ነገሮች ሊቀ ካህናት ሆኖ መጥቷል። 12 ክርስቶስ እጅግ ቅድስት ወደሆነችው ስፍራ አንድ ጊዜ ለሰዎች ሁሉ የገባውና የዘላለም ቤዛችንን ያስገኘልን በፍየሎችና በጥጃዎች ደም ሳይሆን በራሱ ደም ነው። 13 የፍየሎችና የኮርማዎች ደም እንዲሁም የጊደሮች አመድ በሥርዓታዊ ደረጃ ንፁሕ ባልሆኑት ላይ መረጨቱ የሚያጠራቸውና ሰውነቶቻቸውንም ንፁሕ የሚያደርገው ከሆነ፣ 14 ይልቁንም ነውር ሳይኖረው በዘላለማዊ መንፈስ ራሱን ለእግዚአብሔር ያቀረበ የክርስቶስ ደም ሕያው እግዚአብሔርን እናገለግል ዘንድ ሕሊናችንን ከሞተ ሥራ ምን ያህል ያነጻን ይሆን? 15 ከዚህም የተነሳ ክርስቶስ የአዲስ ኪዳን መካከለኛ ነው። ይህም የሆነበት ምክንያት በእግዚአብሔር የተጠሩት ስለ ዘላለም ርስት የተሰጣቸውን የስፋ ቃል ይቀበሉ አንድ በመጀመሪያው ኪዳን ሥር ከነበረባቸው የኃጢአት ቅጣት ነፃ እንዲወጡ የሞት ቅጣት ተፈጽሞ ስለነበረ ነው። 16 ይህም የሆነው አንድ ሰው ኑዛዜ እንደተወ ሲገለጽ ኑዛዜ የተወውን ሰው መሞት ማረጋገጥ አስፈላጊ ነው። 17 ምክንያቱም ኑዛዜ የሚጸናው ሞት ተከስቶ ከሆነ ብቻ ነው፣ ተናዛዡ በሕይወት እስካለ ሊጸና አይችልምና። 18 እንደዚህም በመሆኑ የመጀመሪያው ኪዳን እንኳን ያለ ደም አልጸናምና። 19 በሕጉ ውስጥ ያሉትን ማንኛቸውንም ትዕዛዛት ሙሴ ለሕዝቡ ሁሉ በሰጠ ጊዜ የጥጆችንና የፍየሎችን ደም ከውሃ፣ ከቀይ የበግ ፀጉርና ከሂሶጵ ጋር ቀላቅሎ በራሱ በሕጉ መጽሐፍና በሕዝብ ሁሉ ላይ ይረጭ ነበርና። 20 ይህንንም ካደረገ በኃላ “እግዚቸብሔር ለእናንተ ሕግጋቱን የሰጠበት የኪዳኑ ደም ይህ ነው” ይል ነበር። 21 በዚያው ዓይነት መንገድ ደሙን በመገናኛው ድንኳንና ለክህነት አገልግሎት በሚውሉት ዕቃዎች ሁሉ ላይ ይረጭ ነበር። 22 ሕጉ በሚለውም መሠረት ሁሉም ነገር የሚነጻው በደም ነበር ማለት ይቻላል። ደምም ካልፈሰሰ በስተቀር ይቅርታ የለም። 23 ስለሆነም በሰማይ ያሉት ነገሮች ግልባጮችም በእነዚህ የእንስሳት መሥዋዕቶች ይነጹ ዘንድ አስፈላጊ ነበር። ይሁን እንጂ ሰማያዊ የሆኑት ነገሮች ራሳቸው እጅግ በተሻሉ መሥዋዕት መንጻት ይገባቸዋል። 24 ክርስቶስ በእጅ ወደተሠራው የእውነተኛውም ግልባጭ ብቻ ወደነበረው ቅድስተ ቅዱሳን አልገባምና። ይልቁንም እርሱ የገባው እግዚአብሔር ባለበት ስለ እኛ አሁን እግዚአብሔር ፊት ወደሚቀርብበት ሰማይ በቀጥታ ገብቷል። 25 ወደዚያም የገባው የሌላውን ደም ይዞ በየዓመቱ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን እንደሚገባው እንደ ሊቀ ካህናቱ በየጊዜው ራሱን ለማቅረብ አይደለም። 26 እንደዚያ ቢሆን ኖሮ ከዓለም ጅማሬ አንስቶ ብዙ ጊዜ መከራ መቀበል ባስፈለገው ነበር። አሁን ግን ራሱን መሥዋዕት በማድረግ ኃጢአትን ለማስወገድ በዘመናት መጨረሻ የተገለጠው አንድ ጊዜ ብቻ ነው። 27 እያንዳንዱ ሰው አንድ ጊዜ መሞት ከዚያ በኃላም ወደ ፍርድ መቅረብ እንደሚገባው ሁሉ 28 እንደዚሁም የብዙዎችን ኃጢአት ለማስወገድ መሥዋዕት ሆኖ የቀረበው ክርስቶስ ኃጢአትን ለማስወገድ ዓላማ ሳይሆን በትዕግሥት ለሚጠባበቁት ድነትን ያስገኝላቸው ዘንድ ዳግመኛ ይገለጣል
የመጀመሪያው ኪዳን ይህንን በ HEB 8:7. ላይ በተረጎምከው መሠረት ተርጉመው፡፡ ደንቦች "ዝርዝር መመሪያዎች" ወይም "ሕግጋቶች" ወይም "አቅጣጫ ጠቋሚ ሕጎች" ስለዚህ ጸሐፊው በ HEB 8:7. ላይ የጀመረውን ሐተታ ቀጥሏል፡፡ ክፍል ተዘጋጅቷል "እስራኤላዊያን ክፍል አዘጋጅተው ነበር" በመስዋእት ህብስት "በእግዚአብሔር ፊት የሚቀርብ ህብስት" (UDB) ወይም "ካህናት በእግዚአብሔር ፊት የሚያቀርቡት ህብስት"
ከሁለተኛው ማጋረጃ በኋላ የመጀመሪያው መጋረጃ ከመገናኛ ድንኳኑ ውጨኛው ክፍል ውስጥ የሚገኝ ስለሆነ “ሁለተኛው መጋረጃ” “በቅዱስ ሥፍራው” እና “በቅድስተ ቅዱሳኑ” መካከል የሚገኝ ሥፍራ ነው፡፡ በውስጡም "በቃል ኪዳኑ ታቦት ውስጥም" አድገዋል "አብቧል" ወይም "በቅሏል" ወይም "አድገዋል" የድንጋይ ጽላት የተጻፈበት ጠፍጣፋ ድንጋይ፡፡ ምስል የሆነ ነገርን በመወከል የተቀረጸ ድንጋይ በላዩ ላይ የኩሩቤል ምስል ነበር "ክሩቤል በላዩ ላይ ነበር" ማስተሰሪያ ኪዳን የቃል ኪዳኑ ታቦት የላይኛው ክፍል
ይህ ነገር ከተዘጋጀ በኋላ አማራጭ ትርጉም: "ካህናቱ እነዚህ ነገሮች ካሰናዱ በኋላ" አዘጋጁ "አስቀድሞ ማዘጋጀት" ከመሰዋት በስቀር ምንም አልቀረም "ጉል ጊዜ ይሰው ነበር" ወይም "ሁል ጊዜ ይሰዋል"
መንገዱ . . . ገና አልተገለጠም ነበር "እግዚአብሔር መንገዱን ገና አልገለጠውም ነበር" ቅድስተ ቅዱሳኑ አማራጭ ትርጉሞች: 1) በምድር ላይ በመገናኛ ድንኳን ውስጥ የሚገኘው የውሰጠኛው ክፍል ወይም 2) በሰማይ የእግዚአብሔር መገኛ፡፡ የመጀመሪያው የመገናኛ ድንኳን አሁንም ድረስ ቆሞ ይገኛል አማራጭ ትርጉሞች: 1) "የመገናኛ ድንኳኑ ውጫዊው ክፍል አሁንም ድረስ ቆሞ ይገኛል ወይም 2) "የመስዋእት ሥርዓቱ ቀጥሏል" በምሳሌ ማብራሪያ "ምስል" በአሁኑ ወቅት "አሁን" የአምላኪውን ሕልና ፈጽሞ ለማንጻት አይችልም ነበር "የሚያመልከውን ሰው ከበደለኝነት ፈጽሞ ለማንጻት አይችልም ነበር" የመታጠብ ሥርዓት "ሕግጋት" ወይም "ምሳሌያዊ ተግባራት" ለሥጋ ሥርዓቶች "ለአካላዊ ሰውነት የሚሆኑ ሕግጋቶች" እነዚህ ሁሉ ሕግጋቶች ለሥጋ የተሰጡ ናቸው "እግዚአብሔር እነዚህ ሁሉ ሕግጋቶች የሰጠው ለሥጋ ነው" አዲስ ሥርዓት "አዲስ ኪዳን" (ULB)
መልዕካም ነገሮች “አዲስ ሥርዓት” (HEB 9:8) ቅድስተ ቅዱሳን በሰማይ የእግዚአብሔር መገኘት
መርጫት ... አመድ ሥርዓታዊ መንገድ ንጹሕ ባልሆኑት ላይ ካህኑ ንጹሕ ባልሆኑት ሰዎች ላይ ትንሽ አመድ ይረጭባቸዋል፡፡ ለእግዚአብሔር እንከን ያለሌበትን መስዋእት በዘላለማዊ መንፈስ ያቀረበው፣ ሕያው የሆነውን እግዚአብሔር ማምለክ እንችል ዘንድ ሕልናችንን ከሞተ ሥራ ያነጻው የክርስቶስ ደም ግን ምን ያኽል የተሻለ ነው? "ክርስቶስ በዘላለማዊ መንፈስ አማካኝነት ራሱን ምንም ነቀፋ ያሌለበት መስዋእት አድርጎ ለእግዚብሔር አቅርቧል፡፡" የክርስቶስ ደም ... ሕልናችንን ያነጻል ኢየሱስ ራሱን መስዋእት አድርጎ በማቅረቡ ምክንያት ለሰራነው ኃጢአት በደለኝነት ከእንግዲህ ሊሰማን አይገባም፡፡ ሕልናችንን የጸሐፊውን እና የአንበባቢው ሕልና ቅጣት "ፍርድ" በእግዚአብሔር የተጠሩት በእግዚአብሔር የተሾሙት ወይም የእርሱ ልጆች እንዲሆኑ የተመረጡት
ውርስ አንድ ሰው ስሞት ሌላኛው ሰው የእርሱን ንብረት እንዲወስድ የሚፈቅድለት የሕግ ወረቀት፡፡
ዕብራዊያን 9፡ 18-20 የመጀመሪያው ኪዳንም ቢሆን የተመሠረተው ያለ ደም አልነበረም "እግዚአብሔር የመጀመሪያውን ኪዳንም ቢሆን የመሠረተው በደም ነበር" ደሙን ወስዶ ...ከውሃ ጋር...እና ይረጨዋል . . . ጥቅል መጽሐፍ. . . እና በሁሉም ሰዎች ላይ ካህኑ ሂሶጱን ወስዶ በደም እና ውሃ ውስጥ ይነክረውና በጥቅል መጽሐፉ ላይ እንዲሁም በሕዝቡ ላይ ይረጨዋል፡፡ ሂጾጵ ለመርጨት ሥርዓት ጥቅም ላይ የሚውል እፅዋት
መርጨት ይህንን በ HEB 9:19 ላይ ምን ብለህ እደተረጎምከው ተመልከት፡፡ መያዥያ ዕቃ "አንድ ነገር ለመያዝ የሚያገለግል ዕቃ" ወይም "ማጠራቀሚያ" የክህነት አገልግሎት "የካህናት ሥራ" ሁሉ ነገር በደም ይነጻል "ካህናት ሁሉን ነገር ለማንጻት ደምን ይጠቀማሉ" ዳም ሳይፈስ የኃጢአት ሥርዔት የለም "እግዚአብሔር የሰዎችን ኃጢአት ይቅር የሚለው ካህኑ መስዋእትን ካቀረበ እና ስለእነርሱ ካቀረበ ነው፡፡"
የሰማዩ ቅጂ የሆነው በእነዚህ እንስሶች መስዋእት መንጻት ካለበት "ካህናት የሰማዩ ቅጂ የሆነውን ለማንጻት የእንስሳት መስዋእትን ልጠቀሙ ይገባል፡፡" ሰማያዊው ነገር ራሱም በምበልጥ መስዋእት ልነጻ ይገባዋል፡፡ ምድራዊው ቅጂ ከሚነጻበት መስዋእት ይልቅ "ሰማያዊው ነገርንም እግዚአብሔር በጣም በተሻለ መስዋእት ልያነጻ ይገባዋል" እርሱ . . . በእግዚአብሔር ፊት ይቀርባል እርሱ . . . ወደ እግዚአብሔር መገኘት ይመጣል፡፡
ወደዚያ አይሄድም "ወደ ሰማይ አይገባም" (UDB) ይህ እውነት ከሆነ "እርሱ ሁል ጊዜ መስዋእትን የሚያቀርብ ከሆነ" ከምድር ጅማሬ "እግዚአብሔር ዓለም ፈጠረ" እርሱ ገልጦታል አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር እርሱ ገልጦታል"
መስዋእት ሆኖ የቀረበው ክርስቶስ አማራጭ ትርጉም: "ራሱን መስዋእት አድርጎ ያቀረበው ክርስቶስ"
1 ሕጉ ሊመጡ ላሉ መልካም ነገሮች ጥላ ብቻ እንጂ እውነተኛው አካል አይደለም። ሕጉ ካህናት ያለማቋረጥ በየዓመቱ በሚያቀርቧቸው በነዚያው መሥዋዕቶች ወደ እግዚአብሔር የሚቀርቡትን ከቶ ፍጹም ሊያደርጋቸው አይችልም። 2 ቢችል ኖሮ እነዚያ መሥዋዕቶች መቅረባቸው ይቀር አልነበረምን? እንደዚያ ቢሆን ኖሮ የሚያመልኩት አንድ ጊዜ ከኃጢአታቸው ከነጹ በኋላ ስለ ኃጢአታቸው የሚያስታውሱት ነገር ምንም አይኖርም ነበር። 3-4 ነገር ግን በእነዚያ መሥዋዕቶች ውስጥ በየዓመቱ የተፈጸሙትን ኃጢአቶች የሚያስታውስ ነገር አለ። ለዚህ ምክንያቱ የኮርማዎችና የበጎች ደም ኃጢአትን ማስወገድ ባለመቻሉ ነው። 5 ክርስቶስ ወደ ዓለም ሲመጣ፣ “አንተ መሥዋዕቶችን ወይም ስጦታዎችን አልፈለግህም። ይልቅ ለእኔ ሥጋን አዘጋጀህልኝ። 6 አንተ በሚቃጠል መባ ወይም በኃጢአት መሥዋዕት ደስ አልተሰኘህም። 7 ቀጥሎም፣ “እግዚአብሔር ሆይ በመጽሐፍ ስለ እኔ እንደተጻፈው እነሆ ፈቃድህን ለማድረግ እዚህ አለሁ” ብሏል። 8 ከላይ እንደተጠቀሰው፡“አንተ መሥዋዕቶችን፣ ስጦታዎችን ወይም ለኃጢአት የሚቃጠሉ ሙሉ መሥዋዕቶችን ማለትም በሕጉ መሠረት የሚቀርቡ መሥዋዕቶችን አልፈለግህ፣ በእነርሱም ደስ ስላልተሰኘህም” ብሏል። 9 ደግሞም፣ “እነሆ ፈቃድህን ለማድረግ እዚህ አለሁ” አለ። ሁለተኛውን ሥርዓት ለመትከል የመጀመሪያውን ሥርዓት ወደ ጎን ያደርገዋል። 10 በሁለተኛው ሥርዓት ለአንድ ጊዜና ለዘላለም በቀረበው በኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋ አማካኝነት በእግዚአብሔር ፈቃድ ተቀድሰናል። 11 በእርግጥ እያንዳንዱ ካህን ኃጢአትን ፈጽሞ ሊያስወግድ የማይችሉትን መሥዋዕቶች ለማቅረብ በየዕለቱ ለማገልገል ይቆማል። 12 ነገር ግን ክርስቶስ ለኃጢአት ሁሉ ለዘላለም የሚሆን አንድ መሥዋዕት ካቀረበ በኋላ፣ 13 ጠላቶቹ እስኪዋረዱና የእግሩ መረገጫ እስኪሆኑ ድረስ እየተጠባበቀ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጧል። 14 ይህም በአንድ መሥዋዕት የተቀደሱትን ለዘላለም ፍጹማን ስላደረጋቸው ነው። 15 ደግሞም መንፈስ ቅዱስ ለእኛ ይመሰክርልናል። ምክንያቱም በመጀመሪያ፣ 16 “ ከእነዚያ ቀኖች በኋላ ከእነርሱ ጋር የምገባው ቃልኪዳን ይህ ነው፡ ሕጎቼን በልባቸው ውስጥ አደርጋለሁ፣ ደግሞም በአእምሮአቸው ውስጥ እጽፈዋለሁ” ስላለ ነው። 17 ቀጥሎም፣ “ኃጢአታቸውንና ዓመጻቸውን ከእንግዲህ አላስበውም” አለ። 18 ለእነዚህ ነገሮች ይቅርታ በተረገበት በዚያ ለኃጢአት ከእንግዲህ ወዲያ መሥዋዕት አይቀርብም። 19 ስለዚህ ወንድሞች፣ በኢየሱስ ደም አማካኝነት ወደ ቅድስተ ቅዱሳን የመግባት ድፍረት አለን። 20 ይህም በመጋረጃው ማለትም በሥጋው አማካኝነት ለእኛ የከፈተልን አዲስና ሕያው መንገድ ነው። 21 በእግዚአብሔር ቤት ታላቅ ካህን ስላለን፣ 22 ልባችን በመረጨት ከክፉ ኅሊና ሁሉ ነጽቶ፣ ሥጋችንም በንጹሕ ውኃ ታጥቦ ባገኘነው የእምነት ሙሉ ዋስትና በእውነተኛ ልብ እንቅረብ። 23 ተስፋን የሰጠ እግዚአብሔር ታማኝ ስለሆነ፣ አምነን የምንመሰክረውን ተስፋ ያለ ማወላወል አጥብቀን እንያዝ። 24 ለፍቅርና ለመልካም ሥራ እርስ በርስ እንዴት እንደምንነቃቃ እናስብ። 25 አንዳንዶቹ ልማድ እንዳደረጉት በአንድነት መሰብሰባችንን አንተው። በዚህ ፈንታ ቀኑ እየቀረበ መምጣቱን ስታዩ እርስ በርሳችሁ ይበልጥ ተበረታቱ። 26 የእውነትን እውቀት ከተቀበልን በኋላ ሆን ብለን ኃጢአት ማድረጋችንን የምንቀጥል ከሆንን፣ ከእንግዲህ ለኃጢአት የሚሆን መሥዋዕት አይኖርም። 27 ይልቅ የሚጠብቀን የሚያስፈራ ፍርድና የእግዚአብሔርን ጠላቶች ሊበላ ያለ ብርቱ እሳት ብቻ ነው። 28 የሙሴን ሕግ የናቀ ማናቸውም ሰው በሁለት ወይም በሦስት ምስክሮች ያለ ምንም ምሕረት ይሞታል። 29 ታዲያ የእግዚአብሔርን ልጅ የናቀ፣ የተቀደሰበትን የቃልኪዳኑን ደም እንደ እርኩስ የቆጠረ፣ የጸጋን መንፈስ የሰደበ ሰው ምን ያህል የባሰ ቅጣት የሚገባው ይመስላችኋል? 30 “በቀል የእኔ ነው፤ እኔ ዋጋን እመልሳለሁ” ያለውን እናውቃለንና። ደግሞም፣ “ጌታ በሕዝቡ ይፈርዳል።” 31 በሕያው እግዚአብሔር እጅ መውደቅ የሚያስፈራ ነገር ነው! 32 ነገር ግን ከበራላችሁ በኋላ በእንዴት ያለ ታላቅ ሥቃይ ውስጥ እንደታገሣችሁ እነዚያን የቀደሙ ወቅቶች አስታውሱ። 33 በስድብና በስደት ለሕዝብ መሳለቂያ ተዳርጋችኋል፣ ደግሞም በዚህ ዓይነቱ ሥቃይ ውስጥ ካለፉ ሰዎችም ጋር አብራችሁ ነበራችሁ። 34 ለእስረኞች ርኅራኄ አሳያችሁ፣ የተሻለና ዘላለማዊ ሀብት ለራሳችሁ እንዳላችሁ በመረዳትም የንብረታችሁን መነጠቅ በደስታ ተቀበላችሁ። 35 ስለዚህ ታላቅ ዋጋ ያለውን ድፍረታችሁን አትጣሉ። 36 ፈቃዱን ካደረጋችሁ በኋላ እግዚአብሔር ለእናንተ ተስፋ የገባውን ነገር ለመቀበል መታገሥ ያስፈልጋችኋል። 37 “በጣም በቅርብ ጊዜ ውስጥ የሚመጣው በእርግጥ ይመጣል፣ አይዘገይምም። 38 የእኔ የሆነው ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል። ወደኋላ ቢመለስ በእርሱ ደስ አይለኝም።” 39 እኛ ግን ለጥፋት ወደኋላ እንደሚያፈግፍጉት አይደለንም። ይልቅ እኛ ነፍሳቸውን ለማዳን ከሚያምኑት ነን።
እነዚህ እውነታዎች አይደሉም "እውነት የሆነ ነገር አይደለም" ቅረቡ "ለማመልክ ኑ" (UDB) ወይም "ይበልጥ ቅረቡ" እነዚህ መስዋእቶች መሰዋታቸው በቀረ ነበር? "እነዚህ መስዋእት ማቅረብ በተው ነበር፡፡" ማቆም "ማቆም" ሁኔታ "ሁኔታ" አንድ ጊዜ ከነጻ "እግዚአብሔር ያነጻው" ማወቅ "ሕልውናውን ማወቅ" የተሠራውን ኃጢአት ማስታወስ "እግዚአብሔር ሰዎች የሰሯቸውን ኃጢአት ያስታውሳል" ከዓመት ዓመት "በየዓመቱ" የኮርማ እና ፍየል ደም ኃጢአትን ፈጽሞ ለማስወገድ አይችልም፡፡ "የኮርማ እና የፍየል ደም ኃጢአትን ለማስወገድ አይችልም"
ሥጋን አዘጋጀኸልኝ "ለእኔ ሥጋን አዘጋጀኸልኝ"
ከዚህ በላይ እንደተገለጸው አማራጭ ትርጉም: "ከዚህ በላይ እንደጻፍኩት ኢየሱስ እንዲህ ብሏል፡" መስዋእን፣ መባን ወይም የሚቃጠል መስዋእትን እነዚህ ቃላት በ HEB 10:5-6 ላይ በተረጎምካቸው መሠረት ተርጉማቸው፡፡ የሚቀርቡት መስዋእት አማራጭ ትርጉም፡ "እነርሱ' እነዚህ ሰዎች የሚያቀርቧቸውን ሁሉንም መስዋእት ናቸው፡፡" ተመልከት "ከዚህ በመቀጠል ለሚናገረው ነገር ትኩረት ስጥ:" በእግዚአብሔር ፈቃድ መሠረት እኛም ለእግዚአብሔር ተሰጠን አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር ክርስቶስ ራሱን መስዋእት ያደረግ ዘንድ ፈቃዱ ነበር እንዲሁም በዚህ መስዋእት አማካኝነት እኛ ለእግዚአብሔር የተሰጠን ሆንን"
በእርግጥ ይህ HEB 10:1-4 ከዚያ ቀጥሎ ካለው ጋር ያያይዛል፡፡ ጠላቶቹ ተዋረዱ እንዲሁም የእግሩ መረገጫ ሆኑ "እግዚአብሔር የክርስቶስን ጠላቶች አዋረዳቸው እንዲሁም አሳፈራቸው፡፡" አንድን ሰው በሌላ ሰው እግር በታች ማስቀመጥ የሚያሳፍር ነገር ነው፡፡ ለእግዚአብሔር የተሰጡት አማራጭ ትርጉሞች: "እግዚአብሔር ለራሱ ያዘጋጃቸው"
በመጀመሪያ በ HEB 10:17 ላይ ከተናገረው በፊት የተቀደሱት (HEB 10:14) ከእነዚህ ቀናት በኋላ "የመጀመሪያው ኪዳን ስጠናቀቅ"
ከዚያም በ HEB 10:16 ላይ ከተነገሩት በኋላ ያሉት ከእንግዲህ ወደህ ፈጽሞ አላስታውስም "ከእንግዲህ ወዲህ አላስታውሰውም" ኃጢአት እነና የሕግ አልባነት “ኃጢአት” እና “ሕግ አልባነት” የሚሉት ሁለት ቃልት በመሠረታዊ ሀሳባቸው ተመሳሳይ ናቸው፡፡ በአንድነትም አጽኖት የሚሰጡት የተፈጸመ ኃጢአትን ነው፡፡ ለእዚህ ነገሮች ይቅርታ የሚገኝበት ሥፍራ አማራጭ ትርጉም፡ "እግዚአብሔር እነዚህ ነገሮች ይቅር ሲል" ከእንግዲህ ለኃጢአት መስዋእትን አያቀርቡም አማራጭ ትርጉም: "ሰዎች ከእንግዲህ ለኃጢአት መስዋእትን አያቀርቡም"
ወንድሞች በዚህ ሥፍራ ይህ ቃል ክርስትያኖችን የሚያመለክት ሲሆን ወንዶችን እና ሴቶችን ያመለክታል፡፡ ምክንያም በክርስቶስ የሚምኑ አማኞች ሁሉ የአንድ መንፈሳዊ ቤተሰብ አባላት ናቸውን፣ እግዚአብሔርም ሰማያዊ አባታቸው ነው፡፡ ቅድስተ ቅዱሳን የእግዚአብሔር መገኘት አካሉ አማራጭ ትርጉም: "የእርሱ ሞት" በመጋረጃው በኩል በምድራዊ መ,ቤተ መቅዱስ ውስጥ ያለው መጋረጃ በሰዎች እና በእውነተኛው የእግዚአብሔር መገኘት መካከል የሚለይ ግድግዳ መኖሩን ያሳያል፡፡ የእግዚአብሔር እያንዳንዱ አማኝ ሙሉ ዋስትና ጠንካራ መተማመን ልብን በመርጨት ማንጻት አማራጭ ትርጉም: "በኢየሱስ ደም የተረጨ ደም ንጹሕ ይሆናል፡፡ መረጨረት ይህ በ HEB 9:19 ላይ ምን በማለት እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡
የምንተማመንበትን የተስፋ ቃለል አጥብቀን እንያዝ "የምንተማመንበትን ነገር ለሰዎች በቀጣይነት እንናገር ምክንያቱም እግዚአብሔር እንደሚፈጽም ቃል የገባውን ነገር እንደሚፈጽም እናምናለንና" መናወጥ "እርግጠኛ አለመሆን" ቀኑ ቀርቧል አማራጭ ትርጉም: "ኢየሱስ ተመልሶ የሚመጣት ቀን ቀርቧል"
ሆን ተብሎ "በሙሉ ስምምነት" ከእንግዲህ ወዲህ ለኃጢአት መስዋእ መሰዋት አያስፈልግም "እግዚአብሔር ኃጢአቱን ይቅር ይልለት ዘንድ ማንም ከእንግዲህ መስዋእትን አይሰዋም"
ሁለት ወይም ሦስት "2 ወይም 3" ማንኛውም ሰው ምን ያኸል ቅጣት ይባዋል ብላችሁ ታስባላችሁ . . . ጸጋ? አማራጭ ትርጉም: "ይህ በጣም ከባድ ቅጣት ነው፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ቅጣት ለማንም ቢሆን በጣም ከባድ ነው . . . ጸጋ!" የእግዚአብሔር ልጅ አለመቀበል ይህ ቃል ክርስቶስ ማን እንደሆነ እና የሠራውን ሥራ አለመቀበልን የሚያሳይ ምስለላዊ ምሳሌ ነው፡፡" የእግዚአብሔር ልጅ ይህ የኢየሱስ ወሳኝ የሆነ የማዕረግ ስም ነው፡፡ ለእግዚአብሔር በተሰጠበት ደሙ አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር ለራሱ በሰጠበት ደሙ" የጸጋ መንፈስ "ጸጋ የሚሰጠው የእግዚአብሔር መንፈስ"
እናውቃለን ጸሐፊው እና አንባቢኑ ይህን ያውቃሉ በእጆቹ ላይ ይወድቃሉ አማራጭ ትርጉም: "በሙሉ ፍርዱ ሥር ናቸው"
አንድ ጊዜ ከበራላችሁ በኋላ "እወነቱን ካወቃችሁ በኋላ" ሰዎች ልዘባበቱባችሁ እና ልሰድባችሁ ይችላሉ እንዲሁም ያሳድዷችኋል "ሰዎች በመሳደብ እና በአደባባይ እናንተን በማሳደድ ይዘባበቱባችኋል" እናንተ ራሳችሁ አንባቢያኑ እንደሚዘባበቱባቸው፣ እንደሚያሥሯቸው እና ንብረታቸውን እንደሚዘርፏቸው ሰዎች ሳይሆን
መጣል ምንም እርባና ወይም ጥቅም እንዳሌለው በቅርቡ "በቅርብ ጊዜ"
የእኔ ጻድቅ "የእኔ ተማኝ ተከታዮች"
1 እንግዲህ እምነት ሰው በተስፋ ለሚጠበቀው ነገር ማረጋገጫ ያልታየውም ነገርም አስረጅ ነው። 2 የቀድሞ አባቶቻችንም እምነታቸው የተረጋገጠው በዚሁ ነበር። 3 ፍጥርተ-ዓለሙ በእግዚአብሔር ትእዛዝ መፈጠሩን፣ የሚታየውም ከሚታዩት ነገሮች የተፈጠረ አለመሆኑን በእምነት እንረዳለን። 4 አቤል ከቃየል የበለጠ ተቀባይነት ያለውን መሥዋዕት ለእግዚአብሔር ያቀረበው በእምነት ነበር። ጻድቅ እንደሆነ የተመሰከረለትም በዚህ ምክንያት ነበር። ስላቀረባቸው መሥዋዕቶች እግዚአብሔር መስክሮለታል። ቢሞትም እንኳ አሁንም ይናገራል። 5 ሄኖክ ሞትን ሳያይ ወደ ላይ የተወሰደው በእምነት ነበር። “እግዚአብሔር ስለወሰደው አልተገኘም።” ከመወሰዱ በፊት እግዚአብሔርን ደስ እንዳሰኘ ተነግሮለታና። 6 ያለ እምነት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ምክንያቱም፣ ወደ እግዚአብሔር የሚመጣ፣ እግዚአብሔር እንዳለና እርሱን ለሚሹትም ዋጋን እንደሚሰጥ ማመን ስለሚገባው ነው። 7 ኖኅ ገና ስላልታዩ ነገሮች ከእግዚአብሔር ሲያስጠነቅቀው እግዚአብሔርን በመፍራት ቤተሰቡን የሚያድንበትን መርከብ የሠራው በእምነት ነበር። ይህን በማድረግ ዓለምን ኮንኖ በእምነት የሚገኘውን ጽድቅ ወራሽ ሆነ። 8 አብርሃም በተጠራ ጊዜ ርስትን ወደሚቀበልበት ቦታ ታዞ የሄደው በእምነት ነበር። የወጣው ወዴት እንደሚሄድ ሳያውቅ ነበር። 9 በተስፋው ምድር እንደ ባዕድ የኖረውም በእምነት ነበር። ያን ተስፋ ከእርሱ አብረው ከሚወርሱት እንደ ይስሐቅና እንደ ያዕቆብ በድንኳን ውስጥ ኖረ። 10 ይሄውም እግዚአብሔር መሠረት ያላትን፣ ያቀዳትንና ያነጻትን ከተማ ይጠባበቅ ስለነበር ነው። 11 አብርሃምና ሣራ እጅግ አርጅተው ሳሉ እንደሚወልዱ በተነገራቸው ጊዜ፣ ወንድ ልጅን እንደሚሰጣቸው ተስፋ የገባላቸውን እግዚአብሔር ታማኝ አድርገው ስለቆጠሩ ሣራ ለማርገዝ ኃይል ያገኘችው በእምነት ነበር። 12 በመሆኑም፣ ሊሞት ከተቃረበ ከዚህ አንድ ሰው ቁጥር ስፍር የሌላቸው ዝርያዎች ተገኙ። እነርሱም በሰማይ እንዳሉ ከዋክብትና በባሕር ጠረፍ እንዳለ አሸዋ በዙ። 13 እነዚህ ሁሉ የተሰጧቸውን ተስፋዎች ሳይጨብጡ እምነታቸውን እንደጠበቁ ሞቱ። ይልቁንም እነዚህን ተስፋዎች ከሩቅ አይተው ስለተቀበሏቸው በምድር ላይ እንግዶችና መጻተኞች መሆናቸውን ተገነዘቡ። 14 እንደዚህ የሚሉ ሰዎች የራሳቸው የሆነ አገር እንዲሚሹ በግልጽ ያሳያሉ። 15 በእርግጥ ለቀው የመጡትን አገር ቢያሰቡ ኖሮ ለመመለስ ዕድሉ ነበራቸው። 16 አሁን ግን የሚፈልጉት የተሻለውን ሰማያዊ አገር ነው። ስለዚህም፣ እግዚአብሔር ከተማን ስላዘጋጀላቸው አምላካቸው ተብሎ ሊጠራ አያፍርም። 17 አብርሃም በተፈተነ ጊዜ ይስሐቅን ያቀረበው በእምነት ነበር። አዎን፣ 18 “ዝሮችህ የሚጠሩት በይስሐቅ ነው” የተባሉለትን ተስፋዎቹን በደስታ ስለተቀበለ አንድ ልጁን ለመሥዋዕት አቀረበ። 19 አብርሃም፣ እግዚአብሔር ይስሐቅን ከሞት ሊያስነሣ እንደሚችል አምኖ ነበር። ይስሐቅን ከሞት የመነሣት አምሳያ አድርጎ መልሶ ተቀበለው። 20 ይስሐቅ ገና ወደፊት የሚመጡትን ነገሮች አስቦ ያዕቆብንና ኤሳውን በእምነት ባረካቸው። 21 ያዕቆብ ፍጻሜው በተቃረበ ጊዜ፣ የዮሴፍን ልጆች እያንዳንዳቸውን የባረካቸውና በምርኩዙ አናት ተደግፎ የሰገደው በእምነት ነበር። 22 ዮሴፍ ሊሞት ሲቃረብ የእስራኤል ልጆች ከግብጽ እንደሚወጡ የተናገረውና የእርሱን አጽሙን እንዲወስዱ ያዘዘው በእምነት ነበር። 23 ሙሴ ሲወለድ ወላጆቹ መልከ መልካም ሕፃን መሆኑን አይተው የንጉሡን ትእዛዝ ሳይፈሩ ለሦስት ወራት የደበቁት በእምነት ነበር። 24 ሙሴም ካደገ በኋላ የፈርዖን የልጅ ልጅ፣ እንዳይባል እምቢ ያለው በእምነት ነበር። 25 ለአጭር ጊዜ በኃጢአት ደስ ከመሰኘት ይልቅ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራን መካፈልን መረጠ። 26 ዓይኖቹ ወደፊት የሚቀበለውን ዋጋ አተኩረው ስለተመለከቱ፣ በግብጽ ከሚገኝ ሀብት ይልቅ ክርስቶስን መከተል የሚያስከትልበትን ውርደት የላቀ ብልጽግና አድርጎ አሰበ። 27 ሙሴ ግብጽን ለቆ የወጣው በእምነት ነበር። የማይታየውን እርሱን ተመልክቶ በአቋሙ ስለጸና የንጉሡን ቁጣ አልፈራም። 28 ቀሳፊው የእስራኤልን የበኩር ልጆች እንዳይነካ ሙሴ የፋሲካ በዓልንና የደም ርጭት ሥርዓትን ያካሄደው በእምነት ነበር። 29 እስራኤላውያን በደረቅ መሬት ላይ እንደሚሄዱ ቀይ ባሕርን የተሻገሩት በእምነት ነበር። ግብጻውያን ይህን ለማድረግ በሞከሩ ጊዜ ተዋጡ። 30 የኢያሪኮ ግንብ በእምነት የወደቀው ለሰባት ቀናት ከተከበበ በኋላ ነበር። 31 ሴተኛ አዳሪዋ ረዓብ ሰላዮቹን ለደህንነታቸው ተጠንቅቃ ስለተቀበለቻቸው ከማይታዘዙት ጋር ያልጠፋችው በእምነት ነበር። 32-33 እንግዲህ ከዚህ የበለጠ ምን ልበል? በእምነት መንግሥታትን ድል ስላደረጉት፣ ፍትህን ስላስከበሩትና የተስፋ ቃሎችን ስለተቀበሉት ስለነጌደዎን፣ ባርቅ፣ ሳምሶን፣ ዮፍታሄ፣ ዳዊት፣ ሳሙኤልና ነቢያት እንዳልናገር ጊዜ ያጥረኛል። 34 እነርሱ የአንበሶችን አፍ ዘጉ፣ የእሳትን ኃይል አጠፉ፣ ከሰይፍ ስለት አመለጡ፣ ከበሽታ ተፈወሱ፣ በጦርነት ኃያላን ሆኑ፥ የባዕድን ሠራዊት አባረሩ። 35 ሴቶች ሙታናቸው ከሞት ተነሡላቸው። ሌሎች የተሻለውን ትንሣኤ ያገኙ ዘንድ ከእስር መፈታታቸውን ለመቀበል እምቢ በማለት ተሠቃዩ። 36 የተቀሩት ደግሞ በስድብና በግርፋት፣ እንዲያውም በሰንሰለት በመታሰር ተሠቃዩ። 37 በድንጋይ ተወገሩ። በመጋዝ ለሁለት ተሰነጠቁ። በሰይፍ ተገደሉ። ይህ ዓለም ስላልተገባቸው 38 በምድረበዳ፣ በተራሮች፣ በዋሻዎችና በየጉድጓዱ እየተጎሳቆሉ፣ መከራ እየተቀበሉና ግፍ እየተፈጸመባቸው የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው በመንከራተት ዞሩ። 39 እነዚህ ሰዎች ሁሉ ስለ እምነታቸው በእግዚአብሔር ዘንድ የተመሰከረላቸው ቢሆኑም የተሰጣቸውን ተስፋ አልተቀበሉም። 40 እነርሱ ያለ እኛ ፍጹም ስለማይሆኑ እግዚአብሔር ለእኛ የተሻለውን ነገር አስቀድሞ ሰጠን።
እምነት አንድ ሰው በመተማመን በመጠበቅ ላይ ሳለ የሚኖረው እርግጠኝነት ነው "እምነት አንድ ሰው በመተማመን ለመጠባበቅ የሚሆነው መሠረት ነው" በመተማመን በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ቃል የሚያመለክተው እርግጠኛ የሆነውን የእግዚአብሔርን የተስፋ ቃል ነው፡፡ በተለይም ሁሉም አማኞች በኢየሱስ ክርስቶስ የሆኑት አማኞች አንድ ቀን በሰማይ ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላለም እንደሚሆኑ ያላቸው እርግጠኝነት ነው፡፡ ስለዚህም በዚህ አማካኝነት "ምክንያቱም አሁን ለማይታየው ነገር እንደኳ እርግጠኞች ናቸው" አባቶቻችን በእምነታቸው አስተዋሉ "እግዚአብሔር አባቶቻችን ከእምነታቸው የተነሣ አረጋግጧል"
ይበልጥ ተገቢ ነው "የተሻለ" አቤል አሁንም ይናገራል አማራጭ ትርጉም: "አቤል በቀጣይነት እያስተማረን ያለው ነገር ምንድ ነው"
በእምነት ያዕቆብ ተነጠቀ፣ ሞትም አላገኘውም አማራጭ ትርጉም፡ "በእምነት ያዕቅብ አልሞተም ምክንያቱም እግዚአብሔር ወስዶታልና ሞትን አለየም "ሞት" እርሱ እግዚአብሔርን አስደስቶታል ተብሎ ስለእርሱ ተነግሮአል፡፡ አማራጭ ትርጉሞች: 1) "እግዚአብሔር ሔኖክ እንዳስደሰተው ተናግሯል" ወይም 2) "ሰዎች ሔኖክ እግዚአብሔርን እንዳስደሰተው ተናግሯል፡፡" ከመወሰዱ በፊትም "እግዚአብሔር እርሱን ከመንጠቁ በፊት"
በእግዚአብሔር ማስጠንቀቂያ ስለተሰጣቸው አማራጭ ትርጉም: "ምክንያቱም እግዚአብሔር አስጠንቅቋቸዋል" ያልታዩ ነገሮች አማራጭ ትርጉም: "ከዚህ በፊት ማንም አይቶት የማያውቀው ነገር" ዓለም በዚያን ዘመን በዓለም ውስጥ ይኖሩ የነበሩት ሌሎች ሰዎች፡፡
ወደ . . . ሄደ "ወደ . . . ለመሄድ ቤቱን ተወ" ወደ ተስፋይቱ ምድር "እግዚአብሔር ለእርሱ ቃል የገባው ምድር" አብረን ወራሾች "ከእርሱ ጋር ወራሾች ነን" አርክቴክት የሕንጻ ግንባታ ንድፍ የሚሠራ ሰው
የማርገዝ ኃይል "የማርገዝ በቃት" እግዚአብሔር . . . መቀበል "እግዚአብሔር . . እንደሆነ ማመን" ዘሮችን የማይቆጠሩ . . . በሰማይ እንዳለ ክዋክብት እና በሐይቅ ዳር እንዳለ አሸዋ በጣም ብዙ
ከርቀት ተመልከተው ተሳለሙት This phrase is comparing the prophet's understanding of future events to welcoming a traveler arriving from far away. AT: "having understood what God will do in the future" ተቀብለዋል "ተቀባይነት ማግኘት" ወይም "መቀበል" እንግዶች "መጻፈተኞች" ወይም "የውጪ ሰዎች" ሀገር ቤት "ሀገር"
በእርግጥ "በእርግጠኝነት" ወይም "በእግጥ" ወይም "ለዚህ ነገር ትኩረት ስጡ:" ሰማያዊው ሥፍራ "ሰማያዊው ሀገር" ወይም "በሰማይ ያለው ሀገር" እግዚአብሔርን አምላካቸው ብለው ለመጥራት አላፈሩም "እግዚአብሔር አምላካቸው ብለው ይጠሩት ዘንድ ፈቃደኛ ነው" ወይም "እግዚአብሔር ለሌሎች የእነርሱ አምላክ ብለው ይጠሩት ዘንድ ፈቃደኛ ነው"
መስዋእት ማቅረብ እንደ ስጦታ ወይም ለእግዚአብሔር መስዋእት ከልጅህ ከይሳቅ ዘር "የአንተ ዘሮች ተብለው የሚጠሩት የይሳቅ ልጆች ናቸው" እርሱን መልሰው ተቀበሉት "አብረሃም ይሳቅን መልሶ ተቀበለው"
ያዕቆብ አመለከ "ያዕቅብ እግዚብሔርን አመለከ" የእርሱ መጨረሻ "የእርሱ ሞት"
ሙሴ ከተወለደ በኋላ በወላጆቹ ለሦስት ወር ያኸል ሸሸጉት አማራጭ ትርጉም: "የሙሴ ወላጆች ሙሴ ከተወለደ በኋላ ለሦስት ወራት ያኸል ሸሸጉት" አደገ "ትልቅ ሰው ሆነ" የእግዚአብሔርን ሕዝብ ስቃይ ተካፈለ "ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር ተሰቃየ" ክርስቶስን መከተል ያለው መከራ "ክርስቶስ የሚፈልገውን ነገር በማድረጉ ምክንያት ከሰዎች ዘንድ የሚደርስበት ነቀፋ" ወደፊት የሚያገኘውን ሽልማት ከፊቱ አተኩሮ እየተመለከተ "በሰማይ የሚያገኘውን ሽልማት እያሰበ"
እንዲህ አላደረገም . . . ጸንቶ አለፈ . . . አስቀድሞ ተመለከተ ሙሴ የማይታየውን እየተመለከተ "ያግዘው ዘንድ በእግዚአብሔር ላይ እየተደገፈ" የማይታይ "በዐይን ማየት የማይቻል"
አለፉ እስራኤላዊያን አለፉ ተዋጡ አማራጭ ትርጉም፡ "ውሃው ዋጣቸው" ወይም "ሰመጡ" ለሰባት ቀናት በዙሪያው ዞሩ አማራጭ ትርጉም: "እስራኤላዊያን ለሰባት ቀናት በዙሪያው ተሰልፈው ዞሩ" ለመሰለል የተላት ሰዎች በሰላም ተቀበለች አማራጭ ትርጉም: "ለመሰለል የተላኩትን ሰዎች ሸሸገቻቸው"
ከዚህ በተጨማሪ ምን ማለት እችላለሁ? አማራጭ ትርጉም: "ከዚህ በተጨማሪ በጣም ብዙ ምሳሌዎችን ማንሳት ይቻላል፡፡" ጊዜ ያጥረኛል አማራጭ ትርጉም: "በዚ ጊዜ አይኖረኝም" ተቆጣጠሩት "አሸነፉ" የአንበሳውን አፍ ዘጋ . . . የእሳቱን ነበልባል ያጠፋ . . . ከሰይፍ የታደገ የእስራሴል ሕዝቦች ከሞት ያመለጡባቸው መንገዶች፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "አንበሶች አልበሏቸውም . . . እሳቱ አላቃጠላቸውመረ . . . ሰይፍ አላጠፋቸውም፡፡" ተፈወሱ አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር ፈወሳቸው"
ሴቶች ሙታናቸውን በትንሳኤ ተቀበሉ "ሴቶች የሞተባቸውን ሰው እግዚአብሔር ከሞት አስነስቶ ሰጣቸው" ሌሎች ተገረፉ . . . ሌሎች መዘባበቻ ሆኑ እንዲሁም ተገረፉ . . . በደንጋይ ተወግረው ሞቱ . . .በመጋዝ ተሰንጥቀው ሞቱ . . . ሌሎስ በሰይፍ አንገታቸው ተቀላ አማራጭ ትርጉም: "ሌሎች በሰዎች ተገርፈው መከራን ተቀበሉ . . . ሌሎች በሰዎች መሳለቂያ ሆነው ተገረፉ . . . ሌሎች በደንጋይ ተወገሩ . . . ሌሎስ በመጋዝ ለሁለት ተሰንጥቀው ሞቱ . . . ሌሎች ተገደሉ፡፡" መገረፍ ከፍተኛ ስቃይን መቀበል መለቀቃቸውን አልፈለጉም "ሰዎች ከእስር ይለቋቸው ዘንድ ክርስቶስን ለመካድ ፈቃደኞች አልበሩም" በሰንሰለት መታሰር እንኳ "ሰዎች በሰንሰለት አስረዋቸው በወህኒ ቤት ውስጥ ያኗሮዋቸው ነበር" ተዘዋወሩt "ከቦታ ቦታ ተጓዙ" ወይም "በሁሉም ጊዜ ኖሩ" ተቸገሩ "ምንም ነገር አልነበራቸውም" ወይም "ምንም አልነበራውም" ወይም "ደሃ"
ከእምነታቸው የተነሣ ምንም እንኳ እነዚህ ሰዎች ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት ቢኖራቸውም ተስፋ የገባላቸው ነገር ግን አልተቀበሉም ነበር፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ከእምነታቸው የተነሣ እነዚህ ሰዎች እግዚአብሔር አክብሯቸዋል ይሁን እንጂ እግዚአብሔር የገባላቸውን የተስፋ ቃል እነርሱ አልተቀበሉትም፡፡"
1 እንደነዚህ ያሉ እጅግ ብዙ ምስክሮች ስላሉን፣ የሚከብደንን ነገር ሁሉና በቀላሉ የሚጠላልፈንን ኃጢአት አሽቀንጥረን እንጣል። ከፊታችን ያለውንም ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ። 2 በእምነታችን ጀማሪና ፍጹም አድራጊ ኢየሱስ ላይ ዓይኖቻችን እንትከል። እርሱ ከፊቱ ስላለው ደስታ መስቀሉንና መስቀሉ የሚያስከትለውን ውርደት ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጧል። 3 እንዳትደክሙ ወይም ልባችሁ እንዳይዝል፣ ከኃጢአተኞች የተሰነዘረበትን እንዲህ ያለውን የጥላቻ ንግግር የታገሠውን እርሱን አስቡ። 4 ደም እስከማፍሰስ ድረስ ኃጢአትን አልተቃወማችሁም፣ አልታገላችሁትምም። 5 ደግሞም እንደ ልጆች፡ “ልጄ ሆይ የጌታን ቅጣት አታቅልል፣ በሚቀጣህም ጊዜ ልብህ አይዛል። 6 ጌታ የሚወደውን ይገሥጻል፣ የሚቀበለውን ማንኛውንም ልጅ ይቀጣል" በማለት የተናገራችሁን ማበረታቻ ምክር ረስታችኋል። 7 አባት በልጆቹ እንደሚደረግ እግዚአብሔርም በእናንተ ላይ ስለሚያደርግ፣ መከራን እንደ ተግሣጽ በመቁጠር ታገሡ። ለመሆኑ አባቱ የማይቀጣው ልጅ ማን ነው? 8 ነገር ግን እኛ ሁላችን ከምንካፈለው ተግሣጽ ውጭ ከሆናችሁ፣ ዲቃሎች እንጂ ልጆች አይደላችሁም። 9 ከዚህም በላይ የሚቀጡን ምድራዊ አባቶች ነበሩን፤ እኛም እናከብራቸው ነበር። ይልቁንስ መንፈስ ለሆነው አባት እየታዘዝን መኖር የቱን ያህል ይገባናል? 10 በእርግጥ አባቶቻችን ለእነርሱ መልካም መስሎ እንደታያቸው ለጥቂት ጊዜ ይቀጡን ነበር፣ እግዚአብሔር ግን የእርሱን የቅድስናው ተካፋዮች እንድንሆን ለጥቅማችን ያቀጣናል። 11 ቅጣት በወቅቱ የሚያም እንጂ አስደሳች አይደለም። ይሁን እንጂ፣ ለለመዱት በመጨረሻ ሰላማዊ የጽድቅ ፍሬን ያፈራል። 12 ስለዚህ የዛሉ እጆቻችሁን ወደ ላይ አንሡ፣ የደከሙ ጉልበቶቻችሁንም እንደገና አበርቱ፤ 13 የሚያነክስ ማንም ቢኖር እንዲፈወስ እንጂ እንዳይናጋ እግሮቻችሁ የሚራመዱባቸውን መንገዶች ቀና አድርጉ። 14 ከሰው ሁሉ ጋር ሰላምን ተከታተሉ፣ ቅድስናንም ተከታተሉ፣ ያለ ቅድስና ማንም ጌታን ሊያይ አይችልም። 15 ማንም ከእግዚአብሔር ጸጋ እንዳይጎድል፣ መራራ ሥርም አድጎ እንዳያስጨንቅና ብዙዎችን እንዳይመርዝ ተጠንቀቁ። 16 ለአንድ መብል ብሎ ብኩርናውን እንደሸጠ እንደ ኤሳው እግዚአብሔርን የማይፈራ፣ ወይም ሴሰኛ የሆነ ማንም እንዳይኖር ተጠንቀቁ። 17 ከዚያ በኋላ በረከትን ለመውረስ እያለቀሰ በትጋት ቢፈልግም፣ ከአባቱ ዘንድ የይቅርታ እድል እንዳጣና እንደተጣለ ታውቃላችሁ። 18 የሚቃጠል እሳት፣ ጨለማ፣ ጭጋግና ማዕበል ወዳለበት በእጅ ሊነካ ወደሚችል ተራራ ገና አልመጣችሁም። 19 የሰሙትም ሌላ ቃል እንዳይነገራቸው እስከሚለምኑ ወዳደረሳቸው ቃልን ወደሚያሰማ ድምጽ ወይም የመለከት ጩኹት ገና አልመጣችሁም። 20 ይህም፣ “እንስሳም እንኳ ቢሆን ተራራውን ከነካ በድንጋይ ይወገር” ተብሎ የተሰጠውን ትእዛዝ ሊሸከሙት አልቻሉም። 21 ሙሴ፣ “እጅግ ስለፈራሁ እየተንቀጠቀጥሁ ነኝ” እስከሚል ድረስ ይህ ስፍራ አስፈሪ ነበር። 22 አሁን ግን፣ የሕያው እግዚአብሔር ከተማ ወደሆነችው ወደ ጽዮን ተራራ፣ አእላፋት መላእክት በደስታ ወደሚያመልኩባት ሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም መጥታችኋል፤ 23 በሰማይ ወደሚገኙት የበኩራን ሁሉ ጉባኤ፣ የሁሉም ፈራጅ ወደሆነው እግዚአብሔርና ፍጹም የተደረጉ የጻድቃን መንፈሶች ወዳሉበት መጥታችኋል፤ 24 የአዲስ ኪዳን መካከለኛ ወደሆነው ኢየሱስና ከአቤል ደም የተሻለውን ወደሚናገር ወደተረጨው ደም ደርሳችኋል። 25 የሚናገራችሁን እምቢ እንዳትሉ ተጠንቀቁ። እነርሱ በምድር ላይ ሆኖ ያስጠነቀቃቸውን እምቢ በማለታቸው ካላመለጡ፣ በሰማይ ሆኖ ከሚያስጠነቅቀን በእርግጥ አናመልጥም። 26 በዚያን ጊዜ ድምጹ ምድርን አናወጠ። ነገር ግን፣ “አንድ ጊዜ ደግሜ ምድርን ብቻ ሳይሆን ሰማያትንም አናውጣለሁ” በማለት አሁን ተስፋ ሰጥቷል። 27 “አንድ ጊዜ ደግሜ” የሚል ቃል፣ ያልተናወጡ ነገሮች መጽናታቸውን፣ የተናወጡት ማለትም የተፈጠሩት ነገሮች መወገዳቸውን ያመላክታል። 28 ስለዚህ፣ ሊናወጥ የማይችል መንግሥት ስለተቀብልን አምላካችንን እናመስግነው፣ ደግሞም እግዚአብሔርን ተቀባይነት ባለው በአክብሮትና በፍርሃት እናምልከው፣ 29 ምክንያቱም አምላካችን የሚባላ እሳት ነው።
እኛ . . . እኛ ጸሐፊው እና ተደራሲያኑ በታላቅ የዳመና ምስክሮች ተከበናል አማራጭ ትርጉሞች፡ "ይህን ይኸል ትልቅ የዳመና ምስክሮቹ በዙሪያችን አሉ" ወይም "ይህን የኸል ብዛት ያለው የምስክር እንደ ምሳሌ አሉልን፡፡" ምስክር እነዚህ የብሉይ ኪዳን አማኞች “ሩጫቸውን” እየተመለከቱ የሚከብደንን ነገር ሁሉ እንደ ከባድ ልብስ ወይም ሸክም ሆኖ ሩጫችንን በአግባቡ እንዳንሮጥ የሚያደርገንንን በእግዚአብሔር እንዳንታመን እና እርሱን እንዳንታዘዝ የሚያደርገንን ማንኛውንም አመለካከት ወይም ባሕርይ፡፡ የሚያስችግረንን "ሩጫችንን አስቸጋሪ የሚያደርግን" ወይም "እግዚአብሔርን መታዘዝ አስቸጋሪ የሚያደርግን ነገር" ዐይናችንን . . . አድርገን "ወደፊት እየተመለከትን" ወይ "ስለእርሱ ብቻ እያሰብን" ጀማሪ እና ፈጻሚr አማራጭ ትርጉም: "ፈጣሪ እና ጨራሽ" ድካም ለረጅም ጊዜ እንደሮጠ ሰው መሮጥ ያቃተው ለረጅም ሰዓት ከመሮጡ የተነሣ መሮጥ ያቃተው
ኃጢአትን እስከ ደም ጠብታ ድረስ ገና አልተቃወማችሁትም ወይም አልተቋቁማችሁትም "ኃጢአትን ተቃውማችሁታል እንዲሁም ተቋቁማችሁታል ይሁን እንጂ ሌሎች ግን ይህንን ያደረጉት እስከ ደም ጠብታ ድረስ ነው፡፡" resisted...to...blood "እስከ . . . ሞት . . መቋቋም፡፡" ይህንን በማድረጉ የሚሞት እንኳ ቢሆን ትክክለለኛውን ነገር ያደርጋል፡፡ ለእናንተ የማበረታቻ ትምህርት በብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ውስጥ የሚገኘው የሰለሞን ጽሑፍ በጌታ ቅጣት ውስጥ ሰዎች በሚሆኑበት ወቅት እንዴት መበረታተታች እንዳለባቸው ግንዛቤን እንዲያገኙ ይረዳል፡፡ የጌታን ተግሳጽ በቀላሉ አትውሰደው "ተግሳጹን በቁም ነገር ውሰደው" የጌታን ተግሳጽ "ጌታ ሲገስጽህ" ልብህ አይዛል "ተስፋ አትቁረጥ"
እንደ ተግሳጽ ሁሉ በመከራም ጽና አስቸጋሪ ጊዜያትን ልክ እንደ ተግሳጽ ጊዜያት አድረገህ ተመልከታቸው፡፡ ልጁን የማይገስጽ አባት ማን ነው? አማራጭ ትርጉም: "ማንኛውም አባት ልጆቹን ይገገስጻል" ሕጋዊ ያልሆኑ ልጆች ካልተጋቡ ወንድ እና ሴት የተወለዱ ልጆች
የመንፈስ አባት የመንፈሳችን እና ሌሎች መናፈስትንም የፈጠረው እግዚብሔር፡፡ የጽድቅ ፍሬ ልክ ዛፍ ፍራፍሬ እንደሚያፈራ ሁሉ ጽድቅም የተግሳጽ ውጤት ነው፡፡ በእርሱ ሰልጥኗል በተገሳጽ ተገርቷል
የዛለውን እጆቻችሁን አንሱ እንዲሁም የላላውን ጉልበታችሁን እደገና አጽኑ ተግዳሮት የገጠመው ሰው በሩጫ ብዛት እግሮቹ እና ጉልበቱ የዛለን ሯጭ ይመስላል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ልክ ሯጭ ሩጫውን ለማጠናቀቀው ስወስን አካሉን እንደሚያበረታው ሁሉ እናነት ራሳችሁን አበርቱ" ለእግሮቻችሁ ቀናን መንገድ አዘጋጁ እግዚአብሔርን መታዘዝ ልክ በቀና መንገድ እንደመጓዝ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር እንዲታደርጉ የሚፈልገውን ነገረ አድርጉ" ማቋረጥ የሚፈልግ ሰው አማራጭ ትርጉም: "ሩጫውን ማቋረጥ የሚፈልግ ማንም ሰው" በተሳሳተ አቅጣጫ አትጓዝ "ሌላ ሰው ተከትለህ በተሳሳተ መንገድ አትሂድ፡፡" አማራጭ ትርጉም: "እግዚብሔርን የማያስከብሩ ነገር ግን ቀላል የሆኑ ነገሮችን ለማድረግ አትወስን፡፡" ይልቁን በርታ "ይልቁንም ጠንካራ ሁን"
እንዲሁም ከቅድስና ውጪ ጌታ ማንም ልያየው አይችልም አማራጭ ትርጉም: "በተጨማሪም ለመቀደስ ጠንክረህ ሥራ ምክንያቱም ቅዱስ የሆኑ ሰዎች ብቻ ናቸው ጌታን ማየት የሚችሉት" በተጨማሪም ቅድስና "በተጨመማሪም ቅድስናን ተከታተል" ተጠንቀቅ . . . ማንም እንዳይቀር . . . መራራ ሥር እንዳይበቅል . . . ይህ እንዳይሆን አድረግ መሪዎች ከእነዚህ ሦስ ነገሮች ልጠበቁ ይገባል፡ “ማንም እንዳይገለል . . መራራ ሥር በልባቸውን እንዳይበበቅል . . . ይህ እንዳይሆን መጠንቀቅ ይገባቸዋል፡፡" ከእግዚአብሔር ጸጋ እንዳይጎድሉ "አንድ ጊዜ የእግዚአብሔር ጸጋ ተቀብለው ከዚያ ወደ ኃላ እንዳይመለሱ" መራራ ሥር ሌሎች ሰዎች ክፋት እንዲያደርጉ የሚያደርግ ሰው ሥርን በምግብ ውስጥ እንደሚያደረግ ሰው ነው ተተጠንቀቁ . . . ልክ ኤሳው አማራጭ ትርጉም: "ተጠንቀቁ . . . ከእናንተ መካል እነንደ ኤሳው፡፡ በእንባ አጽንት ቢፈልገውም "እያለቀሰ ከልቡ ቢፈልግ"
እናንተ አንባቢያን ትዕዛዛቱን መፈጸም አልቻሉም የሚትሸከመውን ሸከም እንደሚትቀበለው ሁሉ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ መቀበል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እስራኤላዊያን የእግዚአብሔር ሕግ አልተቀበሉትም ነበር፡፡"
እናንተ አንባቢያን መጥጣችኋል "ወደ . . . ደርሳችኋል" ዐሥር ሺህ መላእክት "ቁጥር ስፍር ወደላሌላቸው መላእክት" ፈራጁ አምላክ . . . ኢየሱስ መካከለኛው ኢየሱስ በፍርድ ቤት ውስጥ እንዳለ ጠበቃ የፈሰሰው የእርሱ ደም እንዴት ለሰዎች በደል ይቅርታ እንደሚሆን ያሳያል፡፡ ከአቤል ደም ይልቅ አብልጦ የሚናገር ደም ተርጭቷል "የተረጨው የኢየሱስ ደም ቃዬል ከገደለው ከአቤል ደም ይልቅ ትርጉም አለው፡፡"
መናወጥ . . . መንቀጥቀጥ በምድር መንቀጥቀጥ ምክንያት የሚከሰትን የምድር መናወጥ እና የሐህንጻዎች መደርመስን ለማመልከት የሚውልን ቃል ተጠቀም፡፡ እናንተ አንባቢያን እነርሱ ማምለጥ ካልቻሉif they did not escape "የእስራኤል ሰዎች ይህንን ፍርድ ማለፍ ካልቻሉ" እኛ ጸሐፊዎች እና አንባቢያን የሚያስጠነቅቁትም . . . የተስፋ ቃል ገብቷል "እግዚአብሔር አስጠንቅቋለል . . . እግዚአብሔር የተስፋ ቃል ሰጥቷል"
ተናውጠዋል "መንቀጥቀጥ" እና "መናወጥ" የሚሉትን ቃላት በ HEB 12:26 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምካቸው ተመልከት፡፡ አመስጋኞች እንሁን "ምስጋናን እንስጥከ" አክብሮት እና አድናቆት ጋር "አክብሮት" እና "አድናቆት" የሚሉት ሁለት ቃላት ተመሳሳይ ትርጉሞች ያሉት ሲሆን አጽኖት ሰጥተው የሚያስተላልፉት መልዕክት ታላቅ አክብሮት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ከታላቅ አክብሮት ጋር" አምላካችን እግዚአብሔር የሚባላ እሳት ነው እግዚአብሔር ልክ እሳት ነገሮችን እንደሚያቃጥል ሁኔ ከእርሱ ዓላማ ጋር የሚቃረንን ማንኛውንም ነገር ለማፍረስ የሚያስችል ኃይል አለው፡፡
1 በወንድማማችነት ፍቅር መዋደዳችሁን ቀጥሉ። 2 እንግዶችን መቀበል አትርሱ፣ አንዳንድ ሰዎች ይህን ሲያደርጉ ሳያውቁት መላእክትን አስተናግደዋል። 3 ከእነርሱ ጋር እንደታሰረ ሆናችሁ፣ በሰውነታችሁም እንደ እነርሱ መከራን እንደሚቀበል ሆናችሁ በእስራት ያሉትን አስቡ። 4 ጋብቻ በሁሉም ዘንድ የተከበረ መኝታውም ንጹሕ ይሁን፣ ምክንያቱም እግዚአብሔር በሴሰኞችና በአመንዝራዎች ላይ ይፈርድባቸዋል። 5 አኗኗራችሁ ከገንዘብ ፍቅር የጸዳ ይሁን። እግዚአብሔር ራሱ፣ “እኔ ፈጽሞ አልተውህም፣ ደግሞም አልጥልህም” ስላለ፣ ባላችሁ ነገር ረክታችሁ ኑሩ። 6 ስለዚህ፣ “ጌታ ረዳቴ ነው፤ አልፈራም። ሰውስ ምን ሊያደርገኝ ይችላል?” ብለን በድፍረት እንናገራለን። 7 የእግዚአብሔርን ቃል የነገሯችሁን መሪዎቻችሁን አስቡ፣ የምግባራቸውንም ፍሬ ተመልከቱ፤ በእምነታቸውም ምሰሏቸው። 8 ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንት፣ ዛሬና ለዘላለምም ያው ነው። 9 በልዩ ልዩ እንግዳ ትምህርቶች አትወሰዱ፣ ለሚከተሏቸው ሰዎች ፋይዳ የሌላቸውን የአመጋገብ ሥርዓቶች በመጠበቅ ሳይሆን ልብ በጸጋ ሲጸና መልካም ነው። 10 በመገናኛው ድንኳን የሚያገለግሉት ከእርሱ እንዲበሉ ያልተፈቀደላቸው መሠዊያ አለን። 11 ሊቀካህናቱ ለኃጢአት ስርየት የተሠዋውን የእንስሳት ደም ወደ ቅድስት ያመጣል፣ የእንስሳቱ ሥጋ ግን ከሰፈር ውጭ ይቃጠላል። 12 ደግሞም ኢየሱስ ሰዎችን በገዛ ደሙ ለመቀደስ ከከተማይቱ ቅጥር ውጭ መከራን ተቀበለ። 13 ስለዚህ እኛም እርሱ የተሸከመውን ውርደት ተሸክመን ከሰፈር ውጭ ወደርሱ እንሂድ። 14 በዚህ ምድር ምንም ዓይነት ዘላቂ ከተማ የለንም። ነገር ግን የምትመጣውን ከተማ እንጠብቃለን። 15 የስሙን ታላቅነት የሚናገሩ የከንፈሮቻችንን ፍሬ፣ ማለትም የምስጋና መሥዋዕቶችን ያለማቋረጥ በኢየሱስ በኩል ለእግዚአብሔር ማቅረብ ይገባናል። 16 ደግሞም መልካም ማድረግንና እርስ በርስ መረዳዳትን አትርሱ፣ ምክንያቱም እግዚአብሔር የሚደሰተው እንደነዚህ ባሉ መሥዋዕቶች ነው። 17 ተጠያቂነት ስላለባቸው ለነፍሳችሁ እንክብካቤ ለሚያደርጉ ለመሪዎቻችሁ ታዘዙ፣ ተገዙላቸውም። ለእናንተ ስለማይጠቅም በሐዘን ሳይሆን በደስታ እንዲንከባከቧችሁ ታዘዟቸው። 18 በሁሉም ነገር የከበረ ሕይወት ለመኖር የሚፈልግ ንጹሕ ኅሊና ስላለን ጸልዩልን። 19 ወደ እናንተ ቶሎ መመለስ እንድችል ይበልጥ ይህን እንድታደርጉ አበረታታችኋለሁ። 20-21 እንግዲህ በዘላለም ኪዳን ደም የበጎች ታላቅ እረኛ የሆነውን ጌታችን ኢየሱስን፣ ከሙታን ያስነሣው የሰላም አምላክ እግዚአብሔር፣በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት በእኛ ውስጥ የሚሠራውን፣ በእርሱ ፊት ደስ የሚያሰኘውን ፈቃዱን እንድታደርጉ በማናቸውም መልካም ነገር ያስታጥቃችሁ። ከዘላለም እስከ ዘላለም ለእርሱ ክብር ይሁን። አሜን። 22 ወንድሞች ሆይ፤ አሁን በዐጭሩ የጻፍሁላችሁን ማበረታቻ እንድትቀበሉ አደፋፍራችኋለሁ። 23 ወንድማችን ጢሞቴዎስ እንደተፈታ ዕወቁ፣ ቶሎ ከመጣም ከእርሱ ጋር አብሬ አያችኋለሁ። 24 ለመሪዎችና ለቅዱሳን ሁሉ ሰላምታ አቅርቡልኝ። በኢጣልያ ያሉት ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። 25 ጸጋ ከሁላችሁም ጋር ይሁን።
የወንድማማች ፍቅራችሁ ይቀጥል አማራጭ ትርጉም፡ "ሁል ጊዜ ለሌሎች አማኞች ልክ ለቤተሰባችሁ አባላት የሚታሳዩትን ዓይነት ፍቅር አሳዩ" አትዘንጉ አማራጭ ትርገጉም: "ማስታወሳችሁን እርግጠኞች ሁኑ" እንግዶችን ተቀበሉ አማራጭ ትርጉም: "የማታውቋቸውን ሰዎች እንደ ጓደኞቻችሁ አድርጋችሁ ተቀበሉ"
ከእርሱ ጋር እንደሆናችሁ በመቁጠር . . . አካላችሁ ልክ እንደ እንደነርሱ እንደተጎሳቆለ በመቁጠር እነዚህ ሁለት ሀረጋት አማኞች የሌሎች ሰዎችን መከራ ልክ እንደ እንደነርሱ መከራ አድርገው ይቆጥሩት ዘነንድ የሚያበረታታ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ከእነርሱ ጋር በእስር እንዳላችሁ እና መከራን እየተቀበላችሁ በመቁጠር" መኝታችሁ ንጹሕ ይሁን ይህ ማለት ባል እና ምስት በትዳራችሁ ውስጥ ያለውን ግንኙነት በማክበር ከሌሎች ሰዎች ጋር አይተኙ፡፡
ያላችሁ ነገር ያርካችሁ "እግዚአብሔር የሰጣችሁ ነገር ያስደስታችሁ"
የተግባራቸው ውጤት አማራጭ ትርጉሞች: 1) "የኖሩበት መንገድ" ወይም 2) "ኖረው የሞቱበት መንገድ" ወይም "ዘመናቸውን ሁሉ የኖሩበት መንገድ" በኢየሱስ አምነው እስከመጨረሻው የኖሩት ኑሮ፡፡
የተለያዩ እና እንግዳ ትምህርቶች "እኛ የነገርናችሁ ወንጌል ሳይሆን ብዙ እና የተለያዩ ትምህርቶች" ልባችን ስለምግብ በሚሰጡ ሕግጋት ሳይሆን በጸጋ መገንባጹ መልካም ነው አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር ለእኛ ምን ያኸል መልካም እነንደሆነ ስነናሰብ እንጠነክራለን ነገር ግን የምግብ ሕግጋትን በመጠበቅ አንጠነክርም" ለኃጢአት መስዋእት መሆን "እግዚአብሔር ኃጢአታችን ይቅር ይላን ዘንድ መስዋእት መሆን" ከቅጥር ውጪ ሰዎች ከሚኖሩበት አከባቢ ርቆ
ስለዚህ "በተመሳሳይ መልኩ" ወይም "መስዋእቱ ከቅጥር ውጪ የሚቃጠል በመሆኑ" (HEB 13:11) ስለዚህም እንሂድ "ስለዚህም ኢየሱስ ከከተማው መግቢያ ውጪ" ከቅጥሩ ውጪ ይህንን በ HEB 13:11 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
የከንፈሮቻችን ፍሬ የሆነውን ምሳጋና ይህ የአነጋር ዘይቤ ልክ ፍራፍሬ ዕጽዋት የሚያፈሩት ዋጋ ያለው ፍሬ እንደሆነ ሁሉ ምስጋና ከአንደበታችን የሚወጣ ዋጋ ያለው ነገር መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡
በዘላለማዊ ኪዳን ደም አማራጭ ትርጉሞች: 1) "እግዚአብሔር ዘላለማዊ ኪዳኑን በደም አረጋግጦዋል" (UDB) ወይም 2) "በዘላለማዊ ኪዳን ደም" አማካኝነት ነው ኢየሱስ "ጌታችን" የሆነው ወይም 3) እግዚአብሔር ኢየሱስን “ከሞት” “መልሶ” ያመጣው "በደም . . . ኪዳን" ነው፡፡ እናንተን አስታጥቆ . . . በእኛ ውስጥ በመሥራት ደራሲው እና ተደራሲያኑ
ኖት የለውም።
1 በኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር እስረኛና አገልጋይ የሆነ ያዕቆብ በክርስቶስ ኢየሱስ ለሚያምኑና በመላው ዓለም ለተበተኑት ለአሥራ ሁለቱ ነገዶች ሰላም ለእናንተ ይሁን፡፡ 2 ወንድሞቼ ሆይ፣ በልዩ ልዩ ፈተናዎች ውስጥ ማለፋችሁን እጅግ ደስ እንደሚያሰኝ ነገር ቊጠሩት፡፡ 3 በፈተና ውስጥ ሳላችሁ በእግዚአብሔር ስታምኑ ይበልጥ ሌሎች ፈተናዎችን በትዕግሥት ለማሳለፍ የሚረዱዋችሁ መሆኑን ትረዳላችሁ፡፡ 4 ክርስቶስን በሁሉም መንገድ ትከተሉ ዘንድ እስከ መጨረሻው በፈተና ጽኑ፤ ያንጊዜ መልካም ማድረግ አይከብዳችሁም፡፡ 5 ከእናንተ አንዱ ምን ማድረግ እንዳለበት ማወቅ ከፈለገ፣ በሚጠይቀው ላይ ሳይቈጣ በልግሥና የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይጠይቅ፡፡ 6 እግዚአብሔርን ስትለምኑ፣ የምትጠይቁትን እንደሚሰጣችሁ እመኑ፤ መልስ እንደሚሰጣችሁና ሁልጊዜም እንደሚረዳችሁ አትጠራጠሩ፤ የሚጠራጠሩ ሰዎች እግዚአብሔርን ሊከተሉት አይችሉም፤ መጠራጠር ልክ ተመልሶ እንደሚመጣ፣ ደግሞም በዚያው አቅጣጫ መጓዝን እንደማይቀጥል የባሕር ማዕበል ያለ ነገር ነው፡፡ 7 በእርግጥ የሚጠራጠሩ ሰዎች የሚጠይቁትን ነገር ለመፈጸም እግዚአብሔር አንድ ነገር ሊያደርግ እንደሚችል አያምኑም፡፡ 8 እነዚህ ሰዎች ኢየሱስን ለመከተል ወይም ላለመከተል ያልወሰኑ ናቸው፤ እነዚህም የሚናገሩትን ነገር የማያደርጉ ሰዎች ናቸው፡፡ 9 ድሀ የሆኑ አማኞች እግዚአብሔር ስላከበራቸው ደስ ሊሰኙ ይገባል፡፡ 10 ባለጠጋ የሆኑ አማኞችም እግዚአብሔር ትሑታን ስላደረጋቸው ደስ ሊሰኙ ይገባል፤ ልክ የበረሃ አበቦች እንደሚደርቁ ሁሉ፣ እነርሱም ሆኑ ሀብታቸው የሚያልፉ ናቸውና፡፡ 11 ፀሐይ በሚወጣ ጊዜ ሞቃታማ የሆነው ነፋስ ተክሎችን ያደርቃል፤ ደግሞም አበቦችን በምድር ላይ እንዲወድቁም ሆነ በውበታቸው እንዳይቀጥሉ ያደርጋቸዋል፡፡ ባለ ጠጎች ልክ እንደሚሞቱ አበቦች ሁሉ ገንዘብን እየሰበሰቡ ሳሉ ይሞታሉ፡፡ 12 በመከራ የሚጸኑትን ሰዎች እግዚአብሔር ያከብራቸዋል፤ ለሚወድዱት ሁሉ ተስፋ እንደ ሰጠው ለዘላለም እንዲኖሩ በማድረግ ብድራታቸውን ይከፍላቸዋል፡፡ 13 በኃጢአት ስንፈተን እግዚአብሔር እየፈተነን ነው ብለን ልናስብ አይገባም፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ክፉን እንድንሠራ አይፈልግምና፤ ክፉን እንዲያደርግ ማንንም አይፈትንምና፡፡ 14 እያንዳንዱ ሰው የሚፈተነው በራሱ ክፉ ምኞት ሲታለልና ሲሳብ ነው። 15 ክፉ ምኞት ከተፀነሰ በኋላ ኀጢአት ይወለዳል፤ ኀጢአትም ካደገች በኋላ ሞት ይወለዳል። 16 የተወደዳችሁ ወንድሞቼ አትታለሉ። 17 ማንኛውም መልካምና ፍጹም ስጦታ እንደሚዘዋወር ጥላ ከማይለዋወጠው ከላይ ከሰማይ ከብርሃናት አባት ይወርዳል። 18 በፍጥረታቱ መካከል እንደ በኵራት እንድንሆን እግዚአብሔር በእውነት ቃል ሕይወት ሊሰጠን ወደደ። 19 የተወደዳችሁ ወንድሞቼ፣ ይህን ዕወቁ። ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ፣ ለመናገር የዘገዬ፣ ለመቆጣትም የዘገዬ ይሁን! 20 ምክንያቱም የሰው ቊጣ የእግዚአብሔርን ጽድቅ አያመጣም። 21 ስለዚህ ርኵሰትንና በየቦታው ሞልቶ ያለውን ክፋት አስወግዳችሁ ነፍሳችሁን ማዳን የሚችለውን በውስጣችሁ የተተከለውን ቃል በትሕትና ተቀበሉ። 22 ለቃሉ ታዘዙ እንጂ፣ ሰሚዎች ብቻ በመሆን ራሳችሁን አታታልሉ። 23 ማንም ቃሉን እየሰማ ቃሉ የሚለውን ባያደርግ፣ ፊቱን በመስታወት እንደሚያይ ሰው ይሆናል። 24 ፊቱን አይቶ ይሄዳል፤ ምን እንደሚመስል ግን ወዲያው ይረሳዋል። 25 ፍጹሙንና ነጻ የሚያወጣውን ሕግ በጥንቃቄ የሚመለከትና የሚኖርበት እንጂ፣ ሰምቶ እንደሚረሳው ያልሆነ ሰው በሚያደርገው ሁሉ የተባረከ ይሆናል። 26 አንድ ሰው ሃይማኖተኛ ነኝ እያለ፣ አንደበቱን ግን ባይቆጣጠር፣ ልቡን ያስታል፤ ሃይማኖቱም ከንቱ ነው። 27 በእግዚአብሔር በአባታችን ፊት ንጹሕና ርኵሰት የሌለበት ሃይማኖት ይህ ነው፤ አባት የሌላቸውንና መበለቶችን በችግራቸው መርዳት፤ በዓለም ካለ ርኵሰት ራስን መጠበቅ።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ከመክፈቻ ሠላምታው በኋላ ያዕቆብ የመከራ ዓላማ እምነትን ለመፈተን መሆኑን ለአማኞች ይነግራቸዋል፡፡ ያዕቆብ "እኔ ያዕቆብ፡፡" ያዕቆብ የኢየሱስ በአንድ ወገን ወንድም ነው፡፡ የእግዚአብሔር እና የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ “እኔ” የሚለው ሀረግ በተዘዋዋር መልኩ የተገለጸ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እኔ የእግዚአብሔር እና የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ነኝ፡፡" ለተበተኑት ዐሥራ ሁለት ነገዶች ያቆብ የጻፈው ከእስጥፋኖስ መወገር በኋላ በተነሣው ስደት ምክንያት ከይሁዳ ውጪ ባሉ የሮም ከተማዎች ውስጥ ለተበተኑት አይሁዳዊያን አማኞች ነው፡፡ ዐሥራ ሁለት ነገዶች ቁጥሮችን በመጸፍ ወጥነት ሊኖራችሁ ይገባል፡፡ ይህ “12 ነገዶች” ተብሎም ሊጻፍ ይችላል፡፡ ሠላምታ እንደ “ሄሎ” ወይም “መልካም ቀን” የመሳሰሉት መሠረታዉ የሠላምታ አሰጣጥ ነው፡፡ ወንድሞቼ ሆይ የተለያዩ መካራዎች ስደርስባችሁ ይህንን እንደ ደስታ ቁጠሩት "የተለያዩ መከራዎች ስደርሱባችሁ ወንድሞች ሆይ በዚህ ደስ ይበላችሁ፡፡" የእምነታችሁ መፈተን ጽናትን እንደሚያመጣላችሁ በማወቅ "እግዚአብሔር እምነታችሁን ለማጠንከት መከራን እንደሚጠበቅ ሰለምታውቁ ነው፡፡"
ጽናት ሥራውን እንዲፈጽም ፍቀዱለት በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ እንኳ በቀጣይነት ጸንተህ ቁም፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በመከራህ ወቅት ጠንከር በል፡፡" የአንተ . . . ይሆን ዘንድ "በዚህ ምክንያት እግዚአብሔር እምነትህን … ያደርግ ዘንድ" ፍጹም ሙሉ "ፍጹም ሙሉ" ምንም የማይጎድለው ይህ አሉታዊ ሀረግ ሲሆን በአወንታዊ መልኩ እንዲህ መገለጽ ይችላል፡ "ብዙ ያለው" ይህን ከሚሰጠው ከእግዚአብሔር ዘንድ ጠይቅ "ይህንን እግዚአብሔርን ጠይቀው፡፡ ይህንን የሚሰጠው እርሱ ነው፡፡" ሳይነቅፍ በልግስና "ሳይነቅፍ" የሚለው ሀረግ አሉታዊ ነው፤ ይሁን እንጂ አዎንታዊ በሆነ መልኩ እንዲህ መገለጽ ይችላል፣ "በልግስና እና በደስታ፡፡" ይህንን እርሱ ይሰጣል "እግዚአብሔር ይህን ይሰጣል" ወይም "እግዚአብሔር ጸሎትህን ይሰማል"
በምንም ሳይጠራጠር በእምነት “በምንም ሳይጠራጠር” የሚለው አሉታዊ ሀረግ ሲሆን አዎንታዊ በሆነ መልኩ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፣ “እግዚአብሔር ለጸሎት መልስ በእርግጠኝነት ይሰጣል፡፡” የሚጠራጠር ሰው ልጅ በባሕር ላይ እንዳለ ወጀብ በማዕበል ወዲህ እና ወዲያ የሚነዳ ነው ይህ የሚጠራጠር ሰውን በንፋስ በየጊዜው አቅጣጫውን ከሚቀያይር ውሃ ጋር ያነጻጽራል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "የሚጠራጠር ሰው ሁል ጊዜ ወደኋላ እና ወደፊት በማመን እና ባለማመን መካል ይዋዥቃል፡፡" ወይም "የሚጠራጠር ውስጥ ሁል ጊዜ የሚያምነውን ነገር ይለዋውጣል፡፡" የእርሱ ጥያቄ "እርሱ የጠየቀው ምንድ ነው" ጌታን "ከጌታ" ሁለት ሀሳብ ላለው ሀሳብ ያለው ሰው - “ሁላት ሀሳብ ላለው” የሚለው ሀረግ የሚያመለክተው አንድ ሰው አንድን ውሳኔ ለመወሰን ያላስቻለው ሀሳቦች ያሉትን ሰው ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ኢየሱስን መከተል ወይም መከተል እንዳሌለበት ለመወሰን አይችልም"
በመንገዱ ሁሉ የተረጋጋ አይሆንም "ስለምንም ነገር እርግጠኛ መሆን አይችልም"
ደሃ ወንድም "ብዙ ገንዘብ ያሌለው አማኝ" በቆመበት ክብር ይመካ "እግዚብሔር ክብር ስለሰጠው በዚህ ደስ ይበለው" ሀብታም የሆነው ወንድም "ብዙ ገንዘብ ያለው ወንድም" በእርሱ ትህትና ውስጥ የዚህ ሀረግ የተወሰነ ክፍል በተዘዋዋር መንገድ የተገለጸው ማለት “በውርደቱ ይመካ” የሚለው ተትቷል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር ትህትናን ስላስተማረው ደስ ይበለው፡፡" ሀብታም ሰዎች በሥራቸው መካል ተፍተው ይቀራሉና "ሀብታም ሰው ተጨማሪ ገንዝብ ለማግኘት ተግቶ ስሠራ በዚያው ይሞታል"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ያዕቆብ የወደቁ አማኞችን ፈተናን እንደማያመጣ ያስታውሳቸዋል፡፡ ስለዚህም እንዴት ፈተናን ማስወገድ እንዳለባቸው ይነግራቸዋል፡፡ የተባረከ ሰው ነው "ደስተኛ ሰው ነው" በፈተና የሚጸና "መከራ ስመጣ በዚያ ውስጥ ጸንቶ የሚቆም ሰው" ፈተናውን የሚያልፍ "በመከራ ውስጥ ጸንቶ የሚቆም ሰው" እርሲ ይቀበላል "እግዚአብሔር ይሰጠዋል" የሕይወትን አክሊል ይቀበላል "የሕይወት አክሊል" እንደ ሽልማት የሚሰጠው የዘላለም ሕይወት ምሳሌያዊ ንግግር ነው፡፡ "የዘላለም ሕይወትን እንደ ሽልማት ይቀበላል" ይህ እግዚአብሔርን ለመውዱት የተስፋ ቃል ተሰጥቶዋቸዋል አማራጭ ትርጉም፡ "እርሱን ለምወዱት እግዚአብሔር የሕይወትን አክሊል እንደሚሰጣቸው የተስፋ ቃል ሰጥቶዋቸዋል፡፡" በሚፈተንበት ጊዜ "ክፉ የሆነ ነገርን ለማድረግ ፍላጎት በውስጡ ስያድር" ይህ ፈተና ከእግዚአብሔር ነው “እግዚአብሔር ክፉ የሆነ ነገርን እንዳደረግ እያደረገኝ ነው” እግዚአብሔር በክፉ አይፈተን "እግዚአብሔር ክፉን ነገር ለማድረግ አይሻም" እግዚአብሔር ማንንም . . . አይፈትንም "እግዚአብሔር ሰዎች ክፋትን እንዲያደርጉ አይገፋፋም"
እያንዳንዱ ሰው የሚፈተነው በራሱ ክፉ መሻቶቹ ነው ክፋትን ለማድረግ መሻት በእያንዳንዱ ሰው ውስጥ አለ፡፡ ይህ የስበዋል እንዲሁም ይጥለዋል "ይህ ይስበዋል እንዲሁም ወደሌላ አቅጣጫ ይመራዋል" ከዚህ በኋላ ምኞት ፀንሳ ኃጢአትን ትወልዳለች፤ ኃጢአትም ካደገች በኋላ ሞትን ትወልዳለች። "ኃጢአታዊ ምኞች፣" "ኃጢአት፣" እና "ሞት" የሰው ልጅ ባሕርያት ናቸው፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ “ኃጢአታዊ ምኞች” የተገለጸው አንድት ሴት አንድን ወንድ ከእርሷ ጋር እንድተኛ ከሚታማልልበት መንግድ ጋር ተያይዞ ነው፡፡ "ኃጢአት" ልጃቸው ነው፡፡ "ሞት" ልጃቸው ሙሉ ለሙሉ ከደገ በኋላ የሚሆነው ውጤቱ ነው፡፡ በተጨማሪም ይህ ክፉ መሻት በመጀመሪያም ምን ያኸል ደስታን እንደሚሰጥ ያሳያል ነገር ግን ይህ ደስታ ወደ ኃጢአት ይለወጣል ከዚያም አካላዊ እና መንፈሳዊ ሞትን ያስከትላል፡፡ አትታለሉ "ማንም ሰው እንዳያታልላችሁ" ወይም "ራሳችሁን ማታለል አቁሙ" (UDB)
ማንኛውም መልካም የሆነ ስጦታ እና ፍጹም የሆነ ስጦታ እነዚህ ሁለት ሀረጋት በመሠረታዊ ትርጉማቸው ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ያዕቆብ እነዚህ የተጠቀመው ያ ሰው ያለው ማንኛውም መልካም ነገር ሁሉ የመጣው ከእግዚአብሔር ዘንድ መሆኑን አጽኖት ሰጥቶ ለማሳየት ነው፡፡ ከላይ ነው "ከሰማይ ነው" ከብርሃን አባት በሰማይ ያሉትን ብርሃናት (ፀሐይ፣ ጨረቃ እና ክዋክብትን) የፈጠረው እግዚአብሔር ነው፡፡ እርሱ በብርሃን መለዋወጥ አይለዋወጥም ይህ የማይለወጠውን እግዚአብሔርን ለመግለጽ ቀጣይነት ካለው ብርሃን እና በሰማይ ላይ ከሚንቀሳቀሱት ሊሰጠን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ያዕቆብን እና የእርሱ ተደራሲያንን ነው፡፡ ሕይወትን ሰጠን "መንፈሳዊ ሕይወትን ሰጠን፡፡" (UDB) የእውነት ቃል "ወንጌል" ወይም "የኢየሱስ አስተምህሮ" እንደ በኩራት እንደ ሰብል በኩራት የእርሱ ተደራሲያን ከመጀመሪያዎቹ አማኞች መካከል መሆናቸውን ያዕቆብ አጽኖት ሰጥቶ በመግለጽ ለወደፊቱ በጣም ብዙ አማኞች እንደሚኖሩ ይገልጻል፡፡
ከፍጥረታት መካከል "ከእርሱ ሕዝብ መካከል"
ይህንን ታውቃላችሁ አማራጭ ትርጉሞች 1) "ይህንን እወቁ" እንደ ትእዛዝ፣ ቀጥሎ ለሚጽፈው ነገር ከፍተኛ ትኩረት ስጡት ወይም 2) "እናንተ ይህንን ታውቁታላችሁ" እናንተ አስቀድማችሁ የሚታውቁትን ነገር አሁን ላታወሳችሁ ነው የሚል ዓረፍተ ነገር፡፡ ሁሉም ሰው ለመስማት የፈጠነ፣ ለማገር ደግሞ የዘገ ይሁን ሰዎች በመጀሪያ በጥንቃቄ ለማድመጥ ከዚያም የሚናገሩትን ነገር በጥንቃቄ መርጠው መናገር ይኖርባቸዋል፡፡ ለቁጣ የዘገዩ "በቀላዩ የማይቆጡ" የሰው ቁጣ የእግዚአብሔርን ጽድቅ አይሠራም አንድ ሰው ሲቆጣ እግዚአብሔር በሚፈልገው መልኩ ነገሮችን ማከናወን ኤችልም፡፡ ርኩሰተን እና ክፋትን ሁሉ አስወግዳችሁ በዚህ ሥፍራ “ርኩሰትን እና ክፋትን” የሚለው ቃል ተመሣሣይ ትርጉም ያላቸወ ናቸው፡፡ እነዚህ ቃላት ያዕቆብ የተጠቀመባቸው ኃጢአት ምን ያኸል መጥፎ መሆኑን ለማሳየት መው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ማንኛውንም ዓይነት ኃጢአታዊ ባሕርይ ማድረግ አቁም፡፡ በትህትና "ያለትምክህት" ወይም "ያለ ጋጠወጥነት" በውስጥ የተተከለው ቃል ተቀበል “መትከል” የሚለው ቃል አንድን ነገር በሌላኛው ውስጥ አስገብቶ ማስቀመጥን ያመለክታል፡፡ ይህ የእግዚአብሔር ቃል በሰው ውስጥ መተከሉን ለማሳየት ጥቅም ላይ የዋለ ምሳሌ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር ለአንተ የተናገረውን መልዕክት ታዘዝ፡፡" ነፍስህን አድን በዚህ ሥፍራ ላይ “ነፍስ” የሚለው ቃል የሰውን ሁለንተና ታሳያለች፡፡ በተጨማሪም ሰውዩው የሚድነው ከምን እንደሆነ በግለጽ መቀመጥ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ከእግዚአብሔር ፍርድ ያድንሃል፡፡"
ቃሉን ታዘዝ “የእግዚአብሔርን ቃል ታዘዝ” ወይም "እግዚአብሔር ለአንተ የላከውን ቃል ታዘዝ" የገዛ ራስህን አታታል "ራስህን አታታል" ወይም "ራስህን አታታል" ቃሉን የሚሰማ ነገር ግን የማያደርገው ማንኛውም ሰው ቢኖር እርሱ ተፈጥሮአዊ ፊቱን በመስታወት እንደሚመለከት ሰው ነው፡፡ Jያዕቆብ የእግዚአብሔርን ቃል ሰምቶ የማይታዘዝን ሰው ተፈጥሮአዊ ፊቱን በመስታወት አይቶ ምን እንደሚመሰል ከዘነጋ ሰው ጋር ያነጻጽረዋል፡፡ ተፈጥሮአዊ ፊቱን ተመልክቶ . . . ወዲያው የዘነጋ ፊቱን በመስታወት ተመልክቶ ወዲያ የተመለከተውን የሚረሳ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል ሰምቶ የሰማውን ከሚረሳ ሰው ጋር ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ፍጹም ሕግ፣ የነጻነት ሕግ "ነጻነት የመከሰጥ ፍጹም ሕግ" የሰሙትን እንደሚረሱት ሰሚዎች ብቻ አትሁኑ "ሰምቶ ከዚያ እንደሚዘነጉት አትሁኑ" የሚያደርገው ይህ ሰው የተባረከ ነው አማራጭ ትርጉም: "ሕጉን በታዘዘ ቁጥር እግዚአብሔር ይህንን ሰው ይባርከዋል"
ራሱን ሃይማኖተኛ አድርጎ የሚቆጥረው ሰው "በትክክል እግዚብሔር እንደሚያመልክ የሚያስብ ሰው" አንደበቱ አማራጭ ትርጉም: "እርሱ የሚናገረው ነገር" ያታልላል "ማታለል" ወይም "መሸወድ" ወይም "ማሳሳት" የእረሱ ልብ በዚህ ሥፍራ ላይ “ልብ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የሰውን ሁለንተና ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "እርሱ ራሱ፡፡" ሃይማኖቱ ከንቱ ነው "አምልኮው ምንም ጥቅም የለውም" በአምላካችን እና በአባታችን ፊት ንጹሕ እና ነውር ያሌለበት አምልኮ ይህ ነው አማራጭ ትርጉም፡ "ይህ እግዚአብሔር የሚቀበለው የሃይማኖት አይነት ነው" ንጹሕ እና ነውር የሌለው በዚህ ሥፍራ ላይ ያዕቆብ እውነተኛ ሃይማኖት ምን እንደሚመሰል አጽኖት ሰጥቶ ለመግለጽ ተመሳሳይ ሀሳብ ያላቸው ነገር ግን አንዱ በአውንታዊ ሌላኛው በአሉታዊ መልኩ የቀረቡ ቃላትን ተጠቅሟል፡፡አማራጭ ትርጉም: "ፍጹም ንጹሕ፡፡" አባት የሌላቸው "አባት የሌላቸው ሰዎች" ወይም "ወላጆቻቸው የሞቱባቸው" ባልቴቶችን በመከራቸው ባላቸው በመሞቱ ምክንያት መከራ የደሰባቸው ሰዎች በዓለምም ከሚገኝ እድፍ ሰውነቱን መጠበቅ በዓለም ያለው ክፋት ኃጢአት እንድናደርግ እንዳያደርገን አለመፍቀድ
1 ወንድሞች ሆይ፤ ለአንዳንዶች አድልዎ እያደረጋችሁ የክብር ጌታ የጌታችን አየሱስ ክርስቶስን እምነት እንከተላለን አትበሉ። 2 የወርቅ ቀለበት ያደረገና የሚያማምሩ ልብሶች የለበሰ ወደ ስብሰባችሁ ሲገባና እንዲሁም አዳፋ ልብሶች የለበሰ ድኻ ቢገባ 3 ትኵረታችሁ የሚያማምሩ ልብሶች የለበሰው ሰው ላይ ይሆንና፣ “እዚህ ደኅና ቦታ ላይ ተቀመጥ” ትሉታላችሁ፤ ድኻውን ግን፣ “እዚያ ቁም” ወይም “ከእግሬ በታች ተቀመጥ” ትሉታላችሁ 4 ታዲያ፣ በመካከላችሁ አድልዎ ማድረጋችሁ አይደለምን፤ ደግሞስ በክፉ ዐሳብ የተያዛችሁ ፈራጆች መሆናችሁ አይደለምን? 5 የተወደዳችሁ ወንድሞች ስሙ፤ በእምነት ባለ ጸጋ እንዲሆኑና፣ እርሱን ለሚወዱ ቃል የገባላቸውን መንግሥት እንዲወርሱ እግዚአብሔር የዚህ ዓለም ድኾችን አልመረጠምን? 6 እናንተ ግን ድኾችን አዋረዳችሁ! የሚጨቁኗችሁ ባለ ጸጎች አይደሉምን? ወደ ፍርድ ቤት የሚጎትቱዋችሁስ እነርሱ አይደሉምን? 7 የተጠራችሁበትን መልካም ስም የሚሳደቡ ባለ ጸጎቹ አይደሉምን? 8 ይሁን እንጂ፣ “ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ” ተብሎ እንደ ተጻፈው የከበረውን ሕግ ብትፈጽሙ መልካም ታደርጋላችሁ፤ 9 ለአንዳንዶች አድልዎ ብታደርጉ ግን፣ ኃጢአት ትሠራላችሁ፤ እንደ ሕግ ተላላፊዎችም ትቆጠራላችሁ። 10 ምክንያቱም ሕጉን የሚፈጽም፣ በአንዱ ግን የሚሰናከል፣ ሕጉን ሁሉ እንደ ተላለፈ ይቆጠራል! 11 “አታመንዝር” ያለው እግዚአብሔር፣ “አትግደልም” ብሎአልና። ባታመነዝር ሆኖም ግድያ ብትፈጽም፣ የእግዚአብሔርን ሕግ ተላልፈሃል። 12 ስለዚህ ነጻ በሚያወጣው ሕግ እንደሚፈረድባቸው ሰዎች ተናገሩ፤ ደግሞም ታዘዙ። 13 ምክንያቱም ምሕረት በማያደርጉ፣ ምሕረት የሌለበት ፍርድ ይመጣባቸዋል። ምሕረት ፍርድን ያሸንፋል! 14 ወንድሞቼ ሆይ፣ አንድ ሰው እምነት እንዳለው ቢናገር፣ ሥራ ግን ባይኖረው ምን ይጠቅማል? ያ እምነት ሊያድነው ይችላልን? 15 አንድ ወንድም ወይም እኅት ልብስና የዕለት ምግብ ባይኖራቸው 16 ከእናንተ አንዱ፣ “በሰላም ሂዱ፤ አይብረዳችሁ፤ በደንብ ጥገቡ” ቢላቸው፤ ለአካል የሚያስፈልጉ ነገሮችን ግን ባትሰጧቸው፣ ምን ይጠቅማል? 17 ሥራ የሌለው እምነትም እንዲሁ በራሱ የሞተ ነው። 18 ምናልባትም አንዱ፣ “አንተ እምነት አለህ እኔ ደግሞ ሥራ አለኝ” ሥራ የሌለው እምነትህን አሳየኝ፤ እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ ይል ይሆናል። 19 አንድ እግዚአብሔር መኖሩን ታምናለህ፤ ትክክል ነህ። አጋንንትም ይህን ያምናሉ፤ በፍርሃትም ይንቀጠቀጣሉ። 20 አንተ ሞኝ፣ እምነት ያለ ሥራ ከንቱ መሆኑን ማወቅ ትፈልጋለህ? 21 አባታችን አብርሃም፣ ልጁ ይስሐቅን መሠዊያው ላይ ባቀረበ ጊዜ በሥራ ጸድቆ አልነበረምን? 22 እምነት በሥራው ታየ፤ በዚያው ሥራ እምነት ዓላማውን ፈጸመ። 23 “አብርሃም እግዚአብሔርን አመነ፤ ጽድቅም ሆኖ ተቆጠረለት” የሚለው የመጽሐፍ ቃል ተፈጸመ። ስለዚህም አብርሃም የእግዚአብሔር ወዳጅ ተባለ። 24 ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን፣ በሥራ እንደሚጸድቅ ታያለህ። 25 በተመሳሳይ ሁኔታ ጋለሞታዪቱ ረዓብ መልእክተኞቹን ተቀብላ በሌላ መንገድ በሰደደቻቸው ጊዜ በሥራ አልጸደቅችምን? 26 ከመንፈስ የተለዬ አካል ሙት እንደ ሆነ ሁሉ፣ ከሥራ የተለዬ እምነትም የሞተ ነው።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ያዕቆብ ለተበተኑት አይሁዳዊያን አማኞች እንዴት እርስ በእርስ በመዋደድ መኖር እንደሚችሉ እንዲሁ አንድን ሰው ከሌላኛው አስበልጠው መውደድ እንዳሌለባቸው መናገሩን ቀጥሏል፡፡ ወንድሞቼ ያዕቆብ የመልዕክቱ ተደራሲያን አይሁዳዊያን አማኞች እንደሆነ ያስበል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "አማኝ ወንድሞች" ወይም "በክርስቶስ ወንድሞቼ እና እህቶቼ የሆናችሁ፡፡" ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል ያዕቆብን እና ሌሎች አማኞችን ያመለክታል፡፡ ለተወሰኑ ሰዎች አድሎ ማድረግ "ልዩ እንክብካቤ ማድረግ" ወይም "ለእርሱ መልካም መሆን" አንድ ሰው ይህንን ካደረገ ያዕቆብ በአንዳንድ ሁኔታዎች ውስጥ አማኞች ከድሆች ይልቅ ለሀብታሞች ይበልጥ ክብር የሚስተዋልባቸውን ሁኔታዎች በማንሳት ማብራራት ይጀምራል፡፡ የቀርቅ ቀለበት ያደረጉ እና መልካም ልብስ የለበሱ "እንደ ሀሰብታም ሰው የለበሱ" በዚህ ጥሩ ሥፍራ ተቀመጠ "በዚህ የክብር ሥፍራ ተቀመጥ" እዚያ ቁም "ክብር ወደሌለው መቀመጫ ሂድ" በእግሬ ፊት ተቀመጥ "ወደ ዝቅተኛ ቦታ ሂድ" በራሳችሁ መካከል ፍርድን እየሰጣችሁ አይደለምን እንዲሁም የሚትፈርዱት ደግሞ በክፉ ሀሳባችሁ አይደለምን ያዕቆብ ተደራሲያኑን ለማስተማር እና ለመገሰጽ ይህንን የመሳሳሉ ጥያቄዊ መንገድን ይጠቀማል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "በራሳችሁ መካከል ፍርድን ትሰጣላች እንዲሁም በክፉ ሀሳባችም ፈራጆች ትሆናለችሁ፡፡"
የተወደድክ ወንድሜ ሆይ አድምጠኝ ያዕቆብ አንባቢዎቹን ልክ እንደ ቤተሰብ ያበረታታቸዋል፡፡ “ውድ ወንድሞቼ ሆይ ትኩረት ሰጥታችሁ አድምጡኝ፡፡" እግዚአብሔር አይመርጥምን በዚህ ሥፍራ ያዕቆብ አንባቢያኑን ለማበረታታት ጥያቄን ይጠቀማል፡፡ አማራጭ ትርጉምለ “እግዚአብሔር ይመርጣል፡፡" በእምነት ሀብታም ሁን "ብዙ እምነት ይኑርህ፡፡" የምታመነው ነገር ምን እንደሆነ በግለጽ መታወቅ አለበት፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በክርስቶስ ጠንካራ እምነት ይኑርህ፡፡" የእግዚአብሔርን መንግስት ይወርሳሉ "ወደ መንግስተ ሰማያት ይገባሉ" እናንተ ግን . . . ይኑራችሁ በዚህ ሥፍራ ላይ ያዕቆብ ለአጠቃላይ ተደራሲያኑ እየተናገረ ነው፡፡ ድሆችን አያከብሩም "ለድሆች ዋጋ አይሰጡም" ወይም "ለድሆች ጥሩ እንክብካቤ አያደርጉም" ሃብታም ስላልሆኑ አይደለምን በዚህ ሥፍራ ላይ ያዕቆብ አንባቢያኑን ለመገሰጽ ጥያቄዎችን ይጠቀማል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ሃብታሞች ናቸው፡፡" ሀብታም "ሀብታም ሰዎች" (UDB) የሚቃወማችሁ "የሚጨቁናችሁ" ወይም "በመጥፎ ሁኔታ የሚይዟችሁ" እነርሱ አይደሉምን በዚህ ሥፍራ ላይ ያዕቆብ አንባቢያኑን ለመገሰጽ ጥያቄዎችን ይጠቀማል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "እነርሱ ናቸው፡፡" ወደ ፍርድ ቤት የሚወስዷችሁ "በዳኞች ፊት እናንተን ለመክሰስ በኃይል የሚጎትቷችሁ" ሀብታሞች አይደሉምን በዚህ ሥፍራ ላይ ያዕቆብ አንባቢያኑን ለመገሰጽ ጥያቄዎችን ይጠቀማል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ሀብታሞች" ወይም "ሀብታም ሰዎች፡፡" መልካም ስም "የክርስቶስ ስም"
ይህንን ካሟላችሁ በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አይሁዳዊን አማኞችን ነው፡፡ የንጉሡን ሕግን መፈጸም እግዚአብሔር በመጀመሪያ በብሉይ ኪዳናት መጽሐፍት ውስጥ የተጻፈውን የሙሴን ሕግጋት ሰጠ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "የእግዚአብሔርን ሕግ መታዘዝ" ወይም "የታላቁ ንጉሣችንን ሕግጋ መታዘዝ፡፡" ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ (አነጻጽር: ዘለዋዊያን LEV 19:18) ጎረቤቶቻችሁ "ሁሉም ሰዎች" ወይም "ሁሉም ሰው" መልካም አድርገዋል "አንተ መልካም አድረገሃል" ወይም "አንተ ትክክለኛ የሆነ ነገር አድርገሃል" አድሎ የሚታደርጉ ከሆነ "ልዩ የሆነ እንክብካቤን ማድረግ" ወይም "ክብርን ለመስጠት" ኃጢአትን ማድረግ ይህ ሕግን መተላለፍ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ኃጢአትን ማድረግ" ኃጢአት፣ በሕግ የሕግን መስበሩ የተረጋገጠበት በዚህ ሥፍራ ላይ ሕግ የሰው ዳኛ ባሕርይ ተላብሷል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "የእግዚአብሔር ሕግ በመስበር ኃጠአት እና በደለኛ መሆን፡፡"
ለሚታዘዝ ሰው ሁሉ "ለምታዘዝ ሰው ሁሉ" ይሁን እንጂ ይሠናከሉበታል . . . በሕግ ሁሉ! መሰናክል አንድ ሰው ለመራመድ ሲል ተደናቅፎ መውደቅን ያሳያል፡፡ ከሕግ የተወሰነ ክፍል አለመታዘዝ ሁሉንም ሕግ ካለመታዘዝ ጋር አንድ ነው፡፡ አታድረግ “ማድረግ” ማለት የሆነ ነገርን መፈጸም ማለት ነው፡፡
ባታመነዝርም፥ ነገር ግን ብትገድል፥ ሕግን ተላላፊ ሆነሃል። ምንም እንኳ ያዕቆብ ይህንን የጻፈው ለብዙ አይሁዊያን አማኞች ቢሆንም የተጠቀመባቸው ቃላት ግን ነጠለቀ ቁጥር ያላቸው በመሆናቸው ለእያንዳንዱ ግለሰብ የጻፈ እንዲመስል አድርጎ ነው የጻፈው፡፡ "እያንዳንዳችሁ"
ስለዚህ ተናገር እንዲሁም ታዘዝ ያዕቆብ ሰዎች ይህንን ያደርጉ ዘንድ ያዛል፡፡ "ስለዚህ መናገር እና መታዘዝ ይኖርባችኋል፡፡" በነጻነት ሕግ ፍርድን ይቀበሉ ዘንድ እንዳላቸው ሰዎች "የጻነት ሕግ በቅርብ እንደሚፈርድባቸው የሚያውቁ ሰዎች" በሕግ አማካኝነት በዚህ ሥፍራ ላይ ሕግ የሰው ዳኛ ባሕርያት ተሰጥቶት እናገኛለን፡፡ የነጻነት ሕግ "እውነተኛ ነጻነትን የሚሰጠው ሕግ" ምሕረት በእርሱ ላይ ይነግሣል "ምሕርት ከ . . . ይበልጣል" ወይም "ምሕረት ያሸንፋል"
አያያዥ ኣረፍተ ነገር: ያዕቆብ በየሥፍራው የተበተኑ አማኞች ልክ አብረሃም እምነቱን በሥራ እንዳሳየ ሁሉ እነርሱም እምነታቸውን በሰዎች ፊት ያሳዩ ዘንድ ያበረታታቸዋል፡፡. ወንድሞቼ ሆይ አንድ ሰው እምነት አለኝ ቢል ነገር ግን እምነቱን ሥራ ካሌለው ምን ይጠቅማል? ያዕቆብ ተደራሲያኑን ለማስተማር ጥያቄ ይጠቀማል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "አንድ ሰው እምነት አለኝ እያለ ነገር ግን እምነቱን በሥራ የማያሳይ ከሆነ ምንም ፋይዳ የለውም፡፡ አንድ ሰው እንዲህ ቢል ያዕቆብ የአንድ ሰው ንግግርን በመጥቀስ ይጽፋል፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ “እርሱ” የሚለው ቃል የተናገረውን ሰው ይወክላል፡፡ ( ያ እምነት ልያድነው ይችላልን? ያዕቆብ ተደራሲያኑን ለማስተማር በዚህ ሥፍራ ላይ ጥያቄን ተጠቅሟል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እንዲህ አይነቱ እምነት አያድነውም፡፡" አያድነውም "ከእግዚአብሔር ፍርድ ልያድነው አይችልም" ወንድምህ ከ . . . ይህ ምን ጥቅም አለው? ያዕቆብ ተደራሲያኑን ለማስተማር በዚህ ሥፍራ ላይ ጥያቄን ተጠቅሟል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ወንድምህ ከ . . . ፈጽሞ ጥሩ ነገር አይደለም፡፡" ወንድም ወይም እህት "በክርስቶስ ወንድም ወይም እህት" ከእናንተ መካከል አንዱ እንዲህ ቢል "አንተ እንዲህ አልክ" ሙት ነው "ጥቅም የለውም"
ይሁን እንጂ አንድ ሰው እንዲህ ይላል ያዕቆብ በ2፡ 14-17 ላይ አንድ የእርሱን ትምህርት የሚቃወም ሰውን በምናቡ እየሳለ ምን ልል እንደሚችል ይናገራል፡፡ ያዕቆብ ይህንን ሰው "ሞኝ ሰው" በማለት በቁጥር 20 ይጠራዋል፡፡ የዚህ ምናባዊ ገለጻ ዋና ዓላማ በተደራሲያኑ ዘንድ ያለው ስለ እምነት እና ሥራ ያለውን አመለካከት ለማስተካከል ነው፡፡ እኔ ሥራ አለኝ እንዲሁም እኔ ሥራ አለኝ ያዕቀብ በእርሱ አስተምህሮ ዙሪያ አንዳንድ ሰዎች ሊያነሱ የሚችሉትን ተቃውሞ ይገልጻል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "አንድ ሰው እምነት ካለው ይህ ተቀባይነት አለው እንዲሁም አንድ ሰው መልካም ሥራ ካለውም እንደዚያው፡፡" እምነትህን አሳየኝ በዚህ ሥፍራ ላይ “እኔ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ያዕቆብን ነው፡፡ ዳብሎስም . . . ይንቀጠቀጣል "በፍርሃት ይንቀጠቀጣል" አንተ ሞኝ ሰው ሆይ እምነት ያለ ሥራ ምንም ዋጋ እንዳሌለው ማወቅ ትፈልጋለህን? ይህ ጥያቄ ያዕቆብን ለማድመጥ ፈቃደኛ ያልሆነ ሰውን ለመገሰጽ ጥቅም ላይ የዋለ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "አንተ ሞኝ! ያለ ሥራ የሆነ እምነት ጥቅም እንዳሌለው ባረጋግጥልህም ይህንን መስማት ግን አንተ ፈጽሞ አትፈልግም፡፡"
አጠቃላይ መረጃ: እነዚህ አይሁድ አማኞች በመሆናቸው ምክንያት የአይሁዳዊያን አባት የሆነውን እና እግዚአብሔር በቃሉ አማካኝነት ከብዙ ዘመናት በፊት የነገራወቸውን የአብረሃምን ታሪክ ያውቃሉ፡፡ አባታችን አብረሃም የጸደቀው . . . አይደለምን ይህ ጥያቄ ጥቅም ላይ የዋለው በያዕቆብ ትምህርት ላይ ሞኙ ሰው በ [JAS 2:18] እምነት እንደለ ታያለህ በዚህ ሥፍራ ላይ “ታያለህ” የሚለው ቃል ምሳሌያዊ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “መረዳት፡፡” በሥራ እምነቱ ዓላማውን ይፈጽማል "ሥራው እምነቱ ፍጹም ይሆናል" ቅዱሳት መጽሐፍት ተፈጸሙ አማራጭ ትርጉም: "ይህ በቅዱሳት መጸሕፍት የተገለጠው ነገር ተፈተመ፡፡" ጽድቅ ሆኖ ተቀጠረለት "እግዚአብሔር እምነቱን ጽድቅ አድርጎ ቆጠረለት" ይህ የታየው በሥራቸው ነው ያዕቆብ እንደገና “እናንተ” የሚለውን የብዙ ቁጥር አመልካች ቃል ተደራሲያንን ተጠቅሟል፡፡ ሰው በሥራ ይጸድቃል "ሰው በሥራ እና እምነት ይጸድቃል"
በተመሳሳይ መልኩ ይህ ተመሳሳይ ሀሳብን መጀመሪያ መንገድ ነው፡፡ (ተመልከት: [[rc://*/ta/workbench/discourse/home]]) ጋለሞታይቱ ረሃብ የጽደቀችው በእምነት አይደለምን ያዕቆብ ተደራሲያኑን ለማስተማር ጥያቄን ተጠቅሟል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ጋለሞታይቱን ረሃብን ያጸደቃት ሥራዋ ነው፡፡" ጋለሞታይቱ ረሃብ “ረሃብ” የተባለች ሴት ታሪክ በብሉይ ኪዳን ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ተደራሲያኑ ይህንን ታሪክ ማወቅ እንዳለባቸው ያስባል፡፡ መልእክተኞች ከሌላ ቦታ ዜናዎችን የሚያመጡ ሰዎች፡፡ በሌላ መንገድ ሸኘቻቸው "ከከተማው እንዲያመጡ ረዳቻቸው" መንፈስ የተለየው አካል የሞተ እንደሆነ ሁሉ ከሥራ የተለየ እምነትም የሞተ ነው፡፡ በእምነታቸውን ሥራ የማይሠራ ሰው ልክ መንፈስ ያሌለው አካልን ይመስላል፡፡ ሁለቱም ሞተዋል እንዲሁም ጥቅም የላቸውም፡፡
1 ወንድሞቼ፣ እኛ የባሰውን ፍርድ እንደምንቀበል በመገንዘብ፣ ከእናንተ ብዙዎች አስተማሪዎች አትሁኑ። 2 ሁላችንም በብዙ መንገድ እንሰናከላለን። በንግግሩ የማይሰናከል እርሱ ሰውነቱን ሁሉ መቆጣጠር የሚችል ፍጹም ሰው ነው። 3 ፈረሶች አፍ ውስጥ ልጓም ብናደርግ ይታዘዙልናል፤ መላ አካላቸውንም መቆጣጠር እንችላለን። 4 ምንም እንኳ መርከቦች ግዙፍና በኃይለኛ ነፋስ የሚነዱ ቢሆኑም፣ የመርከቡ ነጂ በትንሽ መሪ ወደሚፈልገው አቅጣጫ እንደሚመራቸው አስተውሉ። 5 እንዲሁም አንደበት ትንሽ የሰውነት ክፍል ሆኖ፣ በታላላቅ ነገሮች ይኵራራል። ጫካ የቱንም ያህል ሰፊ ቢሆን፣ በትንሽ እሳት ፍንጣሪ እንደሚቃጠል ልብ አድርጉ! 6 አንደበትም እንዲሁ እሳት ነው፤ ሰውነትን ሁሉ የሚያረክስና የሕይወትንም መንገድ የሚያቃጥል፣ እርሱ ራሱም በገሃነም እሳት የሚቃጠል ሰውነታችን ብልቶች መካከል ያለ ኃጢአተኛ ዓለም ነው። 7 ማንኛውም እንስሳ፣ ወፎች፣ በምድር የሚሳቡና ባሕር ውስጥ ያሉ ፍጥረቶች በሰው ተገርተዋል፤ 8 ነገር ግን ከሰው መካከል ማንም አንደበትን መግራት አልቻለም፤ የሚገድል መርዝ የሞላበት ዕረፍት የለሽ ክፉ ነው። 9 በአንደበት ጌታና አባታችንን እንባርካለን፤ በዚያው አንደበት በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠሩትን ሰዎች እንረግማለን። 10 ከአንድ አፍ በረከትና መርገም ይወጣል። ወንድሞቼ፣ እንዲህ መሆን የለበትም። 11 ከአንድ ምንጭ ጣፋጭና መራራ ውሃ ይወጣልን? 12 ወንድሞቼ፣ የበለስ ዛፍ ወይራን ወይስ ወይን በለስን ያበቅላልን? እንዲሁም ከጨው ውሃ ንጹሕ ውሃ ሊገኝ አይችልም። 13 ከእናንተ መካከል ጥበበኛና አስተዋይ ማን ነው? ያ ሰው ከጥበብ በሚገኝ ትሕትና በሥራው መልካም ሕይወትን ያሳይ። 14 በልባችሁ መራራ ቅናትና ራስ ወዳድ ምኞት ካለ ግን አትኵራሩ፤ በእውነትም ላይ አትዋሹ። 15 ይህ ከላይ የሚመጣ ጥበብ አይደለም፤ ይልቁንም ምድራዊ፣ መንፈሳዊ ያልሆንና አጋንንታዊም ነው። 16 ምክንያቱም ቅናትና ራስ ወዳድ ምኞት ባለበት ሁከትና ክፉ ሥራ ይኖራል። 17 ከላይ የሚመጣው ጥበብ ግን በመጀመሪያ ንጹሕ ነው፤ ከዚያም ሰላም ወዳድ፣ ጨዋ፣ ደግ፣ ምሕረትና መልካም ፍሬ የሞላበት፣ ለሰዎች አድልዎ የማያደርግ ቅን ነው። 18 ሰላምን ለሚያደርጉ የጽድቅ ፍሬ በሰላም ይዘራል።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ያዕቅብ እነዚህን አማኞችን ከሰዎች አፍ የሚወጡትን ቃላት መቆጣጠር የሚችለው ከእግዚአብሔር ዘንድ በሚመጣ ጥበብ ብቻ ነው፡፡ ብዙዎቻችሁ እንዲህ አይደላችሁም በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመልከትው የያዕቆብን ተደራሲያን ነው፡፡ ወንድሞቼ "አማኞች" ይህንን እወቁ "ስለዚህ ምክንያት" የባሰውን ፍርድ እንድንቀበል ታውቃላችሁና። አማራጭ ትርጉም: "ኃጢአትን በማደረጋችን ምንም ምክንያት የለንም ምክንያቱም ከሌሎች ሰዎች ይልቅ ቃሉን እናውቃለን ስለዚህም እግዚአብሔር ከሌሎች ሰዎች በላይ እኛን ይቀጣናል፡፡" እንቀበላለን ያዕቆብ ራሱን ከእርሱ ጋር ቅዱሳት መጽሐፍትን ከሚያስተምሩት ሰዎች ጋር በማድረግ ይናገራል፡፡ ምንም እንኳ ይህንን ደብዳቤ የሚያነቡት ሰዎች አንዳንዶቹ የቅዱሳት መጽሐፍት አስተማሪዎች ይሆናሉ ብዙዎቹ ግን አይሆኑም፡፡ በሁሉን እንሰናከላለን ያዕቆብ ሁሉንም ተደራሲያኑን ወደ ማካተቱ ተመልሷል፡፡ በብዙ መንገድ እንሰናከላለን ይህ የአንድ ሰውን ግብረገባዊ ውድቀት አንድ ሰው በጎዞ ላይ ሳለ ከመውደቁ ጋር ያነጻጽራል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "መወደቅ" ወይም "ኃጢአት፡፡" በቃሉ አይሰናከሉም "በተናገረው ቃል ኃጢአትን ያደርጋሉ" እርሱ ፍጹም ሰው ነው "እርሱ መንፈሳዊ ብስለት ያለው ሰው ነው" አጠቃላይ አካሉን የሚቆጣጠር በዚህ ሥፍራ ላይ ያዕቆብ እያመለከተ ያለው ልቡን፣ ስሜቱን እና ተግባሩን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ባሕርውን የሚቆጣጠር ሰው" ወይም "ተግባሩን የሚቆጣጠር ሰው፡፡"
እነሆ፥ ፈረሶች ይታዘዙልን ዘንድ ልጓም በአፋቸው ውስጥ እናገባለን ያዕቆብ የሰውን ምላስ ከልጓም ጋር ያያይዛል፡፡ ልጓም ፈረስ በዬት አቅጣጫ መሄድ እንዳለበት ለመቆጣጠር በአፍ ውስጥ የሚገባ ትንሽ ብረት ነው፡፡ ይህ እንዴት ትንንሽ ነገሮች እንዴት በትልልቅ ነገሮች ላይ ኃይል እንዳለው ያሳያል፡፡ አሁን ከሆነ "ከሆነ" ወይም "ሲሆን" የፈረስ ሉጋም በፈረስ አፍ ውስጥ እንደሚገባ ሁሉ “ፈረስ” ዕቃ ወይም ሰዎችን ለመሸከም የሚውል ትልቅ እንስሳ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "የፈረስ ሉጋምን በፈረስ አፍ ውስጥ የሚናደርግ ከሆነ፡፡" ያኛውን መረከብም ደግሞ ተመልከቱ . . . በትንሽ መሪ የሚቆም ከሆነ በቀመጠል ያዕቆብ የሰውን ምላስ ከመርከብ መሪ ጋር ያነጻጽራል፡፡ “መርከብ” በውሃ ላይ የሚንሳፈፍ ትልቅ ነገር ነው፡፡ “መሪ” በመርከቡ መጨረሻ አከባቢ የሚገኝ ከእንጨት ወይም ከብረት የሚሠራ የመርከብን አቅጣጫ ለመቆጣጠር የሚረዳ ነው፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይም ያዕቆብ ከፈረስ ሉጓም ጋር ተመሳሳይ የሆነ ነጥብን ያስተላልፋል፡፡ ትንሽ ነገር ከትልቅ ነገር በላይ ኃይል ልኖረው ይገባል፡፡ በጣም ትልቅ ናቸው በዚህ ሥፍራ ላይ “እነርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው መርከቦችን ነው፡፡ በጠንካራ ንፋስ ይገፋል አማራጭ ትርጉም: "ጠንካራ ንፋስ ይገፋዋል" በትንሽ መሪ አማካኝነት ሹፌሩ ወደ ወደደው አቅጣጫ ይመራዋል፡፡ "ይህች ትንሽ ዕቃ መርከቡ የሚሄድበትን አቅታጫ ይወስናል፡፡"
በተመሳሳይ መልኩም ይህ ቃል የፈረስ ልጓምን ከመርከብ መሪ ጋር ማነጻጸሩን ያሳያል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "በተመሳሳይ መልኩም፡፡" በታላላቅ ነገር ይመካል "አንድ ሰው በጣም ክፉ የሆኑ ነገሮችን ለመናገር ልጠቅምበት ይችላል" ይህ ምን ያኸል ትልቅ ነገር ነው "ምን ያኸል ትልቅ እንደሆነ አስቡ" ትልቅ ጫካ በትንሽ እሳት እንደሚቃጠል ሁሉ! አማራጭ ትርጉም: "ትንሽ የእሳት ነበልባል ብዙ ዛፎችን ማቃጠል ይችላል!" ምላስም ልክ እንደ እሳት ነው ልክ እሳት የሚቃጥላቸውን ነገሮች ሁሉ እንደሚስወግድ ሁሉ የሰውም አንደበት ሰዎችን በጣም ልጎዳ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ምላስም ልክ እንደ እሳት ነው፡፡" አንደበት በብልቶቻችን መካከል ዓመፀኛ ዓለም ሆኖአል፤ አማራጭ ትርጉም: "ይህ የአካላችን ትንሸሹ ክፍል ነው ይሁን እንጂ ብዙ ዓይነት ኃጢአቶችን ለመፈጸም ያስችላል፡፡" ሥጋን ሁሉ ያሳድፋልና፥ ይህ እንደ አዲስ ዓረፍተ ነገር ሊተረጎም ይችላል፡፡ "ይህ ፈጽም እግዚአብሔር የማናስደስት ያደርገናል፡፡" ወይም "ይህ በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት እንዳናገኝ ያደርገናል፡፡" የፍጥረትንም የሕይወት ሩጫ ያቃጥላል፥ በዚህ ሥፍራ ፤ይ “የሕይወት ሩጫ” የሚለው ሀረግ የሚያመለክተው የአንድ ሰውን አጠቃላይ ሕይወት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "የሰውን ሁለንተናዊ ሕይወት ሊያበላሽ ይችላል፡፡" እንዲሁም በገሃነም እሳትም ይቃጠላል። በዚህ ሥፍራ ላይ “እርሱም” የሚለው ቃል ምላስን የሚያመለክት ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በዚህ ስፍራ ላይ “ገሃነም” የሚለው ቃል የክፋትን ወይም ዳቢሎስን ያመለክታል፡፡ ይህ በቀጥታ እንዲህ ልተረጎም ይችላል፡፡ "ምክንያቱም ዳብሎስ ይህንን ለክፋቱ ይጠቀመዋል፡፡"
የአራዊትና የወፎች የተንቀሳቃሾችና በባሕር ያለ የፍጥረት ወገን ሁሉ በሰው ይገራል፥ ደግሞ ተገርቶአል፤ በዚህ ሥፍራ ላይ “ሁሉንም ዓይነት” የሚለው ሀረግ ያለው ትርጉም “ብዙ ዓይነት” ነው፡፤ ይህ በቀጥታ እንዲህ ልተረጎም ይችላል፡ "ሰዎች ብዙ ዓይነት የዱር እንስሳትን፣ ወፎችም፣ ተሳቢ እንስሳትን እና የባሕር ውስጥ ፍጥረታትን መቆጣጠር ችሏል፡፡" ተሳቢ እንስሳት እነዚህ በምድር ላይ እየተሳቡ የሚሄዱ የእንስሳት ዓይነቶች ናቸው፡፡ የባሕር ውስጥ እንስሳት እነዚህ በውሃ ውስጥ የሚኖሩ እንስሳትን ናቸው፡፡ ነገር ግን አንደበትን ሊገራ ማንም ሰው አይችልም በዚህ ሥፍራ ላይ “አንደበት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አንድ ሰው የሚናገረውን ነገር ነው፡፡ የዚህ ሙሉ ትርጉሙ እንዲህ ልገለጽ ይችላል፡ "ከእግዚአብሔር እገዛ ውጭ ማንም ሰው ምላሱን ልቆጣጠር አይችልም፡፡" የሚገድል መርዝ የሞላበት ወላዋይ ክፋት ነው። ይህ ሰዎችን በተሰበረ ቃል እንዴት ሌላ ሰውን እንደሚጎዱ የሚብራራ ነው፡፡ ይህ “ክፉ የሆነ ፍጥረት እንደማያንቀላፋ ነገር ግን ለማጥቃት ሁል ጊዜ ዝግጁ እንደሆነ ሁሉ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡"
በምላስ እኛ "ቃላትን ለመናገር ምላሳችንን እንጠቀማለን" በእርሱ እኛ "ቃላትን ለመናገር እንጠቀመዋለን" ሰዎችን እንረግምበታለን በሌሎች ሰዎች ላይ ክፋትን እንዲያደርግ እግዚአብሔርን እንጠይቃለን UDB) በእግዚአብሔር መልክ የተፈጠሩትን አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር በገዛ መልኩ የፈጠራቸውን" ወንድሞቼ "ክርስትያኖች" እነዚህ ነገሮች ፈጽመው ሊሆኑ አይገባም "ይህ ትክክል ያልሆነ ነገር ነው"
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ያዕቆብ ከአማኞች አንደበት የሚወጣው ቃል ባርኮት እና ርግማን መሆን እንዳሌለበት ከገለጸ በኋላ ይህንን ሀሳቡን ለመግለጽ ከተፈጠሮ የተለያዩ ምሳሌዎችን ያነሳል፡፡ ምንጭስ ከአንድ አፍ የሚጣፍጥንና የሚመርን ውኃ ያመነጫልን? ጳውሎስ የተፈጥሮን አመክኒዮዋዊ መንገድ ለአንባቢያኑ ለማስረዳት ይህንን ጥያቄ ተጠቅሟል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ምንጭ የሚጣፍጥ እና የሚመርን ውሃ አያመነጭም፡፡" በለስ ወይራን ወይስ ወይን በለስን ልታፈራ ትችላለችን? ያዕቆብ የተፈጥሮን አመክኒዮአዊ መንገድ ለአንባቢያኑ ለማስረዳት ሌላ ሥዕላዊ ቃላትን ይጠቀማል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "የበለስ ዘፍ የወይራ ፍሬን ልያፈራ አይችልም ወይም የወይራ ዘፍ የበለስ ፍሬን ሊያፈራ አይችልም፡፡"
ከእናንተ ጥበበኛና አስተዋይ ማን ነው? በመልካም አንዋዋሩ ስራውን በጥበብ የዋህነት ያሳይ። ያዕቆብ ለተደራሲያኑ በጥያቄ መልክ ትክክለኛውን ባሕርይ ይገልጻል፡፡ “ጠበብ” እማ “አስተዋይ” የሚለው ቃል በዚህ ክፍል ውስጥ ያለው ትርጉም ተመሳሳይ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ጠብብ የሆነ ሰው እንዲህ ልሆን ይገባዋል፡፡" መልካም ሕይወትን ያሳያል "መልካም ባሕርን ያሳያል" ወይም "ያሳይ" በመልካም አንዋዋሩ ስራውን በጥበብ የዋህነት ያሳይ። "ከእውነተና ጥበብ ከሞገኝ መልካ ሥራው እና ትህትናው ጋር" ነገር ግን መራራ ቅንዓትና አድመኛነት በልባችሁ ቢኖርባችሁ፥ “ልብ” የሚለው ቃል ስሜትን ወይም ሀሳብን ያሳያል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ከሌሎች ሰዎች ጋር ተካፈሉ እና ሁል ጊዜም ራሳችሁን መጀመሪያ አድርጉ፡፡" አትመኩ በእውነትም ላይ አትዋሹ። "ስለዚህ ነገር አትዋሹ እንዲሁም ነገሮችን እንደ ጠቢብ ሰው አከናውኑ"
ይህ አይደለም በዚህ ሥፍራ ላይ "ይህ" የሚለው ቃል ከዚህ በፊት ባሉት ቁጥሮች ውስጥ የተብራራውን ጥበብ የጎደለውን ቅንአት እና ራስ ወደድ የሆነ መሻትን ያመለክታል፡፡ ከላይ የወረደ "ከእግዚአብሔር ዘንድ የመጣ" ወይም "ከሰማይ የመጣ" ምድራዊ የሆነ በዚህ ስፍራ ላይ “ ምድራዊ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔርን የማያስከብር የሰዎችን እሴት እና ባሕርን ነው፡፡" ኢ-መንፈሳዊ "ከመንፈስ ቅዱስ ያልሆነ" ወይን "መንፈሳዊ ያልሆነ" የአጋንንትም ነው፤ "ይሁን እንጂ ይህ ከዳቢሎስ ዘንድ ነው" ቅንዓትና አድመኛነት ባሉበት ስፍራ "ስለራሳቸው ብቻ የሚያስቡ እንጂ ስለሌሎች ሰዎች የማያስቡ ሰዎች ባሉበት ሥፍራ ሁሉ" ሁከት ይኖራል "በዚያ ሥርዓት አልበኝነት ይኖራል" ወይም "ወይም ቀውስ ይኖራል" ማንኛውም ክፉ ተግባር ሁሉ "ማንኛውም በኃጢአት የተሞላ ሥራ ሁሉ" ወይም "ማንኛውንም ዓይነት ክፉ ተግባራት" የመጀመሪያው ቅዱስ "የመጀመሪያው ቅዱስ" ከዚያም ሰላም- ፍቅር አፍቃሪ - "ከዚያም ሰላማዊ"
እንግዳ ተቀባይ ገር - "ትሁት" ወይም "አሳቢ"
እና በጎ ፍሬ የሞላበት ይህ መልካም ፍሬ የሞላበት ከመልካም ሥራ ጋር ተነጻጽሯል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “መልካም ሥራዎች” ግብዝነት ያሌለበት "ታማኝ" ወይም "እውነተኛ"
የጽድቅም ፍሬ ሰላምን ለሚያደርጉት ሰዎች በሰላም ይዘራል።
ይህ በሕይወታችን ውስጥ ያለውን ሰላምን እና ድቅድን ከመዝራት እና መከረ ከመሰብሰብ ጋር ያነጻጽራል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “በሰላም የሚኖሩት ሰዎች እግዚአብሔር ትክክል ነው ብሎ የተናገረውን ነገር ያደርጋሉ፡፡"
1 በእናንተ መከከል ያለው ፀብና ጭቅጭቅ ከየት የመጣ ነው? በውስጣችሁ ውጊያ ከገጠሙት ክፉ ምኞቶቻችሁ የመጣ አይደለምን? 2 የሌላችሁን ትመኛላችሁ። ትገድላላችሁ፤ ማግኘት ያልቻላችሁትን በብርቱ ታሳድዳላችሁ። ትጣላላችሁ፤ ትዋጋላችሁ፤ ይሁን እንጂ፣ ከእግዚአብሔር ስለማትለምኑ አታገኙም። 3 ትለምናላችሁ ግን አትቀበሉም፤ ምክንያቱም ክፉ ምኞቶቻችሁን ለማሳካት ክፉ ነገሮችን ስለምትለምኑ ነው። 4 እናንት አመንዝሮች! የዓለም ወዳጅ መሆን፣ የእግዚአብሔር ጠላት መሆን እንደ ሆነ አታውቁም? ስለዚህ ማንም የዓለም ወዳጅ መሆን ቢፈልግ፣ የእግዚአብሔር ጠላት ይሆናል። 5 ወይስ እግዚአብሔር እኛ ውስጥ ያኖረው መንፈስ ለእርሱ ብቻ እንድንሆን አብዝቶ ይቀናል የሚለው የመጽሐፍ ቃል በከንቱ የተነገረ ይመስላችኋል? 6 እግዚአብሔር ግን አብዝቶ ጸጋውን ይሰጣል፤ መጽሐፍ፣ “እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፤ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል” የሚለው በዚህ ምክንያት ነው። 7 ስለዚህ፣ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር አስገዙ፤ ዲያብሎስን ተቃወሙት፤ እርሱም ከእናንተ ይሸሻል። 8 ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ፣ እርሱም ወደ እናንተ ይቀርባል። እናንተ ኃጢአተኞች እጆቻችሁን አንጹ፤ እናንተ በሁለት ሐሳብ የምትዋልሉ ልባችሁን አጥሩ። 9 እዘኑ፤ አልቅሱ፤ ጩኹ! ሳቃችሁን ወደ ሐዘን፣ ደስታችሁን ወደ ትካዜ ለውጡ። 10 በጌታ ፊት ራሳችሁን ዝቅ አድርጉ፤ እርሱም ከፍ ያደርጋችኋል። 11 ወንድሞች ሆይ፣ እርስ በርስ አትወነጃጀሉ። ወንድሙን የሚወነጅልና በወንድሙ ላይ የሚፈርድ ሕጉ ላይ ክፉ ይናገራል፤ በእግዚአብሔርም ሕግ ላይ ይፈርዳል። ሕጉ ላይ የምትፈርዱ ከሆነ፣ ፈራጆች እንጂ፣ ሕጉን አድራጊዎች አይደላችሁም። 12 ሕጉን የሰጠና በሕጉም የሚፈርድ፣ ማዳንም መግደልም የሚቻለው አንዱ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ታዲያ፣ በባልንጀራህ ላይ የምትፈርድ አንተ ማን ነህ? 13 “ዛሬ ወይም ነገ ወደዚህ አገር እንሄዳለን፤ እዚያ አንድ ዓመት እንቆያለን፤ ነግደን እናተርፋለን” የምትሉ እናንተ ሰዎች ስሙ። 14 ነገ የሚሆነውን የሚያውቅ ማን ነው? ሕይወታችሁስ ምንድን ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ ጭጋግ አይደላችሁምን? 15 ይልቁንም፣ “ጌታ ቢፈቅድ እንኖራለን፤ ይህን ወይም ያንን እናደርጋለን” ማለት ይኖርባችኋል። 16 አሁን ግን በዕቅዶቻችሁ ትመካላችሁ። እንዲህ ያለው ትምክህት ሁሉ ክፉ ነው። 17 ስለዚህ መልካም የሆነውን ማድረግ እንዳለበት እያወቀ ለማያደርግ ለዚያ ሰው ኃጢአት ይሆንበታል።
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ያዕቆብ እነዚህ አማኞችን ስለ ዓለማዊነታቸው እና ትህትና ማጣታቸው ይገስጽጻቸዋል፤ አንደበታቸውን ይጠብቁ እና እርስ በእርሳቸው በጥንቃቄ መነጋገር እንዳለባቸው ያበረታታቸዋል፡፡ አጠቃላይ መረጃ: በዚህ ክፍል ውስጥ “እራሳችሁ” የሚለው ቃል ውስጥ “እናንተ” እና እናንተ” የሚለው ቃል የብዙ ቁጥር አመልካች ቃል ሲሆን የሚያመለክተው ያዕቆብ የጻፈላቸውን አማኞችን ነው፡፡ በእናንተ ዘንድ ጦርና ጠብ ከወዴት ይመጣሉ? ያዕቆብ ተደራሲያንኑን ለማስተማር እና ለመገሰጽ ጥያቄን ተጠቅሟል፡፡ አማራጭ ትርጉም "እርስ በእርሳችሁ ሁል ጊዜ ለምን እንደሚትጣሉ አውቃለሁ፡፡" ጠብ እና ክርክር “ጠብ” እና “ክርክር” የሚለው ቃል በመሠረታዊ ትርጉሙ ተመሳሳይ ነው፡፡ ያዕቆብ እነዚህ ሁለት ቃላትን በአንድነት የተጠቀመበት ምክንያት በሰዎች መካከል ያለውን ማንኛውንም አይነት ጠብ ለማመልከት ነው፡፡ በብልቶቻችሁ ውስጥ ከሚዋጉ ከእነዚህ ክፉ ምኞቶቻችሁ አይደሉምን? ያዕቆብ ይህንን ጥያቄ በዚህ ውስጥ የተጠቀመው ተደራሲያኑን ለመገሰጽ ነው፡፡ በእናንተ ቋንቋ ውስጥ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ በዓረፍተ ነገር ቅርጽ ልጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ከክፉ ምኞቶቻችሁ ውስጥ ይወጣሉ" ወይም "ከክፉ ምኞቶቻችሁ ስለምነሱ ነው፡፡" ከሚዋጉ ከእነዚህ ክፉ ምኞቶቻችሁ ያዕቆብ “ክፉ ምኞትን” በሰውኛ መልኩ በመግለጽ አማኞችን በመቃወም የሚዋጋ ወታደር አድርጎ ያቀረበዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “የሚትፈልጉት ክፋት ነው፣ ስለ ሌሎች አማኞች ፍላጎት ግድ አይላችሁም፡፡” በአማኞች ወዳጆቻችሁ መካከል? "በአካሎቻችሁ፡፡" አማራጭ ትርጉም 1) በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ውስጥ በሚገኙ ምዕመናን መካከል ጥል አለ፣ አማራጭ 2) ጥሉ ውስጣዊ ነው ማለትም ክፉ እና መልካም ነገርን በማድረግ መካከል፡፡ ያልለህን ነገር ትመኛለህ "ሁል ጊዜ የሚትፈልገው ያሌለህን ነገር ነው፡፡" ትገድላለህ፣ በብርቱም ትፈልጋለህ በዚህ ክፍል ውስጥ “ትገድላለህ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሰዎች የሚፈልጉትን ነገር ለማግኘት እንዴት በከፋ ሁኔታ እንደሚሄዱ ያመለክታል፡፡ ይህ እንዲህ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል “ማግኘት የማትችሉትን ለማግኘት ስትሉ ሁሉንም ዓይነት ክፋቶችን ታደርጋላችሁ፡፡” ትጣላላችሁ እንዲሁም ትዋጉማላችሁ “መጣላት” እና “መዋጋት” የሚሉት ቃላት በመሠረታዊ ትርጉማቸው ተመሳሳይ ናቸው፡፡ እነዚህ ቃላት ያዕቆብ የተጠቀማቸው ሰዎች እርስ በእርሳቸው ምን ያኸል እንደሚከራከሩ አጽኖት ሰጥተው ለማሳየት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ሁል ጊዜ ትጣላላችሁ፡፡" መጥፎ የሆኑ ነገሮችን ትለምናላችሁ "በመጥፎ ትጠይቃላችሁ፡፡" አማራጭ ትርጉም 1) "በተሳሳተ መነሻ ሀሳብ ትጠይቃላችሁ፣ አመለካካታችሁ መጥፎ ነው፡፡" ወይም 2) "ለተሳሳተ ዓላማ ወይም መጥፎ የሆኑ ነገሮችን ትጠይቃላችሁ፡፡" ታጠፉታላችሁ "ታጠፏቸዋላችሁ"
እናንተ አመንዝሮች! ይህ እግዚአብሔርን የማይታዘዙ ሰዎችን ከባሏ ውጪ ከሌላ ሰው ጋር የሚትተኛ ምስትን ያነጻጽራል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እናንተ ከእግዚአብሔር ታማኞች አልሆናችሁም!" አታውቁምን . . . እግዚአብሔር? ያዕቆብ ተደራሲያኑን ለማስተማር ይህንን ጥያቄ ተጠቅሟል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እናንተ ታውቃላችሁ . . . እግዚአብሔር!" ከዓለም ጋር ወዳጅነት “ከዓለም ጋር ወዳጅነት” የሚለው ሀረግ ከዓለም እሴት ሥርዓት እና ባሕርይ ጋር ራስን ማመሳሰል ወይም መሳተፍ የሚያመለክት ነው፡፡ . ከዓለም ጋር መወዳጀት ከእግዚብሔር ጋር መጣላት ነው የዓለም እሴት ሥርዓት አካል መሆን የእግዚአብሔር ጠላት መሆን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እግዚአብሔር እንደማያከብሩ ሰዎች መኖር ልክ እግዚአብሔር እንደሚቃወም ሰው ነው፡፡" ወይም ቅዱሳት መጻሕፍት ያለ ትርጉም ይመስሏችኋልን ያዕቆብ ተደራሲያኑን ለማረታታት ጥያቄን ይጠቀማል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ቅዱሳት መጻሕፍት እውነት ነው፡፡" እርሱ በውስጣችን ያስቀመጠው መንፈስ አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች የሰው መንፈስን ለማመልከት “መንፈስ” ተጠቅመዋል፡፡ ቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ ቃሉ ያለው ትርጉም ይህም ሊሆን ይችላል፡፡ አንባቢያኑ የሚጠቀሟቸው ሌሎች ትርጉሞች ላይ ያለውን ቃል በትርጉምህ ውስጥ ተጠቀም፡፡
ነገር ግን እግዚአብሔር ሌላ ተጨማሪ ጸጋ ይሰጣል ይህ ሀረግ እንዴት ከዚህ በፊት ካለው ጥቅስ ጋር እንደሚገናኝ ግልጽ ሆኖ መቀመጥ ይችላል: "ምንም እንኳ መንፈሳችን ማግኘት የማንችለውን ነገር የሚመኝ ቢሆን ራሳችንን ዝቅ ዝቅ ካደረግን እግዚአብሔር ከምኞታችን በላይ ጸጋን ይሰጠናል፡፡" እግዚአብሔር ይቃወማል "እግዚአብሔር ይቃወማል" ትብተኛ "ትብተኞች ሰዎችን" ትሁት "ትሁታን ሰዎችን" ስለዚህ "በዚህ ምክንያት" ለእግዚአብሔር ራሳችሁን አስገዙ "ለእግዚአብሔር ራሳችሁን አስገዙ" ወይም "እግዚአብሔርን ታዘዙ" ራሳችሁን . . . እናንተ እነዚህ ተውላጠ ስሞች በብዙ ቁጥር የተጠቀሱ ሲሆኑ የሚያመለክቱትም የያዕቆብን ደራሲያንን ነው፡፡ ዳቢሎስን ተቃወሙት "ዳቢሎስን ተቃወሙት" ወይም "ዳቢሎስ የሚፈልጋቸውን ነገሮች አታድርጉ" እርሱም ከእናንተ ይሸሻል "ዳቢሎስ ከእናንተ ይሸሻል"
አጠቃላይ መረጃ: በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ያዕቆብ የጻፈላቸው በተለያ ስፍራዎች ላይ ተበትነው ያሉትን አማኞችን ነው፡፡ እናንተ ኃጢአተኞች እጆቻችሁን አንጹ እንዲሁም እናንተ ወላዋዮች ልባችሁን አንጹ፡፡ ሀሳብ - “አጆቻችሁን አንጹ” የሚለው ሀረግ በሌላ አገላለጽ “ልባችሁን አንጹ” ተብሎ ተገልጾዋል፡፡ እንዲሁም “አናንተ ኃጢአተኞች” የሚለው ሀረግ “ወላዋዮች” በሚል ሌላ ሀረግ እንደገና ተጠቅሶ እናገኛለን፡፡
እጆቻችሁን አንጹ የዚህ ሀገር አማራጭ ትርጉሞች እነዚህ ናቸው 1) አንድ ሰው ባሕርውን ወይም ተግባራቱን ማስተካከል ወይም 2) አንድ ሰው ኃጢአት ከሞላበት ባሕርይው ወይም ተግባራቱ ሲመለስ ወይም ንሰሓ ይግባ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ : "እግዚአብሔርን በሚያስከብር መንገድ መራመድ፡፡" ልባችሁን አንጹ Here "hearts" refers to a person's thoughts and emotions. AT: "let your thoughts honor God." በሁለት ሀሳብ መወላወል በሁለት ሀሳብ መሆን - “በሁለት ሀሳብ ውስጥ መሆን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አንድ ሰው በአእምሮው ውስጥ ያሉ ሀሳብ ሁለት ከመሆኑ የተነሳ ለመወሰን ስቸገር ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ባለ ሁለት ሀሳብ ሰዎች" ወይም "እግዚአብሔርን መታዘዝ እንዳለባቸው መወሰን ያልቻሉ ሰዎች፡፡"
ኃዘን፣ ለቅሶ እና ማልቀስ “ኃዘን” እና “ለቅሶ” በመሠረታዊ ትርጉማቸው ተመሳሳይ ናቸው፡፡ በዚህ ስፍራ ላይ ያዕቆብ እነዚህ ቃላት በአንድ ላይ የተጠቀማቸው ሰዎች ከልባቸው ማዘን እንዳለባቸው አጽኖት ሰጥቶ ለማሳየት ነው፡፡ “ማልቀስ” የሚለው ቃል ደግሞ የሚያሳየው ሰዎች እያዘኑ መሆናቸውን ነው፡፡ " ሳቀቀችሁን ወደ ኃዘን እንዲሁም ደስታችሁ ወደ እንጉርጉሮ ለውጡት ይህ ተመሳሳይ የሆነ ሀሳብን አጽኖት ለመስጠት በተለያዩ መንገዶች ለመግለጽ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በፍጥነት ሳቃችሁን አቁማችሁ እግዚብሔር ይቅርታ መለመን ጀምሩ፡፡ በጌታ ፊት ረሳችሁን አዋርዱ "በእግዚአብሔር ፊት ራሳችሁን አዋርዱ" እርሱ ያነሳችኋል አማራጭ ትርጉም: "እርሱ ያከብራችኋል፡፡"
አጠቃላይ መረጃ: በዚህ ክፍል ውስጥ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ያዕቆብ የጻፈላቸውን አማኞችን ነው፡፡ ተቃውሞ መናገር "ስለእ . . . መጥፎ ነገር ማናገር" ወይም "መቃወም" ወንድሞች "አማኞች" ይሁን እንጂ እናንተ ፈራጆች ናችሁ አማራጭ ትርጉም: "ይሁን እንጂ የሚታደርጉት ነገር ልክ ሕግን እንደሚያወጣ ሰው ነው፡፡" አንድ ሕግ አውጪ እና ፈረጃ እግዚአብሔር፣ አንድ "ሕግን ማውጣት የሚችል እና በሰዎች ላይ የሚፈርድ አንድ እግዚአብሔር አለ ምክንያቱም ይህንን ማድረግ የሚችል አንድ እርሱ ብቻ ነው፡፡" በባልንጀሮቻችሁ ላይ እናንተ ለመፍረድ ማን ናችሁ? ያዕቆብ ይህንን ጥያቄ የጠየቀው እነርሱን ለመገሰጽ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እናንተ ሰዎች ብቻ ናችሁ ስለዚህም በሌሎች ሰዎች ላይ መፍረድ አትችሉም፡፡"
እንዲህ የሚሉ ይኖራሉ አማራጭ ትርጉም: "ከእናንተ መካከል አንድ ሰው እንዲህ ሊል ይችላል" አንድ ዓመት ቆያለሁ አማራጭ ትርጉም: "ለአንድ ዓመት በዚያ እቆያለሁ" ነገ ምን እንደሚሆን ማን ያውቃል ያዕቆብ ይህንን ጥያቄ የጠየቀው እነርሱን ለመገሰጽ ነው፡፡. አማራጭ ትርጉም: "ነገ ምን እንደሚሆን ማንም ሰው አያውቅም፡፡" ታዲያ ሕይወታችሁን ምንድናት ያዕቆብ ይህንን ጥያቄ በዚህ ሥፍራ ላይ የተጠቀመበት አካላዊ ሕይወት ይህንን ያኸል ጠቃሚ እንዳልሆነ ለማስተማር ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ስለ አካላዊ ሕይወታችሁ አስቡ፡፡" እናንተ ለጥቂት ጊዜ ታይቶ አንደሚጠፋ ጤዛ ናችሁ ይህ አካላዊ ሕይወትን ለጥቂት ጊዜ ብቻ ታይቶ ወዲያው ከሚጠፋው ጤዛ ጋር ያነጻጽራል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "የሚትኖሩት በጣም አጭር ለሆነ ዘመን ነው፤ መቼ እንደሚትሞቱ አታውቁም፡፡
እንኖራለን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል በቀጥታ ያዕቆብን ወይም የእርሱ ተደራሲንን የሚያመለክት አይደለም ይልቁንም የያዕቆብ ተደራሲያን ምን ዓይነት ባሕርይ ሊኖራቸው እንደሚገባ የሚያሳይ ነው፡፡ ይህንን እና ያንን እናድርጋለን አማራጭ ትርጉም: "እና ለማድረግ ያቀድነውን ዕቅድ እንፈጽማለን" ለሚያውቀው ለእርሱ በዚህ ሥፍራ ላይ ያዕቆብ “ለእርሱ” በማለት ሲጽፍ ይህንን ማንንም ለማመልከት አልጻፈውም ይልቁንም መልካም ለማድረግ የሚፈለግ ነገር ግን የማያደርገን ሰው ለማመልከት ጽፎታል፡፡
1 እንግዲህ እናንተ ሀብታሞች ስለሚመጡባችሁ ክፉ ነገሮች አልቅሱ ዋይ ዋይም በሉ። 2 ሀብታችሁ ሻግቶአል፤ ልብሳችሁንም ብል በልቶታል። 3 ወርቃችሁና ብራችሁ ዝጎአል፤ ዝገቱም እናንተ ላይ ይመሰክራል፤ ሥጋችሁንም እንደ እሳት ይበላዋል። ለመጨረሻው ቀን ሀብታችሁን አከማችታችኋል። 4 ልብ በሉ፤ እርሻችሁን ላጨዱ ሠራተኞች ያልከፈላችሁት ደመወዝ ይጮኻል! የአጫጆቹም ጩኸት የሠራዊት ጌታ ጆሮ ደርሶአል። 5 በምድር ላይ በምቾትና በመንደላቀቅ ኖራችኋል። ለዕርድ ቀን ልባችሁን አወፍራችኋል። 6 እናንተን ያልተቃወመውን ጻድቅ ሰው ኮንናችሁታል፤ ገድላችሁታል። 7 ስለዚህ ወንድሞች ሆይ፣ የመጀመሪያውና የኋለኛው ዝናብ እስኪመጣ ድረስ የምድርን ፍሬ በትዕግሥት እንደሚጠብቅ ገበሬ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ታገሡ። 8 እናንተም እንዲሁ ታገሡ፤ ልባችሁን አዘጋጁ፤ ምክንያቱም የጌታ መምጫ ቅርብ ነው። 9 ወንድሞች ሆይ፤ እንዳይፈረድባችሁ እርስ በርሳችሁ አታጉረምርሙ። ልብ በሉ፤ ፈራጁ በሩ ላይ ቆሞአል። 10 በጌታ ስም የተናገሩ ነቢያትን መከራና ትዕግሥት እንደ ምሳሌ ውሰዱት። 11 ልብ በሉ፤ በትዕግሥት የጸኑትን፣ “የተባረኩ” እንላቸዋለን። ስለ ኢዮብ ትዕግሥት ሰምታችኋል፤ ጌታ ለኢዮብ የነበረውንም ዓላማ ታውቃላችሁ፤ ጌታ እጅግ ሩኅሩኅና መሐሪ ነው። 12 ወንድሞቼ ሆይ፣ ከሁሉም በላይ አትማሉ፤ በሰማይም ሆነ በምድር ወይም በሌላ ነገር አትማሉ። ቃላችሁ “አዎን” ካላችሁ፣ “አዎን” ይሁን፤ “አይደለም” ካላችሁም፣ “አይደለም” ይሁን። 13 በእናንተ መካከል መከራ የደረሰበት አለ? እርሱ ይጸልይ። ደስ ያለው አለ? እርሱ ይዘምር። 14 በእናንተ መካከል የታመመ አለ? የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎችን ይጥራ፤ እነርሱም በጌታ ስም ዘይት እየቀቡ ይጸልዩለት፤ 15 የእምነት ጸሎት የታመመውን ሰው ይፈውሳል፤ ጌታም ያስነሣዋል። ኃጢአት አድርጎ ከሆነም እግዚአብሔር ይቅር ይለዋል። 16 እንዲሁ ጌታ ከበሽታ ሊፈውስና ኃጢአትን ይቅር ሊል ስለሚችል ያደረጋችሁትን ኃጢአት በተመለከተ አንዳችሁ ለሌላችሁ ተናዘዙ፡፡ ጻድቃን ሰዎች ከጸለዩና አንድ ነገር እንዲያደርግላቸው ጌታን አጥብቀው ከጠየቁት፣ እግዚአብሔር ይገለጣል፤ ደግሞም በእርግጠኝነት ያን ነገር ያደርገዋል፡፡ 17 ነቢዩ ኤልያስ እንደኛው ያለ ሰው ቢሆንም፣ ዝናብ እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፡፡ ለሦስት ዓመት ከስድስት ወራት ጊዜ ያህልም ዝናብ አልነበረም፡፡ 18 ከዚያም ዝናብ እንዲዘንብ እግዚአብሔርን እየለመነ ጸለየ፤ እግዚአብሔርም ዝናብን ላከ፣ ተክሎችም ዐደጉና ሰብልን ሰጡ፡፡ 19 ወንድቼና እኅቶቼ ሆይ፥ ከእናንተ አንዱ ዕውነተኛውን የእግዚአብሔርን ቃል መልእክት መታዘዝ ቢያቆም፣ ከእናንተ አንዱ ያደርገው ዘንድ እግዚአብሔር ለዚያ ሰው የነገረውን ነገር በመንገር ሊያሳምነው ይገባል፡፡ 20 የሚያሳምነው ሰውም ኃጢአት እየሠራ የነበረውን ሰው ተናግሮ ስሕተት ከመሥራት እንዲመለስ ስላስቻለው፣ እግዚአብሔር ያንን ሰው ከመንፈሳዊ ሞት ያድነዋል፤ ደግሞም ብዙ የሆኑት ኃጢአቶቹን ይቅር ይልለታል፡፡
አያያዥ ዓረፍተ ነገር: ያዕቀብ አማኞች ስለ ደስታ እና ሀብት በጣም መጨነቅን አስመልክቶ ያስጠነቅቃቸዋል፡፡ እናንተ ሀብታም የሆናችሁ ሰዎች በዚህ ሥፍራ ላይ ያዕቆብ ሀብታም የሆኑ ነገር ግን እግዚአብሔርን የማያከብሩ ሰዎችን ይናገራል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እናንተ ሀብታም የሆናችሁ ሰዎች ነገር ግን እግዚአብሔርን የማታከብሩ፡፡" በእናንተ ላይ ክፉ የሆነ ነገር መጥቶባችኋል አማራጭ ትርጉም፡ "እግዚአብሔር በሁሉም ሰዎች ላይ በሚፈርድበት ጊዜ ያኔ እናንተም ላይ አሰቃቂ ነገር ይመጣባችኋል" ሀብታችሁ ይበሰብሳል እንዲሁም ልብሳችሁ ብል ይበላዋል፡፡ ወርቀችሁ እና ብራችሁ ጥቅም አይኖረውም፡፡ ሀብታሁን እና ልብሳችሁ ይበላል፡፡ ወርቃችሁ እና ብራችሁ ጥቅም አይኖረውም - ያዕቆብ የእነዚህ ሀብታሞች ሀብት እና ልብስ ጠፍቷል እያለ አይደለም፡፡ ይልቁንም እነዚህ ነገሮች በአሁኑ ዘመን ምንም ዓይነት መነፈሳዊ እሴት ስላሌላቸው ለብዙ ጊዜ ከእነርሱ ጋር መቆየት አይችሉም፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ዋጋ አላቸው እንዲሁም በጣም አስፈላጊ ናቸው ብላችሁ የሚታስቧቸው ነገሮች ሁሉ ምን ጥቅም የላቸውም እንነዲሁም ከእናንተ ጋር የሚቆዩት በጣም ለጥቂት ጊዜ ያኸል ብቻ ነው፡፡"
መበስበሱ ራሱ ይመሰክርባችኋል በዚህ ሥፍራ ላይ “በእናንተ ላይ ይመስክራል” የሚለው ሀረግ የሚያሳየው አንድ ሰው ሕግን በመተላለፍ በዳኛ ፊት ሲቆም ሀብቱ ምንም የማይፈይድለት ሲሆን ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እግዚአብሔር እናንተ ላይ በሚፈርድበት ዕለት ሀብትህ የአንተ ከሳሽ ይሆናል፡፡" ሥጋህን እንደ እሳት ይበላልe በዚህ ሥፍራ ላይ የተበለሻ ሀብት የሚለው ቃል ሁሉን ነገር ከሚያጠፋው እሳት ጋር ተነጻጽሮ ቀርቧል፡፡ከዚህ በተጨማሪ “እሳት” የሚለው ቃል የእግዚአብሔር ፍርድ የሚያመለክት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እግዚአብሔር አንተን ለመቀጣት ምክንያት ይሆኑታል፡፡" ሀብትህን ለሌሎች ሰዎች አለማካፈል "ሀብትህን ሁሉ ለራስህ ብቻ በመያዝ ለሌሎች ሰዎች አለማካፈል" በመጨረሻው ዘመን ይህ ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔር በሰዎች ሁሉ ላይ የሚፈርድበት ጊዜ ከመድረሱ ጥቂት ጊዜ በፊት፡፡ አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር በአንተ ላይ ከመፍረዱ በፊት"
ለሠራተኞች ደምች መክፈል—ከማሳህ ላይ ሰብልህን ለሰበሰቡት ሰሰዎች ተገቢውን ክፍያ መክፍል በመጀመሪያ ትኩረት የተሰጠው ከዚህ በፊት ላልተከፈለ ክፍያ ወይም ደሞዝ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በማሳህ ላይ ያለውን ሰብል እንዲሰበስብልህ ለቀጠርካቸው ሰዎች አስፈላጊውን ክፍያ አለመፈጸምህ ያስከስስሃል፡፡" እንዲሁም ከማሳህ ላይ ሰብልህን የሰበሰቡልህ ሰዎች አማራጭ ትርጉም፡ "በማሳህ ላይ ያለውን ሰብል እንዲሰበስብልህ ለቀጠርካቸው ሰዎች አስፈላጊውን ክፍያ አልከፍልካቸውም እና እንድትከፍላቸው ወደ አንተ ይጮኻሉ" ወደ ሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ጆሮ ደርሰዋል አማራጭ ትርጉም፡ "በሰብል ማሳህ ላይ ቀጥረህ ስታሠራቸው የነበሩት ሰዎችን ለቅሶ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሐር ሰምቷል፡፡" ልብህን ልክ ለመታደር እንደሚዘጋጀት አስብተሃል ይህ ስግብግብ እና ሁሉን ነገር ለራሱ ማድረግ የሚፍልግን ሀብታም እስኪደልብ እና ለምግብነት እኪታረድ ድረስ ሁሉን ነገር ከሚበላ በሬ ጋር ያነጻጽራል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ስግብግብነትህ ለትልቅ ዘላለማዊ ቅጣት የሚያዘጋጅህ ብቻ ይሆናል፡፡" ጻድቅ ሳ "ትክክል የሆነውን ነገር የሚያድረግ ሰው" አይቋቋሚህም "አይቃወምህም"
አያያዥ ዓረፈት ነገር: በመዝጊያው ያዕቆብ ለአማኞች የጌታን መምጣት ያስታውሳቸዋል እንዲሁም እንዴት ለጌታ መኖር እንዳለባቸው ትንንሽ ትምህርቶችን ይነግራቸዋል፡፡ ስለዚህም ትዕግስተኞች ሁኑ "በዚህም ምክንያት ቆዩ እንዲሁም ተረጋገቱ" እስከ ጌታ መምጠት ድረስ ይህ ሀረግ የሚያመለክተው የኢየሱስን መንግስቱን በምድር ላይ ለመመስረት እና በሰዎች ሁሉ ላይ ለመፍረድ የሚመጣበት ጊዜ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም "ክርስቶስ ዳግም እስክመጣ ድረስ፡፡" ልክ እንደ ገበሬ ያዕቆብ መታገስ ማለት ምን ማለት እንደሆነ አጽኖት ሰጥቶ ለአመኞች ለማሳየት አማኞችን ከገበሬ ጋር ያነጻጽራል፡፡ ልህን አስተካከል አማራጭ ትርጉም: "የተሰጠህ ሁን" ወይም "እምነትህን አጠንክር" የጌታ መምጣ በቅርብ ነው "ክርስቶስ ቶሎ ይመጣል"
ወንድሞች ሆይ አታጉረምርሙ... እናንተ ያዕቆብ በየሥፍራው ተበትነው ላሉት አማኞች ነው የጻፈው፡፡ በሌሎች ላይ "እርስ በእርሳችሁ" አይፈረድህም አመራጭ ትርጉም: "ክርስቶስ ይፈርድባችኋል፡፡" ፈራጁ በደጅ ቆሟል፡፡ ያዕቆብ ኢየሱስን ከዳኛ ጋር በማነጻጸር ኢየሱስ በዓለም ላይ ለመፍረድ ቶሎ እንደሚመጣ አጽኖት ሰጥቶ ይናራል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ዳኛው ቶሎ ይመጣል፡፡” ) የነቢያት መከራ እና ትዕግስት "ነቢያት ምን ዓይነት መከራን እንደደረሰባቸው እና ይኸንን እንዴት እንዳለፉ፡፡" በጌታ ስም የተናገሩ "ጌታን ወክለው ለሕዝቡ የተናገሩ" ተመልከት በዚህ ሥፍራ ላይ “ተመልከት” የሚለው ቃል ከዚያ ቀጥሎ ለሚመጣው ነገር አጽኖት የሚሰጥ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በጥንቃቄ አድምጡ" ወይም "አስታውሱ፡፡" ጸንተው የቆሙትን "መከራን በጽናት የተቋቋሙት" ወይም "በመከራ ውስጥ በጽናት የሚሄዱት" ጌታ ሙሉ ለሙሉ ርሁሩ እና መሐሪ ነው "ጌታ ሁል ጊዜ ምሕረትን እና ርህራሄን የሚያሳይ ነው"
ከሁሉ በላይ አማራጭ ትርጉም: "ይህ በጣም አስፈላጊ ነው" ወይም "በተለይም" ወንድሞቼ "ከእኔ ጋር አማኞች" አትማል “መማል” ማለት አደርገዋለው ማለት ነው እንዲሁም ከአንተ በላይ ሥልጣን ባለው አካል ተጠያቂ እሆናለሁ ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “አትማል” ወይም "አትማል" በምድርም ይሁን በሰማይ “ሰማይ” እና “ምድር” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በሰማይ እና በምድር ላይ ኃይል የሚያመልከታል፡፡ ንግግራችሁ “አዎ” “አዎ” እና “አይ” “አይ” መሆን አለበት፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ያለ ምንም መኃላ አድርጋለሁ ብላቸው ቃል የገባችሁትን ነገር አድርጉም፡፡" ስለዚህ በፍርድ ሥር አይወድቅምt "ስለዚህም እግዚአብሔር ይፈርድባቸውም"
ከእናንተ መካከል መከራ ውስጥ ያለ ሰው አለን? ይጸልይ፡፡ "በመከራ ውስጥ ያለ ማንም ሰው ቢኖር ይጸልይ፡፡" ደስ ያለው ሰው ቢኖር? ይዘምር "ደስ ያለው ሰው ቢኖር የምስጋናን መዝሙር ይዘምር፡፡" በእናንተ መካከል ያታመመ ቢኖር? ይጥራ "በእናንተ መካከል የታመመ ሰው ቢኖር ይጥራ" በእምነት የተደረገ ጸሎት ታማሚውን ሰው ይፈውሳል እና ጌታም ያስነሳዋል አማኞች ለታመመ ሰው በሚጸልዩበት ወቅት ጸሎታቸውን የሚሰማው ጌታ በሽተኞቹን ይፈውሳቸዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ጌታ በእምነት የሚጸልዩ አማኞችን ጸሎት ይሰማል እንዲሁም የታመሙ ሰዎችንም ይፈውሳል፡፡"
አጠቃላይ መረጃ: እነዚህ አይዳዊያን አማኞች በመሆናቸው ምክንያት ያዕቆብ ከጥንት ነቢያት መካል አንዱህ በማስታወስ እንዲጸልዩ ያሳስባቸዋል፡፡ ለእርስ በእርሳችሁ "ለእርስ በእርሳችሁ" አንዳችሁ ለሌላኛችሁ "ለእርስ በእርሳችሁ" ትፈወሱ ዘንድ "እግዚአብሔር ይፈውሳችሁ ዘንድ" የጻድቅ ሰው ጸሎት ታላቅ ነገርን ያደርጋል "እግዚአብሔርን የሚታዘዝ ሰው ሲጸልይ እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን ያደርጋል" ከልብ "ከልብ የሚሆን" ወይም "የእውነት" ከሦስት . . . ስድት "3...6" ሰማያት ዝናብን ያዘንባሉ በዚህ ሥፍራ ላይ “ሰማያት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ነው፡፡ “እግዚአብሔር እንዲዘንብ ያደርጋል፡፡”
ኖት የለውም።
1 የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ከሆነው ከጴጥሮስ፤ በጳንጦስ፣ በገላትያ፣ በቀጰዶቅያ፣ በእስያና በቢታንያ ተበትነው በመጻተኝነት ለሚኖሩ፤ ለተመረጡት፤ 2 እግዚአብሔር አብ አስቀድሞ እንዳወቃቸው፣ ኢየሱስ ክርስቶስን ለመታዘዝ በደሙ ለተረጩትና በመንፈስ ቅዱስ ለተቀደሱት፤ ጸጋ ለእናንተ ይሁን፤ ሰላማችሁም ይብዛ። 3 የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባትና አምላክ ይባረክ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት በመነሣቱ ምክንያት ላገኘነው ርስት ዋስትና እንዲሆነን በታላቅ ምሕረቱ አዲስ ልደትን ሰጠን፤ 4 ይህም የማይጠፋ፣ የማይበላሽ እና የማያረጅ ርስት በመንግሥተ ሰማይ ተጠብቆላችኋል። 5 እናንተም በመጨረሻው ዘመን ይገለጥ ዘንድ ለተዘጋጀው መዳን በእምነት አማካይነት በእግዚአብሔር ኅይል ተጠብቃችኋል። 6 ምንም እንኳን አሁን በብዙ ልዩ ልዩ ዐይነት መከራ ማዘናችሁ ተገቢ ቢሆንም፣ በዚህ እጅግ ደስ ይላችኋል። 7 ይኸውም፣ በእሳት ተፈትኖ ቢጠራም፣ ጠፊ ከሆነው ወርቅ ይልቅ እጅግ የከበረው እምነታችሁ እንዲፈተን ነው። ይህ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ አምነታችሁ ምስጋናን ክብርንና፣ ውዳሴን እንዲያስገኝላችሁ ነው። 8 ኢየሱስ ክርስቶስን ባታዩትም እንኳ ትወዱታላችሁ፤ አሁን ባታዩትም በእርሱ ታምናላችሁ፤ ሊነገር በማይቻልና ክብር በሞላበት ሐሤት በጣም ደስ ይላችኋል፤ 9 አሁን የእምነታችሁን ፍጻሜ እርሱም የነፍሳችሁን መዳን እየተቀበላችሁ ነውና። 10 እናንተ ስለምትቀበሉት ጸጋ ትንቢት የተናገሩት ነቢያት ስለዚህ መዳን ይፈልጉና በጥልቅ ይመረምሩ ነበር፤ 11 የሚመጣው መዳን ምን ዐይነት እንደ ሆነ ለማወቅ ይመረምሩ ነበር፤ እንዲሁም በእነርሱ ውስጥ የነበረው የክርስቶስ መንፈስ ስለ ክርስቶስ መከራና ከመከራው በኋላ ስለሚሆነው ክብር አስቀድሞ የተናገራቸው በምን ጊዜና እንዴት እንደሚፈጸም ይመረምሩ ነበር። ነቢያቱ ያገለግሉ የነበሩት እናንተን እንጂ ራሳቸውን እንዳልነበረ ተገልጦላቸዋል፤ 12 ይኸውም ከሰማይ በተላከው በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ወንጌልን ያበሠሩአችሁ ሰዎች የነገሩአችሁን በመግለጥ ነው፤ መላእክትም እንኳ ይህ ነገር ሲገለጥ ለማየት ይመኙ ነበር። 13 ስለዚህ የልቡናችሁን ወገብ ታጠቁ፤ ጠንቃቆች ሁኑ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ በምታገኙት ጸጋ ላይ ፍጹም መተማመን ይኑራችሁ። 14 ታዛዦች ልጆች እንደ መሆናችሁ ባለማወቅ አስቀድሞ የኖራችሁበትን ምኞት አትከተሉ። 15 ነገር ግን የጠራችሁ እርሱ ቅዱስ እንደ ሆነ፣ እናንተም በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ፤ 16 ምክንያቱም «እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ» ተብሎ ተጽፎአል። 17 ሳያዳላ በእያንዳንዱ ሰው ላይ እንደየሥራው የሚፈርደውን «አባት» ብላችሁ የምትጠሩት ከሆነ፣ በእንግድነት ዘመናችሁ እርሱን በማክበር ኑሩ። 18 ከቀድሞ አባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከማይረባ ሕይወት የተዋጃችሁት በሚጠፋ ነገር ማለትም በብር ወይም በወርቅ እንዳልሆነ ታውቃላችሁ፤ 19 ይልቁንም የተዋጃችሁት ነውርና እንከን እንደሌለበት በግ ደም፣ በክርስቶስ ክቡር ደም ነው። 20 ክርስቶስ የተመረጠው ዓለም ከመፈጠሩ በፊት ነው፤ አሁን ግን በመጨረሻው ዘመን ለእናንተ ተገለጠ። 21 በእርሱ አማካይነት፣ ከሞት ባስነሣውና ክብርን በሰጠው በእግዚአብሔር ታምናላችሁ። ይኸውም እምነታችሁና ተስፋችሁ በእግዚአብሔር ላይ እንዲሆን ነው። 22 ለእውነት በመታዘዝ ለእውነተኛ የወንድማማች መዋደድ ነፍሳችሁን አንጽታችሁ እርስ በርሳችሁ ከልብ አጥብቃችሁ ተዋደዱ። 23 ዳግመኛ የተወለዳችሁት ከሚጠፋ ዘር አይደለም፤ ነገር ግን በሕያውና ለዘላለም በሚኖር በእግዚአብሔር ቃል ከማይጠፋ ዘር ነው። 24 ሥጋ ሁሉ እንደ ሣር፣ ክብሩም ሁሉ እንደ ሣር አበባ ነውና፤ ሣሩ ይጠወልጋል፤ አበባውም ይረግፋል፤ 25 የጌታ ቃል ግን ለዘላለም ይኖራል። የተሰበከላችሁም ወንጌል መልእክቱ ይህ ነው።
ጴጥሮስ ራሱን እንደ ጸሐፊው ገልጦ የጻፈላቸውን አማኞች ለይቶ በማግኘቱ ሰላምታ ያቀርባል ፡፡
ፒተር አንባቢዎቹን ፣ በተለያዩ አገሮች ውስጥ ከቤታቸው ርቀው የሚኖሩ ሰዎች እንደሆኑ ገል asል ፡፡
ጴጥሮስ ከጠቀሳቸው ሌሎች ቦታዎች በተጨማሪ “ቀppዶቅያ” እና “ቢቲኒያ” የቱርክ ሀገር በሆነችው የሮማውያን አውራጃዎች ነበሩ ፡፡
“እግዚአብሔር አብ የመረጠው… እንደ ራሱ አስቀድሞ በማወቅ።” እግዚአብሔር እንደ ራሱ አስቀድሞ በማወቅ መርጦአቸዋል።
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) እግዚአብሔር አስቀድሞ የሚሆነውን ወስኖ ነበር ፡፡ AT: - “እግዚአብሔር አብ አስቀድሞ የወሰነ” (ዩ.አር.ቢ.) ወይም 2) እግዚአብሔር አስቀድሞ የሚሆነውን ያውቃል ፡፡ አት: - "እግዚአብሔር አብ አስቀድሞ ያውቅ ነበር" (የበለስ_ቁጥር መግለጫዎችን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ደሙ” የኢየሱስን ሞት ያመለክታል ፡፡ ሙሴ ከእስራኤል ጋር የገቡትን ቃል ኪዳን ለማሳየት ሙሴ በእስራኤል ላይ ደም እንደ ረጨ ሁሉ አማኞች በኢየሱስ ሞት ከእግዚአብሔር ጋር ቃል ኪዳን ገብተዋል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ እና የበለስ_ማምበል) ፡፡
ይህ ምንባብ ስለ ጸጋ የሚናገረው አማኞች ሊኖሩት የሚችል ዕቃ ነው ፣ እና ሰላምን በመጠን ሊጨምር የሚችል ነገር ነው። በእርግጥ ፣ ጸጋ በእውነቱ እግዚአብሔር ለአማኞች የሚያደርጋቸው ደግነት መንገድ ነው ፣ እናም ሰላም አማኞች በደኅንነት እና ከእግዚአብሔር ጋር ደስ የሚሰኙበት መንገድ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
ጴጥሮስ ስለ አማኞች መዳን እና እምነት መነጋገር ጀመረ ፡፡ እዚህ ላይ እግዚአብሔር ለሁሉም አማኞች ለማድረግ የገባውን ቃል ለእነርሱ ለእነሱ የሚያስተላልፍ ውርስ የሚገለጽበትን ዘይቤ አብራራ ፡፡
“የእኛ” እና “እኛ” የሚሉት ቃላት የሚያመለክቱት ጴጥሮስንና የጻፈላቸውን ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
“እንደገና እንድንወለድ አደረገን”
ይህንን ግስ በመጠቀም መተርጎም ይችላሉ። አት: - "ስለሆነም እኛ ውርሻን ለመቀበል በልበ ሙሉነት እንጠብቃለን" (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
ለአማኞች እግዚአብሔር ቃል የገባውን ቃል መቀበል ከቤተሰብ አባል ንብረትንና ሀብትን እንደሚወርስ ይገለጻል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ርስቱን ፍጹም እና ዘላለማዊ የሆነ ነገር ለመግለጽ ጴጥሮስ ሦስት ተመሳሳይ ሐረጎችን ይጠቀማል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ለእናንተ በሰማይ አድርጎ ያሰናዳችኋል” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ይጠብቅህ” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
“ይህ” የሚለው ቃል ቀደም ባሉት ቁጥሮች ውስጥ ጴጥሮስ የጠቀሳቸውን በረከቶች ሁሉ ያመለክታል ፡፡
እሳት ወርቅ ወርቅን በሚጠራበት በተመሳሳይ ፣ መከራዎች አማኞች በክርስቶስ ምን ያህል እንደሚታመኑ ይፈትሻል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እግዚአብሔር አማኞች በክርስቶስ ምን ያህል እንደሚታመኑ ለመፈተን ይፈልጋል ፡፡
እምነት ከወርቅ የበለጠ ዋጋ ያለው ነው ፣ ምክንያቱም ወርቅ በእሳት ውስጥ ቢጠራም እንኳን ለዘላለም አይቆይምና ፡፡
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) በእምነታችሁ (UDB) ወይም 2) “እምነትህ ክብርን ፣ ክብርን እና ክብርን ያመጣል” የሚሉ 1) ናቸው ፡፡
"ቃላት የማይገልፁ ድንቅ ደስታ"
እዚህ ላይ “ነፍሳት” የሚለው ቃል መላውን ሰው ያመለክታል ፡፡ ይህንን ግስ በመጠቀም ሊተረጉሙት ይችላሉ። አት: - “ማዳንህ” ወይም “እግዚአብሔር ያዳነሃል” (ዩዲቢ) (ይመልከቱ ፡፡
እነዚህ ቃላት ሁለት ሀሳቦችን እንደ ነገሮች ወይም ነገሮች አድርገው ያሳያሉ ፡፡ በተጨባጭ ፣ “ድነት” የሚያመለክተው እግዚአብሔር የሚያድነን እርምጃ ነው ፣ ወይም በውጤቱም ለሚሆነው። በተመሳሳይ “ጸጋ” እግዚአብሔር ከአማኞች ጋር የሚገናኝበትን ደግነት መንገድ ያሳያል ፡፡
“በጥንቃቄ የተጠየቁት” ቃላት በመሠረታዊነት “መፈለጉ” የሚል ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው ፡፡ አንድ ላይ እነዚህ ቃላት ነቢያት ይህንን ደኅንነት ለመረዳት ምን ያህል ጥረት እንዳደረጉ ያጎላሉ ፡፡ አት: - "በጣም በጥንቃቄ ተመርምሯል"
ጴጥሮስ ስለ ነቢያት መዳን ፍለጋ መናገሩን ቀጠለ ፡፡
"ለመወሰን ሞክረዋል"
ይህ ስለ መንፈስ ቅዱስ ማጣቀሻ ነው ፡፡
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ለነቢያት ገልጦላቸዋል” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
“መላእክት ማስተዋል ይፈልጋሉ”
"በዚህ ምክንያት." ጴጥሮስ እዚህ ላይ የተጠቀመው ስለ ድነት ፣ ስለ እምነታቸው እና ስለ ክርስቶስ መንፈስ የነቢያትን መገለጥን አስመልክቶ የተናገረውን ሁሉ ነው ፡፡
ይህ ጠንክሮ ለመስራት መዘጋጀትን ያመለክታል ፡፡ በቀላል ሁኔታ ለመንቀሳቀስ የአንዱን ቀሚሱን የታችኛው ወገብ ላይ በወገብ ላይ በማሰር ባህል ነው የመጣው ፡፡ አት: - “ተዘጋጁ” (ይመልከቱ: የበለስ_ ቪዲዮም)
እዚህ ላይ ‹አስተዋይ› የሚለው ቃል የአእምሮን ግልፅነት እና ንቃትን ያመለክታል ፡፡ አት: - "ሀሳቦችዎን ይቆጣጠሩ" ወይም "ስለምያስቡበት ይጠንቀቁ"
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - "እግዚአብሔር ወደ አንተ ያመጣውን ጸጋ" (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ይህ የክርስቶስን መመለስ ያመለክታል ፡፡ አት: - “ኢየሱስ ክርስቶስ ለሁሉም ሰዎች ሲገለጥ” ይህንን በ 1 6 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - "ሙሴ እንደጻፈው" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እዚህ “እኔ” የሚለው ቃል እግዚአብሔርን ያመለክታል ፡፡
ጴጥሮስ ስለ አንባቢዎቹ የጠቀሰው ከቤታቸው ርቀው በባዕድ አገር የሚኖሩ ሰዎች እንደሆኑ አድርገው ነው ፡፡ አት: - “ከእውነተኛ ቤትዎ ርቀው የሚኖሩትን ጊዜ ያሳልፉ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ሚታልፍ)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ተቤዣችሁ” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ደም” በመስቀል ላይ የክርስቶስን ሞት ያመለክታል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
እግዚአብሔር የሰዎችን ኃጢአት ይቅር እንዲል ኢየሱስ እንደ መስዋእት ሆኖ ሞተ ፡፡ አት: - “የአይሁድ ካህናት ኃጢአት ያለባቸውን እንከን የሌለባቸውን ወይም እንከን የሌለባቸውን በግ” (ተመልከት ፡፡
ጴጥሮስ የክርስቶስን ንፅፅር ለማጉላት ተመሳሳይ ሀሳብ በሁለት መንገዶች ገል expressል ፡፡ አት: - “ያለ ፍጽምና የጎደለው”
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ክርስቶስን መረጠው” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ይህንን በቃል ሐረግ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “እግዚአብሔር ዓለምን ከመፍጠሩ በፊት” (የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎችን ይመልከቱ)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ለእርስዎ ገልጦታል” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ለእርስዎ ገልጦታል” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ጴጥሮስ ፣ ኢየሱስን አንድ ነገር እንደ ሰጠው እግዚአብሔርን እንደሚያከብር ጴጥሮስ ተናግሯል። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
እዚህ ላይ ጴጥሮስ ስለ አማኞች ራሱን ያነጹ ይመስላቸዋል ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ እነሱ ከዳን መዳንን እንጂ ሌላ ምንም አላደረጉም ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
እዚህ ላይ የፅዳት ሃሳብ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት ማግኘትን ያመለክታል ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ይህን የቃል ሐረግ በመጠቀም መተርጎም ይችላሉ። አት: - “በእውነት በመታዘዝ” (የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎችን ይመልከቱ)
ይህ በእምነት ባልንጀሮች መካከል ያለውን ፍቅር ያሳያል።
እዚህ ላይ “ልብ” የሚለው ቃል የስሜቶችን መቀመጫ የሚያመለክት ሲሆን እነሱ ሙሉ በሙሉ መውደድ እንዳለባቸው ያመለክታል ፡፡ አትቲ: - “እርስ በርሳችሁ አጥብቃችሁ ተዋደዱ” ወይም “ከልብ እና በሙሉ ልብ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ” (ይመልከቱ። የበለስ_ ቪዲዮም)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች ማለት ጴጥሮስ ስለ እግዚአብሔር ቃል የተናገረው 1) በአማኞች ላይ አዲስ ሕይወት እንደሚበቅል እና እንደሚበቅል ተክል ወይም 2) ህፃኗን ወደ ውስጥ ለማሳደግ በሚጣመሩ ወንድ ወይም ሴት ውስጥ ያሉ ጥቃቅን ህዋሳት እንደሆኑ ነው ፡፡ ሴት (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
“የማይበላሽ” ወይም “ዘላቂ ያልሆነ”
ጴጥሮስ የእግዚአብሔርን ቃል ለዘላለም እንደሚኖር ተናግሯል ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ፣ ለዘላለም የሚኖር ፣ ትእዛዛቱም እና ቃል ኪዳኑ ለዘላለም የሚዘልቅ እግዚአብሔር ነው። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
በእነዚህ ቁጥሮች ውስጥ ጴጥሮስ በማይጠፋ ዘር ስለ መወለዱ የነገረውን የሚናገር አንድ ጥቅስ ከነቢዩ ኢሳያስ ጠቅሷል ፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስ የሰውን ዘር በፍጥነት ከሚበቅል እና ከሚሞቀው ሣር ጋር አነፃፅሯል ፡፡ አት: - “ሰዎች ሁሉ እንደ ሣር ይሞታሉ” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
“ሥጋ” የሚለው ቃል የሰውን ዘር ያመለክታል ፡፡ አት: - “ሰዎች ሁሉ”
እዚህ “ክብር” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ውበት ወይም ጥሩነትን ነው ፡፡ ኢሳያስ ሰዎች ስለ ሰው ልጆች ጥሩ ወይም የሚያምር የሚመስሏቸውን ነገሮች በፍጥነት ከሚሞቱ አበቦች ጋር ያመሳስላቸዋል። አት-“አበቦች ቶሎ እንደሚሞቱ ሁሉ የሰው ልጅ ሁሉ ጥሩ ሆኖ ይወጣል” (ይመልከቱ ፡፡
እዚህ “ይህ” የሚለው ቃል “የጌታን ቃል” ያመለክታል ፡፡
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ያወጀው ምሥራች” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
1 እንግዲህ ክፋትን ፣ ማታለልን ፣ ግብዝነትን፣ ቅናትንና ሐሜትን ሁሉ አስወግዱ። 2 በድነታችሁ በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ንጹህ የሆነውን መንፈሳዊ ወተት ተመኙ፤ 3 ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ ከሆነ፣ 4 በሰው ዘንድ ወደ ተናቀው፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ወደ ተመረጠውና ክቡር ወደ ሆነው ወደዚህ ሕያው ድንጋይ ቅረቡ። 5 ደግሞም እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ፣ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕት የሚያቀርቡ ቅዱሳን ካህናት ትሆኑ ዘንድ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ትሠራላችሁ። 6 በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተጻፈው «እነሆ፤ የተመረጠና የከበረን የማዕዘን ራስ ድንጋይ በጽዮን አኖራለሁ፤ በእርሱም የሚያምን አያፍርም» ። 7 እንግዲህ ለምታምኑት ለእናንተ እርሱ ክቡር ነው፤ ለማያምኑት ግን፣«ግንበኞች የናቁት ድንጋይ፣ እርሱ የማእዘን ራስ ሆነ» 8 እንደዚሁም ደግሞ «ሰዎችን የሚያሰናክልና የሚጥላቸውም ዐለት ሆነ»። የሚሰናከሉት ቃሉን ባለመታዘዛቸው ነው፤ የተመደቡት ለዚህ ነውና። 9 እናንተ ግን ከጨለማ ወደ አስደናቂ ብርሃኑ የጠራችሁን የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ እንድታውጁ፣ የተመረጠ ትውልድ፣ የንጉሥ ካህናት፣ ቅዱስ ሕዝብ፣ እግዚአብሔር የራሱ ያደረጋችሁ ሕዝብ ናችሁ። 10 ቀድሞ የእርሱ ሕዝብ አልነበራችሁም፤ አሁን ግን የእግዚአብሔር ሕዝብ ሆናችኋል፤ ቀድሞ ምሕረትን አላገኛችሁም ነበር፤ አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል። 11 ወዳጆች ሆይ፤ እንግዶችና መጻተኞች እንደ መሆናችሁ መጠን፣ ነፍሳችሁን ከሚዋጉ ከኅጢኣት ምኞቶች እንድትርቁ እለምናችኋለሁ። 12 ክፉ እንደምትሠሩ አድርገው ቢያሟችሁም፣ እርሱ በሚመጣበት ጊዜ መልካሙን ሥራችሁን አይተው እግዚአብሔርን እንዲያከብሩ፣ በአሕዛብ መካከል አኗኗራችሁ መልካም መሆን አለበት። 13 ስለ ጌታ ብላችሁ ለምድራዊ ባለ ሥልጣን ሁሉ ታዘዙ፤ 14 የበላይ ባለ ሥልጣን ስለ ሆነ ለንጉሥ ቢሆን፣ ወይም ክፉ አድራጊዎችን ለመቅጣት፣ በጎ አድራጊዎችን ለማመስገን እርሱ ለሾማቸው ገዦች ታዘዙ፤ 15 ምክንያቱም፣ መልካም በማድረግ የአላዋቂዎችን ከንቱ ንግግር ዝም እንድታሰኙ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው። 16 እንደ እግዚአብሔር አገልጋዮች ሆናችሁ በነጻነት ኑሩ እንጂ ነጻነታችሁን የክፋት መሸፈኛ አታድርጉት። 17 ለሰው ሁሉ ተገቢውን አክብሮት ስጡ፤ ወንድሞችን ውደዱ፤ እግዚአብሔርን ፍሩ፤ ንጉሥን አክብሩ። 18 እናንተ አገልጋዮች ፤ ለመልካሞችና ለገሮች ጌቶቻችሁ ብቻ ሳይሆን ለክፉዎችም በፍጹም አክብሮት ታዘዙ። 19 ስለ እግዚአብሔር ሲል የግፍ መከራን የሚቀበል ሰው ምስጋናን ያገኛል። 20 ክፉ ሥራ ሠርታችሁ ስትቀጡ ብትታገሡ ምን ያስመሰግናችኋል? ነገር ግን መልካም ሥራ ሠርታችሁ መከራ ስትቀበሉ ብትታገሡ ይህ በእግዚአብሔር ዘንድ ያስመሰግናችኋል። 21 የተጠራችሁት ለዚህ ነው፤ ክርስቶስ ስለ እናንተ መከራን የተቀበለው የእርሱን ፈለግ እንድትከተሉ ምሳሌ ሊተውላችሁ ነው። 22 እርሱ ኅጢአት አላደረገም፥ ተንኵልም በአፉ አልተገኘበትም፤ 23 ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም፤ መከራንም ሲቀበል አልዛተም፤ ነገር ግን በጽድቅ ለሚፈርደው ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤ 24 ለኀጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር እርሱ ራሱ በሥጋው ኀጢአታችንን በመስቀል ላይ ተሸከመ፤ በእርሱ ቊስል እናንተ ተፈውሳችኋል። 25 ቀድሞ ሁላችሁም እንደ ጠፉ በጎች ትቅበዘበዙ ነበር፤ አሁን ግን ወደ ነፍሳችሁ እረኛና ጠባቂ ተመልሳችኋል።
ጴጥሮስ አንባቢዎቹን ስለ ቅድስና እና መታዘዝ ማስተማሩን ቀጠለ ፡፡
እነዚህ የኃጢያተኛ ድርጊቶች ሰዎች ሊጥሏቸው የሚችሏቸው ነገሮች እንደሆኑ ተደርገው ተገልጻል ፡፡ እዚህ ላይ “ስለዚህ” የሚለው ቃል ጴጥሮስ ቅዱስ እና ታዛዥነትን አስመልክቶ የተናገረውን ሁሉ ይመለከታል ፡፡ አት: - “እንግዲያውስ ከዚያ አስወግደው” ወይም “እንግዲያውስ ከዚያ ያቁሙ” (ይመልከቱ: የበለስ_ማታፎር)
ጴጥሮስ አንባቢዎቹን እንደ ሕፃናት አድርጎ ተናግሯል ፡፡ ሕፃናት በቀላሉ ሊፈጩ የሚችሉ በጣም ንጹህ ምግብ ይፈልጋሉ ፡፡ በተመሳሳይም መንገድ ፣ አማኞች ከእግዚአብሄር ቃል ንጹህ ትምህርት ይፈልጋሉ ፡፡ አትቲን: - "ሕፃናት የእናታቸውን የጡት ወተት እንደሚጥሉ ፣ እንዲሁ ንጹህ መንፈሳዊ ወተት መፈለግ ይጠበቅብዎታል" (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
“ከፍተኛ ፍላጎት” ወይም “ናፍቅ”
ጴጥሮስ የእግዚአብሔርን ቃል የተናገረው ልጆችን የሚመግባቸው መንፈሳዊ ወተት ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ጴጥሮስ ስለ አማኞች ስለ እግዚአብሔር እውቀት እያደጉ ስለሄዱ እና ለእነሱም ታማኞች እንደ ሆኑ ልጆች ተናግሯል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እዚህ ለመቅመስ ማለት አንድን ነገር በግል መሞከር ማለት ነው ፡፡ አት: - “በእናንተ ላይ የጌታ ደግነት ካጋጠመዎት” (የበለስ_ማታፎር ይመልከቱ)
ጴጥሮስ ስለ አማኞች እና ስለ አማኞች ሕያው ድንጋዮች ስለመሆናቸው የሚገልፅ ዘይቤ መንገር ይጀምራል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ጴጥሮስ ኢየሱስን በህንፃ ውስጥ እንደ ድንጋይ አድርጎ ተናግሯል ፡፡ AT: - “በሕንፃ ውስጥ እንደ ድንጋይ ያለ ፣ ግን ሕያው እንጂ የሞተ ድንጋይ አይደለም” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “በሕይወት ያለው ድንጋይ ማን ነው” ወይም 2) “ሕይወት የሚሰጥ ድንጋይ” ነው ፡፡
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - "ሰዎች የተቃወሙት" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - "ሰዎች የተቃወሙት" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - "ግን እግዚአብሔር የመረጠው" (እነሆ ፣ የበለስ_ቁጥር ገደቡን ይመልከቱ)
ቅዱሳት መጻህፍት እንደ መያዣ (ኮንቴይነር) ተደርገው ተገልጻል ፡፡ ይህ ምንባብ አንድ ሰው በቅዱሳት መጻሕፍት የሚያነባቸውን ቃላት ይመለከታል ፡፡ አት: - “አንድ ነቢይ ከረጅም ጊዜ በፊት በቅዱሳት መጻህፍት ውስጥ የፃፈው ይህ ነው” (የበለስ_ማታፎርን ይመልከቱ)
እዚህ “ይመልከቱ” የሚለው ቃል ለሚከተሉት አስገራሚ መረጃዎች ትኩረት እንድንሰጥ ያሳስበናል ፡፡
ድንጋዩን የመረጠው እግዚአብሔር ነው ፡፡ አት: - “የመረጥኩት በጣም አስፈላጊ የማዕዘን ድንጋይ” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
በህንፃው ውስጥ እጅግ አስፈላጊ ድንጋይ የሆነው ነብዩ መሲህ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ጴጥሮስ ከቅዱሳት መጻሕፍት እየጠቀሰ መናገሩን ቀጠለ ፡፡
ይህ ዘይቤያዊ አነጋገር ነው ፣ ሰዎች ልክ እንደ ግንበኞች ፣ ኢየሱስን አልተቀበሉትም ፣ ግን እግዚአብሔር በሕንፃ ውስጥ በጣም አስፈላጊው ድንጋይ አድርጎታል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ግንበኞች የናቁት ድንጋይ” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ በህንፃ ውስጥ በጣም አስፈላጊውን ድንጋይ የሚያመለክት ሲሆን በመሠረቱ በ 2 6 ውስጥ “የማዕዘን ድንጋይ” አንድ ዓይነት ነው ፡፡
እነዚህ ሁለት ሐረጎች ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው ፡፡ አንድ ላይ ሰዎች አጽን emphasizeት የሚሰጡት ኢየሱስን በሚናገርበት በዚህ “ድንጋይ” ላይ ነው ፡፡ አት: - “ሰዎች የሚሰናከሉበት ድንጋይ ወይም ዐለት” (ይመልከቱ።
እዚህ “ቃሉ” የወንጌልን መልእክት ያመለክታል ፡፡ አለመታዘዝ ማለት የማያምኑ ናቸው ማለት ነው ፡፡ አት: - “ስለ ኢየሱስ የሚገልጸውን መልእክት ስላላመኑ ነው” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ጥበብ)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - "ለእነርሱም እግዚአብሔር ለእነርሱ አደረጋቸው" (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
በቁጥር 10 ላይ ጴጥሮስ ከነቢዩ ሆሴዕ አንድ ጥቅስ ጠቅሷል ፡፡ አንዳንድ ዘመናዊ ስሪቶች ይህንን እንደ ጥቅስ አይቀርፁም ፣ እሱም ተቀባይነትም ነው ፡፡
እነሱን የመረጣቸው እግዚአብሔር መሆኑን ማስረዳት ይችላሉ። አት: - “እግዚአብሔር የመረጠው ሕዝብ” (የበለስ_ቁጥርን ይመልከቱ)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “የንጉሶች ቡድን እና የካህናት ቡድን” (ዩ.አር.ቢ.) ወይም 2) “ንጉ kingን የሚያገለግሉ የካህናት ቡድን” ናቸው።
“የእግዚአብሔር ሕዝብ”
እንድትወጡ የጠራችሁ
እዚህ “ጨለማ” ሁኔታቸውን እግዚአብሔርን የማያውቁ ኃጢአተኛ ሰዎች ነው ፣ እና “ብርሃን” ሁኔታቸውን እግዚአብሔርን የሚያውቁ እና ጽድቅን የሚያደርጉትን ሰዎች ያመለክታል ፡፡ አት: - "የእግዚአብሔር የኃጢኣትነት እና የእግዚአብሔር ባለማወቅ ሕይወት እሱን እሱን እስከምናውቅ እና በሚያስደስት ሕይወት" (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ ምሕረት ፣ ለእዚህ የማይገባቸውን እግዚአብሔር በደግነት የሚሰራው ፣ አንድ ሰው በእጁ ሊቀበለው የሚችል ነገር ተደርጎ ተገልጻል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
ጴጥሮስ ክርስቲያናዊ ሕይወትን እንዴት መምራት እንዳለበት ጴጥሮስ መነጋገር ጀመረ ፡፡
እነዚህ ሁለት ቃላት በመሠረቱ አንድ ዓይነት ትርጉም አላቸው ፡፡ ጴጥሮስ አንባቢዎቹን ከቤታቸው ርቀው በባዕድ አገር እንደሚኖሩ ሰዎች ተናግሯል ፡፡ በ 1 1 ውስጥ “ባዕዳን” እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ እና በለስ_ማይታፎር)
እዚህ ላይ የሥጋ ሀሳብ የሚያመለክተው በዚህ የወደቀ ዓለም ውስጥ የሰውን ዘር ኃጢአት ሰብአዊነት ነው ፡፡ አት: - “ለኃጢአት ምኞቶች እንዳንሰጥ” (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ነፍስ” የሚለው ቃል የሰውን መንፈሳዊ ሕይወት ያመለክታል ፡፡ የአማኞችን መንፈሳዊ ሕይወት ለማጥፋት እንደሚሞክሩ ጴጥሮስ ስለ ኃጢአተኛ ምኞቶች ተናግሯል ፡፡ አት: - “መንፈሳዊ ሕይወትዎን ለማጥፋት ይፈልጉ” (የበለስ_ቁልፍ እና የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
አማኞች የማያምኑትን በሚያደርጋቸው ድርጊቶች ፋንታ አማኞች ሊኖራቸው የሚችሏቸውን ነገሮች አድርገው በመጥራት መልካም ባህሪን ስለሚያንቀሳቅሱ ተናግሯል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
ቢከሱህ
ጴጥሮስ ስለ አማኞች በጥሩ ሁኔታ ስለሚከናወነው አማኞች ሊያዩት የሚችሉት ነገር ነው ፣ ይልቁንም ክርስቲያኖችን ማየት ይችላሉ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
ይህ የሚያመለክተው እግዚአብሔር በሰዎች ሁሉ ላይ የሚፈርድበትን ቀን ነው ፡፡ ይህን የቃል ሐረግ በመጠቀም መተርጎም ይችላሉ። አት: - “በሁሉም ላይ ለመፍረድ ሲመጣ” (UDB) (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር መግለጫዎች እና የበለስ_ቁጥር)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ሰብዓዊ ባለሥልጣናትን በመታዘዝ ፣ እነዚያን ባለሥልጣናት ያቋቋመውን ጌታን እንደሚታዘዙ ወይም 2) ሰብዓዊ ባለሥልጣናትን በመታዘዝ ሰብዓዊ ባለሥልጣናትን የሚታዘዙትን ኢየሱስን እንደሚያከብሩ ነው ፡፡
“ንጉሱ እንደ ከፍተኛው ሰብዓዊ ሥልጣን”
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ንጉ to ሊቀጣው የላከው” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
"መልካም በማድረግ እናንተ ሞኞች ሰዎች ስለማያውቁት ነገር ከመናገር ያቆማሉ"
ጴጥሮስ እንደ ነፃ ሰዎች ያሉበት ሁኔታ ኃጢአተኛ ባህሪያቸውን ለመደበቅ እንደሚጠቀሙበት ነገር ተናግሯል ፡፡ አት: - “ለመጥፎ ነገር እንደ ሰበብ” (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
ይህ የሚያመለክተው ሁሉንም ክርስቲያን አማኞች ነው።
ጴጥሮስ በተለይ በሰዎች ቤት ውስጥ ላሉት አገልግሎት መነጋገር ጀመረ ፡፡
እዚህ ላይ “ጥሩ” እና “ገር” የሚሉት ቃላት ተመሳሳይ ትርጉሞችን ይጋራሉ እንዲሁም እንደነዚህ ያሉት ጌቶች አገልጋዮቻቸውን በደግነት የሚይዙ መሆናቸውን አፅን emphasizeት ይሰጣሉ ፡፡ አት: - “በጣም ደግ ጌቶች”
“ጨካኞች” ወይም “ክፉዎቹ”
ጴጥሮስ ይህንን ጥያቄ የጠየቀው አንድ መጥፎ ነገር በመሥራቱ ምክንያት የሚመሰገን ነገር እንደሌለ ለማጉላት ነው ፡፡ አት: - “በሚቀጣበት ጊዜ ምንም ዱቤ የለምና” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - "አንድ ሰው ሲቀጣዎት" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - "አንድ ሰው በሚቀጣዎት ጊዜ እርስዎ ይሰቃያሉ" (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ይህ” የሚለው ቃል ጴጥሮስ እንደገለፀው ፣ መልካም በማድረግ ላይ ሲሠቃዩ የሚያዩትን ነው ፡፡ ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ለዚህ ጠራህ” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
የክርስቶስን ፈለግ እንድትከተሉ ነው። አንድ ሰው ኢየሱስ በወሰደው ተመሳሳይ ጎዳና ላይ እየተመላለሰ እንደሚሰማው የኢየሱስን ምሳሌ ስለ መከተላቸው ተናግሯል ፡፡ አት: - “የእርሱን ምሳሌ እንድትመስሉ” (ይመልከቱ: የበለስ_ማታፎር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ማንም በአፉ ተንኮል አልተገኘም” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
“ተሳደ” የሚለው ቃል ለሌላ ሰው መሳደብ ማለት ነው ፡፡ ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - "ሰዎች ሲሰድቡት" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
በትክክል ለሚፈርድ ሰው ራሱን በአደራ ሰጠው። ይህ ማለት በኃይል በሚንከባከቧቸው ሰዎች ላይ የወሰደውን እፍረትን ለማስወገድ በእግዚአብሔር ታምኗል ማለት ነው ፡፡
ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስን ፣ በአፅን .ት ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
እዚህ ላይ “ኃጢያታችንን ተሸከመ” ማለት የኃጢያቱን ቅጣት ተቀበለ ማለት ነው ፡፡ አት: - "በዛፉ ላይ ባለው በሠራው ሥጋችን ላይ የኃጢያታችንን ቅጣት ተቀበለ" (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ይህ ከእንጨት የተሠራውን ኢየሱስ የሞተበትን መስቀል ያመለክታል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ሰዎች በመቁሰላቸው እግዚአብሔር አዳንዎታል” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ጴጥሮስ ኢየሱስን እንደ እረኛ ተናግሯል ፡፡ አንድ እረኛ በጎቹን እንደሚጠብቃቸው ሁሉ ኢየሱስም በእርሱ የሚታመኑትን ይጠብቃል። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
1 ሚስቶች ሆይ፤ እናንተም እንደዚሁ ለባሎቻችሁ ተገዙ፤ አንዳንድ ለቃሉ የማይታዘዙ ቢኖሩ እንኳ፣ ሚስቶቻቸው ቃል ሳይናገሩ በመልካም አኗኗራቸው ሊማርኳቸው ይችላሉ፤ 2 ይህም የሚሆነው ለእነርሱ ያላችሁን አክብሮት በንጹሕ አኗኗራችሁ ሲመለከቱ ነው። 3 ውበታችሁ በውጫዊ ነገሮች በመሽሞንሞን ይኸውም ሹሩባ በመሠራት፣ በወርቅ በመንቆጥቆጥ ወይም ጌጠኛ ልብስ በመልበስ አይሁን፤ 4 ነገር ግን ውበታችሁ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ፣ ገርና ጭምት መንፈስ ያለበት፣ ምንጊዜም የማይጠፋ የውስጥ ሰውነት ውበት ይሁን። 5 የቀድሞ ቅዱሳት ሴቶች የተዋቡት በዚህ ዐይነት ነበር፤ እነርሱ በእግዚአብሔር የሚደገፉና ለባሎቻቸ የሚታዘዙ ነበሩ። 6 ሣራም እንደዚሁ አብርሃምን «ጌታዬ» እያለች ትታዘዘው ነበር፣ እናንተም መከራን ሳትፈሩ መልካም ብታደርጉ፣ አሁን የእርሷ ልጆች ናችሁ። 7 እንዲሁም ባሎች ሆይ፤ ሚስቶቻችሁ ደካማ አጋር መሆናቸውን ዐውቃችሁ፣ የሕይወትን ጸጋ ከእናንተ ጋር አብረው የሚካፈሉ መሆናቸውንም ተገንዝባችሁ አብራችኋቸው ኑሩ። ጸሎታችሁ እንዳይከለከል ይህን አድርጉ። 8 በመጨረሻም፣ ሁላችሁ በአንድ ሐሳብ ተስማሙ፤ ተዛዘኑ፤ እንደ ወንድማማቾች ተዋደዱ፤ ርኅሩኆችና ትሑታን ሁኑ። 9 ክፉን በክፉ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ፤ በዚህ ፈንታ ባርኩ፤ ምክንያቱም እናንተ የተጠራችሁት በረከትን ለመውረስ ነው። 10 ስለዚህ «ሕይወትን የሚወድና መልካም ቀኖችን ሊያይ የሚፈልግ ምላሱን ከክፉ፣ ከንፈሮቹንም ተንኰል ከመናገር ይከልክል። 11 ከክፉ ይራቅ፤ መልካምንም ያድርግ፤ ሰላምን ይፈልግ፤ ይከተላትም። 12 የጌታ ዐይኖች ጻድቃንን ይመለከታሉና፤ ጆሮቹም ጸሎታቸውን ለመስማት የተከፈቱ ናቸው፤ የጌታ ፊት ግን በክፉ አድራጊዎች ላይ ነው።» 13 መልካም ነገር ለማድረግ ብትቀኑ የሚጐዳችሁ ማን ነው? 14 ነገር ግን በጽድቅ ምክንያት መከራ ቢደርስባችሁ ቡሩካን ናችሁ፤ ዛቻቸውን አትፍሩ፤ አትታወኩም። 15 ይልቁንም፣ ክርስቶስ የከበረ መሆኑን ተረድታችሁ በልባችሁ ቀድሱት። እናንተ በእግዚአብሔር ላይ ስላላችሁ መታመን ምክንያቱን ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ሁል ጊዜ የተዘጋጃችሁ ሁኑ፤ ነገር ግን ይህን ሁሉ በትሕትናና በአክብሮት አድርጉት፤ 16 በክርስቶስ ያላችሁን መልካም አናናራችሁን የሚያክፋፉ ሰዎች በሐሜታቸው እንዲያፍሩ በጎ ኅሊና ይኑራችሁ። 17 እግዚአብሔር የሚፈልገው ይህን ከሆነ፣ ክፉ ሠርቶ መከራ ከመቀበል ይልቅ መልካም አድርጎ መከራ መቀበል ይሻላል፤ 18 እንዲሁም ክርስቶስ አንድ ጊዜ ስለ ኀጢአታችን ሞቷል። ወደ እግዚአብሔር ያቀርበን ዘንድ፣ ጻድቅ የሆነው እርሱ ስለ እኛ ስለ ዐመፀኞች ሞተ፤ እርሱ በሥጋ ሞተ፤ በመንፈስ ግን ሕያው ሆነ፤ 19 በመንፈስም ሄዶ በወህኒ ቤት ለነበሩ ነፍሳት ሰበከላቸው፤ 20 በወህኒ የነበሩት እነዚህ ነፍሳት ቀድሞ በኖኅ ዘመን መርከብ ሲሠራ እግዚአብሔር በትዕግሥት ይጠብቃቸው የነበሩ እምቢተኞች ናቸው፤ እግዚአብሔር ከውሃ ያዳናቸው ጥቂት ሰዎችን፣ ይኸውም ስምንት ሰዎችን ብቻ ነበር። 21 ይህም ውሃ አሁን እናንተን የሚያድነው የጥምቀት ምሳሌ ነው፤ ይህ ጥምቀት የሰውነትን ዕድፍ ማስወገድ ሳይሆን ንጹሕ ኅሊናን ለማግኘት ወደ እግዚአብሔር የሚቀርብ ልመና ነው፤ የሚያድናችሁም በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ አማካይነት ነው፤ 22 እርሱ ወደ ሰማይ ሄዶ በእግዚአብሔር አብ ቀኝ አለ፤ መላእክት፣ ሥልጣናትና ኀይላትም ተገዝተውለታል።
አማኞች “ለሰብዓዊ ባለሥልጣን ሁሉ ታዘዙ” (2 13) እና አገልጋዮችም ለጌቶቻቸው “መገዛት” እንደሚጠበቅባቸው (2 18) ፣ ሚስቶች ለባሎቻቸው መገዛት አለባቸው ፡፡ ቃሉ “መታዘዝ” ፣ “ተገዥ መሆን ፣” እና “ማስገባት” የሚሉት ቃላት ተመሳሳይ ቃል ይተረጉማሉ ፡፡
እዚህ “ቃሉ” የወንጌልን መልእክት ያመለክታል ፡፡ አለመታዘዝ ማለት የማያምኑ ናቸው ማለት ነው ፡፡ በ 2 7 ውስጥ ተመሳሳይ ሐረግ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ አት: - “አንዳንድ ሰዎች ስለ ኢየሱስ የሚገልጸውን መልእክት አያምኑም” (ይመልከቱ ፡፡
“እነሱ በክርስቶስ እንዲያምኑ ይበረታታሉ” ይህ ማለት የማያምኑት ባሎች አማኞች ይሆናሉ ማለት ነው ፡፡ ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እነሱ አማኞች ሊሆኑ ይችላሉ” (የበለስ-ቪዲዮ እና የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ሰዎች የሚያደርጓቸው ድርጊቶች ሳይሆን ጴጥሮስ ሊታይ የሚችል ነገር እንደሆነ ጴጥሮስ ተናግሯል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “ለእነሱ ያለዎት ቅን ስነምግባር እና እነሱን የሚያከብሩበት መንገድ” (ዩ.አር.ቢ.) ወይም 2) “ለእነሱ ያለዎት ንጹህ ስነምግባር እና እግዚአብሔርን የሚያከብሩበት መንገድ” ናቸው።
“እሱ” የሚለው ቃል ሚስቶች ለባሎቻቸው መገዛት እና መምራትን ያመለክታል ፡፡
እዚህ ላይ “ውስጣዊ ሰው” እና “ልብ” የሚሉት ቃላት የአንድን ሰው ውስጣዊ ባሕርይ እና ስብዕና ያመለክታሉ ፡፡ አት: - "በውስጥህ ምን እንደሆንክ" (ተመልከት: የበለስ_ቁልፍ እና የበለስ_ቁጥር)
“ገር እና ሰላማዊ አስተሳሰብ።” እዚህ “ፀጥ” የሚለው ቃል “ሰላማዊ” ወይም “መረጋጋት” ማለት ነው ፡፡ “መንፈስ” የሚለው ቃል የአንድን ሰው ዝንባሌ ወይም ኹኔታ ያሳያል ፡፡
ጴጥሮስ እግዚአብሔርን ስለ አንድ ሰው ስለ ሰው አመለካከት በቀጥታ ከፊቱ ቆሞ እንደ ነበር ተናግሯል ፡፡ አት: - "እግዚአብሔር እንደ ውድ አድርጎ የሚቆጥረው" (የበለስ_ማይታፎርን ይመልከቱ)
እርሱ ጌታዋ ነው አለች ጌታዋ
ጴጥሮስ እንደ ሣራ ዓይነት ተግባር የሚፈጽሙ አማኞች ሴቶች እንደ ልጆ children ሊቆጠሩ ይችላሉ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ በ 3 5 ውስጥ ሣራ እና ሌሎች እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሴቶች ባሎቻቸውን እንደታዘዙ ይመለከታል ፡፡
ጴጥሮስ ሴቶችን እንደ መያዣዎች አድርጎ ይናገር ነበር ፣ ወንዶች ደግሞ አንዳንድ ጊዜ እንደሚናገሩት ፡፡ አት: - “ሚስቶች ፣ ሴት ይበልጥ ደካማ አጋር መሆኗን ተረዱ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
እዚህ “ይህ” የሚያመለክተው ባሎች ሚስቶቻቸውን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው ነው ፡፡ አት: - “ከሚስትዎ ጋር በዚህ መንገድ ኑሩ” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
“ማደናቀፍ” አንድ ነገር እንዳይከሰት ለመከላከል ነው ፡፡ ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ስለሆነም ምንም ነገር ጸሎታችሁን የሚያደናቅፍ ነገር እንዳይሆን” ወይም “ምንም እንዳታደርጉት ጸልዩ እንዳያግዳችሁ” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
"አንድ ዓይነት አመለካከት አላቸው" ወይም "ተመሳሳይ አመለካከት ይኑርዎት"
ይህ ለሌሎች ሰዎች ጥልቅ ፍቅርን ያመለክታል ፡፡
ጴጥሮስ ለሌላ ሰው ድርጊቶች ምላሽ መስጠቱ ለእነዚያ እርምጃዎች ክፍያ እንደ ማካተት ነው ፡፡ አት: - "በክፉ ላይ መልካም በሚያደርግ ሰው ላይ ወይም በክፉ በሚሰድብ ሰው ላይ ክፉን አትሥሩ" (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ለዚህ ጠራህ” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ጴጥሮስ ውርስን እንደ ተቀበለ የእግዚአብሔር በረከት እንዳገኘ ተናግሯል ፡፡ አት: - "የእግዚአብሔር በረከት እንደ ዘላቂ ርስትህ ትቀበላላችሁ" (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
እነዚህ ሁለት ሐረጎች በመሠረቱ አንድ ዓይነት ናቸው እና ጥሩ ሕይወት የመኖር ፍላጎትን ያጎላሉ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቅርብ)
“ምላስ” እና “ከንፈሮች” የሚሉት ቃላት የሚናገረውን ሰው ያመለክታሉ ፡፡ እነዚህ ሁለት ሐረጎች በመሰረታዊ ነገሮች አንድ ናቸው እና ውሸት እንዳይናገር የተሰጠውን ትእዛዝ ያጎላሉ ፡፡ አት: - “ክፉን እና አታላይ ነገሮችን መናገር አቁሙ” (የበለስ_ቁልፍ እና የበለስ_ቁልፍ_ቁጥር ይመልከቱ)
“ጆሮ” የሚለው ቃል ጌታ የሚናገረው ሰዎች የሚናገሩትን ጌታ ማወቅ ነው ፡፡ ጌታ ጥያቄዎቻቸውን እንደሚሰማ የሚያመለክተው እርሱ ለእነሱም ምላሽ እንደሚሰጥ ነው ፡፡ አት: - “ጥያቄዎቻቸውን ይሰማል” ወይም “ጥያቄዎቻቸውን ይሰጣል” (ይመልከቱ: የበለስ_ስኔ ደረት እና የበለስ_ቁጥር)
ጴጥሮስ ይህን ጥያቄ የጠየቀው አንድ ሰው መልካም ነገሮችን ካደረጉ አንድ ሰው እነሱን የሚጎዳ አይመስልም ብሎ ለማጉላት ነው ፡፡ አት: - "መልካም ነገር ብታደርጉ ማንም አይጎዳችሁም" (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህንን በቃል ሐረግ መተርጎም ይችላሉ። አት: - "ትክክል የሆነውን በማድረጉ መከራ (ሥቃይዎን ይመልከቱ)"
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ይባርክህ” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
እነዚህ ሁለት ሐረጎች ተመሳሳይ ፍቺዎችን የሚያጋሩ ሲሆን አማኞች እነሱን የሚያሳድ thoseቸውን መፍራት እንደሌለባቸው አጥብቀው ያሳያሉ ፡፡ አት: - “ሰዎች ምን ሊያደርጉልዎት እንደማይፈሩ አትፍሩ” (ይመልከቱ: የበለስ_ፓራላይሊዝም)
እዚህ “እነሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጴጥሮስ የጻፈላቸውን ሰዎች ለመጉዳት መሞከር የሚችል ማንኛውንም ሰው ነው ፡፡
“ከመፍራትና ከመረበሽ ይልቅ”
“ጌታን ክርስቶስን ለዩ… እንደ ቅዱስ” የሚለው ሐረግ የክርስቶስን ቅድስና መቀበል ማለት ነው ፡፡ ይህ እርምጃ አንድን ነገር በክብር ቦታ ያስቀመጠ ያህል ተደርጎ ይገለጻል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እዚህ ላይ አንድ ሰው ውስጣዊ ስሜትና የስሜቶች ማዕከል “ልብ” ይባላል ፡፡ አት: - "በፈቃድህ ሁሉ" (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
“እኛ” የሚለው ቃል ጴጥሮስንና አድማጮቹን ያመለክታል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
በእኛና በእግዚአብሔር መካከል የቅርብ ግንኙነት ለመፍጠር ክርስቶስ የሞተው እዚህ ላይ ጴጥሮስ ሊሆን ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሄ heል” (ዩ.አር.ቢ.) ወይም 2) “በመንፈሳዊ ሕልውናው ፣ ሄ .ል”።
“መናፍስት” የሚለው ቃል ትርጉም 1) “እርኩሳን መናፍስት” (UDB) ወይም 2) “የሙታን ሰዎች መናፍስት” ፡፡
“ትዕግሥት” የሚለው ቃል ለእግዚአብሔር ራሱ ትክክለኛ ምሳሌ ነው ፡፡ ፒተር ስለ እግዚአብሔር ትዕግሥት ግለሰባዊ አካል እንዳለው ጽ writesል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር በትዕግሥት እየጠበቀ በነበረበት ጊዜ” (የበለስ_መስጠት እና የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ) ይመልከቱ
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “በኖኅ ዘመን መርከብ እየሠራ በኖኅ ዘመን” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
እዚህ ላይ “ነፍሳት” የሚለው ቃል ሰዎችን ያመለክታል ፡፡ አት: - “ስምንት ሰዎች” (ይመልከቱ: የበለስ_ስኔክዶቼ)
ጴጥሮስ ጥምቀት እግዚአብሔር ኖኅን እና ቤተሰቦቹን በመርከቡ ውስጥ ከጥፋት ውሃ ያዳነበትን መንገድ ጋር ይዛመዳል ብለዋል ፡፡
ጥምቀት እግዚአብሔር ሰዎችን የሚያድንበት መንገድ ነው ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር አሁን የሚያድንህ ጥምቀት” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “አንድ ሰው ጥሩ ሕሊና እንዲሰጠው እግዚአብሔርን መጠየቅ” (ዩ.አር.ቢ.) ወይም 2) “የአንድ ሰው እግዚአብሔርን በጥሩ ሕሊና ፣ ማለትም በቅን ልቦና ተነሳስቶ” ማለት ነው ፡፡
"በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የተነሳ።" ይህ ሐረግ “ይህ አሁን የሚያድንልዎ የጥምቀት ምልክት ነው” ፡፡
ለኢየሱስ ክርስቶስ ተገዙ ”
1 ክርስቶስ በሥጋው መከራን ስለ ተቀበለ፣ እናንተም በዚሁ ዐላማ ታጥቃችሁ ተነሡ፤ በሥጋው መከራን የሚቀበል ሰው ኀጢአትን ትቶአል። 2 እንዲህ ያለው ሰው ከእንግዲህ በሚቀረው ዕድሜ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንጂ እንደ ሥጋ ምኞት አይኖርም። 3 አሕዛብ ፈልገው እንደሚያደርጉት በመዳራት፣ በሥጋ ምኞት፣ በስካር፣ ቅጥ ያጣ ፈንጠዝያ፣ በጭፈራና ርኵስ ከሆነ የጣዖት አምልኮ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና። 4 እነዚህን ነገሮች ለማድረግ ከአነርሱ ጋር አለመተባበራችሁ እንግዳ ሆኖባቸው ስለ እናንተ ክፉ ያወራሉ። 5 ነገር ግን እነርሱ በሕያዋንና በሙታን ላይ ሊፈርድ ለተዘጋጀው መልስ ይሰጣሉ። 6 ወንጌል ለሙታን የተሰበከው በዚህ ምክንያት ነው፤ በሥጋቸው እንደ ሰው ሁሉ ይፈረድባቸዋል፤ ነገር ግን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በመንፈስ ይኖራሉ። 7 የሁሉም ነገር መጨረሻ ተቃርቦአል፤ ስለዚህ መጸለይ እንድትችሉ ንቁ አእምሮ ይኑራችሁ፤ በአስተሳሰባችሁም ጠንቃቆች ሁኑ። 8 ፍቅር ብዙ ኀጢአትን ይሸፍናልና ከሁሉ አስቀድሞ እርስ በርሳችሁ ከልብ ተዋደዱ፤ 9 ያለ ማጒረምረም እርስ በርሳችሁ በእንግድነት ተቀባበሉ። 10 እንደ ታማኝ የእግዚአብሔር ልዩ ልዩ ጸጋ መጋቢ እያንዳንዱ ሰው በተቀበለው የጸጋ ስጦታ አንዱ ሌላውን ያገልግል፤ 11 የሚናገር ቢኖር እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር፤ የሚያገለግልም ቢኖር እግዚአብሔር በሚሰጠው ብርታት ያገልግል፤ ይኸውም እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት በሁሉም ነገር እንዲከብር ነው፤ ክብርና ኀይል ከዘላለም እስከ ዘላለም ለእርሱ ይሁን፤ አሜን። 12 ወዳጆች ሆይ፤ እንደ እሳት የሚፈትን ብርቱ መከራ ስትቀበሉ፣ እንግዳ ነገር እንደ ደረሰባችሁ በመቍጠር አትደነቁ፤ 13 ነገር ግን ክብሩ በሚገለጥበት ጊዜ ደስታችሁ ታላቅ እንዲሆን የክርስቶስ መከራ ተካፋዮች በመሆናችሁ ሐሴት አድርጉ። 14 ስለ ክርስቶስ ስም ብትሰደቡ፣ የክብር መንፈስ የሆነው የእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ላይ ስለሚያርፍ ቡሩካን ናችሁ። 15 ከእናንተ ማንም እንደ ነፍሰ ገዳይ፣ እንደ ሌባ፣ እንደ ክፉ አድራጊ ወይም በሰው ነገር ጣልቃ እንደሚገባ ሰው ሆኖ መከራን አይቀበል፤ 16 ማንም ክርስቲያን በመሆኑ መከራ ቢደርስበት፣ በዚህ ስም እግዚአብሔርን ያመስግን እንጂ አይፈር፤ 17 ፍርድ ከእግዚአብሔር ቤት የሚጀምርበት ጊዜ ቀርቦአል። እንግዲህ ፍርድ የሚጀምረው በእኛ ከሆነ፣ ለእግዚአብሔር ወንጌል የማይታዘዙ ሰዎች መጨረሻቸው ምን ይሆን? 18 እንግዲህ፣ ጻድቅ ሰው የሚድነው በጭንቅ ከሆነ፣ ዐመፀኛውና ኀጢአተኛው እንዴት ይሆን ይሆን?” 19 ስለዚህ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መከራ የሚቀበሉ መልካም እያደረጉ ነፍሳቸውን ለታመነው ፈጣሪ ዐደራ ይስጡ። ።
"በሰውነቱ ውስጥ"
“ራሳችሁን እጠቁሙ” የሚለው ሐረግ አንባቢዎቻቸውን መሣሪያቸውን ለጦርነት የሚያዘጋጁ ወታደሮችን እንዲያስቡ ያደርጋቸዋል ፡፡ እንዲሁም እንደ “አንድ ዓይነት ዓላማ” እንደ መሳሪያ ወይም ምናልባት እንደ አንድ ትጥቅ ምስል ያሳያል። እዚህ ላይ ይህ ዘይቤ ማለት አማኞች ልክ እንደ ኢየሱስ ለመሰቃየት በአዕምሮአቸው መወሰን አለባቸው ማለት ነው ፡፡ አት-“ክርስቶስ ያሳየውን ተመሳሳይ አስተሳሰብ ያዘጋጁ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር) ፡፡
እዚህ “ሥጋ” ማለት በምድር ላይ የሕይወታችን ዘመን ማለት ነው ፡፡ አት: - “እዚህ ምድር ላይ እያለሁ ሥቃይ”
ኃጢአት መሥራትን አቁሟል ”
ኃጢአተኛ ሰዎች ለሚለመዱት ምኞት
እነዚህ የዱር ፣ ወሰን የሌለው ኃጢአት ምሳሌዎች በሰዎች ላይ የሚወርዱ ታላቅ የውሃ ጎርፍ ይመስላሉ ፡፡
ገደብ የለሽ የሥጋ ምኞቶች
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “ለመፍረድ ዝግጁ የሆነው አምላክ” ወይም 2) “ለመፍረድ ዝግጁ የሆነው ክርስቶስ”
ይህ ማለት በሕይወት ያሉትም ቢሆኑም በሕይወት ያሉ ሁሉም ሰዎች ማለት ነው ፡፡ አት: - “እያንዳንዱ ሰው” (ይመልከቱ: የበለስ_ሚሻሊዝም)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “ወንጌሉ የተሰበከላቸው ቀደም ሲል ለሞቱት ሰዎች ጭምር” (ዩ.አር.ቢ.) ወይም 2) “ወንጌሉ የተሰበከ በሕይወት ላሉት ግን አሁን ለሞቱት” ነው ፡፡
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ክርስቶስ ሰበኩ ፡፡ AT: “ክርስቶስ ወንጌልን ሰበከ” (UDB) ወይም 2) ሰዎች ሰብከዋል ፡፡ አት: - “ሰዎች ወንጌልን ሰበኩ” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) እግዚአብሔር በዚህ ሕይወት በምድር ላይ ፈረደባቸው (UDB) ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር በሰው አካላቸው ፈረደባቸው” ወይም 2) ሰዎች በሰዎች መሥፈርት መሠረት ፈረደባቸው ፡፡ አት: - “ሰዎች በሰውነታቸው ውስጥ በሰው ላይ ይፈር judgedቸው ነበር” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ ሞት የፍርድ የመጨረሻ የፍርድ ዓይነት ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ በክርስቶስ ዳግም ምፅዓት የዓለም መጨረሻን ያመለክታል ፡፡
በቅርቡ ይከሰታል። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እነዚህ ሁለት ሐረጎች በመሠረቱ አንድ ዓይነት ናቸው ፡፡ የዓለም መጨረሻ ስለቀረበ ሕይወትን በግልጽ የማሰላሰልን አስፈላጊነት ጴጥሮስ ጴጥሮስን ተጠቅሞባቸዋል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቅርብ)
እዚህ ላይ ‹አስተዋይ› የሚለው ቃል የአእምሮን ግልፅነት እና ንቃትን ያመለክታል ፡፡ አት: - "ሀሳቦችዎን ይቆጣጠሩ" ወይም "ስለማያስቡበት መጠንቀቅ።" በ 1 13 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ ቪዲዮም)
ከሁሉም በጣም አስፈላጊው (ዩ.አር.ቢ.)
ጴጥሮስ “ፍቅርን” የገለጸበት መንገድ የሌሎችን ኃጢአት የሚሸፍን ሰው ነው ፡፡ ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “ለሚወደው ሰው ሌላ ሰው ኃጢአት መሥራቱን ለማወቅ አይሞክርም” ወይም 2) “ለሚወደው ሰው የሌሎችን ሰዎች ኃጢአት ይቅር ይላቸዋል ፣ እነዚያ ኃጢያቶች ብዙ ቢሆኑም” (ይመልከቱ) በለስ
ይህ የሚያመለክተው እግዚአብሔር ለአማኞች የሚሰጣቸውን ልዩ መንፈሳዊ ችሎታዎች ነው። AT: - “እያንዳንዳችሁ እንደ እግዚአብሔር ስጦታ አንድ ልዩ መንፈሳዊ ችሎታን እንደተቀበሉ” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
እንደ እግዚአብሔር ቃል የሚናገር ይናገር ”
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ስለሆነም በሁሉም መንገዶች እግዚአብሔርን ያከብራሉ” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
የተመሰገነ ፣ የተከበረ
እነዚህ ሁለት ሐረጎች በመሠረቱ አንድ ዓይነት ናቸው እና የደስታን አፅን emphasizeት ይሰጣሉ ፡፡ አት: - “የበለጠ ደስ ይበላችሁ” ወይም “እጅግ ደስ ይበላችሁ” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
ይህንን በቃል ሐረግ መተርጎም ይችላሉ። አት: - “እግዚአብሔር የክርስቶስን ክብር በሚገለጥበት ጊዜ” (የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
እዚህ ላይ “ስም” የሚለው ቃል ክርስቶስን ራሱ ያመለክታል ፡፡ ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “በክርስቶስ ስለምታምኑ ሰዎች ቢሰድቡህ” (የበለስ_ቁጥጥር እና የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ካንተ ጋር ነው
ይህ የሚያመለክተው በሌሎች ጉዳዮች ውስጥ የሚሳተፈውን ሰው መብት የለውም ፡፡
“ክርስቲያን” የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል ወይም “ሰዎች እንደ ክርስትያኖች ስላወቁት”። “ያ ስም” የሚሉት ቃላት “ክርስቲያን” የሚለውን ቃል ያመለክታሉ ፡፡
ይህ ሐረግ የሚያመለክተው ጴጥሮስ እንደ እግዚአብሔር ቤተሰብ የሚናገረውን አማኞችን ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ጴጥሮስ ይህንን ጥያቄ ከምእመናን ይልቅ ወንጌልን ለሚቃወሙ ሰዎች በጣም ከባድ እንደሚሆን ጴጥሮስ ለማጉላት ይጠቀምበታል ፡፡ አት: - በእኛ ውስጥ ከጀመረ ፣ የእግዚአብሔርን ወንጌል የማይታዘዙ መጨረሻቸው በጣም የከፋ ይሆናል ፡፡ (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
“አምላካዊ ያልሆነ ሰው” እና “ኃጢአተኛ” የሚሉት ቃላት በመሠረቱ አንድ ዓይነት ናቸው እና የእነዚህን ሰዎች ክፋት ያጎላሉ ፡፡ አት: - “ፈሪሃ አምላክ የሌላቸው ኃጢአተኞች” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
እዚህ ላይ “ነፍሳት” የሚለው ቃል መላውን ሰው ያመለክታል ፡፡ አት: - “በራሳቸው ይታመኑ” ወይም “ነፍሳቸውን አደራ አደራ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ስኔክዶቼ)
በመስራት ላይ - በመደበኛነት መልካም ነገሮችን እያከናወኑ እያለ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
1 እንግዲህ እኔም ከእነርሱ ጋር ሽማግሌና የክርስቶስ መከራ ምስክር የሆንሁ እንዲሁም ወደ ፊት የሚገለጠው ክብር ተካፋይ የምሆን በመካከላችሁ ያሉትን ሽማግሌዎች እመክራቸዋለሁ፤ 2 ስለዚህ፣ በእናንተ ዘንድ ያለውን የእግዚአብሔርን መንጋ ጠብቁ፤ የምትጠብቋቸውም ማድረግ ስላለባችሁ በግዴታ ሳይሆን፣ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በደስታ ይሁን፤ ጥቅም ለማግኘት በመስገብገብ ሳይሆን፣ በበጎ ፈቃደኝነት ይሁን፤ 3 እንዲሁም በእናንተ ኀላፊነት ሥር ላለው መንጋ መልካም ምሳሌ ሁኑ እንጂ እንደ ዐለቃ በላያቸው አትሠልጥኑ። 4 የእረኞች ዐለቃ በሚገለጥበት ጊዜ የማይጠፋውን የክብር አክሊል ትቀበላላችሁ። 5 ጕልማሶች ሆይ፤ እናንተም እንዲሁ ለሽማግሌዎች ተገዙ፤ ሁላችሁም ትሕትናን ለብሳችሁ አንዱ ሌላውን ያገልግል፤ ምክንያቱም፣ «እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፤ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል» እንደ ተባለው፣ 6 እርሱ በወሰነው ጊዜ ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከእግዚአብሔር ብርቱ እጅ በታች ራሳችሁን ዝቅ አድርጉ፤ 7 እርሱ ስለ እናንተ ስለሚያስብ የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት። 8 ጠንቃቆች ሁኑ፤ ንቁም፤ጠላታችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን በመፈለግ እንደሚያገሳ አንበሳ ወዲያ ወዲህ ይዞራል። 9 በዓለም ዙሪያ ያሉ ወንድሞቻችሁ ተመሳሳይ መከራ እንደሚቀበሉ ዐውቃችሁ በእምነት ጸንታችሁ ተቃወሙት። 10 ለጥቂት ጊዜ መከራ ከተቀበላችሁ በኋላ ፣ በክርስቶስ ወደ ዘለዓለማዊ ክብሩ የጠራችሁ የጸጋ ሁሉ አምላክ ፍጹማን ያደርጋችኋል፤ ያጸናችኋል ፤ ያበረታችኋልም። 11 የገዥነት ሥልጣን ከዘላለም እስከ ዘላለም ለእርሱ ይሁን! አሜን። 12 እንደ ታማኝ ወንድም በምቈጥረው በስልዋኖስ አማካይነት ይህን ዐጭር መልእክት ጽፌላችኋለሁ፤ የጻፍሁላችሁም ልመክራችሁና ይህ እውነተኛ የእግዚአብሔር ጸጋ መሆኑን ልመሰክርላችሁ ነው። በዚህ ጸጋ ጸንታችሁ ቁሙ። 13 ከእናንተ ጋር የተመረጠችው፣ በባቢሎን የምትገኘው ሰላምታ ታቀርብላችኋለች፤ እንዲሁም ልጄ ማርቆስ ሰላምታ ያቀርብላችኋል። 14 በፍቅር አሳሳም እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ። በክርስቶስ ላላችሁ ለሁላችሁም ሰላም ይሁን።
ጴጥሮስ በተለይ ሽማግሌዎች ለሆኑት ወንዶች ተናግሯል።
"የሚካፈል" ወይም "የሚሳተፍ"
ይህ ስለ ክርስቶስ ዳግም ምጽዓት ማጣቀሻ ነው ፡፡ ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ስለሚገለጥለት የክርስቶስ ክብር” (የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ጴጥሮስ አማኞችን እንደ በግ መንጋ ፣ ሽማግሌዎችንም እንደሚንከባከቧቸው እረኞች ተናግሯል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
"ይንከባከቧቸው"
ሽማግሌዎች ምሳሌ በመሆን መምራት አለባቸው እንጂ ለአገልጋዮቹ ጨካኝ ጌታን እንደሚያደርጉት አይደለም ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህን የቃል ሐረግ በመጠቀም መተርጎም ይችላሉ። አት: - ለሚንከባከቡት ”(ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያ)
ጴጥሮስ ኢየሱስን ሁሉ በእረኞች ሁሉ ላይ የበላይነት እንዳለው እረኛ ነው ፡፡ ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “የእረኞች አለቃ ኢየሱስ በሚገለጥበት ጊዜ” ወይም “እግዚአብሔር የእረኞች አለቃ” እግዚአብሔር ሲገለጥ (ይመልከቱ ፡፡
እዚህ ላይ “ዘውድ” የሚለው ቃል አንድ ሰው የድልን ምልክት አድርጎ የሚቀበለውን ሽልማት ይወክላል ፡፡ “የማይሠራ” የሚለው ቃል ዘላለማዊ ነው ማለት ነው ፡፡ አት: - “ለዘላለም የሚከበረው ክቡር ሽልማት” (fig :_metaphor)
ክቡር
ጴጥሮስ በተለይ ለወጣቶች መመሪያን ሰጠ እና ከዚያም ሁሉንም ምእመናን ማስተማሩን ቀጥሏል ፡፡
ይህ በ 5 1 ውስጥ ሽማግሌዎች ለታላላቂው እረኛ ያስረከቡበትን መንገድ ይመለከታል ፡፡
ይህ ወጣት አማኞችን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም አማኞችን ይመለከታል።
ጴጥሮስ ልብሱን እንደለበሰ ትሕትናን የሞራል ጥራት እንዳለው ተናግሯል። አት-“አንዳችሁ ለሌላው በትሕትና እርምጃ ውሰዱ” (UDB) ወይም “በትሕትና እርምጃ ይውሰዱ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
እዚህ ላይ “እጅ” የሚለው ቃል ትሑታን ለማዳን እና ኩራተኞችን ለመቅጣት የእግዚአብሔርን ኃይል ያመለክታል ፡፡ አት: - “በእግዚአብሔር ታላቅ ኃይል” ወይም “ታላቅ ኃይል እንዳለው በመገንዘብ” በእግዚአብሔር ፊት (ይመልከቱ። የበለስ.
ጴጥሮስ ጭንቀትን አንድ ሰው እራሱን ከመሸከም ይልቅ በእግዚአብሔር ላይ እንደሚጭን ከባድ ሸክም ነው ፡፡ አት: - “በሚያስጨንቁዎት ነገሮች ሁሉ ይታመኑ” ወይም “የሚያስጨንቁዎን ነገሮች ሁሉ ይንከባከበው” (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ ‹አስተዋይ› የሚለው ቃል የአእምሮን ግልፅነት እና ንቃትን ያመለክታል ፡፡ አት: - "ሀሳቦችዎን ይቆጣጠሩ" ወይም "ስለምያስቡበት መጠንቀቅ።" በ 1 13 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ ቪዲዮም)
ጴጥሮስ ዲያብሎስን ከሚያገሳ አንበሳ ጋር አነጻጽሮታል ፡፡ አንድ የተራበ አንበሳ ምርኮውን ሙሉ በሙሉ እንደሚበላ ሁሉ ዲያቢሎስም የአማኞችን እምነት ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ይፈልጋል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ሲሚል)
"መራመድ" ወይም "መራመድ እና አደን"
“ተቃወሙት” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ጥበብ)
ጴጥሮስ የእምነት አጋሮቹን የአንድ ማህበረሰብ አባላት እንደሆኑ ተናግሯል ፡፡ አት: - “የእምነት ባልንጀሮችዎ” (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
የጴጥሮስ ደብዳቤ መጨረሻ ይህ ነው ፡፡ እዚህ ስለ ደብዳቤው እና ስለ መደምደሚያው ሰላምታ የመጨረሻዎቹን አስተያየቶች ይሰጣል ፡፡
እዚህ ላይ “ጸጋ” የሚለው ቃል እግዚአብሔር የሚሰጣቸውን ወይም የእግዚአብሔርን ባሕርይ ሊያመለክት ይችላል ፡፡ ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “ሁል ጊዜ የምንፈልገውን የሚሰጠን አምላክ” ወይም 2) “ሁልጊዜ ቸር የሆነው” አምላክ ናቸው ፡፡
"መልሶ እመልስሃለሁ" ወይም "እንደገና ጤናን እሰጥሃለሁ"
እነዚህ ሁለት አገላለጾች ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው ፣ ማለትም ፣ እግዚአብሔር አማኞች በእርሱ እንዲታመኑ እና ምንም ዓይነት መከራ ቢደርስባቸውም እሱን እንዲታዘዙ ያስችላቸዋል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ሲልቫነስ ጴጥሮስ በደብዳቤው ውስጥ እንዲጽፍ የነገረውን ቃል ጻፈ ፡፡
“እሱ” የሚለው ቃል “እውነተኛውን የእግዚአብሔር ጸጋ” ያመለክታል ፡፡ ለዚህ ጸጋ በጥብቅ መፀለይ በአንድ ቦታ ጸንቶ መቆየት ፣ መንቀሳቀስን አለመቀበል ተብሎ ተገልጻል ፡፡ አት: - "ሙሉ በሙሉ ለእሱ ተወስዱ" (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
እዚህ “ሴቲቱ” ምናልባት ምናልባት በ “ባቢሎን” የሚኖሩትን አማኞች ቡድን ያመለክታል ፡፡ ለ “ባቢሎን” ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) እሱ ለሮሜ ከተማ ምልክት ነው ፣ 2) ክርስቲያኖች ለሚሰቃዩበት ቦታ ሁሉ ምልክት ነው ፣ ወይም 3) በጥሬው የሚያመለክተው የባቢሎን ከተማ ነው ፡፡ እሱ ምናልባት የሚያመለክተው የሮምን ከተማ ነው። (ይመልከቱ: መጻፍ_ጽሑፍ ቋንቋ)
ጴጥሮስ ስለ ማርቆስ ስለ መንፈሳዊ ልጁ ተናግሯል ፡፡ አት: - “መንፈሳዊ ልጄ” ወይም “ለእኔ ልጅ የሆነው ማን ነው?” (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
አንዳችሁ ለሌላው ያላችሁን ፍቅር ለማሳየት “አፍቃሪ መሳም” ወይም “መሳሳም” (የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያ)
1 ክርስቶስ አገልጋይና ሐዋርያ ከሆነው ስምዖን ጴጥሮስ፤ በአምላካችንና በአዳኛችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ አማካይነት የተቀበልነውን ዐይነት ክቡር እምነት ለተቀበሉት፤ 2 እግዚአብሔርንና ጌታችንን ኢየሱስን በማወቅ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ። 3 በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን እግዚአብሔርን በማወቅ እንድንኖር ለሕይወትና ለእውነተኛ መንፈሳዊነት የሚያስፈልገን ሁሉ በመለኮቱ ኀይል ተሰጥቶናል። 4 በእነዚህ ነገሮች አማካይነት እጅግ የከበረና ታላቅ ተስፋ ሰጠን፤ ይህንም ያደረገው በክፉ ምኞቶች ሰበብ በዓለም ካለው ምግባረ ብልሹ ሕይወት አምልጣችሁ ከመለኮታዊ ባሕርይ ተካፋዮች እንድትሆኑ ነው። 5 በዚህም ምክንያት፣ የሚከተሉትን ነገሮች ለመጨመር ትጉ፣ በእምነታችሁ ላይ ደግነትን፣ በደግነት ላይ ዕውቀትን፣ 6 በዕውቀት ላይ ራስን መግዛት፣ ራስን በመግዛት ላይ መጽናትን፣ በመጽናት ላይ እግዚአብሔርን መምሰልን፤ 7 እግዚአብሔርን በመምሰል ላይ ላይ ወንድማዊ መዋደድን፣ በወንድማዊ መዋደድ ላይ ፍቅርን ጨምሩ። 8 እነዚህ ነገሮች በውስጣችሁ ቢኖሩና በውስጣችሁ ቢያድጉ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በማወቅ ዳተኞችና ፍሬ ቢሶች እንዳትሆኑ ያደርጉአችኋል። 9 እነዚህ ነገሮች የሌሉት ግን ዕውር ነው፤ በቅርብ ያለውን ብቻ ያያል፤ ከቀድሞው ኀጢአቱ መንጻቱንም ረስቶአል። 10 ስለዚህ ወንድሞች ሆይ፤ መጠራታችሁንና መመረጣችሁን ለማጽናት ትጉ፤ ይህን ብታደርጉ ከቶ አትሰናከሉም፤ 11 በዚህም ወደ ጌታችንና አዳኛችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘላለማዊ መንግሥት መግባት በሙላት ይሰጣችኋል። 12 ስለዚህ ምንም እንኳ እነዚህን ነገሮች ብታውቋቸውና በያዛችሁት እውነት ብትጸኑም፣ ስለ እነዚህ ነገሮች ዘወትር እናንተን ከማሳሰብ ቸል አልልም። 13 በዚህ ምድራዊ ድንኳን ውስጥ እስካለሁ ድረስ ስለ እነዚህ ነገሮች እናንተን ማሳሰብ ትክክል ነው ብዬ አስባለሁ፤ 14 ምክንያቱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ገለጠልኝ ይህን ምድራዊ ድንኳን ቶሎ ለቅቄ እንደምሄድ ዐውቃለሁ፤ 15 ከተለየኋችሁም በኋላ እነዚህን ነገሮች ዘወትር እንድታስቡ የተቻለኝን ሁሉ አደርጋለሁ። 16 ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኀይልና ስለ ዳግም መምጣቱም በነገርናችሁ ጊዜ ግርማውን በዐይናችን አይተን መሰከርን እንጂ በብልሃት የተፈጠረውን ተረት ተከትለን አይደለም። 17 «በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው» የሚል ድምፅ ከግርማዊው ክብር በመጣለት ጊዜ፣ ከእግዚአብሔር አብ ክብርንና ሞገስን ተቀብሎአል። 18 ከእርሱ ጋር በተቀደሰው ተራራ ላይ በነበርንበት ጊዜ ይህን ከሰማይ የመጣውን ድምፅ ሰምተነዋል። 19 ትንቢታዊው ቃል ይበልጥ ተረጋግጦልናል፤ ሌሊቱ እስኪነጋ ድረስ በጨለማ ስፍራ ለሚያበራ መብራት እንደምትጠንቀቁ፣ የንጋቱ ኮከብ በልባችሁ እስኪበራ ድረስ ለዚህ ቃል ብትጠነቀቁ መልካም ታደርጋላችሁ። 20 ይህን በመጀመሪያ ዕወቁ፤ በቅዱሳት መጻሕፍት የሚገኘውን የትንቢት ቃል ማንም ሰው በራሱ መንገድ የሚተረጒመው አይደለም፤ 21 ምክንያቱም ትንቢት ከእግዚአብሔር የተላኩ ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተመርተው ተናገሩት እንጂ ከቶ በሰው ፈቃድ የመጣ አይደለም።
ጴጥሮስ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ስለመሆኑ ተናግሯል ፡፡ በተጨማሪም የክርስቶስ ሐዋርያ የመሆን ቦታና ስልጣን ተሰጥቶታል ፡፡
ጴጥሮስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እውነቱን የተናገረው አማኞች በእውነቱ ተቀባይነት ሊያገኙበት ስለሚችሉት ነገር ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
ለተቀበላችሁት ይህንን ደብዳቤ ሊያነቡ የሚችሉ አማኞችን ሁሉ ጴጥሮስ ይነግራቸዋል ፡፡
እዚህ ላይ እኛ “እኛ” የሚለው ቃል ጴጥሮስንና ሌሎቹን ሐዋርያት የሚያመለክት ነው ፣ እሱ ግን የጻፈላቸውን ሰዎች አይደለም ፡፡ አት: - እኛ “እኛ ሐዋርያት ተቀበልን” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ለአማኞች ጸጋን እና ሰላምን የሚሰጥ እግዚአብሔር ነው ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ጸጋህንና ሰላምህን ይጨምርልህ” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
እዚህ “አምላካዊነት” “ሕይወት” የሚለውን ቃል ያብራራል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔርን ለሚፈራ ሕይወት” (የበለስ_አንድአዴዲስን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል ጴጥሮስንና አድማጮቹን ያመለክታል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እዚህ “እነዚህ” የሚያመለክቱት “የራሱን ክብር እና በጎነት” ነው።
እግዚአብሔር ምን እንደሚመስል
ዓለም እንዲጠፋ የተደረገው ምክንያቶች በዓለም ላይ እንደ ዕቃ ተደርገው ተገልፀዋል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
ይህ በቀደሙት ቁጥሮች ላይ ጴጥሮስ የተናገረውን ያመለክታል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ባደረገው ነገር ምክንያት” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
"የሞራል ልዕልና"
ይህ ለጓደኛ ወይም ለቤተሰብ አባል ፍቅርን የሚያመለክት ሲሆን ምናልባትም ምናልባት መንፈሳዊ ቤተሰቦቻቸውን መውደድ አለባቸው ማለት ነው ፡፡
ይህ የሚያመለክተው ቀደም ባሉት ጥቅሶች ላይ ጴጥሮስ የጠቀሳቸውን እምነት ፣ በጎነት ፣ እውቀት ፣ ራስን መግዛትን ፣ ጽናትን ፣ አምላካዊነትን ፣ ወንድማዊ ፍቅርን እና ፍቅርን ነው ፡፡
ጴጥሮስ ሰብል የማያስፈራው እርሻ እንደሌለው መስክ እነዚህን ባሕርያት ስለሌለው ሰው ተናግሯል ፡፡ ይህ በአዎንታዊ ሁኔታ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ትፈጫለሽ ፣ ፍሬያማም ትኖራላችሁ” ወይም “ውጤታማ ትሆናላችሁ” (ይመልከቱ።
እነዚህ ቃላት በመሠረቱ አንድ ዓይነት ትርጉም ያላቸው ሲሆን ይህ ሰው ኢየሱስን በማወቅ ፍሬያማ እንደማይሆን ወይም ምንም ጥቅም እንደማይሰጡት የሚያጎሉ ናቸው ፡፡ አት: - “ፍሬ አልባ” (ይመልከቱ: የበለስ_አድራሻ)
የቃል ሐረግን በመጠቀም “ዕውቀት” ን መተርጎም ይችላሉ። አት: - "እግዚአብሔርን በማወቁና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል።" በ ውስጥ ተመሳሳይ ሐረግ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
እነዚህ ነገሮች የሌሉት ማንኛውም ሰው
“መደወል” እና “ምርጫ” የሚሉት ቃላት ተመሳሳይ ትርጉምዎችን የሚያጋሩ ሲሆን እግዚአብሔር የእሱ እንዲሆኑ የመረጣቸውን ያመለክታሉ ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር የእሱ እንድትሆኑ የመረጣችሁን በእርግጥ ያረጋግጡ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
“መደወል” እና “ምርጫ” የሚሉት ቃላት ተመሳሳይ ትርጉምዎችን የሚያጋሩ ሲሆን እግዚአብሔር የእሱ እንዲሆኑ የመረጣቸውን ያመለክታሉ ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር የእሱ እንድትሆኑ የመረጣችሁን በእርግጥ ያረጋግጡ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ AT: - “እግዚአብሔር ወደ ዘላለሙ ወደ ጌታችንና አዳኛችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዘላለማዊ መንግሥት የመግቢያ በር ይከፍቶልዎታል” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ለመግባት እድሉ
እዚህ ላይ “እነዚህ ነገሮች” የሚሉት ቃላት ቀደም ባሉት ቁጥሮች ውስጥ ጴጥሮስ የተናገረውን ሁሉ ነው ፡፡
'የእነዚህን ነገሮች እውነት አጥብቀህ ታምናለህ'
እዚህ ‹‹ ‹›››››› የሚለው ቃል አንድን ሰው ከእንቅልፉ ለማስነሳት ማለት ነው ፡፡ ጴጥሮስ አንባቢዎቹ ስለ እነዚህ ነገሮች ከእንቅልፋቸው የሚያነቃቃ ይመስላቸዋል ብለው እንዲያስቡ ያደርጋቸዋል ፡፡ አት: - ስለ እነዚህ ነገሮች እንዲያስታውሱ ለማስቻል ”(ተመልከት: የበለስ_ማይታፎር)
ጴጥሮስ ሰውነቱን የሚያስወግደው ድንኳን ይመስል ስለ ሰውነቱ ተናግሯል ፡፡ እነዚህ ሐረጎች የእርሱን ሞት ያመለክታሉ ፡፡ አት-“በሕይወት እስካለሁ ድረስ እሞታለሁ” (ይመልከቱ ፡፡
ሁልጊዜ እንዲያስታውስዎ ለማድረግ "
እዚህ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጴጥሮስንና ሌሎቹን ሐዋርያት ነው ፣ ግን ለአንባቢዎቹ አይደለም ፡፡ አት: - “እኛ እኛ ሐዋርያቶች የተዋዋሉ ታሪኮችን አልከተሉም ነበር” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
እዚህ “መታየት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የኢየሱስን ዳግም ምጽዓት ነው ፡፡ ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል እና መምጣቱ” ወይም 2) “የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ኃያል መምጣት” ናቸው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ዋንድአዲስ)
እዚህ “የእኛ” የሚለው ቃል ሁሉንም አማኞችን ይመለከታል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት-“ከታላቁ ክብር ድምፅ ሲመጣ” ወይም “ከታላቁ ክብር በተናገረው ጊዜ” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
የቃላቱ ድምፅ
ጴጥሮስ እግዚአብሔርን ከክብሩ አንፃር ጠቅሷል ፡፡ ይህ ለእሱ ካለው አክብሮት የተነሳ የአምላክን ስም ከመጠቀም የሚርቅ ርኩሰት ነው ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ፣ ልዑሉ ክብር” (የበለስ_ቁልፍ እና የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ጴጥሮስ ራሱንና የእግዚአብሄርን ድምጽ የሰሙትን ደቀ መዛሙርቱን ያዕቆብንና ዮሐንስን እየተናገረ ነው ፡፡
“ከኢየሱስ ጋር ነበርን”
ቀደም ባሉት ቁጥሮች ላይ ጴጥሮስና ሌሎቹ ሐዋርያት የገለ thingsቸው ነገሮች ነቢያት የተናገሩትን ያረጋግጣሉ ፡፡ ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ያየነው ይህ ትንቢታዊ ቃል ይበልጥ የተረጋገጠ ያደርገዋል” (የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
እዚህ ላይ እኛ “እኛ” የሚለው ቃል ጴጥሮስንና አንባቢዎቹን ጨምሮ ሁሉንም አማኞች ያመለክታል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ ብሉይ ኪዳንን ይመለከታል ፡፡ አት: - “ነቢያት የተናገሩባቸው ቅዱሳን መጻሕፍት” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
ጴጥሮስ ትንቢታዊ ቃልን ጠዋት እስከሚመጣ ድረስ በጨለማ ውስጥ ከሚበራ መብራት ጋር አመሳስሎታል ፡፡ የንጋት መምጣት የክርስቶስን መምጣት የሚያመለክቱ ናቸው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ሲሚል)
ጴጥሮስ ጎህ ሲቀድና የጨለማው መጨረሻ እንደቀረበ የሚያመለክተው ክርስቶስን “የንጋት ኮከብ” ነው ፡፡ ክርስቶስ በአማኞች ልብ ውስጥ ብርሀን ያመጣላቸዋል ፣ ጥርጣሬውን ሁሉ ያበቃል እና ስለ ማንነቱ ሙሉ ግንዛቤን ያመጣል። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
“የጠዋት ኮከቡ” የሚያመለክተው ፀሐይ ከጠለቀችበት ጊዜ የሚነሳ ሲሆን የንጋት ቀንም መሆኗን ነው ፡፡
ይህ ምንባብ በብዙ መንገዶች ሊረዳ ይችላል-1) ነብያቶቻቸው ትንቢቶቻቸውን በራሳቸው (ኦ.ቢ.ቢ.) አላደረጉም ፡፡ 2) ሰዎች ትንቢቶቹን ለመረዳት በመንፈስ ቅዱስ ላይ መታመን አለባቸው ፣ 3) ሰዎች ትንቢቶችን በጠቅላላው የክርስቲያን አማኞች ማኅበረሰብ እገዛ መተርጎም አለባቸው ፡፡
መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር እንዲናገሩ የሚፈልገውን እንዲናገሩ ሰዎችን ይመራቸዋል ፡፡ ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ AT: - “ሰዎች መንፈስ ቅዱስ ይዘውት እንደሄዱ የእግዚአብሔር ሰው ተናገሩ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
መንፈስ ቅዱስ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ የሚወስድባቸው እግዚአብሔር እንዲጽፉ የሚፈልገውን እንዲጽፉ የሚፈልገውን እንዲጽፉ ጴጥሮስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ተናግሯል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
1 ሐሰተኞች ነቢያት በእስራኤላውያን መካከል ነበሩ፤ በእናንተ መካከል ደግሞ ሐሰተኞች መምህራን ይኖራሉ፤ እነርሱ ጥፋትን የሚያስከትል ሐሰተኛ ትምህርት በስውር ያስገባሉ፤ የዋጃቸውንም ጌታ ክደው ፈጣን ጥፋትን በራሳቸው ላይ ያመጣሉ። ብዙዎች የእነርሱን መዳራት ይከተላሉ። 2 ከእነርሱም አድራጎት የተነሣ የእውነት መንገድ ይሰደባል። 3 እነዚህ ሐሰተኞች መምህራን ለገንዘብ ከመስገብገባቸው የተነሣ የሚያታልሉ ቃላትን በመጠቀም ይበዘብዙአችኋል። በእነርሱ ላይ ያለው ፍርድ አይዘገይም፤ መጥፊያቸውም የራቀ አይደለም። 4 እግዚአብሔር ኀጢአት የሠሩትን መላእክት ሳይራራላቸው ወደ ገሐነም ከጣላቸውና በሰንሰለት አስሮ እስከ ፍርድ ጊዜ ድረስ በጨለማ ውስጥ ካስቀመጣቸው፣ 5 የጽድቅ ሰባኪ የነበረውን ኖኅን ከሌሎች ሰባት ሰዎች ጋር አድኖ ለጥንቱ ዓለም ሳይራራ በኀጢአተኞች ላይ የጥፋት ውሃ ካመጣ፣ 6 ደግሞም ኀጢአት በሚያደርጉ ሁሉ ላይ የሚመጣው ጥፋት ምሳሌ እንዲሆኑ የሰዶምንና የገሞራን ከተሞች ዐመድ እስኪሆኑ ድረስ አቃጥሎ ከፈረደባቸው፣ 7 በሕገ ወጦች ሴሰኝነት ነፍሱ እየተጨነቀ ይኖር የነበረውን ጻድቁን ሎጥን ግን አዳነው፤ 8 ያ ጻድቅ ሰው በመካከላቸው ሲኖር በየቀኑ ያየውና ይሰማው በነበረው ሕገ ወጥ ድርጊታቸው ጻድቅ ነፍሱ ትጨነቅ ነበር። 9 ጌታ፣ እግዚአብሔርን የሚመስሉትን ሰዎች ከፈተና እንዴት እንደሚያድናቸውና ዐመፀኞችን እየቀጣ ለፍርድ ቀን እንዴት ጠብቆ እንደሚያቈያቸው ያውቃል። 10 በተለይም ብልሹ የሥጋ ምኞታቸውን የሚከተሉትንና ሥልጣንን የሚንቁትን ለፍርድ ጠብቆ ያቈያቸዋል። እነዚህ ሰዎች ደፋሮችና እብሪተኞች ስለ ሆኑ የከበሩትን ሲሳደቡ አይፈሩም፤ 11 መላእክት ከሰዎች ሁሉ ይልቅ ብርታትና ችሎታ ያላቸው ሆነው ሳሉ፣ በጌታ ፊት በእነርሱ ላይ ዘለፋ ያዘለ የፍርድ ቃል አይሰነዝሩም። 12 እነዚህ አእምሮ እንደ ጎደላቸው እንስሳት ለምርኮና ለጥፋት የተፈጠሩ ናቸው፤ የሚሳደቡትን ስለማያውቁ ይጠፋሉ። 13 እነርሱ የዐመፃቸውን ዋጋ ይቀበላሉ፤ በቀን በመስከርና ያለ ልክ በመፈንጠዝ ይኖራሉ ፤ እነርሱ አሳፋሪዎችና ነውረኞች ናቸው። ከእናንተ ጋር ግብዣ ላይ ሲገኙ፣ በአታላይ ፈንጠዝያቸው ሐሴት ያደርጋሉ። 14 ዐይናቸው ቅንዝር የተሞላ በመሆኑ ኀጢአትን ከመሥራት ከቶ አይቈጠቡም፤ ጽኑ ያልሆኑትን ሰዎች ያስታሉ፤ መመኘትን የለመደ ልብ አላቸው፤ የተረገሙ ልጆች ናቸው። 15 ቀናውን መንገድ ትተው፣ በክፉ ሥራ የሚገኘውን ገንዘብ የወደደውን የቢዖርን ልጅ የበለዓምን መንገድ ተከትለው ስተዋል፤ 16 እርሱ ስለ መተላለፉ ተገሥጾአል፤ መናገር የማይችል አህያ በሰው ቋንቋ ተናግሮ የነቢዩን እብደት አስቍሟልና። 17 እነዚህ ሰዎች እንደ ደረቁ ምንጮችና በዐውሎ ነፋስ እንደሚነዱ ደመናዎች ናቸው፤ የሚጠብቃቸውም ድቅድቅ ጨለማ ነው፤ 18 ፍሬ ቢስ የዕብሪት ቃል በመናገር፥ በሥጋዊ ፍትወታቸው ሰዎችን ያጠምዳሉ፤ ከተሳሳተና ከብልሹ የሕይወት ዘይቤ ለማምለጥ የሚሞክሩትን ሰዎች ያጠምዳሉ። 19 እነርሱ ራሳቸው የጥፋት ባሪያዎች ሆነው ሳሉ፣ ሌሎችን ነጻ ትወጣላችሁ እያሉ ተስፋ ይሰጧቸዋል፤ ሰው ለሚሸነፍለት ለማንኛውም ነገር ባሪያ ነውና። 20 ጌታችንንና አዳኛችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በማወቅ ከዓለም ርኵሰት ካመለጡ በኋላ፣ እንደ ገና ወደ ቀደሞው የርኵሰት ሕይወት ቢመለሱ፣ ከመጀመሪያው ይልቅ የኋለኛው የከፋ ይሆንባቸዋል። 21 የጽድቅን መንገድ ካወቁ በኋላ ከተሰጣቸው ቅዱስ ትእዛዝ ወደ ኋላ ከሚመለሱ፣ ቀድሞውኑ የጽድቅን መንገድ ባያውቋት ይሻላቸው ነበር። 22 «ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል» እንዲሁም «ዐሣማ ቢታጠብም ተመልሶ በጭቃ ላይ ይንከባለላል» የሚለው ምሳሌ እውን ይሆንባቸዋል።
ሐሰተኛ ነቢያት እስራኤልን በቃላቸው እንደሚያታልሉ ሁሉ ፣ ሐሰተኛ አስተማሪዎችም ስለ ክርስቶስ ውሸት እያስተማሩ ይመጣሉ ፡፡
‹መናፍቅ› የሚለው ቃል ከክርስቶስ እና ከሐዋርያት ትምህርት ጋር የሚቃረኑ አስተያየቶችን ያመለክታል ፡፡ እነዚህ መናፍቃን የሚያምኑትን እምነት ያጠፋሉ ፡፡
እዚህ ላይ “ጌታ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ባሪያዎች የሆኑትን ነው ፡፡ ጴጥሮስ ኢየሱስን የገዛው የሰዎች ባለቤት እንደሆነ በመግለጽ ዋጋው የእሱ ሞት ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር)
“ሥነ ምግባር የጎደለው ወሲባዊ ባህሪ”
“የእውነት መንገድ” የሚለው ሐረግ የክርስትናን እምነት ወደ እግዚአብሔር እውነተኛ ጎዳና መሆኑን ያሳያል ፡፡ ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “የማያምኑ የእውነትን መንገድ ይሰድባሉ” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
"ውሸት በመናገር ገንዘብ እንዲሰጡዎ ያሳምኑዎታል"
ጴጥሮስ ስለ “ኩነኔ” እና “ጥፋት” የሚናገሩ ሰዎች እንደሆኑ አድርገው ተናግሯል ፡፡ ሁለቱ ሐረጎች በመሠረቱ አንድ ዓይነት ትርጉም ያላቸው ሲሆን ሐሰተኛ አስተማሪዎች ምን ያህል በቅርቡ እንደሚኮንኑ አፅን emphasizeት ይሰጣሉ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ከዋክብት እና የበለስ_ተመሳሳዩ)
እነዚህን ሐረጎች በአዎንታዊ ቃላት ከትርጓሜዎች ጋር መተርጎም ይችላሉ። አት: - "እግዚአብሔር በቅርቡ ይቀጣቸዋል ፤ ሊያጠፋቸው ዝግጁ ነው" (የበለስ_ቁጥር አሃዶች እና የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
"ከመቅጣት አልተቆጠበም" ወይም "አልተቀጣም"
“ታርታር” የሚለው ቃል ከግሪክ ሃይማኖት የመጣ ቃል እርኩሳን መናፍስት እና የሞቱት ክፉ ሰዎች የሚቀጡበትን ስፍራ የሚያመለክት ነው ፡፡ አት: - “ወደ ሲ hellል ጣላቸው” (ይመልከቱ: መተርጎም_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “በጨለማ ጨለማ ሰንሰለቱ ውስጥ የሚያደርጋቸው ቦታ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “በጣም በጨለማ ቦታ ውስጥ በሰንሰለት ውስጥ” ወይም 2) “እንደ ሰንሰለቶች በሚታሰሩ በጣም ጥልቅ ጨለማ ውስጥ” ናቸው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ የሚያመለክተው እግዚአብሔር በእያንዳንዱ ሰው ላይ የሚፈርድበትን የፍርድ ቀን ነው ፡፡
እዚህ ላይ “ዓለም” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በውስጡ የነበሩትን ሰዎች ነው ፡፡ አት: - “በጥንቱ ዓለም ይኖሩ የነበሩትን ሰዎች አልታደጋቸውም” (ይመልከቱ።
በጥንት ዓለም የነበሩትን ቀሪ ሰዎች ሲያጠፋ እግዚአብሔር ኖኅንና ሌሎች ሰባት ሰዎችን አላጠፋም ፡፡
“የሰዶምንና የገሞራን ከተሞች አመድ ብቻ እስኪያልፍ ድረስ በእሳት አቃጠሉ”
እዚህ ላይ “እነሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሰዶምን እና ገሞራን እንዲሁም በውስጣቸው የነበሩትን ሰዎች ነው ፡፡
ሰዶምና ገሞራ እግዚአብሔርን የማይታዘዙ በሌሎች ላይ ስለሚሆነው ነገር ምሳሌ እና ማስጠንቀቂያ ሆነው ያገለግላሉ ፡፡
“የእግዚአብሔርን ሕግ የጣሱ የወንዶች ብልሹ ምግባር”
ይህ የሚያመለክተው ሎጥን ነው ፡፡
እዚህ ላይ "ነፍስ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው የሎጥን አስተሳሰብ እና ስሜቶች ነው ፡፡ የሰዶምና የገሞራ ዜጎች ሥነ ምግባር የጎደለው ባህሪ በስሜታዊነት አዝነውት ነበር ፡፡ አት: - “እጅግ ተጨንቆ ነበር” (ይመልከቱ። የበለስ_ስኔክዶቼ)
“ይህ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔር በ 2: 7 ውስጥ የፍርድ ቀንን እስር ቤት እስኪያቆዩ ድረስ ነው ፡፡
እዚህ ላይ “የሥጋ ምኞቶች” የሚለው ሐረግ የኃጢያተኛ ተፈጥሮ ፍላጎቶችን ያሳያል ፡፡ አት: - “ብልሹ እና ኃጢአተኛ ምኞታቸውን ማቅረታቸውን የሚቀጥሉ”
ለእግዚአብሔር ሥልጣን ለመገዛት እምቢ አሉ ፡፡ እዚህ ላይ “ስልጣን” የሚለው ቃል ምናልባት የእግዚአብሔርን ስልጣን ያመለክታል ፡፡
እዚህ “ስልጣን” ትዕዛዙን የመስጠት እና አለመታዘዝን የመቅጣት መብት ያለው ለእግዚአብሔር ነው። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
ምኞት - "ማድረግ የሚፈልጉትን ሁሉ ያድርጉ"
ይህ ሐረግ መላእክትን ወይም አጋንንትን ያሉ መንፈሳዊ ፍጡራንን ይመለከታል ፡፡
ለተጠቀሱት ሰዎች ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ክብር ያላቸው ወይም 2) ሐሰተኛ አስተማሪዎች ናቸው ፡፡
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እነዚህ አእምሮ የጎደላቸው እንስሳት በተፈጥሮ የተወለዱ ናቸው” (የበለስ_ቁጥጥር ይመልከቱ)
እንስሳት ማሰብ እንደማይችሉ ሁሉ እነዚህ ሰዎች በምክንያታዊነት ሊታሰቡ አይችሉም። አት: - “እነዚህ የሐሰት አስተማሪዎች ልክ እንደሌላቸው እንስሳት ናቸው” (See fig_metaphor)
ለማያውቁት ወይም ለማያውቁት ነገር መጥፎ ነገር ይናገራሉ ፡፡
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ያጠፋቸዋል” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
ሐሰተኛ አስተማሪዎች እንደ ሽልማት ይቀበላሉ ስለሚለው ቅጣት ጴጥሮስ ተናግሯል ፡፡ አት: - ለሠራቸው ጥፋት የሚገባቸውን ይቀበላሉ (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_አሮን)
እዚህ ላይ “የቅንጦት” የሚለው ቃል ሆዳምነትን ፣ ስካርን እና የወሲባዊ እንቅስቃሴን ያጠቃልላል ፡፡ በቀን ውስጥ እነዚህን ነገሮች ማድረጉ እነዚህ ሰዎች በዚህ ባህሪ እንደማያዩ ያሳያል ፡፡
“ጉድፍ” እና “ብልሽቶች” የሚሉት ቃላት ተመሳሳይ ትርጉምዎችን ይጋራሉ ፡፡ ጴጥሮስ ስለ ሐሰተኛ አስተማሪዎች በሚለብሱት ሰዎች ላይ የሚያሳፍር ልብስ የለበሱ ይመስላቸዋል። አት: - “እነሱ በልብስ ላይ መናፈሻዎች እና ጉድፍ ናቸው ፣ ውርደት የሚያስከትሉ ናቸው” (የበለስ_ቁልፍ እና የበለስ_ቁጥር)
“ዐይናቸው እንዲሞላ” ማለት በሚመለከቱት ነገር ይጨነቃሉ ማለት ነው ፡፡ ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “አመንዝራ ሴት አድርገው የሚያዩትን እና ከእሷ ጋር ለመተኛት የሚፈልጉትን ሁሉ ያስባሉ” ወይም 2) “አመንዝራ ሴት ሁልጊዜ አብረዋቸው እንዲተኛ ይፈልጋሉ” ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
ምኞታቸውን ለማርካት ቢበድሉም የሚፈጽሙት ኃጢአት በጭራሽ አያረካቸውም።
እዚህ “ነፍሳት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሰዎችን ነው ፡፡ አት: - “ያልተረጋጉ ሰዎችን ያታልላሉ” (የበለስ_ስኔክዶቼን ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “ልቦች” የሚለው ቃል የሰውን አስተሳሰብ እና ስሜቶች ያመለክታል ፡፡ በተለመዱት ተግባራቸው ምክንያት ከስግብግብነት ለማሰብ እና ድርጊትን እራሳቸውን አሠልጥነዋል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
“ልጆች” የሚለው ቃል የተረገመውን ያመለክታል ፡፡ አት: - “እነሱ በእግዚአብሔር ርግማን ስር ያሉ ሰዎች ናቸው” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
ሴቲቱ አባባ… ሳውዝ ተከትን ... ጆሮው ላይ ጆሮ ደግፍ "ሐሰተኛ አስተማሪዎች ትተዋል ... ተሳስተዋል ... ተከተሉ።" ሐሰተኛ አስተማሪዎች ትክክል የሆነውን በመቃወም አምላክን ለመታዘዝ አሻፈረን ብለዋል።
እግዚአብሔርን የሚያስከብር ትክክለኛ ባህርይ የሚከተል ጎዳና እንደሆነ ተደርጎ ይገለጻል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
በለዓምን የገሠጸው እግዚአብሔር መሆኑን መግለፅ ይችላሉ ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ገሠጸው” (UDB) (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያ)
ለመናገር የማይችል አህያ በተፈጥሮ ሰው ሆኖ ይሰማል ፡፡
እግዚአብሔር የነቢዩን የሞኝነት ተግባር ለማስቆም በአህያ ተጠቅሞበታል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
እነሱ አስገራሚ ግን ትርጉም የለሽ ቃላትን ይጠቀማሉ ፡፡
እነሱ ሥነ ምግባር የጎደለው እና ኃጢአተኛ በሆኑ ድርጊቶች ውስጥ እንዲሳተፉ ወደ ኃጢአተኛው ተፈጥሮ ይማራሉ ፡፡
ከኃጢያታቸው ነፃ መውጣት ስለሚያስፈልጋቸው የኃጢያት ባሪያዎች እንደሆኑ ጴጥሮስ በኃጢያት ስለሚኖሩ ሰዎች ተናግሯል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ ሐረግ የሚያመለክተው በቅርቡ አማኞች የነበሩትን ነው ፡፡ “በስሕተት የሚኖሩት” የሚለው ሐረግ አሁንም በኃጢአት የሚመላለሱ የማያምኑትን ያመለክታል ፡፡ አት: - “እንደ ሌሎቹ ሰዎች እና እንደነበረው በኃጢያት ከመኖር ይልቅ በትክክለኛው ለመኖር የሚሞክሩ ሰዎች” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር) ፡፡
ሐሰተኛ አስተማሪዎች ለእነዚህ ሰዎች ነፃነትን ቃል ይሰጣሉ ፣ ሐሰተኛ አስተማሪዎች ግን እነሱ የሙስና ባሮች ናቸው ፡፡ ሐሰተኛ አስተማሪዎች ሰዎች ኃጢአት መሥራታቸውን እንዲያቆሙ ሊረ canቸው እንደሚችሉ ቃል ገብተዋል ፣ ነገር ግን ሐሰተኛ አስተማሪዎች ራሳቸው ኃጢአት መሥራታቸውን ማቆም አይችሉም ፡፡
አንድ ሰው በዚያ ሰው ላይ ቁጥጥር በሚደረግበት ጊዜ ፣ እንደዚያ ሰው የዚያ ሰው ጌታ ሲገዛ ጴጥሮስ ስለ አንድ ሰው እንደ ባሪያ ተናግሯል ፡፡ አት: - “አንድ ነገር በአንድ ሰው ላይ ቁጥጥር ካለው ለዚያ ሰው ያ ባሪያ ለዚያ ነገር ባሪያ ይሆናል” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
“ርኩሰት” የሚለው ቃል አንድን ሥነ ምግባራዊ ርኩስ የሚያደርገው ኃጢአተኛ ባህሪን ያመለክታል ፡፡ “ዓለም” የሚያመለክተው የሰውን ማህበረሰብ ነው። አት: - “የኃጢያት ሰብአዊው ማህበረሰብ ርኩሰት ልምዶች” (ይመልከቱ።
የቃል ሐረግን በመጠቀም “ዕውቀት” ን መተርጎም ይችላሉ። ተመሳሳይ ሐረጎችን በ 1 1 እና 1 8 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ አት: - “ጌታን እና አዳኙን ኢየሱስ ክርስቶስን በማወቅ” (የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎችን ይመልከቱ)
ያሉበት ሁኔታ ከበፊቱ ከነበረው የከፋ ነው ”
ጴጥሮስ ስለ ሕይወት “መንገድ” ወይም መንገድ ብሎ ተናግሯል ፡፡ ይህ ሐረግ የሚያመለክተው እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነን ኑሮ መኖርን ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቃላት ሊገለፅ ይችላል። አት: - "እግዚአብሔር ለእነርሱ የሰጣቸውን ቅዱስ ትእዛዝ" (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ጴጥሮስ ሐሰተኛ አስተማሪዎች ምንም እንኳን “የጽድቅን መንገድ” ቢያውቁም በሥነ ምግባር እና በመንፈሳዊ ርኩስ ወደሆኑት ነገሮች እንዴት እንደተመለሱ ለመግለጽ ጴጥሮስ ሁለት ምሳሌዎችን ይጠቀማል ፡፡ (ይመልከቱ: መፃፍ_የቃላቶች)
1 ወዳጆች ሆይ! ይህን ሁለተኛ መልእክት የምጽፍላችሁ፣ ቅን ልቦናችሁን ለማነቃቃት ነው፤ 2 ደግሞም አስቀድሞ በቅዱሳን ነቢያት የተነገረውን ቃል እንዲሁም በሐዋርያቶቻችሁ አማካይነት በጌታችንና በአዳኛችን የተሰጠውን ትእዛዝ እንድታስታውሱ ነው። 3 በቅድሚያ ይህን ዕወቁ፤ በመጨረሻዎቹ ቀኖች የራሳቸውን ክፉ ምኞት የሚከተሉ ዘባቾች እየዘበቱባችሁ ይመጣሉ። 4 እነርሱም፣ «የመምጣቱ ተስፋ ወዴት አለ? አባቶቻችን ሞተዋል፤ ከፍጥረት መጀመሪያም አንሥቶ እስካሁን ድረስ ሁሉም ነገር እንዳለ ይኖራል» ይላሉ። 5 እነዚህ ሰዎች ሰማያትና ምድር ከብዙ ዘመን በፊት በእግዚአብሔር ቃል ከውሃና በውሃ አማካይነት መፈጠራቸውን ፣ ሆን ብለው ይክዳሉ፤ 6 በቃሉና በውሃ እማካይነት በዚያን ጊዜ የነበረው ዓለም በውሃ ተጥለቅልቆ ጠፋ። 7 ደግሞም በዚያው ቃል አሁን ያሉት ሰማያትና ምድር ኀጢአተኞች እስከሚጠፉበት እስከ ፍርድ ቀን ድረስ ለእሳት ተጠብቀዋል። 8 ወዳጆች ሆይ፤ ፤በጌታ ዘንድ አንድ ቀን እንደ ሺህ ዓመት፣ ሺህ ዓመትም እንደ አንድ ቀን መሆኑን ይህን አትዘንጉ ። 9 አንዳንድ ሰዎች የዘገየ እንደሚመስላቸው ጌታ የተስፋ ቃሉን ለመፈጸም አይዘገይም፤ ነገር ግን ከእናንተ መካከል አንዳችሁም እንድትጠፉ ስለማይፈልግና ሰው ሁሉ በቂ የንስሓ ጊዜ እንዲያገኝ ፈልጎ ስለ እናንተ ይታገሳል። 10 ይሁን እንጂ የጌታ ቀን ግን እንደ ሌባ ይመጣል፤ በዚያም ቀን ሰማያት በታላቅ ድምፅ ያልፋሉ፤ የሰማይም ፍጥረት በእሳት ይቃጠላል፤ በምድርና በእርሷም ውስጥ በተሠራው ነገር ሁሉ ላይ ይፈረድበታል። 11 እንግዲህ እነዚህ ሁሉ ነገሮች በዚህ ሁኔታ የሚጠፉ ከሆነ፣ ታዲያ እናንተ በቅድስናና እግዚአብሔርን በመምሰል ሕይወት ለመኖር እንዴት ዐይነት ሰዎች ልትሆኑ ይገባችኋል? 12 ስለዚህ የእግዚአብሔርን ቀን መምጣት በናፍቆት የምትጠባበቁና የምታፋጥኑ ሁኑ፤ በዚያን ቀን ሰማያት በእሳት ተቃጥለው ይጠፋሉ፤ ፍጥረታትም በእሳት ግለት ይቀልጣሉ፤ 13 እኛ ግን እርሱ በሰጠን ተስፋ መሠረት፣ ጽድቅ የሰፈነበትን አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር እንጠባበቃለን። 14 ስለዚህ ወዳጆች ሆይ፤ እነዚህን ነገሮች የምትጠባበቁ እንደ መሆናችሁ፣ ያለ ነውርና ያለ ነቀፋ ሆናችሁ ከእርሱም ጋር በሰላም እንድትገኙ ትጉ። 15 እንዲሁም ወንድማችን ጳውሎስ በተሰጠው ጥበብ መጠን እንደ ጻፈላችሁ፤ የጌታችን ትዕግሥት እናንተ እንድትድኑ እንደ ሆነ አስቡ፤ ምንም እንኳ በመልእክቶቹ ውስጥ በቀላሉ ለመረዳት የሚያስቸግሩ ነገሮች ቢኖሩም፣ 16 ጳውሎስ ስለ እነዚህ ነገሮች በመልእክቶቹ ሁሉ ጽፎአል፤ ዕውቀት የጐደላቸውና ጽናት የሌላቸው ሰዎች ሌሎችን የቅዱሳት መጻሕፍት ክፍሎች እንደሚያጣምሙ ሁሉ እነዚህም ለገዛ ጥፋታቸው ያጣምማሉ። 17 እንግዲህ ወዳጆች ሆይ፤ ይህን አስቀድማችሁ ስላወቃችሁ፣ በዐመፀኞች ስሕተት ተስባችሁ ጽኑ መሠረታችሁን እንዳትለቅቁ ተጠንቀቁ። 18 ነገር ግን በጌታችንና በአዳኛችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ዕውቀት እደጉ፤ ለእርሱ አሁንም፣ ለዘላለምም ክብር ይሁን፤ አሜን!
ጴጥሮስ አንባቢዎቹ ስለ እነዚህ ነገሮች ከእንቅልፋቸው የሚያነቃቃ ይመስላቸዋል ብለው እንዲያስቡ ያደርጋቸዋል ፡፡ አት: - "ንፁህ ሀሳቦችን እንዲያስቡ" (እነሆ ፣ የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ቅዱሳን ነቢያት ከዚህ በፊት የተናገሯቸው ቃላት” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ AT: - “ሐዋርያቱ የሰጣችሁት የጌታችንና የመድኃኒታችን ትእዛዝ” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ይህንን እንደ በጣም አስፈላጊው ነገር እወቅ ፡፡ ይህንን በ 1 19 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
እዚህ ላይ “ምኞቶች” የሚለው ቃል ከእግዚአብሄር ፈቃድ ጋር የሚቃረኑትን የኃጢያተኛ ምኞቶችን ያመለክታል ፡፡ አት: - “እንደየራሳቸው የኃጢአት ምኞት” የሚመሩ (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
ተግባር ፣ ባህሪይ
ዘባቾች ኢየሱስ የሚመለሰው የማያምኑ መሆናቸውን ለማጉላት ይህንን አፀያፊ ጥያቄ ይጠይቃሉ ፡፡ “ተስፋ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስ ተመልሶ የሚመጣውን የተስፋ ቃል ፍፃሜ ነው ፡፡ አት: - “ኢየሱስ እንደሚመለስ የሰጠው ተስፋ እውነት አይደለም! (የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁልፍ ጥምርን ይመልከቱ)
እዚህ “አባቶች” የሚያመለክቱት ከረጅም ጊዜ በፊት የኖሩትን ቅድመ አያቶችን ነው ፡፡ “ይተኛል” ማለት መሞታቸው ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ ቪዲዮም)
በአለም ላይ ምንም ነገር ስለሌለ ኢየሱስ ተመልሶ ይመጣል የሚለው እውነት ሊሆን እንደማይችል ዘባቾች ይከራከራሉ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ጥበብ)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት-“እግዚአብሔር ሰማያትንና ምድርን በጊዜው የጀመረው በቃሉ መሠረት ነው” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ ማለት መሬቱ እንዲገለጥ ለማድረግ የውሃ አካላትን በአንድ ላይ ሰብስቦ እግዚአብሔር ከውኃ እንዲወጣ አደረገ ፡፡
እዚህ “እነዚህ ነገሮች” የሚያመለክቱት የእግዚአብሔርን ቃል እና ውሃ ነው ፡፡
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “በዚያን ጊዜ የነበረውን ዓለም በውኃ አጥለቅልቆ አጠፋው” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር በዚያው ቃል ሰማያትንና ምድርን በእሳት አጠበ” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
እዚህ “ትዕዛዝ” ትዕዛዙን የሚሰጥ ፣ ለእግዚአብሔር ማለት ነው ፣ “AT” ተመሳሳይ ትዕዛዝ የሚሰጥ ፣ ”
"ይህንን አለመረዳት የለብዎትም" ወይም "ይህንን ችላ አትበሉ"
ከጌታ አመለካከት አንድ ቀን እንደ አንድ ሺህ ዓመት ነው ”
ጌታ ተስፋውን ለመፈፀም በቀስታ አይንቀሳቀስም ”
አንዳንድ ሰዎች ጌታ የገባውን ቃል ለመፈፀም ዘገምተኛ ነው ብለው ያስባሉ ፣ ምክንያቱም የጊዜ አመጣጣቸው ከእግዚአብሔር የተለየ ነው።
ምንም እንኳን ጌታ ታጋሽ እና ሰዎች ንስሐ እንዲገቡ የሚፈልግ ቢሆንም በእርግጥ ተመልሶ ፍርድ ያመጣል ፡፡
እግዚአብሔር በሰዎች ሁሉ ላይ ድንገት የሚመጣ እና ድንገተኛ ድንገት እንደሚመጣ ሌባ እግዚአብሔርን በሚፈርድበት ቀን ላይ ጴጥሮስ ተናግሯል ፡፡ (ይመልከቱ: በለስ
“ሰማያት ይጠፋሉ”
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ንጥረ ነገሮቹን በእሳት ያቃጥላል” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) እንደ ፀሐይ ፣ ጨረቃ እና ኮከቦች ያሉ የሰማይ አካላት ናቸው (2) ሰማይን እና ምድርን ፣ እንደ አፈር ፣ አየር ፣ እሳት እና ውሃ ያሉ ነገሮች።
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር እነዚህን ሁሉ በዚህ መንገድ ያጠፋቸዋልና” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ጴጥሮስ ቀጥሎም ምን እንደሚል ለማጉላት ፣ “ቅዱስ እና እግዚአብሔርን የሚሹ ኑሩ” የተባሉትን ለማጉላት ይህንን የተዛባ ጥያቄ ይጠቀማል ፡፡ አት: - "ምን ዓይነት ሰዎች መሆን እንደምትችል ታውቃለህ ፡፡" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ሰማያትን በእሳት ያጠፋል ፣ ነገሩን በታላቅ ሙቀት ይቀልጣል” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) እንደ ፀሐይ ፣ ጨረቃ እና ኮከቦች ያሉ የሰማይ አካላት ናቸው (2) ሰማይን እና ምድርን ፣ እንደ አፈር ፣ አየር ፣ እሳት እና ውሃ ያሉ ነገሮች። በ 3 10 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
ጴጥሮስ ስለ “ጽድቅ” እንደ አንድ ሰው አድርጎ ተናግሯል ፡፡ ይህ (ጻድቃንም) ለጻድቅ ሰዎች ምሳሌ ነው ፡፡ አት: - “ጻድቃን በሚኖሩበት” ወይም “ሰዎች በጽድቅ በሚኖሩበት” (የበለስ_ከስለስና የለስስ ምልክት / ምስልን ይመልከቱ)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር እንከን የለሽ እና ነቀፋ የሌለበት እና ከእርሱም ሆነ እርስ በእርሱ ጋር በሰላም እንዲኖር እግዚአብሔር በሚስማማ መንገድ ለመኖር የተቻለህን ሁሉ አድርግ” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
“እንከን የለሽ” እና “ነቀፋ የሌለ” የሚሉት ቃላት በመሠረታዊነት አንድ ዓይነት ማለት ሲሆን የሞራል ንፅህናን አፅን emphasizeት ይሰጣሉ ፡፡ አት: "ሙሉ በሙሉ ንፁህ" (ይመልከቱ: የበለስ_አድራሻ)
እዚህ ይህ "እንከን የለሽ" ለሚለው ነው። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ጌታ ታጋሽ ስለሆነ የፍርድ ቀን ገና አልተፈጠረም። ይህ በ 3 8 ላይ እንዳብራራው ሰዎች ንስሐ እንዲገቡና እንዲድኑ እድል ይሰጣል ፡፡ አት-“ደግሞም ፣ ንስሐ ለመግባት እና ለመዳን እድል እንደሰጠህ የጌታችን ትዕግሥት አስብ” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
ግድየለሾች እና ያልተረጋጉ ሰዎች ለመረዳት የሚያስቸግራቸውን በጳውሎስ ደብዳቤዎች ውስጥ ያሉትን ነገሮች በተሳሳተ መንገድ ይተረጉማሉ።
"የገዛ ራሳቸውን ጥፋት አስከተለ"
“ራሳችሁን ጠብቁ”
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “ዓመፀኞች ሰዎች በማታለል ቃላቶቻቸው እንዳያሳሳቱዎት” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ትክክለኛውን ጎዳና ለመከተል እየወሰደ እንደመሆኑ እግዚአብሔርን አለመታዘዝ ተደርጎ መታየት አለበት ፡፡ አታላይ ወይም የሐሰት ትምህርቶች ሌላውን ሰው ከትክክለኛው መንገድ ሊወስድ የሚችል ሰው እንደሆኑ ተደርገው ይገለፃሉ። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ታማኝነት አማኞች ሊያጡ የሚችሉት ንብረት እንደሆነ ተደርጎ ተገልጻል። አት: - "ታማኝ መሆንህን አቆማለሁ" (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
"ፀጋ እና እውቀት ጨምር"
የቃል ሐረጎችን በመጠቀም “ጸጋ” እና “ዕውቀት” ን መተርጎም ይችላሉ። ተመሳሳይ ሐረጎችን በ 1 1 እና 1 1 እና 8 8 እና 2 20 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ አት: - “ጌታችን እና አዳኛችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደግነት ወደ እናንተ ሲመጣ ፣ እናም እሱን በተሻለ እና በተሻለ እሱን እንድታውቀው” (ኤፌ.ቢ.
“እነዚህ ነገሮች” የእግዚአብሔር ትዕግሥት እና የእነዚህ የሐሰት አስተማሪዎች ትምህርቶች እውነቶችን ይመለከታሉ።
1 ከመጀመሪያው ስለ ነበረው፣ ስለ ሰማነው፣ በዓይኖቻች ስላየነው፣ ስለ ተመለከትነው ፣በእጆቻችንም ስለ ዳሰስነው ስለ ህይወት ቃል 2 ህይወትም ተገልጦ ነበር ፤እኛም አይተናል፣ምስክሮችም ነን፤ በአብ ዘንድ ስለ ነበረው ለእኛም ስለ ተገለጠው፣ የዘላለም ሕይወት እንናገራለን፤ 3 ከእኛም ጋር ህብረት እንዲኖራቸሁ፣ ያየነውንና የሰማነውን እንነግራችኋለን፤ ህብረታችንም ከአብና፣ ከልጁ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው፡፡ 4 ደስታችሁም ሙሉ እንዲሆን ፣እነዚህን ነገሮች እንጽፍላችኋለን። 5 ከእርሱ የሰማነው፣ለናንተም የምንነግራችሁ መልዕክት፣ እግዚአብሔር ብርሃን ነው፤ በእርሱም ምንም ጨለማ የለም፤ የሚል ነው፡፡ 6 ከእርሱ ጋር ህብረት አለን እያልን፣ ነገር ግን በጨለማ ውስጥ ብንመላለስ፣እንዋሻለን ፣እውነትንም አናደርግም፡፡ 7 እርሱ ብርሃን እንደሆነ ፣ በብርሃን ብንመለላለስ እርስ በርሳችን ህብረት ይኖረናል፡፡የልጁ የኢየሱስ ክርስቶስም ደም ከሃጢአት ሁሉ ያነጻናል። 8 ሃጢያት የለብንም ብንል፣ ራሳችንን እናስታለን፣ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም። 9 ነገር ግን ሃጢያታችንን ብንናዘዝ፣ሃጢያታችንን ይቅር ሊለንና ከዓመጽ ሁሉ ሊያነጻን፣ የታመነና ፃድቅ ነው፡፡ 10 ሃጢአት አላደረግንም ብንል፣ ሃሰተኛ እናደርገዋለን፣ ቃሉም በእኛ ውስጥ የለም፡፡
ይህ መጽሐፍ በሁለት ዓላማዎች ማለትም - ህብረትና ደስታ ይከፈታል ፡፡
ሐዋርያው ዮሐንስ ይህንን ደብዳቤ የጻፈው ለአማኞች ነው ፡፡ ሁሉም የ “እርስዎ” ፣ “የእርስዎ ፣” እና “የእርስዎ” ሁሉም አማኞች የሚያካትቱ እና ብዙ ናቸው። እዚህ “እኛ” እና “እኛ” የሚሉት ቃላት የሚያመለክቱት ዮሐንስንና ከኢየሱስ ጋር የነበሩትን ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር)
ቁጥር 1 ከፊደል ዐረፍተ-ነገር ነው ፡፡ የተሟላ ዓረፍተ ነገር እንዲኖርዎት ከፈለጉ ዓረፍተ-ነገርን በቁጥር 1 መጀመር ይችላሉ ፣ ቁጥር 2 ን እንደ ቅንፍ ያስተናግዳሉ ፣ እንዲሁም ዓረፍተ ነገሩን በ 1: 3 ይሙሉ ፡፡
“ከመጀመሪያው የሆነው ሐረግ” የሚለው ሐረግ የሚያመለክተው ሁሉም ነገር ከመፈጠሩ በፊት የነበረውን ኢየሱስን ነው ፡፡ አት: - እኛ ሁሉን ነገር ከመፈጠሩ በፊት ስለነበረው ስለ እኛ ጽፈንላችኋለሁ። ”
“የሁሉም ነገር መጀመሪያ” ወይም “የዓለም ፍጥረት”
እርሱ ሲያስተምር የሰማነው
ለማጉላት ይህ ተደግሟል። አት: - እኛ “ያየነው” (ተመልከት: የበለስ_ፓራሊያ)
“የሕይወት ቃል” ኢየሱስ ነው ፡፡ አትቲን: - “ሰዎችን ለዘላለም እንዲኖሩ የሚያደርግ ኢየሱስ
በዚህ ደብዳቤ ውስጥ “ሕይወት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ከአካላዊ ሕይወት በላይ ነው ፡፡ ለኢየሱስ የዘላለም ሕይወቱ እዚህ ይቆማል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት-“እግዚአብሔር የዘላለምን ሕይወት አስታወቅን” ወይም “እግዚአብሔር የዘላለምን ሕይወት እንድናውቅ አስችሎናል” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
እኛም አይተነዋል
እኛም ለሌሎች ስለ እሱ በእርግጠኝነት እንናገራለን ”
እዚህ “የዘላለም ሕይወት” የሚያመለክተው ያንን ሕይወት የሚሰጠውን ኢየሱስን ነው ፡፡ አት: - "ለዘላለም እንድንኖር የሚረዳን" (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ከእግዚአብሔር አብ ጋር የነበረው "
በምድር ላይ ሲኖር ይህ ነበር ፡፡ አት: - "እርሱም በመካከላችን እንዲኖር መጣ" (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
እዚህ ላይ “እኛ” “እኛ” እና “የእኛ” የሚሉት ቃላት የሚያመለክቱት ዮሐንስንና ከኢየሱስ ጋር የነበሩትን ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እኛ ያየነውንና የሰማነውን ለእናንተ ደግሞ እንነግራለን
“የቅርብ ጓደኞቻችን ሁን ፤ ከእግዚአብሔር አብ ጋር ጓደኛሞች ነን”
ዮሐንስ አንባቢዎቹን የሚያካትት ወይም የማያካትት ግልፅ አይደለም ፡፡ በዚህ መንገድ መተርጎም ይችላሉ ፡፡
እነዚህ በእግዚአብሔር እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚገልፁ አስፈላጊ አርዕስት ናቸው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
ደስታችንን ፍጹም ለማድረግ ወይም “ሙሉ በሙሉ ደስታችንን ለማስደሰት”
ከዚህ ወደ ቀጣዩ ምእራፍ ዮሐንስ ስለ ህብረት ማለትም ከእግዚአብሔርና ከሌሎች አማኞች ጋር የጠበቀ ግንኙነት ይጽፋል ፡፡
እዚህ “እኛ” እና “እኛ” የሚሉት ቃላት ዮሐንስ የጻፈላቸውን ሰዎች ጨምሮ ሁሉንም አማኞች ይመለከታሉ ፡፡ በሌላ መንገድ ካልተገለጸ በቀር ፣ የዚህ መጽሐፍ ቅሪት ትርጉም ይህ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ ማለት እግዚአብሔር ፍጹም ንጹህ እና ቅዱስ ነው ማለት ነው ፡፡ ጥሩነትን ከብርሃን ጋር የሚያዛመዱ ባህሎች ዘይቤውን ሳያብራሩ የብርሃን ሀሳቡን መቀጠል ይችላሉ ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ልክ እንደ ንፁህ ብርሃን ጻድቅ ነው” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ.
ይህ ማለት እግዚአብሔር ፈጽሞ ኃጢአት አይሠራም እንዲሁም በምንም መንገድ ክፉ አይደለም ፡፡ ክፋትን ከጨለማ ጋር የሚያያዙ ባህሎች ዘይቤውን ሳያብራሩ የጨለማውን ሀሳብ ሊጠብቁ ይችላሉ ፡፡ አት: - “በእርሱ ውስጥ የኃጢአት ጨለማ የለም” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ይህ ማለት “ክፉን ተለማምዱ” ወይም “ክፉን ማድረግ” ማለት ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ ማለት "መልካምነትን ተለማመድ" ወይም "መልካም የሆነውን አድርግ" ማለት ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ የኢየሱስን ሞት ያመለክታል። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
እዚህ “እሱ ፣” “እሱ” እና “እሱ” የሚሉት ቃላት እግዚአብሔርን ያመለክታሉ ፡፡ (1: 5 ይመልከቱ)
ኃጢአት አይሠሩም
እያታለሉ ነው ወይም እየዋሹ
እውነት የሚነገርው በአማኞች ውስጥ ሊሆን የሚችል ነገር ነው ተብሎ ነው። አት: - “እውነት የሆነውን አናምንም” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እነዚህ ሁለት ሐረጎች በመሠረቱ አንድ ዓይነት ናቸው ፡፡ ዮሐንስ እግዚአብሔር ኃጢያታችንን በእርግጥ ይቅር እንደሚለን ለማጉላት ይጠቀምባቸዋል ፡፡ አት: - "የበደለንን ጥፋት ሙሉ በሙሉ ይቅር ይለናል" (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
እኛ ሀሰተኛ ነን ብለን እንናገራለን “እኛ ሁላችንም ኃጢአት ሠርተናል ብሎ ውሸታም ብሎ መጥራት አንድ ነው” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
የእግዚአብሄርን ቃል መታዘዝ እና ማክበር ቃሉ በአማኞች ውስጥ እንደነበረ ተደርጎ ይገለጻል ፡፡ አት: - "የእግዚአብሔርን ቃል አልገባንም ፣ የሚናገረውንም አልታዘዝም" (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
1 የተወደዳችሁ ልጆቼ ፣ሃጢያት እንዳታደርጉ ይህን እፅፍላችኋላሁ። ግን ማንም ሃጢያት ቢያደርግ ፣ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን ፤እርሱም ፃድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ፡፡ 2 እርሱ የእኛ ብቻ ሳይሆን፣ የዓለሙም ሁሉ ሃጢዓት ማስተስረያ ነው፣፡፡ 3 ትዕእዛዙን የምንጠብቅ ከሆነ ፣በዚህ እርሱን እንዳወቅነው እናውቃለን። 4 "እግዚአብሔርን አውቀዋለሁ" የሚል ፣ግን ትዕዛዛቱን የማይጠብቅ፣ ውሸታም ነው ፣እውነትም በውስጡ የለም፡፡ 5 ሆኖም ማንም ቃሉን ቢጠብቅ፣ በርግርጥ በዚያ ሰው ለእግዚአብሔር ያለው ፍቅር ተገልጧል፤ በዚህም በእርሱ እንደሆንን እናውቃለን። 6 በእግዚአብሔር እኖራለሁ የሚል ፣ኢየሱስ ክርስቶስ እንደኖረ መኖር አለበት። 7 የተወደዳችሁ፣የምጽፍላችሁ በመጀመሪያ የነበረውን አሮጌ ትዕዛዝ እንጂ አዲስ ትዕዛዝ አይደለም።አሮጌውም ትእዛዝ የሰማችሁት ቃል ነው፡፡ 8 ሆኖ በክርስቶስና በናንተ እውነት የሆነውን አዲሱን ትእዛዝ እጽፍላችኋለሁ።ምክንያቱም ጨለማው አልፎ እውነተኛው ብርሃን እያበራ ነው። 9 በብርሃን አለሁ እያለ ፣ወንድሙን ግን የሚጠላ ፣አሁንም እንኳ በጨለማ ውስጥ ነው፡፡ 10 ወንድሙን የሚወድ በብርሃን ይኖራል። የሚያሰናክል ሁኔታም የለም፡፡ 11 ወንድሙን የሚጠላ በጨለማ ውስጥ ነው፣ በጨለማም ይኖራል፤ ወዴት እንደሚሄድም አያውቅም ፣ምክንያቱም ጨለማው ዓይኖች አሳውሮታል፡፡ 12 ልጆች ሆይ! ኃጢያታችሁ በክርስቶስ ስም ይቅር ስለተባለ እፅፍላችኋለሁ፡፡ 13 አባቶች ሆይ! ከመጀመሪያ የነበረውን አውቃኋልና እጽፍላችኋለሁ። ወጣቶች ሆይ! ክፉውን ስላሸነፋችሁ እጽፍላችኋለሁ፡፡ ታናናሽ ልጆች ሆይ! አብን ስላወቃችሁ እጽፍላችኋለሁ፡፡ 14 አባቶችሆይ! ከመጀመሪያ የነበረውን አውቃችኋልና እጽፍላችኋለሁ። ወጣቶች ሆይ! ብርቱዎች ስለሆናቹ ፣የእግዚአብሔርም ቃል በእናንተ ስለሚኖር፣ ክፉውንም አሸንፋችኋልና እጽፍላችኋለሁ፡፡ 15 ዓለምን ወይም በዓለም ያሉት ነገሮች አትውደዱ። ማንም ዓለምን ቢወድ የአብ ፍቅር በርሱ ውስጥ የለም፡፡ 16 በዓለም ያለው ሁሉ፣ የሥጋ ምኞት፣ የዓይን አምሮትና ትምክህት ከዓለም እንጂ ከአብ አይደሉም፡፡ 17 ዓለሙና ምኞቱም ያልፋሉ፣የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል፡፡ 18 ታናናሾች ልጆች ሆይ! የክርስቶስ ተቀዋሚ ስለመምጣቱ እንደሰማችሁት ፣ይህ የመጨረሻው ሰዓት ነው፡፡ አሁንም እንኳ፣ ብዙ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች መጥተዋል፡፡ 19 ከእኛው መካከል ወጥተዋል ፣ከእኛ ወገን ግን አልነበሩም። ከእኛ ወገን ቢሆኑ ኖሮ፣ ከእኛ ጋር ፀንተው ይኖሩ ነበር። ሆኖም ከእኛ ወገን እንዳልነበሩ እንዲገለጥ ወጡ። 20 እናንት ግን፣ከቅዱሱ የተቀበላችሁት ቅባት ስላላችሁ፣ሁላችሁም እውነትን ታውቃላችሁ። 21 የምጽፍላችሁ እውነትን ስለማታውቁ አይደለም፤ነገር ግን ስለምታውቁትና፣ በእውነትም ምንም ሃሰት ስለሌለ ነው። 22 ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን ከሚክድ በስተቀር ሃሰተኛ ማነው ነው? አብና ወልድን ስለሚክድ፣እንዲህ ዓይነት ሰው የክርስቶስ ተቃዋሚ ነው። 23 ወልድን የሚክድ ሁሉ አብ የለውም፤ ወልድንን የሚያውቅ አብም ደግሞ አለው። 24 እናንተ ግን ፣ከመጀመሪያው የሰማችሁት በውስጣችሁ ይኑር። ከመጀመሪያ የሰማችሁት፣በእናንተ ቢኖር፣እናንተም በወልድና በአብ ትኖራላችሁ። 25 እርሱ የሰጠን ተስፋ ይህ ነው፤ እርሱም የዘላለም ሕይወት ነው። 26 የሚያስቷችሁን በተመለከተ ፣ ይህን ፅፌላችኋለሁ፡፡ 27 እናንተ ግን የተቀበለች ቅባት በእናንተ ስለሚኖር ፣ማንም እንዲያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም። የርሱም ቅባት ስለ ሁሉም ነገሮች እውነት እንጂ ሃሰት ስለማያስተምራችሁ ፣ እንደተማራችሁት በርሱ ኑሩ፡፡ 28 አሁንም የተወዳዳችሁ ልጆች፣ በሚገለጥበለት ጊዜ ድፍረት እንዲኖረንና ፣በመምጣቱም እንዳናፍር በእርሱ ኑሩ፡፡ 29 እርሱ ፃድቅ እንደሆነ ካወቃችሁ ፣ፅድቅን የሚያደርግ ሁሉ ከርሱ እንደተወለደ ታውቃላችሁ፡፡
ዮሐንስ ስለ ሕብረት መጻፉን የቀጠለ ሲሆን ይህ ደግሞ ኢየሱስ በአማኞችና በአብ መካከል ስለሚሄድ ሊሆን እንደሚችል ያሳያል ፡፡
እዚህ “እኛ” እና “እኛ” የሚሉት ቃላት ዮሐንስንና ሁሉንም አማኞች ያመለክታሉ ፡፡ “እሱ” እና “የእርሱ” የሚሉት ቃላት እግዚአብሔርን አባት ወይም ኢየሱስን ሊያመለክቱ ይችላሉ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ጆን አረጋዊ እና መሪያቸው ነበር ፡፡ እሱ ለእነሱ ያለውን ፍቅር ለማሳየት በዚህ አገላለጽ ተጠቅሟል። አት-“ውድ ልጆቼ በክርስቶስ” ወይም “እንደ እኔ ልጆቼ ለእኔ ውድ የሆንሽው” (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
ይህንን ደብዳቤ እጽፋለሁ
"ማንም ቢበድል" ይህ ሊሆን የሚችል ነገር ነው።
እዚህ ላይ “ጠበቃ” የሚለው ቃል ኢየሱስን ያመለክታል ፡፡ አት: - "አንድ ሰው ከእግዚአብሔር አብ ጋር የሚናገር እና ይቅር እንዲለን የሚለምን ሰው" (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
"የገዛ ነፍሱን ለእኛ መስዋእት አደረገ በዚህም ምክንያት እግዚአብሔር ኃጢአታችንን ይቅር ይላል"
እሱ ያዘዘንን ካደረግን ከእርሱ ጋር ጥሩ ግንኙነት እንዳለን እርግጠኞች መሆን እንችላለን ”
ከእርሱ ጋራ ህብረት አለን
"የሚናገር" ወይም "የሚናገር ሰው"
ከእግዚአብሔር ጋር ጥሩ ግንኙነት አለኝ ”
"አያደርግም" ወይም "የማይታዘዝ"
እግዚአብሔር ምን እንዲያደርግ ነገረው
እውነት የሚነገርው በአማኞች ውስጥ ሊሆን የሚችል ዕቃ ነው ተብሎ ነው። አት: - "እግዚአብሔር እውነት መሆኑን አያምንም" (የበለስ_ማይታፎርን ይመልከቱ)
“ያደርጋል” ወይም “ይታዘዛል”
እግዚአብሔር ምን እንዲያደርግ የሚነግረው
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “ለአምላክ ያለን ፍቅር” ወይም 2) “እግዚአብሔር ለእኛ ያለው ፍቅር” ናቸው ፡፡
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር በዚያ ሰው ውስጥ ያለውን የእግዚአብሔር ፍቅር ፍጹም አድርጓል ፣” “በእርግጠኝነት ፣ የእግዚአብሔርን ትዕዛዛት የሚታዘዙ ሰዎች በሁሉም መንገድ እግዚአብሔርን የሚወዱ ሰዎች ናቸው ፣ ወይም“ እግዚአብሔር ለሰዎች ፍቅር ሲያደርግ ግቡን አሳክቷል። ያደርግላቸዋል (ተመልከት: በለስ
“እኛ በእርሱ ውስጥ” የሚለው ሐረግ አማኝ ሁል ጊዜ ከእግዚአብሔር ጋር አንድ ነው ወይንም ከእግዚአብሔር ጋር ቀጣይነት ያለው ህብረት አለው ማለት ነው ፡፡ ብዙውን ጊዜ በ 1 ዮሐንስ “በእርሱ ውስጥ መቆየት” የሚለው ሐረግ ተመሳሳይ ነገር ለማመልከት ያገለግላል ፡፡ አት: - "እግዚአብሔር የሚናገረውን ስንታዘዝ ከእርሱ ጋር ህብረት እንዳለን እርግጠኞች መሆን እንችላለን" (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
"ከእግዚአብሔር ጋር ግንኙነት አለው"
የአንድን ሰው ሕይወት መምራት እንደ መራመድ ተደርጎ ተገልጻል ፡፡ አት: - “እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ መኖር አለበት” ወይም “ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳደረገው እግዚአብሔርን መታዘዝም አለበት” (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
ዮሐንስ ለአማኞች መሰረታዊ የህብረት መሰረታዊ መርሆዎችን - ታዛዥነትን እና ፍቅርን ይሰጣል ፡፡
"እኔ የምወዳቸው ሰዎች" ወይም "ውድ ጓደኞቼ"
እርስ በርሳችሁ እንድትዋደዱ እጽፍላችኋለሁ ፣ ይህም አዲስ ነገር አይደለም ፣ ነገር ግን የሰማችሁት የቀድሞው ትእዛዝ ነው። ዮሐንስ ኢየሱስ እርስ በርሳችን እንድንዋደድ የሰጠውን ትእዛዝ ይጠቅሳል።
እዚህ ፣ “መጀመሪያ” የሚያመለክተው ክርስቶስን ለመከተል የወሰኑበትን ጊዜ ነው ፡፡ አት: - “በክርስቶስ በመጀመሪያ ካመንክበት ጊዜ” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
“ነገር ግን የምጽፍላችሁ ትእዛዝ በአንድ በኩል አዲስ ነው”
እዚህ “በ” የሚለው ቃል “ስለ” ማለት ነው ፡፡ አት: - "ይህ እውነት የሆነው ክርስቶስ ስላደረገው እና እርስዎም ስለሚያደርጉት ነገር ነው"
እዚህ “ጨለማ” ክፉን እና “ብርሃን” ጥሩነትን ያመለክታል ፡፡ አት: - “ክፋትን መሥራታችሁን ያቆማችሁ እና ብዙ ጥሩ እያከናወኑ ነው” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
እዚህ “ወንድም” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የእምነት ባልንጀራውን ነው ፡፡
“የሚናገር ሁሉ” ወይም “የይገባኛል ጥያቄ ያነሱ” (ዩዲቢ) ፡፡ ይህ አንድን የተወሰነ ሰው አያመለክትም።
ይህ በትክክል የመኖር ሥዕል ነው ፡፡ ሰዎች ትክክለኛውን ነገር ሲያደርጉ በብርሃን ሊያደርጉት እና በጨለማ ውስጥ መደበቅ አይችሉም። አት: - "ትክክል የሆነውን ያደርጋል" (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ በኃጢአት የመኖር ሥዕል ነው። ሰዎች ስህተት የሆነውን ሲያደርጉ በጨለማ ውስጥ መደበቅ ይወዳሉ። አት: - "በጨለማ ውስጥ ክፉን የሚያደርግ ፣ በጨለማ ውስጥ ነው" (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
ምንም ነገር አያሰናክለውም ፡፡ “ማሰናከል” የሚለው ቃል በመንፈሳዊም ሆነ በሥነ ምግባር ውድቀት ማለት ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - "ምንም ነገር እንዲሠራ አያደርግም" ወይም "እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውን የሚያደርግውን አያደርግም" (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
አንድ ዓይነት የእምነት ባልንጀራችን መጥላቱ ምን ያህል መጥፎ እንደሆነ ትኩረትን ለመስጠት ሁለት ጊዜ ተነግሯል። አት: - "በጨለማ ውስጥ ነው" ወይም "በኃጢያት ጨለማ ውስጥ እየኖረ ነው" (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ይህ እንደ ክርስቲያን የማይኖር አማኝ ስዕል ነው ፡፡ አት: - “መጥፎ ነገር እያደረገ እንኳን አያውቅም” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ሞታፎር)
ጨለማው እንዳይታየ አድርጎታል ፡፡ ጨለማ የኃጢያት ወይም የክፉ ምሳሌ ነው። አት: - “ኃጢአት እውነትን እንዲገባለት አልቻለውም” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ደብዳቤውን ለተለያዩ የዕድሜ ክልሎች ወይም የብስለት ልዩነት ላላቸው አማኞች ደብዳቤውን የፃፈው ለምን እንደሆነ አብራራ ፡፡ ለእነዚህ ዐረፍተ-ነገሮች ተመሳሳይ ቃላትን ለመጠቀም ሞክር ፣ እነሱ በግጥም የተጻፉ ናቸው።
ጆን አረጋዊ እና መሪያቸው ነበር ፡፡ እሱ ለእነሱ ያለውን ፍቅር ለማሳየት በዚህ አገላለጽ ተጠቅሟል። AT: - “በክርስቶስ የምትወዳቸው ልጆቼ” ወይም “እንደ እኔ ልጆቼ እኔን የምትወደውን” በ 2 1 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ኃጢኣቶቻችሁን ይቅር ይላል” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
“ስሙ” ክርስቶስንና ማንነቱን ያመለክታል ፡፡ አት: - "ክርስቶስ ባደረገልህ ምክንያት" (ዩዲቢ) ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
እዚህ ላይ “አባቶች” የሚለው ቃል የበሰሉ አማኞችን የሚያመለክት ዘይቤ ሊሆን ይችላል ፡፡ አት-የበሰሉ አማኞች እጽፍላችኋለሁ ”(የበለስ_ማታፎርን ይመልከቱ)
"እርስዎ ጋር ግንኙነት አለዎት"
“ሁልጊዜ የኖረው” ወይም “ሁልጊዜ የነበረው” እሱ የሚያመለክተው ‹ኢየሱስ› ወይም ‹እግዚአብሔር አብ› ነው ፡፡
ይህ ምናልባት አዲስ አማኞችን ያልሆኑ ግን በመንፈሳዊ ጉልምስና ላይ ያሉትን ሊያመለክት ይችላል። አት: “ወጣት አማኞች” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ማታፎር)
እዚህ “ጠንካራ” የሚያመለክተው የአማኞችን አካላዊ ጥንካሬን አይደለም ፣ ግን ለክርስቶስ ያላቸውን ታማኝነት ነው። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ጸሐፊው የሚያመለክተው አማኞች በክርስቶስ ላይ ያላቸውን ታማኝነትና በእርሱ ውስጥ ስላለው የእግዚአብሔር ቃል የሚናገር ያህል መሆኑን ማወቅ ነው ፡፡ አት: - “የእግዚአብሔርን ቃል ታውቃላችሁ” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
ጸሐፊው እየተናገረ ያለው የአማኞች ሰይጣንን ለመከተል ፈቃደኛ አለመሆናቸው እና የእሱ ዕቅዶች እሱን እንደ ማሸነፍ ጉዳይ አድርገው እቅዳቸውን ስለሚያበሳጩ ነው። (ዩ.አር.ቢ.) (ይመልከቱ: የበለስ_ማይታፎር)
"እግዚአብሔርን የሚያዋርዱትን ያንኑ ነገር አይፈልጉም"
አንድ ሰው ይህንን ዓለም እና እግዚአብሔርን የሚያዋርዱትን ሁሉ እና አብን በተመሳሳይ ጊዜ መውደድ አይችልም። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
“አብን አይወድም”
ይህ በዓለም ውስጥ ያሉ አንዳንድ ነገሮች ዝርዝር ነው። እሱ “በዓለም ያለው ሁሉ” ምን ማለት እንደሆነ ያብራራል (የበለስ_ቁልፍ ቃል ይመልከቱ)
“የኃጢያት አካላዊ ደስታ የማድረግ ጠንካራ ፍላጎት”
“የምናያቸው ነገሮች እንዲኖረን ጠንካራ ፍላጎት”
"የህይወት ኩራት" ይህ ንብረትን እና አመለካከትን ሊያመለክት ይችላል። አንድ ሰው ስላለው ወይም ስላደረገው ጉራ መንዛት ወይም “ሰዎች በእራሳቸው ነገር እና በሚያደርገው ነገር ኩራት ይሰማቸዋል”
ይህ ሰዎች እንደ ኑሮ እና ሀብት እንዲሁም አመለካከቶች ያሉ ለመኖር ለመኖር ያሏቸውን ነገሮች እዚህ ሊያመለክት ይችላል ፡፡
"ከአብ ዘንድ አይመጣም" ወይም "አብ እንድንኖር የሚያስተምረን አይደለም"
“ማለፍ” ወይም “አንድ ቀን እዚህ አይኖርም”
በ 2 15-17 ውስጥ “ዓለም” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሰዎች እግዚአብሔርን የማያከብሩ ማድረግ የሚፈልጉትን ሁሉ ነው ፡፡ አት: - “በዓለም ላይ ያሉ እግዚአብሔርን የማያከበሩ ሰዎችን አትሁኑ” (ዩዲቢ) ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
ዮሐንስ ክርስቶስን ስለሚቃወሙ ሰዎች ያስጠነቅቃል ፡፡
“የጎለመሱ ክርስቲያኖች” በ 2፡1 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
“የመጨረሻው ሰዓት” የሚለው ሐረግ የሚያመለክተው ኢየሱስ ከመመለሱ በፊት ያለውን ጊዜ ነው ፡፡ አት: - “ኢየሱስ በቅርቡ ተመልሶ ይመጣል” (ይመልከቱ: የበለስ.
"ክርስቶስን የሚቃወሙ ብዙ ሰዎች አሉ"
"በዚህም ምክንያት እኛ እናውቃለን" ወይም "ብዙ ብዙ ተቃዋሚዎች ስለመጡ እኛ እናውቃለን"
“ትተውን ሄደዋል”
"እነሱ ግን በምንም መልኩ የእኛ አልነበሩም" ወይም "በመጀመሪያ ደረጃ የእኛ ቡድን አባል አይደሉም።" የቡድኑ አካል ያልነበሩበት ምክንያት የኢየሱስ አማኞች ስላልነበሩ ነው ፡፡
"እኛ እናውቃለን ይህ በእውነት አማኞች ቢሆኑ ኖሮ ለእኛ አይተዉንም ነበር"
በብሉይ ኪዳን “መቀባት” የሚለው ቃል በአንድ ሰው ላይ እግዚአብሔርን ለማገልገል እንዲለይ ለማድረግ ዘይት ላይ ማፍሰስን ያመለክታል ፡፡
“ቅዱስ ግን ቀባህ” እዚህ “መቀባት” የሚያመለክተው አማኞች እግዚአብሔርን ለማገልገል እንዲለዩአቸው ኢየሱስ መንፈስ ቅዱስን መስጠቱን ነው ፡፡ አት-“መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን መንፈሱን ሰጣችሁ” (የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያ)
እዚህ ላይ የውሸት ተግባር እንደ አንድ ነገር ተደርጎ ተገልጻል። አት: - “እውነት ከሆነው ከእግዚአብሔር እውነተኛ ውሸት አይደለም” (ይመልከቱ።
ውሸታም ማን ነው? ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ብሎ የሚክድ ሁሉ ፡፡ ዮሐንስ ውሸታሞች እነማን እንደሆኑ ለማጉላት አንድ ጥያቄ ተጠቅሟል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
"ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ ነው" ለማለት ፈቃደኛ አለመሆኑን ወይም "ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ እርሱ አይደለም"
“ስለ አብ እና ስለ ወልድ እውነቱን ለመናገር ፈቃደኛ አይሆንም” ወይም “አብንና ወልድ አይክዱም”።
እነዚህ በእግዚአብሔር እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚገልፁ አስፈላጊ አርዕስት ናቸው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
የአብ ነው
ስለ ወልድ እውነቱን የሚናገር
የአብ ነው
ዮሐንስ አማኞችን ለመጀመሪያ ጊዜ በሰሙበት እንዲቀጥሉ አሳስቧቸዋል ፡፡
እዚህ ላይ “እርስዎ” የሚለው ቃል ብዙ ነው ፣ እናም ዮሐንስ የጻፈላቸውን ሰዎች እና ሁሉንም አማኞች ይመለከታል ፡፡ “እሱ” የሚለው ቃል አፅንicት የሚሰጥ እና ክርስቶስን ያመለክታል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ዮዎ)
ይህ ዮሐንስ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች እንዴት እንደሚኖሩ ከመናገር ይልቅ ዮሐንስ የኢየሱስን ተከታዮች እንዴት መኖር እንዳለበት መናገራቸውን ያመላክታል ፡፡
ከመጀመሪያ የሰማችሁትን አስታውሱ ያምናሉ። እንዴት እንደ ሰሙ ፣ ምን እንደሰሙ ፣ እና “ጅምር” ማለት ምን ማለት በግልፅ ሊገለፅ ይችላል-AT “መጀመሪያ አማኞች ከሆናችሁ በኋላ እንዳመናችሁት ስለ ኢየሱስ የተማራችሁትን መታመን ቀጥሉ” (የበለስ_ቁጥር ንፅፅር ይመልከቱ)
ለመጀመሪያ ጊዜ አማኞች በሆናችሁበት ጊዜ ስለ ኢየሱስ ምን አስተምረናል?
“የቀረው ቃል የሚናገረው ስለ መዳን ሳይሆን ስለ መዳን ነው ፡፡
እንዲሁም ከወልድና ከአባት ጋርም ግንኙነት አላቸው ፡፡ ይህ በ 2 4 ውስጥ እንዴት እንደተተረጎመ ይመልከቱ ፡፡
እርሱም የዘላለም ሕይወት ይሰጠን ዘንድ ተስፋ የሰጠው ይህ ነው ወይንም ለዘላለም እንድንኖር ሊያደርገን ቃል ገብቷል
በዚህ ደብዳቤ ውስጥ “ሕይወት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ከአካላዊ ሕይወት በላይ ነው ፡፡ ለኢየሱስ የዘላለም ሕይወቱ እዚህ ይቆማል ፡፡ ይህንን በ 1 1 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
“ላሳቅህ እፈልጋለሁ” አማኞችን ከእግዚአብሄር ለማራቅ የሚሞክሩ አሉ ፡፡ አት: - “ከእግዚአብሔር እና ከእውነቱ ለመራቅ እፈልጋለሁ” “ውሸት እንዲያምኑ ለማድረግ ይሞክራሉ” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
አንድ ሰው እግዚአብሔርን እንዲታዘዝ ማሳሰብ አንድን ሰው ትክክለኛውን ትክክለኛ ጎዳና እንዲከተል እንደሚያደርግ ሆኖ ተገልጻል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ከቁጥር 29 ጀምሮ ፣ ዮሐንስ በእግዚአብሔር ቤተሰብ ውስጥ የመወለድን ሃሳብ ያስተዋውቃል ፡፡ የቀደሙት ቁጥሮች የሚያሳዩት አማኞች toጢኣትን እንደቀጠሉ ነው ፡፡ ይህ ክፍል አማኞች ኃጢአት ሊሠራ የማይችል አዲስ ተፈጥሮ እንዳላቸው ያሳያል ፡፡ አማኞች አንዳቸው ሌላውን እንዴት እንደሚገነዘቡ ያሳያል ፡፡
ይህ ዮሐንስ ክርስቶስን የሚቃወሙትን ከመከተል ይልቅ የኢየሱስ ተከታዮች እንዴት መሆን እንዳለባቸው ሌላ ነገር ሲናገራቸው ይህ ምልክት ነው ፡፡
ይህ “የእግዚአብሔርን መንፈስ” ያመለክታል ፡፡ በ 2 20 ውስጥ ስለ “መቀባት” ማስታወሻውን ይመልከቱ ፡፡
"መቀባቱ ያስተምርሃል"
እዚህ ላይ ይህ ሐረግ አጠራር ነው ፡፡ አት: - “ማወቅ ያለብዎት ነገር ሁሉ” (ይመልከቱ: የበለስ_ጥበብ)
"ለእርሱ ኑሩ" ይህ ሐረግ በ 2 4 ውስጥ እንዴት እንደተተረጎመ ተመልከት ፡፡ አንድ ሰው እንዴት እንደሚቆይ የሚያመለክተው ህብረቱን ወይም ግንኙነቱን ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ ሐረግ የ ‹ፊደል› አዲስ ክፍልን ለማመልከት እዚህ ላይ ይውላል ፡፡
ጆን አረጋዊ እና መሪያቸው ነበር ፡፡ እሱ ለእነሱ ያለውን ፍቅር ለማሳየት በዚህ አገላለጽ ተጠቅሟል። AT: - “በክርስቶስ የምትወዳቸው ልጆቼ” ወይም “እንደ እኔ ልጆቼ እኔን የምትወደውን” በ 2 1 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
እናየዋለን
በራስ መተማመን
ዳግም በሚመጣበት ጊዜ
ከእግዚአብሔር የተወለደ ነው ወይም “የእግዚአብሔር ልጅ”
1 የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን እንድንጠራ፣አብ የሰጠን ፍቅር ፣ምን ዓይነት እንደሆነ አስተውሉ ፤ እኛም ልክ እንደዛው ነን! በዚህ ምክንያት ዓለም እርሱን እንደማያውቀው እኛንም አያውቀንም። 2 የተወደዳችሁ፣አሁን የእግዚአብሔር ልጆች ነን፤ ምን እንደምንሆን ገና አልተገለጠም። ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ እርሱን እንደምንመስል እናውቃለን፤ምክንያቱም ትክክለኛ ማንንነቱን እናየዋለን። 3 በእርሱም ላይ ይህ ጽኑ እምነት ያለው ሁሉ፣ እርሱ ንፁህ እንደሆነ ራሱን ያነፃል፡፡ 4 ኃጢያትን የሚሠራ ሁሉ ዐመጽን ያደርጋል፣ ኃጢአትም ዐመጽ ነው፡፡ 5 ኃጢያትን ለማስወገድ ክርስቶስ እንደተገለፀ ታውቃላችሁ፣ በእርሱም ኃጢያት የለም፡፡ 6 በእርሱ የሚኖር ኃጢያት አያደርግም፡፡ ኃጢያት የሚያደርግ እርሱን አላየውም ወይም አላወቀውም፡፡ 7 የተወደዳችሁ ልጆች፣ ማንም አያስታችሁ፡፡ ክርስቶስ ፃድቅ እንደሆነ ሁሉ፣ ፅድቅን የሚያደርግ ፃድቅ ነው። 8 ኃጢያት የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው፤ምክንያቱም ዲያብሎስ ከመጀመሪያው ኃጢያት አድርጓል፡፡ በዚህም ምንክያት የዲያብሎስን ሥራ ለማፍረስ ፣የእግዚአብሔር ልጅ ተገልጧል፡፡ 9 የእግዚአብሔር ዘር በርሱ ስለሚኖር ፣ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢያትን አያደርግም፤ ከእግዚአብሔር ተወልዷልና ኃጢያትን ሊያደርግም አይችልም። 10 በዚህም የእግዚአብሔር ልጆችና የዲያብሎስ ልጆች ይታወቃሉ፡፡ ፅድቅን የማያደርግ ወይም ወንድሙን የማይወድ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም፡፡ 11 ከመጀመሪያው የሰማችኋት መልእክት፣ይህ እርስ በርሳችን እንድንዋደድ የሚለው ነው። 12 ክፉ እንደሆነውና ወንድሙን እንደ ገደለው እንደ ቃየል አይደለም። የገደለው ለምንድን ነው? ምክንያቱ የራሱ ሥራ ክፉ፣ የወንድሙ ጽድቅ ስለነበረ ነው፡፡ 13 ወንድሞች፣ ዓለም ቢጠላችሁ፣አትደነቁ። 14 ወንድሞችን ስለምንወድ ፣ከሞት ወደ ህይወት እንደተሻገርን እናውቃለን። ፍቅር የሌለው በሞት ውስጥ ይኖራል፡፡ 15 ወንድሙን የሚጠላ ነፍሰ ገዳይ ነው፡፡ ነፍሰ ገዳይ የሆነ ሁሉ፣ በውስጡ የዘላለም ህይወት እንደሌለው ታውቃላችሁ፡፡ 16 ክርስቶስ ለእኛ ህይወቱን ሰጥቷልና፣በዚህ ፍቅርን እናውቃለን።እኛም ለወንድሞቻችን ህይወታችንን አሳልፈን መስጠት ይገባናል። 17 ነገር ግን ማንም የዚህ ዓለም ንብረት ያለውና፣ወንድሙም የሚያስፈልገውን አውቆ፣ባይራራለት፣ እንዴት የእግዚአብሔር ፍቅር በርሱ ይኖራል? 18 የተወደዳችሁ ልጆቼ ፣በሥራና በእውነት እንጂ ፣በቃል ወይም በአንደበት አንዋደድ። 19 በዚህም ከእውነት እንደሆንንና፣ልባችንም በፊቱ ትክክል እንደሆነ እናረጋግጣለን። 20 ልባችን ግን የሚፈርድብን ከሆነ፣ እግዚአብሔር ከልባችን ይልቅ ታላቅ ነው፣ሁሉንም ያውቃል፡፡ 21 ወዳጆች ሆይ! ልባችን የማይፈርድብን ከሆነ፣በእግዚአብሔር ፊት ድፍረት አለን። 22 ትዕዛዙን የምንጠብቅና፣በፊቱ ደስ የሚያሰኘውን የምናደርግ ስለሆነ፣ የምንለምነውንና ሁሉ እንቀበላለን፡፡ 23 የርሱም ትዕዛዙ፣በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንድናምንና፣ ትእዛዙን እንደሰጠን እንደዚያው እርስ በርስ እንድንዋደድ ነው፡፡ 24 የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ የሚጠብቅ ፣በርሱ ይኖራል እግዚአብሔርም በርሱ ይኖራል፡፡በዚህም በሰጠን በመንፈሱ፣ በእኛ ውስጥ እንደሚኖር እናውቃለን።
በዚህ ክፍል ዮሐንስ አማኞችን ኃጢአት ስለ መሥራታቸው ስለ አዲሱ ተፈጥሮአቸውም ይነግራቸዋል ፡፡
“አባታችን ምን ያህል እንደሚወደን አስቡ” (ዩዲቤ)
“አብ ልጆቹ ብሎ ጠርቶናል”
እዚህ ማለት ይህ ማለት የእግዚአብሔር በእምነት የሆኑት በኢየሱስ ነው ፡፡
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “እኛ የእግዚአብሔር ልጆች ስለሆንን ዓለምም እግዚአብሔርን ስለማያውቅ እርሱ እኛን አያውቀንም” ወይም 2) “ዓለም እግዚአብሔርን ስላላወቀች እኛን አያውቀንም” ፡፡
እዚህ “ዓለም” የሚያመለክተው እግዚአብሔርን የማያከብሩ ሰዎችን ነው ፡፡ ዓለም ያላወቀው ነገር ግልፅ ሊሆን ይችላል: - AT: “እግዚአብሔርን የማያከበሩ እኛ ከእግዚአብሔር እንደሆንን አያውቁምና እግዚአብሔርን አላወቁምምና” (የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር ግልፅ)
"እኔ የምወዳቸው ሰዎች" ወይም "ውድ ጓደኞቼ" ፡፡ በ 2 7 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል-AT “እግዚአብሔር ገና አልገለጠም” (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ይህ እዚህ “ሊነገር” ወይም “የታየ ፣” “የታየ” ማለት ሊሆን ይችላል።
ክርስቶስን እንደ እርሱ በልበ ሙሉነት የሚጠብቅ ሁሉ ክርስቶስ ንጹህ ስለሆነ ራሱን ያነጻል።
"የእግዚአብሔርን ህግ ለመታዘዝ ፈቃደኛ አይደለም" (ዩ.አር.ቢ.)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት-“ክርስቶስ ተገለጠ” ወይም “አብ ክርስቶስ ተገለጠ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ከእግዚአብሔር ጋር ግንኙነት አለው ፡፡ ይህ በ 2 4 ውስጥ እንዴት እንደተተረጎመ ይመልከቱ ፡፡
ዮሐንስ “የታየው” እና “የታወቀ” የሚሉትን ቃላት ተጠቅሞ ኃጢአት የሚሠራ ሰው ክርስቶስን በመንፈሳዊ አግኝቶ አያውቅም ማለት ነው ፡፡ እንደ ኃጢአተኛ ተፈጥሮው የሚያደርግ ሰው ክርስቶስን ማወቅ አይችልም ፡፡ አት: - ማንም ማንም በእርሱ (በእርሱ) በእውነት አላምንም ”(ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ጆን አረጋዊ እና መሪያቸው ነበር ፡፡ እሱ ለእነሱ ያለውን ፍቅር ለማሳየት በዚህ አገላለጽ ተጠቅሟል። አት: - “በክርስቶስ ውስጥ ልጆቼ” ወይም “እናንተ እንደ ልጆቼ እኔን የምትወደዱኝ” ፡፡ በ 2 1 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ክርስቶስን ላለመታዘዝ ሲታመን አንድ ሰው የሚከተለው ትክክለኛውን ጎዳና እንደሚተው ተደርጎ ይገለጻል። አት: - "ማንም አያታልልህ" ወይም "ማንም እንዳያታልልህ አትፍቀድ" (ዩ.አር.ቢ.)
ክርስቶስ እግዚአብሔርን ደስ እንደሚያሰኘው ፣ ትክክል የሆነውን የሚያደርግ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኛል።
“የዲያቢሎስ ወገን” ወይም “እንደ ዲያቢሎስ ነው” (ዩ.ቢ.ቢ.)
ይህ የሰው ልጆች መጀመሪያ ኃጢአት ከመሥራታቸው በፊት ይህ የፍጥረት የመጀመሪያ ጊዜን ያመለክታል። አት: - “ከመጀመሪያው ፍጥረት ጊዜ ጀምሮ” (ይመልከቱ።
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ልጁን ገለጠለት” (የበለስ_ቁጥር / ተመልከት)
ይህ ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት የሚገልጽ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
ዮሐንስ ይህንን ክፍል በአዲሱ መወለድ እና ኃጢአት ባልሠራው አዲስ ተፈጥሮ ላይ ያጠናቅቃል ፡፡
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ልጁን ያሠራው” (የበለስ_ቁጥርን ይመልከቱ)
ይህ የሚያስተምረው እግዚአብሔር ለአማኞች ስለሰጣቸውና ኃጢአትን እንዲቋቋሙ የሚያስችላቸውን እና በምድር ላይ የተተከለውን የሚያድግ አካላዊ ዘርን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውን ስለሚያደርግ መንፈስ ቅዱስ ነው ፡፡ ይህ አንዳንድ ጊዜ አዲሱ ተፈጥሮ ተብሎ ይጠራል። አት: - “መንፈስ ቅዱስ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት-“እግዚአብሔር አዲስ መንፈሳዊ ሕይወት ሰጠው” ወይም “እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነው” (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ አት: - "እኛ የእግዚአብሔርን ልጆችና የዲያብሎስን ልጆች እኛ በዚህ እናውቃለን።" (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
እዚህ “ወንድም” ማለት የእምነት ባልንጀሮች ማለት ነው ፡፡ "ከእግዚአብሔር ብቻ ጽድቅን የሚያደርጉ እና ወንድሞቻቸውን የሚወዱ ብቻ ናቸው"
እዚህ ላይ አማኞችን እርስ በእርሱ እንዴት እንደሚተያዩ ዮሐንስ ያስተምራቸዋል ፣ አንባቢዎቹ እርስ በእርሱ እንዲዋደዱ ያስተምራቸዋል።
ቃየንና አቤል የመጀመሪያዎቹ ወንድና ሴት የመጀመሪያዎቹ የአዳምና የሔዋን ልጆች ነበሩ ፡፡
ቃየን እንዳደረገው ማድረግ የለብንም ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ሊሴስ)
ይህ ቃየን ታናሽ ወንድሙን አቤልን ያመለክታል ፡፡
ዮሐንስ አድማጮቹን ለማስተማር ጥያቄን ይጠቀማል ፡፡ ይህ እንደ መግለጫ ሊተረጎም ይችላል ፡፡ አት-“እሱን ገደለው ምክንያቱም” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
የወንድሙ ሥራ መልካም ነበር ፡፡ አት: - “እሱ መጥፎ ነገሮችን አድርጓል ፣ ወንድሙም ትክክል የሆነውን አደረገ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ሊሴስ)
አማኞች
እዚህ “ዓለም” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔርን የማያከብሩ ሰዎችን ነው ፡፡ አት: - “እግዚአብሔርን የማያከበሩ እግዚአብሔርን የሚጠሉህ ቢጠሉህ” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
የኑሮ ሁኔታ እና የሞቱ ሁኔታዎች አንድ ሰው ሊሄድበት እና ሊሄድበት የሚችል አካላዊ ሥፍራዎች እንደሆኑ ተደርገው ይገለጻል ፡፡ አት: - “ከእንግዲህ በመንፈሳዊው በድን አይደለንም ፣ ነገር ግን በመንፈሳዊ ሕያው ሆነናል” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
በዚህ ደብዳቤ ውስጥ “ሕይወት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ከአካላዊ ሕይወት በላይ ነው ፡፡ ለኢየሱስ የዘላለም ሕይወቱ እዚህ ይቆማል ፡፡ ይህንን በ 1 1 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
“አሁንም በመንፈሳዊው የሞተ ነው”
ዮሐንስ ሌላውን አማኝ የሚጠላ ሰው ነፍሰ ገዳይ ነው ብሏል ፡፡ ሰዎች ሰዎችን የሚገድሉት ሌሎችን ስለሚጠሉ ፣ እግዚአብሔር የሚጠላውን ሰው እንደ መግደል ጥፋተኛ አድርጎ የሚቆጥር ነው ፡፡ አት: - “ሌላ አማኝ የሚጠላ ሰው አንድን ሰው እንደሚገድል ጥፋተኛ ነው” (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
“የዘላለም ሕይወት” እግዚአብሔር አማኞችን ከሞቱ በኋላ የሚሰጥ ነገር ነው ፣ ግን ደግሞ በዚህ ሕይወት አማኞች ኃጢአት መሥራታቸውን እንዲያቆሙ እና እሱን ደስ የሚያሰኙትን ለማድረግ እንዲረዳቸው እግዚአብሔር የሚሰጥ ኃይል ነው ፡፡ እዚህ የዘላለም ሕይወት በአንድ ሰው ውስጥ ሊሆን የሚችል ዕቃ እንደሆነ ተደርጎ ተገልጻል ፡፡ አት: - “ነፍሰ ገዳይ በሱ ውስጥ የሚሠራ የመንፈሳዊ ሕይወት ኃይል የለውም” (ይመልከቱ።
ይህ አገላለጽ “ክርስቶስ ነፍሱን ለእኛ በፈቃደኝነት ሰጠ” ወይም “ክርስቶስ እኛን በፈቃደኝነት ለእኛ ሞቷል” ማለት ነው (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ ቪዲዮም)
እንደ ገንዘብ ፣ ምግብ ወይም ልብስ ያሉ ቁሳዊ ንብረቶች
የእምነት ባልንጀራችን እርዳታ እንደሚያስፈልገው መገንዘቡ
“የርኅራ heart ልብውን ይዘጋል” ዘይቤ ነው። አት: - “ግን አያሳዝነውም” ወይም “ግን በፈቃደኝነት አይረዳውም” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
ዮሐንስ አድማጮቹን ለማስተማር ጥያቄን ይጠቀማል ፡፡ አት: - “የእግዚአብሔር ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም” (የበለስ_ቁጥር ተመልከት)
ጆን አረጋዊ እና መሪያቸው ነበር ፡፡ እሱ ለእነሱ ያለውን ፍቅር ለማሳየት በዚህ አገላለጽ ተጠቅሟል። አት: - “በክርስቶስ ውስጥ ልጆቼ” ወይም “እናንተ እንደ ልጆቼ እኔን የምትወደዱኝ” ፡፡ በ 2 1 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
ሀረጎች "በቃላት" እና "በምላስ" ሁለቱም አንድ ሰው የሚናገረውን ያመለክታሉ ፡፡ አት: - “ሰዎችን ትወዳለህ ብቻ አትበል” (የበለስ_ቁጥር እና የበለስ_ቁጥር) ይመልከቱ
“ፍቅር” የሚለው ግስ የተወሰደው ከዚህ ዓረፍተ ነገር የመጀመሪያ አጋማሽ ነው ፡፡ አት: - “ግን ሰዎችን በመርዳት በእውነት እንደምትወዱ አሳይ” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ሊሴስ)
እዚህ ላይ ዮሐንስ ምናልባት አማኞች እግዚአብሔርን እና እርስ በእርሱ ከልብ የመውደድ ችሎታቸው (ቁጥር 18 ን ይመልከቱ) አዲሱ አኗኗራቸው በእውነት ስለ ክርስቶስ እውነተኛ የመሆኑ ምልክት ነው ፡፡
እኛ ከእውነት ነን ወይም አ.ማ. “ኢየሱስ እንዳስተማረን እንኖራለን”
እዚህ ላይ “ልብ” የሚለው ቃል ስሜትን ያመለክታል ፡፡ አት: - “የጥፋተኝነት ስሜት አይሰማንም” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ይህ ዘይቤ ነው ፡፡ አት: - “ኃጢአት መሥራታችንን እና በዚህም ምክንያት የጥፋተኝነት ስሜት የሚሰማን ከሆነ” (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
እግዚአብሔር ከአንድ አካል በላይ ያውቃል እንዲሁም በተሻለ ይፈርዳል ፡፡ የዚህ እውነት ውጤት ምናልባት ሕሊናችን ከሚያስበው በላይ እግዚአብሔር መሐሪ መሆኑን ነው ፡፡ ይህ የእግዚአብሔር ባሕርይ “ታላቅ” በሚለው ቃል ይገለጻል። አት: - “እግዚአብሔር ከአዋቂነታችን የበለጠ ያውቃል” (የበለስ_ቁጥር ን ይመልከቱ)
"እኔ የምወዳቸው ሰዎች" ወይም "ውድ ጓደኞቼ" ፡፡ በ 2 7 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
የእግዚአብሔር አመለካከት የሚናገረው በፊቱ ላይ በሚታየው ነገር ላይ የተመሠረተ ስለሆነ ነው ፡፡ አት: - “እሱ እሱን የሚያስደስተውን እናደርጋለን” (የበለስ_ቁጥር ይመልከቱ)
"እግዚአብሔር እንድናደርግ ይፈልጋል"
ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
የአማኞች የቅርብ ትብብር “በእርሱ አለ” በሚለው ሐረግ ይገለጻል ፡፡ በ 2 4 ውስጥ “በእግዚአብሔር ውስጥ መቆየት” እንዴት እንደተተረጎመ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
1 ወዳጆች ሆይ! መንፈስን ሁሉ አትመኑ፣ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር መሆናቸውን መርምሩ፣ ምክንያቱም ብዙ ሃሰተኛ ነቢያት ወደ ዓለም ገብተዋል፡፡ 2 የእግዚአብሔርን መንፈስ በዚህ እናውቃለን፣- ጌታ ኢየሱስ በሥጋ እንደመጣ የሚቀበል መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው። 3 ኢየሱስን የማይቀበል መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም። ይህ እንደሚመጣ የሰማችሁት የክርስቶስ ተቃዋሚው መንፈስ ነው፣ አሁን እንኳ በዓለም ውስጥ አለ፡፡ 4 የተወደዳችሁ ልጆች! እናንተ ከእግዚአብሔር ስለሆናችሁ፣ እነዚህን መናፍስት አሸንፋችኋል፣ ምክንያቱም በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ይበልጣል፡፡ 5 እነዚህ መናፍስት ከዓለም ናቸው፣ስለሆነም የሚናገሩት ሁሉ የዓለምን ነው፣ዓለምም ይሰማቸዋል፡፡ 6 እኛ ከእግዚአብሔር ነን። እግዚአብሔርን የሚያውቅ ይሰማናል። ከእግዚአብሔር ያልሆነ ግን አይሰማንም። በዚህም የእውነት መንፈስንና ፣የስህተትን መንፈስን እናውቃለን፡፡ 7 ወዳጆች ሆይ! እርስ በርስ እንዋደድ፣ምክንያቱም ፍቅር ከእግዚአብሔር ነውና፣ ፍቅር ያለው ከእግዚአብሔር ተወልዷል፣ እግዚአብሔርንም ያውቃል፡፡ 8 ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፣እግዚአብሔር ፍቅር ነውና፡፡ 9 በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በመካከላችን ተገልጧል፣ እግዚአብሔር በርሱ እንድንኖር ፣አንድ ልጁን ወደ ዓለም ላከው፡፡ 10 ፍቅር እንደዚህ ነው፣እግዚአብሔርን ስለወደድነው ሳይሆን፣ እርሱ ስለወደደን ለኃጢያታችን ማስተሰረያ እንዲሆን ልጁን ላከ፡፡ 11 ወዳጆች ሆይ! እግዚአብሔር ይህን ያህል ከወደደን፣እኛም እርስ በርሳችን መዋደድ ይገባናል። 12 ማንም እግዚአብሔርን አላየውም። እርስ በርሳችን ብንዋደድ፣ እግዚአብሔር በኛ ይኖራል፣ ፍቅሩም በእኛ ፍጹም ይሆናል፡፡ 13 መንፈሱን ሰጥቶናልና፣ በዚህም እኛ በእርሱ እንደምንኖር፣ እርሱም በኛ እንደሚኖር እናውቃለን። 14 እኛም አይተናል፣እግዚአብሔር ልጁን የዓለም አዳኝ አድርጐ እንደላከውም እንመሰክራለን፡፡ 15 ማንም ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ቢቀበል፣ እግዚአብሔር በርሱ ይኖራል ፤እርሱም በእግዚአብሔር ይኖራል፡፡ 16 እኛም እግዚአብሔር ለኛ ያለውን ፍቅር አውቀናል ደግሞም አምነናል። እግዚአብሔር ፍቅር ነው፣ በፍቅር የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል፣እግዚአብሔርም በርሱ ይኖራል፡፡ 17 በፍርድ ቀን ድፍረት እንዲኖረን፣ይህም ፍቅር በመካከላችን ተፈጸሟል፣ እኛም በዚህ ዓለም እንደ እርሱ ነን ፡፡ 18 በፍቅር ፍርሃት የለም። ነገር ግን ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል፣ ምክንያቱም ፍርሃት የሚያመለክተው ቅጣት መኖሩን ነው። የሚፈራ ግን ፍቅሩ ፍፁም አይደለም፡፡ 19 አስቀድሞእግዚአብሔር ወዶናልና፣እኛም እንወደዋለን። 20 አንድ ሰው "እግዚአብሔርን እወዳለሁ" እያለ ወንድሙን ግን ቢጠላ ሃሰተኛ ነው፤የሚያየውን ወንድሙን የማይወድ፣ የማያየውን እግዚአብሔርን ሊወድ አይችልም። 21 እግዚአብሔርን የሚወድ ወንድሙን መውደድ አለበት፣የሚል ትእዛዝ ከእግዚአብሔር ተቀብለናል።
ዮሐንስ የሰውን አካል ስላለውና ዓለምን የሚወዱ ሰዎችን በሚናገሩበት መንገድ በሚናገሩ አስተማሪዎች ላይ ዮሐንስ ማስጠንቀቂያ ይሰጣል ፡፡
"እኔ የምወዳቸው ሰዎች" ወይም "ውድ ጓደኞቼ" ፡፡ በ 2 7 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
እዚህ ፣ “መንፈስ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ለአንድ ሰው መልእክት ወይም ትንቢት የሚናገር መንፈሳዊ ሀይልን ወይም መሆንን ነው ፡፡ አት: - “ከመንፈስ መልእክት አለኝ የሚል ማንኛውንም ነቢይ አትመኑ” (ይመልከቱ ፡፡
እዚህ ፣ “መናፍስት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ለአንድ ሰው መልእክት ወይም ትንቢት የሚናገር መንፈሳዊ ሀይልን ወይም መሆንን ነው ፡፡ አት: - “ነብዩ የሚናገረውን በጥሞና ማዳመጥህን እርግጠኛ ሁን” (የበለስ_ቁልፍ ቃል ተመልከት)
“አረጋግጥ”
“በሰው መልክ ተለወጠ” ወይም “በሥጋዊ አካል መጥቷል” (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
“እነሱ ክርስቶስን የሚቃወሙ አስተማሪዎች ናቸው” ወይም “ክርስቶስን የሚቃወሙ አስተማሪዎች ናቸው” (ዩቢቦ)
“የክርስቶስ ተቃዋሚ። እንደዚህ ያሉ ሰዎች በመካከላችን እንደሚመጡ ሰምታችኋል”
“መምጣት ፣ አሁን እንኳ እዚህ አሉ (UDB)
ጆን አረጋዊ እና መሪያቸው ነበር ፡፡ እሱ ለእነሱ ያለውን ፍቅር ለማሳየት በዚህ አገላለጽ ተጠቅሟል። AT: - “በክርስቶስ የምትወዳቸው ልጆቼ” ወይም “እንደ እኔ ልጆቼ እኔን የምትወደውን” በ 2 1 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
“ሐሰተኛ መምህራንን አላመኑም”
"በአንተ ውስጥ ያለው አምላክ"
ሁለት ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “እነዚያ ዓለማዊ አስተማሪዎች ወይም 2)“ በዓለም ያለው ሰይጣን ”፡፡
“ዓለም” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔርን የማይታዘዙትን ሰዎች እና በኃጢያተኛው ዓለም ውስጥ ያለውን የክፋት ሥርዓት ነው። (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
“እነዚያ ሐሰተኛ አስተማሪዎች እግዚአብሔርን የማይታዘዙ ሰዎች ናቸው” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ስለሆነም እግዚአብሔርን የሚቃወሙ ሀሳቦችን ያስተምራሉ ”
"ስለሆነም የማያምኑ ሰዎች እግዚአብሔር ይሰማቸዋል" (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ዮሐንስ ስለ አዲሱ ተፈጥሮ ማስተማሩን ቀጠለ ፡፡ አንባቢዎቹን ስለ እግዚአብሔር ፍቅር እና እርስ በእርስ ስለሚዋደዱ ያስተምራቸዋል።
"እኔ የምወዳቸው ሰዎች" ወይም "ውድ ጓደኞቼ" ፡፡ በ 2 7 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
“አማኞች ሌሎች አማኞችን መውደድ አለባቸው”
የእምነት ባልንጀሮቻቸውን የሚወዱ የእግዚአብሔር ልጆች ሆነዋልና እሱን ያውቃሉ ”(ዩዲ ቢ)
እርስ በርሳችን እንድንዋደድ ያደርገናልና ”
ይህ ዘይቤያዊ አነጋገር ነው አንድ ሰው ከአባቱ ጋር እንደ ልጅ ከአባቱ ጋር ወደ እግዚአብሔር ግንኙነት አለው ማለት ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
"የእግዚአብሔር ተፈጥሮ ሰዎችን መውደድ ነው ፡፡ የእምነት ባልንጀሮቻቸውን የማይወዱ ሁሉ እግዚአብሔርን አያውቁም ምክንያቱም የእግዚአብሔር ባሕርይ ሰዎችን መውደድ ነው ፡፡"
ይህ ዘይቤያዊ አነጋገር ሲሆን "የእግዚአብሔር ባሕርይ ፍቅር ነው" ማለት ነው (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ይህ ንቁ ሊሆን ይችላል። አትቲ: - "በዚህ እግዚአብሔር እንደ ወደደን አሳየን" (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
እግዚአብሔር ሁሉንም ሰው የሚወድ መሆኑ እግዚአብሔር ሊያሳያቸው የሚችል ነገር እንደሆነ ተደርጎ ተገልጻል ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
"ኢየሱስ ባደረገው ነገር ምክንያት ለዘላለም እንድንኖር እኛን ለማገዝ"
"እውነተኛ ፍቅር ማለት እግዚአብሔር አሳየን"
"ፍቅር እውነተኛ ፍቅር እግዚአብሔርን የምንወድበት ሳይሆን እሱ እኛን የወደደን እርሱ ነው ፡፡"
እዚህ ላይ “መስዋእትነት” ወልድ ወልድ ለሰው ልጆች ሁሉ ኃጢአት መስዋእት የሚሆንበትን ክስተት ነው። አት-“እግዚአብሔር ኃጢአታችንን ይቅር እንዲለን ልጁን እንዲሠዋለት ልጁን ልኮታል” (የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
"እኔ የምወዳቸው ሰዎች" ወይም "ውድ ጓደኞቼ" ፡፡ በ 2 7 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
እግዚአብሔር በዚህ መንገድ ይወደናልና።
“አማኞች ሌሎች አማኞችን መውደድ አለባቸው”
"እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ግንኙነት አለው ... ከእግዚአብሔር ጋር ግንኙነት አለን እሱ ደግሞ ከእኛ ጋር ግንኙነት አለው" ብለዋል ፡፡ ይህ በ 2 4 ውስጥ እንዴት እንደተተረጎመ ይመልከቱ ፡፡
"የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ውስጥ ፍጹም ነው"
ከ “በዚህ” ወይም “ምክንያቱም” ብትተው ትርጉምዎ የበለጠ ግልፅ ሊሆን ይችላል ፡፡ AT: “እኛ እናውቃለን… እሱ የሰጠነው” ወይም “በዚህ እናውቃለን… እኛ: ሰጠን”
“መንፈሱን ስለ ሰጠን” ወይም “መንፈሱን በውስጣችን ስላስቀመጠ” ይህ ሐረግ ግን እግዚአብሔር ከሰጠን በኋላ መንፈሱን ያንሳል ማለት አይደለም ፡፡
እኛም እኛ ሐዋርያት የእግዚአብሔርን ልጅ አይተናል ፣ እናም እግዚአብሔር አብ በዚህ ምድር ሰዎችን ለማዳን ልጁን እንደ ላከ ለሁሉም እንናገራለን ”
እነዚህ በእግዚአብሔር እና በኢየሱስ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚገልፁ አስፈላጊ አርዕስት ናቸው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
“ስለ ኢየሱስ የሚናገሩ ሁሉ የእግዚአብሔር ልጅ ነው”
ይህ ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት የሚገልጽ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
"እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ግንኙነት አለው እርሱም ከእግዚአብሔር ጋርም ግንኙነት አለው ፡፡" ይህንን በ 2 4 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡
ይህ ዘይቤያዊ አነጋገር ሲሆን "የእግዚአብሔር ባሕርይ ፍቅር ነው" ማለት ነው ፡፡ ይህንን በ 4 7 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
“ሌሎችን መውደዳቸውን የሚቀጥሉ ከእግዚአብሔር ጋር የጠበቀ ወዳጅነት አላቸው ፣ እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር የጠበቀ ግንኙነትም አለው”
ይህ በንቃት ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) “በዚህ ምክንያት” የሚያመለክተው 4 15 ላይ ነው ፡፡ AT: “በፍቅር የሚኖር ሁሉ በእግዚአብሔር ውስጥ ነው ፣ እግዚአብሔር በእርሱም ውስጥ ስለሆነ ፣ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር ፍጹም አድርጎታል ፣ እናም ስለዚህ ሙሉ ትምክህት ሊኖር ይችላል” ወይም 2) “በዚህ ምክንያት” የሚያመለክተን መተማመን አለብን ፡፡ " አት: - "እግዚአብሔር በሁሉም ላይ በሚፈርድበት ቀን እንደሚቀበለ እርግጠኞች ነን ፣ ስለሆነም እርሱ ለእኛ ያለውን ፍቅር እንዳበቃ እናውቃለን" (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተፈጸመ።
"እኛ ከእግዚአብሔር ጋር ያለው ግንኙነት በዚህ ዓለም ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ተመሳሳይ ግንኙነት ነው"
እዚህ “ፍቅር” ፍርሃትን የማስወገድ ኃይል ያለው ሰው ተብሎ ተገልጻል ፡፡ የእግዚአብሔር ፍቅር ፍጹም ነው ፡፡ አት: - “ፍቅራችን ሲጠናቀቅ ግን ከእንግዲህ አንፈራም” (ይመልከቱ።
በሁሉም ላይ ለመፍረድ በሚመጣበት ጊዜ እግዚአብሔር ይቀጣናል ብለን ስለምንፈራ እንፈራለን ”
"አንድ ሰው እግዚአብሔር ይቀጣል ብሎ ሲፈራ ፍቅሩ አልተጠናቀቀም"
የእምነት ባልንጀራውን ይጠላል (UDB)
በተከታታይ ሁለት አሉታዊ መግለጫዎች ግራ የሚያጋቡ ከሆኑ ይህ በተለየ ሊተረጎም ይችላል ፡፡ AT: - “ወንድሙን የሚወድ ወንድሙን ይወዳል ፣ እግዚአብሔርንም ይወዳል” (ያየዋል)
1 ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ሆነ የሚያምን ሁሉ ከእግዚአብሔር ተወልዷል።አባት የሆነውን የሚወድ ሁሉ፣ከርሱ የተወለደውን ደግሞ ይወዳል። 2 እግዚአብሔርን ስንወድና ትዕዛዙን ስንፈጽም፣ የእግዚአብሔርን ልጆች እንደምንወድ በዚህ እናውቃለን። 3 እግዚአብሔርን የምንወደው የርሱን ትእዛዙን በመጠበቃችን ነው። የርሱም ትእዛዛት ከባዶች አይደሉም። 4 ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋል። ዓለምን የሚያሽንፈው እምነታችን ነው። 5 ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ከሚያምን በቀር፣ ዓለምን የሚየሸንፍ ማነው? 6 በውሃና በደም የመጣው እርሱም ነው፣እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ፣ በውሃ ብቻ ሳይሆን፣ነገር ግን በውሃና በደም የመጣ ነው። 7-8 የጥንቶችቹ የተሻሉት ቅጅዎች ይተውታል። ሦሶት ምስክሮች አሉ፤እነርሱም መንፈሱ ፣ውሃውና ደሙ ናቸው፤ሦስቱም በአንድ ይስማማሉ። 9 የሰዎችን ምስክርነት የምንቀበል ከሆነ፣ የእግዚአብሔር ምስክርነት ደግሞ የበለጠ ነው። እግዚአብሔር ስለ ጁል የሰጠው ምስክር ይህ ነው። 10 በእግዚአብሔር ልጅ የሚያምን በውስጡ ምስክር አለው። በእግዚአብሔር የማያምን ፣እግዚአብሔር ስለ ልጁ የመሰከረውን ምስክር ስለማያምን ሐሰተኛ አድርጎታል። 11 ምስክሩም ይህ ነው ፣እግዚአብሔር የዘላለምን ህይወት እንደሰጥንና፣ይህም ህይወት በልጁ መሆኑ ነው። 12 ልጁ ያለው ሕይወት አለው፥ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም። 13 በእግዚአብሔር ልጅ ስም ለምታምኑ፣የዘላለም ህይወት እንዳላችሁ እንድታውቁ ፣እነዚህን ነገሮች እጽፍላችኋለሁ። 14 በእርሱ ፊት ያለን ድፍረት ይህ ነው፣እንደ ፈቃዱ ማንኛውንም ነገር ብንጠይቀው፣ይሰማናል። 15 የምንጠይቀውን ሁሉ እንደሚሰማን ካወቅን፣ከርሱ የጠየቅነውን ሁሉ እንደተቀበልን እናውቃለን። 16 ማንም ወንድሙ ለሞት የማያበቃ ሃጢዓት ሲያደርግ ቢያይ፣ መጸለይ ይገባዋል፣ሞት የማይገባውን ሃጢዓት ለሚያደርጉት እግዚአብሔር ህይወትን ይሰጣል። ለሞት የሚያበቃ ኃጢዓት አለ። ያንን የተመለከተ ልመና እንዲያደርግ አላልኩም። 17 ዓመጽ ሁሉ ኃጢዓት ነው፣ ነገር ግን ለሞት የማያበቃ ኃጢዓት አለ። 18 ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢዓት እንደማያደርግ እናውቃለን፣ከእግዚአብሔር የተወለደውን፣እግዚአብሔር ከክፉ ይጠብቀዋል ፣ክፉውም አይነካውም። 19 እኛ ከእግዚአብሔር እንደሆንን፣ዓለም ሁሉ በክፉው ቁጥጥር ሥር እንደሆነ እናውቃለን። 20 እኛ ግን የእግዚአብሔር ልጅ እንደመጣና እውነት የሆነውን እንድናውቅ ማስተዋል እንደሰጠን እናውቃለን፤ እኛም እውነት በሆነው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ እንዳለን እናውቃለን። እርሱም እውነተኛ አምላክና የዘላለም ህይወት ነው። 21 ልጆች ሆይ! ከጣዖታት ዓምልኮ ራሳችሁን ጠብቁ።
አንባቢዎቹን ስለ እግዚአብሔር ፍቅር እና አማኞች ሊኖሯቸው ስለሚገባው ፍቅር አንባቢዎቹን ማስተማሩን ቀጥሏል ምክንያቱም ከእግዚአብሔር የተገኘ አዲስ ተፈጥሮ ስላለው ፡፡
የእግዚአብሔር ልጅ ነው
እግዚአብሔርን ስንወድ እና እርሱ ያዘዘውን ስናደርግ ፣ ልጆቹን እንደምንወድ እናውቃለን ፡፡
እሱ ያዘዘውን ነገር ስናደርግ ይህ ለእግዚአብሔር እውነተኛ ፍቅር ነው ”
እሱ ያዘዘውም አስቸጋሪ አይደለም ”
“ከባድ ፣” “ስንጥቅ” ወይም “አስቸጋሪ”
የእግዚአብሔር ልጆች ሁሉ
“በዓለም ላይ ድል አለው ፣” “ከዓለም ጋር ይሳካል ፣” ወይም “የማያምኑትን መጥፎ ነገር ለማድረግ ፈቃደኛ አለመሆን”
በእምነታችን ላይ ኃጢአት እንድንሠራ የሚያደርገንን ማንኛውንም ነገር እንድንቋቋም እምነታችን ይሰጠናል ”
ዮሐንስ ለማስተማር የፈለገውን ነገር ለማስተዋወቅ ይህንን ጥያቄ ተጠቅሞበታል ፡፡ አት: - "ዓለምን የሚያሸንፍ እነግራችኋለሁ" (የበለስ_ቁስለትን ይመልከቱ)
ይህ ምንባብ በዓለም ላይ ያሉትን ኃጢአተኛ ሰዎች እና በዓለም ያሉትን ክፉ ሥርዓቶች ሁሉ ለማመልከት “ዓለምን” ይጠቀማል ፡፡ አት: - "በእግዚአብሔር ላይ ያለው ዓለም ሁሉ" (የበለስ_ቁጥር / ይመልከቱ)
ይህ የሚያመለክተው አንድን የተወሰነ ሰው አይደለም ፣ ነገር ግን ይህንን ለሚያምን ለማንኛውም። አት: - “ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው የሚል እምነት ያለው።”
ይህ ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት የሚገልጽ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እና እግዚአብሔር ስለ እርሱ ምን እንዳለ አስተምሯል ፡፡
“በውኃና በደሙ የመጣው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው” እዚህ “ውሃ” ለኢየሱስ ጥምቀት ምናልባት ምሳሌ ነው ፣ እና “ደም” ደግሞ በመስቀል ላይ የኢየሱስ ሞት ነው። አትቲን: - "ኢየሱስ በተጠመቀበት እና በመስቀል ላይ መሞቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ልጁ መሆኑን እግዚአብሔር አሳይቶታል" (የበለስ_ቁልፍ / ምሳሌን ይመልከቱ)
ውሃ የሚያመለክተው የኢየሱስን ጥምቀት እና ደሙ የኢየሱስን በመስቀል ላይ መሞቱን ነው። AT: "እግዚአብሔር በጥምቀቱ ጊዜ የእርሱ ልጅ መሆኑን አላሳየንም ፣ ግን በጥምቀቱ እና በመስቀል ላይ በሞቱ" (ይመልከቱ። የበለስ_ቁጥር)
ተርጓሚው እግዚአብሔር የሚናገረውን ለማመን የምንችልበትን ምክንያት የበለጠ ግልፅ በሆነ ሁኔታ መግለፅ ይችላል AT ““ ሰዎች የሚናገሩትን የምናምን ከሆነ እግዚአብሔር ሁል ጊዜ እውነቱን ስለሚናገር ማመን አለብን ”(የበለስ_ቁጥር 3 ን ይመልከቱ)
ሰዎች ስለ ብዙ ነገሮች የሚመሰክሩት ወይም የሚመሰክሩት የሚለው እዚህ ስለተጠቀሰው ሌሎች የተቀበሉት ነገር እንደሆነ አድርገው ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
የእግዚአብሔር ምስክርነት በጣም አስፈላጊ እና እምነት የሚጣልበት ነው
ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
"በኢየሱስ የሚያምን ሁሉ በእርግጠኝነት ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ያውቃል"
“እግዚአብሔርን ውሸታም ነው”
እግዚአብሔር ስለ ልጁ እውነቱን እንዳላመነ ስላላመነ "
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል (UDB)
እዚህ “ሕይወት” በእግዚአብሔር ጸጋ እና ፍቅር ለዘላለም የመኖር መብት ይቆማል ፡፡ ይህንን በ 1 1 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
ይህ ሕይወት በልጁ በኩል ነው ፣ ““ ከልጁ ጋር አብረን የምንኖረን ከሆነ ለዘላለም እንኖራለን ”(UDB) ወይም“ ከልጁ ጋር አንድ የምንሆን ከሆነ ለዘላለም እንኖራለን ”
ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
ከወልድ ጋር የጠበቀ ቅርርብ መኖሩ ወልድ እንዳለው ተነግሯል ፡፡ AT: - “በእግዚአብሔር ልጅ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው” (ይመልከቱ ፡፡ የበለስ_ቁጥር)
ይህ የዮሐንስ ወንጌል መጨረሻ ይጀምራል። ለደብዳቤው የመጨረሻ ዓላማ ለአንባቢዎቹ ይነግራቸዋል እንዲሁም የተወሰኑ ትምህርቶችን ይሰጣል ፡፡
ይህ ደብዳቤ
እዚህ “ስም” የእግዚአብሔር ልጅ ስም ነው ፡፡ አት: - በእግዚአብሔር ልጅ ለሚታመኑ
ይህ ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት የሚገልጽ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
እዚህ “ሕይወት” በእግዚአብሔር ጸጋ እና ፍቅር ለዘላለም የመኖር መብት ይቆማል ፡፡ ይህንን በ 1 1 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
እኛ ስለምናውቅ በእግዚአብሔር ፊት ልንተማመን አለብን ”(የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያ)
እግዚአብሔር የሚፈልገውን እንዲያደርግ ከጠየቅን ”
እግዚአብሔርን የጠየቅንበትን እንደምንቀበል እናውቃለን።
“አማኝ”
እዚህ “ሕይወት” በእግዚአብሔር ጸጋ እና ፍቅር ለዘላለም የመኖር መብት ይቆማል ፡፡ ይህንን በ 1 1 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
ይህ የሚያመለክተው ዘላለማዊ ሞት ማለት ነው ፣ ማለትም ከእግዚአብሔር ፊት የተገለጠውን ዘላለማዊነት።
ዮሐንስ ኃጢአትን ስለ መተው የማይችለውን አዲስ አማኞች ተፈጥሮ ምን እንደሚል በመመርመር ደብዳቤውን ይዘጋል እንዲሁም ራሳቸውን ከጣ idolsቶች እንዲጠብቁ ያሳስባል ፡፡
“ዓለም” አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ፀሐፊዎች በዓለም ላይ ስለሚኖሩት ሰዎች እና በዓለም ላይ በሁሉም መንገድ በኃይል ብልሹ ኃይል ውስጥ ለተጠቁት የዓለም ስርዓቶች የሚያመለክቱበት መንገድ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
በክፉው ኃይል ማለት ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
“እሱ” እና “እሱ” የሚሉት ቃላት ኢየሱስ ክርስቶስን ያመለክታሉ ፡፡
ይህ ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት የሚገልጽ ለኢየሱስ አስፈላጊ ርዕስ ነው ፡፡ (መመሪያዎችን ይመልከቱ) መመሪያዎች_ሶፍትዌር መመሪያዎች
"እውነቱን እንድንረዳ አስችሎናል" (UDB)
እዚህ “ሕይወት” በእግዚአብሔር ጸጋ እና ፍቅር ለዘላለም የመኖር መብት ይቆማል ፡፡ ይህንን በ 1 1 ውስጥ እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር ማስታወቂያዎች)
ይህ ክርስቶስ የዘላለምን ሕይወት ይሰጠናል ለሚለው አስተሳሰብ ነው ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁልፍ)
ጆን አረጋዊ እና መሪያቸው ነበር ፡፡ እሱ ለእነሱ ያለውን ፍቅር ለማሳየት በዚህ አገላለጽ ተጠቅሟል። አት: - “በክርስቶስ ውስጥ ልጆቼ” ወይም “እናንተ እንደ ልጆቼ እኔን የምትወደዱኝ” ፡፡ በ 2 1 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጉሙ ይመልከቱ ፡፡ (ይመልከቱ: የበለስ_ቁጥር)
1 ከሽማግሌው በእውነት ለምወዳችሁና እኔም ብቻ ሳልሆን እውነትን የሚያውቁ ሁሉ ለሚወዱአችሁ ለተመረጥች እመቤትና ለልጆችዋ ። 2 ይህም ፍቅር በውስጣችን ካለውና ለዘላለም ከእኛ ጋር ከሚሆነው እውነት የተነሳ ነው። 3 በእውነትና በፍቅር ከእግዚአብሔር አብ ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፣ምህረትና ሠላም ከሁላችን ጋር ይሁን። 4 ከልጆችሽ መካከል ከአብ በተቀበልነው ትዕዛዝ መሠረት በእውነት ሲሄዱ በማግኘቴ እጅግ ሀሴት አደርጋለሁ። 5 እንግዲህ እመቤት አሁን አዲስ ትዕዛዝ እንደምሰጥ ሳይሆን እርስ በእርሳችን እንዋደድ ብዬ ከመጀመሪያው በነበረን ትዕዛዝ እለምንሻለሁ። 6 ይህም በትዕዛዛቱ መሰረት ልንጓዝበት የሚገባን ፍቅር ነው። ይህ ትዕዛዝ ከመጀመሪያው እንደሰማችሁት ልትራመዱበት የሚገባ ትዕዛዝ ነው። 7 ምክንያቱም ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደመጣ የማያምኑ ብዙ አሳቾች ወደ ዓለም ወጥተዋል። ይህም አሳቹና የክርስቶስ ተቃዋሚ ነው። 8 ሙሉ ዋጋችሁን እንድትቀበሉ እንጂ እኛ ሁላችን የደክምንባቸውን ነገሮች እንዳታጡ ስለራሳችሁ ተጠንቀቁ። 9 በክርስቶስ ትምህርት ሳይጸና ዝም ብሎ ወደፊት የሚገሰግስ እግዚአብሄርን አያውቅም። በዚህ ትምህርት የሚጸና አብና ወልድ አሉት። 10 ማንም ወደ እናንተ መጥቶ ይህን ትምህርት ባያስተምር ወደ ቤታችሁ እንዲገባ አትፍቀዱለት ሠላምም አትበሉት። 11 ምክንያቱም ሠላምታ የሚሰጠው ሁሉ በክፉ ሥራው ይካፈላል። 12 የምጽፍላችሁ ብዙ ነገር ነበረኝ ነገር ግን በወረቀትና በቀለም ልጽፈው አልፈለግሁም። ነገር ግን ደስታችን ሙሉ ይሆን ዘንድ ወደ እናንተ ልመጣና ፊት ለፊት ላወራችሁ ተስፋ አደርጋለሁ። 13 የተመረጠችው እህትሽ ልጆች ሠላምታ ያቀርቡልሻል።
ሽማግሌው ይህ የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር የነበረውን ሐዋርያው ዮሐንስ የሚያመለክት ነው፡፡ ራሱን “ሽምግሌው” በማለት ይጠራል፡፤ ምክንያቱ አንድም በእድሜው ስላረጀ ወይም የቤተ ክርስቲያን መሪ በመሆኑ ሊሆን ይችላል፡፡ የተመረጠችው ሴት ሽማግሌ እና ልጆቿ በግሪክ ደብዳቤዎች የሚጀምሩት በዚህ ዓይነት መልኩ ነው፡፡ የደብዳቤው ጸሐፊ ማንነት በግልጽ መቀመጥ ይኖረበታል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "እኔ ሽማግሌው ዮሐንስ በማለት ደብዳቤውን የጻፈው ለተመረጠችው እና ለልጆቿ ነው፡፡ የተመረጠችው ሴት እና ልጆቿ ይህ በዚያ ያሉትን ማህረ ምእመናን እና አማኞችን ያመለክታል፡፡ በእውነት የሚወዳቸው አማራጭ ትርጉም፡ "በእውነት የሚወዳቸው" በእኛ ስለሚኖርና ከእኛ ጋር ለዘላለም ስለሚሆን እውነት፥ አማራጭ ትርጉም፡ "በእውነት ስለሚናምን እና እስከ ዘላለምን በእምነት ስለምናምን" እውነት ይህ የኢየሱስ ትምህርት የሚያመለክት ነው፡፡ አባት . . . ልጅ ይህ በእግዚአብሔር እና በኢየሱስ መካከል ያለው ግንኙነት ምን እንደሚመስል የሚያመለክት ጠቃሚ የማዕረግ ስም ነው፡፡ በእውነት እና በፍቅር አማራጭ ትርጉም: "እውነት ስለሆኑ እና እኛንም ስለሚወዱን" ወይም "በእውነት እኛ ስለሚወዱን"
አንዳንዶቹ ልጆቻችሁ በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በነጠላ ቁጥር ነው፡፡ ከአባት ዘንድ ይህንን ትዕዛዝ ስለተቀበልን "እግዚአብሔር አባት እኛን ስላዘዘን" ይሁን እንጂ ይህን እኛ ገና ከመጀመሪያው ጊዜ አንስቶ ነበረን "ነገር ግን በመጀመሪያ በክርስቶስ ስናምን ክርስቶስ እናደርገውን ዘንድ ያዘዘንን ነገር እጽፍላቿለሁ ፡፡ እርስ በእርሳችን እንዋደድ ዘንድ ይህ እንደ አዲስ ዓረፍተ ነገር ልተረጎም ይችላል፡ "እርስ በእርሳችን እንዋደድ ዘንድ ትዕዛዝን ሰጥቶናል፡፡" ከመጀመሪያው ጊዜ አንስቶ እንደሰማችሁት እንድትኖሩበት የተሰጣችሁ ትዕዛዝ ይህች ናት፡፡ “ይህች” የሚለው ቃል ፍቅርን የሚያመለክት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ከማናችሁበት ጊዜ አንስቶ እርስ በእርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ ትዕዛዝን ሰጥቷል፡፡" ትመላለሱ ዘንድ በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል በበዚህ ሥፍራ ላይ የቀረበው በብዙ ቁጥር ነው፡፡ (ተመልከት: [[Forms of 'You' - Dual/Plural]])
ብዙ አታላዮች ወደ ዓለም ውስጥ ገብተዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ብዙ የስሕተት መምህራን ጉባኤውን ትተው ሄደዋል፡፡" ብዙ አታላዮች አማራጭ ትርጉም: "ብዙ የሐሰት አስተማሪዎች" ወይም "ብዙ አሳሳቾች" ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደመጣ ይህ ማለት “ኢየሱስ ክርስቲስ እውነኛ ሰው ሆኖ መጥቷል” ማለት ነው፡፡" እነዚህ አሳሳቾች እና ሐሰተኛ መስሑ አማራጭ ትርጉም: "ሌሎችን የሚያስቱት እነዚህ ናቸው እንዲሁም ክርስቶስን እራሱንም የሚቃወሙትን እነዚህ ናቸው" ወደ ራሰህ ተመልከት "ተጠንቀቅ" ወይም "ትኩረት ስጥ" ነገሩን ማጣት አማራጭ ትርጉም: "በሰማይ ያለውን ሽልማታችሁን እንዳታጡ" ሙሉ ሽልማት አማራጭ ትርጉም: "በሰማይ ሙሉ የሆነ ሽልማት"
በጭንቅላቱ የሚሄድ ሰው ይህ የሚያመለክተው ስለ እግዚአብሔር እና እውነት ከሁሉም ይበልጥ አውቃለሁ ብሎ የሚናገርን ሰውን ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ስለ እግዚአብሔር ይበልጥ አውቃለሁ ብሎ የሚናገር ሰው፡፡" በትምህርቱ የሚጸና ሰው አብ እና ወልድን አለው "የክርስቶስን ትምህርት የሚከተሉ ሰዎች የአብ እና የወልድ ናቸው፡፡"
በክርስቶስ ትምህርት የማይጸና ሰው "ክርስቶስ ባስተማረው ትምህርት በጽናት የማይቀጥል ሰው" እግዚአብሔርን የለውም "የእግዚአብሔር አይደለም" ወደ እናንተ መጥቷል በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው በብዙ ቁጥር ነው፡፡ ወደ ቤታችሁ ተቀበሉት በዚህ ሥፍራ ላይ ትርጉሙ ወደ ቤት ማስገባት እንዲሁም ከእነርሱ ጋር ግንኙነትን ለመገንባት በክብር አቀባበል ማድረግን ያመለክታል፡፡ በቤታችሁ በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው በብዙ ቁጥር ነው፡፡ በክፉ ሥራው ይካፈላልና። "በእርሱ ክፉ ሥራ ውስት ይሳተፋል" ወይም "ክፉ ሥራውን ይደግፋል"
ኖት የለውም።
1 ሽማግሌው በእውነት ለምወደውና ለተወደደው ጋይዮስ። 2 የተወደድክ ሆይ በነፍስህ እንደበለጸግህ በሁሉ ነገር እንድትበለጽግና በመልካም ጤንነት እንድትሆን እጸልያለሁ። 3 ወንድሞች መጥተው በእውነት እንደምትሄድ ሲመሰክሩልኝ እጅግ ሀሴት አደረግሁኝ። 4 ልጆቼ በእውነት መንገድ እየሄዱ እንደሆነ ከመስማት የበለጠ ደስታ የለኝም። 5 የተወደድክ ሆይ ለወንድሞችም ሆነ ለእንግዶች በምታድርገው ነገር ስላለህ ታማኝነት 6 ሁሉም በጉባኤ ፊት ይመሰክሩልሀል።ለእግዚአብሔር እንደሚገባ በጉዞአቸው በመደገፍህ መልካም አድርገሀል። 7 ምክንያቱም ለተጠሩለት ስም አገልግሎት ሲወጡ ከአህዛብ ምንም አልወሰዱም። 8 ስለዚህም የእውነት ማህበርተኞች እንሆን ዘንድ እንደነዚህ ያሉትን መርዳት ይገባናል። 9 ስለአንድ ጉዳይ ለቤተክርስቲያን ጽፌ ነበር ነገር ግን በመካከላቸውአለቃ ሊሆን የሚወደው ዲዮትሪፈስ አይቀበለንም። 10 ስለዚህ በምመጣበት ጊዜ ያደረገውን ነገርና እንዴት ባሉ ክፉ ቃላት በእኛ ላይ እንደተናገረ አልረሳም።ይህም አልበቃ ብሎት ወንድሞችን አይቀበልም ሊቀበሉ የሚፈልጉትንም ይከለክላቸዋል ከቤተክርስቲያንም ያስወጣቸዋል። 11 የተወደድክ ሆይ መልካሙን እንጂ ክፉን አትምሰል። መልካም የሚያደርግ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው። ክፉን የሚያደርግ ሁሉ እግዚአብሔርን አላየውም። 12 ለዲሜጥሮስ ሁሉም ይመሰክሩለታል እውነት እራሷም ትመሰክርለታልች። እኛም እንመሰክርለታለን የኛ ምስክርነት ደግሞ እውነት እንደሆነ ታውቃላችሁ። 13 የምጽፍልህ ብዙ ነገር ነበረኝ ነገር ግን በወረቀትና በቀለም ልጽፍልህ አልፈለግሁም። 14 ይልቁኑ ልጎበኝህ አስባለሁና በዚያን ጊዜ ፊት ለፊት እንነጋገራለን። 15 ሠላም ለአንተ ይሁን። ወገኖችሰላምታ ያቀርቡልሀል። በአንተ ዘንድ ላሉት ወገኖች በስማቸው እየጠራህ ሠላምታ አቅርብልኝ።
ሽማግሌው r ሽማግሌው ይህ የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር የነበረውን ሐዋርያው ዮሐንስ የሚያመለክት ነው፡፡ ራሱን “ሽምግሌው” በማለት ይጠራል፡፤ ምክንያቱ አንድም በእድሜው ስላረጀ ወይም የቤተ ክርስቲያን መሪ በመሆኑ ሊሆን ይችላል፡፡ የጸሐፊው ስም በግልጽ መቀመጥ ይኖርበታል፡ “እኔ ሽማግሌው ዮሐንስ ይህንን ጽፌላችኋለሁ፡፡" ለጋይዮስ ይህ ዮሐንስ ደብዳቤውን የጻፈለት አማኝ ነው፡፡ በእውነት የሚወደው አማራጭ ትርጉም: "በእውነት የሚወደው" (UDB) በሁሉ ነገር እንዲከናወነልክ እና ጤናማ እንድትሆን "በሁሉ ነገር መከናወንን ታገኝ ዘንድ እና ጤናማ ትሆን ዘንድ" ነፍስህ እንደተከናወነች ሁሉ "በመንፈሳዊ ነገር እንደተከናወነላቸው ሁሉ" ወንድሞች "አማኞች" አንተ በእውነት እንደምትሄድ ስለ እውነትህ ሲመሰክሩ እጅግ ደስ ብሎኛልና። h "በእግዚአብሔር እውነት መሠረት እየኖርክ መሆንህን ነግረውኛል" ከዚህ የሚበልጥ ደስታ ፈጽሞ የለኝም
ልጆቼ ዮሐንስ በኢየሱስ እንዲያምኑ ያስተማራቸውን ከልጆች ጋር ያነጻጽራቸዋል፡፡ ይህ የእርሱን ፍቅር እና ስለ እነርሱ ምን ያኸል ግድ እንደሚለው ያሳያል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "የእኔ መንፈሳዊ ልጆች፡፡"
ወዳጆቼ ሆይ በዚህ ስፍራ ይህ ቃል የሚያሳየው አማኞች ምን ያህል የተወደዱ እንደሆኑ ነው፡፡ ስለ ፍቅር "ለእግዚብሔር ታማኝ መሆንን በተግባር አሳይተሃል" ወይም "ለእግዚአብሔር ታማኝ ሆነሃል" ለወንድሞች እና ለመጻተኞች ሥራ "አማኞችን እና የማታውቃቸውን ሰዎችም እርዳ/አግዝ" በቤተ ክርስቲያን ፊት ስለ ፍቅርህ መስክረዋል፤ ይህ በአዲስ ዓረፍተ ነገር ሊተረጎም ይችላል፡ "በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ላሉ አመማኞች ምን ያኸል እንደወደድካቸው ተናግረዋል፡፡" ለእግዚአብሔር እንደሚገባ አድርገህ በጉዞአቸው ብትረዳ መልካም ታደርጋለህ፤ "እግዚአብሔርን በሚያስከብር መልኩ በመንገዳቸው እባካችሁ ሸኙዋቸው" በወጡት ሰዎች ስም ምክንያት በዚህ ሥፍራ ላይ “ስም” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስን ነወ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “ስለ ኢየሱስ ለመናገር ወጥተዋል፡፡" ከአሕዛብ አንዳች ሳይቀበሉ ስለ ስሙ ወጥተዋልና። በዚህ ሥፍራ ላይ “አሕዛብ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አይሁዳዊ ያልሆነ ሰው ማለት አይደለም፡፡ በኢየሱስ የማያምን ሰው ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ስለ ኢየሱስ ከሚናገሩ ሰዎች ምንም ነገር አልወሰዱም" ስለዚህ እኛ በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ዮሐንስን እና ሁሉንም አመማኞችን ያጠቃልላል፡፡ ለእውነት አጋር ሠራተኞች ነን "የእግዚአብሔርን እውነት ለሌሎች ሰዎች ይነናገሩ ዘንድ እናግዛቸዋለን"
ማህበረ ምዕመናን ይህ ጋዮስን እና እግዚአብሔርን ለማምለክ የሚሰበሰቡ አማኞችን ያመለክታል፡፡ ዲዮጥራጢስ እርሱ የማህበረ ምዕመኑ አባል ነው፡፡ ከሁሉ አንደኛ መሆንን ይወዳል "የእነርሱ መሪ ሆኖ መታየትን ይወዳል" እኛን አይቀበልም በዚህ ስፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ዮሐንስን እና ከእርሱ ጋር ያሉትን ሰዎችን ነው፡፡ ጋዮስን ግን አያመለክትም፡፡ በእኛ ላይ በክፉ ቃል እየለፈለፈ የሚያደርገውን ሥራውን አሳስባለሁ፤ "እውነት ያልሆነ ነገር እየተናገረ በእኛ ላይ ብዙ ክፉ ነገሮችን ይናገራል" እርሱ ራሱ “እርሱ ራሱ” የሚለው ቃል እነዚህ ነገሮችን የሚያደርገውን ዲዮጥራጢስ ያመለክታል፡፡ ወንድሞችን አይቀበለም "ወንድሞችን አይቀበልም" እንዲሁም የሚፈልጉትንም ይከለክላል በዚህ ሀረግ ውስጥ የተተው ቃላት አሉ ነገር ግን ለመረዳት ግን እንቅፋት አይደሉም፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ሌሎች አማኞችን የሚቀበሉ ሰዎችን ያስቆማል፡፡" አውጢቶዋቸዋል "አባሮዋቸዋል፡፡" በዚህ ሥፍራ ላይ “እነርሱ” የሚለው ቃል ሌሎች አማኞችን ለመቀበል ፈቃደኞች የሆኑ ሰዎችን ያመለክታል፡፡
ወዳጆቼ ሆይ በዚህ ሥፍራ ላይ ይህ ቃል የሚያመለክተው የተወደዱ አማኞችን ነው፡፡ ክፉን አትምሰሉ "ሰዎች የሚያደርጉትን ክፋት አትከተሉ" ይልቁንም መልካሙን በዚህ ሀረግ ውስጥ የተተው ቃላት አሉ ነገር ግን ለመረዳት አዳጋጅ አይደለም፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ሰዎች የሚያደርጋዋቻን መልካም ነገሮችን ተከታተሉ፡፡" ከእግዚአብሔር ነው "የእግዚአብሔር ነው" እግዚአብሔርን አላየውም አማራጭ ትርጉም፡ "የእግዚአብሔር አይደለም" ወይም "በእግዚአብሔር አያምንም" ለድሜጥሮስ ሁሉ ይመሰክሩለታል፥ አማራጭ ትርጉም: "ድሜጥሮስን የሚያውቁትን ሁሉም ክርስትያኖች ስለ እርሱ መልካምነት ይመሰክራሉ፡፡" እንዲሁም እውነት እራሷም "እንዲሁም እውነት እራሷ ስለ እርሱ ትናገራለች፡፡" በዚህ ሥፍራ ላይ “እውነት” የሚለው ቃል እንደሚናገር ሰው ሆና ቀርባለች፡፡ አማራጭ ትርጉም: "ስለ እርሱ የተናገሩት ነገር እውነት ነው፡፡ ) እኛም ራሳችን እንመሰክራለን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል ዮሐንስን እና ከእርሱ ጋር ያሉትን ሰዎች ይወክላል፡፡ ነገር ግን ጋዮስን አያካትትም፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ስለ ለድሜጥሮስ እኛም ጭምር እንመሰሰክራለን፡፡" ታውቃለህ በዚህ ሥፍራ ላይ “አንተ” የሚለው ቃል በነጠላ ቁጠትር የተቀመጠ ሲሆን ጋዮስን ያመለክታል፡፡
ኖት የለውም።
1 የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ፥ የያዕቆብ ወንድም ይሁዳ፤ ለተጠሩት፥ በእግዚአብሔር አብ ለተወደዱትና በኢየሱስ ክርስቶስ ለተጠበቁት፤ 2 ምሕረት ለእናንተ ይሁን፤ ሰላምና ፍቅርም ይብዛላችሁ። 3 ወዳጆች ሆይ፤ አብረን ስለምንካፈለው ድነት ልጽፍላችሁ ጥረት እያደረግሁ ሳለ፥ ለቅዱሳን አንዴና ለመጨረሻ ስለተሰጠው እምነት ጸንታችሁ ትጋደሉ ዘንድ ለመምከር እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ። 4 ለፍርድ እንደሚዳረጉ ከብዙ ዘመን በፊት የተጻፈባቸው አንዳንድ ሰዎች ሾልከው ወደ እናንተ ገብተዋልና። እነዚህ ሰዎች ፈሪሃ እግዚአብሔር የሌላቸው፥ የእግዚአብሔርን ጸጋ በሴሰኝነት የሚለውጡ፥ እርሱ ብቻ ገዣችንና ጌታችን የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን የሚክዱ ናቸው። 5 ምንም እንኳ አስቀድማችሁ ሁሉን የምታውቁት ቢሆንም ጌታ አንድ ጊዜ ሕዝቡን ከግብጽ አውጥቶ እንደ አዳናቸው በኋላ ግን ያላመኑትን እንዳጠፋቸው ላስታውሳችሁ እወዳለሁ። 6 እንዲሁም የነበራቸውን የሥልጣን ደረጃ ባለመጠበቅ ተገቢ የመኖሪያ ስፍራቸውን የተውትን መላእክት እግዚአብሔር እስከ ታላቁ የፍርድ ቀን ድረስ በዘላለም እስራት በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ እንዲቆዩ አድርጓል። 7 እንዲሁም ሰዶምና ገሞራ በዙሪያቸውም የነበሩት ከተሞች በተመሳሳይ ሁኔታ ራሳቸውን ለሴሰኝነትና ከተፈጥሮ ሥርዓት ውጪ ለሆነ ግብረ ሥጋ ግንኙነት አሳልፈው ሰጡ፤ እነርሱም በዘላለም እሳት ተጥለው ለሚሰቃዩት ምሳሌ እንዲሆኑ ተደርገዋል። 8 በዚህ ሁኔታ እነዚህ ደግሞ በሚያልሙት ሕልማቸው የራሳቸውን ሥጋ ያረክሳሉ፤ሥልጣንን ይቃወማሉ፤በሰማይ ክብር ያላቸውንም ይሳደባሉ። 9 የመላእክት አለቃ ሚካኤል እንኳ ዲያብሎስን በመቃወም ስለ ሙሴ ሥጋ በተከራከረው ጊዜ «ጌታ ይገሥጽህ» አለው እንጂ በእርሱ ላይ ሊፈርድ ወይም አንዳች የስድብ ቃል ሊናገር አልደፈረም። 10 እነዚህ ሰዎች ግን የማያውቋቸውን ነገሮች ሁሉ ይሳደባሉ። እነርሱም አእምሮ የሌላቸው እንስሳት እንደሚያደርጉት በደመ ነፍስ በሚያውቋቸው ነገሮች ይጠፋሉ። 11 ወዮላቸው፤ በቃየን መንገድ ሄደዋልና፤ለገንዘብ ሲሉ በበለዓም ስህተት ውስጥ ወድቀዋልና፤በቆሬም ዐመፅ ጠፍተዋልና። 12 እነዚህ በፍቅር ግብዣችሁ ላይ አብረዋችሁ ሲጋበዙ ችግር የሚፈጥሩባችሁ ድብቅ እንቅፋቶች ናቸው፤ ደግሞም ያለ ሃፍረት ራሳቸውን ብቻ የሚመግቡ እረኞች ናቸው። እነርሱም በነፋስ የሚነዱ ውሃ አልባ ደመናዎች ናቸው፤ በመከር ወራት ፍሬ የማይገኝባቸው፥ ከሥራቸው የተነቀሉና ሁለት ጊዜ የሞቱ ዛፎች ናቸው። 13 የራሳቸውን የነውር አረፋ የሚደፍቁ የተቆጣ የባሕር ማዕበል፥ ድቅድቅ ጨለማም ለዘላለም የተጠበቀላቸው ተንከራታች ከዋክብት ናቸው። 14 ከአዳም ጀምሮ ሰባተኛ ትውልድ የሆነው ሄኖክ ስለ እነዚህ ሰዎች እንዲህ በማለት ትንቢት ተናግሯል፤ «እነሆ፤ ጌታ ከብዙ ሺህ ቅዱሳኑ ጋር ይመጣል። 15 የሚመጣውም በሰው ሁሉ ላይ ለመፍረድ እንዲሁም ዐመፀኞችንና ኀጢአተኞችን ክፋት በተሞላበት ሁኔታ በፈጸሙት የዐመፅ ሥራቸውና በእግዚአብሔር ላይ በተናገሩት የስድብ ቃል ለመውቀስ ነው።» 16 እነዚህ የሚያጉረመርሙ፥ ሌላውን የሚከሱ፥ የራሳቸውን ክፉ ምኞት የሚከተሉ፥ ጉራ የሚነዙና ጥቅም ለማግኘትም ሰዎችን የሚክቡ ናቸው። 17 እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ፤የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያት አስቀድመው የተናገሩትን ቃል አስታውሱ 18 ለእናንተም ሲናገሩ፥«በመጨረሻው ዘመን የራሳቸውን ክፉ ምኞት የሚከተሉ ዘባቾች ይመጣሉ» ብለዋል። 19 እነዚህ በሰዎች መካከል መለያየትን የሚፈጥሩ፥የሥጋን ምኞት የሚከተሉና መንፈስ ቅዱስ የሌላቸው ናቸው። 20 እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ፤እጅግ ቅዱስ በሆነው እምነታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ ትጉ፤በመንፈስ ቅዱስም ጸልዩ። 21 በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ፤የዘላለም ሕይወትም ታገኙ ዘንድ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ፈልጉ። 22 ለሚጠራጠሩ ሰዎች ርኅራኄ አድርጉላቸው፤ 23 ከእሳት ነጥቃችሁ በማውጣት አንዳንዶችን አድኑ፤ ለሌሎች ድግሞ በእርኩስ ሥጋ የተበከለውን ልብስ እንኳ እየጠላችሁ በፍርሃት ምህረት አሳዩአቸው። 24 እንግዲህ ከመውደቅ ሊጠብቃችሁ፥ ነቀፋ ሳይኖርባችሁ በታላቅ ደስታ በክብሩ ፊት ሊያቀርባችሁ ለሚችለው 25 በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት አዳኛችን ለሆነው ብቸኛ አምላክ ከዘመናት ሁሉ በፊት፥ አሁንና እስከ ዘላለም ድረስ ክብር፥ ግርማ፥ ኀይልና ሥልጣንም ይሁን፤ አሜን።
ይሁዳ፣ አገልጋዩ ይሁዳ የያዕቆብ ወንድም ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ እኔ ይሁዳ ነኝ፣ የ . . . አገልጋይ፡፡" እና ወንድሙ ያዕቆብ ያዕቆብ እና ይሁዳ የኢየሱስ በአንድ ወገን ወንድሞች ናቸው፡፡ በእግዚአብሔር አባት የተወደዱ "እግዚአብሔር አባት ይወዳችኋል ምሕረት ለአንተ ይሁን እንዲሁም ሰላምና ፍቅርም ይብዛላችሁ። በዚህ ሥፍራ ላይ “እናነተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ይህንን ደብዳቤ የተቀበሉት ሁሉንም ክረስትያኖች ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ምህረት፣ ሰላም እና ፍቅር አብዝቶ ይብዛላችሁ፡፡"
ለእናንተ ለመጻፍ ማንኛውንም ጥረት አደርጌያለሁ "ለእናንተ ለመጻፍ ጥሬያለሁ" የጋራ ድነታችን "ተመሳሳይ ድነትን ተጋርተናል" መጻፍ እንዳለብኝ "መጻፍ እንዳለበኝ አጥብቆ ተሰማኝ" ወይም "መጻፍ እንዳለብኝ በጣም ተሰምቶኛል" ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ። "እውነተኛውን ትምህርት እንድትጠብቁ አበረታታለሁ" የተሰጠውን "እግዚአብሔር እውነተኛውን ትምህርት ሰጥቷል" አንዳንዶች ሰዎች ሾልከው ገብተዋልና፤ "አንዳንድ ሰዎች ሳይታወቅ ወደ አማኞች ዘንድ ሾልከው ገብተዋል" ከብዙ ጊዜ በፊት ለዚህ ፍርድ የተጻፉ "ከብዙ ዘመናት በፊት በእነዚህ ሰዎች ላይ እንደሚፈረድ ተጽፏል፡፡ " የአምላካችንን ጸጋ በሴሰኝነት ይለውጣሉ "እነዚህ ሰዎች የእግዚአብሔር ጸጋ አንድ ሰው በግብረስጋ ግንኙነት ኃጢአት እንዲቀጥል ይፈቅዳል በማለት ያስተምራሉ" ንጉሣችንንና ጌታችንንም ብቻውን ያለውን ኢየሱስ ክርስቶስን ይክዳሉ። ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ ወይም ወደ እግዚአብሔር የሚወስድ መንገድ አይደለም ብለው ያስተምራሉ፡፡ ክደው አንድ ነገር ስህተት ነው ለማለት፡፡
ላሳስባችሁ እወዳለሁ "ላስታውሳችሁ እወዳለሁ" ሁሉን ነገር ታውቃላችሁ ይሁዳ በዚህ ሥፍራ ላይ እያመለከተ ያለው ስማሩ የነበሩትን የሙሴን መጽሐፍት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “የሙሴን መጽሐፍት አጠንቅቃችሁ ታውቃላችሁ፡፡" ጌታ ከግብፅ አገር ሕዝቡን አድኖ "ጌታ ከብዙ ዘመናት በፊት እስራኤላዊያንን ከግብጽ ምድር ታድጎ" ይሁን እንጂ ከዚያ በኋላ "በኋላ ዘመናት ላይ" ወይም "አንዳንድ ነገሮች ከሆኑ በኋላ" የራሳቸውን አለቅነት "የራሳቸውን ስልጣን" ወይም "ለእነርሱ የተሰጣቸውን ኃላፊነት" ትክክለኛውን መኖሪያቸውን የተውትን "የተሰጣቸውን ሥፍራ የተውትን" እግዚአብሔር በዘላለም እስራት ከጨለማ በታች እስከ ታላቁ ቀን ፍርድ ድረስ ጠብቆአቸዋል። "እግዚአብሔር እነዚህን መላእክት በጨለማ ውስጥ አስሮ አስቀምጦዋቸዋል" ታላቁ ቀን እግዚአብሔር በሰዎች ሁሉ ላይ የሚፍድበት ቀን
በተሳሳይ መልኩም ራሳቸውን የሰጡትን መላእክት ክፉ መንገዳቸውን እንደተከተሉ ሁሉ ሶዶም እና ጎሞራም በዝሙት ኃጢአታቸውን ተከትለዋል፡፡ በዙሪያቸውም የነበሩ ከተማዎች በዘላለም እሳት እየተቀጡ ምሳሌ ሆነዋል። የሰዶም እና የጎሞራ መጥፋት እግዚአብሔርን የማይቀበሉ ሰዎች እድል ፈንታ ምን እንደሆነ የሚያሳይ ምሳሌ ነው፡፡ እነርሱም ደግሞ ተበክለዋል በዚህ ሥፍራ ላይ “እነርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔር ለመቀበል ፈቃደና ያልሆኑ ሰዎችን ነው፡፡ ልክ ቆሻሻን ወደ ውሃ ውስጥ መጣል ውሃውን እንዲሸት እንደሚያደርገው ሁሉ እነዚህም አካላቸውን በፍተወት በክለውታል፡፡ ስለ ተከበረው "ስለ ተከበረው የእግዚአብሔር መላእክ"
ስለ ሥጋ ስከራከሩ ሳለ አካልን የሚወስደው ማን ነው ብለው በተከራከሩ ጊዜ፡፡ አማራጭ ትርጉም: "አካልን የሚወስደው ማን ነው ብለው ስከራከሩ ሳለ፡፡" ሚካኤል ...እርሱን እንዲቃወም አልፈቀደለትም አማራጭ ትርጉም: "ሚካኤል...ዳቢሎስን መቃወምን ቀጥሎ ነበር" እርግማን ወይም የስድብ ቃላት "ጠንካራ ትችት ወይም ጸያፍ ቃላት" ይሁን እንጂ እነዚህ ሰዎች "እነዚህ ሰዎች" ከዚህ በፊት የተጠቀሱት ፈርሃ እግዚአብሔር ያሌላቸው ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ግን የማያውቁትን ሁሉ ይሳደባሉ፥ "ትርጉሙን የማያውቁትን ነገር ሁሉ ይሳደባሉ" የቃዬል መንገድ ቃዬል ወንድሙን አቤልን ገድሎታል፡፡ የበለአም ስህተት በለአም ለገንዘብ ሲል እስራኤልን ረግሞዋል፡፡ የቆሬ ልጆች አመጽ ቆሬ በሙሴ መሪነት እና በአሮን ካህንነት ላይ አምጸው ነበር፡፡
እነዚህ ናቸው በዚህ ሥፍራ ላይ “እነዚህ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ፈርሃ እግዚአብሐር ያሌላቸውን ሰዎችን ነው፡፡ በበገራ የደረቁ ፍሬ የማያፈሩ ዛፎች ናቸው በበጋ ወራት መጨረሻ ላይ አንዳንድ ዛፎች ፍሬ እንደማያፈሩ ሁሉ ፈርሃ እግዚአብሔር ያሌላቸው ሰዎችን ጽድቅ የሞላበት እምነት እና ሥራ የላቸውም፡፡ ፍሬ ያሌላቸው፣ ሁለት ጊዜ የሞቱ ልክ ሁለት ጊዜ እንደሞተ ዘፍ ፍሬ እንደማያፈራ ሁሉ ፈርሃ እግዚአብሔር ያሌለው ሰውም በውስጡ ምንም እሴት አይኖርም እንዲሁም በውስጡ ምንም ሕይወት የለም፡፡ ከነሥራቸው የተነቀሉ ልክ ከነሥራቸው የተነቀሉ ዛፎች ፈርሃ እግዚአብሔር ያሌላቸው ሰዎች የሕይወት ምንጭ ከሆነው ከእግዚአብሔር የተለዩ ናቸው፡፡ ጨካኝ የባሕር ማዕበል፥ የባሕር ማዕበል በንፈስ እንደሚንቀሳቀስ ሁሉ ፈርሃ እግዚአብሔር ያሌላቸው ሰዎችም የእምነት መሠረት ዬለቸውም እንዲሁም በተለያየ አቅጣጫ በቀላሉ ወዛወዛሉ፡፡ የገዛ ነውራቸውን አረፋ እየደፈቁ ንፋስ ማዕበሉን እየገፋ ቆሻሻ አረፋ እንደሚያስደፍቅ ሁሉ እነዚህ ሰዎችም በስህተት ትምህርታቸው እና ተግበራቸው አማካኝነት ረራሳቸውን ያዋርዳሉ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ማዕበል አረፋ እና ቆሻሻ እንደሚያወጣ ሁሉ እነዚህ ሰዎች በእፍረታቸው ሌሎች ሰዎችን ይበክላሉ፡፡ ድቅድቅ ጨለማ ለዘላለም የተጠበቀላቸው የሚንከራተቱ ከዋክብት ናቸው። ለመከታተል አስቸጋሪ እንደሆኑት በሰማይ ላይ እንደሚበሩት ክዋክብት እነዚህን ሰዎች መከተል የለባችሁም፡፡
እነዚህ ሰዎች...ሥራዎቻቸው ...እነርሱ ያላቸው ይህ የሚያመለክተው ፈርሃ እግዚአብሔር ያሌላቸው ሰዎች ነወ፡፡ ከአዳም ጀምሮ ሰባተኛ የሆነ ሄኖክ ከአዳም ጀምሮ ያለው ሰባተኛው ትውልድ ድረስ፡፡ አንዳንድ ትርጉሞች አዳም መቆጠር አለመቆጠሩን አስመለክቶ ስድስተና ትውልድ ይላሉ፡፡ እነሆ ጌታ "ተመልከቱ ጌታ", ወይም "እነሆ ጌታ" ሁሉንም ከባባድ ነገሮችን "ሁሉንም ክፉ ቃላትን" የሚያንጎራጉሩና ኃጢአተኞች የማይታዘዝ ልብ ያላቸውe ሰዎች፡፡ የሚያንጎራጉሩና ይህንን ግልጽ ባልሆነ መንገድ ሲያደርጉ ኃጢአተኞች ደግሞ በግልጽ ያደርጉታል፡፡ በኩራት ሌሎች ሰዎች ይሰሟቸው ዘንድ ራሳቸውን የሚያሞግሱ ሰዎች፡፡
አንዲህ ይላችኋል "ሐዋርያው እንዲህ ይላችኋል" የራሳቸውን . . . ተከትለው ሄደዋል፡፡ እነርሱ እንዲህ ናቸው፡፡ በዚህ ሥፍራ ላይ ይሁዳ እያመለከተ ያለው ዘባች የሆኑ ሰዎችን ነው፡፡ ክፍፍልን ይፈጠትራሉ "በአማኞች መካከል መለያየትን የሚፈጥሩ ዘባቾች ናቸው" ስሜታዊያን ናቸው "ዘባቾቹ የፍተወት ፍላጎተቸውን ይከተላሉ"
ራሳችሁን እያነጻችሁ ስትሄዱ እየጠነከራችሁ በሄዳችሁ እና ጤናማ አካልን እየገነባችሁ በሄዳችሁ ቁጥር አእምሮዋችሁ እየጎለበተ እና እደገ ይሄዳል፡፡ እንዲሁም በእግዚአብሔር እውቀትም በመንፈሳችሁ ታድጋላችሁ፡፡ ስትጠባበቁ... "ወደፊት የሚሆነውን በናፍቆት ስትጠባበቁ ሳለ"
በጥርጣሬ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ሰዎች "እግዚአብሔር አምላክ ለመሆኑ ገና ያላመኑ አንዳንድ ሰዎች" እነርሱ ከእሳት መንጭቆ በማውጣት "ወደ እሳት ባሕር ውስጥ እንዳይገቡ" እና በፍርሃት ማሩ "ለሌሎች ምህረትን አሳዩ ነገር ግን ልክ እንደ እነርሱ ኃጢአትን እንዳተታደርጉ ተጠንቀቁ፡፡" በሥጋ የረከሰውን ልብስ እንኳ እየጠላችሁ "ልብሳቸውን እንኳ ጥሉ ምክንያቱም በኃጢአት ቆሻሻ ሆነዋል፡፡" ሙሉ በሙሉ በኃጢአት ተበክለዋልና ንጹሕ አይደሉም፡፡
ኖት የለውም።
1 ይህ ፈጥኖ ሊሆን የሚገባውን ነገር ለአገልጋዮቹ እንዲያሳይ እግዚአብሔር ለኢየሱስ ክርስቶስ የሰጠው ራእይ ነው። እርሱም ይህን ራእይ መልአኩን ወደ አገልጋዩ ወደ ዮሐንስ በመላክ እንዲታወቅ አድርጓል። 2 ዮሐንስም የእግዚአብሔርን ቃል በሚመለከት ስላየው ማንኛውንም ነገር እና ክርስቶስን በሚመለከት ስለተሰጠው ምስክርነት ተናግሯል። 3 ዘመኑ ስለ ቀረበ ፥ የዚህን የትንቢት ቃል የሚያነብ የተባረከ ነው፤እንዲሁም የሚሰሙት ሁሉ በውስጡም የተጻፈው ን ነገር የሚፈጽሙ የተባረኩ ናቸው። 4 ከዮሐንስ፥በእስያ ላሉት ለሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት፤ካለው፥ከነበረው፥ወደፊትም ከሚመጣውና በዙፋኑ ፊት ካሉት ከሰባቱ መንፈሶች 5 እንዲሁም ታማኝ ምስክር፥ከሙታን በኩርና የምድር ነገሥታት ገዥ ከሆነው ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን። ለሚወደንና ከኀጢአታችንም በደሙ ነጻ ላወጣን፥ 6 አባቱ ለሆነው እግዚአብሔር መንግሥትና ካህናት እንሆን ዘንድ ላደረገን ለእርሱ ክብርና ኀይል ከዘላለም እስከ ዘላለም ይሁን፤አሜን። 7 እነሆ፤እርሱ በደመና ይመጣል፤የወጉትን ጨምሮ ዐይን ሁሉ ያየዋል። የምድርም ነገዶች ሁሉ በእርሱ ምክንያት ያለቅሳሉ፤እንደዚያም ይሆናል፤አሜን። 8 ጌታ እግዚአብሔር፥«አልፋና ኦሜጋ፥ ያለሁና የነበርሁ፥ወደፊትም የምመጣው ሁሉን ቻይ እኔ ነኝ» ይላል። 9 እኔ ከእናንተ ጋር በመከራው፥በመንግሥቱና በኢየሱስ በሚገኘው ትዕግሥት ተካፋይ የሆንሁ ወንድማችሁ ዮሐንስ፥ በእግዚአብሔር ቃልና በኢየሱስ ምስክርነት ምክንያት ፍጥሞ በምትባል ደሴት ነበርሁ። 10 በጌታም ቀን በመንፈስ ነበርሁ፤በኋላዬም የመለከትን ድምጽ የሚመስል ታላቅ ድምፅ ሰማሁ። 11 ድምፁም እንዲህ የሚል ነበር፤«የምታየውን በመጽሓፍ ጻፈው፤ ከዚያም በኤፌሶን፥ በሰምርኔስ፥ በጴርጋሞን፥ በትያጥሮን፥ በሰርዴስ፥ በፊለደልፍያና በሎዶቅያ ወዳሉት ወደ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት ላከው። 12 ይናገረኝ የነበረው የማን ድምፅ እንደ ሆነ ለማየት ዘወር አልሁ፤ ዘወር በምልበትም ጊዜ ሰባት የወርቅ መቅረዞችን አየሁ። 13 በመቅረዞቹም መካከል እስከ እግሩ ድረስ የሚደርስ ረጅም ልብስ የለበሰና ደረቱንም በወርቅ መታጠቂያ የታጠቀ የሰው ልጅ የሚመስለው ነበር። 14 ራሱና ጸጉሩ እንደ ነጭ የበግ ጸጉር ማለትም እንደ በረዶ ነጭ ነበሩ፤ዐይኖቹ የእሳት ነበልባል፥ 15 እግሮቹም በእቶን እሳት እንደ ነጠረ የጋለ ናስ፥ ድምፁም እንደ ብዙ ወራጅ ውኃ ድምፅ ነበር። 16 በቀኝ እጁ ሰባት ከዋክብት ይዞ ነበር፤ከአፉም በሁለት በኩል የተሳለ ስለታም ሰይፍ ይወጣ ነበር፤ፊቱም ጸሐይ በሙሉ ኀይልዋ ስታበራ የምታበራውን ያህል ያበራ ነበር። 17 ባየሁትም ጊዜ እንደ ሞተ ሰው ሆኜ በእግሩ ሥር ወደቅሁ፤ እርሱም ቀኝ እጁን በእኔ ላይ በመጫን እንዲህ አለኝ፤ «አትፍራ፤እኔ የመጀመሪያውና የመጨረሻው 18 ሕያውም ሆኜ የምኖር ነኝ። ሞቼ ነበር፤እነሆም ለዘላለም ሕያው ነኝ፤የሞትና የሲዖል መክፈቻም አለኝ። 19 ስለዚህ ያየኽውን፥አሁን ያለውን ሁኔታና ከዚህ በኋላ የሚሆነውን ነገር ጻፍ። 20 በቀኝ እጄ ያሉት አንተም ያየሃቸውን የሰባቱን ከዋክብትና የሰባቱን የወርቅ መቅረዞች ምስጢር በተመለከተ ትርጉሙ ይህ ነው፤ሰባቱ ከዋክብት የሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት መላእክት ሲሆኑ፥ ሰባቱ መቅረዞች ደግሞ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት ናቸው።
የእርሱ አገልጋዮች በክርስቶስ አማኞች በቅርቡ ሊሆኑ ስላሉት ነገሮች አማራጭ ትርጉም: "በቅርቡ የሚሆኑ ነገሮች" አስታውቋል "ተነግሮዋል፡፡" ጊዜ ቅርብ ነው አማራጭ ትርጉም: "መሆን የሚገባቸው ነገሮች ብቅርቡ ይሆናሉ"
ሠላም ከሆነው ሠላም ይሁንላችሁ "ሠላም ከሆነ ከእግዚአብሔር ዘንድ ሠላም ይሁንላችሁ" መናፍስት እነዚህ መናፈስት መላእክት መሆናቸው በተዘዋዋር መንገድ ተገልጾዋል ምክንያቱም እነዚህ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት የሚሆኑ ናቸውና፡፡ ነጻ ወጥተናል አማራጭ ትርጉም: "ነጻ አውጥቶናል" መግስት አድርጎናል "ለይቶን በእኛ ላይ መንገስ ጀምሯል"
ዐይን ሁሉ አማራጭ ትርጉም: "ማንኛውም ሰው" ሰቀሉት ገደሉት ወጉት ቀዳዳ አበጁ አልፋ እና ኦሜጋ (ጅማሬ እና ፍጻሜ) እነዚህ የግሪክ ፊደላት መጀመሪያ እና መጨረሻ ናቸው፡፡ ትርጉሙም የሁሉ ነገር ጅማሬ እና ፍጻሜ እግዚአብሔር ነው፤ በመካከልም በሁሉም ላይ የሚገዘው እግዚአብሔር ነው ማለት ነው፡፡ አልፋ . . . ኦሜጋ ይህ በባሕሉ መሠረት መተርጎም ይኖርበታል፡፡ ለምሳሌ ያኸል አልፋ እና ኦሜጋ የሚሉት ቃላት የግሪክ ፊደላትን ለማያውቅ ሰው ምንም ዓይነት ትርጉም የላቸውም፡፡ ስለዚህም በቋንቋቸው ተስመሚ የሆኑ ቃላትን ፈልገው መተርጎም ይርባቸዋል፡፡
እናንተ . . . እናንተ በሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ያሉ አማኞች ከእናንተ ጋር በዚየሱስ ያለው መከራን እና መንግስትን በጽናት የሚካፈሉ "ከእናንተ ጋር የእግዚአብሔርን መንግስት የሚወርሱ፡፡ እንዲሁም የኢየሱስ ከመሆናችን የተነሣ ከእናንተ ጋር መከራን እና ስደተን በጽነናት የሚካፈል፡፡" ከእግዚአብሔር ቃል የተነሣ "የእግዚአብሔርን ቃል በመናገሬ የተነሣ" በመንፈስ ይህ ማለት በእግዚአብሔር መንፈስ አማካኝነት፡፡ የጌታ ቀን በክርስቶስ የሆኑት አማኞች የሚያመልኩበት ቀን፡፡ የመለከት ድምፅ ያለው ክፈተኛ ድምፅ ድምፁ ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሣ የመለከት ድምፅ ይመስላል፡፡ ሰምርኔስ፣ ጴርጋሞንም፣ ትያጥሮንም፣ ሰርዴስም፣ ፊልድልፍያም እና ሎዶቅያም እነዚህ በዘመኗ ቱሪክ አከባቢ በኢስያ ውስጥ የሚገኙ ከተሞች ስሞች ናቸው፡፡
ድምፁ በዚህ ሥፍራ ላይ “ድምፅ” የሚለው ቃል የሚናገረውን ሰው ይወክላል፡፡ ቀበቶ በመቀመጫ ዙሪያ ወይም በደረት ዙሪያ የሚታጠቁት ቁራጭ ጨርቅ ነው፡፡
ራሱ እና ጸጉሩ ልክ የበግ ጸጉር ይመስላል - እንደ በረዶ ነጭ ነው “እንደ ነጭ ነው” የሚለው በድጋሚ የተገለጸው ቃል ራሱ እና ጸጉሩ ምን ያኸል ነጭ እንደሆነ አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ ድምፁም እንደ ብዙ ውኃዎች ድምፅ ነበረ። ይህ ትልቅ ድምፅ ያለው፣ በፍጥነት የሚፈስ፣ ነጭ የወንዝ ውሃ የሚያሰማውን ድምፅ ነው፡፡
He placed his right hand on me አማራጭ ትርጉም: "በቀኝ እጆቹ ነካኝ" እኔ መጀመሪያ እና መጨረሻ ነኝ ይህ ለመኖር የመጀመሪያ መሆንን የሚያሳይ እና ለመኖር የመጨረሻ መሆንን የሚለው የሚያሳየው ዘላለማዊ ባሕርውን ነው፡፡
የወርቅ መቅረዞች ይህንን በ REV 1:12 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት See how you translated this in ይህንን በ REV 1:11 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡
1 “በኤፌሶን ወዳለው መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ፤ ‘ሰባቱን ከዋክብት በቀኝ እጁ የያዘውና በሰባቱ የወርቅመቅረዞች መካከል የሚመላለሰው እንዲህ ይላል፤ 2 ‘ሥራህን፣ ትዕግሥትህንና ጽናትህን አውቃለሁ። ክፉ ሰዎችን መታገሥ አለመቻልህንም አውቃለሁ። ሐዋሪያት ሳይሆኑ “ሐዋሪያት ነን” የሚሉትን መርምረህ ሐሰተኞች ሆነው እንዳገኘሃቸውም አውቃለሁ።” 3 በትዕግሥት እንደ ጸናህ፥ስለ ስሜ ብዙ መከራ ቢደርስብህም እንዳልደከመህ አውቃለሁ። 4 ነገር ግን የምነቅፍብህ ነገር አለኝ፤ይኽውም የቀደመውን ፍቅርህን ትተሃል። 5 እንግዲህ ከወዴት እንደ ወደቅህ ለይተህ እወቅ፤ንስሓ ግባ፤ቀደም ሲል ታደርገው የነበረውንም ነገር አድርግ። ንስሓ ካልገባህ እመጣብሃለሁ፤መቅረዝህንም ከስፍራው አስወግዳለሁ። 6 ነገር ግን ይህ መልካም ነገር አለህ፤ እኔ የምጠላውን የኒቆላውያንን ሥራ ጠልተሃል። 7 ጆሮያለው መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያን የሚለውን ይስማ። ድል ለሚነሣው በእግዚአብሔር ገነት ካለው የሕይወት ዛፍ የመብላትን መብት እሰጠዋለሁ።” 8 «በሰምርኔስ ላለችው ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ፤ "እነዚህ መጀመሪያም መጨረሻም የሆነው የእርሱ ቃሎች ናቸው፤ሞቶ የነበረው፥እንደ ገና ሕያው የሆነው እንዲህ ይላል፤ 9 '"መከራህንና ድኽነትህንም አውቃለሁ፤ነገር ግን ባለጠጋ ነህ፤የሰይጣን ማኅበር ሆነው እያለ፥አይሁድ ሳይሆኑ አይሁድ ነን ብለው የሚናገሩ ሰዎች የሚሳደቡትን ስድብ አውቃለሁ። 10 ወደ ፊት የሚደርስብህን መከራ አትፍራ። ተመልከት ከእናንተ አንዳንዶቹን እንድትፈተኑ ዲያብሎስ እስር ቤት ያስገባችኋል፤ ለአሥር ቀን መከራ ትቀበላላችሁ። እስከ ሞት ድረስ ታማኝ ሁን፤ እኔም የሕይወትን አክሊል እሰጥሃለሁ። 11 ጆሮ ያለው መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያን የሚለው ይስማ። ድል የሚነሻ በሁለተኛው ሞት አይጎዳም። 12 «በጴርጋሞን ላለው ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ፤ "እነዚህ በሁለት በኩል የተሳለ ስለታም ሰይፍ ካለው የተነገሩ ቃሎች ናቸው፤እርሱም እንዲህ ይላል፤ 13 '"የሰይጣን ዙፋን ባለበት በዚያ እንደምትኖር አውቃለሁ፤ነገር ግን ስሜን አጥብቀህ ይዘሃል። ሰይጣን በሚኖርበት በእናንተ መካከል በተገደለው በታማኙ ምስክሬ በአንቲጳስ ዘመን እንኳ በእኔ ያለህን እምነት አልካድህም። 14 ነገር ግን የምነቅፍብህ ጥቂት ነገር አለኝ፤የእስራኤል ልጆች ለጣዖት የተሰዋ ምግብ እንዲበሉና እንዲሴስኑ በፊታቸው ማሰናከያ ያስቀምጥ ዘንድ ባላቅን የመከረው የበለዓምን ትምህርት አጥብቀው የሚከተሉ አንዳንድ ሰዎች በመካከልህ አሉ። 15 እንደዚሁም የኒቆላውያንን ትምህርት አጥብቀው የያዙ ሰዎች እንኳ በአንተ ዘንድ አሉ። 16 ስለዚህ ንስሓ ግባ፤አለበለዚያ ፈጥኜ እመጣብሃለሁ፤ከአፌም በሚወጣው ሰይፍ አዋጋቸዋለሁ። 17 ጆሮ ካለህ፥መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚናገረውን ስማ። ድል ለሚነሳ ከተሰወረው መና እሰጠዋለሁ፤እንደዚሁም ከሚቀበለው ሰው በስተቀር ማንም የማያውቀውን አዲስ ስም የተጻፈብትን ነጭ ድንጋይ እሰጠዋለሁ።> 18 በቲያጥሮን ወዳለው መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ፤ “የእሰት ነበልባል የመሰሉ ዐይኖችና በእሳት ፍም የነጠረ ናስ የሚመስሉ እግሮች ያሉት የእግዚአብሔር ልጅ እንዲህ ይላል። 19 ሥራህን፣ ፍቅርህንና እምነትህን፣ አገልግሎትህንና በትዕግሥት መጽናትህን አውቃለሁ። አሁን በቅርቡ ያደረግኸው ቀድሞ ካደረግኸው የበለጠ መሆኑን አውቃለሁ።” 20 ነገር ግን የምነቅፍብህ አንድ ነገር አለኝ፤ራሷን ነቢይት ብላ የምትጠራውን ሴት ኤልዛቤልን ችላ ብለሃታል። ይህች ሴት በትምህርትዋ አገልጋዮቼ ሴሰኛ እንዲሆኑና ለጣዖት የተሰዋ ምግብ እንዲበሉ ታስታቸዋለች። 21 ንስሓ እንድትገባ ጊዜ ሰጥቻት ነበር ፤ይሁን እንጂ ከርኩሰትዋ ንስሓ ለመግባት ፈቃደኛ አልሆነችም። 22 እነሆ በሥቃይ አልጋ ላይ እጥላታለሁ፤ከእርስዋም ጋር የሚያመነዝሩት እርስዋ ከፈጸመችው ነገር ንስሓ ካልገቡ በስተቀር በከባድ ሥቃይ እንዲወድቁ አደርጋለሁ። 23 በሞት እቀጣለሁ፤በመሆኑም አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ የሰውን ሐሳብና ፍላጎትን የምመረምር እኔ እንደሆንሁ ያውቃሉ። ለእያንዳንዳችሁም እንደ ሥራችሁ እከፍላለሁ። 24 ዳሩ ግን ይህን ትምህርት ለማትከተሉ ሁሉ እንዲሁም አንዳንዶች የሰይጣን ጥልቅ ምስጢር ነው የሚሉትን ነገር ለማታውቁ በትያጥሮን ለምትኖሩ ለቀራችሁት ሌላ ሸክም አልጭንባችሁም።> 25 ሆኖም እስክመጣ ድርስ ያላችሁን ነገር አጸንታችሁ ጠብቁ። 26 ለሚነሣውና እስከ መጨረሻው እኔ የደረግሁትን ለሚያደርግ በሕዝቦች ላይ ሥልጣን እሰጠዋለሁ። 27 በብረት በትር ይገዛቸዋል፤ እንደ ሸክላም ዕቃ የደቃቸዋል። 28 እኔ ከአባቴ እንደ ተቀበልሁ የንጋትን ኮከብ እሰጠዋለሁ። 29 ጆሮ ያለው መንፈስ መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያን የሚለውን ይስማ።”
ሐዋርያት ነን የሚሉትን አማራጭ ትርጉም፡ "ሐዋርያት ነን የሚሉ ሰዎች"
የመጀመሪያው ፍቅር ይህ ማለት "ለክርስቶስ ያላችሁ የመጀመሪያ ፍቅር፡፡" መቅረዝህን እወስድሃለሁ እያንዳንዱ መቅረዝ ሰባቱን ቤተ ክርስቲያናትን ያመለክታል፡፡
ኒቆላውያንን ኒቆላ የሚባለውን ሰው ትምህርት የሚከተሉ ሰዎች፡፡ ጆሮ ያለው ይስማ መንፈሰሳዊ ጆሮዎች፡፡ ይህ ማለት እግዚብሔር ማድመጥ እና መልዕክቱን መረዳት የሚችል ሰው፡፡ እንዲበላ እፈቅድለታለሁ "እንዲበሉ እፈቅድላቸዋለሁ"
ስምርኔ ይህንንነ በ REV 1:11 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ መጀመሪያ እና መጨረሻ ይህንን በ REV 1:17 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
ዳብሎስ አንዳንዶቻችሁን ወደ ወህኒ ቤት ልጥላቸው ነው አማራጭ ትርጉም: "ዳብሎስ አንዳንዶቻችሁን ወደ ወህኒ እንድትገቡ በቅርቡ ያደርጋል" ጆሮ ካላችሁ በ REV 2:7. ላይ በተረጎምከው መሠረት ተርጉም፡፡
በጴርጋሞንም ይህንን በ REV 1:11. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡ አንቲጳስ ይህ የአንድ ሰው ስም ነው፡፡
ባላቅ ይህ አንድ ንጉሥ ስም ነው፡፡ ባላቅን የእስራኤል ልጆች ፊት መሠናከያ ዓለተ እንዲያኖር ያስተማረ አማራጭ ትርጉም: "የእስራኤል ሕዝብ እንዴት ኃጢአት ማድረግ እንደሚችል ለባላቅ ያሳየው" ለጣኦት የተሰዋ ምግብን መብላት አማራጭ ትርጉም: "ለጣኦት የተሰዋ ምግብ እና ያንን መብላት" መሴሰን አማራጭ ትርጉም፡ "ፍትወታዊ ኃጢአት" ወይም "የግብረ ሥጋ ግንኙነት በማድረግ ኃጢአት መፈጸም"
ይህንን የማታደርጉ ከሆነ እኔ "ንሰሓ የማትገቡ ከሆነ እኔ" ከአፌ በሚወጣው ሰይፍ ይህ በ REV 1:16. ላይ የተጠቀሰውን “ሰይፍ” ያመለክታል፡፡ የሚሰማ ጆሮ ያለው በ REV 2:7. ላይ ያለውን ትርጉም ተመልከት፡፡ ድል ለነሣው አማራጭ ትርጉም: "አሸናፉ ለሆነ ለማንኛውም ሰው"
ትያጥሮን ይህንን በ REV 1:11. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጅ ቃላት ናቸው፡፡ ከሞት የተነሣ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ካረገ ብዙ ዓመታት በኋላ አሁንም ለአማኞች በበመናገር ላይ ይገኛል፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ ይህ ለኢየሱስ በጣም ወሳኝ የሆነ የማረግ ስም ነው፡፡
ይሁን እንጂ የምነቅፍ ነገር አለኝ ይህንን በ REV 2:4. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡
በአልጋ ላይ እጥላታለሁ አማራጭ ትርጉም: "ታማሚ እንዲትሆን አደርጋለሁ" ወይም "በበሽታ እቀጣታለሁ" ማመንዘር "ዝሙት መፈጸም" እርሷ ስላደረገችው ነገር እነርሱ ንሰሓ ገቡ አማራጭ ትርጉም: "እንደ እርሷ በመሆናቸው ንሰሓ ገቡ" ልጆቿን በሞት እገድላቸዋለሁ አማራጭ ትርጉም: "ልጆቿን እገድላቸዋለሁ" ሀሳብን እና መሻትን የሚመረምረው እኔ ነኝ አማራጭ ትርጉም: "ሀሳብን እና መሻትን እመረምራለሁ" ወይም "አእምሮን እና ልብን እመረምራለሁ"
የሴጣንን ጥልቅ ነገር አማራጭ ትርጉም: "የሴጣንን የሐሰት ልምምድ" ወይም "የሴጣንን ውሸት" ወይም: እነዚህ መምህራን ምስጥ፣ አስገራም ልምምድ ብለው የሚናገሩት ሴጣን እንደነገራቸው የሚገልጹት ነገር ማለት ነው፡፡
ድል የነሣው አማራጭ ትርጉም: "ያሸነፈ ማንኛውም ሰው" እሰጠዋለሁ በዚህ ሥፍራ "እርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ያሸነፈውን ሰው ነው፡፡ የማለደ ኮከብ ይህ የሚያመለክተው ከንጋት በፊት የሚትታይ ደማቅ ኮከብን ነው፡፡
1 «በሰርዴስ ላለው ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ፤ "ሰባቱን የእግዚአብሔር መንፈሶችና ሰባቱን ከዋክብት የያዘው እንዲህ በማለት ይናገራል፤«ሥራህን ዐውቃለሁ፤ሕያው እንደሆንህ የሚገልጽ ዝነኛ ስም አለህ፤ነገር ግን ሞተሃል። 2 ሥራህን በእግዚአብሔር ፊት ፍጹም ሆኖ ስላላገኘሁት ንቃ፤ሊሞቱ የተቃረቡትን የቀሩትን ነገሮች አጽና። 3 እንግዲህ ምን እንደተቀበልህና ምን እንደሰማህ አስታውስ፤ጠብቀው፤ንስሓም ግባ። ነገር ግን ባትነቃ ፥እንደ ሌባ እመጣለሁ፤በምን ሰዓት እንደምመጣብህም አታውቅም። 4 ነገር ግን በሰርዴስ ልብሳቸውን ያላቆሸሹ ጥቂት ሰዎች አሉ። የተገባቸውም ስለ ሆነ፥ ነጭ ልብሳቸውን ለብሰው ከእኔ ጋር ይሄዳሉ። 5 ድል የሚነሳ ነጭ ልብስ ይለብሳል፤ስሙን ከሕይወት መጽሐፍ ፈጽሞ አልደመስሰውም፤ይልቁን በአባቴና በመላእክቱ ፊት ለስሙ እመሰክራለሁ። 6 ጆሮ ካለህም መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት ይሚናገረውን ስማ።» 7 «በፊላደልፍያ ላለው ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ፤ የዳዊት መክፈቻ ያለው፥የሚከፍት እርሱ የከፈተውን ማንም የማይዘጋ፥የሚዘጋ እርሱ የዘጋውን ማንም ሊከፍት የማይችል ቅዱስና እውነተኛ የሆነው እርሱ እንዲህ ይላል፤ 8 ሥራህን ዐውቃለሁ፤እነሆ፤ማንም ሊዘጋው የማይችል የተከፈተ በር በፊትህ አድርጌአለሁ። ዐቅምህ ትንሽ እንደሆነ አውቃለሁ፤ይሁን እንጂ ቃሌን ጠብቀሃል፤ስሜንም አልካድህም። 9 እነሆ፤አይሁድ ሳይሆኑ አይሁድ ነን የሚሉት እነዚያ ከሰይጣን ማኅበር የሆኑት ውሸተኞች ናቸው። እነርሱንም እኔ እንደ ወደድሁህ ያውቁ ዘንድ መጥተው በእግርህ እንዲወድቁ አደርጋለሁ። 10 በትዕግሥ እንድትጸና የሰጠሁህን ትእዛዜን ስለ ጠበቅህ ፥በምድር የሚኖሩትን ይፈትን ዘንድ በዓለም ላይ ሁሉ ሊመጣ ካለው የፈተና ሰዓት እጠብቅሃለሁ። 11 በቶሎ እመጣለሁ፤አክሊልህን ማንም እዳይወስድብህ፥ያለህን አጥብቀህ ያዝ። 12 ድል የሚነሻውን በአባቴ ቤተ መቅደስ ዐምድ አደርገዋለሁ፤ ከዚያ በፍጹም አይወጣም። እርሱ ላይ የአምላኬን ከተማ ስም፣ ማለት ከሰማይ ከእግዚአብሔር ዘንድ የምትወጣውን የአዲሲቱ ኢዩሳሌምን ስም ደግሞ አዲሱ ስሜን እጽፋለሁ። 13 ጆሮ ያለው መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያን የሚለውን የስማ።” 14 «በሎዶቅያ ላለው ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ፤ "ይህም በእግዚአብሔር ፍጥረት ላይ ገዥ እንዲሁም እውነተኛና ታማኝ ምስክር ከሆነው ቃሉም አሜን ከሆነው የተነገረ ነው፤ 15 ሥራህን አውቃለሁ፤በራድ ወይም ትኩስ አይደለህም። በራድ ወይም ትኩስ ብትሆን ኖሮ መልካም ይሆን ነበር። 16 እንግዲህ ትኩስ ወይም በራድ ሳትሆን በመካከል ለብ ስላልህ ከአፌ ልተፋህ ነው። 17 «እኔ ሀብታም ነኝ፤ብዙ ገንዘብ አለኝ፤የጎደለኝ ምንም ነገር የለም» ትላለህ፤ነገር ግን እጅግ ጎስቋላ፥ምስኪን፥ድኻ፥ዕውርና የተራቆትህ እንደሆንህ አታውቅም። 18 ሀብታም ትሆን ዘንድ በእሳት የተፈተነውን ወርቅ ከእኔ እንድትገዛ፥የራቁትነትህን ሐፍረት ለመሽፈን ነጭ ልብስ እንድትለብስ፥አጥርተህ ለማየትም ዐይንህን እንድትኳል እመክርሃለሁ። 19 እኔ የምወዳቸውን እንዴት መኖር እንደሚገባቸው ያውቁ ዘንድ እቀጣቸዋለሁ፤ አስተምራቸዋለሁም። ስለዚህ ትጋ፤ንስሓም ግባ። 20 እነሆ፤በደጅ ቆሜ አንኳኳለሁ። ማንም ድምጼን ሰምቶ ቢከፍትልኝ ወደ ቤቱ እገባለሁ፤ከእርሱ ጋር እበላለሁ፤እርሱም ከእኔ ጋር ይበላል። 21 እኔ ድል እንደነሳሁና በዙፋኑ ላይ ከአባቴ ጋር እንደተቀመጥሁ፥ድል ለሚነሳም በዙፋኔ ላይ ከእኔ ጋር የመቀመጥን መብት እሰጠዋለሁ። 22 መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚናገረውን ጆሮ ያለው ይስማ።»
ሰርዴስ ይህንን በ REV 1:11. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ቃል "እነዚህ የ ቃል ናቸው" ሥራህ ፍጹም ሆኖ አላገኘሁትም "ያደረከው ነገር ሙሉ ሆኖ አላገኘሁትም"
ንቃ ይህ የሚያመለክተው ትክክለኛ ነገር ለማድረግ መነሳትን ነው፡፡ እንደ ሌባ እመጣብሃለሁ ሌባ በማይታወቅ ሰዓት እንደሚመጣ ሁሉ ኢየሱስም ባልተጠበቀ ሰዓት ይመጣል፡፡ ልብሳቸውን ማቆሸሽ የለባቸውም ቆሻሻ ልብስ የሚያመለክተው በሕይወታቸው ውስጥ ያለውን ኃጢአት ነው፡፡ ነጭ መልበስ ነጭ ልብስ ንጹሕ ሕይወትን ያመለክታል፡፡
ድል የነሣው "ያሸነፈ ማንኛውም ሰው" ነጭ ልብስ መልበስ ነጭ ልብሽ ንጹሕ ሕይወትን ይወክላል፡፡ ጆሮ ያለው ይስማ . . . ቤተ ክርስቲያናት ይህንን በ REV 3:7. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
ፊልድልፍያ ይህንን በ REV 1:11. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ የዳዊት ቁልፍ “ቁልፍ” መንፈሳዊ ስልጣንን ወይም ኃይልን ያመለክታል፡፡ የተከፈተ በር ይህ እግዚአብሔርን የማገልገል ዕድልን ይወክላል፡፡ ያልካዱት አማራጭ ትርጉም: "ያልካዱት" የእኔ ስም "እኔ"
የሴጣን ምኩራብ . . . አይሁድ ሆነው ያልሆኑት ይህንን በ REV 2:9. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ መስገድ ይህ የአምልኮ ሳይሆን የመገዛት ምልክት ነው፡፡ በእግርህ ፊት "በአንተ ፊት" እነርሱን ለመፈተን "እነርሱን ለመፈተን" አጥብቀህ ያዝ "በማመን ቀጥል"
ድል የነሣው አማራጭ ትርጉም: "ያሸነፈ ማንኛውም ሰው" በእኔ አምላክ ቤተ መቅደስ ውስጥ ያለ ምሰሶ “ምሰሶ” በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ ጠቃሚ እና ቋሚ የሆነን ነገር ይወክላል፡፡
ሎዶቅያ ይህንንን በ REV 1:11. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ የአሜን ቃላት ዮሐንስ ለኢየሱስ ክርስቶስ አሜን የሚል ሌላ ስም ይሰጠዋል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "እነዚህ አሜን ተብሎ የሚጠራው ቃላት ናቸው፡፡" በራድ ወይም ትኩ እነዚህ ሁለት የተለያዩ መንፈሳዊ ፍላጎት ጽንፎችን ያሳያሉ፡፡ “በራድ” መሆን ሙሉ ለሙሉ እግዚአብሔር መቃወም ሲሆን፣ “ትኩስ” መሆን ማለት ደግሞ እግዚአብሔርን ለማገልገል ከፍተኛ ቅናት ያለው ሰው መሆን ማለት ነው፡፡ ለብ ያለ "በጥቂቱ የሞቀ፡፡" ይህ በተወሰነ ደረጃ መንፈሳዊ ፍላጎር ወይም እምነት ያለውን ሰው የሚያሳይ ነው፡፡
ጐስቋላና ምስኪንም ድሀም ዕውርም የተራቆትህም እነዚህ ቃላት በጣም መጥፎ በሆነ መንፈሳዊ ሁኔታ ውስጥ ያለን ነገር ግን በመጥፎ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን የማያውቁ ሰዎችን ያመለክታሉ፡፡ ባለ ጠጋ እንድትሆን ይህ በመንፈሳዊነት ንጹሕ መሆንን እና ከእግዚአብሔር ጋር መልካ ግንኙነት መኖርን ያመለክታል፡፡ ጥሩ ነጭ ልብስ ነጭ ልብስ መንፈሳዊ ንጽሕናን ይወክላል፡፡
ቅና ንሰሓም ግባ "በቁም ነገር ንሰሓ ግባ" እኔ በደጅ ቆሜ መዝጊያ በሩን አንኳኳለሁ “መዝጊያ በር” ክርስቶስ ልገባበት የሚፈልገውን ሕይወታችንን ወይም ነፈሳችንን ያመለክታል፡፡ ድምፄን ይሰማሌ “ድምፅ” የክርስቶስን ጥሪ ይወክላል፡፡ በሩን ክፈቱ ይህ ክርስቶስን ለመቀበል መወሰን እና ወደ ውስጥ እንዲገባ መጋዘበዝን ያመለክታል፡፡ ከእርሰሱ ጋር መብላት ይህ ግንኙነትን፣ ጓደኝነትን፣ ሕብረትን ያመልክታል፡፡
ድል የነሣው ይህንን በ REV 2:7 ላይ ምን ብለህ አንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "አሸናፊ የሆነ ማንኛውም ሰው፡፡". በዙፋኔ ላይ ከእኔ ጋር ይቀመጣል፡፡ በዙፋን ላይ መቀመጥ ማለት መግዛት ማለት ነው፡፡ ጆሮ ያለው ይስማ ይህን በ REV 2:7. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
1 ከእነዚህ ነገሮች በኋላ እነሆ የተከፈተ በር በሰማይ አየሁ። እንደ መለከት ድምፅ ሆኖ ሲናገረኝ የነበረው የመጀመሪያው ድምፅ፥«ወደዚህ ና! ከእነዚህ ነገሮች ሁሉ በኋላ የሚሆነውን አሳይሃለሁ።» አለ። 2 ወዲያው በመንፈስ ነበርሁ፤በሰማይ ዙፋን ተዘርግቶ አየሁ፤በዙፋኑም ላይ አንድ የተቀመጠ አካል ነበር። 3 በዙፋኑም ላይ ተቀምጦ የነበረው መልኩ የኢያስጲድንና የሰርዲኖን ዕንቁ ይመስል ነበር። በዙፋኑም ዙሪያ የመረግድ ዕንቁ የመሰለ ቀስተ ደመና ነበር። 4 በዙፋኑም ዙሪያ ሃያ አራት ዙፋኖች ነበሩ፤በእነዚህም ዙፋኖች ላይ ነጭ ልብስ የለበሱና በራሳቸውም ላይ የወርቅ አክሊል የደፉ ሃያ አራት ሽማግሌዎች ተቀምጠው ነበር። 5 ከዙፋኑም የመብረቅ ብልጭታና የነጎድጓድ ድምፅ ወጣ። በዙፋኑም ፊት ሰባት መብራቶች ይበሩ ነበር፤እነዚህም ሰባቱ የእግዚአብሔር መንፈሶች ናቸው። 6 እንደዚሁም በዙፋኑ ፊት እንደ መስተዋት እጅግ የጠራ ባሕር ነበር። በዙፋኑም ዙሪያ ሁሉ ከፊትና ከኋላ በዐይን የተሞሉ አራት ሕያዋን ፍጡራን ነበሩ። 7 የመጀመሪያው ሕያው ፍጡር አንበሳ ሲመስል፥ሁለተኛው ሕያው ፍጡር ጥጃ ይመስል ነበር፤ሦስተኛው ሕያው ፍጡር የሰውን ፊት የሚመስል ፊት ነበረው፤አራተኛው ሕያው ፍጡር ደግሞ የሚበር ንስር ይመስል ነበር። 8 አራቱም ሕያዋን ፍጡራን እያንዳንዳቸው ስድስት ክንፍ ነበራቸው፤ከላይና ከሥርም በዐይኖች የተሞሉ ነበሩ። እነርሱም ቀንና ሌሊት፥ «ቅዱስ፥ቅዱስ፥ቅዱስ፥ በሁሉም ላይ የሚገዛ፥የነበረና ያለ፥ወደፊትም የሚመጣው ጌታ አምላክ» ማለትን አያቋርጡም ነበር። 9 ሕያዋን ፍጡራኑም በዙፋኑ ላይ ለተቀመጠውና ከዘላለም እስከ ዘላለም ለሚኖረው ክብር፥ ሞገስና ምስጋና በሚሰጡበት ጊዜ፥ 10 ሃያ አራቱ ሽማግሌዎች በዙፋኑ ላይ በተቀመጠው ፊት በግምባራቸው ተደፍተው ከዘላለም እስከ ዘላለም ለሚኖረው ሰገዱ፤አክሊላቸውንም በዙፋኑ ፊት አስቀምጠው፥ 11 «ጌታችንና አምላካችን ሆይ፤አንተ ሁሉንም ነገር ስለፈጠርህ፥በፈቃድህ ስለፈጠርሃቸውና እንደዚያም ሆነው ስለተገኙ ክብር፥ሞገስ፥ኅይልም ልትቀበል ይገባሃል።» ይሉ ነበር።
ከእነዚህ ነገሮች በኋላ ዮሐንስ ኢየሱስ ለሰሰባቱ አብያተ ክርስቲያት የተናገረውን ከሰማ በኋላ፡፡ (REV 2:1-3:22). በሰማይ ያለው ያ መዝጊያ በር ተከፈተ አማራጭ ትርጉም፡ "ወደ ሰማይ መግቢያ በር" የኢያስጲድንና የሰርዲኖን እነዚህ በመጠኑም ቢሆን ውድ ድንጋዮች ናቸው፡ ይሁን አንጂ ምን አይነት ቀለም እንዳላቸው ግን በእርግጠኝነት ማናገር አንችልም፡፡ ቀስተ ዳመና የጸሐይ ብርሃን ከኋላቸው ሆኖ ከፊታቸው ደግሞ ዝናብ ስዘንብ ሰዎች የሚመለከቱት ቀለማት ናቸው፡፡ መረግድ አረንጓዴ ቀለም ያለው በተወሰነ መልኩም ቢሆን ውድ የሆነ ድንጋይ ነው፡፡
የመብረቅ ብልጭታ በቋንቋችሄ የመብረቅ ብልጭታ መታየቱን ለማመልከት የሚያገለግል ቃልን ተጠቀሙ፡፡ መብረቅ እና የነጎድጓድ ድምፅ "እንደ ነጎድጓድ ያለ ድምፅ"
ብርጭቆ ሙሉ ለሙሉ ግልጽ የሆነ ነገር፣ አማራጭ ትርጉም: "ብርጭቆ" ወይም "በረዶ፡፡"
የነበረ፣ ያለ እና የሚመጣው እግዚአብሔር ሁል ጊዜ የሚኖር ነው፡፡
ከዘላለምም እስከ ዘላለም በሕይወት ለሚኖረው “ከዘላለም እስከ ዘላለም” ማለት እርስ “ለዘላለም” ይኖራል ማለት ነው፡፡ ጌታችን እና አምላካችን ተናጋሪዎች እንጂ ሰሚዎች አይደሉም ሆነዋል እንዲሁም ተፈጠትረዋል “ሆነዋል” እና “ተፈጥረዋል” የሚለው ቃል ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው ሲሆን እግዚአብሔር ሁሉን ነገር እንደፈጠረ አጽኖት ሰጥተው የሚገልጹ ናቸው፡፡
1 በዙፋኑም ላይ በተቀመጠው ቀኝ እጅ ከፊትና ከጀርባ የተጻፈበት በሰባትም ማኅተም የታሸገ ጥቅልል መጽሓፍ አየሁ። 2 አንድ ብርቱ መልአክ፥«መጽሓፉን ሊከፍት፥ ማኅተሙን ሊፈታ የተገባው ማን ነው?» ብሎ በታላቅ ድምፅ ሲያውጅ አየሁ። 3 በሰማይ ቢሆን በምድር ወይም ከምድር በታች መጽሓፉን ሊከፍት ወይም ሊያነብ ማንም አልቻለም። 4 መጽሓፉን ሊከፍት ወይም ሊያነብ የተገባው ማንም ስላልተገኘ፥አምርሬ አለቀስሁ። 5 ነገር ግን ከሽማግሌዎች አንዱ፥«አታልቅስ፤እነሆ! ከዳዊት ሥር፥ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ መጽሓፉን ይከፍትና ሰባቱንም ማኅተም ይፈታ ዘንድ ድል ነስቷል» አለኝ። 6 በዙፋኑና በአራቱ ሕያዋን ፍጡራን መካከል እንዲሁም በሽማግሌዎች መካከል አንድ ታርዶ የነበረ የሚመስል በግ ቆሞ አየሁ። እርሱም ሰባት ቀንዶችና ሰባት ዐይኖች ነበሩት፤እነዚህም በምድር ሁሉ ላይ የተላኩ ሰባቱ የእግዚአብሔር መንፈሶች ናቸው። 7 ሄዶም በዙፋን ላይ ከተቀመጠው ቀኝ እጅ ጥቅልል መጽሓፉን ወሰደ። 8 ጥቅልል መጽሓፉንም በሚወስድበት ጊዜ አራቱ ሕያዋን ፍጡራን እና ሃያ አራቱ ሽማግሌዎች በበጉ ፊት በግምባራቸው ተደፉ፤ እያንዳንዳቸውም በገና እና የቅዱሳን ጸሎት የሆነው ዕጣን የሞላበት የወርቅ ዕቃ ይዘው ነበር። 9 እነርሱም እንዲህ የሚል አዲስ ቅኔ ዘመሩ፤«መጽሓፉን ትወስድ እና ማኅተሞቹን ተፈታ ዘንድ ይገባሃል፤ ታርደሃልና በደምህም ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ፥ከቋንቋ ሁሉ፥ ከሕዝብና ከአገር ሁሉ ሰዎችን ዋጅተሃል። 10 አምላካችንን ያገለግሉ ዘንድ መንግሥትና ካህናት አደረግሃቸው፤እነርሱም በምድር ላይ ይገዛሉ።» 11 ከዚያም በኋላ ስመለከት፥በዙፋኑ፥በሕያዋኑ ፍጡራን እና በሽማግሌዎች ዙሪያ የብዙ መላእክት ድምፅ ሰማሁ፤ቁጥራቸውም ሁለት መቶ ሚሊዮን ነበር። 12 እነርሱም በታላቅ ድምፅ፥«የታረደው በግ ኀይልና ባለጠግነት፥ጥበብና ብርታት፥ምስጋና እና ክብር ሊቀበል ይገባዋል።» አሉ። 13 በሰማይና በምድር፥ከምድር በታች እንዲሁም በባሕር ላይ ያለ ፍጥረት ሁሉ በእነርሱም ውስጥ ያለ ሁሉ ፥«ምስጋና፥ክብር፥ውዳሴ፥የመግዛትም ኀይል ከዘላለም እስከ ዘላለም በዙፋኑ ላይ ለተቀመጠው እና ለበጉ ይሁን።» ሲሉ ሰማሁ፤ 14 አራቱ ሕያዋን ፍጡራን፥«አሜን» አሉ፤ሽምግሌዎችም በግምባራቸው ተደፍተው ሰገዱ።
ከዚያም ተመለከትኩ "እነዚህ ነገሮች ካየሁ በኋላ ይህንን አየሁ" በዙፋኑ ላይ የተቀመጠው ይህ በ REV 4:2-3. ላይ ከተገለጸው ጋር “ተመሳሳይ ነው”፡፡ ሲያውጅ ከዚህ በመቀጠል ከቀረበው ጥያቄ ጋር የሚስማማ ቃልን ተጠቀም፡፡
በሰማይ ወይም በምድር ወይም ከምድር በታች "በዬትኛውም የተፈጠረ ሥፍራ" ወይም "በሁሉም ሥፍራ፡፡" ይህ እግዚአብሔር እና መለአክቱ፣ ሰዎች የሚኖሩበት እና የሞቱት የሚኖሩበት ሥፍራ ነው፡፡ ተመልከት አማራጭ ትርጉም: "አድምጥ" ወይም "አሁን ልነገርህ ስላለሁት ነገር ትኩረት ሰጥተህ አድምጠኝ"
ወሰደው "በጉ ወሰደው" እያንዳንዳቸው አማራጭ ትርጉሞች 1) "እያንዳንዱ ሽማግሌዎች እና ሕያዋን ፍጥረታት" ወይም 2) "እያንዳንዱ ሽማግሌዎች፡፡"
አንተ ታርደሃልና አማራጭ ትርጉም: "አንተን አረደዋልና" ታርዷል በቋንቋችሁ ውስጥ ለመስዋእትነት የሚቀርቡ እንስሳትን መሰዋትን የሚያመለክት ቃል ካለ በዚህ ሥፍራ ይህን ቃል ለመቀበል ሞክሩ፡፡ ለእግዚአብሔር ሰዎችን ገዝተሃል፡፡ "ሰዎች የእግዚአብሔር መሆን ይችሉ ዘንድ አስፈላጊውን ዋጋ ከፍለሃል፡፡" ገዝተሃል ይህ ሌላ ሰው የተከፈለውን ዋጋ ወስዷል የሚል ትርጉም ሊኖረው አይገባም፡፡ አማራጭት ትርጉም፡ “ዋጅተሃል” (DB)፡፡ ከነገድ፣ ከቋንቋ፣ ከሕዝብ እና ከሀገር ሁሉ ሰዎችን ለእግዚብሔር አማራጭ ትርጉም: "ሁሉንም ዓይነት ሰዎች" ወይም "ሰዎችን ከሁሉም ሥፍራ"
200,000,000
በሰማይ እና በምድር እንዲሁም ከምድር በታች ይህንን በ REV 5:3. ላይ ምን ብለህ እደተረጎምክ ተመለክት፡፡ በባሕር ላይ በጀልባዎች
1 ከዚህም በኋላ በጉ ከሰባቱ ማኅተሞች አንዱን ሲከፍት አየሁ፤ከአራቱ ሕያዋን ፍጡራን አንዱ እንደ ነጎድጓድ ባለ ድምፅ «ና!» ሲል ሰማሁ። 2 አየሁም ፤እነሆም አንድ ነጭ ፈረስ አየሁ፤ባላዩ ላይ የተቀመጠውም ቀስት ይዞ ነበር፤አክሊልም ተሰጠው። እንደ ድል አድራጊ ሆኖ ድል ይነሳ ዘንድ ወጣ። 3 በጉ ሁለተኛውን ማኅተም በሚከፍትበት ጊዜ፥ሁለተኛው ሕያው ፍጡር«ና!» ሲል ሰማሁ። 4 ከዚያም ደማቅ ቀይ ፈረስ ወጣ፤በፈረሱም ላይ ለተቀመጠው ሰዎች እርስ በርስ ይተራረዱ ዘንድ ሰላምን ከምድር እንዲያስወግድ ሥልጣን ተሰጠው፤ትልቅ ሰይፍም ተሰጠው። 5 በጉ ሦስተኛውን ማኅተም በሚከፍትበት ጊዜ፥ ሦስተኛው ሕያው ፍጡር «ና!» ሲል ሰማሁ፤ ጥቁር ፈረስ አየሁ፤በፈረሱም ላይ የተቀመጠው በእጁ ሚዛን ይዞ ነበር። 6 ከአራቱ ሕያዋን ፍጡራን የመጣ የሚመስል ድምፅ፥«አንድ እርቦ ስንዴ በዲናር፥ሦስት እርቦ ገብስም በዲናር፤ ነገር ግን ዘይቱንና ወይኑን አትጉዳ» ሲል ሰማሁ። 7 በጉ አራተኛውን ማኅተም በሚከፍትበት ጊዜ የአራተኛው ሕያው ፍጡር ድምፅ «ና!» ሲል ሰማሁ። 8 ከዚያም በኋላ ግራጫ ፈረስ አየሁ፤በላዩም ላይ የተቀመጠው ስሙ ሞት ተብሎ ይጠራ ነበር፤ሲኦልም ይከተለው ነበር። ሞትና ሲኦልም የምድርን አንድ አራተኛ በሰይፍ፥በረሃብ፥ በበሽታ፥በዱር አራዊት እንዲገድሉ ሥልጣን ተሰጣቸው። 9 በጉ አምስተኛውን ማኅተም በሚከፍትበት ጊዜ ስለ እግዚአብሔር ቃልና በጽናት ስለ ጠበቁት ምስክርነት የተገደሉትን ሰዎች ነፍሶች ከመሠዊያው በታች አየሁ። 10 እነርሱም በታላቅ ድምፅ፥«በሁሉም ላይ የምትገዛ ቅዱስና እውነተኛ የሆንህ ጌታ አምላክ ሆይ፤በምድር በሚኖሩት ላይ የማትፈርደው፥ ደማችንስ የማትበቀለው እስከ መቼ ድረስ ነው?» በማለት ይጮኹ ነበር። 11 ከዚያም በኋላ ለእያንዳንዳቸው ነጭ ልብስ ተሰጣቸው፤እነርሱ እንደ ተገደሉ፥ ገና የሚገደሉ አገልጋይ ጓደኞቻቸው፥ወንድሞቻቸውና እህቶቻቸው ቁጥር እስኪሞላ ድረስ ለጥቂት ጊዜ እንዲታገሱ ተነገራቸው። 12 በጉ ስድስተኛውን ማኅተም በሚከፍትበት ጊዜ አየሁ፤ እነሆ ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ። ፀሐይም እንደ ጥቁር ጨርቅ ጠቆረች፤ ጨረቃም ሙሉ በሙሉ እንደ ደም ቀላች። 13 የበለስ ዛፍ ኀይለኛ ነፋስ በሚወዘውዛት ጊዜ በላይዋ ያለ ያልበሰለ ፍሬ እንደሚረግፍ ሁሉ የሰማይ ከዋክብት ወደ ምድር ረገፉ። 14 ሰማይም እንደ ብራና እየተጠቀለለ ተወገደ፤ እያንዳንዱ ተራራና ደሴት ከስፍራው ተነቀለ። 15 ከዚያም በኋላ የምድር ነገሥታት፥ታላላቅ ሰዎች፥ የጦር መኮንኖች፥ ሀብታሞች፥ብርቱዎች፥ ባሮችና ጌቶች ሁሉ በዋሻዎችና በተራሮች ዐለት ውስጥ ተሸሸጉ። 16 ለተራሮችና ለዐለቶችም እንዲህ ሲሉ ተናገሩ፤«በላያችን ላይ ውደቁ፤ በዙፋኑ ላይ ከተቀመጠው ፊት፥ከበጉም ቁጣ ሰውሩን 17 ታላቁ የቁጣቸው ቀን ስለ መጣ ማን መቆም ይችላል?»
እኔ “እኔ” የሚለው ቃል በሁሉም ሥፍራዎች ላይ የሚያመለክተው ጸሐፊውም ዮሐንስ ነው፡፡ ሰባቱን ማህተሞት የፈታህ ከሰባቱ ማህተሞት መካከል በቁጥር አንድ ላይ የሚገኘውን የፈታህ
ሁለተኛውን ማህተም የፈታህ በሁለት ቁጥር ላይ የሚገኘውን ማህተም የፈታህ የቀይ ዳማ "ደማቅ ቀይ" ፈረስ ላይ ለተቀመጠው ፈቃድ ተሰጠው አማራጭ ትርጉም: "እግዚብሔር ፈረስ ላይ ለተቀመጠው ፈቃድ ሰጠው"
ሦስተኛውን ማህተም ፈታ በሦስተና ተራ ቁጥር ላይ የሚገኘውን ማህተም ፈታ እርቦ ስንዴ ይህ የመሥፈሪያ ዓይነት ሲሆን ከአንድ ሊተር ጋር ይስተካከላል፡፡ አንድ ዲናር ይህ ገንዘብ የአንድ ቀን ሥራ ደሞዝ ጋር እኩል ነው፡፡
ከእምነታቸው የተነሣ አማራጭ ትርጉም፡ "አጥበቀው ያምኑ ነበር" ወይም "በጣም ያምናሉ"
ፀሐይም እንደ ማቅ ጠጕር ጥቁር ሆነ፥ ፀሐይ በጣም ጠቆረች፡፡
ጀነራሎች የጦር አዛዦችን የሚያመልክ ቃል ነው፡፡ በዋሻዎች ውስጥ ተሸሸጉ አማራጭ ትርጉም፡ "በተራሮች መካከል በሚገኙ ትልልቅ ዋሻዎች ውስጥ ተሸሸጉ" ወይም "በምድር ውስጥ በተቆፈሩ ምሽጎች ውስጥ ተሸሸጉ" የእርሱን ፊት “እርሱ” የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ነው፡፡
1 ከዚህ በኋላ አራት መላእክት በአራቱም የምድር ማዕዘን ቆመው አየሁ፤ እነርሱም በምድር ቢሆን በባሕር ላይ ወይም በማንኛውም ዛፍ ላይ ፈጽሞ ነፋስ እንዳይነፍስ አራቱን የምድር ነፋሳትን አጥብቀው ይከለክሉ ነበር። 2 የሕያው አምላክ ማኅተም የያዘ ሌላ መልአክ ከምስራቅ ሲመጣ አየሁ። እርሱም ምድርንና ባሕርን ይጎዱ ዘንድ ሥልጣን ወደ ተሰጣቸው ወደ አራቱ መላእክት በታላቅ ድምፅ እየጮኽ፥ 3 «በአምላካችን አገልጋዮች ግምባር ላይ ማኅተም እስክናደርግ ድረስ ምድርንም ሆነ ባሕርን ወይም ዛፎችን እንዳትጎዱ» አለ። 4 ከእስራኤል ሕዝብ ነገድ ሁሉ የታተሙት ሰዎች ቁጥር አንድ መቶ አርባ አራት ሺህ እንደ ሆነ ሰማሁ። 5 ከይሁዳ ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ ፥ከሮቤል ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ ፥ከጋድ ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ 6 ከአሴር ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከንፍታሌም ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ ፥ከምናሴ ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ 7 ከስምዖን ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ ፥ከሌዊ ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ከይሳኮር ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ 8 ከዛብሎን ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ከዮሴፍ ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ከብንያም ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ ታተሙ። 9 ከዚህ በኋላ ከሕዝብ፥ከነገድ፥ከወገንና ከቋንቋ ሁሉ የመጡ ቁጥራቸው ማንም ሊቆጥረው የማይችል አጅግ ብዙ ሕዝብ ነጭ ልብስ ለብሰው፥ በእጃቸውም የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው በዙፋኑና በበጉ ፊት ቆመው አየሁ። 10 በታላቅ ድምፅም «ማዳን፥ በዙፋኑ ላይ የተቀመጠው የአምላካችንና የበጉ ነው!» እያሉ ይጮኹ ነበር። 11 መላእክቱም ሁሉ በዙፋኑ እና በሽማግሌዎች ዙሪያ እንዲሁም በአራቱ ሕያዋን ፍጡራን ዙሪያ ቆመው ነበር፤እነርሱም በመሬት ላይ ወድቀው በዙፋኑም ፊት በግምባራቸው ተደፍተው ለእግዚአብሔር እየሰገዱ፥ 12 «አሜን! ውዳሴ፥ ክብር፥ጥበብ፥ምስጋና፥ኀይልና ብርታትም ከዘላለም እስከ ዘላለም ለአምላካችን ይሁን፤አሜን» ይሉ ነበር። 13 ከዚያም በኋላ ከሽማግሌዎች አንዱ፥«እነዚህ ነጭ ልብስ የለበሱ እነማናቸው ከየትስ የመጡ ናቸው?» በማለት ጠየቀኝ፤ 14 እኔም «ጌታ ሆይ፥አንተ ታውቃለህ» አልሁት። እርሱም እንዲህ አለኝ፤«እነዚህ በታላቁ መከራ ውስጥ አልፈው የመጡ ናቸው፤ልብሳቸውንም በበጉ ደም አጥበው በማንጻት ነጭ አድርገዋል። 15 ክዚህም የተነሳ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት መሆን ችለዋል፤ እርሱንም በመቅደሱ ውስጥ ቀንና ሌሊት ያመልኩታል። በዙፋኑም ላይ የተቀመጠው ድንኳኑን በእነርሱ ላይ ይዘረጋል። 16 እነርሱም ከእንግዲህ አይራቡም፤አይጠሙምም። ፀሐይ አያቃጥላቸውም፤ ሙቀትም አያሰቃያቸውም። 17 ምክንያቱም በዙፋኑ መካከል ያለው በጉ እረኛቸው ይሆናል፤ወደ ሕይወት ውኃ ምንጭ ይመራቸዋል፤እግዚአብሔር እንባንም ሁሉ ከዐይኖቻቸው ያብሳል።»
የታተመው አማራጭ ትርጉም: "የእግዚአብሔር ምልክት ያለባቸው ሰዎች" 12,000 ከእያንዳንዱ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ 144,000 ከእያንዳንዱ ነገር ዐሥራ ሁለት ሺህ በዐሥራ ሁሉት ቡድኖች ነበሩ፡፡ የእስራኤል ነገዶች ሁሉም በእስራኤል ውስጥ ዐሥራ ሁሉት ነገዶች የነበሩ ሲሆን እያንዳንዱን በያዕቆብ ልጆች ስም ተሰይሟል፡፡
ከዙፋኑ ፊት ቆሙ እንዲሁም በበጉ ፊት ቆሙ "በዙፋኑ እና በበጉ ፊት ቆሙ" ነጭ ልብስ በዚህ ሥፍራ “ነጭ” ቀለም የሚያመለክተው ንጽሕናን ነው፡፡ ድነት የበጉ . . . ለሆኑትነው "በዘፉኑ ላይ የተቀመጠው አምላካችን እና በጉ አድኖናል" ወይም "ድነት በዙፋኑ ላይ ከተቀመጠው እና ከበጉ ዘንድ መትቶልናል"
መላእክት ሁሉ . . . ሕያዋን ፍጥረታት "በዙፋኑ ዙሪያ የቆሙት ሁሉም መላእክት እና ሽማግሌዎች እንዲሁም አራቱ ሕያዋን ፍጥረታት" አራቱ ሕያዋን ፍጥረታት እነዚህ በ REV 4:6-8. ላይ አስቀድመው የተጠቀሰሱት አራቱ ፍጥረታት ናቸው፡፡ ምሳጋና፣ ክብር . . . ለአምላካችን ይሁን "አምላካችን ምስጋና፣ ክብር፣ ትበብ፣ ምስጋና፣ አክብሮት እና ኃይል ሁሉ ይገባዋል" ከዘላለም እስከ ዘላለም እነዚህ ሁለት ቃላት በመሠረታዊ ሀሳባቸው ተመሳሳይ ሲሆን አጽኖት የሚሰጡት ሕያዋን ፍጥረታት ሁሉ ለዘላለም እግዚአብሔርን እንደሚያመልኩት ነው፡፡
ልብሳቸውን አጥበዋል እንዲሁም በበጉ ደም ነጭ አድርገዋል “ነጭ” ቀለም የሚያመለክተው ንጽሕናን ሲሆን “ደም” ብዙ ጊዜ ነገሮችን ለማንጻት ጥቅም ላይ ከሚውለው ከውሃ ጋር ተነጻጽሮ ቀርቧል፡፡ ንጽሕና የሚገኘው “በመታጠብ” ነው ወይም በክርስቶስ ደም በመሸፈን ነው፡፡
እነርሱ . . . እነርሱ . . . እነርሱ እነዚህ ሁሉ ተውላጠስሞች የሚመለክቱት በታላቁ መከራ ውስጥ ያለፉትን ሰዎችን ነው፡፡ ፀሐይ አታሸንፋቸውም ይህ ማለት ፀሐይ ከሙቀቷ የጠነሣ ከእንግዲህ ወዲህ አታሰቃያቸውም፡፡
1 በጉ ሰባተኛውን ማህተም በፈታ ጊዜ በሰማይ ለግማሽ ሰዓት ያህል ጸጥታ ሆነ፤ 2 ከዚያም በእግዚአብሄር ፊት የቆሙ ስባት መላዕክትን አየሁ፡፤ሰባት መለከቶችም ተሰጣቸው። 3 ሌላም መልኣክ መጣ፤በእጁም ከወርቅ የተሰራ ጥና ይዞ ነበር።እርሱም በመሰዊያው አጠገብ ቆሞ ነበር።በዙፋኑ ፊት ባለው በወርቅ በተሰራ መሰዊያ ላይ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር የሚያቀርበው ብዙ ዕጣን ተሰጠው። 4 የእጣኑ ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ ወደ እግዚአብሄር ወጣ፤ 5 መልአኩም ጥናውን ወስዶ ከመሰዊያው በወስድው እሳት ሞላው ከዚያም በኃላ ወደ ምድር ወረወረው፤የነጎድጛድ ድምጽ፤መብረቅ፤የምድር መናወጥም ሆነ። 6 ሰባት መለከቶችን የያዙ ስባት መላዕክት መለከቶቻቸውን ለመንፋት ተዘጋጁ። 7 የመጀመሪያውም መልአክ መለከቱን ነፋ፤ደም የተቀላቀለበት እሳትና በረዶ ሆነ። ይህም ወደ ምድር ተጣለ፤ ከዚህም የተነሣ የምድርም አንድ ሦስተኛ ተቃጠለ፤ የዛፎችም አንድ ሦስተኛ ተቃጠለ፤ የለመለመ ሣር ሁሉ ተቃጠለ። 8 ሁለተኛውም መልአክ መለከቱን ነፋ፤ በእሳት የሚቃጠል ትልቅ ተራራ የሚመስል ነገር ወደ ባህር ተጣለ፤ የባህር አንድ ሦስተኛ ወደ ደም ተለወጠ። 9 በባህር ውስጥ ካሉ ህያዋን ፍጥረታት አንድ ሦስተኛ ሞቱ፤ የመርከቦችም አንድ ሦስተኛ ተደመሰሱ። 10 ሦስተኛውም መልአክ መለከቱን ነፋ፤ እንደ ችቦ የሚቃጠል ታላቅ ኮከብ ከሰማይ ወደቀ፤ የወደቀውም በወንዞች አንድ ሦስተኛ በውሃ ምንጮች ላይ ነው። 11 የኮከቡም ስም እሬቶ ይባላል። የውኆችም አንድ ሦስተኛ መራራ ሆነ። ከውሃው መራራነት የተነሳ ብዙ ሰዎች ሞቱ። 12 አራተኛውም መልአክ መልከቱን ነፋ፤የፀሐይ አንድ ሦስተኛ፣ የጨረቃ አንድ ሦስተኛ የኮከቦች አንድ ሦስተኛ ተመታ። ስለዚህ የእነርሱ አንድ ሦስተኛ ጨለመ፤ በዚህም ምክንያት የቀን አንድ ሦስተኛና የሌሊት አንድ ሦስተኛው ያለ ብርሃን ሆነ። 13 እነሆ በሰማይ መካከል ሲበርር የነበር አንድ ንስር በታላቅ ድምጽ፤ ሦስቱ መላእክት የቀሩትን መለከቶች ስለሚነፉ «በምድር ላይ ለሚኖሩ ወዮላቸው! ወዮላቸው! ወዮላቸው!» ሲል ሰማሁ።
ሰባት መለከቶች ተሰጣቸው አማራጭ ትርጉሞች: 1) እግዚአብሔር ሰባት መለከቶችን ሰጣቸው ወይም 2) በጉ ሰባት መለከቶችን ሰጣቸው፡፡
ወደ ምድር ተወረወሩ አማራጭ ትርጉም: "መለላእኩ ወደ ምድር ወረወረው፡፡" አንድ ሦስተኛው እጅ ተቃጠለ፣ አንድ ሦተኛው ዛፍ ተቃጠል እንዲሁም ሁሉም አረንጓዴ ሣሮች ተቃጠሉ አማራጭ ትርጉም: "የምድር አንድ ሦስተኛው ተቃጠለ፣ የዛፎች አንድ ሦስተኛ ተቃጠለ እንዲሁም አረንጓዴ ሣሮቹ ተቃጠሉ"
በእሳት የሚቃጠል ታላቅ ተራራን የሚመስል ነገር በባሕር ተጣለ፤ "መላእኩ በእሳት የሚቃየል ታላቅ ተራራን የሚመስል ነገር በባሕር ተጣለ" የባሕርም ሲሶው ደም ሆነ በባሕርም ከሚኖሩ ሕይወት ካላቸው ፍጥረቶች ሲሶው ሞተ የመርከቦችም ሲሶው ጠፋ። አማራጭ ትርጉም: "የባሕር ሲሶው ደም እንዲሆን አደረገ፤ በባሕር ውስጥ ከሚኖሩት ሕያዋን ፍጥረታት መካከል ሲሶው ሞቱ እንዲም የመርከቦቹ ሲሶው ጠፋ፡፡" ደም ሆነ አማራጭ ትርጉሞች: 1) "እንደ ደም ሆኑ" 2) literally "became blood."
እና እንደ ችቦም የሚቃጠል ታላቅ ኮከብ ከሰማይ ወደቀ፥ "እና እንደ ችቦ የሚቃጠል ታላቅ ኮከብ ከሰማይ ወደቀ፡፡" የታላቁ ኮከብ እሳት ልክ የሚቃጠል ችቦ ጋር ተመሳሳይነት አለው፡፡ ችቦ በአንድ በኩል መንደድ የሚችል ብርሃን የሚሰጥ እንጨት፡፡ የኮከቡም ስም እሬቶ ነው የኮከቡ ስም “እሬቶ” የሆነው መራራ ጣዕም ካለው ተከል ተነስቶ ነው፡፡ እሬቶ በኮከብ የተመረዘ፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ “መራራ”
የፀሐይ ሲሶ ተመታ አማራጭ ትርጉም፡ "የፀሐይን ሲሶ ጨለማ ዋጠው"
ሊነፉ ያላቸው የሦስቱ መላእክት መለከት ስለሚቀረው ድምፅ በምድር ላይ ለሚኖሩት ወዮላቸው፥ ወዮላቸው፥ ወዮላቸው ሲል ሰማሁ። አማራጭ ትርጉም፡ "የመለከት ድምፅ እሰስካሁን ያላሰሙት ሦስቱ መላእክት ማሰማት ልጀምሩ ስለሆነ"
1 አምስተኛውም መልአክ መለከቱን ነፋ፤ አንድን ኮከብ ከሰማይ ወደ ምድር ሲወድቅ አየሁ። ኮከቡም የጥልቁ ጕድጓድ መክፈቻ ተሰጠው፤ 2 እርሱም ጥልቅ የሆነውን ጕድጓድ ከፈተው፤ ጢስም ከታላቅ ምድጃ እንደሚወጣ ጢስ ሆኖ ከጕድጓዱ ወጣ፤ ከጕድጓዱ በሚወጣው ጢስ ምክንያት ፀሐይና አየር ወደ ጨለማነት ተለወጡ፤ 3 ከጢሱም ውስጥ አንበጣዎች በምድር ላይ ወጡ፤የምድር ጊንጦችን ኅይል የመሰለ ኅይል ተሰጣቸው፤ 4 የምድርንም ሣር ሆነ ማናቸውንም የለመለመ ተክል ወይም ማናቸውንም ዛፍ እንዳይጎዱ ተነገራቸው። መጉዳት የነበረባቸው ግን በግንባራቸው ላይ የእግዚአብሔር ማህተም የሌለባቸውን ሰዎች ብቻ ነው። 5 እነርሱንም ቢሆን ለአምስት ወር ለማሰቃየት ብቻ እንጂ የመግደል ሥልጣን አልተሰጣቸውም። የእነርሱም ስቃይ ጊንጥ ሰውን ነድፎ እንደሚሰማው ስቃይ ዐይነት ነበር። 6 በእነዚያ ቀናት ሰዎች ሞትን ይፈልጋሉ፤ነገር ግን አያገኙትም። ለመሞት በብርቱ ይሻሉ፤ ነገር ግን ሞት ከእነርሱ ይሸሻል። 7 አንበጦቹ ለጦርነት እንደ ተዘጋጁ ፈረሶች ነበሩ። በራሳቸውም ላይ የወርቅ አክሊል የመሰለ ነገር ነበር፤ ፊታቸውም የሰው ፊት ይመስል ነበር። 8 የሴቶች ጠጕር የሚመስል ጠጕር ነበራቸው። ጥርሳቸው የአንበሳ ጥርስ ይመስል ነበር። 9 የብረት ጥሩር የሚመስልጥሩር ነበራቸው፤ የክንፎቻቸውም ድምፅ ወደ ጦርነት የሚጋልቡ ብዙ ፈረሶችና ሰረገሎች የሚያሰሙትን ድምፅ ይመስል ነበር። 10 እንደ ጊንጥ መንደፊያ ያለው ጅራት ነበራቸው። ሰዎችንም በጅራታቸው ባለ መንደፊያ ለአምስት ወር ለመጉዳት ስልጣን ነበራቸው። 11 በእነርሱም ላይ የጥልቁ ጕድጓድ መልአክ የሆነ ንጉሥ ነበራቸው። ስሙም በዕብራይስጥ አብዶን ሲሆን በግሪክ ደግሞ አጶሊዮን ይባላል፥ 12 የመጀመሪያው ወዮ አልፎአል፥ልብ በል! ከዚህ በኋላ ሌላ ሁለት ጥፋቶች ይመጣሉ። 13 ስድስተኛውም መልአክ መለከቱን ነፋ፥ በእግዚአብሔር ፊት ካለው በወርቅ ከተሰራው መሰዊያ ከቀንዶቹ ድምጽ ሲወጣ ሰማሁ። 14 ድምፁም መለከት የያዘውን ስድስተኛውን መልአክ፣ «በታላቁ ወንዝ በኤፍራጥስ የታሰሩትን አራቱን መላእክት ፍታቸው» አለው። 15 ለዚያ ሰዓትና ለዚያ ቀን ለዚያ ወርና ለዚያ ዓመት ተዘጋጅተው የነበሩት አራት መላእክት የሰዎችን አንድ ሦስተኛ እንዲገድሉ ተፈቱ። 16 የፈረሰኛው ሰራዊት ብዛት ሁለት መቶ ሚሊዮን ነበር።ቍጥራቸውንም ሰማሁ። 17 ፈረሶቹና በፈረሶቹ ላይ የሚጋልቡ በራእይ ያየኋቸው በዚህ ዐይነት ነበር፥ በደረታቸው ላይ የነበረው ጥሩር እንደ እሳት ቀይ፣ እንደ ያክንት (ጥቁር ሰማያዊ)፣ እንደ ዲንም ቢጫ ነበር፥ የፈረሶቹ ራስ የአንበሳ ራስ ይመስል ነበር። ከአፋቸው እሳትና ጢስ ዲንም ይወጣ ነበር። 18 በእነዚህ ሦስት መቅሰፍቶች ማለትም ከአፋቸው በወጣው እሳት፤ ጢስና ዲን የሰዎች አንድ ሦስተኛ ተገደለ። 19 የፈረሶቹ ኃይል በአፋቸውና በጅራታቸው ነበር፥ ምክንያቱም ጅራታቸው እባብ ይመስላል፥ ራስ አላቸው፥ ሰውን የሚጎዱትም በእርሱ ነበር። 20 በእነዚያ መቅሰፍቶች ከመሞት የተረፉት ሰዎች ከክፉ ሥራቸው ንስሓ አልገቡም፤ አጋንንትንና ከወር፣ ከብር፣ ከናስ፣ ከድንጋይና ከእንጨት የተሠሩ፣ ማየት ወይም መሄድ የማይችሉትን ጣዖታት ማምለክንም አልተዉም። 21 እንዲሁም ከነፍሰ ገዳይነት ወይም ከሟርት፥ ከሴስኛነትና፥ ከሌብነት ንስሓ አልገቡም።
ጉድጓድ በምድር ውስጥ ያለ ረጅም እና ጠባብ መንገድ ጥልቅ እና ማብቂያ ያሌለው አማራጭ ትርጉም: "መጨረሻ ያሌለው ጥልቅ" ትልቅ ጢስ ከእሳቱ ላይ የሚነሳ በጣም ረጅም ጢስ
አንበጣዎች መንጋ በብዛት የሚበሩ ነፍት የምድርም ጊንጦች ሥልጣን እንዳላቸው ሥልጣን ተሰጣቸው። ጊንጦች የመያዝ እና ሌሎች እንስሳትን በመርዝ የመበከል ኃይል አላቸው፡፡ ጊንጦች ንቦች መርዛቸው ከኋላ እንደሆነ ሁሉ እነዚህም መርዛማ መውጊያ ያላቸውን ትንንሽ እንስሳቶች ናቸው፡፡ ግንባር ከዐይን በላይ በፊት ላይ የሚገኝ፡፡
እነርሱ አንበጣቹ (REV 9:03) እነዚያ ሰዎች አንበጣዎቹ የሚነድፏቸው ሰዎች ሰዎች ነገር ግን መግረፍ ብቻ "ሰዎች፤ እነርሱ የተሰጣቸው ፈቃድ የመግረፍ ብቻ በው" ፍላጎት መሻት
አንበጣዎች አንበጣዎቹ የተገለጹት ሰዎች ከሚያውቋቸው ነገሮች ጋር በማነጻጸር ነው፡፡
ጥልቅ እና መጨረሻ ያሌለው ይህንን በ REV 9:1. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ አብዶን . . . አጶልዮን ሁለቱም “ጥፋት” የሚል ትርጉም አላቸው፡፡
በወርቅ ከተሠራ መሠዊያ ቀንዶች እነዚህ በመሰዊያው አናት ላይ በአራቱም ማዕዘኖች የሚገኙ የቀንድ ቅርጽ ያላቸው ነገሮች ናቸው፡፡
200,000,00 ይህንን በ REV 5:11. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
ጭራቸው እንደ እባብ ነው የፈረሶቹ ጭራ ከእባብ ጋር ተነጻጽሮ ቀርቧል፡፡ አማራጭ ትርጉሞች፡ 1) "ጭራቸው የእባብን ራስ ይመስላል"
በእነዚህም መቅሠፍቶች ያልተገደሉት የቀሩቱ ሰዎች "መቅጸፍቶቹ ያልገደሏቸው" ያዩ ወይም ይሰሙ ወይም ይሄዱ ዘንድ ለማይችሉ ጣኦታት፡፡ አማራጭ ትርጉሞች፡ "ሕያው ያልሆኑ ነገሮች"
1 ከዚህ በኋላ ሌላ ብርቱ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ። እርሱም ደመናን የለበሰ ነበር። በራሱም ዙሪያ ቀስተ ደመና ነበር። ፊቱ እንደ ፀሐይ እግሮቹ እንደ እሳት ዐምድ ነበሩ፤ 2 የተከፈተ ትንሽ ጥቅል መጽሐፍ በእጁ ይዞ ነበር፤ ቀኝ እግሩን በባህር ላይ ግራውንም በምድር ላይ አደረገ። 3 ከዚያም እንደሚያገሳ አንበሳ በመሰለ ታላቅ ድምጽ ጮኸ፤ በጮኸ ጊዜ፣ ሰባቱም ነጎድጓዶች ድምፃቸውን አሰሙ ፤ 4 ሰባቱ ነድጓዶች በተናገሩ ድምፃቸውን ባሰሙ ጊዜ፣ እኔ ልጽፍ አሰብሁ። ነገር ግን «ሰባቱ ነጎድጓዶች የተናገሩትን በምስጢር ያዘው እንጂ አትጻፈው» የሚል ድምጽ ከሰማይ ሰማሁ። 5 ከዚያም በባህርና በምድር ላይ ቆሞ ያየሁት መልአክ ቀኝ እጁን ወደ ሰማይ አነሣና 6 ዘላለም በሚኖረው ሰማይንና በእርሱ ያሉትን፣ ምድርንና በእርስዋ ያሉትን፣ ባህርንና በርስዋ ያሉትን በፈጠረው አምላክ ስም ማለ። እንዲህም አለ፤«ከእንግዲህ ወዲህ አይዘገይም 7 ነገር ግን ሰባተኛው መልአክ መለከቱን በሚነፋበት ቀን ለአገልጋዮቹ ለነቢያት በገለጠላቸው መሰረት የእግዚአብሔር ምስጢር ይፈጸማል።» 8 ከሰማይ የሰማሁት ድምጽ፣«በባህርና በምድር ላይ የቆመው መልአክ በእጁ የያዘውንና የተፈታውን ጥቅል መጽሐፍ ሂድና ውሰድ» ብሎ እንደገና ሲናገረኝ ሰማሁት»። 9 ወደ መልእኩም ሄጄ «ትንሹን ጥቅል መጽሐፍ ስጠኝ?» አልሁት። እርሱም «ውሰድና ብላ በሆድህም ውስጥ መራራ ይሆናል፤ በአፍህ ግን እንደ ማር ይጣፍጣል»አለኝ። 10 እኔም ትንሹን ጥቅል መጽሐፍ ከመልአኩ እጅ ወስጄ በላሁት፤ በአፌ እንደ ማር ጣፈጠ፤ ከበላሁት በኋላ ግን ሆዴ መራራ ሆነ። 11 ከዚህም በኋላ «ስለብዙ ሕዝቦች፤ አገራት፤ ልዩ ልዩ ቋንቋ ስለሚናገሩ ሰዎችና ሰለ ነገሥታት እንደ ገና ትንቢት መናገር አለብህ» ተብሎ ተነገረኝ።
ከዘላለምም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ሆኖ በሚኖረው በዚህ ሥፍራ ላይ “እርሱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ነው፡፡ በውስጡ ያሉትን ሁሉ ይህ ሦስት ጊዜ ያኸል ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን የሚመለክተውም በአየር፣ በባሕር ወይም በምድር ላይ የሚኖሩትን ሁሉንም እጽዋት፣ እንስሳት እና ሰዎችን ነው፡፡ ይፈጻማል "ይህ ልሆን ነው"
እኔ ይህ የሚያመለክተው ዮሐንስን ነው፡፡ መራራ የዚህ ነገር ትርጉሙ የመጽሐፉ መልእክት የሚያበሳጭ ወይም አስደሳች አይሆንም፡፡
1 ከዚያም ለመለኪያ የሚያገለግል አንድ ረዥም ዘንግ ተሰጠኝ፤እንዲህም ተባልሁ፣«ተነሥተህ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ፥ መሰዊያውንና በዚያ የሚያመለኩትንም ቍጠር። 2 ከቤተመቅደሱ ውጭ ያለውን አደባባይ ግን ተወው፤ እርሱ ለአሕዛብ የተሰጠ ስለ ሆነ አትለካው፥አሕዛብ ቅድስቲቱን ከተማ አርባ ሁለት ወራት ይረግጧታል። 3 ሁለቱ ምስክሮቼ ማቅ ለብሰው ለ1260 ቀን ትንቢት እንዲናገሩ ሥልጣን እሰጣቸዋለሁ።» 4 እነዚህም በምድር ጌታ ፊት የቆሙ ሁለቱ የወይራ ዛፎችና ሁለቱ መቅረዞች ናቸው፤ 5 ማንም እነርሱን ሊጎዳ ቢፈልግ እሳት ከአፋቸው ወጥቶ ጠላቶቻቸውን ይበላል፤ እነርሱን ሊጎዳ የሚፈልግ ሁሉ የሚሞተው በዚህ ዐይነት ነው፥ 6 እነዚህ ምስክሮች ትንቢት በሚናገሩባቸው ቀናት ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማይን ለመዝጋት ሥልጣን አላቸው፥ እንዲሁም ውሆችን ወደ ደም ለመለወጥና በሚፈልጉበትም ጊዜ ሁሉ በማንኛውም ዓይነት መቅሰፍት ምድርን ለመምታት ሥልጣን አላቸው፡ 7 ምስክርነታቸውን በጨረሱ ጊዜ ከጥልቁ ጉድጛድ የሚወጣው አውሬ ከእነርሱ ጋር ይዋጋል፤ ያሸንፋቸዋል ይገድላቸውማል። 8 ሬሳቸውም በምሳሌያዊ አጠራር ሰዶም ወይም ግብጽ ተብላ በምትጠራው በታላቂቱ ከተማ አደባባይ ይጋደማል፤ ከተማይቱም የእነርሱ ጌታ የተሰቀለባት ናት፤ 9 ከልዩ ልዩ ወገን፥ ነገድ፥ ከልዩ ልዩ ቋንቋና ሕዝብ የሆኑ ሰዎች ሶስት ቀን ተኩል ሬሳቸውን ይመለከታሉ፥ ሬሳቸውም እንዳይቀበር ይከለክላሉ። 10 ሁለቱ ነቢያት የምድርን ሰዎች ሁሉ አስጨንቀው ስለ ነበር፣ በእነርሱ ሞት በምድር የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ ደስ ይላቸዋል፤ በደስታም በዓል ያደርጋሉ፤ ስጦታም ይለዋወጣሉ። 11 ነገር ግን ሦስት ቀን ተኩል ካለፈ በኋላ፣ የሕይወት እስትንፋስ ከእግዚአብሔር መጥቶ ወደ ሬሳዎቹ ይገባል፤ በእግራቸውም ይቆማሉ፤ የሚመለከቷቸውም ሰዎች ታላቅ ፍርሃት ይወድቅባቸዋል። 12 ከዚህ በኋላ ሁለቱ ነቢያት፣ «ወደዚህ ውጡ» የሚል ታላቅ ድምጽ ከሰማይ ሰሙ፤ ጠላቶቻቸውም እየተመለከቷቸው በደመና ወደ ሰማይ ወጡ። 13 በዚያኑ ሰዓት ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፤ የከተማይቱም አንድ ዐሥረኛ ወደመ። በምድር መናወጥም ምክንያት ሰባት ሺህ ሰዎች ሞቱ፤ ከሞት የተረፉትም እጅግ ፈሩ፤ለሰማይም አምላክ ክብርን ሰጡ። 14 ሁለተኛው ወዮ አልፎአል፤ልብ በል! ሦስተኛው ወዮ ፈጥኖ ይመጣል። 15 ሰባተኛውም መልአክ መለከቱን ነፋ፤በሰማይም«የዓለም መንግሥት የጌታ አምላካችንና የእርሱ ክርስቶስ ሆናለች፤ እርሱም ለዘላለም ይነግሣል» የሚል ታላቅ ድምጽ ሰማሁ። 16 በእግዚአብሔርም ፊት በዙፋኖቻቸው ላይ የተቀመጡት ሃያ አራቱም ሽማግሌዎች በግምባራቸው ተደፍተው ለእግዚአብሔር ሰገዱ፤ 17 እነርሱም እንዲህ አሉ፣«ያለህና የነበርህ፣ ሁሉን የምትችል፣ ጌታ እግዚአብሔር ሆይ ትልቁን ሥልጣንህን በእጅህ አድርገህ ስለ ነገሥህ እናመሰግንሃለን። 18 አሕዛብ ተቆጡ፤ ነገር ግን የአንተም ቁጣ መጣ ።በሙታን ላይ የምትፈርድበት ዘመንም መጣ፤ለአገልጋዮችህ፣ ለነቢያት፣ ለቅዱሳን፣ ስምህንም ለሚያከብሩት ለታናናሾችና ለታላላቆች ሽልማታቸውን የምትሰጥበት ጊዜ እንዲሁም ምድርን ያጠፏትን የምታጠፋበት ጊዜ ደረሰ።» 19 በሰማይም ያለው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ተከፈተ፤የእርሱም የቃል ኪዳን ታቦት በቤተ መቅደሱ ውስጥ ታየ። መብረቅ የመብረቅ ድምጽ፣ነጎድጓድም፣የምድር መናወጥና ታላቅም ማዕበል ሆነ።
ለእኔ ተሰጠኝ . . . ተነገረኝ በዚህ ሥፍራ ላይ “እኔ” እና “ለእኔ” ዮሐንስን የሚያመልክት ነው፡፡ መርገጥ አንድ ነገር የማይጠቅም መሆኑን ለማሳየት በእርሱ ላይ መረማመድ፡፡ አርባ-ሁለት ወራት ሁለት ወራት - አማራጭ ትርጉም: "42 ወራት"
እነዚህ ሁለት ምስክሮች ሁለቱ የወይራ ዛፎች እና ሁለቱ መቅረዞች ናቸው እነዚህ ሁለት ምስክሮች ከዚህ በፊት የተጠቀሱት ሁለቱ የወይራ ዛፎች እና ሁለቱ መቅረዞቸ ናቸው፡፡
ምድርን በሁሉም ዓይነት መቅሰፍቶች መምታት ይህ በምድር ላይ ሁሉንም ዓይነት አስቸጋሪ ነገሮችን እንዲከሰት የሚያድርጉትን ያመለክታል፡፡ ጥልቅ እና ማለቂያ ያሌለው “ማለቂያ ያሌለው” የሚለው ቃል ትርጉሙ መጨረሻ ያሌለው ማለት ነው፡፡ እነዚህ ሁለት ቃላት የትልቀቱን መጠን ለማሳየት ጥቅም ላይ የዋሉ ናቸው፡፡
ሦስት ከግማሽ ቀናት "3 ሙሉ ቀናት እና አንድ ግማሽ ቀን: ወይም"3.5 ቀናት" ወይም "3 1/2 ቀናት"
ሦስት ከግማሽ ቀናት "3 ሙሉ ቀናት እና አንድ ግማሽ ቀን: ወይም"3.5 ቀናት" ወይም "3 1/2 ቀናት"
ሰበባት ሺኅ ሰዎች "7,000 ሰዎች"
ሃያ - አራት ሽማግሌዎች አራት ሽማግሌዎች - "24 ሽማግሌዎች"
በግምባራቸው ተደፍተው የሰውነታቸው የፊት ክፍል “ፌታቸው” ተብሎ ይገለጻል፡፡
ቁጣህ . . . አገልጋዮችህ . . . ስምህ “አንተ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ነው፡፡ የማያስፈልግ "ዝቅተኛ" ወይም "ዝቅ ያለ" ወይም "በዝቅተኛ ሥፍራ ላይ ያለ"
1 በሰማይም ታላቅ ምልክት ታየ ፤ ፀሐይን የለበሰችና ጨረቃን ከእግሯ በታች ያደረገች፣ ዐሥራ ሁለት ከዋክብት ያሉት አክሊልም በራስዋ ላይ የደፋች አንዲት ሴት ታየች። 2 እርስዋም ነፍሰ ጡር ነበረች፤ ምጥ ይዟትም ተጨንቃ ትጮህ ነበር፥ 3 እንዲሁም ሌላ ምልክት በሰማይ ታየ፤እነሆ፤ሰባት ራሶችና ዐሥር ቀንዶች የነበሩት፤በራሶቹም ላይ ሰባት አክሊል የደፋ ትልቅ ቀይ ዘንዶ ታየ። 4 በጅራቱ የኮከቦችን አንድ ሦስተኛ ከሰማይ ስቦ ወደ ምድር ጣለ፤ዘንዶውም ሴቲቱ በምትወልድበት ጊዜ ልጅዋን ለመዋጥ አስቦ ልትወልድ ወደ ተቃረበችው ሴት ፊት ቆመ። 5 ሴቲቱም ሕዝቦችን ሁሉ በብረት በትር የሚገዛ ወንድ ልጅ ወለደች። ልጅዋ ግን ወደ እግዚአብሔርና ወደ እግዚአብሔር ዙፋን ተወሰደ፤ 6 ሴቲቱም ወደ ምድረበዳ ሸሽታ ሄደች፤ በዚያም እግዚአብሔር ለ1260 ቀን በክብካቤ ተይዛ እንድትጠበቅ አደረጋት። 7 በሰማይም ጦርነት ሆነ። ሚካኤልና መላእክቱ ከዘንዶው ጋር ተዋጉ፤ዘንዶውና መላእክቱ መልሰው ተዋጓቸው። 8 ነገር ግን ዘንዶው የማሸነፍ ዐቅም አልነበረውም፤ከዚያም ወዲያ እርሱና መላእክቱ በሰማይ የነበራቸውን ስፍራ አጡ። 9 ታላቁም ዘንዶ ወደ ምድር ተጣለ፤ እርሱም ሰዎችን ሁሉ የሚያስተው ዲያቢሎስ ወይም ሰይጣን ተብሎ የሚጠራው የቀደመው እባብ ነው።እርሱ ወደ ምድር ተጣለ፤ የእርሱም መላእክት ከእርሱ ጋር አብረው ተጣሉ። 10 ከዚህ በኋላ ታላቅ ድምፅ ከሰማይ እንዲህ ሲል ሰማሁ፤«አሁን ማዳንና ኃይል መንግሥትም የአምላካችን ሆኖአል፤ሥልጣንም የእርሱ ክርስቶስ ሆኖአል።ምክንያቱም ወንድሞቻችንን በአምላካችን ፊት ቀንና ለሊት ሲከሳቸው የነበረ የወንድሞቻችን ከሳሽ ተጥሎአል። 11 እነርሱም በበጉ ደምና በተናገሩት የምስክርነት ቃል ድል ነሡት፤ ለሕይወታቸው ሳይሳሱ ራሳቸውን ለሞት አሳልፈው ሰጥተዋልና። 12 ስለዚህ ሰማይና በውስጣቸው የምትኖሩ ሁሉ ደስ ይበላችሁ፤ ምድርና ባህር ግን ወዮላችሁ፤ ምክንያቱም ጥቂት ጊዜ እንደ ቀረው ዐውቆ ዲያቢሎስ በታላቅ ቍጣ ወደ እናንተ ወርዷል። 13 ዘንዶው ወደ ምድር እንደተጣለ ባስተዋለ ጊዜ፤ ወንድ ልጅ የወለደችውን ሴት አሳደዳት፤ 14 ሴቲቱ ከእባቡ ፊት ርቃ ለዘመን፣ ለዘመናትና ለዘመንም እኩሌታ በክብካቤ ተጠብቃ ወደ ምትኖርበት በምድረ በዳ ወደ ተዘጋጀላት ስፍራ በርራ እንድትሄድ ሁለት የታላቅ ንስር ክንፎች ተሰጧት። 15 እባቡ የወንዝ ውሃ የሚያህል ውሃ ከአፉ ተፍቶ ሴቲቱ በጎርፍ እንድትወሰድ ብሎ በስተ ኋላዋ አፈሰሰ። 16 ነገር ግን ምድር አፍዋን ከፍታ ዘንዶው በአፉ ያፈሰሰውን ወንዝ በመዋጥ ረዳቻት። 17 ከዚያም ዘንዶው በሴቲቱ ላይ ተቆጥቶ ከትሩፋን ዝርያዎችዋ ጋር ሊዋጋ ሄደ። እነርሱም የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁና ስለ ኢየሱስ በታማኝነት የሚመሰክሩት ናቸው። 18 ዘንዶውም በባህር ዳር ባለው አሸዋ ላይ ቆመ።
በሰማይ ታላቅ ምልክት ታየ አማራጭ ትርጉም: "በሰማይ ታላቅ ምልክት ታየ" ወይም "እኔ፣ ዮሐንስ በሰማይ ታላቅ ምልክትን አየሁ" ፀሐይን የተጎናፀፈች አንድት ሴት አየሁ አማራጭ ትርጉም: "ፀሐይን የለበሰች ሴት" ዐሥራ ሁለት ክዋክብት "12 ክዋክብት"
ዘንዶ ትልቅ፣ እንሽላልት የሚመስል አደገኛ ተሳቢ እንስሳ፡፡ ይህ ለአይሁዳዊያን የክፋት እና የተዘበራረቀ ነገር ምልከክት ነው፡፡
ልጇ ወደ እግዚአብሔር ተነጠቀ አማራጭ ትርጉም: "እግዚብሔር ልጇን ወደ ራሱ ወሰደው፡፡"
ዘንዶ ይህንን በ REV 12:3. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ በቁጥር 9 ላይ ዘንዶው “ዳቢሎስ ወይም ሴጣን” ተብሎ ተጠርቷል፡፡ ታላቁ ዘንዶ እና የእርሱ መላእክት. . . ወደ ምድር ተጣሉ አማራጭ ትርጉም: እግዚአብሔር ታላቁ ዘንዶን እና የእርሱን መላእክት ከሰማይ ወደ ምድር ጣላቸው፡፡
እኔ ይህ ዮሕንስን ያመለክታል፡፡ ቀን እና ማታ “ቀን እና ማታ” የሚሉት ቃላት ሁል ጊዜ ተጣምረው ጥቅም ላይ ውለዋል፤ እርሱም ሁል ጊዜ ወንድሞችን ይከሳቸዋል፡፡
ዘንዶው ወደ ምድር መጣሉን አውቆ አማራጭ ትርጉም: "ዘንዶው እግዚአብሔር ከሰማይ ወደ ምድር እንደጣለው አውቆ" ዘንዶው ይህንን በ REV 12:3. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
እባብ በ REV 12:9. መሠረት ይህ ከዘንዶው ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ እንደ ወንዝ አማራጭ ትርጉም: "በብዛት" ዘንዶ ይህንን በ REV 12:3. ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ምድሪቱም አፍዋን ከፍታ ዘንዶው ከአፉ ያፈሰሰውን ወንዝ ዋጠችው። አማራጭ ትርጉም: "በምድር ላይ ያለው ቀዳዳ ተከፍቶ ውሃ ወደ ቀዳዳው ውስጥ ፈሰሰ፡፡"
1 ከዚያም አንድ አውሬ ከባህር ሲወጣ አየሁ። እርሱም ዐስር ቀንዶችና ሰባት ራሶች ነበሩት። በቀንዶቹም ላይ አስር አክሊሎች ነበሩ፤ በራሶቹም ላይ እግዚአብሔርን የሚሰድብ ስሞች ነበሩት። 2 ያየሁትም አውሬ ነብር ይመስል ነበር፤ እግሮቹ የድብ እግሮች፤ አፉ የአንበሳ አፍ ይመስል ነበር። ይገዛም ዘንድ ዘንዶው የራሱን ኅይልና የራሱን ዙፋን ትልቅም ስልጣን ለአውሬው ሰጠው። 3 ከአውሬው ራሶቹ አንዱ ለሞት የሚያበቃ ቁስል እንደነበረው ሆኖ አየሁት፤ ነገር ግን ለሞት የሚያደርስው ቁስል ዳነ፤በዚህም ምክንያት ዓለም በሙሉ በመደነቅ አውሬውን ተከተለ። 4 አውሬውም ስልጣኑን በመስጠቱ ሁሉም ለዘንዶው ሰገዱለት «አውሬውን ማን ይመስለዋል? ከእርሱስ ጋር ማን ሊዋጋ ይችላል?» እያሉ ለአውሬው ሰገዱለት። 5 አውሬውም የትዕቢትና የስድብ ቃል የሚናገርበት አፍ ተሰጠው፤ ለአርባ ሁለት ወራትም ስልጣኑን እንዲያሳይ ተፈቀደለት። 6 አውሬው አፉን ከፍቶ እግዚአብሔርን፤ የእግዚአብሔርን ስም፤ መኖሪያውንና በሰማይ የሚኖሩትን መሳደብ ጀምረ። 7 አውሬው ቅዱሳንን እንዲዋጋ ና፤ ድል እንዲነሳቸውም ስልጣን ተሰጠው። በነገድና በወገን በቃንቃና በህዝብ ሁሉ ላይ ስልጣን ተስጠው። 8 ዓለም ሲፈጠር ጀምሮ ስሞቻቸው በታረደው በግ የህይወት መጽሀፍ ያልተጻፈ በዓለም ላይ የሚኖሩ ሰዎች ሁ ሉ ለአውሬው ይሰግዳሉ። 9 የሚሰማ ጆሮ ያለው ቢኖር ይስማ። 10 «የሚማረክ ማንም ቢኖር ወደ ምርኮ ይሄዳል፤ በሰይፍ የሚገደል ማንም ቢኖር በሰይፍ ይገደላል» እንግዲህ የቅዱሳን ትዕግስትና እምነት የሚታየው በዚህ ጊዜ ነው። 11 ከዚህም በኃላ ሌላ አውሬ ደግሞ ከምድር ሲውጣ አየሁ፤ የበግ ቀንዶች የሚመስሉ ሁለት ቀንዶች ነበሩት አነጋግሩም እንደ ዘንዶው ነበር። 12 የመጀመሪያውን አውሬ ስልጣን ሁሉ በመጀመሪያው አውሬ ፊት ሆኖ ይሰራበት ነበር፤ ምድርና በእርስዋ ላይ የሚኖሩት ሁሉ ለአውሬው እንዲሰግዱለት ያደርጋል፤ ይህም አውሬ ያ ለሞት የሚያድርስ ቁስል የዳነለት የመጀመሪያው አውሬ ነው። 13 እርሱም በሰዎች ፊት እሳትን ከሰማይ እስከማውረድ ድረስ ታላላቅ ምልክቶችን ያደርግ ነበር፤ 14 እንዲያደርግ በተፈቀደለት ተዓምራት በሰይፍ ቁስሎ የዳነውን የአውሬውን ምስል እንዲሰሩ በማዘዝ በምድር ላይ የሚኖሩትን ሰዎች ያስት ነበር። 15 እርሱም ምስሉ መናገር እንካ እስከሚችል ድረስ እስትንፋስ ለመስጠትና ለአውሬው የማይስግዱትን መግደል ይችል ዘንድ ለማድረግ ስልጣን ተሰጠው። 16 እርሱም ታናናሾችም ሆኑ ታላላቆች፤ ሀብታሞችም ሆኑ ድኾች ጌቶችም ሆኑ አገልጋዮች ሁሉም በቀኝ እጃቸው ወይም በግምባራቸው ላይ ምልክት እንዲያደርጉ አስገደዳቸው። 17 የአውሬው ስም የሆነው ምልክት ወይም የስሙ ቁጥር የሌለው ማንም ሰው መግዛትም ሆን መሸጥ አይችልም ነበር። 18 ይህ ጥበብን የሚጠይቅ ነው።የሚያስተውል የአውሬውን ቁጥር ያስላው፤ ቁጥሩም የሰው ቁጥር ነው፤ የውሬውም ቁጥር 666 ነው፤
ከዚያም ይህንን አየሁ በዚህ ሥፍራ ላይ “እኔ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ዮሕንስ ነው፡፡ ዘንዶ ይህንን በ REV 12:3. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
ይሁን እንጂ ያ ቁስል ተፈወሰ አማራጭ ትርጉም: "ይሁን እንጂ ቁልስሉ ተፈወሰ" አውሬውን ተከተሉ "ለአውሬው ታዘዙ" ዘንዶ ይህንን በ REV 12:3. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ እርሱን ተቃውሞ ማን መዋጋት ይችላል? አማራጭ ትርጉም: "አውሬንን ተቃውሞ ማንም ልዋጋ እና ልሸንፍ አይችልም!"
ለአውሬው ተሰጠው . . . ተፈቀደለት "እግዚአብሔር ለአውሬው ሰጠው . . . እግዚብሔር ለአውሬው ፈቀደለት" አርባ -ሁለት ወራት ሁለት ወራት - "42 ወራት"
ስሙን እየተሳደበ "የእግዚአብሔርን ስም ወይም ባሕርይ እየተሳደበ"
ስልጣን ለእርሱ ተሰጠው አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር ለአውሬው ስልጣን ሰጠው" ስሙ ያልተጻፈ ማንኛውም ሰው ሁሉ አማራጭ ትርጉም: "በጉ ስማቸውን ያልጻፋቸው ሰዎች ሁሉ" ወይም "ኢየሱስ ስማቸውን ያልጻፋቸው ሁሉ" በግ ይህ ኢየሱስን የሚያመለክት ነው፡፡ ይህንን በ REV 5:6. ላይ ምን ብለህ እደተረጎምከው ተመልከት፡፡ የታረደው አማራጭ ትርጉም: "ሰዎች ያረዱት"
ጆሮ ያለው ይስማ ይህ ማለት የመስማት ችሎታ ያለው እና የእግዚአብሔርን መልዕክት መረዳት የሚችል ማለት ነው፡፡
ዘንዶው ይህንን በ REV 12:3. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ እና ምድርን እና በውስጧ የሚኖሩትን ሁሉ የፈጠረውን "እና በምድር ላይ ያሉትን ሁሉ የፈጠረውን" ለሞት የሚያበቃ ቁስል ያለበት ተፈወሰ አማራጭ ትርጉም: "ለሞት የሚያበቃ ቁስል ያለበት ተፈወሰ"
ያድርጋል "በምድር ካይ ያለው አውሬ ይህንን ያደርጋል" በሰይፍ ቆስሎ የነበረው አማራጭ ትርጉም: "የሆነ ሰው በሰይፍ ያቆሰለው"
ተፈቅዶለት ነበር አማራጭ ትርጉም: "እግዚአበብሔር ለአውሬው በምድር ላይ ፈቅዶለት ነበር" ለአውሬው ምስል ትንፋሽ እንዲሰጠው ተሰጠው። አማራጭ ትርጉም: "ለአውሬው ምስል ሕይወት ለመስጠት" ለአውሬው ምስል ለመስገድ ፈቃደኛ ያልሆኑት ሰዎች ሁሉ እንዲገደሉ አማራጭ ትርጉም፡ "አውሬውን ለማምለከት ፈቃደኛ ያልሆነ ማንኛውም ሰው እንዲገደል"
የሰው ልጅ ቁጥር ነው አማራጭ ትርጉሞች 1) ቁጥሩ የሚያመለክተው አንድን ሰው ነው ወይም 2) ቁጥሩ ሁሉንም የሰው ልጆች ይወክላል፡፡ 666 "ስድስት ስልሳ ስድት"
1 አየሁም እነሆ በጉ በጽዮን ተራራ በፊቴ ቆሞ ነበር። ከእርሱ ጋር የእርሱ ስምና የአባቱ ስም በግንባራቸው ላይ የተጻፈባቸው አንድ መቶ አርባ አራት ሺህ ነበሩ። 2 በሰማይ እንደ ብዙ ውኃ ድምጽና ና እንደታላቅ ነጎድጋድ ድምጽ የመሰለ ድምጽ ሰማሁ፤ የሰማሁትም ድምጽ በገና ደርዳሪዎች በገና እየደረደሩ የሚያሰሙትን ድምጽ ይመስል ነበር። 3 እነርሱም በዙፋኑና በአራቱ እንስሶች በሽማግሌዎችም ፊት አዲስ መዝሙር ዘመሩ። ይህንም መዝሙር ከምድር ከተዋጁት ከአንድ መቶ አርባ አራት ሺህ በቀር ማንም ሊማረው አልቻለም። 4 እነርሱም ራሳቸውን ከሴቶች ጋር ካላረከሱት ናቸው፤ ራሳቸውንም በግብረ ስጋ ግንኙነት ካለማርከስ ጠብቀዋል። እነርሱ ናቸው በጉ ወደሚሄድበት ሁሉ የሚከተሉት እነዚህ ናቸው፤ እነርሱ ለእግዚአብሔርና ለበጉ በኩራት ለመሆን ከሰዎች መካከል የተዋጁ ናቸው። 5 በአንደበታቸውም ሀሰት ተናግረው አያውቁም። ነቀፋም የሌለባቸው ናቸው። 6 በምድር ላይ ለሚኖሩ ለህዝብ፤ ለነገድ፤ ለቃንቃና ለወገን ሁሉ ለማብሰር ዘላለማዊውን የምስራች ቃል የያዘ ሌላ መልዓክ በሰማይ መካከል ሲበር አየሁ 7 እርሱም በታላቅ ድምጽ «እግዚአብሄርን ፍሩ፤ አክብሩትም። ምክንያቱም የእርሱ የፍርድ ሰዓት ደርሳል፤ ሰማይን፤ ምድርን፤ ባህርንና የውሃ ምንጮችን የፈጠረን አምላክ አምልኩ» አለ 8 ሌላም ሁለተኛ መልአክ «የዝሙትዋ ፍትወት የሆነውን የሚያሰክር የወይን ጠጅ ለህዝቦች ሁሉ ያጠጣች ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች፤ ወደቀች» እያለ የመጀመሪያውን መልዓክ ተከተለው 9 ሌላ ሶስተኛ መለዓክ በታላቅ ድምጽ እንዲህ እያለ ተከተላቸው «ለአውሬውና ለምስሉ ቢሰግዱ ምልክቱን በግምባሩ ወይም በእጁ ቢያደርግ፤ 10 የእግዚአብሔርን የቁጣ የወይን ጠጅ ይጠጣል፤ ይህም የወይን ጠጅ ሳይበረዝ በቁጣው ጽዋ የተዘጋጀ ነው፤ ፅሚጠጣውም ሰው በቅዱሳን መላዕክት ፊትና በበጉ ፊት በእሳትና በዲን ይሰቃያል፤ 11 የስቃያቸውም ጢስ ከዘላለም እስከ ዘላለም ወደ ላይ ይወጣል፤ ለአውሬውና ለምስሉ የሚሰግዱ የስሙንም ምልክት ያደረጉ ሁሉ ቀንና ለሊት ዕረፍት የላቸውም። 12 የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ የሚጠብቁና በኢየሱስ የሚያምኑማመኑ ቅዱሳን፤ ትዕግስታቸው የሚታየው እዚህ ላይ ነው። 13 ከሰማይም እንዲህ የሚል ድምጽ ሰማሁ «ይህን ጻፍ ከእንግዲህ ወዲህ በጌታ ሆነው የሚሞቱ የተባረኩ ናቸው» መንፈስም አዎ ስራቸው ስለሚከተላቸው ከድካማቸው ያርፋሉ» ይላል 14 አየሁም እነሆ ነጭ ደመና ነበር በደመናውም ላይ የሰውን ልጅ የሚመስል ተቀምጦ ነበር። በራሱም ላይ የወርቅ አክሊል አድርጎአል፤ በእጁም ስለታም ማጭድ ይዞአል። 15 ከዚህም በኃላ ሌላ መልአክ ከመቅደሱ ወጣ በደመና ላይ የተቀመጠውን በታላቅ ድምጽ «የምድር መከር ደርሶአል የአጨዳ ሰዓትም ቀርቦአል፤ ስለዚህ ማጭድህን ስደድ» አለው። 16 በደመናው ላይ የተቀመጠውም ማጭዱን ወደ ምድር ሰደደው ምድርም ታጨደች። 17 ሌላ መልዓክ ከሰማይ ባለው መቅደስ ወጣ፤ እርሱም ስለታም ማጭድ ይዞ ነበር። 18 በእሳትም ላይ ስልጣን ያለው ሌላ መልዓክ ከመሰዊያው አጠገብ ወጣና ስለታም ማጭድ የያዘውን መልዓክ በታላቅ ድምጽ «የዘለላዎቹ ፍሬዎች ስለበሰሉ የወይን ዘለላዎችን ሁሉ ከምድር ወይን ቁረጥ» አለው። 19 መልዓኩም ማጭዱን ወደ ምድር ሰደደው፤ የምድርንም ወይን ዘለላ ቆረጠ፤ ወደ ታላቁ ወደ እግዚአብሔር የቁጣ ወይን መጭመቂያ ውስጥ ጣለው። 20 ከከተማው ውጭ ባለው በወይን መጥመቂያም ተጨመቀ ከመጭመቂያውም እስከ ፈረስ ልጋም ወደ ላይ ከፍ ያለና 300 ኪሎ ሜትር የሚደርስ ደም ወጥቶ ፈሰሰ።
ተመለከትኩ በዚህ ሥፍራ ላይ “እኔ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ዮሐንስ ነው፡፡ በግ ይህ ኢየሱስን የሚያመለክት ነው፡፡ ይህንን በ REV 5:6. ላይ ምን ብለህ አንንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ 144,000 ይህንን በ REV 7:4.ላይ ምን ብለህ አንንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ስሙና የአባቱ ስም በግምባራቸው የተጻፈላቸው አማራጭ ትርጉም: "በግንባራቸው ላይ የበጉ እና የአባቱ ስም የጻፉ ሰዎች፡፡"
ዘመሩ "144,000ዎቹ ዘመሩ" ከሴትቱ ጋር ራሳቸውን ያላረከሱት እነዚህ ናቸው አማራጭ ትርጉም: "144,000ዎቹ ድንግል በግብረገብ ንጹሕ እንደሆነች በመንፈሳዊነት ንጹሕ የሆኑት ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህ የሐሰት አማልክትን በማምለክ ራሳቸውን አላረከሱም፡፡
ወደቀች፣ ወደቀች ይህ ቃል የተደጋገመው አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ ወደቀች . . . በራሷም ላይ ከፍተኛ ቁጣን አመጣች "በጣም ክፉ ከተማዎች
የእግዚአብሔርን ቁጣ ወይን ይጠጣሉ በዚህ ሥፍራ ላይ “ወይን መጠጣት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የእግዚአብሔርን ቁጣን መቀበልን ነው፡፡ የተዘጋጀውን አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር ያዘጋጀውን" የቁጣው ጽዋ ጽዋው በወይን የተሞላ ሲሆን ይህም የእግዚአብሔርን ቁጣ ይወክላል፡፡ ሳይቀላቀል መቀዳት ይህ በውሃ ያልተቀላቀለ ወይንን ያመለክታል፡፡ ይህ ማለት የእግዚአብሔር ቁጣ ሙሉ ለሙሉ እንደሚመጣባቸው ያሳያል፡፡ የእርሱ ቅዱስ መላእክት "የእግዚአብሔር ቅዱስ መላእክት"
ከሥቃያቸው "ከቀጣይ ሕመማቸው"
ሥራቸው ይከተላቸዋል አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር ስለሥራቸው ይሸልማቸዋልና"
የሰው ልጅ የሚመስለው ይህንን በ REV 1:13. ላይ ምን ብለህ እደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ማጭድህን አንሳ . . . ምድርም ታጨደች ይህ ምሳሌያዊ ንግግር በምድር ላይ ባሉት ሰዎች ሁሉ ላይ ያለውን የእግዚአብሔርን ፍርድ ያመለክታል፡፡ ማጭድ ሣር እና ወይን ለማጨድ ጥቅም ላይ የሚለው የተቆለመመ እና ስለታም ብረትን ያመለክታል፡፡ ከቤተ መቅዱስ ወጣ "ከሰማያዊው መቅደስ ወጣ" ምድር ታጨደች "ምድር አጨደ"
ታላቁ የወይን መጭመቂያ . . . ይህ ተመሳሳይ መያዥያ ዕቃን ያመለክታል፡፡ ልጓም በፈረስ ጭንቅላት ላይ የሚታሠር እና የፈረስን አቅጣጫ ለመምራት የሚገለግል ዕቃ 1,600 ምዕራፍ አንድ ምዕራፍ 185 ሜትሮች ነው፡፡
1 ከዚህም በኃላ ታላቅና ድንቅ ምልክት በሰማይ አየሁ፤ የእግዚአብሔር ቁጣ የሚፈጽምባቸው የመጨረሻዎቹን ሰባት መቅሰፍት የያዙትን ሰባት መላዕክት አየሁ 2 እኔም እሳት የተቀላቀለበት የሚመስል የመስተዋት ባህር አየሁ፤ አውሬውንና የአውሬውን ምስል የስሙንም ቁጥር ድል የነሱትን በባህሩ አጥገብ ቆመው ነበር። እግዚአብሔር የሰጣቸውንም በገና ይዘው ነበር። 3 እነርሱም የእግዚአብሔር አገልጋይ የሙሴን መዝሙርና የበጉን መዝሙር እንዲህ እያሉ ይዘምሩ ነበር «ሁሉን የምትችል ጌታ አምላክ ሆይ ስራህ ታላቅና አስደናቂ ነው። የእዝቦች ንጉስ ሆይ መንገድህ ትክክልና እውነት ነው። 4 ጌታ ሆይ አንተን የማይፈራና ስምህንም የማያከብር ማን ነው? ምክንያቱም አንተ ብቻ ቅዱስ ነህ የጽድቅ ስራህ ስለተገለጠ ሕዝቦች ሁሉ መጥተው በፊትህ ይሰግዳሉ።» 5 ከዚህም በኃላ አየሁ እነሆ የምስክር ድንካን የሆንው ቅድስተ ቅዱሳን በሰማይ ተከፈተ። 6 ከቅድስተ ቅዱሳንም ሰባቱን መቅሰፍቶች የያዙት ሰባት መላዕክት ወጡ፤ የሚያንጸባርቅ ነጭ ልብስ ለብሰው ነበር። ደረታቸውንም በወርቅ መታጥቂያ ታጥቀው ነበር። 7 ከአራቱ ህያዋን ፍጡራን አንዱ ከዘላለም እስከ ዘላለም በሚኖረው አምላክ ቁጣ የተሞሉትን ሰባት የውርቅ ጽዋዎች ለሰባቱ መላዕክት ሰጣቸው። 8 ቅድስተ ቅዱሳኑም ከእግዚአብሔር ክብርና ኃይል የተነሳ በጢስ ተሞላ፤ ሰባቱ መላዕክት የያዙእቸው ስባት መቅሰፍቶች እስኪፈጽሙ ድረስ ማንም ወደ ቅዱሰተ ቅዱሳኑ መገባት አልቻሉም።
ከዚያም አየሁ...ተፈጸመ በዚህ ሥፍራ ላይ ያለው 15:1 ከ15፡2-16፡21 ድረስ ያለው ማጠቃለያ ነው፡፡ ትልቅ እና አስገራሚ አማራጭ ትርጉም: "በጣም ያስገረመኝ ነገር" ከእነርሱ ጋር የእግዚአብሔር ቁጣ ተፈጸመ አማራጭ ትርጉም: "እነዚህ መቅሰፍቶች የእግዚአብሔርን ቁጣ ፈጸሙ፡፡"
ቁጥሩ የሚያመለክተው ስሙን ነው ይህ በ REV 13:18. ላይ የተጠቀሰውን ቁጥር እንደሚመለክት አንባቢያኑ ልገነዘቡ ይገባል፡፡
የጽድቅ ተግባርህ ታወቀ አማራጭ ትርጉም: "ሁሉም ሰው ያደረከውን የጽድቅ ሥራ ተመለከተ እንዲሁም ተገነዘበ፡፡"
ከእነዚህ ነገሮች በኋላ "ሰዎች መዘመራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ" ከተልባ እግር የተሠራ ልብስ ከላይ የሚለበስ የተብለጨለጨ ልብስ
አራት ሕያዊያን ፍጥረታት ይህንን በ REV 4:6. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምካቸው ተመልከት፡፡
1 ሰባቱን መላእክት፣ “ሂዱና ሰባቱን የእግዚአብሔርን ቁጣ ጽዋዎች ምድር ላይ አፍስሱ” የሚል ታላቅ ድምፅ ከመቅደሱ ሲወጣ ሰማሁ። 2 የመጀመሪያው መልአክ ጽዋውን ምድር ላይ አፈሰሰ፤ የአውሬው ምልክት ባላቸውና ለምስሉ በሰገዱት አስከፊና የሚያሠቃይ ቁስል ወጣባቸው። 3 ሁለተኛው መልአክ ጽዋውን ባሕር ላይ አፈሰሰ፤ ባሕሩ እንደ ሞተ ሰው ደም ሆነ፤ ባሕር ውስጥ የነበረ ሕያው ፍጡር ሁሉ ሞተ። 4 ሦስተኛው መልአክ ጽዋውን ወንዞችና የውሃ ምንጮች ላይ አፈሰሰ እነርሱም ደም ሆኑ። 5 የውሃውም መልአክ፣ “ያለህና የነበርህ ቅዱስ ጌታ እንዲህ ስለ ፈረድህ ትክክል ነህ፣ 6 ምክንያቱም የቅዱሳንህና የነበያትን ደም ስላፈሰሱ፣ ደም አጠጣሃቸው፤ ይህም የሚገባቸው ነው” ሲል ሰማሁ። 7 ከመሠዊያውም፣ “አዎን፣ ሁሉን የምትገዛ ጌታ አምላክ ፍርድህ እውነትና ትክክል ነው” የሚል ድምፅ ወጣ። 8 አራተኛው መልአክ ጽዋውን ፀሐይ ላይ አፈሰሰ፤ ለእርሷም ሰዎችን በግለትዋ የማቃጠል ሥልጣን ተሰጣት። 9 ሰዎች በከባድ ሙቀቷ ተቃጠሉ፤ በእነዚህ መቅሠፍቶች ላይ ሥልጣን ያለውን የእግዚአብሔር ስም ሰደቡ። ንሰሐ አልገቡም፤ ክብርም አልሰጡትም። 10 አምስተኛው መልአክ ጽዋውን በአውሬው ዙፋን ላይ አፈሰሰ፤ የአውሬውም መንግሥት በጨለማ ተዋጠ። ከሥቃያቸውም የተነሣ ምላሳቸውን ያኝኩ ነበር። 11 ከሥቃያቸውና ከደረሰባቸው ቁስል የተነሣ የሰማይን አምላክ ተሳደቡ፤ ያም ሆኖ ግን ስላደረጉት ክፉ ሥራ ንስሐ ለመግባት ፈቃደኞች አልሆኑም። 12 ስድስተኛው መልአክ ጽዋውን ታላቁ ወንዝ ኤፍራጥስ ላይ አፈሰሰ፤ ከምሥራቅ ለመጡ ነገሥታት መንገድ ለማዘጋጀት የወንዙ ውሃ ደረቀ። 13 ከዘንዶው አፍና ከአውሬው አፍ እንዲሁም ከሐስተኛው ነቢይ አፍ እንቁራሪት የሚመስሉ ሦስት ርኩሳን መናፍስት ስወጡ አየሁ። 14 እነዚህ ተአምራዊ ምልክቶች የሚያደርጉ የአጋንንት መናፍስት ናቸው። ሁሉን በሚገዛ አምላክ ታላቅ ቀን ለሚደረገው ጦርነት የዓለም መንግሥታችን ሁሉ ለመሰብሰብ ወደ ወጥተው ሄዱ። 15 “ልብ በሉ! እኔ እንደ ሌባ እመጣለሁ! ራቁቱን እንዳይገኝና ሰዎችም ሐፍረቱን እንዳያዩ ነቅቶ ልብሱን የሚጠብቅ የተባረከ ነው።” 16 መናፍስቱ ነገሥታቱን ሰብስበው በዕብራይስጥ አርማጌደን ወደሚባል ቦታ አመጧቸው። 17 ሰባተኛው መልአክ ጽዋውን አየር ላይ አፈሰሰ። በዚያን ጊዜ፣ “ተፈጸመ!” የሚል ታላቅ ድምፅ ከመቅደሱና ከዙፋኑ ወጣ። 18 ከዚያም የመብረቅ ብልጥታ፣ ሁካታ ነጎድጓድና ከባድ የመሬት መናወጥ ሆነ፤ የዚያ ዓይነት የምድር ነውጥ የሰው ልጅ ምድር ላይ መኖር ከጀመረ አንሥቶ ሆኖ የማያውቅ እጅግ ከባድ ነበር። 19 ታላቂቷ ከተማ ለሦስት ተከፈለች፤ የሕዝቦች ከተሞችም ተደመሰሱ። እግዚአብሔር ታላቂቱ ባቢሎንን አስታወሰ፤ ለዚያች ከተማም የብርቱ ቁጣው ወይን ጠጅ የሞላበት ጽዋ እንድትጠጣ ሰጣት። 20 ደሴቶች ሁሉ ጠፋ፤ ተራሮችም በቦታቸው አልተገኙም። 21 አንድ ታለንት የሚመዝን የበረዶ ድንጋይ ከሰማይ ወርዶ ሰዎች ላይ ወደቀ፤ መቅሠፍቱ እጅግ አሰቃቂ ከመሆኑ የተነሣ ሰዎች ስለ በረዶው ድንጋይ እግዚአብሔርን ተራገሙ።
ሰማሁ ጸሐፊው ዮሐንስ (REV 1:9) ሰማ የእግዚአብሔርን ቁጣ ጽዋዎች በ REV 15:7. ተመሳሳይ ሀረጎችን ምን ብለህ እንደተረጎምካቸው ተመልከት፡፡
ከጽዋው ውስጥ ፈሰሰ አማራጭ ትርጉም: "በጽዋው ውስጥ ያለውን ወይን ውስጥ አፈሰሰው" ወይም "በእርሱ ጽዋ ውስጥ ያለውን የእግዚአብሔር ቁጣ አፈሰሰው" የሚያሳምም ቁስል "የሚያሳምም ቁስል፡፡" ይህ ፈውስና ካላገኘ በእንፌክሽን ወይም ከጉዳ የመጣ ልሆን ይችላል፡፡ የአውሬው ምልክት ይህንን በ REV 13:17. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
ከጽዋው ውስጥ አፈሰሰው ይህንን በ REV 16:2 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ባሕሩ ይህ በዓለማችን ውስጥ የሚገኙ ጨዋማ የውሃ አካላትን ያመለክታል፡፡ የሞተ ሰው ደም የሚመስል ይህ ማለት ውሃው ቀይ፣ ወፍራም ሆኖ መጥፎ ጠረን እንዳለው ያሳያል፡፡
ከጽዋው ውስጥ አፈሰሰው ይህንን በ REV 16:2 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ወንዞች እና የውሃ ምንጮች ይህ ንጹሕ ውሃ የሚያመነጩ የውሃ አካላትን ያመለክታል፡፡ የውሃዎች መላእክ ይህ ሦስተኛውን መላእክ የሚመለክት ነው፡፡ እርሱ የእግዚአብሔር ቁጣ በወንዝ እና በውሃ ምንጮች ላይ እንዲያፈስ የተሸመ ነው፡፡ አንተ ጻድቅ ነህ በዚህ ሥፍራ ላይ "አንተ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ነው፡፡ ያለህና የነበርህ ተመሳሳይ ሀረጋትን በ REV 1:4. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡ የቅዱሳንህን እና የነቢትህን ደም አፍስሰዋል አማራጭ ትርጉም: "ክፉ ሰዎች ቅዱሳንን እና ነቢትን ገድለዋል፡፡" ደም እንዲጠጡ ሰጠሃቸው እግዚአብሔር ለክፉ ሰዎች ወደ ደምነት የተቀየረ ውሃ ይጠጡ ዘንድ ሰጣቸው፡፡ ከመሰዊያው ላይ እንዲህ የሚል ምላሽ ሰማሁ አማራጭ ትርጉሞች 1) "ከመሰዊያው አጠገብ የነበረው መላእክ ስናገር ሰማሁት" ወይም 2) "ከመሰዊያው ሥር ያሉት የቅዱሳን ነፍሳት ስነናገሩ ሰማሁ"
ከጽዋው ውስጥ አፈሰሰው ይህንን በ REV 16:2 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ሰዎችን እንዲታቃጥል ፈቃድ ተሰጣት በዚህ ሥፍራ ላይ ዮሐንስ ፀሐይን በሰውና በመመሰል ይናገራል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "ፀሐይ ሰዎችን ክፉኛ ታቃጥል" የእግዚአብሔርን ስም ተሳደቡ አማራጭ ትርጉም: "የእግዚአብሔርን ስም ተሳደቡ"
ጽዋውን አፈሰሰ ይህንን በ REV 16:2. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ የአውሬው ዙፋን የአውሬው ኃይል ማዕከል፣ የመንግስቱ ዋና መቀመጫ ከተማ ሊሆን ይችላል፡፡ ፈሩ በአውሬው መንግስት ውስጥ ያሉ ሰዎች ፈሩ፡፡ ተሳደቡ "ረገሙ"
እንቁራርት ይመስላል እንቅራሪት በውሃ አጠገብ የሚትኖር ትንሽ እንስሳ ናት፡፡አይሁዳዊያን ንጹሕ እንስሳ አድርገው አይቆጥሯትም፡፡ አውሬው ይህንን በ REV 12:3. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
እኔ እንደ ሌባ እመጣለሁ ይህንን በ REV 3:3.ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ይህን አሳፋሪ ሁኔታ ተመለከቱ በዚህ ሥፍራ ላይ “እነርሱ” የሚለው ቃል ሌሎች ሰዎችን ያመለክታል፡፡ በአንድነት ሰበሰቧቸው "የዳቢሎስ መናፈስት ነገስታትን እና ጦራቸውን በአንድነት ሰበሰቧቸው" ተብሎ ወደምጠራ ሥፍራ "ሰዎች ብለው ወደምጠሩት ሥፍራ" አርማንጌዶ ይህ የቦታ ስም ነው፡፡
ጽዋውን አፈሰሰ ይህንን በ REV 16:2. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡ ከዚያ ከቅድስተ ቅዱሳኑ እና ከዙፋነን እንዲህ የሚል ድምጽ ወጣ ይህ ማለት በዙፋኑ ላይ የተቀመጠ አንድ ሰው ወይም በዙፋኑ አጠገብ የቆመ ሰው በከፍተኛ ድምጽ ተናገረ፡፡ ማን እንደተናገረ ግን በግልጽ አይታወቅም፡፡ ታላቅቷ ከተማ ተከፈለች አማራጭ ትርጉም: "የመሬት መንቀጥቀጥ ታላቅቷን ከተማ ከፈላት" ከዚያም እግዚአብሔር አስታወሳቸው "ከዚያም እግዚአብሔር አዘዘ" ወይም "ከዚያም እግዚአብሔር አመጣ" ወይም "ከዚያም እግዚአብሔር አጽኖት መስጠት ጀመረ፡፡" አንባቢያኑ እግዚአብሔር የዘነጋውን ነገር አስታወሰ ብለው ማሰብ የለባቸውም፡፡ ለከተማይቱ በከፍተኛ ቁጣው የተሞላ የወይን ጽዋ ሰጣት እግዚአብሔር ሕዝቡን ክፉኛ ቀጣቸው እንዲሁም በጣም እንዲሰቃዩ አደረገ፡፡ ለከተማይቱ ጽዋ ሰጣት "ከተማይቱ ከጽዋው ትጠጣ ዘንድ አስገደዳት" ከ . . . የተዘጋጀ ወይን አማራጭ ትርጉም: " . . . የሚወክል ወይን"
ታለንት ታለንት 34 ኪሎ ግራም ነው፡፡
1 ሰባቱን ጽዋዎች ይዘው ከነበሩት ሰባት መላእክት አንዱ ወደ እኔ መጥቶ እንዲህ አለን፤ “በብዙ ውሆች ላይ የተቀመጠችውን ታላቂቱ አመንዝራ የፍርድ ቅጣት አሳይሃለሁ፤ 2 የምድር ነገሥታት ከእርሷ ጋር አመንዝረሃል፤ ከዝሙቷ ወይን ጠጅ የምድር ነዋሪዎች ሰክረዋል።” 3 መልአኩ በመንፈስ ወደ በረሐ ወስዶኝ፣ የስድብ ስሞች በሞሉበት ቀይ አውሬ ላይ የተቀመጠች ሴት አየሁ። አወሬው ሰባት ራሶችና አሥር ቀንዶች ነበሩት። 4 ሴትዬዋ ሐምራዊና ቀይ ልብስ ለብሳ፣ በወርቅና በከበሩ ድንጋዮች እንዲሁም በዕንቁዎች አጊጣ ነበር። በእዛም ጸያፍ ነገሮችና የዝሙቷ ርኩሰት የሞላበት የወርቅ ጽዋ ይዛ ነበር። 5 ግንባሯም ላይ፣ “ታላቂቱ ባቢሎን፣ የአመንዝሮችና የምድር ጸያፍ ነገሮች እናት” የሚል ምስጢራዊ ትርጉም ያለው ስም ተጽፎ ነበር። 6 ሴትዬዋ በቅዱሳንና በኢየሱስ ሰማዕታት ደም ሰክራ አየሁ። ባየኋት ጊዜ በጣም ተደነቅሁ። 7 መልአኩ ግን፣ “ለምን ትደነቃለህ? የሴትዮዋንና የተሸከማትን አውሬ (ሰባት ራሶችና አሥር ቀንዶች ያሉትን አውሬ) ምንነት እነግርሃለሁ። 8 ያየኸው አውሬ ቀድሞ ነበረ፤ አሁን የለም፤ ሆኖም በኃላ ከጥልቁ ጉድጓድ ይመጣል። ከዚያም ወደ ጥፋት ይሄዳል። ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ሰማቸው በሕይወት መጽሐፍ ያልተጻፈ በምድር የሚኖሩ ሰዎች ቀድሞ የነበረውን፣ አሁን የሌለውን በኃላ ግን የሚመጣውን አውሬ ሲያዩ ይደነቃሉ። 9 ይህ አስተዋይ አእምሮን የሚጠይቅ ጉዳይ ነው። ሰባቱ ራሶች ሴትዬዋ የተቀመጠችባቸው ሰባት ኮረብቶች ናቸው። 10 እነርሱም ሰባት ነገሥታት ናቸው። አምስቱ ወድቀዋል፤ አንድሱ አሁንም አለ፤ ሌለው ገና አልመጣም፤ በሚመጣበት ጊዜ ግን ለአጭር ጊዜ መቆየት ይገባዋል። 11 ቀድሞ የነበረው አሁን ግን የሌለው አውሬ ራሱ ስምንተኛው ንጉሥ ነው ሆኖም፣ ከሰባቱ አንዱም ነው ወደ ጥፋትም ይሄዳል። 12 ያዩኋቸው አሥር ቀንዶች ገና መንግሥት ያልተቀበሉ አሥር ነገሥታት ናቸው፤ ነገር ግን ለአንድ ሰዓት ያህል ከአውሬው ጋር እንዲነግሡ ሥልጣን ይቀበላሉ። 13 እነዚህ ነገሥታት ተመሳሳይ ሐሳብ አላቸው፤ ኅይልና ሥልጣናቸውን ሁሉ ለአውሬው ያስረክባሉ። 14 በጉን ይዋጋሉ። ይሁን እንጂ፣ በጉ የጌቶች ጌታ የነገሥታት ንጉሥ በመሆኑ እርሱ ያሸንፋቸዋል የተጠሩት፣ የተመረጡትና ታማኝ የሆኑት ከእርሱ ጋር ድል ይነሣሉ።” 15 መልአኩም፣ “አመንዝራዋ ተቀመጣባቸው የነበሩት ያየሃቸው ውሆች ሕዝቦችና ሰዎች፣ ወገኖችና ቋንቋዎች ናቸው” አለኝ። 16 ያየሃቸው አሥር ቀንዶች ከአውሬው ጋር አንድ ላይ ሆነው አመንዝራዋን ይጠላሉ። ያጠፏታል፤ ራቁትዋን ያስቀሯታል፤ ሥጋዋን ይበላሉ፤ ጨርሶ እስክትጠፋ በእሳት ያቃጥሏታል። 17 ምክንያቱም፣ የእግዚአብሔር ቃል እስኪፈጸም ድረስ ሥልጣናቸውን ለአውሬው ለመስጠት በመስማማት ዕቅዱን እንዲፈጽሙ እግዚአብሔር ይህን ሐሳብ በልባቸው ውስጥ አኑሮአል። 18 ያይየሃት ሴት በምድር ነገሥታት ላይ የምትገባ ታላቂቱ ከተማ ናት።”
በብዙ ውሃዎች ላይ የሚተቀመጠው ታላቅቷ ጋለሞታ መላእኩ እየተናገረ ያለው ዮሐንስ ገና ስላላያት ሴት ነው፡፡ ይህች ሴት በ REV 17:5 ላይ እና በ REV 17:18. ላይ የተገለተውን ከተማ የሚትወክል ናት፡፡ ታላቅቷ ጋለሞታ አማራጭ ትርጉም: "ሁሉም ሰው ስለእርሷ የሚያውቀው ጋለሞታ ሴት" ወይም "ሁሉም ሰው የሚጠላት ጋለሞታዋ ሴት፡፡" በብዙ ውኃዎች ላይ "ብዙ የውኃ መውረጫዎች ባሉበት" ወይም "ብዙ ወንዞች አጠገብ" ወይም "በወንዞች እና በባህሮች አጠገብ"
ውድ ድንጋዮች እና እንቁዎች አማራጭ ትርጉም: "ብዙ ዓይነት ውድ ድንጋዮች" እንቁዎች ለስላሳ፣ ጠንካራ እና ነጭ ጨሌ በግምባርዋም ምስጢር የሆነ ስም አማራጭ ትርጉም: "የሆነ ሰው በግንባሯ ላይ ይህንን ስም ጽፏል" . ታላቅቷ ባቢሎን አማራጭ ትርጉም: "እኔ ታላቅቷ ባቢሎን ነኝ"
ከደም ጋር ጠጣችው ይህ ማለት በኢየሱስ የሚያምኑ ብዙ ሰዎችን ጎድታለች እንዲሁም ገድላለች፡፡ ለኢየሱስ ሰማእታት የሆኑ "ለሌሎች ሰዎች ስለኢየሱስ በመናገራቸው ምክንያት የሞቱት አማኞች" ስለምን ተደነቅህ? አማራጭ ትርጉም: "ልትደነቅ አይገባህም" ወይም "እነዚህን ነገሮች ልተገነዘባቸው ይገባል"
is about to come up ከዝቅተኛ ሥፍራ ወደ ከፍተኛ ሥፍራ የመንቀሳቀስ ጉዳይ ነው ወደ ላይ የመምጣት ጉዳይ ነው ከዝቅተኛ ሥፍራ ወደ ከፍተና ሥፍራ የመውጣት ጉዳይ ነው ስማቸው ያልተጻፈ ሰዎች . . . ዓለም ሳይፈጠር በፊት "ስማቸውን እግዚአብሔር ያልጻፈሰዎች . . . ዓለም ከመፈጠሩ በፊት፡፡" ይህ ልሆን ነው ይህ ልመጣ እና እንዲህ ሆኖ ሊቀር ነው
ሴትቱ የተቀመጠችባቸው ሰባት ተራሮች በዚህ ሥፍራ ላይ “ተቀመጠች” የሚለው ቃል ትርጉሙ ሴትቱ በእነዚ ሥፍራዎች እና ሰዎች ላይ ሥልጣን ነበራት ማለት ነው፡፡ ሰባት ነገሥታት እነዚህ ነገሥታት አንዱ ሌላኛውን ይከታተላል፡፡ በተመሳሳይ ጊዜ የሚኖሩ አይደሉም፡፡ አንዱ ይኖራል "አሁን አነንዱ ንጉሥ ነው"
ዘንዶው . . . ራሱ ስምነተኛው ንጉሥ ነው፤ ይሁን አንጂ ከእነዚያ ሰባት ነገሥታት መካከል አንዱ ነው፡፡ ዘንዶው ከሰባቱ እንደ አንዱ ሆኖ ነግሦዋል ወይም ይነግሣል ከዚያም እንደ ስምንተኛ ንጉስም ሆኖ ይነግሣል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ አስቀድሞ የኖረው ዘንዶ እና በሕይወት ያሌለው ስምንተኛው ንጉሥ ሆኖ ይነግሣል፡፡ ልክ እንደ ሰባቱ ነገሥታት ክፉ ይሆል ነገር ግን እግዚአብሔር በእርግጠኝነት ያጠፋዋል፡፡
ዐሥር ነገሥታት እነዚህ ነገሥታት ከዘንዶው ጋር በተመሳሳይ ጊዜያት የሚገዙ ናቸው፡፡ ለአንድ ሰዓት በቋንቋችሁ አንድን ቀን በሃያ አራት ሰዓታትን መከፋፈያ መንገድ ካሌለ በባሕላችሁ ውስጥ በአንድ ቀን ውስጥ የሚከናወኑ ተግባራትን ከፋፍላችሁ በምትገልጡበት መንገድ ይህንን መግለጽ ትችላላችሁ፡፡ በጉ ያሸንፋቸዋል . . . እንዲሁም ከእርሱ ጋርም የተጠሩት፣ የተመረጡት፣ ተማኞች የሆኑት "በጉ—እና ከእርሱ ጋር የተጠሩት፣ የተመረጡት እና ታማኝ የሆኑት- አብረው ያሸንፋሉ"
የተመለከትከው ውሃ ገለሞታዋ ሴት የተቀመጠችበት ነው ይህንን በ REV 17:1. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎም ተመልከት፡፡ ሰዎች . . . ብዙ ሕዝብ . . . ቋንቋዎች እነዚህ ሁሉ ቃላት ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው ናቸው፤ የተዘረዘሩትም አጽኖት ለመስጠት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡ "በዓለም ውስጥ ያሉ ሰዎች ሁሉ፡፡"
ጥላቻ ይህንን በ REV 2:6. ላይ ያለውን በተረጎምክበት መንገድ ተርጉመው፡፡ ባዶዋንና ራቁትዋን አድርግ "ያላትን ሁሉ ስረቃት እና ባዶዋን አስቀራት" ሥጋዋንም ይበላሉ፥ በእሳትም ያቃጥሉአታል። እነዚህ ሁለት ንዑስ ዓረፍተ ነገሮች ያላቸው ትርጉም እርሷን ፈጽሞ ማጥፋት ነው፡፡ የእግዚአብሔር ቃ ፍጻሜን እስኪያገኝ ድረስ አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር ይሆናል ያለውን ነገር እስኪሆን ድረስ"
1 ከዚህ በኋላ ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ። ታላቅ ሥልጣንም ነበረው፤ ምድርም በክብሩ አበራች። 2 በታላቅ ድምፅም ጮኾ እንደኢህ አለ፤ “ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች፣ ወደቀች! የአጋንንት መኖሪያ፣ የርኩሳን መናፍስት ሁሉ ማደሪያ፣ የማንኛውም ርኩስና ጠያፍ ወፍ መጠጊያ ሆነች 3 ሕዝቦች ሁሉ ቁጣ በሚያመጣበት የዝሙቷ ወይን ጠጅ ሰክረዋል። የምድር ነገሥታት ከእርሷ ጋር አመንዝረዋል። የምድር ነጋዴዎች በምቾት ኑሮዋ በልጽገዋል።” 4 ሌላ ድምጽም ከሰማይ እንዲህ ሲል ሰማሁ፤ “ሕዝቤ ሆይ፣ በኃጢአትዋ እንዳትካፈሉ የማመጣበትንም መቅሠፍት እንዳትቀበሉ ከእርሷ ውጡ። 5 ኃጢአቷ እስከ ሰማይ ተከምሯል እግዚአብሔር ክፉ ሥራዋን አስታውሷል። 6 በሰጠችው መጠን ስጧት፤ ባደረገችው መጠን ዕጥፍ አድርጉባት እርሷ በቀካቀከችው ጽዋ መጠን፣ ዕጥፍ አድርጋችሁ ቀላቅሉባት። 7 እርሷ ራስዋን እንዳከበረችውና በምቾት በኖረችው መጠን፣ የዚያኑ ያህል ስቃይና ሐዘን ስጧት እርሷ በልቧ ‘እንደ ንግሥት ተቀምጫለሁ መበለትም አይደለሁም ሀዘንም አይደርስብኝም’ ብላለች። 8 ስለዚህ፣ መቅሠፍቶችዋ በእብንድ ቀን ይደርሱባታል፣ ሞት፣ ሐዘንና ረሐብ ይመጡባታል። በእሳት ትቃጠላለች፤ እርሷ ላይ የሚፈርድ ጌታ እግዚአብሔር ብርቱ ነው” 9 ከእርሷ ጋር ያመነዘሩና ቅጥ ያጣ ሕይወት የኖሩ፣ የቃጠሎዋ ጭስ ሲወጣ ሲያዩ ስለ እርሷ እየጮኹ ያለቅሳሉ። 10 ሥቃይዋንም በመፍራት በሩቅ ቆመው፣ “ታላቂቱ ከተማ፣ አንቺ ብርቱ ከተማ በአንድ ሰዓት ውስጥ ቅጣትሽ መጥቷልና ወዮልሽ ወዮልሽ” ይላሉ። 11 ከእንግዲህ ሸቀጧን የሚገዛ ስለማይኖር የምድር ነጋዴዎች ለእርሷ ያለቅሳሉ፤ ያዝኑላታል፤ 12 ሸቀጦችዋ ወርቅ፣ ብር፣ የከበረ ድንጋይ፣ ዕንቁ፣ ቀጭን ልብስ፣ ሐምራዊ ጨርቅ፣ ሐር ጨርቅ፣ ቀይ ጨርቅ፣ ማንኛውም ዓይነት ጣፋጭ ሽታ ያለው እንጨት፣ ማንኛውም ከዝሆን ጥርስ የተሠራ ዕቃ፣ ማንኛውም ከከበረ ድንጋይ የተሠራ ዕቃ፣ ነሐስ፣ ብረት፣ እብነ በረድ 13 ቀረፋ፣ ቅመም፣ የሚሸር እንጨት፣ ከርቤ፣ ዕጣን፣ ወይን ጠጅ፣ ዘይት፣ንጹሕ ዱቄት፣ ስንዴ፣ ከብቶች፣ በጎች፣ ፈረሶችና ሰረገሎች ባሪያዎችና የሰዎች ነፍሶች ናቸው። 14 አጥብቀሽ የተመኘሻቸው ነገሮች ከአንቺ አምልጠዋል። ምቾትና ውበትሽ ጠፍተዋል ከእንግዲህም አይገኙም። 15 በእርሷ የበለጸጉ እነዚህን ዕቃዎች የሚነግዱ ሰዎች ሥቃይዋን በመፍራት ከእርሷ ርቀው በመቆም በታላቅ ድምፅ ያለቅሳሉ 16 እንዲህም ይላሉ “ቀጭን ልብስ፣ ሐምራዊና ቀይ ልብስ ትለብስ ለነበች፤ በመርቅ፣ በከበረ ድንጋይና በዕንቁ ታጌጥ ለነበረች ታላቂቱ ከተማ ወዮ ወዮ!” 17 በእብንድ ሰዓት ያ ሀብት ሁሉ ጠፍቷል። የመርከብ አዛዦች ሁሉ፣ በመርከብ የሚጓዙ ሰዎች ሁሉ፣ መርከበኞችና በባሕር ላይ የሚሠሩ ሁሉ ርቀው ቆሙ። 18 ያቀጠሎዋን ጭስ ሲመለከቱ፣ “ ታላቂቱን ከተማ የሚመስላት ማነው?” እያሉ ጮኹ። 19 በራሳቸውም ላይ ዐመጽ ነስንሰው እያለቀሱና እያዘኑ፣ መርከቦች ያሏቸውና በእርሷ ሀብት የበለጸጉ ሁሉ ታላቂቱ ከተማ በአንድ ሰዓት ስለ ወደመች ወዮላት ወዮላት” አሉ። 20 “ ሰማይ ሆይ ደስ ይበልህ፤ እግዚአብሔር ስለ እናንተ እርሷ ላይ ፈርዷልና እናንት ቅዱሳን፣ ሐዋርያትና ነቢያት ደስ ይበላችሁ!” 21 ከዚያም አንድ ብርቱ መልአክ ታላቅ የወፍጮ ድንጋይ የሚመስልን ድንጋይ እንዲህ በማለት ወደ ባሕር ወረወሬ፣ “ታላቂቱ ከተማ ባቢሎን በዚህ ሁኔታ በኅይል ተገፍታ ወደ ባሕር ትጣላለች፤ ከእንግዲህ ወዲህ ጨርሶ አትታይም 22 የበገና ደርዳሪዎች፣ የሙዚቀኞች፣ የዋሽንትና መለኮት ነፊዎች ድምፅ ከእንዲህ በአንቺ አይሰማም። ማንኛውንም ዓይነት የጥበብ ሥራ የሚሠራ በአንቺ አይገኝም። የወፍጮ ድምፅም በአንቺ አይሰማም። 23 የመብራት ብርሃን፣ ከእንግዲህ በአንቺ አያበራም። የሙሽራውና የሙሽራይቱ ድምፅ ከእንግዲህ በአንቺ አይሰማም። ነጋዴዎችሽ የምድር ልዑላን ነበሩ ሕዝቦችን በመተትሽ አሳስተሻል። 24 የነቢያትና የቅዱሳን ደም፣ በዚህ ምድር የተገደሉ ሰዎች ሁሉ ደም በእርሷ ተገኝቷል።
የተጠሉ ወፎች "አስጠሊታ ወፎች" ወይም "ደስ የማይሉ ወፎች" ለሁሉም ሕዝቦች "በሁሉም ሀገራት ውስጥ ላሉ ሕዝቦች" ወይኑን ጠጡ . . . ከእርሷ ጋር ኢ-ግብረገባዊ የወሰብ ግንኙነት ፈጸሙ "ከባቢሎን ከተማ ጋር ተባበሩ እንዲሁም በኃጢአቷም ተባበሩ" ያ የእርሷን ፍርድ አመጣ "ይህም የእግዚአብሔር ፍርድ በእርሷ ላይ አመጣ" ነጋዴ የተለያዩ ነገሮችን የሚሸጥ ሰው በተንደላቀቀ ኑሮው ኃይል "በእርሷ ደስታ ላይ በጣም ብዙ ብር ከማውጣቱ የተነሣ"
ሌላ ድምፅ "ሌላ ሰው፣" ምናባትም ኢየሱስ ወይም እግዚአብሔር አስታወሰ ይህንን በ REV 16:19. ላይ “ማስታወስ” የሚለውን ቃል በተረጎምክብ ምንገድ ተርጉመው፡፡ ብድሯን ክፈላት ተናጋሪው ምናልባት ለመላእክቱ እየጠናገረ ይሆናል ወይም በ(REV 17:16) ለተጠቀሱት ለዐሥሩ ነገሥታት እየተናገረም ሊሆን ይችላል ወይም ለራሱ እየተናገረ ሊሆን ይችላል፡፡ እጥፍ ድርብ ደርቡባት አማራጭ ትርጉም: "ሁለት እጥፍ ጠንካራ አድርጉት"
ራሷን አክብራለች . . . ስጧጽ . . እንዲህ ብላለች . . . እኔ . .. እኔ . . እኔ ፈጽሞ አላይም . . . መቅሰፍት ይበላታል አማራጭ ትርጉም: "የባብሎን ሕዝቦች ራሳቸውን አክብረዋል . . . እኛ . . . እና . . እኛ ፈጽሞ አናይም . . . መቅሰፍት ይበላቸዋ፡፡" እንደ ንግስት እቀመጣለሁ፤ እኔ ባልቴት አይደሉም እርሷ በራሷ ስልጣን ገዥ ናት፤ በሌላ ሰው ላይ ፈጽሞ አትደገፍም (እንዲህ ታስባለች)፡፡ እርሷ በእሳት ትበላለች አማራጭ ትርጉም: "እሳት ፈጽሞ ያቃጥላታል"
የግብረስጋ ግንኙነትን በተመለከተ ኢ-ግብረገባው ነገርን የፈጸመ ሰው እና ከእርሷ ጋር ከቁጥጥር ውጪ የሆነ ሰው ይህ ማለት ነገሥታቱ እና ሕዝቦቻቸው ኃጢአትን ሠርተዋል እንዲሁም የባቢሎን ሕዝቦች እንዳደረጉት ሁሉ በእግዚአብሔር ላይ አምጸዋል፡፡ ወዮላችሁ፣ ወዮላችሁ የቃላት ድግግሞሹ የሚያሳየው አጽኖት መሰጠቱን ነው፡፡
ለእርሷ አልቅሱላት "ለባብሎን ሕዝብ አልቅሱለት" እምነ በረድ ሕንጻ ለመገንባት የሚያገለግል ድንጋይ ቅመማ ቅመም ለምግብ ጣዕም ለመስጠጥ የሚጨመር ቅመም
አንዚ . . . ፍሬ በዚህ ሥፍራ ላይ “አንዚ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የባብሎንን ሕዝብ ነው፡፡ በሙሉ ኃይልሽ የተመኘሽውቸ "በጣም መፈለግ" እንደገና መገኘት የማይችል አማራጭ ትርጉም: "እንደገና የአንች ሊሆኑ አይችሉም"
እና አስጌጠውት ነበር አማራጭ ትርጉም: "ራሳቸውን አስግጠው ነበር" ወይም "ለብሰው ነበር" ውድ ጌጣ ጌጦች "ውድ የሆነ ጌጦች" ወይም "ውድ ዋጋ ያላቸው ጌጦች" ዕንቁዎች ይህንን በ REV 17:4. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡
“የእርሷን” የሚለው ቃል የሚያመለከተው የባቢሎንም ከተማ ነው፡፡ ከተማይተዋ ታላቅ ከተማ ትመስላለችን? አማራጭ ትርጉም: "እንደ ባቢሎን ያላ ታላቅ ከተማ የለም፡፡".
የወፍጮ ድንጋይ እህል ለመፍጨት የሚሆን ትልቅ ክብ ድንጋይ፡፡ ታላቂቱ ከተማ ባቢሎን እንዲህ ተገፍታ ትወድቃለች ከእንግዲህም ወዲህ ከቶ አትገኝም። እግዚአብሔር ከተማይቱን ፈጽሞ ያጠፋታል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር ባቢሎን በኃይል ገፍቶ ይጥላታል እና ከቶም አትገኝም" በገና የሚመቱና የሚዘምሩም ድምፅ እንቢልታንና መለከትንም የሚነፉ ድምፅ ከእንግዲህ ወዲህ በአንቺ አማራጭ ትርጉም: "በከተማችሁ ውስጥ ማንም ከእንግዲህ የሙዝቃ ድምፅ እንደገና አይሰማም፡፡" የእጅ ጥበብም ሁሉ አንድ ብልሃተኛ እንኳ ከእንግዲህ ወዲህ በአንቺ ውስጥ ከቶ አይገኝም፥ የወፍጮ ድምጽም ከእንግዲህ ወዲህ በአንቺ ውስጥ ከቶ አይሰማም፥ አማራጭ ትርጉም: "በከተማችሁ ውስጥ ከእንግዲህ ሠራተኞች አይታዩም ዌም አይሰሙም"
የሙሽራና የሙሽራይቱም ድምጽ ከእንግዲህ ወዲህ በአንቺ ውስጥ ከቶ አይሰማም አማራጭ ትርጉም: "ማንም ከእንግዲህ የሙሽራ እና የሙሽራይቱን ደስታ የሞላበት ድምፅ አይሰማም፡፡" ነጋዴዎችሽ የምድር መኳንንት ነበሩና "በሌሎች ከተሞች የሚኖሩ ሰዎች ነጋዴዎችሽን ያከብራሉ" እንዲሁም በአስማትሽም አሕዛብ ሁሉ ስተዋልና። አማራጭ ትርጉም: "እንዲሁም በአስማቶችሽ አሕዛብን ሁሉ አስተሻልና" በእርስዋም ውስጥ የነቢያትና የቅዱሳን ደም በምድርም የታረዱ ሁሉ ደም ተገኘባት። አማራጭ ትርጉም: "ነቢያትን እና ቅዱሳንን እንዲሁም በዓለም ውስጥ ያሉትን ሌሎች ሰዎችን በመግደል እግዚአብሔር በደለኛ አድርጎሻል፡፡
1 ከእነዚህ ነገሮች በኋላ የበዙ ሰዎች ድምፅ የሚመስል ታላቅ ድምፅ ከሰማይ ሰማሁ “ሃሌ ሉያ ማዳን፣ ክብርና ኃይል የአምላካችን ነው። 2 በዝሙቷ ምድርን ያረከሰችውን ታላቂቱን አመንዝራ ስለ ፈረደባት ፍርዱ እውነትና ትክክል ነው። እርሷ ያፈሰሰችውን የአገልጋዮቹን ደም ተበቅሎአል። 3 በድጋሚ “ሃሌ ሉያ፤ ጢስዋ ከዘላለም እስከ ዘላለም ከእርሷ ይወጣል” በማለት ተናገሩ። 4 ሃያ አራቱ ሽማግሌዎችና አራቱ ሕያዋን ፍጡራን በግንባራቸው ተደፍተው፣ “አሜን ሃሌ ሉያ!” በማለት ዙፋኑ ላይ ለተቀመጠው ሰገዱ። 5 ከዚያ በኋላ፣ “ታናናሾችም ታላላቆችም እርሱን የምትፈሩ አገልጋዮቹ ሁሉ እግዚአብሔርን አመስግኑ!” የሚል ድምፅ ከዙፋኑ ወጣ። 6 ከዚያም እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ፣ እንደ ብዙ ውሆች ድምፅና የብርቱ ነጎድጓድ የሚመስል ድምፅ እንዲህ አለ፤ 7 ደስ ይበለን፤ ሐሤት እናድርግ፤ የበጉ ሰርግ ስለ ደረሰ ሙሽራዋም ራስዋን ስላዘጋጀች፤ ደስ ይበለን፤ ሐሤት እናድርግ ፤ ክብርንም እንስጠው።” 8 ደማቅና ቀጭን ንጹሕ ልብስ እንድትለብስ ገሰጣት። ቀጭኑ ልብስ የቅዱሳኑ የጽድቅ ሥራ ነው። 9 መልአኩም፣ “ወደ በጉ ሰርግ እንደመጡ የተጋበዙ ሰዎች የተባረኩ ናቸው ብለህ ጻፍ” አለኝ። በተጨማሪም፣ “እነዚህ እውነተኛ የእግዚአብሔር ቃሎች ናቸው” አለኝ። 10 እኔም ልሰግድለት በእግሩ ሥር ተደፋሁ፤ እርሱ ግን፣ “እንዳታደርገው! እኔ ራሴ ከአንተና ስለ ኢየሱስ የተሰጠውን ምስክር ከያዙ ወንድሞችህ ጋር አገልጋይ ነኝ። ልችእግዚአብሔር ስገድ፤ ስለ ኢየሱስ የተሰጠው ምስክር የትንቢት መንፈስ ነውና” አልኝ። 11 ከዚያም ሰማይ ተከፍቶ አየሁ፤ እነሆም አንድ ነጭ ፈረስ ተመለከትኩ ፈረሱ ላይ የተቀመጠው ታማኝና እውነተኛ ይባላል። በጽድቅ ይፈርዳል፤ ይዋጋል። 12 ዐይኖቹ እንደ እሳት ነበልባል ናቸው፤ ራሱም ላይ ብዙ አክሊሎች ነበሩ። ከእርሱ በቀር ማንም የማያውቀው ስም እርሱ ላይ ተጽፎ ነበር። 13 ደም የተነከረ ልብስ ለብሶ ነበር፤ ስሙ የእግዚአብሔር ቃል ተብሎ ይጠራል። 14 ቀጭን፣ ነጭና ንጹሕ ልብስ የለበሱ ሠራዊት በነጫጭ ፈረሶች ተቀምጠው ይከተሉት ነበር። 15 ከአፉም ሕዝቦችን የሚመታበት የተሳለ ሰይፍ ይወጣ ነበር፤ በብረት በትር ይገዛቸዋል። ሁሉን የሚገዛ የእግዚአብሔርን ቁጣ የወይን ጠጅ መጭመቂያ ይረግጣል። 16 ልብሱና ጭኑ ላይ፣ የነገሥታት ንጉሥ፣ የጌቶችም ጌታ የሚል ስም ተጽፎበት ነበር። 17 አንድ መልአክ ፀሐይ ላይ ቆሞ አየሁ። እርሱም በታላቅ ድምፅ፣ “ኑ፣ ወደ ታላቁ የእግዚአብሔር ግብዣ ተሰብሰቡ። 18 መጥታችሁ የነገሥታትን፣ የጦር አዛዦችን፣ ሥጋ የኅያላንን ሥጋ፣ የፈረሰኞችንና በላያቸው የተቀመጡትን ሥጋ፣ የጌቶችን የባሮችን፣ የታናናሾችንና የታላላቆችን ሥጋ፣ የሰዎችን ሁሉ ሥጋ ብሉ።” 19 አውሬውንና ከእርሱም ጋር የምድር ነገሥታትንና ሰራዊታቸውን አየሁ። ፈረሱ ላይ ተቀምጦ ከነበረውና ከሰራዊቱ ጋር ውጊያ ለመግጠም ተዘጋጅተው ነበር። 20 እነሆ አውሬው ተያዘ፤ ከእነርሱም ጋር በእርሱ ፊት ምልክቶችን የሚያደርገው ሐሰተኛ ነቢይ ተያዘ። በእነዚህ ምልክቶች አማካይነት የአውሬውን ምልክት የተቀበሉትንና ለምስሉ የሰገዱትን አሳሳተ። ሁለቱም በዲን ወደሚቃጠለው የእሳት ባሕር በሕይወት እያሉ ተጣሉ። 21 የተቀሩትም ፈረስ ላይ ከተቀመጠው አፍ በሚወጣው ሰይፍ ተገደሉ። ወፎችም ሁሉ ሥጋቸውን በልተው ጠገቡ።
ሰማሁ
በሥፍራ ላይ “እኔ” የሚለው ቃል ዮሐንስን ያመለክታል፡፡
ሃሌሉያ
የዚህ ቃል ትርጉሙ “እግዚአብሔር ይመስገን” ወይም “እግዚብሔር እናመስግን” ማለት ነው፡፡
ታላቂቷ ጋለሞታ
ይህ በምድር ላይ ያሉትን ሌሎች ሰዎችን የሚመሩትን፣ ትክክለኛ ያልሆኑ አምልክትን እንዲያመልኩ የሚያደርጉትን ክፉ ሰዎችን የሚያመለክት
በምድር ላይ የተበላሹት
አማራጭ ትርጉም: "በምድር ላይ ያሉ ሰዎችን የሚያበላሹት"
ሃሌሉያ ይህንን በ REV 19:1 ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ከእርሷ ከዘላለም እስከ ዘላለም ይወጣልr "ከጣኦት አምላኪዎች ከዘላለም እስከ ዘላለም፡፡" አማራጭ ትርጉም: "ራሳቸውን ጋለሞታ ካደረጉት እና ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ መካራን ከሚቀበሉት" ሃያ አራት ሽምግሌዎች አራት ሽማግሌዎቸ - 24 ሽማግሌዎች
አምላካችን እግዚአብሔር ይመስገን በዚህ ሥፍራ “የእኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ተናጋሪውን እና ሁሉንም የእግዚአብሔር አገልጋዮችን ነው፡፡ ሁለቱም አላስፈላጊዎች እና ኃይለኞች ናቸው ተናጋሪው እነዚህ ቃላት በአንድነት የተተቀመው ሁሉንም የእግዚአብሔርን ሕዝብ ለማመልከት ነው፡፡
ሃሌሉያ ይህንን በ REV 19:1. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
ደስ ይበልን በዚህ ሥፍራ ላይ “እኛ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሁሉንም የእግዚአብሔር አገልጋዮችን ነው፡፡ ክብርን ስጡት "ለእግዚአብሔር ክብርን ስጡ" ለበጉ ሠረግ ድግስ...ሙሽራይቱ ለእርሱ ራሷን አዘጋጅታለች ይህ የኢየሱስ እና የእርሱ ሕዝብ ለዘላለም አብረው ለመሆን መገናኘታቸውን ያመለክታል፡፡ በግ ይህንን በ REV 5:6. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
የበጉ ሠረግ ድግስ የሠርጉ ድግስ የኢየሱስ እና የእርሱ ሕዝብ ለዘላለም መገናኘታቸውን ያመለክታል፡፡ በምድር ላይ ተደፋሁ በምድር ላይ መደፋት ማለት ፊትን ወወደ ምድር በማድረግ መደፋት ሲሆን አክብሮትን እና ለመገልገል ፈቃደኝነተን ያሳያል፡፡ በ19፡3 ላይ ያለውን ማስታወሻ ተመልከት፡፡
ከዚያም የተከፈተ ሰማይ አየሁ ይህ ምስል የአዲስ ራዕይ ጅማሬን ለማሳየት ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ ይህንን ሀሳብ በ REV 4:1, REV 11:19, እና REV 15:5. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ በደም የተነከረ ልብስን ለበሷል አማራጭ ትርጉም፡ "በደም የተጨማለቀ ልብስ ለብሷል" ወይም "በደም የተነከረ ልብስ ለብሷል"
ከአፉ ስለታም ሰይፍ ይወጣል ይህንን ሀረግ በ REV 1:16. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ አሕዛብንም ይመታበት "አሕዛብን አጠፋ" ወይም "አሕዛብን በእርሱ ቁጥጥር ሥር አደረጓቸው" በብረት በተር ይገዛቸዋል ይህንን በ REV 12:5. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ በልብሱና በጭኑም የተጻፈበት፦ የነገሥታት ንጉሥና የጌታዎች ጌታ የሚል ስም አለው። አማራጭ ትርጉም: "በልብሱ ላይ እና በጭኑ ላይ ስም ተጽፎበታል"
የጌታዎችንና የባሪያዎችንም የታናናሾችንና የታላላቆችንም መላእክት እነዚህ ቃለት የተጠቀሙትን በአንድነት ሁሉንም ሰዎች ለማመልከት ነው፡፡
የተቀሩት "የተቀሩት የአውሬው ወታደሮች" ከአፉ የሚወጣቸው ሰይፍ በ REV 1:16. ላይ ያለውን ተመሳሳይ ሀረግ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
1 ከዚህ በኃላ የጥልቁ መክፈቻ ያለው አንድ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፤ በእጁም ትልቅ ሰንሰለት ይዞ ነበር። 2 ዘንዶውን ይዞ ሺህ ዓመት አሰረው፤ ይህ ዘንዶ ዶያብሎስ ሰይጣን የተባለው የቀድሞው እባብ ነው። 3 ወደ ጥልቁ ጣለው፤ ዘግቶም በእርሱ ላይ ማኅተም አደረገበት። ይህን ያደረገው ሺህ ዓመቱ እስኮፈጸም ድረስ ከእንግዚህ ሕዝቦችን እንዳያሳስት ነው። ከዚያ በኋላ ለአጭር ጊዜ መፈታት ይኖርበታል። 4 ከዚያም ዙፋኖች አየሁ። ዙፋኖቹም ላይ የመፍረድ ሥልጣን የተሰጣቸው ተቀምጠው ነበር። ለኢየሱስና ለእግዚአብሔር ቃል ምስክር የተሰየፉ ሰዎችን ነፍሶችንም አየሁ። ለአውሬው ወይም ለምስሉ አልሰገዱም፤ ምልክቱም ግንባራቸው ወይም እጃቸው ላይ እንዲያረግ አልፈቀዱም። ከሞት ተነሥተው፣ ለሺህ ዓመት ከክርስቶስ ጋር ነገሡ። 5 የተቀሩት ሙታን ግን ሺሁ ዓመት እስኪፈጸም ድረስ ከሞት አልተነሡም። ይህ የመጀመሪያው ትንሣኤ ነው። 6 በመጀመሪያው ትንሣኤ ድርሻ የሚኖራቸው ሁሉ የተባረኩና የተቀደሱ ናቸው! እነዚህን በመሳሰሉት ላይ ሁለተኛው ሞት ኅይል አይኖረውም። የእግዚአብሔርና የክርስቶስ ካህናት ይሆናሉ፤ ከእርሱም ጋር ሺህ ዓመት ይነግሣሉ። 7 ሽው ዓመት ካበቃ በኃላ ሰይጣን ከእስራት ይፈታል። 8 በአራቱ የምድር ማእዘን ያሉ ሕዝቦች ማለትም ጎግና ማጎግን ወደ ጦርነት ለማምጣት እያሳተ ወደ ጦርነት ለማምጣት ይወጣል ቁጥራቸውም እንደ ባሕር አሸዋ ያህል እጅግ ብዙ ነው። 9 እነርሱም ወደ ምድር ሁሉ ሄደው የቅዱሳንን ሰፈር፣ እንዲሁም የተወደደችውን ከተማን ከበቡ። ሆኖም፣ እሳት ከሰማይ ወርዶ በላቸው። 10 እነርሱን ያሳሳተው ዲያብሎስ አውሬውና ሐሰተኛው ነቢይ ወደ ተጣለበት በዲን ወደሚነደው የእሳት ባሕር ተጣሉ። ቀንና ሌሊት ከዘላለም እስከ ዘላለም ይሰቃያሉ። 11 ከዚያም አንድ ታላቅ ነጭ ዙፋንና በላዩ የተቀመጠውን አየሁ። ምድርና ሰማይ ከፊቱ ሸሹ፣ ሆኖም፣ መሄጃ ቦታ አልነበራቸውም። 12 በዙፋኑ ፊት መታን፣ ታላላቆችና ታናናሾች ቆመው አየሁ፤ መጽሕፍትም ተከፈቱ። ከዚያም የሕይወት መጽሐፍ የተባለ ሌላም መጽሐፍ ተከፈተ። መታንም መጻሕፍቱም ውስጥ በተመዘገበው መሠረት እንደ ሥራቸው ተፈረደባቸው 13 ባሕር ውስጡ ያሉ ሙታንን ሰጡ። ሞትና ሲኦል ውስጣቸው ያሉትን ሙታን ስጡ፤ ሙታንም እንደ ሥራቸው ተፈረደባቸው። 14 ሞትና ሲኦል ወደ እሳቱ ባሕር ተጣሉ። የእሳቱም ባሕር ሁለተኛው ሞት ነው። 15 ስሙ በሕይወት መጽሐፍ ያልተገኘ ሁሉ ወደ እሳቱ ባሕር ተጣለ።
ከዚያም አየሁ በዚህ ሥፍራ “እኔ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ዮሐንስን ነው፡፡ ጥልቅ እና ማለቂያ ያሌለው መንገድ ይህንን በ REV 9:1. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ዘንዶ ይህን በ REV 12:3. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ አንድ ሺህ ዓመታት "1,000 ዓመታት" ነጻ ልወጣ ይገባዋ አማራጭ ትርጉም: "እርሱን ነጻ ለማውጣት መላእክቱን ያዛል"
የታረደው አማራጭ ትርጉም: "ራሶቻቸው የተቈረጡባቸውን ሰዎች ነፍሳት፥"
ሌሎች የሞቱት "ሁሉም የሞቱት ሰዎች" አንድ ሺህ ዓመቱ አለቀ "1000 ዓመቱ አለቀ" እንደነዚህ ባሉት ላይ ሁለተኛው ሞት ኃይል የለውም በዚህ ሥፍራ ላይ ዮሐንስ “ሞትን” የገለጸው በሰውኛ ኃይል ያለው አድርጎ ገልጾታል፡፡ አማራጭ ትርጉም: "እነዚህ ሰዎች ሁለተኛው ሞት አያገኛቸውም" ሁለተኛው ሞት ይህንን በ REV 2:11. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
በመሬት አራቱ መዓዘናት ላይ ይህንን በ REV 7:1. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ጎግ ማጎግ በነብይ ሕዝቄል ውስጥ የተጠቀሱት የእነዚህ ሰዎች ስም ሩቅ ያሉ ሀገራትን ለመወከል ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ በባሐር ዳርቻ እንዳለ አሸዋ ብዙ ይሆናሉ ይህ በሴጣን ሠራዊት መካል ትልቅ ቁጥር ያለው አንድነት መኖሩን አጽኖት ይሰጣል፡፡
ወጡ "የሴጣን ሠራዊት ወጡ" ወደ እሳቱና ወደ ዲኑ ባሕር ተጣለ፥ ይህንን በ REV 19:20. ላይም ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
ምድር እና ሰማይ ከእርሱ መገኘት ፊት ሸሹ፤ ነገር ግን ልሸሸጉበት የሚችሉበት ሥፍራ አልነበራቸውም ዮሐንስ ምድር እና ሰማይን ከእግዚብሔር ፍርድ ፊት ለመሸሽ ጥረት የሚደርጉ አድርጎ ስሏቸዋል፡፡ ይህ ማለት የእግዚአብሔር መገኘት አሮጌውን ሰማይ እና ምድር ፈጽሞ ያጠፋል፡፡ ታናናሾችንና ታላላቆችን ዮሐንስ እነዚህ ቃላት በማዋሃድ ለመግለጽ ያሰበው የሞቱትን ሰዎች ሁሉ ነው፡፡ መጽሐፉ ተከፈተ አማራጭ ትርጉም: "እናም መጽሐፉ ተከፈተ"
የሞቱት ተፈረደባቸው አማራጭ ትርጉም: "እግዚአብሔር የሞቱት ሰዎች ላይ ፈረደባቸው" ሁለተኛው ሞት ይህንን በ REV 2:11. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡
1 ከዚህ በኋላ አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር አየሁ፤ ምክንያቱም የመጀመሪያው ሰማይና የመጀመሪያው ምድር አልፈው ነበር፤ ባሕርም ከእንግዲህ አልተገኘም። 2 ቅድስቲቱ ከተማ አዲሲቱ ኢየሩሳሌም ለባልዋ እንዳጌጠች ሙሽራ ተዘጋጅታ ከሰማይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስትወርድ አየሁ። 3 ከዙፋኑም እንዲህ የሚል ታላዝ ድምፅ ሰማሁ፣ “እነሆ የእግዚአብሔር መኖሪያ ከሰዎች ጋር ነው፤ ከእነርሱ ጋር ይኖራል። እነርሱ ሕዝቡ ይሆናሉ፤ እግዚአብሔር ራሱም ከእነርሱ ጋር ሆኖ አምላካቸው ይሆናል። 4 እንባን ሁሉ ከዐይናቸው ያብሳል፤ ከእንግዲህ ሞት፣ ወይም ሐዘን፣ ወይም ለቅሶ ወይም ሕመም አይኖርም። ምክንያቱም የቀድሞ ነገሮች አልፈዋል። 5 በዙፋኑ የተቀመጠው፣ “እነሆ ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ” አለ። “እነዚህ ቃሎች የታመኑና እውነተኛ ስለሆኑ ጻፍ” አለ። 6 ለእኔም እንዲህ አለኝ፤”እነዚህ ሁሉ ተፈጽመዋል እኔ አልፋና ዖሜጋ፣ የመጀመሪያውም የመጨረሻውም ነኝ። ለተጠማ ሰው ከሕይወት ውሃ ምንጭ እንዲጠጣ ያለ ዋጋ እሰጣለሁ። 7 ድል የነሣ እነዚህን ነገሮች ይወርሳል፤ አምላኩ እሆናለሁ፤ እርሱም ልጄ ይሆናል። 8 ነገር ግን የፈሪዎች፣ የእምነተ ቢሶች፣ የርኩሶች፣ የነፍስ ገዳዮች፣ የአመንዝራዎች፣ የሟርተኞች፣ የጦዖት አምላኪዎችና የሐሰተኞኦች ቦታቸው በዲን በሚቃጠለው እሳት ባሕር ውስጥ ይሆናል። ይህም ሁለተኛው ሞት ነው። 9 የመጨረሻዎቹ ሰባት መቅሠፍቶች የሞሉበትን ሰባት ድዋዎች ከያዙት ሰባት መላእክት አንዱ ወደ እኔ መጥቶ፣ “ወደዚህ ና፣ የበጉን ሚስት ሙሽራዋን አሳይሃለሁ” አለኝ። 10 ከዚያም ወደ አንድ ታላቅና ከፍ ወዳለ ተራራ በመንፈስ ወሰደኝና ቅዱሳቲቱ ከተማ ኢየሩሳሌም ከሰማይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስትወርድ አሳየኝ። 11 ኢየሩሳሌም የእግዚአብሔር ክብር ነበራት፤ የብርሃንዋ ፀዳል እጅግ እንደከበረ ድንጋይ፣ እንደ አያሰጲድ ድንጋይ ጥርት ያለ ነበር። 12 አሥራ ሁለት በሮች ያሉት በጣም ታላቅ ረጅም ግምብ ነበራት በየበሮቹ አሥራ ሁለት መላእክት ነበሩ። በእነርሱም ላይ የአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ልጆች ስሞች ተጽፈው ነበር። 13 በምሥራቅ ሦስት በሮች፣ በሰሜን ሦስት በሮች፣ በደቡብ ሦስት በሮች፣ በምዕራብ ሦስት በሮች ነበሩ። 14 የከተማዋ ግምብ አሥራ ሁለት መሠረቶች ነበሩት፤ በእነርሱም ላይ የአሥራ ሁለቱ የበጉ ሐዋርያት ስሞች ተጽፈው ነበር። 15 ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረው መልአክ ከተማዋን፣ በሮቹንና ቅጥሮቹን የሚለካበት የወርቅ ዘንግ ነበረው። 16 ከተማዋ አራት ማእዘን ነበረች፤ ርዝመትና ስፋቱ ዕኩል ነበር። በመለኪያ ዘንጉ ሲለካ ርዝመቱ 12,000 ምዕራፍ ሆነ (ርዝመቱ፣ ስፋቱና ከፍታዋ ዕኩል ነበር)። 17 ቅጥሯን ስለካ ስፋቱ በሰው መለኪያ (ይህም የመላእክት መለኪያም ነው) 144 ክንድ ሆነ 18 ቅጥሩ ከኢያሰጲድ፣ ከተማዋም እንደ መስተዋት በጠራ ንጹሕ ወርቅ የተሠራች ነበረች። 19 የቅጥሩ መሠረቶች በከበሩ ድንጋዮች ያጌጡ ነበር። የመጀመሪያው ኢያሰጲድ፣ ሁለተኛው ሶንፔር፣ ሦስተኛው ኬልቄዶን፣ አራተኛው መረግድ 20 አምስተኛው ሰርደንክስ፣ ስድስተኛው ሰርድዮን፣ ሰባተኛው ክርስቲሎቤ፣ ስምንተኛው ቢረሌ፣ ዘጠነኛው ወራውሬ፣ አሥረኛው ክርስጵራስስ፣ አሥራ አንደኛው ያክንት፣ አሥራ ሁለተኛው አሜቴስ ቲኖስ ነበረ። 21 አሥራ ሁለቱም በሮች፣ አሥራ ሁለት ዕንቁዎች ነበሩ፤ እያንዳንዱ በር ከአንድ ዕንቁ የተሠራ ነበር። የየከተማዋ መንገዶች ጥርት እንዳለ መስተዋት ንጽሕ ወርቅ ነበሩ። 22 በከተማዋ ምንም መቅደስ አላየሁም፤ ምክንያቱም ሁሉን የሚገዛ ጌታ አምላክና በጉ መቅደሷ ነበሩ። 23 የእግዚአብሔር ክብር ስለሚያበራለት ከተማዋ የፀሐይ ወይም የጨረቃ ብርሃን አልነበራትም፤ ምክንያቱም በጉ ራሱ ብርሃንዋ ነው። 24 ሕዝቦችም በዚያች ከተማ ብርሃን ይመላለሳሉ። የምድር ነገሥታት ክብራቸውን ወደ እርሷ ያመጣሉ። 25 በሮቿ በቀን አይዘጉም፤ በዚያ ሌሊት የለም። 26 የመንግሥታትን ግርማና ክብር ወደ እርሷ ያመጣሉ 27 ርኩስ ነገር በፍጹም አይገባባትም። ጸያፍ ወይም አታላይ ወደዚያ አይገባም፤ ወደዚያ የሚገቡት ስሞቻቸው በበጉ የሕይወት መጽሐፍ የተጻፈ ብቻ ናቸው።
አየሁ በዚህ ሥፍራ ላይ “እኔ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ዮሕንስ ነው፡፡ ልክ ሙሽሪት ለባሏ እንደሚትዋብ ሁሉ ይህ አዲስቷ ኢየሩሳሌም በጣም የተዋበች መሆኗን አጽኖት ሰጥቶ ያመለክታል፡፡
አልፋ እና ኦሜጋ፣ መጀመሪያ እና መጨረሻ እነዚህ ሁለት ሀረጎች ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው ሲሆን አጽኖት ሰጥተው የሚያስተላልፉት መልዕክትም እግዚአብሔር ዘላለማዊ መሆኑነ ነው፡፡ . አልፋ እና ኦሜጋ ይህንን በ REV 1:8. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ የተተማ ቢኖር . . . የሕይወት ውሃ ይህ ማለት እግዚአብሔር ለሚፈልግ ሁሉ በነጻ የዘላም ሕይወት ይሰጣል፡፡
የሚፈሩት "ትክክለኛ የሆነውን ነገር ለማድረግ በጣም የሚፈሩ ሰዎቸ" ርኩሳን "መጥፎ ነገር የሚያደርጉ ሰዎች" በዲንና በእሳት በሚቃጠል ባሕር ነው፤ ይህንን በ REV 19:20. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ሁለተኛው ሞት ይህን በ REV 2:11. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
ሙሽራ፣ የበጉ ምስት በበዚህ ሥፍራ ላይ የጋብቻ ምስሉ የሚያመለክተው ኢሱስ ከሕዝቡ ጋር መሆኑን እና በእርሱ ቅዱስ ከተማ ለዘላለም እንደሚኖር ነው፡፡ በግ ይህንን በ REV 5:6. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ከዚያም በመንፈስ ወሰደኝ ይህንን በ REV 17:3. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
ኢየሩሳሌም "ሰማያዊዋ ኢየሩሳሌም" ወይም "አዲስቷ ኢየሩሳሌም" ብርጭቆ ይህንን በ REV 4:6. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ኢያሰጲድ ይህንን በ REV 4:3.ላይ ምን ብለህ እደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ዐሥራ ሁለት በሮች "12 በሮች" ተጽፏል አማራጭ ትርጉም፡ "እግዚአብሔር ጽፎታል"
በግ ይህ ኢየሱስን የሚያመለክት ነው፡፡ ይህንን በ REV 5:6. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡
ምዕራፍ እስታዲዬም 185 ሜትሮች ነው፡፡ ክዩብs አንድ ክዩብ 46 ሴንቲሜተር ነው፡፡
ኢያሰጲድ፥ . . . ሰንፔር፥ . . . ኬልቄዶን፥ . . . መረግድ፥ እነዚህን በ REV 4:3. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡ አምስተኛው ሰርዶንክስ፥ ስድስተኛው ሰርድዮን፥ ሰባተኛው ክርስቲሎቤ፥ ስምንተኛው ቢረሌ፥ ዘጠነኛው ወራውሬ፥ አሥረኛው ክርስጵራስስ፥ አሥራ አንደኛው ያክንት፥ አሥራ ሁለተኛው አሜቴስጢኖስ ነበረ። እነዚህ ውድ ጌጣ ጌጦች ናቸው፡፡
ዕንቁዎች ይህንን በ REV 17:4. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከተ፡፡ ጌታ እግዚአብሔር . . . እና በጉ መቅደሳቸው ነው ቤተ መቅዱስ የእግዚአብሔርን መገኘት ይወክላል፡፡ ይህ ማለት አዲስቷ ኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ አያስፈልጋትም ማለት ነው ምክንያቱም እግዚአብሔር እና ቤተ መቅዱስ በዚያ ይኖራሉና፡፡
በጉ ብርሃን ነውና ይህ ማለት የኢየሱስ ክብር ለከተማይቱ ብርሃንም ይሆናል፡፡ ደጆቿ አይዘጉም አማራጭ ትርጉም: "ደጆቿን ማንመ አይዘጋቸውም"
ንጹሕ ያልሆነ ምንም ነገረ ፈጽሞ አይገባባትም "ንጹሕ የሆነ ነገር ብቻ ነው ወደዚህች የሚገባው" ይሁን እንጂ በበበጉ የሕይወት መጽሐፍ ላይ ስማቸው የተጻፉት ብቻ አማራጭ ትርጉም: "ነገር ግን በጉ ስማቸውን በሕይወት መዝገብ ላይ ብቻ የጻፋቸው ብቻ" በጉ ይህን በ REV 5:6. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልክት፡፡
1 ከዚያም መልአኩ፣ እንደ መስተዋት የጠራውን የሆነውን የሕይወት ውሃ ወንዝ አሳየኝ። ወንዙም የሚወጣው ከእግዚአብሔርና ከበጉ ዙፋን ነበር 2 በከተማዋ ዋና መንገድ መካከል ያልፍ ነበር። በወንዙ ግራና ቀኝ አሥራ ሁለት ወር ሙሉ አሥራ ሁለት ዓይነት ፍሬ የሚሰጥ የሕይወት ዛፍ ነበር። የዛፉ ቅጠሎች ሕዝቦችን ሁሉ ይፈውሱ ነበር። 3 ከእንግዲህ ምንም ዐይነት መርገም አይሆንም። የእግዚአብሔርና የበጉ ዚፋን ከተማው ውስጥ ይሆናሉ፤ አገልጋዮቹም ያገለግሉታል። 4 ፊቱን ያያሉ፤ ስሙም ግንባሮቻቸው ላይ ይሆናል። 5 ከእንግዲህ ሌሊት አይሆንም፤ ጌታ አምላክ ስለሚያበራላቸው የመብራት ወይም የፀሐይ ብርሃን አያስፈልጋቸውም። ከዘላለም እስከ ዘላለም ይነግሣሉ። 6 መልአኩም እንዲህ አለኝ፤ “እነዚህ ቃሎች የታመኑና እውነተኛ ናቸው። ጌታ፣ የነቢያት መናፍቅ አምላክ ቶሎ መሆን ያለበትን ለአገልጋዮቹ እንዲያሳያቸው መልአኩን ላከ።” 7 “እነሆ፣ ቶሎ እመጣለሁ! ለዚህ መጽሐፍ የትንቢት ቃሎች የሚታአእ የተባረከ ነው። 8 እነዚህን ነገሮች የሰማሁና ያየሁ እኔ ዮሐንስ ነኝ። እነዚህን በሰማሁና ባይብሁ ጊዜ እነዚህን ነገሮች ላሳየኝ መልአክ ለመስገድ በፊቱ ተደፋሁ። 9 እርሱ ግን፣ “እንዳታደርገው! እኔ ራሴ ከወንድሞችህ ከነቢያት ጋር፣ ለዚህ መጽሐፍ ቃል ከሚታዘዙት ጋር አብሬ አገልጋይ ነኝ። ይልቅ ለእግዚአብሔር ስገድ አለኝ!” 10 እንዲህም አለኝ፤ ጊዜው በጣም ቅርብ ስለሆነ የዚህን መጽሐፍ የትንቢት ቃሎች በማኅተም አትዝጋው። 11 ዐመፀኛው ማመፁን ይቀጥል። ርኩሱም ርኩሰት ማድረጉን ይቀጥል። ጻድቁም ጽድቅ የሆነውን ማድረጉን ይቀጥል። ቅዱስም ቅዱስ መሆን ይቀጥል። 12 “እነሆ፣ ቶሎ እመጣለሁ። ለእያንዳንዱ እንደ ሥራው የምከፍለው ዋጋ ከእኔ ዘንድ አለ። 13 እኔ አልፋና ዖሜጋ፣ ፊተኛውና ኋለኛው፤ የመጀመሪያውና የመጨረሻው ነኝ። 14 ከሕይወት ዛፍ ለመብላትና በበሮቿ ወደ ከተማዋ ለመግባት መብት እንዲኖራቸው ልብሳቸውን የሚያጥቡ የተባረኩ ናቸው። 15 ውሾች፣ ጠንቋዮች፣ አመንዝራዎች፣ ነፍሰ ገዳዮች፣ ጣዖት አምላኪዎችና ሐሰትን የሚወዱና የሚያደርጉ ግን በውጭ አሉ። 16 እኔ ኢየሱስ ለእናንተ እንዲመሰክር መልአኬን ወደ አብያተ ክርስቲያናት ላክሁ። እኔ የዳዊት ሥርጥ ዘር ነኝ፤ የሚያበራም የንጋት ኮከብ ነኝ።” 17 መንፈሱና ሙሽራይቱ፣ “ና!” ይላሉ፤ የሚሰማ ሁሉ፣ “ና!” ይበል። ማንም የተጠማ ቢኖር ይምጣ፣ የሚፈልግ የሕይወትን ውሃ በነጻ ይውሰድ። 18 የዚህን መጽሐፍ ትንቢት ለሚሰሙ ሁሉ እኔ እመሰክራለሁ፣ ማንም ትንቢቱ ላይ ቢጨምር እግዚአብሔር በዚህ መጽሐፍ የተጻፉትን መቅሠፍቶች ይጨምርበታል። 19 ማንም ከዚህ መጽሐፍ ትንቢት ቢያጎድል እግዚአብሔር በዚህ መጽሐፍ ከተጻፈው የሕይወት ዛፍና ቅድስት ከተማ ዕድሉን ያጎልበታል። 20 ለእነዚህ ነገሮች የሚመሰክር እርሱ፣”አዎን! ቶሎ እመጣለሁ” አሜን! ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና! ይላል። 21 የጌታ ኢየሱስ ጸጋ ከሁላችሁ ጋር ይሁን
አሳየኝ በበዚህ ሥፍራ ላይ “እኔ” የሚለው ቃል ዮሕንስ ያመለክታል፡፡ እንደ ብርጭቆ ንጹሕ ይህንን በ REV 4:6. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምከው ተመልከት፡፡ በግ ይህንን REV 5:6.በ ላይ ምን ብለህ እደተረጎምከው ተመልከት፡፡ ዐሥራ ሁለት ዓይነት ፍራፍሬ "12ዓይነት ፍራፍሬ"
አገልጋዮቹ እርሱን ያገለግላሉ “እርሱ” ለሚለው ቃል አማራጭ ትርጉሞች 1) እግዚብሔር አብን ያመለክታል ወይም 2) በጉ የሆነውን እግዚአብሔር ያመለክታል ዌም 3) አባት የሆነው እግዚአብሔርን እና በግ የሆነውን ሁለቱም በጋራአንድ ሆነው የሚገዙትን ያመለክታል፡፡
እነዚህ ቃላት የታመኑ እና እውነተኞች ናቸው ከዚህ ጋር ተመሳሳይ የሆነውን በ REV 21:5. ላይ የሚገኘውን ሀረግ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡ ተመልከት! እነሆ በቶሎ እመጣለሁ ከዚህ ዓረፍተ ነገር በፊት ያለው የጥያቄ ምልክት በቁጥር 6 እና ቁጥር 7 ላይ የተናጋሪ ለውጥ መኖሩን ያመለክታል፡፡ በቁጥር 7 ላይ በ UDB. ላይ በተገለጸው መሠረት ተናጋሪው ኢየሱስ ነው፡፡
ስግደት ይህ በምድር ላይ መውደቅ እና መደፋትን ያመክታል፡፡ ይህ የአምልኮ ወሳኝ ክፍል ነው እንዲሁም አክብሮትን እና ለማገልገል ፈቃደኛ መሆንን ያሳያል፡፡
እንዲህ አለኝ "መልአኩ እንዲህ አለኝ"
አልፋ እና ኦሜጋ፣ የመጀመሪያ እና መጨረሻ፣ ጅማሬ እና ፍጻሜ እነዚህ ሦስት ሀረጋት ተመሳሳይ ትርጉም ሲኖራቸው ኢየሱስ ለዘላለም ኗሪ መሆኑን ያሳያል፡፡ . አልፋ እና ኦሜጋ ይህንን በ REV 1:8. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡ መጀመሪያ እና መጨረሻ ይህንን በ REV 1:17. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡ ጅማሬ እና ፍጻሜ ይህንን በ REV 21:6. ላይ ምን ብለህ እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡
ልብሳቸውን ያጠቡ . . . ከሕይወት ዛፍ ይበላሉ መንፈሳዊ ንጽሕና ያላቸው ሰዎች በዘላለም ሕይወት ፍሬ ይበላሉ፡፡ ከውጪ ይህ ማለት ከከተማ ውጪ ማለት ሲሆን ወደ ውስጥ ለመግባት አይፈቀድም ማለት ነው፡፡ ውሻዎች በዚያ ባሕል ውስጥ ውሻ ንጹሕ ያልሆነ እና የሚጠላ ነው፡፡ ይህ መጥፎ የሆኑ ሰዎችን ለመወከል የሚውል ቃል ነው፡፡
ለአናንተ ለመመሰክር በዚህ ሥፍራ ላይ “እናንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥር አምልካች ቃል ነው፡፡ የዳዊት ሥፍ እና ዘር “ሥር” እና “ዘር” የሚሉት ቃላት በመሠረቱ ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው ቃላት ናቸው፡፡ ሁሉም አጽኖት ሰጥተው የሚገልጹተ ኢየሱስ ከዳዊት ቤተሰብ የመጣ መሆኑን ነው፡፡ . ደማቅ የትዋት ኮከብ ይህ ጥዋት በማለዳ የሚትታየውን ደማቅ ኮከብ የሚያመለክት ነው፡፡ ይህም የቀን ብርሃን በቶሎ እንደሚወጣ አመልካች ነው፡፡ በተጨማሪም ይህ ኢየሱስ መስሑ መሆኑን ያሳያል፡፡
የተጠማ ቢኖር . . . የሕይወት ውሃ ይህ ማለት እግዚአብሔር የዘላም ሕይወትን በእርግጥ ለሚፈልግ ሁሉ በነጻ ይሰጣል ማለት ነው፡፡
እመሰክራለሁ በዚህ ሥፍራ ላይ “እኔ1 የሚለው ቃል የሞመለክተው ዮሕንስን ነው፡፡ ማንም በእነዚህ ላይ ቢጨምር . . . ማንም ቢቀንስ ይህ በዚህ ትንቢት ላይ ለውጥ እንያደረግ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ነው፡፡ ስለዚህ መጽሐፍ የተጻፉ "በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የጻፍኳቸው"
ኖት የለውም